You are on page 1of 30

የኤፌሶን መጽሐፍ

ከምእራፍ 1-6
የኤፌሶን መጽሀፍ መግቢያ

የመልእክቱ ጸሀፊ እራሱ ጳውሎስ መሆኑ መልእክቱ ይገልጻል 1፣1 እና 3፣1 ይህ መልእክት ኤፌሶንን ጨምሮ
ወደ ሌሎች ከተሞች እንዲደርስ የተጻፈ ዘዋሪ ደብዳቤ ሳይሆን ቸአይቀርም 1፣1፣15 6፣21-23 ፓውሎስ
የቆላስያስን መጽሀፍ በጻፈበት ጊዜ በ60 አመተ አለም ግድም በሮም እስር ቤት እያለ ይህንን ደብዳቤ
ጽፎታል፤ 3፣1 እና 4፣1 6፤20

የኤፌሶን ከተማ በትንሹ እስያ በዛሬዋ ቱርክ ምእራፍ ክፍል ከሚገኙት ከተሞች እጅግ የታወቀች ከተማ
ነበረች። ከተማዋ ወደ ኤዥያን ባህር በሚፈሰው የካይስተር ወንዝ ላይ አንድ ወደብ ነበራት ታላላቅ የንግድ
መንገዶች አቋርጠው በሚያልፉበት ቦታ ላይ የተመሰረተች ስለሆነች የንግድ ማእከል ለመሆን በቅታለች።

ግሪኮች አርጤምስ ሮማውያን ዲያና የሚሏት ጣአኦት አምላክ ቤተመቅደስ በዚችው ከተማ ይገኝ ነበር።
ጳውሎስ በኤፌሶን ሶስት አመት ያህል ተቀምጦ የወንጌል ስርጭት ማእከል አድርጓት ነበር ሐዋርያት 19፤10
በዚያን ጊዜ የነበረችው ቤተክርስቲያን በአንድ ወቅት አድጋ ተስፋፍታ ነበር በኋላ ግን በራእይ 2፤1-7 ያለው
ማስጠንቀቂያ ተሰጣት

የመልእክቱ ይዘት እንደ ሌሎቹ የጳውሎስ መልእክቶቸ የስህተት ትምህርት ወይንም ነቀፌታን በተመለከተ
የሚያወሳው ነገር የለም። መልእክቱን ሲጽፍ የአንባቢዎችን አድማስ በማስፋት የእግዚአብሔርን
የዘላለም እቅድና የጸጋውን ጥልቀት ይበልጥ እንዲረዱና እግዚአብሔር ለቤተክርስቲያን ያለውን ታላቅ ግብ
እንዲያደንቁና በዛ ውስጥ መኖር እንዲችሉ ነው ሲሆን ቅዱሳን በክርስቶስ ያላቸውን ህብረትና ማንነት
እንዲያውቁና እርስ በእርስም እንደ አካል አንድነትን በመጠበቅ እንዴት መገንባትና ማደግ እንዳለባቸው
ለማስተማር ነው።

መጽሀፉን ቤሁለት መክፈል እንችላለን


፩ኛ ከምእራፍ 1-3 ከክርስቶስ ጋር ስላለን ህብረት
፪ኛ ከምእራፍ 4-6 የክርስቶስ አካል ስለሆነች ቤተክርስቲያን ስለሚኖረን አንድነት
ክፍል 1 (ከምእራፍ 1-3)
ምእራፈ 1 ከቁጥር 1-14

በዛሬው ትምህርታችን እግዚአብሔር መቼና በማን ለምንስ እንደመረጠን እንማራለን

የመወያያ ጥያቄዎች

1. መልእክቱ የተጻፈው ለማን ነው?

2. እግዚአብሔር እኛን አማኞችን መቼ፣ በምን፤ ለማን እንደመረጠን የሚገልጹትን ሀሳቦች ዘርዝር

3. በዚህ ክፍል ውስጥ በክርስቶስ ኢየሱስ ያገኘናቸውን ጥቅሞች ዘርዝር

4. በቁጥር ሶስት መሰረት ስለበረከት (ስለመባረክ) የተረዳኸውን ሀሳብ ግለጽ

5. በተነበበልህ ክፍል ውስጥ እግዚአብሔር ልጆቹ እንድንሆን የጸጋው ክብር ተካፋዮች እንድንሆን የሚስጥሩና
የመንፈሳዊ በረከት ሁሉ ተካፋዮች እንድንሆን ያደረገው በክርስቶስ በኩል እንደሆነ ተገልጿል፤ በክርስቶስ
ተብሎ በተደጋጋሚ ከተጻፈው ሀሳብ የምትማረው (የምትረዳው) ዋነኛውን ሀሳብ ግለጽ?

6. ከዚህ ካጠናነው ክፍል የተማርከው ምንድነው?

7. በተማርከው ትምህርት መሰረት የምትወስነው ውሳኔ ምን መሆን አለበት?

ማጠቃለያ ዛሬ ከክርስቶስ ጋር ህብረት በማድረግ የሚገኙትን ጥቅሞችና በረከቶች ተምረናል። ክርስቶስ የጁሉ ነገር
ቁልፍ እንደሆነ ካወክ ከክርስቶስ ጋር ፍጹም የሆነ ህብረት እለት እለት እንዲኖርህ ቃሉን በማጥናት፤ በጸሎት፤
ያወከውን እውቀት በተግባር በመተርጎም ትጋ
የእግዚአብሔር አብ ስራ፤ መምረጥ (ኤፌሶን 1፤3-6)
የእግዚአብሔር ወልድ ስራ፤ መዋጀት (ኤፌሶን 1፣7-12)
የመንፈስ ቅዱስ ስራ፤ ጥበቃ (ኤፌሶን 1፤13፣ 14

አማኞች በክርስቶስ የተቀበሉት በረከት

በረከት ቁጥር 3

መመረጥ ቁጥር 4

አስቀድሞ መወሰን ቆጥር 5

ልጅ መሆን ቁጥር 5

ተቀባይነትን ቁጥር 6

እኔ በክርስቶስ ቤዛነትን ቁጥር 7

ይቅርታን ቁጥር 7

እውቀት ጥበብና ማስተዋልን 8-9

የርስት ባለቤትነት ቁጥር 11

በመንፈሱ መታተም ቁጥር 13

የርስት መያዣ ቁጥር 14


ጥናት ሁለት

ኤፌሶን 1፣15-16

ሀዋርያው ጳውሎስ ለኤፌሶን አማኞች


የመወያያ ጥያቄዎች

1. በቁጥር 15 እና 16 መሰረት ሀዋርያው ጳውሎስ ለኤፌሶን አማኞች እንዲጸልይ


ያነሳሳው ምክንያትና የጸሎቱን ይዘት ግለጽ (ዘርዝር)

2. በቁጥር15 መሰረት የኤፌሶን አማኞች እምነታቸው የተገለጸበትን መንገድ ግለጽ?


በተግባር ሲሆን ይህም ለሌሎች ባላቸው ፍቅር ነው

3. ለቅዱሳን ሁሉ ስላላችሁ ፍቅር ከሚለው ሀረግ ስለኤፌሶን አማኞች ፍቅር


የምትረዳው ምንድነው?

4. በዚህ በቁጥር 15 መሰረት ስለ ኤፌሶን አማኞች የተገለጠውን እምነት ተወያዩበት

5. በእምነትና በፍቅር መካከል ያለውን ግንኙነት ተወያዩበት


6. የኤፌሶን ክርሰቲያኖች በስራ የተገለጸው እምነታቸው አንደኛው ውጤት ሀዋርያው
ጳውሎስ እግዚአብሔርን እንዲያመሰግን አድርጎታል ሌላ ውጤት የሚያስከትል ከሆነ
ተወያዩበት

7. ሐዋርያው ጳውሎስ የኤፌሰን አማኞች ተመልክቶ እግዚአብሔርን እንዳመሰገነ


ያንተን ህይወት አይተው ሌሎች እግዚአብሔርን ያመሰግናሉ ብለህ ታምናለህ?
እግዚአብሔር እንዲመሰገን ማድረግ ያለብህ ነገር ምንድነው?

8. የኤፌሶን አማኞች ቅዱሳንን ያለ ገደብ ይወዱ እንደነበር አንተም ቅዱሳንን ሁሉ


ለመውደድ ከኔ ይጠበቃል ብለህ ታምናለህ? ከሆነስ ለቅዱሳን ሁሉ ያለህን ፍቅር
እንዴት ገለጽከው፤ መግለጽ ካልቻልክ ልትወስደው ያለኸው እርምጃ ምንድነው?

ማጠቃለየቅር

በዛሬው እለት የኤፌሶን አማኞች በክርስቶስ ያላቸውን እምነት ቅዱሳንን ሁሉ


በመውደድ እንደገለጹት ተምራችኋል፤ ዛሬም እናንተ እምነታችሁን በተግባር ለመግለጽ
በተማራችሁት መሰረት ፍቅራችሁን ያለ አድሎና ገደብ ለሰው ሁሉ መልካምን ነገር
በማድረግ በዚያም ሰዎች አምላካችሁን እንዲያመሰግኑ ትጉ።
ጥናት 3
ቁጥር 17-19

በዛሬው ትምህርታችነ እግዚአብሔርን በበለጠ በማወቅ በክርስትና ህይወት የበለጠ


እንድናድግ እንማራለን

የመወያያ ጥያቄዎች
1. ከቁጥር 15_23 ጳውሎስ የጸለየላቸውን ሶስት የጸሎት ሀሳቦችን ዘርዝር

2. ሐዋርያው ጳውሎስ ስለኤፌሶን አማኞች በሰማው ነገር አመስግኖ ነገር ግን


ስለናንተ መጸለዬን አላቋርጥም ያለው ለምንድ ነው?

3. እግዚአብሔርን የምናውቅበት መንገዱና ጥቅሙ ምን እንደሆነ ግለጽ

4. በክርስቶስ ያለንን ተስፋ ለማወቅ የልቦናችን አይኖች መብራት ለምን አስፈለገ?

5. በዚህ ክፍል በቁጥር 18 ላይ የተገለጸውን ጥበብ ከያእቆብ 3፤17 ጋር በማነጻጸር


ተወያዩበት

6. ለክርስቶስ ላመኑት የተሰጠው ሀይል ምን አይነት ነው?

7. ይህ ታላቅ ሀይል ለቅዱሳን ነየተሰጠው ለምንድነው

8. በመንፈሳዊ ህይወት ለማደግ ምን ተማርክ?

ማጠቃለያ
እግዚአብሔርነ በበለጠ ለማወቅ የሚረዳህን ጥበብና መገለጥ እንዲሰጥህ።
እንዲሁመ በእርሱ የተጠራህበትን ተስፋ ምን እንደሆነ ታውቅ ዘንድ የልቦናዎችህ
አይኖች እንዲበሩና ከሁሉም በላይ ታላቅ የሆነውን ሀይሉን እንድታውቅ እለት እለት
በዚህ ሀሳብ በመጸለይና ቃሉን በማሰላሰል ትጋ
ጥናት 4

ምእራፍ 1 22-23
በዛሬው እለት በክርስቶስና በቤተ ክርስቲያን መካከል ስላለው ግንኙነት እንማራለን።
የመወያያ ጥያቄዎች

1. እግዚአብሔር ክርስቶስን ከሙታን ካስነሳው በኋላ የሆኑትን ነገሮች ዘርዝር?

2. ክርስቶስ በሰማያዊ ስፍራ በቀኙ አስቀመጠው ሲል ስለ ክርስቶስ ምንን ያመለክታል

3. ሁሉን ከእግሩ በታች አስገዛለት ሲል ሁሉን የሚለው ምንን ያጠቃለ ነው?

4. እራስ እንዲሆን ለቤተ ክርስቲያን ሰጠው የሚል ሀረግ እናነባለን እራስ ሲል ምን


ማለቱ እንደሆነ ተነጋገሩበት

5. እርሱ አካሉና ሁሉን በሁሉ የሚሞላ የክርስቶስ ሙላቱ ናት ከሚለው ሀረግ አካሉና
የእርስ ሙላት የሚለውን ሀሳብ ተወያዩበት

6. ሁሉን አስገዛለት የሚለው እያንዳንዳችንን ይጠቀልላል መክንያቱም በመጀመሪያ


ለክርስቶስ መገዛት ስላለብን እና ለክርስቶስ ያልተገዛ ህይወት ለሌሎች መገዛት
ስለማይችል ነው። ታዲያ ዛሬ ለቤተክርስቲያንና ወይንም እርስ በእርስ መገዛት
ያቃተን ለክርስቶስ ያለመገዛት ውጤት ነው ብለህ ታምናለህ ወይ?

7. ክርስቶስ ሙላቱ የሚገለጸው በቤተክርስቲያን በኩል ነው ታዲያ በኔና ባናንተ


ህይወት ክርስቶስ በሙላት እንዳይገለጽ ያደረገው ነገር ምንድነው? በሙላት መገለጽ
የሚችለውስ እንዴት ነው?

