Professional Documents
Culture Documents
Stra
Stra
መካብ ኢትዮጵያ በ 1995 ዓ.ም በኢንደስትሪው ዘርፍ በኮስሞቲክስ ማምረቻ መስክ በግል ባለሀብት የተቋቋመ
ድርጅት ነዉ፡፡ መካብ ኢትዮጵያ ኮስሞቲክስ ኃ/የተ/የግ/ማህበር የሰውነት ቅባት በማምረት ቀደምት ከሚባሉ
አምራች ድርጅቶች መካከል አንዱ ሲሆን በመስራቹ አቶ መኮንን ቢተው አማካይነት የኢትዮጵያን ገበያን
ሲቀላቀል የወደፊቱን ገበያ በሃገር ውስጥ ምርት ለመቆጣጠር በማሰብና በወቅቱ በውድ ዋጋ በብዛት ወደ ሃገር
ውስጥ ይገቡ የነበሩ የማስዋቢያ ምርቶችን መተካትና ተመሳሳይ ጥራት ነገር ግን ረከስ ባለ ዋጋ መካከለኛና
አነስተኛ ገቢ ያላቸውን ደንበኞች ተደራሽ ለማድረግ ታስቦ የተመሰረተ ድርጅት ነበር፡፡ ይሁንና ያሰበውን
አላማ ከማሳካትም አልፎ በአሁኑ ወቅት በሃገራችን በዘርፉ ከሚንቀሳቀሱ ድርጅቶች ‹ዛላሽ› በሚል መጠሪያ
ስመጥር ለመሆንና በደንበኛ ተፈላጊነትም ቀዳሚው ለመሆን በቅቷል፡፡ መካብ ኢትዮጵያ 30 ሰራተኞችን ይዞ
ወደ ስራ የገባ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ግን ከ 300 ሰራተኞች በላይ በስሩ እያስተዳደረ ይገኛል፡፡ ድርጅቱ
ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ የተለያዩ የማስዋቢያ ምርቶችን ማለትም የፊትና የሰውነት ቅባት፣ የፀጉር ቅባት፣
ሻምፑ፣ ኮንዲሽነር፣ የሰውነት ሎሽን፣ ቫዝሊን፣ እና የመሳሰሉትን ምርቶችን በማምረት ለገበያ በማቅረብ ላይ
የሚገኝ ድርጅት ነዉ ፡፡
ፋብሪካዉ ከጊዜ ወደ ጊዜ እራሱን በማሻሻል በድርጅታዊ አደረጃጀት ፤ በፋይናንስ አቅሙ፤ በሰዉ ኃይል
አመራር እና በማምረት ሂደቱ ላይ ትርጉም ያለዉ ለዉጥ በማስመዝገብ በኢንዱስትሪዉ ዘርፍ
በምርታማነት፤በትርፋማነት እና በተወዳዳሪነት የመሪነት ሚና በመጫወት ላይ የሚገኝ ሲሆን በተለይም
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በድርጅታዊ አደረጃጀት ላይ መዋቅራዊ ለዉጥ በማድረግ እራሱን በማኔጅመንት እና
በዘርፍ መምሪያዎች በማደረጀት በስራቸዉ በቂ ልምድ እና ከፍተኛ የትምህርት ደርጃ ያላቸው ባለሟያዎችን
በመቅጠር እንዲሁም ዘመን አፈራሽ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የደንበኞችን ፍላጎት በማርካት በድርጅቱ
ምርታማነት እና ትርፋማነት ላይ ለዉጥ ማስመዝገብ ተችሏል ፡፡
በድርጅታዊ አደረጃጀት መዋቅራዊ ለዉጥ ከተዋቀሩ የዘርፍ መምሪያዎች ውስጥ አንዱ ማርኬቲንግ እና
ሽያጭ መምሪያ ነዉ፡፡ መምሪያው የሚመራበት የራሱ የሆነ የገበያ አመራር እና የዋጋ ፖሊሲ ፤ የገበያ/
ሽያጭ ስትራቴጅ እቅድ እና የሥራ ማኑዋል ሳይኖረዉ ልማዳዊ የገበያ እና ሽያጭ አሰራሮችን
በመጠቀም እስከ አሁን ድረስ ቆይቷል፡፡ የተጠቀሱት ፖሊሲዎች፤ ስትራቴጂዎች እና መመሪያዎች
ባለመኖራቸዉ በመምሪያዉ የሚከናወኑ የገበያ ጥናት፤ ዳሰሳ፤ የደንበኞች አያያዝ እና ሸያጭ እንዲሁም
ተያያዥነት ያላቸዉ የስራ ሂደቶች ላይ የአሰራር ጉድለቶች ጎልተዉ ከመታየታቸዉም በላይ በድርጅቱ
ምርታማነት እና ትርፋማነት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እያሳደረ ይገኛል ፡፡
ስለሆነም ለድርጅቱ ምርቶች የገበያ ጥናት ዳሰሳ፤ የደንበኞች አያያዝ፤ የዋጋ ፖሊሲ ትመና እና ክለሳ፤ የሸያጭ
ስልቶች እንዲሁም ተያያዥነት ያላቸዉ የስራ ሂደቶች የፋብሪካዉን ጥቅም የሚያስጠብቅ እንዲሆን
እና ለሽያጭ የሚያቀርባቸዉ ምርቶች በተጠና የገበያ ስትራቴጂ፤ ሥረዓትን እና ደንብን በተከተለ
መልኩ ለማከናወን እንዲቻል እንዲሁም በዉጤታማነት በኢንዱስትሪዉ በዘላቂነት ተወዳዳሪ ሆኖ
ለመቀጠል ከማኔጅመንት በተላለፈዉ መመሪያ መሰረት ለፋብሪካዉ አሰራር በሚያመች መልኩ
አጠቃላይ የማርኬቲንግ እና ሽያጭ መምሪያ የስራ ማኑዋል ፤ የገበያ አመራር እና የዋጋ ፖሊሲ
እንዲሁም የገበያ እና ሽያጭ ስትራቴጅክ እቅድ ተዘጋጅቷል፡፡
የማርኬቲንግ እና ሽያጭ መምሪያ ፡- የገበያ አመራር እና የዋጋ ፖሊሲ ፤የአምስት ዓመት ስትራቴጅ እና የሥራ
ማኑዋል ዕቅድ ዝግጅት ፡-
የገበያ ስልት -
የግብይት ስትራቴጂዎ በግብይት ጥረቶችዎ ውስጥ ሊያገኙዋቸው የሚፈልጓቸው ግቦች ማብራሪያ ነው. የገበያ
ስትራቴጂዎ በንግድ ግቦችዎ ቅርፅ ይቀርጻል. የንግድ ግቦችዎ እና የግብይት ስትራቴጂዎ ተካፋይ መሆን አለበት፡፡
የኩባንያው የግብይት እንቅስቃሴዎች ለእነዚህ ህጎች ሙሉ በሙሉ ይገዛሉ፡፡ የግብይት ትንተና ችግሮቹን
የግብይት ውህድ ማለት አንድ ተቋም ወይም ድርጅት የግብይት አላማውን ለማሳካት ለተጠቃሚ
(promotion)፣ በምን ያህል ዋጋ (price)፣ በየትኛው የገበያ መዳረሻ (place)፣ ለማን (people)፣
የምርት ያለፈበት ሂደት (processe)፣ የምርት ተዳሳሽነት ወይም ናሙና (physical evidence)፣
የምርቱ የሚገኝበት ሁኔታ (positioning) የሚሉትን ጥያቄዎች በተቀናጀ ሁኔታ ለመመለስ የሚያስችል
1) በመጀመሪያ ደረጃ መካብ በጊዜው ለገበያ እያቀረበ ያለውን ምርት በዝርዝር ለማሳየትና
2) በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ ድርጅቱ ለገበያ እያቀረበ ያለውን ምርት ከሌሎች አቅራቢዎች ጋር
በመካብ ግብይት ምርት (Product) ማለት የመካብ ድርጅት ጥሬ እቃውን ከሃገር ውስጥና ከውጭ
ሃገራት እና ከሀገር ውስጥ ገዝቶ በማምረት ለህብረተሰቡ የሚያቀርባቸው ምርቶች ማለትም፤ የፀጉር
ቅባት፣ፈሳሽ ቅባት፣ ግሪስሊን፣ ሻምፖና ኮንዲሽነር፣ የሰውነት ሎሽን፣ እና ቫዝሊን ቅባትን የሚያካትት
vii. የምርቱ ማሸጊያ እና የተሰጠው ደረጃ ወይም ለሚሰጠው አገልግሎት ደረጃ (Package and
የተሟሉ ምርቶችን በተለያየ ከለር፣ መጠን፣ ዲዛይንና በሙሉ አቅም ማምረት የምርቱ ተጠቃሚዎች
መወሰን ያለበት በተደረገው የገበያ ጥናት መሰረት መሆን አለበት እንጂ የተወሰኑ ዕቃዎች በጥቂት ሰዎች
በገበያ ላይ ያለው ምርት ተፈላጊነት እየቀነሰ ከመጣ ሽያጩን ባለበት ለማቆየት ዲዛይኑን፣ መጠኑን፣
ወጭና የገበያ ዘመቻን የሚጠይቅ ሲሆን ለዚህ የሚሆን በጀት መመደብ አስፈላጊ ነው፡፡
በቁጥር ትንሽ ግን በጥራት ረገድ ምርጥ የሆኑ ምርቶችን ማምረት ሌላው አማራጭ ነው፡፡
የመካብ ኃ/የተ/የግ/ማህበር ምርቶች ዋጋ ማለት በድርጅቱ ውስጥ ተመርቶ ለገበያ ተደራሽ ለሚሆን
አንድ ምርት መጠን ለማምረት የሚወጣ ወጪን መሰረት አድርጎ የሚከፈል የክፍያ መጠን ነው፡፡
የዋጋ ተመን ማለት ለአንድ የምርት አይነት በገንዘብ ተመጥኖ የሚከፈል ሆኖ ገቢው ከምርት
ልውውጥ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያለው ዋጋ ነው፡፡ የዋጋ ተመን ከግብይት ውህዶች መካከል
1. የምርቱን ዋጋ ለመቆጣጠር፣
ማድረግ ይኖርበታል፡፡
ፍላጎትና ግንዛቤ መሰረት በማድረግ ነው፡፡ በዚህ የአተማመን ዘዴ ለወጣው ወጨና ለተወዳዳሪዎች
በመግባት ትልቁን ገበያ መቆጣጠር ይፈልጋል፡፡ ይህም ማለት ትልቁን የገበያ ድርሻ በመያዝና
አተማመን ሂደት ታሳቢ የሚደረጉ መሰረታዊ ነጥቦችን መሰረት አድርጎ የመሸጫ ዋጋን
ትርፍ እንዲያገኝ የሚዳብር ሲሆን እጅግ በጣም ጥሩ የዋጋ/ እሴት ግንኙነትን ያቀርባል ፡፡
2. መካብ ኃ.የተ.የግ.የሚሠራበትን የገቢያ ሁኔታ ከግምት ውስጥ በማስገባት ዋጋ ሲያስቀምጥ የተለያዩ
