Professional Documents
Culture Documents
ምሥጢራትና ሥርዓት
፳፻፯ ዓ.ም
1
መቅድም
ቅድስት ቤተክርስቲያን ለልጆቿ ቅዱስ ቃሉን እየመገበች ምሥጢራትን
እየፈጸመችና በሥነ ምግባራት ሠናያት እያነፀች ባሕረ ዓለምን ቀዝፋ ወደ ዕረፍት ወደብ
የምታሻግር /የምታደርስ/ መንፈሳዊት መርከብ ናት፡፡ በኢየሩሳሌም (በጸኑት)፣ በይሁዳ
(አምነው፤ እየወደቁና እየተነሡ በሚታገሉት)፣ በሰማርያ (አምነው በካዱት) ና በምድር
ዳርቻ (ፈጽመው ባላመኑት) መካከል በምታደርገው ሐዋርያዊ አገልግሎት የምትመራበት
መንፈሳዊ ሥርዓትም ባለቤት ናት።(ሐዋ፩፥፰)።
3
መክሥተ አርእስት
ርእሰ ጉዳይ
ተ/ቁ ገጽ
ጋር ያላቸው ግንኙነት፤
፫.፩. አመሠራረት፤
፫.፪. አስተምህሮ፤
፫.፫. አፈጻጸም ፤
፬.፩. አመሠራረት፤
፬.፪. አስተምህሮ፤
4
፬.፫. አፈጻጸም፤
፭.፩. አመሠራረት፤
፭.፪. አስተምህሮ፤
፭.፫. አፈጻጸም፤
፭.፬. ቅዳሴ፤
፮.፩. አመሠራረት፤
፮.፪. አስተምህሮ፤
፮.፫. አፈጻጸም፤
፯.፩. አመሠራረት፤
፯.፪. አስተምህሮ፤
፯.፫. አፈጻጸም፤
፰.፩.አመሠራረት፤
፰.፪. አስተምህሮ፤
፰.፫. አፈጻጸም፤
፱.፩. አመሠራረት፤
፱.፪. አስተምህሮ፤
5
፱.፫. አፈጻጸም፤
፲. በዓላት፤
• በዋዜማ፤
• በዕለቱ (ፍጻሜ)፤
፲.፬. ዋና ዋና በዓላት፤
• ንግሥ፤
፲፩.፭. ዕጣን፤
6
መግቢያ
ሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን እግዚአብሔር አምላካችን የጸጋው ግምጃ ቤት
በሆነችው ቤተ ክርስቲያን በኩል የሚያድላቸው የድኅነትና የአገልግሎት ሥጦታዎች
ናቸው፡፡ እነዚህም ሰዎችን ለመዳን ማለትም የእግዚአብሔርን መንግሥት ለመውረስ
የሚያበቁ፣ ቀጣይነት ላለው ክርስቲያናዊ ሕይወት መጠናከር የሚያስፈልጉ፣ በቤተ
ክርስቲያን አገልግሎት የሚያጸኑና ፈውስ ሥጋ፣ ፈውስ ነፍስ የሚያሰጡ ናቸው።
7
• ምሥጢረ ክህነትና አፈጻጸሙ፤
• በዓላትና
• ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን፣
• ሥርዓተ ቤተክርስቲያንና
8
ምዕራፍ አንድ፡-
መግቢያ
9
❖ ቤተ ክርስቲያን ማለት ምን ማለት ነው?
• ታቦተ እግዚአብሔር፣
• መስቀለ ክርስቶስ፣
• ቅዱሳት መጻሕፍት፣
10
• ቅዱሳት ሥዕላት፣
• ንዋያተ ቅዱሳት፣
• ማኅሌት፣
• ሰዓታት፣
• ኪዳን፣
• ቅዳሴ፣
• መዝሙር፣
• ቅኔ፣
• ሊቃነ ጳጳሳት፣
• ቀሳውስት፣
• ዲያቆናት፣
• ዘማርያን፣
11
• ሰባክያን፣
• አንባብያንና
• ምእመናን ሁሉ ናቸው፡፡
እነዚህ ከዚህ በላይ የተዘረዘሩት ካህናትና ምእመናን በቤተ ክርስቲያን አንድ ሆነው
እግዚአብሔርን ያመሰግናሉ፡፡ ቀሪዎቹም እሱን የማመስገኛ መንገዶች መሣሪያዎችና ጸጋ
እግዚአብሔርን የሚሳተፉባቸው መድረኮችና ምሥጢራት ናቸው። ይህቺ ቤት ከባዶ
አዳራሽ የምትለይበት ዋናው ምሥጢርም እነዚህን ሁሉ የሠራና የፈቀደ ያዘዘም
እግዚአብሔር በረድኤት ስለሚኖርባት ነው።
12
እንደማይችል ሁሉ ቤተ ክርስቲያንም ከክርስቶስ ተለይታ መኖር አትችልም መስቀለ
ክርስቶስን ከአናቷ ላይ ጉልላቷ ላይ በክብር የምታስቀምጠውም ለዚህ ነው እያንዳንዱ
ክርስቲያን የክርስቶስ አካ በመሆኑ ነው ክርስቲያኖችን ከዋሉበት አላሳድር ካደሩበትም
አላውል ብሎ ለሚያሳድዳቸው ለሳውል ጳውሎስ ሳውል ሳውል ለምን ታሳድደኛለህ አንተ
የምታሳድደኝ የናዝሬቱ ኢየሱስ ነኝ (ሐዋ ፱፥፬-፮)።በማት ጌታችን የጠየቀውና
የመለሰለት።
• ፩ነገ. ፱፥፫
13
፩.፪ የቤተ ክርስቲያን አመሠራረት
15
ለአምልኮተ እግዚአብሔር እንዲመች በየሀገሩ፣ ምእመናን እየበዙ፣ ሕንፃ ቤተክርስቲያን
እየተሠራ ቤተክርስቲያን በየወገኑ ተስፋፍታ ቅርንጫፎቿ ቢበዙም፤ በቦታና በጊዜ
ቢራራቁም በብሔርና በቋንቋ ቢለያዩም ግንዷና መሠረቷ፣ እምነቷና ሥርዓቷ ታሪኳና
ትምህርቷ፣ መመሪያና ትውፊቷ አንድ ነው፡፡ ይህም በአንድ የወይን ግንድ ላይ በቅለው
በአንድነት አንድ ዓይነት ምግብ እየተመገቡ እንደሚያድጉ የወይን ቅርንጫፎች ማለት
ነው፡፡ (ዮሐ. ፲፭፥፩-፯)፡፡ እኛ ክርስቲያኖችም የአንዲቱ አካል የቤተ ክርስቲያን አባሎች፣
የክርስቶስ አካሎች ነን፡፡ በአንድ እግዚአብሔር በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
የተጠመቅን፣ የአንድ የክርስቶስን ሥጋና ደም የተቀበልን በመሆናችን አንድ የክርስቶስ
አካልም ነን፡፡ (፩ቆሮ. ፲፥፲፮-፲፯)፡፡ በዚህም ሁላችንም አንድ የክርስቶስ አካል (ሥጋ)
በመሆናችን አንድ ቤተሰብ፣ አንዲትም ቤተ ክርስቲያን ነን ማለት ነው፡፡
18
እነርሱም ድውያነ ሥጋን በተአምራት፣ ድውያነ ነፍስን በትምህርት እየፈወሱ ዓለምን ዕጣ
በዕጣ ተካፍለው በወንጌል መረብነት ምእመናንን በውቅያኖስ ከተመሰለው ዓለም ሰበሰቡ፡፡
አንዲት፣ ቅድስትና ኩላዊት የሆነች ቤተ ክርስቲያንንም በመላው ዓለም አስፋፉ፡፡ ክርስቶስ
የእርሱ የባሕርይ ገንዘቦች የሆኑትን ሀብታት በጸጋ አጎናጽፏቸዋልና፡፡ (ማር. ፲፮፥፲፭-፲፱
ዮሐ. ፳፥፳፪-፳፫።፳፩-፲፭-፲፰)፡፡ “ሐዋርያዊት” የሚለው ቃል ለእውነተኛይቱ ቤተ
ክርስቲያን መገለጫ ባሕርይዋ፣ አርማና ምልክቷ ነው፡፡ ትውፊቷ፣ ትምህርቷ፣ ሥርዓቷና
ሥልጣነ ክህነቷ ከአባቶቻችን ከሐዋርያት ተያይዞ የመጣና ሰንሰለቱ ያልተቋረጠ፣ ዛሬ ከኛ
ዘመን የደረሰና ነገም እስከምጽአት የሚጓዝ በመሆኑ ቤተ ክርስቲያን ሐዋርያዊት
ተብላለች፡፡ እነዚህን የቤተክርስቲያን ባሕርያት ማወቅ ምእመናን በቤተክርስቲያን
እንዲኖሩ ኋላም የመንግሥተ ሰማያት እድምተኞች እንዲሆኑ ያነሳሳቸዋል።ሐዋርያዊ
ትውፊት፣ ትምህርት፣ ሥርዓትና ሥልጣነ ክህነት ሳይኖር ቤተ ክርስቲያን ልትኖር
አትችልምና።
ማጠቃለያ፦
የቤተ ክርስቲያንን ፍቺ ከሕንፃውና ከምእመናን ጉባኤ አንጻር ብናስቀምጠውም የተለያዩ
ናቸው ማለት እንዳልሆነ መታወቅ ይኖርበታል። ሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑ ያለ ምእመናን
ጉባኤ (ማኅበረ ካህናት ወማኅበረ ምዕመናን) ቤተ ክርስቲያን ሊባል አይችልም፡፡ የማኅበረ
ካህናትና የማኅበረ ምእመናን ጉባኤም ይነስም ይብዛም ያለ ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን
ሊታሰብና ሊነገር አይችልም፤ መጀመሪያውኑም ያለ ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን መንፈሳውያን
ዜጎችና ክርስቲያኖች የመንግሥተ ሰማያት ዕድምተኞች ሊሆኑ አይችሉም፡፡ አንዱን
ስናነሣ ሁለተኛውም አብሮት እንዳለ መረዳት ጠቃሚ ይሆናል። በውስጡ የሚከናወን
አገልግሎት፣ ሥርዓት፣ ምሥጢራት፣ ንዋያተ ቅዱሳትና አገልጋዮቹ ለብቻቸው መቆም
የሚችሉ ሳይሆኑ የተሰናሰሉ ናቸው። ቤተ ክርስቲያን በሐዋርያትና በነቢያት መሠረት ላይ
ክርስቶስ ያነፃት (የሠራት) ሕይወት አካሉ ናት፡፡ በቅድስና ያጌጠ (የተሸለመ)ና
ከሐዋርያት የተገኘ አንድ መሠረት፣ አንዲት ሕንፃ፣ አንድ ሥርዓት፣ አንድ ትውፊት፣
አንድ ትምህርተ ሃይማኖትና አንድ የሥልጣነ ክህነት መስመር ስላላት በምንም ዓይነት
ምድራዊ መለኪያ ልትመዘንና ልትከፋፈል የማትችል ናት፡፡ የሰውን ልጆች ሁሉ ወደ
ድኅነት ወደብ የምትጠራ፣ የምትቀበል፣ የምትመግብ፣ የምታሳድግና ለፍሬ የምታበቃ እመ
ብዙኅን (የብዙዎች እናት) ናት፡፡ በምድር ያለች የእግዚአብሔር ቤተ መንግሥት
ስለሆነችና ሰማይና ምድርን የምታገናኝ በመሆኗ ኩላዊት ናት:: የቤተ ክርስቲያን ልጅ
የሆነ ሁሉ እንደ ቤተ ክርስቲያን አባልነቱ የቤተ ክርስቲያንን ተልዕኮ (ዓላማ) ከዳር
ከማድረስ (ከማስፈጸም) አኳያ የድርሻውን ሱታፌ ማበርከት ይኖርበታል።
ዋቢ መጻሕፍት
19
• ዲ/ን ያሬድ ገ/መድኅን፤ ኆኅተ ሰማይ፤ ማኀበረ ቅዱሳን፤ ፲፱፻፺፮፤ አ/አ።
• ማ/ቅ፤ ትምህርተ ሃይማኖት ርትዕት፤ ማኀበረ ቅዱሳን፤ ፲፱፻፺፫፤ አ/አ።
• ሊቀ ካህናት ክንፈ ገብርኤል አልታየና ቀሲስ ጌታቸው ደጀኔ፤ ሥርዓተ
ቤተክርስቲያን፤ ማኀበረ ቅዱሳን፤ ፲፱፻፺፯፤አ/አ።
• የኢት/ኦ/ተ/ቤ/ክ፤ ፍትሐ ነገሥት ንባብና ትርጓሜው፤ ትንሣኤ ማሳተሚያ ድርጅት፤
፲፱፻፺፤ አ/አ።
• የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ፤ መጽሐፍ ቅዱስ፤ የኢትዮጲያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኀበር፤ ፳፻፤ አ/አ።
• ዲ/ን ዳንኤል ክብረት፤ኦርቶዶክስ መልስ አላት፤EAMERSEN፤2000፤ አ/አ።
• ሊቀ ጉባኤ አባ አበራ በቀለ፤ ትምህርተ ሃይማኖትና ክርስቲያናዊ ሕይወት፤ ማኀበረ
ቅዱሳን ፤1996፤ አ/አ።
• ክርስቲን ሻዮ፤ መ/ሰ ዳኛቸው ካሳሁን፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ
ትውፊትና መንፈሳዊ ሕይወት፤ ማኅበረ ቅዱሳን፤ 1999፤ አ/አ።
• የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ፣ መጽሐፈቅዳሴ፣ ትንሣኤማሳተሚያድርጅት፣ ፲፱፻፹፰፣ አዲስ አበባ።
20
ምዕራፍ ሁለት
ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያንና ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ከነገረ
ድኅነት ጋር ያላቸው ግንኙነት (፩ ሰዓት)
መግቢያ
ነገረ ድኅነት በክርስቶስ ሰው መሆንና ቤዛነት ለሰው ልጆች ሁሉ እንዲያው በነጻ
የተሰጠ የሕይወት ፈቃድ ነው። ይህን የሕይወት ፈቃድ ለሰው ልጆች ሁሉ እንድትናኝ
(እንድትሰጥ) ሥልጣንና ሓፊነት የሰጠው ደግሞ ለቤተ ክርስቲያን ነው፡፡ በዚህ ምዕራፍ
ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያንና ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ከነገረ ድኅነት ጋር ያላቸው
ትስስር (ግንኙነት) ተገልጧል። በዋናው ርእስ ሥርም፡-
21
፪.፩ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን እነማን ናቸው?
ውድ አንባቢ ሆይ፦
ውድ አንባቢ ሆይ፥
23
፪.፪ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ምንድነው?
የተከበሩ አንባቢ ሆይ፦ በምዕራፍ አንድ የተማሩትን ያስታውሳሉን? እስቲ ከዚህ በታች
የቀረቡትን ጥያቄዎች በማሰላሰል ለመመለስ ይሞክሩ፡፡
፩ኛ. የቤተ ክርስቲያንን ልጆች በአንድ መስመር ለመምራት፣ ወጥና ዘላቂ በሆነ መንገድ
እንዲጓዙ ለማስቻል ሥርዓት ያስፈልጋል፡፡ ለምሳሌ፡- ቤተ ክርስቲያን በየትኛውም ክፍለ
ዓለም ብትታነፅም /ብትሠራም/፣ በየትኛውም ዓይነት ቋንቋ ብትገለገልም፣ አገልግሎቷን
ለየትኛውም ዓይነት ሕዝብ ብታቀርብም መሠረተ እምነቷ፣ የምሥጢራት አፈጻጸሟና
ሁለንተናዊ አገልግሎቷ ወጥና ዘላቂ (የማይቀያየር) በሆነ ሥርዓት መመራቱ የግድ ነው፡፡
ይህ ካልሆነ ግን አስተማሪውና ተማሪው፣ ተናጋሪውና ሰሚው፣ ቀዳሹና አስቀዳሹ፣
አገልጋዩና ተገልጋዩ፣ እረኛውና በጉ፣ ጀማሪውና ተከታዩ … ወዘተ ስለማይታወቅ
የተደበላለቀ (ውጥንቅጡ የወጣ) ይሆናል፡፡ ለዚህ ነው ቅዱስ ጳውሎስ “ነገር ግን ሁሉን
በአገባብና በሥርዓት አድርጉ፤” (፩ቆሮ ፲፬፥፵) በማለት ያስተማረው፡፡
፪ኛ. የክርስቶስ አካላት፣ የቤተ ክርስቲያንም አባላት የሆኑት ካህናትና ምእመናን አንድ
ልብና አንድ አሳብ ለመሆን የሚችሉት አንድ ዓይነት ሥርዓት ሲኖራቸውና ሲመሩበት
ነው፡፡ አለበለዚያ አንዱ ሲያስተምር አንዱ የሚዘምር፣ አንዱ ሲጀምር አንዱ የሚጨርስ፣
አንዱ ሲያበራ አንዱ የሚያጠፋ፣ አንዱ ሲከፍት አንዱ የሚዘጋ … ወዘተ ይሆንና ቤተ
ክርስቲያን ትርምስና ሁከት መለያየትም የሚነግሥባት ቤት ትሆናለች:: ሐዋርያው ቅዱስ
ጳውሎስ “የተጻፈው ሁሉ በመታገሳችንና መጻሕፍትን በማመናችን ተስፋችንን እናገኝ
ዘንድ እኛ ልንማርበት ፤ የትዕግስትና የመጽናናት አምላክ እግዚአብሔር እንደ ኢየሱስ
ክርስቶስ ፈቃድ እርስ በርሳችን አንድ ሀሳብ መሆንን ይስጠን፤ ሁላችን አንድ ሆነን
በአንድ አፍ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እግዚአብሔርን እናመሰግነው ዘንድ፡፡” (ሮሜ
15-4-7) በማለት እንደተናገረው ክርስቲያኖች አንድ ሀሳብ መሆንና አንድ ሆነው በአንድ
አፍ እግዚአብሔርን ማመስገን የሚችሉት ወጥ በሆነ ሥርዓት መመራት ሲችሉ ነው፡፡
ቅዱሳን ሐዋርያት ይህን ስለተረዱ ነው በእግዚአብሔር መንፈስ ተቃኝተው ስምንቱን
የሥርዓት መጻሕፍት የሠሩልን፡፡ ዳግመኛም ቅዱስ ሉቃስ “ያመኑትም ሁሉ አንድ ልቡና
አንዲት ነፍስ ሆነው ይኖሩ ነበር፡፡” (ሐዋ 4፡32) በማለት የጻፈልንን ብንመረምረው አንድ
ልብና አንዲት ነፍስ የመሆን ምሥጢሩ በሥርዓት መመራት መተባበርም መሆኑን
ለመረዳት አያዳግትም፡፡
25
አዘገጃጀት፣ የመብሊያው ሰዓት፣ የአመጋገቡ ሂደትና የተመጋቢዎቹ ዝግጅት በዝርዝር መታዘዙ
ሥርዓት መሆኑንና አዛዡም እግዚአብሔር መሆኑን ማስተዋል ይገባል፡፡ (ዘፀ 12፡6-15)፡፡
• መጻሕፍተ ብሉያት፣
• መጻሕፍተ ሐዲሳት፣
• የሐዋርያት ሲኖዶሳት፣
• ሥርዓተ ጽዮን፣
• አብጥሊስ፣
• ትእዛዝ ፣
• ግጽው፣
• ዲድስቅልያና
26
• ቀሌምንጦስ የሚባሉትን ያካትታል፡፡
በተጨማሪም
• ፍትሕ መንፈሳዊና
27
፪.፬.ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያንና ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን
ከነገረ ድኅነት ጋር ያላቸው ግንኙነት
ቃለ ወንጌልን በመስማት የሚጀምረው የሰው ልጆች ድኅነት በእምነት የሚመሠረት
ቢሆንም የተሟላ የሚሆነው ግን ምሥጢራትን በመፈጸም ነው፡፡ ይህም ድኅነት በአንድ
ጊዜ ተጀምሮ የሚያልቅ ባለመሆኑ በሰው ልጆች ምድራዊ ሕይወት ሁሉ ከሰይጣን፣
ከእኩያት ኃጣውእና ከፍትወታት እኩያት ጋር በሚደረግ ረጅም መንፈሳዊ ተጋድሎ
የሚረጋገጥ ነው፡፡ በዚህ መንፈሳዊ ጉዞ ውስጥ ሁሉ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን
የሚኖራቸው ሚና ከፍተኛ ነው፡፡ በዚህ መሠረት አንድ ሰው መዳን ከፈለገ ቃለ
እግዚአብሔርን መስማት፣ ማመን፣ መጸለይ፣ ሌሎች ትእዛዛትን መፈጸምና የምሥጢራተ
ቤተ ክርስቲያን ተካፋይ መሆን ይኖርበታል፡፡ “… በፍርሃትና በመንቀጥቀጥ ሆናችሁ
ለድኅነታችሁ ሥሩ፡፡” (ፊልጵ. ፪፥፲፪፡፡) እንደተባለ፤ ሁላችንም የምሥጢራተ ቤተ
ክርስቲያን ተሳታፊ ለመሆን መትጋት ይኖርብናል፡፡ ምክንያቱም “ቃሉን የምታደርጉ ሁኑ
እንጂ ራሳችሁን እያሳታችሁ የምትሰሙ ብቻ አትሁኑ፡፡” (ያዕ. ፩፥፳፪፡፡) ተብሎ
ተጽፏልና፡፡ ክርስቶስን ማመናችንና መቀበላችን የሚረጋገጠው፣ በጸጋው መዳናችንም
የሚታወቀው ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያንን በመፈጸም ብቻ መሆኑን ማመን ይኖርብናል፡፡
ይህንንም የምናገኘው በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ብቻ ስንሆን ነው፡፡ ከቤተ ክርስቲያን ውጪ
መሆንና ራስን በራስ ግላዊ አስተያየትና ፍልስፍና ከቤተ ክርስቲያን ምሥጢራት ገለልተኛ
ማድረግ ከድኅነት መስመር መራቅ ነው፡፡
28
ማጠቃለያ
ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ለመንፈሳውያን ልጆቿና በጥላዋ ሊጠለሉ ለሚፈልጉ ሰዎች ሁሉ
የምትፈጽመው አገልግሎት አላት፡፤ አዳዲስ አማንያንን የቤተ ክርስቲያን አባል፣ የክርስቶስ
አካል የምታደርግባቸው ምሥጢራት አላት፡፡ ነባር ልጆቿን በመንፈስ የምትመግብበት
በሃይማኖትም የምትጠብቅበት ምሥጢራትም ገንዘቦቿ ናቸው፡፡ ሁሉንም በቅዱሳት
መጻሕፍት አስተምህሮ መሠረት የምታከናውንበት እንከን የለሽ ሥርዓት ባለቤትም ነች፡፡
ለዘላለማዊ ሕይወት የተጠሩ ሁሉ ያለእነዚህ ምሥጢራት ሊድኑ እንደማይችሉ ቤተ
ክርስቲያን አስተምራለች፡፡ በምዕራፍ ሁለት ሥር የሰፈረው ርእሰ ጉዳይና ዝርዝር
ማብራሪያዎች ይህንኑ እንዲገልጡ ሆነው የተዘጋጁ ናቸው፡፡
ዋቢመጻሕፍት
• ማ/ቅ፤ ትምህርተ ሃይማኖት ርትዕት፤ ማኀበረ ቅዱሳን፤ ፲፱፻፺፫
አ/አ።
29
ምዕራፍ ሦስት፡-
• አስተምህሮ፣
• አፈጻጸምና
፫.፪ አስተምህሮ
• ጥምቀትን የመሠረተው ጌታችን ነው፡፡ ጌታችን የተጠመቀውም በ፴ ዘመኑ ነው፡፡
የእኛ ቤተክርስቲያን ግን ሕፃናትን ታጠምቃለች ፤ ይህ ልክ (ትክክል) ነውን?
