Professional Documents
Culture Documents
ክፍል
እና ምንጮቹን እንዲለዩ ማስቻል ፈተናዎቹን ማለፊያ መንገዶች መጠቆም የአገልጋዮን አዕምሮ ከ secular
ፍፁም ማንነት ጋር እንዲጣጣምና ትግል እንዲጀምር ማስቻል እንዲሁም የቀደሙ የአባቶቻውን ታሪክ
መንፈሳዊ አገልግሎት የያዘ ነው፡፡ሁለተኛው ክፍል ደግሞ በመንፈሳዊ አገልግሎት ስለሚያጋጥሙን ፈተናዎች
እና መፍሄትዎቻቸው የተዳሰሰበት ነው፡፡ በሦስተኛው ክፍልም ስለ ቀደምት ኢትዮጵያ ታሪክ ፣ስለ ወርቃማ
አመሰራረት ታሪክ እንዲሁም የሰንበት ትምህርት ቤቶች አገልግሎት ምን እንደሚመስል ለማየት ተሞክሯል፡፡
ሉቃ 17፡10
ልንተረጉመው እንችላለን፡፡ በቤተክርስቲያን ውስጥ ያለው አገልግሎት ደግሞ ከዚህ ትርጉም በተጨማሪ
“አምልኮት ነው” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል፡፡ ስለዚህ የእግዚአብሔር ልጆች በአገልግሎታቸው ለአምላካቸው
አገልጋዮች ናቸው፡፡ ቅድስት ሥላሴ አንዱንም ፍጥረት ካለዓላማ እንዲሁ በዘፈቀደ አልፈጠሩምና ይልቁንስ
አበው እንዳስተማሩት ሰውና መላእክትን እንዲያመሰግኑ ሌሎቹን ፍጥረታት ደግሞ ለአንክሮ' ለተዘክሮ
'ለምስክርነት ፈጥርዋል፡፡ ስለዚህ ላያገለግል የተፈጠረ ፍጥረት የለም ፡፡ ካልእ ፍጥረታት የሰው ልጅ
በመጣር አገልግለዋል ፡፡ የበለዓም አህያ (ዘፍ 22) እና የቢታኒያ ድንጋዮች (ሉቃ 19)ለዚህ ምስክሮች ናቸው፡፡
እግዚአብሔር አምላክ እስራኤላዊያንን ከዘመናት የግብፅ ስደት ወደ ምድረ ርስት የመመለሻው ወቅት በደረሰ
ጊዜ በሙሴ በኩል ፈርኦንን እንዲያገለግሉኝ ሕዝቤን ልቀቅ (ዘፀ 7፤16) ብሎታል፡፡ የእስራኤላዊያን ከስደት
መመለስ ለመንፈሳዊ አገልግሎት ነው ፡፡ በሌላ አነጋግር ከስደት የመፈታታቸው ዓላማ አገልግሎት ነው፡፡ ከስደት
ተመልሶ እግዚአብሔርን የማያገለግል በስደት ቢኖር ይሻለዋል፡፡ “እንዲያገለግሉኝ” ብሏልና፡፡ በተመሳሳይ የሰው
ልጅ የመፈጠሩ ዓላማ ሃይማኖት እንደመሆኑና ሃይማኖት ደግሞ የማመንና የመታመን ጉዳይ በመሆኑ'
ዘንግቷል፡፡ የመንፈሳዊ አገልግሎት መሰረቱ በቅዱሳት መጻሕፍት የተገለጠው የእግዚአብሔር ፈቃድና ፈቃዱን
ለመፈጸም የሚያተጋን አምላካዊ መመሪያ ነው፡፡ ከዘመነ አበው ጀምሮ፣ በዘመነ ኦሪትም በቅዱሳን አባቶችና
ነቢያት አድሮ የመንፈሳዊ አገልግሎት ተልዕኮንና መመሪያን የሰጠው በፍፁም አንድነትና በልዩ ሦስትነት
የሚመሰገን አምላካችን እግዚአብሔር ነው፡፡ በዘመነ ሐዲስም ከሦስቱ አካላት አንዱ የእግዚአብሔር ልጅ
ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ ከእመቤታችን ድንግል ማርያም ተወልዶ፣ ግዕዘ ህፃናትን ሳያፋልስ በትህትና አድጎ፣
መንፈሳዊ አገልግሎት ምን መምሰል እንዳለበት በተግባር አስተምሮ ለቅዱሳን ሐዋርያት አብነት የሆነ
የአገልግሎት ተልዕኮና መመሪያ ሰጥቷቸዋል፡፡ አብነት የሆነው ተልዕኮ ‹‹እኔ እንደ በጎች በተኩላዎች መካከል
ሁኑ›› የሚለው ታላቅ ቃል ነው (ማቴ 10፡16)፡፡ ጌታችን ይህንን ተልዕኮና መመሪያ የሰጠው ለጊዜው ለደቀ
መዛሙርቱ ሲሆን ኋላም በእነርሱ እግር ተተክተው በመንፈሳዊ አገልግሎት ለሚሳተፉ ሁሉ ነው፡፡
የስልጠናው አላማ
የስልጠናው ይዘት
1.መንፈሳዊ አገልግሎት
1.1 መንፈሳዊነት
1.2 አገልግሎት
በቅዱሱ የእግዚአብሔር መንፈስ የተቃኘ ኑሮ ፡ፈቃደ ሥጋ ወይም የሥጋ ፍላጎት ፈጽመው ቢከተሉት
ከእግዚአብሔር ሊያርቅ፣ ከሕግ ከሥርዓት ሊያናውጽ የሚችል ነው፡፡ ይህ ፈቃድ ለጊዜው ብቻ ይድላኝ፣
ይመቸኝ፣ የሚያሰኝ ሲሆን የወደፊቱንና ዘላለማዊውን የማያገናዝብ ነው፡፡ ይኸው ፈቃድ ሙሉ በሙሉ
1.2 አገልግሎት
አገልግሎት ገለገለ ካለው ግስ ይነሳል፡፡ ገለገለ - ሎሌ ቀጠረ፣ አሽከር አሳደረ ሲሆን አገለገለ - ደግሞ ቀደሰ
፣አወደሰ፣ አመሰገነ፣ ረባ፣ ጠቀመ የሚል ትርጉም ይይዛል፡፡ አገልጋይ -ያገለገለ፣ቅን ሎሌ ሲሆን አገልግሎት
ማንያውም ስጋዊና መንፈሳዊ የማገልገል ስራ ነው፡፡1 ስለዚህ አገልግሎት ማለት መታዘዝ፣ መገዛት፣ መረዳት
መጥቀም... ማለት ይሆናል፡፡ ማንኛውንም ሥጋዊና መንፈሳዊ ሥራ አገልግሎት ነው፡፡ ለመንግሥት የሚሰራ
የመንግሥት አገልጋይ፣ ለግለሰብ የሚሠራ የግለሰብ አገልጋይ፣ ለእግዚአብሔርም የሚሠራ የእግዚአብሔር
አገልጋይ ነው፡፡
1
ደስታ ተክለ ወልድ፡ ዐዲስ የአማርኛ መዝገበቃላት፡ 1921-1950 ዓ.ም ፡ ገፅ 260
የፍቁረ እግዚእ ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት ክፍል የአገልግሎት ማሰልጠኛ ማንዋል ገጽ 5
ስለዚህ ከቀድሞ ዘመን ጀምሮ እግዚአብሔር ሰዎችን ለአገልግሎት ሲመርጥ ሲጠራ ነበረ፡፡ «ማን ይላክልናል፤
ማንን እልካለሁ›› ኢሳ.6፡8 በማለት ኢሳይያስ እንደተናገረው ዛሬም እግዚአብሔር ሰዎች ያገለግሉት ዘንድ
በዚህም የፍቅሩ፣ የበረከቱ ተሳታፊዎች ይሆኑ ዘንድ ይጣራል፡፡
እግዚአብሔር አምላክ ኢሳይያስን ለአገልግሎት ከመጥራቱና የሚላክለት ሰው እንዳጣ ከመናገሩ በፊት ግሩም
የሆነውን ሰማያዊ የምሥጋና ሥርዓት ከሁሉም በላይ የርሱን ክብርና ልዕልና አሳይቶታል፡፡
«ማንን እልካለሁ፤ ማን ይላክልኛል›› ብሎ የተናገረውም ንግግር ኢሳይያስ ከዚህ የምሥጋና ምሥጢር ተሳታፊ
ይሆን ዘንድ እግዚአብሔርን በማገልገል ሱራፌልና ኪሩቤል ያገኙትን ጸጋ ያገኝ ዘንድ እንጂ ቸግሮት እንዳልሆነ
ይረዳ ዘንድ አስቀድሞ ያንን አሳየው፡፡የቤተክርስቲያን አገልግሎት ማለት የዚህ ጥሪ ተሳታፊ መሆን ማለት
ነው፡፡
ኢሳይያስ « ከንፈሮቼ የረከሱብኝ በመሆኔ ከንፈሮቻቸውም በረከሱባቸው ሕዝብ መካከል በመቀመጤ ዓይኖቼ
የሠራዊት ጌታን ንጉሡን እግዚአብሔርን ስላዩ ጠፍቻለሁና ወዮልኝ›› በማለት ተናግሯል፡፡ እግዚአብሔር
ኢሳይያስን ሲጠራው ምስጢሩንም ሲያሳየው ከንፈሮቹ በለምጽ መመታታቸውን ያውቅ ነበር፡፡ኢሳ. 6፡8
2. አገልግሎት መሠረቱን የሚያደርገው የእኛን አቅም ፣ ጉልበት፣ ዕውቀት፣ ችሎታ፣ ክህሎት አይደለም
የመንፈስ ቅዱስን ኃይልን እንጂ፤ ከእኛ የሚጠበቀው ቅንነት፣ ቅናትና ታማኝነት ለአገልግሎትም ታዛዥ
መሆንና መፋጠን ነው፡፡ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ጥበብን የሚሰጥ የጥበብ መንፈስ፣ ዕውቀትን የሚያደል
የዕውቀት መንፈስ፣ ለልግስናው ወደር የሌለው፣ የኃይል መንፈስ ነው፡፡ ጥበብን የሚመላብን የምንናገረውንም
የሚሠጠን እርሱ ነው፡፡ የአገልግሎት ጸጋ ብርታትም ገንዘብም እርሱ ነው፡፡
3. አገልግሎት የክርስቶስ መልእክተኛ መሆን ነው፡፡ መልእክተኛ በሁለንተናዊ ባህርዩ የላከው ማንነት
የሚያስረዳ መሆን ይጠበቅበታል፡፡ እርሱ ቅዱስ ስለሆነ ቅድስናን ፣ እርሱ ፍቅር ስለሆነ ፍቅርን፣ እርሱ ትሑት
4. አገልግሎት የአንድ አገልግሎት ማኅበር አባል ነኝ ብሎ መናገር ወይም ማስመሰል አይደለም በእግዚአብሔር
ቃል መኖር ነው እንጂ፡፡ እንደ እግዚአብሔር ቃል መኖር ስንጀምር ከራሳችን አልፈን የሌሎች ወገኖችን ጭንቀት
የምንካፈል እንሆናለን፡፡ ለሌሎች መኖርንም እንጀምራን፡፡ ክርስቲያን ስለ አራት ነገሮች መኖር ይጠበቅበታል
የመጀመሪያው ለራሱ ነው፡፡ ሰው ለራሱ ማሰብ ሲችል ለራሱ መኖር ይጀምራል፡፡ ለራሱ መኖር የጀመረ ሰው
ቀጥሎ ቤተሰቡን ሊመለከት ይገባዋል፤ ምክንያቱም ቤተሰብ ልዑል እግዚአብሔር የሚመሰገንበት ትንሹ ቤተ
ክርስቲያን ነውና፡፡ ቀጥሎ በዙሪያው ስለሚገኙ ሰዎች ይኖራል፡፡ አራተኛው ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን መኖር
ነው፡፡
5.ሌሎችን ማገልገል ከመጀመራችን በፊት ራሳችንን ማገልገላችንን አለመንዘንጋት ነው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ
መጥምቅ ራሱን ሰላሣ ዘመን ከሰው ተለይቶ አገለገለ፡፡ ሌሎችን ያገለገለው ስድስት ወራትን ብቻ ነበር፡፡ ነገር
ግን አገልግሎቱ ምን ያህል የሰመረ እንደሆነ መመልከት እንችላለን፡፡ ተራራው ዝቅ እንዲል፣ ሸለቆውንም ሜዳ
አደረገ፡፡ ሁሉንም ለክርስቶስ እንዲዘጋጁ አደረገ፡፡ ራሳችን ቃሉ በእኛ ሳይኖር እንደምን ለሌሎች መስጠት
ይቻለናል) እኛ ሕጉንና ትእዛዛቱን ሳንጠብቅ ሌሎችን እንደምን ጠብቁ ማለት ይቻለናል) 6. አገልግሎት
ከእግዚአብሔር ጋር መሆን ነው፡፡ ይህ ደግሞ ጊዜ የሚወሰንለት ሳይሆን ሁሉንም ጊዜ/የወጣትነት፣ ጎልማሳነት፣
የአረጋዊነት ዕድሜ/ ሁሉ የሚመለከት ነው፡፡ ከእውነተኛው የሕይወት ምንጭ ጋር መሆን ነው፡፡ ክርስቶስ
የሰላም ፣ የደስታ፣ የበረከት አምላክ ነው፡፡ ከእርሱ ጋር መሆን ደስታን ያጎናጽፋል፡፡ ሐዋርያት ጌታ ለእኛ በዚህ
መሆን መልካም ነው የማለታቸው ምስጢርም ይኼው ነው፡፡ በሕይወታችን እውነተኛ በረከት ሽልማትም
ነው፡፡ ስለዚህም ነው ጌታ ለደቀመዛሙርቱ እውነት እውነት እላችኋለሁ ስለእኔ ብሎ አባትን ወይም እናትን፣
ወይም ወንድምን፣ እኅትን፣ ልጆችን የተወ በሚመጣው ዓለም መቶ እጥፍን የማይቀበል ማንም የለም /ሉቃ
18፡29-30/ በማለት የተናገረው፡፡
7. ትንሽ መስሎ ቢታይ እንኳን እግዚአብሔር ለእርሱ ተብሎ የሚሠጥን የአገልግሎት ሰዓት ይባርካል፡፡
ከእግዚአብሔር ጋር በመኖራችንና በመስራታችን መባረክ ነው፡፡
8. የምናገልግል ከሆነ አገልግሎት በሕይወታችን ከምንም ነገር በላይ ቅድሚያ ልንሰጠው የሚገባ መሆኑን
አንዘንጋ፡፡ በልባችን ልንገድበው የሚገባ ስፍራ አይኖርም፡፡ አገልግሎትና አገልግሎት ብቻ የምንመካበት ከሆነ
ከእግዚአብሔር የምናስቀድመው ወገን አይኖርም፡፡ የምንኖረው በዓለም ደረጃ ከሆነ የምናስቀድመውም ነገር
በዚሁ መጠን የሚለይ መሆኑን አንዘንጋ፡፡ ስለዚህም ነው ዓለሙንና በዓለሙም ያሉትን አትውደዱ የመባላችን
ምስጢር፡፡ ማንም ዓለሙን ቢወድድ የአባት ፍቅር በእርሱ የለም፡፡/1 ኛ ዮሐ 2፡15/
መንፈሳዊ አገልግሎት
መንፈሳዊ አገልግሎት ምንድን ነው የሚለውን መሰረታዊ ጥያቄ መመለስ በመንፈሳዊ አገልግሎት ውስጥ
የሚኖረንን ሚና ለማወቅ የመጀመሪያው እርምጃ ነው፡፡ መንፈሳዊ አገልግሎት ‹‹መንፈሳዊ (Spiritual)›› እና
‹‹አገልግሎት (Service)›› የሚሉትን ቃላቶች የያዘ ሲሆን ‹‹መንፈሳዊ›› የሚለው ገላጭ የአገልግሎቱን
ዓላማና መሪ የሚያሳይ ነው፡፡ መንፈሳዊ አገልግሎት ዓላማው የሰው ልጆች ድኅነት ነው፡፡ መሪውም መንፈስ
ቅዱስ ነው፡፡ የክህነት አገልግሎትን ጨምሮ ሰው በመንፈሳዊ ሕይወቱ ስለ ጸጋ /በጎ ዋጋ/ ብሎ የሚያደርገው
በጎ ነገር ሁሉ አገልግሎት ሊባል ይችላል፡፡በአጠቃላይ የሰው ልጆች ለመንግስተ ሰማያት እንዲበቁ የሚደረግ
ማንኛውም እንቅስቃሴ ‹‹መንፈሳዊ አገልግሎት›› ሊባል ይችላል፡፡ ይህም የሕይወትን ቃል ያላወቁ ወገኖች
እንዲያውቁና እንዲያምኑ ማድረግ፣ ያመኑት ደግሞ እንዲጸኑና መንፈሳዊ ትሩፋትን እንዲሠሩ ማድረግን
ያካትታል፡፡
ለዚህ የሚስማማ አንድ የግሪክ ቃል አለ «ዲያኮንያ (Diaknia) ይሉታል::2 በቤተክርስቲያን ሱታፌ ማድረግ፣
አንድ ቦታ መያዝ መንፈሳዊ አገልግሎት ይባላል፡፡
ቅዱሳት ነብያት ሐዋርያት ጋር እንዲሁም በቤተክርስቲያን ንዋያተ ቅዱሳት በኩል በሃይማኖት የሚደረግ
ግንኙነት እና ስርአተ አምልኮ ነውመንፈሳዊ አገልግሎት የምንለው የእግዚአብሔር የሆነውና መንፈሳዊ ዓላማን
መሠረት በማድረግ የሚገለገለውን ነው፡፡ መንፈሳዊ አገልግሎትን ከሌሎች አገልግሎቶች/ ሥራዎች የሚለዩት
በርካታ ጠባያት አሉ፡፡ ትልቁና መሠረታዊው ልዩነት ዓላማው ነው፡፡ በመንፈስ ቅዱስ የሚመራ የመንፈሳውያን
በእውነትና በፍቅር የሚሳድግ (ኤፌ. 4፡15) የሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ስንተረጉም ማንኛውም ሥራ ሠርቶ
በዕምነት ብቻ በመሆን (ዕብ. 11፡6)መንፈሳዊ አገልግሎት የመታመን ሥራ ነው፡፡ ሃይማኖት ማለት ማመንና
መታመን ማለት እንደመሆኑ አምላክን አምነን የምንታመነው በመንፈሳዊ አገልግሎት መሆኑን መገንዘብ
ያስፈልጋል፡፡
2
Diakonia is a Christian theological term from Greek that encompasses the call to serve the poor
and oppressed.