ምክንያቶችን ከግምት ያስገባ ነበር፡፡ በተጨማሪም፣ አንድ የንግድ ሥራ የሚያስከፍለው ዋጋ የንግዱን
በየወቅቱ ዋጋ/ዋጋዎችን በብቃት ለማቀናበር፣ ስለ መካብ ኃ.የተ.የግ. ተወዳዳሪነት ተመን አወቃቀሮች አጠቃላይ ግንዛቤ
ማግኘቱ አስፈላጊ ነው ፡፡ ይህ የታተሙ ዋጋዎችን ብቻ ሳይሆን ቅናሽ፣ የጅምላ ሽያጭ፣ ኮንትራት እና ሌሎች
ለኩባንያው የገቢያ ቦታ አስፈላጊ የሆኑ ነገሮችንም ይጨምራል፡፡ በውድድሩ መጠኖች እንዲሁም በፍላጎት ላይ መረጃን
በየጊዜው መሰብሰብ የግብይት መምሪያ ሥራ አስኪያጅ፣ የሽያጭ ክፍሎች ሃላፊዎች እና ተቆጣጣሪዎች ሃላፊነት ነው፡፡
የዋስትና ሲሰጥ በማንኛውም ጊዜ ሊለወጥ ይችላል ፡፡ በልዩ ውል ከተዋዋዩ እና ከድርድር ስምምነቶች በስተቀር ፣
የዋጋዎች አሰጣጥ ወቅታዊ እና የወደፊቱ የገበያ ሁኔታዎችን ለመተግበር እና ምላሽ ለመስጠት በቂ ተለዋዋጭነት ያለው
የዋጋ ትመና ላይ ተጽዕኖ የሚፈጥሩ በርካታ ነገሮች ያሉ ሲሆን በዋናነት የውስጥና የውጪ በሚል
በሁለት እንከፍላቸዋለን፡፡
ሀ. የአካባቢ ገበያ
ይህ የገበያ መዳረሻ በድርጅቱ ምርት ክፍል ተመርቶ የቀረበውን ምርት ሙሉ በሙሉ ለመጠቀም
የአካባቢው ተጠቃሚ የፍላጎት መጠን ውስን በሆነበት እንዲሁም የምርቱ ዓይነት በቀላሉ
የግብይት መዳረሻ ነው፡፡ ከነኚህም መዳረሻዎች ውስጥ በአካባቢው የሚገኙ የሸቀጥ ሱቆች፣
በአገር አቀፍ ደረጃ የሰፋ ከሆነ ይህንን አገራዊ ገበያ እንለዋለን፡፡ ሆኖም ምርቱ ሳይበላሽ ሊቆይ
መዳረሻዎች ውስጥ የሸቀጥ ሱቆች፣ መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት፣ የገበያ ማዕከላት፣ ሱፐር
ይህ የገበያ መዳረሻ በአንድ አገር ውስጥ የተመረቱ ምርቶች ከተመረቱበት አገር የግዛት ክልል
የሁለቱ አገሮች መንግስታት በሚፈቅዱት የግብይት ትስስር እና ባላቸው መልካም የውጪ ግንኙነት
የውጪ ግብይት ማንኛውንም በአገር ውስጥ ግብይት ለማድረግ የሚከናወኑ ተግባሮችን ከማቀፉም
በዘለለ የውጭውን አገር ደንበኛ ፍላጎትን ማወቅና ደንበኛው የሚፈልገውን ነገር ማቅረብና
ማርካትን የሚጨምር ሲሆን በውጭ አገር የሚገኙ ተጠቃሚዎች፣ በውጭ አገር የሚገኙ የምርት
አቀነባባሪዎች እና በውጭ አገር የሚገኙ የንግድ ተቋማት (Trade House) የዓለም አቀፍ ግብይት ዋና
ዋና መዳረሻዎች ናቸው፡፡
የመካብ ምርት ስርጭትና ሽያጭ ስልት በዋነኝነት ሚከናወነው በወኪሎች አማካኝነት ሲሆን እነዚህ
