You are on page 1of 9

8

ጥናት

መንፈሳዊ ሥጦታዎችና
.1
አገልግሎቶች
የወጣቶች መጽሐፍ ቅዱስ ማሕበር ደቀ መዝሙርነት ትምሕርት ቤት
AY Bible Club Discipleship University

የወጣቶች መጽሐፍ ቅዱስ ማሕበር


ስልክ ቁጥር፡ +251 11 5 1 3202
ኢሜይል፡ aybibleclub@gmail.com
ከጋንዲ ሆስፒታል ፊት ለፊት ፍልውሃ አድቬንቲስት ቤተክርስቲያን
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ
በኃጥያት መውደቃችን የመለኮትን ንግግር በቀጥታ እንዳንሰማ አድርጎናል። እግዚአብሔር
አምላክ በቀጥታ ሊናገረን ስላልቻለ በጸጋው በተለያዩ መንገዶች የፍቅር ቃሉን ላከልን።
መ ግቢያ
በበዙ ዘመናት በተለያዩ መንገዶች ከተናገረን በኋላ ልጁን በመላክ በመጨረሻው ዘመን
በልጁ በክርስቶስ ኢየሱስ አማካኝነት ተናገረን። ቃሉ ሥጋ በመሆነ ጸጋንና እውነትን ተመልቶ
በመካከላችን ተመላለሰ። ሙት የሆነው መንፈሳዊ ጆሮአችን ሊሰማው ስላልቻለ እንደጠላት
ቆጠርነው። ሥጋዊው ጆሮ የሥጋን እንጂ የመንፈስን ድምጽ ሰለማይሰማ በፍቅር ሲቀርበን
አልተቀበልነውም። “የምናገራችሁን ሁሉ አሁን ልታስተዉሉት አትቸሉም” በማለት በመንፈሳዊ
ጎዳና የጀመርነውን እድገት በመንፈስ ቅዱስ ስጦታው እንድንቀጥል አደረገ።

የመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮት በሰው ሁለንተዊ የሕይወት ግንኙነትና ብልፅግና ላይ ወሳኝ


ተፅዕኖ አለው። ለማህበረሰብ ደህንነት መሰረታዊ የሆኑ፤ የቤተሰብን ጥምረት ጠብቆ ለማኖር
የሚጠቅሙ፤ ለአንድ አገር ብልፅግና የመሰረት ድንጋይ የሆኑ፤ ለግለሰብ የአላማ ጥንካሬ፤
ደስታ፤ ሞገስና የዘላለም ሕይወትን ለማግኘት ማረጋገጫ የሚሆኑ መሰረታዊ መመሪያዎችን
ይገልጣል። የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ወሳኝ መዘጋጃ የማይሆንበት ምንም አይነት የሕይወት
ደረጃና ልምምድ የለም። የእግዚአብሔር ቃል ሲጠና እና ሲነብብ የሰው ፍልስፍና ከሚሰጠው
ጠቅላላ እውቀት በላይ ጠንካራ እና ሕያው የሆነ የአዕምሮ ጥንካሬን ይሰጣል። ለሰዎችም
የባህርይ ጥንካሬ፤ አስተማማኝነትን፤ ማስተዋልን እና መልካም ፍርድን እየሰጠ ለእግዚአብሔር
ክብርና ለአለም በረከት ያሳድጋቸዋል።

የእግዚአብሔር ቃል ሕይወታችንን በሙሉ የሚቆጣጠር፤ የኑሮ መመሪያችን፣ የሕሊና ሕጋችን


ሊሆን ይገባዋል። የንግግራችን መለኪያ፤ የቃላችን መሰረት፤ የፍርዳችን መነሻ፤ የእምነታችን
ምክንያት፤ የዝማሪያችን ምንጭ፤ የመነሳትና የመቀመጣችን እንዲሁም ሁለንተናችን ነው።
የትምህርት፤ የቤተሰብን፤ የስራ፤ የእረፍት፤ የማንነት፤ የኢኮኖሚ መሰረታችን የእግዚአብሔር
ቃል ይሁን። ወደ ከነዓን ከመግባታቸው ትንሽ ቀደም ብሎ እግዚአብሔር ለእስራኤላዉያን
ያስታወሳቸው ይህንኑ ነበር። “እኔም ዛሬ አንተን የማዝዘውን ይህን ቃል በልብህ ያዝ።
ለልጆችህም አስተምረው፥ በቤትህም ስትቀመጥ፥ በመንገድም ስትሄድ፥ ስትተኛም፥
ስትነሣም ተጫወተው። በእጅህም ምልክት አድርገህ እሰረው፤ በዓይኖችህም መካከል
እንደክታብ ይሁንልህ። በቤትህም መቃኖች በደጃፍህም በሮች ላይ ጻፈው”። ኦሪት
ዘዳግም 6:6-9

ይህ ትምህርት እርስዎንና ቤተሰብዎን በእግዚአብሔር ቃል ለማነጽ፤ እንዲሁም የኢየሱስ ደቀ


መዝሙር በመሆን ለሌሎች ይህን የከበረ ቃል ያሰሙ ዘንደ ለማስታጠቅ የተዘጋጀ ነው። በጸሎትና
በትጋት ሲጠና መንፍስ ቅዱስ ሕይወትን በቃሉ ይለውጣል። በሁሉም ቦታ የክርስቶስን መንፈስ
ለማንጸባረቅ ያግዛል።

የወጣቶች መጽሐፍ ቅዱስ ማሕበር


ደቀ መዝሙርነት ትምሕርት ቤት
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ
 እግዚአብሔር እያንዳንዱ አባል ለቤተ ክርስቲያኑና ለሰብዓዊ
ዘር የጋራ ጥቅም ሥራ ላይ ሊያውላቸው የሚገባውን
መንፈሳዊ ሥጦታዎች በየዘመኑ ላሉ የእርሱ ቤተ ክርስቲያን
አባላት ሁሉ ይሰጣል፡፡ ለእያንዳንዱ ሰው እንደሚፈልገው
በሚያካፍለው በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት የተሰጡት
እነዚህ ሥጦታዎች ቤተ ክርስቲያንዋ በመለኮት የተሰጧትን

