Professional Documents
Culture Documents
የካቲት/2012 ዓ.ም
0
መግቢያ
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር በአዋጅ 1097/2011 በተሰጠው ስልጣንና ኃላፊነት መሰረት የከፍተኛ
የትምርት ተቋማት ውስጣዊ ብቃት ለማሻሻል ብሎም የከፍተኛ ትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በከፍተኛ ትምህርት
እየሰሩ ለሚገኙ የአካዳሚክ ቴክኒክ ረዳት ባለሙያዎችን በተመለከተ ይህንን መመሪያ ማውጣት አስፈላጊ ሆኖ
ተገኝቷል፡፡
ክፍል አንድ
አጠቃላይ ድንጋጌዎች
1.1 አጭር ርዕስ
ይህ መመሪያ በመንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአካዳሚክ ቴክኒክ ረዳት ባለሙያዎች
መተዳደሪያ መመሪያ ቁጥር 001/2012 ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል ፡፡
1.3 ትርጓሜ
በዚህ መመሪያ ውስጥ የቃሉ አገባብ ሌላ ትርጉም የሚያሰጠው ካልሆነ በስተቀር፡-
I. “ የአካዳሚክ ቴክኒካል ረዳት ባለሙያ ’’ ማለት የመማር ማስተማርን የምርምርና ማህበረሰብ
አገልግሎት ስራን በሙያው ለማገዝ የተቀጠረ ሰራተኛ ነው፡፡
II. የተግባር ትምህርት ማለት በቤተሙከራ (በወርክሾፕ) እና በመስክ ትምህርት ለተማሪዎች
የሚሰጥን ትምህርት ያጠቃልላል፡፡
III. ቤተ-ሙከራ ማለት ለተፈጥሮ ሳይንስ፣ ማህበራዊ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ትምህርት በአንድ
ክፍል የተደራጁ መሳሪያዎችን በመጠቀም በሳይንሳዊ ምርምር ሙከራዎች የሚደረግበት
ክፍል ነው፡፡
IV. የመስክ ትምህርት ማለት የተፈጥሮ ሳይንስ፣ የማህበራዊ ሳይንስ እና የቴክኖሎጂ
ትምህርት በተግባር በመታገዝ በመስክ የሚሰጥ ትምህርት ነው፡፡
1
V. ወርክሾፕ ማለት የተለያዩ መሳሪያዎችንና ማሽኖችን በያዘ ክፍል ውስጥ የተግባር
ትምህርት የሚሰጥበት ማለት ነው፡፡
1.6 ዓላማ
1.7 መርህ
I. በሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ወጥ የሆነ የአስራር ስርዓት ለመዘርጋት፣
II. የአካዳሚክ ቴክኒክ ረዳት ባለሙያን ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ፤
III. በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰጡ የተግባር ትምህርትንና የምርምር ስራን ጥራት
ማስጠበቅ፡፡
2
ክፍል ሁለት
IV. ለተግባር ትምህርት የሚያገለግሉ የተለያዩ አይነት ማንዋሎችን በጥራት አዘጋጅቶ ጥቅም ላይ
ውጤታማ ያደርጋል፤
ተማሪዎችንም ያስተባብራል፤
3
XII. አዲስ ቤተ-ሙከራ ለማቋቋም የሚያስችል በጥናት ላይ የተመሰረተ ምከረ-ሃሳብ ሰርቶ
ያቀርባል፤ ሲፈቀድም ተከታትሎ ያስፈጽማል፤
XIII. አመታዊ የስራ እቅድ ከመምህራንና ከተመራማሪዎች ጋር በቅንጅት ያወጣል፣ የተግባር
የመተንተን ስራ ይሰራል፤
4
III. በሁለት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና በአካዳሚ ቴክኒክ ረዳት ባለሙያው መካከል በሚደረግ
እና ስራዎችን የመገምገም ፤
መብት ይኖረዋል፤
5
VIII. የከፍተኛ ትምህርት ዓላማዎችንና ተቋሙ የሚመራባቸውን እሴቶች የማክበር፤ የመተግበርና
በሙያዊ ስነ ምግባርና አግባብነት መወጣት ይኖርበታል፤
IX. ልዩ ፍላጎት የሚሹ ተማሪዎችን የመደገፍ እና የማብቃት ሃላፊነት አለበት፤
ክፍል ሦስት
3. የአካዳሚክ ቴክኒካል ረዳቶች የትምህርት እድል፣ የስራ ጫናና ወደ መምህርነት የመሸጋገር መብት
II. ዩኒቨርሲቲዎች በየአመቱ ለአካዳሚክ ቴክኒክ ባሙያዎች ለብቻ የሚያገኙትን የትምህርት እድል
ይወስናሉ ፣ እድሉም በውድድር እንዲሰጥ ይደረጋል፡፡
ከተማሪዎች ጋር የሚቆዩበት ጊዜ 1 ሰአት የአንድ ሰአት ዝግጅት ይጠይቃል በሚል ስሌት ሳምንታዊ
II. የአካዳሚክ ቴክኒክ ረዳት ባለሙያ በላብራቶሪ/ወርክሾፕ የሚቆዩበት ጊዜ አንድ ሰአት /Contact hour /
6
III. ለመምህርነት የሚያስፈልጉ መስፈርቶች በሙሉ መሟላታቸው መረጋገጥ አለበት፡፡
IV. ወደ መምህርነት ለመወዳደር ሁለተኛ ዲግሪ ኖሮት ሁለት አመት በያዘው የትምህርት ደረጃ
በየኒቨርሲቲው ማገልገል አለበት፣ በቺፍ ቴክኒካል አሲስታንት ደረጃ እያገለገለ ያለ መሆን አለበት፡፡
II. በላብራቶሪ/ወርክሾፕ ውስጥ በሚከናወን የተማሪ ግምገማ 20 በመቶ ድርሻ ይኖረዋል፡፡ የመጨረሻውን
ውጤት የሚሰጠው የኮርሱ ባለቤት መምህሩ ይሆናል፡፡
3.5 የከፍተኛ ትምህርት አካዳሚክ ቴክኒክ ረዳት ባለሙያ የአመት ዕረፍትን በተመለከተ
የከፍተኛ ትምህርት አካዳሚክ ቴክኒክ ረዳት ባለሙያ የአመት እረፍት መደበኛ የመማር ማስተማር ዝግ
በሚሆንበት ወቅት ማለትም ሀምሌ እና ነሀሴ ይሆናል፡፡
3.6 የከፍተኛ ትምህርት አካዳሚክ ቴክኒክ ረዳት ባለሙያ የወጪ መጋራትን በተመለከተ
የከፍተኛ ትምህርት አካዳሚክ ቴክኒክ ረዳት ባለሙያ የመማር ማስተማሩን ስራ በቀጥታ የሚያግዝ በመሆኑ
በመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርት በዩኒቨርስቲ ቆይታቸው የተጋሩትን ወጪ ከክፍያ ነጻ ሆነው በአገልግሎት
እንዲወጡ ይደረጋል፡፡
ይህን ጉዳይ በተመለከተ ከአሁን በፊት የተላለፉ ሰርኩላሮች እና መመሪያዎች በሙሉ ተፈጻሚነት
አይኖራቸውም፡፡
7
ይህ መመሪያ በስራ ላይ ውሎ ለመፈጸም ሲያስቸግርና አዲስ አሰራር በሚያስፈልግበት ወቅት በሚኒስቴሩ
ሊሻሻል ይችላል ፡፡
--------------------------------------------
ሂሩት ወልደማርያም /ፕሮፌሰር/
የካቲት 2012 ዓ.ም - አዲስ አበባ
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር