You are on page 1of 8

የመከላከያ ጤና ዋና መምርያ

የኮሌራ በሽታ
የመከላከል እና
የመቆጣጠር
ኣጠቃላይ እቅድ
የጤና ማበልፀግና በሽታ መከላከል
መምሪያ
የመከላከያ ጤና ዋና መምርያ ስለ ኮሌራ በሽታ የመከላከል እና መቆጣጠር ኣጠቃላይ እቅድ

Table of Contents
የመከላከያ ጤና ዋና መምርያ የኮሌራ የመከላከል ዕቅድ.................................................................................... 2

የእቅዱ ኣላማ ................................................................................................................................................. 2

የእቅዱ ዝርዝር ኣላማዎች................................................................................................................................ 3

ዋና ዋና የእቅዱ ተግባራት ............................................................................................................................... 3

ሀ- በየደረጃው የኮሌራ ወረርሽኝ የመከላከል እና የመቆጣጠር ግብረ ሃይል እና ኮሚቴዎች በማቋቋም ስራ እና


ሃላፊነታቸውን ማስቀመጥ ......................................................................................................................... 3

በመከላከያ ደረጃ (ጤና ዋና መምርያ) የሚኖር ግብረ ሃይል ............................................................................... 3

Technical Working Group (የቴክኒክ ኮሚቴ).......................................................................................... 4

ለ- ስለ ኮሌራ ወርርሽኝ ጤና ትምህርት በመስጠት ማህበረሰቡ የመከላከል ስራ ኣጠናክሮ እንዲሰራ ማነቃነቅ ..... 5

ሐ- ግብኣቶች ማሰባሰብ እና ማሰራጨት....................................................................................................... 5

መ-የህክምና ኣገልግሎት መስጠትን የተመለከተ ............................................................................................... 5

ቁጥጥር እና ግምገማ ..................................................................................................................................... 6

የመከላከያ ጤና ዋና መምርያ የጤና ማበልፀግና በሽታ መከላከል መምርያ Page 1


የመከላከያ ጤና ዋና መምርያ ስለ ኮሌራ በሽታ የመከላከል እና መቆጣጠር ኣጠቃላይ እቅድ

መግብያ
የኮሌራ በሽታ ቫይብሮ ኮሌራ በተባለ ኣንጀትን የሚያጠቃ ባክተርያ ይከሰታል፡፡ ኮሌራ ልጅ ኣዋቂ ሳይል ለሁሉም
የሚያጠቃ በሽታ ነው፡፡ የኮሌራ በሽታ የኣንድ ማህበረሰብ እድገት መመዘኛ የሆነ በሽታ ከመሆኑም በላይ ንፁህ
ውሃ እና የተሟላ ንፅህና (ሃይጅን) የሌላቸው ኣገሮች ዋነኛ ተግዳሮት ነው፡፡

የኮሌራ በሽታ ሊያባብሱ ከሚችሉት ነገርች የህዝቦች መፈናቀል፡ ስደት እና የእውቀት ማነስ ናቸው፡፡ ስለሆነም
በኣገራችን የተለያዩ ክልሎች ኣዲስ ኣበባን ጨምሮ በትግራይ፡ በኣማራ፡ በኦሮምያ እና በሱማሌ ክልሎች በወረርሽኝ
መልክ ተከስተዋል፡፡ ኣሁን ያለው ከዝናብ ወቅት መሆኑ ተያይዞ በሽታው ሊስፋፋበት የሚችልበት እድል ከፍተኛ
ነው፡፡

ኮሌራ የተከሰተባቸው የአገራችን ኣካባቢዎች

 በትግራይ (14 በበሽታው የተጠረጠሩ ሰዎች ) በክልተ ኣውላዕሎ ወረዳ፡ በተምቤን እንዳባ ሃደራ ጸበል፡
በመቀሌ እና በኣዲግራት
 በኣማራ ክልል ( 198 በበሽታው የተጠረጠሩ ሰዎች) ኣምስት ወረዳዎች (በዋግ ህምራ ዞን ኣበርገለ ወረዳ፡
ሰሜን ጎንደር ዞን ጠለምት፡ በየዳ እና ቋራ ወረዳዎች፡ በኣዊ ዞን ጉዋንጓ ወረዳ)
 በኦሮምያ ክልል (225 በበሽታው የተጠረጠሩ ሰዎች) በምዕራብ ሃረርጌ ዞን ኣራት ወረዳዎች (ጭሮ፡ በደሳ
ከተማ፡ ኦዳ ቡሉተመ፡ እና ሜኤሶ ወረዳ) እንዲሁም በወለታ ከተማ
 በኣዲስ ኣበባ (35 በበሽታው የተጠረጠሩ ሰዎች)) ከቦሌ ክፍለ ከተማ ውጭ በሁልም ክፍለ ከተሞች
 በሱማሌ ክልል 33 ውሃማ ተቅማጥ የታየባቸው በግንቦት 9/2011 ታይተው ነበር፡ ከዛ በኃላ የታየ በሽተኛ
የለም

