You are on page 1of 45

አዕማደ ምስጢር

ዲ/ን ኢዮብ ወንድወሰን


ከኒቅያ ጉባኤ በፊትየንበሩ
ምንፍቅናዎች
• ከተገለጠው እውነት የተለየ እና ቤተ
ክርስቲያን በቱዎፊት ካስቀመጠችው አበው
ካ’ስተምሩት ውጭ የሆነ ትምህርት
ምንፍቅና ይባላልባስልዮስ ዘቂሳርያ
• በምንፍቅና ና በሥነ መለኮት አረዳድ
ስህተት መካከል ግን ልዩነት አለ
• በምስጢረ ስላሴ ና ስጋዌ ላይ የሚነስ
ውዝግቦች መነሻች ሁለተኛው ክፍለ ዘመን
ነውነበር
ናቸው
የመወያያ
ጥያቄ
ስህተት እና ምንፍቅና
ልዩነት አላቸው ማለት
እንችላለን?
ከኒቅያ ጉባኤ በፊትየንበሩ
ምንፍቅናዎች
• ግኖስቲክ፥ ሁለት አምላክ ክፉ እና ደግ፣
ስጋዊ እና መንፈሳዊ ብሎ የሚያምን
ነው
• ኢቦኒዝም፥ የኢየሱስ ክርስቶስን
በድንግልና መወለድ ይቀበላሉ፣
አምላክነቱን እና ፈጣሪነቱን
አይቀበሉም
• ዶሴቲዝም ፥ ክርስቶስ ምትሀታዊ ነው
ብለው የሚያምኑ ናቸው
• መርቅያኒዝም፥ ብሉይ ኪዳንን
የማይቀበል፣ ክርስቶስን አምልክ ነው
ብሎ የማያምን ነው
ከኒቅያ ጉባኤ በፊትየንበሩ
ምንፍቅናዎች
• ሞዳሊዝም ፦ አብ ወልድ መንፈስ ቅድስ
አንድ አካል ነው የሰባልዮስ ትምህርት
ነው፤ ሰቃልያነ አብ ይባላሉ (ለኦንልይ
ጅሰሶች ፈርቀዳጅ ነው) ና
• ሰማዕቱ ዮስጢኖስ (150 ዓም) ጥምቀት
በሰለስቱ መለኮታዊ አካላት ስም
እንደሚፈጸም ገልጾአል
• አቴናጎረስ ፦ መለኮታዊ ቃል ወይም
ከሦስቱ አካል አንድ አካል ወልድ ከአብ
ጋር የሚተካከል መሆኑን አረጋግጦ
ጽፏል። ይሁን እንጂ ስለ ሦስተኛው
አካል መንፈስ ቅዱስ ግልጽ ግንዛቤ
ከኒቅያ ጉባኤ በፊትየንበሩ
ምንፍቅናዎች
• ቅድስ ሄሬንያስ ፦ ከግኖስቲኮች ጋ
በሚከራከርበት ወቅት በቅድስት ስላሴ
የባህርይ አንድነት እና ፍጹም ፈጣሪነት
በሚገባ ያስረዳ ነበር። መለኮታዊ
ወልድ እና መንፈስ ቅዱስን
የእግዚአብሔር አብ “ሁለት እጆቹ”
ናቸው በማለት ይገልጻል
• አርጌንስ (185-253 ዓም) ፦
እግዚአብሔር የፍጥረት ኹሉ መሠረት
እና በገሃዱ ዓለም ውስጥ በመፍጠር
በመመገብና በመጠበቅ በአካል እና
በተግባር የሚሰራ ነው፣ አርጌንስ
“ሦስት አካላት በአንድ መለኮት”
ከኒቅያ ጉባኤ በፊትየንበሩ
ምንፍቅናዎች
• ለአርጌንስ አንድ አምላክ ፍጽም አምላክ
እግዚአብሔር አብ ብቻ ነው ብሎ ያምናል
• እግዚአብሄር አብ ከማንም የማይወለድና
ምንም ዓይነትአስገኝ እንደሌለው ወልድ
ደግሞ በተሳትፎ ወይም በመወለድ
አምላክነትን ያገኘ መኾኑን በመግለጽ
መለኮታዊ ወልድን በደረጃ ዝቅ ያደርገዋል
• ስለመንፈስ ቅዱስ የተዛባ አመለካከት
ነበረው መንፈስ ቅዱስ እንደ ወልድ
አልተወለደም በወልድ በኩሉ በአብ
ተፈጠረ ብሎ ያምናል::
ከኒቅያ ጉባኤ በፊትየንበሩ
ምንፍቅናዎች
• በዮሐ 14-28 ላይ ያለውን “እርሱ አብ
ይበልጠኛል”
• ሲተረጉም “አዳኙ እና መንፈስ ቅዱስ
ያለምንን ማወዳደር ከተፈጠሩት ፍጥረታት
ሁሉ እጅግ የበላይ ናቸው ነግር ግን አብ
እነርሱ ከፍጥረት ሁሉ የበላይ ከሆኑበት
ደረጃ ኹሉ በላይ የበላይ ነው እንላለን”
ብሏል።
• አዲስ አፍላጦን “ህልውናወች ከአንድ
ፍጽም ታላቅ አምላክ የሚወጡና
በመጨረሻም ተመልሰው በተለያዩ
