You are on page 1of 1

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡፡

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም በመጋቢት አሥራ ሁለት ቀን በዚህች ዕለት
የመላእክት አለቃ የቅዱስ ሚካኤል በዓል መታሰቢያ ነው፡፡ በዚህች ቀን እግዚአብሔር ቅዱስ ሚካኤልን
ወደፈላስፋው ወደበለዓም ልኮታልና። ባላቅ እስራኤልን ይረግምለት ዘንድ በጠራው ጊዜ፡፡ በጎዳናም በፊቱ ቆሞ
አስደነገጠው፤ አህያው በሰው አንደበት እስክትናገር ድረስ፡፡ እርግማኑንም ወደበረከት ለወጠው፡፡ የጥምቀት
ልጆችን ሁሉ እግዚአብሔር በመላእክት አለቃ በቅዱስ ሚካኤል አማላጅነት ይጠብቀን ለዘለዓለሙ አሜን፡፡

You might also like