Professional Documents
Culture Documents
Thurdsday
Thurdsday
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሰ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መሠረታዊ ዓላማዋ ከሆነው ስብከተ ወንጌልን የማስፋፋት
ተልዕኰዋ በተጨማሪ ለሕዝቡ ማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ባሕላዊና ኤኮኖሚያዊ ዕድገት ከፍተኛ ሚና
ተጫውታለች፡፡ የተጠናከሩ ማኅበራዊ ተቋማት ባልነበሩበት ጊዜ የኅብረተሰቡን ማኅበራዊ ዋስትና ሊያስጠብቁ
የሚችሉ ተግባራትን ፈጽማለች፡፡ ከነዚህ ተግባራት መካከል ዕድር፣ ዕቁብ፣ ሰንበቴ፣ የማስታረቅ አገልግሎት፣
የጋብቻ አገልግሎት፣ የትምህርት አገልግሎት ወዘተ. ይጠቀሳሉ፡፡
ተማኅፅኖ /Asylum/
መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትርጓሜ- በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት ተማኅፅኖ /Asylum/ ከባላጋራው ሸሽቶ ለመጣ ሰው
ፍትሕ ርትዕ እስከ ሚያገኝ ድረስ መጠለያ መሸሸጊያ ወይም የደኅንነት ጥበቃ መስጠት ነው፡፡ ይህ ተግባር
ከዘመነ ኦሪት ጀምሮ የነበረ መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ ይገልጥልናል፡፡
እግዚአብሔርም ሙሴን እንዲህ ተናገረው- «ለእሥራኤል ልጆች እንዲህ ብለህ ንገራቸው፡፡ ወደ ከነዓን ምድር ዮርዳኖስን
በተሻገራችሁ ጊዜ በስሕተት ነፍስ የገደለ ወደዚያ ይሸሽ ዘንድ የመማፀኛ ከተሞች እንዲሆኑላቸው ከተሞችን ለእናንተ
ለዩ፡፡ ነፍሰ ገዳዩ በማኅበሩ ፊት ለፍርድ እስኪቆም ድረስ እንዳይሞት ከተሞቹ ከደም ተበቃይ የመማፀኛ ከተሞች
ይሁንላችሁ፡፡... እነዚህ ከተሞች በመመካከላቸው ለሚቀመጡ እንግዶችና መጻተኞች መማፀኛ ይሆናሉ» /ዘኍ.35÷9-
15/፡፡
እነዚህ ስድስት ከተሞች ኬብሮን፣ ሴኬም፣ ቃዴስ፣ ቦስር፣ ራሞት፣ ጎላን ይባላሉ /ኢያ.20÷7-9/፡፡ በነዚህ
ከተሞች መሠዊያዎች ነበሩ፡፡ ተማፃኙ ሰው የመሠዊያውን ቀንድ ይይዛል 1 ነገሥት 1÷30/፡፡
በዘመነ ብሉይ በእነዚህ የመማፀኛ ከተሞች በመጠቀም ብዙዎች ከደም ተበቃዮቻቸው ተርፈዋል፡፡ ለምሳሌም
ያህል ንጉሥ ዳዊት መንግሥቱን ለልጁ ለጠቢቡ ሰሎሞን ባስረከበ ጊዜ ዳዊት ሳያውቅ በራሱ ጊዜ የነገሠው
አዶንያስ ፈርቶ የመሠዊያውን ቀንድ ያዘ፡፡ መልእክተኛም ልኰ ንጉሡ ሰሎሞን በሠራው ጥፋት ተበቅሎ
