Professional Documents
Culture Documents
መጽሐፍ ቅዱስ የሚለው ሐረግ መጽሐፍ እና ቅዱስ ከሚሉት ሁለት ጥምር ቃላት የተገኘ ሲሆን ‹‹መጽሐፍ››
የሚለው ቃል ተጠቃሎ በአንድ ጥራዝ ሥር የተሰበሰበ ጽሑፍን ሲገልጥ ‹‹ቅዱስ›› የሚለውን ቃል ደግሞ በዕብራይስጥ
‹‹ክዳሽ››፣ በጽርዕ ‹‹ሐጊዮስ››፣ በሱርስት ‹‹ካዲሽ››፣ በግእዝ እና በዐረብኛ ቅዱስ ይለዋል፤ ትርጉሙም የከበረ፣ የተለየ፣ የነጻ፣
የጸና ማለት ነው፡፡ ስለዚህም መጽሐፍ ቅዱስ ማለት የተቀደሰ፣ የተባረከ፣ የተለየ፣ የተከበረ ጥራዝ (ተጠቃሎ የተጻፈ) ማለት
ነው፡፡ ይህን በግእዝ እና በአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ እያልን የምንጠራውን በግሪክ /ቢብሎስ/ አጊያ ግራፊ ሲለው ይገኛል፡፡
ቢብሎስ የተባለው የግሪክ ቃል ///// ከተባለው ሀገር እንደመጣ ይነገራል፡፡ ይህም ከፊንቂያ ወደቦች ውስጥ አንደኛ የነበረና
ከቤይሩት 25 ማይል ያህል ርቆ የሚገኝ ቦታ ነው፡፡ ይህ ቦታ ለመጻፊያ ያገለግል ዘንድ ፓፒረስ /ደንገል/ የተባለውን ተክል
እንደ ወረቀት አድርገው ይሠሩበት የነበረ ቦታ ነው፡፡ ቢብሎስ የሚለውንም ስያሜ ያወጡለት ግሪካውያን እንደሆኑ
ይነገራል፡፡ ቢብሎስ በተባለው ቃል በመጀመሪያ ጊዜ ማንኛውም መጽሐፍ ይጠራበት ነበር፤ እየቆየ ግን ይህ ስያሜ
ለማንኛውም መጽሐፍ መሰጠቱ ቀርቶ ለቅዱስ መጽሐፍ ብቻ ተሰጠ፡፡
በላቲን ቋንቋ መጽሐፍ ቅዱስ ስክሪፕቸር /scripture/ ተብሎ የሚጠራ ሲሆን በእንግሊዘኛው ደግሞ ቀድሞ
ከተሰጠው የግሪክ አጠራር በመነሳት ባይብል /bible/ ተብሎ ይጠራል፡፡ በእኛ ቤተክርስቲያን ግን በፍትሐ ነገሥቱ
‹‹መጻሕፍት አምላካውያን›› ብሎ ሲጠራው እናገኘዋለን፡፡ እንዲሁም (በማቴ 22፡29፤ 22፡42፤ ሉቃ 24፡32፤ ሐዋ 18፡24)
ላይ ‹‹መጻሕፍት›› ተብሎ በብዙ ቊጥር ሲጠቀስ፤ በነጠላ ቊጥር ደግሞ ‹‹መጽሐፍ›› ተብሎ (በሐዋ 8፡32፤ ገላ 3፡22) ላይ
ተጠቅሷል፡፡ ‹‹ቅዱሳት መጻሕፍት›› እየተባለም ተነግሯል፡፡ (ሮሜ 1፡2፤ 2 ጢሞ 3፡15)፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር
የልቡን አሳብ የገለጠበት የምስጢር መዝገብ(አሞ 3፡7)፤ የእግዚአብሔርን አሳብ የያዘ፣ ፍጽም እውነትነት ያለው ቅዱስ
ቃል፣ የማይሻር፣ የማይሻሻል፣ የማይገፋ ጽኑዕ ግንብ ነው (ኢሳ 40፡8፤ ማቴ 5፡17-24፣ዮሐ 10፡35)፡፡
1. አስገኝው እግዚአብሔር ቅዱስ ስለሆነ፡- ከእግዚአብሔር የሆነው ሁሉ ቅዱስ ነው፡፡ እርሱ ለአገልግሎቱ
አክብሮ የለያቸው ሰዎች (ዘጸ 28፡40-41) እንዲሁም ለይቶ ያከበራት ዕለት ዕለተ ሰንበት (ራእ 1፡10) ቅድስት
ናት፡፡ እንደዚሁም ሁሉ መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃል በመሆኑ ቅዱስ ነው፡፡ አስገኝው እግዚአብሔር
ስለመሆኑም ኢሳይያስ ‹‹በእግዚአብሔር መጽሐፍ ፈልጉ አንብቡም›› በማለት ነግሮናል፡፡ (ኢሳ 34፡16)
2. በመንፈሰ እግዚአብሔር የተነሣሱ ቅዱሳን ሰዎች የጻፉት በመሆኑ፡- ከመጻሕፍት ሁሉ የተለየውን መጽሐፍ
ከአማልክት ሁሉ ልዩ በሆነው አምላክ አማካኝነት ከሰዎች ሁሉ የተለዩ ሰዎች ሊጽፉት የተገባ ሆነ፡፡ ስለዚህም
እግዚአብሔር አምላክ አስቀድሞ ፊት ለፊት እየተገለጠ ያናግራቸው የነበሩትን ቅዱሳን እንዲሁም ነቢያት
ለሕዝቡ በቃል ሲያስተምሩ ዝንጉዓን ቢሆኑባቸው አምላካችን ለሰው ልጆች ካለው ፍቅር የተነሣ ቃሉን
በንግግር ብቻ ሳይሆን በጽሑፍ እንዲያሰቀምጡ አነሣሳቸው፡፡ ለዚህም ነው ‹‹እግዚአብሔርም ሙሴን
የአማሌቅን ዝክር ከሰማይ በታች ጨርሼ እደመስሳለውና ይህን ለመታሰቢያ በመጽሐፍ ጻፈው፤ በኢያሱም
ጆሮ ተናገር አለው፡፡›› (ዘጸ 17፡14) ተብሎ የተጻፈው፡፡ (2 ኛ ጴጥ 1፡20-21፤ ራእ 1፡11)
3. ሰውን ወደ ቅድስና የሚያደርስ ስለሆነ ቅዱስ ተብሏል፡- መጻሕፍትን አምኖ መቀበል የእግዚአብሔርን
ድምፅ መስማት ነው፡፡ ‹‹የዚህን መጽሐፍ ቃል ትንቢት የሚጠብቅ ብጹዕ ነው፡፡›› (ራእ 22፡7) የመጽሐፍ
ቅዱስ ዋነኛ ዓላማ በእግዚአብሔር ወደሚኖር ፍጹም ሕይወት መጥራት ነው፡፡ (2 ኛጢሞ 3፡7)
4. ክብረ ቅዱሳንን የሚዘክር ስለሆነ ቅዱስ ተብሏል፡- መጽሐፍ ቅዱስ ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል
ማርያም፣ ስለ ቅዱሳን መላእከት፣ ስለ ቅዱሳን ጻድቃንና ሰማዕታት፣ ስለ ቤተ መቅደስ፣ ስለ ንዋያተ ቅድሳት፣
ስለ ተቀደሱ ዕለታት ወዘተ . . . ስለሚናገር ቅዱስ ተብሏል፡፡
5. የሚያነቡትን፣ የሚሰሙትን፣ የሚያምኑበትንና የተሳለሙትን ሁሉ የሚቀድስ የሚባርክ ስለሆነ ቅዱስ
ተብሏል፡፡
ይህንን ጥያቄ በ 4 ኛው መ/ክ/ዘ ከተነሡት ቅዱሳን ሊቃውንት አባቶች አንዱ የሆነው የአንጾኪያው ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ
ዮሐንስ አፈወርቅ እንዲህ በማለት ይመልስናል፡፡
‹‹በእርግጥም እኛ የተጻፉ ቃላት እርዳታ የሚያሻን ሁነን አልተፈጠርንም፤ ይልቁንም ለነፍሳችን በተጻፉት
መጻሕፍት
ምትክ የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ፣ በብዕር ቀለም በወረቀት ላይ በሰፈሩት ቃላት ፈንታም በልባችን
ሰሌዳ ላይ መለኮታዊ /መንፈሳዊ/ ጽሑፍ ሊጻፍ በተገባ ነበር፤ ነገር ግን ይህንን ታላቅ ጸጋ ፈጽመን
ከእኛ ስላራቀነው ነው፤ ሁለተኛውንና በአንጻራዊነት የተሻለው አማራጭ እንድንይዝ ያስገደደን፡፡
የቀድሞው /በልባችን የነበረው ጽሑፍ/ የተሻለ እንደነበር እግዚአብሔር በቃልም በተግባርም
ገልጦልናል፡፡ እግዚአብሔር ኅሊናቸው ንጹሕ ሆኖ ስላገኘው ለኖኅ፣ ለአብርሃምና ለልጆቹ፣ ለኢዮብ
እንዲሁም ለሙሴ የተናገረው በተጻፈ ጽሑፍ ሳይሆን እርሱ ራሱ ፊት ለፊት ቀርቦ ነበር፤ ነገር ግን
ዕብራውያን በሙሉ በኃጢአት በወደቁ ጊዜና ከዚያም በኋላ እግዚአብሔር ሕግጋቱን በጽሑፍ፣
በጽላት በተግሣፅ መልክ ሰጠ፡፡ ይህ በብሉይ ኪዳን ብቻም ሳይሆን በሐዲስ ኪዳንም የተደረገ ነው፤
ምክንያቱም ጌታ የትኛውም ሐዋርያ የተጻፈ ነገር አልሰጠውም፤ ነገር ግን በተጻፉ ቃላት ፈንታ
የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ እንደሚሰጣቸው ቃል ገባላቸው፡፡ (ዮሐ 14፣ ኤር 31፣ 2 ኛ ቆሮ 3) ዳሩ ግን በጊዜ
ሒደት አንዳንዶች በሃይማኖት ሕጸጽ ሌሎች ደግሞ በምግባር ጉድለት ስላመጡ ቅዱሱን ቃል
ለማስታወስ ይቻል ዘንድ በተጻፈ ቃላት መቀመጡ ግድ ሆነ፡፡››
ዳግመኛም ግብጻዊው ካህን ታድሮስ ማላቲ ስለ መጽሐፍ ቅዱስ መጻፍ ምክንያት ሲገልጡ
‹‹እግዚአብሔር ለሰው ልጅ ካለው ፍቅርና ለሕይወታችንም ከሚሰጠው ዋጋ የተነሣ በዘመናት ሁሉ በእኛው
(ሰዋዊ ቋንቋና አቅም) ሲያናግረን ቆይቷል፡፡ ቅዱስ መንፈሱ ነቢያትን በልዩ ቃላት እየመራቸው እኛን ወደ
እውነቱ እንዲወስዱን፤ ከተሳሳተ መንገድ እንዲጠብቁን፣ የእርሱን ሕያው ቃል በሰው ልጆች ባሕል
ሊመዘግቡና እኛ እንረዳው ዘንድ ጽፈዋል፡፡›› ብለዋል፡፡
ስለዚህም መጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈበት ዓላማ፡-
የመጀመሪያውና ዋነኛው ዓላማ ፈጣሬ ዓለማት እግዚአብሔር እንደሆነና በአካል፣ በአካል ስም እና በአካል
ግብር ሦስት፤ በአገዛዝ፣ በሥልጣን፣ በመሳሰሉት መለኮታዊ ተግባራት አንድ እንደሆነ ሊገልጥልን ነው፡፡
(ዘፍ 1፡26፣ ማቴ 28፡19፣ ዮሐ 1፡1-4)
እግዚአብሔር ብቻ አምላክ እንደሆነ አምነን እንድንቀበል እና በጠባብ ደረት፣ በአጭር ቁመት የተገለጠው
ኢየሱስ ክርስቶስ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ፣ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ
የተወለደው የዘላለምን ሕይወት እንድናገኝ መሆኑ እንድናውቅ ነው፡፡ (ዮሐ 20፡30፤ ዮሐ 5፡13) መጽሐፍ
ቅዱስ በዋነኛነት ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ያስተዋውቀናል፡፡ ብሉይ ኪዳንም ሆነ
ሐዲስ ኪዳን በበደላችን ምክንያት ከመጣው የባሕርያችን መጎስቆል ያዳነን፣ በመስቀል ላይ በፈሰሰው
ደሙ ያነጻንና የቀደሰንን ኢየሱስ ክርስቶስን በሚገባ ይገልጻሉ፡፡
የመጽሐፍ ቅዱስ ሌላው ዋነኛ ዓላማ የእግዚአብሔርን የፍቅር ሥራ፣ አሳቡንና ፈቃዱን ለሰው
ማስታወቅ ነው፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ የፍቅር መልእክት ስለሆነ ሰዎች ሁሉ ተፋቅረው፣ እግዚአብሔርንም በማፍቀር ለቃሉም
በመታዘዝ፣ የክብር ትንሣኤና ዘላለማዊ ሕይወትን በተስፋ እንዲጠባበቁ ለመግለጽ፣ ለማነቃቃት
እንዲሁም እግዚአብሔር እኛን እንደወደደን እንድንወደው ይፈልጋልና በውሰጣችን ያለውን የእርሱን
ክብር ተቀብለን እንድናየው፣ እንድንሰማው፣ እንድናናግረው፣ እንድንይዘውም በመጽሐፍ ቅዱስ ነግሮናል፡፡
14፡14-20፣ ዳን 3፡1፣ 2 ኛቆሮ 11፡22) በውስጡም የድርሳናትን የአጻጻፍ ስልት ይይዛል፡፡ (ሉቃ 3፡3፣ ሐዋ 1፡1)
በተአምር ደረጃም መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሥፍር ቊጥር የሌላቸው በአምላክ ረቂቅ ጥበብ የተሰሩ
ተአምራት እንደሚገኙ እሙን ነው፡፡ (2 ኛ ነገ 6፡17፣ ዮሐ 2፡1-11፣ ሐዋ 14፡8-13፣ ሐዋ 5፡ 15-16)
6. የኪነ ጥበብ ምንጭ ነው፡- የምሕንድስና (ዘጸ 25፡21፣ ዘጸ 31፡1-11፣)፤የሥነ ጽሑፍ (ሐዋ 18፡24) የመሳሰሉትን
ጥበባት የያዘ መጽሐፍ ነው፡፡
7. የሥራ አመራርና የፍትሕ ርትዕ፡- ለዓለም መንግሥታት መልካም አስተዳደር እንዲሰፍን፣ በመንግሥትና
በሕዝብ መካከል ልዩነቶች እነዳይሰፉ፣ ሰላም እንዲሰፍን ጥላቻና መለያየት እንዲጠፋ፣ መልካም
አስተዳደር፣ ፍትሕ ርትዕ እነዳይጓደል ከነሙሴ ዘመን ጀምሮ ለሥራ አመራር ጥበብ (ሳይንስ) ታላቅ
መሠረት የጣለ መጽሐፍ ቅዱስ ነው፡፡ (ዘጸ 18፡13-27)
8. የሥራ መሠረት ነው፡- ሥራን የጀመረው እግዚአብሔር ነው፡፡ (ዘፍ 1፡1፣ መዝ 111፣ ዘፍ 2፡15) መጽሐፍ
ቅዱስ ለሰው ልጆች ‹‹ገነትን ቆፍራት ተንከባከባት›› እንዲሁም ‹‹ ሊሠራ የማይወድ አይብላ›› (2 ኛ
ተሰ 3፡8-10) በማለት በሥራችን ሁሉ ቅንዓት፣ ታማኝነት፣ ታታሪነት፣ትጋት…ወዘተ እንዲኖረን
በአጽንዖት ያስገነዝበናል፡፡
የሰው ልጅ አስቦ ሊደርስባቸው የማይችለውን እጅግ በጣም ጥልቅና ረቂቅ የሆኑ ነገሮችን የያዘ መጽሐፍ
በመሆኑ
ያለ ስህተት ያለ መጋጨት . . . ወዘተ እንዲጻፍ ለማድረግ
አንድ ዓይነት የሃይማኖት፣ የሥነ ምግባር ሥርዓት እንዲኖረን ለማድረግ
እግዚአብሔር ለሰው ልጅ የሚፈልጋቸውን ነገሮች እንዲጻፉና የማይፈልጋቸው ጉዳዮች ደግሞ
እንዳይጻፉ ለማድረግ ማለትም አንድን ጉዳይ የመምረጥና ሌላውን ጉዳይ የመተው ችሎታ
እንዲኖራቸው ነው፡፡
የመጽሐፉ አከፋፈል በጸሐፊው ዕውቀት፣ ችሎታ፣ መጠን የተገደበ ሳይሆን የመጽሐፉ ባለቤት
እግዚአብሔር በሚገልጠው መጠን ይሆን ዘንድ ፤ እንዲሁም የሰው ዕውቀት በጊዜ የተወሰነና ከጊዜ
ውጭ መመልከት የማይቻለው ነው፤ ስለሆነም ዘለዓለማዊ ስለሆነው ስለ እግዚአብሔር ለመናገር ያለ
እግዚአብሔር መንፈስ አይቻልም፡፡ ስለዚህ መንፈስ ቅዱስ ለጸሐፊዎቹ እጅግ አስፈልጓል፡፡ (1 ኛ ቆሮ 2፡11)
አብዛኞቹ ቅዱሳት መጻሐፍት የተጻፉት በዕብራይስጥና በግሪክ ቢሆንም መጻሐፍቱ ለሁሉም መዳረስ ስለሚገባቸው ወደ ሌላ ቋንቋ ይተረጎሙ
ዘንድ እግዚአብሔር መተርጉማንን አስነሣ፡፡ ይህም የእግዚአብሔርን ፈቃዱንና ትእዛዙን በአሕዛብ ምድር እንኳን እንዲታወቅ ዓይነተኛ አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡
ስለዚህም ብሉይ ኪዳን ከክርስቶስ ልደት በፊት ወደ ግእዝና ግሪከ የተተረጎመ ሲሆን የአዲስ ኪዳን መጻሐፍትም ወደ ሱርስት፣ ላቲን፣ ግእዝና ሌሎች
ቋንቋዎች ተተርጉመዋል፡፡
መጻሕፍተ ብሉያት ለመጀመሪያ ጊዜ የተተረጎሙት ወደ ግእዝ ሲሆን ይህም በ 980 ቅ.ል.ክ ነው፡፡ ይህ ትርጉም ከሆነ ከ 480 ዓመት በኋላ
(5 ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ቅ.ል.ክ) ከባቢሎን ምርኮ የተመለሱት አይሁድ ዕብራይስጥ ጠፍቶባቸው ስለ ነበር በወቅቱ የነበሩት ሊቃውንት
የዕብራይስጡን ሀሳብ በአረማይክ አሳጥረው (Paraphrase) ተርጉመውታል፡፡ ይህም ትርጕም ‹‹ኤል ታርጉም›› (El Targum)1 የሚባለው ሲሆን፤
መጀመሪጀያ በቃል በኋላም በጽሑፍ የተረጐሙት ትርጕም ነው፡፡ ከዚህም በኋላ በ 284 ቅ.ል.ክ ሰብዓ ሊቃናት መጻሕፍቱን ወደ ግሪክ ቋንቋ ተርጉመውታል፡፡
ይህ ትርጉምም የዓለም ጥንታዊው ትርጉም ቢባልም የግእዙ ትርጉም እንደሚቀድመው ከዓመቱ መረዳት ይቻላል፤ መካከላቸው 696 ዓመት ልዩነት
ይታያልና፡፡
የሰብዓ ሊቃናት ትርጉም የተደረገው በ 284 ቅ.ል.ክ በግብጽ ንጉሥ ዳግማዊ በጥሊሞስ ፊላደልፎስ(285-247 ቅ.ል.ክ) (Ptolemy II
Philadelphus)
ጠሪነት ከፍልስጥኤም በመጡ ግሪክ ተናጋሪ አይሁዳውያን ነው፡፡ ይህ ንጉሥ በእስክንድርያ ላቋቋመው አዲስ ቤተ መጻሕፍት ከተቻለ
የዓለምን ሁሉ መጻሐፍት ለመሰብሰብ ተመኝቶ እንደነበርና ብዙ መጻሐፍትን እንደሰበሰበ ይነገራል፡፡ በጣም ተፈላጊ የሆነውን የአይሁድ የሕግጋት
2
መጽሐፍ ቅጅ በቤተ መንግሥቱ ቤተ መጸሕፍት አለመኖሩን በመረዳቱ ደብዳቤ ጽፎ አርስቲያስ እና ሌሎች ያሉበትን የመልእክተኞች ቡድን
ኢየሩሳሌም ለሚገኘው ሊቀ ካህናት አልአዛር (Eleazar) ላከ፡፡ በዚህም መልእክቱ የአይሁድን ሕግ ቅጂና እሱን ወደ ግሪክኛ መተርጎም የሚችሉ
ምሁራንን ወደ እስክንድርያ እንዲልክለት ጠየቀ፡፡ መልእክቱም የተሳካ ውጤት አስገኘ፤ ሊቀ ካህኑ አልአዛር 72 ሊቃውንትን መርጦ ልኮለታል፡፡
3
በሊቃውንቱ ቁጥርም ትርጉሙ ሰብዓ ሊቃናት (ሰባው ሊቃውንት) (Septuagint) (LXX) የሚል ስያሜ ተሰጠው፡፡ እነዚህም ሊቃውንት
መጻሐፍቱን ወደ ግሪክ ድንቅ በሆነ ሁኔታ በመንፈስ ቅዱስ እርዳታ ተርጉመውታል፡፡
ትርጉሙም የአይሁድ ካህናት፣ ሽማግሌዎችና ሕዝብ ተሰብስበው በተገኙበት ለብዙ ቀናት ተነበበ፡፡ ከምንጩ ከዕብራይስጡ ጋር
ፍጽም ተመሳሳይነት ያለው ሆኖ በመገኘቱ ሁሉም በአድናቆት ተቀብለውታል፡፡ ንጉሡም መጽሐፍቱን በቤተ መጻሐፍቱ አስቀምጧቸዋል፡፡
በእስክንድርያ ውስጥ የነበሩ አይሁዳውያንም በየምኩራባቸው እንዲጠቀሙበት የአዲሱ ትርጉም ቅጂዎችን እንዲሰጣቸው ንጉሡን
4
ጠይቀው ተሰጥቷቸዋል፡፡ እነርሱም በትርጉሙ ላይ ምንም ለውጥ ሳያደርጉ ለምኩራባቸው ለመገልገያነት ተጠቅመውበታል፡፡
ቀስ በቀስ ይህ ትርጉም በመስፋፋት በግሪክ ተናጋሪ አይሁዳውያን ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነት አግኝቷል፡፡ በታሪክ እንደምንረዳው
በክርስቶስ ዘመን ብቻ በእስራኤል ከሚኖር አይሁዳውያን ከእስራኤል ውጪ የሚኖሩት አምስት ስድስት እጥፍ ይበዙ ነበር፡፡ እነዚህም
1
ይህ ትርጉም በውስጡ የቃል በቃል ትርጉም ብቻ ሳይሆን ማብራርያ ጭምር የያዘ ነው፡፡
2
ይህ ሰው ከመልእክተኛ ቡድኑ መካከል አንዱ ሲሆን ይህንን ታሪክንም ለወደንድሙ ለፊሎከራጥስ (Philocrates) በጻፈው ደብዳቤ ላይ ጽፎ ያቆየልን እርሱ ነው፡፡
3
በመጻሕፍት የሕዳግ ማስታውሻ ላይ LXX የሚለውን ጸሐፊያን አብዛኛውን ጊዜ የሚጠቀሙ ሲሆን፤ በላቲን ቁጥር 70 ማለት ነው፡፡
4
በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም በግእዝ ቋንቋ፣ ቀ/ዶ/ር ም/ሥላሴ ገ/አማኑኤል፣ ገጽ 21-24
አይሁዳውያን የዕብራይስጥን ቋንቋ ቀስ በቀስ ስለረሱ የሚናገሩት በግሪክ ነበር፡፡ ስለሆነም እነርሱም ይጠቀሙት የነበረው ይህን የሰብዓ
5
ሊቃናት ትርጉም ነበር፡፡ ሐዋርያትም የአዲስ ኪዳን መጻሐፍትን በግሪክ ሲጽፉ የተጠቀሙት ይህን ትርጉም ነበር፡፡ ከዚህ በተጫማሪም ይህ
ትርጉም እግዚአብሔርን በማያውቁ በጣዖት አምላኪያን ዘንድ እንኳን ስለ እግዚአብሔርና ስለመሲሑ መምጣት እንዲታወቅ ከፍተኛ የሆነ
አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡ ይህም ለክርስትና መስፋፋት የበኩሉን ድርሻ ተጫውቷል፡፡
የሱርስት ትርጉም
6
ሱርስት በሶርያ የሚነገር የአረማይክ ዲያሌክት ነው፡፡ ጥንታዊ የሱርስት ትርጉም የሚባለው በ 170 ዓ.ም በታቲአኖስ(Tatian) አራቱ
ወንጌላትን በመደባለቅ የተሠራው ዲአቴሳሮን (Diatessaron) የተባለው ትርጉም ነው፡፡ ይህ ለብዙ ዓመታት ለቤተ ክርስቲያን መገልገያነት ከዋለ በኋላ
ሁሉንም መጻሕፍት ባለመያዙ ምክንያት ሌላ ትርጉም አስፈለገ፡፡
ስለዚህም እስካሁን ድረስ የሚገኘው ፔሽታ የተባለው ትርጉም ከ 411-435 ዓ.ም ባለው ዘመን ውስጥ ተሠራ፡፡ ትርጉሙም በኤዴሳው ሊቀ ጳጳስ
በራቡላ እንደተሠራ ይታመናል፡፡ የዚህ ትርጉም ከ 350 በላይ ጥንታዊ መዛግብት (manuscripts) አሁን ሲገኙ አብዛኞቹም የተሠሩት በ 5 ተኛው እና
6 ተኛው መ.ክ.ዘነው፡፡ ይህ ትርጉም ከግሪኩ እጅ ጽሑፍ ጋር በጣም ተቀራራቢነት አለው፡፡ በአንዳንድ ሊቃውንትም የኢትዮጲያው የተሠዓቱ ቅዱሳን
የግእዝ መጽሐፍ ቅዱስ የተተረጎመው ከዚህ እንደሆነ ይነገራል፡፡
ከዚህም በኋላ በምስራቅ ሶርያ ማቡግ በተባለች ቦታ ሊቀ ጳጳስ የነበረው ፊሎክሲነስ (Philoxenus of Mabbug) ፊሎክሲኒዎስ
(Philoxenian) በመባል የሚታቀውን ትርጉም ሠራ፡፡ ከዚህም መጽሐፍ ወንጌላትና የትንቢተ ኢሳይያስ አንዳንድ ክፍላት ብቻ አሁን ተርፈው ይገኛሉ፡፡
የግብጽ የቅብጥ ትርጉም
በግብጽ ከታላቁ እስክንድር ጀምሮ ግሪክ በሰፊው የሚነገርባት የሰብአ ሊቃናት የግሪክ ትርጉም የተሠራባት ሀገር ብትሆንም በገጠር በባላገሩ ብዙ
ዲያሌክቶች ስለ ነበር የግድ ወደ ተለያዩ የክፍለ ሀገራቱ ዲያሌክቶች መተርጎም አስፈለገው፡፡ በዚህም የመጀመሪያው ከሁሉም ጥንታዊ የሆነው ሳዲያክና
ቱባይክ እየተባለ የሚጠራው ትርጉም በ 2 ተኛ መቶ ክፍለ ዘመን ተሠራ፡፡ ይኸውም በላዕላይ ግብጽ ባሉ ሕዝቦች የሚነገር ሳሂዲያክ (Sahidic) በተባለው
ዲያሌክት ነው፡፡
ከዚያ በመቀጠል ከሁሉም የግብጽ ዲያሌክት ይልቅ በሀገሪቱ የተስፋፋና ሁሉንም ዲያሌክቶች መግለጥ ወደሚችል በታህታይ (በታችኛው) ግብጽ
አካባቢ በሚኖሩ ሕዝቦች ወደሚነገረው ቦሃይሪክ (Bohairic) ዲያሌክት ተተረጎመ፡፡ ትርጉሙም ሐይሪክ ወይም ማምፌቲክ በመባል ይታወቃል፡፡
ከዚህም በኋላ ወደ ተለያዩ ዲያሌክቶች ተተርጎሟል፡፡
የአርመን ትርጉም
መጽሐፍ ቅዱስ ወደ አርመን የተተረጎመው በ 5 ተኛው መ.ክ.ዘ ቅዱስ ሜስሮብ ማሽቶትስ በተባለ አባት እና በፓትርያርኩ በይስሐቅ ነው፡፡ ቅዱስ
ሜስሮብ ወንጌልን ለማስፋፋት በሚያደርገው ሐዋርያዊ አገልግሎት ውስጥ የመጽሐፍ ቅዱስ ወደ ሕዝቡ ቋንቋ አለመተርጎም፤ ሕዝቡን ለመምራትና
ለአገልግሎቱ እንቅፋት ሆነበት፡፡ ሕዝቡ ለመጻፊያ የሚጠቀመው የግሪክ፣ የፋርስ እና ሶርያ ፊደላት የቋንቋቸውን የተወሳሰቡ ድምጾች መግለጥ እንደማይችሉ
በተረዳ ጊዜ ለአረመን ቋንቋ የሚሆን አዲስ ፊደላትን ሠራ፡፡ ከዚህም በኋላ ፓትርያርኩ ይስሐቅ መጽሐፍ ቅዱስን ከሶርያ ቋንቋ በ 411 ዓ.ም ወደ አርመን
ተረጎመ፡፡ ነገር ግን ትርጉሙ ፍጹም ስላልነበር የቅዱስ ሜስሮብ ደቀመዛሙርት የሆኑት ዮሐንስና ዮሴፍ ወደ ሶርያው የትርጓሜ ቤት ኤዴሳ እንዲሁም እስከ
ቁስጥንጥንያ ድረስ በመሄድ ብዙ የግሪክ ትርጉሞች ከሰበሰቡ በኋላ የግሪኩን ሰብአ ሊቃናትና የአርጌንስን ሄክሳፔላ በመከተል 434 ዓ.ም የትርጉም ሥራው
ተሠርቷል፡፡ የአርመን ቤተ ክርስቲያንም እስካሁን ድረስ የምትጠቀመው ይህን ትርጉም ነው፡፡
የዐረብኛ ትርጉም
ይህ ትርጉም ዮሐንስ በተባለ ጳጳስ በ 8 ተኛው መቶ ዓመት ተተርጉሟል፡፡ ከዚያም እንደገና ይስሐቅ በተባለ ሰው በ 10 ኛው መ.ክ.ዘ እንደገና
ተተርጉሟል፡፡ አብዛኞቹ የዓረብኛ የጥንት ትርጉሞች አሁን የሚገኙት በሲና ተራራ በቅድስት ካትሪና ገዳም ነው፡፡
የእስላቦኒክ ትርጉም
5
ስለ ሰብአ ሊቃናት ትርጉም በሰፊውና በማስረጃ የተደገፈ በ‹‹የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ ከልደተ ክርስቶስ እስከ ሁለት ሺህ ዓ.ም›› በተሰኘው
መጽሐፍ ላይ ከገጽ 160-166 የተጻፈውን መመልከት ይቻላል፡፡
6
ዲያሌክት ማለት አንድን ቋንቋ በተለየ ዘዬ(ድምጸ ንባብ)፣ በተለየ ፊደል እና ሰዋስው በሆነ አካባቢ ብቻ ሲነገር ነው፡፡
ይህም ቄርሎስና ማቶዲየስ በተባሉ ሁለት ግሪካዊ ወንድማማቾች በ 10 ኛው ምዕተ ዓመት የተሠራ ነው፡፡ እነዚህ አባቶች ወደ እስላቦኒያ ሄደው
ሀገሩን ወንጌል አስተምረው መጽሐፍ ቅዱስን ከግሪክ ተርጉመዋል፡፡ ለትርጉም ሥራቸውም ሲሉ ለአገሪቱ አዲስ ፊደልን ቀርጸዋል፤ በዚህም የሥልጣኔና የሥነ
ጽሑፍ በር ከፍተዋል፡፡
በዐራተኛው መቶ ክፍለ ዘምን መጨረሻ አካባቢ (በ 390 ዓ.ም) ላይ በቃላት አጠቃቀሙም በሰዋሰውም ጥሩ ሆነ የላቲን ትርጉም ተሠራ፡፡
የትርጉሙም ስም ቩልጌት(Vulgate) ይባላል፡፡ ትርጉሙም common (ለሁሉም የሚሆን) ማለት ነው፡፡ በሕዝቡ ቋንቋ ስለተተረጎመ ነው ይህ ስያሜ
የተሰጠው፡፡ ይህንን ትርጉም የሠራው አባት ቅዱስ ጄሮም (አባ ሄሮኒመስ) በመባል ይታወቃል፡፡ ይህ አባት የተወለደው በስትሪዶን (Stridon) (የአሁኗ
ቦዝኒያ (Bosnia)) በተባለች ከተማ በ 347 ዓ.ም ነው፡፡ በዚያም ጥሩ የሚባል የምዕራቡ ዓለም ትምህርትን ተምሯል፡፡ በዚህም በጣም
ታላቅ ተናጋሪ እንደሆነ ይነገራል፡፡ ነገር ግን ልክ እንደ ብዙ አባቶች ቤተ ክርስቲያንን ለማገልገል የዓለሙን ትምህርትና ሥራውን ትቶ
የቤተክርስቲያንን ጥልቅ ትምህርት ለመማር ወደ ምስራቁ ዓለም ሄደ፡፡ አብዛኛው የቤተ ክርስቲያን ጥልቅ አስትምህሮዎች ይሰጡ የነበረው
በግሪክ ቋንቋ ስለነበር እና ቅዱስ ጄሮም ያውቀው የነበረው የግሪክ ቋንቋ ትምህርቱን ለመረዳት በቂ ስላልነበር ግሪክን በሰፊው ተማረ፡፡
በተለያዩ የምስራቁ ዓለም ለብዙ ዓመታት ቆየ፡፡ ወደ ግብጽ በመሄድ ከዲዲሞስ ዕውሩ ሥር ተማረ፡፡ ከአንጾኪያ ከተማ ውጪ
በሚገኝ በርሃ ውስጥ በአንድ ዋሻ ውስጥ ለብዙ ዓመታት በጸሎትና በተጋድሎ ቆየ፡፡ በእነዚህ ዓመታትም በአንጾኪያ ቤተ ክርስቲያን ያገለግል
ነበር፡፡ በቁስጥንጥንያ ውስጥ ለብዙ ዓመታት ከቅዱስ ጎርጎርዮስ ነባቤ መለኮት እና ከተለያዩ አባቶች ሲማር ከቆየ በኋላ ወደ ሮም በመሄድ
የሮም ሊቀ ጳጳስ ለነበረው ለድማሰስ(Pope Damasus) ጸሐፊ ሆነ፡፡ ይህም ጳጳስ ጥሩ የሆነ የላቲን ትርጉም እንደሌለ ያውቅ ስለነበር
አባ ጄሮምን ጥሩ የሆነ በቤተ ክርስቲያን መገልገያ ሊሆን የሚችል የዐራቱን ወንጌላት የላቲን ትርጉም እንዲሠራ ጠየቀው፡፡ በዚህ ሰዓት አባ
ጄሮም ላቲን፣ ግሪክ (በኋላም ዕብራይስጥን) በጥሩ ሁኔታ ይናገር ስለነበር የትርጉም ሥራውን ሠራ፡፡ ምንም እንኳን ጳጳሱ ዐራቱን
ወንጌላት እንዲተረጉም ቢያዘውም እርሱ ሌሎቹን መጻሐፍት መተርጎም ጀመረ፡፡ ትርጉሙ ወደ 20 ዓመት የፈጀ ሲሆን ከአባ ጄሮምም
ጋርም ሎሎች በትርጉም ሥራው ተሳትፈዋል፤ ቢሆንም ትርጉሙ በእርሱ ስም ይጠራል፡፡ ከዚህም በኋላ እስከ ዕለተ ዕረፍቱ ድረስ
ለመጽሐፍ ቅዱስ የተለያዩ ትርጓሜያትን በማዘጋጀት ኖሯል፡፡
ቢድ(Bede) የተባለ የሮም ካቶሊክ ጳጳስ የመጽሐፍ ቅዱስን አንዳንድ ክፍሎች ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ጥንቱ እንግሊዘኛ (Old English) ቋንቋ
የተረጎመው በ 9 ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አካባቢ ነበር፡፡ ነገር ግን ከተለያዩ የካቶሊክ ጳጳሳት ተቃውሞ ደረሰበት፡፡ ይህም የሆነው መጻሕፍቱን ተራው
ምእመን (ከተማሩት ውጪ ያሉት) በተሳሳተ መልኩ ሊተረጉሙት ስለሚችሉ ሊያነቡት አይገባም በማለት ነበር፡፡ ተቀባይነትም ስላልነበረው ትርጉምን አሁን
አናገኘውም፡፡
ጆን ወይክሊፍ በ 13 መቶ ክፍለ ዘመን ሁሉንም መጻሕፍት ወደ እንግሊዘኛ ተረጎመ፡፡ ይህም የመጀመሪያው ሙሉ የእንግሊዘኛ ትርጉም
ያደርገዋል፡፡ ትርጉሙንም የሠራው ከቩልጌቱ የላቲን ትርጉም ነበር፡፡ ይህም ቢሆን የሮማ ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን አመራሮች መጻሕፍቱን አወገዟቸው፡፡
ከዚህም በኋላ ዊልያም ቴንድል ከዕብራይስጡና ከግሪኩ ባማነጻጸር መጽሐፍቱን ወደ እንግሊዘኛ ተረጎመ፡፡ የሮማ ካቶሊክ ቤተክርስቲያንና የእንግሊዝ
መንግሥት በሰዓቱ እጅግ የተያያዙ በመሆናቸው የተነሣ መጻሕፍትን ወደ ሌላ ቋንቋ መተርጎም ወንጀል ስለነበር፤ ሊገደል ሲል ከእንግሊዝ ለመሸሽ ቢሞክርም
ተይዞ በእሳት ተቃጥሎ እንዲሞት ተደርጓል፡፡ መጻሕፍቱም ተሰብስበው ተቃጥለዋል፡፡
በጥንት ጊዜ መጽሐፍ ቅዱስ ይገለበጥ የነበረው በእጅ ነበር፡፡ በዚህም የተነሣ መጽሐፍ ቅዱስ በጣም ውድ ነበር፡፡ ለምሳሌ በቅዱስ ዮሐንስ
አፈወርቅ ዘመን ሐዲስ ኪዳን የአንድ ሰው የዓመት ደሞዝ ነበር ዋጋው፡፡ ነገር ግን ጉትንበርግ (Gutenburg) 1455 ዓ.ም የማተሚያ መሳርያን ከፈለሰፈ
በኋላ ሁሉም ነገር ተቀይሯል፡፡ ስለዚህም መጻሐፍት በብዛት፣ በፍጥነት መታተም ጀመሩ ዋጋቸውም እንደ ድሮ ውድ አልነበረም፡፡ ይህም በሕዝቡ ዘንድ
እንዲስፋፋና ተፈላጊነቱ እንዲጨምር አድርጓል፡፡ በዚህ የተነሣ የእንግሊዝ ቤተ ክርስቲያን መጽሐፍ ቅዱስ ወደ እንግሊዘኛ እንዲተረጎሙ ፈለገች፡፡ ይህን
ሀሳብ የሚደግፍ ጄምስ የተባለ ንጉሥም ነገሠ፡፡ 1611 ዓ.ም የመጀመሪያው የተፈቀደ(ወንጀል ያልሆነ) የእንግሊዘኛ መጽሐፍ ቅዱስ እንዲዘጋጅ ፈቀደ፡፡
በዚህም የተነሣ ይህ መጽሐፍ ቅዱስ የንጉሥ ጄምስ መጽሐፍ (King James Version(KJV)) ወይም የተፈቀደው መጽሐፍ (Authorized
Version) በመባል ይታወቃል፡፡ ከሌሎች ትርጉሞች በተለየ ይህ ትርጉም በአንድ ሰው ሳይሆን በጣም ብዙ የእንግሊዝ የመጽሐፍ ቅዱስ ሊቃውንት
እንዲተረጉሙት አድርጓል፡፡ በኋላም የእንግሊዝኛ ቋንቋ እያደገ በመምጣቱና የተለያዩ የትርጉም ለውጦች በማምጣቱ በ 19 ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አዲሱ
7
በጥንት ቤተክርስቲያን የምዕራቡ ዓለም የሚባሉት ሮም፣ ስፔን፣ ጋውል (Gaul)፣ እንግሊዝ እና ሰሜን አፍሪካ (ከግብጽ በቀር) ያሉት ሀገራት ናቸው፡፡
የንጉሥ ጄምስ ትርጉም(New King James Version(NKJV)) የተባለው ትርጉም ተሠራ፡፡ ካሉት የእንግሊዘኛ እጅግ ብዙ ትርጉሞች ይህ ትርጉም (
NKJV) የተሻለ ቢሆንም እርሱም የራሱ የሆነ አንዳንድ ችግሮች አሉበት፡፡
ከዚህ በተጨማሪ በሰባተኛው መቶ ክፍለ ዘመን በቻይና ቋንቋ፣ በዐሥራ ዐራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን በፋርስ (Persia) ቋንቋ ተተርጉሟል፡፡
እንደነዚህ ያሉ ጥንታዊ ትርጉሞች ቢኖሩም የመጽሐፍ ቅዱስ የትርጉም ሥራ በአያሌው የተስፋፋው ለአለፉት ሁለት መቶ ዓመታት ውስጥ ነው፡፡ ከ 19 ኛ
መቶ ክፍለ ዘመን በኋላ መጽሐፍ ቅዱስ ወደ ሁለት ሺህ በሚጠጉ የተለያዩ ቋንቋዎች በከፊልም ሆነ በሙሉ ተተርጉሟል፡፡
1. ቀጥተኛ (Literal)፡- ከተጻፈበት (ከአቀባዩ) ቋንቋ ቃል በቃል በቀጥታ መተርጎምን ይከተላል፡፡ በተጫለው መጠን የዓረፍተ ነገሩን
አቀማመጥ እንኳን አይቀይርም፡፡ ይህም ለአቀባዩ ቋንቋ ያደላል፡፡
2. ገላጭ(Dynamic)፡- ከቃላት ይልቅ ድርጊትን ሐሳብን በመግለጥ ተነባቢነት ላይ ያተኩራል፡፡ የዓረፍተ ነገሩን ሀሳብ ለመግለጥ
የራሱን አገላለጥ ይጠቀማል፡፡ ይህም ከአቀባዩ ይልቅ ለተቀባዩ ቋንቋ ያደላል፡፡ ለምሳሌ፡- በመጽሐፍ ቅዱስ ኅብስት፣ ዳቦና ቂጣ
የሚሉትን ወደ አማርኛው ሲተረጎም እንጀራ ተብለው ተተርጉመዋል፡፡
1. የተጠቀሙት የትርጉም መንገድ መለያየት፡- ከላይ ከተጠቀሱት የትርጉም ዓይነቶች አንዱን ወይም ሌላውን መጠቀም የገጸ ንባብ
ልዩነት ያመጣል፡፡ ይህም በምስጢራዊው ትርጓሜ የሚቃና ነው፡፡ ከላይ ያሉት ትርጉሞች ሁለቱም የራሳቸው የሆነ ድክመት
አላቸው፡፡
የቀጥተኛ አተረጓጎም ስልት ድክመት የመጽሐፉን ውበት የሚያሳጣው ሲሆን ከዚህ በተጫማሪ አንዳንድ ፊሊጣዊ
ወይም ምሳሌያዊ ንግግሮች በአቀባዩ ቋንቋ ትርጉም የሚሰጡ ለተቀባዩ ግን ምንም ትርጉም የማይሰጡ ሊሆኑ ስለሚችሉ
የትርጉም መዛባትን ያስከትላል፡፡ ለምሳሌ፡- ‹‹አንቺ ሴት ከእኔ ጋር ምን አለሽ›› የሚለው የዕብራውያን አገላለጥ በሌሎች ቋንቋ
የተዛባ ትርጉም ሊሰጠው ይችላል (የመጽሐፍ ቅዱስ ባህል የሚለውን ንዑስ ርዕስ ተመልከት)፡፡
ልክ እንደዚሁም የገላጭ አተረጓጎም ስልትም የራሱ ድክመት አለበት፡፡ ይህም ትርጉሙ የሚወሰነው በተርጓሚው
የአረዳድ መጠን ላይ ስለሆነ ወደ ፈለገው ሀሳብ አጣሞ መተርጎም ይችላል፡፡ በአብዛኛው የእንግሊዘኛ ትርጉሞች ላይ የሚታየው
ይህ ችግር ነው፡፡
2. የዶግማ ልዩነት፡- የዚህ ችግር ምንጭ ሁሉም የእምነት ተቋማት የየራሳቸውን ዶግማ(መሠረተ እምነት) መጽሐፍ ቅዱሳዊ ድጋፍ
ለመስጠት ሲሉ መጽሐፍ ቅዱስ ላይ በሚያስገቡት ሆነ በሚቀንሱት ንባብ ምክንያት የሚፈጠር ነው፡፡
ለምሳሌ፡- ለዚህም እንደ ዋና ተጠቃሽ የሚሆነው የይሖዋ ምስክሮች (Jehovah's Witnesses) የአዲሱ ዓለም
8
ትርጉም በመባል የሚታወቀው ትርጉም ነው፡፡ ይህም ትርጉም ለራሳቸው መሠረተ እምነት እንዲመች አድርገው
ከ 1000 በላይ ቃላትን በማስተካከል ያዘጋጁት ነው፡፡
3. የምንጩ እርግጠኝነት፡- የተጠቀሙት ምንጭ ጥንታዊ መሆንና አለመሆን የንባብና የሀሳብ ልዩነት ያመጣል፡፡ አብዛኞቹ ትርጉሞች
ያለተጠቀሙበትን የዕብራይስጥ ትርጉሞች የግሪኩን ጥንታዊ ትርጉሞች ተጠቅመናል ይላሉ፡፡
ለምሳሌ፡- ምንም እንኳን መጽሐፉ ቢታገድም፣ የአሜርካ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር ባሳተመው መጽሐፍ ቅዱስ ላይ
ኢትዮጵያ የሚሉትን የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች በጠቅላላ ሱዳን በማለት ተክቶት ነበር፡፡ ለዚህም እንደ ምክንያት አድርጎ
ያቀረበው በጥንታውያን ቅጂዎች ላይ አገኘሁት በማለት ነበር፡፡
1. ማመሳከር፡- የተለያዩ ትርጉሙችን ማየት የአንዱንም ከሌላው ማስተያየት ይገባል፡፡ በተለይ የመሠረተ እምነት (ዶግማ) አስተምህሮ
ከሆነ አንድ ትርጉም ላይ ብቻ መመሥረት ተገቢ አይደለም፡፡
2. ማነጻጸር፡- የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሉን ከአጠቃላይ የመጽሐፉ መልእክትና ከሌሎች የመጽሐፍ ቅዱስ ንባቦች ጋር ማነጻጸር፡፡ ከዚህ
በተጨማሪም አንድን ጥቅስ ከሙሉ የመጽሐፍ ቅዱስ መልእክት ለይቶ መመልከት አይገባም፡፡
3. ሙሉ ዓውዱን ማየት፡- ጥቅሱን ከአገባቡ አንጻር ማየት፤ አንድ ጥቅስን ብቻ ገንጥሎ ማየት አይገባም፡፡
8
THE HERESY OF JEHOVAH’S WITNESSES, BY H.H. POPE SHENOUDA III, pp14
4. የቤተ ክርስቲያንን ፈለግ መከተል፡- ቃለ እግዚአብሔርን ከሐዋርያት ጀምሮ በቃልና በጽሑፍ ያሰስተላለፈችልንን የቤተ ክርስቲያንን
ትምህርት በመያዝ ትርጉሙን ማቅናት፡፡
የመጽሐፍ ቅዱስ ቀኖና ስንል በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሊካተቱ የሚገባቸው የቅዱሳት መጻሐፍትን ዝርዝር ያመለክታል፡፡ ቅዱስ አትናቴዎስ
የቅዱሳት መጻሕፍት ዝርዝር በጠቀሰበት የፋሲካ መልእክቱ እነዚህን መጻሕፍት የተወሰኑና የተደነገጉ (Regulated and defined) ይላቸዋል፡፡
ስለዚህም“ቀኖናውያት ቅዱሳት መጻሕፍት” ሲባል የተደነገጉና ፍጹም ተቀባይነት ያላቸውን በእግዚአብሔር ለቤተክርስቲያን
መጠበቂያና መመሪያ ይሆኑ ዘንድ የተጻፉና የተሠጡ የተለዩ የተመረጡ መጻሕፍትን ያመለክታል፡፡ እነዚህም መጻሕፍት
ቤተ-ክርስቲያን ትምህርተ ሃይማኖትን ለማረጋገጥና ለማስተማር በጉባኤ የምታነባቸውና የምትተረጕማቸው፣ ለሃይማኖት
ጉዳይ መነሻና መድረሻ ለክርክርም የመጨረሻ ይግባኝ ሆነው የሚጠቀሱና የሚቀርቡ መጻሕፍት ናቸው፡፡
አስቀድመን እንደተነጋገርነው በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያሉት መጻሐፍት በተለያየ ጊዜ የተጻፉና ራሳቸውን የቻሉ መጻሐፍት ነበሩ፡፡ ስለዚህ እነዚህ
መጻሐፍት በጊዜ ሂደት ተሰባስበው አሁን ያላቸውን ቅርጽ ያዙ እንጂ በአንድ ጊዜና ቦታ የተጻፉ ወይም እንዲህ ሆነው ከሰማይ የወረዱ መጻሕፍት
አይደሉም፡፡ በዚህም የተነሣ የተለያዩ ቤተ እምነቶች ሆነ ዓቢያተ ክርስቲያናት የተለያየ ቀኖና መጻሐፍት (የመጻሐፍት ዝርዝር) አላቸው፡፡ ይህንንም ከዚህ
በመቀጠል እናቀርበዋለን፡፡
አይሁዳውያን ብሉይ ኪዳንን “ብሉይ ኪዳን” ብለው አይጠሪትም፤ ምክንያቱም አዲሱን ኪዳን አይቀበሉምና፡፡ ነገር ግን “ትናክ (TaNaKh)”
በማለት ይጠሩታል፡፡ “ትናክ” የሚለው የዕብራይስጥ ቃል አሕጽሮተ ቃል (acronym) ነው፡፡ ይህም አይሁዳውያን መጻሕፍት (“ብሉይ ኪዳን”)
ከሚከፍሉባቸው ሦስት ክፍሎች የመጣ ነው፡፡ “ት” የሚለው የመጀመሪያው ቃል “ቶራ(Torah)” የተባለውን ክፍል ይክላል፣ “ና” ደግሞ
“ኔቪኢም(Nevi’im)” የተባለውን ክፍል ሲወክል፤ የመጨረሻው “ክ” ደግሞ “ኬቱቪም(Ketuvim)” የተባለውን ክፍል ይወክላል፡፡
1. ቶራ(Torah)፡- የሚለው ቃል በቀጥታ ሲፈታ አስተምህሮ ማለት ነው፡፡ አይሁዳውያን በዚህ ክፍል የመጀመሪያዎቹን አምስት የሕግ መጻሐፍትን
ማለትም ኦሪት ዘፍጥረት፣ ኦሪት ዘጸአት፣ . . . አካተው ይቆጥራሉ፡፡ ከመጻሐፍቱ ይዘትም አንጻር ቶራ የሚለው ቃል ሕግ የሚለውን ስያሜ እንዲይዝ
ሆኗል፡፡
2. ኔቪኢም(Nevi’im)፡- በዕብራይስጥ “ናቪ(Navi)” ማለት ነቢይ ማለት ሲሆን “ኔቪኢም” ማለት ደግሞ በብዙ ቊጥር ነቢያት ማለት ነው፡፡
ይህንንም ክፍል ከዘመን አንጻር በሁለት ንዑሳን ክፍላት ይከፍሏቸውል፡፡ እነዚህም
1. የቀደሙት ነቢያት(former Prophets)፡- በዚህ ክፍልም አራት መጻሐፍትን ሲያካትቱ እነርሱም መጽሐፈ ኢያሱ፣ መጽሐፈ መሳፍንት፣
መጽሐፈ ሳሙኤል(ሁለቱን እንደ አንድ)9 እና መጽሐፈ ነገሥት(ሁለቱን እንደ አንድ) ናቸው፡፡ እነዚህ መጻሐፍት በእኛ አቆጣጠር ከታሪክ
መጻሐፍት ሥር የምንቆጥራቸው ናቸው፡፡
2. ኋለኞቹ ነቢያት(later Prophets)፡- በዚህ ክፍል አራት መጻሐፍትን ብቻ ሲያካትቱ እነርሱም ትንቢተ ኢሳይያስ፣ ትንቢተ ኤርምያስ፣
ትንቢተ ሕዝቅኤልና የዐሥራ ሁለቱ መጻሐፍት በማለት 12 ቱን ደቂቅ ነቢያት እንደ አንድ መጽሐፍ10 አድርገው ይቆጥሯቸዋል፡፡
3. ኬቱቪም(Ketuvim)፡- ጽሑፋት ማለት ሲሆን በዚህም ክፍል ከሕግና ከነቢያት (ከመጀመሪያዎቹ ሁለት ክፍሎች) ውጪ ያሉትን የመዝሙር
የጥበብና የታሪክ 11 መጻሐፍትን አካተው ይቆጥሩታል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ትንቢተ ዳንኤልን ልክ እንደ ትንቢት መጽሐፍ ሳይሆን እንደ ታሪክ መጽሐፍ
ከዚህ ክፍል አካተው ነው የሚቆጥት፡፡
ፈሪሳውይን ከእነዚህ ክፍላት የመጀመሪያዎቹን ሁለቱን ብቻ ሲቀበሉ ሦስተኛውን ክፍል ግን መገልገያና ማስተማሪያ መጽሐፍ እንጂ እንደ አሥራው
መጻሐፍት አድርገው አይቆጥሯቸውም፡፡ ሰዱቃውያንና ሳምራውያን ደግሞ ቶራን ብቻ ይቀበላሉ፡፡ አሁን ያሉት አይሁድ ግን ሦስቱንም ከፍል በአጠቃላይ
22 መጻሐፍትን እንቀበላለን ይላሉ፤ ነገር ግን አቆጣጠራቸው ስሚለያይ ነው እንጂ እንደ እኛ አቆጣጠር ከሆነ 39 መጻሐፍትን ይቀበላሉ፡፡
11
ይህ የአይሁድ ቀኖና “ትናክ” በእንደዚህ መልክ የተዘጋጀው ከ 150-200 ዓ.ም አካባቢ በተበተኑት የአይሁድ ሊቃውንት(ረበናት) ነው፡፡ ለዚህም
ቀኖና መደንገግ ምክንያት የሆኑት ደግሞ ክርስቲያኖች ናቸው፡፡ አይሁዳውይን ከጥንት ጀምሮ በተለያዩ ሀገሮች ተበትነው ይኖሩ ነበር፡፡ በመጀመሪያው መቶ
ክፍለ ዘመን (ድ.ል.ክ) በአነስተኛ ቁጥም ቢሁን በሮማውያን ግዛት የአይሁድ ሕዝብ ያልነበረበት ከተማ አይገኝም ነበር፡፡ ክርስቶስ በተወለደበት ጊዜ በምድረ
እስራኤል ውስጥ ከነበሩት አይሁድ ከምድረ እስራኤል ውጭ የነበሩት አይሁድ አምስት ወይም ስድስት እጥፍ እንደነበር ይነገራል፡፡ ስለዚህም እነዚህ
አይሁዳውያን አብዘኞቹ በጊዜ በብዛት ይነገር የነበረውን የግሪክ ቋንቋን እንጂ ዕብራይስጥ አይናገሩም ነበር፡፡ ስለዚህም ይጠቀሙት የነበረው የሰብዓ
ሊቃናትን የግሪክ ትርጉም እንጂ የዕበራይስጡን አልነበረም፡፡ በዚህም የአይሁድ መሰራጨት የእውነተኛ አምላክ ዕውቀትና የመሲሕ መምጣት ተስፋ በሰብዓ
ሊቃናት ትርጉም አማካይነት በአሕዛብ ምድር በመጠኑም ቢሆን ይታወቅ ነበር፡፡ ይህም ለክርስትና መስፋፋት በእጅጉ ጠቅሟል፡፡
የሰብዓ ሊቃናት ትርጉም ከመጀመሪያው አንስቶ የእስክንድርያ ግሪክ ተናጋሪ አይሁዶች ለምኩራባቸውና ማስተማሪያነት በፍልስጥኤም የሚገኙት ረበናት
መምህራን ሳይቀር ይጠቀሙበት ነበር፡፡ ስለዚህም ይህ ትርጉም በአይሁዳውያን ዘንድ ትልቅ ቦታ ነበረው፡፡ ይህ የሰብዓ ሊቃናት ትርጉም በአይሁድና
12
በአሕዛብ ዘንድ ተሰራጭቶ ስለነበር የመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖች እንደ ክርስቲያን መጽሐፍ ቅዱስ አድርገው ተቀብለውታል፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስም በስብከቱ
9
የዕብራይስጥ ቋንቋ ለየት ባለ መልኩ የአናባቢ ፊደላት የሉትም፡፡ በዚህም የተነሣ ሁለቱም የሳሙኤል መጻሐፍት አንድ መጽሐፍ ነበሩ፡፡ በኋላ ግን ሰብአ ሊቃናት ወደ ግሪክ
ሲተረጉሙት መጠኑ እጅግ ስለበዛ በአንድ ጥቅልል መካተት ባለመቻሉ ለሁለት ከፍለውታል፡፡
10
በጥንት ዘመናት መጻሐፍት ተጠርዘው ሳይሆን የሚቀመት ተጠቅልለው ነበር፡፡ ስለዚህም አንድ ጥቅል ለመስራት ረዘም ያለ ክርታዝ ወይም ብራና ያስፈልግ ነበር፡፡
በመሆኑም እነዚህ 12 መጻሐፍት በመጠናቸው እጅግ አነስተኛ ስለነበሩ ብቻቸውን አንድ ጥቅልል መሆን አይችሉም፡፡ ስለዚህም ሁሉንም ጠቅልለው በአንድ መጻሐፍት
ስለሚያካትቷቸው ነው፡፡
11
አይሁዳውይን በ 70 ዓ.ም በሮም ላይ በማመጻቸው ምክንያት ሮማዊው ቄሳር መጥቶ ኢየሩሳሌምን አፈራርሶ ከሀገራቸው አፈናቅሏቸው ስለነበር እስከ 1945 ዓ.ም ድረስ
በዓለም ሁሉ ተበትነው እንጂ በእስራኤል ሀገር አይኖሩም ነበር፡፡
12
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ ከልደተ ክርስቶስ እስከ ሁለት ሺህ ዓ.ም፣ ገጽ 164
ሐዋርያትም በትምህርታቸውና ሐዲስ ኪዳንን በጻፉበት ወቅት ከብሉይ ኪዳን ሲጠቅሱ ዘወትር የሚጠቅሱት ከሰብዓ ሊቃናት ትርጉም ነበር፤ አብዛኞቹ
የሐዲስ ኪዳን መጻሕፈት በግሪክ ነውና የተጻፉት፡፡ ክርስትና ቀስ በቀስ ከተስፋፋ በኋላ ሰብዓ ሊቃናት በክርስቲያኖች ዘንድ በሰፊው ተሰራጨ፡፡ ይሁን እንጂ
አይሁዳውያን ሰብዓ ሊቃናት በክርክር ወቅት በእነርሱ ላይ እንደ መከራከሪያ ነጥብ እየሆነ በተግባር መዋሉን ባወቁ ጊዜ፣ ለሰብዓ ሊቃናት ይሰጡት የነበረው
አክብሮት ተቃራኒ ወደሆነ ስሜት ተለወጠ፡፡ ይባስ ብሎም ለሰብዓ ሊቃናት የነበረውን ዕውቅናና ሥልጣን ለማሳጣት የሚቻላቸውን ሁሉ አደረጉ፡፡ ሰብዓ
ሊቃናት ትክክለኛ ትርጉም አይደለም እያሉ ይካራከሩም ጀመር፡፡
ታዲያ እነዚህ የአይሁድ ሊቃውንት ከ 150-200 ዓ.ም መካከል ተሰባስበው “ትናክ” የተባለውን የአይሁድ ቀኖና ወሰኑ፡፡ ስለዚህ የመጻሐፍቱን ቁጥር
ሲወስኑ በሰብአ ሊቃናት የሚገኙ ነገር ግን በዕብራየይስጡ የጠፉ እንዲሁም ስለ ክርስቶስ ቀጥተኛ ትንቢትና ሱባኤ ያሉባቸውን መጻሐፍት
13
ከመጻሐፍቶቻቸው አውጥተው ቆጥረዋል፤ ትንቢተ ዳንኤልንም ከታሪክ መጽሐፍ ሥር ቆጠጥረውታል ፡፡ ከዚህ በተጨማሪ መጻሐፍቱ በዕብራይስጥ ብቻ
መነበብ አለባቸው፣ ወደ ሌላ መተርጎም የለባቸውም ብለው ወሰኑ፡፡ የሰብዓ ሊቃናት ትርጉምንም ከምኩራባቸው አወጡት፡፡ ይህም ዕብራይስጥን
የማያውቁትን አይሁድ ያማከለ ስላልነበር ለእነሱ በግሪክ ፊደል የዕብራይስጥን ድምጸ ልሣን በተከተለ መልኩ አዲሱን ቀኖና (“ትናክ”ን) አዘጋጁላቸው፡፡
ቢሆንም የሚያነቡትን ስለማይረዱት በምኩራብ እየተረጎሙ የሚያስተምሯቸውን ሰዎች አዘጋጁላቸው፡፡
ከዚህም የተነሣ የሰብዓ ሊቀናት ትርጉም በ”ትናክ” የሌሉ እንደ መጽሐፈ ጦቢት፣ መጽሐፈ ዮዲት፣ መጻሕፍተ መቃብያን ... ያሉ ብዙ መጻሐፍትን
ይዟል፡፡ ነገር ግን እነዚህን መጻሐፍት አይሁድ አንቀበላቸውም ይበሉ እንጂ መጀመሪያ በዕብራይስጥ የነበሩ መጻሐፍት ናቸው፡፡ ይህንንም በ 1946 ዓ.ም
በሙት ባሕር አካባቢ በአርኪዮሎጂ ጥናት የተገኙት ጥንታዊያን መዛግብት (Dead Sea Scrolls) ያረጋግጡልናል፡፡ ስለዚህም ከዚህ ታሪክ
እንደምንረዳው የሰብዓ ሊቃናት ትርጉም ከተጠናቀቀ ከብዙ መቶ ዓመታት በኋላ ነው የአይሁድ ቀኖና (ትናክ) የተሠራው፡፡ ይህም የሰብዓ ሊቃናት
ጥንታዊነት ያስረዳናል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ እኛ ክርስቲያኖች አይሁዳውያን የሚቀበሉትን ሁሉንም መጻሐፍት ብንቀበልም አከፋፈላችን ሆነ አቆጣጠራችን ግን ከእነርሱ የተለየ
ነው፡፡ ይህም ብሉይ ኪዳንን በ 4 ክፍል ስንከፍለው እነርሱም 1. የሕግ መጻሐፍት 2. የታሪክ መጻሐፍት 3. የጥበብና የመዝሙር መጻሐፍት 4. የትንቢት
መጻሐፍት በማለት ነው፡፡
የፕሮቴስታንት ክፍልፋዮች የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ቀኖና ለምን ከኦርቶዶክሳውያን ቀኖና ተለየ ?
