Professional Documents
Culture Documents
//ያችን ቀን በፀፍፀፍ...!//
ልጄ አይተሽው ቢሆን የመስቀል ላይ ሞቴን፣
👉ፆማችንን በሰላም እንዳስጀመረን በሰላም አስፈፅሞ ለብርሃነ ትንሳኤው እንዲያደርሰን የእመቤታችን የቅድስት
ድንግል ማርያም #ምልጃ የጌታችን የመድሃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጥበቃ አይለየን ...አሜን አሜን አሜን..
ምኑ ነው ስህተቴ ''!!
(ገጣሚ ህሊና ደሳለኝ)
===========
ተሳሳትሽ አትበለኝ የቱ ነው ስህተቴ፤
ጥበብ ነው ማርከሻ የብዕር ጥይቴ።
አዎ መንጋማ አለ ከጥንት መሰረቱ፤
እየሱስን አስረው በርባንን ሲያስፈቱ።
በኔ ዘመን
የመንጋ ፍርድ ነው ሀገሬን የፈታት፤
አዋቂ ዝም ብሎ መንጋ እየፈተታት።
በድንጋይ በርሚል ውስጥ ሽ ድንጋይ ቢቀቀል፤
ሽ ዘመን ተጥዶ እልፍ አመት አይበስል።
አገር ተረክቦ በሰፈረ የኮራ፤
የመንጋ ፍርድ አይደል ያበቃን ለተራ።
የቱ ጋ ነው የሳትኩ አርመኝ መምህሩ፤
ምላስክን አጥፈኽው ሞክር በብዕሩ።
ዘመን የሰጠው ቅል ድንጋይ ቢሰብር ጣሪያ፤
ማዕዘን ተደርጎ አይሆን ለቤት መስሪያ።
ሰውነት ነው ልኩ የሰው ሚዛን ፍርዱ፣
አዋቂ እንዲበይን መንጋዎች ይውረዱ።
እላለው
በመንጋ ተፈጭቶ በመንጋ ተጋግሮ፤
እልፍ ጾም አዳሪ ወና ነው ጉረሮ።
ቤት መምታት ቤት መድፋት ስንኝ መቋጠሩ
ጥበቡ ቢያቅተው፤
እያፈረሰ ህዝብ እያስደደ
አገሩን አመሰው።
እኔ ይሄንን ሰው፣
ሌላ ምን ልበለው፣
መንጋነትም ሲያንሰው።
በባዶነት ሙሌት በዘር እብሪት ታስሮ፣
ከጥበብ ጓዳ ውስጥ ከሰውነት አጥሮ።
አበውን ሲያሰደድ ሲያርድ ሲያጎሳቁል፣
አንተም መንጋ ካልሆንክ መቼም ሰው ነው አትል።
እና ምኑ ላይ ነው ብዕሬ የሳተች፣
ብሔር የነቀፈች ህዝብን ያዋረደች።
በሞቴ የመንጋው ጠበቃ
አንተም ሰው ሁንና መንጋነትህ ይብቃ"
ባለፈ አመት ክረምት ፣ ዛሬ አይታረስም
ጀግኖች አይጠሩም ፣ በፈሪዎች ስም፡፡
ሼር ይደረግ
ስም ብቻ ምን
1.
ሊጠቅመኝ
መጠሪያ ብቻ
ከሆነኝ እኔ
-
ክርስቲያን መባሌ፣
በግብሬ ካላሣየሁት-
ካልተዋሐደ ከአካሌ፣
በጨለማ መቅረዝ
ሆኖኝ እግሬን
-
ከእንቅፋት
ካላዳነ፣
ስሙ ብቻ ምን
ሊጠቅመኝ ምን-
ሊሠራልኝ ነውለኔ፣
በአርባ ቀኔ ስጠመቅ -
ክርስቲያን ተብዬ
ልጠራ፣
በእምነት ዳብሬ
እንዳድግ መልካም -
ፍሬን እንዳፈራ፣
ሥነ-ምግባሬ መጨነቄን-እንዲያሳይልኝ አጉልቶ፣
ክርስትናዬን እንዲናገር-በደረስኩበት ሁሉ ገብቶ
የተቀበልኩት ልጅነት-በእኔነቴ ዙሪያ አብርቶ፣
ለዚህ ነበር ምክንያቱ-በጥምቀት ክርስቲያን መሆኔ፣
ከኃጢአቴ ነጽቼ-ልጁ የተባልኩት እኔ፡፡
በአነጋገር በሥራዬ-ክርስትናዬን ካላሣየሁ፣
ጌታዬ በሰጠኝ መክሊት-አትርፌበት ካልተገኘሁ፣
እንደተዘናጋሁ ካለቀ-ከተጨረሰዘመኔ፣
ክርስቲያንመባሌ ምን ሊረባኝ-ምን ሊጠቅመኝ ነው ለእኔ፡፡
//
ይድረስ ለፈጣሪ መንበረ ጸባዖት
ከትልቁ ሥፍራ ከሰማዩ መንግሥት
ፍርድ ሳይዛነፍ ከሚፈጸምበት፡፡
ላኪው በምድር ላይ ግፍ የደረሰብኝ
ጐስቋላ አገልጋይህ ደካማው ባሪያህ ነኝ፡፡
ሳጥናኤል የሚሉት የቀድሞ ጠላቴ
ቂሙን ሳይዘነጋ እንደ አዳም አባቴ
ከገነት ሊያስቀረኝ ቀጥቅጦ ጥሎኛል
2.አባ ይፍቱኝ
መስቀሉን ያሳልሙኝ
ልጄ የተባረክህ
እማይሰራ ኃጢአት
እግዚአብሔር ይፍታህ
እስኪ ጠጋ በለኝ
ክርህን አሳየኝ።
አንገትህን ልየው
ማተቡን አስረሃል?
እንዴታ አባቴ
ማተብ ምልክቴ
መቼ ትለያለች
በጭራሽ ካንገቴ
ማህተቤ እኮ ናት
እጅግ የማከብራት
ክርስቲያን መሆኔን
በጌታ ማመኔን ምመስክርባት
የውስጥ እምነቴን ለሰው ማሳይባት
መናገሪያ ቃሌ
ይችናት መስቀሌ
በልቤ ያለውን
ውስጤ የሚያምነውን
እንዴት አሳይ ነበር
ማተቤ ከሌለች
እንዴት ልመስክር
አባ ማተቤማ ምስክሬ እኮናት
የመጣው ይምጣ እንጂ ካንገቴ አለያት።
በማለት ሲናገር ለንስሐ አባቱ
አቶ ግብዝነት ሐይማኖት ባንገቱ
አፍ የላትም ብሎ በማተብ ሲደበቅ
ድንገት አፍ አውጥታ "አ" ከማለትዋ
ዝም በይ ብሎ በጁ አፍዋን ሊይዝ ሲል
መናገር ቀጠለች ማተብ የእውነት ቃል
ይቀጥላል....
....የቀጠለ
አባ እኔን ይስሙኝ
ከልብዎ ያድምጡኝ
ሰዎችን ሳይፈራ እግዜርን ሳያፍር
በስንቱ ሰዎች ፊት ሐሰት ሲመሰክር
እኔን እያሳየ ስንቱን ሰው አሞኘ
ብዙ ታግሻለሁ አንገቱ ላይ ሆኜ
በድፍረት ሲያታልል የሐይማኖት አባቱን
ዛሬ ግን አልቻልም ልናገር እውነቱን።
ያለሁበት ሥፍራ ይህ ደንዳና አንገቱ
መካከለኛ ነው ለልብ ላንደበቱ።
ስለዚህ ልቡ ላይ ሲያስብ ሚውለውን
ደግሞም ባንደበቱ የሚናገረውን
እመሰክራለሁ ያየሁትን ሁሉ
በኔ ተሸፍኖ እንዳይጠፋ ዉሉ
ሐይማኖትን ትቶ ቅዱሱን ያምላክ ቃል
ከንቱ ሐሳብ ሲያስብ ራሱን ሲያታልል
አንዱን በሌለበት በሐሰት እያማ
ሌላውን ባፍ ቃል ክፉኛ እያደማ
ሲወረወር ቀስቱን የሾሉ ቃላቱን
በመርዝ አንደበቱ የነደፈው ስንቱን
ውስጡ ክፋት እንጂ ወንጌል ካልተሞላ
ያምላክን ቃል ትቶ የሰውን ከበላ
እንዴት እሆናለሁ የእምነት ምልክቱ
መሸፈኛው እንጂ እንዳይታይ ፊቱ።
ይቀጥላል.....
የቀጠለ...
ማተብ ሚስጢሩ እርስዎ ያስተማሩት
የላይ ምልክት ነው በልብ ላመኑት
ከቅዱስ ያዕቆብ ዘእልበረዳኢ
እንደ ተማረነው ወግ ከአበው መጻኢ
እውነተኛው እምነት በልባቸው ሆኖ
ለፈጣሪ ሲታይ በልበ ተአምኖ
ማተብ ግን ለሰው ነው ልቡን ለማያይ
የውስጣችን እምነት በተግባር እስኪታይ።
ይህ ነበር እውነቱ የኔ ጥቅም ለሰው
ወንጌሉን እንዲኖር ሁሌ ላስታወሰው።
ዛሬ ግን ብዙዎች ይህን ሳይረዱ
ባንገት እያመኑ በምግባር የካዱ።
ውስጣቸውን ዘግተው ከውጭ እያሰሩኝ
መገለጫ ሳይሆን መሸፈኛ አረጉኝ።
ይህም ሰው አባቴ ከእዚህ አንዱ ነው
በኔ ተሸፍኖ ውስጡ ግን ሌላ ነው
እርሱ እንደ ነገርዎት ብዙም አይወደኝም
ከነመኖሬ እንኳ አያስታውሰኝም
ለባለንጀሮቹ ሲናገር በሐሰት
ምንም አይመስለውም በስሜ ሲገዝት።
እኔን ያየ ሁሉ ክርስቲያን ሽፍኜበት።
ብዙ ሰው አታሎአል አባይ ነው ምላሱ
ውስጡን ያሳልሙልኝ ልቡን ይቀደሱ።
ምግብ ቤት ነው ተብሎ ከውጭ ከተጻፈ
እንጀራ ይገኛል ወደ ውስጥ ላለፈ።
እንዲሁም አንገት ላይ ማተብ መታስሩ
ወደ ታች ወደ ልብ ጣቱን መቀሰሩ።
ውስጥ ያለውን ሊያሳይ መሆኑን ንገሩት
ክርስቶስን ለብሶ እንዲኖር ምክሩት።
ብዙ ሰው አታሎአል አባይ ነው ምላሱ
ውስጡን ያሳልሙልኝ ልቡን ይቀድሱ።
ተፈፀመ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
መነባንብ፨
3.የብርሃን እናት
የብርሃን እናት የሁሉ አስታራቂ
እንሆ ምስጋናሽ ከእኛም እንዳትርቂ
ስምሽ ይጣፍጣል ከማር ከወተት
ተብለሻልና የአምላክ እናት።
ማህደር ብርሃን ሃመልማለ ወርቅ
የመወለደሽ ጥበብ እንደምን ይረቅ
በሄዋን ተዘግቶ የነበረው በር
ባንቺ ተከፈተ ምስጋናሽ የከበር።
ጌታ የመረጠሽ ለክብር ለፀጋ
ካንቺ ተወለደ በድንጋሌ ስጋ
ሰማይና ምድርን ያፀና በቃሉ
አምላክ አንቺን መርጦ ከደናግል ሁሉ
ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን የከተመብሽ
እፁብ ድንቅ እመቤት ድንግል አንቺ ነሽ።
ጡቷን እያጠባች አምላክን ታቅፋ
ምድራዊ ችግርን ስንቱን አሳልፋ
ይኸው ትኖራለች ክብሯን ተጎናፅፋ።
የምህርት አማላጅ እመቤቴ ሆይ
እንመስልሻለን በወርቅ ሙዳይ
አንቺን ያመነ ሰው ይኮነናል ወይ?
አማላጅ ነሽና ለሃጥአን ሁሉ
እኔንም ሰውሪኝ ከመከራ ሁሉ።
ነቢያት በትንቢት የተናገሩልሽ
የሰማይ መላዕክት ስምሽን የሚያገኑሽ
ብፅዕት እያሉ የሚያመሰግኑሽ
እነማን አፈሩ ያመኑ በስምሽ?
ምንም ተስፋ የለኝ አንቺውነሽ እምነቴ
አማልጂን ከልጅሽ ክብርት እመቤቴ
እኛን እንዲያድነን ወገኖችሽ ነንና
ቃሉም አይታበይ ፍርዱም የተቃና
የሰጠሽ ቃልኪዳን አይሻርምና።
ደስ ደስ ይበልሽ ቤዛዊተ ዓለም
አምላክን ስለወለድሽ በቤተልሔም
ክብርን አድሎሻል ለዘለዓለም።
ሰማይና ምድርን የማይችሉትን
ወልደሽ አሳድገሽ መድሃኒዓለምን
አዳምን ለማዳን ቃልኪዳን ገባና
ቅድስተ ቅዱሳን አንቺን መረጠና
ስጋሽን ለበሰ ምድር እንድትፀና።
ዓለምን ለማዳን ከሰማያት ወርዶ
መለኮት ከስጋሽ ፍፁም ተዋሕዶ
ነፃነትን ሰጠን ለኛ ሲል ተዋርዶ።
ወደአንቺ ተማፀንኩ ልመናዬ ፀንቶ
የሰውነቴ ሃጢያት በእኔ ላይ በርክቶ
መሳፍንት እርኩሳን እንዳይቀርቡ ከፊቴ
እንዳይ በረታብኝ በኔ ላይ ጠላቴ
አስታግሽልኝ አንቺ ክብርት እመቤቴ።
ይቀጥላል.....
....የቀጠለ
አምላክን የወለድሽ የሰማዩን ጌታ
ምህረትን አሰጭን ያድለን ይቅርታ።
በስምሽ ሲያጠጣ ሲጓዝ በበርሀ
በላይሰብ ጀኘኘአኸ በአንድ ጥሪኝ ውሃ።
እናትና አባትሽ ልጅ በማጣታቸው
ያለቅሱ እንደነበረ ወደ ፈጣሪያቸው
የወለድን እንደሆን ወንድም ሆነ ሴት
እንሰጣለን አሉ ለእግዚአብሔር ቤት።
ያናገራቸው ይህ ነበር ትንቢቱ
ቀድሶ ሰጣቸው ለዘጠኝ ወር ቤቱ።
እናትና አባትሽ ስመው ሳይጠግቡሽ
ለስለት ወሰዱሽ በሶስት ዓመትሽ
በክብር ስለኖርሽ በቤተመቅደስ
ገብርኤል ሲያበስርሽ የመውለድሽን ዜና
ፍፁም አደነቀው ዓለም ያንቺን ዜና
የመላእክት እህት የሰው ልጅ እናት
በገብርኤል ሰላምታ እናመስግናት
በድንጋሌ ስጋ አምላክን ስትወልድ
ኮከቡን አዩና ከምስራቅ ሲወርድ
ይቀጥላል...
....የቀጠለ
ተነስተው ተጓዙ ሄደው ለመስገድ
ኢየሱስ ክርስቶስ መወለዱን አይተው
ወድቀው ሰገዱለት ከመሬት ተደፍተው
ለኛ በመወለዱ በጣም ተደስተው
ኪሩቤል ሱራፌል የጋረዱልሽ
የብርሃን ደመና ዙርያውን ከቦሽ
መላዕክት ወርደው የሰገዱልሽ
አፁብ ድንቅ እመቤት ማርያም አንቺ ነሽ።
የምንመካብሽ መከታ ጋሻችን
አንቺ ስለሆንሽ ጠላት ድል መንሻችን
እንደ እሳት ይነዳል ባንቺ ላይ ፍቅራችን።
ብዙ መምህራኖች መስክረውልሻል
የአምላክ ካህናት ያገለግሉሻል
እንደ መላዕክትም ይዘምሩልሻል።
ካንቺ ይወለድ ዘንድ ፈቀደ እግዚአብሔር
አዳምን ከሲኦል እንዲያወጣው ወዶ
እንደኛ ሰው ሆነ ስጋን ተዋህዶ
በፍቅሩ ጎበኘን ልጁ በምህረት
ዘመን አስቆጥሮ ዳግመኛ ልደት
ለዓለም ቤዛ ሆነ ስረ መለከት
ስሟ የከበረ ከሁሉ በላይ
ታቦተ ፅዮን ናት ንግስተ ሰማይ
ያገለግሏታል አእላፍ መላዕክት
መሆኗን ሲያጠይቅ የሰማይ ንግስት
ምን ያጠራጥራል አማላጅነቷ
ማርልኝ ስትለው ቆማ በጉልበቷ
ልጄ ወደጄ ሆይ ስለ እናትነቴ
እማፀንሃለው ባጠባሁህ ጡቴ
የምትል ነች ድንግል ቸር አማላጃችን
ለስጋችንም ቢሆን እንኳን ለነፍሳችን
ከፅኑ መከራ የምታድን ናት
እንግዲህ ለክብሯ እንስገድላት።×2
ተፈፀመ ዝንቱ መነባንብ
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
4.እሰይ ተወለደ
፨፨፨፨፨፨፨፨
ለአዳምና ዘሩ ቃልኪዳን ገብቶለት
ይኸው ተወለደ ቃሉን ጠብቆለት
ክብሩን ዝቅ አድርጎ አምላክ ሰው ሆነለት
ሁሉን አዘጋጅቶ አሟልቶ ሲፈጥረው
በለስ እንዳይበላ አዳምን ቢያዘው
ሴጣን በተንኮሉ መጣና አሳተው።
አዳም አዳም እያለ አምላኩ ቢጠራው
አቤት አለ አዳም የአምላኩን ጥሪ ደጋግሞ ቢሰማው
ሁሉን ስላወቀ ከወዴት ነህብሎ ደግሞ በጠይቀው
የሆነውን ሁሉ አንዳችም ሳያስቀር አውጥቶ ነገረው።
አምላኩ ሲቆጣው በጣም ሲያዝንበት
አዳም ተፀፀተ ጥፋቱ ገብቶት
እርሱን ማሳዘኑ በደሉ ተሰምቶት።
እንዲህ አስከፍቶት እንዳይቀር በድሎ
ሱባኤ ሲጀምር ሊታርቀው ብሎ
ከይሲው ሰልጥኖበት በገብርኤል ተመስሎ
በፀሎቱ ተግቶ ሱባኤ ሊጨርስ 5 ቀን ሲቀረው
ዛሬ እንደገና ዲያብሎስ መጣና አዳም አዳም አላው
ይበቃህና ውጣ አምላክህ ሰምቶሃል ብሎም አቋረጠው
ድል በመነሳቱ ዳግምበዲያብሎስ
አምላኬ አምላኬ እያለ ሲያለቅስ
እንዲያ ተንሰቅስቆ ደም እምባ ሲያፈስ
አለሁልህ አለው አዳም ሆይ አታልቅስ
አዳም ሲያቅተው ሰይጣንን ማሸነፍ እርሱ ተመልክቶት
እንኳን ደስ አላችሁ ይኸው ተወለደ ዘመኑን ቆጥሮለት
ለአዳምና ዘሩ ከልጅ ልጅህ ብሎ ቃልኪዳን ገብቶለት
ሊያስተምረን ወዶ በታላቅ ጥበቡ ሰይጣንን ድል ነስቶት
እሰይ ተወለደ አሁን ደስ ይበለን
በቃሉ መሰረት አምላክ ሰው ሆነልን
ባጉል ምኞት ወድቀን እኛ እሱን ለመሆን
ደስ ይበለን ብሎ እርሱ እኛን ሆነልን
እሰይ እንበል እስቲ እሰይ ተወለደ እኛን ሊታደገን
ወደ ቀድሞ ክብርም ዳግም ሊመልሰን
ይህው ተወለደ አምላክ ሰው ሆነልን።
6.እምነቴን አልክድም
ሃይማኖት አንድት ናት የሕይወት ጎዳና፣
ጻድቃን የሄዱባት መንገዷ የቀና፣
ይህቺ ናት እምነቴ የሰጠኝ ክርስቶስ፣
ከአበው የአገኘዋት እምዬ ኦርቶዶክስ።
ቢርበኝ ቢጠምኝ ዘመድ እንኳ በአጣ፣
ክፉውን አልፈራም የመጣው ቢመጣ።
መስቀሉ ሃይሌ ነው አለ በልቤ ላይ፣
እናቴም ማርያም ናት አገሬም በሰማይ።
የአንገቴ ማህተም የአሰርኩት ጥቁር ክር፣
ስለ ተዋሕዶ ይናገራል ምስጢር።
እናም አልበጥስም ማኅተቤን ከአንገቴ፣
ብኩርናዬ እኮ ናት ኦርቶዶክስእነቴ።
የደሙን መሰረት ተዋሕዶን ጥዬ፣
እንደት ፍልስፍናን ልመን እውነት ብዬ።
የመሠረተውን ማንም ሰው ተነሰቶ፣
እንደት ይታመናል ፍልስፍና ከቶ።፡
ሃይማኖቴን ክጄ ገነትን ከማገኝ፣
ኦርቶዶክስ ሆኜ አምላክ ይኮንነኝ።
እምነቴን ከምክድ ለገንዘብ ለእንጀራ ፣
7.የፈጣሪ ችሎት
፨፨፨፨፨፨፨፨፨
አባ ተቀምጠው ከሾላ
ለሊት አድርሰው ምህላ
ሲጠባበቁ ፅድቂቱን
ሲኖሩ ሲኖሩ አንድ ቀን
ያባን ዛፍ ላይ መኖር
ሽፍቶቹ ተረድተው
ጠጋ አሉ ከሥፍራቸው
አባም በጥርጥር
ዓይናቸው ሲማትር
አባ አባታችን
አንድ ገዜ ይስሙን
የቃየል መንፈስ እየተከተለን
አንዳች ሳንበደል
ብዙ ነፋስ አጠፋን
ግብራችንን ትተን
ንስሐ ሰጥተውን
ከራሶት እንድንሆን
ፍቃዶት ይሁነን!
አባም በተራቸው
የፈጣሪ ጥሪ እየገረማቸው
እንደዚህ አሏቸው
እኔ ካለሁበት
መራሩ ምግቤ ነው
የአራዊቱ ዜማ
ጣዕመ ዜማዬ ነው
እንደኔ ለመሆን
ፍፁም ከሻታችሁ
የጠራችሁ አምላክ
ፅናቱን ይስጣችሁ።
8.፨ትንቢተ ዮናስ፨
ክፍል ፩
፨፨፨፨፨፨፨፨፨
በሕዝቡ መካከል አመጽ ስለ ጸና
በጣም ተቆጥቼ አዝኛለሁ እና
ይህንን ለነነዌ ንገራት በአዋጅ
አለና ለዮናስ ለአሚታይ ልጅ
እግዚአብሔር አዘዘው እንዲሄድ በቶሎ
ዮናስ እቢተኛው አሰበ ኮብልሎ
ከአምላኩ ተደብቆ አምልሎ ሊጠፋ
ወደ ተረሲስ ሲጓዝ የሄደ ወደ ያፋ።
ዋጋ ክፍልና ከመርከብ ተሳፍሮ
እያጉረመረመ ባሕሩን ተሻግሮ
ዮናስ ተደብቆ ሲሄድ በግስገሳ
ከእግዚአብሔር ተልዕኮ ማዕበል ተነሳ
ታላቅ ሞገድ ሆነ ባሕሩ ተቆጣ
መርከበኞች ፈሩ ታላቅ ሽብር መጣ
መርከቡ እንዲቃለል እናድርግ እያሉ
አንስተው ብዙ ዕቃ ወደ ባሕር ጣሉ
ባህሩም ባሰበት በጣም ተናወጠ
መረከቡ መሰለ የተገለበጠ
ሰው ሁሉ ተነሳ ጸሎት ለማድረስ
ይኽ ሁሉ ሲሆን ተኝቷል ዮናስ
ወደ ዮናስ ሄዶ የመርከቡ አለቃ
ቀሰቀሰው እና ከእንቅልፉ ሲነቃ
እግዜር እንዲያድነን ከዚህ ክፉ ጥፋት
ተነስ ጸልይ አለው ይብቃህ ማንቀላፋት
በመርከቡ ውስጥ ያሉ ሰዎች ተሰብስበው
ተመካከሩ እና ቢናገሩ አስበው
አለው ኃጢአት ሰርቶ ከእኛ ጋር የመጣ
ለይተን ለማወቅ እንጣጣል ዕጣ
አለዚያ አንድንም ስለተባባሉ
ተሰባሰቡና ዕጣ ቢጣጣሉ
እውነትም እንዳሉት አጥፊው ሰው ታወቀ
በእንቢተኛው ነብይ በዮናስ ወደቀ
በዮናስ ተረዳና እጁ እንደ ተያዘ
ያጠፋውን ጥፋት ገልጦ ተናዘዘ
ምነው ባትመጣ ተጣልተክ ከጌታ
እየው መርከባችን እንደሚንገላታ
ቁጣውን እንዲታገስ ለማግኘት ጸጥታ
በል አንተው ፍረደን ምን ይበጃል ቢሉ
ዮናስ መለሰና እዚህ ያለ ሁሉ
ስለምን ይጠፋል በእኔ የተነሳ
ወደ ባሕር ጣሉኝ አለብኝ አበሳ
ተመልከቱ እንሆ ስራውን ዐወቀ
ጥፋቱን ገለጠ ይኽው መች ደበቀ
እሱ ከፈረደ መልሶ በራሱ
ምን እናድርግ ብለው ሊጥሉት ተነሱ
ከደሙ አንጻን ሲሉ ለእግዜር አመልክተው
ወደ ባሕር ጣሉት ዮናስን አውጥተው
በዮናስ ላይ ኖር የመጣው ይህ ጥፋት
ባሕሩ ጸጥ አለ ልክ በዛው ሰዓት
ይቀጥላል.....
ትንቢተ ዮናስ
ክፍል ፪
ዮናስም ተውጦ በእግዚአብሔር ፍቃድ
ሶስት ቀን ሶስት ለሊት ሊያድር በዓሣ ሆድ
ተቀይመህ ኖረህ ከላይ ብትቆጣ
እንዲህ ያለ መአት በራሴ ላይ መጣ
የባሕሩ ሞገድ እኔን አዋከበኝ
ውኃና ጨለማ ሲኦልም ከበበኝ
እያለ በአሳ ሆድ ዮናስ ሲቀመጥ
አምላኩን ለመነው በመለማመጥ
የታዛዥነትም ጠባይ እያሳየ
አዝኖ ተጸጽቶ ከልቡ ጸለየ
ምንጊዜም ቢቆጣ ነውና መሓሪ
ፊቱን መልሶለት ታረቀው ፈጣሪ
ዓሣውም ዮናስን ውጦ ሳያስቀረው
ከባሕር ተፋና መሬት ወረወረው
ይቀጥላል.....
ትንቢተ ዮናስ
ምዕራፍ፫
ይህንን የኔን ቃል ስማና በቶሎ
ሄደህ ለነነዌ እንድትነግራት ብሎ
ደገመና እግዚአብሔር ዮናስን አዘዘ
ነነዌ ሊገባ ዮናስም ተጓዘ
ድምጹን ከፍ አድርጎ ነቢዩ ዮናስም
ከዛሬ ጀምሮ አርባ ቀን ድረስ
ነነዌ ጠፊነች ከስር ተገልብጣ
አለና ለፈፈ የእግዚአብሔርን ቁጣ
ሳያንገራግሩ ሁሉም ቢለምኑ
የነነዌ ሰዎች ተጨንቀው አዘኑ
ከትልቅ ጀምሮ ሕፃኑ ድረስ
ሕይወቱ የቆመች በሥጋ በነፍስ
ሰውም ሆነ እንስሳ ይቀበል ንስሐ
ፍጡር ሁሉ ይጸልይ ይጹም ከእህል ውሃ
ሁሉም ከልብ አዝኖ ማቅ እየለበሰ
ከክፉ ወደ ደግ እየተመለሰ
መቼም ወሰን የለው የእግዚአብሔር ምሕረቱ
ይጸልይ አለና ይለምን በብርቱ
ንጉሡ አሳወጀ ከነ መኳንንቱ
የነነዌ ሰዎች በእውነት ከልቦና
መፀፀታቸውን እግዚአብሔር አየና
ፍጡር ቢለምነው እምባ እያፈሰሰ
ምሕረቱን አውርዶ መአቱን መለሰ።
ይቀጥላል...
ትንቢተ ዮናስ
ምዕራፍ ፬
የተናገረው ቃል ስላልተፈጸመ
ዮናስ ተቆጥቶ እያጉረመረመ
እንደዚህ እያለ ጸለየ ወደ አምላከ
እኔን መጀመሪያ ነነዌ ለመላክ
አሰብህ በታዘኝ ይህንኑ አውቄ
ወደ ተርሴስ ልሄድ ጠፋሁ ተደብቄ
ምሕረት የበዛ መሓሪና ታጋሽ
በደል የምትረሳ ከቁጣ ተመላሽ
የቁጣህን ያህል ምሕረትህ የጸና
መሆንክን ጥንቱን እኔ አውቃለሁና
እኔን ግን ግደለኝ ልሙት ልቀበር
ሐሰት ተናግሬ የማይሆን ነገር
አልፈልግምና ቆሜ ለመኖር
ከከተማ ወጥቶ በምስራቅ በኩል
ከወደ ዳር ሆኖ ነነዌን ሲያሰተውል
ምን እንደሚያገኛት ለማየት ዮናስ
ሠርቶ ተቀመጠ አንድ ትንሽ ዳስ
እግዜር በጥበቡ አንድ ቅል አብቅሎ
ቅሉም እንደገና ከፍ ከፍ ብሎ
የዮናስ እራስ እንዲያገኝ ጥላ
ለጸሓዩ ንዳድ ሆነለት ከለላ
በዚህ ብቅል ነገር ዮናስ ደስ አለው
እንዲህ ቶሎ ደርሶ ሲያገለግለው
እግዜር በማግስቱ ጧት በማለዳ
ቅል የሚበላ ትል ፈጣሪ አሰናዳ
ትሉ ቅሉን በልቶ በፋጥነት ደረቀ
ፀሐይ ወጣችና ጊዜው በጣም ሞቀ
እግዜር አዘዘና ትኩስ ንፋስ መጣ
የሚከለከልበት መጠጊያ ስላጣ
ቅሉ ደረቀና ንዳድ ቢያቃጥለው
ዮናስ ተበሳጭቶ ለአምላክ እንዲህ አለው
እንደዚህስ ሆኜ ቆሜ ከምኖር
እባክህ ግደለኝ ልሙት ልቀበር
ደረቀበኝ ብልህ ይህን ቅል ለመጣት
እውን ይገባል ወይ ያንተ አሁን መቆጣት?
ብሎ እግዜር ቢጠይቅ መለሰ ዮናስ
በንዴት ብዛት እስክሞትም ድረስ
አዎን ይገባኛል መናደድ መጨስ
እግዜርም መለሰ ለምን ጠፋ ስትል
ይህ ያልለፋሕለት ያልደምክለት ቅል
አንተ ስትናደድ ፈጥራያት እኔማ
ሳጠፋት ሳፈርሳት ነነዌን ከተማ
መቶ ሃያ ሺህ ነው የህዝቧ ብዛት
ለምን ትቆጣለህ እኔ ባዝንላት
ብሎ በምሳሌ ሲያስተምር ይቅርታ
ለዮናስ ነገረው የምሕረት ጌታ
ለእግዚአብሔር ቸርነት ምስጋና ይደረስ
በዚህ ተፈጸመ ትንቢተ ዮናስ።
\= ተፈፀመ = /
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
* ከክቡር አቶ ከበደ ሚካኤል" የቅኔ አዝመራ" የተወሰደ 1956 ዓ.ም
እንሆ የነነዌ ፆምም ተፈፀመ የነነዌን ሰዎች ልመና ተቀብሎ በምሕረት እንደጎበኛቸው እኛንም በምሕረቱ ይጎበኝን
ለሀገራችንምም ሰላም ለህዝቦቿም ፍቅር አንድነትን ቁጣውን እና መአቱን መልሶ በምሕረቱ ብዛት ይመልከተን ይቅር
ይበለን!!!አሜን
ቃል...... ብቻ.........ተናገር..........!
10.ተጠቃሚ ያጡ መድኃኒቶች
1/ ቃለ እግዚአብሔር
ጠዋት አንድ
ማታ አንድ
2/ ንስሐ
በየሳምንቱ አንድ አንድ
3/ ስጋወ ደሙ
ቢያንስ በ 40 ቀን አንዴ
4/ ጠበል
ከምግብ በፊት በየቀኑ አንዴ
5/ እምነት
ዘወትር በየሰከንዱ ያለማቋረጥ
6/ ፍቅር
ዘወትር ያለማቋረጥ ለሁሉም
7/ ሰላም
ለተከታታይ ሰዓታት እስከ ዘላለም
8/ጸሎት
11.ኃይሌን መልስልኝ፨
ጧት በማለዳ
ቤትህ ስገሰግስ
ሳልታክት ዘወትር
አንተን ሳገለግል
ስምህን ሳወድስ
ያኔ በኃይል ነበረኝ
ጸጋህም በዝቶልኝ
ስንፍና ርቆልኝ
መሰልቸት የለብኝ
አሁን ግን ጌታዬ ሆይ
ደሊላ ደልላኝ
ጉልበቴ ብርክ ይዞት
ኃይሌን አሳጥታኝ
እንደው ላታዛልቅ
በጥላቻ አፍቅራኝ
በጭንቀቴ ላትደርስ
ለጠላቴ ሰጥታኝ
በምርኮ አለሁና
በኃጢአት ተከብቤ
አንተን እንዳመልክህ
ተመልሶ ልቤ
እንደው ለአንድ አፍታ
ኃይሌን መልስልኝ
የኃጢአቴን ምሰሶ
ነቃቅዬ ጥዬ
የአንተ ሆኜ ልገኝ።
የልቤ ማድጋ፨
ዘወትር ጠዋት ማታ ስለፋ ስተጋ
እሞላለሁ ብዬ የልቤን ማድጋ
ዛሬ በንስሐ ሞላችልኝ ብዬ
በሐሰት ስቦርቅ አይሎ ደስታዬ
ነገ ደግም ባዶ ወና ሆና ሳያት
ኀዘኔ በርትቶ ስሞክር ልሞላት
ጠብም ላይልላት ደግም እየሞላች
ዳግም ስትጎድል ምሬቴ አይሎ
ደክሜ እንዳልዝል
ከዚያ ከምንጩ ዳር አግኝቼ አምላኬን
ዳግም ላይጎድልብኝ ሞልተህ ማድጋዬን
ለስምህ ልዘምር ላብዛ ምስጋናዬን።
12.ተወው ምን በወጣህ ¡
~~> እንዳትበላ!
የቀድሞ ህግ ትዕዛዙ
ፍጡራን ለፈጣሪ እንዲገዙ
ድንበር ገደብ ቢበጅለት
መከልከል መች ሊዋጥለት
"ስለምን ይሆን ቀድሞ መፈጠሩ?
ኋላስ በህግ መታጠሩ?
እንዳልገባበት ነው በሥልጣን በክብሩ?"
እንዳትበላ ቢከብድበት
እጁን ሰዶ ቢያደማት
በባህሪው እኩይ ንዋይ ሸመተበት
ጽነት መርገም ለበሰበት
የእንቢታ ዋጋ ንረት
በሥጋ የመቃብር ግዞት
በነፍስ የሲኦል ርደት
በስብዕናው ላይ አጠላበት
የሞት ሞትን አመጣበት
አተርፍ ባይ አጉዳይ እንዲያ ከሰረበት
+++
"ፍጠረኝ ሳይለኝ ፈጥሬው
ሺውን ሰጥቼ አንዷን ብነፍገው
አትብላን መጠበቅ አቃተው?"