ተግባራት ለማሟላት እንድትችል የሚያስፈልጉ ችሎታዎችንና
አገልግሎቶችን ይሰጣል፡፡
የትምህርቱ መመሪያ

1. ይህ ትምህርት በግል፤ በቤተሰብ ወይም በቡድን መጠናት ይችላል

2. ይህን ጥናት ለመጨረስ የአንድ ሳምንት ጊዜ አለዎት

3. በሳምንት መጨረሻ ላይ ጥያቄዎችን በኢሜይላችን ወይም


በቴሌግራም ልኮ መጠየቅ ይቻላል

4. በግል ማብራሪያ ካስፈለግ በታች በተጠቀሰው እድራሻ ቢሮአችን ብቅ


ቢሉ የሚፈልጉትን እርዳታ ያገኛሉ

5. ይህን ትምህርት ሲጨርሱ ቀለል ያሉና ለማስታወስ የሚያግዙ


ጥያቄዎችን እንልክልወታለን

እግዚአብሔር ይባርካችሁ
መግቢያ
እግዚአብሔር እያንዳንዱ አባል ለቤተ ክርስቲያኑና ለሰብዓዊ ዘር የጋራ ጥቅም ሥራ ላይ ሊያውላቸው
የሚገባውን መንፈሳዊ ሥጦታዎች በየዘመኑ ላሉ የእርሱ ቤተ ክርስቲያን አባላት ሁሉ ይሰጣል፡፡ ለእያንዳንዱ
ሰው እንደሚፈልገው በሚያካፍለው በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት የተሰጡት እነዚህ ሥጦታዎች ቤተ
ክርስቲያንዋ በመለኮት የተሰጧትን ተግባራት ለማሟላት እንድትችል የሚያስፈልጉ ችሎታዎችንና
አገልግሎቶችን ይሰጣል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚገልፀው እነዚህ ሥጦታዎች እንደ እምነት፣ መፈወስ፣
ትንቢት መናገር፣ መስበክ፣ ማስተማር፣ ማስተዳደር፣ ማስታረቅ፣ ርህራሄ፣ ራስን መስዋዕት የሚያደርግ
አገልግሎትና ሰዎችን ለመርዳትና ለማበረታታት የሚያስችሉ የበጎ አድራጎት ሥራዎችን ያጠቃልላል፡
፡ አንዳንድ አባላት በእግዚአብሔር ተጠርተው በተለየ ሁኔታ አባላትን ለአገልግሎት ለማስታጠቅ፣
ቤተክርስቲያንን ወደ መንፈሳዊ ብስለት ደረጃ ለማድረስና የእምነት አንድነትንና እግዚአብሔርን
ማወቅን ለማጎልበት በሚያስፈልጉ ቤተ ክርስቲያን በምታውቃቸው በእረኝነት፣ በወንጌላዊነት፣
በሐዋሪያነትና በማስተማር አገልግሎቶች ማገልገል እንዲችሉ መንፈስ ተሰጥቷቸዋል፡፡ አባላት እነዚህን
መንፈሳዊ ሥጦታዎች እንደ እግዚአብሔር ልዩ ልዩ ፀጋ ታማኝ መጋቢዎች ሥራ ላይ በሚያውሉበት ጊዜ
ቤተ ክርስቲያን አጥፊ ከሆነው የሐሰት አስተምህሮ ተጽእኖ ነፃ ትሆናለች፣ ከእግዚአብሔር የሆነ እድገትን
ታድጋለች፣ በእምነትና በፍቅርም ትገነባለች፡፡ (ሮሜ 12፡4-8፤ 1ቆሮ፣12፡9-11፣27፣28፤ ኤፌ.4፡8፣11-16፤
የሐዋ.6፡1-7፤ 1ጢሞ.3፡1-13፤ 1ጴጥ.4፡10፣11)፡፡

መድኃኒታችን እና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሰማይ ከማረጉ በፊት የተናገራቸው ቃላት ታሪክን የቀየሪ ነበሩ።
ደቀ መዛሙርቱን ‹‹ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱና ወንጌልን ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ›› (ማርቆስ 16፡15) ብሎ አዘዛቸው፡፡

ለዓለም ሁሉ? ለፍጥረት ሁሉ? ደቀ መዛሙርቱ የማይቻል ሥራ ነው ብለው አስበው ይሆናል፡፡ ጌታችን ረዳተ-
ቢስነታቸው ተሰምቶት በኢየሩሳሌም ሆነው ‹‹የአብን ተስፋ እንዲጠብቁ›› አዘዛቸው፡፡ ከዚያም ‹‹መንፈስ ቅዱስ
በእናንተ ላይ በወረደ ጊዜ ኃይልን ትቀበላላችሁ፤ በኢየሩሳሌምም፣ በይሁዳም ሁሉ፣ በሰማሪያም፣ እስከ ዓለም
ዳርቻም ድረስ ምስክሮቼ ትሆናላችሁ›› (የሐዋ.1፡4፣8) በማለት አረጋገጠላቸው፡፡

ከጌታችን ወደ ሰማይ ማረግ ቀጥሎ በነበረው ጊዜ ደቀ መዛሙርት አብዛኛውን ጊዜያቸውን ያሳለፉት በፀሎት ነበር፡
፡ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር አብረው በነበሩ ጊዜ አብዛኛውን ጊዜያቸውን አበላሽተው የነበሩት አለመስማማትና ቅናት
በስምምነትና ራስን ዝቅ በማድረግ ተተኩ፡፡ ደቀ መዛሙርቱ ተለውጠው ነበር፡፡ ከክርስቶስ ጋር የነበራቸው የቅርብ
ግንኙነትና የዚያ ውጤት የነበረው አንድነት ለመንፈስ ቅዱስ መፍሰስ ዝግጅት አስፈላጊ ዝግጅቶች ነበሩ፡፡

ኢየሱስ ለአገልግሎቱ ገጣሚ እንዲሆን በመንፈስ ቅዱስ የተለየ ቅባት እንደተቀበለ ሁሉ (የሐዋ. 10፡38) ደቀ
መዛሙርቱም ለመመስከር እንዲያስችላቸው የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀትን ተቀበሉ (የሐዋ. 1፡ 5)፡፡ ውጤቶቹም
የሰዎችን ስሜት የሚያነሳሱ ነበሩ፡፡ የመንፈስ ቅዱስን ሥጦታ በተቀበሉበት ቀን ሦሥት ሺህ ሰዎችን አጠመቁ
(የሐዋ. 2፡41ን ይመልከቱ)፡፡