እንዴት?
ቀደም ብሎም የእግዚአብሔር ወገን የመሆን የቃል ኪዳን ምልክት የሆነው ግዝረት
ሕፃናት በተወለዱ በስምንተኛው ቀን ይፈጸም ነበር፡፡ (ዘፍ. ፲፯ ፥፩‐ፍጻሜው፡፡ ቈላ.
፪፥፲፩‐፲፬፡፡)
31
በሐዲስ ኪዳን መጻሕፍትም የሕፃናትን ጥምቀት በተመለከተ በርካታ ማስረጃዎች
አሉ፡፡ ሐዋርያት አባቶቻችን አማኞችን ባጠመቁ ጊዜ እንደ ክርስቶስ ፴ ዓመት
እስኪሞላቸው የሚጠብቁ አልነበረም፡፡ ሁሉንም (ሕፃናትንም ጭምር) በተገኙበት ዕድሜ
በማጥመቅ ሀብተ ወልድና ስመ ክርስትና ያሰጧቸው ነበር እንጂ፡፡ እዚህ ላይ ሕፃናት
ባመኑ ወላጆቻቸው እምነት አብረው ይጠመቁ እንደነበር ልብ ማለት ያስፈልጋል፡፡ (ሐዋ.
፲፥፵፯-ፍጻሜ፤ ፲፩፥፲፬፤ ፲፮፥፲፭፡፴-፴፬፤ ፩ቆሮ. ፩፥፲፮፡፡) ከዚህም በተጨማሪ ጌታችን
ኢየሱስም “ሕፃናትን ተውአቸው፤ ወደ እኔም ይመጡ ዘንደ አትከልክሉአቸው፤ መንግሥተ
ሰማያት እንደ እነዚህ ላሉት ናትና፡፡” (ማቴ. ፲፱፥፲፬-፲፮፡፡) በማለት አዝዞናል።
፫.፫ አፈጻጸም
ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ምሥጢረ ጥምቀትን አምነው ሊጠመቁ ለሚቀርቡ ሁሉ
የምታጠምቅበት የተቀደሰ ሥርዓት አላት፡፡ በዚህም መሠረት አዳዲስ ተጠማቂያን ሀብተ
ወልድና ስመ ክርስትና እንዲያገኙ ታደርጋለች።
33
፩. ንዑሰ ክርስቲያን የሚጠመቁት የትንሣኤ ዕለት ከሆነ ተገቢውን ትምህርት ቀድመው
ተምረውና ንስሐ ገብተው በሰሙነ ሕማማት ሐሙስ ልብሳቸውን አዘጋጅተውና
ሰውነታቸውን ታጥበው በመጾም ቅዳሜ ሌሊቱን እሑድ ይጠመቃሉ፡፡ በሌላ ቀን ከሆነ
ደግሞ በዋዜማው ታጥበውና ጾመው ይዘጋጁና የመቁረቢያ ልብሳቸውን በንጽሕና
አዘጋጅተው በዕለቱ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሔደው ይጠመቃሉ፡፡
፬. ጥምቀቱ በትንሣኤ ከሆነ በዶሮ ጩኸት ጊዜ፤ በሌላ ቀንም ከሆነ መጠመቂያው ሰዓት
ሲደርስ ተጠማቂዎችን በመካነ ጥምቀቱ ያቆማቸዋል፡፡ ያውም ካልሆነ ካህኑ ማዩን
በብርት አድርጎ ሥርዓተ ጸሎቱን ያደርሳል፡፡
34
፲፩. ተጠማቂዎች መናገር ከቻሉ ራሳቸው፤ ካልቻሉም የክርስትና አባት (እናት) የሆኑት
ክርስቲያኖች የተጠማቂውን አውራ ጣት ይዘው ጸሎተ ሃይማኖትን በማንበብ
ሃይማኖታቸውን ይመሰክራሉ፡፡
፲፪. ሥርዓተ ቅዳሴውን አድርሰው፣ መጽሐፈ ክርስትናውን ደግመው ማዩን ከባረኩ በኋላ
ነው ማጥመቅ የሚጀምሩት፡፡ የ፵ እና የ፹ ቀን ሕፃናት ከተጠመቁ በኋላ ንዑሰ
ክርስቲያን ወንዶችና ሴቶች ይጠመቃሉ፡፡
፲፭. በዕለቱ ክርስትና የተነሡ (የተጠመቁ) ሕፃናትና ንዑሰ ክርስቲያን የነበሩ አዳዲስ የቤተ
ክርስቲያን ልጆች ከሌሎች ቆራብያን አስቀድመው ቅዱሱን ቁርባን ይቀበላሉ፡፡
ማጠቃለያ
በርሰ ጉዳዩ ሥር ስለ ምሥጢረ ጥምቀትና ዝርዝር አፈጻጸሙ እንዲሁም ስለሚያስገኘው
ጸጋ በመጠኑ ተረድተናል፡፡ ምሥጢረ ጥምቀትን በማስመልከት የሚነሡትን አንዳንድ
ወቅታዊ ጥያቄዎች ለመመለስም ተሞክሯል፡፡ ይህም ግንዛቤያችንን በማስፋት
ትክክለኛውን የአፈጻጸም ሥርዓት ተከትለን እንድንጓዝ፣ በልምድ ያጣመምናቸውን
አቃንተንና ያጐደልናቸውንም ሞልተን እንድናገለግልና እንድንገለገል ይረዳናል፡፡ በዚህም
መሠረት ከራሳችን ተርፈን ለሌሎች ወገኖቻችንም የቀናውን ክርስቲያናዊ አስተምህሮ፣
ትውፊት፣ ሥርዓትና ታሪክ ማድረስ (ማስተላለፍ) ይጠበቅብናል።
ዋቢ መጻሕፍት
• ማ/ቅ፤ ትምህርተ ሃይማኖት ርትዕት፤ ማኀበረ ቅዱሳን፤ ፲፱፻፺፫፤
አ/አ።
36
• ሊቀ ጉባኤ አባ አበራ በቀለ፤ ትምህርተ ሃይማኖትና ክርስቲያናዊ
ሕይወት፤ ማኀበረ ቅዱሳን፤ 1996፤ አ/አ።
ምዕራፍ ዐራት
፬.፩ አመሠራረት
ሜሮን ማለት ቅብዐ ቅዱስ፣ የተባረከ ሽቱ፣ ብፁዓን ጳጳሳት ከበለሳንና ከዕፀወ ዕጣን
ከአስጳዳቶስ ከሌላም ከብዙ ዓይነት ሽቱ፣ ተገቢውን ሥርዓተ ጸሎት ፈጽመው የሚያወጡት
ነው፡፡ (መጽ. ሰዋ. ወግስ መመዝ. ቃላት ሐዲስ ገጽ ፮፻፰፡፡)
4.፪ አስተምህሮ
38
የሐዲስ ኪዳን ሥርዓተ ሜሮን መነሻውና ምሳሌው የብሉይ ኪዳን ቅብዐ ዘይት ነው፡፡
የተከበሩ አንባቢ ሆይ፦ ዘጸ ፴፥፳፪-፴፰ ያለውን ጥቅስ (ኃይለ ቃል) አንብቡና ፍሬ
አሳቡን በማስታወሻዎ ላይ አስፍሩ፡፡ የአዲስ ኪዳኑ ቅብዐ ሜሮን መነሻው ከላይ
እንደገለጽነው ይህ የብሉይ ኪዳኑ ቅብዐ ዘይት አጠቃቀምና አገልግሎት ነው፡፡ ፈቅዶና
መመሪያ ሰጥቶ ያስጀመረውም ራሱ እግዚአብሔር ነው፡፡ በዚህ ክፍለ ንባብ
እንደተብራራው በተጠቀሰው ኃይለ ቃል ውስጥ የከበረው የቅብዐት ዘይት፡-
• እንዴት እንደሚሠራና
ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ በሐዲስ ኪዳን በቅብዐ ሜሮን የሚታደለውን የመንፈስ ቅዱስ
ስጦታ በተመለከተ ሲያብራራ “እናንተስ ከቅዱሱ ያገኛችሁት ቅብዐት አላችሁ፤ ሁሉንም
ታውቃላችሁ፡፡ እውነትን የምታውቁ ስለሆናችሁ፣ ውሸትም ሁሉ ከእውነት እንዳልሆነ
ስለምታውቁ እንጂ እውነትን እንደማታውቁ አድርጌ አልጽፍላችኁም፡፡” (፩ዮሐ. ፪፥፳-
፳፪፡፡) በማለት አስተምሮናል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ከዚህ አሳብ ጋር ተመሳሳይ
የሆነ መልእክት “ከእናንተ ጋር በክርስቶስ ስም የሚያጸናንና የቀባን እግዚአብሔር ነው፡፡
ደግሞም ያተመንና የመንፈስ ቅዱስን ፊርማ በልቦናችን የሰጠን እርሱ ነው::” በማለት
አስተላልፎልናል፡፡ (፪ ቆሮ. ፩፥፳፩-፳፫፡፡)
39
(ሹመት)፣ ማስተዋል (ጥበብ)፣ ኃይል ብርታት)፣ ትዕግሥትና ጽናት የሚያጎናጽፋቸውን ጸጋ
መንፈስ ቅዱስ ለመቀበል እንዲችሉ በሚሾሙበት ጊዜ በሜሮን ይቀባሉ (ይከብራሉ)፡፡
፬.፫ አፈጻጸም
ምሥጢረ ሜሮን እንደሌሎቹ ምሥጢራት ሁሉ የራሱ የሆነ የአቀባብ (የአፈጻጸም)ሥርዓት
አለው፡፡
40
• የተጠማቂው ፴፮ቱ ሕዋሳት በሜሮን ሲከብሩ በሥርዓተ ቤተክርስቲያን የአቀባባቸው
ቅደም ተከተል የታወቀ ነው፡፡ ከላይ እንደገለጽነው ሁሉም በትእምርተ መስቀል
አምሳል የሚታተሙ (የሚቀቡ) ናቸው።
• ደረቱን ፣……………………………………………………………………....1
• ልቡን፣ ………………………………………………………………………..1
• እንብርቱን፣ ……………………………………………………………………1
• ትከሻዎቹን፣……………………………………………………………………2
• ማጅራቱን፣………………………………………………………………………1
• አንገቱን፣ ………………………………………………………………………1
• ክርኖቹን፣ ………………………………………………………………………2
41
• የእግር መገናኛዎቹን (መዳፎች)፣ ………………………………………………2
• ጉልበቶቹን፣ ……………………………………………………………………..2
፬.፬ የሚያስገኘው ጸጋ
❖ በምሥጢረ ሜሮን የሚገኘው ጸጋ ምንድነው?
