Professional Documents
Culture Documents
ትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት በዲላ ዩኒቨርሲቲ አስተባባሪነት የማኅበራዊ ሳይንስና ሥነ ሰብዕ ኮሌጅ የቅድመ
ምረቃ ፕሮግራሞች የሥርዓተ ትምህርት ግምገማ ወርክሾፕ በዲላ ዩኒቨርስቲ ከሚያዝያ 9-10/2013 ዓ.ም
ይካሄዳል።
ከመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ ከሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር መሥሪያ ቤትና ከሌሎች
ባለድርሻ አካላት በወርክሾፑ ይሳተፋሉ።
በማህበራዊ ሳይንስና ሰነ-ሰብዕ ዘርፎች የቅደመ ምረቃ ፕሮግራሞች ሀገራዊ የሥርዓተ-ትምህርቶች ግምገማ
ወርክሾፕ እየተካሄደ ይገኛል
ዲዩ፤ሚያዝያ 9 ቀን 2013 ዓ.ም (ሕ.ግ) ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር
በመንግሥት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በማህበራዊ ሳይንስ ዘርፎች የቅደመ ምረቃ ፕሮግራሞች ሀገራዊ
የሥርዓተ-ትምህርቶች ግምገማ ሀገራዊ ወርክሾፕ በዲላ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ይገኛል፡፡
ወርክሾፑን በንግግር የከፈተቱት የዲላ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደርና ተማሪዎች አገልግሎት ም/ፕ እና የፕሬዚዳንቱ
ተወካይ የሆኑት ዶ/ር ዳዊት ሃዬሶ ከዚህ ቀደም የነበረው የተደራሽነት ሥራ ወደ ጥራት ተኮር ስለመሸጋገሩ የከፍተኛ
ትምህርት ፍኖተ ካርታ፣ የሥርዓተ ትምህርቶች ቀረጻና በትምህርቶች አግባብነትና ጥራት ዙሪያ እየተሠራ ያለው
ሥራ ማሳያ ነው፤ብለዋል፡፡
የዲላ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ፕሮግራሞች ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር ደረጀ ክፍሌ፤ ሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት
ሚኒስቴር በማህበራዊ ሳይንስና ሰነ-ሰብዕ ዘርፎች የቅደመ ምረቃ ፕሮግራሞች ሀገራዊ የሥርዓተ-ትምህርቶች
ግምገማና ወርክሾፕ እንዲያዘጋጅ፣ 26 ዩኒቨርሲቲዎችን እንዲያስተባብርና ይህን በመሰለ ወርክሾፕ ከዘርፉ ምሁራን
ግብረ መልስ ለማግኘት ዩኒቨርሲቲው ዕድል በማግኘቱ መደስታቸውን ገልጸው፤ በሂደቱም ለሥርዓተ ትምህርቶች
የተሻለ መሆን ዩኒቨርሲቲው የበኩል አስተዋጽኦ እንደሚያደረግም አስታውቀዋል፡፡ አክለውም የሥርዓተ
ትምህርቶች ቀረጻ ያስፈለገበት በዋናነት ለ 21 ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥን የዘመነ የትምህርት አሰጣጥ
ለማዘጋጀትና ከዘመኑ ጋር የሚሄድ የሰው ኃይል ወደ ኢንዱስትሪው ለማገባት ወሳኝ በመሆኑ እንደሆነም
አስታወቀዋል፡፡
በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት የፕሮግራሞችና የስርዓተ ትምህርት ከፍተኛ ባለሙያ
የሆኑት አቶ መኮንን ታደሰ በበኩላቸው ዲላ ዩኒቨርሲቲ በማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ ያለውን የሰው ሃይልና ልምድን
ከግንዛቤ ውስጥ በማስገባት በብቃት እንደሚወጣ በመተማመን ይህ ኃላፊነት ለዩኒቨርሲቲው እንደተሰጠው
ጠቅሰው፤የተሰጠውንውም ኃላፊነት በአግባቡ እንደተወጣ ገልጸዋል፡፡
በወርክሾፑ ከ 26 ስድስት የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የዘርፉ ምሁራንና የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት
ሚኒስቴር ተወካዮች የተገኙ ሲሆን ሚያዝያ 10 ቀን 2013 ዓ.ም ይጠናቀቃል፡፡