ወኪሎችም በተለያዩ የሀገራችን ክፍል ምርታችን ወደ ተጠቃሚው እንዲደርስ ጥረት እያደረጉ ይገኛል
ምንም እንኳን ድርጅቱ በሚፈልገውና ባቀደው መጠን ተፈፃሚ ማድረግ ባይቻልም፡፡ ለዚህ ውስንነት
2. የወኪሎች በቂ አለመሆን እና
ላለፉት በርካታ አመታት በታየው ሁኔታ የዛላሽ ቅባት በገበያ ውስጥ በሁሉም የሀገሪቱ አቅጣጫ በተጠቃሚዎች
ዘንድ ያለው ተፈላጊነት እያደገ የሚገኝ ቢሆንም ወኪሎቻችን በመስሪያ ካፒታል እጥረት እና በአወቃቀር ችግር
የገበያውን ፍላጎት ለማሟላት አልቻሉም፡፡ በዚህ ረገድ የሚታየውን ችግር ይቀርፋል በሚል መካብ የሚከተሉትን
ስልቶች አስቀምጧል፡፡
ከሽያጩ የሚገኘው ኮሚሽን ለወኪሉ የሚከፈል ይሆናል፡፡ የተመረጠው ደንበኛ በግለሰቡ ወይም
የገበያ ልማት፣ የድርጅት አወቃቀርና አስተዳደር ወዘተ በሚመለከት ከመካብ ቀጣይነት ያለው
ዋና ስራ አስኪያጅ
ማርኬቲንግና ሽያጭ
መምሪያ
የደቡብ ኢትዮጵያ
ሽያጭ
የምእራብ የሰሜን ኢትዮጵያ የምስራቅ
ኢትዮጵያ ሽያጭ ሽያጭ ኢትዮጵያ ሽያጭ
የዶክመንቶች ዝግጅት ታሳቢዎች
እንደ ወቅቱ የገበያ ሁኔታ እየታየ በየጊዜዉ ለሚዘጋጅ የገበያ አማራጭ፤ ስትራቴጂ፤ ዕቅዶች፤ የዋጋ
ፖሊሲዎች እና የሥራ መመሪያዎች ለሠራተኞች ከሚመለከተዉ አካላት የአቅም ግንባታ እና የክህሎት
ማሻሻያ ስልጠናዎች ይሰጣሉ ብለን
ለምናዘጋጀዉ ሠነዶች የሚያገለግል መረጃዎች የመረጃ ምንጭ ከሆኑ መረቦች፤ ከደንበኞች እና
ከሚመለከታቸዉ አካላታ ሁሉ እናገኛለን ብለን
ተወዳዳሪ ድርጅቶች የምርት ጥራታቸዉን ጠብቀዉ ፍትሀዊ በሆነ የገበያ አመራር፤ የዋጋ ፖሊሲ፤ የገበያ
አቅጣጫ እና ስትራቴጂ ምርቶችን ለገበያ ያቀርባሉ ብለን
መንግስት በዘርፉ የተሰማሩት ድርጅቶችን ለማበረታታት ከውጪ የሚገቡ ተመሳሳይ ምርቶች ላይ
ተገቢዉን ቁጥጥር በማድረግ እና ለምርቶች ጥራት የደረጃ ምደባ መስፈርት በማዉጣት በምርቶቹ ላይ
ቁጥጥር ያደርጋል ብለን
ሰነዶች ለማዘጋጀት የሚያግዙ የሥራ ማስፈፀሚያ ፡-የመረጃ ምንጭ አገልግሎት (የልምድ ልዉዉጥ
፤የንደረ ሀሳብ ፤መፅሀፍት፤ EVDO እና ወ.ዘ.ተ)፤የትራንስፖርት አገልግሎት፤ የፅፈት መሳሪያዎች
አቅርቦት ፤የሚሰበሰቡ መረጃዎችን ማጠናከሪያ ላፕቶፕ እና ቦርሳ፤ የአበል ወጪ እና ሌሎች
ተያያዥነት ያላቸዉን ወጪዎች ይሟሉልናል ብለን
5. የሠነዶች ዝግጅት ጥቅሞች እና ምልከታዎች
የማዘጋጀት ሠነዶች መምሪያዉ የሚመራበት የሥራ ማኑዋል፡ የዋጋ ፖሊሲ እንዲሁም ተያያዥነት