የፕሮቴስታንት እምነት የመጣው አንድ ማርቲን ሉተር የተባለ የጀርመን ሰው የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ለውጥ ያስፈልጋታል ትታደስ ብሎ በተነሣ
ጊዜ ነው፡፡ ከተቃወማቸው ነጥቦቸች መካከል ካቶሊካውያን ምእመኑን መጽሐፍ ቅዱስ እንዲያነቡ አያበረታቱም የሚል ነው፡፡ ይህም የሆነበት ምክንያት
የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ትጠቀም የነበረው ቩልጌት የተባለው የአባ ጄሮምን የላቲን ትርጉም ብቻ ስለነበር ነው፡፡ ከጊዜ ሂደት ሕዝቡ የላቲንን ቋንቋ መናገር
ትቶ በሌላ ቋንቋ ይናገር ስለነበር ሕዝቡ መጽሐፍ ቅዱስን አያነብም ነበር፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ቤተክርስቲያኗ መጽሐፍ ቅዱስ ሊነበበብ የሚገባው
በካህናትና በመምህራን ብቻ ነው፤ እንዲሁም በመጽሐፍ ቅዱስ ወደ ሌላ ቋንቋ መተርጎም የለበትም የሚል አቋም ስለነበራት ነው፡፡ ይህ ግን
በኦርቶዶክሳውያን ዘንድ የነበረ ሀሳብ አልነበረም፤ አባቶቻችን ወንጌልን ለማስፋፋት ሲዘዋወሩ ሕዝቡን ካሳመኑ በኋላ የመጀመሪያው ግብራቸው አንዱ
መጽሐፍ ቅዱስን ወደ ሕዝቡ ቋንቋ መተርጎም ነበር፤ ጽሕፈት ባይኖራቸው እንኳን አዲስ ፊደልን በመፍጠር ይተረጉሙ ነበር፡፡
ስለዚህም ማርቲን ሉተር ወደ ጀርመንኛ ተረጎመው፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የካቶሊክ ቤተክርስቲያንን የተቃወመ እየመሰለው እንግዳ የሆኑ በጥንት
ክርስቲያኖች ዘንድ ያለነበሩ አዳዲስ ትምህርቶችን አስተማረ፡፡ ለምሳሌ፡ - Sola Scriptura (መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ) በማለት ለመጻሐፍት ትርጓሜ ሆነ
ትውፊት አያስፈልጋቸውም፤ ሁሉም ለራሱ ያንብብ እንደሚመቸውም ይተርጉም በማለት አዲስ አስተምህሮን ማስተማር ጀመረ፡፡
ማርቲን ሉተር መጽሐፍ ቅዱስን ሲተረጉም ለብሉይ ኪዳን መጻሐፍት የሰብዓ ሊቃናትን ትርጉም ከመጠቀም ይልቅ “ትናክ”ን ተጠቅሟል፡፡ ለዚህም
እንደምክንያት ያቀረበው ብሉይኪዳን የአይሁድ መጻሐፍት ከሆኑና እነርሱ ሰብዓ ሊቃናትን ከተቃወሙት እኛም ልንቀበላቸው አይገባም በማለት ነው፡፡ ነገር
ግን በዚያ ዘመን እነዚህ መጻሐፍት በሕዝቡ ዘንድ እጅግ ተቀባይነት ስለነበራቸው ለማውጣት አልደፈረም፤ ይልቁንም የማውጫ ዝርዝር ላይ ለብቻቸው
መጨረሻ ላይ አደጋቸው፣ ከብሉይ ኪዳን መጻሐፍትም በመስመር ለያቸው፡፡ በሁለተኛና በሦስተኛ እትሞቹ (Editions) ግን ጨርሶ አጠፋቸው፡፡
ይህንንም የማርቲን ሉተር ሀሳብ ሌሎች በሌላ ሀገር የሚገኙ የተለያዩ ተሀድሶዎች (የፕሮቴስታታዊነት አቀንቃኞች) እንደ ዚዊንግሊ (ስዊዘርላንድ)፣
ካልቪን(እንግሊዝ) ያሉት ደግፈውታል፡፡ ስለዚህ እነርሱም የእርሱን አካሄድ ተከትለዋል፡፡ በዚህም ምክንያት ፕሮቴስታንቶች ልክ እንደ አይሁድ 39
መጻሐፍትን ብቻ ይቀበላሉ፡፡ ይህም ከክርስትናው ዓለም ትንሹ የመጻሐፍት ቀኖና ነው፡፡ ከዚህም አልፎ እነዚህን “ተጨማሪ” ያሏቸውን መጻሕፍት አፖክሪፋ
በማለት ያልተገባ ስም ሰጧቸው፤ የሐሰት መጻሕፍት ማለት ነው፡፡
ይህንንም የሉተርን ሆነ የሌሎቹ ተሀድሶዎችን ሀሳብ ለመቃወም በ 1545 ዓ.ም በሰሜናዊ ጣልያን የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ጉባኤ አደረገች፡፡
ጉባኤውም ጉባኤ ትሬንት ይባላል፡፡ በዚህም የሰብአ ሊቃናትን ትክክለኝነት በወሰን 49 የብሉይ ኪዳን መጻሐፍትን ወስናለች14፡፡ ነገር ግን አነዚህ ተጨማሪ
13
ይህ የሆነበት ምክንያት በነቢዩ ዳንኤል በመጽሐፉ ስለክርስቶስ ልደትና ስቅለት ዘመኑን ቁልጭ አድርጎ ስለሚናገር ነው(ዳን 9፡21-27)፡፡ ትንቢተ ዳንኤል ከዘመነ ባቢሎን
እስከ ዓለም ፍጻሜ ፣ዲ/ን ዳንኤል ክብረት፣ ገጽ 10 ተመልከት፡፡
መጻሐፍት ከሌሎቹ የብሉይ ኪዳን ትርጉም እኩል ጠቀሜታ የላቸውም በማለት የሁለተኛ ቀኖና መጻሐፍት (Deutrocanonical) በማለት ጠራቻቸው፡፡
ነገር ግን ቅድስት ቤተክርስቲያን ይህን ሀሳብ ሆነ ስያሜ አትቀበለውም፡፡
በቅድስት ኦርቶዶክሳዊት በቤተ ክርስቲያናችን ይህ ውዝግብ መጀመሪያውንም አልተነሣም፤ ጉባኤ ትሬንትንም አትቀበለውም፡፡ ስለዚህ መጻሐፍቱን
15
የሁለተኛ ቀኖና መጻሐፍት (Deutrocanonical) ብላ አትጠራቸውም ከሌሎቹ እኩል ጠቀሜታ እንዳላቸውም ታምናለች፡፡
የኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የብሉይ ኪዳን 46 መጻሐፍትን ስትቀበል በሰብአ ሊቃናት የሌሉ ነገር ግን በግእዝ ብቻ የሚገኙ እንደ
መጽሐፈ ሄኖክ፣ መጽሐፈ ኩፋሌ፣ ዮሴፍ ወልደ ኮርዮን ያሉትን መጻሐፍትንም ጨምራ ትቆጥራቸዋለች፡፡
14
የሰብአ ሊቃናቱ 46 ሆኖ ሳለ 49 መጻሐፍት መወሰናቸው አቆጣጠራቸው ስለሚለያይ ነው፡፡ ለምሳሌ ሁለቱን የሳሙኤል መጻሐፍት እንደ አንድ መቁጠርና አለመቁጠር . .
. የመሳሰሉት በመጻሕፍት ቁጥር ላይ ልዩነት ያመጣል፡፡
15
Deutrocanonical የሚለው አጠራር በጣም የተለመደ ስለሆነ በአንዳንድ ኦርቶዶክሳዊ መጻሕፍት ላይም ፕሮቴስታንቶች የማይቀበሉትን መጻሕፍት ለማመልከት
ሊቃውንቱ ይህን ስያሜ ሲጠቀሙበት ይታያል፡፡ ነገር ግን ስያሜውን ይጠቀሙበት እንጂ መጻሕፍቱ ከሌሎች መጻሕፍት ያንሳሉ በማለት አለመሆኑን ልብ ልንል ይገባል፡፡
የጆሆቫ ምስክሮች፡- 66 መጻሕፍትን ብቻ ሲቀበሉ ነገር ግን አዲሲቱ ዓለም ትርጕም የሚለውን የራሳቸውን ትርጕም
ብቻ ይጠቀማሉ፡፡ ይህም ትርጕም ከ 1000 በላይ የሚሆን ቃላትን በመቀየር ለራሳቸው እንዲመች አድርገው
ያዘጋጁት ነው፡፡
በአቆጣጠር ላይ የሚነሡ ጥያቄዎች
1. ፕሮቴስታንቶች ተጨማሪ እያሉ የሚጠሯቸው መጻሕፍትን አይሁድ በቀኖናቸው አላካተቷቸውም፤ ሰብአ ሊቃናትም
አልተረጎሟቸውም ስለዚህ ልንቀበላቸው አይገባም?
አይሁድ በቀኖናቸው ያላካተቱበትን ምክንያት ከላይ በሰፊው ያስረዳን ሲሆን፤ ሰብአ ሊቃናት እነዚህን መጻሕፈት
አላተረጎሟቸውም የሚለው አባባል ግን መሠረት የሌለው ሐሰት ነው፡፡ ሰብአ ሊቃናት መጻሕፈትን በሰበሰቡ ወቅት እነርሱ
እስከነበሩበት ድረስ የተጻፉት ቅዱሳት መጻሕፍት ከጥቂት መጻሕፍት በቀር ሰብስበዋል፡፡ ከሰበሰቧቸውም መጻሕፍት
መካከል እነዚህ መጻሕፈት ይገኙበታል፡፡
ምንም እንኳን እዝራ በ 534 ዓመት ቅ.ል.ክ መጻሕፈትን ሲሰበስብ እነዚህን መጻሕፍት ባገኛቸውም መጻሕፍቱ ግን
ነበሩ፡፡ ኋላም እንደ እዝራ ያለ ተሰሚነት ያለው ነቢይ ባለመነሣቱና ቅድም በዘረዘርናቸው ምክንያት ከእርሱ በኋላ የተጻፉት
መጻሕፈት ሆነ እርሱ ያልሰበሰባቸው መጻሕፍት በአይሁድ ቀኖና ባይካተቱም በአይሁድ ምሁራን ዘንድ ግን ክብር
ነበራቸው፡፡ ለዚህም ዋነኛው ማሳያ የሚሆነው ሰብአ ሊቃናት ቅዱሳት መጻሕፍትን ሲሰበስቡ እነዚህንም አካተው
በመሰብሰባቸውና በመተርጐማቸው ነው፡፡ ይህንንም ለመረዳት ጥንታውያኑን የጽርእ ኮዴክሶች መመልከት ይቻላል፡፡
2. እነዚህ መጻሕፈት የሚታመንባቸው ቢሆን ኖሮ በሐዲስ ኪዳን መጻሕፍ ከአባባላቸው ሆነ ከይዘታቸው በተጠቀሰ ነበር?
ሐዋርያት የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት ሲጽፉ የተቀሙት ሰብዓ ሊቃናትን ስለሆነ ከእነዚህ መጸሕፍት ጠቅሰዋል፡፡
በመሠረቱ ግን አንድ መጻሕፍ ተቀባይነት እንዲገኝ በሐዲስ ኪዳን መጠቀስ የግድ የለበትም፡፡ ለምሳሌ፡- እነ መጽሐፈ
አስቴር፣ መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን፣ መጽሐፈ መክብብ፣ መጽሐፈ ሩት፣ መጽሐፈ መሳፍንትና 1 ኛ ዜና መዋዕል በሐዲስ
ኪዳን አልተጠቀሱም ነገር ግን ከቀኖና ገብተው ተቆጥረዋል፡፡ ይህም ቢሆን እንኳን መጻሕፍቱ ተጠቅሰዋል፡፡
ለምሳሌ፡-
ይሁዳ 1፡14 ላይ ያለው ኃይለ ቃል በመጽሐፈ ሄኖክ 1፡9 ላይ ተጠቅሷል፡፡
ጦቢት 7፡4-16 እና ማቴ 7፡12
ተረፈ ኤርሚያስ 7፡13 እና ማቴ 27፡9
ሲራክ 11፡18-19 እና ሉቃ 12፡19-20
ኢትዮጵያዊቷ ንግሥት ማክዳ /ንግሥተ ሳባ 1 ኛ ነገ 10፡1-13፣ ንግስተ አዜብ ማቴ 12፡42 ሉቃ 11፡31/ በአንድ
አምላክ የምታምን ንግሥት እንደ መሆኗ መጠን የጠቢቡ ሰለሞንን ጥበብ ለማድነቅ ወደ ኢየሩሳሌም
በተጓዘች ወቅት ‹‹በአምላክህ በእግዚአብሔር ፊት ንጉሥ እንድትሆን በዙፋኑ ያስቀመጥህ ዘንድ የወደደህ
አምላክህ እግዚአብሔር ቡሩክ ይሁን›› በማለት አመሰግናለች፡፡ የመጻሕፍተ ሰሎሞን ወሲራክ ትርጓሜ
መግቢያ እንደሚያስረዳን የንግሥተ ሳባ ልጅ ቀዳማዊ ምኒሊክ ከአባቱ ከሰሎሞን ዘንድ የሦስት ዓመት
ቆይታውን ፈጽሞ ሲመለስ ከሄኖክ ጀምሮ እስከ ሰሎሞን ያሉ መጻሕፍትን እንዲሁም 318 ሌዋውያን ይዞ
በመምጣቱ መጽሐፍ ቅዱስ ለመጀመሪያ ጊዜ ከዕብራይስጥ ወደ ግእዝ ቋንቋ በ 982 ቅ.ል.ክ ሊተረጎም
ችሏል፡፡
ከዕብራይስጥ ወደ ግእዝ በተመለሱት መጻሕፍት ላይ አንዳንድ የዕብራይስጥ ቃላት በቁማቸው
መግባታቸው በተለይም በመጽሐፈ ነገሥት መደጋገማቸው ከዕብራይስጥ ወደ ግእዝ የተመለሱ ለመሆናቸው
ማስረጃዎች ናቸው፡፡ ለምሳሌ፡
አዶናይ- ጌታ ኤሎሄ-አምላክ ጸባዖት-አሸናፊ
ከሰሎሞን መጻሕፍት በኋላ ቀጥሎ ወደ ኢትዮጵያ የገባው መጽሐፈ ዳንኤል ነው፡፡ ይህም በ 4905 ዓ.ዓ
እስራኤላውያን በባቢሎን ተማርከው ፋርስ ባቢሎን ከወረዱ በኋላ የኢትዮጵያ ንጉሥ አይሹር ለፋርስ ንጉሥ
ዳርዮስ ስለ እስራኤል አማላጅነት በላከው ሰው አማካይነት እስራኤላውያን ጽፈው የላኩት ነው፡፡ ይህንንም
የዳንኤል መጽሐፍ ተቀብለው በሰሎሞን ጊዜ ከመጡ መጻሕፍት ጋር ደርበውታል፡፡
ከምርኮም መልስ ዘሩባቤል በእስራኤል በነገሠ ጊዜ የኢትዮጵያን ንጉሥ ከእናንተ ያሉትን መጻሕፍት
ላኩልን እኛም እዚህ ያሉትን እንልክላችኋለን ብሎ ጠይቆ እነዚያ የቀሩትን የነቢያት መጻሕፍት እነዚህም
ከሄኖክ ጀምሮ እስከ ሰሎሞን የነበራቸውን መጻሕፍት ሁሉ ልከውላቸዋል፡፡
ኢትዮጵያውያን ክርስትናን ከመቀበላቸው በፊት በቋንቋቸው ቅዱሳት መጻሕፍትን ተርጉመው
ይመሩባቸውና ይጠቀሙባቸው እንደነበር የኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ታሪክ ያስረዳናል፡፡ (ሐዋ 8፡26-40) በዚያን
ዘመን የነበረችው ንግሥት (ሕንደኬ) ገርሳሞት አገልጋይ የነበረ ሲሆን በሠረገላው ውስጥ ተቀምጦ የትንቢተ
ኢሳይያስን መጽሐፍ ያነብብ ነበር፤ በእርሱም አማካይነት በ 34 ዓ.ም ኢትዮጵያ ሕገ ወንጌልን ተቀብላለች፡፡
ሆኖም ግን የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት ወደ ኢትዮጵያ የገቡት በ 4 ኛው መ.ክ.ዘ በአባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን
አማካይነት ወደ ግእዝ ተተርጉመው ነው፡፡ በእርግጥ የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትም በዚህ ዘመን ተተርጉመዋል፡፡
ምክንያቱም የጥንቱ የግእዝ ፊደላት ከአባ ሰላማ በፊት እንደ አሁን ስላልነበሩ ፊደሉ ሲስተካከል
መጻሕፍቱም እንደ ገና ተተርጉመዋል፡፡
ኋላም በ 5 ኛው መ.ክ.ዘ ወደ አገራችን የመጡት ተሰዓቱ ቅዱሳት (ዘጠኙ ቅዱሳን) የሐዲስ ኪዳን
መጻሕፍትን በሙሉ ወደ ግእዝ ቋንቋ ተርጉመዋል፡፡
የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም በኢትዮጵያ
የአማርኛ ትርጉም
መጽሐፍ ቅዱስ ከላይ እንደተጠቀሰው ወደ ግእዝ ተተርጉሞ ሲሠራበት ለረጅም ዓመታት ቆይቷል፡፡ በኋላም ግእዝ ሕዝባዊ ቋንቋ መሆኑ እየቀነሠ
ሲመጣና የሚያነቡት ሆነ የሚረዱት የቤተ ክርስቲያን ምሁራን ብቻ በመሆናቸው በ 17 ኛው ምዕተ ዓመት ጀምሮ የመጽሐፍ ቅዱስ ዘሩ ግእዝ ቢሆንም
የአንድምታ ትርጓሜው ግን በአማርኛ እንዲሆን ተደርጓል፡፡
ከዚህ በኋላ ግን መጽሐፍ ቅዱስን ሙሉ በሙሉ ወደ አማርኛ በአባ አብርሃም (አባ ሮሜ) በተባሉ መነኩሴ ተተርጉሟል፡፡ እኚህ አባት የ 28
ዓመት ወጣት እያሉ በግብጽ ወደ ኢየሩሳሌም ጉዞ አደረጉ፡፡ በኢየሩሳሌም ቅዱሳት መካናትን ከተሳለሙ በኋላ ወደ ሶርያ፣ አርመን፣ ፋርስና ሕንድ ሄዱ፡፡
ከሕንድ ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱም 50 ዓመት ሞልቷቸው ነበር፡፡ በዚህ የተነሣ አባ አብርሃም የዐረብ፣ የፋርስ፣ የኢጣልያ፣ የግሪክና የሌላም ሀገር ቋንቋ
ተናጋሪ ነበሩ፡፡
እኚህ አባት ዳግም ገዳማተ ግብጽን ለመጎብኘት ወደ ግብጽ ሄዱ፡፡ በዚያም በግብጽ የፈረንሳይ ኤምባሲ ምክትል ቆንጽላ የነበረ አስሊን የተባለ
ፈረንሳዊ ወዳጅ ነበራቸው፡፡ ይህ ሰው የአባ አብርሀምን ሊቅነት ስለተረዳ መጽሐፍ ቅዱስን ወደ አማርኛ እንዲተረጉሙ ምክር ለገሳቸው፡፡ አባ አብርሃምም
ምክሩን ተቀብለው በ 10 ዓመት ውስጥ የትርጉም ሥራውን በእጅ ጽሑፍ ሠርተው ጨርሰዋል፡፡ የተረጎሙት የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ የገጽ ብዛት 9539
ነበር፡፡ አባ አብርሃም ትርጉመን ከጨረሱ በኋላ በመጋቢት ወር መጀመሪያ በ 1811 ዓ.ም በኢየሩሳሌም ዐርፈዋል፡፡
የትረጉም ሥራው በቁም ጽሕፈት የተጻፈ እጅግ ውብ ነበር፡፡ ይህንንም ሥራ የእንግሊዝ የመጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር ከአስሊን እጅ ገዝቶ በተለያዩ
የቋንቋ ባለሙያዎች ካስመረመረ በኋላ በ 1816 ዐራቱን ወንጌላትን፣ በ 1821 ሙሉ ሐዲስ ኪዳንንና በ 1832 ደግሞ ሙሉውን መጽሐፍ ቅዱስ
አሳትሟል፡፡16
የትግርኛ ትርጉም፡- የትግርኛ መጽሐፍ ቅዱስ በአለቃ ተወልደ መድኅን ገብሩ ከ 1861-1952 ዓ.ም ተተርጉሟል፡፡ አለቃ ተወልደ መድኅን በትግራይ ውስጥ
የማይ ማሻም ተወላጅ ነበሩ፡፡ በትርጉም ሥራም ሲውዲዊቷ ዊንክቪስት አማካሪያቸው ነበረች፡፡ የሐዲስ ኪዳኑ ትግርኛ ትርጉም በ 1901 ዓ.ም ታትሟል፡፡
17
አለቃ ተወልደ መድኅን ትግርኛ፣ ትግረ፣ ግእዝ፣ አማርኛ፣ ዐረብኛ፣ ዕብራይስጥ፣ ጣልያንኛ እና ሲውድንኛ ያውቁ እንደነበር ሊቃውንት ያስረዳሉ፡፡
የኦሮምኛ ትርጉም፡- መጽሐፍ ቅዱስን ወደ ኦሮምኛ የተረጎሙት የወለጋው ተወላጅ አናሲሞስ ነሲቡ ናቸው፡፡ የትርጉም ሥራውን ሲሠሩ አስቴር ገኖም
የቅርብ ረዳታቸው ነበሩ፡፡ የሐዲስ ኪዳን ኦሮምኛ መጽሐፍ ቅዱስ በ 1886 ዓ.ም ታትሟል፡፡ የብሉይ ኪዳኑ የትርጉም ሥራ በ 1890 ዓ.ም ተፈጽሞ
18
በ 1891 ዓ.ም ሙሉው የኦሮምኛ መጽሐፍ ቅዱስ ታትሟል፡፡
16
የመጽሐፍ ቅዱስ መግቢያ ክፍል አንድ፤ በዲን ኅሩይ ባዬ ፤ገጽ 78
17
ዝኒ ከማሁ
18
ዝኒ ከማሁ፤ ገጽ 79
ሀገሪቱ ከምድረ ግብጽ በዐረብ ምድረ በዳ /የሲና ምድረ በዳ ከታናሷ እስያ በታወርስ ሸንተረር
ትሄዳለች፡፡ የሀገሪቱ አቀማመጥ ከሰሜን ወደ ደቡብ ሲቃኙት እነደሚከተለው ነው፡፡ በስተምዕራብ በኩል
ከሜዲትራንያን /ታላቁ ባሕር/ ድረስ ተራሮች ይታያሉ፡፡ ከዚያም ቀጥሎ በዮርዳኖስ ሸለቆ የተከፈሉ ሁለት
ሸንተረሮች ይገኛሉ፡፡ የኢዝራኤል ሜዳ ደግሞ ምዕራባዊውን ሸንተረር ለሁለት በመክፈል የዮርዳኖስን ሸለቆ
ከባሕር ዳር ከሚነሳው ሜዳ ጋር ያገናኘዋል፡፡
ሄኖቭ እየተባለ የሚጠራው ደቡባዊ ክፍል በአብዛኛው ደረቃማ ሲሆን በቤርሳቤህና በኤውሳጥ ሰላጤ
መካከል ይገኛል፡፡ የሀገረ እስራኤል መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ መጣም ከሚያስደስቱ የዓለም ገፅታዎች
መካከል ይፈረጃል፡፡ ውብ ከሆነው አቀማመጧ በላይ ሃይማኖታዊ ጸጋ ሲታከልባት ልዩ ስፍራ እንዲሰጣት
ያደርጋታል፡፡
በዋናነት እስራኤል ስለሚከተሉት ምክንያቶች ተመረጠች
ሀ. ማዕከላዊ ምድር በመሆኗ
እስራኤል ከዓለም መልክአ ምድራዊ አቀማመጥ አንፃር ስትታይ በመካከል ያለች ሀገር ናት፡፡
የመካከለኛው ምሥራቅ ሀገሮች ተብለው ከሚጠሩት ሀገሮች መካከል አንዷ መሆኗ እውነታውን
ያጠናክረዋል፡፡ ይኸውም በኬክሮስ እና በኬንትሮስ መሥመሮች አኳያ ሳይሆን ለተለያዩ ሀገሮች ካላት
ማዕከላዊነት አንፃር ነው፡፡ ይኸው ማዕከላዊነቷ በመጽሐፍ ቅዱስ ተነግሮላታል፡፡ መዝ 73፡12 ‹‹ እግዚአብሔር
ግን ከዓለም አስቀድሞ ንጉሥ ነው፣ በምድርም መካከል መድኃኒትነትን አደረገ›› ተብሎ እንደተጻፈ፡፡ ይህም
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በኃጢያት ለጎሰቆለው ለአዳምና ለልጆቹ በቀራንዮ የፈፀመውን
መድሀኒትነት ነው፡፡
ማቴ 12፡42 ‹‹የሰሎሞንን ጥበብ ለመስማት ከምድር ዳር መጥታለችና›› ብሏል ኢትዮጵያቷን ንግስት
ሳባ ሲያመሰግናት፣ ‹‹ከምድር ዳር መጥታለችና›› የሚለው ሐረግ የእስራኤልን ማዕከላዊነት ያመለክታል፡፡
በማዕከላዊነቷም በጥንት ጊዜ ለበርካታ ዓመታት የንግድ የሥልጣኔ መናኸሪያ ሆና ቆይታለች፡፡
አፍሪካን፣ እስያን፣ አውሮፓን የምታገናኝ በመሆኗ ታላላቅ አውራ ጎዳናዎች ይገኙባት ነበር፡፡ ዘፍ 37፡28
ለ. አጽመ አዳም ያለበት በመሆኗ
አዳም ከገነት እንደ ተሰደደ የመጣው ወደ መሬት ነው ዘፍ፡፡ 3፡23 በምድረ በዳ ላይ ለዘጠኝ መቶ ሠላሳ
ዓመታት ከኖረ በኋለ ሞተ፡፡ ከዚህ በኋላ ልጆቹ አጽሙን እንደ ታቦት አድርገው መሠዋዕት፣ ጸሎትን ያቀርቡ
ነበር፣ ይህ ሲያያዝ ከኖኅ ዘመን ደረሰ፡፡ ኖኅም ወደ መርከብ ሲገባ አጽመ አዳምን ይዞት ገባ፡፡ ከጥፋት ወኃ
በኋላ ኖኅ ሴምን ጠርቶ አጽመ አዳምን ወስደጅ እግዚአብሔር ካዘዘው ቦታ አኑረው አለው፤ ሴምም
መልከጼዴቅን ከእናቱና አባቱ አሰናብቶ አጽመ አዳምን አሲዞ አብረው ሄዱ፡፡ ከዚያም መላዕክት እየመሯቸው
ቀራንዮ ደረሱ፡፡ ከቀራንዮም በኋላ የክርስቶስ መስቀል ከሚተከልባት ቦታ ላይ ሲደርስ ምድር ተከፈተችለት፡፡
በዚያም አጽመ አዳምን አስገብቶ አኖረው፤ መልከፄዴቅንም ጠብቅ ብሎት ተመለሰ፡፡ መልከፄዴቅም አጽመ
አዳምን እንደ ታቦት አድርጎ መሥዕዋት እና ጸሎት ያቀርብ ነበር፡፡ የአዳምን ሞት ሊሞትለት የመጣውን ሰው
የሆነውን አምላክ አጽመ አዳም በተቀበረበት ሥፍራ ላይ ካሣ ከፈለለት፡፡ የአዳም መቃብር በሆነችው ስፍራ
ካሣ ሊከፍል ይገባው ነበርና ወልደ አምላክ ሀገረ እስራኤልን መረጠ፡፡
ሐ እግዚአብሔር ለቅዱሳን አባቶች ለአብርሃም፣ ለይስሐቅ እና ለያዕቆብ ስለገባው ቃልኪዳን
የመጽሐፍ ቅዱስን የአፃፃፍ ይዘት እና ጠባይ ያልተረዳ ሰው በቀላሉ ትክክለኛውን ምስጢር ለመረዳት
ያስቸግረዋል፡፡ ያለ ስህተትና ያለ ጭንቀት ለማነበብና ለመረዳት የቋንቋውን ጠባይ በሚገባ ተንትኖ
ሁኔታውን ተገቢ ነው፡፡ ስለሆነም በአጠቃላይ መልኩ ጥቂት የመጽሐፍ ቅዱስ የቋንቋ ጠባያትን
እንደሚከተለው እንመልከት፡፡
ሕዝባዊነት
መጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈው ሁሉን ባቀፈና ባገናዘበ፣ ትውልድንም ሁሉ በሚታደግ መልኩ ነው፡፡
የእግዚአብሔር ቃል በመሆኑ ቀድሞም የነበሩትን አሁንም ያሉትን ወደ ፊትም የሚኖሩትን ሕዝቦች
ያጠቃልላል፡፡ ስለሆነም ማንኛውም የእግዚአብሔር ፍጥረት ሁሉ ለራሱ ምግብ የሚሆነውን ሃይማኖቱን
ለማጽናትም ሆነ ምግባሩን ለማስፋፋት ሕዝባዊ ሆኖ የተፃውን መጽሐፍ ቅዱስ በአግባቡ የመረዳትና
በአክብሮት የመቀበል መንፈሳዊ ኃላፊነት ግዴታ አለበት፡፡ ‹‹ ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ
እንጂ በእንጀራ ብቻ አይደለም›› እንዲል ማቴ 4፡4፤ ነቢዩ ‹‹ የዚህ የሕግ መጽሐፍ ….ከአፍህ አይለይ፣ ነገር
ግን የተጻፈበትን ሁሉ ትጠብቅና ታደርግ ዘንድ በቀንም በሌሊትም አንብበው፤ የዚያን ጊዜም መንገድህ
ይቃናልሀልና አስተዋይም ትሆናለህ፡፡››…………………..
ክስተታዊ ነው
መጽሐፍ ቅዱስን በማስተዋል ከተመለከትነው ቋንቋው በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ከሚገልጠው
ነገር ጋር ይዛመዳል፡፡ ማቴ 10፡42 ‹‹ ነብይን በነብይ ስም የሚቀበል የነቢይን ዋጋ ይወስዳል፣ ማንም ከእነዚህ
ከታናሾቹ ለአንዱ ቀዝቃዛ ውኃ ብቻ በደቀመዝሙር ስም የሚያጠጣ እውነት እላች…ለው ዋጋው
አይጠፋበትም፡፡›› በማለት የገለፀውን በአጽንዖት መረዳት ካልተቻለ ለአንዲት ጽዋ ውኃ
…………………….. ልናቃልል ወይንም ቦታ ላንሰጥ እንችል ይሆናል፡፡ ዮሐ 2፡1-11 በቃና ዘገሊላ
የተፈፀመውን ተአምር መረዳት ያስፈልጋል፡፡
የምንባቡ ሥነ ጽሑፍ የአጻጻፍ ባሕርይ
የምንባቡ የሥነ ጽሑፍ አጻጻፍ ባሕርይ ምንድነው? ምን አይነት የአፃፃፍ ዘዴ የተከተለ ነው? ወዘተ
የሚለውን አጠቃላይ ሁኔታ መዳሰስ ይገባል፡፡ የመጽሐፍ ቅዱስ ሥነ ጽሑፋዊ አጻጻፍ ስልት በአራት ዋና ዋና
ክፍሎች ይከፈላል፡፡ እነዚህም፡
1. ትረካዊ አጻጻፍ፡- ታሪኮችን በዘገባ መልኩ ያቀርባል፡፡ ለምሳሌ፡ መጽሐፈ ሳሙኤል፣ የሉቃስ ወንጌል፣
የሐዋርያት ሥራ…ወዘተ
2. ሥነ-ግጥማዊ አጻጻፍ፡- መጽሐፈ ኢዮብ፣ መኃልየ መኃልየ ዘሰሎሞን፣ መ. ጥበብ፣ መ. ተግሳፅ፣መ.
ዳዊት፣ መ. ሲራክ፣ መ. ምሳሌ …ወዘተ
3. ትምህርታዊ አጻጻፍ፡- ዶግማ፣ ቀኖና እና ትውፊትን በትንቢትና በትምህርት መልክ ያሳየናል፡፡ ለምሳሌ፡
ት. ኢሳይያስ፣ ት. ዘካርያስ፣ የጴጥሮስ፣ የዮሐንስና የጳውሎስ መልእክታት
4. ራዕያዊና ሕልማዊነትን የያዘ አጻጻፍ ስልት፡- ለምሳሌ፡ ት. ሕዝቅኤል፣ ት.ዳንኤል፣ ት. ኢዩኤል፣ ራዕየ
ዮሐንስ በዋናነት የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ በትንቢተ ሕዝቅኤል 44፡1-8 ‹‹ ወደ ምሥራቅም ወደ
ሚመለከተው በስተውጭም ወዳለው ወደ መቅደሱ በር አወጣኝ፣ ተዘግቶ ነበር፡፡ እግዚአብሔርም ይህ
በር ተዘግቶ ይኖራል እንጂ አይከፈትም፤ ሰውም አይገባበትም የእስራኤል አምላከ እግዚአብሔር
ገብቶበታልና ተዘግቶ ይኖራል፡፡ አለቃው ግን እርሱ በእግዚአብሔር ፊት እንጀራ ይበላ ዘንድ
ይቀመጥበታል፤ በበሩ ደጅ ሰላም መንገድ ይገባል፤ በዚያም መንገድ ይወጣል፡፡ ›› የሚለው መልእክት
በቂ ማስረጃ ነው፡፡
የመጽሐፍ ቅዱስ ባህል
መጽሐፍ ቅዱስ የራሱ የሆነ ባህል አለው፡፡ ይኸውም ባህል መጽሐፉ የተጻፈላቸውን ሰዎች ወይም
የጽሐፊውን ሁኔታ የሚያመለክትበት ጊዜ አለው፡፡ በዓለም ላይ የተለያየ ባህል ያላቸው በርካታ ሕዝቦች አሉ፡፡
እነዚህ ሁሉ ግን በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚያገ…ቸው ባህሎች ከእነርሱ ባህል ጋር ለማመሳሰል መሞከር
የለባቸውም፤ ምክንያቱም በተጻፈበት ጊዜ ከነበሩት ሁኔታዎች ጋር አብሮ የሚሄድ ስለሆነ ነው፡፡ ስለዚህም
የመጽሐፍ ቅዱስ ባህል ያልነው በወቅቱ የተጻፈላቸውን ሰዎች እና የጸሐፊዎቹን አካሄድ ነው፡፡ የአንዱ ሕዝብ
ባሕል ከሌላው ጋር ሊመሳሰልም ይችላል፡፡ ለምሳሌ፡ ‹‹ወንድም›› የሚለው ቃል በመካከለኛው ምሥራቅ
እና በኢትዮጵያ ያለው ትርጉም አንድ አይነት ሲሆን በምዕራባውያን ዘንድ ያለው ትርጉም ደግሞ ሌላ ነው፡፡
ስለዚህም በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ‹‹ወንድም›› ሳይጨበጥ ይቀራል፤ ምክንያቱም መጽሐፍ ቅዱስ
በአብዛኛው የሚያንፀባርቀው የመካከለኛው ምሥራቅን ባህል ነው፡፡
1. የዕብራዊያን ስም አወጣጥ
በዕብራውያን ዘንድ ስም ጠባይን ግብርንና ሁኔታን እንደሚገልጥ ሆኖ ይሰየማል፡፡ ከዚህም የተነሣ
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ተጠቅሰው የምናገኛቸው አብዛኛዎቹ የእስራኤላውያን ስሞች ከመጠሪያነት
በተጨማሪ ሌሎች ብዙ ጉዳዮችን የሚያመለክቱ ናቸው፡፡ ዕብራውያን ለልጆቻቸው ለቦታዎች ስም ሲያወጡ
በወቅቱ /ስሙ ሲወጣ/ በሀገራቸው በቤታቸው ወይም በግላቸው ተከስቶ ከነበረ ሁኔታ ጋር በማዛመድ ነው፤
ይህም ያንን ጊዜ እና ሁኔታ እንዳይረሱት ያደርጋቸዋል፡፡ ደስታን፣ ሀዘንን፣ ጦርነትን፣ ስደትን፣ ታሪካዊ
ክስተቶችን እግዚአብሔር ያደረገላቸውን ወይም ሌላ ነገርን ሊያመለክት ይችላል፡፡ ለአብነት ያህል
የሚከተሉትን እንመልከት፡
1.1 ለሰዎች የሚሰጥ ስያሜ
ያዕቆብ፡ ትርጉሙ ተረከዝ ይይዛል ማለት ነው፡፡ ይህም በተወለደ ጊዜ የመንትያው የዔሣውን ተረከዝ ይዞ
በመወለዱ የተሠጠው ስም ነው፡፡ ዘፍ 25፡26
ሙሴ፡ ትርጉሙ ከባሕር የወጣ ማለት ነው፡፡ ‹‹እኔ ከውኃ አውጥቼ…ለውና ስትልም ስሙን ሙሴ ብላ
ጠራችው፡፡›› ዘጽ 2፡10፣ ዘጽ 1፡15-22
ምናሴ፡ ትርጉሙ ማስረሻ ማለት ነው፡፡ ‹‹ ዮሴፍም የበኵር ልጁን ምናሴ ብሎ ጠራው እንዲህ ሲል፤
እግዚአግሔር መከራዬን ሁሉ የአባቴንም ቤት አስረሳኝ ›› ዘፍ 41፡51 ዮሴፍ ይህንን ስም ለልጁ ሲሰጠው
የራሱን ታሪክ በማስታወስ ነው፡፡
ኤፍሬም፡ የዮሴፍ ሁለተኛ ልጅ ሲሆን ትርጉሙም ማፍራት ማለት ነው፤ ዮሴፍ ‹‹እግዚአብሔር
በመከራዬ አገር አፈራኝ›› ሲል ያወጣለት ስም ነው፡፡ ዘፍ 41፡52
ፋሬስ፡ ትርጓሜው ጣሽ /የሚጥስ/ ማለት ነው፡፡ ለምን እንዲህ ተባለ ቢባል ሲወለድ የነበረውን ሁኔታ
ያመለከተናል፤ እናቱ ትዕማር በወለደቸው ጊዜ አንድ ለየት ያለ ሁኔታ ተከሰተ፤ ይኸውም እናትየው
መንታ ፀንሳ ነበርና በመውለጃዋ ሰዓት ከሁለቱ አንደኛው ዛራ ቀድሞ እጁን ሲያወጣ አዋላጇ የብኩርና
ምልክት የሆነውን ቀይ ፈትል በእጁ ላይ አሠረችለት፣ ነገር ግን ፋሬስ ዛራን ቀድሞ ተወለደ፡፡ በዚህም
ምክንያት እናቱ ‹‹ለምን ጥሰህ ወጣህ›› ስትል ስሙን ፋሬስ አለችው፡፡ ዘፍ 38፡29
ኢካቦድ፡ የዔሊ ልጅ የፊንሐስ ሚስት ምጥ ደርሶባት ሳለ ፍልስጤማዊያን ታቦተ ጽዮንን እንደማረኩ
ሰማች፤ ልጁንም ከወለደች በኋላ ይህንን ታሪካዊ ክስተት ለማዘከር /ለማስታወስ/ ስትል ‹‹ ክብር
ከእስራኤል ለቀቀ ስትል የሕጻኑ ስም ኢካቦድ ብላ ጠራቸው፡፡›› 1 ኛ ሳሙ 4፡21
ያቤጽ፡ ‹‹እናቱ በጣር ወልጄዋለሁና ብላ ስሙን ያቤጽ አለቸው›› ይህም ሲወለድ የደረሰባትን ሕማም
ያመለክታል፡፡ 1 ኛ ዜና 4፡9
1.2. ለቦታዎች የሚሰጥ ስያሜ
ቤቴል፡ ከሁለት የዕብራይስጥ ቃላት የተገኘ ሲሆን እነርሱም ‹‹ቤት›› እና ‹‹ኤል›› ናቸው፤ ቤት ማለት
በአማርኛም ቤት ማለት ነው፣ ኤል ማለት ደግሞ አምላክ ወይም እግዚአብሔር ማለት ነው፤ በአንድነትም
የ/ደ/ይ/ቅ/ጊ/ቤ/ክ/ፍ/ሃ/ሰ/ት/ቤት ትምህርት ክፍል የተዘጋጀ 22
የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት
1.3.2. በትውልድ ቦታ
መጽሐፍ ቅዱስ በተመሳሳይ ስም የሚጠሩ የተለያዩ ሰዎች ስለሚኖሩት አንዱን ከሌላው ለመለየት
ከተጸውዖ /መጠሪያ/ ስማቸው በተጨማሪ የትውልድ ቦታቸውን እንደ ቅጽል ይጠቀማል፤ ለአብነት ያህልም፡
መግደላዊት ማርያም፡ የትውልድ ቦታዋ ሜጌደል ስለሆነ በዚህም መግደላዊት እየተባለች ትጠራለች፤
ሜጌደል በጥብሪያዶስ ባሕር አጠገብ የምትገኝ መንደር ናት፡፡ ማቴ 15፡39፣ ማር 8፡110
ቴስብያዊው ኤልያስ፡ በዚህ ስም የሚጠራው ታላቁ ነቢይ ኤልያስ ሲሆን በትውልድ ቦታው ‹‹ቴስቡ››
ቴስብያዊው በሚለው ቅጽል በ 1 ኛ ነገ 17፡1፣ 2 ኛ ነገ 1፡3-8 ተጠርቷል፡፡
ሞዓባዊቷ ሩት፡ የትውልድ ሀገሯ ሞዓብ ስለሆነ ሞዓባዊቷ እየተባለች ትጠራለች፡፡ መ.ሩት 2፡21
1.3.3 በቤተሰብ መጠራት
ዕብራዊያን በሀገራቸው ለአንድ ሰው ስም ሲያወጡ ከቤተሰቦቻቸው መካከል የአንዱን ስም
በመውሰድ ነው፡፡ ለምሳሌ፡ መጥምቁ ዮሐንስ በ 8 ኛው ቀን ዮሐንስ ከመባሉ በፊት ዘካርያስ ሊሉት አስበው
ነበር፡፡ ሉቃ 1፡ 59
ኢያሱ ወልደ ነዌ፡ የሊቀ ነቢያት ሙሴ ደቀ መዝሙር የሆነው ኢያሱ፤ ወልደ ነዌ /የነዌ ልጅ/ በሚል
ተጠርቷል፡፡ ከሌሎች በስሙ ከሚጠሩት ሰዎች ይለያል፡፡ ኢያሱ 1፡1
የእልፍዮስ ልጅ ያዕቆብ፡ ከአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት አንዱ ሲሆን በወንጌል የእልፍዮስ ልጅ ያዕቆብ ተብሎ
ተጠርቷል፡፡ ማቴ 3፡17-18፣ ሉቃ 6፡14-16፣ የሐዋ. ሥራ 1፡13-14፤ በማር 5፡40 ላይ ታናሹ ያዕቆብም በሚል
ተጠርቷል፡፡
የያዕቆብ እናት ማርያም፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ማርያም በሚለው ስም ከሚጠሩት አንዷ ስትሆን
በልጆቿ ስም ቅጽልነት የያዕቆብ እናት ማርያም ተብላ ትጠራለች፡፡ ማር 12፡40፣ ማር 16፡1፣ ሉቃ 27፡10፤
ከዚህ በተጨማሪም በዮሐ 19፡25 የቀልዮጳ ሚስት ማርያም እየተባለች በባሏ ስም ቅጽልነትም
ትጠራለች፡፡
የአነጋገር ዘይቤ
በተለያየ ቋንቋ የሚናገሩ እና በተለያየ ሀገር የሚኖሩ ሰዎች ሁሉ የየራሳቸው የሆነ ይትባሀል አላቸው፡፡
ስለሆነም በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በአብዛኛው የሀገረ እስራኤል ነዋሪዎችን የአነጋገር ዘይቤ እናገኛለን፡፡
አንድ ቃል በአንዱ ሀገር ሲነገር ካለው ትርጉም በሌላ ሀገር ሲነገር ካለው ትርጉም ጋር የማይመሳሰልበት ጊዜ
ይኖራል፡፡ ስለዚህ መጽሐፍ ቅዱስን በሚገባ ለመረዳት የሕዝበ እስራኤልን የአነጋገር ዘይቤ ጠንቅቆ ማወቅን
ይጠይቃል፡፡ ዘይቤው ከታወቀ የንግግሩን ፍሬ አሳብ ወይም መዳረሻ በትክክል ያሳያል፡፡ ቀጥለን በመጽሐፍ
ቅዱስ ከሚንፀባረቁት የዕብራዊያን የአነጋገር ዘይቤዎች ጥቂቶቹን እንመልከት፡፡
ደጊሞተ ቃል
አንድን አሳብ በቁርጠኝነት ወይም በአፅንኦት መገለጥ ሲያስፈልግ ዕብራዊያን የሚጠቀሙበት
የአነጋገር ስልት ደጊሞተ ቃል ወይም ከሚናገሩት ዐረፍተ ነገር ውስጥ አንዱን ቃል ደግሞ በመናገር ነው፡፡
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንዲህ ያሉ አነጋገሮችን በብዛት እናገኛለን፡፡ ለምሳሌ፡-
‹‹ኢየሩሳሌም ኢየሩሳሌም ሆይ ነቢያትን የምትገድል ወደ እርሷ የተላኩትነም የምትወግር፣ ዶሮ
ጫጩቶቿን ከክንፎቿ በታች እንደምትሰበስብ ለጆችሽን እሰበስብ ዘንድ ስንት ጊዜ ወደድሁ፣
አልወደዳችሁምም፡፡›› በማለት ጌታችን ሁለት ጊዜ ኢየሩሳሌም ብሎ መናገሩ የኢየሩሳሌም ልጆችን
አመጽ አፅንቶ መናገሩ ነው፡፡ ማቴ 23፡ 37
‹‹እውነት እውነት እልሃለው ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ያይ ዘንድ
አይችልም ›› ሲል ያለ ጥምቀት ጽድቅ እንደሌለ በአጽንኦት መናገሩን ያስረዳናል፡፡ ዮሐ 3፡ 3-5
‹‹ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ ክፈትልን›› ማቴ 25፡11
‹‹አምላኬ አምላኬ ለምን ተውከኝ›› መዝ 21፡1
‹‹እውነት እውነት እላችኃለው ወደ በጎች በረት በበሩ የማይገባ በሌላ መንገድ ግን የሚመጣ እርሱ ሌባ
ወንበዴ ነው፡፡›› ዮሐ 10፡1
‹‹ከ………………ጋር ምን አለኝ››
ዕብራዊያን የተጠየቁትን ነገር ለመፈፀም /ለማድረግ/ እንዳይችሉ የሚያግዳቸው ምንም ጠብ ወይም
ምንም ምክንያት እንደሌለ ለማስረዳት የሚጠቀሙበት የራሳቸው ስልት አለ፡፡ እርሱም ‹‹ ከአንተ ወይም
ከአንቺ ወይም ከእናንተ ጋር ምነ አለኝ›› የሚለው ጥያቄ አዘል አባባል ነው፡፡ በኢትዮጲያዊያን ዘንድ እንዲህ
ያለው አነጋገር/‹‹ ከአንተ ወይም ከአንቺ ወይም ከእናንተ ጋር ምነ አለኝ ››/ ምን ግንኙነት አለን የሚል
የተቃውሞ ትርጉም አለው፡፡ በዕብራዊያን ዘንድ ግን የፍቅር፣ የትህትና ወይም የታዛዥነት አነጋገረር ነው፡፡
ይህንንም ከሚከተሉት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ለመረዳት እንችላለን፡፡
የሰራፕታዋ መበለት፡- ነቢዩ ኤልያስ በምድር ላይ ዝናብ እንዳይዘንብ ሰማይን በለጎመ ጊዜ እግዚአብሔር
ኤልያስን ወደ ሰራፕታ ሂድ በዚያም አንዲት ሴት ትመግብህ ዘንድ አዘጋጅቼልሃለው አለው፡፡ ኤልያስም ወደ
ሰራፕታዊቷ መበለት ቤት ገብቶ የነበረቻትን ጥቂት ዱቄትና ጭላጭ ዘይት ባርኮ ዝናብ እስከሚመጣ ድረስ
ለ 3 አመት ተኩል ያንኑ እየተመገቡ ቆዩ፡፡ ከዚያም ነቢዩ ኤልያስ ወደ ቄርሜሎስ ተራራ (ወደ ባዕቱ) ሄደ፡፡
ነገር ግን ለዚህች መበለት የነበራት ብቸኛ ልጅ በጠና ታመመና ሞተ፤በዚያን ጊዜም ነቢዩ ኤላያስን ካለበት
ድረስ ሄዳ እነዲህ አለችው፡ ‹‹የእግዚአብሔር ሰው ሆይ ከአንተ ጋር ምን አለኝ›› ኃጢአቴንስ ታሳስብ ዘንድ
ልጄንስ ትገስፅ ዘንድ ወደ እኔ መጥተሃልን?›› አለችው፡፡ 1 ኛ 17፡18
ቅዱስ ዳዊት፡- ንጉሥ ዳዊት በኦርዮና በሚስቱ ላይ ኃጢአት በመሥራቱ እግዚአብሔር ሊቀጣው ፈለገ፡፡ በዚህ
ምክንያት ካገኘው ቅጣት አንዱ የልጁ አቤሴሎም በእርሱ ላይ መሸፈት ነው፡፡ አቤሴሎም ራሱን አንግሦ
በነበረበት ወቅት ቅዱስ ዳዊት የዱሩያ ልጆችንና ሌሎችንም አስከትሎ ሸሸ፡፡ በሽሽት ላይ እያለም ከሳኦል
ቤት የሆነ ሳሚ የሚባል ሰው በዳዊትና በተከታዮቹ ላይ እየተሳደበ ድንጋይ ወረወረ፡፡ በዚህ ጊዜ ከንጉሥ ዳዊት
ተከታዮች አንዱ የሆነው የዱሩያ ልጅ የሆነው አቢሳ በንጉሡ መሰደብና መደፈር በጣም ተናደደና ‹‹ይህ
የሞተ ውሻ ጌታዬን ንጉሡን ዳዊት ይረግማል? ልሂድና ራሱን ልቁረጠው›› አለ፡፡ በዚህ ጊዜ ንጉሡ ቅዱስ
ዳዊት እናንተ የጽሩያ ልጆች እኔ ከእናንተ ጋር ምን አለኝ እግዚአብሔር ዳዊትን ስደበው ብሎ አዝዞታልና
ይርገምኝ ለምንስ እንዲህ ታደርጋለህ የሚለው ማነው? ›› አለ፡፡ እንደገናም ‹‹እነሆ ከወገቤ የወጣው ልጄ
ነፍሴን ይሻል፤ ይልቁንም ይህ የብንያም ልጅ እንዴት ነው? እግዚአብሔር አዝዞታልና ተዉት ይርገመኝ ፤
ምናልባት በዚህ ቀን መከራዬን አይቶ ስለ እርግማኔ መልካም ይመልስልኛል አላቸው፡፡›› 2 ኛ ሳሙ 16፡9-12
ኃይለ ቃሉን በረዥሙ ማስፈር ያስፈለገው ቅዱስ ዳዊት ለምን ‹‹ከእናነተ ጋር ምን አለኝ?›› ሊል እነደቻለ
በሚገባ እንድንረዳው ነው፡፡ ቅዱስ ዳዊት እንዲህ ማለቱ የዱርያን ልጆች መሳደቡ አይደለም፣ የአብራኩ
ክፋይ የሆነው ልጁ ሲከዳው እነርሱ ግን ለእረሱ ወግነው ተከትለውታል ይልቁንም ሲሰድባቸው የማይወዱ
ናቸው፤ ታዲያ ቅዱስ ዳዊት ለምን እንደዚያ ተናገረ? ቅዱስ ዳዊት ለአቢሳ ጥያቄ መልስ ሲሰጥ ከተናገራቸው
ውስጥ ‹‹እግዚአብሔር ዳዊትን ስደበው ብሎታልና ይርገመኝ ምናልባት በዚህ ቀን መከራዬን አይቶ ስለ
እርግማኔ መልካም ይመልስልኛል ›› ያለውን ማጤን ያስፈልጋል ፡፡ የቅዱስ ዳዊት እምነት ሳሚ የሚሰድበኝ
በራሱ ተነሣስቶ ሳይሆን እግዚአብሔር ፈቅዶለት ነው የሚል ነው፤ ይህ ደግሞ ለሠራሁት ኃጢአት የሚገባኝ
ቅጣቴ ነው፡፡ አንተ ሔደህ ብትገድለው እግዚአብሔር የወሰነብኝን ቅጣት ሳልቀበል እቀራለሁ፡፡ ለጊዜው
ያዋረደኝ ቢመስልም ግን በኋላ እከብርበታለሁ፤ ይህ ደግሞ ለእኔ ጥቅም ነው፡፡ ታዲያ ይህንን ጥቅም
እንዳላገኝ የሚያደርግ ‹‹ከእናንተ ጋር ምን ጠብ አለኝ? ›› ማለት ነው፡፡
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፡- በገሊላ ቃና በዶኪማስ ቤት ሰርግ ሆነ፤ በዚህም ሰርግ ላይ ጌታችን መድሀኒታችን
ኢየሱስ ክርስቶስ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምና ደቀ መዛሙርቱ አብረው ነበሩ፡፡ ድንገት በሰርጉ
ቤት ውስጥ አስደንጋጭ ጉዳይ ተከሠተ፤ እድምተኛው ገና ሳይሸኝ የወይን ጠጁ አለቀ፡፡ በዚህ ጊዜ
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ማንም ሰው ሳይነግራት የወይን ጠጅ ማለቁን አወቀች፤ ስለሆነም
‹‹የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም›› ብላ ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስን ጠየቀችው፡፡ እርሱም ‹‹አንቺ ሴት ከአንቺ ጋር
ምን አለኝ? ጊዜዬ አልደረሰምና›› አላት፡፡ እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያምም ለአገልጋዮቹ ‹‹የሚላችሁን
አድርጉ›› አለቻቸው፤ ዮሐ 2፡4
በዚህ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ‹‹ከአንቺ ጋር ምን አለኝ? ›› የሚለው የጌታ ንግግር አገባቡ ልክ በሌሎቹ
ክፍሎች እንዳየነው ተመሳሳይ ነው፡፡ ጌታችን በዕብራዊያን የአነጋገር ዘይቤ ነው የተናገረው፤ የሐረጉ ፍቺም
እናቴ የለመንሽኝን እንዳላደርግ የሚከለክል ምን ጠብ አለኝ? ማለት ነው፡፡ እንዲህማ ባይሆን ኖሮ
እመቤታችን ለአገልጋዮቹ ‹‹የሚላችሁን አድርጉ›› ባላለቻቸው ነበር፡፡ እናትና ልጅ በንግግሩ ስለተግባቡበት
የሚቀጥለው ውኃውን ሙላትና ወደ ወይን ጠጅ መለወጥ ስለሆነ አገልጋዮቹን ወዲያውኑ ያለምንም
የሚላችሁን በሚገባ ባለመረዳት ‹‹ከአንቺ ጋር ምን አለኝ?››ስላላት እመቤታችን አታማልድም ይላሉ፡፡
ከደጋሾቹም ይሁን ከታዳሚዎቹ አንድም ሰው ስለደረሰው አስደንጋጭ ችግር ምንም ሳይተነፍሱ የልብን
አውቃ ከውርደት ከማውጣት በላይ ከቶ ምን ሊኖር ይችላል? ለዚህም መጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈው
በዕብራዊያን ነው ስለሆነም የዕብራዊያንን ባህል ይከተላል፡፡ ይህም ከኢትዮጵያውያን ባህል ጋር ፈፅሞ
አይመሳሰልም፡፡ ከላይ እንደተረዳነው ከ……ጋር ምን አለኝ? የሚለው በዕብራዊያን ዘንድ ፍቅርን ሲገልጥ
በኢትዮጵያዊያን ዘንድ ግን ጥላቻን ይገልጣል፡፡
