You are on page 1of 10

“እውነተኛው የዓለም ብርሃን”

ብርሃን÷ ብርሃን የጨለማ ተቃራኒ ነው፤ ለዚያም ነው ብርሃን የሌለበት ጨለማ ተብሎ የሚጠራው።
ጨለማ መኖሩ የሚታወቀው ብርሃን ሳይኖር ሲቀር ነው። ብርሃን በሁለት መልኩ ልንገልጸው
እንችላለን÷ ውጫዊ(ዓለማዊ) እና መንፈሳዊ(ውስጣዊ)፤ የመጀመርያው ከተፈጥሮአዊው(ፀሐይ) ወይም
ከሰው ሰራሽ የሚገኝ ሲሆን ያንን ብርሃን ወደ ዓይናችን ሲያንጸባርቅ ነገሮችን ማየት እንችላለን፤
ዓይናችን ያ ብርሃን ካላገኘ ግን ጨለማ ነው ምንም ማየት አይችልም። ሁለተኛው ግን ከመጀመርያው
በእጅጉ የተለየ የረቀቀ ብርሃን ነው÷ መንፈሳዊ ብርሃን፤ ውስጣዊ ብርሃን።

እግዚአብሔር መንፈስም ብርሃንም ነው(ዮሐ 4:24፤ 1 ዮሐ 1:5) እግዚአብሔር በአማኞቹ ልብም


ያበራል፤ እንዲህ ስንል ግን በመካከላቸው የሚጋርድ ነገር(ኃጢአት) ከሌለ ነው። ምክንያቱም አምላክ
ኃጢአትን ይጸየፋልና።

እንደ ቤተ- ክርስቲያናችን ሥርዓትና ቀኖና ከገና በፊት ያሉት ሦስት ሰናብት ማለትም ስብከት፣ ብርሃን፣
ኖላዊ አንድላይ ዘመነ ስብከት ተብለው ይጠራሉ፡፡ የዘመነ ስብከት ሁለተኛ እሁድ ብርሃን
ይባላል።ሌሊቱን ከቅዱስ ያሬድ መዝሙር «አቅዲሙ ነገረ በኦሪት» በኦሪት መናገርን አስቀደመ
ብለው በመጀመር በሊቃውንቱ ሲዘመር በዜማ አምላክን ሲወደስና ሲመሰገን ካደረ በኋላ ጧት ደግሞ
በሥርዓተ ቅዳሴ (ሮሜ.13፥11-ፍጻሜ)፣ (1 ዮሐ.1፥1-ፍጻሜ)፣ (የሐዋ.26፥12-19) በዲያቆናት እና
በካህናት ይነበባሉ። (መዝ.42፥3) በዲያቆኑ በዜማ ይቀርባል፡፡ (ዮሐ.1፥1-19) በካህኑ ይነበባል እንዲሁም
የሊቁ የአትናቴዎስ የምስጋና ጸሎት ይደርሳል ፡፡

እነዚህም ሁሉ ስለ ብርሃኑ ሰፋ ያለ መልእክት ያላቸው ከብሉያትና ከሐዲሳት እንዲሁም ከሊቃውንቱ


መጻሕፍት የተውጣጡ ብርሃንነቱን የሚመሰክሩ ናቸው ፡፡
ይህ ሳምንት ብርሃን ተብሎ መጠራቱ ክርስቶስ ከመምጣቱ በፊት የነበሩ ሰዎች በመንፈሳዊ ጨለማ
ተውጠው ይህንን ጨለማ የሚያስወግድ መንፈሳዊ ብርሃን በመሻት አምላክን ሲማጸኑት እንደነበሩ
ለማዘከር፤ በአሁን ሰዓት ያሉ አማንያንም ብርሃን መጥቶ ጨለማን በማስወገድ ስለታደጋቸው
ለማመስገን ላላመኑትና ላላወቁት ደግሞ ‹‹እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ›› እንዳለው በዓለም ውስጥ
ብርሃን ሆኖው ብርሃኑን እያመሰገኑ ያ ብርሃን መግለጥና ለዓለም ሁሉ መስበክ ነው። ቅዱሳን ነቢያት
ሰው ሁሉ በጨለማ ውስጥ መሆኑን (መኖሩን) አውቀው ተረድተው ይህንን ጨለማ ለማስወገድ ደግሞ
ብርሃን እንደሚያስፈልግ በማመን የብርሃን ባለቤት ለሆኖው አምላካችንን ብርሃን እንዲልክላቸው
የዘወትር ልመናቸውና ጸሎታቸው እንደነበረና የነፍሳቸውን ብርሃን ይመጣል ብለው መስበካቸውን
ከጽሑፋቸው አይተን እንረዳለን፤ ለሰው ልጅ ድኅነት ከጠበቁባቸው እና ከገለጡባቸው መንገዶችም
አንዱ ይህንን ብርሃን እንዲላክላቸው ነበር፡፡

