Professional Documents
Culture Documents
ሰውዬው እቤቱ ሲገባ ባለቤቱ ያቀረበችለት ምግብ ምንም ሊጥመው አልቻለም፡፡አንዳች ነገር ጎድሎታል፡፡
አሰበ አሰበና አገኘው፡፡ ቅቤ የለውም፡፡
«ምነው?» አለ፡፡
«ውይ በሞትኩት» አለችና የጎረቤቱ ሚስት እንጀራውን በመሶብ ሞልታ ፊቱ ላይ አቀረበችለት፡፡ የምግብ
አምሮቱ ተነቃነቀ፡፡
ወጡን በእንጀራ ሲያጠቅሰው ግን ያ መጣሁ መጣሁ ያለው አምሮት እልም ድርግም አለ፡፡ እዚህም
ያለው ወጥ አንዳች ነገር ጎድሎታል፡፡
«ቤት ያፈራውን ብላ እንጂ ጨው አለቀ ብላ ብዙም አላደረገችበት፡፡ ለረሃብ ይሆንሃል ብላ» አለው አባ
ወራው፡፡
«አይዋ እገሌ እስቲ ጠጋ በል፡፡ እግርህ ርጥብ ነው» አለና አጎዛውን አስተካከለለት፡፡ ተቀመጠ፡፡ የጎረቤቱ
ሴት ልጅ የጣት ውኃ ይዛ መጣች፡፡ ታጠበ እና ቀረበ፡፡
«እቴዋ ገበያ ሄዳ ወጥም አለተሠራ፤ ብላ ምንም አይልህም» አለው እንጀራውን ወደፊቱ እያደረገ፡፡ ጥቂት
ቀማመሰና ተሰናብቶ ወጣ፡፡
«እንዴው የሚጣፍጥ ምግብ በሠፈሩ ሊጠፋ ነው» እያለ ወደ አራተኛው ጎረቤቱ ቤት አመራ፡፡ ማዕድ
ቀርቦ ቤተሰቡ እየተመገበ ነው፡፡
«ሲበሉ አድርሰኝ ሲጣሉ መልሰኝ ማለት ይሄኔ ነው» አለችና እማወራዋ ተቀበለችው፡፡ አባወራውም
ወንበር ለቀቀለት፡፡ እጁን ታጥቦ ቀረበ፡፡
«በርበሬ ስላላስፈጨን አልጫ ነው፡፡ ግን ይጣፍጣል ብላ» አለው አባወራው፡፡ በይሉኝታ ተመቻችቶ
ቀረበ፡፡ እርሱ እቴ በርበሬ ለሌለው ወጥ መች ወስፋቱ ይከፈትለታል፡፡ ለምላሱ ሳይሆን ለሆዱ ቀመሰ፡፡
ጥቂት ተጫወተና ወጥቶ ወደ አምስተኛ ጎረቤቱ አመራ፡፡
እንዲህ እያለ መንደሩን ሁሉ ዞረው፡፡ አንዱ ቤት እንጀራው ይጠቁራል፤ አንዱ ቤት እንጀራው ይደርቃል፣
አንዱ ቤት ወጡ ያርራል፣ አንዱ ቤት ወጡ ይጎረናል፡፡ አንዱ ቤት ቅመም አይኖረውም፣ ሌላው ቤት
በሚገባ አይበስልም፡፡ የተሟላ ማዕድ አላገኘም፡፡
«እንዴት እንዴት?»
«ሁላችንም ጎደሏችንን እናሟላለን እንጂ ሙሉ የት ይገኛል፡፡ ሁሉም ቤት ጎደሎ አለ፡፡ ልዩነቱ የጎደሎው
ዓይነት ነው፡፡ አንተ ቤት የጠፋው እኔ ቤት፣ እኔም ቤት የጠፋው አንተ ቤት ይገኛል፡፡ ያ ማለት ግን
ሙሉ ነው ማለት አይደለም፡፡
«ታድያ ምን ያዋጣናል»
«የሚያዋጣንማ የየራሳችንን ጎደሎ ማሟላት ነው፡፡ ምሉዕ የሆነች ሚስት፣ ምሉዕ የሆነ ባል፣ ምሉዕ የሆነ
ትዳር የት ይገኛል፡፡ ሁሉ እየተሟላ ይሄዳል እንጂ፡፡ ትዳር ማለት በጎደለው ነገር መጨቃጨቅ፣ መነዛነዝ፣
መጣላት እና መኳረፍ፣ መለያየት እና መፋታት አይደለም፡፡ ትዳር ማለት የሚጎድለውን እየሞሉ መቀጠል
ማለት ነው፡፡ ሙሉ ባል ወይንም ሙሉ ሚስት የሉም፡፡ ሊሟሉ የሚችሉ ባል እና ሚስት ግን አሉ፡፡
«እዚያ ማዶ ስናይ ጎደሎው ስለማይታየን ነዋ፤ የሚታየን ከኛ የሌለው እዚያ መኖሩን ነው፡፡ እስቲ እይ
አንዳንድ ሰዎች ሌሎች ባለ ትዳሮች ቤት ደርሰው ሲመጡ የራሳቸውን ያማርራሉ፡፡ እነዚያ የተሻሉ
መስለው ይሰማቸዋል፡፡ ባልም ሚስቱን ሚስትም ባልዋን እንደዚያኛው ቤት እንዲሆኑ ይመኛሉ፤
ይመክራሉ፡፡ እነዚያኞቹንም ብትሰማ ቸውኮ በነዚህኞቹ የሚቀኑ ናቸው፡፡ ወዳጄ ሁሉም የየራሱን ጎደሎ
እያሰበ ያማርራል እንጂ ለመሙላት አያስብም፡፡
«ቅቤ የለውማ»
ጎረቤቱ ቀና ሲል፡፡ እንግዳው ሰውዬ ለቅቤ መግዣ የሚበቃ ገንዘብ መያዙን ለማረጋገጥ ብሩን እየቆጠረ
ነበረ፡፡