Professional Documents
Culture Documents
ያግኙን
Email
office@eotc-gssu.org
YouTube
https://www.youtube.com/channel/UCZl-
WxxCvV2UzcSz1Qxh6UAg
Facebook
http://facebook.com/EOTC.GSSU
Telegram
https://t.me/EOTCNSSU
Website
https://eotc-gssu.org/a/
Twitter
https://twitter.com/tibeb_felege
Copyright ©
2015 E.C
ምዕራፍ አንድ
ነገረ መጽሐፍ ቅዱስ
ዓላማ
ተማሪዎች ይህንን ምዕራፍ ሲያጠናቅቁ
የማስጀመሪያ ጥያቄዎች
፩
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ ክፍል
፫
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ ክፍል
የመልመጃ ጥያቄዎች
ትክክል የሆነውን እውነት ትክክል ያልሆነውን ደግሞ ሐሰት
በማለት መልሱ።
፭
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ ክፍል
፮
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ
ምዕራፍ ሁሉት
የመጽሐፍ ቅዱስ አከፋፈልና ስርጭት
ዓላማ
ተማሪዎች ይህንን ምዕራፍ ሲያጠናቅቁ
የማስጀመሪያ ጥያቄዎች
፯
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ ክፍል
፱
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ ክፍል
፲
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ
2.3 መጽሐፍ ቅዱስ በዓለም መድረክ
መጽሐፍ ቅዱስ ለመጀመሪያ ጊዜ ከክርስቶስ ልደት በፊት በ980 አካባቢ
ወደ ግእዝ ተተርጒሟል። ምንም እንኳን ቅዱሳት መጽሐፍት በመጀመሪያ
የተተረጎሙት ወደ ጽርዕ /ግሪክ/ ቋንቋ ነው የሚሉ ቢኖሩም፤ ሰባው
ሊቃውንት ቅዱሳት መጽሐፍቱን የተረጎሙት ከክርስቶስ ልደት በፊት
በ284 ዓመት ላይ በበጥሊሞስ ዘመነ መንግሥት ነው። በዚህ መሠረት
ወደ ግእዝ ቋንቋ ከተመለሰበት ጋር ሲነጻጸር በመካከላቸው የ696 ዓመት
ልዩነት ይታያል። ስለዚህ የግሪኩ ትርጒም ሁለተኛ መሆኑ ግልጽ
ነው። በሁለቱ መካከል የተተረጎመ የለምና። የግሪኩ ትርጒም ሴፕቱ
አጊንት /የሰባው ሊቃናት ወይም የሰባው ሊቃውንት ትርጒም/ በመባል
ይታወቃል።
ከጌታችን ልደት ወዲህ የግሪኩን ሴፕቱ አጊንት ትርጒም ለማቅናት
በሁለተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የተነሡት ሲማኩስ፣ አኪላ እና በሦስተኛው
መቶ ክፍለ ዘመን የነበረው ሉቅያኖስ ይጠቀሳሉ።
ከዚህም በኋላ ኑን ክሉስ እና ዮናታን የተባሉ የታወቁ የአይሁድ
ሊቃውንት ብሉይ ኪዳንን ወደ አረማይክ ቋንቋ መልሰዋል። በጌታችን
መዋዕለ ስብከት በእስራኤል የሚነገረው ቋንቋ አረማይክ ነበር። በዚህም
ቋንቋ ጌታችን አስተምሯል።
ምንም እንኳን አንዳንድ መጽሐፍት አስቀድመው በላቲን ቋንቋ
ተተርጒመው እንደበር ቢነገርም በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን (በሄሬዲሞስ
ዘመነ መንግሥት በ366 እ.ኤ.አ) የተነሳው ታላቁ የቤተክርስቲያን አባት
አባ ጄሮም ወደ ኢየሩሳሌም በመጓዝ ለ40 ዓመታት የዕብራይስጥና
የግሪክ ቋንቋዎችን በሚገባ በማጥናት መጽሐፍ ቅዱስን ወደ ቩልጌት
ተርጒሞታል። ትርጒሙም ቩልጌት በመባል ይታወቃል። ቩልጌት በሮም
ይኖሩ የነበሩ “ቩልገስ” እየተባሉ የሚጠሩ ሕዝቦች ቋንቋ ነው። አባ
ጄሮም /ሄሮኒመስ/ ከቩልገስ ቋንቋ ወደ ላቲን እየተረጎመው ሳለ አረፈ።
ይህን የእርሱን ትርጒም ከእርሱ በኋላ የተነሡ ሰዎች እንዳጠናቀቁት
ይነገራል።
፲፩
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ ክፍል
፲፬
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ
የመልመጃ ጥያቄዎች
ትክክለኛውን መልስ መልሱ።
፲፮
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ
ምዕራፍ ሦስት
የመጽሐፍ ቅዱስ (የቅዱሳት መጽሐፍት) ንባብ ሥርዓት
ዓላማ
ተማሪዎች ይህንን ምዕራፍ ሲያጠናቅቁ
የማስጀመሪያ ጥያቄዎች
፲፯
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ ክፍል
1.ጸሎት ማድረግ
በባለፈው ትምህርታችን ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ምንነት በስፋት ተመልክተን
ነበር ከዛም መካከል እግዚአብሔር በዘመኑ በነበሩ ቅዱስን ስዎች
አማካኝነት ለእኛ የጻፈው መጽሐፍት እንደሆነ ገልጸን ነበር በመሆኑም
መጽሐፍ ቅዱስ ለማንባብም ለማጥናትም የእግዚአብሔር ረዳትንና
አገዥነት ያስፈልገናል፡፡ ምክንያቱም ለቅዱሳን መጻሕፍትን እንዲጽፉ
ምስጢርን ስለገለጸላቸው ይኸው እስከ ዛሬ ድረስ የስው ልጆችን
የሚመክር የሚያስተምር መጽሐፍ እንዲጽፉ አስችሏችአል። አሁንም
እኛም እግዚአብሔር እኛን በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተገለጹትን ታሪኮች
ሕግች ተግሳጽ እና ምክሮች ምስጢር እንዲገልጽልን እግዚአብሔርን
በጸሎት ልንጠይቅ ይገባል፡፡
፲፰
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ
3.በቤተ ክርስቲያን በምትሰጠው አገልግሎት ውስጥ በመሳተፍ
ቤተ ክርስቲያን የእግዚአብሔር ቃል ከዓመት እስከ ዓመት የሚነገርባት
የእግዚአብሔር ቤት ናት በመሆኑም በዓውደ ምሕረት በሚሰጡ የሰርክ
ጉባኤ በመገኘት፣ በቅዳሴ ሥርዓት በመሳተፍ፣ በሚከበር በዓለት በመገኘት
እና በስንበት ትምህርት ቤት በሚስጡ ተከታታይ ትምህርት በመከታተል
መጽሐፍ ቅዱስን መረዳት እንችላለን።
4.ማስታወሻ ማዘጋጀት
አንባቢው ያነበበውን እንዳይረሳ ከሚያነበው ውስጥ የሚገነዘበውን
የሚጽፍበት ማስታወሻ ማዘጋጀትም ይኖርበታል። “ለሚጠይቋችሁ ሁሉ