ክርስቶስ ከመምጣቱ በፊት በዘመነ ብሉይ÷ ደዌ-ሥጋ፣ ደዌ- ነፍስ የፀናበት፣ ለሰው ሁሉ አስጨናቂ ዘመን
የሆነበት፣ሁሉም ሰው ብርሃን ከሆነው አምላኩ ርቆ በጭንቅ፣ በመከራና በጨለማ ውስጥ በመኖሩ ተስፋ
ቢስ ሆኖ ስለነበር ዘመኑን « ዘመነ-ጨለማ» ብለው በመግለጥ ይህንን ጨለማ አስወግዶ ወደ ብርሃን
የሚቀይር በጨለማ የሚያበራ ብርሃን እንዲላክላቸውና ከብርሃን የተገኘ እውነተኛ ብርሃን፤አማናዊ
ብርሃን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲመጣ ዘወትር ሲጸልዩ ነበር፡፡
መዝሙረኛውም ያን ብርሃን መሻቱን እንዲህ ሲል በመዝሙሩ ጸልዮአል÷<ፈኑ ብርሃነከ ወጽድቀከ
እማንቱ ይምርሐኒ ወይሰዳኒ ደብረ መቅደስከ ወውስተ አብያቲከ እግዚኦ> /መዝ. 42.3/ አቤቱ
ብርሃንህንና እውነትህን (ጽድቅህን) ላክ እነርሱ ይምሩኝ ወደ መቅደስህ ተራራና ወደ ማደሪያህ
ይወሰዱኝ፣ብርሃን የሆነ፣ጽድቅ የሆነ፣ እውነት የሆነውን ቅዱስ ልጅህን (ወልድን) ክንድህን ልከህ ጨለማ
ሆኖ የጋረደንና ካንተ የለየን ኃጢአታችን አስወግዶ ከአንተ አስታርቆ ወደ አንተ ይውሰደን ሲል ነው።
የዚህ ሁሉ ትንቢትና ጸሎት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአባቱ ተልኮና በፈቃዱ ወደዚህ
ዓለም በመምጣት ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ በተዋህዶ ፍጹም አምላክና ሰው
ሆኖ በዓለም ሲያስተምር «እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ» /ዮሐ. 8.12/ በማለት ብርሃንነቱን አረጋግጧል፤
በመቀጠልም እርሱን የሚከተል ሁሉም ያንን ብርሃን እንደሚያገኝ እንዲህ በማለት ተናግሯል‹‹ እኔን
የሚከተል ሁሉ የሕይወት ብርሃን ያገኛል በጨለማም አይመላለስም››(ዮሐ 8:12)። ኢየሱስ ክርስቶስ
የሰው ሁሉ ሕይወት የሆነች ብርሃን ገልጧል፤ ብርሃን መሆኑን ደቀመዛሙርቱም ስለ ብርሃንነቱ እንዲህ
በማለት መስከሯል «ሕይወት በእርሱ ነበረ፣ ሕይወትም የሰው ብርሃን ነበረ፤ ብርሃንም በጨለማ
ያበራል፤ ጨለማም አላሸነፈውም» /ዮሐ. 1.4-5/።

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጨለማ ያላሸነፈው ዘወትር የሚያበራ እውነተኛ ብርሃን ነው።
ሊቃውንትም ‹ዘዘልፈ ያበርህ፣ብርሃን ዘበአማን› ሁሉ ጊዜ የሚያበራ እውነተኛ ብርሃን ‹ዘእንተ ውስጥ
አይነነ አብራህከ ወጽልመተ ሐሊናነ፣ብርሃነ_ፍጹማን ወልደ አምላክ ሕያው› የሕሊናችንን ጽልመት
ያበራ፣ ዓይነ ልቡናችንን የገለጠው፣ የሕያው አምላክ ልጅ የፍጹማን ብርሃን ብለውታል። ዮሐንስም
ስለዚህ ብርሃን ሲመሰክር ለሰው ሁሉ የሚያበራ እውነተኛ ብርሃን ወደ ዓለም መጣ ሲል፣ ቅዱስ
ጴጥሮስም ይህ ብርሃን በልቡናችን ውስጥ የሚያበራ ብርሃን ነው ብሎታል(1 ኛጴጥ 1:19)።

ቅዱስ ጳውሎስም መጀመርያ በብርሃን የነበረ እንኳ ቢመስለውም ያ ብርሃን ሳይበራለት በጨለማ ሆኖ
ይህንን ብርሃን ለማጥፋት የብርሃን ልጆቸና ብርሃን እያሳደደ ሳለ ጌታችንም ትጋቱንና ቅንነቱን
በመመልከት ጌታችን በሚያንፀባርቅ ብርሃን አምሳል እንደተገለጠበት ተናግሯል፡፡ « በመንገድ ሳለሁ እኩለ
ቀን ሲሆን በዙሪያዬና ከኔ ጋር በሄዱት ዙሪያ ከፀሐይ ብሩህነት የበለጠ ብርሃን ከሰማይ ሲበራ አየሁ …
አንተ የምታሳድደኝ የናዝሬቱ ኢየሱስ ነኝ ” አለኝ(የሐዋ 26:13_15) ቅዱስ ጳውሎስ ያ ብርሃን
ከበራለት በኋላ ጨለማ ከእርሱ ውስጥ ስፍራ ስላላገኘ ብርሃንነቱን ለማወጅ ተሯሩጧል፤ ሌሎችም
ሲያሰተምር እርሱንም ራሱ ጨምሮ እንደህ ሲል ተናግሯል ‹‹ቀድሞ ጨለማ ነበራችሁና፥ አሁን ግን
በጌታ ብርሃን ናችሁ፤ የብርሃኑ ፍሬ በበጎነትና በጽድቅ በእውነትም ሁሉ ነውና ለጌታ ደስ የሚያሰኘውን
እየመረመራችሁ፥ እንደ ብርሃን ልጆች ተመላለሱ፤ፍሬም ከሌለው ከጨለማ ሥራ ጋር አትተባበሩ፥
ይልቁን ግለጡት እንጂ፥ እነርሱ በስውር ስለሚያደርጉት መናገር እንኳ ነውር ነውና፤ ሁሉ ግን በብርሃን
ሲገለጥ ይታያል፤ የሚታየው ሁሉ ብርሃን ነውና።

ስለዚህ አንተ የምትተኛ ንቃ ከሙታንም ተነሣ ክርስቶስም ያበራልሃል ይላል›› (ኤፌ 5:8-14)። ክርስቶስ
በአህዛብም ብርሃን እንደሆነ ቀድሞዉኑ ተወስኖ ነበር፤ (ኢሳ 49:6)‹…እስከ ምድር ዳር ድረስ መድኃኒት
ትሆን ዘንድ ለአህዛብ ብርሃን አድርጌ ሰጥቼሃለሁ› ይላል። በጨለማ የተጓዘ እንቀፋት ሳይመታው
አይቀርም፣ ክርስቶስ ግን ይህንን ጨለማ በማስወገድ ብርሃን በመሆን ከእንቅፋትም ከመሰናክልም
ሊያድን መጥቷል፤ እንቅፋቱንም ያሳያል። ስለዚህ ከእንቅፋትም ከውድቀትም ለመዳን በዚህ ብርሃን
መራመድ ይገባል። እመኑ በብርሃኑ ወአንሰውስዉ እንዘ ብክሙ ብርሃን እንዳለው ሊቁ፤ በብርሃኑ አምነን
በብርሃን እንመላለስ።