አስረጂ፡- ‹‹… ውዳሴ ከንቱ መሻት የገሃነመ እሳት እናት ናት ፡፡ ውዳሴ ከንቱ መሻት እሳቱ ለማይጠፋው ትሉ
ለማያንቀላፈው ዓለም መጋቢዋ ናት ፡፡ ›› ቅዱስ ዮሐንስ አፈውርቅ
በዚህ ዓለም ሲኖሩ መልካም ያደረጉ ሁሉ ስማቸውና መልካም ሥራቸው ሲወሳ ይኖራል፡፡ በሰው ፊት
የተመሰገነ ሥራው ይረሳ ይሆናል፡፡ በእግዚአብሔር ፊት የሚያስመሰግን ሥራ የሠራውን ግን ሰው
ቢረሳው እንኳን እግዚአብሔር አይረሳውም፡፡ የእግዚአብሔር ሰዎችም አይረሱትም፡፡ ይልቁንም
ሥራውን ምሳሌ አድርገው ሲያወሱት ይኖራሉ፡፡ «ኤልያስ አንደ እኛ ሰው ነበረ ዝናብም እንዳይዘንብ
አጥብቆ ጸለየ . . . » ተብሎ የተጻፈውም ይህን ያሳያል፡፡ ያዕ. 5፤17
ከዚህ የሚበልጥ ፍቅር የታለ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ዓለሙን እንዲሁ ወድዋልና፡፡ዮሐ 3፣16
የአገልጋይ እጅግ አስፈላጊ የሆነ ባሕርይ ፍቅረ እግዚአብሔር ነው፡፡ እግዚአብሔርን የምንወደው ከሆነ
ፈተናው፣ ችግሩ ፣ ተግዳሮቱ፣ ማስፈራራቱ፣ ራቡ፣ ጥሙ፣ ስደቱ መከራው አይከብደንም፡፡
የቤተክርስቲያን ተልዕኮ
1. ያላመኑትን ማሳመን
2. ያመኑትን ማጽናት
ለ ቅድስት ቤተክርስቲያናችን ዋስ ጠበቃ የሚሆኑ ምዕመናን ማፍራት አንዱ እና ዋነኛው የአገልግሎት ዓለማ
ነው ፡፡ ቤተክርስቲያን ተስፋ የሌለው ወጣት በወጣቱም ተስፋ የሌላት ቤተክርስቲያን እንዳናይ ጠንክረን
በምግባር በሃይማኖት የጽና ትውልድን ማፍራት አለብን ፡፡
ፍጥረታት ሁሉ አገልጋዮች ናቸው፡፡ ቅድስት ሥላሴ አንዱንም ፍጥረት ካለዓላማ እንዲሁ በዘፈቀደ
አልፈጠሩምና ይልቁንስ አበው እንዳስተማሩት ሰውና መላእክትን እንዲያመሰግኑ ሌሎቹን ፍጥረታት ደግሞ
ለአንክሮ፣ ለተዘክሮ፣ ለምስክርነት ፈጥረዋል፡፡ ስለዚህ ላያገለግል የተፈጠረ ፍጥረት የለም፡፡ ካልእ ፍጥረታት
እየመሰከሩ ሰውን ወደተፈጠረበት ዓላማ (አገልግሎት) ለመመለስ በመጣር አገልግለዋል፡፡ የበለዓም አህያ (ዘፍ
በዕብራውያን መልእክቱ ምዕራፍ 1 ቁጥር 14 ላይ ‘ሁሉ መዳንን ይወርሱ ዘንድ ስላላቸው ለማገዝ የሚላኩ
የሚያገለግሉ ያላቸው መላእክትን ነው፡፡ ልበ አምላክ ዳዊትም ‘መላእክቱን መንፈስ የሚያደርግ አገልጋዮቹንም
የእሳት ነበልባል’ በማለት (መዝ 103፡4) ይህንኑ አጠናክሯል፡፡ ነቢዩ ኢሳይያስና ነባቤ መለኮት ዮሐንስም
የሰው ልጅ የመፈጠሩ ዓላማ ሃይማኖት እንደመሆኑና ሃይማኖት ደግሞ የማመንና የመታመን ጉዳይ በመሆኑ፣
እንደዚሁም መታመን በመንፈሳዊ አገልግሎት ይገለጣል፡፡ መንፈሳዊ አገልጋይ ማለት እራሱን ለመንፈሳዊ ስራ
ወይም አገልግሎት የለየ፤ የእግዚአብሔርን መንገድ የመረጠና የሚከተል ማለት ነው፡፡ ማቴ 19÷27-30 «እነሆ
እኛ ሁሉን ትተን ተከተልንህ እንኪያስ ምን እንናገኝ ይሆን »፣መዝ 118፤105‹‹ሕግህ ለእግሬ መብራት
መንፈሳዊ አገልጋይ በተሰጠው ጸጋ የሚያገለግልና ፈቃደኛ የሆነ የእግዚአብሔር መልዕክተኛ ነው፡፡ 1 ኛቆሮ 12
ልዩ ልዩ ነው…» ኢሳ 6፤8 መንፈሳዊ አገልጋይ ሕያው መጽሐፍ ቅዱስ ወይም ተንቀሳቃሽ ቤተ ክርስቲያን
ነው፡፡መንፈሳዊ አገልጋይ የሚናገር ብቻ ሳይሆን ህጉና ስርዓቱ የሚፈጸበት የሚነበብ ፊደል ነው፡፡ 1 ኛ ጢሞ
መንፈሳዊ አገልጋይ ያለ ማቋረጥ ወደ እግዚአብሔር የሚጓዝ ነው፡፡ እግዚአብሔር ሁል ጊዜ በልቡ ውስጥ ስላለ
በሚሰማው ነገር ይማራል፡፡ሉቃ 10፤42 ፣1 ኛ ጢሞ 4፤16 መንፈሳዊ አገልጋይ ሁልጊዜ ይሰራል፡፡ዮሐ 5፤17
በቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ አገልግሎት የሚሠጥ ሰው አስቀድሞ ራሱን ማዘጋጀት ይኖርበታል፡፡ «የልብ
መዘጋጀት ከሰው ነው የምላስ መልስ ግን ከእግዚአብሔር ነው፡፡» /ምሳ.16፤1/ ምክንያቱም
በመንፈሳዊ አገልግሎት ውስጥ ተስፋ የምናደርገውን ሰማያዊ ጸጋ ለማግኘት ስንጥር ፈተና ይገጥመናልና ነው፡፡
ይህንንም አልፎ ለክብር ለመብቃት መዘጋጀት የግድ ያስፈልጋል፡፡
ሀ/ ፈቃደኝነት
እግዚአብሔር የሚሰጠውን የጸጋ ስጦታ ተቀብሎ ማገልገል እንደሚገባ ቅዱሳት መጻሕፍት ያስተምሩናል፡፡
/1 ኛቆሮ.12፤11/ለአገልግሎት የተጠራ ሰው ጥሪውን በፈቃደኝነት መቀበልና ለዚህ አገልግሎትም የጠራው
እግዚአብሔር መሆኑን መገንዘብና ማመን አለበት፡፡2 ኛ ዜና 11፣29 እግዚአብሔርንና ቤቱን ማክበር፣ ራስንም
ዝቅ ማድረግ ይገባል፡፡ ከአምላካችን ከኢየሱስ ክርስቶስ የተማርነውም ይህንኑ ነው፡፡ «እኔ ለእናንተ እንዳደረግሁ
እናንተ ደግሞ ታደርጉ ዘንድ ምሳሌ ሰጥቻችኋለሁ » ዮሐ. 13፤15
ለ/ የዓላማ ጽናት
አንድ ሰው ረዥም ጉዞ ሲጀምር ካሰበው ሳይደርስ የሚጥሙትን ችግሮችና ፈተናዎች ማለፍ የሚችለው
ዓላማ ሲኖረው ነው፡፡ዓላማ የሌለው ሰው ወደየት እንደሚሔድ አያውቅም፡፡ ዓላማ ያለው ሰው ግን መንገዱን
ያውቃል፡፡ መንፈሳዊ አገልጋይም ዓላማው ምን እንደሆነ በአንክሮ ተረድቶ ፣ለምን እንደሚያገለግልና በየት
በኩል እንደሚጓዝ አውቆ ያገለግላል፡፡
መንፈሳዊ አገልግሎት ዓላማው እግዚአብሔርን ማግኘት ከእርሱም ጋር መኖር ነው፡፡ በራሱም ሆነ በሌላው
ሕይወት ውስጥ የመንፈስን ፍሬ ማፍራት ነው፡፡ ይህ ደግሞ ያለ እግዚአብሔር አጋዥነት ሊሆን አይችልም፡፡
«ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉም» ብሏል፡፡ ዮሐ.15፤5 ስለዚህ አገልጋይ የሆነ ሰው ለሥራው መነሻ፣
መገስገሻና መድረሻ የሚያደርገው ዓላማ ሊኖረው ይገባል፡፡
ከዓላማ የሚያርቁ ቀዳዳዎችን መድፈን ከመሳት ይጠብቃል፡፡ መንፈሳዊ አገልግሎት የአንድ ሰሞን የስሜት
ሩጫ ሳይሆን እስከመጨረሻው ድረስ የሚሮጡት ሩጫ ነው፡፡ «እሰከሞት ድረስ የታመንክ ሁን» እንደተባለ፡፡
ራእ.2፤10
ሐ/ አርአያነት
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሕዝቡ አርአያና ምሳሌ እንዲሆኑ ከዓለም ለይቶ የጠራቸውን ቅዱሳን
ሐዋርያትን ለሥራ ያዘጋጀው በምሳሌነትና በቃሉ ትምሕርት ነው፡፡ ኑ ተመልከቱኝ እንዳላቸው የሚሠራውን
እያዩ ጸንተው ኖሩ፡፡ዮሐ 1፣44
የእግዚአብሔርን ፍቅርና ከእርሱ ጋር የመኖርን ጣዕም ያወቀ አገልጋይ በመከራ፣ በችግር፣ በስደት እና
በብቸኝነቱ ጊዜ በሃይማኖቱ በመጽናት ለሕዝቡ ምሳሌ ይሆናል፡፡«እግዚአብሔርን ለሚወዱት እንደአሳቡም
ለተጠሩት ነገር ሁሉ ለበጎ እንዲደረግ እናውቃለን» ተብሎ የተጻፈውም ለዚሁ ነው፡፡ /ሮሜ 8፤28/
አንድ አገልጋይ የምንነግራችሁን እንጂ የምንሠራውን አትዩ እያለ ቢያገለግል የማንንም ሕይወት አያንጽም፡፡
ስለሆነም ራሱን ከነውርና ከነቀፋ ለይቶ ሊኖር ግድ ነው፡፡ ለዚህ ነው ቅዱስ ጳውሎስ «ወንድሞች ሆይ
ሰውነታችሁን እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝና ሕያው ቅዱስም መሥዋዕት አድርጋችሁ ታቀርቡ ዘንድ
በእግዚአብሔር ርኀራኄ እለምናችኋለሁ፡- እርሱም ለአእምሮ የሚመች አገልግሎታችሁ ነው» በማለት
የተናገረው ሮሜ 12፤5 አንድ ሰው ለሌሎች አርአያ ሆኖ ሲያገለግል በውጤቱ ይደሰታል፣ እግዚአብሔርንም
ያስመሰግናል፡፡ራስህ ስትገል ያየህ ሁሉ ሞቷል እንደሚባለው….
