Professional Documents
Culture Documents
1 (PDFDrive)
1 (PDFDrive)
ምዕራፍ 1
አጠቃላይ ዳሰሳ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 12
መንፈሳዊ ስጦታዎችና ተፈጥሯዊ ችሎታዎች. . . . . . . . . . . . . . .
መንፈሳዊ ስጦታዎችና ስላሴ
ተገቢውን አተረጓጎም በተግባር ማዋል . . . . . . . . . . . . . . . . .19
ምዕራፍ 2
በ1ኛቆሮ 12 የተገለጡት መንፈሳዊ ስጦታዎችና አጠቃቀማቸው፡፡
የመገለጥ ስጦታዎች. . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 22
2.1. የእውቀት ቃል.
2.2. የጥበብ ቃል
2.3. መናፍስትን መለየት
ምዕራፍ 4
በኤፌ 4፡7-11 የተገለጡት መንፈሳዊ ስጦታዎች
የአገልግሎት ሰጦታዎች. . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . .76
4.1 ሐዋርያነት
4.2 ነቢይነት
4.3 ወንጌላዊነት
4.4 እረኝነት (መጋቢነት)
4.5 አስተማሪነት.
ማጠቃለያ. . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 89
ምዕራፍ 1
አጠቃላይ ዳሰሳ
(4)ይወቅሳል ዮሐ 16፡7-8
‹‹እኔ ባልሄድ አጽናኙ ወደ እናንተ አይመጣምና፤ እኔ ብሄድ ግን እርሱን
እልክላችኋለሁ።እርሱም መጥቶ ስለ ኃጢአት ስለ ጽድቅም ስለ ፍርድም
ዓለምን ይወቅሳል፡፡›› (ዮሐ 16፡7-8) ወቀሳ አሌ የማይባል ማስረጃን
በታራሚው ኃጢአተኛ ፊት በማቅረብ ተገቢውን ብያኔ መስጠት ነው፡፡
መንፈስ ቅዱስ ኃጢአተኛው ቅጣት የሚገባው ምርጫ የለሽ ጥፋተኛ
መሆኑን አሳይቶ ፊቱን ወደ ምህረት ጌታ እንዲያዞር የፍቅር ግብዣ
ያደርግለታል፡፡ መንፈስ ቅዱስ ኃጢአተኛው ፊቱን ወደ መንፈሳዊ ነገር
እንዲያዞርና ለመንፈሳዊነት ትኩረት እንዲሰጥ ገና ከጅማሬው የወቀሳ
ሥራውን በመሥራት ትክክለኛውን ጎዳና ያመለክታል፡፡ መንፈስ ቅዱስ
ይወቅሳል፣ (ዮሐ 16፡7-8)፡፡ ከእግዚአብሔር ከአምላካችን ተለይተን
የምንሄድበትን መስመር አክሳሪነትና ያለጌታ ያለውን ሕይወት ብልሹነት
ገሐድ በማድረግ የሞራል ብያኔ አስተላልፎ ጥፋተኝነትን ያሳውቃል፡፡
የተሰበከልንን፣ የሚሰበክልንን ወይም ብቻችን ሳለን ያነበብነው ሕያው
ቃል በመጠቀም አንተ(ቺ) ወይም እናንተ ኃጢአተኞች ናችሁ
የሚለውን ውሳኔ በውስጣችን እንድንሰማውና ያለንበት ሰባራ ሁኔታ
ወለል ብሎ እንዲታየን ያደርጋል፡፡ እንዲህ ላለው የመንፈስ ቅዱስ
የወቀሳ ድምጽ አዎንታዊ ምላሽ ስንሰጥ በዚያው ቅጽበት ጌታን በማመን
ራሳችንን ለፈጣሪ ፈቃድ ሰጥተን ከእግዚአብሔር መንፈስ ጋር
የተለያዩ ናቸው
መንፈሳዊ ስጦታዎችና ተፈጥሮአዊ ችሎታዎች የሚመሳሰሉበት ነገር
ቢኖርም አንድ ዓይነት ግን አይደሉም፡፡ ወንዶችና ሴቶች