43
ሰጠነው? ማንን አሠለጠንንበት? ክርስቶስን ወይስ ቤልሆርን? ለሚሉት ጥያቄዎች
ለራሳችን ምላሽ መስጠትና ራስን መመርመር ይገባል፡፡
ማጠቃለያ
45
ምዕራፍ አምስት
ምሥጢረ ቁርባንና አፈጻጸሙ (፪ ሰዓት)
መግቢያ
ምሥጢረ ቁርባን የምሥጢራተ ቤተክርስቲያንና የአገልግሎቶች ሁሉ የማረጋገጫ ማኅተም
ነው፡፡ ይህም ማለት ማንኛውም ምሥጢር በቤተክርስቲያን ከተፈጸመ በኋላ በምሥጢረ
ቁርባን ካልተፈጸመ (ካልታተመ) የቤተ ክርስቲያን ምሥጢር ሊባል አይችልም፡፡
በተጨማሪም በቤተክርስቲያን የሚከናወኑ አገልግሎቶች ሁሉ ማለትም ማኅሌቱ፣ ሰዓታቱ፣
መዝሙሩ፣ ቅኔው፣ ኪዳኑና የመሳሰሉት ሁሉ ፍጻሜያቸውን የሚያገኙት በቅዳሴ ነው፡፡
ቅዳሴውም የምሥጢረ ቁርባን መክበሪያ የጸሎታት ሁሉ ቁንጮ የሆነ፤ የምስጋናና የጸሎት
ሥርዓት ነው፡፡ በዚህ ምዕራፍ ሥር የምሥጢረ ቁርባን አመሠራረት፣ አስተምህሮ፣
አፈጻጸም፣ ቅዳሴውም ከዝርዝር ክፍሎቹና አፈጻጸሞቹ ጋር እንዲሁም በመጨረሻ
የሚያስገኘው ጸጋ የሚሉት የተብራሩበት ነው::
ቁርባን የሚለው ቃል መሠረቱ ከዕብራይስጥ ቋንቋ የመጣ ሲሆን “ስጦታ” የሚል ትርጉም
ይኖረዋል፡፡ በብሉይ ኪዳን ዘመን ሰዎች ለእግዚአብሔር የሚያቀርቡት የተወደደ ስጦታ
46
መሥዋዕትና ቁርባን ይባል ነበር፡፡ ከእንስሳት (ሥጋና ደም) የሚቀርበው መሥዋዕት፤
ከእህል ወገን የሆነው ደግሞ ቁርባን ይባል ነበር፡፡ በሐዲስ ኪዳን ግን አማናዊው ቁርባን
(መሥዋዕት) ሰዎች የሚያቀርቡት (የሚሰጡት) መባዕ ሳይሆን መድኃኔዓለም ክርስቶስ
ዓለሙን ለማዳን በቀራንዮ አደባባይ በአባቱ ፈቃድ፣ በመንፈስ ቅዱስ ፈቃድ፣ በራሱም
ፈቃድ በመስቀል ላይ ለዓለሙ ሁሉ ያቀረበው (የሰጠው) ቅዱስ ሥጋውና ክቡር ደሙ
ነው፡፡ ይህም በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ካህናት በቅዳሴ ጊዜ የሚያቀርቡት ኅብስት
የክርስቶስ ሥጋ፥ወይኑም የክርስቶስ ደም በመሆን የሚፈተት የሚቀዳ አማናዊ የአዲስ
ኪዳን ቁርባን ነው፡፡
፭.፩ አመሠራረት
ምሥጢረ ቁርባንን የመሠረተልን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን
የመሠረተበት ዕለትም በስቅለቱ ዋዜማ ጸሎት ሐሙስ በሚባለው ዕለት ነበር፡፡ የኦሪትን
መሥዋዕትና ቁርባን አሳልፎ (ሽሮ) የወንጌልን መሥዋዕት (ቁርባን) የመሠረተልን
በአልዓዛር ቤት ነበር፡፡ (ማቴ. ፳፮፥፳፮-፳፰፡፡)ከንጹሕ ስንዴ የተዘጋጀውን ኅብስትና
ከንጹሕ ወይን የተጨመቀውን ጽዋዕ እውነተኛ ሥጋውና ደሙ አድርጎ በመስጠት ነው
የመሠረተልን፡፡ (ዮሐ. ፮፥፴፭፡፡) በዕለተ ዓርብ የቆረሰውን ሥጋ፣ ያፈሰሰውንም ደም
አስቀድሞ በዋዜማው ኅብስቱንና ወይኑን ለውጦ ኅብስቱን ፲፫ ቦታ ፈትቶ (ቆራርሶ)፣
አብነት ለመሆንና ለማስደፈር ራሱ በራሱ እጅ ተቀብሎ ለቀደ መዛሙርቱ አቀበላቸው፡፡
በመስቀል ላይ ለአንዴና ለዘለዓለሙ የፈጸመው ይህ አምላካዊ የማዳን ሥራ እስከምጽአት
ድረስ ለዓለሙ ሁሉ በሥርዓተ ቅዳሴ ከብሮ እንዲታደልም (እንዲዳረስም) ሐዋርያት
አባቶቻችንን አዘዛቸው፡፡ በምሥጢረ ክህነት እንዳየነው የምሥራቹን ቃል እንዲያስተምሩ፣
በስሙ ሥርየተ ኃጢአትን እንዲሰጡና ሌሎች ምሥጢራትንም እንዲፈጽሙ የሚያስችል
ሥልጣነ ክህነትን ሰጣቸው፡፡ (ማቴ. ፳፰፥፲፱-፳፡፡ ሉቃ. ፳፪፥፲፬-፳፤ ፳፬፥፵፬-፶፡፡ ፩ቆሮ.
፲፩፥፳፫-፳፯፡፡) በዚሁ መሠረትም ሐዋርያት ቃሉን አስተምረው ካሳመኑ በኋላ
እያጠመቁና በአንብሮተ እድ መንፈስ ቅዱስን እያሳደሩ ምሥጢረ ቁርባንን እየፈጸሙ
በማቁረብ ተተኪዎቻቸውንም በዚሁ ሥርዓት በማጽናት ቤተ ክርስቲያንን እንዲህ
በማስፋፋት ኖሩ፡፡ የዚህ ሥልጣን አገልግሎትና ሓላፊነት ባለቤትም ቅድስት
ቤተክርስቲያን ብቻ ናት፡፡ ይህንንም አውቃ ስትፈጽመው ኖራለች፤ እየፈጸመችም
ትገኛለች፤ እስከ ዕለተ ምጽአት ድረስም ስትፈጽመው ትኖራለች::
፭.፪ አስተምህሮ
የተከበሩ አንባቢ ሆይ እነዚህን ጥያቄዎች ለመመለስ እየሞከሩ ራስዎን ይገምግሙ::
47
❖ እኛ በዚች ዓለም ላይ ስንኖር እሱን የምንፈልግበት ዕቅድና ዓላማ ከሱ አምላካዊ
ዕቅድና ዓላማ ጋር የተነናኘ ነው ብለው ያስባሉ? እንዴት?