ጥናት 8.1 | መንፈሳዊ ሥጦታዎችና አገልግሎቶች ገጽ 1


የመንፈስ ቅዱስ ሥጦታዎች
ክርስቶስ የመንፈስ ቅዱስ ሥጦታዎችን በምሳሌ አሳየ፡- ‹‹የእግዚአብሔር መንግስት ወደ ሩቅ አገር እንደሚሄድና
ባሪያዎቹን ጠርቶ ያለውን ገንዘብ እንዳከፋፈለ ሰው ነው፡፡ ለእያንዳንዱ እንደ አቅሙ ለአንዱ አምስት መክሊት፣
ለአንዱ ሁለት፣ ለአንዱም አንድ ሰጠና ወዲያው ወደ ሌላ አገር ሄደ›› (ማቴ. 25፡14-15)፡፡

ወደ ሩቅ አገር ይሄድ የነበረው ሰው ወደ ሰማይ ሊሄድ የነበረውን ክርስቶስን ይወክላል፡፡ የሰውዬው ‹‹ባሪያዎች››
‹‹በዋጋ የተገዙት›› (1ቆሮ. 6፡20)፣ ‹‹በከበረው በክርስቶስ ደም የተገዙት›› (1ጴጥ.1፡ 19) የእርሱ ተከታዮች
ናቸው፡፡ ክርስቶስ የዋጃቸው ለአገልግሎት ስለሆነ ‹‹ከእንግዲህ የሚኖሩት ለራሳቸው ሳይሆን ለሞተላቸውና
ለተነሣው›› ነው (2ቆሮ. 5፡15)፡፡

ክርስቶስ ለእያንዳንዱ ባሪያ እንደ ችሎታው ገንዘቡንና ‹‹ለእያንዳንዱም ሥራውን›› (ማር.13፡34) ሰጠ፡፡ ከሌሎች
ሥጦታዎችና ችሎታዎች ጎን ለጎን (የዚህን መጽሐፍ ምዕራፍ 21ን ይመልከቱ) ይህ ያከፋፈላቸው ንብረት
በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት የተሰጡአቸውን ልዩ ሥጦታዎች የሚወክሉ ናቸው፡፡

በተለየ ሁኔታ ክርስቶስ እነዚህን መንፈሳዊ ሥጦታዎች የሰጠው በጴንጤ ቆስጤ ቀን ነበር፡፡ ጳውሎስ ‹‹እርሱ
ባረገ ጊዜ ለሰዎች ሥጦታዎችን ሰጠ›› ብሏል፡፡ ስለዚህ ‹‹እንደ ክርስቶስ ሥጦታ መጠን ለእያንዳንዳችን ፀጋ
ተሰጠን›› (ኤፌ 4፡7፣8)፡፡ ቤተ ክርስቲያን የተሰጣትን ሥራ እንድታከናውን የሚያስችሏትን እነዚህን ሥጦታዎች
‹‹ለእያንዳንዱ እንደሚፈቅድ›› (1ቆሮ.12፡11) የሚያከፋፍለው መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡

የመንፈሳዊ ሥጦታዎች ዓላማ


መንፈስ ቅዱስ ለአንድ አባል ቤተ ክርስቲያን ተልዕኮዋን እንድትፈጽም እንዲረዳ የተለየ ችሎታ ይሰጠዋል፡፡

በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ስምምነት መኖር


የቆሮንቶስ ቤተ ክርስቲያን ያልነበራት አንድም መንፈሳዊ ሥጦታ አልነበረም (1ቆሮ.1፡4፣7)፡፡ ባለመታደል እንደ
ህፃናት ከሥጦታዎቹ እጅግ አስፈላጊው የቱ ነው በሚል ክርክር ውስጥ ገቡ፡፡

በቤተ ክርስቲያናቸው የነበረው መከፋፈል ስላሳሰበው ስለ እነዚህ ሥጦታዎች እውነተኛ ባሕርይና እንዴት
መሥራት እንዳለባቸው ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ሰዎች ጻፈላቸው፡፡ መንፈሳዊ ሥጦታዎች የፀጋ ሥጦታዎች ናቸው
ብሎ አስረዳቸው፡፡ ከዚያው መንፈስ ወደ ‹‹የተለያዩ አገልግሎቶች›› እና ‹‹ልዩ ልዩ ተግባራት›› የሚመሩ ‹‹የተለያዩ
ሥጦታዎች›› ይመጣሉ፡፡ ነገር ግን ‹‹ሁሉን በሁሉ የሚሰራ እግዚአብሔር አንድ›› (1ቆሮ. 12፡4-6) እንደሆነ
ጳውሎስ አጽንዖት ሰጥቷል፡፡

መንፈስ ቤተ ክርስቲያንን ለማስተካከልና ለማነጽ ለእያንዳንዱ አማኝ ሥጦታዎችን ያከፋፍላል፡፡ መንፈስ ምንና
ለማን እንደሚያከፋፍል የሚወስኑት የጌታ ሥራ የሚፈልጋቸው ነገሮች ናቸው፡፡ ሁሉም አንድ ዓይነት ሥጦታዎች
አይቀበሉም፡፡ ጳውሎስ መንፈስ ለአንዱ ጥበብን፣ ለሌላው ማስተዋልን፣ ለሌላው እምነትን፣ ለሌላው ትንቢትን፣
ለሌላው መናፍስትን መለየትን፣ ለሌላው ልሳንንና ለሌላው ልሳንን የመተርጎም ሥጦታን ይሰጣል አለ፡፡ ‹‹ይህን
ሁሉ ግን ያ አንዱ መንፈስ እንደሚፈቅድ ለእያንዳንዱ ለብቻው እያካፈለ ያደርጋል›› (ቁጥር 11)፡፡ በቤተ
ክርስቲያን ውስጥ ለሚሠራው ሥራ ምሥጋና መሰጠት ያለበት ሥጦታውን ሥራ ላይ ለሚያውለው ግለሰብ
ሳይሆን ለሰጪው ነው፡፡ ሥጦታዎቹ የተሰጡት ለቤተ ክርስቲያን እንጅ ለግለሰብ ስላልሆነ ተቀባዮቹ ሥጦታዎቹን
እንደ ግል ንብረታቸው መቁጠር የለባቸውም፡፡

