You are on page 1of 1

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡፡

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም፡፡

በዚህች ዕለት ነሐሴ ዐሥራ ሁለት ቀን የመላእክት አለቃ የቅዱስ ሚካኤል በዓል መታሰቢያ ነው፡፡ በዚህች ቀን
በሮሜ አገር ለደጉ ንጉሥ ለቈስጠንጢኖስ ተገልጦለታልና፡፡ በጠላቶቹ ሁሉ ላይም ኃይልን ሰጠውና ድል
ነሣቸው፡፡ መንግሥቱም ጸናች፤ የጣዖታቸውንም ቤት አፍርሶ አብያተ ክርስትያናትን ሠራ፡፡ በልዩ ልዩ ክብር
አከበራቸው፡፡ ስለዚህ በየወሩ በዐሥራ ሁለት ቀን የመላእክት አለቃ የቅዱስ ሚካኤልን በዓል እናደርግ ዘንድ
የቤተክርስትያን መምህራን አዘውናል፡፡ ልመናው ከኛ ጋር ይኑር፡፡ ለዘለዓለሙ አሜን፡፡

You might also like