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሌላው ዝርዝር ማብራሪያ የሰጠበት አንቀጽ ደግሞ አይሁድ
ላቀረቡት ጥያቄ በሰጠው ምላሽ መነሻነት የቀረበ ተጨማሪ ትምህርት ነው፡፡ በክርስቶስ
ለማመን እንዲችሉ ሙሴ ያደረገውን ዓይነት መና አውርዶ እንዲያሳያቸው ማለትም
48
ተአምር /ምልክት/ ማየት እንደሚሹ ጠየቁት፡፡ አምስቱን የገብስ እንጀራና ሁለቱን
ዓሣዎች አበርክቶ ካበላቸው በኋላ ይህን ድንቅ ተአምር ወደጎን ጥለው ሌላ ምልክት
እንዲያሳያቸው ጠየቁት፡፡ ጌታችንም ላባቶቻቸው በምድረ በዳ መና ያወረደላቸው ሙሴ
ሳይሆን እግዚአብሔር መሆኑን አስረግጦ ነገራቸው። በማስከተልም “የእግዚአብሔር እንጀራ
ከሰማይ የሚወርድ፤ ለዓለምም ሕይወትን የሚሰጥ ነው፡፡” (ዮሐ. ፮፥፴፫)።በማለት ከሰማይ
የወረደ እንጀራ ከፈለጉ አማናዊው የሕይወት እንጀራ እሱ ራሱ መሆኑን አረጋገጠላቸው፡፡
እነሱም ያንን እንደጀራ እንዲሰጣቸው ለመኑት፡፡ ቤተ አይሁድ አሁንም ሥጋዊ ከሆነው
አመለካከታቸውና መንገዳቸው ባለመመለሳቸው ሳይሠሩ ዘወትር እያፈሱና እየለቀሙ
የሚበሉትን የአባቶቻቸውን ዓይነት መና ነው እየለመኑ ያሉት፡፡ መድኃኔዓለም ክርስቶስ
ግን ስለሕይወት እንጀራ ማለትም ስለ ሥጋውና ደሙ መንገሩን በመቀጠል ዓይናቸውን
ወደ እውነተኛው የሕይወት እንጀራ (ምግብ) እንዲያዞሩ አሳሰባቸው፡፡
49
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋውን ቆርሶ፣ ደሙን አፍስሶ ከመስጠቱ፣ በስቅለቱም ዋዜማ
ምሥጢረ ቁርባንን ከመመሥረቱ አስቀድሞ በጎላ በተረዳ መንገድ ስለ ቅዱስ ቁርባን
አስተማረ፡፡ አይሁድም “ይህ እንበላ ዘንድ ሥጋውን ሊሰጠን እንዴት ይችላል?” ብለው
እርስ በርሳቸው ተከራከሩ፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም “እውነት እውነት እላችኋለሁ፤
የሰውን ልጅ ሥጋ ካልበላችሁ፣ ደሙንም ካልጠጣችሁ የዘላለም ሕይወት የላችሁም፡፡
ሥጋዬን የሚበላ÷ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው፤ እኔም በኋለኛይቱ ቀን
አነሣዋለሁ፡፡” (ዮሐ. ፮፥፶፫-፶፭፡፡) በማለት የተብራራ÷ የተረዳ÷ ሕይወትም የሆነ ቃሉን
ነገራቸው፡፡ ይህንና ይህን የመሰለውን እውነተኛ ትምህርት በጨመረና ባስተማረ ቁጥር
አይሁድ የበለጠ እየታወኩና እየተደናገሩ በክህደትም ልቡናቸውን እያጸኑ ሔዱ፡፡ ጌታችን
ኢየሱስ ክርስቶስ የሚገልጸውን እውነትና ሕይወት የሆነውን ትምህርት መሸከም የተሳናቸው
አይሁድ ወደኋላቸው ተመልሰው ሸሹ፡፡ ይከተሉት ከነበሩት ብዙዎቹ “ይህ የሚያስጨንቅ
ንግግር ነው፣ ማንስ ሊሰማው ይችላል?” (ዮሐ. ፮፥፷ ፤፤) እያሉ አንጐራጐሩና ወደ ኋላቸው
ተመለሱ፡፡ ጌታችንም ከአምስት ገበያ ሕዝብ መካከል ከእርሱ ጋር ጸንተው የቆዩትን
ዐሥራ ሁለቱን ደቀመዛሙርት “እናንተ ደግሞ ልትሔዱ ትሻላችሁን?” (ቁ. ፷፯) በማለት
ጠየቃቸው:: ለዚህም ጥያቄ ስምዖን ጴጥሮስ “አንተ የዘላለም የሕይወት ቃል እያለህ ወደ
ማን እንሄዳለን? እኛስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ክርስቶስ አንተ እንደሆንህ አምነናል፤
አውቀናልም፡፡” (ቁ. ፷፰-፷፱፡፡) በማለት ለእውነተኛ ክርስቲያኖች ሁሉ የሕይወት
መመሪያ የሚሆን መልስ ሰጠ፡፡
እነዚህ ጥያቄዎች በአንደበት ብቻ ሳይሆን በተግባርም ፈጣን ምላሽ የሚሹ ናቸው፡፡ ከሥጋ
ወደሙ መራቅ ከመስቀሉ መራቅ ነው፡፡ ከመስቀሉ መራቅ ደግሞ ከክርስቶስ መራቅ ነው፡፡
በጥቅሉ ከእግዚአብሔር መለየት ከዘለዓለማዊ ሕይወትም ወጥቶ ወደ ዘለዓለማዊ ሞት
50
መነዳት ነው፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እግዚአብሔር ነውና።
ከሥጋ ወደሙ ለመራቃችን ምንም ዓይነት ምክንያት ብንደረድር በክርስቶስ ፊት አሳማኝ
ሊሆን እንደማይችል መርሳት የለብንም፡፡ እግዚአብሔር ለኛ ያለውን ፍቅርና የከፈለውን
ውለታ ሊያስረሳና ሊሸፍን የሚችል የቱንም ያህል ምክንያትና ችግር ሊኖር አይችልም፡፡
ቅዱስ ጳውሎስ “ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል? መከራ ነውን? ኀዘን ነውን? ስደት
ነውን? ራብ ነውን? መራቆት ነውን? ጭንቀት ነውን? ሾተል ነውን?” (ሮሜ ፰፥፴፭፡፡)”
በማለት ያስተማረን ከላይ የገለጽነውን ቁም ነገር የሚያጠናክርልን ነው፡፡
51
፭.፫ አፈጻጸም
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፣
የሠራውንና ሐዋርያትና፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ያቆዩትን የተቀደሰ ሥርዓት ተከትላ
/መሠረት አድርጋ/ ምሥጢረ ቁርባንን ትፈጽማለች፡፡ በምትፈጽምበትም ጊዜ “ንዜኑ
ሞተከ ወትንሣኤከ ቅድስት ሞትህን የተቀደሰች ትንሣኤህን እንመሠክራለን፡፡” (ፍሬ
ቅዳሴ) እያለች ትዘምራለች፡፡ የምሥጢረ ቁርባን አፈጻጸም ከቅዳሴ ተለይቶ የሚታይ
ባለመሆኑ ከዚህ በታች ከቅዳሴው ሥርዓት ጋር አብረን በዝርዝር የምንመለከተው
ይሆናል፡፡
፭.፬ ቅዳሴ
አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ቃሉ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ በተባለው
መጽሐፋቸው “ቅዳሴ” የሚለውን ቃል “መቀደስ፤ አቀዳደስ፤ ቅደሳ፤ ቡራኬ፤ ምስጋና፤
የቁርባን ጸሎት “በማለት ይፈቱታል፡፡ (ገጽ ፯፻፹፬፡፡) ቅዳሴ ከምሥጢረ ቁርባን ጋር
በቀጥታ የተያያዘ ሲሆን ለሌሎቹ ምሥጢራትም የምሥጢርነታቸው ማረጋገጫ ማኅተም
ነው፡፡ ያለ ሥጋ ወደሙ ምሥጢራቱ በራሳቸው ምሉዕ ሊሆኑ አይችሉምና፡፡
፩ የዝግጅት ቅዳሴ
የዝግጅት ቅዳሴ በሌላ መጠሪያው ግብዓተ መንጦላዕት ይባላል፡፡ በዚህ ክፍል የሚቀርበው
ጸሎት ከመቅደስ በአፍአ (ከመጋረጃ ውጪ) የሚጸለይና ወደ መጋረጃው ውስጥ /መቅደስ/
ለመግባት አሐዱ ብሎ ለመቀደስም የሚያስችል ነው፡፡ ይህም “ሚ መጠን ግርምት ዛቲ
ዕለት-ይህች ዕለት ምንኛ የምታስፈራ ናት…” እስከሚለው ድረስ ያለውን የሚያካትት
ነው፡፡
52
ልብሰ ተክህኖ ከለበሰ በኋላ ቀጥታ የሚያመራው ቀደም ብለን እንደገለጽነው ወደ መቅደስ
ለመግባት የሚያስችለውን ጸሎት ወደ ማቅረብ ነው፡፡ ይህም ወደ እግዚአብሔር መቅደስ
ማደሪያ ለመግባት የሚደረገውን ጥንቃቄ ያሳያል የጸሎቶቹ ዝርዝር መገለጫም
እንደሚከተለው ይቀርባል፡፡
53
• በመጨረሻም “እግዚአብሔር አምላክነ ዘይነብር መልዕልተ ኩሉ…፤ ከሁሉ በላይ
ያለህ /የምትኖር/ እግዚአብሔር አምላካችን” የሚለውን የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅን
ጸሎት ሦስት ጊዜ ሰግዶ ይጸልያል፡፡
• ቀዳስያንና አስቀዳሾች ባንድነት “አንቲ ውእቱ መሶበ ወርቅ ንጹሕ እንተ ውስቴታ
መና ኅቡዕ ኅብስት ዘወረደ እምሰማያት ወሀቤ ሕይወት ለኵሉ ዓለም፤ ለዓለሙ
ሁሉ ሕይወትን የሚሰጥ ከሰማያት የወረደ የተሰወረ መና ያለባት የወርቅ መሶብ
አንቺ ነሽ” እያሉ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ኅብስቱን በያዘችው
መሶበ ወርቅ ምሳሌነት (አንጻር) ያመሰግኗታል፡፡ በዚህን ጊዜ ገባሬ ሠናዩ ቄስ
(ካህን) “እግዚአብሔር አምላክነ ዘተወከፍከ ቁርባነ አቤል ጻድቅ በውስተ በድው…፤”
እግዚአብሔር አምላካችን በምድረ በዳ የሠዋውን የአቤል መስዋዕት የተቀበልክ”
የሚለውን እየጸለየ መብራት የያዘው ዲያቆን ከፊቱ፣ ያልያዘው ከኋላ ሆነው