መንፈስ ሥጦታዎቹን የሚያከፋፍለው ገጣሚ ሆኖ እንዳየው ስለሆነ ማንኛውንም ሥጦታ መናቅ ወይም ዝቅ
አድርጎ መመልከት ተገቢ አይደለም፡፡ ማንኛውም አባል አንድ ኃላፊነት ወይም ተግባር ስለተሰጠው መኩራራት
ወይም ዝቅተኛ ደረጃ ያለው ኃላፊነት ስለተሰጠው የዝቅተኛነት ስሜት ሊሰማው አይገባም፡፡

የአሰራር ተምሳሌት
ጳውሎስ በተለያዩ ሥጦታዎች ውስጥ መኖር ያለበትን መስማማት ለመግለጽ የሰውን አካል ተጠቅሟል፡፡ አካል
እያንዳንዳቸው በተለየ ሁኔታ አስተዋጽዖ የሚያደርጉ ብዙ ክፍሎች አሉት፡፡ ‹‹አሁን ግን እግዚአብሔር እንደ ወደደ
ብልቶችን እያንዳንዳቸውን በአካል ውስጥ አድርጓል (ቁጥር 18)፡፡

ገጽ 2
ማንኛውም የአካል ክፍል ሌላኛውን ‹‹አልፈልግህም!›› ማለት የለበትም፡፡ ሁሉም አንዱ በአንዱ ላይ የሚደገፍ
ስለሆነ ‹‹ዓይን እጅን፡- አታስፈልገኝም ልትለው አትችልም፣ ወይም ራስ ደግሞ እግሮችን፡- አታስፈልጉኝም
ሊላቸው አይችልም፡፡ ነገር ግን ደካሞች የሚመስሉ የአካል ብልቶች ይልቁን የሚያስፈልጉ ናቸው፤ ከአካልም
ብልቶች ያልከበሩ ሆነው የሚመስሉን በሚበዛ ክብር እናለብሳቸዋለን፣ በምናፍርባቸውም ብልቶቻችን ክብር
ይጨመርላቸዋል፤ ክብር ያላቸው ብልቶቻችን ግን ይህ አያስፈልጋቸውም፡፡ ነገር ግን ብልቶች እርስ በርሳቸው
በትክክል ይተሳሰቡ ዘንድ እንጂ በአካል መለያየት እንዳይሆን ለጎደለው ብልት የበለጠ ክብር እየሰጠ እግዚአብሔር
አካልን አገጣጠመው›› (ቁጥር 21-21)፡፡

አንዱ የአካል ክፍል በትክክል መስራቱን ካቆመ ችግሩ አካልን በሙሉ ይነካል፡፡ አካል አእምሮ ከሌለው ጨጓራ
ሥራውን መስራት አይችልም፤ ጨጓራ ከሌለም አእምሮ ዋጋ ቢስ ይሆናል፡፡ ስለዚህ ከአባላት አንዱ፣ የፈለገውን
ያህል ትንሽ ቢሆን፣ ከጎደለ ቤተ ክርስቲያን ትቸገራለች፡፡

በአሰራራቸው ደካማ የሆኑ አንዳንድ የአካል ክፍሎች የተለየ ጥበቃ ይሻሉ፡፡ አንድ ሰው ያለ እጅ ወይም ያለ
እግር መኖር ይችላል፣ ነገር ግን ያለ ጉበት ወይም ያለ ሳንባ ወይም ያለ ልብ መኖር አይችልም፡፡ በተለመደው
ሁኔታ እጆቻችንንና ፊታችንን ገልጠን እንሄዳለን፣ ነገር ግን ሌሎች የአካል ክፍሎቻችንን ጨዋነታችንን ወይም
ውበታችንን ለመጠበቅ ስንል በልብስ እንሸፍናለን፡፡ አነስተኛ ሥጦታዎችን አቅልለን ከመመልከት ይልቅ የቤተ
ክርስቲያን ጤንነት በእነርሱ ላይ የሚደገፍ ስለሆነ ከፍተኛ ጥንቃቄ ልናደርግላቸው ይገባል፡፡

እግዚአብሔር በቤተ ክርስቲያን ውስጥ መንፈሳዊ ሥጦታዎችን ለማከፋፈል ያሰበው ‹‹በአካል ውስጥ
መከፋፈል›› እንዳይኖር ለመከልከልና የመስማማትና በእርስ በርስ ላይ የመደጋገፍ መንፈስን ለመፍጠር ነበር፡
፡ ‹‹ነገር ግን ብልቶች እርስ በርሳቸው በትክክል ይተሳሰቡ ዘንድ እንጂ በአካል መለያየት እንዳይሆን ለጎደለው
ብልት የበለጠ ክብር እየሰጠ እግዚአብሔር አካልን አገጣጠመው፡፡ አንድም ብልት ቢሠቃይ ብልቶች ሁሉ ከእርሱ
ጋር ይሠቃያሉ፣ አንድ ብልትም ቢከበር ብልቶች ሁሉ ከእርሱ ጋር ደስ ይላቸዋል›› (ቁጥር 25-26)፡፡ ስለዚህ አንድ
አማኝ ሲሣቃይ ቤተ ክርስቲያንዋ እንድታውቅ መደረግ አለበት፤ ችግሩን ለመፍታትም መርዳት አለባት፡፡ የቤተ
ክርስቲያንዋ ጤንነት የሚጠበቀው ይህ ግለሰብ ከችግሩ መውጣት ሲችል ብቻ ነው፡፡

ከእነዚህ ሥጦታዎች መካከል የእያንዳንዱን ጥቅም ከተናገረ በኋላ ጳውሎስ የተወሰኑትን ዘረዘራቸው፡
- ‹‹እግዚአብሔር በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በመጀመሪያ ሐዋርያትን፣ ሁለተኛም ነቢያትን፣ ሦሥተኛም
አስተማሪዎችን፣ ቀጥሎም ተአምራት ማድረግን፣ ቀጥሎም የመፈወስን ሥጦታ፣ እርዳታንም፣ አገዛዝንም፣
የልዩ ልዩ አይነት ልሳኖችንም አድርጓል›› (ቁጥር 28፤ ኤፌ.4፡11)፡፡ ማንም አባል ሁሉም ሥጦታዎች ስለሌሉት
ለቤተ ክርስቲያን እጅግ አስፈላጊ የሆኑትን በማመልከት ሁሉንም አባላት ‹‹ነገር ግን የሚበልጠውን የፀጋ ሥጦታ
በብርቱ ፈልጉ›› (ቁጥር 31) ብሎ አበረታትቷል፡፡