2. ቅዱስ ጴጥሮስ ጌታን ክዶ ሲያበቃ ወዲያው በዶሮው ጩኸት ነቅቶና ወደ ልቡ ተመልሶ ንስሐ ገብቶ
ለትልቅ ማዕረግ ሲበቃ ጊዜውን በአግባቡ ያልተጠቀመውና ማስተዋል የተሳነው የአስቆሮቱ ይሁዳ
የሕይወት ሞትን እንዲሞት ሆኖአል፡፡
3.ቅዱስ ዳዊት የኦርዮንን ሚስት በመቀማቱ ሐጢአት መስራቱ ሲነገረው ወዲያው ንስሐ ገብቶ
ከአምላኩ ታርቆ ልበ አምላክ እስኪሰኝ ድረስ በእግዚአብሔር መወደድ ችሎአል፡፡ቆሬና ዳታን
ከወገኖቻቸው ጋር የጠፉት እናንተ ማጠን አትችሉም ፤አልተመረጣችሁም ፤ተብለው በሙሴና በአሮን
ሲገሰጹ አልሰማ በማለታቸውና ፈጥነው ንስሐ ባለመግባታቸው ነበረ፡፡
የመንፈሳዊ አገልግሎት ዋጋ፡-አሁን ተከፍሎ አሁን በሁዋላ እንደሚያጡት ምድራዊ ደመወዝ አይደለም
የሚከፈለው ቃሉ በማይለወጠው አምላክ በልዑል እግዚአብሔር ነው ፡፡ ብልና ነቀዝ የሚያበላሸውና ታይቶ
የሚጠፋ ያይደለ ከሰው አሳብ በላይ የሆነ ስጦታ ነው፡፡አገልጋዮች ተስፋ ሊያደርጉት የሚገባ ደመወዝም ይህ
ነው፡፡ «ወደፊት የጽድቅ አክሊል ተዘጋጅቶልኛል፡፡ ይህንንም ጻድቅ ፈራጅ የሆነው ጌታ ያን ቀን ለእኔ
ያስረክባል፡፡ ደግሞም መገለጡን ለሚወዱት ሁሉ እንጂ ለእኔ ብቻ አይደለም ፡፡» 2 ጢሞ. 4፤8
ቀ/ ፍቅር
ዘመናዊ የሚለው ቃል ቀጥታ ትርጉሙን ስንመለከት፣ “ዘመን” ማለት ዓመትን ወይም ጊዜን የሚያመለክት
የግእዝ ስም ሲኾን ዘመናዊ የሚለው ቅጽልም “ዘመኑ ሲሄድ፣ ሲጨምር ከዘመኑ ጋር አብሮ የሚሄድ፤
በቀድሞው ዘመን ላይ ተኝቶ ኋላቀር ያልኾነ፤ ዕድገቱ ያላቋረጠ፤ ባለፈው ዘመን ከነበረበት ከፍ ብሎ
ከዘመኑ/ከጊዜው እኩል ያደገ” እንደማለት ነው፡፡ ለኦርቶዶክሳዊያን ክርስቲያኖች መዘመን የጊዜ እሳቤ ሳይሆን
የማንነት ጥበቃና ያንን ማንነት ሉላዊ የማድረግ ፍላጎት በመሆኑ፣ የዘመናዊ ሳይንስ ውጤት አጠቃቀም
ከዚህ ዓላማ በሚስማማ መሆን ይገባዋል፡፡
2. በአኗኗር፣
ያለፈውን ትቶ (አዲስና በዘመኑ በተለያየ ዘርፍ የበላይነት ካላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎች ጋር የሚስማማ)፣
አዲስ የመጣ (የተቀዳ) ወይንም የተፈጠረ አስተሳሰብን መቀበልና የተቀበሉትን አስተሳሰብ የሚያንፀባርቅ
አነጋገር፣ አሠራር፣ እምነት፣ ባህል ወዘተ ማሳየት የሚሉት ፅንሰ ሀሳቦች መዘመንን ሊገልፁ ይችላሉ፡፡በፍልስፍና
ክርክርና የኅብረተሰብ ትምህርት ለውጥ ምክኒያት የተወሰነው አይነት አስተሳሰብ አይሎ ብዙሃንና የተለያየ
አቅም ያላቸውን ክፍሎችን ማስከተል ሲችል የአዲሱ አስተሳሰብ ተከታዮች የዘመኑ፣ የተሻሻሉ
ይባላሉ፣ተቃራኒዎቹ ኃላቀር፣ ጎታች፣ ጎጂዎች ይሰኛሉ፡
ሥልጣኔ ፣ እድገት፣ መሻሻል፣ ማወቅ፣ ሰው መሆን ሁሉ በሴኩላር ሂዩማኒዝም ማእቀፈ እሳቤ የሚመራ
በመሆኑ መደበኛ ትምህርት፣ ዘመናዊው ሥርዓተ መንግሥት፣ የማኅበራዊና ኢኮኒሚያዊ ሥርዓት ፣
የአስተዳደር መመሪያ ሁሉ በሴኩላር ሂዩማኒዝም መሥፍርት የሚመዘን ነው፡፡
መንፈሳዊ አገልጋይ በሕይወቱ ዘመን ሁሉ በአገልግሎቱ ውስጥ ምሳሌና በረከት ነው፡፡አገልጋይ ለሚያገለግለው
ሕዝብ ምሳሌና በረከትይሆናል፤ ለእራሱም ከእግዚአብሔር በረከትን ያገኛል፡፡ታዲያ የአገልጋዮች መንፈሳዊነት
በማህበራዊ ህይወት እንዴት ሊገለጥ ይችላል
በቤተክርስቲያን
በስራቦታ
የስራ ቦታ ሰዎች ስራ በመስራ የሚውሉበት ቦታ ነው፡፡እዚያ ቦታ ለምን እንደተቀመጡ እንደ ክርስቲያን ማሰብ
ካልተቻለ ያ ቦታ ደሞዝ የሚገንበት ብቻ እንጂ ሰዎችን የሚረዱበትና የሚገለግሉበት መሆኑን ይረሱታል፡፡
በተሰጠን የሥራቦታ በታማኝነት፣ በታታሪነት፣በርህራሄ፣የግለሰቦችን ችግር እንደራስ በመቁጠር ሃላፊነታችንን
የማንወጣ ከሆነ ከመንፈሳዊነት እየራቅን ነው ማለት ነው፡፡መንፈሳዊ ህይወት በመስሪ ቤት ሲገለጥ
ከአድሎኣዊነት፣ ከዝምድና፣ ከሙስና፣ ከግዴለሽነት፣ ከራወዳድነት፣ ከሌሎችም ስጋዊ አመለካቶች የፀዳ ሆኖ
ይታያል፡፡ይህ መንፈሳዊ ህይወት በመንፈሳዊም ሆነ በስጋዊ መስሪያ ቤቶች ስራ ላይ ከዋለ አገርም ምድርም
የተባረከ፣ ህዝብም የተከበረ ይሆናል፡፡
በትምህርት ቤት
በጎረቤት
ማንኛውም መንፈሰዊ ህይወት ከግል ህይወት ጀምሮበቤተሰብ አልፎ እስከ ጎረቤት እየተጠናከረ ሄዶ አለም
አቀፍ ደረጃ ይደርስና ፀጋን ያጎናጽፋል፡፡በመንፈሳዊ ህይወት የሚመራ አገልጋይ የጎረቤቶቹንም አኗኗረ
ይመለከታል፡፡ምናልባት የማይለምኑ ግን የሚራቡ፣የሚታመሙ ግን መታከሚያ የሌላቸው፣ የሚማሩ ግን
ወደስጋወ ደሙ ያልቀረቡ መኖራቸወን በመገንዘብና የሚችሉትን ማድረግ ተገቢ ነው፡፡ይህን ያላገናዘበ
መንፈሳዊ ህይወት የነዌ ህይወት መሆኑ ነው፡፡መንፈሳዊ ህይወት ከራስ ባሻገር የሌሎችን ችግር መረዳት
የሚጀምር መሆን አለበት፡፡
በቤተሰብ
ቤተሰብ የማህበረሰብ መቅጃ ምንጭ ነወ፡፡ ምንጭ ደግሞ በጥንቃቄ የመያዝ ግዴታ አለበት፡፡ ቤተሰብ
የሚገባውን ህይወት ሳያገኝ መንፈሳዊ ህይወትን በርቀት መጀመር ችግኙን እየረገጡ ዛፉን መንከባከብ ነው፡፡
እንክብካቤ ከችግኝ ከተጀመረ የተዋጣለት ዛፍ ማግኝ ይቻላል፡፡4
በግል ሕይወቱ
አንድ አገልጋይ ጥሩ መንፈሳዊ ሕይወትን መምራት ከቻለ የሰማያዊውን ሕይወት በምድር ላይ የተለማመደ
ብቻ ሳይሆን ራሱን በሥነ ምግባር ያነጸ ምርጥ ዜጋም ይሆናል፡፡ ስለሆነም በቤትና በትምህርት ቤትም ሆነ
ይሰብካል፡፡ እንዲህ አይነቱ አገልጋይ በኑሮው በማይመች አካሄድ ያልተጠመደ፣ ክፉ ባልንጀርነትን ያራቀና
4
አገልጋይ በመንፈሳዊና በማህበራዊ ህይወት መካከል፣ሊቀ ጠበብት ሐረገወይን እና አዱኛ ማእምር፣ ማህበረ ቅዱሳን 1998 ዓ.ም
የምዕራፉ አላማ
የምዕራፉ ይዘት
የአገልግሎት ሕይወት የተሳካ እንዳይሆን የሚያደርጉት ብዙ ነገሮች ይኖራሉ፡፡ እነዚህ ምክንያቶች ሰዎች
በራሳቸው ደካማነት ያመጧቸው ወይም የነበሩበት አካባቢና ማኅበረሰብ ያደረሰባቸው ተጽዕኖና ከሌሎች
ሰዎች አልያም ደግሞ ከርኩሳን መናፍስት የሚመጣ ውጤት ይሆናል፡፡
መጋደላችን ከስጋና ከደም ጋር ስላልሆነ ነው፡፡ ኤፌ 6፤12 “መጋደላችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለምና፥
ከአለቆችና ከሥልጣናት ጋር ከዚህም ከጨለማ ዓለም ገዦች ጋር በሰማያዊም ስፍራ ካለ ከክፋት መንፈሳውያን
ሠራዊት ጋር ነው እንጂ….እንዳለ ሐዋርያው! በምድር በሚኖረን አገልግሎት ሁሉ የመልካም ነገሮች ጠላት
የሆነው ዲያብሎስ አርፎ አይተኛምና በፈተና እንድንፈተን ያደርገናል፡፡
እንዴት?
ሰው በተለያዩ መዝናኛዎች የህይወትን ትርጉም distort እያደረገው ነው፤ ሁልግዜ ማስተዋል ያለብን
ለኦርቶዶክስ ከመስቀል የሚያርቀው ነገር ሁሉ ውበት የለውም!
በአገልግሎት ለሚነሱ ፈተናዎች ምንጮች የሚሆኑት ከሁለት ነገር የሚነሱ ናቸው፡፡እነሱም ውስጣዊእና
ውጫዊ ናቸው፡፡
2.2.1 ውስጣዊ
ከአገልጋዩ ከውስጥ ከራስ የሚመነጭ ፣የሌላ የውጭ አካል ጣልቃገብነት እና ጫና ሳይኖር የሚፈጠር ነው፡፡
ምቹ ሁኔታዎችን መፈለግ
አገልገሎት በሚመቸውም በማይመቸውም ጠመዝማዛ መንገድ ወጥተን ወርደን አንድ ውጤት ማሳየትን ግድ
ይላል፡፡በአገልግሎት ውስጥ የሚከሰቱ ልዩ ልዩ ፈተናዎችን ተቋቁሞ ማገልግል በፈቃዳችን የተቀበልነው
ኃላፊነት ነው፡፡ ይህ ከሆነ የአገልግሎትን ጣዕም እናውቃለን፡፡ፈተናዎችን ለማቃለል ባደረግነው ውጣውረድ
ብዙ እንማራለን፡፡አገልግሎት የማያቋርጥ ሂደት በመሆኑ የሚገጥሙን ችግሮችና ፈተናቸውን አይነትና
መልካቸውን እየለዋወጡ ይከሰታሉ፡፡
ግድየለሽነት እና ቸልተኛነት
It isn't that they can't see the solution. It is that they can't see the problem.” G.K. Chesterton
ቸልተኝነት በግዛቱ ስር እየጣለን ሲመጣ ከግል ሥጋዊና መንፈሳዊ የህይወት ዘይቤ አውጥቶን ብቻ ዝም
አይልም፡፡ለቤተክርስቲያንና ለማህበረሰባችን የምንተርፍበትን እግዚአብሔር ለህዝቦቹ የሚኖረውን ፈቃድ
የምንፈጽምበትን አገልግሎታችንንም እንዳንወጣው ያደርገናል፡፡ልንሸፍነው የሚገባን የቤተክርስቲያን ቀዳዳ
እያለ ተገንዝበን ፀጋዬ ነው አይደለም ብሎ መመንታት የተረበ ሰው አይቶ እንጀራ ልስጠው ወይስ ዳቦ እያለ
የሚያማርጥ ሰውን ይመስላል፡፡
አስረጂ፡- በየ 10 አመታት ልዩነት በሚደረገው የህዝብ ቆጠራ የኦርቶዶክሱ ቁጥር ምን ያህል እያሽቆለቆለ
እንደሆነና የሌሎች ቤተእምነቶች ቁጥር ደግሞ ምን ያህል እያሻቀበ እንደሆነ ያሳያል፡፡ በእርግጥ ይሄ ጠፍቶን
ሳይሆን እንዳላየ እንዳልሰማ በቸልተንነት ስለምናልፈው እንጂ….