ባለንበት ወቅት ሰራዊታችን የተረጋጋ ኑሮ ለመምራት የሚቸገርበት ወቅት ነው ያለው፡፡ በከፍተኛ ደረጃ ከቦታ ቦታ
የሚንቀሳቀስበት ሁኔታ ተፈጥረዋል፡፡ ስለዚህ ለኮሌራ በሽታ የመጋለጥ እድሉ ከፍተኛ ነው፡፡ የዚህ እቅድ ኣለማም
የተቋማችን ማህበረሰብ ከወረርሽኑ በመከላከል የተሰጠውን ግዳጅ በኣግባቡ እንዲወጣ ማደረግ እና ወረርሽኑ
ሲከሰትም በቀላሉ መቆጣጠር እንድንችል ማድረግ ነው፡፡

የዚህ እቅድ መሰረት ኣድረጎ ተግባራዊ የሚደረግባቸው

 የኣድቮኮስይ፡ ያለን ኣቅም የማንቀሳቀስ እና ማህበረሰቡን ፀረ ኮሌራ ማነቃነቅ


 የተጋላጭነት የመለየት እና የቅኝት ስራ
 የውኃ፡ የሳኒቴሽንና የሃዬጅን
 የጤና ማበልጸግና የበሽታ መከላከል ስራዎች
 የወረርሽኝ ዝግጁነት እና ግበረ መልስ ናቸው

የእቅዱ ኣላማ
ሰራዊታችንና እና የተቋማችን የማህበረሰብ ኣባላት ከኮሌራ ወረርሽኝ በመከላከል ሰራዊታችን የተሰጠውን ግዳጅ
በብቃት እንዲፈፅም ማስቻል

የመከላከያ ጤና ዋና መምርያ የጤና ማበልፀግና በሽታ መከላከል መምርያ Page 2


የመከላከያ ጤና ዋና መምርያ ስለ ኮሌራ በሽታ የመከላከል እና መቆጣጠር ኣጠቃላይ እቅድ

የእቅዱ ዝርዝር ኣላማዎች


1- ሰራዊታችን፡ የተቋማችን ማህበረሰብ እና ቤተሰቡ ከኮሌራ ወረርሽኝ መከላከል
2- የኮሌራ ወረርሽኝ ሲያጋጥም በቀላሉ ለመቆጣጠር ማስቻል
3- ከተለያዩ ተቋማት ኣብሮ በመስራት ለሌሎች የመከላከል ስራዎች በተመክሮ የምንበለፅግበት ሁኔታ
መፍጠር

ዋና ዋና የእቅዱ ተግባራት
ሀ- በየደረጃው የኮሌራ ወረርሽኝ የመከላከል እና የመቆጣጠር ግብረ ሃይል እና ኮሚቴዎች በማቋቋም ስራ እና
ሃላፊነታቸውን ማስቀመጥ

ለ- ስለ ኮሌራ ወርርሽኝ ጤና ትምህርት በመስጠት ማህበረሰቡ የመከላከል ስራ ኣጠናክሮ እንዲሰራ ማነቃነቅ

ሐ- ግብኣቶች ማሰባሰብ እና ማሰራጨት

መ- የህክምና ኣገልግሎት

ሀ- በየደረጃው የኮሌራ ወረርሽኝ የመከላከል እና የመቆጣጠር ግብረ ሃይል እና ኮሚቴዎች


በማቋቋም ስራ እና ሃላፊነታቸውን ማስቀመጥ
የኮሌራ ወረርሽኝ ለመከላከል እና ለመቆጣጠር የሚያስችል ከላይ እስከ ታች ግብረ ሃይል፡ ፈጣን ግበረ መልስ ሊሰጥ
የሚችሉ ኮሚቴዎች ማቋቋም ኣስፈላጊ በመሆኑ በየደረጃው የሚቀመጡት ግብረ ሃይል እና ኮሚቴዎቸ ስራና
ሃላፊነታቸው ጨምሮ እንደሚከተለው ተቀምጠዋል፡፡