ችላ ማለት የማይቻለው አቅጣጫ


የመንፈስ ቅዱስ ሥጦታዎች በራሳቸው በቂ አይደሉም፡፡ ‹‹ከሁሉ የሚበልጥ መንገድ›› (ቁጥር 31) አለ፡፡ የመንፈስ
ሥጦታዎች በክርስቶስ ዳግም ምፃት የሚያልፉ ሲሆን የመንፈስ ፍሬ ግን ዘላለማዊ ነው፡፡ የፍቅርንና የሰላምን፣
የበጎነትንና ፍቅር ከራሱ ጋር የሚያመጣውን የጽድቅን መልካም ባሕርያት ይይዛል (ገላቲያ 5፡22፣23፤ ኤፌ.5፡
9)፡፡ ትንቢት፣ ልሳኖችና እውቀት የሚጠፉ ሲሆን እምነት፣ ተስፋና ፍቅር ፀንተው ይኖራሉ፡፡ ‹‹ከእነዚህ ሁሉ
የሚበልጠው ፍቅር ነው›› (1ቆሮ. 13፡13)፡፡

ይህ እግዚአብሔር የሚሰጠው ፍቅር (በግሪክ ቋንቋ አጋፔ የተባለው) ራስን መስዋዕት የሚያደርግና አሳልፎ
የሚሰጥ ፍቅር ነው (1ቆሮ.13፡4-8)፡፡ ‹‹በአንድ በሚወደድ ሰው ወይም ነገር ውስጥ አንድ ዋጋ ያለውን ነገር
መገንዘብ የሚችል ከፍ ያለ የፍቅር ዓይነት ነው፤ በስሜት ላይ ሳይሆን በመርህ ላይ የተመሠረተ ፍቅር ነው፤
በሚወደው ነገር ውስጥ ላሉት አስደናቂ ባሕርያት ካለው አክብሮት ውስጥ የሚያድግ ፍቅር ነው፡፡›› ፍቅር
የሌላቸው ሥጦታዎች በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ውዝግብንና መከፋፈልን ያስከትላሉ፡፡ ስለዚህ ከሁሉ የሚበልጠው
መንገድ እያንዳንዱ መንፈሳዊ ሥጦታ ያለው ግለሰብ የዚህ ሙሉ በሙሉ ከራስ ወዳድነት የፀዳ ፍቅር ባለቤት
መሆን ነው፡፡ ‹‹የፍቅርን መንገድ ተከተሉ፣ መንፈሳዊ ሥጦታዎችንም በብርቱ ፈልጉ›› (1ቆሮ.14፡1)፡፡

ለእግዚአብሔር ክብር መኖር


ጳውሎስ ለሮሜ ሰዎች በፃፈው ደብዳቤውም ስለ መንፈሳዊ ሥጦታዎች ተናግሯል፡፡ እያንዳንዱ አማኝ
ለእግዚአብሔር ክብር እንዲኖር ጥሪ በማድረግ (ሮሜ 11፡36-12፡2) በቤተ ክርስቲያን ውስጥ አንድ በሆኑ
አማኞች መካከል በልዩነት ውስጥ ያለውን አንድነት ለመግለጽ ጳውሎስ እንደገና የአካል ክፍሎችን ተጠቅሟል
(ቁጥር 3-6)፡፡

ጥናት 8.1 | መንፈሳዊ ሥጦታዎችና አገልግሎቶች ገጽ 3


እምነትና መንፈሳዊ ሥጦታዎች ምንጫቸው በእግዚአብሔር ፀጋ ውስጥ መሆኑን በመገንዘብ አማኞች ትሁት
ሆነው ይቆያሉ፡፡ ለአማኙ ብዙ ሥጦታዎች ከተሰጡት፣ መንፈሳዊ ተጽእኖውም ብዙ ስለሚሆን በእግዚአብሔር
ላይ የሚኖረው መደገፍም ብዙ መሆን አለበት፡፡ በዚህ ምዕራፍ ጳውሎስ የሚከተሉትን መንፈሳዊ ሥጦታዎች
ዘርዝሯል፡- ትንቢት (የመገለጥ ንግግር፣ ስብከት)፣ አገልግሎት (ማገልገል)፣ ማስተማር፣ ማደፋፈር (ማበረታታት)፣
መስጠት (ማካፈል)፣ አመራርና ምህረት ማድረግ (ርህራሄ) ናቸው፡፡ ልክ በአንደኛ ቆሮንቶስ እንዳደረገው ሁሉ
ውይይቱን የፈፀመው የክርስትና ትልቁ መርህ በሆነው ፍቅር ነው (ቁጥር 9)፡፡

ጴጥሮስ የመንፈሳዊ ሥጦታዎችን ርዕስ የነገር ሁሉ ፍጻሜ በደጅ መሆኑን ከሚገልፀው አውድ ኋላ ነው የገለፀው
(1ጴጥ.4፡7)፡፡ የጊዜው አስቸኳይነት አማኞች ሥጦታዎቹን እንዲጠቀሙ ያስገድዳቸዋል፡፡ ‹‹ልዩ ልዩ የእግዚአብሔር
ፀጋ ደጋግ መጋቢዎች እንደመሆናችሁ እያንዳንዳችሁ የፀጋ ሥጦታን እንደ ተቀበላችሁ መጠን በዚያው ፀጋ እርስ
በርሳችሁ አገልግሉ›› ብሏል (ቁጥር 10)፡፡ እንደ ጳውሎስ ጴጥሮስም እነዚህ ሥጦታዎች የሚሰጡት ራስን ከፍ ከፍ
ለማድረግ ሳይሆን ‹‹በሁሉም ነገር እግዚአብሔር እንዲከብር›› ነው ብሎ አስተምሯል (ቁጥር 11)፡፡ እርሱ ፍቅርን
ከሥጦታዎቹም ጋር አገናኝቷል (ቁጥር 8)፡፡

የቤተ ክርስቲያን እድገት


በጳውሎስ ሦሥተኛውና የመጨረሻው በሆነው የመንፈሳዊ ሥጦታዎች ውይይት ላይ ‹‹በተጠራችሁበት
መጠራታችሁ ትመላለሱ ዘንድ እለምናችኋለሁ፤ በትህትና ሁሉና በየዋህነት በትዕግስትም እርስ በርሳችሁ በፍቅር
ታገሱ፤ በሰላም ማሰሪያ የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ‹‹ (ኤፌ. 4፡1-3)፡፡