በራሳችን ካልራቅን ጨለማ ካልመረጥን እርሱ ይወደናል ስለ ወደደን ነው ሳያዳላ ስለ ሁሉም ሰው ወደ


ዓለም የመጣ‹ ብርሃን ዘበአማን ዘያበርህ ለኲሉ ሰብእ ለእለ ይነብሩ ውስተ ዓለም በእንተ ፍቅረ ሰብእ
መጻእከ ውስተ ዓለም ወኲሉ ፍጥረት ተፈስሃ በምጽአትከ› ሁሉም ፍጡር የተደሰተብህ፣ ሰውን ወደህ
ወደዚህ ዓለም የመጣህ፣ በዓለም ውስጥ ላለ ሁሉ ሰው የሚያበራ እውነተኛ ብርሃን ነህ ተብሏል። ታድያ
እኛስ በመምጣቱ ደስተኞች ነን? ያለ እርሱስ በጨለማ ውስጥ እንደምንኖር ተገንዝበናል?
በዘመነ ኦሪት ለነበሩ ሰዎች እርሱ ራሱ የፈጠራት ፀሐይ ከእነርሱ አልጠፋችም ነበር አሁንም አለች
እርሷ ለሁሉም ዓለም የፀጋ ስጦታ ናት፤ነገር ግን በመንፈሳዊ ጨለማ ውስጥ ሆኖው ብርሃንህን ላክልን
ሲሉ የነበረ አሁን በግዙፍ ዓይናችን የምናያት የምንመለከታት ፀሐይ የምትሰጠው ብርሃን አጥተው
አይደለም፣ የውስጥን ጨለማ ድንቁርናና ኃጢአትን አስወግዶ ውስጣዊ ሕሊናን በማብራት ያለምንም
እንከን አምላካችንን የምናይበትና የምንከተልበት መንፈሳዊ ዓይናችን ሊያበራ የሚችል አማናዊ ብርሃን
ፈልገው ነው እንጂ፤ አሁንም እኛ የእውራን ዓይንና አእምሮ የሚገላልጠውን አማናዊ ብርሃን
እንጋብዘው፤ እንድያውም እርሱ በበራችን ሆኖ እያንኳኳ ነው እንክፈትለት (ራእ 3:20)፤ እነዚያን ሰዎች
ሲለምኑ ነበር እኛ ደግሞ እየተለመንን ነው፤ አንድ ቀን ጌታችን ሐዋርያትን ሲያነጋግራቸው ብዙዎች
ለማየት፣ ለመስማት፣ ተመኝተው አላዩም አልሰሙምም እናንተ ግን ብፁአን ናችሁ፤ ዓይናችሁም
አይቷል ጆሮአችሁም ሰምተዋል ሲል ዕድለኞች መሆናቸውን መስክሯል።

ዮሐንስም እኛም በዓይናችን አይተናል እንመሰክርማለን ብሏል። ውድ አንባብያን ሆይ! እኛም ሁላችን
በዚህ ብርሃን አምነን በብርሃኑ ከተመላለስን ለእኛ ብሎ ነው የመጣና የዚህ ክብርና ብርሃን ባለቤቶች
ነን። በዚህ ዓለም የምናገኘው የፀሐይ ብርሃን ከሁሉም ዓለም በጋራ ነው የምንጠቀመው ውስጣዊ
ማንነታችንም አይደለም አይገልጽምም፤ የሚያስደንቀው ግን የእግዚአብሔር ቸርንት ነው፤ ምክንያቱም
ያ ብርሃን ለሚያምኑት ሆነ ለማያምኑት፤ ለጠላቶቹም ሆነ ለወዳጆቹም በእኩል መስጠቱ ነው፤ ሙሉ
በሙሉ ባይሆንም ቀኑን በማፈራረቅ ለዓለም ስታበራ የቆየች ፀሐይ እንደ ሌሎቹ ፍጡራን አንድ ቀን
ማለፍዋ ስለማይቀር የምትሰጠው ብርሃን የተፈራረቀና ውጫዊ ብርሃን ቢሆንም እንኳ እሱም
ቀጣይነት እንደሌለው የተረጋገጠ ነው፡፡

ስለዚህ ብርሃን ከሚጠሉና ጨለማን ከመረጡ ሰዎች መለየት አለብን፤ ከጨለማው ዓለምና አስተሳሰብ
ወጥተን በፈጠራት ፀሐይ ዓለምን ያበራ እርሱ ራሱ ብርሃን በመሆን ደግሞ ውጫዊውንና ውሰጣዊውን
የሚያበራ የሥጋና የነፍስ ብርሃን የሆነ የሕይወት ብርሃን እንያዝ እንከተል <የመዳን ቀን አሁን ነው>
እንዳለው ሐዋርያው ከዓለማዊ አስተሳሰብ ወጥተን ወደመንፈሳዊና ዘላለማዊ ሕይወት ግዜው ሳይመሽ
አሁን ተሎ ብለን እንግባ፡፡

ሌላ ጊዜ አንጠብቅ በሆነ አጋጠሚ ሳንዘጋጅ ከዚህ ዓለም ከተለየን የኛ ጊዜ እሱነውና በጸጸት


ሰለማይመለስ፤ ከሁሉም ነገር አስቀድማችሁ መንግስቱንና ጽድቁን ፈልጉ እንዳለን ጌታችን ቃሉን
አክብረን ተዘጋጅተን እንጠብቀው። ይህንን ማድረጋችን ከመብላት፣ ከመልበስ፣ ከመስራትና ከትዳር
አይከለክለንም፤ ከኃጢአትና ሥርዓት አልባ ከሆነ ዓለማዊ ምኞት እንጂ። ቅዱስ ጳውሎስም እንዲህ
ብሎ እየመከረን ነው<ከእንቅልፍ የምትነሡበት ሰዓት አሁን እንደ ደረሰ ዘመኑን እወቁ፤ ካመንንበት ጊዜ
ይልቅ መዳናችን ዛሬ ወደ እኛ ቀርቦአልና። ሌሊቱ አልፎአል፥ ቀኑም ቀርቦአል። እንግዲህ የጨለማውን
ሥራ አውጥተን የብርሃንን ጋሻ ጦር እንልበስ። በቀን እንደምንሆን በአገባብ እንመላለስ፤ በዘፈንና በስካር
አይሁን፥ በዝሙትና በመዳራት አይሁን፥ በክርክርና በቅናት አይሁን፤ ነገር ግን ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን
ልበሱት፤ ምኞቱንም እንዲፈጽም ለሥጋ አታስቡ>። (ሮሜ 13:11-14)። በእርሱ ዘንድ ጨለማ የለም
ሁሌም ብርሃን ነው፡፡ ‹‹ከእንግዲህም ሌሊት አይሆንም ጌታ አምላክም በእነርሱ ላይ ያበራላቸዋልና
የመብራት ብርሃንና የፀሐይ ብርሃን አያስፈልጋቸውም፤ ለዘላለምም እስከ ዘላለም ይነግሳሉ››(ራእ 22፡
5)፡፡ ያ ብርሃንም ራሱ መድኃኔዓለም ነው፤ «ለከተማይቱም የእግዚአብሔር ክብር ስለሚያበራላት
መብራትዋም በጉ ስለ ሆነ ፀሐይ ወይም ጨረቃ እንዲያበሩላት አያስፈልጋትም»(ራእ 21:13)፡፡

ውድ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች በእውነት ይህንን ክብርና ብርሃን ሊያመልጠን አይገባም፤ በዚህ ብርሃን
ከብርሃን አባትና ብርሃን ከሆነው ከጌታችን ከመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቅዱሳኑምጋር ለዘላለም
ለመኖር በብርሃኑ አምነን ከብርሃንና ከብርሃን ልጆች ቅዱሳን ጋር አሁን በትንሳኤ ልቡና በአብ ቀኝ
እንቀመጥ (ቈላ 3:1-3፤ ኤፌ 2:6-7)። በብርሃኑ ልቡናችንና ሁለንተናችንን ያብራ !!!

ወስብሃት ለእግዚአብሔር አሜን!

በመምህር ኪዱ ዜናዊ

ክርስቲያናዊ ህይወት

ክርስትና የሚለው ቃል “XPIETIAVOS” ኽርስቲያኖስ ከሚለው የግሪክ ቃል የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም


የክርስቶስ መሆን ማለት ነው፡፡ ክርስትና ሰዎች በፍቅረ እግዚአብሔር ተስበው፤ ፈጣሪያቸውን
አውቀው፤ እረፍትን ሽተው፤ በህጉና በትእዛዙ ፀንተው፤ ለመኖር ሲሉ ከዓለም ፈቃድ ተለይተው
የሚኖሩበት ህይወት ነው፡፡ ይህንንም ኢየሱስ ይወደው የነበረው ደቀመዝሙር ዮሐንስ “ዓለምን ወይም
በዓለም ያሉትን አትውደዱ በዓለም ያለው ሁሉ እርሱም የስጋ ምኞትና የዓይን አምሮት ስለገንዘብም
መመካት ከዓለም ስለሆነ እንጂ ከአባት ስላልሆነ÷ ማንም ዓለምን ቢወድ የአባት ፍቅር በእርሱ ውስጥ
የለም፡፡

ዓለሙም ምኞቱም ያልፋሉ የእግዚያብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ ግን ለዘለዐለም ይኖራል” (1 ዮሐ 2፡16)


በማለት ክርስቲያን ለመሆን በመጀመሪያ ዓለምን መካድ እንዳለብን ያስተምረናል፡፡ በክርስትና ወድቆ
(ተረግሞ) የነበረው የሰው ዘር እንደ ተነሳ (እንደ ተፈታ)፤ የታመመው እንደ ተፈወሰ፤ የረከሰው እንደ
ተቀደሰ፤ የሞተው እንደተነሳ፤የተሰበረው እንደተጠገነ፤ የሳተው እንደ ተመለሰ ይታመናል፡፡

የክርስትና መስራቹ ራሱ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ነው፡፡ “በዚህችም ዓለት ላይ ቤተክርስቲያኔን


እሰራለሁ፡፡ የገሀነም ደጆችም አይችሏት” (ማቴ 16፡18) በማለት ቤተክርስቲያን ሳይሆን ቤተክርስቲያኔን
የራሱ እንደሆነች በህያው ቃሉ አረጋግጦልናል፡፡

ክርስቲያኖች ክርስቲያን ከመባላቸው አስቀድሞ ምዕመናን (መዝ 100፡7) ፤ ደቀመዛሙርት (ኢሳ 8፡16) ፤
ወንድሞች (ማቴ 8፡10) የመሳሰሉት በመባል ይጠሩ ነበር፤ ነገር ግን ደቀመዛሙርቱ ክርስቲያን ተብለው
ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰየሙት በአንጾኪያ በማርቆስ እናት በማርያም ቤት እንደነበር ቅዱስ መጽሀፍ
ይነግረናል፡፡ (የሐዋ 11፡26)

በምድራችን በሺዎች የሚቆጠሩ ሃይማኖቶች ይገኛሉ፡፡ የሃይማኖታቸውን መስራች ስናጠና ግን ሰዎች


ሆነው እናገኛለን፡፡ ትምህርታቸው ዛሬም በተከታዮቻቸው ይኑር እንጂ እነርሱ ግን በህይወት የሉም፤
የክርስትና ዋና መስራች ግን ትናንት የነበረ ዛሬም ያለ ወደፊትም ዓለምን አሳልፎ የሚኖር ዐልፋና
ዖሜጋ ዘዓአለማዊ በመሆኑ ዛሬም ስራውን አላቆመም ማለት ነው፡፡ ክርስቲያናዊ ህይወት ለመኖር
ክርስቲያኖች የሚከተለውን መተግበር እንዳለብን የህይወት ምንጭ የሆነው መጽሀፍ ቅዱስ
ያስተምረናል፡፡

1. እግዚያብሔርን ማወቅ

መቼም ዓለም አንድ መንደር በሆነችበት ዘመን ስለ እግዚያብሔር ያልሰማ አለ ብሎ ለመናገር


ያስቸግራል፡፡ ይሁን እንጂ ከዕውቀት ብዛት እግዚአብሄርን የካዱ (እግዚአብሔር የለም) ያሉ በርካታ
ሰዎች በምድራችን መኖራቸው ግልጽ ነው፡፡ ይህም ስንፍና እንጂ እውቀት እንዳልሆነ ልበ አምላከ ቅዱስ
ዳዊት ይነግረናል፡፡ “ይበል አብድ በልቡ አልቦ እግዚአብሔር” ሰነፍ በልቡ እግዚአብሔር የለም ይላል
(መዝ 13፡1)፡፡ ፍልስፍና ማለት ጥበብን ማፍቀር ማለት እንጂ እግዚአብሄርን አለማወቅ ወይም መካድ
ማለት አይደለም፡፡ አንድ ልጅ አባቱን አላውቅህም አባቴ አይደለህም ስላለው አባቱ አልወለደውም
ማለት አይደለም እንዳውም ልጁ ሲጠራ አባቱን የካደ ልጅ ተብሎ ይጠራል፡፡

እግዚአብሄርን ማወቅ፡-

ትርጉም ያለው ሕይወት ይሰጣል

በምድራችን ትርጉም ያለው ሕይወት ማለት ምን አልባት የሚመስለን ሀብት፤ ንብረት፤ ስልጣን ፤ ጥሩ
መልበስ፤ ጥሩ መመገብ ፤ ጥሩ ቤት መኖር ሊመስል ይችላል፡፡ ነገር ግን ትርጉም ያው ህይወት መኖር
የሚቻለው እግዚአብሄርን ሲያውቅ ነው፡፡ በዚህ ዘኪዎስ ጥሩ ምሳሌ ይሆናል፡፡ ዘኪዎስ ጌታውን ሳያውቅ
የኖረበት ዘመን ትርጉም አልባ ህይወት ነበር አምላኩን ሲያውቅ ግን “ጌታ ሆይ ካለኝ ሁሉ እኩሌታውን
ለድሆች እሰጣለሁ ማንንም በሃሰት ከስሼ እንደሆንሁ አራት እጥፍ እመልሳለሁ አለው” (ሉቃ 19 ፤9)
በማለት አዲሱ ክርስቲያናዊ ህይወት ምን እንደሚመስል ነግሮናል፡፡

ታሪክን ይቀይራል

ሰዎች እግዚአብሄሔርን ሲያውቁ ዘማዊ የነበረው ድንግል፤ ዘረኛና ወገንተኛ የነበረው ሁሉን በክርስቶስ
አንድ አድርጎ የሚያይ ፍትሃዊ፤ አሳዳጅ የነበረው ስለ ክርስቶስ ተሳደጅ፤ ክፉ የነበረው ደግ፤ ዘፋኝ
የነበረው ዘማሪ፤ ነፍሰ ገዳይ የነበረው የሰውን ህይወት የሚያድን ወዘተ ይሆናል፡፡ለዚህ ቅዱስ ጳውሎስ
ጥሩ አስረጅ ይሆናል፡፡

2. በዕምነት ማደግ

ብዙዎች ክርስቲያን ተብለው ይጠራሉ ጥቂቶች ብቻ በእምነት ውስጥ በጥበብ ይኖራሉ፡፡ “ዕምነት
ተስፋ ስለምናደርገው ነገር የሚያስረግጥ የማናየውንም ነገር የሚያስረዳ ነውና” (ዕብ 11፡1) የሰው ልጅ
በሃይማኖት ካልኖረ ለምኞቱ ገደብ የለውም፡፡ ያለኝ ይበቃኛል አይልም፡፡ አመንዝራ ሲያይ በፍትወት
ስሜት ይቃጠላል፣ የወይን ጠጅ በብርሌ ባማረ መልኩ ባየ ጊዜ መጠጥ ያምረዋል ለዚህ እኮ ጥበበኛው
ጠቢቡ ሰለሞን “ከተማን ከመግዛት ራስን መግዛት ይበልጣል ያለው”

3. በእግዚአብሔር ፍቃድ መኖር

እግዚአብሔር ከእኔ ይልቅ ስለ እኔ ያስባል ብሎ ማመን ነው፡፡ የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ


ለዘለዓለም ይኖራል፡፡ (የሐ 2፡17) የጌታችንም ፈቃድ ሁሉ የእግዚአብሔር እንደሆነ ሲያስተምር “አባት
ሆይ ብትፈቅድ ይህችን ጽዋ ከእኔ ውሰድ ነገር ግን የእኔ ፍቃድ አይሁን የአንተ እንጂ” (ሉቃ 22፡42)
ምክንያቱም ሀዋርያው እንደተናገረው ”ስለ በጎ ፈቃድ መፈለግንም ማድረግንም በእናንተ የሚሰራ
እግዚአብሔር ነውና” እንዲል (ፊሊ 1፡13)