ተካሽን ልካስህ አሰኘው
"አበስኩ ገበርኩ" ብሎ ቢያለቅስበት
አርአያ ገብርን ነስቶ ሞቶ ሞቱን አጠፋለት
+++
የትላንተ የገበያ ውሎ
ለዛሬው ተስተካክሎ
ከመስኩ እንዳትርቅ እረኛው ቢወድህ
ላንተ በዚህ ዘመን ህጉ እንዳይከብድብህ
በይቡስ ሳር ፈንታ እራሱን ሰዋልህ
"ዳግም ብላና ዳን ይኸው ሕይወት" አለህ
አንተማ እንጂ መች ተረዳህ
የተቃርኖ ድንበር ናፈቀህ
የእንዳትበላ ህግ አሰኘህ
ብላና ዳን መች ሊቀልህ
+++
ምነው ያኔ አንተን በገነት ቢያኖርህ
ሺውን ሰጥቶ አንዷን ቢነፍግህ
+++
ግን ተወው ኧረ ተወው ምን በወጣህ
የብላና ዳን ህግ ከከበደህ ካስጨነቀህ
አትናደድ .... አትበሳጭ ..... አትቆጣ
ገሃነመ - እሳት እንጂ ሌላ ምን ሊመጣ¡
13.የመፃጉዕ ትዝታ
በዕብራይስጥ ቤተ-ሳይዳ ከውኃው ዳር መጠመቂያ
ከድኅነቱ ቀዬ ከደዌ ፍታት መላቀቂያ
ህመም የደቃው አካሌን እየወቀረው ንፋስ ብርዱ
ኩምትር መንፈሴን ያዘለ የልቦናዬ አጸዱ
ከተስፋ ጽንፍ የቆመ ተሰውሮበት መንገዱ
ፈውስ ርቆኝ እንደሰማይ ከአልጋዬ እንደተሳፋሁ
የብጤዎቼን ድውያን የጣር ድምጸት እየሰማሁ
መላኩ ወርዶበት ውኃው ቢናወጥም
እዳር ሆኖ መሻት እንጂ ገብቼበት ከቶ አላውቅም
በለስ ቀንቶት ከውኃው ቀድሞ የገባ
ዳግም እንደወለዱት ሲፈነጥዝ እንደ እምቦሳ
ያን ኩምትር መንፈሴን ከጥጋቱ አነቃለሁ
ተስፋ ቀጥላለው ድኅነት እናፍቃለሁ
ግና ሰው የለኝም መላኩ እንደወረደ ከውኃው የሚዘፍቅ
ልድን እወዳለው ከጠፈረኝ ደዌ ልፋታ ልላቀቅ
ሠላሳ ስምንት ዓመት በአንድ ጎልማሳ እድሜ
ህመሜን ታቅፌ ባልተኛሁት እንቅልፍ ከአልጋ ተጋድሜ
ልድን እወዳለሁ የኔ ቀን መቼ ነው
ለካ ዛሬ ደግሞ ዕለቱ ሰንበት ነው
በአይሁድ ሥርዐት ማረፊያ ብቻ ነው
ልድን እወዳለሁ እንደመቶ አለቃው ልጅ በቃል ከሞት መነሳት
እንደዓይነ ስውሩ በጭቃ ዓይን መብራት
ልድን እወዳለሁ
ደግሞ በዚህ መሀል
ደም ግባቱ ያማረ የተጎናጸፈው ከወተት የነጣ
አንድ ሰው አየሁኝ ወደኔ ሲመጣ
ወደኔ መምጣቱ የውበቱ ማማር እጅጉን ገርሞኛል
ይባሱኑ ደግሞ ልትድን ትወዳለህ? ብሎ ይጠይቀኛል
እንዴ!
ካልተኛሁት እንቅልፍ ከደዌ ቅዠቴ
ፋታ ከነፈገኝ ከራቀኝ እረፍቴ
ተኛ እየተባለ ይኸው ተኝቻለሁ
እስከዛሬም ሰው ባይኖረኝ ከኖርኩበት አለሁ
አዎን ጌታዬ ሆይ ልድን እወዳለሁ
ፀሐይን ባስናቁ ዓይኖቹ እያየኝ ይህን ተናገረኝ
አልጋህን ተሸከም ተነስተህ ሂድ አለኝ
የጓጎለ ደሜ በአካሌ ሲራወጥ ተሰማኝ ሙቀቱ
ድንዝዙ ጅማቴ ከውስጤ ላይ ሲያብብ አነቃኝ ንቃቱ
ዕፀ ሕይወት ፉት እንዳለ ከእፍታው እንደቀመሰ
ከራስ እስከ ጥፍሬ አካሌ ታደሰ
በእጆቼ አዘዘ በእግሮቼም አዘዘ
እንደ በትር ቀሎት እጄ አልጋዬን ያዘ ከእንቦሳ ቀልጥፎ ፀንቶ እግሬ ተጓዘ
የዓመታት ሸክም እኩል ከአንድ ቀን
ከውለታ ሚዛን ቀርቦ ባይመዘን
ጽናቱን ለመቅመስ ጣዕሙ ምን እንዲል
የተሸከመንን መሸከም ደስ ሲል
ግና ሸክሜን ረሳሁ
ውቡ ደም ግባትህ በደም ተሸፍኖ ጽሕምህ ተነጭቶ
መለኮት የሞላው ተነስ ያለኝ ቃልህ በመከራ ቃትቶ
እጅህ ለእጄ እግርህ ለእግሬ ከመስቀል ተሰፍቶ
የመታደሴን ቀን የሰንበት ዕለት ፈውሴን ህመሜን ረስቼ
ልማድ ሻረ ብዬ ክንዴን ባንተ አንስቼ
ከወገኔ ወግኜ ከገፉህ ልገፋህ
ባፀናኸው እጄ በጥፊ ስመታህ
ማሩን ቸርነትህን በእሬት የቀየረ
ውለታ ቢስ እጄ ይኸው ደርቆ ቀረ፡፡
በደም ብቻ ወገን ሲመሽ ለሚረሳ
መዳን እየሸሸ አመጽ ለሚያወሳ
ቃል ብቻ ተናግሮ ከደዌ ሚፈታ
ከዘላለም አባት ከምህረት ጌታ
እንዴት ይመረጣል? ብዬ ጠይቃለሁ
ሕመሜን አልጋዬን ደዌን እመኛለሁ
ወደኔ ስትመጣ የበራው ጸዳልህን ዓይንህን እያየሁ ተነሳም ባላልከኝ በቀረሁ እላለሁ
ፍቃድህ ነውና መነሳት ካልቀረ
ከልቤ መንበር ላይ ፍቅርህ እንዳደረ
ማዳንህ ብቻ እንዲታይ አልጋዬን እንደተሸከምኩ
ሐውልት ሆኜ ቆሜ ዘላለም ባሸለብኩ
ከዕብራይስጥ ቤተ-ሳይዳ ከውኃው ዳር መጠመቂያ
ከድኅነቱ ቀዬ ከደዌ ፍታት መላቀቂያ
ጸጸቱ ሲያደብነኝ የክህደት ጅራፉ
አንተን ሳልከተል ያ ጊዜ ማለፉ
ቁጭ አርጎ ያሰተክዘኛል
አሁን ቦታው ረጭ ብሏል
ውኃውም ደራርቆ ትቢያ ብቻ ቀርቷል
የመላኩን መውረድ በጉጉት ሚጠብቅ
ባለደዌ ሽባ በሽተኛ የለም መዳን የሚናፍቅ
ከአስታማሚ ግርግር ከታማሚ ሲቃ
ከሁካታው ሰክኗል ተኝቷል ላይነቃ
ቦታው ረጭ ብሏል
አሁን ከአካል ደዌ ከሽባነት ይልቅ ሌላ ሕመም ገዝፏል
የተጣመመ ልብ የአእምሮ ስብራት ክፋት ብቻ ነግሷል
እንደኔ እጅ ደርቆ ያልታየ ሰልሎ
ከግራህ የቆመ የቀኝህን መስሎ
ብዙ ከሃዲ እጅ አለ ተከልሎ
ኤዲያ እኔን ብሎ ወቃሽ
ከቀድሞ ቦታዬ ዛሬም ከዛው አለሁ አንተን አስባለሁ
የሰንበት ቀን ደም ግባትህን የአርብ ስቃይ ከከለለው አነፃፅራለሁ
የሰንበት ቀን ራስህን የአርብ እሾህ ከነደለው
አነፃፅራለሁ አንተን አስባለሁ
ሞት ድል መንሳትህን ትንሳኤህን ሰምቻለሁ
ግና
እኔ አልተነሳሁም ከፈኔን አልገለጥኩ
እንደተዘጋብኝ አለሁ እንደነበርኩ
አልጋህን ተሸከም ተነስ ሂድ እንዳልከኝ
መስቀልህን ሰጥተህ ና ወደኔ በለኝ
ካንተ ጋር ልነሳ እሱ ነው ሚበጀኝ
አብሬህ ልነሳ እሱ ነው ሚበጀኝ
14.አበው ይናገሩ
እስኪ ቀስቅሷቸው አበው ይናገሩ
የምንኩስና ግብር ምን ነበር ምሥጢሩ
የክርስትና ሕይወት ምን ነበር ተግባሩ
መቃብሩን ክፈቱና አበው ይመስክሩ፡፡
እኔስ ሰው አማረኝ የሃይማኖት ጀግና
ወልድ ዋሕድ ብሎ በእምነቱ የፀና
ጀግና ሰው አማረኝ ጠላት አሳፋሪ
ንጽህት ድንግል ብሎ እምነቱን መስካሪ፡፡
ነብያት በመጋዝ የተሰነጠቁት
ሐዋርያት ቁልቁል የተዘቀዘቁት
ሰማዕታት በእሳት የተለበለቡት
ቅዱሳን በገዳም ደርቀው የተገኙት
ምሥጢሩ ምን ነበር? አበው ይናገሩት፡፡
ይናገር ዝቋላ ግሸን ላሊበላ
የቅዱሳንን ዐፅም ለምን እንዳልበላ፡፡
ዋልድባ ይናገር ዜጋመልም ሳይቀር
እንባቸው መፍሰሱ ለምን እንደነበር፡፡
ነበር ወይ ፈልገው ሹመት ሽልማት?
ወይስ ሀብት ንብረት የተሟላ ቤት?
ወይስ አምሯቸው ነው ፈልገው መሞት?
እናንተ ገዳማት ምሥጢሩን አውሩት፡፡
ጐበዝ ሰው አማረኝ በእምነቱ የፀና
ምግባር ሃይማኖቱ በእጅጉ የቀና፡፡
እንጦንስ የወለደው በምግባር በእምነት
ተምሮ ያደገ ከተክለሃይማኖት፡፡
የጊዮርጊስ ወገን የት ነው የማገኘው?
በመሀል ከተማ በአራዳ ውስጥ ነው?
ወይስ በዝቋላ በደብረ ሊባኖስ በደብረ ዳሞ ነው?
ወገን ሰው ናፈቀኝ ዐይኔን ሰው አማረው
የሃይማኖት ጀግና የትነው የማገኘው?
ልግባ ወይ ዋልድባ ጫካ ካለበት
ማኅበረ ሥላሴ ከቅዱሳን ቤት?
አክሱም ግሸን ማርያም ከቃል ኪዳን ቦታ
ይገኛል ወይ ጀግና ጠላት የሚረታ?
ፈሪሐ እግዚአብሔር በልቡ ያደረ
ቤተ ክርስቲያንን ያልተደፋፈረ፡፡
የት ነው የማገኘው ለሃይማኖቱ ሟች
ለተዋሕዶ እምነት ጠበቃ ተሟጋች፡፡
የወገን መመኪያ የከሀዲ መቅሰፍት
ማነው እሱ ጀግና ተኝቶ እንደሆነ ይነሣ ቀስቅሱት፡፡
እስኪ ቀስቅሷቸው አበው ይናገሩ
የምንኩስና ግብ ምን ነበር ምሥጢሩ?
የክርስቲያን ሕይወት ምን ነበር ተግባሩ?
መቃብሩን ክፈቱት አበው ይመስክሩ፡፡
ወገን ሰው ናፈቀኝ ዐይኔን ጀግና አማረው
በእምነቱ የፀና የትነው የማገኘው?
ብቅ ይበል እንየው እሱ ማነው ጀግና?
በጐችን ከተኩላ ነቅቶ የሚጠብቅ
መከራ ቢከበው ከቶ የማይሰቀቅ
የሃይማኖት ጀግና ቆራጥ ሰው ገበሬ
እንደዚያ እንደ ጥንቱ ይገኛል ወይ ዛሬ?
የወገን የዘመድ ጥቅም ያላወረው
የመናፍቆች እጅ ኪሱን ያልዳበሰው
የዓለም አሸክላ ልቡን ያልማረከው
የክርስቶስ ወዳጅ እሱ ጀግና ማነው?
ምሥጢርን ከምሥጢሩ አንድ አድርጐ ቀምሮ
ወልድ ዋሕድ ብሎ ሃይማኖት መስክሮ
እንጦንስን መቃርስን በልቡ ያኖረ
ከአትናቴዎስ ከቄርሎስ ጥበብ የተማረ፡፡
ድንግል እመቤቴ ብሎ የሚመሰክር
መሆኗን የሚያምን ማኅደረ እግዚአብሔር
ቋቅ እንትፍ ብሎ የጠላ ክህደትን
ትንታግ ምላስም ጭንግፍግፉን
ልሳነ ጤዛ መናፍቅን
ወልደ አርዮስ ዲቃላውን፡፡
በሰይፈ ሥላሴ የሚቀላ
ጀግና ማነው ዝቅ ይበላ፡፡
ነበር ወይ ያን ጊዜ ለሹመት መጓጓት
እስኪ ጎርጎርዮሰ ይምጣና ጠይቁት
ፍቅርንም ይጠየቅ አባ ሕርያቆስ
ምሥጢርን ጠባቂ ወይም አባ መቃርስ፡፡
የክርስቶስ ባርያ የአጋንንት መቅሰፍት
ወንጌል አስተማሪ የሃይማኖት አባት
ይህንን ጉድ እንዲያይ ይምጣ ተክለሃይማኖት
የጸሎት ገበሬ ገብረ መንፈስ ቅዱስንም ይነሣ ቀስቅሱት
ይነሣ ጊዮርጊስ ይመስክር ምሥጢር
የሃይማኖት ፍቅር ምን እንደነበር፡፡
ከእናቶቻችንም አሉ ለፍጥረት ያዘኑ
ዲያብሎስ እንዲማር ጌታን የለመኑ፡፡
ስንቱን ልዘርዝረው የአባቶችን ሙያ
መር ብለው የወጡት ከሥጋ ገበያ
ጾም ጸሎት ነበረ የሃይማኖት ጋሻ
መልከስከስ ምንድነው እንደ አበደ ውሻ፡፡
እንደ መስኖ ውሃ ከነዱት መነዳት
ዓላማው ምንድነው የዘመኑ ወጣት፡፡
እኔስ ሰው አማረኝ የሃይማኖት ጀግና
ወልድ ዋሕድ ብሎ በእምነቱ የፀና
ዐይኔን ሰው አማረው ጀግና ሰው ገበሬ
ሃይማኖት መስካሪ እንደ ጥንቱ ዛሬ፡፡
ምንጭ፡- መለከት 1 ኛ ዓመት ቁጥር 6
ሕያውን ከሙታን መካከል ስለምን ትፈልጋላችሁ? ተነስቶአል እንጂ በዚህ የለም። ሉቃ 24፥5-6
15.ትንሣኤ
የመቃብሩን ድንጋይ ፈንቅሎ
የመግነዝ ጨርቁን አውልቆ ጥሎ
በአይሁድ ወታደሮች ላይ
በኃይል ሰልጥኖ
ክርስቶስ ተነሳ ከፍ ከፍ ብሎ።
ለማያልፍ ርስት ዳግመኛ የወለደን
ሕይወቱን ሰጥቶ ያከበረን
ለአዳም ልጆች ሁሉ ተስፋ የሆነን
ይኸው በኩራት ተነስቶአል ደስ ይበለን።
ከእንግዲህ ቀረልን በሞት መጠቃቱ
ሲፈርስ አይተነዋል የዲያብሎስ ግዛቱ
ክርስቶስ ሲነሳ በግርማ መለኮቱ።
እኛን በገዛ ደሙ ገዝቶ
በፍቅሩ ወድዶ ስቦ
ወደሚደነቅ ብርሃን ጠርቶ
ኃጢአታችንን ሽሮ አጥፍቶ
ዛሬ አየነው በክብር ተነስቶ
የእሱ የሆነውን በዲያብሎስ ላይ ሹሞ
ረግጠን እንድንገዛው ማህተሙን አትሞ
ትንሣኤ ሆነልን በጸጋው ሸልሞ
አማኑኤል የተባለው
አልፋና ኦሜጋ የሆነው
መጀመሪያና መጨረሻ የሌለው
እርሱ እኮ ራሱ ትንሳኤ ነው።
አሕዛብን ሁሉ በብረት በትር የሚገዛ
ከበረዶ ይልቅ እጅግ የነጣ
ነጭ ልብስ ለብሶ ሲነሳ
ሞት ሆይ መውጊያህ ታዲያ የቱ ነው?
አዳምን ከክብሩ አውርዶ የለየው
ወደ መሬት ቁልቁል የጣለው
እኛስ ይኸው ዕልል ብለናል
ዳግማዊው አዳም ሲነሣ አይተናል
ዲያብሎስ እንደማይችለው አውቀናል።
16.ዛፏ አስተማረችን
አለም ለስጋው ያንተን ፍቅር ትቶ
ለክብሩ ቢጨነቅ ዋጋውን እረስቶ
ለስጋው ሲያደላ ነብሱን እየረሳ
ከትቢያ ከደይኑ ያወጣውን ከአበሳ
ለዲያቢሎስ ተገዝቶ
ፀጋውን ተቀምቶ
ተስፋው ጨላልሞ
በጨለማ ቆሞ
የከፈለውን ዋጋ ለአፍታ እንኳን ቢረሳ
ጠላት እያደባ ሲያጓራ እንደ አንበሳ
ምንም እንኳን ቢረሳ የአምላክ ቸርነቱ
ፈጥሮ አሳልፎ ማይሰጥ ለጠላቱ
እየበደልነው የሚያነሳ
ሚያስታውስ ብንረሳ
ብንወድቅ የሚያነሳን
ተርበን ያጠጣ ያበላንን
እንደ ወዳጅህ ይሁዳ ስንበድል አንተን
ንስሃ እንድንገባ ዛፏ አስተማረችን
ለብዙ ምክንያትም ወንጌል እያወጀች
መዳን አሁን ነው ብላ እየሰበከች
አንታዘዝ ብለን አድልተን ለስጋ
የሞታችን ጦማር ከፊት ቢዘረጋ
በሃጥያት ተጨማልቀን ቢገፈፍ ፀጋችን
በባርነት ግዞት ዲያቢሎስ ሲገዛን
በእጃችን ላይ ያለው አርነት ባርነት
ነብሳችን ከወዴት ከሲኦል ወይስ ገነት
ንስሃ ገብተን እንዲምረን በእውነት
አምላክ ይጠብቀን በፍፁም ቸርነት
17.መነባንብ
፨፨፨፨፨፨፨፨
ክፍል ፩
አለሁ አለሁ ለእናቴ
ለብርታት ጉልበት ፅናቴ
አለሁ!አለሁ ለርስቴ
ሀገሬ ከላይ ነው አባቴ እግዚአብሔር ነው
ዘራፋ! በቀራኒዮ የተሠቀለው
የምስጢር ደሙ እጄን ቢነካው
ከመኝታዬ ከእንቅልፌ ነቃሁ
ዘራፋ!2 አትደፈርም ፅኑ ሃይማኖቴ
አትሠደብም ድንግል እናቴ
ይቀዳ ደሜ ይርገፍ አጥንቴ
መቃብር ልግባ ይቀላ አንገቴ
ልሠደድ ልውጣ ይቅርብኝ ቤቴ
ይቅርብኝ እምቢ ሀብት ንብረቴ
አትደፈርም ፅኑ ሃይማኖቴ።
ዘራፍ!2 አይበጠስም ቃል ማህተቤ
አይበረዝም የእምነት ክታቤ
አትናወጥም ታንኳ መርከቤ
አትለወጥም እውቀት ጥበቤ
አትታደስም ታሪክ እንቅቤ
ከምትቃጠል እኔ ጠግቤ
ሁሉም ይቅርብኝ ልሙት ተርቤ።
ዘራፍ!2 የጀግኖቹ ዘር ጀግና የተባለች
የጳውሎስ ወኔ በፅኑ የጠራኝ
የዲዮስቆሮስ የፀጋው ልጅ ነኝ
ማንም አይነካሽ ፊትሽ አይቆዝም አትዘኚብኝ።
ክፍል፪
መነባንብ
፨፨፨፨፨፨
ክፍል፬
ዘራፍ!2 ፍቅርን ታጥቄ ፍቅርን ለብሼ
በንስሐ እንባ ውስጤን አድሼ
የጌታን ስጋ ደሙን ጠጥቼ
በቤትሽ ኖሬ ደጅሽ ፀንቼ
አሁንም ልኑር ጡትሽን ጠብቼ
ዘራፍ!2 ማነው የሚነካሽ የታለወንዱ
ቢፈራገጥም አምላኩ ሆዱ
መሠረትሽን ከቶ አይንዱ
ዘራፍ!2 የቄርሎስ ምላሽ ጥንተ ሃይማኖት
የአባ ጊዮርጊስ ፀሎት ደረሰቱ
የቅዱስ ማርቆስ ወንጌል ስብከት
የአግናጢዎስ የአንበሳ ራቱ
የአባ እንጦስ ብርታት ፅናቱ
የቅዱስ መቃርስ ምናኔ ቤቱ
የቅዱስ ያሬድ ዜማ ስርዓቱ
የአትናቴዎስ ብርታት ስደቱ
የአረጋዊ ወዳጅ እናቱ።
ዛሬም ይስማል ስዓታት ቅኔሽ ዚቅ ማህሌቱ
ይከበራል ነገም ገና ከፍ ይላል መስቀል ፅላቱ
እማ ተዋህዶ መቼም አትጠፋም ይሰማ ፍጥረቱ 2
አትጠፋም... አትጠፋም
አትጠፋም.... እማ ተዋህዶ❕
*/ተፈፀመ ዝንቱ መነባንብ
18.፨አዘክሪ ድንግል፨
በኃጢአት በሽታ በበደል ቁስል
በክፋት በተንኮል በቂም በበቀል
በጭካኔ ጅራፍ በዘር ክፍፍል
ተመተናልና አማልጅን ድንግል።
ለተፈጠርንበት እንድንቆም ለዓላማ
ሕገ እግዚአብሔርን ጆሮአችን ሲሰማ
በወንጌሉ አንድምታ በቅኔው ከተማ
ይፃፍ በውስጣችን አግዥን እማማ።
በማስተዋል ጥበብ ይሰራ ውስጣችን
ለጾም ጸሎት ስግደት ይነሳ ልባችን
ፍቅር ቸርነት ቅንነት ይክበበን
የአማኑኤል እናት ኪዳንሽ ያበርታን።
ከፈጣሪ በታች ከፍጡራን በላይ
ክብርሽ የገነነ እናቱ የአዶናይ
ምሕረትን አሰጭን ይመልከተን ከላይ
አሳዝነነዋል እየሆንን ኮብላይ።
የመከራው ዱላ እስከ አጥንት ደርሶ
ፊታችን ጠቋቁሯል በዕንባ በለቅሶ
በከንቱ እንዳንጠፋ ይማረን መላልሶ
አዘክሪ ድንግል ያቁመን አድሶ።
በተሰጠን መንገድ ዘመን በማይሽረው
በአንዲቷ ጥምቀት በደም በታተመው
በሕያው መዝገብ ላይ በቃል በተፃፈው
ለቅዱሳን ሁሉ አንዴ በተሰጠው
እንድንፀና አድርገን ጠብቀን ከከፋው
አምላከ አማልእክት ስልጣኑ ያንተ ነው።
ድንግል ሆይ አሳስቢ
19.፨የሚያስገርመኝ የለም፨
ያዓለም ከንቱ ካባ አይለብስ ትከሻዬ
ሁሉን ምረታበት እምነት ነዉ ጋሻዬ
ዉዳሴም አይጠቅመኝ አድናቆት አልሻ
ፅድቅነዉ ምኞቴ እስከመጨረሻ
ቢሉኝ ዉበት ለብሰዉ ገፄን ያደንቀዋል
ወይም ጎስቆል ብለዉ ሰዉን ይንቀዋል
እንዳትሳሳቱ አልደክምም ለመልሱ
ጥያቄ ትታችሁ ባንድ ለማመስገን ሁላቹ ተነሱ
ሁሉን የሚቀበል በክብር ዙፋኑ አለ በመቅደሱ
የዘዉትር ድካሜ የሌተ ቀን ህልሜ
እግዚያብሔር ነዉ ሁል ጊዜም ሠላሜ
እሱን ነዉ ማደንቀዉ አንድዬን ነዉ ማዉቀዉ
ማንም ጠቢብ የለም እኔ የምናፍቀዉ
ታዲያ ዉብ ነኝ ብልህ እንዳታስጨንቀኝ
ሰዉ ትጠያለሽ አትበል በቅድሚያ ሳታዉቀኝ፣
ላንቺም ነዉ እህቴ የምልሽን ስሚኝ
አመለካከቴም አይደለም ጨለማ
እስኪ አርቂና እንይ እሱ ነዉ መሪያችንማ
ተደምስሶልናል በሞቱ ሞታችን
እንግዲያዉ ለዚህ ነዉ ዓለምን ማላየዉ
ህያዉ ያደረገኝ ፅድቄን የምለየዉ
ፀባዬን ተረዱኝ ሚስጥሩ የገባችሁ
ሚያስገርመኝ የለም ተዉኝ እባካችሁ
20.ተዋህዶአትፈርስም
ድርጅት አይደለም በሰዉ የታነጰ
ፖለቲካም አይደል ዘርን ያጣቀሰ
ሚስጥሩ ፍቅር ነዉ ቃላቶች ማይበቃዉ
እኛን ስለመዉደድ በፍቅር ተስቦ
መስቀል ላይ የወጣዉ
በደም ታንጰናል በማይጠፋ ቀለም
ለኛ ብሎ እርሱ ቢሰቀልም
መሰረቱ እየሱስ ነዉ
ግርግዳዉ ቅዱሳን
ግንቦቹ እኛ ነን የእርሱ ምእመናን
ልንወድቅ አንችልም በእርሱ ፍቅር ጰንተናል
እግዚአብሔርን ይዘን ማንስ ይንደናል
ማሃመዳዊም ሁን ወይም ጆቫዊትነስ
ፕሮቴስታንትም ሁን ወይ ደሞ ካቶሊክ
አለቱን ላታፈርስ የሰዉ ደም አታፍስስ
ምንጩንም ላታደርቅ ከመቅደሱ እራቅ
ካህኑ ቢታረድ መቅደሱ ቢቃጠል
እንበዛለን እንጂ የለም የሚጎድል
ስንሞት እንበዛለን
መከራዉ ሲበዛ በፍቅር እንጰናለን
በእሳት ስንቃጠል እንለመልማለን
ከማይደክም አባት ተፈጥረናልና
አርዮስ አትልፋ እንላለን ቀና
ሰልፉ የእኛ ነዉ ድልም የኛ ብቻ
እንደ አሸዋ የበዛን እስካለም ዳርቻ
ካህኑን ግደሉ መቅደሱን አቃጥሉ
ቅጥሩንም አፍርሱ ልጆቹን በትኑ
እናንተ ስትጠፉ እነሱ ቀና ብለዉ
ባባታቸዉ እቤት ይሰበሰባሉ
ይህ ነዉ ክርስትና የማይጠፋ ቀለም
በፍጱም ማይጨልም ሁሌ ሚሰጥ ብርሃን
እናማ አርዮስ ቁርጥህን እወቀዉ
ድል ላታደርግ እንደዉ ነብስህን አታስጨንቀዉ
ሃሰት እዉነትን እስኪ የቱጋር ነዉ አሸንፎየሚያቀዉ
ባንድነት ተነሱ የእምነትን ሰይፍ ያዙ
በፍቅር ማርኩና የዲያቢሎስን
በእምነታችሁ ናዱ
በእምነት እንሞላ በጱናት እንቁም
በተስፋ እንዉጣ
ጠላት አፍሮ እንዲቀር መድረሻ እንዲያጣ
የጦር እቃችሁን ልበሱ እንደ ካባ
ዘመቻዉን አጵኑት ቅድስት ምድር
አርዮስ ሳይገባ
የጦርሰልፍ አንሻም ቀስት አንወረዉርም
ደም እያፈሰስን እርሱ የፈጠረዉን እኛ አንገድልም
ቀስትና ጦር ይዘን አንወጣም ዘመቻ
ጠጠርም አንለቅምም አሳዳጁን መምቻ
21.ጾምና ኩነኔ
ልቤ በቂም በቀል በተንኮል ተሞልቶ፣
እጄ ሲተባበር መልካም መሥራት ትቶ፣
ጆሮየ ለመስማት ከመረጠች ክፋት፣
የእግሬ ጉዞ ከሆነ ወደ ሃፂያት ፣
አይኔ ሲቅበዘበዝ ክፉውን በማየት ፣
ምላሴም ሳትፀዳ ተዘፍቃ በሀሜት ፣
ከጮማው ቆርጬ፤መጠጡን ጠጥቼ ፣
ቅበላ ነው ብየ አእምሮየን ስቼ ፣
ቅድመ ዝግጅቴ ሆድ ለመሙላት ሆኖ ፣
ማየት ከተሳነኝ ነገር አመዛዝኖ ፣
በንስሀ ሳልነፃ ከነቆሻሻዬ ፣
ፆሙን ለማስገባት ሽር ጉድ ብዬ ፣
ሠዎችን በድዬ ይቅርታ ካልጠየኩ ፣
ተበድየም ቢሆን ምህረትን ካልፈፀምኩ ፣
ተፈቶ ሲፈሰክ መዳን ካላገኘው፣
ጥፋቱ የኔው ነው ፣
መፆሜም ከንቱ ነው ፣
የበደሉኝን ይቅር ሳልል እኔ ፣
አንተ ይቅር በለኝ ብየ ማላዘኔ ፣
አብረውም አይሄዱ ፆምና ኩነኔ ።
22.፨እንካ ሰላምትያ፨
እንካ ሰላምታ?
በምንትያ
በመሰንቆ
ምን አለ በመሰንቆ?
ለሰው ይበጀዋል መኖር በቤቱ ፈጣሪውን አውቆ።
እንካ ሰላምትያ
በምንትያ?
በደውል
ምን አለ በደውል?
መሆን ያስፈልጋል የዋህ እንደ ርግብ ብልህ እንደ እባብ።
እንካ ሰላምትያ
በምንትያ
በከበሮ
ምን አለ በከበሮ?
ዘመንም ህይወትም አብሮ ይቀየራል ከአምና ዘንድሮ።
እንኪ ሰላምትያ
በምንትያ
በጽላት
ምን አለ በጽላት?
ለተዋህዶ እናት ለቅድስቷ ቤት ጠበቃ ሁንላት።
እንካ ሰላምትያ
በምንትያ
በሰረገላ
ምን አለ በሰረገላ?
ፊተኞች ስንባል እንዳንሆን ኋለኛ መትጋት ያስፈልጋል ከእንግዲህ በኃላ።
እንካ ሰላምትያ
በምንትያ
በጧፍ
ምን አለ በጧፍ?
አይዞህ በርታ ተነስ አምላክ ይመራሃል የህይወትህን ሰልፍ።
እንካ ሰላምትያ
በምንትያ
በጉልላት
ምን አለ በጉልላት?
የቅዱሳን ፀሎት ምልጃ በረከት ትልቅ ዋጋ አላት።
እንካ ሰላምትያ
በምንትያ
በሻማ
ምን አለ በሻማ?
ምልጃ በረከቷ ሁሌም አይለየን የሰማእቷ አርሴማ።
ስብሐት ለእግዚአብሔር
ዘመን እንደዋዛ
ሰከንድ ደቂቃውን ደቂቃ ሰዓቱን
እያደገ ሲሄድ ሰይገታ ጉዞውን
በዚህ ሳያበቃ ሰዓት ቀንን ወልዶ
ቀኑም ሳምንት ሲሆን ተሻግሮ ተራምዶ
ሳምንትም በተራው ወራትን ሲተካ
የተቦካው ሲያልቅ ተፈጭቶ ሲቦካ
ወራት ወደ አመታት በአንዴ ሲቀየሩ
እረፋት የለሽ ሰዓት ሲዞር መዝወሩን
እድሜዬ አብሮ ሮጠ አለፈ ዘመኔ
ጆሮዬ እየሰማ እያየኹት በዓይኔ።
ብልጭ ድርግም ስትል ያቺ ፈጣን ሰኮንድ
በእጄ ላይ አስርያት ተቀምጣ በእኔ ክንድ
እኔ ስስቅባት ፍጥነቷን እያየሁ
ምንድን አስቸኮለሽ አጣደፈሽ እያልሁ
ለካስ ምስጢር አላት ዘመን ትቆጥራለች
በእድሜ መቀለዴን ነጋሪ ኖራለች።
እኔ መች ተረዳሁ ምስጢሩ መች ገባኝ
እብድነች እላለሁ ለካስ እብዱ እኔ ነኝ።
ዛሬ ባስታውሰው ያለፈ ዘመኔን
የሰኮንድ ደቂቃ የሰዓት ምስጢሩን
የሳምንት የወራት የዓመታት ድምሩን
ለካ ሄዶብኛል
ዘመን አልቆብኛል
በራሴ ላይ ሆኖ ሞት ይስቅብኛል።
ልጠይቅ እራሴን ምን ሰራሁ በእድሜዬ❔
በኖርኩበት ዘመን በዚህ ቆይታዬ
አንድ ነገር ቀረቶኛል
ጭንቀት ይሰማኛል
ኑሮ እንዴት እንደሆነ ማሰብ ተስኖኛል
የእኔነቴ መሰረት አምላክ ከእኔ ርቋል።
አዎ❕
24.ፅዩን ማርያም
ፅዮን ማርያም አማላጅዋ
ግሩም ድንቅ ነው ከለላዋ
ተነግሮ አያልቅ ጥበቃዋ።
ስሟን ስጠራ ተጨንቄ
ፅዮን ማርያም ስላት አጥብቄ
ሰለምናት ለመንገዴ እንድትሆነኝ ስንቄ ፣
ተናግሬ ሳልጨርስ
ከተፍ አለች እኔኑ ልታድስ።
ልትመራኝ ደግፋ ልትሆነኝ ተስፋ
ልትታደገኝ በይፋ።
ምኞትህ መልካም ነው ልጄ፣
አትጥፋ እንግዲ ከደጄ
ብፅዕት ነሽ በለኝ አሁንም ወዳጄ
አስታርቅሃለሁ አማልጄ፤
እያለች ስታፅናናኝ
ፅዮን ማርያም እመቤቴ
መታወቂያ የእኔነቴ
መንገድ መሪዬ መስታወቴ
የኑሮዬ ትርጉም የልማቴ
የድካም ሁሉ ብርታቴ
ምቹ ማረፊያ የስደቴ።
ርቄ ብሄድ ባህር ማዶ
መቼ ሆነ ቤቴ ማዶ
እንባዬ ታብሶልኝ
ፀሎቴ ተሰምቶልኝ
መውደዴ ተቆጥሮልኝ
ፅዮን ማርያም አብራኝ መጣች
ጣፋጭ ቃሏን እያሰማች
ብፅዕት ነሽ በለኝ እያለች።
* * */ /* * *
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለ መስቀሉ ክቡር።
25.ከዘማዊቷ አንደበት
________________
በሰው እጅ ወድቄ በደካማው ጎኔ
ይገባታል ስባል ሞትና ኩነኔ
በፊትህ ለመቆም ሳይገባኝ ለኔ
ባንተ ፊት አቁመው አይሁድ እንዲህ ሲሉህ
መምህር ስለዚች ሴት አንተ ምን ትላለህ
ስትዘሙት አግኝተን ይዘናት መጥተናል
ሙሴ በኦሪቱ በደንጋይ ተወግራ እንድትሞት አዞናል
ብለው ሲጠይቁህ አይሁድ ሊፈትኑህ
አትወገር ብትል ህጋችን አፍርሷል
ትወገርም ብትል እንዴት ይጨክናል
ለሰው ሞት አያዝንም? የእግዜር ልጅ ነኝ ይላል
ለማለት አስበው ወዳንተ ሲመጡ
በዚህ ከባድ ሐሳብ አንተን መልስ ሊአሳጡ
ከናንተ መካከል ኀጢአት የሌለበት
መጀመሪያ አንስቶ ደንጋይ ይጣልባት
ብለህ ስትናገር ስትፈርድ ስለእውነት
ከአይሁድ መካከል ማን ነበር ካንተ ፊት
ቁሞ የተገኘ ኀጢአትን ያልሠራት
ባንቺ የሚፈርዱት ሰዎች ወዴት አሉ
ብለህ ስጠይቀኝ አወቅሁ እንደሌሉ
አይሁድ ሲዘጋጁ በኔ ላይ ሊፈርዱ
ዘማ ናት እያሉ እኔን ሊያዋርዱ
ቃላቸውን ሰምተህ መጻፍ ስትጀምር ያንዱን ኀጢአት ባንዱ
ትንሹም ትልቁም እየወጡ ሄዱ
አቤቱ ጌታየ እኔ ግን ከንቱ ነኝ
ኀጢአቴን ሰውረህ ከሞት አድነኸኝ
ኢየሱስ የት አለ? ብለው ሲጠይቁኝ
በጣቴ ጠቁሜ ለአይሁድ ያሳየሁኝ
መልካም ውለታህን መመለስ ያልቻልኩኝ
ወርቀ ደምህ ዋጅቶኝ በደምህ ስትገዛኝ
ስለመልካም ሥራህ ክፉ የመለስኩኝ
ከንቱ ነኝ ከንቱ ነኝ የከንቱ ከንቱ ነኝ
የአንተን ውለታ መመለስ ያልቻልኩኝ።
ዮሐ ፰ ፥ ፫
ወስብሐት ለእግዚአብሔር !
26.ማለዳ ይጨልማል
ባስመሳዩ አለም ሳልሰራ ገና
ፍቅር ነበር ያኔ የዛሬ አያርገውና
ለጥቅማ ጥቅም ስል ቀርቤ ነበር ሰው
ያሻኝን አግንቼ አጣጥሜ እስክጥለው
ነበር ትናንት ዛሬ በርቅርቅታው አለም
በአለም ተሸሽጌ የኖርኩት ያለ ሰላም
የአለምን ሃሳብ ስኖረው ሳስበው
ፍቅር የለም ለካ ከጊዜ ወደ ጊዜው
ትናንትና ዛሬ ሰዎችን ስቀርባቸው
ትህትና ነበር ሲያዩ በአይናቸው
አሁን ወዴት አለ ያ የቀድሞ ፍቅር
አለምን አሸንፎ የኖረ በክብር
ወዴት ተሸሸገ የቱ በለጠበት
አለም እንዲህ እኮ ነወ ፍቅር የሌለበት
አሁንስ ታድያ ወዴት እንታደስ
ከከፋው ተምሳሌት ወይስ ቅዱስ መንፈስ
አይበቃም በአለም ሁሉን ነገር አየው
ክፉውንና በጎውን ሁሉን መርምሬያለው
ፍቅር ዋጋ እንዳለው ስላየው ተከቦ
ማለዳው ጨለመ ለሊቱ ተውቦ
የፍቅር ከፍታው ማሰርያው መንግስቱ
መነገዱ ይቅርብኝ በፍቅር መዋሸቱ
እና ፍቅር ማለት ለሚወደኝ ሳይሆን
ለሚጠላኝ ሁሉ መስጠቴ ነው ነብሴን
ስለዚህ ከጥንቱን ፍቅር ለመመለስ
ያለፈውን ረስቼ መመለስ ወደ መቅደስ
እና ከአለም ዳር ቆሜ አይኖቼ እንዳይፈዙ
በአለም ሃጥያት እንዳይመረዙ
ከልብ ከመነጨ ከሃጥያት ተነስቼ
ከማይጠቅመው አለም ካስመሳይ ወጥቼ
ምዕራባዊውን አለም ሁሉንም ረስቼ
ገስግሼ ወደ ቤቱ እጆቼን ዘርግቼ
በአዲሱ መንፈስ ልብሴንም አጥቤ
መቃኘት ነው ዛሬ ፍቅርን ገና አንግቤ
አሁን እንደ አለፈው አይደለሁምና
ያስመሳይ ማንነት ተወግዷልና
አትዩኝ ሰዎች እንደ በቀደሙ
አትሞኛልና በህያው ቅዱስ ስሙ
አትሞኛልና በህያው ቅዱስ ደሙ.አሁን ግን የሱ ነኝ......
ከአምላኬ ርቄ ለስጋ ያደላው
በእራሴ ዛፕያ ጉዞዬን ያቀናው
ፆም ፀሎት ረስቼ አርብ ሮብ ገድፌ
ነብሴን እየጎዳው ለስጋ አጭልፌ
በብልጭልጭ ነገር ስጋ እንዲደለድል
እራሱን በሰጠኝ አንድም ሳያጎድል
እስከ መስቀል ታዞ ገሎ ሞትን በሞት
ልቡን እስከ መቃብር የሰጠኝ ሳይሰስት
እና አሁንስ እኔ ግን የማነኝ
ባጠፋሁት ጥፋት ወጥቼ ከገነት
ሁለት ሞትን ሞቼ መኖሬ በሃጥያት
ፍጠረኝ ሳይለኝ ፈጥሬያለሁ ብሎ
የፍቅር መገለጫ እፀበለስ ተክሎ
በኋለኛውስ ዘመን በመስቀል ተሰቅሎ
ህይወት የተሰጠኝ ስለኔ ተብሎ
ፍቅርን በተግባር ገልጦ ቢያሳየኝ
እኔስ ለመታገስ በእውኑ የተሳነኝ
በእርግጥ እኔ ግን ማነኝ
ራሱን ጥሎ ከከፍታ ወርዶ
ሊያድነኝ ከሰማይ ከድንግል ተወልዶ
ፍቅር መታገስን ቅንነት ተስፋን
በመከራው መስቀል በመስቀሉ ታሞ
በአደባባይ ለኔ ቀራንዮ ላይ ቆሞ
ስጋውና ደሙን ሰቶ ለህይወቴ
ከሲኦል እሳት ያወጣኝ አባቴ
በኔ ፈንታ ስድብ ምራቅ ለተረጨበት
አንዷን እንኳን መክፈል ያልተቻለኝ በእውነት
እረ ንገሩኝ እኔ ከወዴት ነኝ
ልጁ ለኔ ደስታ ጧት ማታ እየተጋ
እሱ ለኔ ስኬት ለከፈለው ዋጋ
ህግና ስርአቱን ሳልፈፅም ቢመጣ
እና ስበድለው ንስሃም ሳልገባ
ይሆናል እንዴ ወደ ቤቴ ግባ
በፍፁም ካልታጠበ አይችልም ሊገባ
ዳግም ላትሸልመኝ ከንቱነትን ምድር
ልመለስ ወሰንኩኝ ከክርስቶስ ፍቅር
27.፨ምነው እመብርሃን፨
አዬ ምነው እመብርሀን
ኢትዮጵያን ጨከንሽባት
ምነው ቀኝሽን እረሳሻት
እስከመቼ ድረስ እንዲህ መቀነትሽን ታጠብቂባት
ልቦናሽን ታዞሪባት
ፈተናዋን ሰቀቀኗን ጣሯን ይበቃል ሳትያት
አላንቺ እኮ ማንም የላት
አውሮፓ እደሁ ትናጋዋን በፋሺስታዊ ነቀርሳ
ታርሳ ተምሳ በስብሳ
ምድራዊ እባጭ ጫንቃዋን እንደ ኮረብታ ተጭኗት
ቀና ብላ እውነት እንዳታይ አንገቷን ቁልቁል ጠምዝዟት
ነፍሷን ድጦ ያስበረከካት ስልጡን ብኩን መፃጉዕ ናት
እና ፈርቼ እንዳልባክን ሲርቀኝ የሀይልሽ ውጋጋን
አንቺ ካጠገቤ አትራቂ በርታ በይኝ እመብርሀን
ቃልኪዳኔን እንዳልረሳት እንዳልዘነጋት ኢትዮጵያን
አዎን ብቻዬን ነኝ ፈራሁ
እሸሸግበት ጥግ አጣሁ
እምፀናበት ልብ አጣሁ
እማማ ኢትዮጵያን መንፈሴ ተፈትቶ እንዳይክዳት ሰጋሁ
አዋጅ የምስራች ብዬ የትብት ምግቤን ገድፌ
ከእናቴ ማህፀን አልፌ በኢትዮጵያ ማህፀን አርፌ
ካፈሯ አጥንቴን ቀፍፌ ደሜን ከደሟ አጠንፍፌ
ከወዟወዟን ቀፍፌ
በህፃን እግሬ ድኬባት በህልም አክናፌ ከንፌ
እረኝነቴን በሰብሏ በምድሯ ላብ አሳልፌ
ከጫጩት እና ከጥጃ ከግልገል ጋር ተቃቅፌ
በጋው የረኛ አደባባይ ክረምት እንደ ወዙ ፍሳሽ
በገጠር የደመና ዳስ በገደል የሸለቆ አዳራሽ
ከቆቅና ከሚዳቋ ከጅግራ ጠረን ስተሻሽ
በወንዝ አፋፍ ሐረግ ዝላይ መወርወር መንጠልጠል ጢሎሽ
ከፍልፈል ጋር እሩጫ ስገጥም ከቀበሮ ድብብቆሽ
ከራዳ ጫፍ ሳር ለግት ላሜ ትንሽ ግጦሽ
ለጥጃዬ የሌት ግርዶሽ
ለጥማድ በሬዎቼ እራት ለማታቸው ጥቂት ድርቆሽ
ለግልገሌ ከአውሬ ከለል እማሳው ስር ጎጆ መትከል
ለፀሐይ የሾላ ጠለል ለዝናብ የገሳ ጠለል
ውሎ የንብ ቀፎ ማሰስ ያበባ እምቡጥ ሲፈነዳ
የግጦሽ ሳር ሲለመልም ሲሰማሩ ሰደድ ሜዳ
አዝመራው ጣል ከምበል ሲል ከብቱ ለሆራ ሲነዳ
ፈረስ ግልቢያ ስሸመጥጥ ከወፎች ዜማ ስቀዳ
ልቤ በንፋስ ተንሳፎ በዋሽንት ዋይታ ሲከዳ
ያቺን ነው ኢትዮጵያ የምላት
እመብርሀን ምነው እረሳሻት
ያቺን የልጅነት ምስራች የህፃንነት ብስራት
የሳቅ የፍንደቃ ዘመን የምኞት የተስፋ ብፅዓት
ያቺን የልጅነት እናት
አዛኝቱ እንዴት ብለሽ ጥርሶችሽን ትነክሺባት
ስሜን በስምሽ ሰይሜ ባገልግሎትሽ ስዋትት
ከዜማ ቤት ቅኔ ቤት ከድጓ ቤት መጻህፍት
ካንቺ ተቆራኝታ እድሌ ካንቺ ተቆራኝታ ነፍሴ
ከቀፈፋ ደጀ ሰላም ከቤተልሄም ቅዳሴ
አኮ... ቀዶ.. ቀፍፎ .... ዳባ ለብሶ
ቅኔ ዘርፎ .....ግስ ገሶ
መቅደስ አጥኖ ማሕሌት ቆሞ
በልብሰ ተክሕኖ አጊጦ በብር አክሊል ተሸልሞ
እመብርሀን ያንቺ ፅላት ነፍሴ ላይ በሳት ታትሞ
የመናኒው የአባ ተድላ ርድ ሆኜ አብሮኝ ታድሞ
ሕይወቴ እምነትሽን ፀንሶ
ስጋ ፈቃዴ ተድሶ
ለሕንፃሽ መዲና ቆሞ ለክብርሽ ድባብ ምሰሶ
ስሜን በስምሽ ሰይሜ ሆነሽኝ የእምነቴ ፋኖስ
ለዋዜማሽ ግሸን ማርያም ለክብርሽ ደብረ ሊባኖስ
ስሮጥ በወንበሩ አኖርሽኝ በአንበሳው በቅዱስ ማርቆስ
ታዲያን ዛሬ ኢትየጵያ ስትወድቅ ከምትሰጪኝ ለፍርሃት ጦስ
ምነው በእረኝነት እድሜ አይኔን በጓጎጣት የሎስ
የጋኔል ጥምብ አንሳ ከንፎ ወርዶ በጨለማ በርኖስ
እባክሽ እመብርሀን ይብቃሽ እባክሽ ስለ ፍቅሩ ወልዳ
ፅናት ስጪኝ እንድካፈል የእናቴን የኢትዮጵያን ፍዳ
ከነከሳት መርዝ እንድቀምስ ከነደደችበት እቶን
የእሷን ሞት እኔ እንድሞታት ገላዋ ገላዬ እንዲሆን
አዎን ብቻዬን ነኝ ፈራሁ
እምፀናበት ልብ አጣሁ
እሸሸግበት ጥግ አጣሁ
ህፃን ሆኜ የርግብ ጫጩት
አንዳንዴ ራብ ሲያዳክማት
ችጋር ከጎጆዋ ገፍቶ እዛፉ ግርጌ ሲጥላት
እናቷ በርራ ደርሳላት
በአክናፏ ሙቀት ታቅፋት
እፍ እያለች ግንባሯ ላይ ሕይወት ስተነፍስባት
ወዲያው ነፍስ ትዘራለች
ችር.... ብር.... ትር.... እያለች
እባክሽ
28.ወደ ማምሻው
አጭር ግጥማዊ ጭውውት
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ተራኪ .......እገሌ... አንድ ቀን ጠላቴ እንዲ ሲል መጣና
በጓደኞቼ ልብ ከንቱነት ዘራና
አንድቀን በማታ ጓዴዎች ጠሩኝና
እንዲ ሲሉ ነገሩኝ በውስጣቸው አደባና
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ተዋናይ........እገሌ... ለምን አንሰራም የግል ስራችን
ራቅ ያለ ስፍራ እኛ ወጣ ብለን
ለምን የቢዝነሱን ስራ አንሰራም
አንተ ከቤተሰብ ተማከር በሰላም
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ተራኪ......እገሌ...ብለው ተለያየን እኔም ቤት ገባሁና
ቤተሰብ ባለበት ሃሳቤን ዘራሁና
የድርሻዬን ስጡኝ አልኩ ኮራ አልኩና
አባቴ በሃሳቤ እጅግ አዘነና
በትረካው መኋል አባት ድምፁን ዘግቶ ይመክረዋል
ቢለኝ ቢገስፀኝ አልሰማ አልኩኝና
ንብረት ተካፈልኩኝ ወርቄን ሰበርኩና
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ተራኪ.....እገሌ...ጓደኞቼም መተው በጠዋት በማለዳ
እንገስግስ አሉኝ ወደ ሃጥያቱ ጓዳ
በመኋል ጓደኞቹ እያቻኮሉ ይወስዱታል
እኔም ተከትዬ ብዙ በራኩ ጊዜ
ብሬ ከእጄ አለቀ ወደኩኝ በትካዜ
ጓደኞቼም ሸሽተው ከዳር ተበትነው
እኔ ሜዳ ቀረው እንደ መናኝ ሰው
ቀን በቀን ሲጨምር ርሃብና ጥሜ
አይዞህ ሚለኝ ጠፍቶ የሚቆም ለህመሜ
ባጣ ቢቸግረኝ ለስራ ዘምቼ
ሰርቼ አልሆን ሲለኝ ሳድር ተደፍቼ
ወደ አጨዳ ማሳ ዋናውን ለመቃረም
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ተዋናይበመኋል ማጭድ ይዞ ሲያጭድ ባለቤቱ ያባሯል በዝግታ ድምፅ
ስሰራ ሳበላሽ ስገፋ ከአለም
ወደ አንድም ስፍራ አመራና እግሬ
ልጠራርግ ገባው የአሳማ ፍርፋሬ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ተዋናይ ሰውየውም እየተሳደበ እየመታው ያባሯል
የቤቱም አለቃ እያጉረጠረጠ
ገፍቶ አባረረኝ እየረጋገጠ
አሁንስ ሲከብደኝ ኑሮ ሲዛባብኝ
የሰበርኩት ወርቅ ከልቤ ተሰማ
በመኀል ልጄ ተመለስ የሚል ድምፅ ይሰማል
ያኔ ባባቴ ቤት እጅግ ተትረፍርፎ
እበላ እኖር ነበር ሁሉ ነገር ተርፎ
አሁን ወደ አባቴ እንደ ገና አቅንቼ
እንደ ልጅህ ሳይሆን ከጉያህ ተደፍቼ
ከባርያዎችህ አንዱ አድርገኝ ብዬው
ከእግሩ ተደፍቼ እለምነዋለሁ
ብዬ ገሰገስኩኝ ከቀድሞዋ ሃገሬ
ግን እሺ ይለኝ ይሆን እያልኩ ከመንደሬ
አባቴም አይቶኝ ከሩቅ ሳለው ገና
እንባው ከአይኖቹ ዱብዱብ አለና
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ተዋናይ ሲናገር
ወዮ ልጄ እያለ እያቀና
የቀደው ልጄ ጠፍቶ የነበረው
ከኔ ተለይቶ ሞቶ የነበረው
ተራኪ........እገሌ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
እያለ አባቴ በደስታ እያነባ
ከእቅፉ ወሰደኝ ከፍቅሩ እያስገባ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ተዋናዩ አባት ሲናገር
አባቴም አለ ልጄ አሁን መቷል
የጠፋው የሞተው በዳግም ተነስቷል
ንፁሁን በግ አምጡ ፍሪዳው እረዱ
መንገደኛው ሁሉ ጥሩ ከመንገዱ
አባት ሲል ሲናገር ወንድም ከች ሲል
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ተዋናይ ወንድምየው ሲናገር
ይሁሉ ምንድነው ብሎ ሂሳብ ሲስል
ከባርያዎቹ አንዱ ወንድምህ መቶ ነው
አንተም ከደስታው ተቀላቀል ቢለው
ወንድም ልቡ ጠቁሮ ፊቱ እየሳቀ
በንዴት ተጠምዶ አንዴ እየተደነ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ተዋናይ ወንድሙ ሲናገር
ከደስታው ማብቂያ ወንድሙን ጠራና
ለምን ተመልሰህ መጣህ እንደገና
ቢለው ቢጠይቀው መረር አለውና
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ተዋናይ የጠፋው ልጅ ሲናገር
ወንድም መለሰ ቀስ ብሎ እያፅናና
አለምን እንዳያት እግዚአብሔር ላከኝ
ሁሉንም አየሁት ጉዳት ብቻ ታየኝ
ከጎጂው በስተቀር ጥቅሙ ስላልታየኝ
ዳግም እንድመለስ እግዚአብሔር ጠራኝ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ተዋናይ ወንድሙ ሲናገር
ወንድሙ ተደንቆ ልቡ ፊቱ ስቆ
ይቅርታ ጠየቀው ከእግሩ ስር ወድቆ።
--ተፈፀመ--
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
፨ማን ነው አትበሉኝ፨
"ጠበቃ" የሚለውን ቃል ወስዶ "ስለ እኛ ይከራከራል ያማልዳል" ማለት ስህተት ነው፡፡ አምላክን ሊከራከረው የሚችል ማን
አለ?? ይህ ንግግር አምላክነት ካለመረዳት የመነጨ የዘመኑ የግኖስቲክ እርሾ ነው፡፡
ዘወትር ስለሐጢአት እኛን የሚከስ ጠላት ዲያብሎስ የሚያሳፍር ነውና "ጠበቃ" ብሎታል፡፡ እንጂ ስለ እኛ ይከራከራል ማለትስ
አይደለም፡፡ በራዕ 12፡10-11 ላይም "ቀንና ሌሊትም በአምላካችን ፊት የሚከሳቸው የወንድሞቻችን ከሳሽ ዲያብሎስ
ተጥሎአልና ከበጉም ደም የተነሳ ከምስክራቸውም ቃል የተነሳ ድል ነሱት" በዚህም ክፍል ላይ "ዲያብሎስን ከበጉ ደም የተነሳ
ድል ነሱት" ይላል። የክርስቶስ ስጋ እና ደምን በመቀበል ሃጢአታችን ይነፃል። ዲያብሎስንም ድል
እንነሳለን። ይህን ከማስረዳት ውጪ አማናዊውን ትርጉም ባለመረዳት ኢየሱስ ክርስቶሰን "አማላጅ" ማለት ፍፁም ስህተት
ነው፡፡
በመቀጠልም ጠበቃና አማላጅ ያላቸውን ልዩነት እንመልከት
- ማለት ለተከሳሽ የሚከራከር ተከሳሽን ነፃ በማውጣት ከሳሽን የሚያሳፍር ነው፡፡
፡- ማለት በአንድ በከበረ ሰው ፊት አሊያም በእግዚአብሔር ፊት አንድን ሰው ወክሎ ይቅርታ የሚጠይቅ ወይም የሚለምን
ሲሆን በራሱ ምንም ማድረግ የማይችል ከመሆኑም በተጨማሪ የበዳዩን በደል ማለትም የአጥፊውን ጥፋት በመግለጽ በድሏል
እና ይቅር በለው ብሎ የሚለምን(የሚማጸን) ማለት ነው፡፡ በአጠቃላይ አማላጅ ኃጢያትን ገልፆ ይቅርታን የሚለምን ነው፡፡
በዚህ መሰረት የቃሉን ሀሳብ ስንመለከት ቅዱስ ዮሐንስ በመልዕክቱ ላይ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቹን ኃጢያት እንዳያደርጉ
እንዲህ ሲል ይጽፍላቸዋል ቁጥር 1 ላይ ልጆቼ ሆይ ኃጢያትን እንዳታደርጉ ይህንን እጽፍላችኋለሁ ይልና ቁጥር 2 ላይ
ከስጋቸው ድካም የተነሳ ሳያውቁ በስህተት እያወቁ በድፍረት ኃጢያትን ቢያደርጉ ከአብ ዘንድ ጠበቃ አለን በማለት የአብ
የባህሪ ልጅ የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ ጠበቃችን ነው ይላቸዋል፡፡
ምክንያቱም ሰው ኃጢያትን በሰራ ጊዜ በእግዚአብሔር ፊት የሚከስ ከሳሽ አለ እርሱም ሰይጣን ዲያቢሎስ ሰዎችን
በእግዚአብሔር ፊት እንደሚከስ ትን.ዘካ.3፡1-5 ላይ እንዲህ ተብሎ ተጽፏል፡- ታላቁም ካህን ኢያሱን በእግዚአብሔር መልአክ
ፊት ቆሞ አሳየኝ ሰይጣን ይከሰው ዘንድ በስተቀኙ ቆሞ ነበር፡፡ እግዚአብሔርም ሰይጣንን ሰይጣን ሆይ ኢየሩሳሌምን የመረጠ
እግዚአብሔር ይገስጽህ በውኑ ይህ ከእሳት ትንታግ አይደለም አለው፡፡ ኢያሱም እድፋም ልብስ ለብሶ በመልአኩ ፊት ቆሞ
ነበር እርሱም መልሶ በፊቱ የቆሙትን እድፋሙን ልብስ ከእርሱ ላይ አውልቁ አላቸው እርሱንም እነሆ አበሳህን ከአንተ
አርቄያለሁ ጥሩ ልብስን አለብስሀለሁ አለው ደግሞ ንጹህ ጥምጥም በራሱ ላይ አድርጉ አለ እነርሱም በራሱ ላይ ንጹህ
ጥምጥም አደረጉ ልብስንም አለበሱት የእግዚአብሔርም መልአክ በአጠገቡ ቆሞ ነበር፡፡
በዚህ ታሪክ ላይ እንደተመለከትነው እግዚአብሔር ለኢያሱ አማላጅ ሆነለት ወይስ ጠበቃ ሆነለት ብለን ብንጠይቅ? አማላጅ
አልሆነለትም ምክንያቱም ኃጢያቱን በመግለጽ ሲለምን አልታየምና ነገር ግን ሆኖለታል፡፡ ምክንያቱም ከሳሹን(ሰይጣንን)
አሳፍሮለታልና ነው፡፡ እንዲሁም ዳኛ(ፈራጅ) ሆኖለታል ማለት ነው እንጂ አማልዶታል ማለት አይደለም ምክንያቱም
የሀጥያትን ስርየት እራሱ ሰጥቶናልና።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር አሜን።።
ጥያቄ፡
ስለቅዱሳት ሥዕላት ክብርና በሥዕላቱ ፊት ስለመጸለይ ከቅዱሳኑ ሕይወት ተሞክሮ አንጻር ብታሥረዱን?
መልስ፡
ቅዱሳን አባቶቻችን በቅዱሳን ሥዕላት ዙሪያ በስፋት አስተምረዋል። በተለይም በሥምንተኛው መ/ክ/ዘ/ አካባቢ ከጸረ ሥዕለ
ቅዱሳት የተጋደሉት ተጋድሎ የማይረሳና ዛሬ ላለነው ትውልድ ለትምህርት የምንጠቅሰው መጽሐፋችን ነው። አሁን ላይ
በቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ ለአምልኮ ሥርዓት የምንጠቀምባቸው የቅዱሳን ሥዕላት የእነርሱ የተጋድሎ ውጤቶች ናቸውና፡፡
በተለያዩ የአባቶቻችን ድርሳናት ውስጥ ተመዝግበው እንደሚገኘው ቀደምት አበውና እማት በቅዱሳን ሥዕል ፊት ሻማ
በማብራት በጎ በጎ መዓዛ የሚሸት ሽቶን በመቀባት የተለየ ስፍራ:(ቦታ) በማስቀመጥ መጋረጃ በመጋረድ በፊታቸው ጸሎትና
ስግደትን በማቅረብ ለሥዕላቱ ክብር እንደሚሰጡ እናገኛለን። ከነዚህም መሐከል ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ነው። ቡሩክ የሚሆ
ን ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የሐዋርያውን የቅዱስ ጳውሎስን መልእክታት ከመጠን በላይ ይወድ ነበር። የሐዋርያውን ሥዕልም
በሚገባ ቦታ አስቀምጦት ነበርና መልእክታቱን በሚያነብበት ወቅት ሥዕሉን በፊቱ አድርጎና ሐዋርያው አጠገቡ በአካል
እንደተገኘ በማድረግ ይናገር እርሱንም ያመሰግነውና ሐሳቡንም በሙሉ ወደ እርሱ ያደርግ ነበር።ከመምህራችን ከቅዱስ
ዮሐንስ አፈወርቅ አድራጎት እንደተረዳነው የስእሉ ባለቤት ቅዱስ ጳውሎስ በአካል አጠገቡ እንዳለ ሆኖ ያነጋግረውና በፊቱም
የጸሎት ሐሳቡን ይናገር ነበር። እኛም ለቅዱሳኑ ሥዕላት የሚገባውን ክብር ከመስጠት ጋር በዚሁ መንገድ በፊታቸው
ጸሎታችንን ልናቀርብ ይገባል። በመቀጠልም ማር ቅዱስ ዮሐንስ ስለ ሥዕላቱም ክብር ሲገልጽ "የቤተመንግስቱን ልብስ
ብትንቅ ንጉሱን መናቅህ አይደለምን?የንጉሱን ሥዕል መናቅ ንጉሡን መናቅ መሆኑን አትመለከትምን??አንድ ሰው ከእንጨት
ለተሰራ ሥዕል ወይም ከብረት ለተቀረጸው የንጉሡ ሐውልት ንቀት ቢያሳይ ሰውየው የሚዳኘው ሕይወት ለሌለው ቁስ ንቀት
እንደአሳየ ሳይሆን ለንጉሡ ንቀት እንዳሳየ መሆኑን አታውቁምን?? ለንጉሡ ሥዕል የሚቀርብ ማንኛውም ንቀትና ማዋረድ
ለንጉሡ የሚቀርብ ንቀትና ማዋረድ ነው።"" በማለት ለቅዱሳኑ ሥዕላት ክብር መስጠት እንደሚገባ በምድራዊ የንጉሥ ሥዕል
ክብር ምሳሌ በማድረግ አስረድቷል። እኛስ የምድራዊው ንጉሥ ሥዕል ይህንን ያህል ክብርና መፈራት ከተደረገለት ለቅዱሳኑ
አምላክና ለቅዱሳኑ ሥዕል ያለን አክብሮት ምን ያህል ይሆን??ደግመኛም በ 8 ኛው መ.ክ.ዘ. በምሥራቅ አብያተ ክርስቲያናት
ብዙ ክርስቲያኖች የቅዱሳት ሥዕላትን ክብር ለማስጠበቅ መስዋዕትነት የከፈሉ ሲሆን ይህንን የቅዱስ ዮሐንስን ምስክርነት
በደንብ የሚያንጸባርቅ ታሪክ ተከስቷል። ይኸውም:-ከዕለታት በአንድ ቀን በኒቆሜዲያ የሚኖር አንድ ቀናኢ መነኩሴ ቅዱሳት
ሥዕላትን አስመልክቶ ከንጉሡ ፊት ተጠርቶ በቀረበ ጊዜ የሰጠውን አስገራሚ ምላሽ ነው። ይኸውም:- ንጉሡ መነኩሴውን
በቁጣ ቃል ""አንተ ሰነፍ መነኩሴ!!እነሆ ማንኛውም ሰው በክርስቶስ ሥዕል ላይ መረማመድ እንደሚችልና በዚህም ክርስቶስን
ከማክበር እንደማይወጣ አትመለከትምን??አለው። መነኩሴውም ወዲያውኑ የንጉሡ ምሥል ያለበትን ሳንቲም በቤተ
መንግስቱ ወለል ላይ ወርውውሮ ""በዚህ አይነት እኔም አንተን ከማክበር ሳልወጣ በአንተ የፊት ምሥል ላይ መመላለስ
ይፈቀድልኛል ማለት ነዋ!!"" ሲል መለሰለት። በዚያን ጊዜ የንጉሡ ባለሟሎች ፈጥነው መነኩሴውን ከድርጊቱ ከለከሉትና
የንጉሡን ሥዕል በድፍረት ሥላቃለለ በሞት እንዲቀጣ አድርገውታል። ይህ ታሪክ የሚስተምረን የንጉሡ ድርጊት የአስመሳይ
ክርስቲያኖች ምሣሌነትን ይዞ ነው። ብዙ ጊዜ እንደንጉሡ በአንደበታችን ክርስ ቶስን እንደምናከብረው እንናገርና ምግባራችን
ግን ሌላ ይሆናል። ንጉሡ ለክርስቶስ ሥዕል ክብር ከመስጠት ይልቅ ለራሱ ሥዕል ክብር ተጨንቆ ትክክለኛውንና ቀናኢውን
መነኩሴ በሞት አስቀጣው። ስንቶቻችን እንሆን ለራሳችን ጥቅም ብለን ወንድሞቻችንን ጉዳት ላይ የምንጥል?? በአንጻሩም
ደግሞ እንደ መነኩሴው የንጉሥን አሥፈሪ ግርማ ሳያስደነግጠን እውነትን በመመስከር የሃይማኖታችንን ጽናት የምናሳይ
ስንቶቻችን እንሆ?? አንግዲህ የምንፍቅናው ግርማ ሳያስፈራን በጽናት ስለ ቅዱሳት ሥዕላት የአባቶቻችንን አሥተምህሮ
ሳናፋልስ መመስከር ከኛ ከዘመኑ ትውልድ ይጠበቃል። ቅዱሳን አበውም አክብረው እንዳቆዩልን እኛም በሥላቱ ፊት ቆመን
ልንጸልይና ልንሰግድ ያስፈልጋል። በዚህም ከሥዕሉ ባለቤት በረከትና ረድኤት እናገኛለን። ይህንን በማድረጋቸው ብዙሀኑ
ተጠቅመዋልና። በቅዱስ መርቆሪዎስ ገድል እንደ ተገለጸው:- ዓላዊው ንጉሥ ኡልያኖስ ወንድማማቾቹን ባስሌዎስንና
ጎርጎርዮስን ሊገላቸው በሚያሳድዳቸው ወቅት የመርቆሪዮስ አምላክ ከንጉሡ ቁጣ እንዲሰውራቸው በሥዕለ መርቆሪዎስ
ፊት ተደፍተው ቢማጸኑ ሥዕሉ በተአምራት መንገድ ሄዶ ኡልያኖስን ገደለው።" ኡልያኖስን ገደልኩት"" ሲል በሥዕሉ ላይ
የደም ምልክት አሳያቸው። "ገደልከውን??" ሲሉትም ሥዕሉ ከአንገቱ ዘንበል ብሎ "አዎን" እንደማለት አመልክቷቸዋል።
በእውነት:በቅዱሳኑ:ሥዕል:ፊት:ሆነን:በፍጹም:እምነትና:በቅንነት:ብንማጸናቸው:በአጸደ:ሥጋና በአጸ
ደ:ነፍስ:መሀከል:ያለውን:ጥብቅ:ግንኙነትና:አገልግሎት:በግልጽ:የ,ምናይበት:ሌላኛው:ማስረጃ:ነው።ይህም:ከላ:ያየነው:ታሪክ:ከ
ዚህ:ውጭ:ሌላ:ምን:የሚነግረን:ነገር:አለና??
======================በተጨማሪም:በዚሁ:በሀገራችንና:በዘመናችን:የሰማዕቱ:የቅዱስ:መርቆሪዎስ:ሥዕል:ዓመታ
ዊ:ክብረ:በዓሉ:በሚከበርበት:እለት(በህዳር:-25 እና ሐምሌ 25)
ካህናቱ:ሲያሸበሽቡ:አብሮ:ይንቀሳቀሳል።ይህንን:ተአምር:ለማመን:የሚከብደው:ሰው:ካለ:ደግሞ:ቦታው:ድረስ:በመሄድ:ማረጋገ
ጥ:ይችላል።(ቦተው:በሰሜን:ሸዋ:ደብረ:ሲና:ወረዳ:ጋሹ:አንባ:ቅዱስ መርቆሪ ዮስ:ከሚባል:ቤተ ክርስቲያን:ከቅኔ ማህሌት:ፊት
ለፊት:የሚገኝ:ሥዕል ነው።)) ሲጠቃለል:-የቅዱሳንን:ሥ ዕል:ማክበርና በፊታቸው:ቆሞ:መ
ጸለይንና:ከባለ:ሥዕሉ:በረከት:ረድኤትን:ማግኘት:የተማርነው:ከቅዱሳን:አባቶቻችን:እንደሆነ:እንረዳል።==============
==========ወስብሐት:ለእግዚአብሔር=====ወለወላዲቱ:ድንግል========ወለመስቀሉ:ክቡር:አሜን!!!
ጾመ ፍልሰታ
በዓለ መስቀል
የመስቀል በዓል የሚከበረው መስከረም ፲፯ (17) ነው። ይህም በዓል በክርስትያኑዓለም ሁሉ ይከበራል።
ታሪኩም ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ተሰቅሎሙቶ ከተነሳ በኋላ
ህሙማን መስቀሉን እየዳሰሱ በመስቀሉ እየታሹ ይፈወሱ ነበር። በዚህም ተአምራት እየተሳቡ ብዙዎች ክርስትያን ሆኑ። ይህ
ን ያዩም አይሁድ መስቀሉን ባንድ ቆሻሻ መድፊያ ቦታ ጣሉት። ከጊዜ ብዛትም ያ ቦታ እንደ ጉብታ ሆኖ ምስቀሉ ውስጥ ተደበ
ቀ። በጊዜው ምንም እንኳን ክርስትያኖች መስቀሉን ማውጣት ባይችሉም ቦታውን ለይተው ያውቁት ነበር። በኋላ ግን በጥጦ
ስ ወረራ ክርስትያኖች ኢየሩሳሌምን ጨርሰው ለቀው ስለወጡና የከተማዋም መልክ ፈፅሞ ስለተለወጠ መስቀሉ የተደፈነበት
ቦታ ወዴት እንድሆነ ለማወቅ አልተቻለም። በዚህም ምክንያት ከ 300 አመታት በላይ ተዳፍኖ ቆይቷል።
ማንም "እኔ ድሀ ነኝ መመጽወት አይቻለኝም አይበል፡፡" ባለጸጎች ለቤተ መቅደስ እንደሚሰጡት ልታደርግ ባትችል ድሀዋ
መበለት እንደሰጠችው ሁለት ናስ ብትሆን እንኳ ስጥ፡፡ ሁለቱ ናስ እንኳ ባይኖርህ ለታመመው በማዘን በህመሙ ጊዜም እርሱን
በማገልገል ምፅዋት አድርግ፡፡ ይህንንም ማድረግ ባይቻልህ የወደቀው ወንድምህን አጽናናው፡፡ "መልካም ቃል ከስጥታዎች ሁሉ
ይበልጣልና፡፡"
አባ ዶሮቴዎስ
ቅዱስ ጳውሎስም "በጎ ፈቃድ ቢኖር እንዳለው መጠን የተወደደ ይሆናል እንጂ እንደሌለው መጠን አይደለም፡፡" 2 ኛ ቆሮ.
