Professional Documents
Culture Documents
The Role of Intelectual
The Role of Intelectual
1.መግቢያ
የምሁራን ሚና ለቅቡል ሀገረ መንግስት ግንባታ መወያያ ሰነድ ላይ በብልጽግና ፓርቲ አስተባባሪነት በየደረጃው
ለሚመለከተው አካል በቂ ኦረንቴሽን በመስጠት በዞንና በወረዳ የፓርቲ ጽ/ቤቶች፤ በዞንና በወረዳ ስራና ስልጠና
መምሪያና ጽ/ቤቶች እንዲሁም በኮሌጅና ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲኖች በጋራ የተደራጀ መድረክ እንዲመቻች በማድረግ
ለውይይት በሚያመች መልክ የምሁራን መድረኩ በክልላችን በሁሉም ዞኖችና ወረዳዎች ውይይት ተደርጓል፡፡
ውይይቱም በዋናነት የምክክር መድረኩ ዋና አላማ ምሁራን በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ላይ በቂ ግንዛቤ ኑሯቸው በሀገረ
መንግስት ግንባታ ሂደት የራሰቸውን አስተዋፆ ማበርከት እንዲችሉ ያለመ ሲሆን ሀገራችን በኢኮኖሚው፤ በዴሞክራሲ
ስርዓት ግንባታና በዲፕሎማሲ ደረጃ እንዲሁም የገጠማትን በርካታ የውስጥና የውጭ ጠላቶች በመቋቋም
እያስመዘገበችው ያለውን ድል በሌላ በኩል በርካታ ተግዳሮቶ ያሉባት መሆኑን የምክክር መድረኩ ማጠንጠኛ ሆኖ ።
ምሁራኑ በሀገር ግንባታ ያለውን የፖለቲካ ባህል በማሳደግ፣ቀጣይነት ያላቸው ጠንካራ ተቋማትን በመገንባት፣እየታዬ
ያለውን የፅንፈኝነትና አክራሪነት ሁኔታን በመታገል እንዲሁም ምቹ የሆነ ሰላም የተረጋገጠበት ሀገር ከመገንባት አንፃር
ምሁራኑ ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው ታሳቢ ተደርጎ የተፈጠረ መድረክ ነው።
በክላላችን በሚገኙ የመንግስትና የግል ኮሌጆች መምህራንና ሰራተኞች መካከል የተደረገ ሲሆን የምክክር
መድረኩ ሁለት ቀናትን የሸፈነ ነበር
የኮሌጅ ዲኖች እያስተባበሩ በዞን፤በወረዳና በከተማ አስተዳደር ደረጃ የሚገኙ የመንግስትና የፓርቲ አመራሮች
መድረኩን መርተውታል
3.የዝግጅት ምዕራፍ
በዝግጅት ምእራፍ የተከናወኑ ተግባራት የሚከተሉት ናቸዉ
4.የተግባር መዕራፍ ፤-
በ%
ወንድ ሴት ድምር ወንድ ሴት ድምር
7 ምዕራብ ጎጃም
717 270 987 654 216 870 88.2
8 አዊ ብሄረሰብ ዞን 590 235 825 537 202 739 90
9 ባህርዳር
474 270 744 247 81 328 44
10 ምስራቅ ጎጃም
582 323 903 556 291 847 93.8
11 ሰሜን ወሎ 310 113 423 298 103 401 94.8
15 ኮምቦልቻሪጂኦፖሊታን 80.89
73 16 89 59 13 72
ት
16 ኦሮሞ 59 23 82 54 20 74 91.35
በአዎንታ
ዉይይቱ የተሻለ፣ወቅቱን የዋጀ እንዲሁም ምሁራኑን የሚያነቃቃ መሆኑ ማንሳት ችሏል
ሁሉም ተሳታፊ ሰፊ ዉይይት ማድረግ ተችሏል