4. እግዚአብሔርን መምሰል

ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህች ዓለም ሶስት ዓመት ከሶስት ወራት
በአገልግሎት ሲቆይ በርካታ ትምህርቶችን ከማስተማሩም በላይ በሕይወቱ አብነት ለመሆን መልካም
ሥራ ካደረገ በኋላ ከመዝ ግበሩ እናንተም እንዲሁ አድርጉ(ዮሐ 13፡14)(ምንም እንኳን መልካምነት
የባህርይው ቢሆንም) በማለት ክርስቲያኖች በሕይወት ዘመናቸው ክርስቶስን መምሰል እንዳለባቸው
መጽሀፍ ይስተምረናል፡፡ሐዋሪያው ቅዱስ ጳውሎስም ይህንን ቃል ”እኔ ክርስቶስን እንደምመስል እኔን
ምሰሉ”(1 ኛቆሮ 11፡1) በማለት ያረጋግጥልናል፡፡በመሆኑም የመንፈስን ፍሬ በማድረግ የስጋን ሥራ
በመተው አምላካችንን መምሰል ይገባናል ማለት ነው፡፡(ገላ 5፡18)ይህንን በማድረግ ቅዱሳን ቅድስናን
ገንዘብ አድርገዋል፡፡“እግዚአብሔር መምሰል ግን ለአሁኑ እና ለሚመጣው ተስፋ ስላለው ለነገር ሁሉ
ይጠቅማል”(2 ጢሞ 4፡8)
5. ፍቅር ሊኖረን ይገባል

በክርስትና መጀመሩያውም መጨረሻውም ፍቅር ነው፡፡ ምክንያቱም “ፍቅር የሌለው እግዚአብሔርን


አያውቅም፡፡እግዚአብሔር ፍቅር ነውና” (1 ዮሐ 4፡8) በመሆኑም ያለ ፍቅር ክርስትና የለም፡፡ቢኖር
እንኳን ቅ/ጳውሎስ እንደተናገረው ከንቱ ነው “ሁሉ ቢኖረኝ ፍቅር ግን ከሌለኝ ከንቱ ነኝ”(1 ቆሮ 13፡1)

6. ከመስቀሉ መካፈል

የጠፋውን በግ ፍልጋ ራሱን ባዶ ያደረገው ክርስቶስ (ፊሊ 2፡8) ድሉ በመስቀል ስለ ተጠናቀቀ


ክርስቲያኖች በሕይወት ዘመናቸው ከመስቀሉ ተካፋይ መሆን አለባቸው፡፡ ለዚህም ከመስቀሉ ስር
የተሰጠችንን እናት ቅድስት ድንግል ማርያምን መውሰድ፤ የተቆረሰውን ቅዱስ ስጋ መብላት፤
የፈሰሰውን ክቡር ደም መጠጣት ይኖርብናል ማለት ነው፡፡ (ዮሐ 19፡27፤ ዮሐ 6፤56) ይህ ሁሉ ሲሆን
ለዘለዓለም በሕይወት እንኖራለን ማለት ነው፡፡

ሰባቱ ምስጢራተ ቤተ ክርስቲያን


ምሥጢር ማለት ቃሉ የግሪክ ቋንቋ ሆኖ ቃሉ ከግዕዝና ከአማርኛ በቀጥታ የተወረሰ ሲሆን ትርጉሙም
ድብቅ ፣ ስውር፣ ሽሽግ፣ ረቂቅ ፣ ለቅርብ ዘመድ ካልሆነ በቀር የማይገለጥ ማለት ነው፡፡ ለሁለት
የሚከፈል ሲሆን ይኸውም የፍጡር ሚሥጢርና የፈጣሪ ሚስጥር በመባል ይታወቃል፡፡ የፍጡር ምስጢር
ሁለት ይዘት አለው፡፡ የሰውና የመላዕክት ምስጢር ይባላል፡፡ በቤተክርስቲያን ውስጥ የሚገኘው የፈጣሪ
የእግዚአብሔር ሚስጥር ይህ የከበረ የተወደደ የሚናፈቅ የበረከት ስጦታ ነው፡፡ ብርሃነ አለም ሀዋርያው
ቅዱስ ጴጥሮስ እንዲህ ሲል በከበረ ቃሉ ገልፆታል፡፡ “እርሱንም ሳታዩት ትወዱታላችሁ አሁንም ምንም
ባታዩት በእርሱ /በክርስቶስ/ አምናችሁ የእምነታችሁን ፍጻሜ እርሱን የነብሳችሁን መዳን
እየተቀበላችሁ በማይናገርና ክብር በሞላበት ሀሴት ደስ ይበላችሁ”፡፡ በማለት ስውር ረቂቅ ከሆነው ጸጋ
እግዚአብሔር የምንሰጠው ሀብት መሆኑን በማብራራት ገልፆታል፡፡ በዚህ መሰረት በቤተክርስቲያናችን
ውስጥ ከሚፈጸሙት ሚስጥራት በቁጥር 7 ተወስነው ተቀምጠዋል፡፡ ውሳኔነታቸው ለሰባቱ ሰማያት
ስብዐተ እግዚአብሔር ለማይከፈልባቸው ከተሞች ገላጭ ናቸው፡፡ እነዚህ ሰባት ሚስጥራት
ቤተክርስቲያን የሚስጥርነታቸው ምክንያት በአይናችን ልናያቸው በእጃችን ልንዳስሳቸው የማንችል ልዩ
ልዩ የመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች በእነዚህ ሚስጥራት አማካኝነት የሚሰጡን ስለሆነ ነው፡፡ አበው ሲናገሩ
በንባብ የተሰወረ ብሂል ምስጢር ይባላል ብለው ስውርነቱን ረቂቅነቱን ይናገራሉ፡፡ ሰባቱ ሚስጥራተ
ቤተክርስቲያን የሚባሉት እንደሚከተለው ይዘረዘራሉ፡፡