ማጠቃለያ
በዘህ እለት የተማርነው ለክርስቶስ ሁሉም ነገር እንደተገዛለትና እግዚአብሔርም
ክርስቶስ ለቤተክርስቲያን ራስ አድርጎ በመስጠት ቤተክርስቲያን ደግሞ የክርስቶስ
የሙላቱ መገለጫ መሆኗን ነው፤ ስለዚህም አንተም ደግሞ በክርስቶስ አካል ውስጥ
ስላለህ ጌታ ባስቀመጠህ ቦታ እሱን ለመግለጽ ድርሻህን ተወጣ
ጥናት 5
ምእራፍ 2፣1-10
በዛሬው ጥናታችን እግዚአብሔር እኛን ከምን እንዳዳነን፣ እንዴት እንዳዳነንና፤ ለምንስ
እንዳዳነን የምንማርበት ክፍል ነው።

1. ከቁጥር 1-3 ባለው ክፍል ስለቀድሞ ህይወታችን የተጻፈውንና እኛን ከምን


እንዳዳነን የተጻፉትን ሀሳቦች ዘርዝር

2. ስላለፈው ህይወታችን ሲናገር ከሀጢያት ከበደል ከስጋ ከክፉ ምኞት፤ ከሞትና


ከሰይጣን አዳነን ይላል። ይህንን ሀሳብ እንዴት ተረዳችሁት?

3. ነገር ግን እግዚአብሔር በምህረቱ ባለጸጋ ስለሆነ ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሳ


ምን አደረገልን

4. ከቁጥር 4-9 ባለው ክፍል መሰረት ደህንነትን ያገኘነው እንዴት እንደሆነ


ተወያዩበት

5. ከክርስቶስ ኢየሱስ ጋረ በሰማያዊ ስፍራ አስቀመጠን ከሚለው ሀሳብ ስለራስህ


ምን ትረዳለሀ

6. በቁጥር 10 ላይ በክርስቶስ ፈጠረን የሚለውን ሀሳብ እንዴት ትረዱታላችሁ?

7. መልካም ስራ ለመስራት በክርስቶስ ተፈጠርን ይላል ይህ መልካም ስራ ምን


እንደሆነ ተወያዩበት በግልም ሆነ በጋራ ይህንን መልካም ነገር እያደረግን ነን
ወይ?

ከምህረቱ ባለጠግነት የተነሳ በጸጋው አድኖ መልካሙን ስራ እንድትሰራ የመረጠህን


አምላክ ፈቃዱን በማድረግ አክብረው
ጥናት 6
ምእራፍ 2፤ 11-22

በዛሬው ጥናታችን በክርስቶስ ስለሚገኘው አንድነት እንማራለን

የመወያያጥያቄ
1. ስለ ኤፌሶን አማኞች የቀድሞ ማንነታቸው ሐዋርያው ጳውሎስ የገለጸውን
በዝርዝር አስፍር?

2. ሐዋርያው ጳውሎስ አሁን ያሉበትን ሁኔታ የገለጸባቸውን መንገዶች


ከቁጥር 13-22 ተመልከትና ዘርዝር

3. በአህዛብና በአይሁድ መካከል ያለው ልዩነት ምንድነው ሐዋርያውስ ይህንን


ልዩነት እንዴት ገለጸው?

4. ክርስቶስ ሁለቱን ማለትም አህዛብንና አይሁድን ያዋሀደው እንዴት እንደሆነ ነው


የተገለጸው?

5. የጥልን ግድግዳ በስጋው አፍርሶ በራሱ አንድን ሰው ፈጠረ የሚለውን ሀሳብ


ተነጋገሩበት

6. ዛሬ ክርስቶስ የሰራውን አንድነት እንዳንጠብቅ በፈረሰው ግድግዳ ላይ


ሰለሚገነቡት ግድግዳዎች አንሱና ተነጋገሩበት፤ ለነዚህ ችግሮች መፍትሄው
ምንድነው ብለህ ታምናለህ
7. በዚህ ክፍል ውስጥ አህዛብ ከአይሁዳውያን ጋር በክርስቶስ አንድ እንደሆኑና
እኩል ባለመብት እንደሆኑ የሚገልጹትን ሀሳቦች ከቁጥር 17-19 ያለውን
ተመልክተህ አብራራ፤ ዛሬስ በክርስቶስ የዳኑ ሁሉ ይህ የተገለጸው አይነት
አንድነትና መብት አላቸውን?

8. በሐዋርያትና በነቢያት መሠረት ላይ ታንጻችኋል፥ የማዕዘኑም ራስ ድንጋይ


ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፤ በሚለው ሀሳብ ላይ ተወያዩበት።

9. በቁጥር 20-22 እኛ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ሆነን የምንሰራው እንዴት


እንደሆነና የእግዚአብሔረ ማደሪያዎች ነን ሲል ምን እንደሆነ ተወያዩበት፤

10. በዛሬው ውይይታችን ስለ አንድነት የተማርከውን እንዴት በተግባር


መተርጎም እንደምትችል ተወያይበት

መጠቃለያ
በዘሬው ትምህርት በክርስቶስ ስለሚገኝ አንድነት ተምረሀል። ክርስቶስ በአይሁዳውያንና
በአህዛብ መሀከል የነበረውን ልዩነትና ጥላቻ በሞቱ አስወግዶ እንዴት አንድነትን
(ቤተክርስቲያን) እንደመሰረተና በዚህች አዲስ በተፈጠረችው የክርስቶስ አካል ውስጥ
ሁላችንም አንድ እንደሆንና እኩል መብት እንዳለን አውቀሀል። ዛሬ ክርስቶስ በመስቀል ላይ
ሞቶ የፈጠራትን አንድነት ለመጠበቅ እንደቃሉ በመሰረቱ ላይ በመታነጽ የጌታ ቤተመቅደስ
በመሆን ተሰራ።
ጥናት 7
ምእራፍ 3፣1-13
መግቢያ በዚህ ጥናት ውስጥ ሀዋርያው ጳውሎስ ስለተሰጠው የወንጌል አገልግሎትና
ሰለተገለጠለት የአገልግሎት ሚስጥር እንወያያለን

የመወያያ ጥያቄዎች
1. ሐዋርያው ጳውሎስ ስለተሰጠው አገልግሎት የጠቀሰውነ ግለጽ

2. ከቁጥር ሁለት እስከ አስራሶስት ስታነብ ጳውሎስ ሚስጥር ብሎ የሚናገረው ምን


እንደሆነ በሰፊው ተወያዩበት

3. አህዛብ ወደክርስቶስ እንዲመጡ ጳውሎስ የተጠቀመበት መንገድ ምንድነው?