መልስ ለመስጠት ዘውትር የተዘጋጃችሁ ሁኑ” 1ኛጴጥ 3፥1
የመልመጃ ጥያቄዎች
፲፱
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ ክፍል
የተግባር ልምምድ
፳
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ
ምዕራፍ አራት
የመጽሐፍ ቅዱስ መልክዐ ምድር
ዓላማ
ተማሪዎች ይህንን ምዕራፍ ሲያጠናቅቁ
የማስጀመሪያ ጥያቄዎች
፳፩
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ ክፍል
፳፪
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ
4.1 በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚገኙ ከተሞችና ሀገሮች
ከተማ ማለት ብዙ ሰዎች አንድ ላይ ተሰባስበው የሚኖሩበት ቦታ
ነው። በዓለም ላይ የመጀመሪያዋ ከተማ ሄኖሕ ትባላለች። ይህች ከተማ
የተሠራችው በቃየን ሲሆን የተሰየመችውም በቃየን የመጀመሪያ ልጅ ስም
እንደሆነ መጽሐፍ ቅዱስ ያስረዳል።“... ከተማም ሠራ። የከተማይቱንም
ስም በልጁ ስም ሄኖሕ አላት” ዘፍ 4፥16-17 ከዚያም ወዲያ ሰዎች
በአንድነት ለመኖር ሲፈልጉ ውኃ በሚገኝበትና ለምሽግ በሚያመች አምባ
ወይም ተራራ ላይ ቤቶችን በመሥራት ከተማን ይመሠርቱ ነበር።
ሀ) ናዝሬት
ነጭ ድንጋይ ማለት ነው። በገሊላ አውራጃ በስተ ደቡብ ምዕራብ ከገሊላ
ባሕር በስተምዕራብ 24 ኪ.ሜ ርቃ የምትገኝ ከተማ ናት። የእመቤታችንና
የዮሴፍ የትውልድ ሥፍራ ናት። መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል እመቤታችንን
ያበሠረው በዚህች ሥፍራ ነው።
፳፫
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ ክፍል
ለ) ቃና
ከናዝሬት ከተማ በስተ ሰሜን ምሥራቅ በቅርበት የምትገኝ መንደር
ናት። በብሉይ ኪዳንም የምትታወቅ ከተማ ናት። ኢያ19፥28 ጌታችን
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በእመቤታችን አማላጅነት የመጀመሪያውን
ተአምር በዶኪማስ ቤት የፈጸመባት ክብርት ቦታ ናት። ዮሐ2፥1-11
ሐዋርያው ናትናኤል የተወለደው በቃና ነው። ጌታችን ውኃውን ወደ
ወይን የለወጠባቸው ስድስቱ ጋኖች ዛሬም ይጎበኛሉ።
ሐ) ቅፍርናሆም
የዕብራይስጥ ቃል ሲሆን ትርጒሙም የናሆም መንደር ማለት ነው።
በገሊላ ባሕር በስተ ሰሜን የምትገኝ የወደብ ከተማ ናት። የታወቀች የዓሣ
ማጥመጃ ሥፍራ ናት። ጌታችን የምኩራብ አለቃውን የኢያኤሮስን ሴት
ልጅ “ጣቢታ ቁሚ” ብሎ ከሞት ያስነሣት በዚህች ቦታ ነው። ማር 5፥22
ትርጒሙም ‘አንቺ ብላቴና ተነሽ እልሻለሁ ’ማለት ነው። በዚህች ከተማ
ምኩራብ ስለ ነበር ጌታችን ብዙ ጊዜ አስተምሮባታል። ማር 1፥21 ጌታችን
ከአህዛብ ሀገር የነበረውን የመቶ አለቃውን ልጅ ከሽባነቱ የተረተረባት
ማቴ8፥5፣ አጋንንት ያደረባቸውን ሰዎች የፈወሰባት ማቴ8፥16፣ የቅዱስ
ጴጥሮስን አማት ከንዳድ በሽታ ያዳነበት ፣ማቴ8፥ 14፣ እንዲሁ ከ12
ዓመት ጀምሮ ደም ይፈስሳት የነበረችውን ሴት ያዳነባት ማር5፥25-
34 ሥፍራ ናት። ይሁን እንጂ በውስጧ የነበሩት ሰዎች ይህን ሁሉ
ተአምራት ቢያዩም አላመኑም ነበር። ማቴ11፥23-25 በዚህም ምክንያት
ጌታችን ስለረገማት ከተማይቱ ጥፍታለች። በመሬት መንቀጥቀጥና
በጦርነት እንዳልነበር ሆናለች። ቅዱስ ማቴዎስ ከመመረጡ በፊት ቀረጥ
ይቀርጥባት የነበረች ሥፍራ ናት። ማቴ9፥ 9-13፣ ማር2፥13-17
መ) ቤተ ሳይዳ
የዓሣ አጥማጅ ቤት ማለት ነው። በኢየሩሳሌም ከተማ በበጎች በርከ
ምትገኘው ቤተ ሳይዳ የተለየች ናት። በገሊላ የባሕር ወደብ በስተሰሜን
፳፬
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ
ጫፍ ሆና የተሠራች ናት። የቅዱስ ጴጥሮስ፣ የወንድሙ የእንድርያስ እና
የፊልጶስ የትውልድ ቦታ ናት። ዮሐ1፥45፣ዮሐ12፥21 ጌታችን አምስቱን
እንጀራ እና ሁለቱን ዓሣ አበርክቶ ያበላው ከቤተሳይዳ አጠገብ በሚገኘው
ምድረ በዳ ነው።ሉቃ 9፥10-17 ጌታችንም ዕውር የነበረውን ሰው ያዳነውም
በዚህች ከተማ ነው። ማር8፥22-26 እንደዚህ ዓይነት ታላላቅ ተአምራት
ቢደረግባትም ነዋሪዎቿ ግን የጌታን አምላክነት ሊቀበሉ ባለመቻላቸው
በስተሰሜን ምሥራቅ ከምትገኘው ኰራዚን ጋር በአንድ ላይ ተረግመው
ከምድረ ገጽ ጠፍተዋል ።ማቴ 11፥20-21
ሠ)ጌርጌሴኖን
የገሊላ የባሕር ወደብ ሆና ከባሕሩ በስተምዕራብ አዋሳኝ ያለች ከተማ
ናት። ጌታችን በዚህች ከተማ አጋንንት ያደሩባቸውን ሰዎች ፈውሷል።
ነዋሪዎቹ ግን አልተቀበሉትም። ይልቁንም ከሀገራችን ውጣልን
ብለውታል። ማቴ 8፥28-34
የተግባር ልምምድ
.ተማሪዎች ሌሎች በገሊላ አውራጃ ከሚገኙ ከተሞች ውስጥ
ቤቴል፣ ጌልጌላ፣ ጊብዓ፣ ገባዖን፣ ፊልጶስ ቂሣርያ እና
ዓይነከርም ስለ ተሰኙ ከተሞች አጠር ያለ ጽሑፍ ይዛችሁ
በመምጣት ለመምህራችሁ እና ለተማሪዎች በክፍል ውስጥ
አንብቡላቸው።
፳፭
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ ክፍል
ሀ) ኢየሩሳሌም
በይሁዳ ኰረብታዎች ላይ ተንጣልላ የምትገኝ በዓለም ላይ የሚኖሩ የብዙ
ሰዎችን ቀልብየ ምትስብ ታሪካዊትና ቅድስት ከተማ ናት። በዕብራይስጥ
“የሩሻላይም” /yerushalayim/ ትባላለች፤ ትርጒሙም የሰላም ከተማ
ማለት ነው። ዐረቦች ግን የተቀደሰች ሲሉ ኤልኩድስ /elkuds/ ይሏታል።
በአራት ተራሮች የተከበበች ከተማ ናት። እነዚህም፦ የሞሪ ተራራ፣ የጽዮን
ተራራ፣ የጋሬብ ተራራ /ኤር31፥39/ እና የቤዜታ ተራራ ናቸው። ከባሕር
ወለል በላይ 750 ሜትር ከፍ ትላለች። ጥንታዊ ስሟ ሳሌም ነበር።
ዘፍ14፥ 18፣ ቀጥሎም ኢያቡስ ተባለች። ኢያ15፥63፣18፥16 ፣ጽዮን
እየተባለችም ተጠርታለች። መዝ136፥1፣ ቅድስቲቱ ከተማ በመባልም
ትታወቅ ነበር። ነህ11፥1 ቅዱስ ዳዊት ኢያቡሳውያንን ድል ካደረጋቸው
በኋላ የይሁዳ ዋና ከተማ አደረጋት። 2ኛሳሙ5፥6-14 ከተማይቱ በተለያዩ