8:12 እንዳለ ለመመጽወት ባለጸጋ መሆንን ሳንጠብቅ ያለችንን ከዕለት ምግባችን፣ ከሻይ ሳንቲም ቀንሰን ለድሆች ብንሰጥ
በእግዚአብሔር ዘንድ የተወደደ ይሆንልናል!
✞ በመጨረሻም...አንድ ባህታዊ ወደ አባ ቴዎዶር ዘንድ ሄዶ "የመኖርን አላማ ጠንቅቄ አውቃለሁ፡፡ እግዚአብሔር ሰውን
የሚያዘውን እርሱን ለማገልገል ምርጡን መንገድም አውቃለሁ፡፡ ነገር ግን ጌታዬን ለማገልገል ማድረግ የሚገባኝን ለማድረግ
እየተቻለኝ አይደለም በማለት ይነግራቸዋል፡፡
አባ ቴዎዶርም በዝምታ ከቆዩ በኋላ "ከባህሩ ማዶ ከተማ እንዳለ ታውቃለህ፡፡ ነገር ግን መርከብ የለህም እቃዎችህን
አልጫንክም፣ ባህሩንም አልተሻገርክም፡፡ ከተማው ምን እንደሚመስል በከተማዎቹ ጎዳና ስለ መዘዋወር ማውራቱ ምን
ይረባል?" በማለት መለሰለት፡፡✝
እኛም_ስለ_ምጽዋት_በቃልም_በጽሁፍም_ብንሰማ_እግዚአብሔርን_ደስ_የሚያሰኘውን_ነገር_ብናውቅ_በስራ_ካልገለጥ_
ግን_በዜሮ_ማባዛት_ይሆንብናል፡፡ እግዚአብሔር ይርዳን!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር!
በወንድም ተክለ ማርያም.
የዚቅ ድርሰት የሚወጣው ለአንድ ቅዱስ ከተደረሰው መልክእ ነው። ከመልክኡም ከወቅቱ የሚስማማውና አመቺ የሆነው
ይመረጣል። በመቀጠልም ከመልክኡ ጋር የሚሄድ ጥቅስ ከመጽሐፍ ቅዱስ ወይ ከሌላ ሊቃውንት መጽሐፍ ተፈልጎ ዚቁ
ይደረሳል፡፡ በዚህ መሠረት ከላይ ያለ የዚቅ ድርሰት የወጣው በቅዱስ መርቆሬዎስ መልክእ ለዝክረ ስምከ ከሚለው ላይ ነው።
ንባቡም እንዲህ ይላል። "የኢየሱስ አገልጋይ ማለት ለሆነው ስም አጠራርህና ጥቁር ጸጉርህ ሰላም እላለሁ። ኃይልና ተአምር
የምትሰራ ሰማዕት መርቆሬዎስ ለዮሐንስ በምድረ በዳ የድኅነትን ጎዳና እንደመራኸው እኔም ልጅህን የእውነትና የይቅርታ
ጎዳና ምራኝ።" ቀጥሎም ከመልክኡ "ምራኝ" የሚለውን ይዞ ከመዝሙረ ዳዊት "ይምሩኝ ይውሰዱኝ" የሚለውን
ቀጠለ።(መዝ 43፥3) ሌሎቹም ከዚሁ ከዳዊት መዝሙር ተያይዘው የመጡ ናቸው። (ዘፍ 1÷9 : 19) ( መዝ 64÷1-2)
ተአምር አይደለም ሰማይንና ምድርን አስጊጦ መፍጠር ይቅርና ማንኛውም በጎ ተአምራት ሁሉ ከእግዚአብሔር ነው፡፡ ነገር
ግን አንዳንዱ ቀጥታ በአምላካችን ሲገለጽ ሌሎቹ ደግሞ በቅዱሳኑ ይገልጣል። ለምሳሌ፡ ሙሴ ባህረ ኤርትራን በበትሩ ለሁለት
ከፈለ ሲባል ይህን ያደረገው እግዚአብሔር መሆኑ ይታወቃል ግን ይህን ተአምር በሊቀ ነቢያት ሙሴ እንዲነገር አድርጓል።
ምክንያቱ ደግሞ እግዚአብሔር ወዳጆቹ ቅዱሳን እንዲመሰገኑ ክብር እንዲያገኙ ስለሚፈልግ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ
እግዚአብሔር ለምን በሙሴ አደረገው? ካልን ምላሹ ሙሴ በቅድስና የሚኖር መሪ ስለነበረ ነው። ከዚህም በተጨማሪ ያዕቆብ
በፍኖተ ሎዛ በሌሊት ካልባረከኝ አለቅህም ብሎ ከእግዚአብሔር እንደታገለ ቢገለጽም ነቢዩ ሆሴዕ ግን "ያዕቆብ በጎልማሳነቱ
ጊዜ ከአምላክ ጋር ታገለ ጋር ታግሎ አሸነፈ" (ሆሴ 2፡4) ብሏል። የእግዚአብሔር ለመልአኩ የሰጠው መላእክት ሁልጊዜ
ከአምላካችን እንደማይለዩ ለመግለጽ ስለተፈለገ ነው።
ፈቃዱንና ነገሮችን ሁሉ ለእግዚአብሔር የሚያስገዛ ለራሱ ሕያው አይደለም። ራሱን ክዷልና ከዚያ ጊዜ ጀምሮ በእርሱ
የሚኖረው እግዚአብሔር ነው። ቅዱስ ጳውሎስም "ከክርስቶስ ጋር ተሰቅዬአለሁ፤ እኔም አሁን ሕያው ሆኜ አልኖርም
ክርስቶስ ግን በእኔ ይኖራል" (ገላ 2:20) ያለውን ይህን ሲያመለክት ነው። አውግስጢኖስ በቀደመ ሕይወቱ የምታውቀው ዘማ
ሴት ወደ በአቱ በመምጣት በሩን ታንኳኳለች። እርሱም "አውግስጢኖስ ሞቷል!" ብሎ መለሰላት። ሴቲቱም "ይህ
የአውግስጢኖስ ድምጽ ነው እኮ" ብትለው "አውግስጢኖስ ሞቷል አሁን የሚያናግርሽ ክርስቶስ ነው" ብሏታል። ይህንንም
ያለበት ምክንያት እርሱ የበቃ ስለነበረና እርሱ ለዚህ ዓለም ሞቶ በእርሱ ክርስቶስ ይኖር ስለነበር ነው።ከዚህ የምንረዳው
ቅዱሳን የክርስቶስ መገለጫ መሆናቸውን ነው፡፡ ስለዚህ መገለጫው የሆኑትን ቅዱሳንን ማመስገን እግዚአብሔርን ማመስገን
ነው። ልበ አምላክ ዳዊትም ይህን በመረዳት በመዝሙሩ "አእምሩ ከመ ተሰብሐ እግዚአብሔር በጻድቁ--- እግዚአብሔር
በጻድቁ እንደ ተገለጠ (ተመሰገነ) እወቁ" (መዝ 4:3፤) ያለው፡፡ስለዚህ ወደ መነሻ ጥያቄው ስንመለስ በድርሰቱ ላይ ያሉት
ምስጋና ቅዱስ መርቆሬዎስ ያደረጋቸው ሳይሆን በእርሱ በኩል እግዚአብሔርን ለማመስገን የታሰበ ነው። ምክንያቱ ደግም
ቅዱስ ዳዊት እንደገለጸልን እግዚአብሔር በወዳጆቹ በቅዱሳን በኩል እንዲመሰገን ፈቃዱ ነውና። በመቀጠልም ወቅቱ የአበባ
ጊዜ በመሆኑ ምድርን በአበባ ያስጌጥክ የሚለውን ምስጋና ደራሲው መርጦታል።
በአጠቃላይ ስንመለከተው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በውስጧ ያሉት የምሥጋናም ሆኖ ሌሎች ሥርዓቶች የእግዚአብሔርን
ክብር የሚሻሙ ሳይሆን እግዚአብሔርን በልዩ ልዩ መልክ ማመስገኛ ዘዴዎች መሆናቸውን ተገንዝበን እኛም ከምስጋናው
ተሳታፊዎች ልንሆን ይገባል።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር!
የማርያም መንገድ
ከሥራ እንደተመለስኩኝ ... የሰፈራችንን ሜዳ አቋርጬ በቀጥታ ወደቤት ነበር የምሄደው ውሎዬን ሳወጣና ሳወርድ ስለነበር
በሀሳብ ተውጫለሁ ድንገት ሳላስበው ከሚጫወቱት ልጆች አንዱ ገጨኝና ሚዛኔን አሳተኝ ልቆጣው ይሁን ለምን እንደሆነ
ባላውቅም ተከተልኩት ጥቂት ሮጦ መሬት ላይ በተከበበ መስመር ውስጥ ገባና “እቤቴ . . . እቤቴ . . .” አለ። ቀጥሎም ትንሽ
እንደ ማሰብ አለና “’የማርያም መንገድ’ . . . ‘የማርያም መንገድ’ . . . ስጡኝ” አለ። ጥቂት መንገድ ከፈቱለት በዚያች መንገድ
አምልጦ ወጣ… በማርያም መንገድ አምልጦ ታስረው የነበሩ የቡድን አጋሮቹን አስፈታ በልጁ ቅልጥፍና ይሁን በጨዋታው
ተስቤ ንዴቴን ረሳሁት ትንሽ አለፍ ብለው ሦስት ህፃናት ሴቶች መሬት ላይ አስምረው የሰኞ፣ የማክሰኞ ቤት ብለው
በሰየሟቸው ቤቶች ላይ በእነርሱ አጠራር ከምች እየወረወረሩ ይጫወታሉ።
በጨዋታው ሕግ የተገዛ ወይም የተወረሰ ቤትን መደገፍ መርገጥም አይቻልም አንድ ነገር ካልተባለ በቀር . . . . ‘ማርያም
ብታነሳኝ’. . . ቤት የተገዛባት ወይም የተወረሰባት ልጅ ቀድማ ‘ማርያም ብታነሳኝ’ አለች።
ተፈቀደላት ተደግፋ ከምቿን አነሳች ቀድማ ቤት ቢገዛባትም ብዙ በመግዛት ወይም በመውረስ ጨዋታውን አሸነፈች፡፡ህፃን
ሁኜ ተጫውቼ ያሳለፍኩት ዛሬ ግን እንደ አዲስ የተረዳሁት ጨዋታ ልቤን ነካኝ ወደ ልጅነት ዘመኔ ተመልሼ የቻልኩትን ያህል
ስለ እመቤቴ ቅድስት ድንግል ማርያም ማስታወስ ሞከርኩ፡፡ ከነፍሳት በተለየ መልኩ ‘የማርያም ፈረስ’፣ ቀስተ
ደመናው-‘የማርያም መቀነት’፣ በሰውነት ላይ የታየች ጥቁር ነጥብ- ‘ማርያም የሳመችኝ’፣ማንም ሰው ሳይጠራን ስማችን
የተጠራ በሚመስለን ጊዜ ‘የማርያም ብቅልእየፈጨሁ ነው’፣ እኛ ስንወለድ ‘ማርያም’፣ ‘ማርያም’ እየተባለልን ነበር . . .
አባቶቻችን ግን ምን ያህል ጥበበኛ ናቸው? የእመቤታችንን ፍቅር በልባችን፣ ጣዕሟን በአንደበታችን የቀረፁበት መንገድ
ይገርማል:: በህፃንነት ዘመናችን በምንወጣበትና በምንገባበት ሁሉ ከለላ ጠባቂ የነበረው አጋንንትን ድል እየነሳ ዛሬ እዚህ
ለደረስንበት ዕድሜ ፣ ረድኤትና በረከት የሆነን፤ ለዚህ ያበቃን ‘ማርያም’፣ ‘ማርያም’ የሚለው ስም ነው::
በተአምረ ማርያም ላይ ያለው ህፃን ትዝ ይላችኋል . . . በወላጆቹ ስህተት ለአጋንንት የተሰጠውን ህፃን ከአጋንንት ቀንበር
ለማውጣት በቤተ መቅደስ የሚያሳድጉት ካህን ህፃኑን አጋንንት እንዳይነጥቃቸው ዘወትር ከእጃቸው አይለዩትም ነበር።
ከዕለታት በአንዱ ቀን ለቅዳሴ ሲቻኮሉ ህፃኑን ረስተው ወደ ቤተመቅደስ ይገሰግሳሉ፤ ይህን መልካም አጋጣሚ ያገኘው
አጋንንት ህፃኑንይዞት ወደ መቀመቃት ይወርዳል፡፡ በዚህ ሰዓት ያ ህፃን ያጠናው ምን መሰላችሁ በኮልታፋ አንደበቱ ‘ማርያም’፣
‘ማርያም’ የሚለውን ቃል እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከዓይን ጥቅሻ ደርሳ ያንን አጋንንት ድል ነስታ ህፃኑን በቤተ
መቅደስ አቆመችው፡፡ ለእኛም ውለታዋ እንደዚህ ነው፡፡ ደግሞም ጨዋታውን ሁሉ ካስተዋላችሁት በሕይወት ዘመናችን
የሚጠቅም ቁም ነገር ነው፡፡ እንደ በላኤሰብ በኃጢአት በወደቅን ጊዜ በጽድቅ እንድንነሳ ለንስሐ እንድንበቃ ቃል ኪዳኗን
ምርኩዝ አድርገን ማርያም ብታነሳኝ እንላለን፤የዓለም ድሪቶ ተብትቦን መንገድ በጠፋብን ጊዜ የማርያም መንገድ ብለን
በቀናች በጸናች በተዋሕዶ መንገድ ተጉዘን ሀገረ ሕይወት መንግሥተ ሰማያት እንደርሳለን መርሕ ለመንግሥተ ሰማያት
ናትና፤ጠላት ዲያቢሎስ ባስጨነቀን ጊዜ የማርያምን ብቅል እየፈጨን በዝክሯ በጸበሏ ድል እንነሳዋለን፡
በዮሐንስ ራዕይ ዘንዶ ሆኖ የተነሳው ዲያቢሎስ በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ላይ ካለው መሪር ጥላቻ የተነሳ
በሄሮድስ ላይ አድሮ በግብጽ በረሃ ለሦስት ዓመት ከመንፈቅ አሳደዳት፡
ዛሬም እንደሄሮድስ እንደ አሽን በፈሉ መናፍቃን ላይ አድሮ ምርኩዛችንን ሊያስጥለን ከላይ ከታች ይላል እኔስ እንደ ቅዱስ
ባስልዮስ እንዲህ እላለሁ. . . “ቅድስት ድንግል ማርያም ማንስ ነው ከቅዱሳን ሁሉ በላይ እንደሆነች ያላስተዋለ?
እግዚአብሔር ለአገልጋዮቹ የሚልቅ ጸጋን ከሰጠና የሚነኩት ሰው ሁሉ ከበሽታው ከተፈወሰ፣ ጥላቻው ያረፈበት ተአምር
ከተፈጸመለት፣ቅዱስ ጴጥሮስ በጥላው ከዳነ፣ የቅዱስ ጳውሎስ የልብሱ ጨርቅ እራፊ መናፍስትን ካወጣ፣ለእናቱማ ምን
ዓይነት ሥልጣንና ኃይል ሰጥቷትይሆን?
ለቅዱሳኑ ይህንን ያህል ድንቅ እንዲያደርጉ ባለሟልነትን ከሰጣቸው ወልዳ ላሳደገችው እናቱማ ምን ያህል ይሰጣት ይሆን?
በምን ዓይነት ስጦታ አስጊጧት ይሆን? ቅዱስ ጴጥሮስ “ክርስቶስ አንተ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ ነህ” ስላለው ብፁዕ
ከተባለና የመንግሥተ ሰማያት ቁልፍ ከተሰጠው እርሷ ከሁሉም ይልቅ እንዴት የተባረከች /ብፅዕት/ አትሆን?
ቅዱስ ጳውሎስ ታላቅ ክብር ያለውን የክርስቶስን ስም በመሸከሙ ምርጥ ዕቃ ከተባለ የአምላክ እናትማ የምእመናን ምግብ
የሆነ መናውን ሳይሆን የሕይወትን ሰማያዊ እንጀራ ያስገኘች እርሷ ምን ዓይነት ልዩ ዕቃው ትሆን?
”እኔስ እላለሁ አብዝቼ እንደ ልጅነቴ ቅድስተ ቅዱሳን ንጽሕተ ንጹሐን ድንግል ማርያም . . . ማርያም . . . ማርያም…”
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
"ሂድና ውደዳት!"
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
በአንድ ወቅት አንድ ሰው ሚስቱ እንድትወደው ብዙ ነገር አድርጎ ስላልተሳካለት ሚስቱም ስላልወደደችው ተበሳጭቶ
ወደሰባኪው ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ይሄዳል፡፡
"ሚስቴ እንድትወደኝ ብዙ ለፋሁ ፤ ያላደረኩት ነገር የለም ፤ምንም ልትወደኝ አልቻለችም፡፡ እንድትወደኝ ማድረግ
የምችለው በምን መንገድ ነው?" ሲል በሀዘን ተሰብሮ ይጠይቀውና የሚነገረውን ጥበባዊ መንገድ በጥንቃቄ ለመረዳት
እዝነልቦናውን አዘጋጅቶ የአባቱን ዓይን ዓይኑን እየተመለከተ የአንደበቱን ጥኡም ቃል ይጠባበቃል፡፡
ቅ/ዮሐንስ ግን የነገሩት በአጭሩ በሁለት ቃል ብቻ የተዋቀረ ነበር፡፡ "ሂድና ውደዳት!"
ሰውየው 'ያልኩትን አልተረዳኝ ይሆን እንዴ?' እያለ እያሰበ ጥያቄውን ደግሞ አቀረበ። "ሚስቴ አልወደኝ አለች ምንም ባደርግ
ልትወደኝ አልቻለችም ነው ያልኩት" አለ በድጋሜ፡፡
"ሂድና ውደዳት" አለው ሰባኪው በድጋሜ፡፡
አሁንም ለሶስተኛጊዜ ሰውየው "ልትወደኝ የሚገባት ሚስቴ አልወደደችኝም ነው ያልኩዎትኮ!" አለ፡፡
ሰባኪውም መልሶ "ሂድና ውደዳት!" አለው፡፡
በዚህ ጊዜ ሰውየው እርሱ እንደሚወዳት ለመናገር 'እኔማ...' ብሎ ጀምሮ ራሱን መፈተሽ ጀመረ፡፡ እሱ ውስጥ ያለው፣ እርሱ
የሚወደው፣ የእርሱ ፍላጎት የእርሱን የራሱን በእርሷ መወደድ እንጅ እርሷን መውደድ አልነበረም፡፡ ጊዜውን ለመወደድ
በመጣር ብቻ አሳልፎታል፤ ጥረቱ ሁሉ እንድትወደው እንጅ እንዲወዳት አልነበረም፡፡ አዘነ፡፡ እርሷን መውደድ ሲገባው ራሱን
በርሷ ለማስወደድ ሲጥር ኖሯል፤ አልተሳካለትም፡፡
ፍቅር የሚመጣው በራሱ በፍቅር እንጅ በሌላው ሁሉ ጥረት አይደለም፡፡ በሌላ ጥረት የሚመጣ ሰው ሰራሽ "ፍቅር" ካለ ግን
ፍቅሩ ሀሰተኛ ነው፡፡
ራስን ከመውደድ አልፈን ራስን ወደማስወደድ ከመሄድ ይልቅ ሌላውን በመውደድ መወደድን አናጣውም፤ ፍቅር ሌላውን
የሚወድ ከሆነ ፍቅርንማ እንደምን አይወድ!
እርሷን ስትወዳት ፍቅሯን ታገኛለህ እንጅ ፍቅሯን ያለፍቅርህ አትሞክረው! አንዳንዶቻችን እኔ ላደረኩት ነገር ለምን
አልተደነቅሁም ለምንስ አልተወደድኩም እንላለን። እንደዚህ ካልን ያደረግነውን ላደረግንለት ሳይሆን ለራሳችን ነው ማለት
ነው ያደረግነው፤ ይህ ደግሞ የፍቅር ባህሪ አይደለም፡፡ እኛ ለሌሎች የሌለንን ፍቅርም ሌሎች ጋ ወደኛ መጠበቅ የለብንም፡፡
ለባለቤቴ ባደረኩላት ነገር ከእርሷ ምስጋናን የምሻ ከሆነና ካልተመሰገንኩ ከከፋኝ እኔ ከፍቅር የነፃሁ ምስኪን ነኝ፡፡ በርቅጥ
ሚስቴ ደስ ስትሰኝ ማየት ሊያስደስተኝ ይገባል፤ ይህ ማለት ግን እንደዋጋ አድርጌ ልወስደው ሳይሆን መደሰቷን
ስለምመርጥላት ስለእርሷ ደስታ ስል ነው፡፡ ስለእኔ በደስታዋ መደሰት ያይደለ፡፡
"ሂድና ውደዳት !" የሁልጊዜም መርሃችን ልትሆን ይገባል፡፡ እንድትወደን ሳይሆን እንድወዳት ስወዳት የምር ትወደናለች፡፡
ስንወድ ከተወዳጁ በምንጠብቀው ነገር መመስረት የለብንም የፍቅራችን መሰረት መመስት ያለበት ፍቅራችን ላይ እንጅ
በሚጠበቅ በሌላ ፍቅርም ሆነ ሌላመሰረት ላይ መሆን የለበትም፡፡
አምላክ እኛን ስለወደድነው አይደለም የወደደን ፤ በራሱ ፍቅር ተመስርቶ ወደደን እንጅ፡፡ እኛም በራሳችን ፍቅር ተመስርተን
ልንወደው ወይም ስለማይናድ በራሱ ፍቅር ተመስርተን ልንወደው ይገባል፡፡
ሰው ላይ ግን መመስረቻው የሰው ፍቅር አይደለም ፤ አያስተማምንም፡፡ በራስ ፍቅር መሠረት ላይ የተተከለች ፍቅር በራስ
ይዞታ ላይ እንደተሰራች ቤት ናት፡፡ ማንም መጥቶ አያፈርሳትም፡፡ ወዳኝ ከምንዋደድ ወድጃት ብንዋደድ ይሻለኛል፡፡ መሰረቱን
ራሴ ላይ ራሴ ብይዘው!
ብጹእነታቸው ከጻፋቸው አንዱ ከሆነው መንፈሳዊ ውጊያዎች ከሚለው መጽሐፍ የተገኝ ተከታታይ ጽሁፍ
ክፍል ፩
ውስጣዊ ውጊያዎች
ክፍል ፪
.......የአሳብ ውጊያ
አሳቦች በውንም ይሁን በእንቅልፍ ሊመጡ ይችላሉ ፡፡ አሳቦች አሳብ ወለዶች ቀን የተደረጉ ነገሮች ውጤት ወይም በምኞትና
በአሳብ ምክንያት ሕሊና ውስጥ የሰፈሩ ጉዳዮች ወይም በሰውየው የተደመጡ ወሬዎችና ወጎች ሆነው በሕሊናው ውስጥ
የተተከሉ ሊሆን ይችላል ።
እነዚህ ሁሉ በሕልም ፤ በሕሊና ፤ ብክነት ወይም ሰው ልቡ እስከ ተቀበላቸው ድረስ በቁሙ ቅዠቱ ውስጥ የሚያመላልሳቸው
ሆነው ሊገለጡ ይችላሉ ፡፡ ልብ ካልተቀበላቸው ግን ሊቆሙ ስለሚችሉ ሰውየው ወደ ማንነቱ መመለስ ይችላል ።
አሳቦች ወደ ህሊና እንዲገብ የሚፈቅደው ሁነኛ ተቆጣጣሪ የሰው ፈቃድ እንዲቆይ ወይም እንዲወጣ ማዘዝ ይችላል ።
ዲያብሎስ ያለ ሰው ፈቃድ በሕሊና ውስጥ አንድ አሳብ ሊያስተዋውቅ ይችላል ። ይሁን እንጂ አሳብ ወደ ሕሊናህ እንዲገባ
ኃላፍነቱን ባትወስድም ልትቀበለው ኃላፊነቱን የምትወስደው ግን አንተ ነህ ።
ከፈለግህ እንዲህ ያለውን አሳብ ልታጠፋው ወይም ላትሞገተው ወይም እንኳን ደህና መጣህ ብለህ ላትቀበለውም ትችላለህ
። ይህን የኃጢአት አሳብ ከተቀበልህ ግን በአንተ ውስጥ ያደረውን መንፈስ ቅዱስንና የእግዚአብሔርን ፍቅር ትክዳለህ ፡፡ በዚህ
ምክንያት የእግዚአብሔርን ትእዛዛትና የልብህን ቅድስና መጠበቅ ያልቻልህ ሰው ሆነህ ትቆጠራለህ ማለት ነው ።
አሳቦች እንዳይቆጣጠሩህ በፈቃድህና በአንተ ውስጥ ባለው ጸጋ ልታሸንፋቸው ትችላለህ ። አንተ ካልታዘዝካቸው በስተቀር
የኃጢአት ሀሳብ ንጽሕናህን ሊያሳጡህ አይችሉም ፡፡
ስለሆነም የሀሳብህ ተገዢ አትሁን ፨ አሳብ እንዴት እንደሚጀምር ፤ እንደሚዳብር ፤ በሕሊና ውስጥ እንደሚመላለስ
እያንዳንዱ ሰው ሊያውቅ ይገባዋል ። አሳብ በገርነትና በዝግታ ከጀመረ በኀላ መጨረሻው በኃጢአት እንደሚጠቃለል ሁሉም
ሰው ይወቅ ። አሳብ የበለጠ እንዳይበረታታ ዕድሉን እንዳይሰጠው እያንዳንዱ ሰው የራሱ ዘብ ይሁን ።
☞ አሳብ አጥብቆ ቢይዝህና ያለማቋረጥ ቢወተውትህ ተስፋ አትቁረጥ መቋቋም ምንም ጥቅም የለውም ብለህም አትረታ ።
ተስፍ መቁረጥ ሰውን ቸልተኛ ስለሚያደርገው የውስጥ መዝጊያዎችን ወለል አድርጎ እንዲከፍት ያደርገዋል ። በመጨረሻም
ደግሞ ይወድቃል ፡፡ የምንመክራችሁ ግን አሳብን ተዋግታችሁ ድል እንድትነሱት ነው ፡፡ ግን እንዴት ???
አሳብን ድል የምንነሣው እንዴት ነው ??
ለቀጣይ ይቆየን ........