በመከላከያ ደረጃ (ጤና ዋና መምርያ) የሚኖር ግብረ ሃይል


ይህ ግበረ ሃይል በመከላከያ ጤና ዋና መምርያ ኣዛዥ የሚመራ ሁኖ ከበሽታ መከላከል መምሪያ፡ ከፈውስና
እንክብካቤ መምርያ፡ ከመድሃኒት እና መሳርያዎች መምርያ፡ ሰው ሃይል መምርያ፤ ከጦር ሃይሎች ሀይሎች፡
እንዲሁም በተጓዳኝ ከመከላከያ ሎጅስትክስ መምርያ ከኢንዶክትሪናሽና ዳርክጸሬት የተውጣጣ ይሆናል፡፡

የግብረ ሓይሉ ዋና ዋና ተግባራት

 ለወርሽኙ የመከላከል ተግባራት እና ወረርሽኝ ሲከሰት ወረርሽኑ ለመቆጣጠር የሚያስችል ኣደራጃጀት እና


ቁመና መፍጠር፡፡ ሊዚህም የሚያስፈልግ ማተርያል እና የሰው ሃይል ዝግጀት መኖሩን ማረጋገጥ፡ ፡
 በየደረጃው ወርርሽኑ ለመከላከል እና ለመቆጣጠር የሚያስችል ኣደረጃጀት መፍጠር፡፡ በየእዞች ግበረ
ሃይሎች እንዲቋቋሙ ማድረግ፡፡
 ከእዞች የሚሰሩት የመከላከል ስራዎች እና መረጃዎች በመቀበል፡ መረጃዎችን በመተንተን ውሳኔ ይሰጣል፡፡
ወረርሽኝ የተከሰተባቸው ቦታዎች ይለያል፡፡ የታመሙ፡ የሞቱ በየክፈሉ ይለያል፡፡ መልከኣ ምድራዊ
(ጂኦግራፊያዊ) ስርጭቱ ከክፍሎች ኣቀማመጥ ጋር ያስቀምጣል፡፡
 ወረርሽኝ ለሞቀጣጠር የሚደረጉ የኣካባቢ ስራዎች መደገፍ፡ መከታተል፡ ግበረ መልስ መስጠት፡፡
 በሰው ሃይል፡ በማተርያል እና ኣስፈላጊ የሚባሉት ኣቅርቦቶች መደገፍ፡፡ በስልጠና ኣቅምን መገንባት፡፡

የመከላከያ ጤና ዋና መምርያ የጤና ማበልፀግና በሽታ መከላከል መምርያ Page 3


የመከላከያ ጤና ዋና መምርያ ስለ ኮሌራ በሽታ የመከላከል እና መቆጣጠር ኣጠቃላይ እቅድ

 ተጨማሪ የኢመርጀንሲ ድጋፍ ከጤና ጥበቃ ወይም ከተለያዩ ኣጋር ድርጅቶች በመጠየቅ ማቅረብ

የእዝ ግብረ ኃይል ስራና ሃላፊነት፡-

 የእዙ ወረርሽኝ ኮሚቴ በማቋቋም ሰራዊቱ ስለ ኮሌራ ወረርሽኝ ቅድመ ጥንቃቄ እንዲያደርግ ማንቀሳቀስ፡
የሚያስፈልጉ ማተርያሎች ከሚመለከተው ኣካል መጠየቅ፡
 የእዙ ፈጣን ግበረ መልስ ቡድን (Rapide Response Team) በማቋቋም ኮሚቴው ዝግጁነትን
ማረጋገጥ፡ ወረርሽኝ ሲከሰት ወረርሽኑ ወደ ኣጋጠመበት በኣፋጣኝ በማሰማራት በኣፋጣኝ እንዲቆጠጠር
ማድረግ፡፡
 የቅኝት ስራ በማጠናከር፡ መረጃዎች በግዜ ትንታኔ በመስጠት ውሳኔ መስጠት፡ ወደ ላይ መላካቸውን
ማረጋገጥ
 ወርረሽኙ የተከሰተባቸው ኣሃዱዎች በቦታ መለየት፡ እንቅስቃሰያቸው የተወሰነ እንዲሆን በማድረግ
የሚያሰፈልግ ማተርያል እንዲቀርብ ማደረግ
 ለኢመርጀንሲ የሚላኩ ማተርያሎች በኣግባቡ ማስተዳደር
 ወርርሽኝ ሲያጋጥም ያለውን የሰው ሃይል ተጠቅሞ ምርመራ ማድረግ፡፡ ጉብኝት ማድረግ፡፡
 ወረርሽኝ ሲያጋጥም በየቀኑ ለበላይ ኣካል፡ የተከናወኑ ተግባራት፡ ያጋጠሙ የበሽተኞች ቁጥር እና የሞት
ቁጥር ሪፖርት ማድረግ
 በየገዜው የሚያሰፈልግ ማተርያል እና ኣቅረቦት እየገመገመ የጎደለውን ማሟላት
 የኮሌራ የህክምና ማዕከል መለየት
 ከክልሎች ተቆራኝቶ የመስራት ግንኙነት መፍጠር