60.0
54.0
50.6
50.0
43.5
40.0
32.9 32.8 33.9
30.0
18.6
20.0
10.2
10.0 6.6
5.5 5.6
3.3
1.0 0.9 0.7
0.0
Orothodox Protestant Catholic Muslim Others
የስሜት ጫና
አስረጂ፡-
Emotional
ስሜ ታ ዊ
Intellectual
አዕም ሮ ኣዊ
Spiritual
መን ፈ ሳ ዊ
የመንፈስ ዝለት
መንፈሳዊ እንደሆንን እያሰብን እና እየተሰማን ነገር ግን ቀድሞ የነበረንን ብርታት በመተው የሚሰማን
የድካምና የመሰልቸት ስሜት ነው፡፡ተራ፣አንፃራዊ ወይም አደገኛ ሊሆን ይችላል፡፡
ዝለት በጥልቀት ሳይገቡ ከእግዚአብሔር ጋር ከላይ ከላይ የሚደረግ ውጫዊ ግንኙነት ነው፡፡ መንፈሳዊ
እንደሆንን እያሰብን እና እየተሰማን ነገር ግን ቀድሞ የነበረንን ብርታት በመተው የሚሰማን የድካምነሰ
የመሰልቸት ስሜት ነው፡፡ሂደቱም ከፍቅር ወደ ወረት፣ ከመንፈሳዊነት ወደ ዓለማዊነት፣ ከመንፈሳዊ ተግባር
ወደ ዓለማዊ ተግባር፣ስለእግዚአብሔር ከማሰብ ስለሰው ማሰብ፣ወዘተ የሚወስድ ነው፡፡
የዝለት መንስኤዎች
መንፈሳዊ ሰው በተለያዩ ምክንያቶች ሊዝል ወይም ሊደክም ይችላል፡፡ሰው በተፈጥሮው የሥጋ ድካም ያለበት
በመሆኑ፡ ይህ ድካም በራሱ ስህተት የመጣ ሳይሆን በአካሉ ወይም በህሊናው የተወሰነ ድካም ወይም በስራ
ብዛት ሲጠመድ የሚመጣ ነው፡፡”መንፈስ ተዘጋጅታለች ሥጋ ግን ደካማ ነው፡፡” ማቴ 26፡41 ይህ የአካል ድካም
ለመንፈሳዊ ሥራ እንቅፋት ሆኖ መንፈሳዊ ዝለትን ያመጣል፡፡
2.2.2 ውጫዊ
በሌላ የውጭ አካል ጣልቃገብነት እና ጫና እንዲሁም ግፊት አማካኝነት ከመንፈሳዊ አገልግሎት የሚያርቅ
ነው፡፡
በአገልግሎት አለመናበብ
አስረጂ፡ ሐዋ 15፡36 “በርናባስም ማርቆስ የተባለውን ዮሐንስን ደግሞ ከእነርሱ ጋር ይወስድ ዘንድ አሰበ፤
ጳውሎስ ግን ይህን ከእነርሱ ጋር ሊወስድ አልፈቀደም፥ ከእነርሱ ዘንድ ከጵንፍልያ ተለይቶ ነበርና፥ ወደ ሥራም
ከእነርሱ ጋር አልመጣም ነበርና።ስለዚህም እርስ በርሳቸው እስኪለያዩ ድረስ መከፋፋት ሆነ፥ በርናባስም
ማርቆስን ይዞ በመርከብ ወደ ቆጵሮስ ሄደ። ጳውሎስ ግን ሲላስን መረጠ፥ ወንድሞችም ለእግዚአብሔር ጸጋ
አደራ ከሰጡት በኋላ ወጣ”
በአሳብ መለያየት
በአገልግሎት ውስጥ የሚሰበሰቡ ሰዎች የየራሳቸው ጠባይና አስተዳደግ ሁኔታ ያላቸው ናቸው፡፡ ሰዎች
በመንፈሳዊ ህይወት ያላቸው የብስለት ደረጃም እንደዚሁ ይለያያል፡፡በመሆኑም ስለ ችግሮችም ሆነ ስለሌሎች
ጉዳዮች ያላቸው የግንዛቤ ደረጃም ይለያያል፤ ቸግሮች ስለሚፈቱበት ስልትና ስለአፈፃፀማቸው የሚኖራቸው
ግንዛቤ ይለያያል፡፡
በመጀመሪያ በሰዎች መካከል የአሳብ ልዩነቶች መኖሩ ከሚያስከትለው ችግር ይልቅ ጠቃሚ ጎኑ ያመዝናል፡፡
የተለያዩ ስብባዎች መኖራቸው ያስፈለገው የብዙ ሰዎችን አሳብ ወደ አንድ ለማምጣት ነው፡፡ አንዳንድ ግዜ
በአገልግሎት ወቅት ተግባብተን የማናገለግል ከሆነ የሰራን እየመሰለን እናፈራሳለን እና በፍቅር እና በ መግባባት
ማገልገል ያስፈልጋል ፡፡
በመጥፎ ባልንጀራቸው ምክንያት ወደ ክሕደትና ኃጢአት ያመሩ ሰዎች ጉዳይም በስፋት ተጠቅሶ እናገኛለን፡፡
ስለዚህ ወጣቶች ባልንጀራዬ ማነው? ብለው ራሳቸውን መጠየቅ ይገባቸዋል፡፡ በተለያዩ አጋጣሚዎች
ጓደኞቻቸውን መምረጥ እንኳን ቢከብዳቸው መጥፎ የአቻ ግፊትን በመከላከል ለፈቃደ እግዚአብሔር እና
ለሕይወት ግባቸው ቅድሚያ በመስጠት በንቃትና በቆራጥነት ለመጥፎ ተጽዕኖዎች አይሆንም እምቢ ማለትን
ሊለማመዱ ይገባል፡፡
ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት በመዝሙሩ “ምስለ ጻድቅ ትጸድቅ ወምስለ ብእሲ ንጹሕ ንጹሐ ትከውን
ወምስለ ጠዋይ ትጠዊ፤ ከጻድቅ ሰው ጋር ጻድቅ ትሆናለህ፤ ከቅን ሰው ጋርም ቅን ትሆናለህ፤ ከንጹሕ ሰው ጋር
ውሎውን ካላስተካከለ አወዳደቁ የከፋ ይሆናልና ጓደኞቻችንን መምረጥ ያስፈልጋል፡፡ በጓደኛ ተጽዕኖ
ሕይወታቸው የተበላሸባቸው በርካታ ምሳሌዎችን ከመጽሐፍ ቅዱስ መጥቀስ ይቻላል፡፡ ከነዚህም መካከል
አምኖን ከኢዮናዳብ ጋር፣ ሶምሶን ከደሊላ ጋር ያደረጉት ጓደኝነት ሕይወታቸውን እንደጎዳው ተጠቃሽ ነው፡፡
ሉላዊነት (Globalizatin)
አንድ እሳቤ፣ አንድ ፍልስፍና፣ አንድ አሠራር፣ አንድ እምነት፣ አንድ ሂደት፣ አንድ አመለካከት፣ አንድ ሕግ
አለም አቀፋዊ እንዲሆን የሚሠራ ነው፡፡
“Today I resigned from the staff of IMF after over 12 years … hawking your medicine and your
bag of tricks to governments and to peoples in Latin America and the Caribbean and Africa. To
me resignation is a priceless liberation, for with it I have taken the first big step to that place
where I may hope to wash my hands of what in my mind’s eye is the blood of millions of poor
and starving peoples. … The blood is so much, you know, it runs in rivers. It dries up, too; it
cakes all over me; sometimes I feel that there is not enough soap in the whole world to cleanse
me from the things that I did do in your name.”5
ሉላዊነት ለቤተክርስቲያን ሥጋት የመሆኑን ያህል መልካም አጋጣሚዎችንም የፈጠረ በጎ ጎን አለው፡፡ ለስብከተ
ወንጌል እስከ ዓለም ዳርቻ ድረስ ያለውን ሰው እንደ ጥንቱ በእግር ሐዋርያነት ብቻ ሳይኾን ፈጣንና ቀላል
በሆኑት የሥነ ዝማኔ/ቴክኖሎጂ/ ውጤቶች በመጠቀም ወንጌልን ማስፋፋት ተችሏል፡፡ ሆኖም በምዕራቡ ዓለም
የአሜሪካውያኑ ድርጊት እና ሁኔታ በደቂቃ ልዩነት እየተነገረው እንደነሱ ለመሆን ሲሻ ከማንነቱ ተራርቆ
በአስከፊ ጥገኝነትና የማንነት እጦት እንዲሁም የመንፈስ ድርቀት ውስጥ ይገኛል፡፡የመገናኛ ብዙኃኑም በዚሁ
5
D. L. Budhoo, Enough is Enough: Dear Mr Camdessus … Open Letter of Resignation to the
Managing Director of the IMF (New York, New Horizons Press, 1990)
ሴኩላሪዝም የመንግሥትና የሃይማኖትን መለያየት የሚሰብክ ጽንሰ ሐሳብ ነው፡፡ እሳቤው በብዙ መልኩ
ቤተክርስቲያንን ጎድቷታል፡፡ ይዞታዎችዋና ቅዱስ ትውፊቷ ላይም ከባድ ተጽእኖን አሳርፏል፡፡ ጽንሰ ሐሳቡ
በመሥሪያ ቤት የሌላውን መብት ሳይረግጥም ቢሆን እንዳይተገብር ፈተና ሆኗል፡፡ በጽናት የሚተገብሩትም
በሹፈትና በማላገጥ እንዲሸማቀቁ አስተዋጽኦን በማበርከቱ ከዕለት ዕለት የጠንካራው አማኝ ቁጥር ቀንሷል፡፡
እንደውም ሃይማኖታዊነትን መመስከር ሞኝነትና ኋላቀር እንዲመስልና ዘመናዊነት ከሃይማኖት እጅግ የራቀ
ሆኖ እንዲታሰብ አድርጓል፡፡6
የሚሰብክ ጽንሰ ሐሳብ ብቻ አለመሆኑን ነው። በሌላ አገላለፅ የሃይማኖት ፀር ነው። ለዚህም 'ሴኩላሪስት'
የሚለውን ቃል ትርጉም ከመዛግብተ ቃላት መመልከት በቂ ነው። ቃሉን ብዙዎች ፀረ-ሃይማኖታዊነት ብለው
የመንግሥትና የሃይማኖት መለያየት ሳይሆን የፀረ-ሃይማኖታዊነት ስያሜ ፣ 'ሴኩላር' የሚለው ደግሞ የኢ-
አማኒ ቅጽል እንደሆኑ ይብራራሉ።በእግዚአብሔር መኖር ከማያምን ማእቀፈ እሳቤ የሚመነጭ ፣ “ለሰው
ልጅ አዳኙ ራሱ የሰው ልጅ ነው፣ ሌላ ከዚህ ዓለም ውጭ የሆነ መንፈሳዊ ኃይል የለም፣ መንፈሳዊ ዓለም
የለም” ባይ ነው፡፡ No regard to spiritual, religious, or ecclesiastical doctrines, beliefs, or power
structures.If God does not exist, then He cannot establish an absolute moral code. Humanist
Max Hocutt says that human beings "may, and do, make up their own rules... Morality is not
discovered; it is made.” 7
6
ዘመናዊነትና ክርስትና በሚል የተፃፈ ፅሁፍ፣ ዲ/ን ህሊና በለጠ
7
Max Hocutt, "Toward an Ethic of Mutual Accommodation," in Humanist Ethics, ed. Morris B. Storer , Buffalo:
Prometheus Books, 1980), p. 137.
Modern of relating to the present or recent times, characterized by or using the most up-to date
techniques.8 Modernity is development without dependency.9
ዘመናዊነት ከዘመኑ ጋር አብሮ የሚሄድ ሁለንተናዊ እድገት ጥገኝነት የሌለበትን መሆን አለበት እኛ ግን አድርጉ
መለኪያም በላይ መሆናቸውን አንድ አገልጋይ/ክርስቲያን መረዳት ይገባዋል፡፡ ክርስትና በዘመን ውስጥ ሳይሆን
ዘመን ስለ ክርስትና ተፈጥሯልና /ዘመን/ በክርስትና ውስጥ ንዑስ ጽንሰ ሐሳብ ነው፡፡ ለክርስትና መገለጫ
ቢያሰኙም ከዚያም በላይ መሆናቸውን መገንዘብ ተገቢ ነው፡፡ ዘመናዊ መሳይ የሆኑና አገልጋዮችን
ዘመናዊነት ማለት 'ዕድገት ካለ ጥገኝነት' ነው፡፡ አንድ ክርስቲያን ለመንፈሳዊነት ዕድገቱ ኢክርስቲያናዊ ነገሮች
ጥገኝነት ኹለንተናዊ ዕድገትን ማደግ አለበት፡፡ ኹለንተናዊ ዕድገት የሚለውን ወደ ግለሰብዕ ካመጣነው
እንደሚከተለው ነው፡፡ የሰው ልጅ ኹለንተናዊ ዕድገትን ዐደገ ስንል በአካሉ /በሥጋው ፣ በስሜቱ/ ፣
8
Merrium Webster dictionary
9
The muse of modernity: essays on the culture as development in Africa:Altbach, Phillip G, Hssan, Salah M.
2. የግዜ አጠቃቀም ፡-ግዜ ሀብት ነው፡፡ ሀብተ እግዚአብሔር በሆነው ሰዓትም የትኛውን ሰዓት በየትናው ሥራ
ላይ ማዋል እንዳበት ለሰው ልጅ ሙሉ ስልጣን ተሰጥቶታል፡፡ቤተክርስቲን ለዚህ አብነታችን ናት፡፡ ም/ም
የሰዓታት ግ፣ የኪዳን ግዜ፣ የክርስትና ማንሳት ግዜ፣ የትምሀርት ግዜ፣ የግል የፀሎት ግዜ መድባ በመንቀሳቀሷ
አገልግሎቷ ኤይቋረጥም፡፡10 ለመንፈሳዊያን አገልጋዮች ከእግዚአብሔር ጋር እንደመኖር የሚናፈቅ ነገር
የላቸውም፡፡ ግዜ ሀብትህ ስለሆነ የት እንደምታውለው ካንተ ጋር ተመከካር፡፡መንፈሳዊነትህንና አገልሎትህን
የሚያዳክሙ ነገሮችን መመጠን ይገባል፡፡የማሀበራዊ ሚድያ አጠቃቀም፣ለፊልም፣ ለመጽሐፍት ነብብ
፣ለአገልግሎት የምትመድበው ግዜ ይኑርህ፡፡
3. ከንቱ ውዳሴ፡- ከንቱ ውዳሴን የሚያመጣው ለታይታ ማገልገል ነው፡፡በአገልግሎት ውስጥ ለታይታ የሚሆን
ቦታ የለም፡፡ አገልጋይ ታይታ የሚወድድ ከሆነ ወደ ውድቀት ያመራል፡፡ አደገኛ በሽታም ነው፡፡ ታይታ ለውጫዊ
እንጂ ለውስጣዊ ማንነት አለመጨነቅ ነው፡፡ በውጭ ሲመለከቱን ጻድቅ በውስጥ ግን ግዴለሽ የመሆን ዝንባሌ
ነው፡፡
ከንቱ ውዳሴ በመንገድ ሁሉ የሚከተልህ የተሸሸገና ጭንብል ያጠለቀ ሌባ ነው፡፡አሳዳጅ በመሆኑ በጣም ደህንነት
በሚሰማህ አሳቻ ሳታውቀው ያዘርፍሀል፣ይገድልህማል እንዲል ቅ.ጎርጎርዮስ ፣ “ሰዎች ሁሉ መልካም