ክፍል ፫
፩ . አሳቦችን አትፍራ በእነሱ እሸነፋለሁ ብለህ አታስብ ። ይልቁንም "ኃይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ "በል {
ፊል 4*13}
አሳቦችን በመዋጋት ጽኑ ሆነህ እነዚህን ድንቅ ቃላት አስታውስ ፦ "የሰውንም አሳብ በእግዚአብሔርም እውቀት ላይ
የሚነሣውን ከፍ ያለውን ነገር ሁሉ እናፈርሳለን .. { 2 ቆሮ 10*5}
፪ . አሳቦችህን ለመምራት ራስህን አለማምድ እንጂ አሳቦችህ አይምሩህ ።
፫ . ሁል ጊዜ ሕሊናህን በመንፈሳዊ ነገሮች ሙላ ፦ ይህን የምታደርግ ከሆነ ዲያብሎስ መጥፎ አሳብ ሊያስተዋውቅህ ሲመጣ
እንኳን ደህና መጣህ የሚለው ሕሊና አያገኝም ፡፡ ዘወትር በስራ ራስህን ባተሌ አድርግ ፡፡ ዲያብሎስ ወደ እርሱ ገብቶ
የወደደውን ዘር እንዳይዘራበት ሕሊናህን ባዶ አታድርግ ፡፡
፬ . ባልጠበኸው ሰዓት የኃጢአት አሳብ እንዳይጥልህ የልብህን ንጽሕና በመጠበቅ ሁልጊዜ ንቁ ሁን ፡፡
አሳቦች ደካማ አንተ ደግሞ ብርቱ በሆናችሁበት ጊዜ አሳቦችን ከጅምሩ አጥፍቸው ። አሳቦችን ለጥቂት ግዜ በሕሊና ውስጥ
ካቆየሀቸው ወዲያውኑ ሰፍረው ይቆጣጠሩሃል ። በአንተ ውስጥ ተደራጅተው ሲሰፍሩ ስለምትደክምና ልትቋቋማቸው
ስለማትችል ትወድቃለህ ። ስለዚህ አሳቦችን ካንተ ለማራቅ ንቁና ቀልጣፍ ሁን ።
፭ . የአሳብ መንፈሳዊ ባሕርይና የአሳብ ይሉኝታ ።
ሕሊናህ በጸሎት በተመስጦ ፤ በፍቅር ቃላት ፤ በውዳሴና ፤ በመዝሙር ከእግዚአብሔር ጋር አንድ ይሆናል ። በዚህ ግዜ ሕሊና
በሌሎች የኃጢአት አሳቦች ላለመጠመድ ይሉኝታ ይይዘዋል ። በመሆኑም እነዚህን አሳቦች ያስወግዳል ።
፮ . በሌላ መልኩ ጥቃቶችን ሊያመጡብህ ከሚችሉ የኃጢአት አሳቦች መራቅ አለብህ ።
ከማንኛውም ክፍ ስብሰባ ፤ ከማንኛውም ክፍ ባልጀርነት ወይም ከማንኛውም ግንኙነት ራቅ ። መጥፎ አሳብ ሊያስከትሉብህ
የሚችሉና ከመንፈሳዊ አሳቦችህ ሊያስወጡህ የሚችሉ አሳቦች ያላቸው ጹሁፎችን ከአንተ ዘንድ አስወግድ ። በአጠቃላይ ክፋ
አሳብ ሊያመጡብህ የሚችሉ ነገሮችን ከአጠገብህ አስወግድ ፡፡
፯. ስሜቶችህ የሕሊናህ መግቢያዎች ስለሆኑ ንጹሕ አሳቦችን ይሰጡህ ዘንድ ንጹሕ አድርገህ ጠብቃቸው ።
በስሜቶችህ ቸልተኛ ከሆንህ ራስህን ተዋጋው ። ራስህን ጠብቅ ። ስሜቶችህ ያገልግሉህ እንጅ አይቃወሙህ ። ከዚህ በኀላ
በቅዱሳን ሥዕላት ላይ ተመስጦ አድርግ ስለ እነርሱ አድምጥ ፤ ማህሌቱን ቅዳሴውን አድምጥ ። እነዚህ ሁሉ ለልብህ
መንፈሳዊ አሳቦችን ያቀርባሉ ።
፰ . መልካም ወይም መጥፎ ያልሆኑ የጥርጥር አሳቦችን ተጠንቀቅ ።
እነዚህ አሳቦች በአብዛኛው ወደ ኃጢአት አሳቦች የሚመሩ ናቸው ። ሕሊናውን ሊቆጣጠር የማይችለውን ሰው ሕሊናውን
እንደ ወደደው እንዲባዝን ስለሚተወውና በኃጢአት የተሞላ ጉዳይ እንዲያገኝ ስለሚረዳው በእርሱ የተጠመደ ይሆናል ።
ሕሊናህን በጎ በሆነው በእግዚአብሔር ፍቅር ወይም በሌሎች ጠቃሚ ጉዳዮች ሙላው ።
፱ .በአሳብ ታውከህ ልታሸንፈው ካልቻልክ ከሌሎች ጋር በማውራት ከእርሱ ሸሽተህ ሂድ ፡፡
ሕሊናህ በተመሳሳይ ሰዓት በአሳብና በንግግር ሊጠመድ ስለማይችል በግንኙነትህ ውስጥ ያለውን ንግግር የኃጢአት አሳብህን
ያጠፋል ።
፲ .አሳብን ለማጥፋት የጸሎት እርዳታ ፈልግ ፡
ወደ እግዚአብሔር አንተን የማያስደስት ማንኛውንም ዓይነት አሳብ ከእኛ አርቅልን ብለን እንጸልያለን ፡፡
ክፍል ፬
....... ካለፈው የቀጠለ
+ የምኞት ውጊያ
ብዛት ያላቸው የምኞት ዓይነቶች አሉ ። ከእነርሱ መካከል ፦ የሥጋ ምኞት ፤ የስልጣንና የደረጃ ፤ የብቀላ ፤ የበላይነት ፤
የሀብት ፤ የባለቤትነት ፤የክብርና ፤የዝና ምኞት ዋና ዋናዎቹ ናቸው ።
እዚህ ላይ ልብ ንብረትነቷ ከእግዚአብሔር ይልቅ ወደ ሌላ ስለሚሸጋገር "ልጄ ሆይ ልብህን ስጠኝ ...( ምሳ 23*26) ለሚለው
የእግዚአብሔር ቃል የምትሰጠው ምላሽ አይኖርህም ።
1, በአንድ ምኞት ከተጠቃህ በእርሱ አትግፋ
ባገኛችሁት ምኞት ሳይሆን ባሸነፋችሁት ምኞት ደስ ይበላችሁ ፡፡ ሰውን ይበልጥ ደስ የሚያሰኝው ራሱን ማሸነፍ ሲችል ነው
።
2, ምኞት ቢያሰለችህም ተስፋ አትቁረጥ ! ምንም ጥቅም የለውም ብለህም አታስብ አንተ ልትመለከተው የሚገባህ መድህን
አለም ኢየሱስ ክርስቶስ ለአንተ የሚያደርግልህን ነገር እንጅ አንተ ለራስህ ልታደርገው ያቃተህን ነገር አይደለም ጌታ
ሳምራዊቷን ሴት ወደ ወንጌል መስካሪነት መቅደላዊት ማርያምን ወደ ቅድስትነት የለወጠ አምላክ ነው ። እግዚአብሔር
ከሌሎቹ ጋር በጸጋ እንደሰራ ሁሉ ከአንተም ጋር ይሰራል ፡፡ ስለዚህ ብቻህን እንደምትዋጋ አድርገህ አታስብ ።
3, ድል ከተቀዳጁ በሗላ በፊትህ የቀደሙ ውድቀቶችህንና ደካማ ተፈጥሮህን ያላጎሉብህን ቅዱሳንን አስብ ።
እግዚአብሔር ድል የነሡትን እንደወዳቸው አንተንም ይወድሃል ። ከሌሎች ጋር ሆኖ እንደሚሰራውም ከአንተም ጋር የሠራል
። ጥቃት ሲጨምር የእግዚአብሔር ጸጋ ይበልጥ ይጨምራል ፡፡ ስለዚህ ወደ የእግዚአብሔር በመጠጋት የእርሱን እርዳታ ፈልግ
።
4, በምኞትህ ውስጥ ስትሆን እግዚአብሔር በምሕረቱ እስኪጎበኝህ ድረስ ከእርሱ ጋር በጽናት ታገል ።
በጠለቀ ኃጢአት ውስጥ ስትሆን ለመጸለይ አትፈር ። አባታችን አዳም ኃጢአት ከሠራ በሗላ ከእግዚአብሔር ፊት በመሸሽ
ራሱን ከዛፍ በስተ ጀርባ እንደደበቀ አንተም ራስህን አትደብቅ ። በወደቅህ ቁጥር እግዚአብሔር እንዲያነሳህ ወደ ንስሓ
እንዲመራህና እንዲያነጻህ በእርሱ ላይ ተጣበቅ ። "አቤቱ ጌታዬ ሆይ !አንተ በእኔ ላይ አድረህ ተዋጋ ። የእኔንና የአንተን
ጠላቶች ድል ንሳቸው !አንተ አትተወኝ በለው! " ፡፡
እንዲህ በለው "አቤቱ ጌታዬ ሆይ በኃጢአት ብወድቅም የአንተ የሆንሁና ከአንተ ጋር የተዛመድኩ ልጅህ ነኝ ! ከጋጣህ
ብጠፋም የመንጋህ በግ ነኝ !ከገንዘብ ቦርሳህ ውስጥ ብጠፋም የአንተ ድሪም ነኝ !ጠላት ከአንተ ጋር ሊለየኝ ቢሞክርም እኔ
አንተን ፈጽሞ አልረሳም አንተም እንዲሁ ! ።
5, ኃጢአት ከእግዚአብሔር ፍቅር እንዲለይህ አይሁን ። ይልቁንም ልብህን ለእርሱ ከፍተህ "አቤቱ አምላኬ ሆይ ! ይህን
ኃጢአት የፈጸምኩት ከድካሜ የተነሣ ነው እንጅ ከጥላቻ ወይም ከክህደት የተነሣ አይደለም ! "በለው ።
6, እግዚአብሔር ድካምህን እንደሚያውቅና እስካሁን ድረስም እንደሚወድህ እርግጠኛ ሁን ! በኃጢአት ውስጥ ብትሆንም
እግዚአብሔር ሊያድንህ ወደ እርሱ ሊያቀርብህና ወደ ቀደመ ደረጃህ ሊመልስህ እንደሚሰራ እመን ። አዳም የዳነው ንሥሐ
ለመግባት ባደረገው ሙከራ ሳይሆን አዳምን በተመለከተው የእግዚአብሔር ቸርነት ነው ።
7, የኃጢአት ምኞትህን የሚዛን ልክ በልብህ ውስጥ ያመጣጥን ዘንድ ማንኛውንም ዓይነት መንፈሳዊ ሥራ በመሥራት
የክፋታቸውንና የአደጋቸውን መጠን ቀንስ ። የምኞት ኃጢአት እስክታስወግደው ድረስ መልካም ፈቃድ በልብህ ውስጥ ቀስ
በቀስ እንደሚያብብ እርግጠኛ ሁን ። መንፈስ ቅዱስ በውስጥህ እንደሚሰራ ሲታወቅህ ችላ አትበለው ! ከእርሱ ጋር ሥራ
እንጂ በምኞትህ ልትቀጥል አትሞክር ።
8, ድካምህን ስታውቅ በሌላ ጊዜ ራስህን ለውጊያ አታጋልጥ ።
❖ ውጪያዊ ውጊያዎች ፦ ለቀጣይ ይቆየን
ከብጹዕነታቸው መንፈሳዊ ውጊያ ከተሰኝው መጽሐፋቸው የተገኝበስመ አ
ክፍል ፭ ......ከለፈው የቀጠለ
ውጪያዊ ውጊያዎች
እነዚህ ውግያዎች የሚመጡት በሚገባ ከሚታወቁ ምንጮች ነው ። የሚመጡት ከዲያብሎስና ጠላት ከሆኑ ሰዎች ወይም
የቅርብ ወዳጆች ከሆኑ ሰዎች ነው ። እነዚህ ውጊያዎች ከዓለም ከቁሳዊ ነገሮች ፤ ወይም በውስጡ ጥቃት ከያዘ ከአካባቢ
ሊመጡ ይችላሉ ።
❖ የዲያብሎስ ውጊያዎች
የዲያብሎስ ውጊያዎች ዝግ ብለው የተራዘሙ ወይም ድንገተኛና ከባድ ሊሆኑ ይችላሉ ።
ዲያብሎስ ሰለባዎቹን የሚስበው በተራዘመ ለዘብተኛ አቀራረብ ስለሆነ ተጠቂዎቹ ምን ሊመጣባቸው እንደሚችል
አያውቅም ። ስለሆነም እነዚህን ዝግ ያሉ ውጊያዎቹን አንገነዘባቸውም ።
ዲያብሎስ ሕይወታቸውን እስኪለወጥ ድረስ መንፈሳዊ ፍቅራቸውን በዝግታ እያሳጣ ወደ ሰፊው የውጊያ ዓውድ ቀስ በቀስ
ይጎትታቸዋል ። የሚባንኑት እድላቸው ካለፈ በሗላ ስለሚሆን ዲያብሎስ ባልተዘጋጁበት ሰዓት ድንገት ይመታቸዋል ።
ምናልባት ጠቢቡ ሰለሞን የተወጋው ቅንጦት ፤ ድሎት ፤ብዙ ሴቶችና ይሉኝታ ባሉበት በዚህ መንገድ ነው ።በመሆኑም ወደቀ
። 1 ኛ ነገ 11*1-8 የወደቀው በእድሜው የመጨረሻ ዘመን ላይ ነው ።
ከባድ ከሚባሉትና ድንገት ከሚደርሱት ውጊያዎች መካከል በጻዲቁ እዮብ ላይ የወረደው አንዱ ነው ። ይህ ውጊያ
በእግዚአብሔር ፈቃድ የሆነ ኢዮብ ሊሸከመው በሚችለው መጠን የተወሰነና በመልካምና በተባረከ መንገድ የተጠናቀቀ
ውጊያ ነው ።
ከዚህ የተለዩ ዲያብሎስ የሚቀሰቅሳቸው ሌሎች ውጊያዎች አሉ ። እነዚህም ዲያብሎስ በአሳብ ውስጥ ወደ ሕሊና
የሚያስወነጭፋቸው ወይም በልብ ውስጥ የሚያሳድራቸው ውጊያዎች ናቸው ። እነዚህ ውጊያዎች ሲጀምሩ በአብዛህኛው
ደካማ ከመሆናቸው በላይ ለሰውየው እንግዳ ስለ ሆኑ ነው ። ሰውየው ወደ ልቡና ወደ ፍላጎቶቹ ዘልቀው እንዲገቡ
መዝጊያውን እስኪከፍትላቸው ድረስ በዚያው ይቆያሉ ። ከከፈተላቸው እዚህ ላይ ከፍተኛውን ስህተት ይፈጽማል ።
በአንተ ውስጥ ያለውን የእግዚአብሔርን መንግሥት ለሚያጠፋ ጠላት መዝጊያዎችህን መክፈት መንፈሳዊ ክህደት ነው ። ይህ
ክህደት ወደ ቤትህ ገብቶ ሊቀመጥ በወደደው በእግዚአብሔር ላይ የሚደረግ ክህደት ነው ። እርሱ ለአንተ ቅዱሳት
ምሥጥራትን ከመግለጡም በላይ ልብህን የመንፈስ ቅዱስ ማደርያ አድርጎልሃል ። አንተ ግን ለዲያብሎስ በመታዘዝ ልብህን
ከፍተህ የእርሱን ተቃዋሚ አሳቦችመቀበልህ ታላቅ ክህደት ነው ። በዚህ ክህደት ምክንያት በአንተ ውስጥ ያለውን
የእግዚአብሔርን የጸጋ ስራ ስለምትቃወም ዲያብሎስ በአንተ ላይ ኃይል ይቀዳጃል ።
ውጫዊ ውጊያዎች ከባድ ናቸው በማለት ምንም ዓይነት ምክንያት አታቅርብ ። ይህን የምታደርግ ከሆነ ለእነርሱ እጅህን ስለ
ሰጠህ ኃይል የምታጎናፅፋቸው አንተ ትሆናለህ ። የምትቃወማቸው ከሆንህ ግን ሐዋርያው እንደተናገረው ዲያብሎስ በአንተ
ፊት ደካማ ይሆናል "ዲያብሎስን ተቃወሙ ከእናንተም ይሸሻል "{ያዕ 4*7}
አንተ በውስጥህ ያለው ልብህ ብርቱ እስከሆነ ድረስ በዲያብሎስ ውጊያዎች ፊት በጭራሽ ደካማ አትሆንም ።
የርኩሳን መናፍስት አለቃ የሆነው ዲያብሎስ ከረዳቱ አንዱን ወደ አንድ ክርስቲያን እንዲዋጋው ሲልከው ርኩስ መንፈሱ
እየተንቀጠቀጠ ። ከዚህ የመንፈስ ቅዱስ ማደርያና የእግዚአብሔር መላእክት ዙርያውን የከበብት ይህን ብርቱ ሰው እንዴት
እዋጋለሁ እንዴትስ እቀርባለሁ ይላል ። በመስቀልስ ቅርፅ እጆቹን ለጸሎት ቢያነሳብኝ ወዴት አመልጣለሁ "ሂድ አንተ ሰይጣን
ቢለኝ" ወዴት እገባለሁ በማለት ይጠይቃል ።
ለዲያብሎስ ውጊያዎች ዓይነተኛ ምሳሌ ከሚሆኑን መካከል እግዚአብሔርን አለማመንና ተስፋ መቁረጥ ዋና ዋናዎቹ ናቸው
። ይሁን እንጂ እነዚህ የአንተ እጅ የሌለባቸውና የአንተ ያልሆኑ ውጪያዊ አሳቦችና ጥቃቶች ስለሆኑ አትፍራቸው ።
☞ ዲያብሎስ ወደ ሕሊናህ የሚያስወነጭፋቸው ፍላፃዎች የእግዚአብሔርን ሕልውና ፣ ፍቅሩንና ፣ጥበቃውን እንድንጠራጠር
የሚያደርጉ ናቸው ። የጸሎትህን ውጤታማነትና የቅዱሳንን አማላጅነት የሚያጠራጥሩ አሳቦችም በሕሊናህ ውስጥ
ይጨምራል ። ይሁን እንጅ አንተ በዚህ አልተደሰተሁም ብለህ አሳቦቹን በመቃወም እግዚአብሔር ከአንተ ያርቅልህ ዘንድ ወደ
እርሱ ስትጸልይ ዲያብሎስ "እነዚህ ሁሉ አሳቦች በአንተ ውስጥ እያሉ እንዴት ልትድን ትችላለህ ?" ይልሃል ። ይህ የአሳብ
ውጊያ ነው እንጂ በአሳብ የሚመጣ ውድቀት አይደለም ። ለጥቂት ደቂቃዎች ብትወድቅም እንኳ ከድካም የተነሣ እንጂ
በእግዚአብሔር ባለመታመን አይደለም ። ስለዚህ እርሱም ይቅር ይልሃል ።
አሳቦች ወደ ሕሊናህ የሚያመጣ ጽሑፍ እንዳታነብ እመክርሃለሁ ።እነዚህ አሳቦች የሚያቀብሉህን ክፋ ግንኙነቶች አስወግድ
። ዲያብሎስ አሳቦች አንተን ለመዋጋት ሊጠቀምባቸው ስለሚችል ቀድመኸው ብልህ ሁን ።
✞ ክፉ ባልጀርነት
ለቀጣይ ይቆየን
ክፍል ፮
.........ካለፈው የቀጠለ
ክፋ ባልጀርነት
እንዲህ ያለ ባልጀርነት ለመንፈሳዊነትህ ፣ ለእምነትህና ለሕሊናህ ጎጂ ነው ። አልፎ ተርፎም ሕሊናህንና ስሜቶችህን
ሊያጠፋ ይችላል ።
የእናታችን የሔዋን የመጀመርያ ውድቀት የተከተለው ከእባብ ጋር በመሠረተችው ክፍ ባልጀርነት ምክንያት ነው ። ንጉሥ
አካአብ የወደቀው በክፋ ሚስቱ በኤልዛቤል ከንቱ ምክር ነው ።
ስለዚህ የአሳቦቻቸውን ተጽዕኖዎች በእናንተ ላይ በቀላሉ ሊያሳድሩ ስለሚችሉ ባልጀሮቻችሁን በሚገባ እንድትመርጡ
ትመከራላችሁ ። የትዳር ጓደኛ ደሚሆናችሁንም በጥንቃቄ እንድትመርጡ ትመከራላችሁ ። ምክንያቱም እነሱ
መንፈሳዊነታችሁን ሊክብም ሆነ ሊንድ የሚያስችል የአሳብ ተጽዕኖ በእናንተ ውስጥ ማሳደር ስለሚችሉ ነው ።
የቅርብ አጋሮች ከጓደኞች ወይም ከወዳጆች ወይም ከባልጀሮች የበለጠ ጥልቀትና አደገኛ ውጤት ሊያስከትሉ ይችላሉ ።
ከባልጀሮች ጋር የምትገናኙት አልፎ አልፎ ሲሆን ከቅርብ አጋሮች ጋር የምትኖሩት ግን እስከ መጨረሻው ድረስ ነው ። ስለዚህ
ከምንም ነገር አንጻር የእግዚአብሔር ሰው የሆነ አጋር መምረጥ የግድ ነው ። ልትደሰቱ የሚገባችሁ በውጭያዊው ገጽታ
ሳይሆን በውስጣቸው ባለው ጥልቀት ነው ። ይህን አስመልክቶ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተጻፈው ቃል እንዲህ ይላል ፦
"አትሳቱ ክፋ ባልንጀርነት መልካሙን አመል ያጠፋዋልና "።{1 ኛ ቆሮ 15*33} ። ..ለሰውም ቤተ ሰዎቹ ጠላቶች ይሆኑበታል
።{ማቴ 10*36}ለዚህ ምሳሌ የሚሆኑን ልጆቻቸው እንዳይጾሙ እግዚአብሔርን እንዳያመልኩ በጉባኤ ላይ እንዳይሳተፍና
በቤተ ክርስቲያን እንዳያገለግሉ የሚከለክሉ ወላጆች ናቸው ። አልፎ ተርፎም እነዚህ ወላጆች ልጆቻቸው ራሳቸውን
እንዲያስጌጡና በተለያዩ ዓለማዊ መዝናኛዎች እንዲሞላቀቁ የሚመክሩ ናቸው ። በመሆኑም ይህን የሚመስለው ቤተሰብ
ራሱን እንደ አንድ መንፈሳዊ ቤተሰብ የሚመራ ቤተሰብ አይደለም ።አንድ ሰው ራሱን ከቤተሰቦቹ ወይም ከባልጀሮቹ መለየት
ሊያዳግተው ይችል ይሆናል ። ይሁን እንጂ እነርሱን ከመውደድ ይልቅ እግዚአብሔርን ሊወድ ለእነርሱ ከመታዘዝም
ለእግዚአብሔር ሊታዘዝ ይገባዋል ። እምነቱንና መንፈሳዊነቱን ስለ ወዳጆቹ ሲል መሥውአት አድርጎ ማቅረብ የለበትም ።
አንድ ሰው ምን ግዜም ቢሆን "ከሰው ይልቅ ለእግዚአብሔር ልንታዘዝ ይገባልናል ።{ሐዋ 5*29} የሚለውን የሐዋርያውን ቃል
ሊያስታውስ ይገባዋል ። ከእግዚአብሔር የሚሻል ወይም ከእርሱ ይበልጥ የሚወደድ ማንም ሊኖር አይገባውም ።
ከዘላለማዊነትህ የሚበልጥ ምንም ዓይነት ጠቃሚ ነገር አይኖርም ።ይሁን እንጅ ልትርቃቸው የሚገብ አንዳንድ ዘመዶች
ይኖሩሃል ። ይህም መራቅ በአካል መራቅ ሳይሆን በሥራቸው ፤ በንግግራቸውና በማናቸውም የተሳሳቱ ድርጊቶቻቸው ውስጥ
ተባባሪ ባለመሆን ሊሆን ይገባዋል ። ይህ በዚህ እንዳለ ክፋ አድራጊ ዘመዶቻቸውንም ሆነ ባልጀሮቻቸውን ስለ ይሉኝታቸው
ብለው የማይርቁ ሰዎች ብዙዎች ናቸው ። በመሆኑም ስለ ይሉኝታቸው የክፋ ስራቸው ተባባሪ ይሆናሉ ።መንፈሳዊ ሰው ግን
ይሉኝታ ወሰን እንዳለው ያውቃል ። ከዚህም በተጨማሪ ከእነዚህ ጥቃቶችና ምክንያቶቻቸው ለመራቅ ጠበቅ ያለ አቋምና
ብርቱ ሰብእና ሊኖር ያስፈልጋል ።ስለ መንገዱ ከመጠየቅህ በፊት ስለ ጓደኛህ ጠይቅ የሚባል አባባል ትክክለኛ ነው ።
ምክንያቱም አንዳንዶቹ ወዳጆችህ ነፍስህን ሊያጠፋ የሚችል መጥፎ ተጽዕኖ ሊያሳድሩ ስለሚችሉ ነው ። እነዚህ ሰዎች
ለልብህና ለአዕምሮህ እንግዳ የሆኑ መመሪያዎችንና አሳቦችን በማስተዋወቅ ሕይወትህን ከትክክለኛው መንገድ ያስወጧቸዋል
።የአንተ እውነተኛ ጓደኛ ወደ እግዚአብሔር የሚያቀርብህ መሆኑን እወቅ ። እውነተኛ ጓደኛህ መልካም ዝናህን የሚጠብቅና
ስለ ድኀነትህ የሚያስብ ጻድቅና ልባም ሊሆን ይገባል ።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር።
ጥያቄ፡
አንድ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ከሌላ የእምነት ድርጅት ተከታይ ጋር የፍቅር ግንኙነት ቢጀመር ወይም ቢጋባ ችግሩ
ምንድንነው?
መልስ፡
ምስጢር ያፋልሳል።
አምላካችን ቅዱሱን ጋብቻ ሲሰጠን በውስጡ ምስጢር አለበት። ይህም ቅዱስ ጳውሎስ እንዳስተማረው ጋብቻ የኢየሱስ
ክርስቶስና የቤተ ክርስቲያን ምሳሌ ነው፡፡ ባል ሚስቱን የሚወዳትን ያህል ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያንን ይወዳታል። ሚስት
ለባልዋ የምትታዘዘውን ያህል ቤተ ክርስቲያንም ለክርስቶስ ትታዘዛለች። (ኤፌ 5፥23) ጋብቻ በሚያምኑና በማያምኑ ሰዎች
መካከል ከተፈጸመ ምሥጢሩ ከክርስቶስና ከቤተ ክርስቲያን ተዋሕዶ ጋር አይስማማም፡፡ ከዚህም አልፎ ባልና ሚስት በጋራ
መፈጸም ያለባቸውን ምስጢራት (ምስጢረ ተክሊል፡ ምስጢረ ቍርባን...) የማይፈጽሙ ይሆናሉ።
የጌታችንና የአባቶቻችን ትዕዛዝን ይጣረሳል።
"እግዚአብሔር እስራኤልን ከሰባቱ አሕዛብ ጋር አትጋባ ሴት ልጅህን ለወንድ ልጁ አትስጥ ሴት ልጁንም ለወንድ ልጅህ
አትውሰድ" (ዘዳ 7፥3) ስለዚህ የጌታችንን ትዕዛዝ ከመተላለፍ ባለፈ አምላካችንን የካደን ሰው ስናገባ ለአምላካችን ያለን
ፍቅርን ጥያቄ ውስጥ ይከታል።
ቅዱስ ጳውሎስም በተደጋጋሚ ከሌላ የእምነት ድርጅት ተከታዮች ጋር ያለንን ከልክ ያለፈ ግንኙነት ያወግዛል። "ከማያምኑ
ጋር በማይመች አካሄድ አትጠመድ ጽድቅ ከአመጽ ጋር ምን ተካፋይነት አለው? ብርሃንም ከጨለማ ጋር ምን ኅብረት አለው?
ወይስ ከሚያምኑ ከማያምን ጋር ክፍል አለው?" (2 ኛ ቆሮ 6÷14) "ከእነርሱ ጋራ እንዳትተባበሩ፣
እንደነዚህ ካሉት ጋር መብል እንኳ እንዳትበሉ እጽፍላችኋለሀ" (1 ቆሮ 5÷11-12)
መልካም አመልን ያጠፋል።
አባቶቻችን ሲያስተምሩ ሰው ውሎውን ጓደኛውን ይመስላል "ከቸር ሰው ጋር ቸር ሆነህ ትገኛለህ፣ ከቅን ሰው ጋር ቅን ሆነህ
ትገኛለህ፣ ከንጹህ ጋር ንጹህ ሆነህ ትገኛለህ ከጠማማ ጋር ጠማማ ሆነህ ትገኛለህ" (መዝ 17÷26) "አትሳቱ፤ ክፉ ባልንጀርነት
መልካሙን አመል ያጠፋል።"(1 ኛ ቆሮ 15÷33) በመሆኑም ከአሕዛብ የተጋባ መጨረሻው አሕዛብ መሆን ነው። ለዚህም
ትልቁ ማሳያ በምድራችን ከእርሱ በላይ ጠቢብ ያልነበረ አባታችን ሰሎሞን ነው። ሰሎሞን ፍቅር አዘንብሎት የአሕዛብን
ሴቶች አገባ በመጨረሻም አምላኩን ረስቶ ለጣዖቶቻቸው ሰግዷል። (1 ኛ ነገ 11፥4-8) ስለዚህ "እሷም በሃይማኖቷ እኔም
በሃይማኖቴ" የሚለውን አባባል ከተለያዩ ማኅበረ ሰብእ ለመኖር እንጂ ለትዳር እንደማይሆን አውቀን ቢቻል እምነታችንን
ሊያዳብርልን ከሚችል ሰው ጋር ነው መጋባት ያለብን።
ክፉ ፍሬ ይወጣበታል፡፡
የተለያየ እምነት ያላቸው ሰዎች የሚወልዱት ልጅ ሃይማኖት ለመምረጥ ይቸገራል። ብዙ ጊዜ እምነት የለሽ ወይም
የአሕዛቡን እምነት ተከታይ ይሆናል። "እግዚአብሔር እስራኤልን ከሰባቱ አሕዛብ ጋር አትጋባ... እኔን እንዳያመልክ ሌሎችንም
አማልክት እንዲያመልክ ልጅህን ያስታልና" (ዘዳ 7፥3)
በመጨረሻም ከእግዚአብሔር ዘንድ ቁጣ እና መቅሰፍት ያስከትላል።
"እናንተ ግን ተመልሳችሁ በመካከላችሁ ወደ ቀሩት ወደ እነዚህ አሕዛብ ብትጠጉ ከእነርሱም ጋር ብትጋቡ እናንተም ወደ
እነርሱ እነርሱም ወደ እናንተ ብትደራረሱ አምላካችሁ እግዚአብሔር ከሰጣችሁ ከዚህችም ከመልካሚቱ ምድር እስክትጠፋ
ድረስ መውደቂያና ወጥመድ በጎናችሁ መግረፊያ በአይናችሁ እሾህ ይሆንባችኋል…." (ኢያ 23÷12-13)
በእርግጥ ከአሕዛብ ወይም ከመናፍቃን ወገን የትዳር አጋር የመረጥን ካለን ትምህርተ ሃይማኖትን እንዲማሩና የክርስትና
ጥምቀትን እንዲጠመቁ በማድረግ ቀድሰን ማግባት እንችላለን። "ያላመነ ባል በሚስቱ ተቀድሶአልና፥ ያላመነችም ሚስት
በባልዋ ተቀድሳለች፤ አለዚያ ልጆቻችሁ ርኵሳን ናቸው፤ አሁን ግን የተቀደሱ ናቸው።" (1 ኛ ቆሮ 7:14፤) (ፍት. አን. ፳፬፣
ቍ. ፱፻፲፪-፱፻፲፭)
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር
መልስ
በቅዳሴያችን ገና ከጅምሩ "እምነ በሐ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን፡ እናታችን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንደምን አለሽ" ብለን
እየተሳለምን ቤተ ክርስቲያን እናታችን መሆኗን እንመሰክራለን። ይህም በስጋዊ ልደት ያይደለ በጥምቀት የወለደችን ናት፡፡
ስለዚህ ሁሉም በሕይወታችን የሚከናወኑ ነገሮች በእሷ በኩል ማለፍ አለበት። ይህም ጥምቀታችን፡ ሠርጋችን፡ ሞታችን
ሁሉንም ለማስተናገድ ቤተ ክርስቲያን ስርዓት አዘጋጅታ እጆቿን ዘርግታ ትጠብቀናለች።
ከእነዚህ ውስጥ በሞት ጊዜ ጸሎተ ፍትሐትና ተዝካር የመሳሰሉት ታከናውናለች። ፍትሐት ማለት ፈትሐ ከሚለው የግእዝ
ግስ የወጣ ሲሆን መፍታት፡ ማስለቀቅ ማለት ነው። ተዝካር ደግሞ ተዘከረ ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ ሲሆን ማስታወሻ
ማለት ነው። ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ልጆቿ በሕይወተ ስጋ ሲሞቱባት በድለው ከሆነ ብላ የፍትሐት ጸሎት ታደርጋለች
እንዲሁም ከክርስቲያኖች ኅበረት እንዳልተለዩ ስትገልጽ በቅዳሴ ጊዜ ስም እየጠራች፡ በእነሱ ስም ምጽዋት እየሰጠች
ያረፉትን ታስታውሳቸዋለች።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ለምን ሰው ከሞተ በኋላ ጸሎተ ፍትሐት ወይም ተዝካር ይደረግለታል ቢሉ?
1) እግዚአብሔር ቸርና መሐሪ ስለሆነ የሞተው ሰው በደለኛ ቢሆንም ከእርስ በርስ ፍቅር አንጻር በአሁኑ ፍርድ ሆነ በዳግም
ምጽአት እንዲምረው ለመለመን ነው።
ለምሳሌ፡ ሙሴ ከእሱ 100 ዓመት በፊት ለሞተው ለያዕቆብ ልጅ ሮቤል ከአምላክ ዘንድ ምሕረት እንዲያገኝ ለምኗል። ይህም
ሮቤል በሕይወተ ስጋ እያለ ከአባቱ ሚስት ጋር ዝሙት በመፈጸሙ እስራኤላውያን ከግብጽ ሲወጡ ከ 12 ቱ ልጆች አጽም
የእሱ ተለይቶ በመጥቆሩ ነበር። (ዘዳ 33፥6)
እንዲሁም ቅዱስ ጳውሎስ ብዙ አገልግሎት በኋላም በሞት ለተለየው ለሄኔሲፎሩ በዳግም ምጽአት ጊዜ ምሕረት እንዲያገኝ
ለምኗል። (1 ጢሞ 1፥16)
2፡ የቤተ ክርስቲያን ባህርይዋ የሚገጽበት ስለሆነ
ቤተ ክርስቲያን ሲባል ብዙ ትርጉም ቢኖሩትም ከእነሱ ውስጥ የክርስቲያኖች አንድነት ይግኝበታል። ይህም አንድነት ልዩ ነው
ምክንያቱም በውስጡ በዘመን፡ በቦታ፡ በእድሜ እና በመሳሰሉት የሚለያዩ ሰዎች ስብስብ ስለሆነ ነው። ለዚህም አንድነት ራስ
የሆነው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን ብልቶቹ ደግሞ እኛ ነን። "አካልም አንድ እንደ ሆነ ብዙም ብልቶች እንዳሉበት ነገር
ግን የአካል ብልቶች ሁሉ ብዙዎች ሳሉ አንድ አካል እንደ ሆኑ፥ ክርስቶስ ደግሞ እንዲሁ ነው፤" (1 ኛ ቆሮ 12:12፤) እንዲል
ቅዱስ ጳውሎስ። በመሆኑም አንድ ሰው በሕይወተ ስጋ ስለሞተ ብቻ ከዚህ አንድነት አይለይም ይልቁንም በመንፈሳዊው
ዓለም ውስጥ ካሉት ጋር ተርታ ተሰልፎ አንድነቱን ያጠነክራል። በመሆኑም ጸሎተ ፍትሐት ይህን አንድነት ከሚሰብኩ
ጸሎቶች አንዱ ነው፡፡ ምክንያቱም ላረፉ ወገኖቻችች ስንጸልይ ምሕረትን ለመለመን ብቻ ሳይሆን የራሳችን አካል ናቸውና
እነሱን ማሰብ፡ መዘከር ተአጥሮአዊ ስለሆነም ጭምር ነውና።
3፡ ከሞት በኋላ ሊሰረይ የሚችል ኃጢአት ስላለ ነው።
በወንጌል "በሰው ልጅ ላይ ቃል የሚናገር ሁሉ ይሰረይለታል፤ በመንፈስ ቅዱስ ላይ ግን የሚናገር ሁሉ በዚህ ዓለም ቢሆን
ወይም በሚመጣው አይሰረይለትም።" (ማቴ 12:32፤) ተብሎ እንደተጻፈ በዛኛው ዓለም ይቅር የሚባል ኃጢአት እንዳለ
እናውቃለን። ይህም ከሞት በኋላ ንስሐ አለ ማለት ሳይሆን በሕይወተ ስጋ ያሉትና በቅዱሳኑ ምልጃ ምክንያት የሚመጣ
ስርየት ነው።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ሕይወት ዘመኑን በሙሉ በኃጢአት ኖሮ በጸሎተ ፍትሐት ምሕረትን አገኛለሁ የሚል ፈጽሞ ተሳስቷል።
ምክንያቱም ይህ ጸሎት ተግባራዊ የሚሆነው በንስሐ ሕይወት ለሚመላለሱና በኑሮዋቸው እንደየአቅማቸው ተጋድሎ
ለሚያደርጉ ነው።
በመጨረሻም ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ "በዚህ በሚደረግለት ጸሎትና ቁርባን እንዲሁም ምጽዋት ያረፈው ሰው ጥቅም
እንደሚያገኝ አትጠራጠር" ሲል ይመክረናል።
ምንጭ፡ መድሎተ ጽድቅ (ዲ/ን ያረጋል አበጋዝ)
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
የድንግል ማርያም ልጅ፣ የእግዚአብሔር ልጅ እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ማስተዋልና ጥበቡን ያድለን::
ከላይ በቀረበው ምሳሌ መሠረት የ"ተ" ቤተሰብ የሆኑት:-
ተቱቲታቴትቶ
ሲሆኑ "ተ" ማለት ከላይ በምሳሌ እንደተመለከትነው እግዚአብሔር አምላክ ለአዳም በሰጠው የተስፋ ቃልኪዳን መሠርት
ጊዜው ደረሰና የሚወደውን አንድያ ልጁን ከሦስቱ ቅዱስ አንዱ ቅዱስ ከሦስቱ አካል አንዱ አካል የሆነውን ጌታችንና
አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መለኮታዊ የሆነ በፍጹም ተዋህዶ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም
ከሥጋዋ ሥጋን ከነፍሷ ነፍስን ነስቶ ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው የሆነበትን ምሥጢር ወይም ምሥጢረ ሥጋዌን ያመሣጥል
ፊደል "ተ":: "ቃል ሥጋ ሆነ በእኛም አደረ " (ዮሐ 1:14) "የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ልጁን ላከ ከሴትም
(ከድንግል ማርያም) ተወለደ" (ገላ 4:4) በዚህም መሠረት "ተ" ፊደል የሚወክለው ወይም የሚያመሣጥረው "ተሰብአ
ወትሰገወ፣ አምላክ ሰው ሆነ" የሚለውን ነው::
ታድያ አምላክ ሰው መሆንን እና "ተ" ፊደልን ምን አገናኛቸው? የሚል ጥያቄ ሊነሳ ይችላል:: ይህንን ጥያቄ ለመመልስ የ"ተ"
ፊደል ቅርጽን ልብ ብለን ማስተዋል ይገባናል:: የ"ተ" ፊደል ቅርጽ ሁለት ነገሮች የተመሳቀሉ የሚመስሉ ማለትም የላይኛው
ክፍል አጠር ያለ፣ የታችኛው ደግሞ ርዘም ያለ፣ እንዲሁም በግራና በቀኝ የተቀመጡት አግድም ክፍሎች እኩል የሆኑ ሲሆን
ለዚህም ነው ሁለት እጁን የዘረጋ የሰው ልጅ ምስልን ወይም ቅርጽን ይወክላል ወይም ይመስላል የተባለው"ተ" ፊደል::
በዚህም መሠረት "ተ" ፊደልን አባቶች "ተሰብአ ወተሰግወ፣ አምላክ ሰው ሆነ" ብለው ያመሠጥራሉ::
"ተ" ፊደል ይህን ያህል ከዳሰስን የ"ተ" ቤተሰብ የሆነውን "ቶ" ፊደልን እንደሚከተለው እንመለከታለን::
በቅድሚያ የ"ቶ" ፊደል ቅርጽን ልብ ብለን ልናስትውል ይገባል:: እንደምንመለከው "ቶ" ከ"ተ" ፊደል አናት ላይ ክብ (o)
ተቀጥሎበት "ቶ" ቅርጽን ይሰጣል:: በዚህም መሠረት በመጀመሪያ "ተ" የነበረው ፊደል በመጨረሻም ወደ "ቶ" ፊደል
ይቀየራል:: "ቶ" ፊደል የሚመስለውም የሰው ቅርጽን ይዞ ከላይ ያለው ክቡ ነገር የሰው ልጅ የራስ ክፍል ወይም የራስ ቅልን
የሚመስል ሲሆን ሌላው የፊደሉ አካል ግን ከ"ተ" ጋር አንድ ዓይነት ነው:: ስለዚህ "ቶ" ፊደል ሁለት እጆቹ በመስቀል ቅርጽ
የተዘረጉ እንዲሁም በራሱ ላይ ደግሞ ክብ ነገርን ወይም አክሊልን የደፋ የሰው ልጅ ምስልን (ቅርጽን) ይዟል:: በዚህም
መሠረት "ቶ" ፊደል ክርስ"ቶ"ስን የሚወክል ሲሆን ምንም በደል የሌለበት ጌታችንና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ አዳምንና
ልጆቹን ከወደቁበት የኃጢአት መርገም ለማዳን ሲል በመስቀል ላይ የፈጸመውን ዋጋ ያመሣጥርልናል፣ ያሳየናል፣
ያስተምረናልም "ቶ"::
ጥያቄ፡
ለምንድነው ስንጸልይ ወደ ምሥራቅ ማየት ያለብን?