ኃዘን
በመካከለኛው ምሥራቅ ይኖሩ የነበሩት ሰዎች ኃዘናቸውን በተለያየ መንገድ ይገልጡ ነበር፡፡ ከእነዚህም
መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፡
ልብስ መቅደድ፡- ጥንት በመካከለኛው ምሥራቅ አካባቢ የመሪር ኃዘን ምልክት ነበር፡፡ ለምሳሌ፡ ታላቁ
የእግዚአብሔር ሰው ያዕቆብ ልጆቹ ዮሴፍን ሸጠው አውሬ በላው ባሉት ጊዜ የደረሰበትን ኃዘን ልብሱን
በመቅደድ ገልጧል፡፡ ‹‹ያዕቆብም ልብሱን ቀደደ በወገቡም ማቅ ታጥቆ ለልጁ ብዙ ቀን አለቀሰ፡፡››
እንደተባለ ዘፍ 37፡ 34
አካን የተባለው ሰው እርም የሆነ ነገር በምንካቱ እግዚአብሔር ተቆጣ፤ በሁኔታውም ኢያሱ እጅግ አዘነ፡፡
ይህንንም ‹‹ኢያሱም ልብሱን ቀደደ እርሱና የእስራኤልም ሽማግሌዎች በእግዚአብሔር ታቦት ስር
…….ተደፋ፡፡›› መ.ኢያሱ 7፡6 ከዚህም እንደምንረዳው ልብስን መቅደድ ከኃዘን በተጨማሪ ቁጣንም
ያመለክታል፡፡
ታቦተ ጽዮንን ፍልስጤማውያን በማረኩ ጊዜ ‹‹አንድ የብንያም ሰው ከሰልፍ /ከጦር ሜዳ/ እየበረረ ልብሱን
ቀድዶ በራሱም ላይ ትቢያ ነስንሶ ወደ ሴሎ መጣ፡፡›› ይላል 1 ኛ ሳሙ 4፡12 ብንያማዊው ሰው ልብሱን
የቀደደው ታቦተ ጽዮን በመማረኳ እጅግ በማዘኑ ነው፡፡
ነቢዩ ኤርሚያስ በእስራኤል ላይ ስለመጣው መከራ ሲያዝን ልብሱን ቀድዶ ነበር፡፡ ‹‹ያን ጊዜ ልብሱን ፤ቀደደ
በራሱም ላይ ትቢያ ነሰነሰ፡፡›› ተብሎ እንደ ተጻፈ ተረፈ ኤር 7፡19
እስራኤላዊያን ኃዘናቸውን ለመግለጥ ከልብስ መቅደድ በተጨማሪ ሌሎች ድርጊቶችንም ያከናውኑ ነበር፡፡
ለምሳሌ፡ ያዕቆብ ኃዘኑን ሲገልጥ ማቅ ታጥቆ ነበር፤ ዘፍ 37፡ 34
ንጉሥ ሕዝቅያስም በራፋስቅያስ ድንፋታ ስለተበሳጨ እና ስላዘነ ልብሱን …..ማቅ ለብሷል፡፡ 2 ኛ ነገ 19፡1፤
ከእነዚህ በተጨማሪም ያዘኑ ሰዎች በራሳቸው ላይ ትቢያ መነሥነስ የተለመደ ነው፡፡ 1 ኛ ሳሙ 4፡12፣ 2 ኛ
ሳሙ 15፡32 ተረፈ ኤር 7፡19፣ መርዶክዮስ በመቶ ሃያ ሀገር ያሉ ወገኖች እንዲሞቱ በታወጀ ጊዜ ልብሱን ቀደደ
ማቅም ለበሰ አመድም ነሰነሰ፤ መ.አስቴር 1፡1 እንዲሁም ደረት መድቃት፣ የኃዘን መግለጫ ነው፡፡ በተለይም
በሴቶች ይፈፀማል፡፡ ሉቃ 18፡13
ራስን መላጨት፡- ራስን ሌላው የኃዘን መግለጫ ነው፡፡ መ.ኢያሱ 1፡20፤ ት. ኢሳ. 22፡12፣ 2 ኛ፣ የሐዋ ሥራ
4፡37፣ ማር 16፡1፣ ዮሐ 19፡40፣ ዮሐ 12፡3-7፣ ዮሐ 11፡44 ዘፍ 23፡4፣ ዮሐ 11፡38-41፣ ማቴ 27፡60፤ በኃዘን
ጊዜራስን መላጨት በእኛም ሀገር ያለ ባህል ነው፡፡
ዳቦ ወይም ቂጣ የሚጋገረው ከስንዴ ከገብስና ከበቆሎ ነው፡፡ እንጀራ ወይም ቂጣን በእጅ ቆርሶ
መብላት የተለመደ አመጋገብ ነው፡፡ እንደዚሁም እንጀራና ቂጣ በእጅ እየቆረሱ መስጠት ወይም መቀበል
በእንግዳ ተቀባይና በእንግዳው መካከል ሰላምና ፍቅር መኖሩን ያሳያል፤ እንደ እኛ ሀገር መጎራረስ ያለ ነው፡፡
የአስቆሮጡ ይሁዳ ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ እጅ እንጀራ ተቀብሎ ከበላ በኋላ ጌታውን አሳልፎ
በመስጠቱ ይህን የአይሁድ ሥርዓት ጥሷታል፡፡
የከብት ሥጋ በእስራኤል ዘንድ የተለመደ ምግብ ነው፡፡ ከጎመን፣ ከአትክልት ጋር ከበሰለ በኋላ በቂጣ እያጠበቁ
መመገብ የተለመደ ነው፡፡ ለማዕድ ከተሰበሰቡ በኋላ ቂጣ ቆርሶ መስጠት የፍቅር መግለጫ ነው፡፡ ጌታ ለይሁዳ
ቁራሽ አጥቅሶ ሰጥቶታል፡፡ ዮሐ 13፡26 ይህም ምንም እንኳን ይሁዳ አሳልፎ እንዲሰጠው ጌታችን ቢያውቅም
እርሱ ግን በፍፁም ፍቅር እንደሚወደው ያሳየናል፡፡ ሌላም ተወዳጅ ምግባቸው ዓሣ ነው፡፡
ከፍራፍሬ ውስጥ በእስራኤል በብዛት የሚበቅሉት በለስና ወይን ናቸው፤ እነዚህም በጣም የሚወደዱ
ሲሆን ከቂጣና ከዳቦ ጋር ይመገቧቸዋል፡፡ በምግብ ሰዓት ብዙ ውኃ መጠጣት የተለመደ ነው፡፡ ውኃ ሲጠጡ
የመጠጫውን ዕቃ በከንፈራቸው ሳይነኩ ወደ አፋቸው እንዲንቆረቆር ያደርጋሉ፡፡ የወይን ጠጅ በመጠጣትም
የሚታወቁ ሲሆን ብዙ ግን አይጠጡም፡፡
በቀን ሁለት ጊዜ ምግብ የመመገብ ልማድ አላቸው፡፡ አንደኛው ከገበያ ተመልሰው በሚያርፉበት ሰዓት
በቀትር ሲሆን በዚህም ሰዓት ቀላል ምግብ ፡ ቂጣ በወይን ጠጅ ወይም ዓሣ ሊሆን ይችላል፡፡ በሁለተኛው ጊዜ
ዋናው ምግብ የሚበላው ጀምበር መጥለቂያ ላይ ነው፡፡ ይህም ተሠርቶ ድንክ ጠረጴዛ ላይ ያደርጋል፡፡
ቤተሰቡም በማዕዱ ዙሪያ ይሰበሰቡና ይመገባሉ፡፡ ሰዎች ለማዕዱ ሲቀርቡ እንደ ክብራቸው እንደ
ዕድሜያቸው በቅደም ተከል ነው፡፡ የሕገ ኦሪት መምህራን ምንም እንኳን ድሃ ቢሆኑም ከሀብታሞች ይልቅ
ከፍተኛውን ወንበር እንዲይዙ ይደረጋል፡፡ ይህም የአቀማመጥ ሥርዓት በሀገራችን ይደረጋል፡፡
የሰዓት አቆጣጠር
በእስራኤል አንድ ቀን የሚባለው ፀሀይ ወጥታ እስክትጠልቅ ድረስ ያለውን ጊዜ ነው፡፡ ስለዚህም
የመጪው ቀን ዋዜማ በቀዳሚው ቀን ማታ ይጀምራል፡፡ ይህም ማለት አንድ ቀን የሚባለው 24 ሰዓት ያለው
ሲሆን ዕለቱ የሚጀምረው ከምሽት ነው፡፡ ለምሳሌ፡ የቅዳሜ ሰንበት ዕለቱ (ቀኑ) ከዓርብ ምሽት ይጀምራል፡፡
ለዚህም ነው ጌታችን በተሰቀለ ጊዜ ዓርብ እየመሸ ሲሄድ ‹‹ሰንበትም ሲጀምር ነበር›› የተባለው ማር 15፡54
፡፡ ለሥራም የሚሠማሩት ፀሀይዋ ስትወጣ ነው፡፡ ከቀኑ ስድስት ሰዓት ሲሆን እኩለ ቀን ይባላል፡፡ አሥራ አንድ
ሰዓት የሚባለው ፀሀይ ልትጠልቅ አንድ ሰዓት ሲቀራት ነው፡፡ ይህም ማለት ፀሀይ የምትጠልቀው አሥራ
ሁለት ሰዓት ላይ ነው፡፡
ሰርግ
የሀገረ እስራኤል ሰርግ ከፍተኛ ከበሬታ ነበረው፡፡ የመተጫጨት ውልም የሚፈፀመው በአብዛኛው
በወላጆች አማካኝነት ነው፡፡ የጋብቻው ሥነ ሥርዓት የሚፈፀመው በወንድየው ቤት ውስጥ ነው፡፡ ሙሽራው
የጋብቻው ዕለት ከቤቱ ወጥቶ ወደ ዘመድ ቤት ሄዶ ይቀመጣል፡፡ በዚህ ጊዜ መሽራይቱ ወደ እጮኛዋ ቤት ሄዳ
የሰርግ ልብስዋ….ን ለብሳ የሙሽራውን መምጣት ትጠባበቃለች፡፡ ዘመድ አዝማድ በዕለቱ በመሰብሰብ
አመሻሽ ላይ በሙሽራው ቤት ይገኛሉ፡፡ ሚዜዎቹና እድምተኞች ሙሽራው ቤት ተሰብሰበው የሙሽሮቹን
ቤተሰቦች በማሞገስ ሲጫወቱ ያመሻሉ፡፡ ከምሽቱ አምስት ሰዓት ላይ ሙሽራው ወደ ቤቱ ለመመለስ ፈቃድ
ይጠይቅና ሲፈቀድለት ለመሄድ ይነሳል፡፡ የሙሽራው አጃቢዎች መውጣት ሲጀምሩ አንዳንድ የሻማ ወይም
የኩራዝ መብራት ይሠጣቸውና እያያዙ ጉዞውን በዝግታ ይቀጥላል ሸኚዎቹ ችቦ እያበሩ ይከተላሉ፡፡
እድምተኞችም ወደ ሰርጉ ቤት ሲሄዱ የሰርግ ልብሳቸውነ ይለብሳሉ፡፡ ይህንን ካላደረጉ ደጋሹን ንቀዋል
ተብሎ እንዲወጡ ይደረጋል፡፡ ማቴ 22፡3-13
እግር ማጠብ
እስራኤላዊያን እንግዳ ወደ ቤታቸው ሲመጣ እግሩን የማጠብ ባህል ነበራቸው፡፡ እንግዳን በሚገባ
መቀበልና ማስተናገድ በዘመነ ብሉይም ሆነ በዘመነ ሐዲስ ታዝዟል፡፡ ኦ. ዘሌ 19፡34፣ ሮሜ 12፡13፣ 1 ኛ ጴጥ 4፡9
በዚህም መሠረት ለእንግዳ አቀባበል ከሚከናወኑ ሥርዓቶች አንዱ እግር ማጠብ ነው፡፡ አብርሃም የሥላሴን
እግር ያጠበው በዚሁ መሠረት ነው፡፡ ዘፍ 18፡4፣ ዘፍ 24፡32 ጌታችን ዝቅ ብሎ የደቀመዛሙርቱን እግር
ያጠበውም ማንም እንግዳ ወደ ቤታችን ሲመጣ ዝቅ ብለን እንድናገለግለው ለማሳየት ነው፡፡ ዮሐ 13፡1-10
ጌታችንን በቤቱ ያስተናገደው ፈሪሳዊው ሰምዖን እንደ እንግዳ አቀባበል ሥርዓት የጌታችንን እግር
ባለማጠቡ ተወቅሷል፡፡ ማርያም እንተእፍረት የጌታችንን እግር በአልባስፕሮስ ሽቱ እየቀባች ሳለች ስምዖን
ተቃወመ፤ ያን ጊዜ ጌታችን ‹‹እኔ ወደ ቤትህ ገባሁ ውኃ ስንኳ ለእግሬ አላቀረብክልኝም እርሷ ግን በእንባዋ
እግሬን አራሰች በፀጉሯም አበሰች፡፡›› ሲል ገልፆታል፡፡ ሉቃ 7፡44 እግርን ከማጠብ በተጨማሪ እንግዳን ስሞ
መቀበልና ራሱን ዘይት መቀባት የተለመደ ነበር፡፡ ሉቃ 7፡45-46
የበግ እረኛ
መጽሐፍ ቅዱስ በአብዛኛው በእስራኤላዊያን ባህል የተጻፈ እንደመሆኑ የበግ እረኛንም ሁኔታ
ስንመለከት ከእኛ ሀገር የተለየ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ በሀገራቸው እረኛ ከበጎች ሆኖ መንጋውን እየነዳ ነው
የሚጠብቀው፡፡ በዮሐንስ ወንጌል ላይ ‹‹የራሱንም ሁሉ ካወጣቸው በኋላ በፊታቸው ይሄዳል በጎቹም
ድምፁን ያውቃሉና ይከተሉታል፡፡›› የተባለውም ለዚህ ነው ዮሐ 10፡3 በጎች እረኛውን በድምፁ በጠሩኑና
በበትሩ ያውቁታል፡፡
‹‹በሬ የገዥውን አህያም የጌታውን ጋጣ አወቀ፡፡›› በኢሳ 1፡3 ላይ የተባለው የቃሉ ፍፃሜ ጌታ ሲወለድ
እንስሳቱ ትንፋሻቸውን ገበሩ የሚለው ቢሆንም ከብቶች የጌታቸውን ቤት ማወቅ ግን የተለመደ እንደ ሆነ
ያሳየናል፡፡
ጫማ ማውለቅ
በመካከለኛው ምሥራቅ ጫማ ማድረግ የተለመደ ነው፤ ጫማ በምድር ላይ ያለውን ማንኛውንም
ነገር የሚነካ ስለሆነ በእስራኤላዊያን ዘንድ የተናቀ ነው፡፡ መጥምቀ ዮሐንስ ስለ ጌታችን ክብር ሲናገር
‹‹የጫማውን ጠፍር ልፈታ የማይገባኝ›› ብሏል፡፡ ዮሐ 1፡27፣ ሉቃ 3፡16 ዮሐንስ የተናቀውን ነገር እንኳን
መንካት አይገባኝም በማለት የክርስቶስን ክብር መስከሯል፡፡
እግዚአብሔር ሙሴን፣ ቅዱስ ሚካኤልም ኢያሱን ‹‹የቆምክባት ስፍራ የተቀደሰች መሬት ናትና ጫማህን
ከእግርህ አውጣ፡፡›› ያላቸው ጫማ የተናቀ ነገር በመሆኑ ለስፍራው ክብር ሲባል ማውለቅ እንዲገባ
ያስረዳል፡፡ ዘዳ 3፡5፣ መ.ኢያሱ 5፡15
ከዚህም በተረፈ በጥንት ጊዜ አንድ ሰው የራሱ የሆነውን ነገር ቢሸጥ ወይም ቢለውጥ ነገሩን ለማጽናት
ወይም እርግጠኛ መሆኑን ለማሳየት የእግሩን ጫማ ያወልቅ ነበር፤ ጫማውነ ካወለቀ በኋላ ለባልንጀራው
መስጠት የተለመደ ነው፡፡ መ.ሩት 4፡7
በኵር
በኵር የግእዝ ቃል ሲሆን በዕብራይስጥ ደግሞ ቤኩራቲ ይባላል፡፡ ትርጉሙም የመጀመሪያ ልጅ ማለት
ነው፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ በኵር የሚለው ቃል ማህፀን ከፋች ማለት እንደ ሆነ ያስረዳል፡፡ ዘኁ 18፡15-16 ከአንድ
እናትና አባት የተወለዱ ሁለትና ከዚያም በላይ ልጆች ቢኖሩ ከእነዚህ መካከል የመጀመሪያ የሆነው የበኵር
ልጅ ይባላል፡፡ ይሁን እንጁ የበኵር ለመባል የግድ ተከታይ ሊኖረው አይገባም፤ ብቸኛ ልጅ ከሆነም በኵር
ይባላል፡፡ አባ ጄሮም ‹‹ብቸኛ ልጅ የበኵር ልጅ ነው፣ የበኵር ልጅ ሁሉ ግን ብቸኛ አይደለም›› ብሏል፡፡
ቃየን የአዳም (ዘፍ 4፡1)፣ ሴም የኖኅ (ዘፍ 4፡32)፣ ኩሽ የካም (ዘፍ 10፡6)፣ አብርሃም የታራ (ዘፍ 11፡27)፣
ኤሳው የይስሐቅ (ዘፍ 25፡25)፣ ሮቤል የያዕቆብ (ዘፍ 49፡2) የበኵር ልጆች ናቸው፡፡ ዕብ 1፡ 6 እግዚአብሔር
ወልድ የበኵር ልጅ እንደተባለ እንመለከታለን፡፡ ዮሐ 3፡16 ‹‹አንድያ ልጁ ነውና›› ተቀዳሚ ተከታይ የሌለው
የአብ ብቸኛ የባሕርይ ልጁ ቢሆንም ግን በኵር ተብሏል፡፡ ስለዚህ በኵር ለመባል ግድ ተከታይ መኖር
የለበትም፡፡ ዘጸ 12፡29
በባልንጀራነት፡- የቅርብ ወዳጅ ወይም ጓደኛ ማለትም ባልንጀራ ወንድም ይባላል፡፡ ምሳሌ፡ ቅ. ዳዊትና
የሳኦል ልጅ ዮናታን 2 ኛ ሳሙ 1፡26
በቤተሰብ አባልነት፡- አብርሃም ሎጥን ‹‹እኛ ወንድማማቿች ነንና በእኔና በእናንተ በእረኛህና በእረኛዬ
መካከል ጠብ እንዳይኖር እለምንሃለው፡፡›› ዘፍ 13፡8 አብርሃም የሎጥ አጎት ሲሆን የሎጥ አባት ሐራን
የአብርሃም ወንድም ነው፡፡ ዘፍ 11፡27
በሃይማኖት፡ ሮሜ 1፡13 ቅዱስ ጳውሎስ ለሮሜ ሰዎች ‹‹ወንድሞቼ ሆይ በሌሎች አሕዛብ ደግሞ
ልማድ እንደ ሆነ በእናንተም ፍሬ አግኝ ዘንድ ብዙ ጊዜ ወደ እናንተ ልመጣ እንዳሰብኩ እስካሁን ግን
እንዳልተሳካልኝ ታውቁ ዘንድ እወዳለሁ፡፡›› ፊል 1፡12፣ ፊል 3፡1፣ የሐዋ ሥራ 12፡17
አዋልድ መጻሕፍት
አዋልድ ቃሉ የግእዝ ሲሆን ትርጉሙም “ልጆች” (በአነስታይ ፆታ) ማለት ነው፡፡ አዋልድ መጻሕፍት ሲልም ልጆች
የሆኑ መጻሕፍት ማለት ነው፡፡ ልጅነታቸውም ለመጽሐፍ ቅዱስ ነው፡፡ ልጅ ከአባቱ አብራክ፣ ከእናቱ ማኅጸን ተከፍሎ
ወላጆቹን መስሎ እንደሚወጣ እነዚህም መጻሕፍትም በቅርጽ፣ በይዘት፣ በመንፈስ፣ በምስጢር እና በመሠረተ አሳብ
አሥራው መጻሕፍትን መስለው የተገኙ ናቸው፡፡ ከመጽሐፍ ቅዱስ አሳብ ና እውነታ ሳይወጡ በእርሱ ላይ ተመሥርተው
የመጽሐፍ ቅዱስን ኃይለ ቃልና ውስጠ ምስጢር ለመተርጎም፣ ለማብራራት፣ ለማተትና ለመተንተን፣ ለልዩ ልዩ የቤተ
ክርስቲያን አገልግሎት የሚውሉትን የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባቦች በአንድ ላይ ለማሰባሰብ(እንደ መጽሐፈ ግጻዌ ያሉት)፣
በመጽሐፍ ቅዱስ በተገለጸው መሠረት ተዛማጅና አስረጅ የሆኑ ነገሮችን ለማዘጋጀት፣በነቢብ የተገለጠውን በገቢር፣
በትምህርት የተሠጠውን በሕይወት ለማሳየት የሚጻፉ መጻሕፍት በአጠቃላይ አዋልድ መጻሕፍት ይባላሉ፡፡
መሠረታቸውና ቊጥራቸው
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያሉ መጻሕፍት አሥራው መጻሕፍት ይባላሉ፡፡ አሥራው ማለትም ሥሮች ማለት ሲሆን
አሥራው መጻሕፍት ማለት ደግሞ ለሌሎች መጻሕፍት ሥሮች ወይም መገኛዎች (መሠረቶች) የሚሆኑ መጻሕፍት ማለት
ነው፡፡ ስለዚህም አዋልድ መጻሕፍት በአሥራው መጻሕፍት ሥርነት የሚበቅሉ እና የሚያድጉ ቅርንጫፎች ናቸው፡፡
ስለዚህም የአዋልድ መጻሕፍት ነቅዕ እና መሠረት አስቀድመን እንደተናገርነው መጽሐፍ ቅዱስ ነው፡፡
አዋልድ መጻሕፍት ከመጽሐፍ ቅዱስ መሠረተ አሳብ ፈጽመው መውጣት የለባቸው፡፡ ከወጡ ግን ልጅ መባላቸው
ቀርቶ ዲቃላ መጻሕፍት ይባላሉ፡፡ ዲቃላ መጻሕፍት የሚባሉት በአንዳንድ ይዘታቸው መጽሐፍ ቅዱስን የሚመስሉ ነገር ግን
ከመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮ፣ በጌታችን ከተገለጠውና ከሐዋርያት ጀምሮ ሲያያዝ ከመጣው የቤተ ክርስቲያን እምነትና
ትምህርት ጋር ተቃርኖ ያላቸው መጻሕፍት ናቸው፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንም ከመሠረታዊ አስተምሮዋና እምነቷ
እንዲሁም ከአሥራው መጻሕፍት ጋር የሚቃረኑትን መጻሕፍት አትቀበላቸውም ይልቁንም ታወግዛቸዋለች፡፡ ሐዋርያው
ቅዱስ ጳውሎስ “ነገር ግን እኛ ብንሆን ወይም ከሰማይ መልአክ ከሰበከላችሁ ወንጌል የሚለይ ወንጌልን ቢሰብክላችሁ
የተረገመ ይሁን፡፡”(ገላ 1÷8) ብሏልና ከአሥራው መጻሕፍት ውጪ የምያስተምሩ ከሆነ ተቀባይነት አያገኙም፡፡
ስለዚህ ከእነዚህ ዲቃላ መጻሕፍት አዋልድ መጻሕፍትን መለየት እንድንችል የነገረ መለኰት ሊቁ የሆኑት ሕንዳዊው
ጢሞቴዎስ እነዚህን ነጥቦች ሰጥተውናል፡፡
ዓላማቸው መንግሥተ እግዚአብሔር የሆነ፣
በአሳብ ፣ በመንፈስ፣ በምስጢር፣ በነገረ መለኰት ከአሥራው መጻሕፍት እና ከቅዱሳት የቤተ ክርስቲያን ትውፊት ጋር
የማይጋጩ፣
ለክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር፣ ሞራል፣ ሕይወት፣ እና አነዋወር ተስማሚ የሆኑ፣
በቤተክርስቲያን አበው፣ ትውፊት ወይም ጉዞ ምስክር ያላቸው፣
የሚገለጠው በአዋልድ መጻሕፍት ነው፡፡ በገመድ ውስጥ ያለ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚታየው በአምፖል ሲበራ እንደሆነ ሁሉ
በአሥራው መጻሕፍት (በመጽሐፍ ቅዱስ) የሚገኝ ጥበብ ትምህርትና ምስጢርም የሚረዳው የሚገለጠው በአዋልድ
መጻሕፍት ተብራርቶ ሲታይ ነው፡፡ አንዳንድ ሰዎች የመጽሐፍ ቅዱስን ኃይለ ቃል ባለመረዳት (በራሳቸው በመተርጎም)
ወደ ምንፍቅና የሚሄዱት እነዚህን በመንፈስ ቅዱስ የተቃኙ የአባቶችን የትርጓሜ መጻሕፍት ባለ ማንበባቸው ምክንያት
ነው፡፡ ለዚህም ነው ቅዱስ ኤጲፋንዮስ “ቅዱሳት መጻሕፍትን አለማወቅ በአዘቅትና በጥልቅ ጉድጓድ ውስጥ መኖር ነው፡፡”
ያለው፤ ስለዚህም አዋልድ መጻሕፍት በጨለማ ውስጥ ከመኖር የምንድንባቸው መብራቶች ናቸውና ለእኛ እጅግ አስፈላጊ
ናቸው፡፡ ስለዚህ በአጠቃላይ የመጽሐፍ ቅዱስን መሠረተ አሳብ ለመረዳት ሆነ ለመንፈሳዊ ሕይወት እጅግ ወሳኝ ናቸው፡፡
የአዋልድ መጻሕፍት ዓይነቶች
አባቶች ቅዱሳን በመንፈሰ እግዚአብሔር እየተቃኙ የደርሷቸው እጅግ ብዙ ቅዱሳት መጻሕፍት አሉ፡፡
እነዚህ ቊጥር የለሽ መጻሕፍት አንድ በአንድ ለማየት እጅግ አስቸጋሪ ስለሆነ ከይዘታቸው አንጻር እንደሚከተለው
እንከፍላቸዋለን፡፡
1. የትርጓሜ መጻሕፍት- እነዚህ መጻሕፍት የመጽሐፍ ቅዱስን ውስጣዊ ምስጢር ለማተትና ለማብራራት መሠረታዊ
ሐሳቡንና ይዘቱን ለማትትና ለመተንተን የሚጻፉ መጻሕፍት ናቸው፡፡ የእነዘህ መጻሕፍት ይዘትም እያንዳንዱን
የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ምዕራፍና ቊጥር አንድ በአንድ የያዙትን መንፈሳዊ መልእክት የሚያስረዱ ናቸው፡፡
በተጨማሪም በተለያዩ ቅዱሳን አባቶች የተደረሱትን የጸሎትና ነገረ ሃይማኖታዊ መጻሕፍትን ለመተርጎም የሚጻፉትን
መጻሕፍትንም ያጠቃልላል፡፡ አብዛኛዎቹ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተጻፉት የትርጓሜ መጻሕፍት በስፋት የተደረሱት
በሐዲስ ኪዳን (ከክርስቶስ ልደት በኋላ) ይልቁንም ደግሞ ዘመነ ሊቃውንት ተብሎ በሚጠራው ዘመን ነው፡፡
ምክንያቱም በዚያ ዘመን የተነሡት መናፍቃን (በተለይ ግኖስቲኮች) መጽሐፍ ቅዱስን ለራሳቸው ትምህርት ይመች ዘንድ
እያጣመሙ በመተርጎማቸውና የምንፍቅና ትምህርታቸውን በመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ ለማመሳከር በመሞከራቸው ነው፡፡
ስለዚህም አበው ሊቃውንት ምእመኑን ከዚህ የሐሰት ትምህርት ለመጠበቅ በእግዚአብሔር አጋዥነትና መሪነት
አሥራው መጻሕፈትን ተርጉመዋል፡፡ ከነዚህም ሊቃውንት መካከል ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ውብ በሆነ አገላለጽ እጅግ
የሚደንቁና ጠቃሚ የሆኑ መጻሕፍትን ሲጽፍ በትርጓሜ ሥራዎቻቸውና በሊቅነታቸው የሚታወቁት እነ ቅዱስ አትናቴዎስ፣
እነ ቅዱስ ቄርሎስ፣ ሦስቱ የቀጰዶቅያ አባቶች (ቅዱስ ባስልዮስ፣ ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ፣ ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ)፣ እነ
ቅዱስ ኤጲፋንዮስ፣ እነ ሰማዕቱ ዮስጢኖስ(Justin Martyr)፣ እነ ቅዱስ ጀሮም(አባ ሄሮኒመስ) . . . እንዲሁም ሌሎች
አባቶች ተጠቃሽ ናቸው፡፡
ወደ ሀገራችን አትዮጵያ ስንመጣ ደግሞ በዜማ ሊቅነቱ የሚታወቀው ቅዱስ ያሬድ፣ በግሩም በሆነ የነገረ መለኮት
እውቀታቸውና ትርጓሜያቸው የሚታወቁት ሊቁ ቅዱስ አባ ጊየርጊስ ዘጋስጫ፣ በትርጓሜ መምህርነታቸው የሚታወቁት
መምህር ኤስድሮስ . . . እንዲሁም በተለያየ ዘመን የተነሡ ቅዱሳንና ሊቃውንት ተጠቃሽ ናቸው፡፡
ለእነዚህ መጻሕፍት እንደ ምሳሌነት የሚጠቀሱት ወንጌል ትርጓሜ፣ ሠለስቱ ሐዲሳት፣ መጽሐፈ ቅዳሴ ትርጓሜ፣
ፍትሐ ነገሥት ትርጓሜ . . . ናቸው፡፡
2. በመናፍቃን መልስ ላይ የሚጻፉ መጻሕፍት- ቅዱሳን አባቶች መጽሐፍ ቅዱስ በተለያየ የምንፍቅና ትምህርት
እንዳይበረዙ ከመጠበቃቸው በተጨማሪ ለግሪክ ፈላስፎች ሆነ ለዐላውያን በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ ለሚያነሡት ጥያቄ
መልስ የሚሆን እንዲሁም ምንፍቅናቸውን መጽሐፍ ቅዱስን በመጥቀስ ለሚያስተምሩ አወናባጅ መናፍቃን መልስ ይሆን
ዘንድ የጻፏቸው መጻሕፍት ናቸው፡፡ እነዚህም መጻሕፍት ምዕመናን በመናፍቃን የማተለያ ቃል ተስበው ቅድስት
ከሆነቸው እምነታቸው እንዳይወጡ የሚረዱ ናቸው፡፡
ለምሳሌ፡- ቅዱስ አትናቴዎስ በአርዮስ21 ላይ፣ ቅዱስ ጄሮም በሄሊቪዲየስ22 ላይ ፣ ቅዱስ ቄርሎስ በንስጥሮስ23 ላይ፣
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ በአርዮሳውያን ላይ እና የእግዚአብሔርን ሀልዎትና ጥበቃ በሚጠራጠሩ ሰዎች ላይ፣ ቅዱስ
ኤጲፋንዮስ በተለያዩ መናፍቃን ላይ፣ አባ ጊዮርጊስ በቢቱ24 እና በተለያዩ መናፍቃን ላይ የጻፉት መጽሐፍ . . . እንዲሁም
በተለያዩ ቅዱሳን አባቶች የተደረሱ ድርሰቶች ተጠቃሽ ናቸው፡፡
3. የነገረ ሃይማኖት መጻሐፍት- እነዚህ መጻሕፍት የቤተ ክርስቲያንን መሠረተ እምነት ማለትም አምስቱ አዕማደ ምስጢር፣
ሰባቱ ምስጢራተ ቤተ ክርስቲያን፣ ነገረ ማርያም፣ ነገረ ቅዱሳን . . . በአጠቃላይ ትምህርተ ሃይማኖታዊ ይዘት ያላቸውን
መጻሕፍት የሚያካትት ነው፡፡ ለምሳሌ ፡- ሃይማኖተ አበው፣ መጽሐፈ ቄርሎስ፣ ተረፈ ቄርሎስ፣ መጽሐፈ አክሲማሮስ፣
መጽሐፈ ምስጢር፣ መጽሐፈ ባሕርይ፣ እንዚራ ስብሐት፣ ተአምኆ ቅዱሳን፣ … ተጠቃሽ ናቸው፡፡
4. ገድላት፡- ገድል ለሚለው የግእዝ ቃል ብዙ ቊጥር ሲሆን ገድል የሚለው ቃል በቁሙ ሲፈታ ደግሞ ትግል፣ ፈተና፣
ውጊያ፣ ሰልፍ፣ ድልና አክሊል እስኪገኝ ድረስ የሚደክሙት ድካም፣ የሚሠሩት ሥራ የሚቀበሉት መከራ ማለት ነው፡፡
ከዚህ ጽሑፍ ዐውድ አኳያ ግን መንፈሳዊ ዜና፣ ወግ፣ ታሪክ፣ የቅዱሳንን መከራ ጸጋን ተጋድሎ የሚናገር መጽሐፍ
የሚለውን ትርጓሜ ይይዛል፡፡25 ገድል በተለያዩ ቋንቋዎች የተለያየ መጠሪያ ሲኖረው በግሪክ ሃጊዮስ {HAGIOS} ሲባል
ትርጉሙም የቤተ ክርስቲያን አባቶች ታሪክ የሚይዝ ጽሑፍ ማለት ነው፡፡ በላቲን ደግሞ አክታ {ACTA} ሲባል
ትርጉሙም ግብረ ቅዱሳን ማለት ነው፡፡26
ስለዚህ በጥቅሉ ዲን ኤፍሬም እሸቴ በ 1992 የገድላት ዘመናዊ አከፋፈልና ሥነ ጽሑፋዊ ፋይዳ በሚል ርእስ ባዘጋጀው
ጥናታዊ ጽሕፍ ላይ እንደ ገለጸው “ገድል ማለት ገድሉ የተጻፈለትን ቅዱስ የተመለከቱ ወጎችን፣ ታሪኮችን፣ ጸዋትወ
መከራዎችን የያዙ፣ የተቀበለውን ጸጋና በእርሱ ቃልኪዳን ምእመናን ሊያገኙ የሚችሉትን በረከት የሚያትት መጽሐፍ
ነው፡፡” ብሏል፡፡ ገድል በተናጥል የአንድ ቅዱስ ሆነ የብዙ ቅዱሳንን ተጋድሎ ሊይዝ ይችላል፡፡ በቤተ ክርስቲያናችን የተለያዩ
የቅዱሳንን በክርስትና ሕይወት ሳሉ ከሚመጡባቸው እና ከሚያጋጥማቸው ፈተና ጋር የሚደረግ መንፈሳዊ ተጋድሎን
የሚገልጹ “ገድለ እገሌ” እየተባሉ የሚጠሩ ብዙ ገድላት አሉ፡፡
ለምሳሌ፡- ገድለ አዳም፣ ገድለ ጊዮርጊስ፣ ገድለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት፣ ገድለ አቡነ ዜና ማርቆስ፣ ገድለ አርሴማ፣
ገድለ ሐዋርያት፣ ገድለ ሰማዕታት፣ . . . ተጠቃሽ ናቸው፡፡
5. ድርሳን፡- ይህን ቃል አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ በመዝገበ ቃላታቸው ላይ እንዲህ ብለው ፈተውታል “የተደረሰ፣ የተጻፈ፣
ቃል፣ ነገር፣ ሰፊ ንባብ፣ ረዥም ስብከት፣ ትርጓሜ፣ አፈታት፣ ከልብ የሚወጣ መዝሙር፣ ምስጢሩ የሚያጠግብ፣ ቃሉ
የሚያረካ፣ አነጋገሩ የተሳካ፣ ጣዕመ ቃሉና ኃይለ ቃሉ ደስ የሚያሰኝ፣ ልብ የሚነካ” ማለት ነው ብለዋል፡፡ ስለዘህ
ድርሳን ማለት ስለ አንድ ነገር የሚናገር የሚተነትን መጽሐፍ ሲሆን አብዛኛውን ጊዜ ለመላእክት ተሰጥቶ ይነገራል፡፡
ነገር ግን ከቃሉ ትርጉም አኳያ ለጌታ፣ ለድንግል ማርያም፣ ለሰንበት፣ . . . ሊደረስ ይችላል፡፡ በዚህም ጊዜ “ነገር”
በሚለው ፍቺው ይተረጎማል፡፡
ስለዚህም ድርሳነ ማርያም ሲል ነገረ ማርያም እንደማለት ነው፡፡ ድርሳን ከሚባሉት መጻሕፍት መካከል ለምሳሌ፡-
ድርሳነ ማኅየዊ (ስለ ጌታ ሕማም የሚናገር) ፤ ድርሳነ ሰንበት (ስለ ሰንበት ክብር ቅድስና ቃልኪዳን የሚናገር) ፤ ድርሳነ
ማርያም (ስለ እመቤታችን ልደት፣ ዕድገት፣ ጌታን ስለመውለዷ፣ ስለ ተቀበለችው መከራ፣ ስለዕረፍቷና ስለ ትንሣኤዋ፣
ስላደረገቸው ተአምራት የሚናገር)፣ ድርሳነ ሚካኤል፣ ድርሳነ ገብርኤል፣ . . . ተጠቃሽ ናቸው፡፡
6. የሥርዓት መጻሕፍት፡- በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ብዙ ሥርዓቶች አሉ፡፡ እነዚህን ሥርዓቶች ሥርዓቱ ከሚሠራላቸው
ሰዎች (ማኅበረሰብ) ተጨባጭ ሁኔታ ጋር በማዛመድ ዘረዘር ያሉ የአሠራር ፣ የአኗኗር፣ . . . ሥርዓቶችን የሚገልጹ
መጻሕፍት ናቸው፡፡ እነዚህም መጻሕፍት አብዛኛውን ጊዜ በማኅበር ለሚኖሩ መነኮሳት እና ለባሕታውያን ይጻፋሉ፡፡
21
በክርስቶስ አምላክነት ላይ ላነሣው የምንፍቅና ትምህርት የተሰጠ ምላሽ
22
የእመቤታችንን ዘላለማዊ ድንግልና አስመልክቶ ለጻፈው አጸያፊ ትምህርት የተሰጠ ምላሽ
23
በምስጢረ ሥጋዌ ላይ ላነሣው የተሳሳተ የምንፍቅና ትምህርት የተሰጠ ምላሽ
24
ቢቱ አትዮጵያዊ ሲሆን በጌታ ዳግም ምጽአት ላይ ላነሣው የምንፍቅና ትምህርት በዘመኑ የነበሩት ሊቅ አባ ጊዮርጊስ በመጽሐፈ ምስጢር ላይ መልስ ሰጥተውታል፡፡
25
አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት ገጽ 301
26
The complete book orthodox pp 161
የ/ደ/ይ/ቅ/ጊ/ቤ/ክ/ፍ/ሃ/ሰ/ት/ቤት ትምህርት ክፍል የተዘጋጀ 34
የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት
ለምሳሌ ቅዱስ ጳኩሚስ (290-346 ዓ.ም) ማኅበረ መነኮሳት የሚመሩበትን በነሐስ ሰሌዳ ላይ የተጻፈ ሥርዓተ ማኅበረ
ገዳም ከመልአክ እጅ ተቀብሎ ሥርዓት ሠርቷል፡፡
በተጨማሪ እነዚህ መጻሕፍት ምእመናን፣ ዲያቆናት፣ ካህናትና ጳጳሳት ለሚፈጽሟቸው ለእያንዳንዱ መንፈሳዊ ተግባራት
መመሪያ ይሆኑ ዘንድ የተጻፉ ናቸው፡፡ ለዚህም የሚጠቀሰው በ 318 ቱ ሊቃውንትና በሌሎች ቅዱሳን የተጻፈው ፍትሐ
ነገሥት ፍትሕ መንፈሳዊ ወሥጋዊ ነው፡፡ በአጠቃላይ የሥርዓት መጻሕፍት ከሚባሉት ውስጥ
ለምሳሌ፡- ሥርዓተ ቤተክርስቲያን በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የተደረሰ፣ ፍትሐ ነገሥት ፣ በቅዱስ ባስልዮስ ፣ በአባ
መቃርዮስ፣ በአባ ሲኖዳ እና በሌሎች የተደረሱ ሥርዓተ ገዳማት . . . ተጠቃሽ ናቸው፡፡
7. ተአምራት፡- ተአምር ማለት በእግዚአብሔር አማካኝነት ክብሩ ይገለጥ ዘንድ በወዳጆቹ በቅዱሳን እያደረ የሠራቸውና የሚያሠራቸውን ድንቅ ሥራ
ማለት ነው፡፡ ተአምራት የተባሉበትም ምክንያት ከተለመደው ነገር ወጣ ያሉ፣ ከዚያም አልፎ ከተፈጥሮ ሕግ ውጭ የሚፈጸሙ ስለሆነ ነው፡፡
በተጨማሪም የሚከተሉትን ነጥቦች የያዘ መሆን አለበት፡፡
1. በእግዚአብሔር ቸርነት የሚፈጸም
2. ሃይማኖታዊ ዋጋ ያለው
3. ትርጉም ያለው ተግባር
4. የተፈጥሮ ሕግጋትን ሊተው ወይም ሊጥስ የሚችል
ስለዚህ ቅዱስ ዳዊት እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ላይ ድንቅ ነው፡፡ (መዝ 67፥35) እንዳለ የእግዚአብሔር ድንቅ ሥራ የሚገለጥባቸውን ስሙ
የሚመሰገንባቸውን እነዚህን ተአምራት ያካተተ መጽሕፍ “ተአምር” ይባላል፡፡ በእነዚህ የተአምር መጻሕፍት ውስጥ የሚመደቡ መጻሕፍት በመጽሐፍ
ቅዱስ ውስጥ ያሉትን ተአምራት በማብራራትና በመተንተን እንዲሁም መጽሐፍ ቅዱስ መጻፍ ካቆመ በኋላ የተፈጸሙትን የተለያዩ ተአምራትን የተጸፉባቸው
መጻሕፍት ናቸው፡፡
8. የጸሎት መጻሕፍት፡- በግልና በማኅበር (የቤተ ከርስቲያን) ጸሎት የሚያገለግሉ ናቸው፡፡ እነዚህ መጻሕፍት ሰባቱ ምስጢራተ ቤተ ክርስቲያንን
ለመፈጸም ወሳኝና እጅግ አስፈላጊ ናቸው፡፡ በተጨማሪ ምእመናን ከእግዚአብሔር ጋር የሚገናኙባቸው፣ ዘመናዊ ሐኪም ባልነበረበት ወቅት በሽተኞችን
በመፈወስ፣ የተጨነቁትን በማጽናናት፣ እንዲሁም አጋንንት ያደረባቸውን ክፉ መንፈሱን ከእነርሱ በማስወገድ ለምእመናኑ ታላቅ አስተዋጽኦ
አበርክተዋል፡፡ የጸሎት መጻሕፍት ከሚባሉት መካከል
9. የጥበብ መጻሕፍት፡- እነዚህ መጻሕፍት ቅዱሳን አበው እግዚአብሔር እንደገለጠላቸው መጠን ስለ ከዋክብት፣ ስለ ካልዕ ፍጥረታት (እንስሳት፣
አራዊት፣ አዕዋፋት) ፣ ስለ አኃዝ፣ ስለ ማኅበራዊ ኑሮ፣ ስለ መድኃኒት፣ እንዲሁም ከቤተ ክርስቲያን መሠረተ እምነት ጋር ፍጹም የማይገጩ ዓለማዊ
ፍልስፍናዎችን የዘገቡባቸው መጻሕፍት ናቸው፡፡ እነዚህም መጻሕፍት ጥበብ መንፈሳዊና ሥጋዊ ተብለው ይከፈላሉ፡፡
ለምሳሌ ፡- መጽሐፈ ማትያስ (ስለ ዓለማት፣ስለ ዓለም ክብነት ... የሚናገር)፣ መጽሐፈ ፊሳሊጎስ (ሥነ ፍጥረትን ከትምህርተ ሃይማኖት ጋር
27
እያያዘ የሚያስተምር)፣ መጽሐፈ ሐዊ (ስለ ማኅበራዊ ኖሮ)፣ መጽሐፈ አቡሻኸር (ስለ ዘመን አቆጣጠርና ስለ ከዋክብት ዑደት) . . . መጻሕፍት ተጠቃሽ
ናቸው፡፡
10. የታሪክ መጻሕፍት ፡- የቤተ ክርስቲያንን ጉዞ፣ የደረሰባትን ፈተናዎች፣ የመካናትን ታሪክ በየዘመናቱ ከታሪክ አንጻር የሚተርኩ መጻሕፍት
ናቸው፡፡
27
ይህ መጽሐፍ ከኢየሩሳሌም በስተምስራቅ በኩል በሆነችው ደብረ ሲቅ በምትባል ቦታ በታላቁ አባትና ሊቅ በአንትያኩስ የተደረሰ ሲሆን ለሕፃናት
ማስተማሪያነት ብሎ የጻፈው መጽሐፍ ነው፡፡ በውስጡም የቅዱስ ጎርጎርዮስ፣ የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እና የሌሎች አባቶች አባባሎቸች በሰፊው
ይገኙበታል፡፡
ለምሳሌ፡- ጊዮርጊስ ወልደ አሚድ፣ መጽሐፈ ጤፉት፣ ክብረ ነገሥት፣ የአውሳቢዮስ የኤጲፋንዮስ እና የዮሐንስ አፈ ወርቅ የታሪክ መጻሕፍት ..
. ተጠቃሽ ናቸው፡፡
28
በብሉይ ኪዳን ጸሐፊያን ከተጠቀሱ መጻሕፍት ውስጥ የያሻር መጽሐፍ (2 ሳሙ 1፥18፣ ኢያ 10፥13) ፣ የእግዚአብሔር የጦርነት መጽሐፍ29
(1 ነገ 11፥43) ፣ የእስራኤል የነገሥታት ታሪክ መጽሐፍ30 (1 ነገ 15፥23፣ 15፥32፣ 16፥14፣ 16፥20፣ 16፥27) እና የይሁዳ ነገሥታት የታሪክ መጽሐፍ31
(2 ነገ 8፥23፣ 2፥20፣ 15፥6) ተጠቃሽ ናቸው32፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በመጽሐፍ ቅዱስ ጸሐፍያን ያልተጠቀሱ የአይሁድ ሊቃውንት በየዘመኑ
ያሰባሰቧቸው የሐተታ፣ የትርጓሜ እና የትምህርት መጻሕፍት ይገኛሉ፡፡ ለምሳሌ በረበናተ አይሁድ የተደረሰ ሚሽናህ የተባለ መጽሐፍ እና ገማራ የተባለ
የሚሽናህ ትርጓሜ ተጠቃሽ ናቸው፡፡
በሐዲስ ኪዳንም ሐዋርያት በብሉይ ዘመን የነበሩትን አዋልድ መጻሕፍት በመጥቀስ የአዋልድ መጻሕፍትን አስፈላጊነት አጽንተውታል፡፡ ለምሳሌ
ሐዋርያው ይሁዳ በኦሪት መጻሕፍት ላይ ተጽፎ የማይገኘውን ቅዱስ ሚካኤል ስለ ሙሴ ሥጋ (መቃብር) ከዲያቢሎስ ጋር ያደረገውን ክርክር
ሲናገር የጠቀሰው “ዜናሁ ለሙሴ” (The Assumption of Moses) የተባለውን የሙሴን ገድል ነው፡፡ በተጨማሪም ቅዱስ ጳውሎስ በ 2 ጢሞ 3፥8
ላይ “ኢያኔስ እና ኢያንበሬስ” ብሎ የጠራቸው የፈርዖን ጠንቋዮች ስማቸው በሙሴ የኦሪት መጻሕፍት በአንዱም አልተጠቀሰም ፤ ነገር ግን ከአይሁድ ትውፊት
መጻሕፍት ወስዶ የጻፈው ነው፡፡ ወንጌላዊው ማቴዎስም በምዕራፍ 2 ቊጥር 23 ላይ “በነቢያት ናዝራዊ ይባላል” በማለት በዓበይትም ሆነ በደቂቅ ነቢያት
ያልተጻፈ ነገር ግን በትውፊት የተገኘ ትንቢትን አስቀምጧል፡፡ ይህም አዋልድ መጻሕፍት በሐዲስ ኪዳንም ተቀባይነት እንዳላቸው በግልጥ ያስረዳል፡፡
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ስለ አዋልድ መጻሕፍት አስፈላጊነት በምሳሌ አስተምሯል፡፡ ይህም በሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 10 ላይ ተጽፎ
በሚገኘው በደጉ ሳምራዊ ታሪክ ነው፡፡ በዚህ ታሪክ ላይም አንድ መንገደኛ ከኢየሩሳሌም ወደ ኢያሪኮ ሲወርድ ወንበዴዎች ደብድበው በሞትና በሕይወት
መካከል ጥለውት ይሔዳሉ፡፡ ሌሎች እያዩት ትተውት ሲሔዱ አንድ ርኅሩኁ ሳምራዊ ግን አይቶት አዝኖለት ወደ እንግዶች ማረፊያ በመውሰድ ከጠበቀው
በኋላ በነጋታው ለእንግዶች ማደሪ ጠባቂው ሁለት ዲናር በመስጠት “ጠብቀው፣ ከዚህ በላይ የምትከስረውን ሁሉ እኔ ስመለስ እከፍልሃለው” አለው፡፡ ይህም
ምሳሌ ነው፡፡ በወንበበዴዎቹ የተመሰሉት አጋንንት ሲሆኑ ፣ መንገደኛው ደግሞ አዳም ነው፡፡ ደጉ ሳምራዊ የተባለው ደግሞ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ሲሆን
የእንግዶች ማረፊያ የተባለቸው ደግሞ ቤተክርስትያን ናት፤ ቅዱስ ዳዊት “እኔ በምድር መጻተኛ ነኝና፤ እንደ አባቶቼም እንግዳ ነኝ፡፡” (መዝ 38፥12) እንዳለ
እንግዶች የተባሉትም ምዕመናን ናቸው፡፡ ቅዱስ ሉቃስ በሐዋርያት ሥራ ላይ “በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁ ዘንድ መንፈስ
ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመበት ለመንጋው ተጠንቀቁ፡፡” (ሐዋ 20፥28) እንዳለ የእንግዶች ማረፊያ ጠባቂ የተባሉት ደግሞ መምህራን ካህናት
ጳጳሳትና ሊቃውንት ናቸው፡፡ ደጉ ሳምራዊ የተባለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለእንግዶች ቤት ማደሪያ ጠባቂ (ለቤተ ክርስቲያን መምህራን) የሰጠውን ሁለቱ
ዲናሮች ደግሞ የብሉይ ኪዳንና ሐዲስ ኪዳንን ምሳሌ እንደሆነ እንደ ቅዱስ ሳዊሮስ ዘአንጾኪያ፣ ቅዱስ አምብሮስ እና ሊቁ ኦሪገን ያሉ ታላላቅ
የቤተክርስቲያን ሊቃውንት አስተምረዋል፡፡ ሁለቱን ዲናር ከሰጠው በኋላ በዚያ ብቻ ሳይወሰን “ከዚህም በላይ የምትከስረው ሁሉ እኔ ስመለስ
እከፍልሃለሁ፡፡” ብሎታል፡፡(ሉቃ 10፥29-35) ይህም የሚያመለክተው መምህራነ ቤተክርስቲያን (ሊቃውንት) በሁለቱ ዲናሮች ማለትም በብሉይና
በሐዲስ ኪዳን መጻሕፈት ተመሥርተው የረቀቀውን አጉልተው የተሰወረውን ምስጢር ገልጠው ምእመናንን የሚያስረዱ የተለያዩ የትርጓሜ፣ የምክር፣
የተግሣጽ፣ የታሪክ፣ . . . በአጠቃላይ አዋልድ መጻሕፍትን በመጻፍ እንዲያስተምሩና የዚህም ተጨማሪ መጻሕፍትን የመጻፋቸውን የድካማቸውን ዋጋ
እንደማያጡ ይልቁንም “እኔ ስመለስ እከፍልሃለሁ” በማለት በዳግም ምጽአቱ ዋጋቸውን እንደሚከፍላቸው አስረድቷል፡፡
መጽሐፈ ነገሥት ያሉ)፣ ስለ አንድ ቅዱስ (ቅድስት) የሚናገሩ መጻሕፍት (እንደ መጽሐፈ ኢዮብ፣ መጽሐፈ ሩት ያሉት )፣ የሕግ መጻሕፍት እና ሥርዓት
(እንደ ኦሪት ዘጸአት የመሰሉ)፣ የትንቢትና የራእይ መጻሕፍት (እንደ ትንቢተ ኢሳይያስ፣ ራዕየ ዮሐንስ ያሉ)፣ የጥበብ የምስጋና እና የቅኔ መጻሕፍት (እንደ
መጽሐፈ ምሳሌ፣ መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን ያሉት)፣ የጸሎት (እንደ መዝሙረ ዳዊት ያሉት) . . . ተጠቃሽ ናቸው፡፡ እነዚህም አስቀድመን ካየነው
ከአዋልድ መጻሕፍት ዓይነት ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡ ስለዚህም ስለ ገድላት እና ስለ ተአምራት ከመጽሐፍ ቅዱስ አንጻር እንመለከታለን፡፡
1 ገድል ፡- ገድላትና መጽሐፍ ቅዱስ አንድ ዓይነት የአጻጻፍ ስልት አላቸው ይኸውም የመጀመሪያው መጽሐፍ ቅዱስ ሲጻፍ የቅዱሳኑ ታሪክ
ዋና የታሪኩ ማዕከል በማድረግ መጻፍ ሲሆን በዚህም የአብርሃም፣ የይስሐቅ፣ የያዕቆብ፣ የመልከጼዴቅ፣ የሙሴ፣ የዳዊት፣ የሰሎሞን፣ . . . ወዘተ ታሪክ
ተጽፏል፡፡ ሁለኛተው መንገድ ደግሞ በቅዱሳኑ ስም ለብቻ መጻሕፍትን መጻፍ ነው፡፡ በዚህም መጽሐፈ አስቴር፣ መጽሐፈ ሩት፣ መጽሐፈ አዮብ፣ መጽሐፈ
ዮዲት፣ መጽሐፈ ሶስናና ግብረ ሐዋርያት የመሳሰሉ መጻሕፍት ተጽፈዋል፡፡ በአዋልድ መጻሕፍትም በመጀመሪያው መንገድ የተጻፉ እንደ መጽሐፈ ገነት፣ እንደ
መጽሐፈ ስንክሳር ያሉ ስለ ብዙ ቅዱሳን የሚናገሩ መጻሕፍት ተጠቃሽ ናቸው፡፡ በሁለተኛው መንገድ ማለትም በቅዱሳኑ ስም ለብቻቸው ከተጻፉላቸው
መጻሕፍት መካከል ደግሞ ገድለ ጊዮርጊስ፣ ገድለ ፋሲለደስ፣ ገድለ አዳም. . . ተጠቃሽ ናቸው፡፡
ከሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት መካከል ከገድላት ጋር አንድ አይነት አጻጻፍ ያለው ደግሞ ግብረ ሐዋርያት ( የሐዋርያት ሥራ) ነው፡፡ ይህ መጽሐፍ
ሐዋርያት ኃይለ መንፈስ ቅዱስን በማግኘት ከዲያቢሎስ፣ ከሐሳውያን መምህራን፣ ለባለሥልጣናት፣ ከጠንቋዮች፣ እና በክርስትና መስፋፋት ጥቅማቸው
ከተነካባቸው ሰዎች ጋር ያደረጉትን ተጋድሎ ማለትም ሲታሠሩ፣ ሲገረፉ፣ ሲከሰሱ፣ መርከባቸው ሲሰበር፣ በባዕድ ሀገር ሲንገላቱ በአጠቃላይ የደረሰባቸውን
መከራ የሚናገር መጽሐፍ ነው፡፡ ይህም አጻጻፍ ከገድላት ጋር ከፍተኛ የሆነ መመሳሰል ይታይበታል፡፡
2 ተአምር፡- በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በእግዚአብሔር እንዲሁም እርሱ በፈቀደላቸው ቅዱሳን የተፈጸሙ ብዙ ተአምራት ይገኛሉ፡፡ ለምሳሌ
ሊቀ ነቢያት ሙሴ በግብጻውያን ላይ መቅሰፍት ማምጣቱና ሕዝቡን የኤርትራ ባሕርን ከፍሎ በደረቅ ማሻገሩ (ዘጸ 8፥12፣ 14፥21-31)፣ ኢያሱ ፀሐይን
በገባዖን ማቆሙ(ኢያ 10፥12-13)፣ ካህናተ ኦሪት ታቦተ ሕጉን ተሸክመው ዮርዳኖስን መክፈላቸውና በደረቅ መሻገራቸው (ኢያ 3፥1-15)፣ ሦስቱ ሕጻናት
በእቶን እሳት ውስጥ ተጥለው አለመቃጠላቸው (ዳን 3)፣ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሕቱም ድንግልና እንበለ ዘር ተጸንሶ መወለዱ፣ ውኃን ወደ ወይን
