Professional Documents
Culture Documents
10
10
መግቢያ
የነገር ሁሉ ፍጻሜ
የንጉሥ ካህናት
➢ዓለም ሳይፈጠር፥ በፊቱ ቅዱሳንና ነውር የሌላችሁ በፍቅር ትሆኑ ዘንድ በክርስቶስ
መረጣችሁ። (ኤፌሶን 1፡4)
➢ በዚህ ዓለም ያለው ኑሮኣችሁ ሲያበቃም፣ ከሁሉም የላቀ ክብርና ውበት ያለው
ብሎም በሰው ልብና አእምሮ ያልታሰበ የዘላለም ሥፍራ አዘጋጅቶላችኋል፡፡(ራዕይ
ምዕራፍ 22፡1-5)
እስከዚያ ድረስ አንድ ከሁሉም በላይ በጣም አስፈላጊ የሆነ ነገር ማድረግ
ትችላላችሁ፡፡ ዮሐንስ 15: 4-5 እናንብብ. (ጥቅሱ ይነበብ)
ኢየሱስ በርሱ እንድትኖሩ ይጠይቃችኋል፡፡ ያለ ኢየሱስ ምንም ልታደርጉ
አትችሉም፤ ምንም ዓይነት ዘላቂ ፍሬ ሊያፈራ የሚችል ነገርን ኣታደርጉም፡፡
ኢየሱስ የወይን ግንድ ነው፤ እናንተ ቅርጫፎች ብቻ ናቸው፡፡
ፍሬውን የሚያፈራ ቅርንጫፍ አይደለም፤ ቅርንጫፍ ከግንዱ ውስጥ
የሚመጣውን የወይን ዕፅ ፈሳሽ ምግብ የሚተላለፍበት ነው!
የክርስትና ሕይወት የሚሠራው እንዲህ ነው፤ ራሳችን ፍሬን ማመንጨት
(ልንሰጥ) አንችልም፣ በእኛ ውስጥ የሚፈሰው መንፈስ ቅዱስ ብቻ ነው ፍሬን
የሚያፈራው!
መንፈስ ቅዱስ በውስጣችሁ እንዲፈስላችሁ በክርስቶስ ኑሩ!
ሀ) "ከክርስቶስ ጋር መሰቀል"?