እንዳይቀጣው ምሕረትን ለመነ፡፡ ሰሎሞንም «እርሱ አካኼ Ä#ን ካሣመረ ከእርሱ አንዲት ጠጉር እንኳን
በምድር ላይ አትወድቅም» ብሎ ቃል ስለ ገባለት /1 ነገሥት 1÷32/ ከቅጣቱ ሊተርፍ ችሏል፡፡
በሌላም በኩል የመሠዊያውን ቀንድ ይዞ የተማፀነው ኢዮአብ እንደ አዶንያስ ሳይተርፍ በሰሎሞን ትእዛዝ
ተገድሏል /1 ነገሥት 2÷28-35/፡፡
ተማኅፅኖ በኢትዮጵያ
- ኢትዮጵያ ብሉይ ኪዳንን ተቀብላ የኖረች ሀገር እንደ መሆንዋ ይህ ሥርዓት ወደ ሀገሪቱ ገብቶ የሥርዓቷና
የባሕሏ አካል ሆኖ የቀጠለ ይመስላል፡፡ በስድስተኛው መ.ክ.ዘ የዓረቢያ ቆሪሾች የነቢዩ መሐመድን ተከታዮች
ባሳደዷቸው ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው ጥገኝነት /Asylum/ ጠየቁ፡፡ በወቅቱ ንጉሥ የነበሩት ንጉሥ
አርማሕ የሳዑዲ ዐረቢያ ገዥዎች ስደተኞቹን አሳልፈው እንዲሰጧቸው ቢጠይቋቸውም በሀገሪቱ ነባር
ሥርዓት መሠረት ተማፃኝን ለባላጋራ መስጠት ክልክል በመሆኑ አሳልፈው አልሰጧቸውም፡፡ ይህም ቤተ
ክርስቲያኒቱ ለሀገሪቱ ሥርዓተ መንግሥት ካበረከተቻቸው ደንቦች አንዱ በመሆኑ ነው፡፡
በሌላም በኩል ይህን የኢትዮጵያን ሥርዓት ያወቁ ብዙ ክርስቲያኖች በሀገራቸው የሃይማኖት ስደት በተነሣ ጊዜ
ወደ ኢትዮጵያ መጥተው እንደ ሀገሪቱ ዜጎች ለመኖር ችለዋል፡፡ በኬልቄዶን ጉባኤ ምክንያት በተዋሕዶዎች
ላይ በአውሮፓ፣ በታናሽ እስያና በመካከለኛው ምሥራቅ የተነሣውን ስደት ሸሽተው የመጡት ተሰዓቱ ቅዱሳን
ታሪክ ከዚህ ጋር የተያያዘ ነው፡፡
በየጊዜውም ግብፆች፣ የመናውያን፣ አርመኖች፣ ሕንዶች ወዘተ. ወደ ኢትዮጵያ ገብተው በዚህ ሥርዓት
ኖረዋል፡፡ ለምሳሌ በአጼ ዳዊት ዘመነ መንግሥት የነበረውና ለበልበሊት ኢየሱስ ገዳም መመሥረት አስተዋጽዖ
ያደረገው የመናዊው ነጋዴ ፊቅጦር፣ በ 10 ኛው መክዝ ኢትዮጵያ ውስጥ በጥገኝነት የነበረውና በኋላም ጵጵስና
ለእኔ ይገባል እያለ ያስቸግር የነበረው አብዱን የተባለው ግብፃዊ፣ በ 10 ኛወ መክዘ በቱርኮች ወረራ በተነሣው
ስደት ወደ ኢትዮጵያ መጥተው በየገዳማቱ የገቡት አርመኖች፣ በአጼ ምኒሊክ ዘመን የመጡትና በባለሟልነት
ደረጃ ባለ ርስት ለመሆን የበቁት ሐጂ ቀዋስ [ ሐጂ ቀዋስ ከሕንድ የመጡ አርክቴክት ናቸው፡፡ ከአጼ ምኒሊክ ጋር
የተገናኙት አንኮበር ነው፡፡ እዚያ ብዙ ሕንፃ ገንብተዋል፡፡ ሚስታቸው ሞታባቸው ከሰንዳፋ ሐሊማ የተባለችውን አገቡና
ልጅ ወለዱ፡፡ ነገር ግን ሚስታቸውና ልጃቸው በ 1910/11 በእንፍሉዌንዛ ሞቱባቸው፡፡ አማርኛ አጣርተው የሚናገሩት ሐጂ