ያላቸዉን የሥራ ሒደቶች የድርጅት ጥቅም የሚያስጠብቁ እንዲሆኑ በማድረግ እና የአሰራር
ግድፈቶችን በማስወገድ የሚከናወኑት ሥራዎች በግልፅነት ሥርዓት እና መመሪያን በተከተለ መልኩ
እንዲከናወን ማስቻል
በመምሪያዉ የሰፋነዉን ልማዳዊ የገበያ እና ሽያጭ አሰራሮች በማስወገድ በዘመናዊ የገበያ አመራር
የሚመራ በወቅታዊ የገበያ እና ሽያጭ መረጃ የተደገፈ የዋጋ ፖሊሲ የገበያ አቅጣጫ ዕቅድ እና
ስትራቴጂዎች መንደፍ እና መዘጋጀት እንዲቻል
6. የመረጃ መረቦች እና የአፈፃፀም ክትትል
በዶክመንቶች ዝግጅት ወቅት ለሠነዶች ዝግጅት የሚያገለግሉ መረጃዎችን ለማግኘት አስቀድሞ የመረጃ
ምንጮች እና መረጃዎች የሚሰበሰቡበትን ዘዴዎች ማስቀመጥ ያስፈልጋል፡፡ ለሚዘጋጁት ዶክመንቶች የመረጃ
ምንጭ እና የመረጃ መሰባሰቢያ ዘዴ ይሆናሉ ብለን በሠነዶች ዝግጅት እቅድ ፕሮፖዛል ዉስጥ ያከተትናቸዉ
የሚከተሉት ናቸዉ፡፡
የመረጃ ምንጮች
የድርጅቱ ዉስጣዊ አሰራር እና በመምሪያ ዉስጥ የሚገኙ ሰነዶች፤
የድርጅቱ ምርት ተጠቃሚዎች እና ደንበኞች፤
ከተመሳሳይ ድርጅቶች ጋር የሚደረጉት የልምድ ልዉዉጦች
ክበባዊ ሁኔታዎች
የቢዝነስ ነክ መፀሓፍት እና የኢንተርኔት አገልግሎቶች
ሌሌች
የመረጃ መሰብሰቢየ ዘዴዎች
የደንበኞች ቅሬታ እና የአሰራር ግድፈቶች መቀበያ ቅፅ በማዘጋጀት ለድርጅቱ ምርት
ተጠቃሚዎች በማሰራጨት እና አስተያየታቸዉን በመሰብሰብ፤
በምርቶቻችን እና በአሰራሮቻችን ላይ ሙሉ መጠይቅ በማዘጋጀት ለምርት ተጠቃሚዎች እና
ለደንበኞች በማሰራጨት እና መልሶቻቸዉን በመሰብሰብ፤
በአካል በመሄድ ስለምርቶቻችን እና ስለአሰራሮቻችን ያለቸዉን ቅሬታ በመቀበል፤
ክበባዊ ሁኔታዎች እና ወስጣዊ አሰራሮችን በመተንተን እና በመፈተሸ
ቢዝነስ ነክ መፀሃፍትን በማንበብ እና ኢንተርኔት (ድህር-ገፅ) በመጠቀም ጠቃሚ መረጃዎችን
በመውሰድ
ሌሎች ዘዴዎችን በመጠቀም፡፡
7. የዶክመንቶች ዝግጅት ትግበራ ማስፈፀሚያ
የሚዘጋጅ ሠነዶች በዘለቄታዊ ነት በመጠቀም በድርጅት እና በመምሪያዉ ዉስጥ ለዉጥ ለማስመዝገብ
ሰነዶች በጥራት በአማራጭ ወቅታዊ መረጃዎች የተደራጀ እና የተነደፈ እንዲሆን የሚመለከተሉት ትግበራ
ማስፈፀሚያ ነጥቦች አስፈላጊ ናቸው፡፡
በቂ የመረጃ ምንጭ እና የፅህፈት መሳሪያዎች አገልግሎት
ለሚሰበሰቡ መረጃዎች ማጠናከሪያ ላፕቶፕ ከነ ቦርሳዉ፤ ፍላሽ እና EVDO ጋር
የትራንስፖርት አገልግሎት እና የአበል ወጪዎች
ከተመሳሳይ ድርጅቶች ልምድ ልዉዉጥ እና ንድፈ ሀሳብ እና ሌሎች አገልግሎቶች