Technical Working Group (የቴክኒክ ኮሚቴ)


የቴክኒክ ኮሚቴ ከፊልድ ኢፒደሞሎጂስት፡ ከደረጃ ሶስት ሆስፒታል፡ ከላብራቶሪ፡ ከበሽተ መከላከል ፓኬጅ ቡድን
እና ከህክምና የተውጣጣ በማእከል እና በዕዞች የሚቋቋም ይሆናል፡፡ የዚህ ቡድን ተግባር እና ሃላፊነት

 የኮሌራ ወረርሽኝ የተከሰተባቸው ኣካባቢዎች ወይም ቦታዎች ይለያል


 መረጃዎች ይሰበስባል፡ ይተነትናል፡ መላምት ያስቀምጣል፡ ለውሳኔ ያቀርባል
 ከሚመለከታቸው በተለይ ከጤና ጥበቃ፤ ከክልል ጤና ቢሮዎች እና ከኢትዮጵያ ሕ/ሰብ ጤና ኢንሰትዩት
ግንኙነት በመፍጥር የሚያሰፈልጉ ኣስፈላጊ ስራዎች እንዲሰሩ ያግዛል
 የቀን ተቀን ሪፖርት ይሰበስባል
 ግብኣቶች ይሰበስባል፡ ያዘጋጃል፡ ያሰራጫል
 ወርርሽኝ ሲከሰት ወረርሽኙ የሚቆጣጠር ቡድን በማቋቋም ይልካል፡፡ ተግባራቱ ይከታተላል፡፡
 ወረርሽኙ ከተከሰተ የህክምና እርዳታ የሚሰጥበት ሁኔታ እና ቦታ በለየት ወትሮ ዝግጁነት ያረጋግጣል
 ኣስፈላጊውን ስልጠናይሰጣል/ እንዲሰጥ ያደርጋል፡፡

የህክምና ተቋማት ተግባር እና ሓላፊነት

 የተጠረጠሩ የኮሌራ በሽተኞች መለየት


 በሽተኞች በህክምና ፕሮተኮሉ መሰርት ማከም
 የላብራቶሪ ናሙናዎች መሰብሰብ እና ለምርመራ መላክ

የመከላከያ ጤና ዋና መምርያ የጤና ማበልፀግና በሽታ መከላከል መምርያ Page 4


የመከላከያ ጤና ዋና መምርያ ስለ ኮሌራ በሽታ የመከላከል እና መቆጣጠር ኣጠቃላይ እቅድ

 ዳታዎች በመሰብሰብ ለሚመለከተው ኣካል መላክ


 ለህክምና የሚያስፈልጉ ማተርያሎች መኖራቸው ማረጋገጥ/መጠየቅ
 ማህበረሰቡን ማስተማር

ለ- ስለ ኮሌራ ወርርሽኝ ጤና ትምህርት በመስጠት ማህበረሰቡ የመከላከል ስራ ኣጠናክሮ


እንዲሰራ ማነቃነቅ
ስለ ኮሌራ መንነት፡ የሚተላለፍበት መንገድ እና መከላከያው እንዲሁም ለኮሌራ ሊያጋልጡ የሚችሉ ነገሮች
ማህበረሰቡ እንዲያውቅ ማድረግ፡፡ በሰፊው የጤና ትምህርት በመስጠት የሰራዊቱ ማህበረሰብ በከላከል ተግበር
በሰፊው እንዲሰተፍ ማድርግ፡፡ ይህንንም በሁለት መንገድ ይከናወናል፡፡