ጦርነቶች ሰባት ጊዜ ፈርሳለች። ጌቴሴማኒ፣ ጐልጐታ እና ጽርሐ ጽዮን
የሚገኙት በኢየሩሳሌም ውስጥ ነው።
ጐልጐታ
የምትገኘው በኢየሩሳሌም በስተ ምሥራቅ ነው። በዕብራይስጥ የራስ
ቅል ማለት ነው። ጥንት አጽመ አዳም የተቀበረባት ኋላም ጌታችን
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለባት ቅድስት ቦታ ናት።
፳፮
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ
ጽርሐ ጽዮን
የምትገኘው በጽዮን ተራራ ነው። በጸሎተ ሐሙስ ጌታችን ለደቀ
መዛሙርቱ ምሥጢረ ቁርባንን የመሠረተባት፣ እግራቸውን ዝቅ ብሎ
ያጠበባት፣ ከትንሣኤውም በኋላ ሁለት ጊዜ የተገለጠባት፣ ቅዱስ ቶማስ
“ጌታዬ አምላኬም” ብሎ የተናገረባት፣ በበዓለ ጰራቅሊጦ ስለ ሐዋርያት
ጸጋ መንፈስ ቅዱስ የተሰጠባት ቅድስት ቦታ ናት። እመቤታችን ለአሥራ
አራት ዓመታት ተቀምጣበታለች።
ለ) ኬብሮን
የቃሉ ትርጒም ኅብረት ማለት ነው። ከሙት ባሕር በስተ ምዕራብ
ከኢየሩሳሌም ደግሞ በስተደቡብ 30ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ
ከተማ ናት። ከባሕር ወለል በላይ 297 ሜትር ከፍታ አላት። የጥንት
ስሟ ቂርያት አርባቅ ትባል ነበር። ዘፍ23፥2፣ዘፍ35፥27 መቃብረ
አበው እና/ ወይም የመድፌላ ዋሻ እየተባለች ትጠራለች። ዘፍ29፥1-
35፣49፥31፣50፥13 ቅዱስ ዳዊት በእስራኤል ላይ ለ40 ዓመታት ሲነግስ
ሰባቱን ዓመታት ኬብሮንን ሠላሳ ሦስቱን ዓመታት ደግሞ ኢየሩሳሌምን
ዋና ከተማው አድርጎ ነግሧል። 2ኛሳሙ2፥1-5
ሐ) ቤተልሔም
የእንጀራ ቤት ማለት ነው። ጥንት በያዕቆብ ዘመን ኤፍራታት ባል
ነበር። ትርጒሙም የፍሬ መያዣ ማለት ነው። ከብታ እየተባለችም
ትጠራለች። ትርጒሙም ቤተ ስብሐት ማለት ነው። ለዚህ ሥፍራ
ሦስቱን ስም የሰጠው ካሌብ ነው። የቅዱስ ዳዊት የትውልድ ሥፍራ
ናት። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተወለደባት ሥፍራ
ናት። ጌታችንም በተወለደ ጊዜ እንስሳት ትንፋሻቸውን የገበሩላት፣ ሰውና
መላእክት በአንድነት ያመሰገኑባት ሰብአ ሰገልን ይመራቸው የነበረው
ኮከብ የቆመባት ቅድስት ከተማ ናት።
፳፯
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ ክፍል
መ) ቢታንያ
ከኢየሩሳሌም በስተምሥራቅ በኩል3 ኪሎ ሜትር ርቃ በደብረዘይት
ተራራ ምሥራቃዊ ቁልቁለት ላይ ያለች ኮረብታማ ከተማ ናት። ዛሬ
የዐረቦች መንደር ስትሆን ኤልአዛርያ /የበለስቤት/ ትባላለች። የአልአዛር
፣የማርታና የማርያም ቤት በዚህች ከተማ ነበር። ዮሐ 11፥1፣17፣12፥1-
2 በስምዖን ቤት ማርያም ጌታን ሽቱ የቀባችው በዚህች ከተማ ነው።
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያረገው በቢታንያ ነው። ሉቃ 24፥50-51
ሠ) ኢያሪኮ
የጨረቃ ከተማ ማለት ሲሆን በጨረቃ የሚያመልኩ ሰዎች ስለነበሩባት
የተሰጣት ስያሜ ነው። በዐርብኛ ደግሞ ሪሃ ትባላለች። ትርጉሙም ሽቱ
ማለት ነው። የቴምር ዛፍ በብዛት ስለሚገኝባት የቴምር አገርም ተብላለች።
እስራኤል ከግብጽ ወጥተው በመጀመሪያ የያዟት ታላቅ ከተማ ናት።
ኢያ6፥1 -21 በኢያሪኮ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
ይዞታ አላት። ከባሕር ጠለል በላይ 250 ሜትር ከፍታ አላት። ዘኬዎስ
ጌታችንን ለማየት የበቃውና ወደቤቱ አስገብቶ ያስተናገደውም በዚህች
ከተማ ነው። ሉቃ19፥1-10 በርጤሜዎስም ከዕውርነት የተፈወሰው
በኢያሪኮ ነው። ማር10፥46-52
ረ) ጌቴ ሴማኒ
በአረማይክ የዘይት መጭመቂያ ማለት ሲሆን በግእዝ ደግሞ አፀደ ሐመል
ትርጒሙም የአትክልት ቦታ በመባል ይታወቃል። ጌታችን በሰቃዮች
እጅ አልፎ ከመሰጠቱ በፊት በዚህች ሥፍራ ጸልዮአል። ማር14፥32-42
ጌታችን የተያዘውም በዚህች ሥፋራ ነው። የእመቤታችን፣ የእናትና
አባቷ (ሐና እና ኢያቄም) የጠባቂዋ የጻድቁ ዮሴፍ መቃብር የሚገኘው
በዚህ ሥፍራ ነው።
ሀ)ቂሣርያ
በሜድትራንያን ባሕር ዳርቻ ያለች ከተማ ስትሆን በብሉይ ኪዳን ታሪክ
የላትም። በሐዲስ ኪዳን ግን በይሁዳ ላይ የሚሾሙ የሮማ ገዥዎች
ይቀመጡባት የነበረች በታላቁ ሄሮድስ ዘመን የተሠራችው ከተማ ናት።
ከፊልጶስ ቂሣርያ ትለያለች። ቅዱስ ጴጥሮስ ቆርኔሌዎስን ከእነ ቤተሰቡ
ያጠመቀው በቂሣርያ ነው። ሐዋ10፥1-48 ቅዱስ ጳውሎስ በቂሣርይ
ለሁለት ዓመታት ታስሯል። ሐዋ24፥27 የሐዋርያው ፊልጶስ ቤትም
በቂሣርያ ነበር። እነ ባስልዮስ ዘቂሣርያን የመሰሉ አባቶች ተገኝተውባታል።
ለ)ሰማርያ
ትርጒሙ የጠባቂ ግንብ ማለት ነው። ከተማዋም አውራጃዋም በዚሁ
ስም ይጠሩታል። ከሰሜን በስተ ሰሜን ምዕራብ ትገኛለች። ከኢየሩሳሌም
በስተ ሰሜን 65 ሜትር ርቀት ላይ ትገኛለች። በሳምርስም ሰማርያ ተብላ
ተጠራች። 1ኛነገ 16፥24 ከተማዋን የመሠረታት ግን ንጉሡ ዘንበሪ ነው።
ዘንበሪ ከሳምር ላይ ተራራውን ሁለት መክሊት በሚመዝን ብር ገዝቶ
ከተማዋን ሠራ። መጥምቁ ዮሐንስ የታሠረውና አንገቱ የተቆረጠው
በሰማርያ ነው።
ለ) ኢትዮጵያ
በመጽሐፍ ቅዱስ ከ40 ጊዜ በላይ ስሟ ተጠቅሷል። በመጽሐፍ ቅዱስ
ኢትዮጵያ የሚለው በሰሜን ግብጽ በምሥራቅ ደግሞ የሕንድ ውቅያኖስ
የሚያዋስኑትን ቦታ ሁሉ የሚያካልል ነው። ሀገሪቱ ብዙ መለያዎች
አሏት። ለአብነትያህል፦
የኢትዮጵያ የስም አመጣጥ ይች ሀገር የደረገችው በጌታ ልደት ጊዜ
በንጉሥ ሰለሞን ጊዜ እና ጌታም የመሰከረላት ሀገር መሆኑ
1. በአምልኮተ እግዚአብሔር፦ ዘኁ12፥1
2. በማዕድን ሀብቷ፦ ኢዮ28፥19
3. በተዋጊነቷ፦ 2ኛነገ19፥9፣ 2ኛዜና19፥9፣19፥8፣ ኤር46፥9፣
ዘጸ18፥1፣2፥21፣ ዘኁ12፥ 1፣ ዘጸ18፥12፣ ዘጸ18፥13-27፣ ኤር38፥7-12፣
ኤር39፥15-18፣ ተረፈ ኤር9፥1፣ኤር13፥23፣ አሞጽ9፥7፣ መዝ71፥9-10፣
መዝ67፥31፣ 1ኛነገ10፥1-13፣ 2ኛዜና9፥1-12፣ ማቴ 12፥42፣....