4. ጳውሎስ የተሰጠው ጸጋ ምንድ ነበር? ይህ ጸጋ በዚህ ዘመን ለቤተክርስቲያንም


እንደተሰጠ ተገልጿል።

5. ታዲያ አሁን የቤተክርስቲያን ተግባርና ሀላፊነት ምንድነው ብለህ ታምናለህ?


ከማቴዎስ 28፤18-20 ያለውን ክፍል በማገናዘብ ተወያዩ።

6. በቁጥር 1 እና 13 መሰረት ጳውሎስ ይህንን መልክት በጻፈበት ወቅት ስለነበረበት


ሁኔታ ምን ይላል እኛስ ከዚህ ምን እንማራለን

7. ይህ ለጳውሎስና ለቤተክርስቲያን የተሰጠው የወንጌል ጸጋ በየግላችንም ሆነ እንደ


ቤተክርስቲያን እንዳይገለጽና እንዳይሰራ የሚያደርጉት እንቅፋቶች ምን እንደሆኑና
እንዴት እነዚህን እንቅፋቶች ልናስወግድ እንደምንችል ተነጋገሩበት

8. ይህንን ለቤተክርስቲያን የተሰጠ ጸጋ ዋጋ በመክፈል ለሌሎች ለማዳረስ ምን ያህል


ዝግጁ ነህ?

ማጠቃለያ
ጳውሎስ ይህንን ጸጋ ለአህዛብ ለማድረስ ህይወቱን እንደከፈለ፤ አንተም የተጠራህለት ዋነኛ
አላማ እንደሆነ አውቀህ ይህንን የእግዚአብሄርን የጸጋ ወንጌል ለሌሎች በቃልና በስራል ትጋ
ጥናት 8
ከምእራፍ 3፤14-21
በዚህ ክፍል የምንማረው ጸሎት የሐዋርያው ጳውሎስ የአገልግሎት አንዱ ክፍል እንደሆነና
እኛም ያለብንን ሀላፊነት ለመወጣት ለሌሎች መጸለይ እንደሚገባን ያስተምረናል።

የመወያያ ጥያቄዎች
ሐዋርያው ጳውሎስ የጸለየው የጸሎት ዋና ሀሳቦች በምንና በምን ላይ ያተኮረ ነው?

1. እነዚህን ጸሎቶች እንዲጸልይ የተነሳሳበት ዋና ምክንያት ምንድነው?

2. የጳውሎስ አንደኛው ጸሎት በውስጥ ሰውነት እንዲጠነክሩ ነው ይህ ምን ማለት


ነው? የውስጥ ሰውነት የሚጠነክርበት መንገዱ ምንድነው?

3. ፕውሎስ ለኤፌሶንን አማኞች ክርስቶስ በልባቸው ውስጥ በእምነት እንዲኖር


እጸልያለሁ ሲል፤ ክርስቶስ በአማኝ ህይወት ውስጥ በእምነት መኖሩ የሚታወቀው
እንዴት ነው?

4. ሐዋርያው ጳውሎስ ከጸለየው ጸሎት ለኤፌሶን አማኞች ሊኖራቸው የፈለገው ፍቅር


ምን አይነት እንደሆነ አስረዳ

5. ለኤፌሶን አማኞች የክርስቶስን ፍቅር በማወቅ ይበረቱ ዘንድ ሲጸልይላቸው ለአንድ


አማኝ ይህ አይነት ፍቅር ማወቁ አስፈላጊነቱ ምንድ ነው?

6. በቁጥር 20 እና 21 መሰረት አማኞችን ለጸሎት ለማበረታታትና እንዲተጉ ስለጸሎት


ከገለጸው ሀሳብ ዋነኛ ነገር ምንድነው?

ማጠቃለያ
ዛሬ ከጳውሎስ ፀሎት በተማርከው መሰረት ያንተም ሆነ የሌሎች ውስጣዊ ሰውንት
እንዲጠነክር፤ክርስቶስ በእምነት በልባችሁ እንዲኖርና ፍቅሩም በሙላት በአንተና
በአመኑት ሁሉ እንዲኖር፤ በግል ህይወትህም ሆነ በሌሎች ህይወት ውስጥ የጎደሉትን
ነገሮች በማየት በእግዚአብሔር ፊት በፀሎተ ትጋ።
ክፍልሁለት
ከምእራፍ አራት እስከ ስድስት
የዛሬንውን ጥናታችንን ከመጀመራችን በፊት ስለዚህ ክፍለ ማለት ከምእራፍ አራት እስከ
ስድስት ውስጥ ሀዋርያው ጳውሎስ የስተማረውን ዋና ሀሳብ እንመልከት። በክፍል አንድ
ጥናታችን ከምእራፍ አንድ እስከ ሶስት እንደምታስታውሱት አማኞች ከክርስቶስ ጋር
ስላላቸው አንድነትና እንዴት ክርስቶስ ቤተክርስትያንን እንደመሰረተ ተምረናል።በዚህ ክፍል
ሁለት ከምእራፍ አራት እስከ ስድት ባለው ክፍል ደግሞ በቅዱሳን መሀከል በቤተክርስትያን
ሊኖር ስለሚችለው አንድነትመ እንዲሁም በባልና በሚስት፤ በወላጆችና በልጆች
በተጨማሪም በአሰሪና በሰራተኛ መካከል ሊኖር ስለሚገባው ግንኙነትና ክርስቶስ
የመሰረተውን አንድነታችንን (ቤተክርስትያንን) እንዴት መገንባት ወይንም ማነፅ
እንደሚገባን የሚያስተምር ክፍል ሲሆን በመጨረሻም የእግዚአብሔርና የህዝቡ ጠላት
የሆነውን ሰይጣንን እንዴት መዋጋት እነደሚገባን ንማራለን።
ጥናት ዘጠኝ
ምእራፍ 4:1-6
መግቢያ: በዛሬው ጥናታችን በክርስቶስ ያለንን አንድነት ወይንም ቤተክርስትያንን
ለማነፅ(ለመገንባት) መሰረታዊና ዋነኛ ስለሆኑት ጠቃሚ ነገሮች እንማራለን።
የመወያያ ጥያቄዎች
1. በቁጥር አንድ እስከ ሶስት መሰረት ሀዋርያው ጳውሎስ ለኤፌሶን አማኞች
እንዲያደርጉት ያዘዛቸውን ነገሮች ዘርዝር።

2. ከቁጥር አራት እስከ ስድስት የተዘረዘሩትን ለአንድነታችን እንደ መሰረት ሊሆኑን


የሚችሉትን ዋና ነገሮች የትኞቹ ናቸው።

3. ጳውሎስ በተጠራችሁበት መጠራት ተመላለሱ ሲል ምን ማለቱ ነው?