መንበሩን አንድ ጊዜ ይዞራሉ፡፡ ዲያቆኑም “እግዚአብሔር ይሬእየኒ…፤
እግዚአብሔር ይጠብቀኛል” (መዝ. ፳፪፥፩፡፡) የሚለውን ይደግማል፡፡
55
ተቀዳሚ ተከታይ የሌለው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ክቡር ምስጉን
ነው፣ መጽንዒ መንጽሒ የሚሆን መንፈስ ቅዱስም ክቡር ምስጉን ነው…፤“
የሚለውንና ተመሳሳዩን ጸሎት እየጸለየ መጀመሪያ ኅብስቱን በማስከተልም ወይኑን
፤ በመጨረሻም ለሦስተኛ ጊዜ ያንኑ ጸሎት እየጸለየ ኅብስቱንና ወይኑን ባንድነት
ይባርካል፡፡ ሕዝቡም “አሜን፤ አሜን፤ አሜን” ይላሉበመቀጠልም እየሰገደ
“ስብሐት ወክብር ለሥሉስ ቅዱስ ይደሉ፤ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ሥሉስ
ዕሩይ ኵሎ ጊዜ ይእዜኒ ወዘልፈኒ ወለዓለመ ዓለም አሜን፡፡ በዘመን በክብር አንድ፤
በአካል ሦስት ለሚሆኑ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ክብር ምስጋና ይገባቸዋል
ዛሬም ዘወትርም ለዘለአለሙ አሜን፡፡” በማለት ቡራኬውን ይፈጽማል፡፡
ከዚህ በኋላ ያሉትን ጸሎታት ደግሞ ዝርዝር ማብራሪያውን ተወት አድርገን በጥቅል
በጥቅሉ እንደሚከተለው የምናያቸው ይሆናል፡፡ በቅድሚያ ግን የሚከተለውን ጥያቄ
ለመመለስ ይሞክሩ።
የሃይማኖት ምስክርነት
ብዙዎቻችን የቅዳሴ መጀመያ አድርገን የምንመለከተው ጸሎት ገባሬ ሠናዩ ካህን እጅቹን
ዘርግቶ፣ ዐይኖቹን አቅንቶ በዐቢይ ዜማ የሚያዜመው የሃይማኖት ምስክርነት ነው፡፡
ይኸውም “አሐዱ አብ ቅዱስ፣ አሐዱ ወልድ ቅዱስ፣ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ፤
ከወልድ ከመንፈስ ቅዱስ በስም፣ በአካል በግብር ልዩ የሆነ አብ ከወልድ ከመንፈስ ቅዱስ
ጋር በመለኮት÷ በባሕርይ÷ በሕልውና አንድ ነው፡፡ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ በስም፣
56
በአካል፣ በግብር ልዩ የሆነ ወልድ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በመለኮት÷ በባሕርይ÷
በሕልውና አንድ ነው፡፡ ከአብ ከወልድ በስም፣ በአካል፣ በግብር ልዩ የሆነ መንፈስ ቅዱስም
ከአብ ከወልድ ጋር በመለኮት÷ በባሕርይ÷ በህልውና አንድ ነው፡፡” በማለት ምሥጢረ
ሥላሴን እንደ ሸማ ጠቅሎ፣ እንደ ወርቅም አንከብሎ የሚያመሠጥርበት የቅዳሴው ዐቢይ
አንቀጽ ነው፡፡ ይህን የቅዳሴ መጀመሪያ አድርጎ መመልከት ግን ከዚህ በፊት ያሉትን
ጸሎታት ከቅዳሴው የወጡ ያስመስላቸዋልና ጥንቃቄ ያሻል፡፡ ካህኑን ይህን ምስክርነት
ለመስጠት የሚያበቁት የቀደሙት ጸሎታት ናቸውና፡፡
ጸሎተ መባዕ
ይህ ጸሎተ መባዕ ማለትም ጧፍ፣ ሻማ፣ ዘይት፣ ዕጣን፣ ዘቢብ፣ መጋረጃ፣ ምንጣፍ፣
አልባሳት፣ መጻሕፍትና የመሳሰሉትን ሁሉ ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ለሚያገቡ
(ለሚሰጡ) ሁሉ ወደ እግዚአብሔር የሚቀርብ ነው፡፡ የሚጸለየውም በጸሎተ አኰቴት
(በምስጋና ጸሎት) መካከል ነው፡፡ ይህም ጸሎት እንደ ላይኛው “ተንሥኡ ለጸሎት፤
ለጸሎት ተነሡ፤” በሚለው ይጀምራል። ካህኑ የሐዋርያትን የመባዕ ጸሎት የሚያደርስበት
ወቅት ሲደርስ ዲያቆኑ “ጸልዩ በእንተ እለ ያበውኡ መባዐ፤ መባ ስለሚያገቡ ሰዎች
ጸልዩ፤” ብሎ ያዝዛል፡፡
ሕዝቡም “ተወከፍ መባዖሙ ለአኃው ወተወከፍ መባዖን ለአኀት ለነኒ ተወከፍ መባዐነ
ወቁርባንነ፤ የወንድሞችን፣ የእኅቶችን መባቸውን ተቀበልላቸው እንዲሁም የእኛንም
ቁርባናችንን ተቀበልልን፡፡” እያሉ ይጸልያሉ፡፡ ካህኑም የሰጡትን ብቻ ሳይሆን ሊሰጡ
ያሰቡትን ሁሉ እንኳን ሳይቀር እንደሰጡ እንዲቆጥርላቸው ወደ እግዚአብሔር
ይጸልይላቸዋል፡፡
57
“ዕንፎራ” የሚለውን ቃል አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ በጽርዕ “አናፎራ” ይባላል ብለው
ትርጉሙን ደግሞ “አኰቴት፣ ኅብስተ መሥዋዕት” በማለት ያስቀምጡታል፡፡ (ገጽ. ፮፻፺፱)
ይህ ጸሎትም እንደትርጉሙ ሁሉ ስለኅብስቱና ስለወይኑ ክብር በተለይ የሚጸለይ፣ ቡራኬ
የሚተላለፍበትና እማሬ /ምልከታ/ የሚደረግበት ጸሎት ነው፡፡ ካህኑ “ኦ ሊቅየ ኢየሱስ
ክርስቶስ…፤ ጌታዬ ኢሱስ ክርስቶስ…፤” የሚለውን ጸሎተ ዕንፎራ /አንፎራ/ በሚጀምርበት
ጊዜ ሁለት መሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበት የቤተ ክርስቲያን አባቶች
ይመክራሉ፡፡
ጸሎተ መግነዝ
ጸሎተ መግነዝ ማለት የመገነዣ ጸሎት ማለት ነው፡፡ ካህኑ ይህን የሚጸልየው በማኅፈድ
ኅብስተ ቁርባኑንና ጽዋውን ሲሸፍን ነው፡፡ ኅብስቱንና ወይኑን የመሸፈኑ ምክንያትም
ጌታችን የመገነዙ ምሳሌ ነው፡፡ ካህኑ “አንበርነ ዲበ ዝንቱ ጻሕል ቡሩክ በአምሳለ
መቃብር…፤ ፫ መዓልት፣ ፫ ሌሊት ባደርህበት መቃብር አምሳል ክቡር በሚሆን በዚህ
ጻሕል ላይ አኖርን::” እያለ በመጸለይ ኅብስቱንና ጽዋውን በማኅፈድ ይሸፍናል፡፡ በአንድ
ላይም መጎናጸፊያ ያለብሳቸዋል፡፡ ምሳሌነቱም ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ጌታን ገንዘው
የመቅበራቸው ነው፡፡
ከዚህ ጋር ተያይዞ ዲያቆኑ ፊቱን ወደ ሕዝቡ መልሶ “ሰው በልቡናው ቂምንና በቀልን
ቅንዓትንና ጠብን በባልንጀራው ላይ፣ በማንም ላይ ቢሆን አይያዝ” በማለት አስጠንቅቆ
“ስግዱ ለእግዚአብሔር በፍርሃት፤ ለእግዚአብዘሔር በፍርሐት ስገዱ፤” በማለት ያውጃል፡፡
ምእመናን በፍርሃት ለእግዚአብሔር እንዲሰግዱና ስለኃጢአታቸው ሥርየት ካህኑ
የሚጸልይላቸውን የፍትሐት ጸሎት እንዲያደምጡ ትእዛዝ ያስተላልፋል፡፡ ሕዝቡም “አቤቱ
ባንተ ፊት እንሰግዳለን እናመሰግንህማለን፡፡” በማለት ታዛዥነታቸውን በተግባር
(በመስገድ) ይገልጣሉ፡፡
58
በዚህ ጊዜ አንዳንዶች ካህናትና አስቀዳሽ ምእመናን ራስን ዝቅ በማድረግ ጉልበትና
ግንባር ምድር በማስነካት ለእግዚአብሔር ሊቀርብ የሚገባውን ስግደት ባለማወቅ ወይም
ከምንም ባለመቁጠር የዕረፍት፣ ተቀምጦ የማንቀላፊያ፣ የመዝናኛና የወሬ ማውሪያ ጊዜ
ሲያደርጉት ይስተዋላሉ፡፡ እኛ ግን እንደ ትእዛዙ መሬት በመውደቅ፣ የኃጢአታችንን
ሥርየት መለመንና የጸሎቱን ሒደት ከልብ መከታተል ይኖርብናል፡፡
ጸሎተ ዕጣን
ይህ ጸሎት ካህኑ ዕጣኑን ለማክበርና ለመባረክ በዕጣኑ ላይ የሚጸልየው ጸሎት ነው፡፡
አምስት ቆቀር ዕጣን ተመርጦ ይቀርብና ካህኑ በዕጣኑ ላይ ጸሎቱን አድርጎ ይባርከዋል፡፡
ሦስቱን ቆቀር ዕጣን ወዲያው እንደባረከው በማዕጠንቱ ውስጥ ይጨምረዋል፡፡ አንዱን
በጸሎተ ወንጌል ጊዜ፤ አንዱን ደግሞ “ተዘከረነ እግዚኦ በውስተ መንግሥትከ፤ አቤቱ
በመንግሥትህ በመጣህ ጊዜ አስበን፤” በሚባልበት ወቅት ይጨምረዋል፡፡ በዚህ ጊዜ
ሰግደው የነበሩ ሁሉ ይነሣሉ፤ ጳጳስ ካለ ጳጳሱ ከሌለም ቀዳሹ ቄስ ዕጣኑን ይባርካል፤
ያከብራል፡፡ ይህንንም ጸሎት የሚያደርግ ካህን ሌሊቱን፣ መዓልቱን፣ ዕለቱን፣ ወርኁን፣
ዓመቱን፣ ወንጌላዊውን ቀምሮ (አስልቶ) ማውጣት የሚችል መሆን ይኖርበታል፡፡
በመቀጠል ባለው ጸሎት ውስጥ “እማሬ” ሲል በጥንቃቄ እያመለከተ፤ “ቡራኬ” ሲልም
እየባረከ ይጸልያል፡፡ ሠራዒ ቄስና ዲያቆን ከንፍቅ ዲያቆን ጋር ሁነው መንበሩን
ይዞራሉ፡፡ ከዚያ በኋላ “ጸልዩ በእንተ ሰላመ ቤተ ክርስቲያን …” የሚለውን ጸሎት ዲያቆኑ
አሰምቶ ከጸለየ በኋላ “ንስግድ” የሚለውና ቀሪ ጸሎታት በቅደም ተከተላቸው ይቀርባሉ፡፡
59