ከኢየሩሳሌም ውጪ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን
በአራት የተለያዩ ቦታዎች ይዞታዎች አሏት።
፴
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ
ሐ) ግብጽ
በብሉይ ኪዳን በጣዖት አምላኪነት ከሚታወቁት ሀገሮች አንዷ ናት።
ነገሥታቶቹ “ፈርዖን” በሚል ማዕረግ ይጠሩ ነበር ። የእስራኤላውያን
የረሃብ ጊዜ የስደት ሀገር ነበረች። አብርሃም በረሃብ ጊዜ ወደ ግብጽ
ተሰዷል። ዘፍ12፥10፣ ያዕቆብና ቤተሰቦቹ በረሃብ ምክንያት ወደ
ግብጽ ተሰደዋል። ዘፍ 48፥27 ፣ ዮሴፍ ተሸጦ ወደ ግብጽ ሄዷል።
ዘፍ 39፥21 ፣እስራኤላውያን በባርነት ለ430 ዓመታት ኖረውባታል።
ዘፍ15፥13 እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ልጇ ክርስቶስን ይዛ
ከጠባቂዋ ዮሴፍና ከሰሎሜ ጋር ወደ ግብጽ ተሰደዋል። ማቴ2፥14-
15፣ሆሴ11፥1በሐዲስ ኪዳን ቀድመውክርስትናን ከተቀበሉት ሀገሮች
አንዷ ናት።ኢሳ 19፥21፣ሐዋ2፥10
መ) ባቢሎን
የዛሬዋ ኢራቅ ስትሆን በዕብራይስጥ “ባብኤል” ይሏታል። ትርጒሙም
ድብልቅልቅ ማለት ነው። ጥንት ሰናኦር ይባል የነበረው አካባቢ ነው።
ዘፍ11፥9 በጣዖት አምልኮ ከታወቁት ሀገሮች አንዷ ናት። እግዚአብሔር
ተግሣፅ ቢሰጣትም በእንቢተኝነት ጸንታ ቀርታለች። ከክርስቶስ ልደት በፊት
፴፩
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ ክፍል
ሠ) ፋርስ
ከጤግሮስ ወንዝ በስተ ምሥራቅ የነበረች ሀገር ናት። መንግሥቷ ሲስፋፋ
ሱሳ መናገሻ ከተማ ሆነ። የዛሬዋ ኢራን ናት። በንጉሧ አርጤክስ ዘመን
ከኢትዮጵያ እስከ ሕንድ የሚደርስ ግዛት የነበራት ታላቅ ሀገር ነበርች።
ቂሮስ እስራኤላውያንን ወደ ኢየሩሳሌም ተመልሰው ቤተመቅደስ እንዲ
ሠሩ ፈቀደ። ዕዝ 1 የፋርስ ንጉሥ አርጤክስስ አስቴርን አገባ። ስለ አይሁድ
ሕዝብ የለመነችውንም ልመና ተቀበል። (መጽሐፈ አስቴርን ይመልከቱ)
ዕዝራም ብዙ ሰዎችን አስከትሎ ወደ አየሩሳሌም እንዲ መለስና ሕጉን
እንዲያስተምር ፈቀደለት። (ዕዝ7፥8) እንደገናም ተለምኖ የእስራኤልንም
ቅጥር እንዲሠራ ነህምያን ላከው። ነህ2፥1-8 የፋርስ መንግሥት ለረጅም
ዓመታት በገናናነት ቆይቷል። ኋላ ግን ከጌታችን ልደት 330 ዓመታት
አስቀድሞ የተነሣው የግሪኩ ንጉሥ ታላቁ እስክንድር ድል አድርጎታል።
ረ) ግሪክ
ከጥንቷ ታናሽ እስያከ ዛሬዋ ቱርክ /በመካከል ታላቁ ባሕር ቢኖርም/ በስተ
ምዕራብ የምትገኝ ሀገር ናት። በስተ ደቡብ፣ በስተ ምሥራቅና በስተ ምዕራብ
የሜዲትራንያን ባሕር ያዋስኗታል። በብሉይ ኪዳን ነቢዩ ዳንኤል ባየው
ራእይ ውስጥ ተጠቅሳለች። ዳን8፥21 በማርቆስ ወንጌል እንደ ተጠቀሰው
ልጇ ንጋኔን ያሰቃይባት የነበረችው ሴት ግሪካዊ ናት። ማር 7፥26 የግሪክ
ሰዎች ሐዋርያው ፊልጶስን ወደ ጌታ እንዲያቀርባቸው በጠየቁት ጊዜ
ጥያቄያቸውን ተቀብሎ አቅርቧቸዋል። ዮሐ12፥20 ግሪካውያን ቋንቋቸው
፴፪
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ
ሰ) ሶርያ
ከገሊላ ወይም ከእስራኤል በስተ ሰሜን በኩል ያለች ሀገር ናት። ዛሬ
የምትጠራው በጥንቷ ስሟ ነው። የሴም ልጅ የአራም ሀገር ናት። ዘፍ
10፥22-23 በአራምም ቋንቋቸው አረማይክ ተብሏል። ከጥንት ከክርስቶስ
ልደት 2000 ዓመት በፊት ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ዋና ከተማዋ ደማስቆ
ናት ። ሶርያውያን ከክርስቶስ ልደት 850 ዓመት አካባቢ በፊት አዴር
ለሚባል ጣዖት ይሰግዱ ነበር። ብዙ ጊዜ ከእስራኤል ጋር ስትዋጋ ኖራለች።
በንጉሡ በዳዊት ዘመን በጦርነት ተሸንፋለች። 2ኛሳሙ10፥6-19
በሰሎሞን ጊዜ ግን በእስራኤል ላይ አመፀችና ነፃ ወጣች። 1ነገ11፥23-
25 ባኋላ ደግሞ ለበርካታ ጊዜያት በእስራኤል ላይ ጦርነት እያወጀች
በጦርነት ቆይታለች። 2ኛነገ5፥7፣8፥12-13፣ 2ኛዜና16፥10፣20፣28፣27
በሐዲስ ኪዳንም በመጀመሪያው ምዕተ ዓመት ክርስትና ከተሰበከባቸው
ሀገሮች አንዷ ናት። ታላቁ ሐዋርያ ቅዱስ ጳውሎስ ወደ ክርስትና
የተጠራውና የተመለሰው ወደ ደማስቆ ከተማ ሲጓዝ ነው። ሐዋ9፥1-18
ወንጌልን ማስተማር የጀመረውም በደማስቆ ነው። አባናና ፋርፋ የተባሉ
ወንዞች በደማስቆ ዙሪያ ይፈስሳሉ። ደማስቆን በ628ዓ.ም እ.ኤ.አ ግን
ሙስሊሞች በጦርነት ከተማዋን ከያዙ በኋላ የትምህርታቸው ማስፋፊያ
አደረጓት። ነገር ግን ዛሬም በርካታ ተጽዕኖዎችን ተቋቁመው በሶሪያ
የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች ይገኛሉ። አንጾኪያና ሴሌውቅያ
የተባሉት ከተሞች በሶርያ ይገኛሉ። አንጾኪያ ከክርስቶስ ልደት 301
፴፫
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ ክፍል
የመልመጃ ጥያቄዎች
፴፬
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ
ምዕራፍ አምስት
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚገኙ የውሃ አካላት እና የየብስ