መንገዶች ወደ እርሱ የሚገቡናቸው” ይላሉ
ኑፋቄ በኒቅያ ጉባኤ
አርዮሳዊ ኑፋቄ
• አርዮስ ስለ ባህርየ እግዚአብሔር እና ስለ
ሀልዎተ እግዚአብሔር ለአእምሮ በሚመች
መልኩ በአመክንዮ የተደገፈ ማብራሪ
መስጠት ዓላማው ነበር
• “እግዚአብሔር ወልድ በእግዚአብሔር አብ
ፍጹም ፈቃድ የተፈጠረ አምላክነትን
ከእግዚአብሔር አብ ያገኘ በእርሱ ሁሉ
ፍጥረት የተፈጠረበት ነው” ብሎ
ያስተምራል
• ““የተወልደ” የሚለው ቃል የተፈጠረ
መሆኑን የሚያሳይ ነው” ብሎ ይላል
ኑፋቄ በኒቅያ ጉባኤ
አርዮሳዊ ኑፋቄ
• እግዚአብሔር ወልድ ዘላለማዊ አይደለም
ያልኖረበት ዘምን አለ
• “እግዚአብሔር ማለታችን በጸጋ ነው
በስይሜ አምላክ ብንለው እንኳ እውነተኛ
አምላክ አይደለም”
• ፍጽም አምላክነት ስለሌለው መውደቅ
መሰናከል ሊያጋጥመው ይችላል
• ሌሎች ፍጥረታት(መንፈስ ቅዱስን ጭምር)
በእርሱ ተፈጥረዋል
ኑፋቄ በኒቅያ ጉባኤ
አርዮሳዊ ኑፋቄ
የአርዮስን ትምህርት ብንቀበል
• እግዚአብሔር አብ እና እግዚአብሔር
ወልድ በባህርይ አንድ አይደሉም
• ልዩ ሶስትነት አይኖርም
• ክርስቶስ ፍጽም ሰውም ፍጽም አምላክም
ሳይሆን ከፊል ሰው ከፊል አምላክ ነው
ያስብላል
• አምላክ ሰው መሆኑ ትረት ሁኖ አዳም
አልዳነም ያስብላል
• ክርስቶስን ማምለክ ፍጡርን ማምለክ
ይሆናል
ለአርዮሳዊ ኑፋቄ
የቅዱስ አትናቴዎስ መልስ
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ በባህርይ አንድ
ናቸው
• ኢየሱስ ክርስቶስ ፍጽም ሰው ፍጽም
አምላክ ነው
• ኢየሱስ ክርስቶስ ዘለዓለማዊ ሊቀ
ካህን(ዕ.ብ 6፥20) የተወልደ እንጂ
ያልተፈጠረ
• ፍጽም ንጽህ በደላችንን የተሸከመ ነው
• ልደቱ እና ሞቱ ለድኅነታችን መሠረት ነው
• ምንም እንኳን ምስጢረ ስላሴ
ያማይመረመር ቢሆንም ፍጽም እውነት
፫ ቱ የቀጰዶቅያ አባቶች

• ቅዱስ አትናቴዎስ እና በኒቅያ የተሰበሰቡ


አባቶቻቸውን ትምህርት ተቀብለው የነገረ
ሥላሴን ትምህርት በጥልቀት ያስተማሩ
የቀጰዶቅያ ሶስቱ አባቶች የምስጢረ ሥላሴ
አባቶች ይባላሉ እነርሱም፡-
• ባስልዮስ ዘቂሳርያ
• ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ
• ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ ናቸው
 የእግዚአብሔር የባህርይ አይመረመሬነት
በኦርቶዶክሳውያን አባቶች ዘንድ የትመህርቶች
መነሻ ነው
 “እኔ እግዚአብሔር እራሱን በሚያውቀው
መጠን አውቀዋለሁ” የሚለው የመናፍቁ
የዩኖሚያስ ትምህርትን ውድቅ አድርገዋል
 ይህ ምንፍቅና ክርስትናንን በአመክኖያዊ እይታ
እና በሰው የማሰብ ችሎታ ላይ ብቻ እንዲደገፍ
የሚያስብ ነው
 ዩኖሚዎስ እግዚአብሔር የማይመረመር ነው
ብሎ ማስብ እግዚአብሔር የለም ብሎ ማመን
እንደሆነ ያስባል
 እግዚአብሔርን በባህርይው እናውቀዋለን ማለት
የሃይማኖት የለሽነት ጥግ ነው ቅዱስ ዮሐንስ አፈ
ወርቅ “የክፋት ሁሉ ምንጭ ነው” ይላል
 ቅዱስ ጎርጎርዮስ ነባቤ መለኮት “ባህርየ መለኮት
በሰው ህሊና ሊመረመር እና ሊታሰብ አይቻልም”
ይለናል
 ለምን እግዚአብሔር በባህርይ መለኮት
አይታወቅም?