1. ጥምቀት
2. ሜሮን
3. ቁርባን
4. ክህነት
5. ንስሀ
6. ቀንዲል
7. ተክሊል ናቸው፡፡
1. ሚስጢረ ጥምቀት

ይህ ምሥጢረ ጥምቀት ከኃጢያት ነፃ የምንሆንበት ከዲያቢሎስ አገዛዝ አርነት የምንወጣበት


ከእግዚአብሔር በጸጋ የምንወለድበት የምስጢር አይነት ነው፡፡ በቅሰዱሳት መጻህፍት እንደተገለጸው
በነብየ እግዚአብሔር በቅዱስ ሕዝቅሌል ት.ሕዝ 36፡25 “ጥሩ ውሀንም ጥምቀትን እረጫችኋለሁ፡
እናንትም ትጠራላችሁ ከርኩስነታችሁም ሁሉ ከጣኦቶቻችሁ ሁሉ አጠራችኋለሁ አዲስ ልብ
እሰጣችኋለው” በማለት የዚህን ምስጢር ክብርነት በረከትነት አምልቶ አስፍቶ ተናገሯል፡፡ በዚህ ሀሳብ
ሌሎች ንፁሐን አበው ሀዋርያት ተባብረውታል፡፡ በምልአት ሰብከውታል፡፡ የሐዋ.2፡38 ፣ 1 ቆሮ 6፡11 ፣
ዮሐ. 3፡5 ፣ ኤፌ 5፡26 ፣ ገላ 3፡27 ፣ ቲቶ 3፡5 ጥምቀት ዳግመኛ ተወልደን ወደ እግዚአብሔር መንግስት
የምንገባበት ምስጢር ነው፡፡ ከመጸሕፍ ቅዱስ ውስጥ ጥምቀት ብዙ ምሳሌዎች ይኖሩታል፡፡ እነሆ
ከማየአይኅ የዳነበትን መርከብ ቅዱስ ጴጥሮስ የጥምቀት ምሳሌ እንደሆነ ገልጾታል፡፡ 1 ኛ ጴጥሮስ 3፡21
ምዕመናን ከሐጢያት ከጥፋት የሚድኑት በጥምቀት ነውና
ቅዱስ ጳውሎስም እስራኤል ከግብጽ የባርነት ቀንበር ተላቀው የኤርትራን ባህር ተሻግረው ወደምድረ
ርስት ያደረጉትን ጉዞ የጥምቀትን ምሳሌ አድርጎ አመስጥሮታል፡፡ 1 ኛ ቆሮ 10፡1-2 ምዕመናን ባህረ
ኃጢያትን ተሻግረው ምድረ ርስተ መንግስተ ሰማያትን የሚወርሱት በጥምቀት ነውና፡፡ ዳግመኛም ይህ
ብርሃናዊ ሐዋርያ ጥምቀትን በሞትና በመቃብር ይመስለዋል፡፡ ሮሜ 6፡3-4 ቆላ 2፡12 በሞት ጊዜ ነፍስና
ስጋ እንደሚለያዩ በጥምቀትም አሮጌው ሰውነት ይሞታል ይቀበራል አዲስ ሰውነት አዲስ ሕልውናን
ይጀምራልና፡፡

2. ምስጢረ ሜሮን

ይህ ቃል የጽርዕ ቋንቋ ነው ትርጉሙም መአዛ ያለው የሚያውድ ፣ የሚጣፍጥ፣ ልብ የሚመስጥ ፣


ጣዕም ያለው መልኩ ጽርየቱ ዘይት ነው፡፡ በግዕዝ ቅብዕ፣ ቅብዐ ሜሮን ይባላል፡፡ ከብዙ እጽዋት ተቀምሞ
የሚሰራ ነው፡፡ ሕዝበ እስራኤልን የሚያስተዳድሩ የእግዚያብሔር እንደራሴዎች ነገስታትን መሲሀን
የሚባሉት ለዚህ ቅብ ተቀብተው ስለሚነግሱ ነው፡፡ ዘፍ 20፡23 1 ኛ ሳሙ 10፡1 ዘዳ 28፡41 1 ኛ ሳሙ 9፡6
1 ኛ ነገስት 1፡34 ይህ ብቻ አይደለም እግዚአብሔር የሚገለገልባቸው የቤተመቅደስ ነዋያተ ቅድሳትን
አስቀድሞ በዚህ መታተም አለባቸው፡፡ ከተቀቡ በኋላ ለቤተ መቅደስ እንጂ ለተራ አገልግሎት አይውሉም
ስለ ቅብዐ ሜሮን ቅዱስ መጽሐፍን የፃፉ ሰዎች የመንፈስ ቅዱስን ስጦታ ቅብዐት ይሉታል፡፡ 2 ኛ ቆሮ
1፡21 ዮሐ 2፡20 ቅብዕን በመንፈስ ቅዱስ ማህተምን ይሉታል፡፡ ኤፊ 1፡13 ፣4፡30 ይህ ቅብዓ ማህተመ
ሕይወት በመሆኑ ለአገልግሎት ይውላል፡፡

3. ምሥጢረ ቁረባን

ይህ ቃል የሱርስት ቃል ነው፡፡ ትርጉሙም አምኃ ስጦታ ማለት ነው፡፡ ሥጋውና ደሙ የተሰጠን በነፃ ያለ
ዋጋ ሳይገባን በችሮታ ነውና፡፡ በቤተክርስቲያን ምሥጢራት ሁሉ መደምደሚ ቅዱስ ቁርባን ነው፡፡
መስዋዕት ማቅረብ የተጀመረው በአዳም ጊዜ ሲሆን ከአዳም እስከ ሙሴ የተነሱ አበው ሁሉ በህገ ልቦና
ለእግዚአብሔር መስዋት ይሰው ቁርባን ያቀርቡ ነበር፡፡ መስዋዕታቸው ከእንሰሳ ቁርባናቸው ከእህልና
ከአትክልት ማለት ከስንዴ እህል፣ ከወይን ፍሬ የሚቀርብ ነው፡፡ ዘመነ ኦሪት በብሉይ ኪዳን በሙክራብ
የተሰዋ እንሰሳት ሁሉ በአዲስ ኪዳን በቤተክርስቲያን ለሚሰዋው ሁሉ የክርስቶስ ሥጋና ደም ምሳሌ
ነበር፡፡ መልከ ጼዴቅ ያበረከተው ኅብስተ አኮቴት ጽዋዐ በረከት ለአምላክ የሥጋውና የደሙ ምሳ ሆነው
አልፈዋል፡፡ ከምሥጢራት አንዱ መሆኑ ሕብስቱ ተለውጦ የክርስቶስ ሥጋ ጽዋው ተለውጦ የክርስቶስ
ደም ሲሆን አይታይም፡፡ ነገር ግን እምነት ያለው ሁሉ በእምነት መነጽር ይመለከተዋል፡፡ ይህ ሳይሆን
ሳይታይ የሚወደድን ሕይወት ለማግኘት ከቁርባን በፊት ንስሐ መግባት ለአስራ ስምንት ሰዓት መጾም
አለበት፡፡ ንጽሕናውን በጠበቅ አለበት፡፡ መምክረ ካህን ጸንቶ መገኘት ያስፈልጋል፡፡