4. በዚህ ክፍል መሰረት እንዴት ነው በክርስቶስ ያገኘነውን አንድነታችንን መጠበቅ


የምንችለው?

5. በሰላም ማሰሪያ የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ የሚለውን ሀሳብ እንዴት


ትረዳዋለህ?
6. ለአንድነታችን እንቅፋት የሚሆኑ ነገሮች ምንድናቸው ትላላችሁ?

7. አንድ ተስፋ፣ አንድ አካል፣አንድ መንፈስ፣አንድ ጌታ፣አንድ ሀይማኖት፣አንድ


ጥምቀትና አንድ አምላክ በሚሉት ሀሳቦች ላይ ተወያዩ።

8. በጥያቄ ቁጥር አምስት ውስጥ የተዘረዘሩት ነገሮች ለአንድነታችን እንዴት


ሊጠቅሙን ይችላሉ?

9. በዛሬው ትምህርት መሰረት ቤተክርስቲያንን ለማነፅ የሚጠበቅብህን ለመፈፀም


በግል የተማርከውን በአጭሩ ግልፅ።

ማጠቃለያ
በክርስቶስ የተገኘኸውን አንድነት ለመጠበቅ ዛሬ በተማርከው መሰረት በትህትና፣
በየዋህነት፣በትእግስት፣እርስ በርስ በመፋቀር የተጠራህበትን መጠራት የሚያስመሰግን
ኑሮ በመኖር የሚቻልህን ሁሉ በታማኝነት ፈፅም።
ጥናት አስር
ምእራፍ 4 ፣ 7- 16
መግቢያ
በዛሬው ጥናታችን ክርስቶስ ለቤተክርስትያን ስለ ሰጣቸው ስጦታዎች እንዲሁም
የስጦታዎቹን አስፈላጊነትና ጥቅም እንማራለን።
የመወያያ ጥያቄዎች
1. በዚህ ክፍል ውስጥ ጌታ የሱስ ክርስቶስ ለቤተክርስትያ የሰጠውን ስጦታዎችንና
ጥቅማቸውን ዘርዝር።

2. የስጦታዎቹ አነዱ ጥቅም ሁላችን ክርስቶስን ወደ ማወቅ ሙላት እንድንደርስ ነው።


ሁላችን የሚለው ሀሳብ የሚያስተምረን ዋና ነገር ምንድን ነው?በቁጥር13 ውስጥ
ካለው አካል ሁሉ ከሚለው ሀሳብ ጋር አብራችሁ ተወያዩበት።

3. ወደ ላይ በወጣ ጊዜ፣ምርኮ ማረከ፤ ለሰዎችም ስጦታን ሰጠ ተብሎ ስለክርስቶስ


የተፃፈውን ሀሳብ እንዴት ትረዳዋለህ? ከቆላስያስ ምእራፍ ሁለት ቁጥር
አስራአምስት ጋር አንብባችሁ ተወያዩበት።

4. በቁጥር 11 ላይ የተዘረዘሩት ስጦታዎች አሁን በዚህ ዘመን ባለችው ቤተክርስትያን


ውስጥ ይኖራሉ ብለህ ታምናለህ? ካሉስ ለቤተክርስትያን መታነፅ ሊኖራቸው
የሚችለውን ድርሻና ጠቃሚነትን ምንድነው።
5. የስጦታው ሰጪ ማን ነው? የተሰጠውስ ለማን ነው?

6. በቁጥር 7ና 11 በተጨማሪም 1ኛ ቆሮንጦስ ምእራፍ 12ን ሙሉ በማንበብ


ስለስጦታዎቹና አሰጣጣቸው ተወያዩበት?

7. የተሰጠንን መንፈሳዊ ስጦታዎችን ተጠቅመን ቤተክርስትያንን ለማነፅ በመንፈሳዊ


ህይወታችን ማደግ ለምን ይጠቅማል?

8. በቤተክርስትያናችን ውስጥ የተሰጡንን ስጦታዎችን በአግባብ አለመጠቀማችን


በክርስትና ህይወታችን አለማደግ ውጤት ነው ብለህ ታስባለህ?

9. ዛሬ አንተ የተሰጠህን ስጦታምን እንደሆነ ለይተህ አውቀሀልን?በዚህስ በተሰጠህ ልዩ


ስጦታ በመጠቀም ቤተክርስትያንን ለማንፅ ድርሻህን በታማኝነት እያደረግህ ነው?

ማጠቃለያ
በክርስቶስ ያገኘነውን አንድነት ተግቶ የመጠበቅ የሁላችን ድርሻና ሀላፊነት ነው።
ለዚህም ይረዳን ዘንድ ክርስቶ እየሱስ ይህቺ በደሙ የዋዧትን አካሉ የሆነችውን
ቤተክርስትያንን በሚገባ እንድትታነፅ የተለያዩ የፀጋ ስጦታዎችን ሰቷል።አንተም
የሚገባህ ለመፈፀም የተሰጠህ የፀጋ ስጦታ ምን እንደሆነ ለይተህ በማወቅ ድርሻህን
በታማኝነት እለት እለተ በመፈፀም ትጋ።ይህንንም ሀላፊነት በሚገባ መፈፀም
የምንችለው በትህትና፣በየዋህነት፣በትእግስት፣እርስ በርስ በመዋደድና በመንፈሳዊ
ህይወታችን ስናድግ ነውና ይህንን ሁሉ ለማድረግ ትጋ።
ጥናት 11
ከጥናት አስር የቀጠለ
መግቢያ በዛሬው ጥናታችን በክርስትና ህይወታችን እንዴት ማደግ እንዳለብንና
ማደጋች በቤተክርስቲያን ላይ የሚያስከትለውን ውጤት ምን እንደሆነ እንማራለን።
የመወያያ ጥያቄዎች
10. የእያንዳንዳችን መንፈሳዊ እድገት ቤተክስትያንን እንዴት ማነፅ ይችላል?