መቀየሩ፣ አላዛርንና ወለተ ኢያኢሮስን ከሞት ማስነሣቱ፣ . . . እና ሌሎች ድንቅ ተአምራቶች ተጽፈው ይገኙበታል፡፡ በአጠቃላይ ተአምርና መጽሐፍ ቅዱ
ተለያይተው አያውቁም፡፡ የተለያዩበት ጊዜም የለም፣ ሊኖርም አይችልም፡፡ ምክንያቱም ጻድቁ ኢዮብ “የማይመረመረውን ታላቅ ነገርና
የማይቈጠረውን ተአምራት ያደርጋል።” (ኢዮ 5፡9) እንዳለ እግዚአብሔር ተአምራትን አድራጊ ነውና ነው፡፡ ታዲያ በዘመነ ብሉይና ሐዲስ
እኒህን ተአምራት ያደረገ እግዚአብሔር ለሐዋርያት ቃል እንደገባው እስከ ምጽአት ከቅዱሳን ጋር ነውና ቅዱሳን አባቶቻችን በእርሱ እርዳታ ታላላቅ
ተአምራትን ያደርጋሉ፡፡ ቅዱስ ዳዊት “ተቀኙለት፥ ዘምሩለት፥ ተአምራቱንም ሁሉ ተናገሩ።” (መዝ 105፥2) እንዳለ አሥራው መጻሕፍት መጻፍ ካቆሙ
በኋላ አምላካችን እግዚአብሔር በቅዱሳን ላይ አድሮ ያደረገውን ተአምር አዋልድ መጻሕፍት ልክ እንደ መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራሉ፡፡
ምዕራፍ ሁለት
ብሉይ ኪዳን ከመጀመርያ ፍጥረት መፈጠር ጀምሮ እስከ ክርስቶስ መወለድ ድረስ የነበውን የሰዎችንና
የእግዚአብሔርን ግንኙነት የሚናገር መጽሐፍ ነው፡፡ የተጻፈው ከ 1400-400 ቅ.ል.ክ ሲሆን ሠላሳ ሁለት ያህል
ጸሐፍት ጽፈውታል፣ የተጻፈበት ቋንቋ በአብዛኛው በዕብራይስጥ ሲሆን፣ በአርማይክ ቋንቋም የተጻፉ
መጻሕፍትን አካትቶ ይይዛል፡፡ ለምሳሌ፡ ትንቢተ ኤርምያስ፣ መጽሐፈ ዕዝራ፣ ትንቢተ ዳንኤል እና
የመሳሰሉትን መጥቀስ ይቻላል፡፡
ከክርስትና በፊት በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ያለው የአምልኮ ሥርዓትና የመሥዋዕት አቀራረብ፣ የሰንበት
አከባበርና የመሰለው ሁሉ በሀገራችን ተሠርቶበታል፣ ከክርስትናውም በኋላ መጻሕፍተ ብሉያት ለሐዲስ
ኪዳን ትንቢትና ታሪክ፣ አምሳልና መርገፍ እንደመሆናቸው መጠን ከመሥዋዕዋቱና ከሥርዓተ አምልኮቱ በቀር
ሃይማኖታዊና ሥነምግባራዊ ሕጋቸውና ትእዛዛቸው፣ እንደዚሁም ትምህርታቸው ዛሬም እንደተጠበቀ ነው፡፡
በመሆኑም እነዚህ ኪዳናት የማይነጣጠሉ መሆናቸውን መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡
የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ከተጻፉበት ጊዜ፣ ከይዘታቸው አንጻርና ከአጻጻፋቸው ሁናቴ የተነሣ
1. የሕግ፣
2. የታሪክ፣
3. የመዝሙር የቅኔና የጥበብና
4. የትንቢት ክፍል በመባል በአራት ዐበይት ክፍል ይከፈላሉ፡፡
1. የሕግ መጻሕፍት
የሕግ በመባል የሚታወቁት መጻሕፍት ሊቀ ነቢያት ሙሴ በሲና ምድረ በዳ የጻፋቸው አምስቱ ብሔረ
ኦሪት ናቸው፡፡ ጥንተ ነገሩስ እንደምን ነው ቢሉ፤ ጌታ እስራኤልን ከግብጽ ካወጣቸው በኋላ ሙሴን ጠርቶ
ሕግ እሠራላችኋለሁና ወደ ደብረ ሲና ውጣ አለው፣ እሱም ሕዝቡን ለአሮንና ለሖር አስጠብቆ ግርግር
አትበሉ፤ ‹‹ነገርም ያለበት ሰው ቢኖር እነዚህ ይስሟቸው፤ ካስተማርኋችሁ ትምህርት፣ ከሠራሁላችሁ
ሥርዓት አትውጡ›› ብሎ ኢያሱን አስከትሎ ወደ ደብረ ሲና ወጣ፤ ኢያሱን ከእግረ ደብረ ትቶ እርሱ ከርእሰ
ደብር ወጣ፤ ሰባት የብርሃን መጋረጃ ተጋርዶ ነበር፣ ስድስቱን ገብቶ ከሰባተኛው ሲደርስ ቆመ፣ ስድስቱን ቀን
በስድስቱ ዕለታት የተፈጠሩ ሀያ ሁለቱን ሥነ-ፍጥረት በልቡናው ሲሥልበት ሰንብቷል፡፡ ይህንንም በደብረ ሲና
የነገረውን ጻፍ ብሎት አምስት ክፍል አድርጎ ጽፎታል፡፡ 33
ኦሪት ቃሉ የሱርስት ሲሆን ትርጉሙም ብርሃን ማለት ነው፡፡ ‹‹ሕግህ ለእግሬ መብራት፣ ለመንገዴ
ብርሃን ነው›› መዝ 118፡105 እንዲል፡፡ በዕብራይስጥ ቶራ፣ በግሪክ /ዕርእ/ ኖሞስ ይባላል፤ ትርጉሙም ሕግ
ማለት ነው፡፡ እነዚህም መጻሕፍት በመጽሐፍ ቅዱስ ‹‹የሙሴ መጻሕፍት››(1 ዕዝ 6፡18) ‹‹የሕግ
መጻሕፍት››(ገላ 3፡10) ‹‹የሙሴ ሕግ››(ሉቃ 2፡22፤ ዮሐ 1፡16) ‹‹የጌታ ሕግ››(ሉቃ 2፡23፤ 10፡16፤ ማቴ 5፣17)፡፡
33
ኦሪት ዘፍጥረት መቅድም
34
ኦሪት ዘፍጥረት መቅድም
ይህስ አይደለም ሐዋርያት በሲኖዶስ፣ ሠለስቱ ምዕት በፍትሐ ነገሥት አምስቱ መጻሕፍተ ሙሴ ብለው
ቆጥረውታል፡፡ እኛም ይህን ተከትለን አምስቱን የኦሪት መጻሕፍትን ብቻ በሕግ መጻሕፍት ሥር አካተን
እንቆጥራለን፡፡
እነዚህም መጻሕፍት እያንዳንዳቸው በዕብራይስጥ ያለው ስያሜ ከግእዙ ጋር ይለያያል፡፡ ይህም የሆነበት
ምክንያት ግእዙ የሰብዓ ሊቃናትን የመጽሐፍት አሠያየም ሲከተል ዕብራይስጡ ግን የየመጻሕፍቱን
የመጀመርያ ቃል እንደ መጽሐፉ ርዕስ አድርጎ ይወስደዋል፡፡
ከዚህ በመቀጠል የመጻሕፍቱን ስያሜና ትርጉም፣ የተጻፉበትን ዓላማ እንዲሁም አጠቃላይ ይዘታቸውን
እንመለከታለን፡፡
1. ኦሪት ዘፍጥረት /ዘልደት/
ኦሪት ዘልደት ማለት ዜና ፍጥረት (የፍጥረት ዜና) ማለት ነው፡፡ የዚህ መጽሐፍ ስያሜ የተወሰደው
ከመጽሐፉ አንደኛ ምዕራፍ መጀመሪያ ቊጥር ላይ ባለው ‹‹በመጀመርያ እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን
ፈጠረ›› በሚለው መነሻ ቃል ነው፡፡ መጽሐፉ ዘልደት መባሉ ሃያ ሁለቱን ሥነ ፍጥረት ቆጥሮ ስለሚናገር
ነው፤ ከአዳም ጀምር እስከ ዳዊት ያለውን ትውልድ እገሌ እገሌን ወለደ እያለ ልደተ አበውን ይናገራልና ነው፡፡
ዘፍ 12-26፡- ስለ አበው የእምነት ተጋድሎ፣ ስለ አብርሃም መጠራትና የእምነት ጉዞና ጽናት፣ አብርሃም
ኮሎዶጎሞርንና ከእርሱ ጋር የነበሩትን ነገሥታት ስለማሸነፉ፣ ስለ ካህኑ መልከጼዴቅና ስለ መሥዋዕት፣
ስለ ሎጥና ቤተሰቦቹ፣ የሰዶምና የጎሞራ ጥፋት፣ ቅድስት ሥላሴ በአብርሃም ቤት በእንግድነት ስለ
መገኘታቸው፣ ስለ አብርሃምና ስለ አቤሜሌክ፣ ስለ ተስፋው ልጅ ይስሐቅ ውልደትና ለመሥዋዕት
ስለመቅረቡ እንዲሁም ስለ አብርሃም እረፍት በሰፊው ያትታል፡፡
ዘፍ 27-50፡- የያዕቆብና የዔሳው ታሪከ፣ የዮሴፍ ታሪክ፣ የእስራኤልን ወደ ግብጽ መውረድ እናገኛለን፡፡
2. ኦሪት ዘጸአት
‹‹ዘጸአት›› የግእዝ ቃል ሲሆን ትርጉሙም መውጣት ማለት ነው፡፡ የዚህ መጽሐፍ ስያሜ የተወሰደው
‹‹ከያዕቆብ ጋር ወደ ግብጽ የገቡት የእስራኤል ልጆች›› ከሚለው ከመጽሐፉ መጀመሪያ ምዕራፍ ከቊጥር
አንድ ላይ ነው፡፡ ኦሪት ዘጸአት ማለት የአወጣጥ ወይም የመውጣት መጽሐፍ ማለት ነው፡፡ የእስራኤልን
ከ 430 ዓመት በኋላ ከግብጽ መውጣት ስለሚያወሳ ይህ ስም ተሰጥቶታል፡፡
ይህ መጽሐፍ በዕብራይስጥ የኦሪት ዘጸአት የመጀመርያው ቃል በሆነው ‹‹ኤልሼሞት›› ተሰይሟል፡፡
ትርጉሙም ‹‹ስሞች እነዚህ ናቸው›› ማለት ነው፡፡ ይህም የያዕቆብን ትውልድ ስም በመዘርዘር ይጀምራልና
ነው፡፡ ዘጸአት የሚለውን ስያሜ ያገኘው ከሰብዓ ሊቃናት ትርጉም በኋላ ነው፡፡
የመጽሐፉ ዓላማ
የዚህ መጽሐፍ ዋና ዓላማዎች ሁለት ናቸው፡፡ እነርሱም፡-
በገፋዕያን ላይ የተደረገው ፍትሐ እግዚአብሔር፣ ለግፉዓን የተሰጠውን ነጻነት ይናገራል፡፡
እግዚአብሔር የሰው ልጆች ምንም እንኳን በኃጢኣት ቢወድቁም የሚቀደሱበትን መንገድ
እንዳዘጋጀላቸው ይገልጻል
የሃይማኖትና የአስተዳደር ሕግ ስለተሰጠው ስለ አዲሱ ሕዝበ እግዚአብሔር ያስረዳል፡፡
የመጽሐፉ አከፋፈል
መጽሐፉ 40 ምዕራፎች ሲኖሩት፤ ለማጥናት ያመች ዘንድ በአራት ዋና ዋና ክፍሎች ይከፈላል፡፡ እነርሱም፡-
ዘጸ 1-4፡- ግብጻውያን በእስራኤል ላይ ያደረሱት ግፍና መከራ፣ ሙሴ ከልደቱ እስራኤልን ነጻ ለማውጣት
በእግዚአብሔር እስከመጠራቱ ጊዜ ያለውን ታሪክ ይተርካል፡፡
ዘጸ 5-11፡- ሙሴ፣ አሮንና እስራኤላዊያን በፈርዖን ፊት ቆመው ነጻ እንዲወጡ ስለመጠየቃቸው፣
በእስራኤላውያን ላይ የባርነት ቀንበር ስለመጥበቁ፣ በግብጻውያን ላይ ስለወረዱት 10 መቅሰፍቶች
ዘጸ 12-15፡- እስራኤላውያን ከግብጽ ወጥተው የኤርትራን ባሕር በእግዚአብሔር ኃይል ስለ መሻገራቸው፣
ግብጻውያንም በባሕር ውስጥ ሰጥመው መቅረታቸውን፣ ሙሴና የእስራኤል ልጆች በእግዚአብሔር ፊት
የምሥጋና መዝሙር ስለማቅረባቸው ይናገራል፡፡
ዘጸ 16-40፡- ሙሴ በሲና ሕግ መቀበሉን፣ ስለ ደብተራ ኦሪት አሠራር የተሰጠ መመርያ፣ ስለ አሮን ሥልጣነ
ክህነት፣ ስለ ልብሰ ተክህኖና ሥርዓተ አምልኮ፣ የእስራኤል በጣዖት ማምለክና መቀጣት፣ መና ከሰማይ
እንደወረደላቸው እናገኛለን፡፡
3. ኦሪት ዘሌዋውያን
ሌዋውያን ከ 12 ቱ የእስራኤል ነገድ የአንዱ የሌዊ ዘር ናቸው፡፡ የብሉይ ኪዳን ካህናትና ዲያቆናት
ሌዋውያን ስለነበሩ፣ ስለ ኦሪት ካህናት፣ ስለ ክህነትም ሥርዓትና አገልግሎት በሰፊው የሚገልጸው ይህ 3 ኛው
የሙሴ መጽሐፍ ዘሌዋውያን ሊባል ችሏል፤ ነገር ግን መጽሐፉ ዘሌዋውያን ተብሎ ይሰየም እንጂ ስለ
ሌዋውያን ብቻ አይናገርም፡፡
የመጽሐፉ ዓላማ
የታሪክ መጻሕፍት ተብለው የሚጠሩት ከኢያሱ ወልደ ነዌ እስከ መጽሐፈ ዮሴፍ ወልደ ኮርዮን ያሉት ሲሆኑ የመጻሕፍቱ ብዛት 17 ነው፡፡
35
በዕብራይስጡ ጽሑፋት ድርሳናት (a-kethubim) በተባለው ክፍል ውስጥ ይካተታሉ፡፡ በመጻሕፍቱ ውስጥ የምናገኘው ጠቅላላ ሐሳብ
በተለይ እስራኤላውያን የአምላካቸውን ሕግ ሲያከብሩ ሰላምና ብልጽግና ያገኙ እንደነበር፤ ከአምላካቸው ፈቃድ ሲወጡ ደግሞ ጦርነት እና
መዓት ይገጥማቸው እንደነበር ነው፡፡
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ስምና የኢያሱ ስም በዕብራይስጥ አንድ ዓይነት ትርጓሜ አላቸው፡፡ ይኽውም መድኃኒት፣ አዳኝ
ማለት ነው፡፡ ኢያሱ አዳኝ፣ መድኃኒት መባሉ የእስራኤልን ሕዝብ ከሥጋ ጠላቶቻቸው ከአማሌቃውያን በማዳኑ ምክንያት ነው፡፡
አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ቅዱስ ሥጋውን ቆርሶ ክቡር ደሙን አፍስሶ ከነፍሳችን ጠላትና ከዘለዓለም ሞት አድኖናልና
እርሱ እውነተኛ መድኃኒት ተብሏል፡፡ ሉቃ 2፡10፣ የሐ 4፡42
35
ይህ ክፍል ከነዚህ ውጪ ሌሎች መጻሕፍትን ያካተተ ክፍል ነው፡፡
ኢያሱ የተወለደው በግብፅ ነው፡፡ እስራኤላውያን ከግብጽ ከወጡ በኋላም በዘጸ 17፣9 ከአማሌቃውያን ጋር ሲዋጉ 44 ዓመቱ ነበር፡፡ ኢያሱ
ሙሴን ሲያገለግል የኖረ ሲሆን ከሙሴ ሞትም በኋላ እስራኤልን አገልግሏል፡፡ ከነዓንን ሊሰልሉ ከተላኩት ከዐሥራ ሁለቱ ሰላዮች መካከል
አንዱ ነበር፡፡ ዘጸ 24፡13፣ ዘኁ 13፡2
አብዘኞቹ የአይሁድ ምሁራን እንደሚስማሙት ከመጨረሻዎቹ አምስት ሐረጎች (ቊጥሮች) በስተቀር የመጽሐፉ ጸሐፊ ኢያሱ ነው፡፡
እነዚህን አምስት ሐረጎች (ኢያ 24፣29-33) ግን ከነቢዩ አያሱ እረፍት በኋላ አልአዛር ልጅ ፊንሐስ ጨምሯቸዋል ይባላል፡፡
36
መጽሐፉ በአጠቃላይ 31 ዓመታትን ማለትም በሙሴ ዕረፍት እና የአሮን ልጅ አልአዛር ዕረፍት መካከል ያለውን ታሪክ የያዘ
ነው፡፡ የመጽሐፉም ዋና ሐሳብ የእስራኤል ሕዝብ በእግዚአብሔር ኃይል እና በኢያሱ መሪነት የዮርዳኖስን ወንዝ ተሻግረው፣ የኢያሪኮን
ከተማ ወርረው፣ የከነዓንን ነገሥታት አሸንፈው ምድረ ርስት ከነዓንን እንደወረሱና ምድሪቷም በነገድ ኢያሱ እንዳከፋፈላቸው ይተርካል፡፡
ታሪኩ የተፈፀመው በቤተ ክርስቲያን ትውፊት 1450 ቅ.ል.ክ ባለው ዘመን ውስጥ ነው፡፡ ኢያሱ በ 110 ዓመቱ አርፎ በኤፍሬም ሀገር
ተቀብሯል፡፡ ኢያ 24፡29-31
የመጽሐፉ ዓላማ
የመጽሐፉ ዋና አሳብ የእስራኤል ሕዝብ በእግዚአብሔር ኃይል እና በኢያሱ መሪነት የዮርዳኖስን ወንዝ
ተሻግረው የኢያሪኮን ከተማ ወርረው የከነዓንን ነገሥታት ማሸነፉን ይተርካል፡፡ ታሪኩ የተፈጸመው ከ 1400-
1300 ዓ.ዓ ባለው ዘመን ውስጥ ነው፡፡
የመጽሐፉ አከፋፈል
መጽሐፉ 24 ምዕራፎች አሉት፤ በ 3 ዓበይት ክፍሎች ከፍለን እናየዋለን፡፡
ኢያ 1-7፡ የሕዝበ እስራኤል ዝግጅት፣ የዮርዳኖስ ወንዝን ስለመሻገራቸው፣ የኢያሪኮ ግንብ መፍረስ፣ ረዓብ
ሁለቱን ሰላዮች በማዳኗ ከኢያሪኮ ሕዝብ መካከል ከቤተሰቦቿ ጋር መዳኗ፣ የኢያሪኮ መያዝና
እስራኤላውያን ወደ ኢያሪኮ ሲገቡ እርም የሆነውን እንዳትነኩ የሚለውን ትእዛዝ ያፈረሰው የአካን
መቀጣትን ያነሣል፡፡
ኢያ 8-12፡ የሕዝብ እስራኤል ወደ ከነዓን መዝመት፣ ኢያሱ የከነዓንን፣ የአሞራውያንንና የአሦርን
ነገሥታት አሸንፎ ግዛቶቹን እንደያዘና ያሸነፋቸውን ነገሥታት ስም ዝርዝር ይገኝበታል፡፡
ኢያ 13-24፡ የኢያሱ የመጨረሻ ምክር ፣ ስንብትና ዕረፍት በስፋት ተገልጽዋል፡
2. የመጽሐፈ መሳፍንት
መሳፍንት ማለት አስተዳዳሪዎች፣ ፈራጆች ማለት ነው፤ መጽሐፉ ከኢያሱ በኋላ የተነሡትን የ 13 ቱን መሳፍንት የአገዛዝ ታሪክ
ስለሚተርክ መጽሐፈ መሳፍንት ተብሏል፡፡ ጸሐፊው ነቢዩ ሳሙኤል ሲሆን ከመሳፍንት ዘመን በኋላ የተነሣ ነቢይ ቢሆንም እግዚአብሔር
ያለፈውን ነገር ገልጾለት ጽፏል፡፡
ከነዓናውያን የሚያመልኳቸው የነበሩት በአል እና አስተሮት የተባሉት አማልክት በሕዝበ እስራኤላውያን ዘንድ ገብተው ይመለኩ
እና ሕዝቡን ይመርዙ ነበር፤ እስራኤላውያንም በእስራኤል ዘንደ ቋሚ አስተዳደር አልነበረም፡፡ በዘመኑ ራሱ እግዚአብሔር የሕዝቡ መሪና
አስተዳዳሪ ነበር እንጂ፤ ሆኖም ኃጢአታቸው ሲበዛ ጠላት እያስነሳ ሲቀጣቸው ምሕረት፣ ይቅርታን ሲጠይቁት ከሕዝቡ መካካል
መሳፍንትን እያስነሳ ነጻ ያወጣቸው ነበር፡፡ መጽሐፉ ከ 1380-1050 ቅ.ል.ክ. ክርስቶስ እንደተጻፈ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ይናገራሉ፡፡
በመጽሐፍ መሳፍንት ላይ ተመሳሳይ ታሪክ ይደጋገማል፡፡ ይኸውም ወረተኛ የሆኑት የእስራኤል ሕዝቦች ለጥቂት ጊዜ ያህል
እግዚአብሔርን ያመልኩና ሲደላቸው አምላካቸውን በመርሳት ወደ ጣዖታት ማምለክ ይጀምራሉ፡፡ ረድኤተ እግዚአብሔርም ከእነርሱ
ይርቃል፡፡ በዚህም በዙሪያቸው ያሉት ፍልጤማውያንና ሌሎች ሕዝቦች መጥተው ይወሯቸዋል፣ በባርነትም ይገዟቸዋል፡፡ በዚህ የመከራ
ወቅትም አምላካቸውን እግዚአብሔርን ያስታውሳሉ፤ ንስሓ በመግባትም እንዲያድናቸው ወርሱ ይጮሀሉ፡፡ ጌታችንም መሐሪ ነውና
የሚያድናቸውን መስፍን ያስነሳና ያድናቸዋል፡፡ ይህ ዓይነቱ ታሪክ በዚህ በመጽሐፍ ላይ ከ 10 ጊዜ በላይ ተጽፏል፡፡ አባ ዳውድም ከዚህ ታሪክ
በመነሣት “መጽሐፈ መሳፍንት የሚያስተምረው ስንፍና ወደ ኃጢአት (ከእግዚአብሔር መለየት)- ኃጢአትም ወደ ቅጣት (ባርነት)-
36
ኢያሱ ካረፈ ከ 6 ዓመት በኋላ ዐርፏል
የ/ደ/ይ/ቅ/ጊ/ቤ/ክ/ፍ/ሃ/ሰ/ት/ቤት ትምህርት ክፍል የተዘጋጀ 44
የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት
ባርነትም (በስቃይ ምክንያት የሚመጣው ጸጸት) ወደ ንስሓና ድኅነት እንደሚመራ ነው” ብለዋል፡፡ ይህም የእግዚአብሔርን መሐሪነት
የሚያስረዳ ነው፡፡
የመጽሐፉ ዓላማ
ጎቶንያል መሳ 3፡7-11
ናዖድ መሳ 3፡12-30
ስሜገር መሳ 3፡31
ባርቅ መሳ 4፡1-5፣31
ጌዴዎን መሳ 6፡11
አቤሜሌክ መሳ 9፡22
ቶላ መሳ 10፡1-2
ኢያዕር መሳ 10፡3-5
ዮፍታሔ መሳ 11፡1
ኢብጻን መሳ 12፡11
ኤሎም መሳ 12፡8
ዓብዶን መሳ 12፡13
ሶምሶን መሳ 13፡1-16
3. መጽሐፈ ሩት
37
በዕብራውያን ታልሙድ መሠረት የመጽሐፉ ጸሐፊ ነቢዩ ሳሙኤል ነው፡፡ መጽሐፉ በቅዱሳት አንስት ስም ከተጠሩ መጻሕፍት
መካከል አንዱ ነው፡፡ የተጻፈበት ዘመንም በ 1100 ቅ.ል.ክ ነው፡፡
ሩት ማለት መልከ መልካም፣ ቅንጆ፣ ወዳጅ፣ ጓደኛ ማለት ነው፡፡ መሳፍንት እስራኤልን ይገዙ በነበረበት ዘመን የነበረች ከሞዓብ
ወገን የሆነች አሕዛባዊት ሴት ናት፡፡ ሞዓባውያን ከጨው ባሕር በስተ ምሥራቅ የሚኖሩ፣ ጣዖት ያመልኩ የነበሩ ሕዝቦች ናቸው፡፡
38
አቤሜሌክ የተባለው እስራኤላዊ በሀገሩ ረሀብ ተነሥቶ ኑኃሚን ከተባለች ሚስቱና ከሁለት ልጆቹ ጋር ወደ ሞዓብ ሀገር ሄደዋል፤
በሞዓብ ሳሉም የአቤሜሌክ ልጅ ሩትን አግብቷት ነበር፤ ልጅ ሳይወልድም ሞቷል፡፡ በሞዓብም አቤሜሌክና ልጆቹ በመሞታቸው ኑኃሚን
በሰው ሀገር ብቸኝነቱን ጠልታ ወደ ሀገሯ ከነዓን ስትመለስ ሩትም ‹‹ሕዝብሽ ሕዝቤ፣ አምላክሽ አምላኬ ነው ፡፡›› በሚል የእምነት ቃል
ከእርሷ መለየት አለመፈለጓን ገልጻ ከኑኃሚን ጋር ከነዓን ገብታለች፤ ከዚያም ከይሁዳ ወገን የሆነውን ቦኤዝን አግብታ ኢዮቤድ የተባለውን
የዳዊትን አያት ወልዳለች፤ ይህ ጽኑ እምነቷና ጥንካሬዋ ከአሕዛብ ወገን ሆና የክርስቶስ የዘር ሐረግ ውስጥ እንድትካተት አድርጓቷል፡፡ ግብሯ
ልክ እንደ ስሟ ያመረ እናት ነበረችና፡፡/ሩት 1፡16-17፣ ማቴ 1፡5/
የመጽሐፉ አከፋፈል
ይህ መጽሐፍ 4 ምዕራፎች ሲኖሩት፤ በ 4 ከፍለን እንመለከተዋለን
ሩት 1፡ የአቤሜሌክ ቤተሰብ በሞዓብ ሀገር፣ ሩት ከኑኃ፣ም ጋር ወደ በቤተልሔም እንደሄደች
ሩት 2፡ ሩት ከኑኃሚን ጋር ወደ ከነዓን መጓዟና በቦኤዝ አውድማ ውስጥ እንደቃረመች
ሩት 3፡ ሩት ቦኤዝ እንዲያገባት ያደረገችው ጥረትና ጥበብ
ሩት 4፡ ሩት የቦዔዝ ሚስት ሆና የዳዊትን አያት ኢዮቤድን እንደወለደችው ይተርካል፡፡
4. መጻሕፍተ ሳሙኤል
በውስጡ ሁለት መጻሕፈትን ይይዛል፡፡ እነዚህ መጻሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊና ካልዕ ናቸው፡፡ እነዚህ መጻሕፍት በዕብራይስጡ እንደ አንድ
መጽሐፍ ይቆጠራሉ፡፡ በኋላም ሰብአ ሊቃናት መጻሕፈትን ከዕብራይስጥ ወደ ግሪክ ሲተረጕሙ ለሁለት ከፍለዋቸዋል፡፡ ይህም የሆነበት
ምክንያት የዕብራይስጥ ቋንቋ አናባቢ የሌለው በመሆኑ በአንድ ጥቅልል መጠቅለል ሲችል ወደ ግሪክ በተረጎሙት ጊዜ ግን እጅግ ስለበዛ ወደ
ሁለት መጻሐፍት ከፍለውታል፡፡
የመጻሐፉ ስምም በዕብራይስጡ ልክ እንደ አማርኛው “ሳሙኤል” ይባላል፡፡ ይህን ስያሜ ያገኘውም መጽሐፉ ስለ ነቢየ እግዚአብሔር
ሳሙአል እና እርሱ ቀብቶ ስላነገሣቸው ነገሥታት የሚተርክ ስለሆነ ነው፡፡ ሳሙኤል ማለትም እግዚአብሔር ሰማኝ ማለት ነው፡፡ ነገር ግን ሰብአ
ሊቃናት መጽሐፉን ሲተረጕሙረት “የመንግሥት መጻሕፍት” (kingdom books) ብለውታል፡፡ ቅዱስ አባ ሄሮኒመስ (ጄሮም) መጻሕፍትን
ወደ ላቲን ቋንቋ በተረጎመበት ቩልጌት ትርጉሙ የሰብአ ሊቃናትን አከፈፈል ተከትሏል፡፡ ነገር ግን መጻሕፈቱን “የነገሥት መጻሕፍት” (Regum
books; namely The Royal Books) ብሏቸዋል፡፡
በ 14 ተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የዕብራጥስጡም ትርጉም ይህን የግሪክ አከፈፈል በመከተል መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊና ካልዕ ተብሏል፡፡
አማርኛው ይህን ይከተላል፡፡ በግእዙ ግን ነገሥት ቀዳማዊና ካልዕ ነው የሚባለው፡፡ ግእዙ ለያይቶ ቢጠራቸውም ሲቆጥራቸው ግን እንደ አንድ
መጽሐፍ ነው፡፡ “መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ ወካልእ አሐዱ መጽሐፍ ” እንዲል ፍትሕ መንፈሳዊ፡፡
የመጽሐፉ ጸሐፊ በተመለከተ በአይሁዳውያን ትውፊት መሠረት እስከ ምዕራፍ 25 ማለትም ነቢዩ ሳሙኤል እስከሚያርፍበት ድረስ
ያለውን የጻፈው ራሱ ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ሳሙኤል ሲሆን ከዚያ በኋላ እስከ መጨረሻ ድረስ ያለውን ግን ነቢዩ ናታንና ጋድ እንደጨረሱት
ይነገራል፡፡ (ሳሙ 10፡25)
የእግዚአብሔር ስም ወይም አምላካዊ ስም፣ እግዚአብሔር ጸሎቴን ሰማኝ ማለት ነው፡፡ ሳሙኤል ከዘመነ መሳፍንት
መጨረሻ የነበረ ነቢየ እግዚአብሔር ነው፡፡
ይህ መጽሐፍ ከሰባው ሊቃውንት ትርጓሜ በፊት ከሁለተኛው መጽሐፈ ሳሙኤል ጋር አንድ መጽሐፍ ነበር፡፡ ሰባው
ሊቃውንት ግን ለሁለት ከፍለውታል፡፡
የመጽሐፉ ዓላማ
የመጽሐፉ ዓላማ
5. መጽሐፈ ነገሥት
6. ሀ. መጽሐፈ ነገሥት አንደኛ
7. ለ. መጽሐፈ ነገሥት ሁለተኛ
እነዚህ ሁለት መጻሕፍት በዕብራይስጡ አንድ እንደነበሩና በኋላ ዘመን በ 150 ቅ.ል.ክ 70 ሊቃናት ብሉያትን ወደ ግሪክ ቋንቋ
በተረጎሙት ጊዜ በሊቃውንት ውሳኔ ሁለት እንደሆኑ የብሉይ ኪዳን ሊቃውንት ይናገራሉ፡፡ በዕብራይስጥ ሁለቱም
መጻሕፍት አንድ ላይ መለኪያ ይባላሉ፡፡ የመጽሐፉ ጸሐፊ በታልሙድ 17 (15) ላይ እንደተጠቀሰው ነቢዩ
ኤርምያስ እንደሆነ ይታመናል፡፡ ይህም ነቢዩ ኤርምያስ በነገሥት 24 እና 25 ላይ መጠቀሱ በዘመኑ እንደ
ነበርና መጽሐፉን ለመጻፉ ማስረጃ ነው፡፡ የተጻፈበትም ዘመን በ 567 ቅ.ል.ክ ነው፡፡
፡ ስምንቱ የእስራኤል ነገሥታት፡ ኢዮርብአም፣ ናዳብ፣ ባኦስ፣ ኤላ፣ ዘምሪ፣ አክዓብ፣ አካዝያስ
ይናገራል፡፡
ተ.ቁ ንጉሥ የነገሠበት መግለጫ
ጊዜ
1 ኢዮርብአ 21 ዓመት የናባጥ ልጅና ቴቴልን መናገሻ ከተማ ያደረገ
ም
2 ናዳብ 2 ዓመት የኢዮርብዓም ልጅ
3 ባኦስ 23 ዓመት ናደብንና ቤተሰቡን ሁሉ ገድሎ የነገሠ
4 ኤላ 2 ዓመት የባኦስ ልጅ
5 ዘምሪ 7 ቀን የባኦስን ቤተሰብ ከገደለ በኋላ ራሱን የገደለ
6 ዖምሪ 12 ዓመት ሰማርያን ዋና ከተማ ያደረገ
7 አክዓብ 21 ዓመት የዖምሪ ልጅን የጣዖት አምልኮን ከሚስቱ ከኤልዛቤል ጋር ያስፋፋና በነቢዩ
ኤልያስ የተገሠጸ
8 አካዝያስ 2 ዓመት የአክዓብ ልጅና የቤተሰቡን መጥፎ አርአያ የተከተለ
በግእዙና በቩልጌት ትርጉም ነገሥት አራተኛ በመባል ይጠራል፡፡ መጽሐፉ በአጠቃላይ የሁለቱን
መንግሥታት ታሪክ ከመጽሐፈ ነገሥት ቀዳማዊ ተቀብሎ በመቀጠል ሁለቱ መንግሥታት በጠላት ተከበው
እስከተያዙበትና ሕዝቦቻቸውም በምርኮ እስከተወሰዱበት ድረስ ያለውን ታሪክ ይተርካል፡፡
ይህ መጽሐፍ 25 ምዕራፎች ሲኖሩት በ 2 ዋና ዋና ክፍሎች ከፍለን እናየዋለን፡፡
2 ኛ ነገ 1-17፡ ይህ ክፍል እስራኤላውያን በአሦራውያን እስከተማረኩበት ባለው ጊዜ ስለ ይሁዳና ስለ
እስራኤል መንግሥታት የሚናገር ነው፡፡
2 ኛ ነገ 18-25፡ በዚህ ክፍል ውስጥ ናቡከደነፆር ይሁዳንና ኢየሩሳሌምን አስፋፍቶ ሕዝቡን ወደ
ባቢሎን እስከ ወደሰበት ጊዜ ድረስ የነበረውን ሁኔታ የሚገልጥ ነው፡፡ እንዲሁም በወቅቱ ስለበነሩት 16
የይሁዳ ነገሥታትና 11 የእስራኤል ነገሥታት ታሪክ በሰፊው ይገልጻል፡፡
ዐሥራ ስድስቱ የይሁዳ ነገሥታት
ኢዮራም፣ አካዝያስ፣ አታልያ፣ ኢዮአስ፣ አሜስያስ፣ ዖዝያን፣ ኢዮአታም፣ አካዝ፣ ሕዝቅያስ፣ ምናሴ፣
አሞን፣ ኢዮስያስ፣ ኢዮአክስ፣ ኢዮአቄም፣ ዮአኪን፣ ሴዴቅያስ
ተ. ንጉሥ የግዛት መግለጫ
ቁ ዘመን
1 ኢዮራም 7 ዓመት የኢዮሳፍጥ ልጅና የአካዓብን ልጅ በማግባትና ወንድሞቹን ሁሉ በመግደል
በክፋት የቆመ ነበር
2 አካዝያስ 1 ዓመት የኢዮራም ልጅና በኃጢያት እግዚአብሔርን ያሳዘነ
3 አታልያ 6 ዓመት የአካዝያስ እናት የነገስታት ዘሮችን ሁሉ ክኢዮአስ በስተቀር የገደለች
4 ኢዮአስ 40 ዓመት ጣዖት አምላኪ የሆነና በክፉ ስራው በአገልጋዮቹ የተገደለ
5 አሜስያ 29 ዓመት እግዚአብሔርን በማምለክ ጀምሮ ጣዖት በማምለክ የጨረሰ
ስ
6 ዖዝያን 52 ዓመት የእግዚአብሔርን ፈቃድ ፈጻሚ የነበረ
7 ኢዮአታ 16 ዓመት ጻድቅ እና ደግ ሰው የነበረ
ም
8 አካዝ 16 ዓመት አምልኮ ጣዖትን ያስፋፋ ክፉ ሰው
9 ሕዝቅያ 29 ዓመት በጣም ጻድቅ የይሁዳ ንጉሥና በንስሐው 15 ዓመት ከእድሜው ላይ
ስ የተጨመረለት
10 ምናሴ 45 ዓመት መምላኬ ጣዖት የነበረ
11 አሞን 2 ዓመት ክፉ የነበረና በአገልጋዮቹ የተገደለ
12 ኢዮስያስ 31 ዓመት ባዕዳን አማልክትን ሁሉ ከአገሩ ያጠፋ እግዚአብሔርን የሚወድ ጻድቅ
ንጉሥ
13 ኢዮአክስ 3 ዓመት በክፉ መንገድ ቆሞ የነበረና በግብፃውያን ተማርኮ እዚያው የሞተ
14 ኢዮአቄ 11 ዓመት ኃጢአት በመስራት እግዚአብሔርን ያሳዘነ
ም
15 ዮአኪን 3 ወር ናቡከደነፆር ኢየሩሳሌምን በወረረ ጊዜ የነበረና ተማርኮ ወደ ባቢሎን የወረደ
16 ሴዴቅያስ 11 ዓመት በክፉ ስራው እግዚአብሔርን ያሳዘነ
ዐሥራ አንዱ የእስራኤል ነገሥታት
ኢዮራም፣ ኢዩ፣ ኢዮአክዝ፣ ዮአስ፣ ዳግማዊ ኢዮርብአም፣ ዘካርያ፣ ሰሎሞን፣ ምናሔም፣ ፍቂስያስ፣
ፍቁሔ፣ ሆሴዕ
ተ. ቁ ንጉሥ የነገሠበት መግለጫ
ዘመን
6. መጽሐፈ ዜና መዋዕል
ዜና መዋዕል ሁለት ክፍሎች አሉት፡
የሁለቱም መጻሕፍት ጸሐፊ ካህኑ ዕዝራ ነው፡፡ መጻሕፍቱንም ከምርኮ ሲመለሱ በኢየሳሌም ጽፏቸዋል፡፡ ዘመኑም ከ 450
እስከ 300 ቅ.ል.ክ ባለው ጊዜ ውስጥ ነው፡፡
ይህ መጽሐፍ ሠላሳ ስድስት ምዕራፎች ያሉት ሲሆን ከዜና መዋዕል አንደኛ የሚቀጥል መጽሐፍ ነው፡፡
መጽሐፉም በ 4 ዋና ዋና ክፍሎች ተከፍሏል፡፡
2 ኛ ዜና 1-9 ፡ የሰሎሞን ሀብታምነት
፡ የቤተ መቅደሱ መታነጽና የፈጀው ገንዘብ
፡ ስለ ሰሎሞን ገናናነትና ክብር
፡ ጥበቡን ለማየት ስለመጣችው ስለ ንግሥት ሳባ
2 ኛ ዜና 10-16፡ ከሰሎሞን ሞት በኋላ የልጁ የሮብአም መንገሥ
፡ በሮብአም ዘመን የመንግሥቱ ለሁለት መከፈል
፡ የይሁዳ ንጉሥ አብያ የእስራኤልን ንጉሥ ኢዮርብአምን ማሸነፉ
፡ የይሁዳ ንጉሥ አሳ ኢትዮጵያውያንን ድል ማድረጉና ሌሎችን በሰፊው ያትታል፡፡
2 ኛ ዜና 17-21፡ ኢዮሳፍጥ የአባቱን ዙፋን መውረሱ
፡ መምነኬው የእስራኤል ንጉሥ አክዓብን ለመርዳት መውጣቱ፣ ኢዮሳፍጥ የእግዚአብሔርን
መንገድ መከተሉ
፡ የአሞንና የሞአብ ሰዎች በኢዮሳፍጥ መንግሥት ላይ በተነሡ ጊዜ በእግዚአብሔር ኃይል
መደምሰሳቸው
፡ ኢዮሳፍጥ ከሞተ በኋላ ልጁ ኢዩራም ዙፋኑን መውረሱ
፡ ኢዮራም በአባቱ መንገድ ባለመሄዱ በኤልያስ መገሰፁ ይገኛል፡፡
2 ኛ ዜና 22-36፡ በዳዊት ስርው መንግሥት ስር ስለተነሱት ነገስታት ታሪክ
፡ ናቡከደነፆር ዋና ከተማዋን ኢየሩሳሌምን አፍርሶ አብዛኛዎቹን የይሁዳ ሕዝብ ማርኮ
መውሰዱ ተዘርዝሮ ይገኛል፡፡
ጸሎተ ምናሴ
የንጉሡ ምናሴ የጸሎት መጽሐፍ ባለ አንድ ምዕራፍ ሲሆን ይኸውም 13 ቁጥሮችን የያዘ ነው፡፡ በ 2 ኛ
ዜና 33፡18 ላይ የሕዝቅያስ ልጅ ንጉሡ ምናሴ የጸለየው ጸሎት እንደሆነ ስለሚናገርና ሙሉ በሙሉ
ተያያዠወነት ስላለው ጸሎተ ምናሴ የተሰኘው የጸሎት መጽሐፍ በሰማንያ አሐዱ የቀኖና ቅዱሳት
መጻሕፍት አቆጣጠር ከሁለተኛ ዜና መዋዕል ጋር በአንድነት ይቆጠራል፡፡
የመጽሐፉ ይዘትም የንስሐ ጸሎት ሲሆን በውስጡም ምናሴ ከኃጢአቱ መመለሱንና ምህረትን
ከእግዚአብሔር መለመኑን ያስረዳል፡፡
7. መጽሐፈ ኩፋሌ
ኩፋሌ ማለት ዘተከፍለ እምኦሪት (ከኦሪት የተከፈለ) ማለት ነው፡፡ አንዳንዴም ትንሹ ኦሪት በመባል ይታወቃል፡፡ መጽሐፉ በኦሪት ዘፍጥረትና
በኦሪት ዘጸአት በከፊል የተጻፈውን አብራርቶና አስፍቶ የሚተርክ መጽሐፍ ሲሆን ጸሐፊው ነቢየ እግዚአብሔር ሙሴ ነው፡፡ መጽሐፉ ሠላሳ ዐራት
ምዕራፎች ሲኖሩት ከዘፍጥረት 1፤1 እስከ ዘፀ 14፤31 ያለውን ታሪክ ከአይሁድ ትርጓሜ መጻሕፍት ጋር በመቀላቀል የተጻፈ ነው፡፡
አንዳንድ በመጽሐፉ ላይ ጥናት አድርገናል የሚሉ ሰዎች ጸሐፊው ሙሴ ሳይሆን እጅግ በጣም ጥብቅ የሆነ አቋም ያለውና ከፈሪሳውያን ወገን የሆነ
ሰው እንደጻፈው ይናገራሉ፡፡ የተጻፈበትንም ዘመን ከክርስቶስ ልደት በፊት በነበሩት አንድ መቶና ሁለት መቶ ዓመታት እንደነበር ያስቀምጣሉ፡፡ በኢትዮጵያ
ቤተክርስቲያን ትውፊት መሠረት የመጽሐፈ ኩፋሌ ጸሐፊ ሊቀ ነቢያት ሙሴ ነው፡፡ ይህንንም መጽሐፉ ራሱ ሲጻፍ ሙሴ እግዚአብሔር ራሱን እያነገረው
እንደሆነ አድርጎ ጽፎታል፡፡ ከዚህም ሌላ የታሪኩ ሂደት የሚቋጨው ራሱ ሙሴ እስከነበረበት ጊዜ ነው፤ ይህም ጸሐፊው ራሱ ሙሴ እንደሆነ ያስረዳናል፡፡
የመጽሐፉ ተቀባይነት
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከቀኖና መጻሕፍት ውስጥ አንዱ ነው፡፡ እነ ቅዱስ ኤጲፋንዮስ፣ እነ ቅዱስ ዮስጢኖስ ሰማዕት፣ እነ
ሊቁ ኦሪገን፣ እነ ቅዱስ የጠርሴሱ ዲዮዶሮስ፣ እነ ቅዱስ ጊዮርጊስ ኑንክሉስ፣ እነ ቅዱስ አባ ጄሮም፣ እነ ዲዲሞስ ዘእስክንድርያ ስለመጽሐፉ እውነተኛነት
በጽሑፎቻቸው ገልጠዋል፡፡ መጽሐፉ በእንግሊዝኛ 'The book Jubilees' (መጽሐፈ ኢዮቤልዩ) ይሰኛል፡፡ ይኸውም መጽሐፉ ዓመታቱን በኢዮቤልዩ
እየከፋፈለ ስለሚናገር ነው፡፡ ኢዮቤልዩ በሰባት ብዜት ላይ የተመሠረተ ሲሆን አንዱ ኢዮቤልዩ (ሰባት የዓመት ሳምንታትን 'year-weeks' ) ዐርባ ዘጠኝ
ዓመታትን ይይዛል፡፡
ወደ 12 የሚሆኑ በሙት ባሕር ጥቅሎች እስኪገኙ ድረስ በወቅቱ የመጽሐፈ ኩፋሌ ብቸኛ ማስረጃ ሆነው ያገለገሉት በኢትዮጵያ የሚገኙት አራት
የተሟሉ የግእዝ ጽሑፎችና ከላይ የጠቀስናቸው አባቶች የጻፏቸው ጽሑፎች ናቸው፡፡ እ.ኤ.አ. በ 1947 እና በ 1956 ዓ.ም መካከል በአምስት የቁምራን
ዋሻዎች ውስጥ በእብራይስጥ ቋንቋ የተጻፉ አሥራ አምስት የመጽሐፈ ኩፋሌ ጥቅሎች ተገኝተዋል፡፡ በዚያ የተገኙት ብዛት ያላቸው ጽሑፎች የሚያመለክቱት
ከሌሎች መጻሐፍት በሚበልጥ መልኩ (ከመዝሙረ ዳዊት፣ ከኦሪት ዘዳግም፣ ከትንቢተ ኢሳይያስ፣ ከኦሪት ዘጸአት እና ከኦሪት ዘፍጥረት በስተቀር ) መጽሐፈ
ኩፋሌ በቁምራን ደሴቶች በስፋት ያገለግሉ እንደነበር ነው፡፡ ጄምስ ቫንደርካም (James VanderKam) በተባለው ሰው በደረገው የማነጻጸር ሥራም
ኢትዮጵያዊው ቅጂ በቁምራን ከተገኘው ጋር ፍጹም ተመሳሳይና በቀጥታ ቃል በቃል የተተረጎመ እንደሆነ ተረጋግጧል፡፡
በመጀመርያ መጽሐፉ ከዕብራይስጥ ወደ ግሪክ ቋንቋ የተተረጎመ ሲሆን ኋላ ወደ ላቲንና ወደ ግእዝ ቋንቋዎች ተተርጉሟል፡፡ እንዲሁም ከጠቅላላ
መጽሐፉ አንድ አራተኛውን የሚይዘው ከግሪክ ወደ ላቲን የተተረጎመው መጽሐፍም አንዱ ማስረጃ ነው፡፡ የግእዙ ትርጉም ለመጀመርያ ጊዜ በኦገስት ዲልማን
አማካኝነት በ 1859 ዓ.ም እ.ኤ.አ ታትሟል፤ ይህ ሰው መጽሐፉን ወደ ጀርመንኛ ቋንቋ ተርጉሞታል፡፡ ሮበርት ሄነሪ ቻርልስ የተባለው ሰው ደግሞ የግእዙን
መጽሐፍ ለሁለተኛ ጊዜ ተሻሽሎ እንዲታተም ያደረገው ሲሆን ከዚህ እትም ወደ እንግሊዘኛ ተርጉሞታል፡፡
በሱርስት ቋንቋ የተጻፈውና “የካህናት ሚስቶች ስም ኢዮቤልዩ በሚለው የአይሁድ መጽሐፍ ላይ እንደተጻፈው” (“Names of the wives of
the patriarchs according to the Hebrew books called Jubilees”) የተሰኘው መጽሐፍ የተወሰኑ ክፍሎቹ በብሪታንያ ሙዚየም
ውስጥ መገኘታቸው በአንድ ወቅት በሶርያኛ ቋንቋ የተተረጎመ ቅጂ እንደነበረው ያመለክታል፤ እንዲሁም ብዙ ተጨማሪ የመጽሐፉ ክፍሎች መኖራቸውንም
ያሣያል፡፡
በፈሪሳዊና በረበናዊ (Pharasidic and Rabbinic) ቋንቋዎች (አይሁድ ከ 6 ኛው-15 ኛው መክዘ የነበረ የዕብራውያን ቋንቋ) የተጻፈ
አልተገኘም፤ ይህም ሳንኸርዲን (የአይሁድ ሸንጎ) ከሚቀበሏቸው ቀኖና መጻሕፍት ውጪ መሆኑን ያመለክታል፡፡
መጽሐፈ ኩፋሌ ከኦሪት ዘፍጥረት ጋር በአብዛኛው የሚመሳሰል ይዘት ቢኖረውም ታሪኩን የበለጠ በዝርዝር አስፋፍቶ ይጽፋል፡፡ ሙሴ በአጠቃላይ
የፍጥረትን እንዲሁም የእስራኤልን ታሪክ በኢዮቤልዩ (በዐርባ ዘጠኝ ዓመት) እየተከፋፈለ የተነገረውን የጻፈበት ነው፡፡ ከፍጥረተ ዓለም ሙሴ በስደት ወቅት
በሲና ተራራ ጽላቶቹን እስከተቀበለበት ድረስ ያለው ጊዜ አምሳ ኢዮቤልዩ ሲቀነስ ከነዓን ከመግባታቸው በፊት በበረሃ የተንከራተቱበት ዐርባ ዓመት ነው፤
ይህም 2,410 ዓመታትን ይሰጠናል፡፡
የመጽሐፈ ኩፋሌ ጸሐፊ የሆነው ሙሴ የመጀመርያዎቹን ሰዎች፣ የአበውን እና የእስራኤልን ወደ ግብፅ ስደት ታሪክ በድጋሜ
ጽፎታል፤
የመጽሐፉ አከፋፈል
ይህ መጽሐፍ 34 ምዕራፎች አሉት፣ በ 4 ክፍሎች ከፍለን እናየዋለን፡
ኩፋ 1- ሙሴ ከእግዚአብሔር ጋር መገናኘቱን
ኩፋ 2-7- ከአዳም እስከ አብርሃም እና ኖኅ ድረስ ያለውን ታሪክ ይዟል፡፡
ኩፋ 8-32- የያዕቆብንና የልጆቹን ታሪክ
ኩፋ 33-34- የሙሴ ከግብጽ አርነት ነፃ በመውጣት ያገኘውን ድል እናገኛለን፡፡
8. መጽሐፈ ሄኖክ
ሄኖክ የአዳም 7 ኛ ትውልድ ሲሆን የያሬድ ልጅ የማቱሳላ አባት ነው፡፡ ሄኖክ ማለት አዲስ ወይም
ተሐድሶ ማለት ነው፡፡ የሄኖክ እናት ስም ባረካ ይባላል፤ ሄኖክ በ 12 ኛው ኢዮቤል ሚስት አገባ ስሟ አድኒ
ይባላል፡፡ በ 6 ኛው ዓመት ልጅ ወለደችለት ልጁንም ማቱሳላ ብሎ ጠራው፤ ሄኖክም 365 ዓመት ከኖረ በኋላ
ተነጠቀ ሄኖክም እስከ አሁን ድረስ ሞትን ሳይቀምስ በሕይወት ይገኛል፡፡ ሞትን ባይቀምስም፤ ነገር ግን ሰው
ሟች ነውና ለእለተ ምጽአት ዋዜማ ሞትን ይቀምሳል፡፡ የመጽሐፈ ሄኖክ ጸሐፊው ራሱ ቅዱስ ሄኖክ ነው፡፡
ይህ መጽሐፍ የተጻፈው በ 4014 ዓ.ዓ ነው ወይም አዳም ከተፈጠረ ከ 1486 ዓመት በኋላ ነው፡፡
የመጽሐፉ ዓላማ
9. መጽሐፈ ዕዝራ
ዕዝራ ማለት ረድኤት ማለት ነው፡፡ ዕዛራ ካህን፣ ነቢይ፣ ጸሐፊም ነበር፡፡ አባቱ አዛርያስ ይባላል፡፡ ነገዱ
ከነገደ ሌዊ ሲሆን በባቢሎን ምርኮ በሰባው ዘመን የተወለደ ሰው ነው፡፡ ጸሐፊው ራሱ ዕዝራ ነው፡፡ የጻፈውም
ከምርኮ መልስ በኢየሩሳሌም ነው፡፡
መጽሐፈ ዕዝራ በዋነኝነት የእስራኤል ሕዝብ ከ 70 ዓመት የባቢሎን ምርኮ በኋላ ወደ ሀገራቸው
መመለሳቸውንና ቤተመቅደስንም እንደገና መሥራታቸውን ይገልጻል፡፡ በሰማንያ አሐዱ መጽሐፍ ቅዱስ
አቆጣጠር መጽሐፈ ዕዝራ የሚቆጠረው ከመጽሐፈ ነህምያ ጋር በመጣመር ነው፤ ለዚህም ምክንያቱ፡-
ሁለቱም መጻሕፍት የተጻፉት በአንድ ሰው ሲሆን ጸሐፊያቸውም ካህኑ ዕዝራ ነው፤ ለዚህም
የመጽሐፍ ቅዱስ ምሁራን የሚያቀርቡት መረጃ ሁለቱም መጻሕፍት በይዘት ተመሳሳይ መሆናቸውን
ነው፡፡
ሁለቱም መጻሕፍት በይዘት ተመሳሳይ መሆናቸውን በመጽሐፈ ዕዝራ ላይ የመጀመሪያዎቹ ከስደት
ተመላሾች መሪዎች ነበሩ ተብለው ስሞቻቸው ከተጠቀሱት ሰዎች መካከል ነህምያ ይገኝበታል፤
በመጽሐፈ ነህምያ ደግሞ በምዕራፍ 8 እና 9 ላይ ካህኑ ዕዝራ የእግዚአብሔርን ሕግ አንብቦ ኃጢአቱን
እንደተናዘዘ ስለተገለጠ ነው፡፡
ጸሐፊው ራሱ ካህኑ ዕዝራ ነው፡፡ ዕዝራ 8፡1፣ ዕዝ 10፡ 1፡፡ የተጻፈበት ዘመን በ 467 ቅ.ል.ክ ሲሆን ቦታው
ከባቢሎን መልስ በኢየሩሳሌም ነው፡፡
የመጽሐፉ ዓላማ፡-
ስለሚጠት፡- ከባቢሎን ምርኮ ስለመመለሳቸው፣ ስለ ቤተ መቅደስ መታነጽ፣ እስራኤላውያን ከአሕዛብ ጋር
በጋብቻ ስለመቀላቀላቸውና እግዚአብሔር ለሕዝቡ ስላለው ፍቅር፣ እስራኤላውያን ወደ እውነተኛ አምልኮ
መመለሳቸውን ይገልጻል፡፡
የመጽሐፉ አከፋፈል
መጽሐፈ ዕዝራ 10 ምዕራፎች ያሉት ሲሆን፤ ለጥናትም ያመች ዘንድ በ 2 ዋና ዋና ክፍሎች ይከፈላል፡፡
ዕዝ 1-6፡ በዚህ ክፍል ውስጥ የፋርሱ ንጉሥ ቂሮስ የእስራኤል ልጆች ወደ ሀገራቸው ወደ ኢየሩሳሌም
እንዲመለሱ ሲል የደነገገው አዋጅ ይገኝበታል፡፡ ከተመላሾቹም አብዛኛዎቹ ከይሁዳ፣ ከብንያምና
ነህምያ እግዚአብሔር አጽናኝ /አዳኝ/ ነው ማለት ነው፡፡ በሰብዓ ሊቃናት ኒምያ ይባላል፡፡ ነህምያ
የፋርስ ንጉሥ የነበረው አርጤክስ ጠጅ አሳላፊ የነበረ አይሁዳው ነው፡፡ ነህ 1፡ 1-2፤ ነህምያ የኢየሩሳሌምን
ፍርስራሽ ከተመለከተ በኋላ ከአርጤክስ ፈቃድ ተቀብሎ የከተማይቱን ሹማምንት ለሥራ በማነሣሣት
የጠላቶቹን ተቃውሞ ሳይፈራ በ 52 ቀናት የኢየሩሳሌምን ቅጥርዋን ለማሠራት የቻለ የእምነት ሰው ነበር፡፡
ጸሐፊው ራሱ ነህምያ ነው፡፡ /ነህ 1፡ 1-4/
የተጻፈበት ዘመን በ 446 ቅ.ል.ክ ሲሆን ቦታው በኢየሩሳሌም ነው፡፡
የመጽሐፉ ዓላማ ፡-
ስለ ኢየሩሳሌም ቅጽር ድጋሚ መታነጽ፣ የጸሎትን ኃይልና ነህምያ በማስተዳደር ዕዝራ በካህንነት ሕዝቡን
በማኅበራዊ ኑሮና በሃይማኖት ማገልገላቸውን ይገልጻል፡፡
የመጽሐፉ አከፋፈል
መጽሐፈ ነህምያ 13 ምዕራፎች ሲኖሩት በ 3 ዐበይት ክፍሎች ይከፈላል፡፡
ነህ 1-2፡ በዚህ ክፍል ነህምያ ወደ ኢየሩሳሌም የሚመለስበት ምክንያት የኢየሩሳሌም ቅጽሮች
በመፍረሳቸውና፡፡ በሮቹም በእሳት በመቃጠላቸው እነርሱን ለማሠራት እንደሆነ ተገልጽዋል፡፡
ነህ 3-6፡ በዚህ ክፍል የአይሁድ ጠላቶች በነህምያ ላይ ተቃውሞና ትችት ቢሰነዘሩም ነህምያ በነበረው
ድፍረትና እምነት የኢየሩሳሌም ቅጽሮችና በሮች መሥራት መቻሉ ተገልጽዋል፡፡
ነህ 7-13፡ በዚህ ክፍል ውስጥ፡ የሕጉ መጽሐፍ መነበቡ፣ የተደረገው የንስሐ ጸሎት፣ ነህምያ
የእግዚአብሔርን ቤት ማስተዳደሩና፣ ነህምያ ሕግ ተላላፊዎችን መገሰጹ ተገልጽዋል፡፡
የመጽሐፉ ዓላማ
ካህኑ ዕዝራ በተማረከበት በባቢሎን ሀገር በነበረበት ጊዜ ስላያቸው ሰባት ራዕዮች፣ ዕዝራ ለጠየቃቸው ጥያቄዎች
በምሳሌ የተሰጠውን መልስና በመጨረሻ ዕዝራ እግዚአብሔርን በጸሎት ጠይቆ መንፈሳዊ ጸጋና ዕውቀት ተሰጥቶት 40 ቀን
ጾሞ ቅዱሳት መጻሕፍትን እንደጻፈ ይገልጻል፡፡
የመጽሐፉ አከፋፈል፡-
በመጽሐፈ ዕዝራ ሱቱኤል 13 ምዕራፎች ሲኖሩት በ 3 ዓበይት ክፍሎች ይከፈላል፡፡
ዕዝ.ሱቱ 1-3፡ ዕዝራ ከእግዚአብሔርና ከሊቀ መልአኩ ኡራኤል ጋር መነጋገሩ
ዕዝ.ሱቱ 4-7፡ ስለ አዕማደ ምስጢራት፣ ስለ ጻድቃንና ስለኃጥአን ያየው ራእይ
ዕዝ.ሱቱ 8-13፡ ስለ ዕዝራ ጾምና ስለተገለጸለት ምስጢር ይገልጻል፡፡
የመጽሐፉ ጸሐፍያን ጦቢትና ልጁ ጦቢያ እንደሆኑ ተለያዩ ሊቃውንት ያስረዳሉ፡፡ ለዚሀም እንደመነሻ ያደረጉት በመጽሐፉ ላይ ያሉትን ኃይለ
ቃላት ነው፡፡ ለምሳሌ “ሩፋኤልም የዚያን ጊዜ ሁለቱን ሁሉ ጦቢያና ጦቢትን ጠርቶ ቆይታ አድርጎ ፡ እግዚአብሔርን አመስግኑ አላቸው፡፡ . . .