ነባቤ መለኮት “በሰው እና በእግዚአብሔር
መካከል የሰውነት ጨለማ አለ ልክ
በእስራኤላውያን እና በፈርዖን ግብጽ መካከል
እንደነበረው ጨለማ ኦ ዘጸ 10-22”
ቅዱስ ጎርጎርያስ ስጋ በሰው እና በእግዚአብሔር
መካከል እንደ ግድግዳ በመሆኑ የማይመር ሆነ
በሚለው ትምህርቱ ውስጥ ስጋ ከነፍስ ከተለየ
በኀላ ማወቅ ይቻላል? ለሚለው ጥያቄ ግልጽ
መልስ አልሰጠም 1ቆ 13-12።
ልዩ ሶስትነት
 የደማስቆው ዮሐንስ “እግዚአብሐር አንድ ነው
ብዙ እግዚአብሔር እንዳለ ቅዱሳት መጻህፍት
አልነገሩንም “ በማለት የእግዚአብሔርን አንድነት
ይናገራል።
 ቅዱስ ቄርሎስ ዘእስክንድርያ “በኒቅያ እና
በቁስጥንጥንያ የወጣውን የሃይማኖት መግለጫ
“በአንድ እግዚአብሔር አምናለሁ” ማለት በአንድ
እግዚአብሔር ከማመን ውጭ ወስን የሌለው
አምላክ እንደሆነ ያስረዳል” ይላል
“አሚን በአብ ወላዲ አስራጺ፣ አሚን በወልድ ከአብ
አካል ዘእም አካል ባህርይ ዘእም ባህርይ አብን አህሎ
መንፈስ ቅዱስን መስሎ በግብር የተለየ ሆነ ተወለደ
፣አሚን በመንፈስ ቅዱስ ከአብ የሰረጸ በባህርይ በህልውና
ከአብ ከወልድ ያልተለየ ነው “ ብሎ ማመን ።
ልዩ ሶስትነት
 ቅድስ ጎርጎርዮስ “ሶስቱም አንድ እግዚአብሐር
ናቸው አንድ ባህርይ ናቸው የሁለቱም መገኛ አብ
ነው የአካል ሶስትነት ከእሱ ይገኛል ይህ ማለት
መፈጠር ማለት አደለም መገኘትም የጊዜ
መቀዳደም የለበትም”
ቅዱስ አትናቴዎስ - አርዮስን ተከራክሮ የረታ
“አብ አምላክ ነው ወልድ አምላክ ነው መንፈስ
ቅዱስም አምላክ ነው ነገር ግን ሦስት አማልክት
አይባሉም” ሲል የሥላሴን አንድነትና ሦስትነት
ይነግረናል
የውይይት ጥያቄ

እግዚአብሔር ፈጣሪ ነው።


ከፍጣሪነቱ የተለየበት ፈጥረት
ያልፈጠረበት ዘመን ይኖር
ይሆነ?
ልዩ ሶስትነት

የአካል ሶስትነት
አብ በተለየ አካሉ ፍጹም አካል፣ ፍጹም ገጽ፣
ፍጹም መልክእ አለው
ወልድም በተለየ አካሉ ፍጹም አካል፣ ፍጹም
ገጽ፣ ፍጹም መልክእ አለው
መንፈስ ቅዱስም በተለየ አካሉ ፍጹም አካል፣
ፍጹም ገጽ፣ ፍጹም መልክእ አለው
 ይኽነንም ምስጢር ሊቁ አቡሊዲስም
“ባሕርያቸው በእውነት አንድ ሲኾን በመልክእ፣
በአካል ፍጹማን የሚኾኑ ሶስት ገጻት እንደኾኑ
በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ እናምናለን”
በማለት በጥልቀት ገልጾታል
ልዩ ሶስትነት

የአካል ሶስትነት
የሥላሴ አካላቸው ምሉእ በኲለሄ፣ ስፉሕ፣ ረቂቅ
ሲኾን ዳር ድንበር፣ ወሰን፣ ዳርቻ የለውም
በመጽሐፈ ቀሌምንጦስም ምሉእነቱን ሲገልጽ
“ኹሉን እኛ እንሸከመዋለን እንጂ እኛን
የሚሸከመን የለም፤ ከኛ በላይ ከኛም በታች ቦታ
የለም፤ የባሕርያችን ምልአት ኹሉን ይወስናል
እንጂ የሚወስነው የለም”
 ሊቁ አረጋዊ መንፈሳዊ ስለ ርቀታቸው
“የመንፈሳዉያን የኅሊናቸው ርቀት በአንተ ዘንድ
