You are on page 1of 2

በዛሬው ሹራ ላይ ላልተገኛችሁ አባላት በሙሉ፡-

አሰላሙ ዓለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካትሁ ውድና የተከበራችሁ የጠለሃ መስጂድ ወጣቶች ጀመዓ ቋሚ አባላት በሙሉ
ዛሬ በነበረን ሹራ ላይ 12 አባላት የተገኙ ሲሆን ከሹራው ያለ በቂ ምክንያት ሰምተው የቀሩ ከሆኑ ይህ የቋሚ አባል፣
የጀመዓው ክንፍ የሆነ፣ እንዲሁም የጀመዓው መቋቋም እና መጠናከር ከሚያሳስበው አካል ፈፅሞ የሚጠበቅ አልነበረም፡፡
ይህ ተግባር ሃላፍትናን ከመዘንጋትና ለጉዳዩ ተትኩረት ባለመስጠት ስለሆነ ለቀጣይ ይህ እንዳይፈጠር መንቀቅ
ይኖርብናል፡፡ በከባድ ሀጃ ተወጥረውና ሀጃዎት ከሹራው በላይ አሳሳቢ ሆኖብዎት ባለመመቸት አልያም ሳይሰሙ ቀርተው
ከሆነ አላህ ባሰባችሁት(በኒያችሁ) ኸይር ምንዳችሁን ይከፍላችኋል፡፡ በእኛ ዘንድም ምንም ቅሬታ አይኖረንም፡፡

የዛሬው የሹራ ውሎ ዳሰሳ፡-

የዛሬው ሹራ የሚያጠነጥነው ጀመዓው በሁለት እግሩ የመቆም ህልውና ጋር የተያያዘ ሲሆን በቅድሚያ ለጀመዓው
የተጠናከረ መዋቅር እንዲኖረው በሹራው ላይ የተገኙት ሁሉም አባላት በአንድ ድምፅ በመስማማታቸው
መዋቅሩን በትቂቱ ለመንደፍ ተሞክሯል፡፡ በሹራው ለይ የተለያዩ ሀሳቦችን በማመንጨትና በማጤን መዋቅሩ እጅግ
የተጠናከረና ስር መሰረት ያለው እንዲሆን ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት ተደርጓል፡፡

ሆኖም 7 ዘርፎችን በማፅደቅ የእነርሱን የውስጥ ህግና ደንብ አብራርተው እንዲያቀርቡ ብቻ 7 ቡድኖች
ተዋቅረዋል፡፡ አንዱ ቡድን ላይም 2 ሰው ተመድቧል፡፡ በአጠቃላይ የተመደቡት 14 ሰዎች ናቸው እያንዳንዳቸው
ቡድኖች ይዘውት የሚመጡት የዘርፍ ህግጋት ማብራሪያ በፍላጎታቸው መሰረት ተሰጥቷቸዋል፡፡ ቀጣይ ቅዳሜ
ድረስ የጊዜ ገደብ የተሰጣቸው ሲሆን ቀጣይ ቅዳሜ ከዓሱር በኋላ በሚኖረው ሹራ ላይ ህግና ደንቡን ይዘው
እንዲቀርቡና ማብራሪያ ተሰጥቶበት የሚጨመረው ተጨምሮ የሚቀነሰውም ተቀንሶ መዋቅሩ እንዲጠናከር
በሚል ተጠናቋል፡፡ የተሰጣቸው የስራ ዘርፍና ተጠሪዎቹ እነዚህ ይሆናሉ፡-

አካዳሚክ ዘርፍ

- የጥናት ክፍል
- ምክር ሰጪ ክፍል
- የኮርስ ፕሮግራሞች አዘጋጅ ክፍል

(አብደቹል ሀሚድ መሀመድ እና መሀመድ ሙኽታር)

የስፖርት ዘርፍ

- የጨዋታ ክፍል
- የሰውነት ማጠናከሪያ ክፍል

(አብዱረዛቅ ተማም እና ዚያድ በሽር)

የንብረት ዘርፍ
- ቤተ-መፅሐፍት
- የዕቃ ግዢ ክፍል

(አዩብ አምሩ እና ኻሊድ አንዋር)

የገንዘብ ቁጥጥር ዘርፍ

- የሽያጭ ክፍል
- የግዢ ክፍል

(ሀይደር ሙኒር እና ሙሀመድ አህመድ)

መረዳጃ ዘርፍ

- የዚያራ ፕሮግራም
- የድጋፍ ዘርፍ

(ሚዕራጅ እና ዑመር)

የህትመትና ማስታወቂያ ዘርፍ

- የዕቃ ግዢ እና ሽያጭ ክፍል

(አቡበከር ሙሀመድ እና ሰሚር አወል)

የዳዕዋ ዘርፍ

- ቂርዓት ክፍል
- ሙሀደራ ክፍል
- ጽህፈት ቤት

(ሙባረክ ሙሀመድ እና ፉአድ ሙሀመድ)

ሀላፍትና ያለባችሁ ሀላፍትናችሁን እንዳትዘነጉ ስንል ለማስታወስ እንወዳለን፡፡ አላህ ያበርታችሁ፡፡

You might also like