ሲናገሩላችሁ፥ ወዮላችሁ፤ አባቶቻቸው፤ ለሐሰተኞች ነቢያት እንዲሁ ያደርጉላቸው ነበርና።” ሉቃ. 6:26
4. ትዕግስት ማጣት፡- በአገልግሎት ውስጥ ሁልግዜ ደስታ ሁልግዜ መከራ የለም፡፡ሁልግዜ ማጣት ሁልግዜ
ማግኘት፣ ሁልግዜ ጤንነት ሁልግዜ ሕመም የለም ፡፡አንዱ ባንዱ እየተተካ ጉዞው ይቀጥላ፡፡ አገልግሎት ያለ
ትዕግስት አይታሰብም ክርስትና ሩጫ ነው ሐዋርያት በብዙ መከራ እያለፉ በትዕግስት ዝም ያሉት የሚጠብቁት
ነገር ስለነበር ነው፡፡
10
አገልጋይ በመንፈሳዊና በማህበራዊ ህይወት መካከል፣ሊቀ ጠበብት ሐረገወይን እና አዱኛ ማእምር፣ ማህበረ ቅዱሳን 1998 ዓ.ም
1. አላማን አለመርሳት፡- መንፈሳዊ አገልግሎት ዓላማው እግዚአብሔርን ማግኘት ከእርሱም ጋር መኖር ነው፡፡
ከአላማ የሚርያቁ ቀዳዳዎችን መድፈን ከመሳት ይጠብቃል፡፡ስለዚህ አንድ አገልጋይ አላማውን ሁልግዜ ማሰብ
አለበት፡፡መንፈሳዊ አገልግሎት የአንድ ሰሞን የስሜት ሩጫ ሳይሆን እስከመጨረሻው ድረስ የሚሮጡት ሩጫ
ነው፡፡እስከ ሞት ድረስ የታመንክ ሁን እንደተባለ………ራዕ 2፡10
አላማ ርዕይ ተኮር እንጂ ክስተት (ግለሰብ) ተኮር አይደለም Being objective not subjective. አባቶቻችን
ጉዳይ ተኮር እንጂ ግለሰብ ተኮር አልነበሩም፡፡ሰዎችን ከስህተት ማውጣትና ከእውነት ጋር ማሰለፍ የቻሉት
ለዚህ ነበር፡፡
2. ትህትና፡- ትሕትና የአገልግሎት መሠረት ነው፡፡ሌሎችን አገልግሎቶች የሚያቃና ትሕትና ነው፡፡ የትሕትና
መጉደል አገልግሎትን ያጠፋል፡፡ በአገልገሎት ላይ የማሰናከያ ድንጋይ ይሆናል፡፡ በአገልግሎት ትሑት ለመሆን
ማን እንደሆንን፣ ከየት እንደመጣን ወዴትም እንደምንሄድ ማወቅ ይጠበቅብናል፡፡
እንደ ርግብ የዋህ መሆን (innocence)፡-ጌታችን እንደ ርግብ የዋህ ሁኑ ሲል ለመንፈሳዊ አገልግሎት
ተልዕኮ ታመኑ (የቁራ መልእክተኛ እንዳትሆኑ)፣ በመንፈሳዊ አገልግሎት ሰላምን ስበኩ (ጥልና ክርክር
ከእናንተ ይራቅ)፣ በመንፈስ ቅዱስ ተመሩ (የራሳችሁን ፍላጎት ግቱ)፣ ሰው የሚፈልገውን ሳይሆን
ለሰው የሚያስፈልገውን በመስበክ አስፈላጊ ሆኖም ሲገኝ መስዋዕትነት ክፈሉ ማለቱ ነው፡፡ ነገር ግን
‹‹እንደ ርግብ የዋህ ሁኑ›› አለ እንጂ ‹‹ርግብ ሁኑ›› አላለም፡፡ ርግብን መምሰል ያለብን በሦስት ነገሮች
ነው፡፡
11
አገልጋይ በመንፈሳዊና በማህበራዊ ህይወት መካከል፣ሊቀ ጠበብት ሐረገወይን እና አዱኛ ማእምር፣ ማህበረ ቅዱሳን 1998 ዓ.ም
የማይደለሉ ጆሮዎች (Focused ears) ፡- በአስመሰዮች አሉባልታና በወሬ የማይታለሉ፣ የማይረቱ ጆሮዎች
እንዲኖሩን
3. ፅናት፡- ክርስትና በቦታና በግዜ የሚወሰን ሳሆን እስከ መጨረሻው የምንጸናበት ምስጢር በመሆኑ
ተጋድሎውም የሚገለው በምናሳየው ብርታና ፅናት ይሆናል፡፡የተገድሎ መጀመሪያህን ራስን በማሸነፍ ከሆነ
4. ትጋት፡- ከዘመነ አበው ጀምሮ የእግዚአብሔር ወዳጆች እየተባሉ የሚጠሩ ሁሉ የፍቅረ እግዚአብሔር
መግለጫቸው ትጋታቸው ነበር፡፡ የመጨረሻው ደሞዝ የሚከፈለው ከጥዋት እስከ ማታ በስራ ገበታቸው ላይ
ለተገኙ ሰራተኞች መሆኑን ስታይ የመንፈሳዊ ህይወት መታወቂያው ትጋት መሆኑን ያመለክታል፡፡ማቴ 20፡1-
12 ራስህን ከማገልገል ጀምር፣ 2 ኛ ጴጥ 5፡7 ፣1 ኛ ቆሮ 9፡27
5.መንፈሳዊነትን መላበስ ፡-ፆም ፣ፀሎት ፣ስግደት የተባ መንፈሳዊ የጦር እቃዎችን ልበስ፡፡
አንድ አገልጋይ ከሚመራቸው ሰዎች በላይ የሆነ መንፈሳዊ ደረጃ ላይ የደረሰ መሆን ይገባዋል፡፡ ጹሞ ጹሙ
የሚል፣ ጸልዮ ስለጸሎት ጠቃሚነት የሚያስረዳ፣ የፍቅር ሰው ሆኖ ፍቅርን የሚሰበክ፣ አትዋሹ ብሎ የማይዋሽ
ሰው መሆን አለበት፡፡
“ያለ ጸሎት ከሚደረግ አገልግሎት ያለ አገልግሎት የሚደርግ ጸሎት እርሱ ይበልጣል ፡፡” አቡነ ሺኖዳ
7.ፍፁም እስክሆን ጠብቄ አገለግላለሁ አትበል ፡-በፍቅረ እግዚአብሔር መሞላትና ጣፋጩን እግዚአብሔርን
ማወቅ እንጂ ዛሬ በደለኛ ነኝ፣ ሃጢአተኛ ስለሆንኩ ስስተካከል አገለግላለሁ አትበል፡፡ መቼም ፍፁም አትሆንም
እና ባለህ ነገር ሁሉ አገልግል፡፡
“እኔ ራሴን አስተካክዬ ጥሩ ስሆን አገለግልሀለሁ,ጥሩ ስሆን አገለግልሀለሁ? መቼም ጥሩ አትሆንም ራስህን ጥሩ
አድርገህ ወደእኔ ከምትመጣ ወደእኔ ናና ጥሩ አደርግሃለሁ፣እኛ ምን እንላለን እኔ ቤትህ የማልገባበት ም/ት
ንፁህ ስላልሆንኩ ነው፣አይደለም ወደ እኔ ና አፀዳሃለሁ፣ እኔ ቤትህ የማልገባበት ም/ት ጥሩ ሰው ስላልሆንኩ
ነው፣አይደለም ወደ እኔ ና ጥሩ ሰው ትሆናለህ፣ለምንድን ነው ብቻህን መስራት የምትፈልገው እስቲ የማዳን
ስራውን ተመልከት፣ለምፃሙ የሄደው እንዲፀዳ፣በሽተኛው የሄደው እንዲድን ሽባውም የሄደው ደጋሜ
መመሄድ እንዲችል ነው፡፡እኔም እንደዛው ነኝ በሉትወዳንተ የምመጣው በመላ ደካማነቴ፣በመላ ጉድለቴ፣በመላ
አወዳደቄ፤ልክ እንደጠፋው ልጅ ወደአባቱ ሲመለስ ከነቆሻሻው እንደተመለሰው፡፡እና እግዚአብሔር ካንተ ጋር
እንዲሰራ ሞክር ከእግዚአብሔር ረህ ራስህን ለማስተካከል አትሞክር በፍፁም አትችልም !”
8.ፍቅር ፡- የአገልሎት መሰረቱ ፍቅር ነው፡፡መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነፍሱን አሳለፎ የሰጠወ ለሰው
ልጆች ባለው ፍቅር ነው፡፡ የአገልግሎት መነሻው እግዚአብሄርንና የእግዚአብሔር የሆኑትን መውደድ ነው፡፡
የሰወን ልጅ ሁሉ መውደድ እግዚአብሄርን ከመውደድ ይመነጫል፡፡ቤተክርስቲንንና ሀገርነ መውደድ ሌላው
የፍቅር ፍሬ ነው፡፡
እኔ እጠቀምበት ብለህ የምትሰራው ደሞዝ እንጂ ፍቅር አይደለም፣ ፍቀር ሳትቀበል የምትሰጠው ነው፡ማንም
ከእናንተ ወገን ይህች ፍቅር ደክመን የምንሰራውን ያለድካም እንዲሆን ታደርጋለችና እሱዋን እሹዋት፡፡”
ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ፣1 ኛጴጥ 4፡8
9.ዋጋ የሚከፍል ትውልድ ለመሆን ተዘጋጅ፡-ዋጋ ለመክፈል ያልተዘጋጀ ትውልድ ውጤት ማግኘት አይችልም፡፡
ይህንንም ማድረግ የምችለው መጀመሪያ ለአገልግሎት የሚያበቃ እውቀተ እንዲኖረን ራሳችን ላይ በመስራት
ነው፡፡አንድ አገልጋይ ስለተሰጠው የአገልግሎት ድርሻ በማወቅ ምን እንደሚሰራና የሚሠራበትንም መንገድ
ከመገንዘብ ባሻገር አገልግሎቱ የሚጠይቀውን መስዋዕትነት እንዲረዳው ረዳዋል፡፡ከመጠምጠም መማር
ይቅደም እንዲሉ አበው ሳይማሩ ማስተማርም ከተሳዳቢነት ይቆጠራል፡፡12
12
ኰኲሐ ሃይማት፣ መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀንበሬ፣የካቲት 1989 ዓ.ም አዲስ አበባ
የፍቁረ እግዚእ ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት ክፍል የአገልግሎት ማሰልጠኛ ማንዋል ገጽ 35
ክርስትናን ህይወት እንጂ ሆቢ አታድርገው
ሁለገብ የሆነ ሰው
1 ኛ ሳሙ 14፡6-23፣2 ኛ ሳሙ 9፡10
ክፍል 3
የስልጠናው አላማ
ጥንታዊ የግሪክ ባለ ቅኔዎች፣ ገጣሚዎችና የታሪክ ጸሐፊዎች ስለኢትዮጵያ ብዙ ጽፈዋል፤ ከነዚህ መካከል
ሆሜር ስለአገሪቱና ስለሕዝቧ ሲገልጽ “በጉልበት ሃያላን፣ በውበት የተደነቁና በጠባይ ጭምቶች፣ትህትናን
የተሞሉ እንከን የሌለባቸው ዘሮች” ሲል በ 490 ከጌታ ልደት በፊት የነበረው ምዕራባውያኑ የታሪክ አባት
10፥1-13 ተጽፎ ሲገኝ በኢትዮጵያውያንም ዘንድ ይህ ጉዞ ብሉይ ኪዳን በኢትዮጵያ እንዲስፋፋ ያደረገና፤
የንጉሥ ሰለሞንና የንግሥት ሳባ ልጅ የሆነው ቀዳማዊ ምኒሊክ ጽላተ ሙሴን ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጣ ያደረገ
ነው ተብሎ ይታመናል። ከዚያን ጊዜ በኋላ የአይሁድ እምነትና ሥርዓተ አምልኮ የሕዝቧ እምነትና የቀን ተቀን
ኑሮ መመሪያ ሆኗል። በቀዳማዊ ምኒሊክ የተመሰረተው የአክሱም ሥርወ መንግሥት ተብላ ትታወቅ ነበር።
የክርስትና እምነት ወደ ኢትዮጵያ የገባው በሐዋርያት ዘመን እንደሆነ መጽሐፍ ቅዱሳዊ የሆኑና ሌሎች ታሪካዊ
ማስረጃዎች ይመሰክራሉ። (ሐዋ. 8፥26-36) ላይና በአራተኛው ክፍለ ዘመን የነበረው ታላቁ የቤተ ክርስቲያን
ታሪክ ጸሐፊ አውሳቢዮስ “የኢትዮጵያው ጃንደረባ ጥምቀት በዓለም የመጀመሪያው የክርስትና እምነት
ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች የተባለው ተፈፀመ፤ So that through him in truth the
propicency obtained itsfulfilment ,which declares that :Ethiopia streatches out her hand unto
ታላቅ ሁኔታ ዘግበውታል። ይኸውም የሕንደኬ ጃንደረባ ኢየሩሳሌም ደርሶ በኦሪቱ ልመድ የፋሲካን በዓል
አክብሮ በጋዛ በኩል ሲመለስ ፊልጶስ ጃንደረባውን የ ትንቢተ ኢሳይያስ ክፍል እንዲገባው አስረድቶት
አሰማ፡፡የሊጰን ጳጳስ የነበረው ቅዱስ ሄሬኒዎስ ጃንደረባው ለወገኖቹ ሐዋርያ ሆነ ያላል፡፡ “But again: Whom
13
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ታሪክ፣ አቡነ ጎርጎርዮስ የሸዋ ሊቀ ጳጳ፣ሰኔ 1974 ዓ.ም
14
Ecclesiastical History(History of the church), Eusebius the Caesarea,Book II,ch1, No 13.
ከ 4 ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ እስከ 5 ኛው መቶ ክፍለዘመን መጀመሪያ የኖረው ሩፊኖስ የተባለው የቤ/ክ
ታሪክ ፀሐፊ ስለ ክርስትና እምነት ወደ ኢትዮጵያ መግባ ይህንን ፅፏል፤ ”በ 4 ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አብርሃና
አፅበሀ(ክርስትናን ከመቀበላቸው በፊት ኢዛናና ሳይዛና ይባሉ ነበር) የተባሉ ወንድማማቾች አክሡም ነግሰው
ከሲድራኮስ ጋር ከሞት ተርፎ መፅዋ አጠገብ የተገኘው የጢሮስ ተወላጅ ግሪካውው ፍሬሚናጦስ ከህፃንነቱ
ጀምሮ ወንጌልን እየተማረ ያደገ ስለነበር ፤ከኦሪቱ ሊቀካህናት ከእንረም ጋር ተመከክሮ የሚያስተምር
የኢትዮጵያን ቋንቋና ልማድ ስለምታውቅ አንተው ጳጳስ እና ሐዋርያ ሁን ብሎ ሰላማ በሚል መዓርገ ጵጵስና
ሰጥቶ በ 330 ዓ.ም ወደ ኢትዮጵያ ሰደደው፡፡”16ንጉሥ ኢዛና በገንዘቦቹ ላይ የነበሩትን የጨረቃ ሥዕልን ቀይሮ
በኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ሃይማኖቱን መስክሮ መጠመቅ በሯን ለክርስትና የከፈተችው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ
ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በሐዋርያት ስብከት ተጀምራ ከዚያም በመንበረ ጵጵስና ራሷን ችላ ወንጌልን
እየሰበከችና ምሥጢራትን እየፈጸመች ከዛሬ ደርሳለች፡፡በአባ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ጳጳስነት፣በቅዳሳን ነገሥታት
በአብርሃና አጽብሐ አስተባባሪነት፣ በሌሎች ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ሠራተኛነት ወንጌል በአራተኛው መቶ
ዓመት በተለያዪ አቅጣጫዎች ተሰበከ፤ ክርስትናም ተስፋፋ፡፡ ብዙ መጻሐፍት ተተረጎመ፡፡ነገር ግን
ቤተከርስጢያን በወርቃማ ግዜያት እንደሳለፈችው ሁሉ የደረሱባ ዐበይት ፈተናዎችም ነበሩ፡፡እነዚህንም ከዚህ
ቀጥለን ለማየት እንሞክራለን….