ካለው ረቂቅነት አንጻር እንደ ሥጋ የገዘፈ ነው”
በማለት አስተምሯል
ልዩ ሶስትነት
የአካል ስም ሥስትነት
አካላት በሥላሴ ዘንድ ስም አላቸው
ይኽም የሥላሴ የአካል ስም አካል ቀድሞት እንደ
ሰው ስም በኋላ የተገኘ አይደለም
 “ሰብእ” (ሰው) ማለት ስሙ ከአካሉ አካሉ
ከስሙ ሳይቀድም እንደ ተገኘ የሥላሴም ስማቸው
ከአካላቸው፤ አካላቸው ከስማቸው ሳይቀድም
ቅድመ ዓለም የነበረ ስም ነው እንጂ ድኅረ ዘመን
የተገኘ አይደለም
ቅዱስ ጎርጎሬዎስ ገባሬ መንክራት "ደግሞ አብ
ወልድ መንፈስ ቅዱስ እንላለን ግን አካላት
ተቀድመው ተገኝተው እሊኽ ስሞች ኋላ
የተጠሩባቸው አይደሉም፤ ሰው ማለት ኋላ የወጣ
ስም አይደለም ባሕርዩ ነው እንጂ”
ልዩ ሶስትነት
 ቅዱስ አግናጥዮስም “አብም አብ ነው ወልድን
አይደለም መንፈስ ቅዱስንም አይደለም፤ ወልድም ወልድ
ነው አብን አይደለም መንፈስ ቅዱስንም አይደለም፤
መንፈስ ቅዱስም መንፈስ ቅዱስ ነው አብን አይደለም
ወልድን አይደለም፤ አብ ወልድንና መንፈስ ቅዱስን
ለመኾን አይለወጥም፤ ወልድም አብንና መንፈስ ቅዱስን
ለመኾን አይለወጥም፤ መንፈስ ቅዱስም አብንና ወልድን
ለመኾን አይለወጥም”
የአካል ግብር ስም ሥስትነት
 ቅዱስ አግናጥዮስም “አብ መቸም መች ወላዲ ነው
እንጂ ተወላዲ ሠራፂ አይደለም፤ ወልድም ተወላዲ
ይባላል እንጂ ወላዲ ሠራፂ አይባልም፤ መንፈስ ቅዱስም
ሠራፂ ይባላል እንጂ ወላዲ ተወላዲ አይባልም፤ አብ
ሠራፂ ተወላዲ ወደመሆን አይለወጥም፤ ወልድም ወላዲ
ሠራፂ ወደመሆን አይለወጥም፤ መንፈስ ቅዱስም ወላዲ
ተወላዲ ወደመሆን አይለወጥም”
የባህርይ አንድነት
 ሥላሴ በባህርይ አንድ ናቸው
በሥላሴ ዘንድ መበላለጥ የለም የአንድነታቸው
ማዕከል አብ ነው
 ብርሃን ከብርሃን እንደሚወለድ ይህ ዓለም
ከመፈጠሩ አስቀድሞ ወልድ ከአብ ያለ እናት
ተወለደ አባቱ አብ እውነተኛ አምላክ እንደሆነ
እሱም እውነተኛ አምላክ ነው አብ ወለደው እንጂ
አልፈጠረውም አብ ብርሃን እንደ ሆነ ወልድ
ብርሃን ነው አብ ከባህርይው ወለደው ከአብ
ባህሪይ የተወለደ በባህሪይ አብን የሚመስለው
/የሚተካከለው/ ነው
የባህርይ አንድነት
 ስለ ሥላሴ በባህርይ ስንናገር ግብረ ባህርይዎን
ለይተን መናገር ይገባናል
ቅዱስ ሳዊሪያኖስ ዘ ገብሎን “ሁሉን ቻይ
እግዚአብሔር አንድ ነው ፡፡ መ. ኢዮ. ፵፪፡፩-፪
‹‹ ሁሉን ታደርግ ዘንድ ቻይ እንደሆንህ
የሚሳንህም እንደሌለ ዐወቅሁ ፡፡›› ማር. ፱፡፳፫
‹‹ ቢቻልህ ብለሃል ብታምንስ ለሚያምን ሁሉ
ይቻላል ›› መ.ኢዮ. ፴፪፡፰ ‹‹ ሁሉን የሚችል
የእግዚአብሔር መንፈስም ያስተምራል ››
በማለት አንድነቱን ያስረዳል
የባህርይ አንድነት

ቅዱስ ሳዊሪያኖስ ዘ ገብሎን “በመፍጠር አንድነት


ለምሳሌ ኦ.ዘዳ. ፴፪፡፮ ‹‹ ለእግዚአብሔር ይህን
ትመልሳለህን ? የፈጠረህ አባትህ አይደለምን?