በተፈጥሮአቸው እንደሚለያዩ ሁሉ ተፈጥሮአዊ ችሎታዎችና
መንፈሳዊ ስጦታዎች ራሱን የቻለ ልዩነት አላቸው፡፡ እርግጥ ነው
የሁለቱም ምንጭ እግዚአብሔር ነው፣ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ
ሊመሳሰሉ የሚችሉበት ሁኔታ አለ፡፡ ይሁን እንጂ ተፈጥሮአዊ
ልደትና ዳግም ልደት እንደሚለያዩ ሁሉ መንፈሳዊ ስጦታዎችና
ተፈጥሮአዊ ችሎታዎች የዚያኑ ያህል ይለያያሉ፡፡ ባመኑትና
ባለመኑት መካከል ያለውን ልዩነት በግልጽ የሚያስገነዝቡን
መንፈሳዊ ስጦታዎች ናቸው፡፡ መንፈሳዊ ስጦታዎች ያመነ ሰው
እድል ፈንታ ናቸው፡፡ መንፈሳዊ ስጦታዎች ለአማኙ በክርስቶስ
አካል ውስጥ ሥፍራን ይሰጡታል፡፡ ያለእነዚህ ስጦታዎች አማኝ
የተጣለበትን አደራ በቀላሉ አይገነዘብም፡፡ ስለ ልዩነታቸው እንዲህ
ብንናገርም የሚገናኙበት ሁኔታ የለም ማለት ግን አይቻልም፡፡
መንፈሳዊ ስጦታዎች
የጸጋ ስጦታዎች ስማቸው እንደሚያመለክተው እግዚአብሔር
ከርህራሄው የተነሳ ቅጣት ለሚገባቸው ሰዎች ያደረገው ልግስናዎች
ናቸው፡፡ ሁሉም አማኞች የዚህ እድል ፈንታ ተካፋይ ናቸው፡፡
ምዕራፍ 2
በ1ኛቆሮንቶስ 12 የተገለጡት መንፈሳዊ ስጦታዎችና
አጠቃቀማቸው፡፡
የመገለጥ ስጦታዎች
የመገለጥ ስጦታዎች ስያሜቸው እንደሚያመለክተው ከአምስቱ
ስሜተ ሕዋሳት መረጃና ድጋፍ ሳይመረኮዙ አንድን እውነት
በትክክለኛ ገጽታው በመገንዘብ ጠቃሚና የሚያንጽ መመሪያን
ለማስተላለፍ የሚገለጡ የመለኮት እገዛ ናቸው፡፡
የእውቀት ቃል ያልሆነው
የሰውን ጥረት ጠግኖ በማረም አሻሽሎ ማቅረብ አይደለም
የአስተዋዮች ቅደመ ትንበያ፣ ግምገማና ምክር አይደለም
በምርምር የሚገኝ ግኝት አይደለም
ቃሉን በማጥናት የሚገኝ ብርሃንም ሆነ አስደናቂ የቃሉ
እውቀት አይተካውም
በእድሜና በልምምድ የሚደረስበት ብልህነት የተሞለባት
ድምዳሜ አይደለም
የጥበብ ቃል ያልሆነው
የአእምሮ ብሩህነትና ብልጥነት አይደለም፡፡
አንድን እውነት እየፈለቀቁ የማሳየት ልዩ ተስጥኦ አይደለም፡፡
አስተዳደራዊ የአመራር ብልሃት አይደለም
የነገሮችን አዝማሚያ እያዩ የሚሰጥ በብልሃት የተሞላ
አይደለም
የጥበብ ቃል የሆነው
የጥበብ ቃል ለአስፈላጊው መንፈሳዊ ሥራ መንፈስ ቅዱስ
በሚመርጠው ጊዜና ቦታ የሚላክ የመለኮት ልዩ ድጋፍ እንጂ
የሁልጊዜ ንቃት አይደለም፡፡
የኃይል ስጦታዎች
የፈውስ ጸጋ ያልሆነው
ክርስቶስን የማይገልጠው የተለምዶ አደራረግ
በመጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ ያልተቀመጠ እንግዳ ልምምድ
ላለመፈወስ ስህተቱ (የአለማመን ችግር) በሕመምተኛው
ላይ ብቻ የሚያሳብበው
ተአምራት ያልሆነው
በፍጡር ብልሃት የሚከወን ምትሃት አይደለም
የአምላክን ክብር የማይገልጽ የፍጡር ትንግርት አይደለም
ከእውነተኛ አምልኮ የሚያርቅ ብርቅ ነገር አይደለም
ፍቅር የራቀው ኃይል አይደለም