ምድር
ዓላማ
ተማሪዎች ይህንን ምዕራፍ ሲያጠናቅቁ
የማስጀመሪያ ጥያቄዎች
፴፭
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ ክፍል
ባሕሮች
በሀገረ እስራኤል ሁለት ታላላቅ ባሕሮች ይገኛሉ። አንደኛው የገሊላ
ባሕር ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ሙት ባሕር ነው።
የገሊላ ባሕር
ዛሬ ጥብርያዶስ እየተባለ የሚጠራው ነው። ዮሐ21፥1 የጌንሳሬጥ ባሕርም
ይባላል። ማቴ4፥18፣ሉቃ5፥1 ጥብርያዶስ እና ጌንሳሬጥ በባሕሩ ወደብ
የሚገኙ ከተሞች ናቸው። ሄሮድስ አንቲጳስ በገሊላ ባሕር ምዕራባዊ ዳርቻ
ከተማ ከመሠረተ በኋላ በጢባርዮስ ቄሣር ስም ጥብርያዶስ ብሎ ሰየማት።
የባሕሩ ርዝመት 4.5 ኪ.ሜ ሲሆን ወርዱ ደግሞ 8ኪ.ሜ ነው። የባሕሩ
ጥልቀት በአማካይ ከ208.5ሜትር እስከ 213ሜትር ከባሕር ጠለል በታች
ነው። የመጨረሻው ጥልቅ ቦታ ግን ከባሕር ጠለል በታች እስከ 254
ሜትር ይጠልቃል። በባሕር ውስጥ 25 የዓሣ ዓይነቶች ስለሚገኙ በዓሣ
ምርት የታወቀ ነው። በዚህ ባሕር ላይ ጌታችን ለማስተማር ብዙ ጊዜ
ተመላልሷል። ብዙ ተአምራትንም አድርጎበታል።
ሙት ባሕር
ጨው ይበዛበታልና “ጨው ባሕር” ተብሏል። ከባሕሩ 3 ኪሎ ውኃ
ውስጥ 1ኪሎ ጨው ይወጣል። “ሙት ባሕር” ይባላል ። የባሕሩ ዙሪያ
በድኝና በቅጥራን (ዝፍት) የተከበበ ስለሆነ ሕይወት ያለው ነገር ፈጽሞ
አይገኝበትም። ከኢየሩሳሌም በስተ ምሥራቅ በ ኢያሪኮ በስተደቡብ የሚገኝ
ባሕር ነው። 88 ኪሎ ሜትር ርዝመት አለው። ከባሕር ወለል በታች
467 ሜትር ከፍታ ላይ ይገኛል። ከጊዜ ወደ ጊዜ ወደ ታች እየወረደ
ነው ይባላል። “ባሕረ ሎጥም” ይባላል። ሰዶምና ገሞራ ከመጥፋታቸው
በፊት የብስ የነበር ቦታ ነበር። ዘፍ19፥1-29 የዮርዳኖስ ወንዝ በየቀኑ
6 ሚሊዮን ቶን ውኃ ለባሕሩ ይገብራል። ሌሎችም ወንዞች ወደ ባሕሩ
፴፯
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ ክፍል
የሚገብሩ አሉ።
ባሕረ ኤርትራ
እስያና አፍሪካን የሚለያይ ባሕር ነው። ርዝመቱ 2175ኪ.ሜ ሲሆን ስፋቱ
ደግሞ 370ኪ.ሜ ነው። በአንዳንድ ቦታዎች የ1830 ሜትር ጥልቀት
አለው። ወደ ባሕሩ የሚገባ ምንም ዓይነት ወንዝ የለም። እስራኤላውያን
ከግብጽ ባርነት ነጻ ሲወጡ በዚህ ባህር ውኃው እንደ ግንብ ቆሞ መሀሉ
ደረቅ መሬት ሆኖ ተሻግረው ሀገራቸው ገብተዋል ።ዘጸ14፥15-31
በባሕረ ኤርትራ እና በሜዲትራን ያን መካከል የስዊዝ ቦይ (Suez Ca-
nal) በመባል የሚታወቅ ሰው ሠራሽ ልሳነ ምድር ይገኛል። ይህ ምግብ
ጽና እስራኤልን በደረቅ መሬት የሚያገናኘው ቦታ ነው።
ወንዞች
ወንዝ ማለት ከአንድ ቦታ ተነሥቶ ወደ ሌላ ስፍራ የሚፈስ (ፈሳሽ) ውኃ
ነው። ሁለት ዓይነት ወንዞች አሉ።ክረምት ከበጋ የማይደርቁ ወንዞች እና
በዝናብ ጊዜ ብቻ የውኃ ፈሳሽ የሚገኝባቸው ናቸው። በመጽሐፍ ቅዱስ
ውስጥ የታወቁ ወንዞች አሉ። እነዚህ ወንዞችም በእስራኤል ምድርና
፴፰
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ
ከለምጽ ነጽቷል።2ኛነገ5፥10-14
ታላቁ የእግዚአብሔር ሰው ኢዮብ በሰውነቱ ላይ ከወጣበት ደዌ የተፈወሰው
በዮርዳኖስ ወንዝ ተጠምቆ ነው።
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ አርአያ ሊሆነን ና የጥምቀትን ሥርዓት
ሊሠራልን ምስጢረ ሥላሴንም ሊገልጥልን የተጠመቀው በዚህ ወንዝ
ነው።ማቴ3፥13-17
ግዮን
በኢትዮጲያ የሚገኝ ወንዝ ነው። የጣናን ሐይቅ ከሁለት ከፍሎ ይጓዛል።
በተለያዩ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች የዓባይ ወንዝ ተብሎ ተጠቅሷል።
ኢሳ19፥7-8፣23፥3 በበረሃማው የግብጽ ምድር የዓባይ ወንዝ የሚያልፍበት
ቦታ ሁሉ ለምለም ነው። ሱዳንና ግብጽን አጠጥቶ ወደ ሜዲትራንያን
ባሕር ይገባል። ከመነሻው እስከ መድረሻውያለው ርቀት 6470 ኪሎ
ሜትር ያህል ነው። የሙሴ ወላጆች ከፈርዖን ትእዛዝ የተነሣ ሙሴ
እንዳይሞትባቸው ከዓባይ ወንዝ ዳር ሸሽገውታል።ዘጸ2፥1-10 ፈርዖን
እስራኤልን አልለቅም ብሎ ልቡን ባጸናበት ወቅት ከእግዚአብሔር
በታዘዘው መሠረት በግብጽ ምድር ብቻ የዓባይ ውኃ ወደ ደምነት
ተቀየረ። ዘጸ7፥20-21
ተራሮች
ተራራው ከሜዳውና ከደልዳላው መሬት ከፍ ያለ የመሬት ክፍል ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስም ብዙ ተራሮች ተጠቅሰው ይገኛሉ።
1. ደብረ ሲና
ደብር ማለት ተራራ ማለት ነው። ደብረ ሲና ማለት የሲና ተራራ ማለት
ነው። ኮሬብ እየተባለም ይጠራል። ዘጸ3፥1 ፣ዘዳ4፥ 9-10 የእግዚአብሔር
ተራራም ይባላል። ዘጸ3፥1 ፣1ኛነገ19 ፥8 ከግብጽ በስተ ምሥራቅ
ከእስራኤል ደግሞ በስተ ደቡብ ይገኛል። እግዚአብሔር ለሊቀ ነቢያት
፵
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ
2.ሞሪያ
ከኢየሩሳሌም ከተማ በስተ ምሥራቅ ይገኛል። አብርሃም በስተርጅና