የፈጠረህና ያጻናህ እርሱ ነው፡፡›› ኤፌ.፪፡፲ ‹‹
እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ
ላዘጋጀው በጎ ሥራ በኢየሱስ ክርስቶስ የፈጠረን
ፍጥረቱ ነንና ›› መ.ኢዮ. ፴፫፡፬ ‹‹
የእግዚአብሔር መንፈስ ፈጠረኝ ›› በማለት
አንድነትን ያስረዳል
 ቅዱስ አግናጥዮስም “አብም አብ ነው ወልድን
አይደለም መንፈስ ቅዱስንም አይደለም፤ ወልድም ወልድ
ነው አብን አይደለም መንፈስ ቅዱስንም አይደለም፤
መንፈስ ቅዱስም መንፈስ ቅዱስ ነው አብን አይደለም
ወልድን አይደለም፤ አብ ወልድንና መንፈስ ቅዱስን
ለመኾን አይለወጥም፤ ወልድም አብንና መንፈስ ቅዱስን
ለመኾን አይለወጥም፤ መንፈስ ቅዱስም አብንና ወልድን
ለመኾን አይለወጥም”
የአካል ግብር ስም ሥስትነት
 ቅዱስ አግናጥዮስም “አብ መቸም መች ወላዲ ነው
እንጂ ተወላዲ ሠራፂ አይደለም፤ ወልድም ተወላዲ
ይባላል እንጂ ወላዲ ሠራፂ አይባልም፤ መንፈስ ቅዱስም
ሠራፂ ይባላል እንጂ ወላዲ ተወላዲ አይባልም፤ አብ
ሠራፂ ተወላዲ ወደመሆን አይለወጥም፤ ወልድም ወላዲ
ሠራፂ ወደመሆን አይለወጥም፤ መንፈስ ቅዱስም ወላዲ
ተወላዲ ወደመሆን አይለወጥም”
ምስጢረ ስጋዌ
ምስጢረ ስጋዌ “ቃል ስጋ ሆነ… በእኛም አደረ” በሚለዉ
የወንጌል ቃል ላይ የተመሠረተ ምስጢር ነው (ዮሐ 1፥14)
 ይህ ምስጢር እግዚአብሔር ልጅ ወልድ በተለየ አካሉ
ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ከስጋዋ ስጋን ከንፍሷ
ነፍስን ነስቶ በስጋ መገለጡን የምንማርበት ነው
 አምላክ ሰው የሆነበት፣ ሰው አምላክ የሆነበት ልዩ
ምስጢር ነው
 ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስለ ምስጢረ ሥጋዌ ታላቅነት
ሲናገር “የተነገረውን አስተውል፤ እግዚአብሔር ከእኛ
ባሕርይ የተዋሐደው ተዋሕዶ ጥቂት ክብር አይምሰልህ፣
ይህንን ለመላእክት አላደረገውምና” ብሏል
እንዴት ሰው ኾነ?
በኹለቱ ትምህርት ቤቶች(በአንጾኪያ እና በእስክንድርያ)
እነዚህ ኹለት ጥያቄዎች የተለያየ መልስ አላቸው
1) ክርስቶስ ማን ነው?
2) ተልእኮውስ ምንድን ነው?
 ኹለቱ ትምህርት ቤቶች እነዚህን ጥያቄዎች በመመለስ
ውስጥ ባለ መስማማት ለብዙ ጊዜ በውዝግብ ቆይተዋል
 በዚህ መካከል በነገረ ስጋዌ ዙሪያ የከረሩ ምንፍቅናዎች
ተወልደዋል
 ምንም እንኳን ምንፍቅናዎቹ ከምስጢረ ስላሴ የሚነሱ
ቢሆንም በዚህ ዐውድ ደግመን ልናነሳቸው እንችላለን
ንስጥሮሳዊነት
 ንስጥሮስ በአንጾኪያ ትምህርት ቤት ከተማሩ ተማሪዎች
መካከል አንድ ነው(የቴዎዶሬት ዘሞፖሴስቴ ተማሪ)
 በ428 በቁስጥንጥኛ መንበር ሲቀመጥ የክህደት
ትምህርቱን ማስተማር ጀመረ
1) ቃል እና ስጋ ተደራረቡ(የፈቃድ ልዩነት ያላቸው አካላት)
2) ድንግል ማርያም ወላዲተ ሰብእ እንጂ ወላዲተ አምላክ
አትባልም
 “አምላክ በፍጽም ሊወለድ አይችልም የትኛውም
ፍጥረት ለአምላክ እናት መኾን አይችልም” ይል ነበር
ቅዱስ ቄርሎስ
 ቅዱስ ቄርሎስ ይኽን የንስጥሮስን ምንፍቅና “አንዱ
አካላዊ ቃል ከድንግል ማርያም ስጋን ነእሳ” ብሎ
አስተማራ
1) ድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክ ናት
2) ተዋህዶ አካላዊ ሁኖ አካላዊ ቃል ከሰጋ ጋ ተዋሃደ
3) ተዋህዶ ፍጽም ተዋህዶ እንጂ መጣመር አይደለም
4) ክርሰቶስ ባህርያት የሉትም
5) ክርስቶስ ፍጽም አምላክ ነው
6) መንፈስ ቅዱስ ኢየሱስ ክርስቶስን ሊያከብር የመጣ
አይደለም ህልው ነው እንጂ
7) ስግው ቃል በስጋ መከራ ተቀብሎ በስጋ ሞተ 1ኛ
ጴ.ጥ 3፥18
ቅዱስ ቄርሎስ
1) ክርስቶስ ማን ነው?