11. በቁጥር 14 መሰረት በመንፈሳዊ ህይወት አለማደግ ሊያስከትለወ በሚችለው


ችግር ላይ በተጨማሪም በቤተ ክርስቲያን ላይ ሊያመጣ የሚችለውን ችግሮች
ተወያዩባቸው።
በተለያየ የሀሰት ትምህርቶች ለመወሰድ ያጋልጠናል፤ ቤቤተ ክርስቲያንም ላይ
የሚያስከትለው ችግር ጤናማ እንዳትሆን ያደርጋታል፤

12. እድገታችን ሙሉ ሰው በመሆን በክርስቶስ ወዳለው ፍፁምነት ደረጃ


እስክንደርስ ነው(ቁ.13)።በመጀመሪያ ሙሉ ሰው በሚለው ሀሳብና ቀጥሎም
የእድገታችን ምሳሌ(ሞዴል) ክርስቶስ የሆነበትን ምክንያት በሰፊው ተወያዩበት።

13. ቤተክርስቲያንን ለማነፅ እውነትን በፍቅር መናገርና ራስ ወደ ሆነው ክርስቶስ


በነገር ሁሉ ማደግ አለብን ቁ.15 ።

14. በነገር ሁሉ ማደግ የሚለው ሀሳብ ምን ያስተምረናል?


15. ጳውሎስ የሰውን አካል ምሳሌ አድርጎ ያስተማረው ስለምንድነው?

16. በቁጥር 16 መሰረት እያንዳንዳችን እንደአካሉ ብልቶች ስራችንን መፈፀም


የምንችለው እንዴት ነው? ከ1ኛ ቆሮንጦስ ምእራፍ 12 ስለ አካል ብልቶች
የሚናገረው ክፍል ተመልክታችሁ በማገናዘብ ተወያዩበት።

17. የአካሉ ብልቶች ተግባራቸውን በሚገባ ማከናወን የሚያስከትለውስ ውጤት


ምንድነው?

18. ቤተክርስቲያን ሙሉ እድገትና የተሰጣትን ሀላፊነት በሙላት መፈጸም


የምትችለው በአካል ውስጥ ያሉት ብልቶች ሁሉ ተግባራቸውን ሲፈጽሙ ብቻ
እንደሆነ ተምረሀል። አንተስ በእንድ አካል ውስጥ እንዳለ ብልት መሆንህን ተረድተሀ
ካንተ የሚጠበቅብህን በታማኝነት እየፈጻምክ ነወይ?

ማጠቃለያ
ለቤተክርስቲያን መታነፅ እንዲሁም ወደ ክርስቶስ ሙላት በማደግ የተሰጣትን ሀላፊነት
መፈፀም የምትችለው እያንዳንዱ የአካል ብልቶች የራሳቸውን ተግባር ተግተው በታማኝነት
ሲፈፅሙ ብቻ ነው። ይህም ሊሆን የሚችለው ብልቶች ሁሉ ወደ ክርስቶስ ሙላት ማደግ
ሲችሉ ነው።ስለዚህ የተሰጠንን ፀጋ በሚገባ ተጠቅመን ቤተክርስትያን ትታነፅ ዘንድ
ሁላችንም በክርስቶስ እርስበርስ ተገጣጥመን ሙላት ወደሆነው ወደ ክርስቶስ እንደግ።
ጥናት 12
ምእራፍ 4፤17-32
በዚህ ክፍለ ትምህርት ላይ አካልን ለማነጽና ለቤተ ክርስቲያን እድገት በክርስቶስ ስለሚገኝ
አዲስ ማንነት እንማራለን፤

1. ጳውሎስ የጠቀሳቸውን አህዛብ የተመላለሱበትን መንገድ፤ ዘርዝር

2. ከቁጥር 20 ጀምሮ እንደተገለጸው አማኞቹ ይከተሉት ዘንድ የሚገባው መንገድ


ዘርዝር፤

3. (ከቁጥር 17-19 እና ቁጥር 31) በዚህ ክፍል መሰረት ከእግዚአብሔር መራቅ


የሚያስከትለውን ውጤት ተወያዩበት

4. ከቁጥር 20 -24 ያለውን ተመልክተህ ከርስቶስን ማወቅ የሚያስከትለውን ውጤት


ተወያዩበት

5. ሐዋርያው አዲሱ ሰውና አሮጌው ሰው ብሎ የጠቀሰው ማንን ነው?

6. የአሮጌው ሰው ባህርይና ስራዎችን እንዲሁም የአዲሱን ሰው ባህርይና ስራዎች


ዘርዝር

7. አሮጌውን ሰውነት አስወግዳችሁ አዲሱን ሰውነት ልበሱት ይላል እንዴት ነው ይህንን


ልናደርግ የምንችለው?

8. በዛሬው ትምህርት አኳያ እራስህን ስትመለከት በህይወትህ ጎልቶ የሚታየው የትኛው


ሰው ነው።
ማጠቃለያ፤
በዛሬው ትምህርታችን የአሮጌውና የአዲሱን ሰው ማንነት፤ ተጽእኖና የሚያስከትለውን
ውጤቶች፤ ተምረሀል ስለዚህ አሮጌውን ሰው እያስወገድክ አዲሱን ሰው ለመልበስ በቃሉ
የተሰጠህን መመሪያ እለት እለት በመጠቀም በተግባር ግለጽ፤ ይህንንም ብታደር
ቤተክርስቲያን በመታነጽ ወደክርስቶስ ሙላት ትደርሳለች
ጥናት 13
ምእራፍ 4፤25-32

በዛሬው ጥናታችን እርስ በእርስ በሚኖረን ግንኙነት ውስጥ የአዲሱ ሰው ባህሪ ምን


እንደሆነ እንማራለን
የመወያያ ጥያቄዎች
1. እርስ በእርስ በሚኖረን ግንኙነት አዲሱ ሰው ሊኖረው የሚገቡትን ባህርያት ዘርዝር

2. በዚህ ክፍል ውስጥ በግል ሕይወታችን ከሌሎች ጋር ያለንን ግንኙነት


የሚያበላሹብንን ነገሮች አንድ ባንድ ግለጽ

3. እነዚህ የሚገለጡ የአሮጌው ሰው ባህርያት እርስ በእርስ በቻ ሳይሆን በቤተ


ክርስቲያንም የሚፈጥሩትንም ችግሮች ተነጋገሩበት፤

4. እነዚህን አሮጌ ባርያቶች ማስወገድ የምንችለው እንዴት ነው?

5. በቁጥር 27 መሰረት ለዲያብሎስ ስፍራ ልንሰጠው የምንችለው እንዴት ነው?

6. በቁጥር 29 መሰረት እርስ በእርስ ባለን ግንኙነት በንግግራችን አዲሱን ሰው መግለጽ


ያለብን እንዴት ነው?

7. በቁጥር 28 እና 32 መሰረት በስራችን አዲሱን ሰው መግለጽ ያለብን እንዴት ነው?

8. የአዲሱ ሰው ባህሪ ይቅርታ ማድረግ ነው ይህ ባህሪይ ጎልቶ የማይታየው ለምን


ይመስልሀል?