15
Ireanaeus of Lyons : Adversus Hæreses Book III. Ch. 12. 8
16
የቤተክርቲያን ታሪክ በሉሌ መልአኩ፣ 1986 አዲስ አበባ
17
የኢትዮጰያ የ የ 5 ሺህ አመት ታሪክ ከኖህ-ኢህአዴግ፣ፍስሐ ያዜ፣ 2003 አዲስ አበባ
ብዙዎች ክርስትናን ሲቀበሉ ጥቂቶቹ ደግሞ አንቀበልም ብለው በሀገሪቱ ተራራማና ቆላ ቦታዎች ይኖሩ ነበር፡፡
እነዚህም በሌላው ሕዝብ ዘንድ ፈላሾች እየተባሉ ይጠራሉ፡፡ ስደተኞች ማለት ነው፡፡ የሚያስተዳድራቸውም
ጌዴዎን የሚባል ሹም ነበር፡፡ እሱም ዮዲት የምትባል ልጅ ነበረችው ፡፡መልከ መልካምና ኃይለኛ ነበረች፡፡
በ 624 ዓ.ም ገደማ ዮዲት አክሱም ከተማ ገብታ ወረራዋ አደረገች፡፡ በክርስቲያኖች ላይ ከአባቷ የወረደ ጥላቻ
ያደረሰው ተፅዕኖ
ቤተክተርስቲያን አቃጠለች፤
በዐፄ ልብነ ድንግል ዘመነ መንግሥት በኢትዮጵያ ወሰን ላይ የተወለደው ግራኝ አህመድ ከቱርክ ባለስልጣናት
ዓመት ሙሉ በኢትዮጵያ ላይ ዘመቱ፡፡ ከዮዲት ወረራ ተርፈው የቀሩትና ከርሷም በኋላ የተተኩት የክርስቲያን
ያደረሰው ተፅዕኖ
ሊባኖስ ገዳም…
ቤ/ክ ይዞታዎች የስምና የቦታ ተፋልሶ ለምሳሌ ባሌ የነበረው በአቡነ አኖሬዎስ ስም ይጠራ የነበረ ቦታ
ዛሬ ኑር-ሁሴን ነው የሚባለው
ኢየሱሳውያን የሚባሉት ካቶሊኮች ውስጥ ውስጡን ሲሄዱ ቆይተው በይፋ የተከሠተው በዐፄ ሱስንዮስ ዘመነ
መንሥት ነው፡፡ዐፄ ሱስንዮስም ከፖርቹጋል መንግሥት የጦር መሣርያ ድጋፍ ለማግኘት ሲሉ በ 1626 ዓ.ም
ወደ ካቶሊክ እምነት ያልገባና ይህንን ሕግ ያላከበረ የአካል ቅጣት እንዲፈጸምበት የሚል አዋጅ እንዲታወጅ
ጳጳሱ አቡነ ስምዖን ደግሞ ለኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተቆርቋሪ የሆኑትን ይዘው ከንጉሱ ጋር ጦርነት ገጠሙ፡፡
በጦርነቱ ላይ ድሉ የዐፄ ሱስንዮስ ሆነ፡፡ በዚህም ከጎጃም፣ ከበጌ ምድር፣ ከትግራይና ከላስታ ሰማዕትነት
እንዳያመልጣቸው በማለት እየተጠራሩ ከ 8 ሽህ በላይ ሕዝብ ረገፈ፡፡ በዚህ የተነሣ ለሰባት ዓመታት ያህል
በኢትዮጵያ የሃይማኖት ጦርነት ተደረገ፡፡ የኢትዮጵያ ቅዱሳን ዐፅም ከያለበት እየወጣ ተቃጠለ፣ ብዙ ካህናት፣
ያደረሰው ተፅዕኖ
ለተክለሃማኖት ዘሸዋ አስተማራቸው፡፡ቅባት እና ጸጋ በንባብ እንጂ በምሥጢር አንድ ናቸው፡፡ ሁለቱም የሮማ
የቅባትና የጸጋ አዲስ ትምህርት ሆነ ተብሎ ለማለያየት የተተከለ እሾህ ስለሆነ በጥቂት ጊዜ ውስጥ ካህናት ብቻ
ሳይሆን ሕዝቡን ከመንግሥት፣ መንግሥትን ከሕዝቡ መለያየቱ ቀጠለ፡፡ ከዐፄ ፋሲል ጀምሮ የሚነግሡ ነገስታት
አንዱ አንዱን ሲደግፉና ሲከራከሩ ብዙ ችግሮች ተፈጥረዋል፡፡ ለምሳሌ፡-በዐፄ ዳዊት የደረሰው እልቂት
ከ 1769-1855 ዓ.ም ድረስ ኢትዮጵያ በመሳፍንት አገዛዝ እንደ ቅርጫ ሥጋ ተከፋፈለች፡፡ በዚህ ጊዜ
ቤተክርስቲያን እየተዳከመች ሄደች፡፡ መኳንንቱ እና መሳፍንቱ እርስ በእርስ ስለማይስማሙ አንዱ ሌላውን
ያደረሰው ተፅእኖ
ተለወጠ፡፡
በመሀል ሀገር ያለውን ምዕመን ለመከፋፈል የሮማ ፖፖ የነበሩት ጎርጎርዮስ ብዙ ሚስዮኖችን ላኩ፤
ብዙዎቹ ተወስደዋል፡፡
ጦርነቱን ቅ.ዘመቻ በማለት የሞሶሎኒን ጦርና መድፍ ባረኩ፡፡ፖፑና የኢጣሊያ ካርዲናሎችም ለጦርነቱ ብዙ
ርዳታ አደረጉ፡፡
ያደረሰው ተፅዕኖ
ቤ/ክ ተንከባክባና ጠብቃ ያቆየቻቸው የታሪክና የሀይማት ቅርሶች ተዘርፈው ለቫቲካን ተሰጡ
በየአድባራ ገዳማቱ በደ/ሊባኖስ፣ በላሊበላ፣ አክሱም፣ ጎንደርና ዝቋላ ብዙ ካህናትና ምዕመናን ተገለዋል
ክፍል 4
የምዕራፉ አላማ
4. የኢ/ኦ/ተ/ ቤተ ክርስቲያን ዛሬ
1. ዳርዊኒዝም (Darwinism)
2.ሉላዊነት (Globalization)
4. ሊበራሊዝም (Liberalism)
5.የፕሮቴስታንት እንቅስቃሴ
6.ተሐድሶ
7.አክራሪእስልምና (Fundamentalism)
ምክንያቶች ነው፡፡ለዚህም ደግሞ ትልቁን ሚና ይጫወት የነበረው የፖለቲካው እንቀስቃሴ ነበር፡፡በደርግ ዘመነ
መንግስት ቤተክርስቲያኗ ብዙ የሚባሉ ፈተናዎችን አሳልፋለች፡፡ለዚህም ዋነኛ ምክያት የነበረው ደርግ ይከተል
የነበረው የሶሻሊዝም ርዕዮተ አለም መሆኑ ነበር፡፡ይህ የሶሻሊዝም ርዕዮተ አለም የሩሲያ ኦርቶዶክስ
ቤተክርሰቲያንን በእጅጉ የፈተናት እንደነበር የታሪክ ድርሳናት ያትታሉ፡፡በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤ/ክም የሆነው
እንዴት አደራችሁ ሲባል እንኳን እግዚአብሔር ይመስገን ማለት የማይቻልባቸው ሁኔታዎች ነበሩ
ማህሌት ሰዐታት እና ቅዳሴ በማይክ ጮሀችሁ እየተባለ በለሆሳስ እንዲሆን ይገደዱ ነበር
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ራስዋን የቻለች ዓለም አቀፍ ተቋም መሆኗ እንዲሁም
እሙን ነው፡፡ ከዚህም የተነሣ አመራሩና ምእመኑ የሚፈልገውን መንፈሳዊ ዓላማ ለመፈጸምና ለማስፈጸም
ከዘመኑ ጋር በተጣጣመ አቅም ማከናወን ሲቸገሩ ቆይተዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር ይህን እንደሽፋን ሊጠቀምባት
የሚፈልግ የተለየ የእምነት፤ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ጥቅም ፍላጎት ያለው ሁሉ ለራሱ ጥቅም እየገባ ያሻውን
የቤ/ክ የገንዘብ አጠቃቀም ግልፅነት የጎደለው መሆን፣የአንደነድ ደብር አስተዳደር አካላት ለዚህም
ያመቻቸው ዘንድ ምንም አይነት የስራና የሂሳብ ሪፖርት አለማቅረብ፣ቢቀርብም አጥጋቢ ያልሆነ ነገር
ማቅረብ
የቤተክርስቲያኒቱን ገንዘብ ለግል ጥቅም ማዋል፤(በአሁን ሰዓት እንደውም G+ ቤትና መኪና የሌለው
ለቤተክርስቲያኒቱ ጥቅም እና ልማት ከሆነ መልካም ነበር ነገር ግን ሀሳባችን በሙሉ ገንዘብ፣ጥቅም እና
ዘረኝነት እና ሙስና
ያለመገኘት
በሰንበት ትምህርት ቤቶች የውስጥ አስተዳደር ላይ አላስፈላጊ ጣልቃ ገብነት እንዲሁም ሰንበት
አለመሆን
በቤተክርስቲያን ዕድሳት፣ በአብነት ትምህርት ቤቶች እና በገዳማት ስም፣ ገንዘብ እየሰበሰቡ ኦዲት
2. የጀመረውን ሳይቋጭ በሆታና በወረት ተጩዋጩሆ ሲያበቃ ተመልሶ ወደአርምሞ የሚገባ ወረተኛ
ምዕመንና ተቆርቋሪ መበርከት፣
4.ከመግለጫና የይምሰል የቃላት ጋጋታ (lipservice) በቀር ገቢር የማያውቅ ልምሾ አስተዳደር መሥፈኑና
ከእርሱም ብሶ ከአጥቢያ እስከ መንበረ ፓትርያርክና ቋሚ ሲኖዶስ በኔትወርክና የጎሰኝነት ውድድር የተዘፈቀ
5.ሥራዎች የሚመሩበት የጨረታ፣ የግንባታ፣ የኪራይ፣ የሽያጭ፣ ሕግ፤ እንዲሁም የአገልጋይና አስገልጋይ
ላይ በኔትወርክ ተደራጅቶ ፊጥ በማለት ኪሷን የዳበሰ ሁሉ ወርቅ ይዞ ያለጠያቂ የሚወጣባት አሳዛኝ ቤ/ክ
ፈጠረ፡፡
የአመለካከት
ታሪክ ብቻ በማንሳት አሁን ላይ እንኳን የተቀናጀ አደረጃጀት ሊኖር ቀርቶ ህዝበ ክርስቲያኑም እርስ
አይመስለኝም
ንዝህላነትና ቸልተኝነት
የክህሎት
እንዲሁም የሚያበሳጩ ነገሮች ሲከሰቱ የምናስተናግድበት መንገድ “Just as athletes win crowns
by their struggles in the arena, so are Christians brought to perfection by the trial of their
temptations, if only we learn to accept what is sent us by the Lord with becoming
patience, with all thanksgiving. All things are ordained by the Lord’s love. We must not
accept anything that befalls us as grievous, even if, for the present, it affects our
weakness.19
ፅናት ማጣት አገልግሎት መንገዱ ከባድ ቢሆንመም በከባድ ቦታ ሆኖ መራራ ህይወት ማሳለፍ ዋጋን
1.ዳርዊኒዝም (Darwinism):
አምሳልነትን ከአንድ የዘር ግንድ መገኘታቸውን ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባነው፡፡ የዳርዊን የዝግመተ ለውጥ
መላምቶችን ወደ ፍጹም ሳይንሳዊ ግኝት ለማድረስ የሚጥር የትምህርት መሥመር ነው፡፡ ሰውንም የዝንጀሮ
2.ሉላዊነት (Globalization)
አዲሱ የዓለም ሥርዓትና የሃያ አንደኛው መቶ ክፍለ ዘመን ዐቢይ ክሥተት ነው እየተባለ ብዙ የሚባልለት
ሉላዊነት (Globalization - ግሎባላይዜሽን) ዓለምን በሙሉ በድንበር የለሽ አንድ የምጣኔ ሀብት ሥርዓት ጥላ
ሥር ለማድረግና ነጻ የካፒታል፣ የሸቀጥ፣ የሰው ኃይል፣ የአገልግሎት ወዘተ ዝውውር እንዲኖር ለማድረግ
ሉላዊነት - አንድ እሳቤ፣ አንድ ፍልስፍና፣ አንድ አሠራር፣ አንድ እምነት፣ አንድ ሂደት፣ አንድ አመለካከት፣
ሉላዊነት ዓላማው ዓለምን ለጥቂት ሀብታም ኮርፖሬሽኖች (በተለይም ለአሜሪካ ግዙፍ ኮርፖሬሽኖች)
ማመቻቸት ነው፡፡ ከዚህም የተነሣ ሉላዊነትን Operation Corporate - ዘመቻ ኮርፖሬሽን ይሉታል፡፡
የሰው ልጆች መታሠረዊ ፍላጎት ማሟያ ምንጭ የሆኑትን የተፈጥሮ ሀብት /በተለይ የእፅዋትና እንስሳትን
ማደፋፈርና በዚህም ብድሩ ከሀገሪቱ የመክፈል ዓቅም በላይ ሲሆንባት የኢኮኖሚ ነጻነቷንና
ሌላው ደግሞ ሚሲዮናውያንን በመላክ በሃይማኖት ሽፋን ገብተው ለኮርፖሬሽኖቹ የኢኮኖሚ ዘመቻና
2. የፖለቲካ ፖሊሲእና
ኢኮኖሚያዊ ትሥሥር፣
መወሰዳቸው ይጨምራል፡፡
አስረጂ፡-የኢንተርኔት ዓለም አቀፍ ተደራሽነት እንደ ማሳያ ከዓመት በፊት ከ 100 የዓለም ሰው 40 ው
“ለሰው ልጅ አዳኙ ራሱ የሰው ልጅ ነው፣ ሌላ ከዚህ ዓለም ውጭ የሆነ መንፈሳዊ ኃይል የለም፣ መንፈሳዊ
Humanist Max Hocutt says that human beings "may, and do, make up their own rules... Morality
is not discovered; it is made.”20
አስረጂ፡-
20
Max Hocutt, "Toward an Ethic of Mutual Accommodation," in Humanist Ethics, ed. Morris B. Storer , Buffalo:
Prometheus Books, 1980, p. 137.