መልስ፡
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖታችን ቤተክርስቲያን የምትታነጸው ምስራቁን አቅጣጫ ጠብቃ ነው እንዲሁም
ከቤተክርስቲያኑ ጋር አብሮ የሚሰራው ቤተልሔም በስተምስራቅ በኩል ይደረጋል፡ በጸሎት ሰዓትም ወደ ምስራቅ ዞረን ነው
የምንጸልየው፡ በሥርዓተ ቀብር ላይም የሞተ ሰው ሲቀበር ራሱ ወደ ምዕራብ እግሩ ወደ ምስራቅ ሆኖ ይቀበራል ፡፡
ሌላው ዲይቆኑ በሥርዓተ ቅዳሴው ላይ ወደ” ነጽሩ ውስተ ጽባሕ ምስራቅ ተመልከቱ” ይላል። ምክንያቱ ደግሞ፡
ይህች ርስታችን በአዳም በደል ምክንያት በኪሩቤል ሰይፍ ተዘግታ ስትኖር ሞትን ድል አድርጎ በበደልን ክሶ ጌታችን
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሞቱ ከፈተልን። (ሉቃ. 23፥4)
ወደ ምስራቅ በተመለከትን ቁጥር ወደ ገነት ለመግባት የተሰጠን ተስፋ ትዝ ይለናል የተከፈተችውም ቤታችን ገነት በእምነት
ወለል ብላ ትታየናለች በክርስቶስ ያገኘነውን ጸጋ እናስባለን ምድራውያን አለመሆናችንም ይታወሰነል።
2• ጌታ የተወለደው በምስራቅ ነው።
ሰብአ ሰገል ኮከቡን ያዩት በምስራቅ ሲሆን ያ ኮከብ የምሕረተ እግዚአብሔር ምሳሌ ነው። እነርሱን ወደ እግዚአብሔር
እንዳደረሳቸው ሁሉ እኛንም ወደ ለመለመው መስክ ይመራናል። ማቴ 2፥2 መዝ 22፥14
ወደ ምስራቅ በተመለከትን ቁጥር የጌታ መወለድ እና ያደረገልን ውለታ ይታወሰናል የምሕረቱ ኮከብ እየመራን መሆኑ ትዝ
ይለናል።
3• ፦ ምስራቅ የእመቤታችን ምሳሌ ነው።
ከምስራቅ ጨለማውን የሚገፈው ፀሐይ እንደሚወጣ ሁሉ ከእመቤታችን ከድንግል ማርያምም የዓለምን የኃጢአት ጨለማ
የሚገፍ ፀሐዬ ጽድቅ ኢየሱስ ክርስቶስ ተገኝቷል፡፡ "ለእናንተ ስሜን ለምትፈሩ የፅድቅ ፀሐይ ትወጣላችሁለች" ሚል 4፥1
ሕዝ 44፥1፦4 ነብዩ ሕዝቅኤልም እመቤታችንን ያያት በምስራቅ ነው ስለዚህ ወደ ምስራቅ በተመለከተ ቁጥር እመቤታችን
ትዝ ትለናለች የጽድቅ ፀሐይ ክርስቶስ ስለተወለደልን በጨለማ አለመሆናችን ትዝ እያለን ከኃጢአት እንርቃለን።
ጌታ የተሰቀለው እና ዓለምን ያዳነው በምስራቅ ነው ኢየሩሳሌም ምስራቃዊት ከተማ ናት እና በመሆኑን ወደ ምስራቅ በዞርን
ቁጥር የተሰቀለውን ክርስቶስን እና የተከፈለልንን ዋጋ እናስባለን።
5• ፦ክርስትናና ቤተክርስቲያን የተመሰረቱት በምስራቅ ነው።
የመጀመሪያው ቤተክርስቲያን የተመሰረተው ኢየሩሳሌም ሲሆን ወንጌል የተሰበከውም ከዚሁ በመነሳት ነው ።ስለዚህ
ወደምስራቅ ስንዞር የቤተክርስቲያን ጉዞ የወንጌል መስፍፍት እና የሕዝበ ዓለም መዳን ትዝ ይለናል።
ኢሳ 28:13 እግዚአብሔርን በምስራቅ የእስራኤልንም አምላክ የእግዚአብሔርን ስም በባሕር ደሴቶች አክብሩ ት.ሕዝ 43፦2
የእስራኤል አምላክ ክብር ከምስራቅ መንገድ መጣ።
ዘካ 14፥14 በዚያን ቀን እግሮቹ ኢየሩሳሌም ትይዩ በምስራቅ በኩል ይቆማሉ ሐዋ 1፦11 ይህ ከእናንተ ወደሰማይ የወጣው
ኢየሱስ ወደሰማይ ሲርግ እዳያችሁት እንዲሁ ይመጣል ።
8• ፦ቅዱሳን አበው ሲጸልዩ ወደ ምስራቅ ይዞሩ ነበር።
ዳን 6፥ወደ ኢየሩሳሌም ያለውን መስኮት ከፍቶ ይጸልይ ነበረ ነብዩ ዳንኤል እግዚአብሔር ምሉዕ በኩልሄ (የሌለበት ቦታ የሌለ)
መሆኑን ያውቃል።
9• ፦ታቦቱ በምስራቅ በኩል ባለው ቤተ መቅደስ አስቀምጠን ስጋወ ደሙ የሚፈተተው ጌታ በምስራቅ ሀገር ጎለጎታ ለኛ
ስጋውን መቁረሱ ደሙን ማፍሰሱበማሰብ ነው
10• ፦በሥርዓተ ቅዳሴ ላይ ዲያቆኑ ወደ ምስራቅ ተመልከቱ በምስራቅ የተደረገልንን ውለታ የተከፈለልንን ዋጋ ከድንግል
ማርያም ከሆነችው እመቤታችን የተገኘውን ፀሐየ ፅድቅ ኢየሱስ ክርስቶስን አስቡ ማለቱ ነው ።
11• ፦ በቀብር ሥነ-ሥርዓት የአስከሬኑን ፊት ወደ ምስራቅ የሚዞርበት ምክንያት በዳግም ምጽአት በሚነሳበት ጊዜ ፊቱን
ወደ ጌታ እንዲያዞር እና እንዲመለከት በማስብ ነው ።
እንግዲህ ወደምስራቅ መዞር የክርስቶስን የማዳን ስራ የቅዱሳንን ሕይወት የሰማዕታትን ገድል የክርስቲያንን ተስፈ
የሚያሳስበን ነው እና ወደ ምስራቅ እንዞራለን ይህንን ሥርዓት ያስተማሩን ቅዱሳን አበው በረከታቸው ይደርብን።
ምንጭ፡ ሐመረ ኖኅ ድረ ገጽ
ወስብሐት ከእግዚአብሔር!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለ መስቀሉ ክቡርበስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
ጥያቄ (6-2)
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰጋዬን ብሉ ደሜን ጠጡ ብሉ የሰጠበት ምክንያት ምንድን ነው?
መልስ፡
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምድር ላይ 33 ዓመት ከ 3 ወር ከተመላለሰ በኋላ በምሴተ ኀሙስ ለሐዋርያት
የዘለዓለምን ሕይወት እንዲያገኙ በሕጽበተ እግር ካጠመቃቸው በኋላ ስጋውንና ደሙን ሰቷቸዋል።
ይህም ቍርባን የሚያስገኘው ጥቅም
(1) የሕይወትን ምግብ እና ዘለዓለማዊ ሕይወትን ያስገኛል።
"ኢየሱስም እንዲህ አላቸው። የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ፤ ወደ እኔ የሚመጣ ከቶ አይራብም በእኔ የሚያምንም ሁልጊዜ ከቶ
አይጠማም። ... "54፤ ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው፥"
(ዮሐ 6:35-54)
(2) ሥርየተ ኃጢአትን
"ስለ ብዙዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው።" (ማቴ 26:28፤)
(3) ከክርስቶስ ጋር አንድ መሆንን
"ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ በእኔ ይኖራል እኔም በእርሱ እኖራለሁ።" (ዮሐ 6:56፤)
(4) እርስ በርስ በፍቅር መተሳሰርን
"የምንባርከው የበረከት ጽዋ ከክርስቶስ ደም ጋር ኅብረት ያለው አይደለምን? የምንቆርሰውስ እንጀራ ከክርስቶስ ሥጋ ጋር
ኅብረት ያለው አይደለምን?
አንድ እንጀራ ስለ ሆነ፥ እኛ ብዙዎች ስንሆን አንድ ሥጋ ነን፤ ሁላችን ያን አንዱን እንጀራ እንካፈላለንና።" (1 ኛ ቆሮ
10፥16-17)
ይህ በእንዲህ እንዳለ ታዲያ ለምን በምግብ መልክ መስጠት አስፈለገ ቢሉ?
(1) በምግብ የመጣውን በደል በምግብ ለማጥፋት አዳምና ሔዋን አትብሉ የተባሉትን ዕፀ በለስ በልተው እንደወደቁ ሁሉ እኛ
ደግሞ የክርስቶስ ስጋና ደም እየተመገብን ከወደቅንበት እንነሳለን።
(2) ምግብ ከሰውነት ይዋሃዳል። እኛም ስጋና ደሙን ስንቀበል ከላይ እንደገለጽነው ከክርስቶስ ጋር አንድ እንሆናለን።
(3) መብል መጠጥ ያፋቅራል፡፡ እንደዚሁም የክርስቶስ ስጋና ደምም በፍቅር የተሞላን አድርጎን እርስ በርስ ያፋቅረናል።
ምንጭ፡ ትምህርተ ሃይማኖት ጥራዝ /ዘኆኅተ ብርሃን/
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
የፊደል ገበታ
እንጠይቅ ታምሯን
፦ዮሐ ፦2 ፥1-11
፦ሉቃ ፦1 ፥ --
እንጠይቅ ስለሷ እውነታው ያልገባችሁ
ከምትናገሩ እንደመጣላችሁ
አበዉን እንጠይቅ ይንገሩን ባካችሁ ።
ብዙ አባቶች አሉ የለበሱ ፍቅሯን እነሱን እንጠይቅ የንገሩን ታምሯን ።
ታምራቱዋን ያየው የተደረገለት
ዶኪማስ ይመስክር ይናገር ስለ እውነት ፦
በዛ በሰረጉ ቤት ቃና ዘገሊላ
ሰርገኛዉ ታድሞ ሲጠጣ ሲበላ ፦
ድንገት በመሀከል ወይኑ በመጥፋቱ
ዶኪማስ ተጨንቆ ሲርድ ሰዉነቱ
የነበረው ደስታ ሁሉም ሲሆን ከንቱ
መቋቋም አቅቶት ሲዝል ጉልበቱ
ተዋረድኩኝ ብሎ ሲታየዉ ሽንፈቱ
እማምላክ አንብባ ጭንቀቱን ከፊቱ ።
እሩህሩህ ናትና እናቴ አዛኚቱ
የዶኪማስ ጭንቀት ሀዘኑ እንዲፈታ
ድንግል ልታማልድ ሄደች ወደ ጌታ
ተዓምር የሚያደርግ ስላላት ቃልኪዳን
"ወይንኪ ዓልቦሙ "አለችው ልጇን ።
ልጇም ሰማና የናቱን ልመና
ውሃውን ቀየረዉ ወደ ወይን ቃና ።
ትናገር ኤልሳቤጥ ትመስክር ታምሯን
የሰላምታዋን ቃል ስትሰማዉ ድምጿን
በምንፈስ ተሞልታ ለክብሯ መስገዷን
በማሕፀኗ ያለዉን ፅንስ ማዘለሏን ።
ልቧ ሀሴት አርጎ መጮኋን በደስታ
ፅንሱም እደዘለለ በድንግል ሰላምታ ።
ምድራዉያንን እኛን ወክላ
ለክብሯ ሰገደች "ሰላም ለኪ "ብላ
ሰማያዉያንን ሁሉ ወክሎ
ገብረኤል አበሰራት" ሰላም ለኪ "ብሎ
ታደያ በኛም ዘመን አሁን ባለንበት
የድንግል ተዓምር በሚገለጥበት
ዓለም በምልጃዋ ድህነት ባገኝበት
ታድያ ለምን ካዱ ጠፋባቸው እውነት ።
አይናቸው እያየ ገድል ታምራቷን
ጆሮአቸውም ሰምቶ ሙታን ማስነሳቱዋን
ታድያ ለምን ይሆን ሰው ናት ማልታቸዉ
ስላልተፃፈ እንጂ ፍቅሯ በልባቸው ።
ከዚህ ሓጥያት ለመዉጣት ለመቅመስ ፍቅሯን
እንጠይቅ ስለሷ ይንገሩን ታምሯን ።
እውነትን ተማሩ ግቡ ወደ በረቱ
የእውነት አማላጅ ናት ድንግል አዛኚቱ ።
እውነት አለቀሰች
እኔ እመረቃለሁ
እንጠይቅ ተዓምሯን
፦ዮሐ ፦2 ፥1-11
፦ሉቃ ፦1 ፥ --
እንጠይቅ ስለሷ እውነታው ያልገባችሁ
ከምትናገሩ እንደመጣላችሁ
አበዉን እንጠይቅ ይንገሩን ባካችሁ ።
ብዙ አባቶች አሉ የለበሱ ፍቅሯን እነሱን እንጠይቅ የንገሩን ታምሯን ።
ታምራቱዋን ያየው የተደረገለት
ዶኪማስ ይመስክር ይናገር ስለ እውነት ፦
በዛ በሰረጉ ቤት ቃና ዘገሊላ
ሰርገኛዉ ታድሞ ሲጠጣ ሲበላ ፦
ድንገት በመሀከል ወይኑ በመጥፋቱ
ዶኪማስ ተጨንቆ ሲርድ ሰዉነቱ
የነበረው ደስታ ሁሉም ሲሆን ከንቱ
መቋቋም አቅቶት ሲዝል ጉልበቱ
ተዋረድኩኝ ብሎ ሲታየዉ ሽንፈቱ
እማምላክ አንብባ ጭንቀቱን ከፊቱ ።
እሩህሩህ ናትና እናቴ አዛኚቱ
የዶኪማስ ጭንቀት ሀዘኑ እንዲፈታ
ድንግል ልታማልድ ሄደች ወደ ጌታ
ተዓምር የሚያደርግ ስላላት ቃልኪዳን
"ወይንኪ ዓልቦሙ "አለችው ልጇን ።
ልጇም ሰማና የናቱን ልመና
ውሃውን ቀየረዉ ወደ ወይን ቃና ።
ትናገር ኤልሳቤጥ ትመስክር ታምሯን
የሰላምታዋን ቃል ስትሰማዉ ድምጿን
በምንፈስ ተሞልታ ለክብሯ መስገዷን
በማሕፀኗ ያለዉን ፅንስ ማዘለሏን ።
ልቧ ሀሴት አርጎ መጮኋን በደስታ
ፅንሱም እደዘለለ በድንግል ሰላምታ ።
ምድራዉያንን እኛን ወክላ
ለክብሯ ሰገደች "ሰላም ለኪ "ብላ
ሰማያዉያንን ሁሉ ወክሎ
ገብረኤል አበሰራት" ሰላም ለኪ "ብሎ
ታደያ በኛም ዘመን አሁን ባለንበት
የድንግል ተዓምር በሚገለጥበት
ዓለም በምልጃዋ ድህነት ባገኝበት
ታድያ ለምን ካዱ ጠፋባቸው እውነት ።
አይናቸው እያየ ገድል ታምራቷን
ጆሮአቸውም ሰምቶ ሙታን ማስነሳቱዋን
ታድያ ለምን ይሆን ሰው ናት ማልታቸዉ
ስላልተፃፈ እንጂ ፍቅሯ በልባቸው ።
ከዚህ ሓጥያት ለመዉጣት ለመቅመስ ፍቅሯን
እንጠይቅ ስለሷ ይንገሩን ታምሯን ።
እውነትን ተማሩ ግቡ ወደ በረቱ
የእውነት አማላጅ ናት ድንግል አዛኚቱ ።
አቃጥሏት ግድ የለም
የታወረ ትውልድ
ፍቅር ማለት
ያን ሁሉ መስዋእት ያን ሁሉ ግርፋት
ልጅን ከአባት ጋር አባትን ከልጅ ጋር
አስታርቆ ለማየት ፤
እኔ ያያ ሰው ነኝ የከበረ ዋጋ የተከፈለበት
እኔ ያ. ሰው ነኝ በደሙ ታጥቤ ነፃ የሆንኩበት ፤
ታድያ ለዚህ ከንቱ አለም ላልወደደው
በትንሽነቱ ሰው ሁሉ ለናቀው ፤
እንዴትስ ተገብቶት ጌታ ሊሞትለት
እንዴትስ ተደርጎ ክብሩን ሊተውለት ፤
ይህ ፍጡር ማን ቢሆን ነው ከቶ
የሰማዩ ንጉሥ ግዛቱን አስትቶ
በሀጥያቷ ክርፋት ወደ ገማች ምድር
ጠርቶና ጎትቶ ፤ሞትን ያቀመሰው የትኛው ፍቅር ነው
የቱ ቅድስና የቱ ማንነቴ የቱ ንፅህና ፤
ንፁህ የሆነውን ፅድቅ የለበሰውን
ስጋ ያለበሰው ሀጥያት ያደረገው
የቱ እኔነቴ እሱነቱን ትቶ እንዲያ
ሚያዋርደው ? ፤
ያንን ፍቅራማ ቃላት ተቆፍረው
ያንን መውደድማ ፊደላት ተጣምረው ፤
ከቶ አይገልፁትም ፍፁም አይደርሱትም
ብርሀን አያደምቀው ጨለማ አይጋርደው
የቀናት መገስገስ የአመታት መንጎድ
ዘመን የማይሽረው ፤
ፍ ቅ ር ማለት ያ ያ ነው
ፍቅር ውልደቱ ነው ፍቅር መከራው ነው
ፍቅር መሞቱ ነውፍቅር ትንሳኤው ነው ፤
በዘመን ጅማሬ በዘመን ፍፃሜም
የፍቅር ስንኙ የፍቅር ሀረጉ
እ የ ሱ ስ ብቻ ነው !
______________________
የአምላክ መገኛ
ተዋህዶ አትፈርስም
መስከረም ሲታጠን
ከብሶት አድማስ ሥር - ከጽልመቱ ማዶ - የብርሃን ጎህ ሲቀድ፣
በሃይማኖት ፍቅር - ሀገር ልቡ ነዶ - ፍርሐት ሲቀረደድ፣
የእማትን ልቅሶ - የአበውን እንባ - የውርዛዌን ወኔ፣
የአንድነትን እርሾ - የአትንኩንን ካባ - የፍትሕን ጠኔ፣
ከእግዚኦታው ማዕድ - ከካህናቱ ዕድ - ይህን ኹሉ ይዞ፣
ዕጣኑ ዐረገ - ወጣ ወደ ሰማይ - ሺ ጸሎት አርግዞ።
በታደለች ሰንበት - ዣን ተከል ሥር ያለው - ወዲህም ከጦሳ፣
በሃይማኖት እሳት - ልቡ የተቃጠለው - የመንፈሱን እንጂ - የምድሩን ቢረሳ፣
ይግባኙን ወደ ላይ - በእግዚኦታ ሊያደርስ - በአንድነት ሲነሣ፣
ምድር ሰማይ ሆነች - ሰውም መልአክ ሆነ - ግዙፋን ረቀቁ፣
ሰላማዊ ብለው - በሰማያዊ ሰልፍ - ከሰማይ ታረቁ።
በዚህችስ ሰንበት - ግዙፍ አይደለች ምድር - አፈርም የለባት፣
ከኢዮር ከኤረር - ከራማ የተለየ - ምንስ ተሠራባት?
በዚህችስ ሰንበት.....
የመላእክት ሀገር - ኢዮር ኤረርና - ራማ ብቻ አይደሉ፣
ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ - መሐረነ ክርስቶስ - እግዚኦ እያሉ፣
ማዕጠንቱን ይዘው - ጎንደርና ወሎም - ለሦስቱ ሰማያት - ራብዓይ ሆነው ዋሉ።
እኛስ የምናውቀው - በዕለተ መልአኩ - በ 12 ኛው ቀን - ኅዳር ሲታጠን ነው፣
ሀገር መልአክ ኾኖ - በ 12 ኛ ዓመት (2012) - ወሎና ጎንደር ላይ -መስክዬን አጠነው።
መስከረም ሲታጠን...
ከልቡና ደጃፍ - ብሔር ሚሉት ዕድፍ፣
በማዕጠንት ምድጃ - ተጠርጎ ሲራገፍ፣
ጎጥ ሚሉት ቆሻሻ - ዘር የሚሉት ትቢያ፣
ነዶ ሲቀጣጠል - በፍቅር ማራገቢያ፤
መስከረም ሲታጠን - ከኦርቶዶክስ አድማስ ሥር፣
የምድሩ ያየሩ - የሲዖሉ ጋኔን - በጢሱ ሲታወር፣
ወዶ የታወረው - የጋኔኑ ቢጤም - ተባሉ ተጣሉን - በትግኃት ሲዘክር፣
ይህን ለመመስከር - አላየሁ አልሰማሁ - ብሎ ሲግደረደር፣
ያደለው ዐይናማ - የመላእክቱን ዐይን - ዐይኑ ያደረገ
ከሰልፈኞቹ ጋር - ያየውን መስክሮ - በክብር ዐረገ።
መስከረም ሲታጠን....
የተስፋ ብርሃን - በአቅሌስያ ደጃፍ - ጭል ጭል እያለ፣
የበሯ ላይ ጽልመት - በአንድነቱ ክንድ - የሚናድ መሰለ።
መስከረም ሲታጠን - የዕጣኑ መዓዛ - ደቡብ ላይም ሔደ፣
ሰሜንና ምሥራቅ - ምዕራብ ላይም ሔደ፣
ለሃይማኖት የመሞት - ሰማዕት የመሆን - ጥብዓት እያወደ።
መስከረም ሲታጠን....
ጥቅምትና ኅዳር - ታኅሣሥና ጥር - መጋቢት ሚያዝያም - ፈክተው ይውላሉ፣
ቤተ ክርስቲያን ሆይ - ክረምትሽ አለፈ - በጋ ነው እያሉ።
ብዙ ልጆች አሉት
ለካስ ዛሬም አለ
ትዕቢት ያጀገነው
ራሱን መውደዱ ልቡን ያሳበጠው
አምላኩን ለመግደል ሰይፍ የመዠረጠው
እንደ ነዳጅ ረግጦ ሰይጣን 'ሚሾፍረው
የጋኔን መኪና ሄሮድስ የተባለ
144 ሺህ ጠርቶ የገደለ
ለካስ ዛሬም አለ።
ጳውሎስ ቃል ሲያወጣ ጴጥሮስም ሲፈውስ
'ግደል' የሚል ጋኔን ከአንጀቱ ተጣብቆ ክፋቱ 'ሚላወስ
ከነገሥታት መኻል ኔሮን የተባለ ነበረ አንድ ቀውስ።
የስንቱን ከተማ መኖሪያ አቃጠለ
አንዱን በሰይፍ ጣለ
በእንጨት ላይ ዘቅዝቆ አንዱንም ሰቀለ።
ለካስ ንጉሥ ኔሮን ዛሬም ሰይፉን ስሏል
ዘቅዝቆ የመስቀሉ ሥራውም ቀጥሏል
መቅደሱን አቃጥሎ እሳቱንም ሞቋል
እንደ በቆሎ እሸት የሰው አካል ጠብሷል
ለካስ ዛሬም ኖሯል!
በቅድስቲቱ አገር ባገሬ በ'ማማ
ከጥንት ግፍ መኻል ምን አለ ያልተሰማ?
መንኮራኩር ሠርቶ አካል የሚፈጨው
የሰው አካል ገፎ የሚነሰንስ ጨው
ከአንበሳ 'ሚያታግል
በዕብን ወግሮ 'ሚገ'ል
በቁም አሥሮ 'ሚያነድድ
ቆዳ 'ሚቀረድድ
እንደ ጥንቱ ኔሮ
እልፍ ነው ዘንድሮ።
ግራኝ ግብሩ አልሞተም ሕያው ነች ዮዲትም
መቅደስ ሚያነድና ካህንን የሚሰድ አይታጣም የትም።
የነ ሜንዴዝ እሾኽ መቼ ተነቀለ?
ይኸው አመርቅዞ ስንት አማኝ ገደለ።
በአየር ላይ በሮ መርዙን የረጨብን ጥልያን መች ጠፋ
መርዝ የሚያዘንብ ኪይ ቦርድ በዘመኑ አየር ቀጥሏል ቀጠፋ።
እነ ሄሮድስ አሉ
እነ ኔሮን አሉ
እነ ግራኝ አሉ
እነ ዮዲት አሉ
ድምጥያኖስ አለ ዲዮቅልጥያኖስ
የጋኔን ቀኝ እጅ የዲያቢሎስ በርኖስ::
መክስምያኖስ አለ አማኝ እየቀጣ
ቆስጠንጢኖስ 'ሚባል ንጉሥ እስኪመጣ
በስመ ሥላሴ
በክርስቶስ ፍቅር በስመ ስላሴ፤
ከእግሬ በርከክ ብዬ ዝቅ ብዬ ከራሴ።c
በወልድ ሀብተ ወልድ በድንግል ተዋህዶ፤
በክርስቶስ ክርስትያን ያ’ረጋችሁ ፈቅዶ።
በሰማታት አማንያን የተሰኛችሁ፤
ወልደና ወለተ ይህ ድምፅ ሚሰማችሁ፤
እንደምን ከረማችሁ? እንደምን ሰነበታችሁ?
እንደምንስ እስከዚች ሰአት ደረሳችሁ?
አሜን አልፋና ኦሜጋ የሰራዊት ጌታ፣
ይመስገን በፍጥረት ከጥኋት እስከ ማታ።
አምላክ ሲመሰገን ሁሌም በባህሪ፣
ለአዳም ዘር በሙሉ የሆነች ተጠሪ፣
ሁል ጊዜም ከቀኙ አትለይም እና፣
ከፍጥረት ይድረሳት የፀጋ ምስጋና።
መላእክት ሰማታት ፃድቃናት በሙሉ፤
ስላዳም ዘር ድነት በመማፀን ያሉ፤
መርጦ ለኛ ድነት ፀጋ ያደላቸው፤
ሁሌም ይመስገኑ እንደዬ ክብራቸው።
ቃል ነበረ
ጨረቃ ክዋክብት ፀሀይ እና ምድር፤
መላእክት ሰማእታት ስነ-ፍጥረት ሳይኖር፤
አልፋ እና ኦሜጋ የማይመረመር፤
የሁሉ መሰረት ያን ጊዜ ቃል ነበር።
ምድርና ሰማይን በአንድ ቀን ፈጠረ፤
ደግሞም ለአምስት ቀናት ሌሎችን ጨመረ፤
እንደየ አይነቱ ሁሉን አሳመረ፤
*:ጊዜ ምን በደለ;*
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
እውነትን ደብቀን ሀሰትን አንግሰን
አባቶች እያሉ ልጆች እያስተማርን
አርብ እሮቡን ሳናውቅ ሁልጊዜ አየበላን
ቤቱ መመላለስ ጭራሹን አቁመን
*
*
የእግዛብሔርን መቅደስ በሀጢያት ስንሞላ
እንደሰዶም ሆነን ህግን ስንጠላ
አህዛቦች ሲቀድሙን እኛ ቁመን ሇላ
ፀጋችን እያለ እሱን ሳናውቅበት ስንፈልግ ሌላ
*
*
የምንጓዝበት መንገዱ ረዝሞብን ቤቱ መሄድ ሲቀር
ሀይማኖት በገንዘብ እንደስም ሲቀየር
መፅሀፍትን ሳናነብ አባቶች እግር ስር ቁጭ ብለን ሳንማር
ቅዱስ ሁኑ ተብለን ምርጫችን ሲቀየር
*
*
ውበት ከአምላክ በላይ እኛ ስንሰራ
ቀለም እያማረጥን አለምን ስንመርጥ አምላክን ሳንፈራ
ማህሌት አዳር ትተን ስንመርጥ ጭፈራ
ሀብታችን ሀጢያት ገዝቶ ሲያስመስል ተራራ
*
*
ልብሳችንን ጥለን እርቃንን ስንመርጥ
በማናውቀው አለም ከላይ ሁነን ሳለ ወደ ታች ሰንዘቅጥ
አማርጠን ስንበላ ከደረቅ እስከ ቁርጥ
በደካማው ስጋ ለነፍሳችን ስንቅ ጭራሽ ሳናስቀምጥ
*
*
አወቀን ብለን ሳናውቅ በትቢት እየተጓዝን
ምርጫችን ከኛ በልጦ እኛኑ ሲመክረን
አልመለስ ስንል አምላክ እላይ ሁኖ በትዝብት ሲያዩን
ፍርጃ እላይ ቆመን ጌታ ሊመዝነን
እኛ ከሱ በልጠን ጭራሽ ፈራጅ ሁነን
*
*
ክፋትን አንግሰን ጠፋቶብን በጎነት
የውጩን አድንቀን ስንጓዝ በስህተት
ምርጫችን ተምታትቶ ስናማርጥ ውሸት
ሚስጥሩን ሳናውቀው ለመፋረድ ስንዋትት
*
*
በል በትርርህን አፅና የሚባል ሲጠፋ
መገንዘብ ሲያቅተን ምንድነን እንደሆነ የወደፊት ተስፋ
በማይጠቅም ህይወት ስንማስን ስንለፋ
ማወቁ ሲጠፋን ሁሉም ሟች መሆኑን ጠብቆ ወረፋ
*
መቶ ለማይሞላው ለዚህ አጭር እድሜችን
ምን ለማይጠቅመው እንጨነቃለን ለአፈሩ ስጋችን
አድሜአችን ሲቀንስ ከግባራችን ሲለቅ ፀጉራችን
መመለስ ሲያቅተን ዛሬ ነገ እያልን ሲመርሽ ቀናችን
*
አባቶችን ሰምተን ታሪክ ካልጠበቅን
ዘመናዊነት ሚስጥሩ ካልገባን
በአምና ተምረን ዘንድሮ ካልነቃን
ጊዜ ምን በደለ በሱ የፈረድን
*
ጊዜማ ሂደት ነው ድሮም የነበረ
እራሱን ሳይለውጥ ይሆን ሁሉ ዘመን በክብር የኖረ
ታዲያ ምን አጠፋ በሰው ተደፈረ
ንገረኝ ወንድሜ(ቴ) ጊዜ ምን በደለ":;"""''!?
ዜና ሕማሙ የመድኃኔዓለም
በጥፊ ማን መታህ
በዱላ ማን ገጨህ
በል ተንቢይ ትንቢት
ኢየሱስ ናዝራዊን አሉት በትንቢት
ጌታዬ !
ቤተክርስቲያን እኔ ፥ በመቅደስህ ሳለው
ራሴን ስመረምር ፥ ዙርያዬን ስቃኘው
የመቅደስህ ታዛ ፥ እጅግ አሸብርቋል
በቀለም ተውቧል ፥ እዩኝ እዩኝ ይላል
የህንፃ ቤተክርስቲያንህ ፥ የአሰራር ጥበብ
ፈፅሞ ቢደንቀኝ ፥ አልኩኝ መንክር ዕፁብ።
የቤተክርስቲያንህ አፀድ ፥ ልምላሜን ታጥቆ
ንፁሕና ፅዱ ሆኖ ፥ በደንብ ተጠብቆ
መዓዛው ያውዳል ፥ ሜትሮችን ርቆ።
በውስጥ የሚገኙ ፥ ችግኞች በሙሉ
የሚተጉላቸው ፥ ወንድሞች ስላሉ
መጠውለግ መጠንዘል ፥ ምንም ሳይኖራቸው
ባለ ደምግባቶች ተወዳጆች ናቸው።
ይህንን ተመልክቼ
በዚህ ተደስቼ
በአድናቆት እንዳለሁ..
ወደ ራሴ ሳይ ግን ፥ እኔ ያንተ መቅደስ
ለመውደቅ ተዛምሜ ፥ ተንጋድጀ ልፈርስ
ለመንፈሳዊ ዓይን ፥ ደምግባቴ ጠፍቶ
በረቂቅ ለሚያሸትተኝ ፥ ሽታዬ ከርፍቶ
ራሴን አየሁት
ደግሞም የሚገርመው
ለታቦትህ ማደርያ ፥ ቅፅር የሚተጉ
ሲቆሽሽ የሚያፀዱ ፥ የሚያደገድጉ
የቅጥርህን ችግኞች ፥ ውሃ የሚያጠጡ
የጠወለጉ ቅርንጫፎችን ፥ በጊዜው የሚቆርጡ
ብዙ ሰራተኞች ፥ እንዳሉ አይቼ
ይህንን ፥ ተመልክቾ ...
እኔ ምስኪን ልጅህ ግን ፥ ይህ ዕድል ተነፍጎኝ
ለነፍሴ ጠባቂ ስለመገናኘት ፥ ድካሙ በዝቶብኝ
ከቀናትም ወራት ፥ እንዲህ ይነጉዳሉ
ሚዛን በማይደፋ ምክንያት ፥ ይሸኛሉ
የዛሬን ጨምሮ ፥ ብዙ ቀናቶችን
ስለ ነፍሴ ውበት ፥ ለማግኜት አባቴን
ደጅ መጥናትን ባዘወትር ፥ አብዝቼ ብፈልግ
አልሆንልህ አለኝ ፥ እኔስ ግራ ገባኝ ፥ እንግዲህ ምን ላድርግ?
ይገርማል !
ህንፃ ቤተክርስቲያን ለመስራት ፥ እንዲሁም ለማደስ ብዙዎች ሲተጉ ፥ ብዙ ጉልበትና ብዙ ፥ ንዋይ ሲፈስስ
ነገር ግን ፦
ሕንፃ ሰብ ሲጎሳቆል ፥ ዕለት ዕለት ሲፈርስ
በፍትወት ሲቃጠል ፥ ከሰውነት ሲያንስ
ቅጠልነቱ ጠውልጎ ፥ ልምላሜ ሲለየው
ዘወር ብሎ የሚያይ ፥ አይዞህ ባይ ጥቂት ነው።
ዮሴፍ ጌትነት
እኛ ለእኛ ሳንኖር !
ጌታ ሆይ !
ከመናገር ማዳመጥ
እንዲሻል ስትገልጥ
ሁለት ጆሮን እና አንድ ምላስን ብትሰጥ ፤ ...
ከመናገር ይልቅ ፥ ቢቀልልም ማዳመጥ
የአሁን ዘመን ትውልድ ፥ እኛ የሰው ልጆች
ተቃርኖን የምንወድ ፥ ግሩማን ፍጥርቶች
ማዳመጥን አንቅረን
መደመጥን የሙጥኝ ብለን..
አንድም
ራሳችን ማዳመጥን ፥ ቸል ብለን
የህሊናችን ደጅ ፥ ጥርቅም አድርገን ዘግተን
ግልፅ ዓላማ ፣ ግልፅ ርዕይ ፣ እኔነት ሳይኖረን
የማንነት ጥያቄያችንን ሳንመልስ በውዝግብ ቆመን
ግራ መጋባት ሸብቦን ፥ ባለማወቅ አሮንቋ ተዘግተን
የሌሎችን እኔነት ለመኖር መወራጨት
አሳጥቶን ማንነት ፥ አድርጎን ባዶ ወጭት..
ለመሞት መኖር
በእኛ ዘንድ እንዲኖር ፥ ትንሣኤ ና ሕይወት
ሞትን ለማሸነፍ ፥ በእኛ ሕያውነት
ሙተንም እንዳንሞት
ለመኖር ከመስራት
አንድም
ብል የማያገኘው
ሌባ የማይሰርቀው
በመጽሐፍ የሚያስፅፍ ፥ መልካምን ከመስራ
የማይጠፋ መዝገብ ፥ ለእኛ እንዲኖረን አጥብቀን ከመትጋት
ለሚጠፋውና ፥ ለሚያጠፋን መስራት ፥ ምን አይነት ሞኝነት?
አንድም ፥
ከሞትንም በኋላ ፥ ሕያው የሚያደርገን
በሰወች ልቦና ፥ አትሞ የሚያስኖረን
ከመቃብር በላይ ፥ እኛን የሚያስጠራን
ይህንን እየሰራን ፥ ትውልድ ከማሻገር
ለዚህ ከመቅናትና ፥ ለዚህ ከመታተር
ለመስራት ከመትጋት ፥ ለመስራት ከመኖር
ከዚህ ሁሉ ይልቅ፦
ለመስራት ከመትጋት ፥ ለመስራት ከመኖር
የመረጥነው ጉዞ ፥ የዘመናችን ስሌት የኑሮአችን ቀመር
ስንሞት መቀበርያ ፥ ስናንፅ መቃብር
ቀባሪ እንዳናጣ ፥ ስንገባ እድር
ሌሎች እንዲኖሩ ፥ ከምንተጋው በላይ
ሲሞቱ ለመቅበር ፥ ስንል ከታች ከላይ
ቀባሪ አታሳጣኝ ፥ ብለን ስንፀልይ
ለመኖር ከመስራት
ስንሰራ ስንተጋ ፥ "ስንኖር - ለመሞት"
እንዲህ መጎሳቆል ፥ ራሳችን ማጣት
ከእውነት መደህየት ፥ ከክብር መታጣት
አቤት የእኛ ነገር ፥ ቅኔ ኑሮ ቅኔ ሕይወት
በሰም ኑረን ፥ በወርቁ ተዘርፈን ፥ በፍፃሜው መሞት !
ዮሴፍ ጌትነት
08/05/2013 ዓ.ም
ምን ይሆን ምስጢሩ ?
መርከብ ልቦናችን ፥ በባህር ዓለም ውስጥ
ማዕበል ሲያማታው ፥ በሞገድ ሲናወጥ
የኑፋቄና የክህደት ፥ ጎርፍና ውሽንፍር
የዓለማዊነት ትኩሶት ፥ የዘረኝነት ሀሩር
በላያችን ሲወርድ ፥ ልባችን ሲሸበር
እንዲህ ስንቸገር ...