መንፈሳዊ ሥጦታዎች ቤተ ክርስቲያን እንድታድግ የሚያደርገውን አንድነት ለማሳደግ አስተዋጽዖ ያደርጋሉ፡


፡ እያንዳንዱ አማኝ እነዚህን ሥጦታዎች ስለመቀበሉ ‹‹…እንደ ክርስቶስ ሥጦታ መጠን ለእያንዳንዳችን ፀጋ
ተሰጠን›› (ቁጥር 7) ተብሏል፡፡

ክርስቶስ እራሱ ‹‹አንዳንዶችን ሐዋርያት፣ ሌሎችን ነቢያት፣ ሌሎችን ወንጌላውያን፣ ሌሎችን ደግሞ እረኞችና
መምህራን እንዲሆኑ ሰጠ፡፡›› እነዚህ ሥጦታዎች ‹‹ሁላችን የእግዚአብሔርን ልጅ በማወቅና በማመን ወደሚገኝ
አንድነት፣ ሙሉ ሰውም ወደ መሆን፣ የክርስቶስም ሙላቱ ወደሚሆን ወደ ሙላቱ ልክ እስክንደርስ ድረስ፣ ቅዱሳን
አገልግሎትን ለመስራትና ለክርስቶስ አካል ህንፃ ፍፁማን ይሆኑ ዘንድ›› (ቁጥር 11-13) ማገልገልን ያማከሉ
አገልግሎቶች ናቸው፡፡ እነዚያ መንፈሳዊ ሥጦታዎችን የሚቀበሉ ሰዎች በተለየ ሁኔታ አማኞችን ማገልገልና
ከሥጦታዎቻቸው ጋር አብሮ ለሚሄድ አገልግሎት ማሰልጠን አለባቸው፡፡ ይህ ቤተ ክርስቲያንን ወደ ክርስቶስ
ሙላትና ሙሉ ሰው ወደ መሆን የብስለት ደረጃ ያደርሳታል፡፡

እነዚህ አገልግሎቶች መንፈሳዊ መረጋጋትን በመጨመር ቤተ ክርስቲያን የስህተት ትምህርቶችን መቋቋም


እንድትችል ያጠነክሯታል፡- ‹‹እንደ ስህተት ሽንገላ ባለ ተንኮል በሰዎችም ማታለል ምክንያት በትምህርት ንፋስ
ሁሉ እየተፍገመገምን ወዲያና ወዲህም እየተንሳፈፍን ሕፃናት መሆን ወደ ፊት አይገባንም፤ ነገር ግን እውነትን
በፍቅር እየያዝን በነገር ሁሉ ወደ እርሱ ራስ ወደሚሆን ወደ ክርስቶስ እንደግ›› (ቁጥር 14 እና 15)፡፡

በመጨረሻም መንፈሳዊ ሥጦታዎች በክርስቶስ የቤተ ክርስቲያንን አንድነትና ብልጽግና ያመጣሉ፡፡ ‹‹ከእርሱም
የተነሣ አካል ሁሉ እያንዳንዱ ክፍል በልክ እንደሚሰራ፣ በተሰጠለት በጅማት ሁሉ እየተጋጠመና እየተያያዘ፣ ራሱን
በፍቅር ለማነጽ አካሉን ያሳድጋል›› (ቁጥር 16)፡፡ እግዚአብሔር የሚፈልገውን ዓይነት እድገት ቤተ ክርስቲያን
እንድትለማመድ እያንዳንዱ አባል እርሱ የሰጠውን የፀጋ ሥጦታዎች መጠቀም አለበት፡፡

ከዚህ የተነሣ ቤተ ክርስቲያን ሁለት ዓይነት እድገትን ትለማመዳለች፡፡ እርሱም በአባላት ቁጥር ማደግና በግል
መንፈሳዊ ሥጦታዎች ማደግ ናቸው፡፡ እንደገና ቤተ ክርስቲያን ይህን መታነጽና እድገት መገንዘብ የምትችለው
እነዚህን ሥጦታዎች በፍቅር ስትጠቀም ብቻ ስለሆነ ፍቅር የዚህ ጥሪ አካል ነው፡፡
የመንፈሳዊ ሥጦታዎች አንድምታ

የጋራ አገልግሎት
የተቀቡ አገልጋዮች ብቻ ማገልገል እንዳለባቸውና ተራ ምዕመናን ወንበር እያሞቁ ለመመገብ ብቻ መጠበቅ
እንዳለባቸው የሚያስብ አመለካከትን መጽሐፍ ቅዱስ አይደግፍም፡፡ ‹‹የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን››
(1ጴጥ.2፡9) የሚመሠርቱት ቀሳውስቱና ተራ ምዕመናን ናቸው፡፡ ለቤተ ክርስቲያን ደህንነትና ብልጽግና ሁለቱም
ተጠያቂ ናቸው፡፡ እያንዳንዳቸው ክርስቶስ እንደ ሰጠው ልዩ ሥጦታዎች መጠን እንዲያገለግሉ ተጠርተዋል፡፡
የሥጦታዎች ልዩነት የእግዚአብሔርን መንግስት ለማስፋትና ዓለም አዳኝን ለመገናኘት እንድትዘጋጅ ለማድረግ
ሁሉም በምስክርነታቸው አንድ እንዲሆኑ የሚያግዙ የተለያዩ አይነት አገልግሎቶች እንዲኖሩ ያደርጋል (ማቴ.28፡
18-20፤ ራዕይ 14፡6-12)፡፡

ገጽ 4
የተቀቡ አገልጋዮች (ቀሳውስት) ሚና
የመንፈሳዊ ሥጦታዎች አስተምህሮ ጉባኤውን የማሰልጠን ኃላፊነትን በአገልጋዩ ጫንቃ ላይ ያስቀምጣል፡፡ እግዚአብሔር
ሐዋርያትን፣ ነቢያትን፣ ወንጌላውያንን፣ እረኞችንና መምህራንን የሾመው የእግዚአብሔርን ሕዝብ ለአገልግሎት
እንዲያስታጥቁ ነው፡፡ ‹‹አገልጋዮች ራሳቸውን እያደከሙና ሌሎች ተግባራቸውን እንዳያከናውኑ እየከለከሉ ቤተ ክርስቲያን
መሥራት ያለባትን ሥራ መስራት የለባቸውም፡፡ አባላት በቤተ ክርስቲያን ውስጥና በማህበረሰቡ ውስጥ እንዴት መስራት
እንዳለባቸው ማስተማር አለባቸው፡፡››