ምንአልባትም ይጠላዋል፡፡
ናቸው፡-
• የሃይማኖት መሠረት አምላካዊ መገለጥና በመጽሐፍ ቅዱስና በቤ/ክ ያለው እውነት ሳይሆን በሰው
• የሰው ልጅ አእምሮና አመክንዮ የመጨረሻው ወሳኝ አካልና የእውነታ ሁሉ መለኪያና መዳረሻው እርሱ
ነው ይላሉ፡፡
• የእግዚአብሔር መንግሥት የሚገለጠው በዚህ ዓለም በሚደረግ ሳይንሳዊ ምርምራና ዕድገት ከሚመጣ
ይላል፡፡
• በተለየ ሁኔታ ጥሩ ወይም መጥፎ የሚባል እምነት (አንቀጸ እምነት) የለም፣ እያንዳንዱ የመረጠው
• ማመንም ሆነ አለማመን የግለሰቡ አመለካከትና መብት ብቻ ናቸው፡፡ ይህንም በሐሰት የበጎ አድራጎት
ተግባራት ሽፋንና በሐሰት ነጻነት በተባለ ከለላ ያራምዳሉ፡፡ መቻቻል የሚሉትም የዚሁ አካል ነው፡፡
5.የፕሮቴስታንት እንቅስቃሴ
“ሚሽነሪዎች ለአውሮፓውያን ግዛት ወረራ እንደ መንገድ ጠራጊ ወይም ፍታውራሪ በመሆን አገልግለዋል” 21
አገልግሎት ሽፋን ስር ሃይማኖታዊ ተፅእኖ በመፍጠር ፣መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን ለምሳሌ ክሊኒክ፣
ከሚሠሩት በላይ በብሮድካስትና በማኅበራዊ ሚዲያዎች በስፋት እየሠሩ ነው፡፡ ሕገወጥና ከሞራል ተቃራኒ
የሆኑ ጉዳዮችን የሚፈጽሙ ፓስተሮች በዝተዋል፡፡ የቤተክርስቲያንን አስተምህሮ በግልጽ የሚነቅፉና የሚተቹ
ፓስተሮች አሉ፡፡ ኢትዮጵያን ፕሮቴስታንት ለማድረግ ከ 2007 ዓ.ም ጀምሮ የሃያአምስት ዓመታት ስልታዊ
ዕቅድ ነድፈዋል፡፡ ዕቅዱን ለማሳካት አራት ማስተባበሪያዎች ከፍተው እየሠሩ ይገኛሉ፡፡ የዕቅዱ ባለቤት
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ሊያበለጽጋት ስለ ፈለገ ፕሮቴስታንት መሪ ሰጣት ተብሎ ተዘግቦ ነበር፡፡ በአንዳንድ
21
Donald Crummey, Priests and Politicians, p. 2
የፍቁረ እግዚእ ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት ክፍል የአገልግሎት ማሰልጠኛ ማንዋል ገጽ 54
ቦታዎች በተለይም ደቡብና ምዕራብ ኢትዮጵያ አካባቢ ጊዜው የእኛ ነው በሚል በኦርቶዶክሳውያን ላይ ጫና
እያሳደሩ ነው፡፡
6. ተሐድሶ
3 ኛ. ከ 1990 ወዲህ
ፓውል ባሊስኪ (Paul Balisky) የተባለ “የዓለም አቀፍ ተልእኮ ማኅበር” የኢትዮጵያ ዳይሬክተር
በ 1992 ዓ.ምየደከሙት ድካምና ያወጡት ገንዘብ ሁሉ ወደ ጠበቁት ግብ እንዳላደረሳቸው፡-
“ይህ ሁሉ ጥረት ቢደረግም ወንጌላውያኑ አሁን በማደግ ላይና በመካከለኛ ኑሮ ላይ ያለውን
የከተማውን ኅብረተሰብ መቀየር አልቻሉም፡፡ ምክንያቱም የተማረና ቤ/ክንን ለማገልገል ከፍተኛ
ቅንዓት ያለው የወጣቶች ኃይል ማኅበረ ቅዱሳን የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን በ 21 ኛው መ/ክ/ዘመን
ዘልቃ መጓዝ ትችል ዘንድ እየተጋደለ ነውና፡፡”(The Christian Science Monitor, 8 June, 2000)
ስለሆነም ከዚያ በፊት ያደርጉት እንደ ነበረው በውጭ ሆኖ ምእመናንን ለመንጠቅ በመሥራት ብቻ
ካሰቡት ቤተ ክርስቲያኒቱን ሙሉ በሙሉ የማጥፋት ግብ ለመድረስ ቀላል እንዳልሆነ ተረዱ፡፡
ስለዚህ አዲስ ስልት መቀየስ አስፈለጋቸው፡፡ ይህም “እናድሳለን” በሚል ሽፋን ከውጭ ወደ ውስጥ
ሠርጎ በመግባት ምእመኑን እስከ ሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑ የመረከብ ስልት ነው፡፡
ይህንም ኬንያ ውስጥ የሚታተመው “The Horn of Africa, Challenge and Opportunity”
የተባለው መጽሔት “The objective is not to set up a new church as such but to introduce
reforms within the church22 - ዓላማው አዲስ ቤተ ክርስቲያን መመሥረት አይደለም፤ ቤተ
ክርስቲያኗን (ኦርቶዶክስን) መለወጥ (ፕሮቴስታንት ማድረግ) እንጂ” በማለት ገልጾ
22
The Horn of Africa, Challenge and opportunity, p. 6
3.አስተምህሮን መቀየር፡-ስልቶቹም፡-
የቤተ ክርስትያኒቱ መገለጫ የሆኑትን ነገሮች (Icons) ማስረሳት፣ ማስጠላት (ጾም፣ ጸሎት፣
ስግደት፣ ሲኖዶስ፣ ጳጳሳት፣ ሊቃውንት፣ ሰንበት ት/ቤቶች … )፣
የባህል፣ የአስተምሮ፣ የቀኖና ፣ የዶግማ እና የሥርዓት ድንበር ማጥፋት፣
ምዕመኑ በቤተ ክርስቲያን አስተዳደር፣ በአባቶች፣ በገንዘብ አያያዝ፣ በምግባር፣ በመሳሰሉት
የተነሣ ቤተ ክርስቲያንን እንዲጠላ ማድረግ፣
ቤተ ክርስቲያንን ያረጀች ያፈጀች “አሮጊቷ ሣራ’’ አድርጎ መሳል
6.ተሐድሶ እንኳን እንደ ሆነ የማያውቅ ግን ተሐድሶ የሆነ ትውልድ መፍጠር እና ሳያውቀው የሚደግፍ ቲፎዞ
ማፍራት፤ ስልቶች፡-
7.አክራሪእስልምና (Fundamentalism)፡-
ውሀቢዝም በ 18 ኛው መ/ክ/ዘመን የተጀመረ የእስልምና አካል ሲሆን መስራቹም መሐመድ ኢብን አብደል
የእስልምናን እድገት የቀበረች ኢትዮጵያ ናት፡፡ስለዚህ አድስ ኢትዮጵያ ታስፈልገናለች የሚል እሳቤ ይዘው
ተነስተዋል፡፡
1. በፍጥነት መዋለድ
በሀገራችን ሙስሊሞችና ክርስቲያኖች አንዳንዴ በውጭ ሀይል ከሚጋጩት በስተቀር በስምነት ሲኖሩ ነበር፡፡
በአሁኑ ወቅት ግን ቀስ በቀስ ዝየጠነከረ የመጣው የውሃቢዝም እንቅስቃሴ ምክንያጥ ይህ ስምነት እየተቀየ
በሀገረ ስብከቱ 18 አብያተ ክረስቲያናት ሲኖሩ 7 አብያተክርስቲናት ሙሉ በሙሉ የተቃጠሉ ሲሆን 3 በከፊል
መቁረጥ፣አገልጋዮች መሰደድ፣
በጅማ ሐ/ስብከት፡-
ከመጋቢት 5፣2010 ዓ.ም .እስከ ሚያዝያ 5፣2011 ዓ.ም.ድረስ 12(አስራሁለት) ምእመናን ተገድለዋል፡፡
ድሬዳዋሐ/ስብከት፡-
በማህበራዊ ዘርፍ
ኢትዮጵያን ብሎም አፍሪካን መቆጣጠር አላማቸው ያደረጉት ሀገራት በዋናኛነት በሶስት ቡድን መመልከት
ምዕራባውያኑ እና ሩቅ ምስራቃውያኑ
ዘረኝነት
Refer to Immacuile Ilibagiza “Left to tell:Discovering God Amidst the Rwandan Holocust”
ስንተኛው ላይ ነን ?
1. Classification (መከፋፈል)
3. Dscrimnation (ማግለል)
የምዕራፉ አላማ
5.3.3 በጎ አድራጎት
ልማት ስታካሔድ ኖራለች፤ The education system of the church served the nation for centuries,
preparing graduates for religious and governmental leaders.The epistemology of the education
system was faith.23 በተለይም ደግሞ በትምህርት ዘርፍ ወጣቱን ከሕፃንነቱ ጀምሮ በማስተማር ለሰው ልጅ
በሚያስፈልጉት የአእምሮና የመንፈስ እድገት የተሟላ እንዲሆኑ ስትሰራ ቆይታለች ፤ ወደፊትም ትሰራለች፤24
በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ሰንበት ት/ቤቶች አሰራር መታየት የጀመረው በሃያኛው መቶ ክፍለ ዘመን መባቻ
ላይ እንደሆነ ይነገራል፡፡ ይህም ዘመን የዘመናዊ ትምህርት ሐሳብ ወደ ሀገሪቷ መግባት የጀመረበት ከመሆኑ
ይታያል፡፡ ቀደም ሲል መማር የፈለገ ወጣት ሁሉ በቤተክርስቲያን መስመር ውስጥ የሚያልፍበት ዘመን ነበር፤25
ሥርዐት የሚያኙበት ዘመን ነበር፡፡ ከዚህም የተነሣ ወጣቶች ወላጆቻቸውን፤ ትተው ሙሉ ሕይወታቸውን
ሰጥተው ወደ አብነት ት/ቤት በመግባት ተጠልቆ ከሚያልቀው የእውቀት ማዕድ የቻሉትን ያህል በብዙ ድካም
ሸምተው ገሚሱ የመምህራቸውን ወንበር በመተካት አልያም በተለያዪ ቦታዎች ወንበር ዘርግቶ ቀጣይ
ወጣቱን ለሁለት ከፈለው፡፡ ወላጆቹን ትቶ ‹‹በእንተ ስማ ለማርያም ››እያለ ከምዕመናን የዕለት ምግብ
እያሰባሰበ በአብነት ት/ቤት የሚማር ወጣት እና መኝታና ምግቡ በሞግዚት እየተዘጋጀለት በዐዳሪ ት/ቤት
የሚማሩ በሚል፡፡ በተለይ የዐዳሪ ት/ቤት የወጣቱን ስሜት እየሳበበ መምጣቱ ወደ አብነት ት/ቤት ከሚሔደው
ወጣት ይልቅ ወደ ዘመናዊ ት/ቤት የሚገባው ቁጥሩ እየጨመረ እንዲሄድ አድርጓል፡፡ ከዚህም የተነሣ
23
Tamene Mamo (2019), Study on the Role of Orthodox Churches in Tourism Development of Ethiopia: The
Case of Addis Alem St. Mary Church
24
Aselefech G/Kidan Tikuye (2014), The Role of Ethiopian Orthodox Church in the Development of
Adult Education: The Case of Ye’abnet Timhirt Bet
25
አለቃ ዕንባቆም፣ የኢትዮጵያ ባህል ጥናት ለማጥናት የተሰበሰቡ ፅሁፎች፤ሰለ ኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ትምህርት፣ ሰኔ
1957፣አዲስ አበባ
ትውልድ በመንፈሳዊ እድገቱም የተስተካከለ ይሆን ዘንድ ፈቃደኛ በሆኑ ወጣቶችና ካህናት አነሳሽነት
የቅዳሜና እሑድ ት/ቤት በኢትዮጵያ መቋቋም የጀመረው ከ 1939 ዓ.ም ጀምሮነው፡፡ መሰረቱ የተጣለውም
መሥራቹም ከተፈሪ መኮንን ት/ቤት እና ከቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዪንቨርስቲ ይማሩ የነበሩ አንዳንድ የኦርቶዶክሰ
ተዋህዶ ሃይማኖት ተቆርቋሪ ተማሪዎች ናቸው፡፡ ምክንያት የሆናቸው በዩኒቨርስቲው ውስጥ በአስተማሪነት
ትምህርታቸውንማስተማር በመጀመራቸውነው፡፡
በተፈሪ መኮንን ት/ቤት የተጀመረው የኦርቶዶክሳውያን ወጣቶች እንቅስቃሴ ተጠናክሮ ወደ ምስካየ ኅዙናን
መድኀኔዓለም ገዳም ተዛውሮ ተምሮ ማስተማር የወጣቶች መንፈሳዊ ማኅበር ተመስርቶ ሕፃናትና ወጣቶች
በሚሰጠው መንፈሳዊ አገልግሎት የተፈሪ መኮንን እና የእቴጌ መነን ት/ቤት ተማሪዎችን በብዛት መሳብ
በመቻሉ በየሳምንቱ እሑድ ተማሪዎች በብዛት ወደ ቤ/ክ እየመጡ በመንፈሳዊ አገልግሎት ተሳታፊ ከሆኑ
በኋላ ብዙዎች በቤ/ክ እንዳንድ ሥራዎች በፈቃደኝነት መሳተፍ ጀመሩ፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በተማሪዎችና
በገዳሙ መካከል አንድነትን መፍጠር የሚችልና የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት የሚሰጥበት ሰንበት ት/ቤት
እንዲቋቋም ወጣቶቹ በመጠየቃቸው “ተምሮ ማሰተማር” የተባለው ታዋቂው ሰንበት ት/ቤት በ 1939 ዓ.ም
ተመሠረተ፡፡
በነበረው ምቹ ሁኔታ በመታገዝ ወደቅድስት ሥላሴ፤ ታዕካነገስት፤ መንበረ መንግስት ቅዲስ ገብርኤል እና
ወደሌሎችም አከባቢዎች ለመስፋፋት ችሏል፡፡ በ 1960 ዓ.ምይህ የሰንበት ት/ቤቶች እንቅስቃሴ ለማስተባበር
ለማጠናከር ይቻል ዘንድ በጠቅላይ ቤተክህነት በስብከተ ወንጌልንና ማስታወቂያ መመሪያ ሥር ማእከላዊ
ጽ/ቤት ተቐቁሞለታል ሰያሜ የሰንበት መምህራን ጽ/ቤት ይባል ነበር፡፡በኃላ በ 1965 ዓ.ም ራሱን ችሎ ወደ
ወጣቶች ጉዳይ መምሪያነት አድጎ የተለያዪ የወጣቶችን መንፈሳዊ ማኅበራትን ያስተምር ጀመረ፡፡26
ከ 1970-1982
26
መጽሔተ ወራዙት፣ ግንቦት 25 2004 ዓ.ም፣ ልዩ እትም
ሲኖዶስ ደረጃ ተቀባይነት አግኝቶ ‹‹ሰንበትት/ቤት›› በሚል ስያሜ ይዞ ሕጋዊ ሆኖ እንዲቀጥል እና በሁሉም
ተሻሽሎ በተዘጋጀው ቃለ ዐዋዲ ጸድቋል፡፡ በማያያዝም 1976 ዓ.ም በቅዱስ ሲኖዶስ የጸደቀ መተዳደሪያ ሕግ
ሲመጣም ወጣቱ ለጦርነት ይፈለግ ስለነበር በሰንበት ት/ቤት እንደ ልብ መሰብሰብ አዳጋች ሆነ፡፡ ከዚህም የተነሳ
ያደረጉት ወረራ በፈጠረው ቁጭት እና ሌሎች በጎ አጋጣሚዎች ተጨምረው ወጣቱ ፊቱን ወደ ቤተክርስቲያን