እግዚአብሔርን አመሰገኑት ስሙንም አመሰገኑ የእግዚአብሔርን ክብር ሥራ በክብር ተናገሩ፡፡” ጦቢ 12፡6 የሚለውን በግሪኩ ትርጉም “የሆነውን ሁሉ
በመጽሐፍ ጻፍ፡፡” ይላል፡፡ በተጨማሪም “አሁንም በእግዚአብሕር እመኑ፤ ይህን ሁሉ በመጽሐፍ እጽፍ ዘንድ መጣሁ አለ፡፡” ጦቢ 12፡20 የሚሉት
ኃይለ ቃላት ተጠቃሽ ናቸው፡፡
መጽሐፉ በነነዌ በሰባተኛው መቶ ዘመን ቅ.ል.ክ በአረማይክ ቋንቋ የተጻፈ ሲሆን በምርኮኞች ተጠብቆ የቆየ ነው፡፡ በወቅቱ በኢየሩሳሌም
ባለመኖሩም ዕዝራ መጻሕፍትን ሲበስብ ይህን መጽሐፍ አላገኘውም፡፡ ሰብአ ሊቃናት ግን ወደ ግሪክ ቋንቋ ተርጕመውታል፡፡ ቤተ ክርስቲያናችንም
ከ 46 መጻሕፍተ ብሉይ መካከል ትቆጥረዋለች፡፡ ለምሳሌ ቅዱስ ያሬድ በድጓው “ይኄይስ ምጽዋት እምዘጊቦቱ ለወርቅ . . . ይበሉ
በኵሉ ፍናዊሃ ሃሌ ሉያ ይትባረክ እግዚአብሔር” እያለ ከርሱ ጠቅሶ ይዘምራል፡፡
የመጽሐፉ አጠቃለይ ይዘት ጦቢት ስለተባለው ቅዱስ በንጉሥ ስልምናሶር ዘመን ወደ አሦር ከተማረከ በኋላ እርሱና ልጁ ጦቢያ ተቸግረው ሳለ
እግዚአብሔር በመልአኩ ሩፋኤል አማካኝነት ጠፍቶ የነበረውን ዓይኑን እንዴት እንዳበራለት እንዴት እንደረዳቸው እና ጦቢት በስፋት የነበሩ አይሁዳውያን
ይመክራቸው፣ የሞቱትንም ተደብቆ ይቀብራቸው እንደነበር በስፋት ይተነትናል፡፡
ጦቢት 1-3፡ በዚህ ክፍል ጦቢት በበጎ ሥራው ስላገኘው መከራና ወደ እግዚአብሔር ያደረገው ምስጋናና ልመና ይገኝበታል፡፡
ጦቢት 4-12፡ ጦቢት በመከራው ጊዜ ልጁን ጦቢያን ወደ ወገኖች ሲልክ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል በሰው ተመስሎ እንዴት እንዳዳነውና
እንደረዳቸው በዝርዝር ይገልጻል፡፡
ጦቢት 13-14፡ በዚህ ክፍል ጦቢት እግዚአብሔርን ስላደረገለት ነገር ሁሉ ያመሰገነበት ጸሎትና በእርጅናው ጊዜ ልጁንና የልጁን ልጆች ጠርቶ
የሰጣቸውን አባታዊ ምክርና ኑዛዜ ይገኛል፡፡
ዮዲት ማለት ኃያል፣ አሸናፊት ማለት ነው፡፡ መጽሐፉን የጻፉት በስደት የነበሩ አይሁድ ነበሩ፡፡ የተጻፈበት ዘመን
በ 600 ቅ.ል.ክ ሲሆን ቦታውም በኢየሩሳሌም ነው፡፡
የመጽሐፉ ዓላማ
ንጉሥ ናቡከደነፆር እስራኤላውያንን ለመውጋት የተላከው የጦር መሪ ሆሎፎርኒስ የተባለውን እስራኤላዊቷ ዮዲት ገድለው
ወገኖቿን ነፃ ማውጣቷን ይገልጻል፡፡
የመጽሐፉ አከፋፈል፡
መጽሐፈ ዮዲት 16 ምዕራፎች ሲኖሩት በ 3 ዐበይት ክፍሎች ይከፈላል፡፡
ዮዲ 1-4፡ ናቡከደነፆር ጠላቱን ሁሉ የማጥፋት ሥልጣንን ለጦር መሪው ለሆሊፎርኒስ እንደሰጠውና ይህ መሪ
የሠራቸውን ሥራዎች
ዮዲ 5-10፡ የኢየሩሳሌም በናቡከደነፆር ትእዛዝ መከበቧን
ዮዲ 11-16፡ ዮዲት የጦር መሪ የሆነውን ሆሊፎርኒስን እንዴት እንደገደለችውና ይህንን ያደረገላት አምላኳን
እግዚአብሔርን እንዳመሰገነችው እና ዕረፍቷን ይገልጻል፡፡
15. መጽሐፈ አስቴር
ይህ መጽሐፍ ስያሜውን ያገኘው ከመጽሐፉ ባለ ታሪክ አስቴር ነው፡፡ አስቴር ማለት ቃሉ የፋርስ (በአርማይክ) ሲሆን ትርጓሜውም ኮከብ ማለት ነው፤
የዕብራይስጥ ወይም የቀድሞ ስሟ ሀዳሳ ሲሆን ትርጕሙም አዲስ ማለት ነው፡፡
እንደ ዮሴፍ ወልደ ኮርዮን (ጆሴፈስ) እና እንደተለያዩ የአይሁድ ሊቃውንት አስተሳሰብ የመጽሐፉ ጸሐፊ የአስቴር አጎት ልጅ መርዶክዮስ ነው፡፡ ይህም
አመለካከት በአብዛኛዎቹ የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት የሚደገፍ ነው፡፡ /አስ 9፡ 20-30/ (Flavius Josephus, The Antiquities of the
Jews, Book 11 Chapter 6:11)
መጽሐፉ የተጻፈበትን ዘመን ለማወቅ ታሪኩ የተፈጸመበትን ዘመን መረዳት ያስፈልገዋል፡፡ በ 536 ቅ.ል.ክ በቂሮስ (539-530 ቅ.ል.ክ)
የእስራኤላውያን የመጀመሪያው ሚጠት(ከምርኮ መመለስ) ሆነ፡፡ በዚህም ቂሮስ ወደ ሀገሩ ለመመለስ የፈለገ ሁሉ እንደሚችል ዓዋጅ አስነገረ (ዕዝ 1፡1) ፡፡
ከቤተ አይሁድ አንዳንዶች ግን በዚሁ ንብረት አፍርተናል፣ አግብተን ወልደናል፣ እርሻን አርሰን ዘር ዘርተናል በማለት ለመመለስ ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል፡፡
ሌሎቹ ግን በዘሩባቤል መሪነት ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል፡፡ አስቴር የምትገኘው እምቢ ብለው ከቀሩት አይሁድ ጋር ነው፡፡ አስቴርን ያገባት ንጉሥ
አሕሳዌሮስ (486-464 ቅ.ል.ክ) (በግእዙ አርጤክስስም) ሲባል ንጉሥ ቂሮስ ከነገሠ በኋላ ሦስተኛው የነገሠ ንጉሥ ነው፡፡ ይህም ማለት ቂሮስ ከሞተ
ከ 90 ዓመት በኋላ ነው፡፡ የመጽሐፉም መጻፍ በዚህ ዘመን እንደ ሆነ ይታመናል፡፡
ይህ መጽሐፍ ከሌሎቹ መጻሕፍት የሚለየው በአንድም ቦታ ላይ የእግዚአብሔርን ስም አለመጥቀሱ ነው፡፡ ለዚህም ምክንያቱ በወቅቱ የእግዚአብሔርን
ስም መጥራት ወይም ስለ ሃይማኖት አንስቶ መነጋገር ችግር የሚያስከትል ስለ ነበር ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ መርዶክዮስ የመጽሐፉን ቅጅ ፋርሳውያን
እንደሚፈልጉትና በስመ እግዚአብሔር ፈንታ የጣኦታን ስም እንዲገባላቸው እንደሚጠይቁ ስለ ተረዳ ስመ አምላክን ሳያስገባ ጽፎታል፡፡ ነገር ግን
እግዚአብሔር ለአይሁድ ሕዝብ ያደረገው ጥበቃና ተራዳኢነት በሰፊው ይዘግባል፡፡ የግእዙ ትርጉም ግን ስመ እግዚአብሔርን እያስገባ ይጽፋል፡፡
የመጽሐፉ አጠቃላይ ይዘት በአርጤክስስ ዘመነ መንግሥት በምርኮኝነት ይኖሩ በነበሩ እስራኤላውያን ላይ በሐማ ምክር የደረሰውን ስደት የሞት አደጋ
አስቴር የተባለችው እስራኤላዊት በእግዚአብሔር ሞገስ አክሽፋ ወገኖቿን ማዳኗን ይገልጻል፡፡
ከምዕ 1-2፡ በዚህ ክፍል ውስጥ የፋርሱ ንጉሥ አርጤክስስ ሚስቱን አስጢንን ፈትቶ አይሁዳዊቱን አስቴርን ያገባ መሆኑን
ከምዕ 3-5፡ በዚህ ክፍል ሐማ የተባለው ሰው ወደ ከፍተኛ ሹመት ማደጉና ሐማ ሲወጣና ሲገባ መርዶክዮስ የማይሰግድለት መሆኑን በተረዳ ጊዜ
ከቁጣው የተነሳ የአይሁድን ዘር በሙሉ በአንድ ቀን ለማጥፋት ከንጉሡ ፈቃድ መቀበሉ ተገልጽዋል፡፡
ከምዕ 6-10፡ በዚህ ክፍል መርዶክዮስ የአስቴርን እርዳታና ድጋፍ መጠየቁ፣ አይሁድ በጾም፣ በጸሎት በእግዚአብሔር ፊት መቆማቸው፣ አስቴር
ንጉሡንና ሐማን ግብዣ መጥራቷ፣ የመርዶክሰዮስ መሾምና የሐማ መሰቀል እንዲሁም አይሁድ ጠላቶቻቸውን መበቀላቸውንና የፋሪም በአል
አከባበር ይገኙበታል፡፡
መጽሐፈ መቃብያን
መቃቢስ /መቃባ/ ማለት ጸረ ጠላት፣ ቀስት፣ ጀግኖች ማለት ነው፡፡ ጀግኖች የሚለው ትርጉም ቃሉ ሲበዛ (መቃብያን)
ሲሆን ነው፡፡ የመቃብያን ታሪክና ልዩ ልዩ መንፈሳዊ ትምህርቶችን የያዙ ስምንት መጻሕፍተ መቃብያን መኖራቸው
ታውቋል፡፡ በግእዝና በአማርኛ ተተርጉመው የሚገኙ ሦስቱ የመቃብያን መጻሕፍት ናቸው፡፡ የመቃብያንን መጻሕፍት ማን
እንደጻፋቸው በውል አይታወቅም፡፡
በፍትሐ ነገሥት የተገለጹት መጻሕፍት፡
1. መቃብያን ዘመቃቢስ አልዓዛር
2. መቃብያን ዘመቃቢስ ሞአብ
3. መቃብያን ዘመቃቢስ ዘብንያም
4. መጽሐፈ መቃብያን ራብዕ ዮሴፍ ወልደ ኮርዮን ዜና አይሁድ ዜና ሥርው
ያልተተረጎሙት መጻሕፍተ መቃብያን
አንደኛው መጽሐፈ መቃብያን 16 ምዕራፎች ሲኖሩት ወንድሞቹ የአይሁድን ሃይማኖታዊ ሕግና ሥርዓት ለመጠበቅ ሲባል
ከሌሎች መንግሥታት ጋር ያደረጉትን ተጋድሎ የሚተርክ ነው፡፡ ሁለተኛው መጽሐፈ መቃብያን ደግሞ 15 ምዕራፎች ያሉት
ሲሆን የመጀመሪያው መጽሐፍ ተከታይ ሲሆን በተለይ በግብጽ የሚኖሩ አይሁድ በኢየሩሳሌም ቤተ መቅደስ ላይ ይደርሳል
ብለው ስለሚፈሩት ስደት ዘርዝሮ የሚያስረዳ ነው፡፡ እነዚህ አንደኛና ሁለተኛ መጽሐፈ መቃብያን ተብለው የተጠቀሱት
መጻሕፍት በትልቁ የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ካሉት ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ መጽሐፈ መቃብያን የተለዩ ናቸው፤
የታሪኩም ይዘት የተለየ ነው፡፡ በሰማንያ አሐዱ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያሉት መጻሕፍተ መቃብያን ደግሞ እንደሚከተለው
ናቸው፡፡
በግእዝና በአማርኛ ተተርጉመው ከሚገኙት ሦስቱ የመቃብያን መጻሕፍት አንዱና ራሱን ችሎ የሚቆጠር መጽሐፍ ነው፡፡
የመጽሐፉ ጸሐፊ አንድ ፍልስጤማዊ /አይሁድ/ ነው፡፡ የተጻፈበት ቋንቋ ዕብራይስጥ ሲሆን ዘመኑ በ 103 ቅ.ል.ክ
በኢየሩሳሌም ነው፡፡
የመጽሐፉ ዓላማ፡-
የመቃቢስ ዘብንያም ልጆች አብያ፣ ሲላስና ፈንቶስ ለጣዖት አንሰግድም በማለታቸው አመጸኛው ንጉሥ ጺሩዳይዳን
እንዳሰቃያቸውና የተቀበሉትን ሰማዕትነት
ከብሉይ ኪዳን ታሪኮችና ምሳሌዎች እየጠቀሱ ስለ ትንሳኤ ሙታን መናገራቸውን የሰው ልጅ የነፍስና ሥጋ በረከትና
ሕይወት ስለሚያገኝበት መንገድ የመከሩትን ይገልጻል፡፡
ከቀድሞ ጀምሮ የነበሩትን የቅዱሳት አበው ታሪክን በማንሳት በዘመናቸው በአመጽ ምክንያት የጠፉትን የእስራኤል
ሕዝቦች ማለትም በኖኅ ዘመን፣ በሎጥ ዘመንና በግብጽ ተሰደው መከራን የተቀበሉትን ሕዝቦች ታሪክም ይተርካል፡፡
የመጽሐፉ አከፋፈል፡-
1 ኛ መቃብያን 36 ምዕራፎች ሲኖሩት በ 3 ዐበይት ክፍሎች ይከፈላል፡፡
1 ኛ መቃ 1-5፡ ስለ ጺሩዳይዳንና የመቃቢስ ልጆች ሰማዕትነት
1 ኛ መቃ 6-11፡ ስለ ዳግም ምጽአት
1 ኛ መቃ 12-36፡ በብሉይ ኪዳን ስለነበሩ አበውና ስለ እስራኤላውያን ይናገራል፡፡
የዚህ መጽሐፍ ጸሐፊ የኮርዮን ልጅ ዮሴፍ ሲሆን በ 1 ኛው መ.ክ.ዘ ድ.ል.ክ በኢየሩሳሌም አካባቢ በግሪክ /በጽርዕ/ ቋንቋ ጽፎታል፡፡ ዮሴፍ ማለት
ይጨመር፣ ይደገም ማለት ነው፡፡ ከካህናት ቤተሰብ በ 37 ዓ.ም የተወለደ ታዋቂ የአይሁድ የታሪክ ጸሐፊ ነው፡፡ በልጅነቱ የቤተ እስራኤልን ትምርት ቦኖስ
ከተባለው ሊቅ ሥር መናኝ ደቀ መዝሙር ሆኖ ለ 3 ዓመታት በበረሃ ኖሯል፡፡ በ 64 ዓ.ም ወደ ሮም በመጓዝ አንዳንድ አይሁድን ለማስፈታት ሞክሮ ነበር፤
በዚያም የኔሮል ቄሳር ሚስት ለእርሱ ቀና አመለካከት ነበራት በዚያም ምንም ችግር ሳይደርስበት ወደ ሀገሩ ተመልሷል፡፡
በ 66 ዓ.ም አይሁድን ከወራሪዎች ነጻ ለማድረግ ጦሩን ከመሩት ሰዎች መካከል አንዱ ነበር፡፡ በ 67 ዓ.ም በቬስፓስያን ወታደሮች ተማረከ፡፡ ዮሴፍ
ኤስፓስያን ንጉሥ እንደሚሆን ትንቢት ተናግሮ ነበርና ይህም ትንቢት በ 69 ዓ.ም ሲፈፀም ንጉሡ ዮሴፍን በነፃ አሰናብቶታል፡፡
በ 70 ዓ.ም ኢየሩሳሌም በጥጦስ ስትከበብ ለሮማውያን አስተርጓሚ ሆኖ አገልግሏል፤ በዚህም የተነሳ በአይሁድ ዘንድ ለመጠላት ምክንያት ሆነው፡፡
ከዚያም በኋላ በሮም በነገሡ ነገሥታት ዘንድ የከበረ ሰው ሆነ የሮምን ዜግነትም አግኝቷል፡፡ በመንግሥት የተፈቀደለት የጡረታ ገንዘብም ሙሉ ጊዜውንም
ወደ ጽሐፍ እንዲያደርግ ረድቶታል፡፡
ይህ መጽሐፍ ከጌታችን ልደት በኋላ የተጻፈ ብቸኛ የብሉይ ኪዳን መጽሐፍ ነው፡፡ በይዘቱም ከአዳም ጀምሮ እስከ 70 ዓ.ም በጥጦስ መሪነት
የተፈፀመው የኢየሩሳሌም ቤተ መቅደስ መቃጠል ድረስ ያለው የአይሁድን ታሪክ የሚገልጽ መጽሐፍ ነው፡፡ በዚህም ዜና አይሁድ ተብሏል፡፡ ከጌታ ልደት
በኋላ ተጽፎ ከሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት ጋር ያልተካተተበት ምክንያት መጽሐፉ በአብዛኛው በብሉይ የነበሩ ታሪኮችን የሚያነሣ ስለሆነ ነው፡፡ በዓለሙም
እንደታሪክ ማጣቀሻ ከሚጠቀሱ መጻሕፍት መካከል አንዱ ነው፡፡
የመጽሐፉ ዓላማ፡-
ከአዳም ጀምሮ እስከ 70 ዓ.ም በጥጦስ መሪነት የተፈፀመው የኢየሩሳሌም ቤተ መቅደስ መቃጠል ድረስ ያለው የአይሁድን
ታሪክ የሚገልጽ መጽሐፍ (ዜና አይሁድ) ነው፡፡
የመጽሐፉ አከፋፈል፡-
መጽሐፈ ዮሴፍ ወልደ ኮርዮን 8 ምዕራፎች ሲኖሩት በ 8 ዐበይት ክፍሎች ይከፈላል፡፡
ስለ አዳም
ስለ ንጉሥ አንጥያኮስ መቄዶናዊ፣ ስለ ዮናናውያንን ንጉሥ
የእስክንድርያ ንግሥት፣ የህርቃሎስና የአስትሮቦሎስ ልጅ
የህርቃሎስ ከፋርስ መግባቱና መንገሡ
ስለ አስቴር ንግሥና እና ስለ አርኬላዎስ ታሪክ
የሄሮድስ ልጅ አርኬላኦስ ታሪክ
ስለ ስምዖን ያርብሃዊ
ስለ ቤተ መቅደስና ሮማውያን ከአይሁድ ጋር መጣላታቸውን
የመጽሐፈ ኢዮብ የአጻጻፍ ይዘት ጠቢቡ ሰሎሞን ከጻፋቸው መጻሕፍት ጋር ይመሳሰላል፤ የጥበብ
መጻሕፍት ከሚባሉት ከመጽሐፈ ምሳሌና ከመጽሐፈ መክብብ ጋር አጻጻፉ አንድ አይነት ነው፡፡ ከምዕራፍ
አንድ እስከ ሦስት የተጻፈው በስድ ንባብ ሲሆን ከምዕራፍ አራት እስከ አርባ አንድ ያለው በግጥምና በጥበብ
መልክ ነው የተጻፈው፡፡
መጽሐፈ ኢዮብ 41 ምዕራፎች አሉት፣ መጽሐፉ መቼና በማን እንደተጻፈ በእርግጠኝነት
አይታወቅም፤ በብዙ ሊቃውንት ዘንድ ኢዮብ እስራኤላውያን በግብጽ በነበሩበት ዘመን የኖረ ሰው እንደነበረና
ከአብርሃም ጀምሮ ሲቆጠር አምስተኛ ትውልድ አንደሆነ ይነገራል፤
የመጽሐፉ ዓላማ
ይህ መጽሐፍ አጠቃላይ ይዘቱ እግዚአብሔርን በሚወዱና ለሕጉ በሚታዘዙ ሰዎች ላይ መከራ ሊደርስ
እንደሚችልና በትዕግስት ካሳለፉት ግን መከራው እንደሚወገድና በረከትንም ከእግዚአብሔር በእጥፍ
እንሚያገኙ የሚያስተምር ነው፡፡ቅዱሳን አላውያን የሚያደርሱባቸውን ጽኑ መከራ ችለው መቀበላቸው
ብዙዎችን ወደ እምነት መልሷቸዋል፤ እግዚአብሔር ልጆቹን ያስተምራል፣ እግዚአብሔር ትዕግስተኛ
እንደመሆኑ ልጆቹም ትዕግስተኛ እንዲሆኑ ያስተምራል፡፡ የእግዚአብሔር ትዕግስት ወደ ጭንቀት ሳይሆን
በጸሎት ወደ መትጋት ይመራል፤ እምነትና ትዕግስት በምድርም ምንጊዜም በድል ይጠናቀቃሉ፡፡ ጻዲቁ
ኢዮብም መከራና ችግር በደረሰበት ጊዜ እግዚአብሔር ሰጠ፣ እግዚአብሔር ነሳ በማለት በእምነትና
በትዕግስተኛነቱ ዲያቢሎስን አሳፍሯል፡፡
የመጽሐፉ አከፋፈል
ኢዮ 1-2፡ የኢዮብ መፈትን
ኢዮ 3፡ ኢዮብ በሕይወቱ በደረሰበት መከራ አምላኩ እግዚአብሔርን የጠየቀው ጥያቄ
ኢዮ 4-31፡ ሦስቱ የኢዮብ ጓደኞች ኢዮብ የደረሰበትን መከራ በመታገሱ መጥተው እንደተከራከሩት
ኢዮ 32-42፡ የእግዚአብሔር መልስና የኢዮብ መጽናናት
2. መዝሙረ ዳዊት
መዝሙረ ዳዊት ቅድስት ቤተክርስቲያናችን ለአገልግሎት ዘወትር ከምትጠቀምባቸው ቅዱሳት መጻሕፍት መካከል
አንዱ ነው፡፡ ጸሐፊውም ከእስራኤል ነገሥታት ሁሉ ታላቅና ተወዳጅ የሆነው ንጉሥ ዳዊት ነው፡፡ ጸሐፊም የተባለው
ብዙውን ክፍል እርሱ ስለ ጻፈ ነው፡፡
መዝሙር የሚለው ቃል ዘመረ፣ አመሰገነ ከሚለው ቃል የወጣ ሲሆን ትርጓሜውም ምሥጋና፣ ማመስገን ማለት ነው፡፡
መዝሙረ ዳዊት በውስጡ 150 መዝሙራት፣ ጸሎት፣ ትምህርት እና ቅኔ በአንድነት ይገኙበታል፡፡ መዝሙረ ዳዊት የዳዊት
መዝሙር የሚባሉት አብዛኛውን 73 መዝሙሮችን እርሱ ስለደረሳቸው ነው፤ በሌሎች ሰዎች የተደረሱ መዝሙራት እንዳሉ
ከመዝሙረ ዳዊት ራሱ መገንዘብ እንችላለን፡፡ ለምሳሌ፡
መዝ 90 የሙሴ መዝሙር መሆኑ ተገልጧል፡፡
መዝ 146፣ 147 እና 148 የሐጌና የዘካርያስ መዝሙሮች ናቸው፡፡
በቆሬ ልጆች ስም የሚጠሩ 11 መዝሙሮች አሉ (መዝ 2፣ 4፣ 84፣ 86፣ 87….ወዘተ)
የአሳፍ መዝሙሮች የሚባሉት 12 መዝሙሮች አሉ (መዝ 50፣ 73፣ 79፣ 80፣ 81…. ወዘተ)
ኤታን በሚባል እስራኤላዊም የተደረሱ መዝሙሮች አሉ፡፡ (ለምሳሌ፡ መዝ 68)/ 1 ኛ ዜና 15፡16-24፣ 1 ኛ ዜና 25-
ፍፃሜ/
መጽሐፈ መዝሙርን (መዝሙረ ዳዊትን) አሁን ባለበት ሁናቴ ያዘጋጀው ካህኑ ዕዝራ ነው፤ መዝሙሮቹም በተለያዩ
ዘመናት እንጂ በአንድ ዘመን ብቻ የተዘጋጁ አይደሉም፡፡ ለምሳሌ፡ መዝ 74፣ 96፣ 137 የተዘጋጁት ከእስራኤላውያን ምርኮ
በኋላ ነው፡፡
መዝሙረ ዳዊት የሰውን የሕይወት ዘመን ሳይለይ ሰው በሕይወቱ የሚያጋጥሙትን ኃዘንና ደስታ፣ መልካሙንና
ክፉውን፣ በመውደቅና በመነሣት፣ ችግርና ምቾት፣ ከእግዚአብሔር መራቅና ወደ እግዚአብሔር መቅረብ የያዘ መጽሐፍ
ነው፡፡
መዝሙረ ዳዊት ለአራት ነገሮች ይጠቅመናል
ለሕያዋን ዕቅበት (ጥበቃ)
ለሙታን ጸሎት ማድረጊያ
ለሕፃናት ትምህርት
ለቤተክርስቲያን ስብከት፡ ለቤተክርስቲያናችን የጸሎትና የመዝሙር መጻሕፍት (ምሳሌ፡ መጽሐፈ ደጓ)
መሠረታቸው መዝሙረ ዳዊት ነው፡፡ መዝሙረ ዳዊት መዘምራን በዜማ ስልት የሚገለገሉበት፣ መነኮሳትና ካህናት
በመዓልትና በሌሊት በቤተክርስቲያን እግዚአብሔርን የሚያመሰግኑትን ምእመናን በያሉበት ሆነው እየጸለዩ
መላእክተ ብርሃንን የሚያቀርቡበት ፣ መላእክተ ጽልመትን የሚያርቁበት፣ ሕሙማንን የሚፈውሱበት እጅግ ጠቃሚ
የሆነ መጽሐፍ ነው፡፡
መዝሙረ ዳዊት በ 5 ክፍሎች የተከፈለ መጽሐፍ ነው፡፡ እነዚህም፡- 1. ከመዝ 1-መዝ 40፤ 2. ከመዝ 41-መዝ 71፤ 3.
ከመዝ 72-መዝ 88፤ 4. ከመዝ 89-መዝ 105፤ 5.ከመዝ 106-መዝ 150 ናቸው፡፡
የእያንዳንዱ ክፍል ፍጻሜ የሚታወቀው ‹‹ከዘለዓለም እስከ ዘለዓለም እግዚአብሔር ይባረክ አሜን አሜን›› የሚሉ
ቃላት ስለተጻፈባቸው ነው፡፡ በቤተክርስቲያናችን ደግሞ ዐሥሩን በአንድነት አንድ በማለት ‹‹አንድ ንጉሥ›› በማለት በዐሥራ
አምስት ይከፈላል፡፡
መዝሙረ ዳዊት ሰዎች በዚህች ዓለም በሚኖሩበት ጊዜ ስለሚያጋጥማቸው ሁኔታዎች በሙሉ ምን መጸለይ
እንደሚገባቸው የሚያስረዳ መጽሐፍ ነው፡፡ መዝሙራቱ የሃይማኖታዊውን ሥርዓት አብዛኛውን ክፍል ይሸፍናሉ፡፡
የመዝሙራቱን ዓላማ በዝርዝር ለመግለጽ አስቸጋሪ ነው፤ ሆኖም በዓይነት በዓይነት ለማየት እንሞክራለን፡፡ መዝሙራት
የተለያየ አርዕስት ኖሮአቸው በሁለት ባለቤት ክፍል ይከፈላሉ፡፡ እነርሱም፡- የማኅበርና የግል ናቸው፡፡
የማኅበር የሚባለው ሕዝቡ በኅብረት እንደሚዘመሩና እንደሚጸለዩ ሲያመለክቱ፤ የግል የሚለው ደግሞ ሕዝቡ እንደ አንደ ሰው
ሆነው መዘመራቸውን ያመለክታል፡፡ ከዚህ ቀጥሎ በቀረበው ሰንጠረዥ አማካኝነት የመጽሐፉን አብዛኛውን ይዘት መረዳት ይቻላል፡፡
አንድ ኃጢአተኛ ከኃጢአቱ በንስሐ ተመልሶ መዝ 6፣ 31፣ 37፣ 50፣ 85፣ 101፣ 102፣ 142
የእግዚአብሔርን ይቅርታ የሚጠይቅበት
ጭንቀት፣ ፈተና ፣ ውርደት፣ ኃዘን፣ ስደትና ጭቆና መዝ 2፣ 6፣ 13፣ 21፣ 35፣ 41፣ 43፣ 44፣ 52፣ 56፣
በሚያጋጥም ጊዜ 59፣ 64፣ 68፣ 74፣ 77፣ 79፣ 80፣ 83፣ 88፣ 90፣
94፣ 102፣ 109፣ 140፣ 143
ፍርሃት፣ ፈተና ሲያጋጥም በእግዚአብሔር መዝ 11፣ 16፣ 18፣ 20፣ 25፣ 25፣ 27፣ 28፣ 30፣ 32፣
ለመተማመን 37፣ 46፣ 54፣ 57፣ 62፣ 70፣71፣ 91፣ 115፣ 124፣
125፣ 144፣ 146
የእግዚአብሔር ሕጉና ቤቱ በሚናፈቅበት ጊዜ መዝ 16፣17፣18፣40፣41፣44፣63፣72፣
83፣119፣121፣131
ካህናት የቤተመቅደሱን ደረጃዎች ሲወጡና መዝ 102 እና 103
ሲወርዱ የሚዘምሯቸው የማዕረግ መዝሙሮች
ሃሌሉያ ብለው የሚጀምሩ የስብሐት (የምሥጋና) መዝ 148-150
መዝሙሮች
እነዚህን መዝሙራት ሰው በማኅበርም ሆነ በግል የሚጸልይበት /የሚዘምርበት/ የትኛውን የመዝሙረ ዳዊት ክፍል
እንደሆነ መረዳት ይቻላል፡፡
ሌሎች ትምህርቶችንና ድርጊቶችን የያዙ የመጽሐፍ ክፍሎች
መሠረተ እምነትንና የእግዚአብሔርን ብቸኛ አምላክነት መዝ 50፣ 86፡8፣ 89፡6፣ 135፡5፣ 139፡7፣33፡
የሚያመለክቱ 13
አባቶች እያንዳንዱ መዝሙር ስለ እመቤታችን እና ስለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ምስጢርን የያዘ ነው ይላሉ፤ በመቶ
አምሳው መዝሙራት ሁሉ መዝሙረ ድንግልና መዝሙረ ክርስቶስ መዘጋጀቱ ይህን የሚያመለክት ነው፡፡
ከጥንት ኢትዮጲያውያን ሊቃውንት ሲወርድ ሲዋረድ በመጣው የመዝሙረ ዳዊት የመዝሙረ ዳዊት ንባብና
ትርጓሜ መሠረት ደግሞ መዝሙረ ዳዊት በ 10 አርዕስት እንደሚከፈል ይገልፃል፡፡ እነርሱም፡
1. ተግሣጽ ለኩሉ (ለሁሉም የሚሆን ተግሣጽና ምክር)፡ ‹‹ምስጉን ነው በክፉዎች መንገድ ያልሄደ፣
በኃጢአተኞች መንገድ ያልቆመ…›› እንዲል /መዝ 1፡1/
2. ትንቢት በእንተ ክርስቶስ (ስለ ክርስቶስ የተነገረ ትንቢት)፡ ‹‹አሕዛብ ለምን ያጉረመርማሉ? ወገኖችሽ
ለምን በከንቱ ይናገራሉ? በእግዚአብሔርና በመሢሑ ላይ . . . እግዚአብሔር አለኝ አንተ ልጄ ነህ እኔ ዛሬ
ወለድሁህ›› /መዝ 2፡1/
3. ትንቢት በእንተ ርእሱ (ስለ ዳዊት የተነገረ ትንቢት)፡ ‹‹አቤቱ የሚያስጨንቁኝ ምነኛ በዙ፤ በእኔ ላይ
የሚቆሙት ብዙ ናቸው፡፡›› /መዝ 3፡1/
4. ትንበት በእንተ ትሩፈን /ስለ ትሩፋት የተነገረ ትንቢት/፡ ‹‹አቤቱ ቃሌን አድምጥ፣ ጩኸቴንም
አስተውል፡፡›› /መዝ 5፡1/
5. ትንቢት በእንተ ሕዝቅያስ ወሰናክሬም /ስለ ሕዝቅያስና ሰናክሬም የተነገረ ትንቢት/፡ ‹‹ሰነፍ በልቡ
አምላክ የለም ይላል፤ በሥራቸው ረከሱ፣ ጎሰቆሉ፣ በጎ ነገርን የሚሠራ የለም፡፡›› /መዝ 13፡1/
6. ትንቢት በእንተ ኤርሚያስ /ስለ ኤርሚያስ የተነገረ ትንቢት/፡ ‹‹አቤቱ የሚበድሉኝን በድላቸው፣
የሚዋጉኝንም ተዋጋቸው፡፡››
7. ትንቢት በእንተ መቃብያን /ስለ መቃብያን የተነገረ ትንቢት/፡ ‹‹አቤቱ በጆሮአችን ሰማን ፤ አባቶቻችንም
በዘመናቸው በቀድሞ ዘመን የሠራኸውን ሥራ ነገሩን፡፡›› /መዝ 43፡1/
8. ትንቢት ዘለፋ ካህናት /ስለ ካህናት ተግሣጽ/፡ ‹‹የአማልክት አምላክ እግዚአብሔር ተናገረ፤ ከፀሐይም
መውጫ ጀምሮ እስከ መግቢያዋ ድረስ ምድርን ጠራት፡፡›› /መዝ 49፡1/
9. ትንቢት በእንተ ሰሎሞን ወልዱ /ትንቢት ስለ ሰሎሞን ልጁ/፡ ‹‹አቤቱ ፍርድህን ለንጉሥ ስጥ ጽድቅህንም
ለንጉሥ ልጅ፣ ሕዝብህን በጽድቅ…..ለችግረኞች ሕዝብ በጽድቅ ትፈርዳለህ፡፡›› /መዝ 71፡1/
? ? የተነገሩ ትንቢቶች አሉ የተቀሩት 140 ው ምዕራፎች በእነዚህ ሥር ይካተታሉ፡፡ ከዚህም በተጨማሪ መዝሙረ ዳዊት
በውስጡ ሰባት ዓበይት ትምህርቶችን ይዟል፡፡ እነርሱም፡
1. ጠላትን መውደድ፡ ‹‹ስለ ከንፈሮችህ ቃል ጭንቅ የሆኑ መንገዶች ጠበቅሁ›› /መዝ 16፡4/
2. ትህትና፡ ‹‹እኔ ትል ነኝ ሰውም አይደለሁም፡፡›› /መዝ 21፡6/
3. ሃይማኖት፡ ‹‹ከማህፀን ጀምሮ በአንተ ተጣልሁ ከእናቴ ሆድ ጀምሮ አንተ አምላኬ ነህ፡፡›› /መዝ 21፡6/
4. ተስፋ መንግሥተ ሰማያት፡ ‹‹የእግዚአብሔርን ቸርነት በሕያዋን ምድር አይ ዘንድ አምናለሁ፡፡›› /መዝ 26፡13/
5. ኃጢአትን ማመን፡ ‹‹ኃጢአቴ በራሴ ላይ ከፍ ከፍ ብሎአልና እንደ ከባድ ሸክምም በላዬ ከብዷልና፡፡›› /መዝ 37፡4/
6. ይቅርታ ስለመለመን፡ /መዝ 50/
7. ስለ ምጽዋት፡ ‹‹በተነ ለችግረኞችም ሰጠ፤ ጽድቁ ለዘለዓለም ይኖራል፡፡›› /መዝ 111፡8/ ናቸው፡፡
መዝሙረ ዳዊት በ 6 ተከፋፍሎ ለጸሎት አገልግሎት ይውላል፡፡ ይኸውም፡
3. መጽሐፈ ምሳሌ
መጽሐፈ ምሳሌ በጠቢብ ሰሎሞን በ 950 ቅ.ል.ክ የተጻፈ እና 24 ምዕራፎች ያሉት መጽሐፍ ነው፤
መጽሐፉ የተጻፈው በግጥም መልክ ነው፤ ምክንያቱም በግጥም የተሰጠ ትምህርት በልብ ስለሚያዝ ነው፡፡
መጽሐፉ ትምህርትና ምክርን በምሳሌ የሚያስተምር ነው፡፡ መጽሐፉ የተጻፈበት ዘመን በሰሎሞን ዘመነ
መንግሥት በ 950 ዓ.ዓ አካባቢ ነው፡፡
ሰሎሞን እግዚአብሔርን በጸሎት ለምኖ የተቀበለው ነገር ጥበበኛና አስተዋይ ልቡናን ነበር፡፡ ስለዚህም
መጻሕፍቱ የጥበብ መጻሕፍት ናቸው፡፡ በዘመኑ ከነበሩ ጠቢባት ሁሉ የበለጠ ስመጥር ፈላስፋ፣ ሊቀ ሥነ
ፍጥረት (ሳይንቲስት)፣ ርዕሰ ብሔር፣ ሊቀ ሥነልቡና (ሳይኮሎጂስት) ነበር፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞን ሦስት ሺህ
ምሳሌዎችንና አንድ ሺህ አምስት መዝሙሮችን ተናግሯል፡፡ 1 ነገ 4፣32
የመጽሐፉ አቀማመጥ
በዕብራይስጥ መጽሐፍ ቅዱስ መጽሐፈ ምሳሌ በመዝሙራትና በኢዮብ መካከል ይገኛል፤ በሰባው
ሊቃናትና በግእዝ የብሉይ ኪዳን መጽሐፍ ላይ ግን መጽሐፈ ምሳሌ በመዝሙራትና በመጽሐፈ መክብብ
መካከል ይገኛል፡፡
በግእዙ የብሉይ ኪዳን መጽሐፍ ላይ መጽሐፈ ምሳሌ ሁለት መጽሐፍ ነው፤ ከምዕራፍ 1-24 ያለው
እንዲሁም ከምዕራፍ 25-31 ያለው ሌላ መጽሐፍ ነው፡፡ የመጀመሪያው ምሳሌ ዘሰሎሞን ሲባል ሁለተኛው
ተግሣጽ ዘሰሎሞን ተብሎ ይጠራል፡፡ የአማርኛውም ሁለተኛው ትርጉም ብሉይ ኪዳን ምዕራፍ ሃያ አምስትን
በግእዙ ‹‹መጽሐፈ ተግሣጽ›› ይባላል በማለት ርዕሱን ይገልጣል፡፡
መጽሐፈ ምሳሌ በዕብራይስጥ ብሉይ ኪዳን 31 ምዕራፎች አሉት፤ የሰባው ሊቃውንት ግን ባለ 29
ምዕራፎች ብቻ ያደርጓቸዋል፤ ይህም ምዕራፍ ሠላሳንና ሠላሳ አንድን በምዕራፍ 24 እና 29 ውስጥ
በማስተባበር ነው፡፡
የመጽሐፉ ዓላማ፡-
እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው እንዴት መኖር እንደሚገባው ያስተምራል፡፡ ይህንንም ‹‹የጥበብ መጀመርያ
እግዚአብሔርን መፍራት ነው›› ምሳ 1፣7 በማለት ገልጾታል፡፡
የመጽሐፉ አከፋፈል
መጽሐፈ ምሳሌ በ 3 ዋና ዋና ክፍሎች ይከፈላል፤ እነርሱም፡
ምሳ 1-9፡ በዚህ ክፍል ውስጥ ስለ ጥበብ ገለጻ የተደረገበትና ጥበብን መማር እንደመጠቅም ፤ አለመማር
እንደሚጎዳ የተነገረበት ነው፡፡
ምሳ 10-22፡ ይህ ክፍል፡ ልብን ማደስ፣ ጠባይን ስለማረም፣ አስተሳሰብን ለማጎልበት፣ በሥነ ምግባር
ለመታነጽ የሚረዱ ትምህርቶችን በተለያዩ ምሳሌዎች የሚገልጽ ነው፡፡
ምሳ 23-24፡ በዚህ ክፍል ውስጥ በቀላል የስብከት መንገድ ጥበብን ለመማር ትእዛዞችን ምክሮችና
መመሪያዎች ቀርበዋል፡፡
4. መጽሐፈ ተግሣጽ
5. መጽሐፈ ጥበብ
መጽሐፈ ጥበብ በሌላ ስሙ ባጎር ይሉታል ጥበብ ማለት በቁሙ ሲፈታ ዕውቀት ማለት ነው፤ ጸሐፊው ንጉሥ
ሰሎሞን ሲሆን የተጻፈበት ዘመን በ 900 ቅ.ል.ክ አካባቢ ነው፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በ 1 ኛ ቆሮ 15፡32 ላይ ‹‹ነገ
ስለምንሞት ዛሬ እንብላ እንጠጣ›› ስለሚሉ ሰዎች የጻፈው መልእክት በብሉይ ኪዳንም ከአምስቱ የሰሎሞን መጻሕፍት
አንዱ በሆነው በመጽሐፈ ጥበብ በአስደናቂ ሁኔታ ተጽፎ ይገኛል፡፡ ይህም በመ.ጥበብ 2፡1-9 ያለው ነው፡፡
በአጠቃላይ ይዘቱም እንደ መጽሐፈ ምሳሌ መንፈሳዊ ምክርና ስለ መነናውያንና አይሁዳውያን ይገልፃል፤ እንዲሁም
ስለ ጥበብ ጥቅም በመምከር ሰው ጥበብን እንዲፈልግ ይመክራል፡፡ መጽሐፈ ጥበብ 19 ምዕራፎች ሲኖሩት በ 3 ዐበይት
ክፍሎች ይከፈላል፡፡
የመጽሐፉ ዓላማ
ስለ ጥበብ ጥቅም በመምከር ሰው ጥበብን እንዲፈልግ ያስተምራል፡፡
የመጽሐፉ አከፋፈል
ጥበ 1-6፡ ስለ ነገሥታትና ስለ ክርስቶስ
ጥበ 7-15፡ ስለ ሰው ተፈጥሮና ስለ ጣዖት አምልኮ
ጥበ 16-19፡ ስለ ግብጻውያንና ስለ ኢየሩሳሌም ይናገራል፡፡
6. መጽሐፈ መክብብ
መክብብ ማለት ሰባኪ ማለት ነው፤ በዕብራይስጥ ቁሃልት ሲባል፣ ሰብአ ሊቃናት ኤክሊሲያስተርስ
ብለውታል፣ አባ ኤሮኒሞስ /ጄሮም/ ደግሞ ኮንሲአናቶር ብለውታል፡፡ ጸሐፊው ንጉሥ ሰሎሞን ነው /መክ 1፡1/፤
የተጻፈበት ዘመን በ 900 ቅ.ል.ክ አካባቢ ነው፡፡
ይዘቱም ስለ ሕይወት አስቸጋሪ ነገሮች ሁሉም ከንቱ መሆኑንና ጥበብ ከእግዚአብሔር ዘንድ መሆኑን
በዓለም ስላሉ ተቃራኒ ነገሮች እያነሳ ሁሉም ከንቱ መሆኑን ይገልጻል፡፡
የመጽሐፉ ዓላማ
ይህ መጽሐፍ በ 500 ዓመት ቅ.ል.ክ ካህኑ ዕዝራ ከሰበሰባቸው መጻሕፍት ውስጥ ይገኛል፡፡ በኋላም በ 300 ዓመት ቅ.ል.ክ ሰባ ሊቃንት ብሉይ
ኪዳንን ከዕብራይስጥ ወደ ግሪክ ሲተረጕሙት ይህን መጽሐፍ በመንፈሳዊ ትርጕሙ በመረዳት አካተው ተርማውታል፡፡ ነገር ግን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
በነበረበት ዘመን ልክ እንደ ዘመኑ መናፍቃን መጽሐፉን በሥጋዊ እይታ በማየት ሀካም ሼሜይ (Hakham Shemey) ከብሉይ አውጥቶ ቆጥሮት ነበር፤
ነገር ግን የአይሁድ ባሕላዊ ትምህርት ቤት (Helil School or House of Hellil) የቀኖና መጽሐፍ ነው በማለት ተቃውሞታል፡፡ በ 95 ዓ.ም
የተደረገውም የናሚኒያው የአይሀድ ጉባኤም (council at Jamnia) ይህ አጽንቷል፡፡ በ 135 ዓ.ም የነበሩት የአይሁድ ሊቅ ሀካም አኪባ ስለመጽሐፉ
ታላቅነት ሲናገሩ ‹‹መጽሐፍ ቅዱስ ቅዱስ መጽሐፍ ነው፤ ነገር ግን መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን የበለጠ የከበረ መጽሐፍ ነው . . . ዓለሙ ሁሉ የዚህን ያህል
ጠቃሚ መጽሐፍ አልሰጠንም፡፡›› ብለዋል፡፡
ይህን መጽሕፍ ጠቢቡ ሰሎሞን ከሌሎች መጻሕፍቱ በተለየ በሰዎችና በእግዚአብሔር መካከል ያለውን መንፈሳዊ ፍቅር (Agape in Greek)
ለማስረዳት በወንድና ሴት ፍቅር (Eros in Greek) በመመሰል ጽፎታል፡፡ በዚህም ምክንያት አንዳንዶች ምስጢሩን ባለ መረዳት ሰሎሞን የፈርኦንን ልጅ
ሲያገባት የጻፈው ነው በማለት የያዘውን መንፈሳዊ ትርጕም ሊያዛቡ ይሞክራሉ፡፡ ነገር ግን ይህ መጽሐፍ ለሥጋዊ ፍቅር (Carnal Love) ሳይሆን
መንፈሳዊ ፍቅርን ለማስረዳት የተጻፈ፤ እነርሱም ፍጹም የተሳሳቱ መሆኑን የመጽሐፉ መጀመሪያ ያስረዳናል፡፡
ይህም መጽሐፉ ሲጀምር (ቊ 2-7) ያለው ንግግር የመርዓት (የሙሽራዋ) ነው፤ ለሙሽራውም እንዲህም ትለዋች ‹‹በአፉ መሳም ይሳመኝ፥
ፍቅርህ ከወይን ጠጅ ይልቅ መልካም ነውና።›› አገላለጹ እጅግ ያስደንቃል፤ ምክንያቱም ‹‹በአፍህ አሳሳም ሳመኝ›› ሳይሆን ያለቸው ‹‹ በአፉ መሳም
ይሳመኝ›› ነው፡፡ ስለዚህ የሚስማት ሌላ፣ ፍቅሩ ደግሞ የመሽራው መሆኑን ገልጣለች፡፡ ምክንያቱም ‹‹ፍቅሩ›› ሳይሆን ያለቸው ‹‹ፍቅርህ›› ነውና፡፡ ይህ
አገላለጽ ከመንፈሳዊ ትርጕሙ በስተቀር በሌላ ሊተረጎም ፈጽሞ አይችልም ምክንያቱም ሙሽሪት ሌላ ወንድ እንዲስማት ሙሽራዋን ፈጽማ አትጠይቅምና፡፡
39
ይህ ትርጕም ‹‹ኤልታርጉም›› የሚባለው ሲሆን አይሁዳውያን ከባቢሎን ምርኮ ሲመጡ ከመከራው ጽናት የተነሣ ዕብራይስጥን ረስተው ስለነበር በዘመኑ የነበሩት
ሊቃውንት ወደ አረማይክ በቃል በኋላም በጽሑፍ የተረጐሙት ትርጕም ነው፡፡
ከዚህ ቀጥሎ ያለውም የሙሽራዋ ንግግር ይህንኑ ያስረዳል ‹‹ ሳበኝ፥ ከአንተም በኋላ እንሮጣለን ንጉሡ ወደ ቤቱ አገባኝ በአንተ ደስ
ይለናል፥ ሐሤትም እናደርጋለን ከወይን ጠጅ ይልቅ ፍቅርህን እናስባለን በቅንነት ይወድዱሃል።›› በዚህ አገላለጥ ደግሞ ሙሽራዋ ወደ
ሙሽራው እንድትቀርብ እንዲስባት ስትጠይቀው ነገር ግን ሌሎች ደናግላንን ከርሷ ጋር ይዛ እንደምትመጣ በርሱም በፍቅሩም ደስ እንደሚላቸው ተጽፏል፡፡
ይህም ጠቢቡ ሊያስረዳ የፈለገው ሥጋዊ ፍቅርን አለመሆኑን ያሳየናል፡፡ ምክንያቱም የትኛዋም ሙሽሪት እጮኛዋን ለሌሎች ሴቶች የምትፈቅድ
አይደለችምና፡፡
መጽሐፉ ከቅዱሳት መጻሕፍት የሚመደብ ከሆነ ለምን እንደዚህ ዓይነት አገላለጽ መጠቀም አስፈለገ ብለው ብዙዎች ይጠይቃሉ፡፡ ነገር ግን ይህ
የመጽሐፍ ቅዱስ ባሕል ነው፡፡ እግዚአብሔር እኛ እንረዳው ዘንድ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ በእኛ አገላለጾች ተናግሯል፡፡ ለምሳሌ እግዚአብሔር
ተናደደ፣ ተጸጸተ ... የሚሉት አገላለጾች ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ለእግዚአብሔር ዓይን፣ ጆሮ፣ ቅንድብ፣ ወይም መቀመጥ መቆም ሲነገርለት
እግዚአብሔር ልክ እንደ እኛ ዓይነት ዓይን ጆሮ አለው፤ ወይ መቀመጥ መነሣት ይነገርለታል ማለት ሳይሆን እኛ እንረዳው ዘንድ በእኛ
አገላለጥ ሲገልጸው ነው፡፡ ስለዚህ እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን ፍቅር ለማሳየት ምን ያህል እንደሆነ እኛ እንድንረዳው ጠቢቡ ሰሎሞን
በወንድና በሴት መካከል በሚፈጠረው ፍቀር አስረድቶናል፡፡ መንፈሳዊውን ፍቅር በዚህ መመሰል ደግሞ በሌሎች መጻሕፍት ላያም
እናገኘዋለን፡፡
በብሉይ ኪዳን
ኢሳ 62፡5 ‹‹ጕልማሳም ድንግሊቱን እንደሚያገባ፥ እንዲሁ ልጆችሽ ያገቡሻል ሙሽራም በሙሽራይቱ ደስ እንደሚለው፥ እንዲሁ
አምላክሽ በአንቺ ደስ ይለዋል።››
ኤር 3፡1 ‹‹በሰው ዘንድ ሰው ሚስቱን ቢፈታ፥ ከእርሱም ዘንድ ሄዳ ሌላ ወንድ ብታገባ፥ በውኑ ደግሞ ወደ እርሱ ትመለሳለችን?
ያች ሴት እጅግ የረከሰች አይደለችምን? ይባላል። አንቺ ከብዙ ውሽሞች ጋር አመንዝረሻል፥ ወደ እኔም ትመለሻለሽን? ይላል
እግዚአብሔር››
በሐዲስ ኪዳን
ኤፌ 5፡24-26 ‹‹ዳሩ ግን ቤተ ክርስቲያን ለክርስቶስ እንደምትገዛ እንዲሁ ሚስቶች ደግሞ በሁሉ ለባሎቻቸው ይገዙ። ባሎች
ሆይ፥ ክርስቶስ ደግሞ ቤተ ክርስቲያንን እንደ ወደዳት ሚስቶቻችሁን ውደዱ፤ በውኃ መታጠብና ከቃሉ ጋር አንጽቶ
እንዲቀድሳት ስለ እርስዋ ራሱን አሳልፎ ሰጠ፤ ››
ዮሐ 3፡ 27-29 ‹‹ ዮሐንስ መለሰ፥ እንዲህ ሲል፦ ከሰማይ ካልተሰጠው ሰው እንዳች ሊቀበል አይችልም። እናንተ። እኔ ክርስቶስ
አይደለሁም፥ ነገር ግን። ከእርሱ በፊት ተልኬአለሁ እንዳልሁ ራሳችሁ ትመሰክሩልኛላችሁ። ሙሽራይቱ ያለችው እርሱ ሙሽራ
ነው፤ ቆሞ የሚሰማው ሚዜው ግን በሙሽራው ድምጽ እጅግ ደስ ይለዋል። እንግዲህ ይህ ደስታዬ ተፈጸመ።››
ይህን መጽሐፍ የአይሁድ ሊቃውንት ከነቢያቱ ቃል በመነሣት በእግዚአብሔርና በእስራኤላውያን መካከል ባለ ፍቅር መስለው ያስተምሩታል፡፡
የቤተ ክርስቲያንም አባቶች ይህን መጽሐፍ በሦስት ዓይነት መንገድ ይተረጉሙታል፡፡
ቅዱስ ጄሮም፣ ሊቁ አርጌንስና ሊቁ አውግስጢኖስ የቅዱስ ጳውሎስን ቃል መሠረት በማድረግ በቤተ ክርስቲያንና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ መካከል
ባለ ፍቅር መስለው ተርጉመውታል፡፡
ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ ደግሞ በሰው ነፍስና በእግዚአብሔር መካከል ባለው ፍቅር መስሎ አስተምሯል፡፡ ሊቁ አርጌንስም በአንዳንድ አገላለጹ ላይ ይህን
ተጠቅሟል፡፡
40
አንዳንድ አባቶች ሊቃውንት እንዲሁም ኢትዮጲያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ የተወሰኑ የመጽሐፉ ክፍሎችን በሥጋዌ ምስጢር ሙሽራዋንም
በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እንዲሁም ቆነጃጂቱን በቅዱሳን መስለው አስተምረዋል፡፡
ይህ መጽሐፍ 8 ምዕራፎች ያሉት ሲሆን ለአከፋፈል ትንሽ አስቸጋሪ ቢሆንም በሙሽራዋና በሙሽሪቱ ንግግር አንጻር ለ 4 ይከፈላል፡፡
40
ቅዱስ ያሬድ ከዚህ መጽሐፍ አወጣጥቶ በግጥም መልክ ያዘጋጀው መጽሐፍ የሰሎሞን ምቅናይ ይባላል፡፡ ይህም መጽሐፍ ጌታችንን በፍሬ እመቤታችንን በአበባ እየመሰለ
የሚያስተምር ነውና የቤተክርስቲን ሊቃውንት በዘመነ ጽጌ (መስከረም 25- ኅዳር 6) ለምስጋና ይጠቀሙበታል፡፡ በተጨማሪም በሥርዓተ ተክሊል ጊዜ ከመጽሐፈ ተክሊል
ጋር እንደ አንድ ክፍል ተደርጎ ይጸለያል፡፡
5. የትንቢት ክፍል
ነቢይ ማለት ምን ማለት ነው ?
ነቢይ ማለት አፈ አምላክ /የእግዚአብሔር አፍ/፣ መምህር ማለት ነው፡፡ ቃለ እግዚአበብሔርን
ተቀብሎ ለሕዝቡ የሚናገር ‹‹ነቢይ›› የእግዚአብሔር ሰው ይባላል፡፡ ነቢያት ቃሉ ከእግዚአብሔር እንደመጣ
ቢረዱም እንዴት እንደመጣላቸው ብዙ ጊዜ አይገልጡም፤ ነገር ግን ‹‹እግዚአብሔር እንዲህ አለ›› እያሉ
ትንቢት ይናገሩ ነበር፡፡ አሞ 1፡3፣ 6፡9፤ ሚክ 3፡8 የእግዚአብሔር ቃል አንዳንድ ጊዜ በራዕይ፣ በህልምም፣
በመልአክም ይገለጥላቸው ነበር፡፡ ዘካ 12፡6፣ ዳን 10፡11 ቃሉ በብዙ ዓይነት መንገድ ቢሰጣቸውም (ዕብ 1፡1)
እስኪናገሩት ድረስ እንደሸክም ይከብዳቸው ነበር፡፡ በእግዚአብሔር መንፈስ ስለተጠሩና ስለሚናገሩም (ኢሳ
15፡1፣ 2 ኛ ጴጥ 1፡21) ሕዝቡ በኃጢአት ከመጥፋቱ በፊት ወደ እግዚአብሔር እንዲቀርቡና ይቅርታን
እንዲጠይቁ ያደርጉ ነበር፡፡
ነቢያት በሁለት መንገድ ከእግዚአብሔር ተቀብለው ለሕዝቡ ይናገራሉ፡፡
1. ትንቢተ ኢሳይያስ
ኢሳይያስ ማለት እግዚአብሔር ደህንነት ነው፣ መድኃኒት፣ አዳኝ ማለት ነው፡፡ አባቱ አሞፅ ይባላል፤
ይህም ከነቢዩ አሞፅ የተለየ ነው፡፡ /2 ኛ ነገ 17፡1፣ ኢሳ 1፡1/ ኢሳይያስ ባለትዳር ሲሆን ሚስቱም እንደ እርሱ
ነቢይት ነበረች፤ ሁለት ልጆቹም ነበሯቸው የልጆቹም ስም አንደኛው ማሄር ሻላል ሲባል ሌላኛው ሺያር
ያሼብ ይባላል፡፡
ነቢዩ ኢሳይያስ አገልግሎቱን የጀመረው በዖዝያን መንግሥት መጨረሻ አካባቢ ነው፡፡ /ኢሳ 6፡1-13/ ነቢዩ
ኢሳይያስ በአራት የይሁዳ ነገሥታት (በዖዝያን፣ በኢዩአታም፣ በአካዝና በሕዝቅያስ) ዘመን ከክርስቶስ ልደት
በፊት ከ 740-688 ዓመት አካባቢ ትንቢት የተናገረ ነቢይ ነው፡፡ ኢሳይያስ የታወቀ የኦሪት ምሁር ሲሆን
ትንቢቱንም የተናገረው በኢየሩሳሌም ሆኖ ነው፡፡ ትንቢተ ኢሳይያስ የተጻፈው ከምርኮ በፊት በኢየሩሳሌም
2. ትንቢተ ኤርሚያስ
ኤርሚያስ ማለት እግዚአብሔር ያሌዕል (ከፍ ያደርጋል) ማለት ነው፡፡ የቤተ ክርስቲያናችን ሊቃውንት
ግን ‹‹ብርሃነ እግዚአብሔር ማለት ነው›› ብለው ይተረጉማሉ፤ ለዚህም እንደ ማስረጃ የሚያቀርቡት
ኤርምያስ በእናቱ ማህጸን ሳለ የተመረጠና በወጣትነቱ እግዚአብሔር ለአገልግሎት ያዘጋጀው ታላቅ ነቢይ
ነው፡፡
ኤርሚያስ ከእግዚአብሔር የመጣለትን ቃል ሁሉ በቃል እየነገረው ባሮክ ይጽፍለት ነበር /ቁ 4/
ከዓመታት በኋላ በኢዩዋቄም ዘመነ መንግሥት በ 5 ኛው ዓመት በዘጠነኛው ወር የጻም ዓዋጅ በሚነገርበት
ቀን ባሮክ የኤርምያስን መጽሐፍ በአደባባይ አነበበ፤ ይህንንም ንጉሡ ሰማ መጽሐፉንም አቃጠለው፡፡ ነቢዩ
ኤርሚያስም ባሮክን ጠርቶ በድጋሚ በቃል እየነገረው የቀድሞውን የትንቢት ቃል አጽፏታል፤ አንዳንድ ቃል
ተጨምሯል፤ ለምሳሌ ቁ፡32
ኤርምያስ በ 650 ዓመት ቅ.ል.ክርስቶስ ተወለደ፤ አባቱ ከካህናት ወገን የነበረ ኬልቅያስ የተባለ ሰው
ነበር፡፡ /2 ኛ ነገ 22፡8/ የትውልድ ቦታውም በኢየሩሳሌም ሰሜን አናቶች ትባላለች፤ በዛሬው አጠራር አናታ
ትባላለች፡፡ ኤርምያስ ገና ወጣት የ 20 ዓመት ሳለ ለነቢይነት ተጠራ /ኤር 1፡6/ በጠቅላላ ለ 40 ዓመታት ያህል
በነቢይነት አገልግሏል፤ ሚስትም አላገባም ነበር፡፡ /ኤር 16፡1-4/
3. ትንቢተ ሕዝቅኤል
ሕዝቅኤል ማለት ‹‹እግዚአብሔር ብርታትን ይሰጣል›› ማለት ነው፤ አባቱ ቡዝ ይባላል፡፡ ሕዝቅኤል
በ 622 ዓመት ቅ.ል.ክ ክርስቶስ ተወለደ፤ ነገዱ ከቤተ ሌዊ፣ ትውልዱ ከቤተ ሳዶቅ ነው፡፡ ከልጅነቱ ጀምሮ
የነቢዩ የኤርምያስ ደቀ መዝሙር እንደ ነበረ ይነገራል፡፡
ከክርስቶስ ልደት በፊት 597 ዓመት በንጉሥ ኢኮንያን ዘመን የእስራኤል ልጆች ወደ ባቢሎን በተማረኩ
ጊዜ ነቢዩ ሕዝቅኤል ከምርኮኞቹ አንዱ ነበር፤ በባቢሎን ምርኮ ይኖርበት የነበረው ቦታ በከበር ወንዝ አጠገብ
4. ትንቢተ ዳንኤል
ነቢዩ ዳንኤል ማን ነው?