4. ምሥጢረ ክህነት

ይህ ቋንቋ የግዕዝ ቋንቋ ነው፡፡ ተክህነ አገልገለ ከሚለው ግስ የወጣ ነው፡፡ ክህነት የተጀመረው በአባታች
አዳም ነው፡፡ ክህነት የአገልግሎት ስም ሆኖ የቤተክርስቲያን ከፍተኛ መንፈሳዊ ማዕረግ ነው፡፡
እግዚአብሔር አዳምን ፈጥሮ በልጅነት አክብሮ ነብይና ካህን አድርጎ ሾሞ በኦሪት በወንጌል ሥርዓት
እስኪወሰን ድረስ ከአዳም ጀምሮ እስከ ሙሴ የነበሩ አበው በበረከት አበው ከእግዚአብሔር እየተሾሙ
ትንቢትን ክህነት ከቅዱሱ መንፈስ እየተቀበሉ (እየተሾሙ) በነብይነታቸው ያለውን የሚመጣውን
ሲገልጽ ሲያስተምሩ በሀብተ ክህነታቸው መስዋዕት ሲቀርቡ ነበር፡፡ ክህነት በዘመነ ኦሪት ለሌዊ ነገድ
ከተሰጠ በኋላ ሲወርድ ሲወራረድ እስከ ክርስቶስ ደርሷል፡፡ ታላቁ ሊቀ ካህናት እየሱስ ክርስቶስ እንደ
ብሉይ ኪዳን መስዋዕት እንሰሳ ሳሆን እራሱን መስዋዕት፣ እርሱ ሰዋዒ ሆኖ ወደ መቅደስ ገብቷል፡፡ ዮሐ
20፡22 ማሬ 18፡18 1 ኘና ቆሮ 4፡1 ማሬ 28፡20
5. ምሥጢረ ንስሐ

ይህ ቃል የግዕዝ ቃል ነው፡፡ ትርጉሙም በሰሩት ኃጢያት መጸጸት ምነው ባልሰራሁት ባላደረኩት ብሎ


ማልቀስ ወደ ኃጢያት ላለመመለስ መወሰን፣ በሕጉ ጸንቶ ለመኖር ቃል መግባት፡፡ ክርስቲያን በጥምቀት
ከአለም ክፉ ስራዎች ሁሉ የተለየ ነው፡፡ ህይወቱ ለክርስቶስ የተሰጠ ነው፡፡ ሮሜ 12፡1 የመጨረሻው
ግቡና ዓላማው ሥርየተ ኃጢያትን ማግኘት እና የዘላለም ሕይወት መወረስ ነው፡፡ አካሉ የመንፈስ
ቅዱስ ነው፡፡ 1 ቆሮ 6-19

6. ምሥጢረ ቀንዲል

ይህ ቃል የላቲን ቋንቋ ነው ትርጉሙም ፍፁም መብራት ማለት ነው፡፡ ከሰባቱ ሚስራት አንዱ ቀንዲል
ነው፡፡ በብሉይ ኪዳን ዘይት የፈውስ ምልክት ነው፡፡ በደዌ ዳኛ በአልጋ ቁራኛ ተይዘው የሚሰቃዩ
ህሙማን ወይም በድንገተኛ አጋጣሚ የመቁሰል አደጋ የደረሰባቸው ቁስለኞች እየተቀቡ ይፈወሱ ነበር፡፡
ኢሳ 1፡6 ሉቃ 10፡34 ራዕ 3፡18 ማር 6፡13 ይህ ቅብዓተ በሐዲስ ኪዳን ለሚጠመቁ ከሚደረግ ቅብዐ
ሜሮን ጋር ግንኙነት የለውም ራሱን የቻለ ሕሙማነ ሥጋ ብቻ ሳይሆን ሕሙማነ ነፍስ ኃጥአን
የሚቀቡት ፈውስ የሚያገኙበት ነው፡፡ ማር 6፡13 ያዕ 5፡13-15 ራዕ 1፡17፡፡

7. ምሥጢረ ተክሊል

ይህ ማለት “ተከለለ” ተቀናጀ ከሚለው የግዕዝ ግስ የተገኘ ነው፡፡ በሥርዓተ ጋብቻ ቅደም ተከተል
መሰረት በመተጫጨት እና በቃል ኪዳን የተመሰረተ ጋብቻ በተክሊል ይፈጸማል፡፡ ቤተክርስቲያን
ምስክርነት የሚፈጸመው ጸጋ መንፈስ ቅዱስን የሚያሰጥ ስለሆነ ነው፡፡ ክርስቲያናዊ ጋብቻ
ትክክለኛነቱም የሚታወቀው በተክሊል ሥጋወ ደሙ ሲፈጸም ነው፡፡ ክርስቲያናዊ ጋብቻ ትክክለኛነቱም
የሚታወቀው በትክሊል ሥጋወ ደሙ ሲፈጸም ነው፡፡ ዘፍ 1፡27-28 ፣ 2-18 ማቴ 19-4 እነዚህን
ምሥጢራተ ቤተክርስቲያን አውቀን ተረድተን የእምነታችን ፍጻሜ የሆነውን አምላካችንን
ለተፈጠርንለት ዓላማ በመገዛት የነፍሳችንን መዳን ልናረጋግጥ ይገባል፡፡

ለዚህም ቸሩ አምላካችን እግዚአብሔር እንዲረዳን የወላዲተ አማላክ አማላጅነት እንዳይለየን የጻድቃን


ፀሎት የቅዱሳን በረከት እንዳይለየን ፈቃዱ ይሁንልን አሜን!!!

You might also like