ቀዋስ ከምኒልክ ጋር ከመግባባታቸው የተነሣ እንደ ባለሟል ይታዩ ነበር፡፡ ብዙ መሬትም ተሰጥቷቸዋል፡፡ ከሕንድና ከየመን
ዕቃ እያስመጡ የሚሸጡበት ትልቅ ሱቅ አዲስ አበባ ውስጥ ነበራቸው፡፡ መጀመርያ ባሻ ወልዴ ሠፈር በኋላም ደጃች
ነሲቡ ሠፈር ይኖሩ ነበር ፡፡ከአዲስ አበባ አዲስ ዓለም የሚያመላልስ በበሬ የሚጎተተት ጋሪ ሠርተው ነበር፡፡ በ 1905 ዓም
አርፈው ጉለሌ ተቀበሩ፡፡] የሚጠቀሱ ናቸው፡፡
«ይህ ቦታ ዳሩ እሳት መሐሉ ገነት ይሁን፤ ከዛሬ በኋላ ማንኛውም የሀገር ገዥ የዚህን ደብር ክብር እንዳይሽር፡፡ አበሉንም
በጉልበት እንዳይቀማ፡፡ በጳጳሳቱ አንደበት የተወገዘ ይሁን፡፡ በስሕተት ለገደለም መማፀኛ ይሁን» በማለት ያውጃል፡፡
ጳጳሱም ዐዋጁን በግዝት ያጸኑታል፡፡ ወዲያውም ጸሐፊ ተመርጦ ቃሉን በደብሩ ወንጌል ዳር ያሠፍረዋል፡፡ ንጉሡም
ማኅተሙን ያትምበታል፡፡
4. ጉዳዩን በእርቅ ለመፍታት ከተቻለ ከባለጋራው ያስታርቁታል ካልተቻለ ግን ፍርድ ሊያገኝ ወደሚቻልበት
ቦታ ያደርሱታል፡፡ ከዚያ ውጭ ባላጋራው ወይም ደመኛው እጁን ስጡኝ ብሎ ቢጠይቅ ካህናቱ /መነኰሳቱ
አሳልፍው ላለመስጠት ዐቅማቸው የፈቀደውን ያህል ተጋድሎ ያደርጋሉ፡፡ ከዐቅማቸው በላይ በሆነ ኃይል
ካልተሸነፉ በቀር አሳልፈው አይሰጡም፡፡
/
ማኅደረ ማርያም ደቡብ ጎንደር /
በተለይም የደቡብ ጐንደርዋ ማኅደረ ማርያም በዘመነ መሳፍንት ከፍተኛ የመማፀኛነት አገልግሎት ትሰጥ
ነበር፡፡ ዐፄ ሠርፀ ድንግልና እቴጌ ማርያም ሥና በ 1589 ዓ.ም ሲደብሯት አቡነ ማቴዎስና እጨጌ ዮሐንስ
በተገኙበት «መሐሏ ገነት ዳሯ እሳት ይሁን፣ የመማፀኛ ቦታ ትሁን፡፡ ማንም በኃይል አይድፈራት፤ የወደቀ
አይነሣባት የተተከለ አይቆረጥባት» ተብሎ ታውጆ ነበር፡፡
በዚህም የተነሣ ብዙ መኳንንትና መሳፍንት በደብርዋ ክልል ቤት ሠርተው አስቀምጠው ነበር፡፡ በመከራ ጊዜ
ለመጠለል፡፡ ለምሳሌም ያህል ንጉሥ ወልደ ጊዮርጊስና ራስ ጉግሣ ወሌ በደብሯ የመማፀኛ ቤቶች ነበሯቸው፡፡
በዚህች ደብር ተማኅፅኖ ያቀረቡት የመጀመርያው ባለ ሥልጣን አቤቶ ኃይሉ ናቸው፡፡ አቤቶ ኃይሉ ከንጉሥ
ተክለ ጊዮርጊስ ጋር ተጋ u ተው ጐጃም ቡሬ ታስረው ይኖሩ ነበር፡፡ አቤቶ ኃይሉ ከቡሬ አምልጠው ማኅደረ
ማርያም ገብተው ተማፀኑ፡፡ ካህናቱ በደብሩ ካስጠለሏቸው በኋላ ወደ ላስታ ዘመዶቻቸው ዘንድ እንዲሄዱ
አደረጉ፡፡ ይሁን እንጂ በዚያም ሊመቻቸው ባለመቻሉ ተመልሰው ወደ ማኅደረ ማርያም መጥተው ለአራት
ዓመታት በጥገኝነት ተቀምጠዋል፡፡