ነቢዩ ዳንኤል የዮናኪር የልጅ ልጅ ሲሆን በ 618 ዓመት ቅ.ል.ክርስቶስ ተወለደ፤ ዳንኤል የስሙ ትርጉም
እግዚአብሔር ፈራጅ ነው ማለት ነው፡፡ ዳንኤል ከክርስቶስ ልደት 605 ዓመት በፊት በናቡከደነፆር ተማርኮ
ወደ ባቢሎን የተጓዘ አይሁዳዊ ነው፡፡ ዳንኤል ጠቢብ እና አስተዋይ ለቤተመቅደስም ተልዕኮ ብቁ የሆነ
የሃይማኖቱን ሥርዓት የሚጠብቅ ሰው ነበር፡፡ ዳንኤል በስደት ሀገር ስሙ ብልጣሶር ተባለ፣ የከለዳውያንንም
ትምህርት ተማረ ተምሮም በባቢሎን ተሾመ፡፡ ዳንኤል በምርኮ ሀገር ካገኘው ሹመት ጋር ባለ ትንቢትም
ነበር፤ በፆም፣ በጸሎት የሚተጋ ሰው ነበር፡፡
ዳንኤል በምርኮ ሀገር እያለ አራት የአሕዛብ ነገሥታትን አሳልፏል፡፡ እነርሱም፡ ናቡከደነፆር፣ ብልጣሶር፣
ዳርዮስ እና ቂሮስ ናቸው፡፡ እርሱም እነዚህን ነገሥታት በማስተማር ህልምን በመፍታት እና ጽሑፍን
በመተርጎም አገልግሏል፡፡ ዳንኤል ምንም እንኳ የአሕዛብ የመንግሥት ባለስልጣን ቢሆንም ለእግዚአብሔር
ሕዝብ እየጸለየ ሕዝቡ በአምልኮተ እግዚአብሔር እንዲጸና ያደረገ ነቢይ ነው፡፡ ነቢዩ ዳንኤል በብሉይ ኪዳን
የሚገኘውን ትንቢተ ዳንኤል፣ መጽሐፈ ሶስና፣ ተረፈ ዳንኤል እና ጸሎተ ሠለስቱ ደቂቅን የጻፈልን አባት ነው
፤ የኖረውም ከ 618-534 ዓመት ቅ.ል.ክርስቶስ ሲሆን በመጋቢት 23 እንዳረፈ ስንክሳር ያስረዳል፡፡
ትንቢተ ዳንኤልን ከቅዱሳት መጻሕፍት እና ቀኖና አንፃር ስናየው፡-
1. ነቢዩ ዳንኤል ረበናቱ ያልተቀበሉትን የጌታን ልደት እና ሞት በተመለከተ ዘመኑን ቁልጭ አድርጎ በመግለጡ
2. ሁሉም ነቢያተ እስራኤል ሙሉ ጊዜያቸውን ለነብይነት አገልግሎት ሲያውሉ ነብዩ ዳንኤል ግን በቤተ
መንግሥት በማገልገሉ
3. ነብያተ እስራኤል ሕዝቡን በየጊዜው ስለ ኃጢአታቸው ሲገስፁ ዳንኤል ግን ይህን ሲያደርግ ባለመታየቱ
4. ነብዩ ዳንኤል የትንቢቱ መጽሐፍ በምርኮ ጊዜ በመጻፉ የሚሉ ልዩ ልዩ ሀሳቦች ተሰጥተዋል፡፡
የመጽሐፉ ዓለማ
ዳንኤልና ሠለስቱ ደቂቅ (አናንያ፣ አዛርያ፣ ሚሳኤል) በሃይማኖታቸውና በሥርዓታቸው በመጽናት በባዕድ
አገር ለእግዚአብሔር ታማኝ ስለሆኑ መከራ ቢደርስባቸውም እርሱ እንደሚጠብቃቸው፤ እግዚአብሔር የዚህ
ዓለም መንግሥታትን እንደሚቆጣጠርና የራሱ መንግሥት ደግሞ ዘላለማዊ መሆኑን የሚያመለክት ነው፡፡
የመጽሐፉ አከፋፈል
ይህ መጽሐፍ ዐሥራ ሁለት ምዕራፍ ሲኖረው ከምዕራፍ አንድ እስከ ስድስት የታሪክ ክፍል ሲሆን ከሰባት
እስከ ዐሥራ ሁለት ያለው የራዕይ ክፍል በመባል ተሰይሟል፡፡
የየምዕራፉ ዐበይት መልእክታትና ይዘት እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡
ዳን 1፡ የዳንኤል በባቢሎን መማረክንና በዚያም ዳንኤል በንጉሡ መሾሙን ይገልጣል፡፡
ዳን 2፡ ዳንኤል፣ ናቡከደነፆር የተመለከተውን ታላቅ ህልም የተረጎመበት ክፍል ነው፡፡
ዳን 3፡ በባዕድ ሀገር አናንያ፣ አዛርያ እና ሚሳኤል ናቡከደነፆር ላቆመው የወርቅ ምስል አንሰግድም
በማለታቸው ወደ እቶን እሳት መጣላቸውና በእግዚአብሔር አዳኝነት በመልአኩ ተራዳኢነት መዳናቸውን
ይገልጻል፡፡
1. ትንቢተ ሆሴዕ
ይህ መጽሐፍ 14 ምዕራፎች ያሉት ሲሆን ጸሐፊው ነቢዩ ሆሴዕ ነው፡፡ ሆሴዕ ማለት እግዚአብሔር
ያድናል ማለት ነው፡፡ ሆሴዕ አባቱ ብኤረ ይባላል፡፡ ይህ ነቢይ ዳግማዊ ኢዮርብዓም በሰማርያ ነግሦ በነበረበት
ዘመን በሰሜናዊው የእስራኤል መንግሥት የተነሣ ሲሆን በዘመኑም ዖዝያን፣ ኢዮአታም፣ አካዝና ሕዝቅያስ
የተባሉ የይሁዳ ነገሥታትን አሳልፏል፡፡ ከጌታችን ልደት በፊት 700 ዓመት ቀድሞ እንደነበር መጻሕፍት
ተባብረውበታል፡፡ ከነቢያት መካከል የኢሳይያስ፣ የኢሞጽና የሚክያስ የዘመን ኋደኛ ነበር፡፡
የመጽሐፉ ዓላማ
ኃጢአተኛ ዐመጸኛና አመንዝራ የሆነው ሕዝበ እስራኤል አለመታመንና ለእነርሱ የእግዚአብሔር ፍቅርና
ጸጋ ምን ያህል እንደሆነ ለመግለጥ
የእስራኤልን አምልኮተ ጣዖት ለባልዋ ታማኝነት በሌላት በአመንዝራ ሴት በመመሰል ሆሴዕ አመንዝራዋን
ሚስቱን እንዲታረቅ፣ እግዚአብሔርን ትተው ወደ አምልኮተ ጣዖት የሔዱትን ሕዝበ እስራኤል ቢመለሱ
እግዚአብሔር በፍቅር የሚቀበላቸው መሆኑን ለማመልከት
በግልሙትና ከተመሰለው ኃጢአታቸው እንዲመለሱ ‹‹እስራኤል ሆይ ወደ ፈጣሪህ ወደ እግዚአብሔር
ተመለስ›› በማለት ንስሐን ለማወጅ
እግዚአብሔር የማይለወጥ አምላክ በመሆኑ ሕዝቡ እግዚአብሔርን ወደ ማወቅ በመመለስና
ተመልሰውም በመንፈስ እንዲድኑ ጥሪ ለማስተላለፍ ነበር፡፡
የመጽሐፉ አከፋፈል፡-
ይህ መጽሐፍ በ 5 ዐበይት ክፍሎች ይከፈላል፡፡ እነርሱም፡
ሆሴ 1-3፡ የእስራኤል ልጆች እግዚአብሔርን ጣዖት በማምለካቸው ምክንያት ስለማሳዘናቸውና
ስለሚደርስባቸው ቅጣትና ተግሣጽ
እግዚአብሔር ፍቅሩን ከእስራኤል ሕዝብ ላይ ሙሉ በሙሉ ያላነሣ መሆኑንና ንስሐ ቢገቡ ይቅርታ
እንደሚያደርግላቸው
2. ትንቢተ አሞጽ
የዚህ መጽሐፍ ጸሐፊ ከበግ እረኝነትና የሾላ ፍሬ ከመጠበቅ ለነቢይነት የተጠራው ነቢዩ አሞጽ ነው፡፡
(አሞ 7፡14) አሞጽ ማለት ኃይል ማለት ነው፡፡ ትውልዱ ከነገደ ስምዖን ሲሆን አባቱ ቴና እናቱ ሚስታ ይባሉ
ነበር፡፡ አሞጽ በዕለታዊ ተግባሩ ተሠማርቶ ሳለ ለሰሜኑ ሕዝብ ነቢይ እንዲሆን እግዚአብሔር ጠራው፡፡ ይህ
ነቢይ ሥራውን የጀመረው በይሁዳ ዖዝያን፣ በእስራኤል ደግሞ ዳግማዊ ኢዮርብዓም ነግሠው በነበረበት
ዘመን ማለትም ከ 793-733 ቅ.ል.ክ ሲሆን ሁለቱን ጨምሮ አካዝ፣ ኢዮአታምና ሕዝቅያስ የተባሉ ነገሥታት
አሳልፏል፡፡ ይህ ነቢይ በ 2 ኛ ነገ 19፡20 ላይ የተገለጸው የነቢዩ ኢሳይያስ አባት የሆነው አሞጽ አይደለም፡፡
የመጽሐፉ ዓላማ
እግዚአብሔር ለኃጥአን የሚያደርገውን ምህረት ለማስረዳት
የፍርድ ቀን እንደደረሰና እስራኤላውን ፍርድ እንደሚቀበሉ፣ በመጨረሻም ለእስራኤላውያንም ሆነ
ለአሕዛብ የደኅንነትና የሰላም ጊዜ እንደሚመጣ የሐዲስ ኪዳንን ዘመን በትንቢት ለማመልከት
የመጽሐፉ አከፋፈል፡-
ትንቢተ አሞጽ 9 ምዕራፎች ሲኖሩት በ 3 ዐበይት ክፍሎች ይከፈላል፡፡ እነርሱም፡
አሞ 1-2፡ በእስራኤላና በአጎራባቾቿ (ሶርያ፣ ፍልስጤም፣ ጢሮስ፣ ኤዶም፣ ቴማን፣ ሞዓብ፣ ይሁዳ)
የእግዚአብሔር ፍርድ እንደደረሰባቸው
አሞ 3-6፡ ሕዘበ እስራኤል የተደረገላቸውን የንስሃ ጥሪ ባለመቀበላቸው የተነገረው የትንቢት ቃል
ተግባራዊ እንደሚሆን በድጋሚ ማስጠንቀቂያ ስለመሰጠቱ
አሞ 7-9፡ እግዚአብሔር በእስራኤላውያን ላይ ስለሚያመጣው ፍርድ በራዕይ ለአሞጽ እንዳሳየው፣
እንዲሁም በፍጻሜው ዘመን (በዘመነ ሐዲስ) ስላለው ተስፋ
3. ትንቢተ ሚክያስ
ይህ መጽሐፍ ከጌታችን ከአምላካችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ልደት ከ 700 ዓመታት በፊት
በነበረው በነቢዩ ሚክያስ የተጻፈ ነው፡፡ ሚክያስ የስሙ ትርጉም እግዚአብሔርን የሚመስል ማን ነው? ማለት
ሲሆን አንድምታዊ ፍቺውም እግዚአብሔርን የሚመስል አዳም (ሰው) ነው የሚል ነው፡፡ ሰውን እንደ
አርአያችንና እንደ ምሳሌያችን እንፍጠር እንዲል ዘፍ….፤ ይህ ነቢይ በ 1 ኛ ነገ 22፡8 ላይ ከተጠቀሰው በይሁዳ
ንጉሥ በኢዮሳፍጥና በእስራኤል ንጉሥ አክዓብ ዘመን ከነበረው ነቢዩ ሚክያስ የተለየ ነው፡፡ ይህንን ትንቢት
4. ትንቢተ ኢዩኤል
ትንቢተ ኢዩኤል በነቢዩ ኢዩኤል ከጌታ ልደት 600 ዓመታት በፊት የተጻፈ መጽሐፍ ነው፡፡ ኢዩኤል
ማለት እግዚአብሔር አምላክ ነው ማለት ነው፤ ነገዱ ከነገደ ሮቤል ሲሆን አባቱ ባቱኤል እናቱ መርሱስ
ይባላሉ፡፡ ይህ ነቢይ ከነቢይነቱ በተጨማሪ ካህን እንደ ነበር ይነገራል፤ ኢዩኤል አገልግሎቱ በይሁዳ መንግሥት
ሲሆን በመጀመሪያ ለአገልግሎት የተጠራበት ምክንያት በሕዝቡ ላይ ሊወርድ ስላለው የአንበጣ መንጋ ጾምና
ጸሎት ይደረግ ዘንድ ሕዝቡን እንዲያስጠነቅቅ ነው፡፡ በኢዩኤል ትንቢት በጣም የሚታወቀው ክፍል
እግዚአብሔር በመጨረሻው ክፍለ ዘመን (በዘመነ ሐዲስ) በሥጋ ለባሽ ሁሉ ላይ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ
ለማፍሰስ የሰጠው ተስፋ ነው፡፡ (ኢዩ 2፡ 28-30)
የመጽሐፉ ዓላማ
ሕዘቡ ከእግዚአብሔር መአትና ቁጣ እንዲድኑ የሚመጣውን የእግዚአብሔር ፍርድ በመግለጥ ንስሐ
እንዲገቡና እንዲጾሙ ለማስጠንቀቅ
5. ትንቢተ አብድዩ
አብድዩ ማለተ የጌታ አገልጋይ ማለት ነው፡፡ ከጌታ ልደት 600 ዓመታት በፊት የነበረ ነቢይ ነው፡፡ ይህ
ነቢይ ኤልዛቤል የእገዚአብሔር ነቢያትን ባስገደለበችበት ወቅት መቶውን ነቢያት ወስዶ ወደ ዋሻ በመሸሸግ
ያዳነ ነቢይ ነው፡፡ ነቢዩ አብድዩ በኤዶማውያን (የዔሳው ዘሮች) ትዕቢትና ትምክህት ስለሚመጣው ፍርድ
ተንብይዋል፣ ጽፏል፡፡ ትንቢቱን የተናገረው በይሁዳ ንጉሥ በአክዓብ ዘመን እንደሆነ ይነገራል፤ ይህ ትንቢት 21
ቁጥሮች ያሉት ባለ 1 ምዕራች መጽሐፍ ነው፡፡
የመጽሐፉ ዓላማ
የኤዶማውያንን በአይሁድ ላይ ማመጽ፣ ትዕቢትና ውርደት ለመግለጥ
በሚመጣው የእግዚአብሔር ቀን ኤዶማውያን በኃጢአታቸው ምክንያት እንደሚቀጡ ለማስረዳት
በመጨረሻ ድኅነት ለእስራኤል፣ መንግሥትም ለእግዚአብሔር እንደሆነ ለማስረዳት
የመጽሐፉ አከፋፈል
ይህን መጽሐፍ በሦስት ክፍል በመክፈል ማጥናት ይቻላል፡፡
አብ 1፡1-9- በኤዶማውያን ላይ ስለሚፈጸመው ፍርድ ይናገራል፡፡
አብ 1፡10-14- በኤዶማውያን በእስኤላወያን ላይ ስለፈጸሙት በደል ያትታል፡፡
አብ 1፡15-21- ኤዶማውያነና አሕዛብ ስለሠሩት በደል ፍርድ እንደሚያገኙና እስራኤላውያን ነጻ
ወጥተው ወደ ሀገራቸው እንደሚመለሱ ይገልጽልናል፡፡
6. ትንቢተ ዮናስ
ዮናስ ማለት ርግብ ማለት ነው፡፡ በገሊላ ውስጥ የምትገኘው የጋትሔፈር ሰው የአማቴ /አሚቴ/ ልጅ
ነው ፤ የነቢዩ ኤልያስ ደቀመዝሙርም ነበረ፡፡ በዳግማዊ ኢዮርብዓም ዘመን በሰሜን የእስራኤል መንግሥት
የተነሣ ነቢይ ሲሆን ከኤልያስ ጋር ሳለም ሀብተ ትንቢት ተሰጥቶት ነበርና ባለ 4 ምዕራፍ የሆነው ትንቢትን
ተንብየዋል፡፡ ይህም ዘመን ከጌታ ልደት በፊት 400 ዓመታት ገደማ ነው፡፡ በአይሁዳውያን ልማድ
እንደሚጠቀሰው በሰራጵታ ትኖር የነበረችው ባልቴት ከሞትም ኤልያስ ያሥነሳላት ልጅ ነው ይባላል፡፡
መጽሐፉ ነቢዩ ዮናስ ወደ አሕዛብ ሀገር ነነዌ ወደ ተባለችው ከተማ በመሔደ በሕዝቡ ላይ
የተቃጣውን ፍርድ ለነነዌ ሰዎች በመንገር በንስሐ እንዲመለሱና ከእግዚአብሔር ትእዛዝ እንደደረሰው
ይገልጣል፡፡ ነገር ግን ዮናስ ትእዛዘ እግዚአብሔርን ባለ ማክበር ወደ ተርሴስ እንደተጓዘና በጉዞው ወቅት
የ/ደ/ይ/ቅ/ጊ/ቤ/ክ/ፍ/ሃ/ሰ/ት/ቤት ትምህርት ክፍል የተዘጋጀ 84
በተነሣው ማዕበል ምክንያት እግዚአብሔር ባወቀ በባለመርከበኞች ወደ ባሕር ተጥሎ በዓሣ አንበሪ ሆድ 3
ቀንና ሌሊት አድሮ በመጨረሻም ነነዌ ደርሶ የንስሐ ስብከት በማሰማት ሕዘቡን ከጥፋት እንዳዳነ ይገልጻል፡፡
የዮናስን ትንቢት የሰሙት የነነዌ ሰዎች ዛሬ ቃሉን ሰምተው ንስሐ ለሚገቡት ምዕመናን ምሳሌዎች ናቸው፡፡
ነቢዩ ዮናስ በትንቢቱ በአንድምታዊ ፍቺ የጌታቸንን ሞትና ትንሣኤ መስሎ አስረድቶናል፡፡
የመጽሐፉ ዓላማ
ዮናስ ከእስራኤል ወደ አሕዛብ የተላከ ነቢይ በመሆኑ እግዚአብሔር ለአሕዛብ ያለውን ፍቅር ለመግለጥ
ለእስራኤላውያን እግዚአብሔር አንድ እንደሆነ፣ በጠቅላላ በዓለም ላይ እንደሚፈርድና ጸጋውና
ክብሩም በሚከተሉት ላይ እንደሆነች ለማመልከት ሲሆን፤ እግዚአብሔር የእስራኤል ብቻ ሳይሆን
የአሕዛብም አምላክ እንደሆነና እስራኤላውያንም ለአሕዛብ ብርሃን እንጂ ጠላት መሆን
እንደሌለባቸው፣ የእግዚአብሔርን ቸርነት ለማመልከትና እግዚአብሔር አሕዛብ እንዲጠፉና
የማይፈልግ ርኅሩኅ አምላክ በመሆኑ በንስሐ ወደ እርሱ የተመለሱነትን ሁሉ በምሕረት እንዲጎበኝ
ለማሳየት ነው፡፡
የመጽሐፉ አከፋፈል
ይህ መጽሐፍ በ 4 ክፍሎች የሚከፈል ሲሆን እነርሱም፡
ዮና 1- ወደ ነነዌ እንዲሄድ የቀረበለትን ጥሪና አሻፈረኝ በማለቱ የገጠመውን ችግር እንመለከታለን፡፡
ዮና 2- ዮናስ በዓሣ አንበሪ ሆድ ውስጥ ሳለ ያሰማው ጸሎትና ጸሎቱም ተሰምቶ ወደ ቀድሞ ግብሩ
(ሥራው) መመለሱ
ዮና 3- ለነነዌ ሕዝብ የሚድኑበትን መንገድ መንገሩና እርሱን በመተግበራቸው ከመአቱ እንዳመለጡ
ምሕረት እንደተደረገላቸው
ዮና 4- ነቢዩ በከተማይቱ መዳን እንዳልተደሰተና እግዚአብሔርም ቅልን ምሳሌ በማድረግ ምሕረት
መልካም መሆኑን እንዳስተማረው ይነግረናል፡፡
7. ትንቢተ ናሆም
ናሆም ማለት መጽናናት ማለት ነው፤ ነገዱ ከነገደ ይሁዳ ሲሆን ከጌታ ልደት 700 ዓመታት በፊት
የተነሣ ነቢይ ነው፡፡ ከነቢያት መካከል የሆሴዕ፣ የሶፎንያስ፣ የዕምባቆምና የኤርምያስ የዘምን ጓደኛ ነበር፤
ከአነጋገሩ እንደሚታየው በነቢዩ ኢሳይያስ ዘመንና በንጉሥ ሕዝቅያስ ዘመን እንደነበር ይገመታል፡፡
መጽሐፉ የእስራኤልን መጽናናትና የነነዌን ፍርድ በአንድነት የያዘ ነው፤ ስለ ይሁዳ ሕዝብ
ከአሶራውያን ነጻ መውጣትና ስለ ነነዌ ዳግም መጥፋት የተነበየ ነቢይ ነው፡፡ ነነዌ በዮናስ ንስሐ ብትገባ
እንደምታመልጥ ሲነገር በናሆም ጊዜ ግን በቀጥታ ስለ ውድቀቷ ብቻ ነበር የተናገረው፡፡
የመጽሐፉ ዓላማ
ስለ ይሁዳ መጽናናትና ሁሉን ቻይ ስለሆነው እግዚአብሔር ትእግስት ለመናገር
በቀል የእኔ ነው በሚለው የእግዚአብሔር ቃል መሠረት የእስራኤል ሕዝብ ጠላት የነበረቸውን ነነዌን
ከጥፋት ከተመለሰች በኋላ ባሳየቸው ጭካኔ እግዚአብሔር የሚበቀላት መሆኑን ለመግለፅ
ነነዌና አሦር ምን ታላቅ ከተማና ገናና መንግሥት ቢሆኑም በእግዚአብሔር ኃይል ስላልነበሩ
መጥፋታቸውን ለማሳወቅ
የመጽሐፉ አከፋፈል
መጽሐፉ 3 ምዕራፎች ያሉት ሲሆን አከፋፈሉም እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡
ናሆ 1- እግዚአብሔር የፍርድና የበቀል አምላክ እንደሆነ ፍርዱም እንደማይዛባና ሰው ደግሞ ስለ
ሠራው በደል ዋጋውን እንደሚቀበል፤
8. ትንቢተ ዕንባቆም
ትንቢተ ዕንባቆም ከጌታ ልደት 600 ዓመታት በፊት የተጻፈ መጽሐፍ ሲሆን ጸሐፊው ዕንባቆም
ይባላል፡፡ ዕንባቆም ማለት እቅፍ ማለት ነው፤ ነገዱ ከነገደ ሌዊ ሲሆን አባቱ ኢያሱ በመባል ይታወቃል፡፡ ይህ
ነቢይ ያላገባ ድንግል፣ ካህንና የቤተመቅደስ ዘማሪ የነበረ እንደሆነ ሊቃውንት ይናገራሉ፡፡ በሌላ ታሪክ ደግሞ
ዳንኤል በባቢሎን ተማርኮ ሳለ ዕንባቆም ለአጫጆች ምሳ ይዞ ሲሄድ የእግዚአብሔር መልአክ በራሱ ጠጉር
አንጠልጥሎ ወደ ባቢሎን ወስዶ ለዳንኤል ምግብ እንዳቀበለው ተተርኳል፡፡
መጽሐፉ የአይሁድ ሕዝብ በኃጢአት ስለሚደርስበት መከራ፣ ከለዳውያን በሚገዟቸው ሕዝቦች
ባደረሱት ግፍ የሚደርስባቸውን ቅጣትና ነቢዩ የጸለየውን ጸሎት የያዘ ነው፤ ዕንባቆም ብዙ በደልና ክፋትን
ስለተመለከተ እግዚአብሔር እንደቸርነቱ ብዛት የማይፈርድ መስሎት ደጋግሞ ጠይቆታል፡፡ ይህ ነቢይ
ትንቢቱን የተናገረው በይሁዳ ኢዩአቄም በነገሠበትና ነቢዩ ኤርምያስ በነበረበት ዘመን ነው፡፡
የመጽሐፉ ዓላማ
የእግዚአብሔር ፍርድ ፣ የኢየሩሳሌም መደምሰስና በእግዚአብሔር ኃይል የሚያምነውን ሀገረ
ባቢሎንን ለማሳየት
ጻድቅን ደግሞ ስለ እምነቱ የሚያድነው መሆኑም ለማሳወቅ
የመጽሐፉ አከፋፈል
መጽሐፉ ሦስት ምዕራፎች ሲኖሩት የየምዕራፉ መልእክትም የሚከተለው ነው፡
ዕን 1- ዕንባቆም ኃጢአት ሲበዛ የጸለየውን ጸሎትና ጸሎቱ እንደተሰማ፤ እግዚአብሔርም በሰጠው
መልስ በባቢሎናውያን መሣሪያነት ቅጣት እንደሚያመጣና ጊዜው ሲደርስም ነቢዩ ትንቢት
እንዲናገር ማዘዙ
ዕን 2- ከለዳውያን (ባቢሎናውያን) በትዕቢታቸው፣ በግፍ ሥራቸው፣ ሌሎች ሀገራትን በግድ
በማስገበራቸው፣ በዝርፊያቸውና ጣዖትን በማምለካቸው ምክንያት ስለሚያገኛቸው ችግርና ቅጣት
የተተነበየበት ክፍል ነው፡፡
ዕን 3- ነቢዩ እግዚአብሔር ለሕዝብ ያደረገውን ጥበቃ በማሰብ የጸለየውን የምሥጋና ጸሎት፣ ወደ
ፊትም እስኤራላውያን መልካም ሥራቸውን እንዲጠብቁ፣ የእግዚአብሔር ርዳታና ጥበቃ
እንዳይለያቸው ያቀረበው ተማጽኖ ይገኝበታል፡፡
9. ትንቢተ ሶፎንያስ
ይህ የትንቢት መጽሐፍ ከጌታ ልደት 700 ዓመታት በፊት በይሁዳ በነበረው ነቢይ ሶፎንያስ የተጻፈ
ነው፤ ሶፎንያስ የስሙ ትርጓሜ እግዚአብሔር ሰውሯል (ጠብቋል) ማለት ነው፤ ነገዱ ከነገደ ንፍታሌም ሲሆን
እናቱ ንሠባ ትባላለች፡፡ በሶፎ 3 ላይ የተጠቀሰው ሕዝቅያስ አያቱ ሲሆን የኢዮስያስ የአጎት ልጅ እንደነበረም
ይተረካል፡፡
ካህናትና ነቢያት በዘመኑ በብልጽግና ሥራ፣ በጣዖት የአምላክን ቤተመቅደስን በማርከስና
የእግዚአብሔርን ሕግ በመጣስ የታወቁ ነበሩ፡፡ የሶፎንያስ ትንቢት በይሁዳ ላይ ብቻ ሳይሆን በምድር ሁሉ ላይ
ስለሚመጣው የእግዚአብሔር የፍርድ ቀን ጭምር የተነገረ ነው፡፡ እግዚአብሔርን የሚፈሩት ትሑታን ሁሉ
ግን ፍጽም የሆነ ተስፋ እንዳላቸው ተንብዮላቸዋል፡፡
10. ትንቢተ ሐጌ
ትንቢተ ሐጌ ከጌታችን ከመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልደት 520 ዓመታት በፊት በኢየሩሳሌም
ይኖሩ ለነበሩ አይሁድ የተነገረ ትንቢት ነው፡፡ የመጽሐፉ ጸሐፊም ነቢዩ ሐጌ ነው፡፡ ሐጌ ማለት በዕብራይስጠተ
‹‹በዓላዊ›› ማለት ነው፤ ይህም በበዓል ቀን ተወለደ እንደማለት ነው፡፡ በቤተክርስያናችን ትውፊት ነቢዩ
ሐጌ ካህን እንደነበር ይነገራል፤ ይህ አስተሳሰብ የተመሠረተው በሰብዓ ሊቃናት ትርጉም በመዝሙረ ዳዊት
ውስጥ በሐጌና በዘካርያስ ስም የተሰየመ መዝሙር (መዝ 145-148) ስለሚገኝ ነው፡፡ ይህም ሐጌ በክህነት
አገልግሎት ጊዜ የዘመረው መዝሙር ነው ለማለት ነው፡፡
የመጽሐፉ ዓላማ
ሕዝቡ የተጀመረውን ቤተ እግዚአብሔር እንዲሠሩ በማበረታታት ለእግዚአብሔር ሊያደርጉት
የሚገባቸውን ሳያስቀድሙ የራሳቸውን ቢሠሩ በረከተ እግዚአብሔርን ማግኘት እንደማይችሉ
ለማስገንዘብ፡፡
የመጽሐፉ አከፋፈል
ትንቢተ ሐጌ ባለ 2 ምዕራፍ መጽሐፍ ሲሆን በ 4 ክፍሎች ተከፍሎ ሊጠና ይችላል፡፡
ሐጌ 1- የእግዚአብሔርን ቤተመቅደስ ለመሥራት ተነሡ የሚል የነቢዩ መልእክት የቀረበበት ነው፡፡
ሐጌ 2፡1-9- አዲሱን ቤተመቅደስ ምንም እንኳ ሰዎች ቢሠሩትም በእነርሱ ላይ አድሮ የሚሠራውእግዚአብሔር
እንደሆነና ይሄኛው ቤተ መቅደስ በወርቁና በውበቱ ከበፊተኛው ቢያንስ በመንፈሳዊ ጌጡ እጅግ የተዋበ እንደሆነ
ነቢዩ የገለጠበት ክፍል ነው፡፡
ሐጌ 2፡10-19- በጎ ነገርን ለሚያደርጉና የእግዚአብሔርን ቤተመቅደስን ለሚሠሩ እግዚአብሔር ‹‹እባርካችኋለሁ››
እያለ የነገራቸውን የተስፋ ቃል ይዟል፡፡
ሐጌ 2፡20-23- የይሁዳ አለቃ የነበረው ዘሩባቤልን እግዚአብሔር የጠላቶቹን ኃይል በማደስም እርሱን ከፍ ከፍ
እንደሚያረገው የተነገረውን የትንቢት ቃል ይዟል፡፡
የመጽሐፉ ዓላማ
የቀረውንና ተጀምሮ የተቋረጠውን የቤተመቅደስ ሥራ መፈጸም ታሪካዊ ግዴታ እንደሆነ ለማሳወቅ
ሁለተኛውን ቤተመቅደስ በመሥራት ላይ ያሉ ሕዝቦችን ለማጽናናተ፣ ኢየሩሳሌም እንደምትበለጽግና አሕዛብ
አንደሚወድቁ ለማጠየቅ
የሚመጣው በረከትም በመሲሑ በኩል መሆኑን ለማስገንዘብ
የመጽሐፉ አከፋፈል
መጽሐፉ 14 ምዕራፎች ሲኖሩት በ 3 ዋና ዋና ክፍሎች ይከፈላል፡፡
ዘካ 1-6፡ በዚህ ክፍል ነቢዩ ዘካርያስ ያያቸው የተለያዩ ራእዮች ተገልጸዋል፤ ከእነዚህም ውስጥ፡ ከምርኮ የተመለሱ
ሰዎች ታዛዥነት እንደሚጠበቅባቸው፣ ስለ ቤተመቅደሱ አሠራር፣ ስለ ካህኑ ዘውድ መጫን፣ ስለ ክህነት ሥራዎች፣
ሕግጋቱን በተዳፈሩትና በሚያፈርሱት ላይ ስለሚደረሰው ርግማን፣ ስለ ጌታ መምጣትና ስለ መለኮታዊ ክብሩ
ዘካ 7-8፡ በኢየሩሳሌም መፍረስ ጊዜ አረማውያን ሕግን አፍርሰው የጾም ቀናትን በዓላት የበዓል ቀናተን አጽዋማት
አድርገዋቸው ነበርና እነርሱ ተለውጠው ሥርዓቱ እንደቀድሞው እንዲሆን የተሰጠውን ትእዛዝ ይዟል፡፡
ዘካ 9-14፡ በዚህ ክፍለ ወስጥ ስለ ጌታችን የተነገሩ ትንቢቶች ይገኙበታል፡፡ እነዚህም፡-
ወንጌል ስለሚሰበክበተ ዘመን፣ ስለ ወንጌል መስፋፋተና ያመኑ ሰዎች ስለሚወረድላቸው በረከት
ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያ ውርንጭላ ላይ ሆኖ ወደ ኢየሩሳሌም ስለ መግባቱ
አይሁድ የጌታን ሕይወት ለማጥፋት የከፈሉትን የገንዘብ መጠን
ስለ ጌታችን ጎን መወጋትና ከጎኑ ደምና ውኃ (ማየ ገቦ) ስለመፍሰሱ፣ አይሁድም ወደ ክርስቶስ ሲመለሱ
አባቶቻቸው ያደረሱነትን ሕማም በማስታወስ የሚያዝኑ ስለ መሆናቸው
በጌታችን ሕማም ወቅት ደቀመዛሙርቱ ጥለውት እንደሚሸሹ
የቤተክርስቲያን አባላት አይሁድ፣ አረማውያንና ሌሎች ሕዝቦች እንደሚሆኑ የተነገረ ትንቢትን አካትቶ
ይዟል፡፡
የመጽሐፉ ዓላማ
የእግዚአብሔር እስራኤልን መክሰስና በንስሐ በኩል ወደ እርሱ እንዲመለሱ ወይም እንዲቀርቡ ለማድረግ
ምዕራፍ ፫
የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት
ኪዳን በሁለት ወገኖች መካከል የሚመሠረት፣ በመሐላ የሚጸና ከተመሠረተ በኋላ በሁለቱ ወገኖች መካከል እንደ ሕግ
ኾኖ የሚሠራ ስምምነት ነው፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ኪዳን ሲባል ከእግዚአብሔር ለሰዎች የተሰጠ እና ሰዎች በእምነት
የተቀበሉት ውል ነው፡፡ ከእግዚአብሔር ለሰዎች የተሰጠ የደኅንነት ኪዳን ነው፡፡ ይኸውም በወልደ እግዚአብሔር በኢየሱስ
ክርስቶስ የሚያምን ሁሉ የዘለዓለም ሕይወት እንደሚያገኝ የሚያረጋግጥ ኪዳን ነው፡፡ የዚህ የደኅንነት ኪዳን ቃላትም፡-
‹‹ያመነ የተጠመቀ ይድናል፡፡›› (ማር 6፤16)
‹‹በልጁ የሚያምን የዘለዓለም ሕይወት አለው፡፡›› (ዮሐ 3፤16)
‹‹እውነት እውነት እላችኋለሁ፤ በእኔ የሚያምን የዘለዓለም ሕይወት አለው፡፡›› (ዮሐ 6፤47)
‹‹ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃል፤ በአፉም መስክሮ ይድናል፡፡›› (ሮሜ 10፤131 ዮሐ 2፤21) የሚሉትና የመሳሰሉት ናቸው፡፡
ሐዲስ ኪዳን ሲባል ፊተኛ ኪዳን እንዳለ ያመለክታል፡፡ ይህም ፊተኛ ኪዳን ብሉይ ኪዳን ነው፡፡ ብሉይ ኪዳንን “ብሉይ”
ያሰኘው የሐዲስ ኪዳን መምጣት ነው፤ ‹‹አዲስ በማለት ፊተኛውን አስረጅቷል›› እንዲል (ዕብ 8፤13)፡፡ ‹‹ያረጀ›› የሚለው
ቃል ያለፈበት መሆኑን አያመለክትም፡፡ እርጅናው የዕድሜ ባዕለጸግነቱም የሚገልጽ ብሉይነቱም በዘመን ብዛት ነው
እንጂ፡፡ የምሥጢራት አፈጻጸም ሁኔታ ተለወጠ እንጂ ቃሉ አይሠረዝም ወይም አይሻርም፡፡ ማቴ 5፣17-20
የማቴዎስ ወንጌል 28 ምዕራፎች በመያዙ በምዕራፎች ብዛት የመጀመሪያው ወንጌል ሲሆን 1068
ቁጥሮችን በመያዝ በቁጥሮች ብዛት ከማርቆስ ወንጌል ቀጥሎ በሁለተኛ ደረጃ ተቀምጧል፡፡ ከአንድ ሺህ
ስድሳ ስምንት ቁጥሮች መካከል ስድስት መቶ አርባ አራቱ የጌታን ትምህርቶች የያዙ በመሆናቸው ከሌሎቹ
ወንጌላት በተለየ መልኩ ከዮሐንስ ወንጌል ጋር ይበልጥ ይዛመዳል፡፡ ወንጌሉን የጻፈው ለአይሁድ በመሆኑ ከ 150
በላይ ጥቅሶችን ከብሉይ ኪዳን አቅርቧል፡፡ በዚህ የተነሣ ብሉይ ኪዳንን አብዝቶ በመጥቀስ ከሌሎች
ወንጌሎች ይበልጣል፡፡ ወንጌላዊው ይህንን ወንጌል ሲጽፍ ትውፊትን በብዛት ተጠቅሟል፡፡ ይህንንም
ያደረገው ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሲስ ክርስቶስ ቀድሞ በነቢያት የተነገረለት መሲሕ መሆኑን
ለማረጋገጥ ነው፤ ስለዚህም አንድን ታሪክ ከጻፈ በኋላ በነቢዩ የተጻፈው ተፈጸመ ብሎ ይመሰክራል፡፡
የማቴዎስ ወንጌል ከማርቆስ ወንጌል ቀጥሎ በሁለተኛነት ተጽፎ እያለ የመጀመርያውን ተርታ ያገኘበት
ዋናው ምክንያት አቀራረቡ ለብለይና ለሐዲስ ኪዳን ድልድይ ስለሆነና የብሉይ ኪዳን ትንቢትና ምሳሌ
በሐዲስ ኪዳን መፈጸሙን ስለሚያሳይ ነው፡፡
ወንጌሉ የተጻፈላቸው ሰዎች
ቅዱስ ማቴዎስ ወንጌሉን የጻፈው ከዕብራውያን /ከአይሁድ/ ወደ ክርስትና ለተመለሱ ሰዎች ነው፡፡ በወንጌል
ትርጓሜ እንደተገለጠው ‹‹ ምድረ ፍልስጥኤም ለማቴዎስ በዕጣ ደረሰችው፣ ከዚያ ገብቶ ጌታ ከጽንስ
ጀምሮ ያደረገውን ተአምራት፣ ያስተማረውን ትምህርት የሠራውን ትሩፋት ቢነግራቸው በወንጌል አምነው
ተጠመቁ፡፡ ትምህርት ካልደረሰበት ለማዳረስ ወጥቶ በሚሄድበት ጊዜ በቃል ያለ ይረሳል፤ በመጽሐፍ ያለ
ይወረሳል ብለውት ጽፎላቸዋል፡፡›› ማቴዎስ ወንጌሉን የጻፈው ለዕብራውያን መሆኑ ከጥንት የቤተክርስቲያን
አባቶች መካከል ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ የቅዱሳት መጻሕፍትን ቀኖና በገለጸበት ጽሑፉ ‹‹ማቴዎስ
ለዕብራውያን ተአምራተ ኢየሱስን ጻፈ›› ብሏል፡፡ የመጽሐፉም አጠቃላይ ይዘት ለዕብራውያን ክርስቲያኖች
የተጻፈ መሆኑን ያሳየናል፡፡
የመጽሐፉ ዓላማ
አይሁድ ጌታ በድንግልና አልተወለደም ብለው ስለነበር ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ያለ አባት
መወለዱን ለመመስከር
ኦሪትን ሊሽር መጣ ብለውት ነበርና ኦሪትን ሊፈጽም እንጂ ሊሽር አለመምጣቱን ለመግለጥ
ጌታችን ከአብርሃምና ከዳዊት ዘር የተወለደ ፍጹም ሰው መሆኑን ለማስረዳት
በሰዎች ዘንድ ጌታ ከነቢያት አንዱ ነው ቢባልም ከነቢያት አንዱ እንዳልሆነና የእግዚአብሔር ልጅ
እግዚአብሔር መሆኑን ለመግለጥ
በዘመነ ብሉይ የተነገረለት፣ ሱባኤ የተቆጠረለት መሲሕ፣ የዓለም ጌታ፣ የአይሁድና የአሕዛብ መድኃኒት
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መሆኑን ለማስረዳት
በሕግና በነቢያት መጻሕፍት ስለ ጌታ የተነገረለትን ትንቢታዊ ቃላት በመጥቀስ ፍጻሜያቸውን
ለማስረዳት
የ/ደ/ይ/ቅ/ጊ/ቤ/ክ/ፍ/ሃ/ሰ/ት/ቤት ትምህርት ክፍል የተዘጋጀ 90
የመጽሐፉ አከፋፈል
ወንጌሉ 28 ምዕራፎች ሲኖሩት እያንዳንዱን ከፍለን እናያቸዋለን፡፡
ነገር ግን ሌሎች የላቲን ቃላትን አልተረጎመም፡፡ ለምሳሌ፡ - ጴጥሮስ የሚለውን ዓለት ማለት ነው ብሎ
አይተረጉመውም፡፡
ሌሎች ሥልጣናት
ሳይነግሩት እንደሚያውቅ /2፡8/
የአምስት ገበያ ሕዝብ ስለመመገቡ /6፡23-44፣ 8፡1-9/
የሰንበት ጌታዋ ስለመሆኑ /2፡28/
በቤተመቅደሱ ካህናቱ እንኳ ሊገፉት ያሰተቻላቸው ታላቅ ሥልጣን እንደነበረው /11፡33/
ጌታ መሆኑንና ኃጢአትን ይቅር የማለት ሥልጣን እንዳለው /11፡3፤ 2፡10/
ወደፊት ስለሚሆነው እንደሚያውቅ(ትንቢት)/8፡3-38/
ብዙ ሕዝብ ይከተለው እንደነበር /1፡28-33፣ 3፡7-9፣ 4፡1-2፣ 6፡32-34፣ 5፡24፣ 9፡15፣ 7፡24
የ/ደ/ይ/ቅ/ጊ/ቤ/ክ/ፍ/ሃ/ሰ/ት/ቤት ትምህርት ክፍል የተዘጋጀ 94
በአጠቃላይ የማርቆስ ወንጌል ምንም እንኳ አጭር ቢሆንም ለአጠናን ይመቸን ዘንድ 16 ቱን የማርቆስ
ወንጌላት ምዕራፍ በ 15 ዐበይት ክፍሎችና የመጽሐፉ አከፋፈል እንከፍላቸዋለን፡፡
ምዕራፍ 1፡- የመጥምቁ ዮሐንስ ስብከትና የኢየሱስ ክርስቶስ መጠመቅ
ምዕራፍ 2፡- ሽባውን ሰለመፈወሱ እንዲሁም ስለጾምና ሰንበት የቀረበ ጥያቄ
ምዕራፍ 3፡- ጌታ በገሊላ ስላደረገው ስብከት
ምዕራፍ 4፡- በምሳሌ ስለማስተማሩ
ምዕራፍ 5 ና 6፡- ሕሙማንን ስለመፈወሱና ሐዋሪያትን ስለመላኩ
ምዕራፍ 7፡- ሰውን ሰለሚያረክሱ ነገሮች
ምዕራፍ 8፡- እንጀራውን አበርክቶ ስለመመገቡ
ምዕራፍ 9፡- ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከደብረ ጣቦር ብርሐን መለኮቱን፤ክብሩን ስለመግለጡ
ምዕራፍ 10፡- በይሁዳ ስለማስተማሩና በኢሪኮ ዓይነ ስውሩን ስለመፈወሱ
ምዕራፍ 11፡- በክብር ወደ ኢየሩሳሌም እንደገባ
ምዕራፍ 12፡- ስለ ወይን ቦታ ሰራተኞች
ምዕራፍ 13፡- ስለ ዓለም ፍፃሜ ማስተማሩ
ምዕራፍ 14፡- ስለጌታ እራትና ስለጌቴ ሴማኒ ጸሎት
ምዕራፍ 15፡- ስለጌታ መያዝ፣ስለጌታ መሰቀል፣መሞትና መቀበር
ምዕራፍ 16፡- ስለጌታ ትንሣኤና ስለ ሐዋርያት መላክ
ቅዱስ ዮሐንስ አባቱ ዘብዴዎስ፣ እናቱ ደግሞ ሰሎሜ (ማርያም ባውፍልያ) ይባላሉ፡፡ በአባቱ ከነገደ ይሁዳ ሲሆን በእናቱ ደግሞ ከነገደ
ሌዊ ነው፡፡ ሀገሩም የገሊላ ክፍል በምትሆን በሲዶና ነው፡፡ ታላቅ ወንድሙም ያዕቆብ ይባላል፤ ርሱም በሄሮድስ አግሪጳ ዘመን በ 44 ዓ.ም
በሰማዕትነት ያረፈው ነው፡፡ እናቱ ቅድስት ሰሎሜም ከ 36 ቱ ቅዱሳት አንስት መካከል አንዷ ስትሆን ጌታ በገሊላ ሳለ ያገለግሉት ከነበሩት
ቅዱሳት አንስትም አንዷ ነበረች፤ ጌታችን በተነሣባት ማለዳ ሽቱ ለመቀባት ከሔዱት ሴቶችም መካከል አንዷ ነች፡፡ (ማር 16፤1) እጅግ
መልካምና ጻድቅ ሴት እንደ ነበረችም አባቶች መስክረውላታል፡፡ (ማቴ 27፤56)
ወንጌላዊው ዮሐንስ ከሦስቱ አዕማደ ሐዋርያት (ምስጢረ ሐዋርያት፤ መዝገበ ሐዋርያት) መካከል አንዱ ነው፡፡ ይህንንም ቅዱስ
ጳውሎስ በገላትያ መልእክቱ ላይ፣ “አዕማድ መስለው የሚታዩ ያዕቆብና ኬፋ ዮሐንስም. . .” በማለት ገልጦታል፡፡ ገላ 2፤9፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ
አዕማድ ሐዋርያ መባሉም ለጌታ ፍቅር ስለሚቀና ነው፡፡ ከጽኑ ፍቅሩም የተነሣ አይሁድን ሳይፈራ እስከ እግረ መስቀል የደረሰ ሐዋርያ ነው፡፡
በዚህም ምክንያት ጌታችን በመስቀል ሥር የተገኘችውን እናቱን በመስጠት ለርሱ ያለውን ፍቅር ገልጾለታል፤ ምክንያቱም አባት ለሞት በተቃረበ
ጊዜ ያለውን ሃብቱን የሚናዘዘው ለሚወደው ልጁ እንደሆነ ሁሉ ጌታችንም ምድራዊ ሃብት ባይኖረውም የዕውቀት ማኅደር፣ መዝገበ ምስጢር
የሆነችውን የቀረችውን አንድ ሃብቱን እመቤታችንን የሰጠው ለሚወደው ደቀመዝሙሩ ለቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ነው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ
እመቤታችንን ከተረከበ በኋላ እስካረፈችበት ጊዜ ድረስ ለ 15 ዓመታት በቤቱ አኑሯታል፡፡
ከበዓለ ጰራቅሊጦስ በኋላ ከቅዱስ ጴጥሮስ ጋር በመሆን በኢየሩሳሌም፣ በአንጾኪያ፣ በሎዶቅያ፣ በእስያ ከተሞች በተለይም በኤፌሶን
አስተምሯል፡፡(ዮሐ 19፡27) በኤፌሶን በሚያስተምርበት ጊዜ ንጉሥ ድምጥያኖስ ለራሱ ምስል እንዲሰግድ ባዘዘበት ወቅት ዮሐንስ ይህን
በመቃወም ወደ ፍጥሞ ደሴት ተግዟል፡፡ በወጣትነቱ ተጠርቶ በዕለተ ዓርብ ያየውን የጌታች መከራ እያሰበ ያነባ የነበረ የተጠራበት የአገልግሎት
ጊዜው ጀምሮ በፍቅር በታማኝነት እስከመጨረሻው ድረስ የጸና ከጌታው ያልተለየ ሐዋርያ ነው፡፡
የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌል
የቅዱስ ወንጌል የተጻፈው ከፍጥሞ ደሴት ግዞቱ ሲመለስ በኤጂያን ባሕር ወደብ በ 96 ዓ.ም አካባቢ ነው፡፡ ወንጌሉ ከትረካ ይልቅ ነገረ መለኮታዊ
(theological) ይዘት ስላለው ከሌሎቹ ወንጌላት(Synoptic Gospels) ይለያል፡፡ ሐዋርያው ዮሐንስ ወንጌላትን ሲጽፍ ዋና ሐሳቡ የወልደ
እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ የባሕርይ አምላክነት መመስከር ነው፡፡ (ዮሐ 20፡21) በመደጋገምም ‹‹የዘለዓለም ሕይወት የሚሰጥ የእግዚአብሔር ልጅ››
ይለዋል፡፡ ተአምራቱም አምላክነቱን የሚገልጡ ናቸው፡፡ (ዮሐ 2፡11) ኢየሱስ ክርስቶስ በሚጸልዩበት ጊዜ የእግዚአብሔር አብ ልጅ መሆኑን በዚሁ ወንጌል
ላይ ገልጧል፡፡ (ዮሐ 17፡1-5) በዚህ ወንጌል ሰባት ጊዜ “እኔ ነኝ” በማለት ማንነቱን ገልጧል፡፡ (ዮሐ 6፡35) ቅዱስ ቶማስም በዚህ ወንጌል ‹‹ጌታዬ
አምላኬም›› በማለት ጌትነቱንና አምላክነቱን መስክሯል፡፡ (ዮሐ 20፡28)
መጽሐፍ በአጠቃላይ የጌታችንን ታሪክ፣ ትምህርትና ተአምራት በጥልቀት የሚመረምር ቢሆንም ወንጌሉ የተጻፈበት ሌሎች ዝርዘር ምክንያቶች
አሉት፡፡ ከእነርሱም በጥቂቱ
1. የሐዋርያት ሥራ
መጀመሪያ ክቡራን ቅዱሳን ሐዋርያት ለተልእኮ የተመረጡተት በራሱ በጌታችን በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
መሆኑን እንጠቅሳለን፡፡ ሐዋርያት የሚለው ቃል የሐዋርያ ብዙ ቊጥር ሲሆን ሐዋርያ ማለትም ‹‹ሖረ›› ‹‹ሔደ›› ካለው
የግእዝ ቃል የወጣ ሲሆን ትርጉሙም ደጃዝማች ፣የተላከ፣ሔያጅ፣ለዑክ ማለት ነው፡፡(ማቴ ትርጓሜ 10፡2)፡፡
የሐዋርያት ሥራ የ 12 ቱን የመላውን ታሪክ በመጠኑ ይናገራል፡፡ይህም በኢየሩሳሌም ውስጥ 12 ቱም ሐዋርያት
የሠሩትን ሥራ የሚገልጽ ክፍል ነው፡፡
41
የግሪክና የላቲን አባቶች እና ሌሎች የአሌክሳንድሪያ ጽሑፎች ላይ ተጠቅመውበታል፡፡
42
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
የመልእክታት ክፍል
የቅዱስ ጳውሎስ የቀድሞ ስሙ ሳውል ሲሆን ትርጉሙም የእግዚአብሔር ጥያቄ ማለት ነው። ቅዱስ ጳውሎስ ታላቅ አእምሮ የነበረው የማስተዋል
ኃይል የተሰጠው መንፈሳዊ ፍላጎትም የነበረው ሰው ነው። ወላጆቹ በልጅነት ወደ ኢየሩሳሌም ወስደው ለታላቁ የሕግ መምህር ለገማልያ ሰጡት።
በአይሁድም የአስተዳደግ ሥርዓት አሳደጉት። ሐዋ 5፣34 ዕብራውያን ከትምህርትም በተጨማረ ጥበብ ዕድ አብረው ስለሚያስተምሩ ጳውሎስም ድንኳን
መስፋት ተምሮ ነበር። ሐዋ 22፣3 ቅዱስ ጳውሎስ የሕግና የፍልስፍና ትምህርት ቤቶች መናኽሪያ በሆነችው ስመ ጥር የጠርሴስ ከተማ የኖረና በዘመኑ
የነበረውን የሕግ ትምህርት እንደተማረ ይታወቃል።
ቅዱስ ጳውሎስ ለአባቶቹ ሕግ ቀናተኛ በነበረ ጊዜ የክርስትናን ትምህርት በበኩሉ ይቃወም ነበር። ስለዚህ ጳውሎስ ለአባቶች ሕግ ቀናተኛ ሆኖ
ክርስቲያኖችን ከሚያስተምሩበት ሀገር አስወጥቶ ለማሳደድ ተነሣ፣ ክርስቲያኖችም ከጳውሎስና ከሌሎች አይሁድ ፍራቻ የተነሣ ከኢየሩሳሌም እየወጡ ወደ
ተለያዩ ቦታዎች ይሰደዱ ነበር። ገላ 1፣13-14
የቅዱስ ጳውሎስ መጠራት ከቀዳሜ ሰማዕት ከቅዱስ እስጢፋኖስ ሞት የተነሣ ነበር፡፡ በተለይ ወደ ሶርያ፣ ወደ ደማስቆ ክርስቲያኖች ገብተው ብዙ
አይሁዶችን አጠመቁ፤ ሳውልም በዚህ ብስጭት ክርስቲያኖችን ከኢየሩሳሌም ለማሳደድ ከሊቀ ካህናቱ ፈቃድ ወስዶ አብረው ከሚጓዙት ጋር ከደማስቆ በር
ሲደርስ ድንገት ከሰማይ መብረቅ ወረደና መታው፡፡ ወደቀም፣ ዓይኖቹም ታወሩ፡፡ (ሐዋ 9፡4-28፣ ሐዋ 22፡1-12) ከሰማይም “ሳውል ሳውል ለምን
ታሳድደኛለህ” የሚል ድምጽ ሰማ፡፡ ሳውልም “አንተ ማን ነህ አቤቱ” አለው፡፡ ጌታም “የምታሰድደኝ የናዝሬቱ ኢየሱስ ነኝ” አለው፡፡ ጌታም የምትድነበትን
ታገኛለኛህና ወደ ከተማው ሂድ ብሎ አጽናናው፡፡ ተነስቶ አብረውት ከነበሩት ተጓዦቹ ጋር ገባ፡፡ አብረውት የነበሩት ሰዎች ጳውሎስን ድምጽ ይሰሙ ነበር
እንጂ የሚያናግረውን ሰው አያዩም ነበር፡፡ ወደ ከተማውም ገብቶ ሦስት ቀን ሦስት ሌሊት ሳይበላ ሰነበተ፡፡ በዚያ ከተማ ከ 72 አርድዕት ወገን ለሚሆን
ለሐናንያ ጌታ በሕልም ሳውልን እንዲያጠምቀው ነገረው፡፡ ሳውልን ካለበት ቤት ሲያጠምቀው ዓይኑ በራለት፣ መንፈስ ቅዱስ አደረበት ምስጢርም
ተገለጠለት፣ ማን ያሳድድ እንደነበርም ተረዳ ወዴት መጓዝ እንደነበረበትም ወሰነ፡፡ ለአዲሱ የክርስትና ሃይማኖቱም ቀናተኛ ሆኖ ሳይውል ሳያድር ዕለቱኑ
ማስተማር ጀመረ፡፡
ቅዱስ ጳውሎስ ጥቂት ቀን በደማስቆ ቆይቶ በዓረቢያ ምድረ በዳ ሦስት ዓመት ተቀመጠ፡፡ ሱባኤውንም ፈጸመ (ገላ 1፡17)፡፡ ከዚያም በኋላ ወደ
ደማስቆ ተመልሶ ብዙ አይሁድንና አሕዛብን በማሳመኑና በማጥመቁ ብዙዎች አይሁድ ተቆጥተው ሊገድሉት የደማስቆን በር ቀንና ሌሊት ሲጠብቁ የሰሙ
ክርስቲያኖች በመስኮት አስወጥተው በቅርጫት አውርደው ወደ ኢየሩሳሌም ላኩት፡፡
ቅዱስ ጳውለስ በሦስት ሐዋርያዊ ጉዞዎቹ በተለያዩ ሀገራት አስተምሯል፡፡ ሲያስተምርም የተመቸ ጊዜና ቦታ እየጠበቀ ሕዝብ በተሰበሰበበት ቦታ
በምኩራብ፣ በአደባባይ፣ በገቢያ፣ በትያትር ቦታ፣ በደስታም በኃዘንም ጊዜ ያስተምር ነበር፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ በቃል ካስተማራቸውና ካሳመናቸው ሰዎች ይልቅ
በመልእክቱ ያስተማራቸውና ያሳመናቸው ሰዎች እጅግ ብዙ ነበሩ፡፡ ራሱም ድንኳን በመስፋት እየሠራ ራሱንና ሰውንም ይረዳ እንደነበር ተጽፏል (1 ኛ ቆሮ
4፡12፣ 9፡6፣ 2 ኛ ቆሮ 11፡17፣ 1 ኛተሰ 2፡9፣ ሐዋ 20፡34)፡፡ አንዲህ ዓይነቱ የውሸት ያይደለ የእውነት፣ በቃል ብቻ ተነግሮ ያልቀረ በሥራ የተተረጎመ፣
የሐውልት ጥቅስ ብቻ ያይደለ የሕይወት ተልዕኮውን ሲፈጽም ‹‹ መልካሙን ገድል ተጋድዬአለሁ፥ ሩጫውን ጨርሼአለሁ፥ ሃይማኖትን ጠብቄአለሁ፤ ወደ
ፊት የጽድቅ አክሊል ተዘጋጅቶልኛል፥ ይህንም ጻድቅ ፈራጅ የሆነው ጌታ ያን ቀን ለእኔ ያስረክባል፥ ደግሞም መገለጡን ለሚወዱት ሁሉ እንጂ ለእኔ ብቻ
አይደለም።›› ሲል መስክሯል (2 ኛ ጢሞ 4፡7-8)፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚያስረዳን ቅዱስ ጳውሎስ በተለያዩ ዓመታት በብዙ ቦታዎች ሦስት የተላያዩ ሐዋርያዊ ጉዞዎችን አድርጓል።
ሀ. የመጀመሪያው ሐዋርያዊ ጉዞ
ከክርስቶስ ልደት በኋላ በ 45 ዓ.ም በርናባስንና ማርቆስን አስከትሎ ከአንፆኪያ ወደ ቆጰረሮስ ወረዳ ጳፋ፣ ስልማና በሚባሉ የቆጵሮስ ከተማዎች
ትምህርት ሲያስተምር ተአምራት ሲያደርግ ቆይቷል። “ጳውሎስ” የሚለውን ስምም በዚሁ እንረዳገኘ ይነገራል። ከዚህም ጳውሎስ እንጂ ሳውል ሲባል
አናገኝም። ከዚያም ወደ ታናሿ እስያ ሲደርስ ማርቆስ መከራውን ተሰቅቆ ስለተመለሰ በርናባስን አስከትሎ ዛሬ ቱርክ የተባለውን ሀገር ፍርግያ፣ ጵንፍልያ፣
ጵስድያ፣ አንፆኪያን፣ ልስጥራን፣ ደርቤን እያስተማረ ከሔደ በኋላ እንደገና በእነዚሁ ሀገሮች እያስተማረ ወደ አንፆኪያ ተመለሰ። (ሐዋ 13፣1-3 ፤14)
አንፆኪያ እንደደረሰ ከአይሁድና ከአረማውያን ወገን ክርስቲያን የሆኑት ተጣልተው ነበር። ምክንያቱም አይሁድ አረማውያንን በክርስቶስ ብታምኑና
ብትጠመቁ ነገር ግን ካልተገረዛችሁ ምን ይረባችኋል ? ምን ይጠቅማችኋል? እያሉ ያዳክሟቸው ነበርና ቅዱስ ጳውሎስ ሁከቱን ለማረጋጋት ድካማቸውንም
ለማበረታት ሲል ሐዋርያት ወዳለቡት ወደ ኢየሩሳሌም ወረደና ሁኔታውን አስረዳ። ሐዋርያትም ተሰብስበው የመጀመሪያውን ሲኖዶስ ከክርስቶስ ልደት በኋላ
በ 5 ኛው ዓመት አድርገው ነበርና በዚህ ጊዜ በመጨረሻ ውሳኔያቸው ከዝሙት፣ ከርኩሰት፣ ጣዖት ከማምለክ የተለያዩ ፀያፍ ነገሮች ከመሥራት ግርዘትም
በብሉይ ኪዳን ኃይል ቢኖረውም በሐዲስ ኪዳን ሕግ ቦታ እንደሌለው ወሰኑ። ቅዱስ ጳውሎስም ይህንን ውሳኔ ለአንፆኪያ ምዕመናን አደረሰ። ሐዋ 15
ለ. ሁለተኛው ሐዋርያዊ ጉዞ
ሐ. ሦስተኛው ሐዋርያዊ ጉዞ
በ 54 ዓ.ም በሦስተኛው ሐዋርያዊ ጉዞ ሉቃስን፣ ጢሞቴዎስን፣ ቲቶን አስከትሎ ከአንፆኪያ ተነሥቶ ገላትያን፣ ፍርግያን፣ ኤፌሶንን፣ መቄዶንያን፣
ፊልጵስዩስን፣ ቆሮንቶስ፣ ጢሮአዳን፣ አሶንን፣ ሚሊጢኒን፣ አንጠቀከስዩን፣ ትርጊልዩም፣ መስጡን፣ ቆስን፣ ጳጥርን፣ ጢሮስን፣ ጵቶልማስን፣ ቂሳርያን፣
ኢየሩሳሌምን ወዘተ የተለያዩ ሀገሮችን የሃይማኖት ልጆቹን በማበረታታት ተዘዋውሮ በቀደሙ ሐዋርያዊ ጉዞዎቹ ያቋቋማቸውን አብያተ ክርስቲያናት
እያስተማረ እልኮሪቆን የተባለው ሀገርም እንደጎበኘ ተገልጿል። ሮሜ 16፣3
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ከተለያዩ ሀገሮችና ክርስቲያኖች የሰበሰበውን ርዳታ ለኢየሩሳሌም ቤተክርስቲያን በመያዝ ሦስተኛውን ሐዋርያዊ ጉዞ
አጠናቆ ኢየሩሳሌም ሲገባ የፋሲካ በዓል ስለነበር ከልዩ ልዩ ሀገሮች የተሰበሰቡ በዝርወት የሚኖሩ አይሁድ ቅዱስ ጳውሎስን ቀድሞም በየሀገራቸው
በትምህርቱና በተአምራቱ ሲቃወሙት የነበሩ በኢየሩሳሌም ሲያዩት ታላቅ ተቃውሞ ሲያስነሱ ተቃውሞዋቸውን ለመግታት እንደ አይሁድ ሕግ በቤተመቅደስ
የመንጻት ሥርዓት መፈጸም ጀመረ። ነገር ግን ከኤፌሶን የተከተለውን ፕሮፈምስን ወደ መቅደስ ያስገባው ስለመሰላቸው ተቃውሞአቸው በረታ፤ ሐዋ 22፣29
ከተማውንም አወኩት። ይህ ነበር ቅዱስ ጳውሎስን በ 58 ዓ.ም ለሮም እስር የዳረገው ከብዙ መከራና ሥቃይ በኋላ ታስሮ ሮም ገባ። በዚያም በቁም እስር
ሆኖ ለሁለት ዓመታት ያህል ወንጌልን ሳይፈራና ሳያፍር መከራውን እየታገሰ ሰበከ። የሁለቱን ዓመት የቁም እስራት እንደጨረሰ ወደ ኔሮን ፍርድ ቤት ቀረበ።
በፍርድ ቤቱ በተደረገው ምርመራ የሮሜን ሕግ የሚቃወም ምንም ዓይነት ወንጀል ስላልተገኘበት በነጻ ተለቀቀ። ከዚህ በኋላ ነው ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ
የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ያልመዘገበውን ተጨማሪ ዐራተኛ መንፈሳዊ ሐዋርያዊ ጉዞውን ያደረገው። ይህ ጉዞው ኢየሩሳሌምን፣ ኤፌሶንን፣ ሎዶቅያን፣
መቄዶንያን፣ ቀርጤስን፣ ጢሮአዳን፣ ድልማጥያን፣ እልዋሬቆን፣ ኒቀጵልዮን፣ ብረንዲስን ጎብኝቷል። በዚህ የመጨረሻው የስብከት ጉዞ ለዐራት ዓመታት ያህል
ቆይቷል።
ከዚያም በ 64 ዓ.ም ኔሮን በጥጋቡ የሮም ከተማ ስትቃጠል ምን እንደምትመስል ማየት እፈልጋለሁ ብሎ አቃጠላት። የሮም ሕዝብ በከተማው
መቃጠል በማዘኑና በማመፁ ነገሩን ሁሉ በክርስቲያኖች ላይ አሳበበ። በዚህም የተነሣ ክርስቲያን የተባለ ሁሉ መሰደድ፣ መሰየፍ፣ መታረድ ዕጣ ፈንታው ሆነ።
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም በኒቆጵልዮን ከተማ ሲያስተምር በ 65 ዓ.ም ተይዞ ወደ ወህኒ ቤት ገባ። ለሁለት ዓመት ከስድስት ወር በጨለማ የግዞት ቤት
ታስሮ ከቆየ በኋላ በ 74 ዓመት ዕድሜው በሮም ከተማ በኦስትርያ መንገድ አንገቱን ተሰይፎ በ 67 ዓ.ም ሐምሌ 5 ቀን በሰማዕትነት አረፈ።
የቅዱስ ጳውሎስ መልእክታት ዘመናቸውንና ቅደም ተከተላቸውን ጠብቀው ባይጠረዙም የቅዱስ ጳውሎስ መልእክታት 14 ናቸው። የጥራዙ
ሁኔታም የሚለያየው እንደመልእክቱ ከባድነትና እንደየሀገሩ የቤተክርስቲያን ታላቅነት ነው። መልእክታቱንም በክፍል እንደሚከተለው እንከፍላቸዋለን።
የመጀመሪያው ክፍል ሁለቱ ወደ ተሰሎንቄ የተጻፉትን ይይዛል። እነዚህም በሁለተኛው ሐዋርያዊ ጉዞ በ 52 እና በ 53 ዓ.ም እንደተጻፉ
ይነገራል። እነዚህ መልእክታት ምስጢረ ምጽአትን በሚመለከት የሚናገሩ ናቸው።
ሁለተኛው ክፍል ሁለቱን የቆሮንቶስ መልእክታትና የገላትያን፣ የሮሜን መልእክታት ይይዛል። እነዚህ በ 3 ኛው የሐዋርያው ጉዞው በ 56 እና
በ 58 ዓ.ም መካከል የተጻፉ ናቸው። በዚህም ጊዜ አይሁድ ከመቼውም ጊዜ ይልቅ ቤተክርስቲያንን የተቃወሙበት፣ የጳውሎስንም ዝና ሆን ብለው
ያበላሹበት ጊዜ ነበር። እርሱ እነርሱን ይዘልፍበት ሕጋቸውን ይቃወምበት የነበረበት ጊዜ ነበር። በተለይም የገላትያ መልእክቱን ስንመለከት የክርስቶስን
ትምህርት አስፋፍቶ የአይሁድን ጥፋት ገልጦ የጻፈበት ነው።
ሦስተኛው ክፍል ቅዱስ ጳውሎስ በመጀመሪያው የሮም እስራት ጊዜ በ 62 እና በ 63 ዓ.ም የተጻፉ ናቸው። እነዚህም ወደ ፊልጵስዩስ፣ ወደ
ኤፌሶን፣ ወደ ቆላስይስና ወደ ፊልሞና የተጻፉ መልእክታት ናቸው። እነዚህ ስለ ክርስቶስ ማንነት አስፋፍተው የሚናገሩ ናቸው።
ዐራተኛው ክፍል በመጀመሪያ ከእስራት የተፈታበት ከ 63-68 ዓ.ም የተጻፉት 1 ኛ እና 2 ኛ ጢሞቴዎስና ቲቶን ይይዛል። እነዚህ መልእክታት
የካህናትን ተግባር የጠባቂዎችንም ሓላፊነት ስለሚገልጡ የጠባቂነት መልእክታት ይባላሉ። የቅዱስ ጳውሎስ መልእክታት የይዘት ተመሳሳይነት አላቸው።
ይኸውም የሚያመለክተው በአንድ መንፈስ ገላጭነት መጻፋቸው ነው። የመልእክታቱ ክፍል ጠባይ አጠቃላይ 6 ክፍል አለው።
1. ሰላምታ፡- በሰላምታ አገላለጡ ሰፊ ትምህርት ስለሚገኝበት የመሳብ፣ የማቅረብ፣ ወገንም የማድረግ ኃይል አለውና በሰላምታ መጀመርን ተግባር
አደረገው። የሰላምታ አሰጣጡም “ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን” የሚል ነው። ይኸውም የዕብራውያንን ሰላምታ በክርስቶስ የሚሰጠውን ጸጋ
እንደሚያገኙ የሚያነቃቃ ነው።
2. ምስጋና፡- ወደ ዋናው ርዕሱ ከመግባቱ በፊት ስለ ልዩ ልዩ መንፈሳዊ ስጦታው እግዚአብሔርን አመስግኖ ጽሑፉን ይቀጥላል።
3. መሠረተ ሃይማኖትን ማሳወቅ፡- እንደሚጽፍበት ምክንያት ይለያይ እንጂ የያዘውን ርዕስ አተኩሮ የርዕሱን ዓላማ አስፋፍቶ ይገልጣል። እንዲሁም
መልእክቱን ለመጻፍ የተነሣሣበትን ምክንያት በመከተል ሰፊ ትምህርተ ሃይማኖትን ይሰጣል።
4. ተግባራዊ ትምህርት፡- የክርስትና ምግባር እንዴት መሆን እንደሚገባው በግልጥ ይጽፋል። ሃይማኖትና ምግባርን በማዋሐድ ያስተምራል።
5. ለግል ሰዎች፡- ለጳውሎስ የፍቅሩ መገለጫ ለእያንዳንዱ ቤተክርስቲያን አባል የሚሰጠው አክብሮትና አገላለጥ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን እንዴት
የሁሉ እናት እንደሆነች የሚያስረዱ ምልክቶች ናቸው።
ሮም ስያሜዋን ያገኘችው ከመስራቿ ከንጉሥ ሮሙለስ (Romulus) እንደሆነ ይነገራል፡፡ ከተማዋም በ 753 ቅ.ል.ክ ተመሥርታለች፡፡ ከተማዋ
ከፍ ባለ ቦታ ላይ የተሠራች በመሆኗና በታላቅነቷ የተነሣ ለሮማውያን ግዛት (Roman Empire) ዋና ከተማ ሆናለች፤ እጅግ እያደገች በመምጣቷም
የተነሣ ለዓለም ገዥዎች መሰባሰቢያ እንዲሁም የሳይንስ፣ ሥዕልና የፍልስፍና መማሪያ ማዕከል ለመሆን በቅታለች፡፡ በዚህም ምክንያት ለተለያዩ ሀገራት
ሕዝቦች መሰባሰቢያ ሆናለች፡፡ ይህም ሐዋርያው በመጀመሪያ ምዕራፍ ላይ ለሚነግረን ክፉ ምግባርና ጣዖት አምልኮ ማዕከል እንድትሆን አድርጓታል፡፡
የሮም ከተማ አንድ ሦስተኛ ሕዝብ በክፉና አጸያፊ ምግባር የሚኖር ሕዝብ ነበር፡፡ (ሮሜ 1፡20-32) እንዲሁም በ 63 ቅ.ል.ክ ፖምፔይ የተባለው
የሮም ገዥ ሶርያን በወረረበት ወቅት የማረካቸው ብዙ አይሁዳውያን ነበሩ፡፡ እነዚህም በኋላ ነጻነታቸውን አግኝተው ቅዱስ ጳውሎስ መልእክቱን በሚጽፍበት
ወቅት እስከ 16 ሺህ ደርሰው ነው፡፡ እነዚህም አይሁዳውያን በ 14 ዓ.ም ጢባርዮስ ቄሳር እንዲሁም በ 34 ዓ.ም ቀላውዴዎስ ቄሳር ሮምን ለቀው
እንዲወጡ እስካዘዙበት ጊዜ ድረስ በሰላም በዚህ ከተማ ውስጥ ይኖሩ ነበር (ሐዋ 18፡2)፡፡
1. በሐዋርያት ሥራ ላይ እንደተገለጠው ለእምነታቸው ቀናኢ የሆኑ አይሁዳውያን ከተለያዩ ሀገራት በዓለ ጰንጠቆስጤን(በዓለ ሰዊት(ኀምሳ)) ለማክበር
ተሰባስበው ነበር፡፡ ከእነዚህም መካከል በሮም የነበሩ አይሁዳውያንም ሆነ ወደ አይሁድ እምነት የተቀየሩ አሕዛብ እንደነበሩ ተገልጧል (ሐዋ 2 )፡፡
እነዚህም በቅዱስ ጴጥሮስ ስብከት አምነው ተጠምቀው ወደ ሀገራቸው ወደ ሮም ተመልሰዋል፡፡ እነዚህም አይሁዳውያን በሮም ለነበሩት አይሁድ
የክረስትናን እምነት ሰብከውላቸዋል፡፡
2. የሮማውያን ግዛት (Roman Empire) ከሚታወቅበት ነገር አንዱ ከአንድ ግዛት ወደሌላው በተለይ ደግሞ ወደ ዋና ከተማው ለመጓጓዝ ቀላልና
ሙሉ ነጻነት ያለው በመሆኑ ነው፡፡ ይህም የሮምን ከተማ ለተለያዩ ነጋዴዎች፣ መምህራንና መሪዎች ምቹ አድርጓታል፡፡ ከእነዚህም መካከል ደግሞ
ከአጂያን ከተሞች፣ ከመቄዶንያ፣ ከግሪክ አንዳንድ ከተሞች እና ከታናሿ እስያ ከቅዱስ ጳውሎስ ሆነ ከሌሎች ሐዋርያት ክርስትናን የተቀበሉ ክርስቲያኖች
ይገኙባቸዋል፡፡ ስለዚህ በእነዚህ አማካኝነት ወደ ሮም ሊገባ ችሏል፡፡ የሮሜ መልእክት የመጨረሻው ምዕራፍም ይህን ያሳየናል፤ ምክንያቱም ቅዱስ
ጳውሎስ በሮም ለነበሩ ለብዙ ክርስቲያኖች ሰላምታ ያቀርባልና፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ገና ወደ ሮም ሳይሄድ እነዚህን ሁሉ ክርስቲያኖች ማወቁ ደግሞ
አስቀድመው ከርሱ በሌላ ሀገራት የተማሩ ደቀ መዛሙርቱ እንደሆኑ ያስረዳናል(ሮሜ 16)፡፡
3. ቀላውዴዎስ ቄሳር፣ አይሁዳውያን ሮምን ለቀው እንዲወጡ ባዘዘ ጊዜ እነዚህ አይሁዳውያን ወደ ሌሎች ከተሞች ተፈናቅለው ሄደው ነበር፡፡ ብዙም
አልቆዩም ተመልሰው ወደ ሮም መጥተዋል፡፡ ከእነዚህም መካከል አንዳንዶች ክርስትናን የተቀበሉ ነበሩ፡፡ በእነርሱ አማካኝነት ክርስትና ወደ ሮም ሊገባ
ችሏል፡፡ ለዚህም እንደምሳሌ የሚሆኑን አቂላና ጵርስቅላ ናቸው፤ ቅዱስ ጳውሎስን በቆሮንቶስ ያገኙት ሲሆን አስቀድመው በሮም ይኖሩ ነበር (ሐዋ
18)፡፡
የተጻፈበት ጊዜና ቦታ
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ይህን መልእክት የጻፈው ወደ ሮም ለመሄድ ባሰበ ጊዜ ነበር፡፡ ወደ እስፔን ሲሄድ ሮምን ሊያይ እንደወደደም በመልእክቱ
ጽፏል(ሮሜ 15፡23-24)፡፡ መልእክቱንም የታጻፈው ከመቄዶንያና ከአካይያ ክርስቲያኖች የሰበሰበውን ገንዘብ በኢየሩሳሌም ለነበሩት ድሆች ከመስጠቱ
በፊት ነው(ሮሜ 15፡25-26፣1 ኛ ቆሮ 16፡1-16፣2 ኛ ቆሮ 8፡1-4)፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ወደ ኢየሩሳሌም የሄደው ደግሞ በ 58 ዓ.ም መጀመሪያ ስለሆነ
መልእክቱን የጻፈው ከ 55-58 ዓ.ም መካከል(ከ 58 ዓ.ም በፊት) ነው፡፡ ስለዚህም መልእክቱ የተጻፈ በሦስተኛው ሐዋርያዊ ጉዞው በቆሮንቶስ ለሦስት
ወራት ያህል በተቀመጠ ጊዜ ነው ፡፡
የተጻፈበት ቦታ ደግሞ በቆሮንቶስ በጋይዮስ ቤት ሲሆን ጋይዮስንም ‹‹የእኔና የቤተ ክርስቲያን ሁሉ አስተናጋጅ›› (ሮሜ 16፡23) ይለዋል፡፡
መልእክቱን ከቅዱስ ጳውሎስ አፍ ተቀብሎ የጻፈው ጤርጥዮስ ሲሆን መልእክቱን ወደ ሮም የወሰደችው ደግሞ ዲያቆናዊቷ ፌቤን ናት፡፡ እርሷም ከቆሮንቶስ
በስተምዕራብ በሆነችው በክንክራኦስ ባለች ቤተክርስቲያን አገልጋይ ነበረች(ሮሜ 16፡1)፡፡ የተጻፈበትም ቋንቋ በአብዛኛው በሕዝቡ ዘንድ ይነገር በነበረው
በግሪክ ቋንቋ ነው፡፡
43
ክርስትናን በሮም የሰበከው ቅዱስ ጴጥሮስ እንደሆነና ለ 25 ዓመታት በጳጳስነት ቤተክርስቲያኒቱን እንደመራት ብዙ ጊዜ ቢነገርም ይህን ሀሳብ የምስራቅም ሆነ የምዕራብ
አብያተ ክርስቲያናት ሊቃውንት አይስማሙበትም፡፡ ለዚህም እንደምክንያት የሚያቅርቡት ቅዱስ ጴጥሮስ የሐዋርያት ሲኖዶስ (በ 50 ዓ.ም) እስከሚደረግበት ጊዜ ድረስ
በኢየሩሳሌም ነበር(ሐዋ 15)፡፡ በ 55 ዓ.ም ደግሞ በአንጾኪያ ነበር፣ በዚህም ጊዜ ከቅዱስ ጳውሎስ ጋር ተገናኝቷል (ገላ 2፡11)፡፡ በ 60 ዓ.ም ደግሞ በባቢሎን የመጀመሪያ
መልዕክቱን እየጻፈ ነበር፡፡ አንዳንዶች እንደሚሉት ቅዱስ ጴጥሮስ በ 41 ዓ.ም የሮምን ቤተ ክርስቲያንን የመሠረታት ቢሆን ኖሮ ቅዱስ ጳውሎስ ወደ ሮም መልእክትን ባላከ
ነበር፡፡ ቢልክ እንኳን ‹‹በሌላው ሰው መሠረት ላይ እንዳልሠራ የክርስቶስ ስም በተጠራበት ስፍራ ሳይሆን ወንጌልን ለመስበክ ተጣጣርሁ፤›› (ሮሜ 15፡20) ባላለን ነበር፤
ወይም ቅዱስ ጴጥሮስን በስም በጠቀሰው ነበር፤ ወይም ሰላምታን ባቀረበለት ነበር፡፡
ይህ ጥያቄ መልእክቱን እንድነረዳው ታላቅ እገዛ ያደርግልናል፡፡ ተቀባዮቹን ማወቅ ሐዋርያው የጻፈበትን ዓላማ ለማወቅ እጅግ ይጠቅማልና፡፡
በሮም ስለነበሩት ክርስቲያኖች ሦስት ዓይነት አመለካከት አለ፡፡ የመጀመሪያው አብዛኞቹ አይሁዳውያን ናቸው የሚል ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ አብዛኞቹ
አሕዛብ ናቸው ሲል ሦስተኛው አመለካከት ደግሞ የእነርሱ ድብልቅ ነው የሚል ነው፡፡ ብዙ ሊቃውንት የሚስማሙበት አሳብ ግን የመጀመሪያውን ሲሆን፤
ይህም ከአይሁድ ወደ ክርስትና የተቀየሩት በቁጥር ከአሕዛብ ወደ ክርስትና ከተቀየሩት እንደሚበዙ ነው፡፡ ይህም የቅዱስ ጳውሎስ አጻጻፍ ያረዳናል፡፡ ቅዱስ
ጳውሎስ በዚህ መልእክቱ ከብሉይ ኪዳን ብዙ የጠቀሰ ሲሆን የአብርሃምንም ታሪክ ይተርካል፡፡ አብርሃምንም አባታችን በማለት ይጠራዋል፤ ይህም አብዛኞቹ
አይሁዳውያን ያስረዳናል፡፡ ይህ ማለት ግን ለአይሁዳውያን ብቻ ነው የተጻፈው ማለት አይደለም፤ ቅዱስ ጳውሎስ ራሱ ‹‹ለእናንተ ለአሕዛብም
እናገራለሁ››(ሮሜ 11፡13) በማለት ለአሕዛብም እንደላከው ያሳየናል፡፡
ይህ በጥንት ክርስቲያኖች ዘንድ ትልቅ ጠቀሜታ ነበረው፡፡ ለምሳሌ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ይህንን መልእክት በሳምንት ሁለት ጊዜ ያነበው ነበር፡፡
ይህን መልእክት ማጥናትም አሁን ላለነው ክርስቲያኖች ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው፡፡ በመጀመሪያም ቅዱስ ጳውሎስ ይህን መልእክት የጻፈበትን ዓላማ
እንመልከት፡፡
በቁጥር እጅግ ብዙ የሆኑ በሮም የሚኖሩ አይሁዳውያን በክርስቶስ አመኑ፡፡ እነዚህም በትውልድ አይሁዳውያን የሆኑ ወይም መጀመሪያ አሕዛብ
የነበሩ በኋላ ይሁዲነትን የተቀበሉ ናቸው፡፡ እነዚህ ክርስትናን እንደ ተቀበሉ ሁሉ የተማሩ አሕዛብ፣ የግሪክ ፈላስፎችም በክርስቶስ አመኑ፡፡
ስለዚህም ሁሉም አንድ መንፈስና አንድ አካል ሆነው ማገልገል መቻል ነበረባቸው፡፡ ነገር ግን አይሁዳውያኑ ክርስቲያኖች፣ ከአሕዛብ ወደ
ክርስትና ከመጡት እንበልጣለን ማለት ጀመሩ፡፡ አይሁዳዊ ዘር ባሕልና አስተምህሮ ከሁሉም ይበልጣል እያሉ ከአሕዛብ ወደ ክርስትና
የመጡት ይንቋቸው ጀመር፡፡ እንበልጣለን ያሉት ስለነዚህ ሦስት ምክንያቶች ነበር፡፡
1. እኛ የአብርሃም ልጆች ነን ስለዚህ እግዚአብሔር የገባለት ቃልኪዳን ለእርሱና ለልጆቹ ብቻ ነውና በማለት
2. ከሁሉም ሕዝብ ተለይተው ሕግ በሙሴ አማካኝነት የተሰጠን እኛ ነን በማለት
3. እግዚአብሔር የመረጠን ሕዝብ እኛ ነን በማለት ነበር፡፡
ከቀደመ አይሁዳዊ ማንነታቸው የወሰዱት ይህ አስተሳሰብ ወደ ከፋ ትዕቢትም መራቸው፡፡ ይህም ትዕቢትም የአብርሃም ልጅ መባል ምን ማለት
መሆኑን፣ ሕግ የመሰጠቱን ዓቢይ ዓላማ እና ለምን እግዚአብሔር ሕዝቡን አንደመረጠ እንዳይረዱ እንቅፋት ሆነባቸው፡፡ ምንም እንኳን በክርስቶስ አዳኝነት
ቢያምኑም እንኳ ራሳቸውን ከሌላው አማኝ በላይ አድርገው ያስቡ ነበር፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም በመልዕክቱ ላይ ስለነዚህ በሰፊው እያነሳ ያስተማረው ስለዚህ
ነው፡፡
በተቃራኒው ደግሞ ይህን የአይሁዳውያንን አስተሳሰብ በመቃወም አሕዛብ የራሳቸውን ተቃራኒ ጽንፍ ያዙ፡፡ አይሁዳያውን የተዋረዱ እንደሆኑና
እግዚአብሔርም የመዳንን ደጅ በእነርሱ ላይ ዘግቶ ለአሕዛብ እንደከፈተላቸው አድርገው ያስቡ ጀመር፡፡ ይህም ልክ ከትዕቢተኞቹ አይሁዳውያን እኩል
ጥፋተኞች አደረጋቸው፡፡
በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሳሉ ነው ቅዱስ ጳውሎስ ለሁለቱም ወገኖች ይህን መልእክት የጻፈው፡፡ በመልእክቱ ውስጥም የእምነትን ተግባራዊነትና በዕለት
ተዕለት ኑሯችን ሊኖረን የሚገባውን መንፈሳዊ ጠባይን ያነሣል፡፡ ስለመዳንም በሰፊው ያነሣል፡፡ መዳንም የሚሆነው በፍቅር በሚሠራ ምግባር የተገለጠ፣
ሕይወት ባለው እምነት ለሁሉም ሕዝብ ነው ይለናል፡፡ (He proclaims that the door has been opened to all nations through
a living faith that is evident in deeds of love.)