በዚህ ክፍል ልዩ ልዩ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ምንባባት በልዑካኑ በየተራቸው፣ በየአባባላቸውና
በየቦታቸው ሆነው ይነበባሉ፡፡ ገባሬ ሠናይ ዲያቆን የቅዱስ ጳውሎስን፣ ንፍቅ ቄስ
የሐዋርያት ሥራን፣ ገባሬ ሠናዩ ካህን ወንጌልንናንፍቅ ዲያቆን ቀሪውን መልእክት
ያነባሉ፡፡ ሁሉም በዜማ የሚደርስ የራሳቸው የሆነ የመግቢያና የመሰናበቻ ምስጋና
(መርገፍ) ስላላቸው ከንባብ በፊትና በኋላ በዜማ ይቀርባሉ፡፡ እነዚህም መርገፎች ራሳቸውን
የቻሉ ሃይማኖታዊ ምስክርነት ያላቸው ናቸው፡፡ በየመሐሉ “ተንሥኡ ለጸሎት” የሚለውና
“ሰላም ለኵልክሙ” በማለት የሚቀርበው የበረከት ቃል በየቦታቸው በቅብብሎሽ ይባላሉ፡፡
“ዝ ውእቱ ጊዜ ባርኮት..፤ ይኽ የቡራኬ (ምስጋና) ጊዜ ነው…፤” የሚለውን፤ በበዓለ ሃምሳ
ከሆነ ደግሞ “ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን ሞተ ወኬዶ ለሞት…፤ ክርስቶስ ከሙታን ተነሣ
ሞቶ ሞትን ቀማው…፤” የሚለውን ጸሎት ያደርሳሉ፡፡
ጸሎተ ኪዳን
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እስከ ዕለተ ዓርብ ያስተማረው ወንጌል፣ ከትንሣኤው እሰከ
ዕርገቱ ያስተማረው ደገሞ ኪዳን ይባላል፡፡ ይህም ጸሎት የዚሁ አካል የሆነ በመጽሐፈ
ኪዳንም ሰፍሮ የሚገኝ ነው፡፡ ለጸሎት የተለዩ ሰባት ኪዳናት ሲኖሩ አንዱ ይህኛው ነው፡፡
የኪዳን አዳራረስ ሥርዓት በሦስቱ ጊዜያት ማለትም በሌሊት፣ በነግህና በሠርክ የተከፋፈለ
ሲሆን በሥርዓተ ቅዳሴ የሚደረሰው የነግሁ በነግህ፣ የሠርኩም በሠርክ ነው፡፡ “ቅዱስ”
ተብሎ የሚጀምረው ጳጳስ ካለ ጳጳስ ከሌለም ሠራኢው ካህን ነው፡፡ የሚቀርብበት ዜማ
በአራራይ ነው፡፡ ሕዝቡም ኪያከ ንሴብህ (ንዌድስ)እግዚኦ፤ አቤቱ አንተን እናመሰግናለን”
እያለ በየክፍሉ ከካህናት ጋር አብሮ ተሰጥዖውን በመቀበል ያመሰግናል፡፡
ጸሎተ ወንጌል
የኪዳን ጸሎት ተፈጽሞ አቡነ ዘበሰማያት ከተደገመ በኋላ ቀጣዩ የቅዳሴ ሥርዓት ወንጌል
የሚነበብበት ክፍል ነው፡፡ ጸሎተ ወንጌል ደግሞ ካህናትና ምእመናን በአንድነት ሆነው
የወንጌልን ቃል በንቃት የሚያዳምጡበትና የሚያስተውሉበት ኃይል እንዲያገኙ ቅድመ
ወንጌል የሚጸለይ ጸሎት ነው፡፡ ጸሎቱ እንደተለመደው ዲያቆኑን፣ ሕዝቡንና ካህኑን
የሚያሳትፍ ሆኖ የተዘጋጀ ነው፡፡
ዲያቆን፡- ፊቱን ወደ ሕዝቡ መልሶ “ጸልዩ በእንተ ወንጌል ቅዱስ፤ ስለ ቅዱስ ወንጌል
ጸልዩ” በማለት ያዝዛል፡፡
ሕዝቡ፡- በያለበት በንቃት ቆሞ በአንድ መንፈስና ድምፅ “ረስየነ ድልዋነ ለሰሚዓ ወንጌል
ቅዱስ፤ ቅዱስ ወንጌልን ለማዳመጥ (ለማስተዋል) የተዘጋጀን (የተገባን) አድርገን” በማለት
እግዚአብሔርን ይለምናሉ፡፡
60
ካህኑ፡- ከቅዱሳት መጻሕፍት እያውጣጣና እየመሰከረ የሚነበበው ወንጌል ከሰሚዎቹ ጋር
እንዲዋሐድ ሰሚዎቹም እንዲዘጋጁ እንዲህ በማለት ይጸልያል፤ አምላካችንና
መድኃኒታችን ሰውንም የምትወድ እግዚአብሔር ሆይ ቅዱሳን የሚሆኑ ደቀመዛሙርትህንና
አገልጋዮችህን ንጹሐን ሐዋርያትን ወደ ዓለም ዳርቻ የሰደድሃቸው አንተ ነህ፡፡
የመንግሥትህን ወንጌል ይሰብኩና ያስተምሩ ዘንድ በሕዝብህም ውስጥ ያለውን ደዌውን
ሁሉ በሽታውንም ሁሉ ያድኑ ዘንድ፤ ከዓለም አስቀድሞ የነበረውን የተሰወረውን
ምሥጢርህንም ያስተምሩ ዘንድ፤ አሁንም ጌታችን አምላካችን ሆይ ብርሃንህንና ጽድቅህን
ላክልን፤ ያሳባችንንና የልቡናችንን ዓይኖች አብራልን፤ የከበረ የወንጌልን ቃል በመጨከን
እንሰማ ዘንድ የበቃን አድርገን፤ የምንሰማ ብቻ አይደለንም እንደሰማን ልንሠራም ነው
እንጂ። ስለ አንዱ ፈንታ ሠላሳና ስልሳ መቶም ያማረ ፍሬ በላያችን ያፈራ ዘንድ
የወገኖችህን ኀጢአት ታስተሠርይ ዘንድ በመንግሥተ ሰማያትም የበቃን እንሆን ዘንድ።”
ከዚህ በኋላ ዲያቆኑ ከቅዱስ ዳዊት መዝሙር ለዕለቱ የተወሰነውን አባቶቻችን በመጽሐፈ
ግጻዌ ቀምረው ባዘጋጁት መሠረት ሦስቱን ስንኞች በዐቢይ ዜማ ያዜማል (ያቀርባል)፡፡
ሕዝቡም ተሰጥኦውን እየተቀባበሉ ሁለት ሁለት ጊዜ፤ ሦስተኛውን ደግሞ በጋራ (በኀብረት)
ይዘምራሉ (ያቀርባሉ)፡፡ ካህኑ በዚህ ጊዜ አራቱን መዓዘን “እግዚአብሔር ልዑል ይባርክ
ላዕለ ኵልነ ወይቀድሰነ በኵሉ በረከት፤ እግዚአበሔር ልዑል ሁላችንንም ይባርከን፤
በመንፈሳዊ በረከትም ያክብረን” እያለ ይባርካል፡፡ ከዚህ በማስከተል አብሮ (ተያይዞ)
የቀረበውን ጸሎት ከጸለየ በኋላ በመሠዊያው ዙሪያ እያጠነ አብሪ ዲያቆን ከፊት፣ ንፍቅ
ካህን ወንጌሉን ይዞ አብሪውን ዲያቆን እየተከተለው መሐል ላይ ሠራኢው ካህን፣ ከኋላውም
ሠራኢው ዲያቆን መስቀሉን ይዞ፣ በመጨረሻም ጥላ (ድባብ) የያዘው ዲያቆን ሆነው
በመሠዊያው (በመንበሩ) ዙሪያ ዑደት ያደርጋሉ፡፡ ይህም ምሳሌ አለው፤ ንፍቅ ዲያቆን
(አብሪ) የነቢያት፣ ንፍቅ ቄስ የመጥምቁ ቅ/ዮሐንስ፣ ሠራኢው ካህን የጌታ፣ ሠራኢ ዲያቆን
የቅ/እስጢፋኖስ ምሳሌዎች ናቸው፡፡
61
የያዘ ነው፡፡ “ወንጌል ቅዱስ” ብሎ ወደ ቅድስት ከወጡ በኋላ በመጀመሪያ ሠራኢው ካህን
“ነዋ ወንጌለ መንግሥት” ጌትነቱን የምትናገር ወደ መንግሥተ ሰማያት የምታገባ ወንጌል
ይህቺ ናት::” በማለት ለንፍቁ ካህን ይሰጠዋል፡፡ ንፍቁ ካህን ደግሞ “መንግሥቶ ወጽድቆ
ዘአወፈየኒ አወፈይኩከ፤ ጌትነቱን ቸርነቱን የምትናገር ቄሱ የሰጠኝን ወንጌልን ሰጠሁህ”
እያለ ለዲያቆኑ ይሰጣል፡፡ ዲያቆኑ ደግሞ “ነስሑ ወእመኑ እስመ ቀርበት ይእቲ
መንግሥተ ሰማያት፤ መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ” ብሎ በማወጅ ለካህኑ
አመቻችቶ ይይዝለታል፡፡ ይህም ለጊዜው “ወንጌል የምትነገርበት ጊዜ ቀርቧልና
ነቅታችሁ÷ ተግታችሁ ስሙ፤” ማለት ሲሆን ለፍጻሜውም “ልጅነት፣ መንግሥተ ሰማያት
የምትሰጥበት ጊዜ ቀርባልና ንስሐ ግቡ፤” ማለት ነው:: ሠራኢው ካህን ፊቱን ወደ
ምሥራቅ መልሶ የዕለቱን ወንጌል ጎላ ባለ ድምፅ ያነባል፡፡
62
ጸዋትው
ይህ ጸሎት ስለ ቤተ ክርስቲያን፣ ስለ ካህናትና፣ ስለ ማኅበረ ምእመናን ካህናት ወደ
እግዚአብሔር የሚያቀርቡት ነው፡፡ ጸዋትው ማለት የምእመናን ወገኖች ማለት ነው፡፡ ስለ
ጾታ ምእመናን ስለሚጸለይ ጸዋትው ተብሏል፡፡ ስለ አንዲቷ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን
ፍጹም ሰላምና አነድነት፣ ከፓትርያርኩ ጀምሮ ስለ ጳጳሳት፣ ካህናት፣ ዲያቆናትና ምእመናን
ሕይወት፣ ጤንነትና ሰላም፣ አንድነት ሠራኢው ካህንና ዲያቆኑ እያስተዛዘሉ ወደ
እግዚአብሔር ምልጃ የሚያቀርቡበት ክፍል ነው፡፡ ካህኑ “ኵሎ ሕዝበ ወኵሎ መራእየ
ባርኮሙ፤ ሕዝቡንና መንጋውን ሁሉ ባርክ” እያለ የሚባርክበት፣ ሕዝቡም ኪሪያላይሶን
(አቤቱ ይቅር በለን!) እያለ የሚማፀንበትና ቡራኬውን የሚቀበሉበት የሥርዓተ ቅዳሴ አንዱ
አካል ነው፡፡ ዲያቆኑ “ጸልዩ በእንተ ዛቲ ቤተ ክርስቲያን ቅድስት ወማኅበርነ ዘውስቴታ፤
ስለ አንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በውስጧም ስለሚገኙ ማኅበር (ስለ ምእመናን
አንድነት) ጸልዩ” ባለ ጊዜም ሕዝቡም “ማኅበረነ ባርክ ዕቀብ በሰላም፤ ማኅበራችንን
ባርክልን፣ በሰላምም ጠብቅልን” በማለት እምነቱን፣ ፈቃዱንና ፍላጎቱን የሚገልጽበት ጸሎት
ነው፡፡
ጸሎተ ሃይማኖት
❖ ጸሎተ ሃይማኖትን በቃልዎ መድገም ይችላሉን? በቃልዎ እያነበቡ በማስታወሻ
ደብተርዎ የቻሉትን ያህል ለመጻፍ ይሞክሩ፡
63
ቂምን የያዘ ልዩ አሳብና ዝሙትም ያለበት ቢኖር አይቅረብ፡፡” በማለት
የሚያውጀውን ዐዋጅ እንዴት ያዩታል?