የትግሬና የሰሜን ገዥ ደጃች ውቤና የጐጃሙ ገዥ ደጃች ጐሹ በራስ ዓሊ ላይ በተነሡ ጊዜ የራስ ዓሊ ባለቤት
ወ/ሮ ኂሩት የራስ ውቤ ልጅ በመሆናቸው ፈርተው ማኅደረ ማርያም ገቡ፡፡ ራስ ዓሊ ድል ሲሆኑ ደጃች ውቤ
መጥተው ወ/ሮ ኂሩትን ለመውሰድ ጠየቁ፡፡ የማኅደረ ማርያም ካህናት ግን ድርጊቱን ተቃወሙት፡፡ በኋላ ላይ
ግን በኃይል ገብተው ወ/ሮ ኂሩትን ወሰዷቸው፡፡
ይህ አገልግሎት ፍትሕ ርትዕ እንዳይጓደልና መበቃቀል በፍርድ ምትክ ቦታውን እንዳይዝ ያደርጋል፡፡ በግርግርና
በፀጥታ መታወክ ጊዜ የሰው ሕይወት በቀላሉ እንዳይጠፋ ክፉውን ዘመን ለማለፍ ያገለግላል፡፡ በመሆኑም
ኅብረተሰቡ ይህንን በመረሳት ላይ ያለ አገልግሎት እንዲያስታውሰውና እንዲጠቀምበት ቢደረግ መልካም ነው፡፡
ይኽም፡
በተለይ በገጠር የሚገኘውን በመበቃቀል መገዳደል በመቀነስ ሰዎች በሕጋዊና በሕጋዊ ፍርድ ብቻ መብታቸውን
እንዲያጡ ያደርጋል፤
በሴቶች ላይ የሚደርሰውን ጥቃት ለመቀነስ የተበደሉ ሴቶች ወይም በደል ሊደረስባቸው የታሰቡ ሴቶች
ተማጽነው ፍትሕ እንዲያገኙ ያደርጋል፤
በሀገሪቱ ሰላም በሚናጋበት ጊዜ በባለሥልጣናት እና ሕዝቡ መካከል መገዳደል እንዳይኖርና ሰላም ነግሦ ፍትሕ
እስኪሰፍን ድረስ ፖለቲካዊ ጥላቻ እንዳይባባስ ያደርጋል፡፡
ዋቤ መጻሕፍት
ተክለ ጻድቅ መኩሪያ፣ የኢትዮጵያ ታሪክ ከዐፄ ልብነ ድንግል እስከ ዐፄ ቴዎድሮስ፣ 1953፣ ትንሣኤ ዘጉባኤ
ማተሚያ ቤት
ልሳነ ወርቅ ገብረ ጊዮርጊስ /መሪጌታ/፣ ጥንታዊ ሥርዓተ ማኅሌት ዘአቡነ ያሬድ፣
Tareqegn Yibabe, The History of Mahidere Maryam. CA. 1596-1939. AAU. May 1988 (BA
Thesis)
Posted by danielkibret
32 comments:
ታዴዎስ ዘአዲስ said...
ቃለሕይወት ያሰማልን
ረጅም ዕድሜ ከጤና ጋር ያድልልን
Anonymous said...
haileleul said...
Bisotegnaw said...
ሃሳቡ ጥሩ ነበር ፡፡ ግን እኔ እንጃ በዚህ ዘመን ሊገድል የመጣው የሚመለስ አይመስለኝም ካህናቱም
ደፍረው ተው የሚሉ አይመስለኝም፡፡
ፈሪሃ እግዚአብሔር የለ ፤
ዘመኑ እኮ እልቅ ሙጥጥ ብላል፡፡
I thought what happened in 1993 EC in St. Mary abbey had never done before. I have
now learned that is not the case. All the times the priests were unable to protect the
asylum seekers so long as the kings are looking for them.