 ክርስቶስ አካላዊ ቃል እግዚአብሔር ወልድ ከድንግል
ማርያም ስጋን የነሳው ነው
2) ተልእኮውስ ምንድን ነው
 አካላዊ ቃል ከቅድስት ድንግል ማርያም በነሳው ስጋ
መከራን ተቀብሎ ያድነን ዘንድ ወደዚህ ምድር መጣ
 የዓለም ድኅነትም የተፈጸመው ወልዲተ አምላክ
በኾነችው በቅድስት ድንግል ማርያም ልጅ ሞት እና
ትንሳኤ ነው
አውጣኬ
 የእስክንድርያ ትምህርት ቤት ደጋፊ ነው
 የንስጥሮስ ተቃዋሚ በምሆኑ የሚታወቅ ሰው ነው
 ከተዋህዶ በኋላ ያለው አንድ ባህርይ ነው ብሎ አስተማራ
 የክርስቶስን ሰውነት ከእኛ ባህርይ የተለየ ነው አለ
 ተከራካሪዎቹ ግን የክርስቶስን ሰወኛ ባህርይ መለኮታዊ
ባህርይ መጠጠው ብሏል ብለው ከሰውታል
 በትምህርት የክርስቶስ ፍጽም ሰውነት አልታየም በሚል
ይወቀሳል
ኬልቄዶን (451 ዓ.ም)
 በዚህ ጉባኤ እነዚህ ውሳኔዎች ተወስነዋል
 አንድ ልጁ ከአባቱ ጋ በባህርይ አንድ ነው
 ፍጽም ሰውነት ከእመቤታችን የነሳ ነው
 ያለ መከፈል የተገለጠ
 ያለ መለወጥ እና ያለ መጠፋፋት
 በሁለት ባህርይ ያለ መቀላቀል ያለ መጠፋፋት
 ሁለት ባህርያ በተዋህዶ አንድ የሚሆን አይደለም
ሁለትነት ይኖራል እንጂ
 ቅዱስ ቴዎዶስዮስ “ከተዋሕዶ በኋላስ ሁለት ባሕርይ
አንልም፤ እንደ ንጹሐን አባቶቻችን ክርስቶስ (መለኮትና
ትስብእት) በአንድ አካል ሁለተኛ የሌለው አንድ እንደሆነ
እንናገራለን እንጂ፡፡”
፫. ምሥጢረ ጥምቀት
 ተጠምቀ - ተጠመቀ፣ ተነከረ፣ ታጠበ፣ ተጣጠበ፣ በገዛ
እጁ ወይም በሰው እጅ
 ጥምቀት የሚሥጥራት ኹሉ በር ነው
 ጥምቀተ ክርስቶስ የጥምቀትን ሥርዓት ሠራልን ‹‹
የክርስቲያኖች ጥምቀት መሠረት የጌታ መጠመቅ ነው ››
ቅዱስ ኤፍሬም ዘሶርያ
 በክርስቶስ መጠመቅ የምንጠመቅባቸው ውሆች ተባረኩ
‹‹ ኢየሱስ ክርስቶስ በጥምቀቱ የጥምቀትን ውሃ ቀድሶ
ቤተ ክርስቲያን ልጆቿን የምትወልድበት ማህጸን
አድርጓታል ›› ቅ.ኤፍሬም ዘሶርያ
 ቅዱስ ያዕቆብ ዘስሩግ ‹‹ ክርስቶስ ወደ ጥምቀተ ባህር
መጣ ወደ ውስጥም ገባ በዚያም ቆመ የቀድሞውን
የአዳም ጸጋ ይመልስ ዘንድ ›› አለ
ጥምቀት ጸጋ ናት
 ጸጋ የሚለው ቃል በሐዲስ ኪዳን መቶ ሃያ አራት ጊዜ
ሲጠቀስ በብሉይ ኪዳን ግን አንድ ጊዜ በት.ሚል ፩፡፲፱
ተገልፃል
 ጸጋ ማለት በልግስና የሚሰጥ ስጦታ ማለት ነው፤ ጸጋ
ከክርስቶስ እስከ ትንሳኤ ሙታንም እንደ አገባቡ
ይተረጎማል
 ጥማቀት ከጎኑ ውሃን አፍልቆ የሰጠን ስለሆነ ጸጋ
ተብላለች
 በጥምቀት ጸጋ እናገኛለን ሀብተ ውልድና (የልጅነት
ሃብት) ፣ አሚነ ልቡና ( የእምነት ልብ፣ የሚያምን ልብ
ይሰጣል) ፣ ገቢረ ተአምራት ወመንክራት (ተአምራትን
ድንቆችን መስራት ) ፣ ሀይው ከመ መላእክት (እንደ
መላእክት ህያው መሆን )፣ ስርየተ ኃጥያትን ታስገኛለች
ጥምቀት ሞት፤ መቃብር ናት
 ሮሜ. ፮፥፯-፬ ‹‹ እንግዲህ ክርስቶስ በአብ ክብር
ከሙታን እንደተነሣ እንዲሁ እኛም በአዲስ ሕይወት
እንድንመላለስ ከሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ በጥምቀት
ከእርሱ ጋር ተቀበርን ››
 ጌታ በጥምቀት ሶስት ጊዜ ብቅ ጥልቅ ለምን አለ ቢሉ
ሞቱን የሳየበት ናትና አረጋዊ መንፈሳዊም ‹‹ ይህች
ጥምቀት የሞቱ ምሳሌ ናት በዚያም እንቀበራለን በዚያም
እንነሳለን ››
 ጌታም ማር.፲’፥፳፱ ‹‹ እኔ የምጠጣውን ጽዋ ልትጠጡ
እኔ የምጠመቀውን ጥምቀት ልትጠመቁ ትችላላችሁን?
