Professional Documents
Culture Documents
ምዕራፍ ሁለት-ሣልሳይ
ምዕራፍ ሁለት-ሣልሳይ
፫.ማህበራዊ ክርስትና
‹‹ ቢቻላችሁስ ከሰው ሁሉ ጋር በሰላም ኑሩ ሮሜ 12 ፤ 18 ››
የማኅበራዊ ኑሮ ጠቀሜታ
1. ችግርን ለማስወገድ ለመጽናናት ለመረጋጋት ዲድስቅልያ አንቀጽ 8 አንዱ
የአንዱን በደል ይቅር ይበል
2. ሀሳብ ምክር ለመለዋወጥ
3. ደስታን ለመጋራት ሀዘንን ለማቅለል
ሮሜ 12፤ ¹⁴ የሚያሳድዱአችሁን መርቁ፥ መርቁ እንጂ አትርገሙ።¹⁵ ደስ
ከሚላቸው ጋር ደስ ይበላችሁ፥ ከሚያለቅሱም ጋር አልቅሱ።
4. መንፈሳዊ በረከትን ለመቀበል ምሳሌ እንግዳን መቀበል
5. በኑሮ መሻሻል እና እድገትን ለማምጣት መክ 4፤9
መክብብ 4 ⁹ ድካማቸው መልካም ዋጋ አለውና አንድ ብቻ ከመሆን ሁለት
መሆን ይሻላል።
¹⁰ ቢወድቁ አንዱ ሁለተኛውን ያነሣዋልና፤ አንዱ ብቻውን ሆኖ በወደቀ ጊዜ
ግን የሚያነሣው ሁለተኛ የለውምና ወዮለት።
¹¹ ሁለቱም በአንድነት ቢተኙ ይሞቃቸዋል፤ አንድ ብቻውን ግን እንዴት
ይሞቀዋል?
6. መልካም ቤተሰባዊ ህይወትን ለመመስረት
7. እቅድን ለማሳካት
8. የምጣኔ ሀብት እድገት ለማምጣት
9. ለመንፈሳዊ ህይወት ምሳሌ የሚሆኑ ሰዎችን ለማግኘት
10. ቅዱስ ትውፊትን ለመከተል
3.4.2.መንፈሳዊ ኑሮ በአካባቢያችን
አካባቢያቸችን ከግቢያችን ከመኖሪያ ህንጻችን ይጀምራል፡፡በዚያም
መንፈሳዊነታችንን በተለያዩ መንገዶች ልንገልጥ ይገባናል እንደ ምሳሌ
1. ስንገባ እና ስንወጣ ለጎረቤቶቻችን ሰላምታ መስጠት
2. ለችግሮቻቸው ፈጥነን መፍትሄ መስጠት
3. ሊረዳ የሚገባውን ለይተን የምንረዳ፣ የግጭት ምክንያቶችን የምናጠፋ፣
ግጭቶች ከተከሰቱ ደግሞ ፈጥኖ ይቅርታ የምንጠይቅ እና በትህትና ነገሮችን
የምናረግብ መሆን ይገባል
4. አካባቢያችን የሚጠይቀንን ማንኛውም ዓይነት ማኅበራዊ ተሳትፎ ማድረግ
ምሳሌ ጽዳት፣ እድር፣… እንዲሁም አካባቢያችንን በንጽህና መጠበቅ፣
በደስታ እና በሀዘን ጊዜ መረዳዳት፣ ቤታችን ጠርተን ዝክሩን ተበል ጠዲቁን
ማድረስ፣ ሻይ ቡና ተጠራርቶ ስለ ህይወታቸው ማውራት፣ በተቻለን መጠን
በሁሉ ነገር በጎ አርአያ መልካም አብነት ሆኖ መገኘትና ሌሎቸችንም ከእኛ
የሚጠበቁ ነገሮችን ማድረግ ይገባል፡፡
ማኅበር ኀብረ አንድ ሆነ ካለው የግእዝ ግስ የተገኘ ሲሆን ማኅበር ኅብረት አንድነት