የማሰልጠን ተስጥኦ የሌለው አገልጋይ በእረኝነት (ቅስና) አገልግሎት ውስጥ ሳይሆን በሌላ የእግዚአብሔር ሥራ ዘርፍ
መሰማራት አለበት፡፡ እግዚአብሔር ለቤተ ክርስቲያኑ ያለው እቅድ ስኬታማነት የሚደገፈው አገልጋዮች አባላቱን
እግዚአብሔር የሰጣቸውን ሥጦታዎች መጠቀም እንዲችሉ ለማሰልጠን ፈቃደኛ በመሆናቸውና ባላቸው ችሎታ ላይ
ነው፡፡
ሥጦታዎችና ተልዕኮ
እግዚአብሔር መንፈሳዊ ሥጦታዎችን የሚሰጠው ዝም ብሎ ተቀባዮቹን ግለሰቦች ለመጥቀም ሳይሆን ሙሉውን አካል
ለመጥቀም ነው፡፡ ተቀባዩ ሥጦታውን የሚቀበለው ለራሱ ብቻ እንዳልሆነ ሁሉ ቤተ ክርስቲያንም አጠቃላይ ሥጦታዎችን
ለራስዋ ብቻ አትቀበልም፡፡ እግዚአብሔር ለቤተ ክርስቲያን ማህበረሰብ ሥጦታዎችን የሚሰጠው ቤተ ክርስቲያን ለዓለም
እንድታስተላልፍ እርሱ የሰጣትን ተልዕኮ ለመፈፀም ነው፡፡

መንፈሳዊ ሥጦታዎች በደንብ ለተሠሩ ሥራዎች የተሰጡ ሽልማቶች ሳይሆኑ ሥራውን በደንብ ለመስራት የሚረዱ
መሳሪያዎች ናቸው፡፡ ምንም እንኳን የተፈጥሮ ሥጦታዎች ብቻቸውን መንፈሳዊ ሥጦታዎች ባይሆኑም መንፈስ
አብዛኛውን ጊዜ ከግለሰቡ የተፈጥሮ ችሎታዎች ጋር የሚጣጣሙ ሥጦታዎችን ይሰጣል፡፡ አዲስ ልደት ግለሰቡን በመንፈስ
ኃይል ይሞላዋል፡፡ መንፈሳዊ ሥጦታዎችን ለመቀበል እንደገና መወለድ አለብን፡፡

አንድ-ወጥነት ሳይሆን በልዩነት አንድነት


አንዳንድ ክርስቲያኖች እያንዳንዱ አማኝ እንደ እነርሱ እንዲሆን ለማድረግ ይሞክራሉ፡፡ ይህ የሰው እንጂ የእግዚአብሔር
እቅድ አይደለም፡፡ ቤተ ክርስቲያን የሥጦታዎች ልዩነት ቢኖራትም አንድነትዋን ጠብቃ መኖርዋ የሚያመለክተው
ሥጦታዎቹ የመደጋገፍ ባሕርይ ያላቸው መሆናቸውን ነው፡፡ ይህ የሚያሳየው የእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን እድገት
የሚደገፈው በእያንዳንዱ አባል ላይ መሆኑን ነው፡፡ የእግዚአብሔር ሐሳብ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያሉ ሁሉም
ሥጦታዎች፣ አገልግሎቶችና ሥራዎች ባለታሪኳ ቤተ ክርስቲያን በጣለችው መሠረት ላይ ለመገንባት እንዲዋሐዱ ነው፡
፡ የማዕዘኑ ድንጋይ በሆነው በኢየሱስ ክርስቶስ ‹‹በእርሱ ሕንፃ ሁሉ እየተጋጠመ በጌታ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንዲሆን
ያድጋል›› (ኤፌ. 2፡21)፡፡

መመስከር- ሥጦታዎቹ የተሰጡበት ዓላማ


አማኞች የተለያዩ ዓይነት ሥጦታዎችን መቀበላቸው እያንዳንዱ ግለሰብ ግላዊ አገልግሎት እንዳለው የሚያመለክት ነው፡
፡ ሆኖም እያንዳንዱ አማኝ የሚያምናቸውን ነገሮች ለሌሎች በማካፈልና እግዚአብሔር በሕይወቱ ያደረጋቸውን ነገሮች
ለሌሎች በመንገር ስለ እምነቱ መመስከር መቻል አለበት፡፡ ሥጦታው ምንም ቢሆን እግዚአብሔር እያንዳንዱን ሥጦታ
የሚሰጥበት ምክንያት ተቀባዩን መመስከር እንዲችል ለማድረግ ነው፡፡

መንፈሳዊ ሥጦታዎችን መጠቀም አለመቻል


መንፈሳዊ ሥጦታዎቻቸውን ሥራ ላይ ማዋል እምቢ የሚሉ ሰዎች ሥጦታዎቻቸው ሲጠፉ ማየት ብቻ ሳይሆን
ዘላለማዊ ሕይወታቸውንም አደጋ ውስጥ ይጥላሉ፡፡ ኢየሱስ ፍቅር ባለበት የኃላፊነት ስሜት መክሊቱን ያልተጠቀመው
ባሪያ ዘላለማዊ ሽልማትን ካጣው ‹‹ክፉና ሐኬተኛ ባሪያ›› (ማቴ.25፡26-30) ያልተሻለ መሆኑን በጥብቅ አስጠንቅቋል፡
፡ ታማኝ ያልነበረው ባሪያ መክሊቱን አለመጠቀሙ አስቦበት በራሱ ውሳኔ የተደረገ መሆኑን በነፃነት ገለፀ፡፡ ስለዚህ ስለ
አለመጠቀሙ ኃላፊነቱን መሸከም አለበት፡፡ ‹‹ያገኙአቸውን እድሎች ላለመጠቀም በመደበቅና ኃላፊነቶችን በመሸሽ
ከመንገድ የሳቱት ሰዎች በታላቁ የመጨረሻ ፍርድ ቀን በታላቁ ፈራጅ ከክፉ አድራጊዎች ጋር ይፈረጃሉ፡፡››