አላቸው ;›› ለምን ቢሉ ሞት ለሁሉ በተራ እንደሚደርስ
ጥምቀትም አማኝ ለተባለ ሁሉ በተራ ይደርሳል
 ሞት ትንሳኤ እንደሚከተለው ጥምቀትም የአዲስ
ሰውነት መነሻ ነው
ጥምቀት እሳት ትባላለች
 ማቴ. ፫፥፲፪ ‹‹ በመንፈስ ቅዱስ እና በእሳት
ያጠምቃቹኾል ››
 አረጋዊ መንፈሳዊ ‹‹ ይህች እሳት አዳም በገነት
አስቀድሞ የለበሳት እጸ በለስን በልቶ ከእግዚአብሔር
ሲጣላ የተራቆታት ልብሱ ናት ፡፡ ሁለተኛው አዳም እስኪ
መጣ ከእሳትና ውሃ የተፈተለ ልብስ እስከሚያለብሰው
ድረስ አዳም የተራቆታት ልብስ ናት”
 ጥምቀት ብትሰጥ የማታልቅ ስለሆነች እሳትም ቢወሰድ
አያልቅምና ፡፡
 እሳት አብስሎ ጣዕም ያመጣል ጥምቀትም ሰውን
በመንፈሳዊ ነገር አብስላ የመንፈሳዊ ህይወት ትሰጠዋለች
(ታሳድርበታለች)፡፡
 እሳት በአግባቡ ቢሞቁት ደዌይ ያርቃል ብርድ ያርቃል
ጥምቀትም በአግባቡ ከያዙት በጸጋላይ ጸጋ እያሰጠች
ትሄዳለች ፡፡
ጥምቀት
 አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ - በጥምቀት መወለድ ልክ
ክርስቶስ ከድንግል እንደ መወለዱ ነው ፡፡ ምክንያቱም
አንደኛ አይመረመርም ሁለተኛ ፍጹም መንፈሳዊ ነው
 በዲዲስቅልያ አንቀጽ አራት ላይ ‹‹ሴቶች ማጥመቅ
ቢችሉ ኑሮ ጌታ ለመጠመቅ ወደ ዮሐንስ ዘንድ ባልሄደ
ነበር ይልቁንም እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም
ባጠመቀችው ነበር እሷ ከሁሉም ትበልጣለችና ››
 ቅዱስ ቴዎፍሎስ በ፬ኛ ድርሳኑ በፍትሐ ነገሥት
‹‹ ሦስት ማህተም ያለው ንጉሥ ያለው ማህተም
የእንጨት፣ የብርና፣ የወርቅ ነው፡፡ ደብዳቤ ጽፎ በእንጨት፣
በብርና በወርቅ ደብዳቤው ቢታተም አይለይም ሁሉም
የንጉሡ ነውና፡፡ ጥምቅርትም በበቃ ካህን ቢጠመቁት ፣
ባልበቃ ካህን ቢጠመቁት በጳጳስ ቢጠመቁት ሁሉም አንድ
የሥላሴን ማህተም ከመስጠት አይገደብም ››
የመወያያ ጥያቄ
የእግዚአብሔር
ወልድ ሰው መኾን
የአዳም መውደቅ
ውጤት ነው?
፬. ምሥጢረ ቁርባን
 ቁርባን - በቁሙ፣ መንፈሳዊ አምኀ፣ ስለት፣
መሥዋዕት፣ መባዕ፣ ለአምላክ የሚሰጥ የሚቀርብ
ገንዘብ
 ካህኑ በመሰዊያው ላይ ወይኑንና ኅብስቱን አድርጎ
ይቀድስበታል ተለውጦ ወይኑ ደመ መለኮት ኅብስቱም ስጋ
መለኮት ሆኖ ይቀየራል
 ማቴ. ፳፮፡፳፮-፳፰ ‹‹ ሲበሉም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
አንስቶ ባረከ ፣ ቆረሰ ለደቀመዛሙርቱም ‹ ይህ ሥጋዬ
ነው እንኩ ብሉ› ብሎ ሰጠ…..” ፩ኛ ቆሮ. ፲፩፡፳፬-፳፭
“አመሰገነ ፣ባረከ፣ፈተተ እንዲህ አላቸው ‹እንኩ ብሉ ፤
ስለ እናንተ የሚሰጠው ሥጋዬ ይህ ነው› ….”
 እንዴት እና መቼ ነው ኅብስቱ እና ወይኑ የሚቀየረው?