በመንፈስ ቅዱስም መሪነት በእምነትና በመዳን መካከል ያለውን ጥብቅ ግንኙነት በሰፊው
ያትታል፡፡ ለክርስቶስና እርሱ ለተሰቀለላት ለዓለም ሁሉ ያለውን ፍቅርም ይገልጥልናል፡፡ በተመሳሳይ በአይሁዳውያኑና በአሕዛቡ ዘንድ ስላለው ትዕቢትም
ያነሣል፡፡ ስለ ቅድስና፣ በክርስቲያኖች ዘንድ ስላለው ግንኙነትና ከማኅበረሰቡ ጋር ሊኖራቸው ስለሚገባው ግንኙነት ይናገራል፡፡
የሮሜ መልእክት 16 ምዕራፎች አሉት፤ 16 ቱንም ምዕራፎች በስምንት ዐበይት ክፍሎች ከፍለን
እናጠናለን፡፡
ሮሜ 16፡ የቅዱስ ጳውሎስ ሰላምታ የአደራ ምሥጋናና ጸሎት፣ የጳውሎስ ያለፈው አገልግሎቱና
የአሁኑ ዕቅድ
ቆሮንቶስ የአካይያ ግዛት ዋና ከተማ ስትሆን የምትገኘውም ግሪክ ውስጥ ነው፤ የመጀመሪያይቱ
የቆሮንቶስ መልእክት የተጻፈችው በኤፌሶን ነው፡፡ ዘመኑም በ 3 ኛው ሐዋርያዊ ጉዞ ሳለ በኤፌሶን ለሁለት
ዓመት በቆየበት ጊዜ ነው፡፡ ይህም በ 55 ዓ.ም ገደማ እንደሆነ ይነገራል፡፡ ይህቺ መልእክት ከኤፌሶን
እንደተለከች የሚያስረዳ ቃል በውስጧ ይገኛል፡፡ ይህም ቅዱስ ጳውሎስ እስከ በዓለ ሃምሳ ድረስ በኤፌሶን
እሰናበታለሁ ብሎ የጻፈው ቃል ነው፡፡ /1 ኛ ቆሮ 16፡8/ ይህም ቃል ቅዱስ ጳውሎስ መልእክታቱን በጻፈ ጊዜ
በኤፌሶን እንደነበር ያስረዳል፡፡
ይህች ከተማ ስመጥርና ታላቅ በንግድም የታወቀች የሀብታሞች መናኸሪያ ነበረች፤ በምስራቁና
በምዕራቡ ዓለም ለንግድ ቅርብ ስለሆነች የበለፀገች ሀገር ነበረች፡፡ ከስድስት መቶ እስከ ሰባት መቶ ሺህ
ከሚሆነው ሕዝቧ ውስጥ አይሁዶች፣ ሮሜዎች፣ ግሪኮች ይገኙበታል፤ በቆሮንቶስ ብዙ ዓይነት ኃጢአት
በተለይም ዝሙት ይሠራ ነበር፤ እንዲህ በሆነበት ዘመን ቅዱስ ጳውሎስ ከአቴና ወደ ቆርንቶስ መጣ /ሐዋ 18፡
1/ እርሱም ይህን ያህል ኃጢአት በመሥራታቸው ብዙ ሰዎች ተጸጽተው ሰማዕያነ ወንጌል በዝተው ሲመለከት
በዚሁ ብዙ ጊዜ ቆየ፤ ለአንድ ወር ያህል ቆይቶ ሐዋርያዊ ጉዞውን ለመቀጠል ተነሣ፡፡ /ሐዋ 18፡9/ ቅዱስ
ጳውሎስ ቆርንቶስን ለቆ ኢየሩሳሌም ገብቶ ሁለት ዓመት ያህል ቆይቶ እንደገና 3 ኛ ሐዋርያዊ ጉዞውን
ቀጥሎ እያስማተረ ኤፌሶን ደረሰ፤ ከዚያም በጠዋት በማታ በሚያደርገው ስብከት ስብከት የእስክንድርያው
ሰው አጵሎስ የተባለው አይሁዳዊ አምኖ ተጠመቀ፡፡
በኋላ የቅዱስ ጳውሎስ ረዳት ሆኖ ቆርንቶስን ለመጎብኘት ሄደ፤ ከዚያም እንደደረሰ የተማረውን ሁሉ
ያስተምር፣ ይመሰክር ጀመረ፡፡ መሠረታዊና ጠለቅ ያለ ትምህርት ያስተምር ስለነበር ብዙ ሰዎች አምነው
ተጠመቁ፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ በሁለተኛ ጉዞው በ 54 ዓ.ም ደግሞ በኤፌሶን እያለ ልጁ ጢሞቴዎስ
ቤተክርስቲያኗ ውስጥ በምዕመናን መካከል መለያየትና መከፋፈል እንዳለ ይነግረው ነበር፡፡
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ አስተምሮ ከሄደ በኋላ ከእስክንድርያ የመጣው አይሁዳዊ አጵሎስ ተጠምቆ
ለአይሁድ ብሉይን ከሐዲስ እያስማማ ጥልቅና ጠንካራ ምስጢራዊ ትምህርቱን ሲያስተምር ብዙ ሰዎች
ወደ ቤተ ክርስቲያን መምጣት ጀምረው ነበር፡፡ እነዚህ በልዩ ልዩ ምክንያት ያመኑ ክርስቲያኖች የሐሳብ
መለያየትና የወገንተኝነት ስሜት ስለጠናባቸው ከዚያም “እኔ የጳውሎስ ነኝ፣ እኔ የአጵሎስ ነኝ” እያሉ
ሲከፋፈሉና ሲለያዩ ክርስቶስ ተከፋፍሏልን፣ ጳውሎስ ስለ እናንተ ተሰቀለን ወይስ በጳውሎስ ስም
ተጠምቃችኋል በመካከላችሁ መለያየት እንዳለ እሰማለው፡፡ መለያየት ለአንዲት ቤተክርስቲያን የማይበጅ
ነው በማለት ቅዱስ ጳውሎስ ይህንን ችግር ከቀለዮጳ ቤተ ሰዎች ሲሰማ ይህችን የመጀመሪያ መልእክቱን
ጻፈላቸው፡፡ /1 ኛ ቆሮ 1፡12/
ከአምልኮ ጣዖት ከተመለሱ በኋላ የቆርንቶስ ሰዎች የቀድሞ የአምልኮ ጣዖት ባህላቸውን ወደ
ቤተክርስቲያን እምነት ሥርዓትና ትውፊት በመቀላቀል ይኖሩ ነበር፤ ለምሳሌ ወደ ቅዳሴ ሲመጡ ሁሉም
ለየግሉ ወይንና ኅብስት ይዘው ይመጡና እስኪጠግቡ በልተው እስኪሰክሩ ጠጥተው እየተጨቃጨቁና
የ/ደ/ይ/ቅ/ጊ/ቤ/ክ/ፍ/ሃ/ሰ/ት/ቤት ትምህርት ክፍል የተዘጋጀ 107
እየተደባደቡ ቊርባን እንደፈጸሙ ይሰማቸው ነበር፤ ይባስም ብለው ወይንና ኅብስት ማምጣት ያልቻሉ
ድሆችን እንደ እነርሱ ሐሳብ እንዳይቆርቡ ይከለክሏቸው ነበር፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ከጌታና ከቅዱሳን
ሐዋርያት ያገኘውን ሃይማኖት ሥርዓትና ትውፊት አብራርቶ ይመክራቸው ዘንድ ይህችን መልእክት
ጻፈላቸው፡፡
የቆሮንቶስ ሰዎች በዝሙት ኃጢአት የታወቁ ነበሩ፤ በዚያ “ቆርንቶሳዊ” ማለት ዘማዊ የሚለውን
ትርጉም ይዞ ነበር፤ ቅዱስ ጳውሎስም በእናንተ መካከል ዝሙት እንዳለ ይወራል፣ የዚህን ዓይነት ዝሙት
በአሕዛብ እንኳ የማይገኝ ነው እያለ የተማረውን የወንጌሉን ቃል መሠረት በማድረግ ይህን መልእክት
ከዝሙት ጠንቅ እንዲጠበቁ ጻፈላቸው፡፡ /1 ኛ ቆሮ 5፡1/
የቆርንቶስ ሰዎች ችግር በመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች እርስ በእርስ መቀናናታቸው ነበር “እኔስ ከማን
አንሳለው” እያሉ ሁሉም ትንቢት ተናጋሪ፣ ሁሉም ተርጓሚዎች፣ ሁሉም በልሳን ተናጋሪዎች ስለሆኑ
ሁሉም ራሳቸውን ከፍ በማድረጋቸው ጭቅጭቅ ነበር፡፡ ለእነዚሁ ሁሉ ችግሮች ክርስቲያናዊ መልሶችን
ጽፎ አዘጋጅቶ በጢሞቴዎስ፣ በእስጢፋኖስ፣ በፈርዶናጥስና በአካያቆስ እጅ ይህችን መልእክት በ 54 ዓ.ም
ገደማ ላከላቸው ፡፡ /1 ኛ ቆሮ 15፡2-58፣ 16፡1-24/
በመጨረሻ ቅዱስ ጳውሎስ ጥያቄ አዘል ደብዳቤዎችን ጽፈውለት ነበርና የተለያዩ ችግሮቻቸውን
በመጠየቅና መልስ በማዘጋጀት ለሃይማኖት ይጸኑ፣ በምግባር ያድጉ ዘንድ ይህን መልእክት ጻፈላቸው፡፡ /1 ኛ
ቆሮ 7፡1፣ 8፡1፣12፡1፣16፡1/
የመልእክቱ ይዘት
የአንደኛው የቆሮንቶስ መልእክት ይዘት የተግሳፅ ትምህርት ነው፡፡ /1 ኛ የቆሮ 4፡14/ ቅዱስ ጳውሎስ
በዚህች መልእክት ውስጥ ለጊዜው በቆሮንቶስ ክርስቲያኖች መካከል ተፈጥረው የነበሩ ስህተቶች እንዲወገዱ
የሚያደርጉ ትምህርቶችን ጽፏል፤ ትምህርቱንም ሥነ ምግባርን፣ ሥርዓትንና ሃይማኖትን የሚመለከቱ
ናቸው፡፡
የመልእክቱ አከፋፈል
1 ኛ የቆሮንቶስ መልእክት 15 ምዕራፎች አሉት እነዚህም በሰባት ዐበይት ክፍሎች ከፍለን እናጠናለን፡፡
1 ኛ የቆሮ 7፡ ስለ መጋባት
1 ኛ የቆሮ 8-10፡ ለጣዖት ስለተሠዋ ሥጋ፣ ጳውሎስ ስለ ወንጌል ራሱን ምን ያህል እንዳስገዛ
1 ኛ የቆሮ 11፡ ስለ ቅዱስ ቊርባን፣ በጸሎትና ትንቢት ለመናገር ወንድ ራሱን እንዳይከናነብ ሴት ግን
ራስዋን እንድትሸፍን፣ ከሁሉም የጸጋ ስጦታዎች ፍቅር እንደሚበልጥ
የመጀመሪያውን መልእክት ምን ያህል ተግባራዊ እንዳደረጉት ለመረዳት ቲቶን ላከ፡፡ ከቅዱስ ጳውሎስ
ጋርም በመቄዶንያ ተገኝተው ሲጠይቀው፤ የላከላቸውን መልእክት ብዙዎችን በክፉ ሥራቸው እንዲጸጸቱ
ንስሐም እንዲገቡ እንዲያውም የአባቱን ሚስት ያገባ እንዲለይ አድርገዋል በማለት ደስ የሚያሰኘውን ወሬ
ነገረው /2 ኛ ቆሮ 7፡5-16/፤ የቲቶን ወሬ ሲሰማ ቅዱስ ጳውሎስ እዚያው በመቄዶንያ እያለ ይህችን
“ሁለተኛይቱ” የተባለችውን መልእክት ጻፈላቸው፡፡
ቀድሞ በጻፈላቸው መልእክት፣ ተግሣጽና ምክር ተደናግጠው ሀዘናቸውም ከልክ ያለፈ ነበር፡፡ ከልክ ያለፈ
ሀዘናቸውን ለማስታገስ የመልእክቱን፣ የተግሳጹንና የምክሩን ጠቃሚነት አብራርቶ ጻፈላቸው፡፡
የመልእክቱ አከፋፈል
4. ወደ ገላትያ ሰዎች
ይህች ገላትያ የተባለች ሀገር በታናሿ እስያ አጋርያስና አሊያስ በተባሉ ሁለት ወንዞች መካካል
የምትገኝ አውራጃ ስትሆን ዛሬ የቱርክ መናገሻ ናት፡፡ አውራጃው ውስጥ ጵስድያ፣ አንጾኪያ፣ ኢቆንዮስ፣
ልስጥራንና ደርቤን የተባሉ ከተማዎች ይገኛሉ፡፡ አውራጃዋ በምስራቅ ከጳንጦስና ከቀጰዶቅያ፣ በምዕራብ
ከፍርግያ፣ በሰሜን ከቢታንያ፣ በደቡብ ደግሞ ከሊቃኦንያ ትዋሰናለች፡፡
ወደ ገላትያ አብያተ ክርስቲያናት የገባው በሥጋ ድካም ነበር፤ ይህንን የሥጋ ድካም ዘመናውያን
የሆኑት ሊቃውንት ጳውሎስ በአንደኛው ሐዋርያው ጉዞ ወቅት ወደ ገላትያ ከመግባቱ በፊት በቆላማዋ
ሥፍራ በጰርጌን ዘጵንፍልያ ደርሶበት የነበረው የወባ ሕመም እንደነበር ይነገራሉ፡፡ “በሥጋ ድካም እንኳን
ሆኖ አልተጸየፉትም፣ አልናቁትም” ነገር ግን እንደ እግዚአብሔር መልአክ፣ እንደ ክርስቶስ ኢየሱስ
ተቀበሉት፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ለመጀመሪያ ጊዜ በሰበከላቸው ወቅት አክብረው በደስታ ተቀብለውት ነበር፡፡
ይህች የገላትያ ሰዎች መልእክት የተጻፈላቸው በ 48 ዓ.ም ሲሆን የተላከቸውም በቲቶ እጅ ነው፡፡
የመልእክቱ ዓላማ
የአይሁድ መምህራን ቅዱስ ጳውሎስ እንደ ሌሎች ሐዋርያት ጌታን አላየም በማለት ከቅዱሳን ሐዋርያት
እኩል አይቆጠርም ይሉት ስለነበር ይህንን የእነርሱን ሐዋርያነትና ሥልጣኑን ያውቁ ዘንድ
ቅዱስ ጳውሎስ ከሐዋርያት እንጂ ከጌታ ስላልተማረ ክብሩ ያነሰ ነው እያሉ የአይሁድ ካህናት የገላትያን
ሰዎች ያወናብዱ፣ ያስጨንቁ ስለነበር ይህን ለማስረዳት
ሐዋርያት ከአይሁድ ተፋቅረው ሕገ ኦሪትን ጠብቀው ሥርዓተ አይሁድን አክብረው በኢየሩሳሌም እየኖሩ
እርሱ ግን እናንተን አላዋቂ አድርጎ የሐሰት ትምህርት ያስተምራችኋል በማለት የሚናገሩትን ለማስተማር
ጽፎላቸዋል፡፡
የመልእክቱ አከፋፈል
የ/ደ/ይ/ቅ/ጊ/ቤ/ክ/ፍ/ሃ/ሰ/ት/ቤት ትምህርት ክፍል የተዘጋጀ 110
የገላትያ መልእክት ስድስት ምዕራፎች አሉት፡፡ በአምስትም ከፍለን እናጠናዋለን
ገላ 1፡6 – 2፡21፡- ቅዱስ ጳውሎስ ሐዋርያነቱን እያስረዳ ሐሰተኞችን እየተቃወመ ስለ ጽድቅ የጻፈላቸው
ትምህርት
5. ወደ ኤፌሶን ሰዎች
ኤፌሶን በታናሽ እስያ ውስጥ በምዕራብ በኩል በኤጅያን ባሕር አጠገብ የምትገኘው የእስያ አውራጃ ዋና
ከተማ ነበረች፡፡ ብዙ ነጋዴዎችም ይገኙባት ነበር፡፡ የታወቀው የአርጤምስ (በላቲኑ አጠራር) “ዲያና” ቤተ
ጣዖት እንዲሁም በስደትና በምርኮ የተሰበሰቡ አይሁዳውያን ምኩራብ ሠርተው ይኖሩባት ነበር፡፡ የፋርስ ግዛት
ሆና ስትኖር ታላቁ እስክንድር ፋርሱን ንጉሥ ዳርዮስን ድል አድርጎ ከተማዋን የግሪክ ግዛት አድርጓታል፡፡
የኤፌሶን መልእክት ቅዱስ ጳውሎስ በ 1 ኛው እስራቱ ወቅት በሮም እስር ቤት ሆኖ ከጻፋቸው የጳውሎስ
መልእክታት አንዷ ናት፡፡ /ኤፌ 3፡1፣ 4፡1-20/ የተላከችውም ከቆላስያስና ከፊልሞና መልእክታት ጋር
በተመሳሳይ ጊዜ ነው፡፡ የቅዱስ ጳውሎስ የመጀመሪያ የሮም እስራቱ ከ 62-64 ዓ.ም ስለሆነ በ 62 ዓ.ም ገደማ
እንደተጻፈች ይነገራል፡፡ መልእክቷን ይዟት የሄደው ቲኪቆስ የተባለው የጳውሎስ ደቀመዝሙር ነው፡፡ ኤፌ 6፡
21
የኤፌሶን ክርስቲያኖች አሕዛብ ወገን ቢሆኑም ከእስራኤል ጋር አንድ ሆነው በክርስቶስ ጸጋ መዳናቸውንና
ሰማያዊ ክብር ማግኘታቸውን አውቀው በእምነታቸው እንዲጠነክሩ ለማድረግ፡፡
የኤፌሶን መልእክት ከወቀሳና ከተግሣጽ ነጻ የሆነ ትምህርትን ይዛለች፤ ትምህርቱም የሃይማኖት፣ የሥነ
ምግባር ትምህርት ነው፡፡
6. ወደ ፊልጵስዮስ ሰዎች
ፊልጵስዩስ በቀድሞ ዘመን ኣሌኒደስ ትባላለች፤ ፊልጵስዩስ የሮሜ ቅኝ ግዛት የሆነች በመቄዶንያ
አውራጃ ውስጥ የምትገኝ የአንድ ወረዳ ዋና ከተማ ነበረች፡፡ ቀደም ሲል ቅዱስ ጳውሎስ በዚህች ከተማ
ልድያ የተባለችውን ሴትና የእስር ቤቱን ኃላፊ ከእነ ቤተሰቦቻቸው አስተምሮ ወደ ክርስትና መልሷቸዋል፡፡
(የሐዋ ሥራ 16፡9-40)
ቅዱስ ጳውሎስ በሮም እስር ቤት በመሰቃየት ላይ መሆኑን የተረዱ የፊልጵስዩስ ምዕመናን አፍሮዲጡ
በተባለው ወኪላቸው ያዋጡትን አስተዋጽኦ አስይዘው ላኩለት፡፡ እርሱም መከራው የማይዘነጉት፣
በሃይማኖታቸው ጽኑ መሆናቸውን አይቶ የሚያበረታታ ምስጋና፣ ምክርና ትምህርት ላከላቸው፡፡ /ፊል 4፡
14-20/
ራሳቸውን ከፍ ከፍ ያደርጉ ይመኩም ስለነበር የክርስቶስ አርአያነት ይኑራችሁ እያለ በመምከር
ጽፎላቸዋል፡፡
መታሰሩን የሰሙ ቢጽ ሐሳውያን እኛም መምህራን ነን እያሉ በፊልጵስዩስ ክርስቲያኖች ላይ ችግር
ፈጥረውባው ነበርና መልስ ለመስጠት
በተጨማሪም በከተማዋ የነበሩት አይሁድ እኛ የአብርሃም ዘር ነን እያሉ በአሕዛብ ላይ ይመኩባቸው
ስለነበር ከንቱ የሆነ ትምክህታቸውን እኔም እኮ የብንያም ዘር ነኝ በማለት ለሁሉም መልስ በመስጠት
ጽፎላቸዋል፡፡
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ የፊልጵስዩስን መልእክት የጻፋት በሮም በእስር ቤት ውስጥ ሆኖ እንደ ነበር
ከመልእክቲቱ እንረዳለን፡፡ (ፊል 1፡7፣ 13፡14) ጊዜውም ከእስራቱ ሊፈታ አካባቢ እንደሆነ ይታመናል፡፡ (ፊል 2፡
19፣ 23፡24)
ፊል 1፡1-11፡- ሰላምታ
ፊል 1፡12-26፡- በሮም እስራቱ ጊዜ ስለ ወንጌል መስፋፋትና አንድነታቸው
ፊል 1፡27-2፡18፡- ስለ ፊልጵስዩስ ምዕመናንና ክርስቲያኖች ኑሮ
ፊል 2፡19-30፡- ስለ ጢሞቲዎስና አፍሮዲጡ መላክ
ፊል 3፡1-21፡- ስለ ሐሰተኞች መምህራን
7. ወደ ቆላስይስ ሰዎች
ቆላስይስ ከኤፌሶን 100 ማይል ወደ ምስራቅ ርቃ በፍርግያ ውስጥ የምትገኝ ከፍርግያ ዋና ከተማ ከሎዶቅያ ደግሞ 13 ማይል የምትርቅ ከተማ ናት፡፡ ዛሬ
ቱርክ በሚባለው ሀገር ትገኛለች፡፡ ከምዕራቡ ዓለም ወደ ምስራቁ በሚወስደው መንገድ ዳር ስለምትገኝ ዋና የንግድ ማዕከል ናት፡፡ በእንጨትና በበግ ጠጉር
ምርቷ ትታወቃለች፡፡
የቆላስይስ ከተማ ምዕመናን ወንጌልን የተማሩት ኤጳፍራ ከተባለው ታማኝ የክርስቶስ አገልጋይ ነው፡፡ (ቆላ 1፣7) ኤጳፋራ የቆላስይስ ተወላጅ ሲሆን ቅዱስ
ጳውሎስ በ 3 ኛው ጉዞ ወቅት በኤፌሶን እያስተማረ ሁለት ዓመት በቆየ ጊዜ ያመነ ሰው ነበር፡፡ ኤጳፋራ ክርስቶስን ካመነ በኋላ ከጳውሎስ ጋር የክርስቶስ
አገልጋይ ሆኗል፡፡ በሀገሩ ቆላስይስ ወንጌልን ሰብኮ ቤተክርስቲያኒቱን መሥርቷል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ በሮም መጀመሪያው እስራት ጊዜ ከቆላስይስ መጥቶ ስለ
ቤተክርስቲያኒቱ ነግሮት ነበር፡፡ በዚያም ከጳውሎስ ጋር አብሮ ታስሮ እንደነበረ ተገልጦአል (ፊልሞ 1፣23)፡፡ ስለ አመኑት ምዕመናን ኤጳፋራ ሁልጊዜ
አብዝቶ ይጸልይ ነበር፡፡ (ቆላ 4፣12) በዚህም ወቅት የቆላስይስ ቤተክርስቲያን መሪ የነበረው የባለጸጋው የእግዚአብሔር ወዳጅ የፊልሞና ልጅ አክሪጳ ነው
(ቆላ 4፣17 ፊልሞ 1፣2)፡፡ በቆላስይስ ከኤጳፋራ በተጨማሪ ፊልሞናና ልጁ አክሪጳ ወንጌልን አስተምረውባታል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም ስለ እነርሱ ታላቅ
ተጋድሎ ነበረው፡፡ (ቆላ 2፣1)
1. ኤጳፋራ ቅዱስ ጳውሎስን ሊጠይቀው በመጣ ጊዜ በመንፈስ ስለሚሆን ፍቅራቸው ስለነገረው ሊያመሰግናቸውና ሊያበረታታቸው ስለወደደ ቆላ 1፣3-
7
2. የፊልሞና አገልጋይ አናሲሞስ የቆላስይስን የኑሮ ሁኔታ ስለነገረው ስለ ክርስቲያናዊ የኑሮ ሁኔታ አብራርቶ አስረድቷል፡፡
3. በተጨማሪም በፍልስፍና የተመሠረቱ የተለያዩ የሐሰት ትምህርቶች መግባታቸውን ነግሮት ስለነበር ከእነዚህ ይጠበቁ ዘንድ ነው፡፡
ሀ. ግኖስቲኮች፡- ግኖሲስ (እውቀት) ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም አዋቂዎች ማለት ነው፡፡ እምነታቸውም ግኖስቲዝም (Gnostism)
ይባላል፡፡ እነዚህም ሰው የሚድነው ካለው እውቀት ብዛት ነው እንጂ በምግባር አይደለም የሚሉ ናቸው፡፡
ቅዱስ ጳውሎስም ለእነዚህ መልስ ሲሠጥ እውቀት ለሰው ልጅ እጅግ ጠቃሚና አስፈላጊ መሆኑን ካስረዳ በኋላ ነገር ግን ከምግባር ፈጽሞ መለየት
እንደሌለበት ይናገራል፡፡ ምክንያቱም እውቀቱ ተግባራዊ መሆን አለበትና፤ ያለዚያ ግን ረብ ወይም ጥቅም የለውም፡፡ ሐዋርያውም በመልእክቱ “እውቀት”
የሚለው መንፈሳዊውን እውቀት ወይም ስለእግዚአብሔር ምስጢራት ማወቅን ነው፡፡ በዚህ መልእክት ላይም እንዲህ ብሏል “… የፈቃዱ እውቀት መንፈሳዊ
ጥበብና አእምሮ ሁሉ እንዲሞላባችሁ እየለመንን፣ ስለ እናንተ ጸሎትን አልተውንም፡፡ በበጎ ሥራ ሁሉ ፍሬ እያፈራችሁ በእግዚአብሔር እውቀት እያደጋችሁ
…” ቆላ 1፣8-10 በማለት እውቀት ብቻ ሳይሆን በበጎ ሥራ ፍሬ እንዲያፈሩ አስተምሯል፡፡
በተጨማሪ እነዚህ መናፍቃን ‹‹ሥጋ ኃጢኣተኛ ስለሆነ እግዚአብሔርን ማወቅና ማምለክ አይቻልም፣ እግዚአብሔርም ሰውን የራሱ ማድረግ አይቻልም፡፡
ሰውና እግዚአብሔርም በጣም የተራራቁ ናቸው ይላሉ፡፡ ስለዚህ ሰዎች አምልኮ ማቅረብ የሚችሉት ከእነርሱ በላይ ከእግዚአብሔር በታች ለሆኑት ለመላእክት
ከዚህ በተጨማሪ እነዚህ መናፍቃን ነፍሳችንን ወደ እግዚአብሔር ለማቅረብ ከፈለግን በሥጋችን ላይ ጨካኝ መሆን አለብን በማለት “ አትያዝ፣ አትንካ፣
አትቅመስ” የሚሉ ትምህርቶችን ያስተምሩ ነበር፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም እንዲህ ብሏል “እንደሰው ሥርዓትና ትምህርት አትያዝ፣ አትቅመስ፣ አትንካ ለሚሉት
ትእዛዛት በዓለም እንደምትኖሩ ስለምን ትገዛላችሁ? እነዚህ ሁሉ በማድረግ ሊጠፉ ተወስነዋልና፡፡…” በማለት ለእርሱ ትእዛዝ እንዳይገዙ አስጠንቅቋል፡፡ ቆላ
2፣22-23
ለ. የአይሁድ እምነትና ሥርዓት፡- አይሁዳውያን ለሁለት መቶ ዓመታት ያህል በፍርግያ ውስጥ ተቀምጦአል፡፡ ስለዚህም ግዝረትንና የኦሪትን በዓላት
ክርስቲያኖችን ያስገድዱ ነበር፡፡ አንድ ሰውም ክርስቲያን ለመሆን መጀመሪያ አይሁዳዊ መሆን አለበት በማለት ያስተምሩ ነበር፡፡ ስለዚህም ወንጌል ያለ ኦሪት
፣ ክርስቶስ ያለ ሙሴ፣ ጥምቀት ያለ ግዝረት ጥቅም የለውም ይሉ ነበር፡፡ እነዚህ መናቅቃን ጁዲያይዘር ሲባሉ በሮምና በገላትያም በብዛት ነበሩ፡፡
ሐዋርያውም ስለዚህ ሲናገር “እንግዲህ በመብል ወይም በመጠጥ ወይም ስለ በዓል ወይም ስለ ወር መባቻ ወይም ስለ ሰንበት ማንም አይፍረድባችሁ፡፡” ቆላ
2፣16-17 በማለት አስተምሯቸዋል፡፡
ሐ. እግዚአብሔር አብ ብቻ ፍጥረታትን ፈጠረ፡- ፍጥረታትን አብ ብቻውን ፈጠረ በኋላም የሰው ልጅ ሲበድል ሊያድነው ኢየሱስ ክርስቶስ መጣ ነገር ግን
እርሱ አስቀድሞ አልፈጠረውም የሚሉ መናፍቃን ነበሩና ለእነርሱ መልስ ይሆን ዘንድ ጽፎታል፡፡ ሐዋርያውም “…እርሱ የማይታይ አምላክ ምሳሌ ነው፡፡
የሚታዩትንና የማይታዩትን … ሁሉ በእርሱ ተፈጥረዋል፡፡ … ሁሉ በእርሱና ለእርሱ ተፈጥሮአል፡፡” በማለት ከአብ ጋር የሚተካከል የፍጥረታት ሁሉ ፈጣሪ
መሆኑን አስረድቷል፡፡ ቆላ 1፣14-15
የመልእክቱ አከፋፈል
ቆላ 1፡1-8 (መግቢያ)፡- ላኪው ለተተቀባዮች ያቀረበው ሰላምታ፣ ስለ ቆላስይስ ክርስትያኖች እምነትና ፍቅር
ሰምቶ ለእግዚአብሔር ያቀረበው ምስጋና
ቆላ 2፡8-23፡- በዚህ ክፍል ቅዱስ ጳውሎስ ሐሰተኞች እንዳይማርኳቸው የጻፈው ማሳሰቢያ፣ በጥምቀት
የክርስቶስ የመለኮት ምስጢር እንዳወቁ፣ ስለ ኦሪት በዓላትና ስለ መላዕክት አምልኮ እንዲፈርድባቸው፣ አትያዝ
አትቅመስ አትንካ ለሚሉት ትእዛዛት እንዲገዙ ያስተማራቸው ትምህርት ይገኝበታል፡፡
ቆላ 3፡- ስለ ሥነ ምግባር የጻፈላቸው ትምህርት፣ በምድር ያለውን ሳይሆን በላይ ያለውን እንዲሹ፣
ሊያስወግዷቸው ሊሽሯቸው ስለሚገቡ ነገሮች፣ ስለ ቤተሰብ ኑሮ ስለባሪያዎችና ስለጌቶች የጻፋላቸው ትእዛዛት
እንዲሁም እንዲጸልዩና በጥበብ እንዲመላለሱ የጻፈው ማሳሰቢያ ይገኝበታል፡፡
ቅዱስ ጳውሎስ እናትና አባት ልጆቻቸውን እንደሚመክሩ በትህትና ቃል ሲሰብክላቸው እንደ እግዚአብሔር መልአክ
አክብረው ተቀበሉት (1 ኛ ተሰ 2፡13) ለምቀኝነት የተነሣሱ አይሁድ ደበደቡት በገበያ ቦታም እየጎተቱ ያሰቃዩት ነበር፤
እንዲህ አድርጎ በትዕግስትና በታማኝነት ያቋቋማትን ቤተክርስቲያን መከራውን ሳይፈራ በየጊዜው እየተመላለሰ ይጎበኛት
እነርሱንም ይጠይቃቸው ይመክራቸው ነበር፡፡ ሐዋ 20፡6፣ 1 ኛ ጢሞ 1፡3
ቅዱስ ጳውሎስ ይህችን የመጀመሪያቱን መልእክት የጻፋት በአቴና ውስጥ ነው፡፡ የተሰሎንቄ ሰዎች ያለን ይበቃናል
እያሉ ሥራ መሥራት ማቆማቸውን አይሁድም ደግሞ መከራ ዝላበዙባቸውና የገዛ ወጋቸውንና ሥርዓታቸውን
ስለጫኑባቸው ጽድቅ በዚህ የሚገኝ ከሆነማ እያሉ በክርስትና ሕይወታቸው ተስፋ የቆረጡ ነበሩ፡፡ ሁሉንም መንፈሳዊ
ችግራቸውን እንደሰማ አስቀድመው በያዙት እምነት ይጸኑ ዘንድ ትክክለኛውንም የክርስትና ሕይወትና ትምህርት ያውቁ
ዘንድ ይህችን መልእክት በ 50 ዓ.ም አካባቢ ጽፎ በስልዋኖስ (በዕብራይስጥ ሲላስ የተባለው) እና በጢሞቴዎስ እጅ
ለላከላቸው፡፡
ቀድሞ በብጥብጥ ምክንያት በድንገት ስለወጣ የተሰሎንቄ ክርስቲያኖችን ለማጽናናት፣ ጠላት ሰይጣን
እንዳይቃወማቸው የእርሱም ድካም ከንቱ እንዳይሆን የመንፈስ ልጁን ጢሞቲዎስን አስይዞ ላከላቸው፡፡
ምንም እንኳ መከራና ስደት ቢበዛባቸውም ከሃይማኖት ያለመናወጣቸውን፣ እርስ በእርስም በፍቅር መኖራቸውን፣
ቅዱስ ጳውሎስንም ያልረሱ መሆኑንና ሌሎችንም አስደሳች ዜና ነገሮች ስለነበር በዚህ ምክንያት ጻፈላቸው፡፡ 1 ኛ
ተሰ 1፡6
የተሰሎንቄ ምዕመናን መከራከር ያበዙ ስለነበር የተማሩትን ትምህርትና ሃይማኖት መጠበቅ እንጂ ክርክርን
እንዳያበዙ ሊያስተምራቸው
አንዳንድ ያልበሰሉ ምዕመናን ከጌታ መምጣት በፊት የሞቱ ሰዎች እንደገና ተነሥተው ጌታን የሚገናኙ
አይመስላቸውም ነበርና ኃዘን ያበዙ ነበር፤ ስለሆነም ከጌታ መምጣት በፊት ትንሣኤ ሙታን እንዳለ በመግለጥ
ሊያጽናናቸው
እርስ በእርሳቸው የተፈቃቀሩ እየመሰላቸው አንዱ ሚስቱን ለሌላው በመስጠት የማይገባ ሥራ ይሠሩ ስለነበር፤
እነርሱን ለመገሰጽ
የመልእክቲቱ አከፋፈል
ይህች ሁለተኛይቱ ወደ ተሰሎንቄ ሰዎች የተጻፈች የቅዱስ ጳውሎስ መልእክት የተጻፈችው የመጀመሪያይቱ
መልእክት ከተጻፈች ከጥቂት ጊዜ በኋላ በቆሮንቶስ ሳለ እንደሆነ ይነገራል፡፡ ስለ ዳግም ምጽአት ብዙ መናፍቃን
እንደሚያስቸግሯቸው በሰማ ጊዜ ፈጥኖ ይህቺን መልእክት ጻፈላቸው፡፡ በተሰሎንቄ የሚገኙ አይሁድ ራሱ ቅዱስ ጳውሎስን
ሲያስጨንቁት እንደነበር የተሰሎንቄ ክርስቲያኖችንም ያስጨንቋቸው ነበርና የሚያጽናና መልእክቱን በ 51 ዓ.ም
በጢሞቲዎስና በሲላስ እጅ ልኮላቸዋል፡፡
በነገረ ምጽአት ዙሪያ ብዙዎች መናፍቃን ያስቸግራቸው ስለነበር በሰማ ጊዜ ይህችን መልእክት ጽፎላቸዋል፡፡
ከመጠን በላይ እርሱን ያስጨንቁት እንደነበር እነርሱንም ሲያስጨንቋቸው ምን ማድረግ እንደሚገባቸው በመምከር
ጽፎላቸዋል፡፡
የሁለተኛይቱ የተሰሎንቄ መልእክት ይዘት ከመጀመሪያይቱ መልእክት ይዘት ጋር ተመሳሳይ ነው፤ በውስጡ
የሚገኘው የሃይማኖት እና የሥርዓት ትምህርት ነው፡፡ 3 ምዕራፍ ሲኖሩት በሦስት ፍለን እናጠናዋለን፡፡
2 ኛ ተሰ 1፡ ክርስቲያንና መከራው
የዚህች መልእክት ጸሐፊ ማን ነው? የሚለው ጥያቄ እጅግ አነጋጋሪ ነበር፡፡ የቅዱስ ጳውሎስ ጸሐፊነት ለብዙ
ጊዜያት አነጋጋሪ ሆኖ ቆይቷል፡፡ ብዙዎች ይህ መልእክት የቅዱስ ጳውሎስ አይደለም ለማለት የሚገልጧቸው
ምክንያቶች፡-
ከ 185-254 ዓ.ም የነበረው አርጌንስ (origen)፣ ከ 150-215 ዓ.ም የነበረው ቀሌምንጦስ ዘእስክንድርያ ፣
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ቅዱስ አትናቴዎስና ታሪክ ጸሐፊው አውሳብዮስም የዕብራውያንን መልእክት
ከቅዱስ ጳውሎስ መጻሕፍት ዝርዝር ውስጥ አካተውታል፡፡ ሌሎች አባቶችም የቤተክርስቲያን ትውፊትን
መሠረት በማድረግ ቅዱስ ጳውሎስ እንደጻፈው ተናግረዋል፡፡
የአጻጻፉ ባሕርይ የተለየው ቅዱስ ጳውሎስ ጥልቅ የኦሪት ዕውቀት ስላለው መልእክቱ ተቀባይነት
እንዲኖረው ከሌሎቹ መልእክታት በአቀራረቡ ለየት አድርጎታል፡፡
ቅዱስ ጳውሎስ በዕብራይስጥ ቋንቋ ከጻፈው በኋላ ወደ ግሪክ ቋንቋ የተረጎመው ወንጌላዊው ቅዱስ
ሉቃስ ነው፡፡
ቅዱስ ጳውሎስ በሌሎቹ መልእክቶቹ ሁሉ በእርሱ እንደተጻፈ ማረጋገጫ አድርጎ የተናገረው የሰላምታ
ቃል በዚሁ መልእክት ላይም ተገልጧል፡፡ ዕብ 13፡5
ጥልቅ ዕውቀት ያለው ለአቀራረቡ ምንም ችግር የሌለበት ቅዱስ ጳውሎስ የዕብራውያን ሰዎች
ከእግዚአብሔር ተለይተው እንዳይቀሩ ሕጉን ሥርዓቱን፣ ትውፊቱን እንዲጠብቁ በሚገባቸው ኦሪታዊ
አገላለጽ እንዲመለሱ ለማድረግ የተጻፈላቸው በመሆኑ ነው፡፡
አስቀድሞ የእነርሱ ተማሪና ለወጋቸው ቀናተኛ ስለነበር ስሙን ቢያዩ ኖሮ በበቀል ስሜት መልእክቱን
ስለማይቀበሉት
ዘመኑ አይሁድ በሮማውያን ላይ ለማመጽ የተዘጋጁበት ጊዜ ስለነበር በሮም መንግሥት የቁም እስረኛ
የነበረ በመሆኑ በግዞትና በጦርነት ጊዜ መተማመን ስለማይኖር ሮማውያን ካወቁ ወገኖቹን ያነሳሳብናል
ብለው እንዳይቃወሙትና ምክንያት አግኝተው እስራቱን ወደ ፓለቲካ እንዳያዞሩበት፡፡
ቀድሞውንም ያሳሰሩት እነርሱ ናቸውና ገና ስሙን ሲያዩ ኦሪት አለፈች ሊለን ይሆናል ብለው ከማንበብ
እንዳይሰናከሉ፣ ነጻ ሆነው መልእክቱን አንብበው ፣እንዲረዱ ወደ ክርስትና ያልመጡትን ለማምጣት፤
የመጡትን ደግሞ ለማጽናት ጽፎላቸዋል፡፡ ይህችን መልእክት በመጀመሪያዋ እስራቱ በሮሜ እያለ በ 60
ዓ.ም አካባቢ ጽፎ በጢሞቴዎስ እጅ ልኮላቸዋል፡፡
የ/ደ/ይ/ቅ/ጊ/ቤ/ክ/ፍ/ሃ/ሰ/ት/ቤት ትምህርት ክፍል የተዘጋጀ 117
መልእክቱ የመጽሐፉ ዓላማ
የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ወደ እዚህ ምድር መምጣት ሱባኤ የተቆጠረለት፣ ትንቢት
የተነገረለት እንጂ እንደ እንግዳ ደራሽ እነደ ውኃ ፈሳሽ አለመሆኑን ለማስረዳት
ኢየሱስ ክርስቶስ ከነቢያት፣ ከመላዕክት እንዲሁም በክህነቱ በመሥዋዕቱ፣ በሕጉ፣ በኪዳኑ በሚያወርሰን
መካነ ዕረፍት . . . ወዘተ የሚበልጥ መሆኑን ለማስረዳት
በወቅቱ ክርስትናን በተቀበሉ ግሪክኛ ተናጋሪ በነበሩ አይሁድ ላይ ስደትና መከራ ስለጸናባቸው
በእምነታቸው ጸንተው መከራውን ታግሰው የጽድቅ አክሊል ተካፋዮች እንዲሆኑ ለመምከርና
ለማጽናት፡፡
መልእክቲቱ የተጻፈችበት ቦታና ዘመን በዕብ 13፡24 ላይ “ከኢጣልያ የሆኑ ሰላምታ ያቀርቡላችኋል”
የሚል ቃል ይገኛል፤ ስለዚህ ጸሐፊው ቅዱስ ጳውሎስ ታስሮ ከተፈታ በኋላ መሆኑ ይታወቃል፡፡ የተጻፈው
በኢጣሊያ ውስጥ ስለሆነ ጊዜው ከተፈታ በኋላ ከኢጣሊያ ሳይወጣ ነው ማለት ነው፤ ይህም በኢጣሊያ
ተጽፎ በጢሞቴዎስ እጅ መላኳን ይገልጣል፡፡
እንደሌሎቹ የቅዱስ ጳውሎስ መልእክታት ሁሉ የዕብራውያን መልእክትና የሥነ ምግባር ትምህርት ነው፡፡
የመልእክቱ አከፋፈል
የኖላዊነት መልእክታት
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለግለሰብ የላካቸው መልእክታት የኖላዊነት መልእክታት በመባል ይታወቃሉ፡፡
እነርሱም 1 ኛና 2 ኛ ጢሞቴዎስ፣ ቲቶ እና ፊልሞና ናቸው፡፡ ለመልእክታቱ ይህ ሥያሜ የተሰጣቸው
በውስጣቸው ትምህርተ ኖሎትን (አገልግሎትን) በስፋት ስለሚያነሡ ስለሆነ ነው፡፡ እነዚህንም መልእክታት
እያንዳንዳቸውን ቀጥሎ እንመለከታለን፡፡
የቅዱስ ጢሞቴዎስ የትውልድ ሀገር በሊቃኦንያ በምትገኘው የልስጥራን ከተማ ነው፡፡ አባቱ ግሪካዊ
ሲሆን ስሙ በታሪክ ተመዝግቦ አይገኝም፤ እናቱ አውንቄ የምትባል አይሁዳዊት ነች፡፡ /ሐዋ 16፡1-3/ በሐዋርያት
ሥራ ላይ እንደተገለጸው የቅዱስ ጢሞቴዎስ እናት ያመነች አይሁዳዊት ተብላ ተጠርታለች፡፡ /ሐዋ 16፣1/
ሴት አያቱ ሎይድ ትባላለች፡፡ ምንም እንኳን ባይገዘርም እናቱና አያቱ ክርስቲያኖች በመሆናቸው ጢሞቴዎስ
ስለ እምነቱ የተማረና ከሕፃንነቱ ጀምሮ ቅዱሳት መጻሕፍትን የሚያውቅ ነበር፡፡ /2 ጢሞ 3፣15 2 ጢሞ 1፣5/
ቅዱስ ጢሞቴዎስ በዕድሜው ወጣት ቢሆንም በሃይማኖትና በምግባር የጸና እንዲሁም መንፈሳዊ ቅናት ያለበት
ነበር፡፡ ጾም በጣም ይወድ ስለነበር ሥጋ፣ ቅቤ፣ ወይን ወዘተ... በአጠቃላይ የላመ የጣመ አይቀምስም ነበር፡፡ በዚህ የተነሣ
ሰውነቱ የመነመነ ሥራው ግን የፈጠነ ነበር፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ “ስለሆድህና ስለ በሽታህ ብዛት ጥቂት የወይን ጠጅ ጠጣ
እንጂ ወደፊት ውኃ ብቻ አትጠጣ” በማለት የመከረው ሰውነቱ በበሽታ እንዳይጠቃ መድኃኒት ይሆነው ዘንድ ነበር፡፡ /1
ጢሞ 5.23/
ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ጢሞቴዎስ የቅዱስ ጳውሎስ ደቀመዝሙር ሆነ የመንፈስ ቅዱስ አባቱ ከሆነው ከቅዱስ ጳውሎስ
በዋለበት እየዋለ ባደረበት እያደረ ክርስትናን በሚገባ ተማረ፡፡ ለቅዱስ ጳውሎስ የሥራ ረዳቱ፣ የመከራ አጋር ሆኖት
በሄደበት ሀገር አብሮ እየዞረ ቆይቷል፤ በልዩ ልዩ ሀገሮችም ብዙ መልእክታትን ሳይደክም እየተላከ መንፈሳዊ ግዳጁን
ፈጽሟል፡፡ እነዚህ ቦታዎች በእግር፣ በባሕር፣ በከብት የሚኬድባቸው ከመሆናቸው ባሻገር ሌትተቀን መጓዝን ይጠይቃሉ፤
ነገር ግን ቅዱስ ጢሞቴዎስ የመንፈስ አባቱን መልእክት ያለመታከት ያደርስ ነበር፡፡
ቅዱስ ጳውሎስ ቅዱስ ጢሞቴዎስን ለኤፌሶን ቤተክርስቲያን ጳጳስ አድርጎ ሹሞታል፡፡ /1 ጢሞ 1፣3/ የቤተክርስቲያን
ታሪክ ጸሐፊ የሆነው አውሳብዮስ የኤፌሶን ሀገረ ስብከት የመጀመሪያው ሊቀጳጳስ ቅዱስ ጢሞቴዎስ መሆኑን መስክሯል፡፡
በዚህ መንበሩ ቅዱስ ጳውሎስ እስካረፈበት 67 ዓ.ም ድረስ አብያተ ክርስቲያናትን እየመሠረተ ትምህርተ ወንጌልን እያስፋፋ
አገልግሏል፡፡ ከሀገረ ስብከቱ ሥራ በተጨማሪ ቅዱስ ጳውሎስንም በየጊዜው ያገለግለው ነበር፡፡ ከቅዱስ ጳውሎስ ዕረፍት
በኋላ ግን ወደ መንበሩ ተመልሶ ለ 33 ዓመታት ያህል ከኤፌሶን ሳይወጣ ቤተክርስቲያኒቱን አገልግሏል፡፡
የኤፌሶን ሰዎች በዓመት አንድ ጊዜ አርጤምስ የተባለ ጣዖታቸውን በዓል ያከብሩ ነበር፡፡ የበዓሉ አከባበር
እያንዳንዱ ሰው ፊቱን በጨርቅ ተሸፍኖ ከቤቱ በመውጣት ያገኘውን ሰው ሁሉ እያፈሰ ከፍ ዝቅ በማድረግና አናት አናቱን
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ጢሞቴዎስን የኤፌሶን ሊቀጳጳስ አድርጎ ሹሞት ነበር፤ ነገር ግን የሥርዓተ ኖላዊን (ሥርዓተ
ክህነትን) ትምህርት የሚያሰተምርበት ጊዜ ስላላገኘ የሁለት ዓመቱን የቁም እስር ጨርሶ ከሮም ሲወጣ በ 80 ዓ.ም
አካባቢ በሎዶቂያ ጥቂት የእረፍት ጊዜ በማግኘቱ ለልጁ ለጢሞቴዎስ ስለ ሊቀጵጵስናው ሥራ አጠቃላይ ሁኔታ
ጻፈለት፡፡ /1 ጢሞ 3፣4-15/
በኤፌሶን ከተማና በአካባቢዋ ባሉት ሀገሮች የተስፋፋውን የግኖስቲኮችን ፍልስፍና አጠቃላይ ሁኔታ ክርስቲያናዊ
ምላሽ በመስጠት ጻፈለት፡፡
ጢሞቴዎስ ወጣት በመሆኑ ማንም እንዳይንቀው ለራሱና ለትምህርቱ እንዲጠነቀቅ ሊመክረው ጽፎለታል /1 ጢሞ
4፣16-20 ፤ 20-21/
በኤፌሶን ገብተው ከነበሩት የሐሰት አስተማሪዎች ምእመናንን እንዲጠብቅ ሊያሳስበው ነው፡፡ /1 ጢሞ 1፣18-20 ፤ 4፣1-
4 ፤ 6-3/
ጢሞቴዎስን ለመምክርና ለማበርታት ጽፎለታል፡፡
1 ኛ ጢሞ 1፡- ላኪው ለተቀባዩ ያቀረበው ሰላምታ፣ ለጢሞቴዎስ ምክርና መመሪያ ለመስጠት፣ ስለ ቤተክርስቲያን
አገልግሎት የጻፈለት ትምህርህተ ጸሎትቅዱስ ጳወሎስ ስለመጠራቱ ያቀረበው ምስጋና፣ የሕግ አስተማሪ ሊሆኑ
ወደው ልዩ ትምህርትን ስለሚያስተምሩ ሐሰተኞች፣ምእመናን የሐሰተኞችን ትምህርት ከማዳመጥና ከክርክር
እንዲቆጠቡ እንዲመክራቸው
1 ኛ ጢሞ 2፣1-7፡- ስለ ጸሎትና ምልጃ፣ ስለ ሥርዓተ ጸሎት፣ ለሰዎች ሁሉ መጸለይ እንዲገባ
1 ኛ ጢሞ 2፣8-15፡- ስለ ሴቶች የአለባበስ ሁኔታ፣ ሴቶች በጉባኤ ማስተማር እንደማይገባቸው
1 ኛ ጢሞ 3-4፡- ስለ ዲያቆናትና ሊቀጳጳሳት ሹመትና ስለ ግዴታዎቻቸው ዝርዝር፣ የአጋንንትን ትምህርት
ስለሚያዳምጡ ሐሰተኞች፣ ስለ ጢሞቴዎስ የግል ሕይወት
1 ኛ ጢሞ 5-6፡- ስለ ምእመናን ከሐሰተኞች መምራን እንዲጠበቁ ትምህርት፣ ደንቦች እንዲሁም ለጢሞቴዎስ
ምክር ፣ በተለያየ ዕድሜ ስላሉ ሰዎች /ስለ ባልቴቶች፤ ስለ ሽማግሌ /ቀሳውስት/ስላመኑ ባሪያዎች፣ ጢሞቴዎስ የተጻ
ፈለትን አደራ እንዲጠብቅ የጻፈለት ማሳሰቢያ /1 ጢሞ 6፣3-16/ ፣ቃለ ቡራኬ
2. ሁለተኛው የሐዋርያው የቅዱስ ጳውሎስ መልእክት ወደ ጢሞቴዎስ
ጳውሎስ በመከራ ላይ እንደሆነ ሁሉ ጢሞቴዎስም በመከራ ውስጥ ስለነበር በእስረኛው በጳውሎስ ሳያፍር በጊዜውም
አለጊዜውም በተማረውና በተረዳው ነገር ጸንቶ እንዲኖርና መከራ እየተቀበለ የወንጌል አገልግሎቱን እንዲፈጽም
ለመምከር ነው፡፡ /2 ኛ ጢሞ 1፡8፣ 3፡10-14፣ ፣ 1-5/
ጳውሎስ ጢሞቴዎስን ከመሞቱ በፊት ሊያየው ስለናፈቀ ማርቆስን አንዳንድ ዕቃዎችን ይዞ በቶሎ እንዲመጣለት
ለማድረግ ነው፡፡ /2 ኛ ጢሞ 1፣4 ፤ 4፣9-11 ፤ 13፣21 /
ለጢሞቴዎስ መሰነባበቻ መልእክት ጽፎለታል
የመከረውን ምክር በድጋሚ ለማጽናት ጽፎለታል
ከሐሰተኞች መምህራን ሕዝቡን እንዲጠብቅ ለማሳሰብና ለመምከር ጽፎለታል፡፡
ቅዱስ ጢሞቴዎስ በኤፌሶን እየተዘዋወረ ሲያስተምር ግማሹ አምኖ እየካደ የቀረው በፍልስፍና እየተራቀቀ ሌላው
በአምልኮ ጣዖት እየተወሰደ ቢያስቸግረው እየተዘዋወረ መስበኩን አቁሞ በረሃ ገብቶ በብህትውና መኖርን መርጦ
ነበር፡፡ በዚህ ምክንያት ቅዱስ ጳውሎስ የተቀበለውን አደራ እንዲጠብቅ የደረሰበትን ፈተና እንዲታገስ በተማረው
ትምህርት ጸንቶ እንዲኖር ለማበረታታትና ለመምከር ጻፈለት
ጢሞቴዎስና ማርቆስ ለአገልግሎት የሚረዱትን ዕቃዎች ይዘው ቶሎ ወደ ርሱ እንዲመጡ በማሳሰብ ጻፈላቸው፡፡
/ሐዋ 25፣12 ፤ 27፣1፤ 28፣16 ና 30 2 ጢሞ 1፣6-14፤ 2፣1፤ 3፣10-17፤ 4፣6-8 16 ና 17/
2 ኛ ጢሞ 1፡- ሰላምታ፣ ጳውሎስ ለጢሞቴዎስ ያለው ናፍቆትና ሐሳብ፣ ስለተሰጠው ቃልኪዳን፣ ቅዱስ
ጳውሎስ ቅዱስ ጢሞቴዎስን እንዳበረታው
2 ኛ ጢሞ 2፡- ስለ ቤተክርስቲያን፣ በጌታችን ምስክርነትና በእሥረኛው በጳውሎስ እንዳያፍር፣ መልካም
ውጤትን ለማግኘት በመከራ እንዲጋደል፣ ከሐሰት አስተማሪዎች እንዲርቅ
2 ኛ ጢሞ 3፡- ስለሚመጣው አስጨናቂ ዘመን፣ በመጨረሻው ዘመን ካለው ክፋትና ስህተት ርቆ በተማረውና
በተረዳው ነገር እንዲጸና፣ በጊዜውም አለጊዜውም የወንጌል ሰባኪነትን ሥራ እንዲያደርግ፣
2 ኛ ጢሞ 4፡- ከመሞቱ በፊት እንዲመጣለት የጻፈለት ቃል፣ ሕይወቱ እንደሚሰዋ ሲመጣ ማርቆስንና
በጢሮአዳ የተዋቸውን በርኖሱንና መጻሕፍትን እንዲያመጣለት፣ ፊተኛው ሙግቱ፣ ጳውሎስ ለሌሎች ሰዎች
ያቀረበው ሰላምታ፣ ስለ አርስጦስና ስለ ጥሮፊሞስ፣ ስማቸው የተጠራ አራት ሰዎች ለጢሞቴዎስ ያቀረቡት
ሰላምታ፣ የጳውሎስ ቃለ ቡራኬ፣ ስለ ወንጌል አገልግሎትና ስለመሞቱ
3. የሐዋርያው የቅዱስ ጳውሎስ መልእክት ወደ ቲቶ
ቅዱስ ጳውሎስ ከሚወዳቸውና የወንጌል አገልግሎት የሥራ ረዳቱ ከሆኑት አንዱ ቲቶ ነው፡፡ ቲቶ የተወለደው
ከአሕዛብ ወገን ከግሪክ /የአንጾኪያ/ ሰዎች ነው፡፡ /ገላ 2፣3/ ቅዱስ ጳውሎስ በገላትያ መልእክቱ ውስጥ “ከዚያ ወዲያ
ከዐሥራ አራት ዓመት በኋላ ከበርናባስ ጋር ቲቶን ይዤ ወጣሁ” በማለት ለአገልግሎት የተጠራበትን ጊዜ ይነግረናል፡፡ ይህም
ጊዜ በሐዋርያት ሥራ ላይ ለተመዘገበው ለኢየሩሳሌም ጉባኤ በሄደ ጊዜ መሆኑን ብዙ መምራኖች ይናገራሉ፡፡ /የሐዋ 15፣2/
የቅዱስ ጳውሎስ ደቀ መዝሙር ከሆነበት ጊዜ ጀምሮ እንደ ጢሞቴዎስ አብሮት አገልግሏል፡፡ በ 3 ኛው የቅዱስ