9. ለቤዛ ቀን የታተማችሁበትን ቅዱሱን መንፈስ አታሳዝኑ ይላል ታዲያ መንፈሰ ቅዱስ


ሊያዝንብን የሚችለው እንዴት ነው?
10. ከዚህ ትምህርት በኋላ ምን ለማረግ ወስነሀል?

ማጠቃለያ

ጤናማ የሆነ ግንኙነት ከሌሎች እንዲኖርህ ከፈለክ አዲሱን ሰው ልበስ


ጥናት አስራ አራት
ምእራፍ 5፣1- 20
መግቢያ
ዛሬ የእግዚአብሄር ልጆች የሆኑ ሁሉ አንዴት መሮር አንደሚገባቸው እንማራለን።
የመወያያ ጥያቄዎች

1. በዚህ ክፍል ውስጥ እንደ እግዚአብሄር ልጆች ከእኛ የሚጠበቁብንን ነገሮች ዘርዝር።

2. በእግዚአብሄር መንግስት ውስጥ ድርሻ የሌላቸው እነማን ናቸው?

3. ጳውሎስ የማይታዘዙትን ሰዎች አትምሰሉ ብሎ የገለፃቸውን ሶሥት መንገዶችን


ለይታችሁ አውጡና ተወያዩበት።

4. ቀድሞ ጨለማ ነበራችሁ አሁነ ግን በጌታ ብርሀን ናችሁ ሲል ምን ማለቱ ነው?

5. ከአላመኑ ሰዎች ጋር በምን መንገድ ነው ተባባሪዎች መሆን የሌለብን?

6. እንዴት ባለ መንገድ ነው እንድንመላለሥ የእግዚአብሄር ቃል የሚያዘን?

7. አንተ የምትተኛ ንቃ ከሙታንም ተነሳ ክርስቶስም ያበራልሀል ሲል ምን ማለቱ ነው?


8. ሀዋርያው ጳውሎስ ለጌታ ደስ የሚያሰኘውን እንድንመረመርና የጌታ ፈቃድ ምን
እንደሆነ እንድናስተውል ያዘናል። እንዴት ነው ጌታን ደስ የሚያሰኘውን ነገርና
ፈቃዱን ማወቅ የምንችለው?

9. በመንፈስ መሞላት ማለት ምንድ ነው? እንዴትስ ልንሞላ እንችላለን


የመሞላታችንስ ውጤቱ ምንድነው?

10. ዘመኑን ዋጁት ሲል ምን ማለቱ ነው?

11. በዚህ ቃል ህይወትህን ስትመዝን እንደተወደደ የእግዚአብሄር ልጅ


ብርሀን መሆንህ ይታያልን?

12. ከዛሬ ጥናት ምን ተማርክ?

ማጠቃለያ
ዛሬ በተማርነው መሰረት የጨለማንና ስራውን ክደን እለት በለት የብርሀንን ፍሬ
እያፈራን እንደ ተወደዱ ልጀች እግዚአብሄርን እንከተል።
ጥናት አስራ አምስት
ምእራፍ 5፣21- 6፣9
መግቢያ
በዛሬው ጥናታችን በቤተክርስቲያን፤ በባለና በሚስት፣በወላጆችና በልጆች እንዲሁም
በአሰሪና በሰራተኛ መሀከል ሊኖር ስለሚገባ ግንኙነት ይህም ቤተክርስቲያንን ለማነፅ
የሚያስከትለውን ጥቅም እንማራለን።

የመወያያ ጥያቄዎች
1. በዚህ ክፍል ውስጥ ግንኙነትን በተመለከተ የተገለጹትን ዋና ሀሳቦችን ዘርዝር።

2. እያንዳነዳችሁ በክርስቶስ ፍርሀት የተገዛችሁ ሁኑ ሲል ምን ማለቱ ነው?

3. መገዛት (submission) ማለት ምን ማለት ነው?

4 በቁጥር 21 መሰረት እያንዳንዳችሁ የሚለው እነ ማማንን ይጠቀልላል?

6. በመሀከላችን ሊኖረን ለሚገባ ግኑኝነት የእርስ በርስ መገዛት የሚያስከትለው


ውጤት ምንድነው?

7. እንደእግዚአብሔር ቃል መገዛት የሚያስገኘው ጥቅም ምንድነው?

8. የባልንና የሚስትን ሃላፊነትና ድርሻን በመዘርዘር ተወያዩበት።

9. በወላጆችና በልጆች መሀከል እንዲኖራቸው ስልተገለጸው የእያንዳንዳቸው ሃላፊነትና


ድርሻን በመዘርዘር ተወያዩበት።

10. ምእራፍ ስድስት ቁጥር አንድ ላይ ልጆች ሆይ ለወላጆቻችሁ በጌታ


ታዘዙ ይላል በጌታ ሲል ምን ማለቱ ነው?
11. ዛሬ በወላጆችና በልጆች መሀከን ሊኖር የሚገባውን መልካም ግኑኝነት
ላይ እንቅፋት በሆኑ ነገሮችን አንሱና በሰፊው ተነጋገሩበት።

12. በአሰሪና ሰራተኛ መሀከል ሊኖር ስለሚገባው ግኑኝነት ዛሬ ካለንበት


ሁኔታ ጋር በማነጻፀር ተወያዩበት።

13. በቤታችንና በስራ ቦታችን የሚኖረን መልካም ግኑኝነት


በቤተክርስትያን ላይ ሊያስከትል በሚችለው ተፅእኖ ላይ በሰፊው ተነጋገሩበት።

14. ለታይታ መገዛት ምን ማለት እንደሆነና ከትክክለኛው መገዛት ጋር


ያለውን ልዩነት ተወያዩበት

15. በእግሂአብሄር ቃል መስታወት እራስህን ስትምለከት ከሌሎች ጋር ያለህ


ግንኝንት ምን ይመስላል?

16. ዛሬ አንዳችን ለሌላው መገዛት የሚቸግረን ለምን ይመስልሀል?

ማጠቃለያ
ዛሬ በተማርከው በእግዛብሄር ቃል ህይወትህን እየመረመርክ እራስህን ለሌሎች
እያስገዛህ በቤትና በውጭ በቅርበት ካሉ ሰዎች ጋር ሁሉ መልካም ግኑኝነት እንዲኖርህ
የተቻለህን ሁሉ አድርግ። ይህንን ድርሻችንን ብንወጣ ቤተክርስቲያን ትታነጻለች
ቤተክርስቲያንም እንደሚገባ ታድጋለች።
ጥናት 16
ኤፌሶን 6፤10-13
በዛሬው ጥናታችን ጠላታችንን ስለማወቅና ውጊያችን ከማን ጋር እንደሆነ ለዚህም
ለመንፈሳዊ ውጊያ የሚያስፈልጉንን መንፈሳዊ የጦር እቃዎች ምን እንደሆኑ እናጠናለን።
1. የዲያብሎስን ስራ ይቃወሙ ዘንድ፤ ጳውሎስ የገለጸላቸውን ሀሳቦች ዘርዝር፥
2. ለዚህ መንፈሳዊ ውጊያ የሚያስፈልጉንን የጦር እቃዎች ምን ምንድናቸው?