ምሥጢረ ቁርባን
 ይለወጣል ሲባል በመዓዛ ፣በጣዕም ወይም በቀለም
አይደለም ሊቃውንቱ ይህን ውላጤ እንበለ ውላጤ
ይሉታል
 መለወጥ እንደ ሎጥ ሚስት አይደለም ይህ በረቂቅ
ምሥጢሩ እሱ ባወቀ ይቀየራል ይህም መንፈሳዊ ለውጥ
ነው
 መቼ ይቀየራል? ለሚለው ጥያቄ ኦርቶዶክሳውያን
አባቶች በአንድነት በሥርዓተ ቅዳሴ ውስጥ ይለወጣል
ይላሉ
 ማነው የሚቀይረው? የዚህ ምሥጢር ፈጻሚ እራሱ
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፣ የካህኑ ሥራ
ማገልገል መቀደስ ነው፡፡
 ቅዱስ ዩሐንስ አፈወርቅ ‹‹ ካህኑን ስታይ እንዳትሳሳት
የሚያቀብልህ ለሐዋርያት ያቀበለው ራሱ ክርስቶስ ነው››
ምሥጢረ ቁርባን
 ይኽ የሐዲስ ኪዳን መስዋዕት ከብሉይ ኪዳን መስዋዕት
የተለየ ነው ዕብ.፱፡፲፩-፲፪
በዕለተ ዓርብ የተፈጸመው መስዋዕትነት የማያልፍና
ዘለዓለማዊ ነው
 በጸሎተ ቅዳሴ የሚቀርበው መሥዋዕት ሌላ ሳይሆን ጌታ
በዕለተ ዓርብ የፈጸመው ነው
 ቅዱስ ዩሐንስ አፈወርቅ “ይህ በየዕለቱ የምናቀርበው
መሥዋዕት በዕለተ ዓርብ የቀረበውን መሥዋዕት ነው
እንጂ ሌላ አዲስ መሥዋዕት አይደለም”
 የምናቀርበው መሥዋዕት ሞቱን የምናስብበት ነው፤
መታሰቢያ ሲባል ግን ታሪክ ወይም ድርጊት ማስታወስ
ማለት አይደለም “ንዜኑ ሞተከ እግዚኦ ወትንሳኤከ
ቅድስት ነአምን ዕርገተከ…..”
የሶርያ ቅዱሳን አባቶች ቅዱስ ቁርባንን መቀበል ክርስቶስን
የመረዳት ችሎታ ተጸንሶ እንዲወለድ ያደርጋል
፭. ምሥጢረ ትንሣኤ ሙታን
 ተንሥአ - ተነሣ
 ትንሣኤ - ጥሬ ዘር ሲሆን ትርጉም መነሣት
ሞተ - ሞተ
ሙታን /ሳድስው. ዘቅጽል በብዙ/
ትንሣኤ ሙታን - የሙታን መነሳት ማለት ነው፡፡
ሰው እንደመላእክት ሕያው ሆኖ እንዲኖር እንጂ
እንዲታመም እንዲሞት አልተፈጠረም
ሞት ሰው በገዛ ፈቃዱ ያመጣው ዕዳ ነው፡፡
ሞት በአቤል ተጀምሯል
ትንሣኤ እንደለ በሄኖክ ነገረን
ጌታችን ትንሣኤን ተነሥቶ አማናዊ አደረገው
በምጽአት በግርማ መለኮት በመጣ ጊዜ ሁሉም ለፍርድ
ይነሣል፡፡
ምሥጢረ ትንሣኤ ሙታን
 ሞት፡- የነፍስ ከስጋ መለየት ነው
ሞት ይህን ዓለም ለማየት እንደተወለድን ሁሉ ክርስቶስን
ለማየት የምንሄድበት መንገድ ነው
ቅዱስ ቄርሎስ ‹‹ ሞትን ድልድይ ብሎታል›› ቅዱስ
አግናጥዮስ ‹‹ ወደ ክርስቶስ የምሄድበት ከዚህ የበለጠ
አጋጣሚ አላገኝም›› ይላል
 በእምነት ሆነው በሥጋ ሞት የተለዩ ከቤተክርስቲያን
ህብረት እንዳልተለዩ እናምናለን ፡፡ ፪ኛ ጴጥ.፩፡፲፪-፲፭
ዩሐ.፳፩፡፲፰-፲፱
 በፕሮቴስታንቱ ዓለም ከሞት በኋላ ያለውን ሕይወት
እንደ እንቅልፍ ስለሚቆጥሩት ቅዱሳን ሊያማልዱ
አይችሉም የሚል አስተሳሰብ አላቸው
ዳግም ምጽአት
 የትንሣኤ አካል ዘላለማዊ ነው፡፡ ቅዱስ ዩሐንስ አፈወርቅ
፪፡፲፱ ላይ ‹‹ አካሉ ከመሞታችን በፊት የነበረውን
የሚመስል የሚሆን ነው››
 ያለች እና የምትመጣ መንግሥት
 ሁለት ፍርድ ወይስ አንድ ፍርድ?
በዕለተ ፍርድ ፃድቃን ይቀድማሉ ምክንያቱም ኃጥአን
መንግሥተ ሰማያት አመለጠችን ብለው እንዲቆጩ ነው

You might also like