ተአምራት የማድረግ ጸጋ ጠቀሜታውና ተግባራዊ ምሳሌዎች
ሀ) ልዩነታቸው
የነቢይነት ቢሮ ከሚያገለግሉት ቅዱሳን ማንነት ጨርሶ የተለየ
አይደለም፣ የትንቢት ስጦታ ግን መሣሪያ ነው (1ቆሮ 12፡ 10) ስጦታው
የነብይነት ምልክት ሳይሆን የአገልግሎት መሣሪያ ነው፡፡ ነቢይ
የሚያሰኘው ነገር የላቀ የመለኮት እጅ ይጠይቃል፡፡ በ1ኛቆሮ 14፡1
ፍልጉ የተባልነው ስጦታውን እንጂ ቢሮውን አይደለም፡፡
የነቢይነት አገልግሎት በመገለጡ እጅግ የላቀ ስለሆነ፣ ያለፈውን፣
የዛሬውንና የወደፊቱን በተለየ መንገድ ማየት መቻልን ይጠይቃል
እንዲህ ዓይነቱ ሁኔታ በ1ኛቆሮ 14፡1 ሁላችሁም ፈልጉት ከተባለው
ስጦታ ጋር በፍጹም ይለያል፡፡ በሌላ በኩል የትንቢት ስጦታ ከልሳን ጋር
ተወዳድሯል፡፡ ይህም መሣሪያነቱን ብቻ ያመለክታል (1ኛቆሮ 14፡5)፡፡
ነቢይነት መሪነትን የሚያካትት ሲሆን የብሉይም ሆነ የአዲስ ኪዳን
የመጀመሪያዎቹ ነቢያት አመራር በመስጠት አገልግለዋል፡፡ በተለይ
የብሉይ ኪዳን ነቢያት የፓለቲካ አመራር ጭምር እስከ መስጠት
ያገለገሉበትን ሁኔታ በእግዚአብሔር ቃል ውስጥ እንመለከታለን፡፡
በአዲስ ኪዳን ግን የትንቢት መልእክት የሚያመጡ ሰዎች መልእክቱን
የእርዳታ ጸጋ ጠቀሜታ
የታመሙ እንዲታወሱ፣ የተራቡ እንዲጎርሱ፣ያጡ እንዲታሰቡ፣
ብቸኞች እንዲከበቡ፣ የተራቆቱ እንዲለብሱ ያለቀሱ እንዲዳሰሱ የዚህ
ስጦታ ጠቀሜታ እጅግ የጎላ ነው፡፡ ይህንን የሚያደርጉት በችሎታ
ሳይሆን ከመንፈስ ቅዱስ በሚገኝ ስጦታ ነው፡፡ ይህንን ስጦታ በተፈጥሮ
ከሚገኝ ገራገርነት ርህሩህነት ጋር በማጣመር የጸጋውን ተአምራዊ
ተፈጥሮ ማሳነስ ተገቢ አይሆንም፡፡
መምከር ያልሆነው
መስበክ አይደለም፣ በስብከት ጊዜ በአብዛኛው ሰባኪው
ሰሚው የሚሰበከውን እውነት እንዲቀበል መገፋፋት
ይፈጸማል በምክር ጊዜ አውራው ማሳመን ሳይሆን አማራጭ
ማሳየት ነው፡፡
ትዕዛዝ መመሪያ መስጠት አይደለም፣ በድንጋጌ የተሞላ
አይደለም ከተመካሪው ችግር ጋር ራስን ማቆራኘት ነው፡፡
ማስተማርና ነገሮችን መተንተን አይደለም፣ የተመካሪው
ዓለም ውስጥ በመገኘት አብሮ ነገሮች ለማየት መሞከር ነው
መገሰጽም አይደለም፣ የተሳሳተን ሰው ብርሃን በመስጠት
ለማረም ጥረት ማድረግ አይደለም፡፡ ይልቁንም ራሱን
እንዲያይ መስተዋት ሆኖ ማገልገል ነው፡፡
መስጠት ያልሆነው
አባካኝነት አይደለም፣ ጥሪትን ፍላጎትን ባላገናዘበ መንገድ
መበተን አይደለም፤
ማባበያ አይደለም፣ የሰጪውን አጀንዳ ለማስፈጸም የሚውል
ገጸ በረከት አይደለም፡፡
የታይታ ትእይንት አይደለም፣ አድራጊውን ሳይሆን ፈጣሪን
ብቻ ለማሳየት የሚውል ድርጊት ነው እንጂ ሰዎች አንቱ
እንዲሉን የሚከናወን የእዩልኝ እንቅሰቃሴ አይደለም፡፡
4.2 ነቢይነት
ምዕራፍ 1
የውይይት ጥያቄዎች
1. በዚህ ክፍል ከተጠቀሱት ሌላ ከማንነቱ ጋር በሚያያዝ
መንገድ መንፈስ ቅዱስ ያደርጋቸዋል የሚባሉት ነገሮች ምን
ምን ናቸው?