1- ሚድያ መጠቀም፡- ይህ በጤና ዋና መምርያ ጤና ማበልፀግ እና በሽታ መከላከል መምርያ የኣድቾኮስይ


ቡድን የሚመራ ሁኑ፡ ለሚድያ የሚያገለግሉ ፅሁፎች፡ ቪዶዎች እና ማተርያሎች የማዘጋጀት እና
የማሰባሰብ ስራ ያከናውናል፡፡ ያሰራጫል፡፡ ከሚድያ ኣብሮ ይሰራል፡፡ ለሚድያ የሚያስፈልግ ስልጠና ካለ
ከህብረሰተብ ጤና ኢንስቲትዩት በመነጋገር ያከናውናል፡፡
2- በጤና ሙያተኞች የሚደረግ ጤና ትምህርት፡- በየደረጃው ያሉት የጤና ሙያተኞች በራሳቸው
በማዘጋጀት፡ ከላይ የሚላክላቸው የጤና ትምህርት ፅሁፎች በመጠቀም የሰራዊቱ ማህበረሰብ ትምህርት
ይሰጣሉ፡፡ የተሰጠው የትምህርት ኣይነት፡ የወሰደው ግዜ፡ የተሳታፊው ብዛት ለሚመከተው ኣካል ሪፖርት
ያደርጋሉ፡፡ ይህ በቀጣይነት በየሳምቱ የሚከናወን ይሆናል፡፡ የጤና ትምህርት ተጨማሪ ግብኣቶች
በኣድቮኮሲና በቅድመ ትንበያ ቡደን ይዘጋጃሉ፡ ከሚመለከታቸው ኣካላት ይሰበሰባሉ፡ ይሰራጫሉ፡፡

ሐ- ግብኣቶች ማሰባሰብ እና ማሰራጨት


የመከላከል እና የህክምና ግብኣቶች የማዘጋጀት እና የማቅረብ ስራ ቅድሚያ የሚሰጥበት ከመሆኑ ኣንፃር ትኩረት
ሊሰጥባቸው የሚገቡ የሚከተሉት ናቸው፡፡

 የውሃ ማከምያ መድሃኒቶች ማለትም እንደ ሰራዊቱ በግሉ እና በቡድን ለውሃ ማከምያ የሚጠቀምባቸው
መድሃኒቶች በቀን በሳምንት፡ በወር እና በሰው ሃይል ተሰልቶ መጠየቅና ማሰራጨት
 የማከምያ መድሃኒቶች እንደ ቴትራ ሳይክሊን፡ ዶክሲ ሳይክሊን ኦኣር ኤስ እና በደም ስራ የሚሰጡ ፈሳሾች
የኮሌራ ማንዋል በሚያዘው መሰረት ተሰልቶ መጠየቅ፡፡ ይህ ሰራዊቱ ባለበት ወርርሽኑ የገባባቸው
ወረዳዎች ያለውን የታማሚዎች ፕሪቫለንስ በመወሰድ ማስላት ይቻላል፡፡
 የኮሌራ ማከምያ ማእከል ለማቋቋም ኣስገዳጅ በሚሆንባቸው ክፍሎች ማእከሉን ለማቋቋም
የሚያሰፍልግ ማተርያል እና የሰው ሃይል ማዘጋጀት፡፡
 እንደ ፖስተሮች፡ በራሪ ጽሁፎች የመሳሰሉ የመከላከል ግብኣቶች በማዘጋጀት ወይም ከሚመለከታቸው
ኣካላት በመጠየቅ ማሰራጨት
 የሪፖርት ፎረማቶች፡ መመርያዎች እና የህክምና ፕሮቶኮሎች ማሰባሰብ እና ማሰራጨት

መ-የህክምና ኣገልግሎት መስጠትን የተመለከተ


በሰራዊቱ ማህበረሰብ የሚያጋጥሙ የኮሌራ ታማሚዎች በቂ የመጀመርያ ህክምና እየተደገላቸው ወደ
ኣከባቢያቸው የሚገኘው የኮሌራ የህክምና ማእከል ይላካሉ፡፡ ይህ የህክምና ማዕከል ያለበት ኣካባቢ ክፍሎች

የመከላከያ ጤና ዋና መምርያ የጤና ማበልፀግና በሽታ መከላከል መምርያ Page 5


የመከላከያ ጤና ዋና መምርያ ስለ ኮሌራ በሽታ የመከላከል እና መቆጣጠር ኣጠቃላይ እቅድ

ኣስቀድመው ማወቅ ይጠበቅባቸዋል፡፡ እስከ ኣሁን በኣዲስ ኣበባ በጦር ሓይሎች ኮምፕረሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ
ሆስፒታል ኣንድ የኮሌራ የህክምና ማእከል ለማቋቋም በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡

እዞች እንደ በሽታው ስጋት ከክልሎች በመረዳዳት ኣስፋላጊ ሁኖ ሲገኝ በካምፖች የኮሌራ የህክምና ማእከል
ማቋቋም አለባቸው፡፡ ለዚህ የሚያስፍልግ የሰው ሃይል እና ማተርያል በማንዋል መሰረት ማዘጋጀት፡፡ ለቅደመ
ዝግጅት እና ጥንቃቄ የሚያስፈልግ የወትሮ ዝግጁነት ስለሚያስፈልግ ለዚህም የሚያስፈልግ ማተርያል እና
የህክምና መድሃኒቶች በኮሌራ ማንዋል መሰረት ማዘጋጀት፡፡ የኦኣርስ እና የሪንገር እንዴት መጠቀየቅ እና ማዘጋጀት
እንዳለባቸው በሰንጠረዥ ኣንድ በምሳሌ ተቀምጠዋል፡፡

Table 1 የኦኣር ኤስ እና ሪንገር ፍላጎት መጠየቅያ ግምት

ሊያጋጥሙ በከፍተኛ
የተገልጋይ የሚቸል የኮሌራ ደረጃ
ክፍል ብዛት በሽተኞች የተጠቁ ORS Ringer
A B C D E F
C*Sever
XX OOO B*AR Rate C*6.5 D*6
ማእበል 6000 12 2.4 78 14.4
ኣዋሽ 870 1.74 0.348 11.31 2.088
ደንበል 2500 5 1 32.5 6

Note AR in Urban = Total Population X 0.2%


AR in Rural = Total Population X 2%
Number of Sever Cases = Expected Cholera cases X 20%

ቁጥጥር እና ግምገማ
 ሁሉም ክፍሎች ከታች ወደ ላይ በየቀኑ ሪፖርት ማድረግ ግዴታ ኣለባቸው፡፡ ሪፖርት በስልክ፡ በቴክስት
መልእክት፡ ወይም በሬድዪ ሁኖ የቀኑ የታዩ በሽተኞች ብዛት በሽተኛ ካልታየም ኮሌራ ዜሮ ብለው ሪፖርት
ማደረግ፡፡
 ወረርሽኑ ለመከላከል የተከናወኑ ተግባራት፡ ያጋጠሙ ተግዳረቶች እና እንዴት እንደተፈቱ እንዲሁም
ያልተፈቱ ችግሮች በሳምንት ሪፖርት ይደረጋሉ፡፡
 የጤና ዋና መምርያ የሚቋቋመው ግበረ ሃይል በወር ኣንድ ግዜ ይሰበሰባል፡፡ የተቀመጡ ኣቅጣጫዎች እና
ተፈፃሚነታቸው በዝርዝር በማየት ውሳኔ ያስተላልፋል
 የዕዝ የኮሌራ መከላከል ግበረ ሃይል በየሁለት ሳምንት ይሰበሰባል፡፡ የተሰሩት ስራዎች ይገምግማል፡፡
ኣቅጣጫዎች ያስቀምጣል፡፡
 እላይ የተጠቀሱ ዋና ዋና ተግባራት በዕዝና ተመጣጣኝ ክፍሎች በእቅድ እየተመሩ በተዋረድ እስከ ታች
ክፍሎች ተግባራዊ መሆናቸውን ማረጋገጥ

የመከላከያ ጤና ዋና መምርያ የጤና ማበልፀግና በሽታ መከላከል መምርያ Page 6


የመከላከያ ጤና ዋና መምርያ ስለ ኮሌራ በሽታ የመከላከል እና መቆጣጠር ኣጠቃላይ እቅድ

Table 2 የግዜ ሰሌዳ

ተቁ የሚከናኑ ተግባራት የሚፈፀምበት ግዜ ማብራ


ሰኔ 1ኛ ሰኔ 2ኛ ሰኔ 3ኛ ሰኔ 4ኛ ሃምሌ ነሃሴ መስከ ርያ
ሳምነት ሳምንት ሳምንት ሳምንት ረም
1 እቅድ ዝግጀት
2 እቅድ ኦሬንተሸን
3 በየደረጃው ኣደረጃጀት
መፍጠር
4 በጦር ሓይሎች
ህክምና ማቋቋም
5 የጤና ትምህርት
መስጠት
6 ግብኣት ማሰባሰብ
7 ስልጠና/ኦሬንተሸን

የመከላከያ ጤና ዋና መምርያ የጤና ማበልፀግና በሽታ መከላከል መምርያ Page 7

You might also like