ያገኘውን ልጁን ሊሠዋበት የሄደበት ተራራ ነው። ዘፍ22፥2 ጠቢቡ
ሰሎሞንም በዚህ ተራራ ቤተ መቅደሱን እንደሠራ መጽሐፍ ቅዱስ
ይናገራል። 2ኛዜና3፥1
3. ደብረ ታቦር
ከገሊላ ባሕር በስተ ደቡብ ምዕራብ አቅጣጫ 10 ኪሎ ሜትር ርቀት
ላይ ከናዝሬት ደግሞ በስተ ምሥራቅ ከዮርዳኖስ ወንዝ በስተ ምዕራብ
የሚገኝ ተራራ ነው። ከባሕር ጠለል በላይ 572 ሜትር ከፍታ አለው።
የዛብሎንን ፣ የይሳኮርን ና የንፍታሌምን ርስት ያዋስናል ።እንግልጣሮች
(እንግሊዘኛ ተናጋሪዎች) Transfiguration Mount ይሉታል። ጌታችን
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ መለኮቱን እንደ ገለጠበት
ሲያጠይቁ ነው። ዐረቦች ደግሞ ጀበልቶር (DjebolTor=Mountainoft-
hebull) ይሉታል። በዚህ ተራራ ባርቅና ዲቦራ የእስራኤል ጠላት ሆኖ
የተነሣውን ሲሣራን ድል አድርገውበታል። መሳ4፥4-2 4 በልምላሜ
የተሞላ ተራራ መሆኑ ይነገርለታል። በሐዲስ ኪዳን ስሙ አይጠቀስ
እንጂ ጌታችን ብርሃነ መለኮቱን የገለጠበት ረጅም ተራራ የተባለው
እርሱ ነው። ማቴ17፥1- 9፣ መዝ88፥ 12 በዚህ ምክንያት ሊቀ ሐዋርያት
፵፩
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ ክፍል
4.ደብረ ዘይት
የዘይት ታራራ ማለት ሲሆን በወይራ ዛፍ የተሸፈነ በመሆኑ የተሰጠው
ስያሜ ነው። 800 ሜትር ያህል ከባሕር ጠለል በላይ ከፍታ አለው።
ከኢየሩሳሌም በስተ ምሥራቅ በቅርብ የሚገኝ ቦታ ነው። ጌታችን ቀን
ቀን ኢየሩሳሌም ከተማ ሲያስተምር ውሎ ወደ ማታ በደብረ ዘይት ተራራ
በኩል ወደ አልዓዛር ቤት ቢታንያ ለማደር ይሄድ ነበር። ማር11፥ 19፣
ማቴ21፥17 ከተራራው ግርጌም ቤተፋጌና ቢታንያ የሚባሉ መንደሮች
ይገኛሉ። ከፍታ ያለው ተራራ በመሆኑ ከጫፉ ላይ ሆኖ ኢየሩሳሌምን፣
፵፪
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ
፵፫
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ ክፍል
ምንጮች
ትናንሽ የሆኑና ለመጠጥነት የሚያገለግሉ ውኃማ ቦታዎች ምንጮች
ይባላሉ። የአጋር ምንጭ የሣራ አገልጋይ የነበረችው አጋር ከአብርሃም
እንዳረገዘች ባየች ጊዜ ሣራን ናቀቻት። በዚህ የተነሣ ከአብርሃም ቤት
ተባርራ ወጣች ፤ በምድረ በዳ ውኃ ጥም ጸንቶባት በተቸገረችና ባለቀሰች
ጊዜ መልአከ እግዚአብሔር ወደ ሱር በምትወስደው መንገድ አጠገብ
ባለች ምንጭ ጎን ተገለጠላት። የዚያችም ምንጭ ስም ብኤርለሃይሮኢ
ተባለ። ዘፍ 16፥1-14
የያዕቆብ ምንጭ
ሲካር በምትባለው የሰማርያ ከተማ ትገኛለች። ሲካርም ከሴኬም በስተ
ደቡብ በአንድ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ ከተማ ነች። የዕቆብ
ከአጎቱ ሀገር ከሶርያ ሲመለስ በከንዓን ምድር ወዳለችው ወደ ሴኬም
ከተማ መጣ። ድንኳኑን ተክሎበት የነበረውን የእርሻ ማሳ ከሴኬም አባት
ከኤሞር ልጆች በመቶ በጎች ገዛ። በዚያም ያዕቆብ ለራሱ ያስቆፈራት
ምንጭ ነበረች። ያዕቆብ ና ቤተሰቦቹ ሁሉ ከዚያች ምንጭ ሲጠጡ ኑረዋል
። ዘፍ 33፥18-20 ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይሁዳን
ትቶ ወደ ገሊላ በሔደበት ወቅት በሰማርያ ወደ ምትገኘው ወደ ሲካር
መጣ የሥጋን ገንዘብ ባሕርይው አድርጓልና ከመንገዱ ርዝመት፣ ከዋዕዩ
ብርታት የተነሣ ደከመው፤ ተጠማም በሲካር ወደምትገኘው የያዕቆብ
ምንጭ ቀርቦ ከአንዲት ሳምራዊት ሴት ውኃ ለመነ። እርሱ የሕይወት
ውኃ እንዳለውና እርሱ ከሚሰጠው የሕይወት ውኃ የሚጠጣ ሁሉ እንደ
ማይጠማ አስተማራት። የተሠወረ ሕይወቷን ገልጦ በማስተማሩም
ሳምራዊቷ ሴት በእርሱ ከማመኗም በላይ የከተማውን ሰው በሙሉ
ጠርታ ከእርሱ ተምረው አምነውበታል። ይህ ሁሉ የተከናወነው በያዕቆብ
ምንጭ አጠገብ ነው። ምንጩ 32 ሜትር ያህል ጥልቀት አለው።
ዮሐ4፥1-32
፵፬
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ
ሜዳዎች
ሜዳዎች በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በብዛት ተጠቅሰው አይገኙም።
የሰናዖር ሜዳ
በባቢሎን ዙሪያ ያለ ሰፊ ሜዳ ሲሆን ከኖኅ ዘመን የጥፋት ውኃ በኃላ
የተነሡ ሰዎች ግን በመገንባት የጀመሩት በዚህ ሜዳ ነው። የሰው ልጆች
ቋንቋ የተለያየበት (የተደበላለቀበት) ስለሆነ ባቢሎን ተብሏል። ባቢሎን
ማለትም ድብልቅልቅ ማለት ነው። ዘፍ11፥1-9
የአርማጌዶን ሜዳ
ከቀር ሜሎስ ተራራዎች በስተ ደቡብ ከደብረ ታቦር ተራራዎች ፊት
ለፊት የሚገኝ ሜዳ ነው። ቀድሞ በቀርሜሎስ ተራራዎች ከሰሜን ወደ
ደቡብ ጋዛንና ደማስቆን የሚያገናኘውን መንገድ ለመጠበቅ የተመሸገ
ከተማ ነው። ይሁን እንጂ በዚህ ሜዳ ሰዎች አይኖሩበትም። ዲቦራና
ሲሣራን ድል ያደረገችው፣ ፈርዖን ኒካውም ኢዮስያስን የገደለው በዚሁ
፵፭
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ ክፍል
ሸለቆዎች