2. በእናንተ እይታ የተፈጥሮአዊና የመንፈሳዊ ስጦታ ልዩነት
መመሳል ምኑ ላይ ነው?
ምዕራፍ 2
የውይይት ጥያቄ
የመገለጥ ስጦታዎች
1. የመገለጥ ስጦታዎችን በዚሕ ሥም እንዲጠሩ ያደረጋቸው ነገር
ምንድነው? ትክክለኛ ነው ብላችሁ ታስባላችሁ?
2. በዕውቀት ቃልና በጥበብ ቃል መካከል ያለው ልዩነትና
ተመሳሳይነት ምንድነው?
3. በእውቀት ቃል አማካኝነት ለሚመጡ ፈውሶች የሩቅ ጊዜ
ቀጠሮ አያሻቸውም ሲባል ምን ማለት ነው? ሰዎች
ባልተፈወሱ ጊዜ ስላላመናችሁ ነው የሚባለውን ማብራሪያ
እንዴት ታዩታላችሁ?
4. መናፍስትን መለየት የአጋንንት ዓለም ከመረዳት ጋር ብቻ
ማያያዝ ምን ዓይነት አደጋ አለው?
5. እነዚህ ጸጋዎች በቤተ ክርስቲያን በሙላት እንዲታዩ ምን
መደረግ አለበት?
የማነቃቂያ ስጦታዎች
1. ልሣን አብዛኛው የሚለማመደው ሆኖ ሌሎች ጸጋ በብዛት
አለመታየታቸው ችግሩ ከምን የመነጨ ነው?
2. ቀጥታ ትንቢት መናገርና ልሣን ተርጉሞ መልእክት ማምጣት
ልዩነታቸው ምንድነው?
3. ትንቢትና እውቀት ለወደፊት መልእክት ሲተላለፍባቸው
አንዱን ካንዱ ለመለየት የሚቻለው እንዴት ነው?
4. ትንቢት ከወደፊት ጋር የተያያዘው ከመናገር ጋር የተሳሰረ ነው
የሚለውን አባባል እንዴት ታዩታላችሁ?
ምዕራፍ 4
የውይይት ጥያቄዎች
1. ሐዋርያት በዘመናችን አሉ? ካሉስ የት? መለያቸውስ ምንድነው?
2. ነቢያት በዘመናችን አሉ? ከመጽሐፍ ቅዱሳዊ መገለጫቸው አኳያ
ከቤተ ክርስቲያን አድማስ ያለፈ ተጽእኖ አላቸው ? ካሉስ የት?
3. በወንጌላዊነት የረጅም ጊዜ አገልግሎት ወደ መጋቢነት የማደጉ
ልምምድ አደጋው ምንድነው? ከአንዱ ጸጋ ወደ ሌላው ይታደጋል?
4. በእረኛውና በአስተማሪው ጸጋ መካከል ያለው ልዩነት
ምንድነውከአንዱ ጸጋ ወደ ሌላው ይታደጋል? አስተማሪ እረኛ
ሊሆን ይችላል? እረኛስ አስተማሪ?