ማለት ነው፡፡ዘሌ 4፤13
ሙሴ
ሙሴ የእስራኤል ነቢይ መስፍንም ነበር ህዝቡን በመልካም መርቶ ወደ
ምድረ ርስት ያደረሰ ነው፡፡
የሚመረጠውም ሙሴ የሚባለውም ሰውን በህይወት፣ በትምህርት፣
በትሩፋት እና በአመራሩ ህዝቡን መርቶ ለመንግስተ ሰማያት ማብቃት
ይገባዋል፡፡ ሙሴ የሚመረጠው በጸሎትና በእጣ ነው፡፡ወንድም ሴትም ሊሆኑ
ይችላሉ፡፡ለሴቶች ማኅበር ሴት ለወንዶች ደግሞ ወንድ ይሆናል፡፡
ሙሴው ለማኅበርተኞቹ በማንኛወም ችግራቸው ወቅት ፈጥኖ
የሚደርስላቸው በበጎ አጠባበቅ የሚጠብቃቸው መሆን አለበት
ሙሴው በሶስት ይከፈላል
ሙሴ ሁሉን የሚያከናውን ለሁሉ ተጠሪ ሲሆን
ደርገ ሙሴ ደግሞ የአገልግሎት ተባባሪው ነው፡፡
ግልገል ሙሴ ሙሴው በሌለበት ወቅት ሙሴውን ሆነው የሚያስተናብሩ
የሚያስተናግዱ ናቸው፡፡
የሙሴ ተግባር
1.አዲስ አባል ወደ ማኅበሩ ሲመጣከማኅበሩ ጋር መክሮ ፈቃድ ይሰጣል
3. ቃለ እግዚአብሔርን ይማማራሉ
6. ቅዱሳንን ይዘክራሉ
7.የተጣላ ያስታርቃሉ
8. ችግረኛ ካለ እንደቆሮንቶነስ ምዕመናን እርዳታ አሰባስበው ይጠይቃሉ 1 ቆሮ 8፤
ሰአልናከ
ሰአልናከ ማለት ለመንህ ማለት ሲሆን ይህ በቤተክርስቲያናችን ደወል ተደውሎ
የኅብረት ጸሎት ደርሶ ማኅበሩ የሚበላው የሚጠጣው ነገር ሰአልናከ ይባላል
ከጸሎት ከልመና በኋላ የሚደረግ በመሆኑ ይህ መደረግ የሚገባው ምንም ምግብ
ሳይበላ ነው ምክንያቱም አንድ ነን ልባችን አንድ ነው ሲሉ ነው እንዲህ
የሚያደርጉት የመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖች በአንድ ልብ ይኖሩ እንደነበር፡፡የሐዋ 2፤
ቅዳሜና እሁድ በዓለ ሃምሳ ሲሆን በጠዋት ነው ማኅበሩ የሚሆነው፡፡ይህ ከስጋ
ወደሙ ጋር የሚገናኝ አይደለም አንዳንዶች እንደዛ የሚያስቡ አሉ፡፡
3.ብሔራዊ( ሲቪል)
መንፈሳዊ ጋብቻን ሰው እንደየ እምነቱ የሚፈጽመው ሲሆን
ባህላዊ ጋብቻ ማኅበረሰቡ እንዳደገበት አካባቢ ባህል የሚፈጽመው ነው
ብሔራዊ የሚባለው መንግስታዊ የሆነ እና ይህንን ጉዳይ ለማስፈጸም በተዘጋጀ
አካል የሚደረግ የጋብቻ ዓይነት ነው፡፡ ቅዱስ ተርቱሎስ ከቤተክርስቲያን እውቅና
ውጭ የሚደረግ ግቢ ሁሉ የዝሙት መንገድ ነው ብሎ አስተምሯል በመሆኑም
በባህላዊ እና በብሔራዊ ( ማዘጋጃዊ) ግቢ የፈጸሙ ሁሉ ጋብቻቸውን በህገ ቤተ
ክርስቲያን ሊያጸኑት ይገባል፡፡