በጥፋት ውሃ ፊት ፥ ከሞት ጋር ተፋጥጠን
የፈርዖን ግልምጫ ፥ ፊታችን ሲገርፈን
የዲዮቅልጥያኖስ ጡጫ ፥ ሲያደማን ሲገፋን
እንዲህ ባሁን ዘመን ...
እናርፍበት ወደብ ፥ እንከለልበት ጥሩር
እንመክትበት ጋሻ ፥ እንሸሽበት አውጋር
መጠጊያ ፍለጋ ፥ ነፍሳችን ተርባ
በዓይናችን ሲያቀርር ፥ ፅኑ ትኩስ እንባ
ድረስልን አምላክ ፥ ራራልን ጌታ
የሚል ተማፅኖና ፥ የምዕመናን ዋይታ
መቅደሱን ሲሞላው ...
በጸሎቱ የሚደግፍ
በቃሉ የሚያሳርፍ
ለሕይወታችን ጨው ፥ ለጨለማችን ብርሀን
የሕይወት መንገድን ፥ ገልጦ የሚያሳየን
የምንድንበትን መርከብ ፥ የአሰራር ብልሀት
ጥበብን የሚነግረን ፥ የምስጢር ባለቤት
ኖኅን የምንሻ ፥ ሳለን የእናንተ ልጆች
ኖኅን የምትመስሉ ፥ ብፁዓን አባቶች
በአሳቻ ሰዓት ፥ ከእኛ መለየት
ምስጢሩ ምን ይሆን ፥ አልገባኝም በእውነት?
ከፊታችን ሆኖ ፥ በእረኝነት በትር
የኤርትራን ባህር ፥ ከፍሎ የሚያሻግር
መዓትና መቅሰፍት ፥ በእኛ ላይ እንዳይወርድ
ራሱን አስይዞ ፥ ስለ እኛ የሚማልድ ፥ ስለ እኛ የሚጋረድ
የክርስቶስን መንጋ ፥ ከጥፋት የሚያድን
ከነዓን ሊያስገባን ፥ የተሰጠው ኪዳን
ሙሴን የምናሻ ፥ ልጆቻችሁ ሳለን
የደጋግ አባቶች ፥ ከእኛ ዘንድ መለየት
ምስጢሩ ምንድን ነው ፥ አልገባኝም በእውነት !
ስለ ሀገርና ስለ ሃይማኖት ክብር
በጥብዓት የሚቆም፥ አዋጅ የሚያስነግር
ሰማዕትነትን ባርኮ ፥ ለእኛ የሚሰጠን
የእምነት አርበኛ ፥ ስንሻ ጴጥሮስን
አሁን በዚህ ሰዓት ፥ የእናንተ መለየት
ምስጢሩ ምን ይሆን ፥ አልገባኝም በእውነት !
ይህንን ስለ ማሰብ ፥ ይህንን ስለ ማየት
ሀዘናችን በረታ ፥ አቃተን መጽናናት
እንኪያስ እኛም ፥ ከእናንተ ፥ አባቶቻችን አንበልጥም
በረከታችሁ ደርሶን ፥ የምናርፍበት ፥ ተራው የኛ ይሁን !
27/03/2013 ዓ.ም
ምን ተሰምቶህ ይሆን ?!
ሀገር የምትኖረው ፥ ሀገር የምትድነው
ለሀገር ፅኑ ደዌ ፥ ፈውስ የሚገኜው
አንተ የሀገር ልጅ ፥ ጠቢብ ስትሆን ነው !
ርሃብ ቸነፈር ፥ ከሀገር የሚጠፋው
ደስታና ሀሴት ፥ ፍስሐ የሚሆነው
መሰደድ ተሰድዶ ፥ ባይንህ የምታየው
በሀሳብ ልዑል ስትሆን ፥ ልጄ ስትማር ነው !
ያለማወቅ ፅልመት ፥ ከሀገር ተወግዶ
ህዝብ ሰላም ሆኖ ፥ ርስ በርስ ተዋድዶ
በሀገር የሚኖረው
ልጄ ስትማር ነው !
ሥራችን ፥ ምንድን ነው ?
እንዲህ ባገራችን
ባሁን ዘመን ሚዛን
አዋቂነት ቀልሎ
ግልብነት አይሎ
"እኛ" ነት ተገድፎ
ለእኔ ማለት ገዝፎ
ብፁዕ ተሰይፎ
ዕቡይ ተደግፎ
አማኝነት ተከስሶ
ህዝብነት ኮስሶ
አለማመን ገንኖ
ፍቅር ተመናምኖ
አውሬነት ጀግኖ
ጥበብ ስትገፋ
ስንፍና ሲሰፋ
የሚያስታርቅ ጠፍቶ
የሚያጣላው በዝቶ
ጥላቻና ሴራ
በሀገር ሲዘራ...
እያዬን ፥ በዓይናችን
ይሄው እንዳለን አለን...
ከመሆን ተራቁተን
መኖርን ረግጠን
በመምሰል ተፅናንተን
አለመሆናችን እሽሩሩ ብለን
ከአለመኖራችን ፥ ተዋደን ተላምደን
መምሰልን ፥ ለዛሬ ብለን
በታይታ ተሸምነን
መኖርን ለነገ ቀጥረን
በመምሰል ተቃኝተን
መኖርን ተዘርፈን...
መታወቅን ደጅ ጠንተን
ማወቅን አወስልተን
እያዬን ባይናችን
ይሄው ፥ እንዳለን አለን !
ትላንትን አማግጠን
ዛሬ ላይ ተኝተን
ዛሬን አዘሙተን
ነገን አገልሙተን
ዛሬ ሳንሰራ ፥ ለነገ ሳናቅድ
በትላንት ትውልድ ፥ መርገም ስናወርድ
እያዬን በዓይናችን
ይሄው እንዳለን አለን!
ዛሬን ላለመኖር ፥ ትላንትን ስንጠቅስ
ታሪክን አጣርሰን ፥ ትውልድን ስንከስ
የመዋደድን ፥ ታሪክ ዘንግተን
የጥላቻን ድርሳን ፥ አንግበን
ጥርስ መንከስ በቀልን ፥ በልባችን ከትበን
ታሪክን መስራትና ፥ ዛሬን መኖር ታክቶን
ትላንትን ማወደስ ፥ ትላንትን ማነወር ፥ ስራ የሆነብን
ብዙ ብኩን ሰዎች ፥ ብዙ ጉስቁል ሰዎች ፥ ይሄው ዛሬም አለን ?
ከዚህ ሁሉ ነገር ፥ በዕድሜያችን -ዛሬ ፥ እኛ ከሰራነው
ለነገ የሚሆን ፥ ትውልድ የሚወርሰው ፥ ስራችን ምንድን ነው?
ዶ/ር ዮሴፍ
19/2/2013 ዓ.ም
12/02/2013 ዓ.ም
ዶ/ር ዮሴፍ ጌትነት
ጉዞ ወደ ቅዱስ ቁርባን
ክፍል አንድ
፨፨፨
ከሁለት አመት በፊት ነው ጊዜው አብይ ፆም ነበር። ፆም ለነፍስ ደስታን ስትሰጥ ለስጋ ደግሞ ምቾት ትነሳለች።
ለመንፈሳዊነት ብርታትን ከእግዚአብሔር እንደሚያስገኝ ስላመንኩና የቤተክርስቲያናችን ቀኖና ስለሆነ እየጾምኩ ነበር።
ወጣት ነኝ
መንፈሳዊ መፅሀፍትን በቻልኩት መጠን ለማንበብ እተጋለሁ።
መጽሐፍ ቅዱስና ልዩ ልዩ አዋልድ መጽሐፍትን አነባለሁ።
ስለ አምስቱ አዕማደ ምሥጢር ለአንድ ክርስቲያን በቂ የሚባል ዕውቀት ያለኝ ይመስለኛል
ስለ ቅዱስ ቁርባንም አንዱ pillar እንደመሆኑ እግዚአብሔር ባሳወቀኝ ያህል አውቃለሁ።
ስለ ቅዱስ ቁርባን ልዩ ልዩ መርሐ ግብር ተካፍያለሁ።
ስጋውን ካልበላን ደሙን ካልጠጣን ንሰሀ ብንገባም የዘላለም ህይወት እንደማይኖር በተለያዩ ትምህርቶች አውቃለሁ።
ነገር ግን እንኳን ወደ ቅዱስ ቁርባን መቅረብ ስለ ቅዱስ ቁርባን ሲወራ ራሱ እጅግ እፈራ ነበር።
መቅረብ ብፈልግም ምክንያት እየደረደርኩ አልቻልኩም ነበር።
እንዲህም አሉኝ "ቆይ አንተ ክርስቲያን ነህ አደል። አስርቱ ትዕዛዛት ታውቃለህ ታዲያ ከነዚህ ውስጥ ላለመፈፀም ያቀድከው
ዕቅድ አለህ?"
"እኔም የለም አልኩት" "ታዲያ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር የባህርይ ልጅ እንደሆነ ካመንክ ስጋውንና
ደሙን ለሀጢዓት ስርየት ለዘላለም ህይወት እንደሰጠን ካመንክ እግዚአብሔር ሌላ ምን ይፈልጋል።" እምነትህንና አሥርቱን
ትዕዛዛትን መፈጸምንና እምነትህን ብቻ እንጅ
አሥርቱ ትዕዛዛትን ደግሞ እንኳን የተማረ ክርስቲያን የማያምኑ አህዛብ እንኳን በህሊናቸው በተጻፈ ህግ ካለማመን ውጭ
ትዕዛዙን አይሽሩም ።
ቆይ እግዚአብሔርን ትወደዋለህ?' አለኝ
ዝም አልኩ "ዝም ብትልም መቸም በልብህ እወደዋለሁ ትለኝ ይሆናል።ከወደድከው ትዕዛዙን ጠብቅ በወንጌሉ ይህንን
ብሏልና። "
" አንድ ንጉስ ሰዎችን ቢጠራና ኑ እናንተ ይሄን ምግብ ልትበሉ ይገባል በማለት ሄዳችሁ ነገር ግን ባትበሉ ንጉሱ ምን ሊል
ይችላል?
ምሳሌውም;
ንጉሱ፡ ክርስቶስ
መጠራታችን፦ ኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ መሆናችንና ቤተክርስቲያን መሄዳችን
ምግብ፦ ስጋና ደሙ
የእግዚአብሔር ቃሉ እንደማይለወጥና እውነት እንደሆነ ታውቃለህ አደል?
መቸም የእምነት ችግር ያለብህ አይመስለኝም ያለ መስራት እንጅ።
ስለዚህ ይህን ብሏል
ስጋየን ያልበላ ደሜን ያልጠጣ የዘላለም ህይወት የለውም።'"
"ጫካ ገብተህ ባህታዊ ሁን አልተባልክ
ገዳም ሄደህ መንኩስ አልተባልክ
እዚሁ በቃ ክርስቲያናዊ ሰዉ ሁን ነው የተባልክ..."
፨ክፍል ሁለት፨፨
ወደ ስጋውና ደሙ መቅረብ እንዳለብኝ ባምንም ልቤ ፈራ
የፈራሁትም ምክንያትም
1 ወጣት ነኝ እኔ እንደፈለግኩ የማላዛቸው አካላት ወይም ሁለተኛ ስሜት አለኝ። ብበድልስ?
2 ሰው ምን ይለኝ ይሆን ሽማግሌው እንኳን በማይቀርብበት ዘመን እኔ ቀርቤ...
አይገባኝ ይሆን?
3) ሥርዓቱንም ስለማላውቅ ምን እነደሚደረግ ባነብም በጣም ከበደኝ።
4) ከጓደኞቸ ጋር ያለኝ ግንኙነት ሙሉ በሙሉ ይለወጣል እናም በብቸኝነት ልፈተን እችላለሁ።
5) ብዙ ለመተው የሚያስቸግሩ ሃጢዓቶች ወይም የኃጢአትና ሀጢዓት ጥንስሶች ብየ ያሰብኳቸው
ለምሳሌ ምኞት፣ የልማድ ውሸቶች፣ ስድብ፣ ሙዚቃ ማዳመጥ፣ አልኮል መጠጣት፣ መጥፎ ትውስታዎች፣ የተለያዩ ፊልሞች
የምቀለደው ቀልድ አይነት ይለወጣል
በጊዜው ብዙ የሚያስጨንቁኝ ነገሮች ነበሩ አሁን ባላስታውስም
አነዚህንና የመሳሰሉትን በማሸነፍ ወደ ቅዱስ ቁርባን የሚያደርሰኝን መንገድ እንደ እግዚአብሔር መልካም ፈቃድ መጥረግ
ጀመርኩ
በመጀመሪያ ችግርን ወይም ደካማ ጎንን መለየት ለአንድ ነገር መፍትሄ የመጀመሪያው ስቴፕ ነውና።
ችግሮቸን በማስታወሻ መዘገብኩ።
1 ላመንኩበት ነገር ወደ ስራ ቶሎ ያለመግባት
2 አርአያየ የምለውን ሰው አለመከተል
3 ፈራሁ ብየ ያስቀመጥኳቸው ነገሮች
ክፍል ሦስት
፨፨፨
በክፍል ሁለት እንዴት ቀስ በቀስ መንፈሳዊነትን ብሎም ወደ ቅዱስ ቁርባን እንዴት እግዚአብሔር መቅረብ እንዳስቻለኝ
እንደምገልጽ ቃል ገብቸ ነበር።
ቀስ በቀስ እንዴት መንፈሳዊ ልሁን ወደ ቅዱስ ቀርባን እንዴት ልቅረብ
ካለወቁ አያምኑ ካለመኑ አይጸድቁ የሚለው Universal Truth ነው ስለዚህ ይህን ማድረግ አስፈላጊ ነው
ይህን ያላደረገ እግዚአብሔር በተዓምሩ የመረጠው/ የጠራው ካልሆነ በስተቀር ሊለወጥ ወደ በጎው መንገድ ሊጓዝ አይችልም
ይመስለኛል። ምክንያቱም ለምን እና እንዴት ለውጥ ማምጣት እንዳለበት አያውቅምና።
ብዙውን ጊዜ ሰዎች ለራሳችን መጥፎ አይደለነም መጥፎ እንኳን እንደሆን ህሊናችን ጎሰም ሲያደርገን ራሳችን መጥፎ
የሆንበት ምክንያት እያቀረብን ክፉ አለመሆናችን ለራሳችን ለማሳመን እንሞክራለን።
ጥፋት አጥፍተን ምንም እንዳላጠፋን አያደረግን ተላምደነው እንኖራለን።
አንተ የእግዚአብሔር ቤተመቅደስ መሆንህን ማሰብ
ትልቁ ኃጢአትን እንድንጸየፍ የሚደርገን ነው
1 ኛ ቆሮ 3፥16 " የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደ ሆናችሁ የእግዚአብሔርም መንፈስ እንዲኖርባችሁ አታውቁምን?
ማንም የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ቢያፈርስ እግዚአብሔር እርሱን ያፈርሰዋል፤ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ቅዱስ
ነውና፥ ያውም እናንተ ናችሁ። "
እግዚአብሔርን እወደዋለሁን?
ዮሐ 14፥ 16 የምትወዱኝ ትዛዜን ጠብቁ
ብሎናልና የመውደዳችን ጥግ በትዕዛዙን በማክበር ይወሰናል
"በውኑ ለውጥ ያስፈልገኛልን?"
አሁን የምሰራው ምንድን ነው? የማስበውስ
ስለ እግዚአብሔር ስለ ቸርነቱ ብዛት ስለ መስቀሉ ነገር ወይስ ስለ ዝሙት መዳራት ና በወንድሜ ላይ ስለ መበደል?
የሚለውን ጥያቄ መመለስና ለውጥ እንደሚያስፈልግ ማመን
3) ጥፋታችን ካመንን ትልቁ ነገር ቀለለ ማለት ነው ይኸውም ለማስተካከል ለመስራት አቅደሃል ማለት ነው።
አሁን ፍላጎትህ እግዚአብሔር ነው ማለት ነው
አሁን ፍላጎትህ ከቅዱሳን በረከት መሳተፍ ነው
አሁን ፍላጎትህ መስቀሉ ነው ቅድስት ድንግል ማርያም ናት።
አዘውትሬ ከአቡነ ዘበሰማያት ጋር የምጸልያት ጸሎት አለች። ባስታወስኩት መጠን በቅደም ተከተል እጸልያለሁ።
አባታችን ዳዊት እንዲህ ሲል ለመነህ አንዲት ነገርን ለመንኩህ በቤትህ ለዘላለም እኖር ዘንድ በቤተመቅደስህ አገለግል ዘንድ
።አቤቱ እነሆ እኔም እንዲሁ ይኸውን እማጸንሃለሁ በቤትህ ለዘላለም እኖር ዘንድ።
ከመሞቴ በፊት ወደ ንሰሀ ጎዳና ምራኝ
ከበረከትህ አድለኝ
ለስጋወ ደሙ እንደ ቸርነትህ አብቃኝ
ህዝበ ክርስቲያኑን ሀገራችን ኢትዮጵያን በቸርነትህ ጠብቃት
ስብሐት ለእግዚአብሔር
አቡነ ዘበሰማያት..
ክፍል አራት
፨፨፨
በክፍል ሦስት እንዴት ቀስበቀስ መለወጥ እንደምንችል 3 ነጥቦችን አንስተን
1) መንፈሳዊ ጥበብን ማንበብ መማር ና መጠየቅ
2) እኔ ማን ነኝ በማለት መመርመር
3) ጥፋትን አምኖ መቀበልና መጸለይ
ከሶስተኛው ነጥብ ስለ ጸሎት እያነሳሁ እንደሚቀጥል ጽፌ ነበር
ይህንም እጸልያለሁ
እንደልቤ የምትለው አባታችን እንዲህ አለህ "እጠበኝ ከበረዶ ይልቅ ነጭ እሆናለሁ።" አሁንም እኔ ባሪያህ ልባል የማይገባኝ
እንዲሁ እለምንሀለሁ።
አቤቱ የልቦናየን ድክመት አንተ ታውቃለህ በኔ ሀሳብ ያይደል ዘወትር በአንተ ሀሳብ እኖር ዘንድ ሁሉን ቻይ አምላክ ሆይ
እለምንሀለሁ።
አቤቱ የአብርሃም የያዕቆብ የይስሃቅ የቅዱሳን አምላክ ሆይ እንደቸርነትህ እንጂ እንደበደሌ አታድርግብኝ
አቤቱ በቅድስት ድንግል ማርያም ምልጃና ፀሎት
በቅዱስ ሚካኤል ምልጃና ጸሎት
በቅዱስ ጊዮርጊስ ፣በሁሉ ቅዱሳን ምልጃና ጸሎት እለምንሀለሁ እማጸንሀለሁ።
ስብሀት ለእግዚአብሔር
አቡነ ዘበሰማያት...
የመጨረሻ ክፍል ፨፨፨
7) መጽሐፍትንና ለመንፈሳዊ ልምምዱ ሊረዱ የሚችሉ ነገሮችን መሰብሰብ ምሳሌ ተግባራዊ ክርስትና በዲያቆን ሄኖክ
ኃይሌ እንዲሁም የ አቡነ ሽኖዳ The spritual man ወይም ትርጉሙን መንፈሳዊው ሰው በአያሌው ዘኢየሱስ
13) ሰው ሴትም ሆነች ወንድ ሁሌም ማለት ይቻላል ስለ ትዳር ያስባል ስለዚህ በዚህ ዙሪያ አንድ አቋም ልትይዝ ይገባል
ትዳር ካለህ እግዚአብሔር ትዳርክን እንዲባርከው እየፀለያችሁ በፍቅር መኖር
ትዳር ካልያዝክ ድንግል ከሆንክ እድለኛ በተክሊል ለማግባት ቁርጠኛ አቋም ይዘህ ከእግዚአብሔር ጋር ፈተናዎችን እያራቁ
በተክሊል ለማግባት ወስነህ ጠይቅ ይሰጥሀል ብሏልና መጸለይ።
ድንግል ባትሆንም የስጋን መመለስ ባይቻልም በነፍስ ይቻላልና በቤ/ክ ስርዓት ለማግባት ወስነህ ራስክን ከፈተናዎች እያራቅክ
እግዚአብሔርን የምትፈራ የትዳር አጋር እንዲሰጥህ እየለመንክ በቤ/ክ ስርዓት መኖር ።
ዮሐ 6÷53-56 "ስለዚህ ኢየሱስ እንዲህ አላቸው። እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ የሰውን ልጅ ሥጋ ካልበላችሁ ደሙንም
ካልጠጣችሁ በራሳችሁ ሕይወት የላችሁም።
ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ።
" እንግዲህ ያለ እርሾ እንዳላችሁ አዲሱን ሊጥ ትሆኑ ዘንድ አሮጌውን እርሾ አስወግዱ። ፋሲካችን ክርስቶስ ታርዶአልና፤"
(1 ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 5:7)
የዘላለም ህይወት ማን ማይፈልግ አለ።
ስለዚህ ለዚህ ለመቅረብ ብዙ ምክንያት መደርደር አያስፈልግም እውነት የዘላለም ሕይወት ምንፈልግ ከሆነ
ብዙዎች እኔ ራሴ የራሴን ማንነት አስተካክየ ወደ እግዚአብሔር ቤት እሄዳለሁ ከዛ ቅዱስ ቁርባን እቀበላለሁ ይላሉ። ነገር ግን
አይችሉም ስራውን ለእግዚአብሔር አልሰጡምና ።
እግዚአብሔር ግን ወደ ቤቴ ና እና እኔ አስተካክልሀለሁ ይላል። ልባችን እግዚአብሔር እንዲነግስበት ከፈቀድንለት በጸሎት
ከጠየቅን ሁሉን ያደርግልናልና።
እግዚአብሔር አምላክ ቅዱስ ቁርባን ተቀብለን የክብሩ ወራሽ የስሙ ቀዳሽ ያድርገን። አሜን
ስብሐት ለእግዚአብሔር
"በእኔ የምትኖር"
ማቴ 6 ፥ 9
አባታችን ሆይ
የምትኖር በሰማይ
ብዬ እንድፀልይ
ለኔ ስታስተምር
ለኔ ስትናገር ...
ደግሞም ፥ ስጋዬን የሚበላ ደሜን የሚጠጣ ፥ በእኔ ይኖራል
ብለህ መናገርህ በቅዱስ መጽሐፍ ፥ በዮሐንስ ወንጌል
(ዮሐ 6)
ቀጠል አድርገህም ...
የምትወደኝ ብትሆን ፥ ትዕዛዜን ብትጠብቅ ፥ በቃሌ ብትኖር (ዮሐ 14)
ከአባቴ ጋር ወደ አንተ እንመጣለን ፥ በአንተ ውስጥ ለመኖር (ዮሐ 14)
ብለህ መናገርህ ምን ይሆን ምስጢሩ ?
በእኔ እንደምታደር ባንተ መነገሩ
ስል እጠይቃለሁ ፥...
በሰማይ የምትኖር ፥ ተብለህ መመስገንን
የዘወትር ጸሎት ፥ አድርገህ ስትሰጠን
እውን በሁሉ የመላህ አንተ ፥ በምድር አትኖርም ?
ዓለማተ ዓለም ስላሴ ፥ በዓለም የለህም?
ስል እጠይቅና ፥ ይህንን አምናለሁ ፥
በረድኤት መኖርህ ፥ ክብርህን መግለጥህ
ነውና የሚደነቅ ፥ ከምድራዊ ሀሳብ ከፍ ባሉ ልጆችህ !
ደግሞም ...
መልስ ቢሆን ስል ሀሳብ አወጣለሁ ፥
ሀሳብ አወርዳለሁ...
አንተ ፥ በእኔ እንደምታደር ፥ ቃልን ከሰጠኸኝ
"በሰማይ የምትኖር" ፥ ብለህ ፀልይ ያልከኝ
መሆኑ ነው ይሆን ፥ ሰማይ ልታደርገኝ?...
ልዑል ሀሳብ ልዑል ምክር ለእኔ ልትሰጠኝ
ከምድራዊነት ዕንቅብ ልትለየኝ ፥ እኔን ልታወጣኝ ፥ ከፍ ልታደርገኝ ፤
በዕርገተ ህሊና ፥ በዕርገተ ልቡና ፥ እኔን ልትሾመኝ እኔን ልታከብረኝ ፤
የፀሐይና ጨረቃ የከዋክብት ውበት
የሚገለጥብኝ በእኔ ሰማይነት
ፍጥረትን የማሞቅ ፥ ብርሃንን የምሰጥ ፤
የፀሀይ ህላዌ በእኔ የሚገለጥ ???
"አትናቅ"
፠፠፠
በዘር በወገንህ: ከመመካት ራቅ
የፈለገ ቢወድቅ: የፈለገ ቢደቅ
ሰው ሆነህ ተፈጥረህ፡ ሰዎችን አትናቅ!
ያደርገዋልና የተዋረዱን: ከፍ የከበሩትን ዝቅ::
(በእርሱ ፊት)
ዘርህ አንተ ምነው፡ ቅማንት ወይ አማራ?
ይህን አትጠየቅ! ስምክን አትጠራ!
( ምነው ታዲያ )
ዘሬን እየጠራህ፡ ማለትህ አህያ¡
ምርጥ ነን ማለትህ: ሰውስ ከኛ ወዲያ!
አህያን ብታውቃት፡ ጌታ ሰጧታል ክብር
የከበረ አምላኳ ፡ተቀምጦባት ነበር፡፡
"
፠ ያንችስ ወዳሴሽ ፠፠"
ያንችስ ወዳሴሽ፡ አያልቅም ቢነገር
ትንሽ ጨለፉ እንጂ ፡ከምስጋናሽ ባህር
ከ ምድር ኤልሳቤጥ፡ ከሰማይ ገብርኤል
ሉቃስ እንደፃፈ አመስግነውሻል ፡እናታችን ድንግል
በማህፀን ሳለ ፡ቅዱስ ዮሐንስ
ከአባ ኤፍሬም፡ እስከ አባ ጊዮርጊስ
ከቅዱስ ያሬድ ፡እስከ ህርያቆስ
የተነሱት ሁሉ ፡በየዘመናቱ
ፅፈው አስቀመጡ፡ እንደየፀጋቸው እንደበረከቱ
ዜማችን ሆነሻል ፡እናታችን ማርያም
አምላክን መውለድሽ፡ታአምር ሆኖብናል ዛሬም ለዘላለም፡፡
ከመቅደሱ አገቡሽ፡ ሲደርስ አመትሽ ሶስት
መላዕኩ ፋኑኤል፡ ሲመግብ ያኖራት
ድንግል እመቤቴ ፡ዕፁብ ድንቅ ሰው ናት፡
ፀጋን የተመላሽ፡ በአካላትሽ ሁሉ
ዛሬም አናግንሽ፡ ከቅዱሳን ሁሉ
"የህይወት መድሀኒት"
እንካ እየተባለክ፡የህይወት መድሀኒት:
ምነው መቀለድህ: ጌታህ አዘጋጅቶት
ተቀበለው እንጅ:ምነው ማቅማማት
የዘላለም ህይወት፡ አትፈልግም እንዴ?
ሁሌም ዝግጁ ነው፡ ተቀበል ዘመዴ
ና ቅረብ ወንድሜ: መራቅ ምን ያደርጋል?
ከሰዎች ለይቶ: ህይወትን ያመራል
አስብ!
እስኪ ልጠይቅህ?
መድሀኒት ያለው፡ ቢኖር አንድ ዶክተር
ክትባት ልስጥ ቢል ፡በደስታ ዘላለም የሚያኖር
እርሱን ስለማግኘት: አትታገልምን?
በስንት ወርቅ በስንት ብር ፡ትለውጠው ይሆን?
አሀቲ ቃል ተበቅዑ ፡ይሄውልህ ውዴ
ራስክን አረጋግተህ፡ ይችን ስማኝ አንዴ
(የአንድ ደቂቃ ጥሞና)
በነፃ ሰጥቶሀል፡ አርብ ላይ ተሰቅሎ
ለአለም ቤዛ ሆኗል፡ ብሉኝ ጠጡኝ ብሎ
ራስክን አንፃና፡ ነገ ዛሬ ሳትል
የህይወት መድሀኒትን፡ በክብር ተቀበል፡፡
እናማ ወንድሜ ፡ራስክን አዘጋጅተክ
ከአለም ሰው ሁሉ፡ መርጦህ ከተቀበልክ
መንፈስ ቅዱስ ቀርቦህ
ፀጋው ሁሉ ከቦህ
ዲያቢሎስ ተጨንቆ
ከዙሪያህ ርቆ
ፀሎትህ ደርሶልህ፡ ያልከውን አግኝተህ
በድል ትኖራለህ፡ አክሊል ተቀዳጅተህ፡፡
*:ጊዜ ምን በደለ;*
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
እውነትን ደብቀን ሀሰትን አንግሰን
አባቶች እያሉ ልጆች እያስተማርን
አርብ እሮቡን ሳናውቅ ሁልጊዜ አየበላን
ቤቱ መመላለስ ጭራሹን አቁመን
*
*
የእግዛብሔርን መቅደስ በሀጢያት ስንሞላ
እንደሰዶም ሆነን ህግን ስንጠላ
አህዛቦች ሲቀድሙን እኛ ቁመን ሇላ
ፀጋችን እያለ እሱን ሳናውቅበት ስንፈልግ ሌላ
*
*
የምንጓዝበት መንገዱ ረዝሞብን ቤቱ መሄድ ሲቀር
ሀይማኖት በገንዘብ እንደስም ሲቀየር
መፅሀፍትን ሳናነብ አባቶች እግር ስር ቁጭ ብለን ሳንማር
ቅዱስ ሁኑ ተብለን ምርጫችን ሲቀየር
*
*
ውበት ከአምላክ በላይ እኛ ስንሰራ
ቀለም እያማረጥን አለምን ስንመርጥ አምላክን ሳንፈራ
ማህሌት አዳር ትተን ስንመርጥ ጭፈራ
ሀብታችን ሀጢያት ገዝቶ ሲያስመስል ተራራ
*
*
ልብሳችንን ጥለን እርቃንን ስንመርጥ
በማናውቀው አለም ከላይ ሁነን ሳለ ወደ ታች ሰንዘቅጥ
አማርጠን ስንበላ ከደረቅ እስከ ቁርጥ
በደካማው ስጋ ለነፍሳችን ስንቅ ጭራሽ ሳናስቀምጥ
*
*
አወቀን ብለን ሳናውቅ በትቢት እየተጓዝን
ምርጫችን ከኛ በልጦ እኛኑ ሲመክረን
አልመለስ ስንል አምላክ እላይ ሁኖ በትዝብት ሲያዩን
ፍርጃ እላይ ቆመን ጌታ ሊመዝነን
እኛ ከሱ በልጠን ጭራሽ ፈራጅ ሁነን
*
*
ክፋትን አንግሰን ጠፋቶብን በጎነት
የውጩን አድንቀን ስንጓዝ በስህተት
ምርጫችን ተምታትቶ ስናማርጥ ውሸት
ሚስጥሩን ሳናውቀው ለመፋረድ ስንዋትት
*
*
በል በትርርህን አፅና የሚባል ሲጠፋ
መገንዘብ ሲያቅተን ምንድነን እንደሆነ የወደፊት ተስፋ
በማይጠቅም ህይወት ስንማስን ስንለፋ
ማወቁ ሲጠፋን ሁሉም ሟች መሆኑን ጠብቆ ወረፋ
*
መቶ ለማይሞላው ለዚህ አጭር እድሜችን
ምን ለማይጠቅመው እንጨነቃለን ለአፈሩ ስጋችን
አድሜአችን ሲቀንስ ከግባራችን ሲለቅ ፀጉራችን
መመለስ ሲያቅተን ዛሬ ነገ እያልን ሲመርሽ ቀናችን
*
አባቶችን ሰምተን ታሪክ ካልጠበቅን
ዘመናዊነት ሚስጥሩ ካልገባን
በአምና ተምረን ዘንድሮ ካልነቃን
ጊዜ ምን በደለ በሱ የፈረድን
*
ጊዜማ ሂደት ነው ድሮም የነበረ
እራሱን ሳይለውጥ ይሆን ሁሉ ዘመን በክብር የኖረ
ታዲያ ምን አጠፋ በሰው ተደፈረ
ንገረኝ ወንድሜ(ቴ) ጊዜ ምን በደለ":;"""'
፨ግጥማዊ ተውኔት፨
አባ ይፍቱኝ
መስቀሉን ያሳልሙኝ
ልጄ የተባረክህ
እማይሰራ ኃጢአት
እግዚአብሔር ይፍታህ
እስኪ ጠጋ በለኝ
ክርህን አሳየኝ።
አንገትህን ልየው
ማተቡን አስረሃል?
እንዴታ አባቴ
ማተብ ምልክቴ
መቼ ትለያለች
በጭራሽ ካንገቴ
ማህተቤ እኮ ናት
እጅግ የማከብራት
ክርስቲያን መሆኔን
በጌታ ማመኔን ምመስክርባት
የውስጥ እምነቴን ለሰው ማሳይባት
መናገሪያ ቃሌ
ይችናት መስቀሌ
በልቤ ያለውን
ውስጤ የሚያምነውን
እንዴት አሳይ ነበር
ማተቤ ከሌለች
እንዴት ልመስክር
አባ ማተቤማ ምስክሬ እኮናት
የመጣው ይምጣ እንጂ ካንገቴ አለያት።
በማለት ሲናገር ለንስሐ አባቱ
አቶ ግብዝነት ሐይማኖት ባንገቱ
አፍ የላትም ብሎ በማተብ ሲደበቅ
ድንገት አፍ አውጥታ "አ" ከማለትዋ
ዝም በይ ብሎ በጁ አፍዋን ሊይዝ ሲል
መናገር ቀጠለች ማተብ የእውነት ቃል
ይቀጥላል....
...የቀጠለ
አባ እኔን ይስሙኝ
ከልብዎ ያድምጡኝ
ሰዎችን ሳይፈራ እግዜርን ሳያፍር
በስንቱ ሰዎች ፊት ሐሰት ሲመሰክር
እኔን እያሳየ ስንቱን ሰው አሞኘ
ብዙ ታግሻለሁ አንገቱ ላይ ሆኜ
በድፍረት ሲያታልል የሐይማኖት አባቱን
ዛሬ ግን አልቻልም ልናገር እውነቱን።
ያለሁበት ሥፍራ ይህ ደንዳና አንገቱ
መካከለኛ ነው ለልብ ላንደበቱ።
ስለዚህ ልቡ ላይ ሲያስብ ሚውለውን
ደግሞም ባንደበቱ የሚናገረውን
እመሰክራለሁ ያየሁትን ሁሉ
በኔ ተሸፍኖ እንዳይጠፋ ዉሉ
ሐይማኖትን ትቶ ቅዱሱን ያምላክ ቃል
ከንቱ ሐሳብ ሲያስብ ራሱን ሲያታልል
አንዱን በሌለበት በሐሰት እያማ
ሌላውን ባፍ ቃል ክፉኛ እያደማ
ሲወረወር ቀስቱን የሾሉ ቃላቱን
በመርዝ አንደበቱ የነደፈው ስንቱን
ውስጡ ክፋት እንጂ ወንጌል ካልተሞላ
ያምላክን ቃል ትቶ የሰውን ከበላ
እንዴት እሆናለሁ የእምነት ምልክቱ
መሸፈኛው እንጂ እንዳይታይ ፊቱ።
ይቀጥላል.....
የቀጠለ...