ሸለቆ ማለት ጎድጓዳ የሆነና የሚሞቅ፣ ሐሩር የበዛበት ቦታ ማለት ነው።
የሄኖም ሸለቆ
ስያሜውን ሄኖም ከተባለው ሰው እንዳገኘው ይነገርለታል። ከቄድሮስ
ወንዝ በታች ከጥንታዊው የኢየሩሳሌም ከተማ በምዕራብና በደቡብ በኩል
ይገኛል። ይሁዳና ብንያም በዚህ ሸለቆ ይዋሰናሉ። ኢያ15፥8 ከኢዮስያስ
በፊት የነበሩ ነገሥታት በሄኖም ሸለቆ የጣዖት መስገጃዎችን ሠርተው
ሴቶችና ወንዶች ልጆቻቸውን ሳይቀር ይሠዉቡት ነበር። ኤር19፥1-9 ፣
2ኛ ዜና28፥1-4፣ 2ኛዜና33፥1 7 ፣ 2ኛነገ16፥3 ይሁን እንጂ ኢዮስያስ
በነገሠ ጊዜ እንደ አባቱ እንደ ዳዊት በእግዚአብሔር መንገድ በመሔዱ
በሄኖም የነበሩ የማምለኪያ አፀዶችንና መሠዊያዎችን አጠፋቸው።
2ኛነገ23፥10-14
የኢዮሳፍጥ ሸለቆ
ኢዮሳፍጥ ከ870 እስከ 845 ከክርስቶስ ልደት በፊት በይሁዳ የነገሠ
አራተኛው ንጉሥ ነው። እግዚአብሔር ጠላቶቹን ያሸንፍ ዘንድ ኃይል
ስለሰጠውና ጠላቶቹንም ድል ስላደረጋቸው፣ ምርኮአቸውንም ከወሰደ
በኋላ በዚህ ሸለቆ ፈጣሪውንም ስላመሰገነበት የኢዮሳፍጥ ሸለቆ ተባለ።
የኢዮሳፍጥ ሸለቆ በኢየሩሌምና በደብረ ዘይት መከከል የቄድሮን ወንዝ
ይፈስበታል። በአሁኑ ጊዜ ብዙ የአይሁድና የእስላም መቃብር ይገኝበታል።
ነቢዩ ኢዩኤል በኢዮሳፍጥ ሸለቆ በሕዝብና በአሕዛብ ላይ እግዚአብሔር
የሚፈርድባቸው መሆኑን ተናግሯል። ኢዩ3፥2-12 በኢየሩሳሌም ነግሠው
፵፮
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ
ዋሻዎች
ዋሻ ማለት በተፈጥሮም ሆነ በሰው ኃይል የተቦረቦረ፣ የተፈለፈለ
መሬት ቋጥኝ ነው። ብዙውን ጊዜ ዋሻ መናንያን ገብተው ይጸልዩበታል።
ስደተኞች ይጠጉበታል። አራዊትም ይኖሩበታል። በመጽሐፍ ቅዱስም
የተለያዩ ዋሻዎች ተመዝግበዋል።
የኤልያስ ዋሻ
በይሁዳ በረሃ ይገኛል። በዐረብኛ ዋዲከልት ይባላል። ነቢዩ ኤልያስ
ለእግዚአብሔር ቀንቶ አምልኮቱን የዘነጉትን አክዓብንና ኤልዛቤልን
ከነሠራዊታቸው ለመቅጣት ሲል ሰማይ ዝናብ ለዘር ፣ ጠል ለመከር
እንዳትሰጥ ለጎመ። በዚህ የተነሣ አክዓብ እንዳይገድለውና በረሃብም
እንዳይጎዳ ልዑል እግዚአብሔር “ከዚህ ተነሥተህ ወደ ምሥራቅ ሒድ
፣ በዮርዳኖስም ትይዩ ባለው በኮራት ፈፋ ውስጥ ተሸሸገ። ከወንዙም
ትጠጣለህ ቁራዎችም በዚያ ይመግቡህ ዘንድ አዝዣለሁ” አለው።
እንደተናገረውም ቁራዎች በጠዋትና በማታ ኅብስትና ሥጋ እያመጡ
ኤልያስን ይመግቡት ነበር። ያቺ ኤልያስ የተሸሸገበት ፈፋ (ዋሻ) የኤልያስ
ዋሻ ትባላለች። 1ኛ ነገ 17፥1-7
፵፯
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ ክፍል
የመልመጃ ጥያቄዎች
፵፰
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ
ምዕራፍ ስድስት
የሥራ መስክ እና መገበያያ በመጽሐፍ ቅዱስ
ዓላማ
ተማሪዎች ይህንን ምዕራፍ ሲያጠናቅቁ
የማስጀመሪያ ጥያቄዎች
፵፱
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ ክፍል
የሥራ መስክ
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተለያዩ የሥራ መስኮች ተጠቅሰው ይገኛሉ።
አዳም “በሕይወት ዘመንህ ሁሉ በድካም ከእርሷ ትበላለህ ”ከተባለበት ጊዜ
ጀምሮ የሰው ልጅ ኑሮውን ለማሸነፍ በተለያዩ የሥራ መስክ እየተሰለፈ
ኖሯል። ዘፍ 3፥17 የሰው ልጅ እንደተፈጠረ ሥራ እንዲሠራ ተደርጓል።
ዘፍ 2፥15 ከአስርቱ ትእዛዛት መካከልም አንዱ ሥራ መሥራት እንደሚገባ
የሚናገር ነው። ዘጸ 20፥9
፶፪
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ
የተግባር ልምምድ
ተማሪዎች በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ጎላ ብሎ ከተነገረላቸው
/ከተጻፈላቸው/ የሥራ መስኮች መካከል አንጥረኝነት እና
ቀጥቃጭነት፣ ልብስ ሥራ፣ ሸክላ ሥራ፣ ሽቱ ቀማሚነት፣
ቁርበት ፋቂ እና ቀንድ አንጣጭ ይገኛሉ። ስለ እነዚህ
የሥራ መስኮች በመጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈውን ጽፋችሁ
በመምጣት ለተማሪዎችና ለመምህሩ ያንብቡላቸው።
፶፮
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ
መስፈሪያ
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተጠቀሱ የርዝመት /Length/ ፣ የክብደት
/Weight/ እና ይዘት /Volume/ መስፈሪያዎች /MeasuringUnits/
አሉ። እነዚህም ከጥንት ጀምሮ የነበሩ ናቸው። “በፍርድ በመለካትም ፣
በመመዘንም ፣ በመስፈርም አመፃ አታድርጉ።” ዘሌ 19፥36-37
ገንዘብ
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ገንዘብ የሚለው ቃል ሁለት ዓይነት አገባብ
አለው። አንደኛው ለመገበያያ ይሆን ዘንድ ከተለያዩ ዓይነት ማዕድናት
/ከወርቅ፣ ከብር፣ ከመዳብ እና ከነሐስ/ በተለያየ መጠን የሚሠራውን
ሲያመለክት፣ ሁለተኛው ደግሞ በአጠቃላይ ሀብትን ወይም ንብረትን
ያመለክታል። ሆኖም የመጀመሪያውን የገንዘብ ዓይነት በተመለከተ
