You are on page 1of 1

ሙስናን የምመለከት ቁልፍ ሃሳቦች

(ከተዘጋጆዉ ጽሑፍ የወጣ)

ህዳር 19፣ 2015

1) የሙስና ምንነት፣
 በአደራ የተሰጠን ሥልጣን ለግል ጥቅም ማዋል፣ እምነትን ማጉደል ወይም አለመታመን፣ በጉቦ፣
በምልጃና በአድሎ ሃቅን፣ ውሳኔን ወይም ፍትህን ማዛባት ነው (Transparency International
2008)፡፡
 ሙስና የመንግስትን ሥራ ሥነምግባራዊ እና ህጋዊ መሠረት ባለው መመሪያና ደንብ ላይ ተመርኩዞ
ማከናወን አለመቻል ነው ይለዋል /የሙስና ቅኝት በኢትዮጵያ 1993/፡፡
 ሙስና ለግል ወይም ለቡድን ጥቅም ሲባል ሥርዓቶችን፣ ህጎችን፣ ደንቦችን፣ አሰራሮችን፣ መርሆዎችን
የመጣስ ማንኛውም ተግባር ነው (Kato, 1995)፡፡
 ሙስና የፖለቲካና የመንግስት አስተዳደራዊ ኃላፊነትን ካለመወጣት የሚመነጭ፣ ማህበራዊና
አስተዳደራዊ ሥርዓቶችን የመጣስ የሥነምግባር ግድፈት ሲሆን ይህም ለግል ጥቅም ሲባል በህዝብ
የተሰጠ ሥልጣንና ኃላፊነትን አላግባብ በመጠቀም ህግና ደንብ የመጣስ እኩይ ተግባራትን
ያካትታል / ቻርለስ ሳን ፎርድ 1998/፡፡
2) የሙስና ወንጀል ልዩ ባህሪያት
 የሙስና አንዱ ባህሪ በተለያዩ ዘርፎች እና በተለያየ ደረጃ ከታችኛው እርከን ጀምሮ እስከ ከፍተኛው
እርከን ድረስ የሚከሰት መሆኑ ነው፡፡
 የአፈጻጸሙ ሂደትና ሥልት እንዳይደረስበት ለማድረግ በከፍተኛ ጥናት፣ በጥንቃቄና በሚስጢር
የሚፈጸም ነው፡፡
3) በማደግ ላይ ያለዉ የህብረተሰቡ የፀረሙስና ትግል
 ሙስናና ብልሹ አሰራርን ከመከላከል አንጻር ሙሰኞችን በማጋለጥና ኢ-ሥነምግባራዊ ድርጊቶችን
በግልጽ በመኮነን የሚያበረክተዉ አስተዋጽኦ ጉልህ ነዉ፡
 የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ በሥነምግባር ግንባታ ሥራ ረገድ ቁልፍ ሚና መጫወት
ጀመሩ፣የህብረተሰቡ የሚዲያ አጠቃቀም ማደግ፣የማህበራዊ ሚዲያዎች ተጠቃሚዎች መበረካት
ችግሩን ለመከላከል በሚደረገዉ ጥረት አጋዥ ሚና ይኖረዋል፡፡
4) ተግዳሮቶች፤
 የተደራጀ ፖሊሲ ያለመኖር፣
 በአንዳንድ የመንግስት አመራሮች ትኩረት ያለማግኘት፣
 በሀገሪቱ ያለው የፖለቲካ አለመረጋገት፣
 የኑሮ ዉድነት መጨመር፣
5) የፀረ-ሙስና ትግል ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች፤
 ተቋማዊ አደረጃጀትና አሠራር ማጠናከር፣
 የሥነምግባር እና የሞራል ዕሴቶች ግንባታ ማጠናከር፣

You might also like