በማዞር በወጣት የቤተክርስቲያን አገልግሎት እምርታ የታየበት ነው፡፡ቀደም ሲል እግዚአብሔር የለም በሚል
ርዕዮተ አለም የተመታው እና ፕሮቴስታንቲዝምን እንደ ስልጣኔ ይመለከት የነበረው የከፍተኛ ትምህር
ተቋማት ተማሪ ፊቱን ወደቤተክርስቲያን መመለሱ የሰንት ትምህርት ቤቶችን አገልግሎት ከፍ ወዳለ ምዕራፍ
እንዲሸጋገር አድርጎታል፡፡27 በ 1986 ዓ.ም ሀገር አቀፍ የሰንበት ት/ቤቶች መተዳደሪያ ደንብ በቅዱስ ሲኖዶስ
ጸድቆ በሥራ ላይ መዋሉ፤ በመንፈሳዊ እና በብሔራዊ በዓላት እና የንግሥ በዓላት በታላቅ ድምቀት እንዲከበሩ
ቤተክርስቲያን የሚጎርፉትን ወጣቶች መሰረታዊ የክርስትና ትምህርት መርሐ ግብር ዘርግቶ በማስተማር
በኮርስ መልክም በማሰልጠን እና የሰንበት ት/ቤት አባል በማድረግ፤ የስብከተ ወንጌል ፕሮግራም እንዲጠናከርና
እንዲስፋፋ ሆኗል፡፡
እያከናወኑ ቢሆንም ከሚጠበቅባቸው አንጻር ሲታዩ ገና ያልደረሱባቸው በርካታ አዝመራዎች አሉ፡፡ ከላይ
ተተኪ አገልጋይ የሚሆን ትውልድ ከማፍራት አኳያ ብዙ አልተጓዘም፤ በየጊዜው በተለዋዋጭ መቋቋም
27
መጽሔተ ወራዙት፣ ግንቦት 25 2004 ዓ.ም፣ ልዩ እትም
በበለጠ መንጋዋን ለመጠበቅ ያለባት ኃላፊነትም በዚሁ መጠን ስፊና ጥልቀት ያለው መሆኑ በግልጽ ይታወቃል፡፡
በአገሪቱ ውስጥ በሚገኙ 37,332 አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ ከ 20,000,000 በላይ ወጣቶች እንዳሉ
የሚገመት ሲሆን፣ እስከ አሁን በ 8610 አብያተ ክርስቲያናት በሥርዓት ተመዝግበው አገልግሎት በማግኘት ላይ
በሰንበትትምህርት ቤቶቻችን የክፍተት መፈጠር በሀገሪቱ ያሉት ሰንበት ት/ቤቶችን ወጥነት ያለው አንድ
ዓይነት አሰራር የሌላቸው መሆኑ፤ እርስበርስ ተገናኝተው አሠራርንም ሆነ ልምድን የሚለዋወጡበት መድረክ
የሌላቸው በመሆኑ ነው፡፡ እንዲሁም ዘመኑን የዋጀ ወደሰንበት ት/ቤት የሚመጣውን ወጣት እንደ ዕድሜው እና
እያንዳንዱ የአጥቢያ ቤተክርስቲያን የሰንበት ት/ቤት በሰበካ ጉባኤ አስተዳደር ት/ቤት ችግር መፍታት
አለመቻል
ከሀገረ ስብከት ጀምሮ እሰከ አጥቢያ ቤተክርስቲያን ያሉ አስፈጻሚ አካላት የቃለ ዓዋዲውን ሕግ
ተግባራዊ አለማድረጋቸው፤
ወጣቶችን ቅዱስ ሲኖዶስ በ 1986 ባወጣው መተዳደሪያ ደንብ ማደራጀትና መምራት አለመቻል፣
28
የኢ/ኦ/ቤ/ክ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ አመሰራት ታሪክ፣ በመጋቤ ሐዲስ መኮነን ወ/ትንሳኤ
29
መጽሔተ ወራዙት፣ ግንቦት 25 2004 ዓ.ም፣ ልዩ እትም
ወጣቶች ከልዩ ልዩ ገቢዎች ያሰባሰቡትን ገንዘብ ከሰበካ ጉባዔ ጋር በመተማመን ገቢና ወጪ ማድረግ
አለመቻል፤
የሰንበት ትምህርት ቤቶችን አስተዳደርና ፋይናስ ስርዓት ወጥ ለማድረግ መተዳደሪያ ደንቦች የሒሳብ
ተለያዩ የግል ሥራዎች ላይ በመጠመድ የሰንበት ት/ቤትን ሥራ በትርፍ ሰዓት የሚሰራ አድርጎ ማሰብ
የሠንበት ት/ቤቱን አባላት ቁጥር፣ ያቋረጡትን፣ ያሉትን፣ ወደ ዩኒቨርስቲ የገቡትን፣ ያገቡ፣ ንስሃ አባላት
ያላቸውንና የሌላቸውን ብሎ የተጣራ መረጃ ያለመያዝ ችግር በአብዛኞቹ ሠንበት ት/ቤቶች የሚታይ
ችግር ነው፡፡
አባላት ሐዘንና ደስታ ሲገጥማቸው ለሌሎች አባላት ማሳወቅ የሚቻልበት መደበኛ የሆነ መንገድ
አለመኖር
እያንዳንዱ የሰ/ት/ቤት አባል በመንፈሳዊና በስጋዊ እድገቱ ውስጥ በየአመቱና በረጅም ግዜ የት መድረስ
ሁኔታን ተለዋዋጭነት ዳሰሳ በማካሄድና በመተንተን ምላሽ የሚሰጡ ብቃት ባላቸው መንፋሳዊ
በሰንበት ትምህር ቤቶች ዙሪያ ያለውን አስተዳደራዊ ችግሮች በጥናት መዳሰስና የመፍትሄ አቅጣጫ
ማቅረብ
በሰንበት ትምህርት ቤቶችና በሰበካ ጉባዔ አመራር አባላት መካከል ግልፅ የሆነ አስተዳደራዊ ግንኙነት
እንዲፈጥሩ ማድረግ
በየደረጃው ያሉት የሰንበት ት/ቤት መዋቅሮች በዕቅድና በዝግጅት እንዲመሩ አሰራር መዘርጋት
በቃለ ዓዋዲው መመሪያ መሠረት በካህናትና በሰንበት ት/ቤት ወጣቶች መካከል ጤናማ ግንኙነት
በተለያዩ በአቅም የሚበላለጡ የሰንበት ትምህርት ቤቶች መካከል የመረዳዳትና አብሮ የመደጋገፍ
ስርዓት ማበጀት
ልማት በቁጥር የሚለካ አመርቂ ውጤት ማምጣት ብቻ (Quantitative) ሳይሆን በቁጥሮች መለካት የሚቸግር
(Qualitative) ገፅታ አለው፡፡ እንዲያውም የልማት ዋነኛ ግብ በቁጥሮች ለመለካት አስቸጋሪ የሆነውን ደስተኛ
ማህበረሰብ መፍጠር ነው፡፡ ልማት የዛሬ ኑሮ ወይም የነገ ተስፋ ላይ ተጨባጭ አዎንታዊ ለውጥ መፍጠር ነው፡፡
30
Wikipedia
31
አለቃ ኪዳነወልድ ክፍሌ፣
ኦርቶዶክሳዊ ፍቺ
ልማት የሚሆነው በፍፁም የእግዚአብሔር መውደድ ላላቸው እንዲሆን ቅዱስ ዳዊት ፅፏል፡፡መዝ 121፡6-7
“ለኢየሩሳሌም ሰላምን ለምኑ፣ አንተን ለሚወዱ ሁሉ ልማት ይሁን በኃይልህ ሰላም በጌጠኛ ቤትህም ልማት
ይሁን፡፡” ስለዚህ ልማት በቤተክርስቲያናችን መጥፎ ስራዎችን አስወግደን መልካም ምግባራትን እንድናተርፍ፣
ከትናንት የተሻለ ስንቅን ለዛሬ እንዲሁም ለነገ የምናስቀምጥበት የሚያስችለን ፅንሰ ሀሳብ የያዘ ቃል ነው፡፡
የሰው ሀብትን በሰንበት ትምህርት ቤቶቻችን ለማልማት ዋነኛው ነገር ፍቅር ነው፡፡ ለዚያም ነው ሐዋርያው
ቅዱስ ዮሐንስ በመልዕክቱ ምዕራፍ ቁጥር 20 ላይ ማንም እግዚኣብሔርን እወዳለሁ እያለ ወንድሙን ቢጠላ
ሐሰተኛ ነው ያየውን መንድሙን የማይወድ ያላየውን እግዚብሔርን ሊወደው እንዴት ይችላል ብሎ የፃፈልን፡፡
የአባላትን ቁጥር ማብዛት ብቻ ሳይሆን ያለውን አባል በትክክል አዋዋሉን፣ ምግባሩን ማወቅ በሚቻልበት
መልኩ መስራት ሲቻል እና የተማረውን የሀይማኖት ትምህርት የሚፈፀም፣ ለሰንበት ትምህርት ቤት እና
ለቤተክርስቲያን የሚቆረቆር ቅኝ፣ ታዛዥ፣ ደግና ታማኝ አገልጋይ ማፍራት ሲቻል ሰው ለማ ለማለት
ያስችላል፡፡ 2 ኛ ጤሞ 2፡6 ”የሚደክመው ገበሬ ፍሬውን ከሚበሉት መጀመሪያ ሊሆን ይገባዋል” እንደተባለ
ከምንሰጣቸው አገልግሎቶች ቀዳሚ ተካፋይ መሆን አለብን፡፡
እያንዳንዱ አባል በመንፈሳዊና በስጋዊ እድገቱ ውስጥ በየአመቱና በረጅም ግዜ የት መድረስ እንደሚፈልግ፣
ምዕመንን ከቤተክርስቲያን የሚጠብቀውን ድጋፍ በመተንተን እንዲያቅድ በመርዳት፣ የነገረ ሃይማኖት
ትምህርት፣ የግልና የማህበር አምልኮ ሥርዓትን በሚመለከት የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት ከሌሎች
ምዕመናን በተሻለ መንገድ እንዲያሳዩና ምሳሌ እንሆኑ በመርዳት ፣በአሁኑ ወቅት እጅግ የተሻለ አገልግሎት
ያላቸውን ሰንበት ትምህር ቤቶች በማጥናት እና በሚቀጥሉት አመታት ሊደረስበት ይገባል ተብሎ
የሚታመነውን ግብ በማየት ያለውን የክፍተት ርቀት መገምገም ይህም የግብ ከፍታ
(benchmark)በማዘጋጀት፣ ሴኩላር ጠባይ ያላቸውን ትምህርቶች ይዘትና አሰጣጥ ከቤተክርስቲያኒቱ
አስተምህሮ አንፃር በመቃኘትና አሰጣጡን መቆጣጠር፣ለምሳሌ የፆታና ስነተዋልዶ፣ ኤች.አይቪ፣ ህገወጥ
ስደት… እንዲሁም በሰንበት ትምህር ቤቶች ዙሪያ ያለውን አስተዳደራዊ ችግሮች በጥናት መዳሰስና የመፍትሄ
አቅጣጫ በማቅረብ የሰውሀተን ማማት እንችላለን፡፡
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማፈራጃ መምሪያ መሪ ዕቅድ፣ 2005-
32
2010
የሰንበት ትምህርት ቤቶችን አስተዳደርና ፋይናስ ስርዓት ወጥ ለማድረግ መተዳደሪያ ደንቦች የሒሳብ
አሰራችና ዘገባዎች አቀራረቦችን የተመለከቱ ጥልቅ ጥናቶችን ሁሉንም ባማከለ መልኩ በማዘጋጀት ፣
የበጀት፣የሰው ሃይልና የንብረት አስተዳደር ስልጠናዎችን በማሰናዳት፣ ለሰንበት ትምህርት ቤቶች ወጥ
የፋይናንስ አሰራርን የሚያስፈልጉ ውሳኔዎችን የገንዘብና ሞያ ድጋፎችን፣ ትምህርትና አመራር ጥራት
ቁጥጥርን በሚመለከት መወጣት ያለባቸውን ግዴታዎች በግልጽ ማሳየትና አፈጻጸማቸውን ክትትል
የሚያደርግ አካል በማዘጋጀት ፣የሒሳብ አጠቃቀምና አያያዝ መመሪያዎች በስራ ላይ እንደዋለ በመከታተል
የገንዘብ ሀብ ልማተን ማሳደግ ይቻላል፡፡
የግዜ ልማት ስንል አንድን ተግባር ለማከናወን የሚወስድብንን ግዜ በእግብቡ መጠቀም ነው፡፡የግዜ ልማት ጥሩ
የሆነ የመርሀ ግብራት ዝርዝር ከማዘጋጀት ጀምሮ ፣ ግብን ማስቀመጥ፣ ከአንዱ ስራ የትኛው መቅደም
እንደዳለበት መለየት፣ ስራዎችን በቀላሉ መከፋፈል፣ ትኩረትን በአንድ ቦታ ሰብስቦ የተሻለ ስራ መስራት፣ጥሩ
የሆነ ዕቅድ ግብን እና አላማን ቀድሞ ማስቀመጥ ለስራዎች የመጨረሻ ቀን መቁረጥ የሚሉትን ፅንሰ ሀሳቦች
በዋነኛነት ይይዛል፡፡
መረጃ የተበታተነውንና ጥሬ የሆነውን ነገር እንዲሰበሰብ እና የበሰለ እንዲሆን የማድረግ አቅም አለው፡፡ አርቆ
የሚያይና ዘመኑን የሚዋጅ የመረጃ አያያዝ ለሰንበት ትምህርት ቤቶቻችን ያስፈልጋቸዋል፡፡ ለቤተክርስቲያን
ሥርዓትና ለሁሉም ነገር ጠንቃቃ የሆነ፣ በቴክኖሎጂ የታገዘ አስተዳደራዊ ሥርዓት ያስፈልገናል፡፡የመረጃ ልማት
ስንል የመረጃ አያያዝን፣ አባላት እርስ በራሳቸው ያላቸው ግንኙነት እንዲሁም አንድ ሰንበት ትምህርት ቤት
ከሌሎች ሰንበት ትምህርት ቤት ጋር፣ ከምዕመናን ጋር፣ ከሰበካ ጉባኤው ጋር፣ ከማህበረቅዱሳን እነ ከሌሎች
ማህበራት ጋር ያለው ግንኙነት ምን ይመስላል የሚሉትን በዋነኛነት ይይዛል፡፡
አሁን ባለው የቤተክርስቲያን መዋቅር ጊዜን፣ ገንዘብን በሚቆጥብና በአንድ ወጥ አመራ ከላይ ወደታች
የማያቋርጥ ክትትልና የወጣቶችን ፍላጎትና ተለዋዋጭ አካባቢያቸውን የሚቃኝ ከአመራር ወደ አባሉ
የሚወርድ፣ የመረጃ ፍሰት ሰንሰለት እንዲኖር መተለምና መተግበር ያስፈልጋል፡
ብቻውን የሮጠ አሸናፊ አይባልም እና ከሁሉም ሰንበት ትምህርቶች ጋር የሚደረግ የልምድ ልውውጥ (የመረጃ
መጋራት) መፈጠር አለበት፡፡ ቋሚ የልምድ ልውውጥ በማድረግ፣ በሰንበት ትምህርትቤች አንድነት በመሳተፍ
፣ከአጋር አካላት ጋር ጥሩ መስተጋብር በመፍጠር ፣ የተለያዩ የአንድነት መርሃግብራትን በማዘጋጀት እንዲሁም
በመረጃ አያያዝ ዙሪያ የተለያዩ ጥናቶችን በማዘጋጀት የመረጃ ልማትን ማድረግ ይቻላል፡፡
5.3.3 በጎ አድራጎት
በጎ አድራጎት ማለት መልካም ነገሮችን ለመስራት ያለማንም ሰው ጫና በራስ ፍላጎትና ተነሳሽነት ለማከናወን
መፈለግና ማድረግም ጭምር ነው፡፡ 1 ኛ ተሰ 5፡15 “እርስ በእርሳችሁ ለሁሉም መልካሙን ማድረግ ትጉ!”
ለጽድቅ
1. መጽሐፍ ቅዱስ
5. ኰኲሐ ሃይማት፣ መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀንበሬ፣የካቲት 1989 ዓ.ም አዲስ አበባ
6. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ታሪክ፣ አቡነ ጎርጎርዮስ የሸዋ ሊቀ ጳጳ፣ሰኔ 1974 ዓ.ም
10. መፅሐፈ ድጓ
11. ትምህርት በእንተ ምክንያተ ሐውልታት በገብረእግዚአብሄር ኪደ፤ 2009 ዓ.ም አዲስ አበባ
12. የኢትዮጵያ ኦርቶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ታሪክ ከልደተ ክርስቶስ እስከ 2000 ዓ.ም
13. የኢትዮጵያ ቤተክርስቲን ወርቃማ ዘመናት በዲ/ን ሰሎሞን ዮሐንስ፣ መጋቢት 21 2001 ዓ.ም አዲስ
አበባ
16. አለቃ ዕንባቆም፣ የኢትዮጵያ ባህል ጥናት ለማጥናት የተሰበሰቡ ፅሁፎች፤ሰለ ኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን
ወ/ትንሳኤ
20. በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ መሪ
ዕቅድ፣ 2005-2010