Good to know!
Anonymous said...
I don't think that even the church administration is aware of this fact. A case in point is
when the Patriarch allowed the police to take and imprison university students sheltered
in "KIDIST MARIAM" church in Addis Ababa. I am disappointed by the falling
trajectory of our church and our loss of trust on our fathers
Anonymous said...
ደብረ ቁስቋም
ወንድማችን በእውነት ይህንን የሚያክል ነገር ስላስታወስከንና ስላስተማርከን በጣም
እናመሰግናለን.በርግጥ አሁንም ቢሆን ቤተክርስትያናችን የመማፀኛ ከተማ ናት ነገር እኔ እንደማስበው
አባቶች{አሁን ያሉት}ክብሯንና ስርአትዋን አላስጠበቁላትም ይህንም በተለያየ ጊዜና በተለያየ ቦታ
አይተንዋል.ህግ ቢወጣም አስፈፃሚ ያስፈልገዋል አሁን ችግሩ ህግ አስፈፃሚ ነው
የጠፋው.ለማንኛውም ቃለ ህይቀት ያሰማልን በርታ.
Anonymous said...
ዳኒዬ በአሁን ሰዓት በተሰጣቸው ጸጋ ከሚጠቀሙ ሰዎች አንዱ አንተ ትመስለኛለህ እግዚአብሔር
ይህን ጸጋህን እስከመጨረሻው አይውሰድብህ ጨምሮ እንዲሰጥህ ምኞታችን ነው፡፡ ላንተ ያለኝን
አድናቆት እንዴት መግለጽ እንዳለብኝ አላውቅም በህይወቴ ብዙ እንድለወጥ ነገሮችን በበጎ
እንዳስተውልና ለሰዎች ጥሩ አመለካከል እንዲኖረኝ ትልቅ አስተዋጽኦ አድርገህልኛል በዛሬው ጽሁፍህ
ደግሞ ስለቤተክርስቲያናችን አስተዋጽኦ አሳይተኸናል እግዚአብሔር ዕድሜና ጤና ሰጥቶህ
ከነቤተሰቦችህ ያቆይህ፡፡ አሜን!ፅ
Anonymous said...
Anonymous said...
የሒወትን ቃል ያሰማልን!
Anonymous said...
Anonymous said...
አሁን ባለንበት ዘመን ተማኅፅኖ /Asylum/ ለስንቱ ተነፈገ ስንቱስ ተላልፎ ተሰጠ ?
ጌታ ለቤተክርስቲያናችን የቀደመ ክብሯን ይመልስላት
Belehennet said...
A very interesting piece! Thank you.
Was it deliberate on your side to include only certain historical episodes of refuge in our
beloved church and leave out the recent tragic attacks against Mi'imenan who took refuge
at Debre Mariyam in Addis, etc. with the full knowledge of the current Patriarch?
Anonymous said...
የማኅደረ ማርያም ካህናት ራስ ዓሊን ከኃይ ለኛው ከዐፄ ቴዎድሮስ በመደበቃቸውና አሳልፈው
ባለመስጠታቸው ምክንያት ንጉሡ ካህናቱንና ሊቃውንቱን አርደዋል፡፡
Was King Theowodros a tyrant leader? .When he was crowned ,he obeyed the church
rule .however ,During his regime ,he had killed so many inocent citizines and yet
historians admire as if he is the only outstanding leader.
SendekAlama said...
+++
selome said...
Anonymous said...
+++
Yetwededk wendmachn huulem endamnelaw QHY abzto yagelglot zemn yadlh. Ye enat
Betkirstianen bego sera endh masayet lehulachnem telk temhert new. Bezuwach
yemimseln betkrstian tela zegeta meba teyakinewan melkam neger senasaye tiru new. If
u are in Ethiopian it could be great if u send for Addis Zemen or other government news
papaers. Behuulu Amlak yektlh. +++ Ye toronto akbari betsebochn
Anonymous said...