ጳውሎስ ሐዋርያዊ ጉዞ ወቅት ወደ ቆሮንቶስ ቤተክርስቲያን ተልኮ እንዳገለገለ ከ 2 ኛው የቆሮንቶስ መልእክት እንረዳለን፡፡
/2 ቆሮ 2፣13 ፤ 2 ቆሮ 8፣6 ፤ 2 ቆሮ 8፣16-24/ ከዚህ በተጨማሪም ቲቶ ከቅዱስ ጳውሎስ እና ከበርናባስ ጋር ከአንጾኪያ ወደ
ኢየሩሳሌም በመመላለስ በገላትያና በቆሮንቶስ እንዲሁም በተለያዩ አብያተ ክርሰቲያናት ብዙ አገልግሎት እንዳበረከተ ቅዱስ
ጳውሎስ ተናግሯል፡፡ (ገላ 2፣ 2 ኛ ቆሮ 8፡18) በአይሁድ ክርክር የተነሣ የአንጾኪያ ቤተክርስቲያን ጳውሎስንና በርናባስን
ቲቶ ክርስትና የተቀበለው በቅዱስ ጳውሎስ አስተማሪነት በመሆኑ የመንፈስ ቅዱስ ልጁ ነው፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ
ጳውሎስም ስለ ቲቶ ሲመሰክር “በሃይማኖት ኅብረት እውነተኛ ልጄ” በማለት ጠርቶታል፡፡ /ቲቶ 1፣1/ በቅዱስ ጳውሎስ
ስብከት ስላመነ በሃይማኖት የወለደው ልጁ ነው፡፡ /ቲቶ 1፣4/
ይህን ሐዋርያዊ ተልእኮውንና መንፈሳዊ ትጋቱን ተረድቶ ቅዱስ ጳውሎስ በሜዲትራንያን ባሕር አጠገብ በምትገኝ
የቀርጤስ ቤተክርስቲያንን እንዲያደራጅና እንዲያስተዳድር በውስጧ አይሁድ በሚኖርበት ሀገር ሊቀጳጰስ አድርጎ ዲያቆናትን
ቀሳውስትን እንዲሾም እንዲያስተምር ሾሞታል፡፡ (ቲቶ 1፡5)
ቅዱስ ጳውሎስ እስከሚያርፍበት ጊዜ ድረስ እንደ ጢሞቴዎስ ሁሉ ቲቶ እየተመላለሰ ሲያገለግለው ከቆየ በኋላ
ቅዱስ ጳውሎስ ሲያርፍ ከእነ ቅዱስ ሉቃስ ጋር በመሆን ከቀበረው በኋላ ወደ ሀገረ ስብከቱ ተመልሶ በቀርጤስ ዋና ከተማ
በጎርቲና ሲያገለግል ቆይቶ በ 94 ዓመቱ ዐረፈ፡፡
መልእክቲቱ የተጻፈችው ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ከቀርጤስ ወደ ኤፌሶን ጢሮአዳና መቄዶንያ ቆይቶ ወደ
ድልማጥያና እልዋሪቆን በመግባት ካስተማረ በኋላ መቄዶንያ አጠገብ ወዳለው ወደ ሂቆጵልዮን ገብቶ ጥቂት ዕረፍት አድርጎ
ለቀርጤሱ ቤተክርስቲያን ሊቀጳጳስ ለቲቶ በ 63 (1 ኛ ጢሞቴዎስ በተጻፈበት ዘመን ነው) ዓ.ም አካባቢ ስለ ሥርዓተ ኖሎት፣
ስለ ወንጌል አገልግሎት እና ክብር አርጣ በተባለው ደቀመዝሙር አጽፏታል፡፡ /ቲቶ 3፣12/
የቀርጤስ አብያተ ክርስቲያናት በቁጥር በዝተው ስለነበር ወንጌል እንዲስፋፋባቸው በአስተዳደርም በኩል መመሪያ
ለመስጠት ይህችን መልእክት ጻፈለት፡፡
ለቲቶ ሥርዓተ ኖሎትን የእረኝነትን ሥርዓት ለማስተማር፤ የቀርጤስ ሰዎችን ሊገሥጻቸውና ሊመክራቸው ስለፈለገ
መልእክቱን ጽፎለታል
ኤጵስ ቆጶሳትና ቀሳውስት ሆነው ለመሾም የሚችሉት ምግባራቸው ምን መምሰል እንዳለበት ይጽፍለታል
ለሌሎች አርአያ በመሆን ቤተክርስቲያኒቱን እንዲመራ ጽፎለታል
ሕዝቡን የሚጠራበትን ሥርዓት ሊጽፍለት ስለፈለገ
የቀርጤስ ሰዎች ጠባያቸው የከፋ ሰማቸው የጠፋ ነበርና መከራ እንዳይበዛበት፣ መከራ ቢመጣበትም እንዲታገስ
አስቀድሞ የሰዎቹን ጠባይ በማስገንዘብ አገልግሎቱም እንዳይጎዳ ጽፎለታል፡፡ /ቲቶ 1፡12/
በሀገሪቱ ብዙ ዓለማውያን ሰዎችና መናፍቃን ስለነበሩ ከእነርሱ እንዲርቅ ምዕመናኑም ግንኙነት እንዳይኖራቸውና በከፋ
ትምህርታቸው እንዳይስቡ ክህደታቸውንና ክፋታቸውን እየገለጠ ጽፎለታል፡፡ /ቲቶ 1፡9-11/
ለድሆች ርዳታ የሚሆን የልግስና ስጦታን ለማሳሰብ፡፡
ወደ ርሱ እንዲመጣ ሊጠራው ስለፈለገ
በመጨረሻም በትምህርትና በግብረገብነት የታወቁ ሰዎችን በመምረጥ የቤተክርስቲያን ጠባቂ የሚሆኑትን እንዲሾም
እርሱም በትጋት እንዲያገለግልና እንዲጸና ለሌሎች አርአያ በመሆን ቤተክርስቲያኒቱን እንዲመራ ጽፎለታል ፡፤/ቲቶ 1፡5-
10/
ቲቶ 1፡- ላኪው ጳውሎስና ማንነት፣ ተቀባዩ ቲቶና ከጳውሎስ የቀረበለት ሰላምታ፣ ስለ ቀርጤስ ቤተክርስቲያን
አስተዳደር፣ ስለ ቀሳውስትና ኤጲስ ቆጶሳት ሹመት፣ ከተገረዙት ወገን ስለሆነ የሐሰት አስተማሪዎች
ቲቶ 2፡- ስለ ቤተክርስቲያን መሪዎች አርአያነት፣ በተለያየ ዕድሜና ደረጃ ስለሚገኙ ምእመናን ሕይወት፣ ሰዎችን
የሚያድነው የእግዚአብሔር ጸጋ መገለጡና ጥቅሙ፣ ስለ ቤተክርስቲያን መሪዎች አርአያነት
ቲቶ 3፡- ስለ ሐዋርያት ግብረ ገብነትና መንፈሳዊ ተልዕኮ፣ ድኅነት በእግዚአብሔር ቸርነት ስለመሆኑ፣
እግዚአብሔርን የሚያምኑ መልካም ሥራ መሥራት እንዳለባቸው፣ የመጨረሻ ቃላት፣ ሰላምታና ቡራኬ
የ/ደ/ይ/ቅ/ጊ/ቤ/ክ/ፍ/ሃ/ሰ/ት/ቤት ትምህርት ክፍል የተዘጋጀ 122
4. የሐዋርያው የቅዱስ ጳውሎስ መልእክት ወደ ፊልሞና
ሀገሩ ቆላስይስ የሆነው ፊልሞና ደግ ባለጸጋ ሲሆን አፉብያ የተባለች ሚስትና የቈላስይስ ቤተክርስቲያን ኤጲስቆጶስ
የነበረው አክርጳ የተባለ ልጅ ነበረው፡፡ ወደ ኤፌሶን ለሥራ በሄደ ጊዜ የሐዋርያው የቅዱስ ጳውሎስን ስብከት ሰምቶ
ከነቤተሰቡ አምኖ ተጠምቋል፡፡
ይህ ሰው አብርሃማዊ ሕይወት የነበረው ሲሆን እንግዶችን በቤቱ እየተቀበለ ያበላ፣ ያጠጣ፣ ያሳድርም ነበር፡፡
በቤቱም ክርስቲያኖች ይሰበሰቡ እንደነበርም ተገልጧል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስን ይንከባከበው፣ በአገልግሎቱም የሚያስፈልገውን
ያደርግለት ነበር፡፡ በመልእክቲቱ ውስጥም ጳውሎስ እንደ ወንድም እንደ ልብ ወዳጅ ወይም እንደ ባልንጀራ አድርጎ
እያቀረበ “የማስተናገጃ ቤት አዘጋጅልኝ” እያለ በመልእክቱ ይጽፍለታል፡፡
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ መልእክቲቱን የጻፈው ለፊልሞና ቢሆንም ከርሱ ጋር ላሉ ክርስቲያኖችም ጭምር መሆኑን
የሚገልጹ ቃላት አሉ፡፡ /ፊል 1፣1-25/ መልእክቱንም በ 62 ዓ.ም (የቈላስይስ መልእክት በተጻፈበት ጊዜ) ነው በሮም እስር
ቤት የጻፈው፡፡ /ቲቶ 1፡1-23/ በኋላም ከቲኪቆስ ጋር አናሲሞስን አስከትሎ ለርሱና ለቤተሰቡ ላከላቸው፡፡
ፊልሞና አናሲሞስ የተባለ አገልግጋይ ነበረው፤ ይህ አገልጋዩ የሚጠብቃቸው የፊልሞና ከብቶች ሲጠፉበት ሀገሩን ትቶ
ሄደ፡፡ “ማን ባስታረቀኝ” እያለ ሲያዝን ቅዱስ ጳውሎስን ስለጠቆሙት ወደ ሮሜ ሲገባ ቅዱስ ጳውሎስ በመጀመሪያ
እስራቱ ላይ አግኝቶት ትምህርቱንም ሰምቶ አምኖ ተጠመቀ፡፡ ወደ ሮሜ ለምን እንደመጣም የደረሰበትንም ሁኔታ
ሲነግረው ይህቺን የማስታረቂያ መልእክት ለፊልሞናና ለቤተሰቦቹ ጻፈ፡፡
ቅዱስ ጳውሎስ የፊልሞናን አገልጋይ አናሲሞስን ለራሱ ሊያስቀር ፈልጎ ነበር፤ ነገር ግን ከፊልሞና ሳይማከር ሊያደርግ
ስላልወደደ በመልእክቱ ለመነው፡፡ በዚህም ቅዱስ ጳውሎስ አናሲሞስን “በእሥራት የወለድሁት ልጄ “ ብሎ
ጠርቶታል፡፡ /ፊል 1፣11/
ፊልሞናና አፍብያ በአናሲሞስ መጥፋት እንዳያዝኑ፣ መንፈሳዊዉ አገልግሎታቸውን ከመወጣት ወደ ኋላ እንዳይሉ፣
ከብቶችን መጠበቅ ብቻ ሳይሆን የተጠመቁ ክርስቲያን ወገኖቹን ሁሉ እያስተማረ ከእነርሱ ጋር ሆኖ ያበረታታቸው
ዘንድ መልእክቷን በእጅ አስይዞ ልኮላቸዋል፡፡
ስለጠፋው የፊልሞና ንብረትና በዚህ ምክንያት በክርስቲያኖች መካከል ልዩነት እንዳይኖር አጠቃላይ ሁኔታ
ጽፎለታል፡፡
አናሲሞስን ከጌታው ከፊልሞና ጋር ለማስታረቅ፤ “ያለበትን ብድር እኔ እመልሳለው ብዬ በእጄ እጽፋለው፡፡” እያለ ቃል
በመግባት እንደ ባርያ ሳይሆን እንደ ወንድም እንዲቀበለው ሊማልደው ጻፈለት፡፡ /ፊል 1፡11-20/
በእነ ፊልሞና ጸሎት ወደ እነርሱ የመሄድ ተስፋ ነበረውና ሲሄድ በፊልሞና ቤት ለማረፍና ለማገልገል ስለፈለገ
የማስተናገጃ ቤት እንዲያዘጋጅለት ሊለምነው ይህችን መልእክት ላከ
ፊል 1፣1-7፡- ሰላምታና ምስጋና፣ በላኪው እሥር ላይ ያለው ጳውሎስና ተቀባዩ ፊልሞና ከነቤተሰቡ፣ ጳውሎስ
በፊልሞና እምነትና ፍቅር ለአምላኩ ያቀረበው ልመና
ፊል 1፣8-21፡- ስለ አናሲሞስ የቀረበ ምልጃ፣ ክርስቲያን ስላደረገው እንደ ወንድሙ እንዲቀበለው ስለማድረጉ፣
ስለ አናሲሞስ በደል ጳውሎስ የወሰደው ኃላፊነት፣ ጳውሎስ በፊልሞና ላይ ያለው መታመን
ፊል 1፣22-25፡- ከጳውሎስ ጋር ካሉት ሰዎች ለፊልሞና የቀረበ ሰላምታ፣ የአደራ ሰላምታ እንዲሁም ቡራኬ
ሰባቱ መልእክታት
መልእክታቱም ሲላኩ ከአንዱ ቤተክርስቲያን ይደርስና ለምእመኑ ከተነበበና ከተረዱ በኋላ ሀብት ያላቸው አጽፈው
ቅጅ ያስቀሩና ዋናውን ለአዋሳቸው ወይም ለሌላ ቤተክርስቲያን እንዲዳረስ በማሰብ ያስተላልፉና ይጠቀሙበት ነበር፡፡
ቅዱስ ጴጥሮስ የቀድሞ ሰሙ ስምዖን ይባል ነበር፡፡ /ሉቃ 5፡34/ ስምዖን ማለት “ስምኦኒ እግዚአብሔር-
እግዚአብሔር ሰማኝ ማለት እንደሆነ የትርጓሜ መምህራን ይናገራሉ፡፡ እናቱ ትወደው ስለነበር በነገድዋ ስም ስምዖን
ብላ ጠርታዋለች፡፡ በኋላ ግን ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርሰቶስ ኬፋ ብሎ ሰየመው፤ ኬፋ በአርማይክ
ቋንቋ ሲሆን በግሪክ እና በላቲን ቋንቋ ጴጥሮስ ማለት ነው፡፡ ጴጥሮስ ማለት ዐለት ማለት ነው፡፡ /ናቴ 16፡18፣ ዮሐ 1፡43/
ጴጥሮስ ተብሎ ከተሰየመ በኋላ ስምዖን በሚለው ሰሙ የተጠራበት ጊዜ አለ፡፡ /ዮሐ 21፡15-16/ በአንዳንድ ንባቦችም ስምኦን
ጴጥሮስ እየተባለ ይጠራል፡፡ /2 ኛ ጴጥ 1፡1/
የጴጥሮስ አባት “ዮና” ሲባል እናቱ ግን ስሟ አልተዘገበም፡፡ እንድርያስ የተባለ ወንድም አለው፤ ሚስት እንደነበረችውም
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ተገልጧል፡፡ /1 ኛ ቆሮ 9፡5/ ስሟ ግን አልተገለጠም፤ አንዳንድ ትውፊቶች “ጴርጴተዌ” ትባል
እንደነበር ይገልጻሉ፡፡
ቅዱስ ጴጥሮስ ከወንድሙ ከእንድርያስ ጋር ያደገበት ሀገር ከገሊላ ባሕር በስተሰሜን ዮርዳኖስ አቅራቢያ በምትገኘው
“ቤተሳይዳ” ተብላ በምትጠራ ቦታ ነበር፡፡ /ዮሐ 1፡45/ ይህቺ ከተማ የወላጆቹ ሀገር ናት፡፡ በትዳር ሳለ ግን ከወንድሙ
ከእንድርያስ ጋር የዓሣ ማጥመድ ሥራ እየሠራ በቅፍርናሆም ከተማ ይኖር እንደነበር በማር 1፣21 ላይ ተገልጧል፡፡
ከጴጥሮስ በፊት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን የተዋወቀው ወንድሙ እንድርያስ ነው፤ እንድርያስም “መሲህን
አግኝተናል” ብሎ ከነገረው በኋላ ነው ጴጥሮስ ወደ ጌታችን ሄዶ ኬፋ /ጴጥሮስ/ ትባላለህ ብሎ የሰየመው፡፡ /ዮሐ 1፡41-43/
ብዙም ሳይቆይ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በገሊላ ሀገር አጠገብ ሲመላለስ ጴጥሮስና እንድርያስ
መረባቸውን ወደ ባሕር ሲጥሉ አየ፤ በስምዖን ጴጥሮስ ታንኳ ውስጥ ሆኖ ለሕዝቡ ትምህርት ከሰጠ በኋላ ብዙ ዓሣ
እንዲያጠምዱ አደረጋቸው፡፡ ጴጥሮስ ግን “ኃጢአተኛ ነኝና ከእኔ ተለይ” ብሎት ነበር፤ ጌታችን ግን “አትፍራ ከእንግዲህ
ወዲህ ሰውን የምታጠምድ ትሆናለህ” ብሎ ጠራው፤ ያን ጊዜም ሁሉን ትቶ ተከተለው፡፡ /ማቴ 4፡18-22/
ክርስቶስም ቅዱስ ጴጥሮስን ዐለት ብሎ ከሰየመው በኋላ በዚህ ዐለት ላይ ቤተክርስቲያኔን እሠራለው
የገሀነም ደጆችም አይችሏትም ብሏል፡፡ /ማቴ 16፡18/ ቅዱስ ጴጥሮስ ይህንን ለመባል ያበቃው የክርስትና
እምነት መሠረት የሆነውን ምሥጢረ ሥጋዌ /ምሥጢረ ተዋሕዶን/ በመመስከሩ ነው፡፡ አይሁድ አንዶቹ
የዮሴፍ ልጅ ነው፣ ሌሎቹ ደግሞ ከነቢያት አንዱ ነው ሲሉ የክርስቶስን አምላክነት ቁልጭ አድርጎ
በመመስከሩ ምስክርነቱ የእምነት መሠረት ነውና “ዐለት” ተባለ፡፡ ከሦስቱ ምስጢር ሐዋርያትም
ተቈጠረ፡፡
ቅዱስ ጴጥሮስ በሰማዕትነት ያረፈው በኔሮን ቄሳር (54-68 ዓ.ም) ዘመን ነው፤ ከቅዱስ ጳውሎስ ጋር
በአንድ ቀን እንደሆነና ቀኑም ሐምሌ 5 ቀን 68 ዓ.ም ነው፡፡ ሌሎች ሊቃውንት ደግሞ በአንድ ቀን ይሁን እንጂ
የተሰዉት በአንድ ዓመት አይደለም ይላሉ፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ሁለት መልእክታትን ጽፎልናል፡፡ እነዚህን
እያንዳንዳቸውንም ቀጥሎ እንመለከታለን፡፡
ቅዱስ ጴጥሮስ ይህቺን መልእክት የጻፈው በ 60 ዓ.ም በርሱ ተናጋሪነት በስልዋኖስ እጅ ሲሆን
የጻፈበት ቦታው “ባቢሎን” መሆኗን ከራሷ ከመልእክቲቱ መረዳት ይቻላል፡፡ ይህንንም መረዳት
የሚቻለው “ከእናንተ ጋር ተመርጣ በባቢሎን ያለች ቤተክርስቲያን ልጄም ማርቆስ ሰላምታ
ያቀርብላችኋል” ብሎ በጻፈው ቃል ነው፡፡ /1 ኛ ጴጥ 5፡13/ ስለዚህ ጴጥሮስ ያን ጊዜ በባቢሎን ነበር ማለት
ነው፡፡
የመልእክቲቱ ተቀባዮች በልዩ ልዩ ፈተና አዝነው ነበርና ለጥቂት ጊዜ መከራ ቢቀበሉም ታላቅ ክብርና ጸጋ
እንደሚያገኙበት እየመሰከረ ሊያጽናናቸው ጽፎታል፡፡ /1 ኛ ጴጥ 2፡20፣ 4፡12-14/
በአሕዛብ መካከል ሲመላለሱ ከቀድሞ ሥራቸው ተለይተው ኑሯቸው መልካም እንዲሆን ሊመክራቸው
ጽፎታል፡፡ /1 ኛ ጴጥ 2፡12/
ያለምንም ምክንያት ሊደርስ ከሚችል ፈተናና ችግር ጌታችን እንደታገሠ እንዲታገሡ ለመምከር
በንጹሕ ደም የተዋጁ ስለሆነ በንጽሕና እንዲኖሩ በክርስቶስ ላይ እንደተመሠረቱት ካህናትና ቤተመቅደስ
እግዚአብሔርን እንዲያገለግሉ
የዘለዓለም ሕይወት እንዳላቸው ያውቁ ዘንድ
ከሥጋ ምኞት እንዲጠበቁ
ከምእመናን ሁሉ ጋር ባላቸው የሚገባ ግንኙነት ትሑታን እንዲሆኑ ጽፎላቸዋል
በክርስትና ሕይወታቸው የጸኑ ቢሆኑም ከፊት ይልቅ እንዲተጉ ስለፈለገ ጻፈላቸው፡፡ /2 ኛ ጴጥ 1፡10 /
ኑፋቄን አሾልከው ከሚያገቡ ሐሰተኛ አስተማሪዎች እንዲጠበቁ /2 ኛ ጴጥ 2፡1/
የመልእክቲቱ ተቀባዮች እውነትን ቢያውቁም በእውነት ቢጸኑም የሚያነቃቃቸው አድርጎ ጽፎላቸዋል፡፡
ሐሰተኞች ነቢያትና መምራን ለዚህ ዓለም ሠራኢ መጋቢ የለውም፣ ትንሣኤ ሙታን የለም፣ ኅልፈተ ሰማይ ወምድር
የለም፣ አንድ ጊዜ ካመኑ ምግባር አይጠቅምም እያሉ የክህደት ትምህርታቸው ያላመኑትን ምግባር ያላቸውን
ክርስቲያኖች ያውኳቸው ስለነበር ለእነዚህ ሰዎችና ለጥያቄዎቻቸው መልስ በመስጠት ይህን መልእከት ጽፎላቸዋል፡፡
የሚገባውን የክርስቲያን አኗኗር ሕይወትና መሠረቱ፣ የቤተክርስቲያን መሥራች የቅዱሳን ሁሉ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ
መሆኑን ያውቁና በክርስትና እምነት ይጸኑ ዘንድ ጽፎላቸዋል፡፡
ያመኑት ሰዎች ይህን መልእክት ተረድተው በሃይማኖት በምግባር እንዲኖሩ ሌላዎቹ ምግባር ሃይማኖት የሌላቸው
አንብበው ተረድተው ይመለሱ ዘንድ ይህን መልእክት ጽፏል፡፡
በሐዲስ ኪዳን ውስጥ የዮሐንስ መልእክታት የሚባሉት ሦስት ናቸው፡፡ ነገር ግን በሦስቱም መልእክታት መጀመሪያ
ላይም ሆነ በውስጣቸው የዮሐንስ ስም አይገኝም፤ ይሁን እንጂ አራተኛውን ወንጌል የጻፈው ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ
እንደሆነ ከጥንት ጀምሮ የታመነ ነው፡፡ የሐዋርያው የቅዱስ ዮሐንስ ደቀመዝሙር እንደሆነ የሚነገርለት ፖሊካርፕ የተባለው
የቤተክርስቲያን አባት ወደ ፊልጵስዮስ በጻፈው ጽሑፍ ውስጥ እነዚህን ሦስቱን መልእክታት ዮሐንስ እንደጻፋቸው
መስክሯል፡፡
ፍቁረ እግዚእ ቅዱስ ዮሐንስ ይህንን መልእክት የጻፈው ለሰባት ዓመታት በፍጥሞ ደሴት ታሥሮ ከተፈታ በኋላ በ 96
ዓ.ም አካባቢ ነው፡፡
በዚያ ዘመን ከተነሡት የሐሰት መምህራን እንዲጠበቁ ምዕመናን ለማሳሰብ ነው፡፡ /1 ኛ ዮሐ 2፡26/ እነዚህን ሰዎች
ቅዱስ ዮሐንስ “የክርስቶስ ተቃዋሚዎች” በማለት ይጠራቸዋል፡፡ /1 ኛ ዮሐ 2፡18/ የመልእክቲቱንም አጠቃላይ ይዘት
ቅዱስ ዮሐንስ “እግዚአብሔር ፍቅር ነው” በማለት ይናገራል፡፡ /1 ኛ ዮሐ 4፡9-16/
ትንሣኤ ሙታን የለም፤ በመናገርና መሥራት እንጂ በማሰብ የሚሠራውን ኃጢኣት እግዚአብሔር አያውቅም፤ ኢየሱስ
ክርስቶስ በሥጋ አልተገለጠም ከጥምቀት በኋላ ምግባር መሥራት ጥቅም የለውም ዋጋም አያሰጥም፤ አዋቂዎች
“ግኖስቲኮች” ነን በማለት ያለ እነርሱ እውነተኛ ክርስቲያን እንደሌለ በማሰብ ለእኛ የመጨረሻ ዕውቀት ተገልጦልናል
ስለዚህ ያለ ሕግ ልንኖር እንችላለን ብለው ላስተማሩ ከሀድያን መልስ ይሆን ዘንድ
በቤተክርስቲያናችን ባለው የዚህች መልእክት ትርጓሜ መግቢያ ላይ የተመረጠችው እመቤት ስሟ “ሮምና” እንደምትባል
ተገልጧል፡፡ ዮሐንስ በዚህች መልእክቱ ራሱን እኔ “ሽማግሌው (ቀሲስ)” ብሎ ይጠራል፡፡
በመጀመሪያው መልእክት የተገለጹት መናፍቃን ምዕመናንን ለማስካድ ይጣደፉ ስለነበር የሐሰት ትምህርታቸውን
በመቃወም እውነተኛዋን የክርስትና ትምህርት እንዲያጸኑ ነው፡፡
በአጠቃላይ ቅዱስ ዮሐንስ በፍጥሞ ደሴት በታሠረ ጊዜ በመናፍቃን የክህደት ትምህርት የተነሣ በቤቷ ያለው
የክርስቲያኖች ጉባኤ መከፋፈል ደረሰበት፤ ጠብ ክርክር ተነሣ፡፡ ይህን የሰማው ቅዱስ ዮሐንስ የቀድሞ ኑሮዋን ወይም
3 ኛ ዮሐ 1፣1-4፡- ስለ እምነቱ ጠንካራነት ለጋይዮስ የቀረበ ምስጋናና ጸሎት፣ ስለ ጋይዮስ እውነተኛነት የወንድሞች
ምስክርነት
3 ኛ ዮሐ 1፣5-8፡- ስለ እንግዳ ተቀባይነቱ ለጋይዮስ የቀረበ ምስጋና ስለ ጌታም ከአሕዛብ የወጡ ወንድሞችን
በእንግድነት ተቀብሎ ያሳየው የፍቅር ሥራና እንዲህ ያሉትን በእንግድነት መቀበል በሃይማኖት እንደሚገባ
3 ኛ ዮሐ 1፣9-11፡- በትዕቢታቸው ዲዮጥራጢስ ላይ የተሰጠ ማስጠንቀቂያ
3 ኛ ዮሐ 1፣12-14፡- ስለ ድሜጥሮስ የተሰጠ ምስክርነት፣ ጋይዮስን ሄዶ ሊያየው እንደነበር የሰጠው ተስፋ
3 ኛ ዮሐ 1፣15፡- የጋይዮስና ለወገኖቹ የቀረበ ሰላምታ
6. የሐዋርያው የቅዱስ ያዕቆብ መልእክት
የመልእክቱ ጸሐፊ
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያዕቆብ ተብለው የተጠሩና በተቀራራቢ ዘመን የኖሩ ከሦስት በላይ ሰዎች አሉ፡፡ ከእነዚህም
መኸከል፡-
ይህ ከዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያት አንዱና የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ወንድም ነው፡፡ (ማቴ. 10-2 ፣ 4-21) በሄሮድስ
አግሪጳ ዘመን በ 44 ዓ.ም ሰማዕትነትን የተቀበለ ነውና የዚህ መልእክት ጸሐፊ እርሱ ሊሆን አይችልም፡፡ (ሐዋ. 12-2)
ይህ በማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 10 ከቊጥር 3 ላይ ስሙ የተጠቀሰ ሐዋርያ ነው፡፡ አንዳንድ ሰዎች የጌታችን ወንድም
የተባሉት የእልፍስ ልጆች ናቸው፤ ስለዚህም የዚህ መልእክት ጸሐፊ ያዕቆብ ወልደ እልፍዮስ ነው ይላሉ፡፡ ሆኖም ግን
መልእክቱን እርሱ አልጻፈውም፡፡ ይሄን ከሚያረጋግጡልን ነገሮች አንዱ በዮሐ 7-5 ላይ“ወንደሞቹ ስንኳ አላመኑትም”
ተብሎ እንደተጻፈ የጌታ ወንድም ያዕቆብ በጊዜው ገና በኢየሱስ ክርስቶስ የማያምን መሆኑ ነው፡፡ ነገር ግን የእልፍዮስ ልጅ
ያዕቆብ የጌታችን ሐዋርያ እንደመሆኑ መጠን በጌታ አላመነም ሊባል አይችልም፡፡44
በመጽሐፈ ስንክሳር ላይ “ይህም ቅዱስ የጠራቢው የዮሴፍ ልጅ ነው፡፡ እርሱም ከልጆቹ ሁሉ የሚያንስ ነው፡፡
እርሱም ንጹሕ ድንግል የሚሆን ከጌታችን ጋር አደገ ስለዚህም ክብር ይግባውና የጌታችን ወንድም ተባለ” 45 በማለት
እንደሚነግረን የመልእክቱ ጸሐፊ የጌታ ወንድም ቅዱስ ያዕቆብ ይህ ነው፡፡ ቅዱስ ጄሮም እንደገለጸው ቅዱስ ያዕቆብ
በኢየሩሳሌም ጳጳስ ሆኖ የተሾመ እና እስከ ዕለተ ዕረፍቱም በዚያው ስፍራ የነበረ ነው፡፡ ቅዱስ ኤጲፋንዮስና ታሪክ ጸሐፊው
አውሳብዮስ እንደሚሉት ያዕቆብ ለጌታ የተለየ ናዝራዊ ነበር፡፡ ከእናቱ ማኅፀንም የተመረጠ ነው፡፡ ወይንና የሚያሰክር
መጠጥን አልጠጣም በፀጉሩም ላይ ምላጭ አላረፈበትም፡፡
መልእክቱ የተጻፈው ለተበተኑት ዐሥራ ሁለቱ ነገዶች ነው፡፡ /ያዕ.1፡1/ ይህንን በተመለከተ የተለያዩ ሀሳቦች አሉ፡፡
ዋና ዋናዎቹን እንደሚከተለው አስቀምጠናቸዋል፡፡
-መልእክቱ የተጻፈው አስቀድሞ አይሁድ ለነበሩ ከክርስትና መነሣት በፊት በተለያየ ሀገር ተበትነው ላሉ አይሁድ
ነው፡፡ እግዚአብሔር የአይሁድን መበተን ለክርስትና መሰበክና መስፋፋት ተጠቅሞበታል፡፡
ከእነዚህ አይሁድ መካከል በበዓለ ኀምሳ በኢየሩሳሌም የነበሩ ብዙዎች ወደ ክርስትና ተመልሰዋል፡፡ አስቀድሞ አይሁድ
የነበሩ በክርስቶስም ያመኑ ወገኖች ከአይሁድ ወንድሞቻቸው ብዙ መከራ ደርሶባቸዋል፡፡ ይኸውም አይሁድ በክርስቶስ
ባለማመናቸው ምክንያት ነው፡፡
አንዳንድ ወገኖች ደግሞ 12 ቱ ነገዶች መጠቀሳቸው ከአይሁድ የነበሩ ናቸው ለማለት አይደለም ይልቁንም ይህ
የሚያመለክተው ቤተ-ክርስቲያንን ነው ይላሉ፡፡ ቤተ-ክርስቲያን አማኞቿ ሰማያውያንም ይሁኑ ምድራውያን፤ መንፈሳዊ
የሆኑ አካላት ያሉባት ናት፡፡ እሥራኤል የሚለው ቃልም ለእሥራኤል ዘሥጋ የተሰጠ ሳይሆን ለእሥራኤል ዘነፍስ ነው፡፡
ስለዚህ አይሁድ አዲሲቱ እሥራኤል መሆናቸውን ማስረገጥ ከፈለጉ በጌታችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ማመን
ነበረባቸው፡፡ ምክንያቱም አዲሲቱ እሥራኤል በአዲስ ኪዳን በመድኃኒታችን ያመኑት ወገኖችን የያዘች የቅድስት ቤተ-
ክርስቲያን ጉባኤ ናትና በማለት ይናገራሉ፡፡
የመልእክቱ አላማ
44
ከጌታችን ትንሣኤ በኋላ ግን በጌችን በኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹም የሚያምን ሆኗል፡፡ በሐዋርያት ሥራ ላይም እንዲ ተብሎ ትጽፏል፡- “እነዚህ ሁሉ ከሴቶችና ከኢየሱስ
እናት ከማርያም ከወንድሞቹም ጋር በአንድ ልብ ሆነው ለጸሎት ይተጉ ነበር፡፡” ሐዋ. 1-14፡፡
45
ስንክሳር፤ ሐምሌ 18
ቊጥሩ ከመጽሐፍ ቅዱስ የቀኖና መጽሐፍት ለመቆጠሩ ከሚያረጋግጡል ማስረጃዎች መካከል አንዱ በ 2 ተኛው
መቶ ክፍለ ዘመን ኦሪገን የቅዱስ ያዕቆብ መልእክት በማለት መጥቀሱ፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ ጸሐፊው ቅዱስ ያዕቆብ
እንደሆነ ከሚያረጋግጡልን ነገሮች መካከል፡-
የመልእክቱ አከፋፈል
የመልእክቱ ጸሐፊ ቅዱስ ይሁዳ ሲሆን የቅዱስ ያዕቆብ ወንድም ነው፡፡ ይህ ያዕቆብ የኢየሩሳሌም ኤጲስ ቆጶስ የነበረና የያዕቆብ መልእክትን የጻፈልን
ነው፡፡ የይሁዳ የጌታ ወንድም ተብሏል፡፡ የተባለበትም ምክንያት የእመቤታችን ጠባቂ የሆነው ቅዱስ ዮሴፍ ከሟች ሚስቱ የወለደው ስለሆነና እመቤታችን
ከጌታ ጋር ስላሳደገችው ነው፡፡ ይሁዳ መጀመሪያበጌታ አያምንም ነበር (ዮሐ 7፡3-5)፡፡ ነገር ግን ከጌታችን ትንሣኤ በኋላ የክርስቶስ ተከታይ ሆኗል፡፡ (ሰኔ
25 ስንክሳርን ተመለከት)
የተጻፈላቸው ሰዎች
በመልእክቱ መጀመሪያ ላይ ተቀባዮቹ ‹‹በእግዚአብሔር አብ ተወደው በኢየሱስ ክርስቶስም ተጠብቀው ለተጠሩ›› ስለሚል በየትኛውም ቦታ
ለሚገኙ ክርስቲያኖች እንዲያነቡአት የተጻፈች አጠቃላይ መልእክት ናት፡፡
የይሁዳ መልእክት የተጻፈበት የት እንደሆነ የተመዘገበ ነገር የለም፡፡ የተጻፈበት ዘመንም የሁለተኛይቱ ጴጥሮስ መልእክት ከተጻፈች በኋላ ብዚም
46
ሳይቆይ እንደሆነ ብዙ ሊቃውንት ያስረዳሉ፡፡ ስለዚህም መልእክቱ በ 68 ዓ.ም ገደማ ተጽፋለች፡፡
የመልእክቱ ዓላማ
ሐሰተኞች መምህራን እየበዙ መሄዳቸውን፣ ስለዚህም ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ስለተሰጠ ሃይማኖት እንዲጋደሉ ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የእነዚህ
ሐሰት መምህራን መገለጫዎች በናገር ከእነርሱ እንዲጠበቁ ነው፡፡
የመልእክቱ አከፋፈል
46
ይህም የተባለበት ምክንያት ቅዱስ ይሁዳ ሲጽፍ ከሁለተኛው የጴጥሮስ መልእክት ይጠቅሳልና ነው፡፡ (ይሁ 1፡18 እና 2 ኛ ጴጥ 3፡21)
ተ. የመጽሐፉ ስም መሪ ምልክት
ቁ
የመሪ ምልክቱ ትርጉም አንቀጽ
1 ትእዛዝ ረስጠብ ‹‹ረስ››- ሩሱል ከሚለው ዐረብኛ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም 72
ሐዋርያት ማለት ነው፡፡
‹‹ጠ››- የቅዱስ ቀሌምንጦስን ስም በማሳጠር የመጣ ነው፡፡
አንድም ተጥላሳት የሚለውን የዐረብኛ ቃል በማሳጠር
የተወሰደ ሲሆን ትርጉሙም ቀኖናተ ትእዛዛት ማለት ነው፡፡
‹‹አ››- በግብጻውያን የአኃዝ (ቊጥር) የአቆጣጠር ሥርዓት
አንደኛ፣ ቀዳማዊ ማለት ነው፡፡
2 ግጽው ረስጠጅ ‹‹ረስጠ›› የሚለው ከላይ ተገልጧል፤ ‹‹ጅ›› ደግሞ በግብጻውያን 57
የአኃዝ አቆጣጠር ‹‹ሦስተኛ›› ማለት ነው፡፡
3 አብጥሊስ ረስጠብ ‹‹ብ›› በግብጻውያን የአኃዝ አቆጣጠር ‹‹ሁለተኛ›› ማለት ነው፡፡ 82
4 ሥርዓተ ጽዮን ዓይን ‹‹ዓ››- የሚለው ቃል ከጽርሕ ‹‹ይን›› ደግሞ ከጽዮን ከጽርሐ 30
ጽዮን ሥርዓተ ጽዮን (ዓይን) እንደተገኘ ይነገራል፡፡ በሌላም
በኩል ዓይን ሐዋርያት ከተሰበሰቡበት ቦታ የጽርሐ ጽዮን ሰገነት
የመጀመሪያው ፊደል ነው ይባላል፡፡
5 መጽሐፈ ኪዳን ቀዳማዊ -/…. ኪዳን 59
ቀደም ባሉት ክፍሎች እንደተማርነው ኪዳን ማለት በተለያዩ ወገኖች መካከል የሚደረግ ውል፣
ስምምነትና መሐላ እንደሆነ ተገንዝበናል፡፡ እግዚአብሔር አምላክ የሰውን ልጅ ከፈጠረው በኋላ አስቀድሞ
ሕግ በመስጠት ኋላም ምንም እንኳን ሕጉን ቢያፈርስ የሰውን ኃጢአትና በደል ሳይመለከት እንደ ቸርነቱ
ብዛት እንደገና ውሉን በማደስ ለእኛ ካለው ፍቅር የተነሣ መሐላ እንደሚምልልን፣ ቃል እንደሚገባልን፣
በተለያየ ዘመንም የተለያዩ ቃልኪዳን እንደሰጠን ተመልክተናል፡፡
ነገር ግን በዘመናችን አንዳንድ መናፍቃን ቅዱሳት መጻሕፍት እርስ በእርስ ይጣላሉ፣ ይጣረሳሉ
በማለት ያላዋቂ ሲናገሩ ይደመጣሉ፤ ይህ ችግር ከምን እንደሚመጣ ራሱ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ
ክርስቶስ በወንጌል ‹‹መጻሕፍትንና የእግዚአብሔርን ኃይል ባለማወቃችሁ ትስታላችሁ›› በማለት
አስረድቷል፡፡
ቅድስት ቤተክርስቲያናችንም መጻሕፍትን ባለማወቃቸው እንደሚስቱ እየተናገረች ትክክለኛውን
ርቱዕ የሆነውን መንገድ በማሳየት ምዕመኗን በተገቢው መንገድ ታስተምራለች፡፡ በመሆኑም ከዚህ በመቀጠል
እንደ ቤተክርስቲያናችን አስተምህሮ ቅዱሳት መጻሕፍት እርስ በእርሳቸው የማይጣሉና የማይጣረሱ
ይልቁንም ተወራራሽና ተዛማጅ መሆናቸውን እንመለከታለን፡፡
ከላይ የተጠቀሱት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች ገጸ ንባባቸው የተጣላ ቢመስልም ዓይነ ልቡናውን
እግዚአብሔር መንፈስቅዱስ ያበራለት ሰው ትርጉማቸው አንድ እንደሆነ በእርግጠኝነት ይረዳል፡፡
የመጀመሪያውን ጥቅስ ስንመለከት ሁለቱም የብሉይ ኪዳን ጥቅሶች የሚሳማሙበት ምስጢር ወይም ቁም
ነገር እግዚአብሔር አይጸጸትም በሚለው ነው፡፡ ነገር ግን ለእኛ በሚገባን መንገድ የሰዎችን ኃጢአትና የበደል
ክብደት መጠኑ ከልክ ያለፈ መሆኑንና እግዚአብሔር የሚጸጸት አምላክ ቢሆን ኖሮ ሥራችን የሚያጸጽት
መሆኑን ለማሳየት ሲል ‹‹ተጸጸተ›› ብሏል፤ እንጂ አምላካችን እግዚአብሔር በባሕርይ የነበረውን፣ ያለውን፣
ወደ ፊት የሚሆነውን የሚያውቅ ስለሆነ በሥራው አይጸጸትም፡፡
ወደ ሁለተኛውም ስንመጣ በአንድ በኩል ዕጣንን በንጽጽር አቅርቦ ‹‹ጸሎቴን እንደ ዕጣን
ተቀበለልኝ›› በሌላም በኩል ‹‹ዕጣናችሁ በእኔ ፊት አጸያፊ ነው›› ሲል ተናግሯል፡፡ የዚህ ምስጢሩና ችግሩ
ከዕጣኑ ንጽሕናና ርኩሰት ጋር የተያያዘ ሳይሆን ከአቅራቢዎቹ ሕይወት ጋር የተገናኘ ነው፡፡ ችግሩ የዕጣኑ ሆኖ
ቢሆን ኖሮ ጸሎቴን እንደ ዕጣን ተቀበለልኝ ብሎ ነቢዩ ባልጸለየም ነበር፡፡ ሰብአ ሰገልም ከአመኃዎቻቸው
መካካል ዕጣን ይዘው ወደ አምላካቸው ባልቀረቡ ነበር፡፡ ስለዚህ የአድራጊውን ሕይወት ከተደራጊው፣
መሥዋዕቱን ከመሥዋዕት አቅራቢው ሕይወት ለይቶ ማየት እንጂ በጭፍኑ መሥዋዕቱንም መሥዋዕት
አቅራቢውንም ከተነገረለት የመልእክቱ ይዘት ውጪ መተርጎም ተገቢ አይደለም፡፡
እንደዚሁም ሦስተኛው ላይ የተጠቀሱት ኃይለ ቃሎች በትርጓሜ ሲፈቱ የመጀመሪያው በዚህ ዓለም
ሎሌ ሆኖ ለሰው ሲገዙ ከመኖር በገዳም ውስጥ ለእግዚአብሔር በመገዛት ብዙ ትርፍ ማትረፍ እንደሚችል
እንደቀደሙት ምንባባት ሁሉ በዚህ ክፍል ያሉት የብሉይና የሐዲስ ኪዳን ጥቅሶች በደፈናው
ስንመለከታቸው ልዩነት ያላቸው ይመስላል፡፡ ነገር ግን በምስጢረ እግዚአብሔር አንድ ናቸው፡፡
የመጀመሪያውን ብንመለከት ዘመነ ብለይ ዕውቀት ያልሰፋበት፣ ኃጢአት የበዛበት ዘመን በመሆኑ
ሕዝቡ ሊሰማው የሚገባው ስም አንድ እግዚአብሔር የሚል መሆን ነበረበት፤ ምክንያቱም የብዙ ጣዖታት
አምልኮዎችን ለመከላከል እና የእግዚአብሔር አንድነትና ሦስትነት ስም ለእስራኤላውያን የመገለጫ ጊዜው
ስላልነበረ (ገና ስላልጸኑ) ‹‹አምላክህ እግዚአብሔር አንድ ነው›› በሚል ተቀምጧል፡፡
ወደ ዘመነ ሐዲስ ስንመጣ ደግሞ አምልኮ ጣዖታት የጠፋበት፣ ስመ እግዚአብሔር በአንድነትና
በሦስትነት በግልጥ የታየበት፣ ለሰዎች የታወቀበትና የተገለጠበት ዘመን በመሆኑ አንድ እግዚአብሔር
የሚለው ምስጢር ሳይፋለስ፣ ሳይጨመርና ሳይከለስ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ በሚለው ተገልጧል፡፡
በመሆኑም እግዚአብሔር የሚለው ስም ቀድሞም አሁንም ወደፊትም አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ አንድ
እግዚአብሔር ተብሎ ይታመናል፡፡ /ዮሐ 1፡1/
ሁለተኛው ጋር ስንመጣ ‹‹ሰማይ ዙፋኔ ፣ ምድር የእግሬ መረገጫ ናት፣ ምን አይነት ቤት
ትሠሩልኛላችሁ›› ብሉ የተናገረ እግዚአብሔር በሐዲስ ኪዳን በመዋዕለ ሥጋዌው ‹‹ቤቴ የጸሎት ቤት
ትባላለች፣ እናንተ ግን የሽፍቶች ቤት አደረጋችኋት›› እያለ ቤተ መቅደሱን ሲያጸዳና ሲባርክ ፈቅዶም
ሲቀበል እናገኛለን፡፡ ነቢዩ ኢሳይያስ በመለኮታዊ ባሕርዩ የማይጠቀለል፣ የማይወሰን፣ የማይገደብ መሆኑን
ሲያስተምር፤ ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ ደግሞ ምእመናን ተሰባስበው ቃለ እግዚአብሔርን የሚማማሩበት
ቅዱስ ሥጋውና ክቡር ደሙ የሚፈተትበት የሚቀዳበት እርሱም በረድኤት የሚገኝበት ቤተመቅደስ
እንደሚያስፈልጋቸው ያስተምራል፡፡ በመሆኑም የባሕርይ መለኮቱን ርቀትና ጥልቀት እየተረዳን ነገር ግን
ስሙን የምንቀድስበትና የምንጠራበት የተለየና የተቀደሰ ቦታ እንደሚያሰፈልግ መገንዘብ ያሻል፡፡
3. የሐዲሳት መጻሕፍት እርስ በእርስ የማይጣሉ ስለመሆናቸው
ሐዲስ ሐዲስ
እኔና አብ አንድ ነን፡፡ ዮሐ 10፣ 30 ከእኔ አብ ይበልጣል ዮሐ 14፣28
ቃልም እግዚአብሔር ነበር፡፡ (ዮሐ 1፡1) የሐዲስ ኪዳን መካካለኛ ወደሚሆን ወደ ኢየሱስ
ክርስቶስ (ዕብ 12፡24)
እርሱ በእግዚአብሔር መልክ ሲኖር ሳለ ከእግዚአብሔር
ከእኔ ጋር የነበሩትም ብርሃኑን አይተው ደነገጡ ከእርሱም ጋር የነበሩት ሰዎች ድምፅ እየሰሙ
የሚናገረኝን አልሰሙም (ሐዋ 22፡9-7) ማንንም ሳያዩ ተደንቀው ቆሙ፡፡ ሐዋ 9፡7
በመጀመሪያው የወንጌል ክፍል ‹‹እኔና አብ አንድ ነን›› ሲል በመለኮት፣ በአገዛዝ፣ በሥልጣን፣ ይህን
ዓለም በመፍጠር በመመገብ በማሳለፍ በእግዚአብሔርነት አንድ መሆናቸውን ያሳያል፡፡ ‹‹አብ ከእኔ
ይበልጣል›› ሲል ደግሞ የአብና የመንፈስ ቅዱስ ቃል ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
በምስጢረ ሥጋዌው ሥጋን በመዋሐዱ በመራቡ፣ በመጠማቱ፣ በመሞቱ፣ በመነሣቱ አብን ከእኔ ይበልጣል
ብሏል፤ ምክንያቱም ወልድ በምስጢረ ሥጋዌው የተቀበላቸው የማዳን ሥራዎች እግዚአብሔር አብ
በመለኮታዊ ባሕርዩ ሊቀበላቸው አይችልምና አብ ከእኔ ይበልጣል አለ እንጂ ክብር ይግባውና ጌታችን
በመለኮት ከአብ ያነሰ ሆኖ አይደለም፤ ስለዚህ በመለኮት አንድ ሲሆን በምስጢረ ሥጋዌ ወልድ በተለየ አካሉ
በለበሰው (በተዋሐደው) ሥጋ ‹‹ከመላዕክት እንኳ ጥቂት አሳነስከው›› እንደተባለ ከተዋረደ አብ ከእኔ
ይበልጣል ቢል የንባብ እንጂ የምስጢር ተፋልሶ የለውም፡፡
በሌላ ምስጢር ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ‹‹ቃልም እግዚአብሔር ነበረ›› ብሎ ጽፏል፡፡ ሐዋርያው
ቅዱስ ጳውሎስ ደግሞ እርሱ በእግዚአብሔር መልክ ሲኖር ሳለ ከእግዚአብሔር ጋር መስተካከልን መቀማት
እንደሚገባ ነገር አልቆጠረውም ካለ በኋላ በሌላው መጽሐፉ የሐዲስ ኪዳን መካከለኛ ጽፏል፡፡ ይህም
ትርጓሜው ከላይ ከተገለጠው ጋር አንድ ነው፡፡ ምክንያቱም በመጀመሪያ እግዚአብሔር ነበረ ሲል መለኮታዊ
ባሕሪውን፣ የሐዲስ ኪዳን መካከለኛ ሲል ደግሞ ፍጽም ሰው ፍጽም አምላክ ከማለቱ በስተቀር
በእግዚአብሔር እና በሰው መካከል ያለ ትንሽ (ዝቅተኛ) አምላክ ነው ማለት አይደለም፤ ይህ ፍፁም የተሳሳተ
አስተሳሰብና ክህደት ነው፡፡ ክብር ይግባውና አምላካችን እንደ አምላክነቱ ሥጋዌን እነደ ምሥጢረ ሥጋዌ
አምኖ መቀበል ያስፈልጋል፡፡
ሦስተኛው ጥቅስ ጋር ስንመጣ እግዚአብሔር ወልድ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ
ክርስቶስ የማዳን ሥራውን ፈጽሞ ከሐዋርያት ሊለይ ሲል የነገራቸው ምስጢር ‹‹ከእንግዲህ ስለ እናንተ
አብን የምለምን አይደለሁም›› የሚል ሲሆን ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ደግሞ ‹‹ስለ እኛ ዘወትር
ሊያማልድ ይኖራ›› ብሎ ጽፏል፤ ጌታችን ለሐዋርያት የገለጠው በነቢያት የተናገረው፣ በሱባኤ የተቆጠረው
የማዳን ሥራ የተፈጸመ መሆኑን ነው፤ ሐዋርያው የገለጠው ደግሞ ይህ የድህነት ሥራ በሌላ ዘመን በሌላ
ኪዳን የማይተካና የማይሻሻል ለዘለዓለም የድኅነት በር የመንግሥተ ሰማያት መንገድ ሆኖ እስከ ዕለተ
ምጽአት ድረስ እንደሚቀጥልና እንደ ኦሪት ሥርዓት የማይሻሻል የማይለወጥ ኪዳን መሆኑን አረጋግጦ ጻፈልን
እንጂ ክብር ይግባውና ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አማላጅ ነው ለማለት ተፈልጎ
አይደለም፡፡ ይህንን በምሳሌ ለመረዳት አንድ ካህን በቅዳሴ ሰዓት ቀዳሲ ዲያቆን ጠፍቶ ለዚያን ዕለት እንደ
ቢያገለግሉ ከቅዳሴ ሲወጡ ካህንነታቸው ተሽሮ ዲያቆን እገሌ አይባሉም፡፡ ጌታችንም ሰው ሁሉ በበደለ እና
ሁሉም በኃጢአት ተይዞ በነበረበት ጊዜ ሰው ሆኖ መጥቶ በሥጋው በፈፀመው የቤዛነት ሥራ ከራሱ ጋር
አስታርቆናል፤ ይህ ማለት ግን ክብር ይግባውና ጌታችን መድኃኒታቸን ኢየሱስ ክርስቶስ ሁልጊዜ አማላጅ ነው
ማለት አይደለም፡፡ እርሱም ቢሆን በገዛ ቃሉ ‹‹ተፈፀመ›› በማለት በመስቀል ተሰቅሎ የቤዛነቱን ሥራ
አስታውቆናል፡፡ ‹‹እኔም ስለ እናንተ አብን እንድለምን የምላችሁ አይደለሁም›› በማለትም አስረግጦ
ገልጦልናል፡፡ ዮሐ 16፡26
ሰዱቃውያን ግን ነፍሳችን ከሥጋችን ከወጣች በኋላ ትንሣኤ ሙታን የለም የሚሉ ሰዱቃውያን…ማቴ
ከሞቱ ሰዎች ጋር አንነሣም ለሥጋና ለነፍስም ከሞቱ
ከላይ በተዘረዘሩት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች የብሉይ ኪዳንንና የሐዲስ ኪዳንን አንድነት፣ አንድ ዓላማ
ያላቸው መሆኑን፣ የማይለወጡ፣ የማይሻሩ የእግዚአብሔር ቃል መሆናቸውን ተመልክተናል፤ በመሆኑም
ቅዱስ ሉቃስ ‹‹ከኦሪትና ከነቢያት አንዲት ቃል ከምትወድቅ ሰማይና ምድር ቢያልፍ ይቀላል›› ሉቃ 16፡17
እንዳለ ተገንዝበን እግዚአብሔር በመንፈስ ቅዱስ ምስጢር ገላጭነት ተመርተን ቅዱሳት መጻሕፍትን
አንብበን ሕይወት እንድናገኝባቸው እግዚአብሔር አምላካችን ይርዳን፡፡