ማተብ ሚስጢሩ እርስዎ ያስተማሩት
የላይ ምልክት ነው በልብ ላመኑት
ከቅዱስ ያዕቆብ ዘእልበረዳኢ
እንደ ተማረነው ወግ ከአበው መጻኢ
እውነተኛው እምነት በልባቸው ሆኖ
ለፈጣሪ ሲታይ በልበ ተአምኖ
ማተብ ግን ለሰው ነው ልቡን ለማያይ
የውስጣችን እምነት በተግባር እስኪታይ።
ይህ ነበር እውነቱ የኔ ጥቅም ለሰው
ወንጌሉን እንዲኖር ሁሌ ላስታወሰው።
ዛሬ ግን ብዙዎች ይህን ሳይረዱ
ባንገት እያመኑ በምግባር የካዱ።
ውስጣቸውን ዘግተው ከውጭ እያሰሩኝ
መገለጫ ሳይሆን መሸፈኛ አረጉኝ።
ይህም ሰው አባቴ ከእዚህ አንዱ ነው
በኔ ተሸፍኖ ውስጡ ግን ሌላ ነው
እርሱ እንደ ነገርዎት ብዙም አይወደኝም
ከነመኖሬ እንኳ አያስታውሰኝም
ለባለንጀሮቹ ሲናገር በሐሰት
ምንም አይመስለውም በስሜ ሲገዝት።
እኔን ያየ ሁሉ ክርስቲያን ሽፍኜበት።
ብዙ ሰው አታሎአል አባይ ነው ምላሱ
ውስጡን ያሳልሙልኝ ልቡን ይቀደሱ።
ምግብ ቤት ነው ተብሎ ከውጭ ከተጻፈ
እንጀራ ይገኛል ወደ ውስጥ ላለፈ።
እንዲሁም አንገት ላይ ማተብ መታስሩ
ወደ ታች ወደ ልብ ጣቱን መቀሰሩ።
ውስጥ ያለውን ሊያሳይ መሆኑን ንገሩት
ክርስቶስን ለብሶ እንዲኖር ምክሩት።
ብዙ ሰው አታሎአል አባይ ነው ምላሱ
ውስጡን ያሳልሙልኝ ልቡን ይቀድሱ።
ተፈፀመ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
፨መነባንብ፨
የብርሃን እናት
የብርሃን እናት የሁሉ አስታራቂ
እንሆ ምስጋናሽ ከእኛም እንዳትርቂ
ስምሽ ይጣፍጣል ከማር ከወተት
ተብለሻልና የአምላክ እናት።
ማህደር ብርሃን ሃመልማለ ወርቅ
የመወለደሽ ጥበብ እንደምን ይረቅ
በሄዋን ተዘግቶ የነበረው በር
ባንቺ ተከፈተ ምስጋናሽ የከበር።
ጌታ የመረጠሽ ለክብር ለፀጋ
ካንቺ ተወለደ በድንጋሌ ስጋ
ሰማይና ምድርን ያፀና በቃሉ
አምላክ አንቺን መርጦ ከደናግል ሁሉ
ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን የከተመብሽ
እፁብ ድንቅ እመቤት ድንግል አንቺ ነሽ።
ጡቷን እያጠባች አምላክን ታቅፋ
ምድራዊ ችግርን ስንቱን አሳልፋ
ይኸው ትኖራለች ክብሯን ተጎናፅፋ።
የምህርት አማላጅ እመቤቴ ሆይ
እንመስልሻለን በወርቅ ሙዳይ
አንቺን ያመነ ሰው ይኮነናል ወይ?
አማላጅ ነሽና ለሃጥአን ሁሉ
እኔንም ሰውሪኝ ከመከራ ሁሉ።
ነቢያት በትንቢት የተናገሩልሽ
የሰማይ መላዕክት ስምሽን የሚያገኑሽ
ብፅዕት እያሉ የሚያመሰግኑሽ
እነማን አፈሩ ያመኑ በስምሽ?
ምንም ተስፋ የለኝ አንቺውነሽ እምነቴ
አማልጂን ከልጅሽ ክብርት እመቤቴ
እኛን እንዲያድነን ወገኖችሽ ነንና
ቃሉም አይታበይ ፍርዱም የተቃና
የሰጠሽ ቃልኪዳን አይሻርምና።
ደስ ደስ ይበልሽ ቤዛዊተ ዓለም
አምላክን ስለወለድሽ በቤተልሔም
ክብርን አድሎሻል ለዘለዓለም።
ሰማይና ምድርን የማይችሉትን
ወልደሽ አሳድገሽ መድሃኒዓለምን
አዳምን ለማዳን ቃልኪዳን ገባና
ቅድስተ ቅዱሳን አንቺን መረጠና
ስጋሽን ለበሰ ምድር እንድትፀና።
ዓለምን ለማዳን ከሰማያት ወርዶ
መለኮት ከስጋሽ ፍፁም ተዋሕዶ
ነፃነትን ሰጠን ለኛ ሲል ተዋርዶ።
ወደአንቺ ተማፀንኩ ልመናዬ ፀንቶ
የሰውነቴ ሃጢያት በእኔ ላይ በርክቶ
መሳፍንት እርኩሳን እንዳይቀርቡ ከፊቴ
እንዳይ በረታብኝ በኔ ላይ ጠላቴ
አስታግሽልኝ አንቺ ክብርት እመቤቴ።
ይቀጥላል.....
....የቀጠለ
አምላክን የወለድሽ የሰማዩን ጌታ
ምህረትን አሰጭን ያድለን ይቅርታ።
በስምሽ ሲያጠጣ ሲጓዝ በበርሀ
በላይሰብ ጀኘኘአኸ በአንድ ጥሪኝ ውሃ።
እናትና አባትሽ ልጅ በማጣታቸው
ያለቅሱ እንደነበረ ወደ ፈጣሪያቸው
የወለድን እንደሆን ወንድም ሆነ ሴት
እንሰጣለን አሉ ለእግዚአብሔር ቤት።
ያናገራቸው ይህ ነበር ትንቢቱ
ቀድሶ ሰጣቸው ለዘጠኝ ወር ቤቱ።
እናትና አባትሽ ስመው ሳይጠግቡሽ
ለስለት ወሰዱሽ በሶስት ዓመትሽ
በክብር ስለኖርሽ በቤተመቅደስ
ገብርኤል ሲያበስርሽ የመውለድሽን ዜና
ፍፁም አደነቀው ዓለም ያንቺን ዜና
የመላእክት እህት የሰው ልጅ እናት
በገብርኤል ሰላምታ እናመስግናት
በድንጋሌ ስጋ አምላክን ስትወልድ
ኮከቡን አዩና ከምስራቅ ሲወርድ
ይቀጥላል...
....የቀጠለ
ተነስተው ተጓዙ ሄደው ለመስገድ
ኢየሱስ ክርስቶስ መወለዱን አይተው
ወድቀው ሰገዱለት ከመሬት ተደፍተው
ለኛ በመወለዱ በጣም ተደስተው
ኪሩቤል ሱራፌል የጋረዱልሽ
የብርሃን ደመና ዙርያውን ከቦሽ
መላዕክት ወርደው የሰገዱልሽ
አፁብ ድንቅ እመቤት ማርያም አንቺ ነሽ።
የምንመካብሽ መከታ ጋሻችን
አንቺ ስለሆንሽ ጠላት ድል መንሻችን
እንደ እሳት ይነዳል ባንቺ ላይ ፍቅራችን።
ብዙ መምህራኖች መስክረውልሻል
የአምላክ ካህናት ያገለግሉሻል
እንደ መላዕክትም ይዘምሩልሻል።
ካንቺ ይወለድ ዘንድ ፈቀደ እግዚአብሔር
አዳምን ከሲኦል እንዲያወጣው ወዶ
እንደኛ ሰው ሆነ ስጋን ተዋህዶ
በፍቅሩ ጎበኘን ልጁ በምህረት
ዘመን አስቆጥሮ ዳግመኛ ልደት
ለዓለም ቤዛ ሆነ ስረ መለከት
ስሟ የከበረ ከሁሉ በላይ
ታቦተ ፅዮን ናት ንግስተ ሰማይ
ያገለግሏታል አእላፍ መላዕክት
መሆኗን ሲያጠይቅ የሰማይ ንግስት
ምን ያጠራጥራል አማላጅነቷ
ማርልኝ ስትለው ቆማ በጉልበቷ
ልጄ ወደጄ ሆይ ስለ እናትነቴ
እማፀንሃለው ባጠባሁህ ጡቴ
የምትል ነች ድንግል ቸር አማላጃችን
ለስጋችንም ቢሆን እንኳን ለነፍሳችን
ከፅኑ መከራ የምታድን ናት
እንግዲህ ለክብሯ እንስገድላት።×2
ተፈፀመ ዝንቱ መነባንብ
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ስደቷ ፍቅር ነው
ደረሰ ሰዓቱ
ሰላም ለኪ
ሰላም ለኪ ልበል
ስምሽን ለመጥራት ከቶ ባይገባኝም
ከአፌ መልካም ነገር ከቶ ባይገኝም
በኃጢያቴ ብዛት አንደበቴ ቢያድፍም
ሰላም ለኪ ብየ ማመስገጌ አይቀርም
ሰላም ለኪ ካላልኩ ሕይወቴም አይሰምርም ።
ሰላም ለኪ ብየ ቀኔን ልጀምር
ከጠዋት ጀምሮ ዉሎየ እንዲያምር
የዕለት ፍላጎቴ ለለት እንዲሰምር
የሚያምረዉ ስምሽ ነዉ ኑሮን የሚያሳምር ።
ሰላም ለኪ ብየ ስምሽን ልሰንቅ
ለጉዞ ስነሳ መንገዴ ነዉ ሩቅ
ጥላሽ እንዲያርፍብኝ እንዲከልለኝ
ከክፉ ነገሮች እንዲጠብቀኝ ።
ጥናቴን ስጀምር ሰላም ለኪ ምለዉ
ፈተናም ስሰራ ሰላም ለኪ ምለው
ስራየን በሙሉ እንድትባርኪዉ ነዉ ።
በቃ በአጠቃላይ ስምሽ ስንቄ ነው
በርሃቤ ጊዜ የምመገበዉ
በጥማቴ ጊዜ የምጎነጨዉ ።
ስለዚህ ድንግል ሆይ ሰላም ለኪ ማለት
ሁሉ ነገሬ ነዉ የተቸገርኩ እለት ።
ሰላም ለኪ ልበል አንደበት ባይኖረኝ
ስምሽን ለመጥራት ፍፁም ባይገባኝ
ስምሽን ላመስግን ሰላም ለኪ እያልኩኝ
ድንግል ሆይ ከልጅሽ እንድታስታርቂኝ ።
ድንግል ሆይ የአንቺ ስም ዕፁብ ድንቅ ነዉ
የአዳም ዘር በሙሉ ይህንን ቢያዉቀዉ
ከራሱ ሰላምታ ቀድሞ ሳያወጣ
ሰላም ለኪ ይላል በመልዐኩ ሰላምታ
ከገብርኤል ሰላምታ ትዉልድ የሚዋሰው
የራሱ አንደበት ስለሚያንስሽ ነው
በሰላመ ቅዱስ ገብርኤል ሰላምታ ሰላም ለኪ
ድንግል ሆይ ይጠብቀኝ ዘንድ ኪዳንኪ ።
ቅዱስ ገብርኤል ሆይ አብሳሪዉ መልዐክ
ድንግልን ለማብሰር ከላይ ስትላክ
እንደምን ደስ አለህ ስለተመረጥክ መጠን ነበረዉ ወይ ለደስታህ ልክ?
ቅዱስ ገብርኤል ሆይ አንደበት አዉሰኝ
ስሟን እንዳልጠራ እኔማ ርካሽ ነኝ ።
ቢሆንም በሆነዉ ባልሆነዉ ሰላም ለኪ እላለሁ
ለሆነዉ ላልሆነዉ ስሟ መልስ ስላለዉ ።
ሊቁ ቅዱስ ያሬድ እንደምን ታደልክ
ከማዜምህ በፊት ሰላም ለኪ ብለህ ምስጋና ጀመርክ ።
ስለዚህ ድንግል ሆይ
ሰላም ለኪ ማለት እኔ አላቆምም
ስለ እናትሽ ሀና ስለእ
ኢያቄም
ታድያለሽ እና የእዉነት ሰላም ።
ድንግል ሆይ
በሕይወቴ ላለዉ የቁልፍ ዘመቻ
ሰላም ለኪ ሆኗል የሁሉም መክፈቻ ።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
መነባንብ
፨፨፨፨፨፨፨፨
ክፍል ፩
አለሁ አለሁ ለእናቴ
ለብርታት ጉልበት ፅናቴ
አለሁ!አለሁ ለርስቴ
ሀገሬ ከላይ ነው አባቴ እግዚአብሔር ነው
ዘራፋ! በቀራኒዮ የተሠቀለው
የምስጢር ደሙ እጄን ቢነካው
ከመኝታዬ ከእንቅልፌ ነቃሁ
ዘራፋ!2 አትደፈርም ፅኑ ሃይማኖቴ
አትሠደብም ድንግል እናቴ
ይቀዳ ደሜ ይርገፍ አጥንቴ
መቃብር ልግባ ይቀላ አንገቴ
ልሠደድ ልውጣ ይቅርብኝ ቤቴ
ይቅርብኝ እምቢ ሀብት ንብረቴ
አትደፈርም ፅኑ ሃይማኖቴ።
ዘራፍ!2 አይበጠስም ቃል ማህተቤ
አይበረዝም የእምነት ክታቤ
አትናወጥም ታንኳ መርከቤ
አትለወጥም እውቀት ጥበቤ
አትታደስም ታሪክ እንቅቤ
ከምትቃጠል እኔ ጠግቤ
ሁሉም ይቅርብኝ ልሙት ተርቤ።
ዘራፍ!2 የጀግኖቹ ዘር ጀግና የተባለች
የጳውሎስ ወኔ በፅኑ የጠራኝ
የዲዮስቆሮስ የፀጋው ልጅ ነኝ
ማንም አይነካሽ ፊትሽ አይቆዝም አትዘኚብኝ።
ይቀጥላል....
ክፍል፪
ዘራፍ!2 ታሪክ እምነቴን አልሸጥም ከቶ
የተዋህዶ ስም አይቀርም ጠፍቶ
ፅላት ብራናው አይሔድም ወጥቶ
አይቀርም በእንቶ ፈንቶ
ነገም ይኖራል ልጆች አፍርቶ
ሰው ይማርካል በደማቅ በርቶ
ከቶም አይሞትም ይቆያል ፈክቶ
በብርቱ አለት ዘላለም ፀንቶ
እማ አትዘኚ ልጆች አለንሽ
ይተላለፋል ገድል ታሪክሽ
አይኮበልሉም ውድ ቅርሶችሽ።
ይቀጥላል.
ክፍል፫
ዘራፍ!2 በቀራንዩ የተሠቀለው
የምስጢር ደሙ እጄን ቢነካው
ከመኝታዬ ከእንቅልፌ ነቃሁ
ዘራፍ!2 ሞቶም ተቀብሮም የሚፈሩት
ገድለውት እንኳ የሚሠጉት
መቃብሩ ሳይቀር የሚጠበቅ
ገዳያችንን የሚጠረቅ
ሞትን በሞቱ እየገደለ
የጥንቱን ጠላት ከጥልቅ የጣለ
የሞትን መዝጊያ የሰባበረ
ቀበሪያችንን የቀበረ
መስቀል ላይ ሆኖም የሚያሸንፍ
የጥልን ሠነድ ክስን የሚያጠፋ
ጅራፋ እያየ የማይፈራ
ሁሉን በፍቅር የሚጠራ
የአለም መድሃኒት የይሁዳ አንበሳ
በሶስተኛው ቀን ፈጥኖ የተነሳ
የንጉስ ልጅ ነኝ ስሙም ተፈሪ
ነፃ የሚያወጣ ወጥመድ ሰባሪ
ከቶ አልሠጋ አልሆንም ፈሪ
ዋጋ ከፋዩ ሆኖኛል መሪ።
ይቀጥላል.....
ክፍል፬
ዘራፍ!2 ፍቅርን ታጥቄ ፍቅርን ለብሼ
በንስሐ እንባ ውስጤን አድሼ
የጌታን ስጋ ደሙን ጠጥቼ
በቤትሽ ኖሬ ደጅሽ ፀንቼ
አሁንም ልኑር ጡትሽን ጠብቼ
ዘራፍ!2 ማነው የሚነካሽ የታለወንዱ
ቢፈራገጥም አምላኩ ሆዱ
መሠረትሽን ከቶ አይንዱ
ዘራፍ!2 የቄርሎስ ምላሽ ጥንተ ሃይማኖት
የአባ ጊዮርጊስ ፀሎት ደረሰቱ
የቅዱስ ማርቆስ ወንጌል ስብከት
የአግናጢዎስ የአንበሳ ራቱ
የአባ እንጦስ ብርታት ፅናቱ
የቅዱስ መቃርስ ምናኔ ቤቱ
የቅዱስ ያሬድ ዜማ ስርዓቱ
የአትናቴዎስ ብርታት ስደቱ
የአረጋዊ ወዳጅ እናቱ።
ዛሬም ይስማል ስዓታት ቅኔሽ ዚቅ ማህሌቱ
ይከበራል ነገም ገና ከፍ ይላል መስቀል ፅላቱ
እማ ተዋህዶ መቼም አትጠፋም ይሰማ ፍጥረቱ 2
አትጠፋም... አትጠፋም
አትጠፋም.... እማ ተዋህዶ❕
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
*/ተፈፀመ ዝንቱ መነባንብ\*
የማጀት ሥር ወንጌል
ሙያተኛ ሀገሬ ከማጥገብ ጎደለ በረከት እራቀው የገበታሽ ለዛ፣
ተሻምቶ ለመጉረስ ከበላነው ይልቅ የደፋነው በዛ፡፡
ሙያሽ ባያስደፍር አጀብ ቢሰኙበት፣
ማዕዱ ቢሙላላ ዓይነቱ ቢያምርበት፣
አበዛዙ አይደለም አበላሉ ላይ ነው የገበታሽ ውበት፡፡
እየተማመንን! የፉክክር ቅሚያ በርሃብ እየናጥን፣
ከደፋነው ጠግቦ ውሻችን በለጠን፡፡
ከምርት አላነስን፣
ጎተራችን ሙሉ ጀግና አራሽ መች አጥተን፣
ማሰብ የጎደለው አያያዛችን ነው ገደል የከተተን፡፡
ይልቅ ግዴለሽም! ከምግባር ምጣድ ላይ ሳንበስል አንጋግተሸ ከማዕድ አትምሪን፣
ገበታሽ እንዲያምር ከእግዜር የሚያስታርቅ ፍቅር አስተምሪን፡፡
ገበታ ዕድሜ ነው ባለ ማሰብ መክነን፣
ሳንፀነስ ጃጀን፣
ሳንጣድ አረርን፣
ከዘመን ገበታ ከፊደል አቅድመን ዘር እየቆጠርን፡፡
ገበታ ሀቅ ነው በክፋት ሊጥ ጋግረው ያሻገቱት እውነት፣
በሆዳም እስክስታ ረግጠው ያፈኑት የምስኪናን ጩኸት፡፡
እስከ ልጠይቅሽ በጥም ደዌ ደቆ የረሃብ ጠኔ ደፍቶት እልፍ ትውልድ ያልፋል፣
ቢራ ለመጥመቂያ ሚበተን ገብስ ግን ከሀገር መች ይጠፋል፡፡
ከሆድ በማይሻገር የማጀት ቤት ዕውቀት አጥብበሽ አትለኪን፣
እስቲ መኖር ይግባን ከማስተዋል መቅደስ ሰው መሆን ስበኪን፡፡
ዘመን ካልገበረው ከችጋር ተራራ ከሲኦል ዳር ኑሮ፣
እንዴት ነው መሻገር ከመርፌ ቀዳዳ በጠበበ አይምሮ፡፡
ከምስኪን ዘመን ላይ የማይኖሩበትን ዕድሜ መበዳደር፣
ለአንዲት ማምሻ ደስታ በአያት እስትንፋስ ላይ ቁማር መደራደር፣
ያሳፍራል አይደል?
እያደጉ ማነስ እያነሱ መዝቀጥ፣
አጎንብሶ ያፀናን የድሃ እናት ጉልበት በጭካኔ መርገጥ፣
ያሳምማል አይደል?
መንገስ ከሚያባላስ መጥገብ ከሚያቃቅር ማግኘት ከሚያጎለን፣
ማጣት ውሎ ይግባ ባርነት ይሰንብት ድህነት ይግደለን፡፡
ከረፈደ ፀፀት ደረት እየደቁ ከእግዜር ቢዋቀሱ፣
ትርጉሙ ምንድነው ሲኖር ተቃቅሮ ሲሞት መላቀሱ፡፡
በእናታችን አድባር በፍቅሯ ይሁንብን፣
መድመቅ ካጋደለን ቆሽሸን ይመርብን፡፡
በመጠማት ሲቃ እስትንፋስ እስኪያንቃት ነፍሳችን ትርበትበት፣
ብቻህን ከመጥገብ አብሮ መራብህ ነው ሰው የመሆን ውበት፡፡
በድፍን ግልብ እሚያጋድል ህዝብ የመሆን መንጋ አይንዳን፣
በማሰብ ስር እንፈወስ በሰውነት ፀበል እንዳን፡፡
አየህ! ሰው ስትሆን ከመንጋነት ሚያግድ እረኛ አያሻህም ከህሊናህ በላይ፣
ስታስብ መሪ ነህ በብስለት ከፍታ በማስተዋል ሰማይ፡፡
አየህ! ሰው ስትሆን የጎጥ አረም ነቅለህ በአንድነት መስክ ላይ ፍቅር ትዘራለህ፣
በወረወሩብህ የጥላቻ ድንጋይ ትውልድ የሚያፋቅር ድልድይ ታበጃለህ፡፡
አየህ! ሰው ስትሆን ዝምታህ ኃያል ነው ጀግና የሚያንበረክክ፣
ከፈሪ ቀረርቶ ከባዶ ሰው ጩኀት፣
ሀገር ላምስ ከሚል በመንደር አጀንዳ በአሽኮለሌ ተረት፡፡
አየህ! ሰው ስትሆን ነጻ ነህ እያሉህ መታሰር ያምርሃል፣
መቀመቅ መበስበስ፡፡
የኖርክለት እውነት ሀገር እስኪፈታ፣
በሀቁ እስኪመዘን ስለ በርባን ክብር የቆሸሸው ፍቅር የታሰረው ጌታ፣
ከድል ታሪክ ሰማይ ከሥልጣኔ ዳር ከጥበብ ከፍታ፣
እንሻገራለን ህዝብነትን ትተን ሰው የሆንን ለታ፡፡
በትረ ጥበበ ቢካን ዓለም ሊያንቀጠቅጥ ድል ሥልጣን ቢሰጠው፣
ጀግና መሪ አይደለም ብርቱ ተመሪ ነው ሀገር ሚለውጠው፡፡
አስተውል ወዳጄ ጠልተን ላንጣላ ችለን ላንጋደል ነደን ላንፋጀው፣
የኛው ትርምስ ነው በልቶ ለሚያባላ ጠላት ሚበጀው፡፡
ስጋና ደም እንጂ የአንድነታችን ውል የፍቅራችን ቀለም፣
ያሰመርነው ክልል የታጠርንበት ዘር ቋንቋችን አይደለም፡፡
ከመዋሃድ መቅደስ ትውልድ እናስተምር፣
ዘመን ይመርቀን ፍቅራችን ምን ጎድሎት ደማችን ያስታርቀን፡፡
በልጆቿ አጥንት በደም ኪዳን ምለን የገባንላት ቃል፣
ከጩኀት ያለፈ ዘመን የሚሻገር ተግባር ይጠይቃል፡፡
በአንድ ሃሳብ ተጋምደን በድል ድር እናብር ውድቀታችን ያንቃን፣
ሠርተን እናሳምን ሆነን ድል እንንሳ የአፍ ጀግንነት ይብቃን፡፡
ምስኪኒቷ እናቴ! በሞላ ጎዳና ባልጠበበ ድንበር በዘር ገመድ ታግዳ፣
ነጻ ነኝ ትላለች መንጋነት ያሰረው ባሪያ ትውልድ ወልዳ፡፡
የጀግንነት እብሪት ልባችንን ደፍኖት ማሰብ እየከዳን፣
እንዴት ነው ነጻነት እንዳበደ ፈረስ ስሜት እየነዳን፡፡
ገድሎ የመንገስ ጥማት ጩኀት ላገነነ አመጽ ላጀገነው፣
ለዚህ ምስኪን ትውልድ በጅምላ እየነዱት፣
በመንጋ እያሰበ ነጻነት እንዴት ነው?
ነጻነት ምርጫ ነው አምሮ ቢደላደል ጥፋት ያመነነው የመንጋዎች መንገድ፣
እንቅፋቱን ወዶ ለኖሩለት እውነት ለብቻ መራመድ፡፡
ነጻነት ማመን ነው ቀን ወዶ ቢያጀግን ቀን ጠልቶ ቢከዳም፣
ቢቆሽሹም ቢደምቁም እራስን መቀበል ራስን መምሰል ነው የነጻነት ገዳም፡፡
ነጻነት ማሰብ ነው በአንድነት መለምለም የኔነትን አረም ከህሊና ማጥፋት፣
ዘር ሆኖ ከማነስ ሀገር ሆኖ ማበብ ዓለም ሆኖ መስፋት፡፡
ንገሯት ለሀገሬ በጀግኖቿ ትግል ድንበር ባታስደፍር ከእጀ ገዥ ብትወጣ፣
ነጻ ነኝ እንዳትል በገዛ ልጆቿ በእጅ አዙር ተሸጣ ፡፡
ስሩን ካልሸመነው በመዋሃድ ጥለት በማስተዋል ሸማ፣
ታሪክ አናደምቅም በጭብጨባ ድግስ በሆይ ሆይታ ዜማ፡፡
ምን ብናቀነቅን በየሰልፉ ሜዳ ወኔ ብንደግስም፣
በፈረሰ አይምሮ በደቀቀ አንድነት ሀገር አናድስም፡፡
በጭፍን ከመሮጥ አስቦ ማዝገም ነው የመራመድ ውሉ፣
ሁሉም እንቅፋቶች እስኪጥሉን ድረስ ምርኩዝ ይመስላሉ፡፡
በድፍን ግልብ እሚያጋድል ህዝብ የመሆን መንጋ አይንዳን፣
በማሰብ ስር እንፈወስ በሰውነት ፀበል እንዳን፡፡
ከእግዜር ልንወዳጅ ለምህረቱ ጥላ እምባ ብንደግስም፣
ልብን ሳይመልሱ ለንስሃ መሮጥ ከጽድቅ አያደርስም፡፡
ውብ ነገን እናውርስ ትላንትን አክመን በይቅርታ ፀበል፣
ትውልድ ይጨርሳል ያረገዝነው እምባ የቋጠርነው በቀል፣
ከመስጠት አንጉደል ከቀማኞች ገደል ተረግጠን ብንጣል፣
ካሸከሙን በቀል ምናወርሰው ፍቅር ሀገር ይለውጣል፡፡
ከዕድሏ ጣሪያ ላይ ዘር የቀዳደው ሽንቁሯ ቢበዛም፣
ያ ከንቱ ፎካሪ ባፈጀ ቀረርቶ ሺህ ጉራ ቢነዛም፣
ሚሊዮን ዘር ቢሸጥ አንድ ሀገር አይገዛም፡፡
ኢዮጵያዊነት ነው የትርታችን ልክ የነፍሳችን ግጥም፣
መልስ ቤት በራቀው በከረመ ፀሎት ሰርክ ብታንጋጥም
አጎንብሳ ድሃ ባፀናችው ጉልበት ብትረጋገጥም
ነፍሷን አደህይታ ባሻረችው ቁስል ብትገሸለጥም፣
ሀገር ሆና ገዝፋ በየ ጎጣጎጡ አትርመጠመጥም፡፡
የዘመን እውነት ነን ከደግነት ሰማይ በጥበብ የኖርን፣
ትዕግስትም ልክ አለው ፈርተን እንዳይመስለው ስላቀረቀርን፡፡
ማተብ አስሮን እንጂ ተጣልተን እንዳንቀር በክፍፍል ገደል፣
ከሀገር ክብር በልጦ ሞት ብርቃችን አይደል፡፡
ንገሩት ለዛ ሰው ከዓለም ጫፍ እስከ ጫፍ ኃይል እንደ ተራራ ገዝፎ ቢከመርም፣
ክንዱን አፈርጥሞ እልፍ የሰገደለት ጀግና ቢሰድርም፣
ዓለም የሞተበት የጠላት ማርከሻ ጦር ቢደረድርም፣
በአንድ ዓይናችን ሰላም በኢትዮጵያችን ክብር አንደራደርም!!!
ተዋህዶአትፈርስም
ድርጅት አይደለም በሰዉ የታነጰ
ፖለቲካም አይደል ዘርን ያጣቀሰ
ሚስጥሩ ፍቅር ነዉ ቃላቶች ማይበቃዉ
እኛን ስለመዉደድ በፍቅር ተስቦ
መስቀል ላይ የወጣዉ
በደም ታንጰናል በማይጠፋ ቀለም
ለኛ ብሎ እርሱ ቢሰቀልም
መሰረቱ እየሱስ ነዉ
ግርግዳዉ ቅዱሳን
ግንቦቹ እኛ ነን የእርሱ ምእመናን
ልንወድቅ አንችልም በእርሱ ፍቅር ጰንተናል
እግዚአብሔርን ይዘን ማንስ ይንደናል
ማሃመዳዊም ሁን ወይም ጆቫዊትነስ
ፕሮቴስታንትም ሁን ወይ ደሞ ካቶሊክ
አለቱን ላታፈርስ የሰዉ ደም አታፍስስ
ምንጩንም ላታደርቅ ከመቅደሱ እራቅ
ካህኑ ቢታረድ መቅደሱ ቢቃጠል
እንበዛለን እንጂ የለም የሚጎድል
ስንሞት እንበዛለን
መከራዉ ሲበዛ በፍቅር እንጰናለን
በእሳት ስንቃጠል እንለመልማለን
ከማይደክም አባት ተፈጥረናልና
አርዮስ አትልፋ እንላለን ቀና
ሰልፉ የእኛ ነዉ ድልም የኛ ብቻ
እንደ አሸዋ የበዛን እስካለም ዳርቻ
ካህኑን ግደሉ መቅደሱን አቃጥሉ
ቅጥሩንም አፍርሱ ልጆቹን በትኑ
እናንተ ስትጠፉ እነሱ ቀና ብለዉ
ባባታቸዉ እቤት ይሰበሰባሉ
ይህ ነዉ ክርስትና የማይጠፋ ቀለም
በፍጱም ማይጨልም ሁሌ ሚሰጥ ብርሃን
እናማ አርዮስ ቁርጥህን እወቀዉ
ድል ላታደርግ እንደዉ ነብስህን አታስጨንቀዉ
ሃሰት እዉነትን እስኪ የቱጋር ነዉ አሸንፎየሚያቀዉ
ባንድነት ተነሱ የእምነትን ሰይፍ ያዙ
በፍቅር ማርኩና የዲያቢሎስን
በእምነታችሁ ናዱ
በእምነት እንሞላ በጱናት እንቁም
በተስፋ እንዉጣ
ጠላት አፍሮ እንዲቀር መድረሻ እንዲያጣ
የጦር እቃችሁን ልበሱ እንደ ካባ
ዘመቻዉን አጵኑት ቅድስት ምድር
አርዮስ ሳይገባ
የጦርሰልፍ አንሻም ቀስት አንወረዉርም
ደም እያፈሰስን እርሱ የፈጠረዉን እኛ አንገድልም
ቀስትና ጦር ይዘን አንወጣም ዘመቻ
ጠጠርም አንለቅምም አሳዳጁን መምቻ
የአምላክ መገኛ
አንድ እለት አንድ ወጣት
አንድን የበቁ አባት
በማለት ጠየቀ በጣም ፈልጋለሁ አምላኬን ለማየት
ከልብህ ከፈለክ አምላክን ለማግኘት
ልምራህ ወዳለበት ተነስ ተከተለኝ
ታዲያ ግን አደራ ልመለስ አትበለኝ
አምላክን ለማየት ከልብህ ከፈለግክ
እርሱ ወዳለበት ስንሄድ ታየዋለክ
ካሉት በኋላማ ተነሱ በአንድነት ወደ አምላክ ሊሄዱ
ከጠበቀው በላይ ሩቅ ሲሆንበት ወጣቱ መንገዱ
እስኬት ነዉ ምንሄደው አምላክ የት ነው ያለው
እርሱ አምላክ ሳለ በዚህ በበረሃ ለምን ነው ሚኖረው
እኔ ግን አባቴ ልሞት ነው ደክሞኛል
ከምነግሮት በላይ ጉሮሮዬ ደርቋል
አባቴ ይንገሩኝ አምላክ የት ይገኛል
እኔስ ሄድኩ እንበል እርሱ ግን ያውቀኛል
አሁን ተቃርበናል ልንደርስ ነው አምላክ ጋ
እዚሁ ጠብቀኝ እኔ ግን ልሄድ ነው ሚጠጣ ፍለጋ
አሉትና እኚያ አባት ፈጥነው ተራመዱ
ወጣቱም በድካም ተንጋሎ አያቸው በፍጥነት ሲሄዱ
እራሱን ጠየቀ እጅጉን ተገርሞ
እኚህ አባት ጥንካሬያቸውን ኬት አመጡት ደግሞ
እኚያ አባት ሄደው ትንሽ እንደቆዩ
ወጣቱ ዞረበት ምድርና ሰማዩ
አምላኬን ሳላየው ልሞት ይሆን እንዴ
ምነው ግን ቢያቆየኝ እስካገኘው አንዴ
ብሎ ሳይጨርሰው እዚያው ራሱን ሳተ ተንጋሎ ሜዳ ላይ
ልክ እንደ ነቃ ዙሪያ ገባውን ሲያይ
እኚያ አባት ተቀምጠው ይፀልዩ ነበር
እሱም ቀና ብሎ የሚፀልዩትን ይሰማቸው ጀመር
ይስሙኝማ አባቴ
አምላኬን አየሁት ለዚያውም ሁለቴ
ወዴት አገኘኸው እንዴትስ ለየኸው
ባገኘኸው ጊዜስ ምንድን ነበር ያልከው
እኔ ወጣት ሆኜ በድካም ስሰቃይ
እርሶ ግን ሸምግለው ጥንካሬዎትን ሳይ
ያን ጊዜ አየሁት አምላኬን በእርሶ ላይ
ውሃ ጠምቶኝ ደክሞኝ ህሊናዬን ስቼ
ስነቃ ለየሁት ፀሎቶን ሰምቼ
በል አድምጠኝ ልጄ ታዲያ አሁንስ ገባህ
አምላክ ሁሌም አለ በዙሪያ በደጅህ
ይገለፅልህ ዘንድ
የትም ሳትሰደድ
በተስፋ ጠብቀው ልቦናህን ከፍተህ
ይህንን ስትፈፅም ያኔ ታየዋለህ
አስብ!
እስኪ ልጠይቅህ?
ምን እናድርግ ?
በተፈጥሮ ህግ!
አይጣል ነው አይድረስ...
አይጣል ነው አይድረስ...
(አይመርጤ አሉ)
አይጣል ነው አይድረስ
ሰማይ አይታረስ ንጉስ አይከሰስ።
ይኸው ዛሬም አለ
*
*
አምላኬ አምላኬ!
ተመስገን ጌታዬ ለዚ ላደረስከኝ
በህይወት አኑረህ ዛሬን ላሳየኸኝ
ላልተውከኝ እንዲሁ ምግባሬን አስበህ
ከ ሀፅያቴ ብዛት በኔ ተስፍ ቆርጠህ!።
እኔማ እኔማ!
ምግባረ ከንቱ ነኝ ስሜም አመንዝራ
በሞት አደባባይ ለሞት የምሰራ
ባዶ ነው ኑሮዬ ታሪክ ነው ህይወቴ
ሳልቀበር የሞትኩ ሳልሞት አስቀድሜ
ሻማ የሚበራልኝ በመቃብሬ ላይ ሊከበር ልደቴ!
ኖሬ ማላውቅ አኔ ልታሰብ በሞቴ!!።
ግን ግን አምላኬ ግን!
ይኸው ዛሬም አለ....ልጄ ሆይ እያለ!
ለሀጥአን ነዉ እንጂ ለፃድቃን ያይደለ
ያ የደም መስዋት ላንቺ የተከፈለ
ህይወት አለሽ ልጄ በቃል የታተመ
ነይ ተመለሽ ልጄ...ነይ ወደኔ እያለ!......ይኸው ዛሬም አለ!።