Anonymous said...
Anonymous said...
Anonymous said...
ሰናይ said...
ቃለ ህይወት ያሰማልን መምህራችን! በ 1993 ዓ.ም ከቅድስት ማራያም ከተጋዙት ውስጥ አንዱ ነኝ።
በዕለቱ እንደመጠለያነት የቀረቡ ሌሎች ምርጫዎችም ነበሩ። ከሁሉም ትሻላለች የተባለችው ግን
ቤተክርስቲያን ነበረች። ትሻላለች ተብሎ የታመነበትም አንተ በደንብ ያብራራህልን የአሳይለም
አስተምህሮ በግቢ ጉባዔ አስተባባሪዎች ስለተነገረ ነበር። በቅድስት ማሪያም ቤተክርስቲያን
የተሰበሰብነው ሃይማኖት ሳይለየን ነበር። መስሊምናፕሮቴስታንት ጋደኞቻችንም አብረውን ነበሩ።
የህዝቡ እንክብካቤ እና የቤተክርስቲያን እጣን መዓዛ አስደሳች እና እንኳንም የዚህች ሃይማኖት
ተከታይ ሆንኩ ያሰኘን ነብር። ግና..... ተስፋችን እና በእናት ቤተክርስቲያን ላይ የነበረን ተስፋ
ከሰዓታት አልዘለቀም። ቅዱስ ፓትርያርኩ እና አባቶች አሳልፈው ሰጡን!!! እኛም አዘንን። ተሰበርን።
የሰበረን እስሩ ሳይሆን የቤተክርስቲያን መደፈር ነበር። በዚህም የተነሳ ጥቂት የማይባሉ የግቢ ጉባዔ
አባላት ላይመለሱ ተለዩን። ሌሎችም በቤተክርስቲያን ላይ ምላሳቸውን አስረዘሙ። ህግ ዶግማ
ቀኖና... ጠብቆ የሚያስጠብቀው ካልተገኘ ምን ዋጋ አለው።
"...ትንሣኤሽን ያሳየን..."
Anonymous said...
ተሰዓቱ ቅዱሳን ወደኢትዮጵያ የመጡት ሸሽተው አይደለም። ገድላቸውም ይህን አይልም። በሽሽት
ቢሆንማ ኖሮ ሊመጡ የሚገባቸው ዘጠኝ ብቻ ሳይሆኑ ዘጠኝ መቶ ሊሆን በተገባው ነበር።
T/D said...
I think in 1993 St Markos Church of Sidist Killo saved many asylum seeker students and
we should be greatful for the church.
Anonymous said...
The administration of this church collects money from educational, health and
recreational services and went their vacation to Debre-Zeit to drink and dance. In the
mean time, Dn. Zebene Lema collected money from America and gave to this church. All
these secular life styles of the church administrators including the so called “papas”
forced them from spiritual acts like you discussed above and under your article entitled
“SEWOCH LEMIN BEKUMACHEW HAWULT YASERALU?”.
Keep it up Dn. Daneal. God knows, your effort may lead them to NESEHA.
Gebre-Georgis
Anonymous said...
Getachew said...
Dani,
Please elaborate and print out in a small book form. That is just with the size of ''YE
NAGRAN SEMAYTAT''
Other wise where can we gate the reference? unless we see on book stores.
Getachew
Anonymous said...
Great thanks Dn. Daniel. I appreciate your quality of looking things in depth. May God
protect your wisdom.
Esdros Ze Gondar
Anonymous said...
One of the monastries in Lake Tana is very blessed for saving many lives. They have a
wooden bell any body who needs their temporary shelter is not denied the shelter, be it
women who had extra maritial sex, men who did kill some one with simple quarrel to get
some clemancy from victems relative and the government. The monastery sends
representative to the government, the victms family and the husband tried to find some
forgiveness. The church worked very hard to create a peaceful society. Mengistu was the
bigger devil that happen to the church. Then comes gebere medhn with his big horn of
lucefer.