፶፱
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ ክፍል
የግሪክ ገንዘቦች
1. መክሊት፦ የወርቅ መሐለቅ ነው። በእስራኤል ዘንድ የታወቀ የመገበያያ
ገንዘብ ነው። ጌታችንም እየመሰለ በተናገረባቸው አንዳንድ ቦታዎች ላይ
ተጠቅሞበታል። ማቴ18፥24፣ ማቴ25፥14-15 አንድ መክሊት 2100
የኢትዮጲያ ብር ያህል ይመነዘራል።
2. ምናን፦ 35 የኢትዮጲያ ብር ያህል ይመነዘራል። ጌታችን በማቴዎስ
ወንጌል ላይ በመክሊት መስሎ ያስተማረው በሉቃስ ወንጌል ደግሞ በምናን
ተተክቶ መነገሩ ሁለቱም የገንዘብ መጠን መናገሪያዎች በመሆቸው
ነው። ሉቃ 19፥13-27
3. ድራክማ፦ ድሪም እየተባለ በአማርኛው መጽሐፍ ቅዱስ የተጠቀሰው
ገንዘብ ነው። ዲናር ተብሎ የሚጠራው የሮማውያንን ገንዘብ ያህል ዋጋ
አለው። ዕድሜው ከሃያ ዓመት በላይ የሆነው አይሁዳዊ ሁሉ በየዓመቱ
ለቤተ መቅደስ ሁለት ሁለት ድሪም /ድራክማ/ ግብር ይከፍል ነበር።
ሉቃ15፥8
፷
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ
የሮም ገንዘቦች
1.ዲናር፦ የብር መሐለቅ ነው። አንድ ዲናር የአንድ ቀን ሠራተኛ ዋጋ
ነበር። ማቴ 20፥9-10 በጌታችን መዋዕለ ስብከት በዲናሩም ላይ የሮማ
ነገሥታቶች /ቄሣሮች/ ምስል ይታተምበት ነበር። ማር12፥15-17 ፣ ሉቃ
10፥35
2. እስታቴር፦ አንድ እስታቴር ዐራት ዲናር ያህል ነው።ማቴ17፥
3. አሣርዮን፦ የቄሣር መልክ ያለበት የመዳብ ገንዘብ ነው። በአማርኛው
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አምስት ሳንቲም የተባለው አንድ አሣርዮን ነው።
“ሁለት ድንቢጦች በአምስት ሳንቲም ይሸጡ የለምን? ” ማቴ1 0፥29
4. ካድራንስ፦ የአሣርዮን ሩብ ነው። ይህም በአማርኛው መጽሐፍ ቅዱስ
አንድ ሳንቲም የተባለው ነው። ማር 12፥ 42
5. ሌፕቶን፦ እስካሁን ከተጠቀሱት ሁሉ የሚያንስ ሲሆን የኳድራንስ
፷፩
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ ክፍል
የጦር መሣሪያ
የሰው ልጅ እርስ በእርሱም ሆነ ከአራዊት ጋር መታገል ከጀመረበት ጊዜ
አንስቶ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎችን ሲገለገልባቸው ኖሯል ። ከድንጋይ
ጀምሮ እስከ አጥንት፣ እሳትና የተለያዩ ብረታ ብረቶች ሁሉ በጥንት
ጊዜ እንደ ጦር መሳሪያ አገልግለዋል። የመጀመሪያው ሟች አቤልም
የሞተው በድንጋይ ነው። ዘፍ4፥8 ሶምሶም ፍልስጤማው ያንን ሸነፋቸው
በአንድ የአህያ መንጋጋ ነው። መሳ15፥15 ከዚህ ቀጥሎ በመጽሐፍ ቅዱስ
የተጠቀሱትን አንዳንድ የጦር መሳሪያዎች እንመለከታለን።
ወንጭፍ፦ በዘመነ መሳፍንት እንደ ጦር መሳሪያ ተጠቅመውበታል።
መሳ20፥16 ቅዱስ ዳዊትም ጎልያድን አሸንፎበታል። 1ኛሳሙ17፥40-49፣
1ኛዜና12፥2
ጦር ፦ ጎልያድ ዳዊትን ለመግደል ጦር ይዞ ወጥቶ ነበር። ከጦሩም ጋር
አብሮ ጭሬ ይዞ ነበር። 1ኛሳሙ 17፥6-7 ጭሬ ቀጭንና አጭር ጫፉ
ጠባብ የሆነ የጦር ዓይነት ነው። ሳዖል ባይሳካለትም ዳዊትን ለመግደል
ጦር ወርውሯል። 1ኛሳሙ18፥ 11 ሌንጊኖስ የተባለው የሮማውያን
፷፪
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ
ቁር
ቁር፦ በራስ ላይ የሚጠለቅ ከናስ፣ ከብረትና ከሌላም ቁሳቁስ ሊሠራ
የሚችል የጦር መከላከያ ነው። “በራሱም ላይ የጦር ቁር ደፋለት።
1ኛሳሙ17፥38፣ ቁር የመዳኛ ምሳሌ ነው።“ የመዳንንም ራስ ቁር
የመንፈስንም ሰይፍ ያዙ” ኤፌ6፥17
ቀስትና ፍላፃ፦
ፍላፃ ቀስት ከእንጨት ወይም ከሌሎች ብረታ ብረት
የሚሠራ እንደ ደጋን ያለ ቅርጽ ያለው ሲሆን ከአንዱ ጫፍ እስከ
ሌላው ጫፍ ከጅማት ወይም ከጭራ የተገመደና የተወጠረ ክር ያለው
መሣሪያ ነው። ፍላፃ ደግሞ በቀስቱ አማካኝነት እንዲፈናጠር ሆኖ ዘንጉ
ብረት ወይም እንጨት የሆነ ጫፉ ግን ሹል ብረት ያለው መሣሪያ
ነው።ዘፍ21፥20፣1ኛዜና5፥18፣1ኛዜና12፥2
፷፬
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ
፷፭
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ ክፍል
፷፮
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ
፷፯
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ ክፍል
፷፰
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ
፷፱
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ቅዱሳት መጻሕፍት ጥናት አራተኛ ክፍል
፸
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
የሰንበት ት/ቤት አመራር እና መምህራን
እንዲሁም ተማሪዎችና ወላጆች በመጽሐፉ ላይ
ያላችሁን ማንኛውም አስተያየት እና ግብዓት
በሚከተለው አድራሻ ላኩልን
office@eotc-gssu.org
https://t.me/GSSUCurricu-
lum_bot