መንፈሳዊ ሥጦታዎችን ለይቶ ማወቅ


አባላት በቤተ ክርስቲያንዋ ተልዕኮ ውስጥ በተሳካ ሁኔታ መሳተፍ እንዲችሉ ሥጦታዎቻቸውን ማወቅ አለባቸው፡፡
ሥጦታዎቹ ባለቤቱን ወደ አገልግሎትና የተትረፈረፈ ሕይወትን ወደ መደሰት በመምራት እንደ አቅጣጫ መጠቆሚያ
ያገለግላሉ (ዮሐ.10፡10)፡፡ ሥጦታዎቻችንን ለመገንዘብ፣ ለማሳደግና ለመለማመድ ‹‹ፈቃደኛ ላለመሆን ወይም ችላ
ለማለት ከመረጥን›› ቤተ ክርስቲያን መሆን ከሚገባት በታች የሆነች ትሆናለች፡፡ እግዚአብሔር እንድትሆን ከሚፈልግባት
በታች ትሆናለች፡፡››

ጥናት 8.1 | መንፈሳዊ ሥጦታዎችና አገልግሎቶች ገጽ 5


መንፈሳዊ ሥጦታዎቻችንን የመለየት ሂደት የሚከተሉት ባህሪያት ሊኖረው ይገባል፡-

መንፈሳዊ ዝግጅት
ሐዋርያት ኃጢአተኞችን ወደ ክርስቶስ ሊመሩ የሚችሉ ቃላትን መናገር እንዲችሉ ገጣሚዎች ለመሆን ተግተው
ፀልየዋል፡፡ በመካከላቸው ቆመው የነበሩ ልዩነቶችንና ከሌሎች የበላይ የመሆን ፍላጎቶችን አስወገዱ፡፡ የኃጢአት
ንስሐና ኑዛዜ ከክርስቶስ ጋር የቅርብ ህብረት እንዲፈጥሩ አደረጋቸው፡፡ ዛሬም ክርስቶስን የሚቀበሉ ሰዎች
ለመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት እየተዘጋጁ ሳለ ተመሳሳይ ልምምድ ያስፈልጋቸዋል፡፡

የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት የአንድ ጊዜ ክስተት አይደለም፤ በየቀኑ ልንለማመደው እንችላለን፡፡ ለቤተ ክርስቲያን
የመመስከርንና ወንጌልን የማወጅን ኃይል ስለሚሰጥ ጌታ ያን ጥምቀት እንዲሰጠን መለመን ያስፈልገናል፡
፡ ይህን ለማድረግ ያለማቋረጥ ሕይወታችንን ለእግዚአብሔር መስጠት፣ ሙሉ በሙሉ በክርስቶስ መኖርና
ሥጦታዎቻችንን ለይተን ማወቅ እንድንችል ለጥበብ መጠየቅ አለብን (ያዕቆብ 1፡5)፡፡

መጽሐፍ ቅዱስን ማጥናት


ስለ መንፈሳዊ ሥጦታዎች አዲስ ኪዳን የሚያስተምረውን ትምህርት በፀሎት ሆነን ማጥናታችን መንፈስ ለእኛ
ያለው የተለየ አገልግሎት አእምሮአችንን እንዲነካ ያደርጋል፡፡ እግዚአብሔር በአገልግሎቱ ውስጥ ልንጠቀመው
የምንችለውን ቢያንስ አንድ መክሊት እንደሰጠን ማመን አስፈላጊ ነው፡፡

ለሚሰጥ አመራር ግልጽ መሆን


እግዚአብሔር በሕዝቡ ውስጥ ‹‹ስለ በጎ ፈቃዱ መፈለግንም ማድረግንም›› (ፊል. 2፡13) የሚፈጽም እርሱ
ስለሆነ እኛ መንፈስን አንጠቀምም፣ እርሱ ግን እኛን ይጠቀምብናል፡፡ የእግዚአብሔር መልካም ፈቃድ በፊታችን
በሚያቀርበው በማንኛውም መስመር ለመስራት ፈቃደኛ መሆን መልካም እድል ነው፡፡ በሌሎች አማካይነት
የእኛን እርዳታ እንዲጠይቅ ለእግዚአብሔር እድል መስጠት አለብን፡፡ ራሳቸውን በሚያቀርቡበት ጊዜ ለቤተ
ክርስቲያን ፍላጎቶች ምላሽ ለመስጠት ዝግጁ መሆን አለብን፡፡ አዳዲስ ነገሮችን ለመሞከር መፍራት የለብንም፣
ነገር ግን የእኛን እርዳታ ለሚጠይቁ ሰዎች ስለ መክሊቶቻችንና ልምምዳችን ለመንገርም ነፃነት የሚሰማን
መሆን አለብን፡፡

ማረጋገጫ ከአካል
እነዚህን ሥጦታዎች እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን ለመገንባት የሚሰጥ ከሆነ የሥጦታዎቻችን የመጨረሻ
ማረጋገጫ ከራሳችን ስሜት ሳይሆን ከክርስቶስ አካል ውሳኔ እንዲነሣ ልንጠብቅ እንችላለን፡፡ አብዛኛውን ጊዜ
የሌሎች ሰዎችን ሥጦታ ከማወቅ ይልቅ የራሳችንን ሥጦታዎች መገንዘብ ይከብዳል፡፡ ስለ ሥጦታዎቻችን ሌሎች
የሚነግሩንን ለመስማት ዝግጁ መሆን ብቻ ሳይሆን እኛም በሌሎች ላይ ያሉትን የእግዚአብሔርን ሥጦታዎች
መገንዘብና ማረጋገጫ መስጠት አስፈላጊ ነው፡፡

የእግዚአብሔር መልካም ፈቃድ ለእኛ የሰጠንን ቦታ ወይም አገልግሎት ይዘን እንዳለን ከማወቅ የበለጠ
የሚያስደስትና የስኬት ስሜት እንዲሰማን የሚያደርግ ምንም ነገር የለም፡፡ ክርስቶስ በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት
የሰጠንን ልዩ ሥጦታ ለእርሱ አገልግሎት ማዋል እንዴት ያለ በረከት ነው፡፡ ክርስቶስ የእርሱን የፀጋ ሥጦታዎች
ለማካፈል ይናፍቃል፡፡ ዛሬ የእርሱን ግብዣ መቀበልና ሥጦታዎቹ በመንፈስ በተሞላ ሕይወት ውስጥ ምን
ማድረግ እንደሚችሉ ማወቅ እንችላለን!

ገጽ 6

You might also like