የተመደቡ አመራሮች ትኩረት ሰጥተዉ ዉይይቱን ማሰኬድ መቻሉ
የሰነድ ዝግጅቱ ከኋላ አመጣጣችንን ሰለሚያሳየን ጥሩ ነበር
ምሁራንን ሃሳብ መቀበል እና ማዳመጥ መታሰቡም በራሱ ጥሩ ነው
ውይይቱ የአለውን ነባራዊ ሁኔታ ተረድተን መንግስትን ለመደገፍ ጠቃሚ ነው
ራሳችንን በማየት እንዳለብ እና የሚፈጠሩ ችግሮች በጋራ ታግለን ማስተካከል እንደሚገባን
ሁላችንም የተሰጠንን ኃላፊነት በአግባቡ በመወጣት ለሀገር ግንባታ የበኩላችን መወጣት
አለብን
አመራሩ በየጊዜው አዳዲስ ነገሮችን ለማህረሰቡ ማሳወቅ አለበት
በአሉታ፤-
መድረኩ የተዘጋጀው የዩንቨርስቲ መምህራን ጥያቄ ሲያነሱ ነወይ
የአማራን ሞትና መፈናቀል ማቆም ሳይቻል መንግስት እኛን የሚያወያየን ምን እንድንፈጥር
ነው መጀመሪያ የሚጠበቅበትን ሰርቶ የኛን ድርሻ ቢያሳውቀን አይሻልም ወይ
ሰነዱ የተዘጋጀው እንደ ሀገር ነው ወይስ ለአማራ ብቻ ነው
ብልጽግና የኦሮሞን ተረኝነት እንዴት ያየዋል
-የሚዲያ ነፃነት አለ የተባለው በፊትም ጋዜጠኞች እና የተፎካካሪ ፓርቲ አባላት ይታሰሩ ነበር
አሁንም በተለይም የአማራን ብሄር እየተመረጠ እየታሰረ ነው ምንድን ነው ልዩነቱ?
-የሰላም ስምምነት ሰነዱ ግልፅ አይደለም ለምን ህዝብ አልተወያየበትም በስምምነቱስ
የወልቃይት እና የራያ ጉዳይ ምን መፍትሄ አገኘ?
በአዲስ አበባ የሚፈጠሩ ችግሮችን ማስቆም አለመቻል
ሰነዱ ስለ ሽብርተኛው ኦነግ አሁን ላይ እያደረሰው ስላለው የሰው ህይወት መቅጠፍ ያለው ነገር
የለም፡፡
ወጣቱ ላይ ሰፊ ስራ እተሰራ ባለመሆኑ ስራ አጥነት ተበራክቷል፣
የርቀት ት/ቤቶች መብዛትና አላግባብ የሆነ ሰርተፊኬት አሰጣጥ የመንግስት ኮሌጆችንና
ት/ቤቶችን ከተማሪ ውጭ እያደረጋቸው ነው፣
የአመራሩን ፖለቲካል አቅም ከማሳደግ አንፃር ስራ እየተሳራ አይደለም፣ምደባውም በአቅም
አይደለም፣
በሀገራችን ወቅታዊ ሁኔታ ጋር ተያይዞ አንዳንድ አካባቢዎች (በተለይ ወለጋ) ጦርነቱ ለምን
መቆም አልቻለም;
ከአማራ ክልል ወደ አዲስ አበባ በሚወስደዉ መንገድ በአፋኞች ምክንያት በሰላም መጓዝና ደርሶ
መመለስ አስቸጋሪ ለምን ይሆናል; እንዲሁም ከቡሬ ወለጋ ያ፤ያለዉ መንገድ ለምን ክፍት
አይሆነም;
1 መሬታችን ለሱዳ አስረክበን ሉዓላዊነታችን ተከብሮ ል ማለት ይቻላል ወይ ?
ለኦሮሞ ተንበርካኪ አማራ አመራር ነው ያለው
በጦርነቱ ወቅት ሰፈር ለሰፍር ውይይትና ሀብት ፍለጋ ነበር በእርቅ ጊዜ ግን በከተማ ደረጃም
ውይይት አልተደረገ ይህ የሚያሳየው አማራ ምንም አያመጣም በሚል ነው.
የችግር ሁሉ መንስዔ ህገ መንግስቱ ስለሆነ ለምን አይሻሻልም?
የሀገር ግንባታ ስራችን ተጠናቃል ማለት ይቻላል ወይ?ኦነግ ሸኔ ኢትዬጵያ አይደለሁም እያለ
ነው.
የኑሮ ውድነቱ የስሚንቶ ውድነት ሰው መኖር የማይችልበት ደረጃ ደርሶል ምን የታሰብ ነገር አለ?
የሚሉ ዋና ዋና ጥያቄወች ተነስተዋል