3. ጠላታችን ዲያብሎስ ማነው?

4. ጳውሎስ ስለውጊያው ከመግለጹ በፊት በመጀመሪያ በጌታና በሀይሉ ችሎት


የበራታችሁ ሁኑ ሲል ምን ለማለት ፈልጎ ይመስላችኋል?

5. መጋደላችን ከደምና ከስጋ (ከሰው) ጋር አይደለም ሲል ከዚህ አገላለጽ ልንማር


የሚገባን ዋነኛ ሀሳብ ምን እንደሆነ ተነጋገሩበት?

6. መጋደላችን ብቸኛ ጠላታችን ከሆነው ከዲያብሎስ ጋር ከሆነ እንዴትና በምን አይነት


መንገድ ነው በክርስቶስ ያመነውን እኛን የሚዋጋው?

7. በቁጥር 12 ውስጥ የተጠተቀሱት ጠላቶች ተብለው የተዘረዘሩትን ተወያዩባቸው።

8. ከቁጥር 13 ጀምሮ የተጠቀሱትን የቅዱሳን የጦር መሳሪያዎች በመዘርዘር


ጥቅማቸውንና አጠቃቀማቸውን ግለጽ

9. ቁጥር 13 ላይ ጳውሎስ በመንፈሳዊ ውጊያ አስቀድሞ ስለመዘጋጀት ይመክረናል


አስቀድመን የምንዘጋጀው ለምን እንደሆነና አስቀድሞ የመዘጋጀት ጥቅሙን
ተወያዩበት።
10. በመንፈሳዊ ጦርነት ውስጥ መሆንህን ታውቃለህ ወ? ካወቅክስ እንደሚገባ
ለመዋጋት እንድትችል እግዚአብሔር ያዘጋጀልህን የጠር እቃ ዘወትር መታጠቅህን
እርግጠኛ ነህ ወይ?
ማጠቃለያ
በዛሬው ትህምህርት መጋደላችን ከዲያብለስ ጋር እንደሆነ ለውጊያው እንዴት አይነት
ዝግጅት ማድረግ እንደሚገባን ተምረናል ስለዚህ ዘወትር በጦርነት ውስጥ እንዳለህና ከማን
ጋር እንደምትጋደል በማወቅ ለውጊያ እንደሚወጣ ወታደር ዘግጁና ንቁ ሁን
ጥናት 17
ኤፌሶን 6፤14-24
መግቢያ፤ በዚህ ጥናት የመንፈሳዊ ውጊያ ለመጋዋት የሚጠቅሙንን የጦር እቃዎች
ምንነትና አጠቃቀማቸውን እንመለከታለን

የመወያያ ጥያቄዎች
1. በዚህ ክፍል ውስጥ ከተዘረዘሩት የመጀመሪያ የጦር እቃ እውነት ነው፤ ይህ እውነት
ምንድነው? ይህንን የጦር እቃ በመንፈሳዊ ውጊያ ውስጥ እነዴት ነው
ልንጠቀምበት የምንችለው?

2. በሀለተኛ ደረጃ የተሰጠን የእቃ ጦር የጽድቅ ጥሩር ነው፤ ይህ የጽድቅ ጥሩር ምን


እንደሆና ከዚያም አጠቃቀሙን እንዲሁም ሊያስገኝ በሚችለው ውጤት ላይ
ተወያዩበት።

3. የሰላም ወንጌሌ ሶስተኛው የጦር እቃ ነው፤ አጠቃቀሙን ሲገልጽልን ይህንን የእቃ


ጠር በእግራችሁ ተጫምታችሁ ዝግጁ በመሆን ይላል ይህንን አባባል
እንዴትረዳዋለህ?

4. በአራተኛ ደረጃ የተጠቀሰው የጦር እቃ የእምነት ጋሻ ነው ይሀ የእምነት ጋሻ ምንድ


ነው? በመንፈሳዊ ውጊያ ላይ አጠቃቀሙንና የሚያስገኘውን ውጤት አስረዳ።

5. የመዳን ራስ ቁር ምንድነው? በዚህ የመንፈሳዊ ጦር ስልት ውስጥ እንዴት


ልንጠቀምበት እንችላለን ጥቅሙስ ምንድነው?

6. በቁጥር 17 መሰረት የመንፈስ ሰይፍ እሱም የእግዚአብሔር ቃል፤ ጠላታችንን


እንድናጠቃበት የተሰጠን የማጥቂያ መሳሪያ ሲሆን፣ እንዴት መጠቀም
እንደምንችልና ሊያመጣ የሚችለውንም ውጤት አስረዳ።

7. ጳውሎስ ስለ መንፈሳዊ የጦር እቃ ካሳያቸው በኋላ ጸልዩ የሚል ትእዛዝ ያዘዛቸው


ለምንድነው?
8. በቁጥር 16 መሰረት ጳውሎስ ያዘዛቸው እንዴት እንዲጸልዩ ነው?

9. በመንፈስ መጸለይ ምን ማለት ነው?

10. ሐዋርያው ጳውሎስ ስለራሰሱ እንዲጸልዩለት የጠየቀው በምን አቅጣጫ ነው?


ከዚህስ የምትማረው ነገር ምን አለ?

11. በመጨረሻም ሐዋረያው ጳውሎስ ቲኪቆስን ለመላክ ያነሳሳው ምክንያት


ምን ነበር ከዘህም የምትማረው ምንድነው

12. የዛሬው አጠቃላይ ጥናታችን ቤተክርስቲያንን እንዴት ሊያንጽ ይችላል ብለህ


ታምናለህ?

ማጠቃለያ
የጠላትህን ማንነትና ምንነት በደንብ ከተረዳህ በቂ ዝግጅት ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ
እንደ ክርስቶስ ወታደር አቋምህ በተስተካከለ ሁኔታ ላይ እንዲገኝ በማድረግ በውጊያው
ባለድል ለመሆን አስቀድመህ በመዘጋጀት የእግዚአብሔርን እቃ ጦር ለብሰህ በጸሎት
መጋደልህን ቀጥል።

You might also like