ጸሎተ ሃይማኖት ከተደገመ በኋላ ካህኑ እጁን ሲናጻ (ሲታጠብ) የሚከተለውን ትእዛዝ
ያስተላልፋል፡፡ “ዘኮነ ንጹሐ ይንሣእ እምቁርባን፤ ወዘኢኮነ ንጹሐ ኢይንሣእ ከመ ኢየዐይ
በእሳተ መለኮት ዘተደለወ ለሰይጣን ወለመላእክቲሁ፤ ዘቦ ቂም ውስተ ልቡ ወዘቦ ውስቴቱ
ኅሊና ነኪር ወዝሙት ኢይቅረብ፤- ንጹሕ የሆነ ከቁርባኑ ይቀበል፤ ንጹሕ ያልሆነ ግን
አይቀበል፤ ለሰይጣንና ለመልእክተኞቹ በተዘጋጀው በመለኮት እሳት እንዳይቃጠል፤
በልቡናው ቂምን የያዘ ልዩ አሳብና ዝሙትም ያለበት ቢኖር አይቅረብ፡፡” በሂደት ለማወቅ
እንደተቻለው ይህን አንቀጽ ብዙዎች ምእመናን ይፈሩታል፡፡ አንዳንዶችም “ሰው ወደ
ሥጋ ወደሙ እንዳይቀርብ ካህናት ምእመናንን የሚያስፈራሩበት መሣሪያ ነው፡፡”
እስከማለትም ይደርሳሉ፡፡ የዚህ አንቀጽ /ክፍለ ንባብ/ ዋነኛ መልእክት ግን እንደተባለው
ሳይሆን ምእመናን ንስሐ ሳይገቡ በድፍረትና በግዴለሽነት ወደ ሥጋውና ደሙ
እንዳይቀርቡ ማድረግ ነው፡፡ የተጣሉ ታርቀው፣ የቀሙ መልሰው፣ የበደሉ ክሰውና ንስሐ
ገብተው ወደ ቅዱስ ሥጋውና ደሙ እንዲቀርቡ የሚያሳስብ ትምህርት ነው፡፡ በርግጥ ከዚህ
ውጪ በድፍረትና በማንአለብኝነት (ንስሐ ሳይገቡ) ተንደርድረው የሚቀርቡ ካሉ
መቀጣታቸው አይቀሬ ነው፡፡ ስለዚህም በድፍረትና ባለማወቅ ምእመናን እንዳይጎዱ
ለመጠበቅ እንጂ በማስፈራራት ለማራቅ አለመሆኑ መታወቅ አለበት።
ፍሬ ቅዳሴ
የአጠቃላዩ ሥርዓተ ቅዳሴ የመጨረሻ ክፍል ፍሬ ቅዳሴ ነው፡፡ ይህ ክፍል ኅብስቱና ወይኑ
ወደ ሥጋ ወደሙ የሚለወጥበትን ጊዜ የሚመለከት ጸሎትና ቡራኬ የያዘ ነው፡፡ ከላይ
እንደተገለጸው መረሳት የሌለበት ጉዳይ ኅብስቱና ወይኑ ሥጋ ወልደ እግዚአብሔርና ደመ
ወልደ እግዚአብሔር ወደመሆን የሚለወጠው በአንድ ክፍለ ጸሎት ብቻ አለመሆኑን ነው፡፡
የኅብስቱና የወይኑ የክርስቶስን ሥጋና ደም ወደ መሆን መለወጥ የአጠቃላዩ የሥርዓተ
ቅዳሴው /ሥርዓተ ጸሎት/ ውጤት ነው፡፡
ከዚህ በታች የምናየው የፍሬ ቅዳሴ ክፍል ለማሳያ ያህል የአባቶቻችን የሐዋርያትን
ይሆናል፡፡ በጥቅሉ የፍሬ ቅዳሴው ክፍል በውስጡ በስማቸውና በአፈጻጸማቸው ልዩ ልዩ
የሆነ በዛ ያሉ ንዑሳን ክፍሎችን ይዞ ይገኛል፡፡ ዐሥራ ዐራቱ ቅዳሴያት በዝርዝር ሲታዩ፡-
ቅዳሴ እግዚእ፣ ዘሐዋርያት፣ ቅዳሴ ማርያም፤ ዘዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ፣ ዘጎርጎርዮስ፣
ዘአትናቴዎስ፣ ዘቄርሎስ፣ ዘሠለስቱ ምዕት፣ ዘባስልዮስ፣ ዘዮሐንስ አፈወርቅ፣ ዘኤጲፋንዮስ፣
ዘዲዮስቆሮስ፣ ዘያዕቆብ ዘስሩግ፣ ዘጎርጎርዮስ ካልዕ በመባል የሚታወቁ ናቸው፡፡
66
ይ.ካ፡- ነአኵተከ እግዚኦ በፍቁር ወልድከ እግዚእነ ኢየሱስ፤ አቤቱ ልጅህ ወዳጅህ ኢየሱስ
ክርስቶስ ለምስጋናው አብነት ሁኖን፣ በልጅህ በወዳጅህ ባደረግኸው ቸርነት
እናመሰግንሃለን፡፡”
ጸሎተ አስተብቍዖት
ይህ የጸሎት ክፍል “ጸሎተ አስተቍዖት፤ የምልጃ ጸሎት” ይባላል፡፡ ይህም ፍሬ ቅዳሴ
እንደተጀመረ አብሮ ይጀምራል፡፡
ይ.ዲ፡- “በእንተ ብፁዕ ወቅዱስ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት አባ (እገሌ)፤ ንዑድ፣ ክቡር ስለሚሆን
ስለ ሊቀ ጳጳሱ አባ (እገሌ)” በማለት በጊዜው የተሰየመውን ፓትርያርክ ስም አስገብቶ
ይጸልያል፤ ይማጸናል፡፡ በዚህ ክፍል አሁን በቤተ ክርስቲያን በአገልግሎት ላይ (በአጸደ
ሥጋ) ካሉት ጀምሮ እመቤታችንን፣ ወንጌላውያንን፣ ሐዋርያትን፣ አርድዕትን አንድ ባንድ
እያነሣ፤ ቅዱስ እስጢፋኖስን፣ ካህኑ ዘካርያስን፣ መጥምቁ ዮሐንስን…. በአጸደ ነፍስ ካሉ
ቅዱሳን ዋና ዋናዎቹን ስማቸውን እየጠራ “ስለነሱ ብለህ ማረን” እያለ ይማጸናል፤
ይማልዳል፡፡ በዚህ ወቅት በቤተ ክርስቲያን የኖሩትንና ያረፉትን ስለ ክርስቶስና ስለ ቤተ
ክርስቲያን ታላቅ ሥራ የሠሩትን አባቶች ሁሉ በጸሎት ያስታውሳቸዋል፡፡
ጸሎተ ቡራኬ
ይህ የቡራኬ ጸሎት ነው፡፡ ንፍቁ ካህን ቅዱስ ባስልዮስ የተናገረውን የቡራኬ ጸሎት
ይጸልያል፡፡ ሠራኢው ካህን ደግሞ ንፍቁ ካህን “ባርክ” በሚልበት ጊዜ በሕዝቡና
በሚጠራው ሁሉ ላይ ይባርካል፡፡ በዚህም ቡራኬና ጸሎት የሚደረግላቸው ሕዝቡ፣ ቤተ
ክርስቲያን፣ ሕሙማን፣ መንገደኞች፣ ነጋዴዎች፣ ነፋሳተ ሰማይ፣ ዝናማት፣ የምድር ፍሬ፣
ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ ነገሥታትና የሀገር መሪዎች፣ ነፍሳተ ሙታን፣ ለቤተ
ክርስቲያን መባዐ የሚሰጡ፣ የተጨነቁ ነፍሳት (ሰውነት)፣ እስረኞች (ታራሚዎች)፣ በጽኑ
አገዛዝ (በምርኰ) የተያዙ፣ የተሰደዱ (ስደተኞች)፣ በጸሎታችሁ አስቡን ብለው የተማጸኑ
ምእመናንና አገልጋይ ካህናቱ ሁሉ ናቸው፡፡
❖ የትና መቼ ነው ያቀረበው?
“ተዘከረነ” የሚለውን ጸሎት ካህኑና ሕዝቡ እየተቀባበሉ ሲጸልዩ ንፍቁ ካህን ደግሞ ዕጣን
ያሳርጋል (ያጥናል)፡፡ ሠራኢው ካህንም የዕጣኑን ጭስ በእጁ እየታፈነ ፫ ጊዜ ከኅብስቱ፣ ፫
ጊዜ ከወይኑ ያደርገዋል /ያሳርጋል/፡፡ይህን ምስጋና ከሰው ልጆች መካከል ለመጀመሪያ ጊዜ
ያቀረበው በክርስቶስ ቀኝ የተሰቀለው ሽፍታ /ፊያታዊ ዘየማን/ ጥጦስ የሚባለው ነው፡፡
ይህም ወንበዴ ተሰቅሎ በታላቅ መከራ ውስጥ እያለ አቤቱ በመንግሥትህ በመጣህ ጊዜ
ዐስበን በማለት ለመነው፡፡ ጓደኛው /በግራ የተሰቀለው/ ወንበዴ በክርስቶስ ላይ
በሚሳለቅበት ጊዜ እርሱ አምላክነቱን አምኖ ግሩም ጸሎት አቀረበና ለምእመናን ሁሉ
አብነት ምሳሌ ሆናቸው፡፡ በመከራ ሰዓት ወዴትና እንዴት መጸለይ እንዳለብን አሳየን፡፡
መድኃኔዓለም ክርስቶስም “እውነት እልሃለሁ፤ ዛሬ በገነት ከእኔ ጋር ትሆናለህ፤”
(ሉቃ፳፫፥፵፪-፵፬፡፡) በማለት የይቅርታ ድምፁን አሰማው፡፡
69
ዲያቆኑ በመቀጠል “አንሥኡ እደዊክሙ ቀሳውስት፤ ሠራዒው ካህን ኅብስቱን፣ ንፍቁ ካህን
ማኅፈዱን ለማንሣት እጆቻችሁን አንሡ” በማለት ያሳስባል፡፡ ይህም የትንሣኤ ክርስቶስ
ምሳሌ ነው፡፡ ሠራዒው ካህን ኅብስቱን ከጻሕሉ ላይ ማንሣቱ፡- ክርስቶስ ሞትን ድል
አድርጎ የመነሣቱ፤ ንፍቁ ካህን ማኅፈዱን ማንሣቱ፡- በመቃብር ላይ የተገጠመችውን
ድንጋይ መልአከ እግዚአብሔር የማንከባለሉ ምሳሌ ነው፡፡ በመቀጠልም ካህኑ ክርስቶስ
በተያዘባት በዚያች ዕለት ቀደም ብሎ ኅብስቱንና ወይኑን አክብሮ ሥጋውን ደሙን አድርጎ
መስጠቱን ይመሰክራል፡፡ ሕዝቡም “ነአምን ከመ ዝንቱ ውእቱ በአማን ነአምን፤ የተነሣው
ይህ እንደሆነ፤ አንድም ይህ አሁን ካህኑ የሚያከብረው ኅብስትና ወይን እንደያኔው
በእውነት በዕለተ ዓርብ የቆረስከውን ሥጋ ወልደ እግዚአብሔር፣ ያፈሰስከውንም ደመ
ወልደ እግዚአብሔር እንደሆነ እናምናለን” እያለ ሥጋ ወደሙን ደጅ ይጠናል፤
ይጸልያልም፡፡ ሕዝቡም የካህኑን ምስክርነት እያዳመጠ የሃይማኖቱን ማረጋገጫ መስጠቱን
ይቀጥላል፡፡ ካህኑ በቃል የሚናገረው ምስጋናና ጸሎት በድርጊትም የሚገልጠው ምሥጢር
ጠቅላላ የዕለተ ዓርቡን ሕማማተ መስቀል የሚያዘክር (የሚያስብ) ነው፡፡ በማስተዋል
የሚከታተለው ክርስቲያን ቢኖር ክርስቶስ በቀራንዮ በተሰቀለ ጊዜ በቦታው ተገኝቶ
በዓይኖቹ ያየ እስኪመስለው ድረስ ልቡ በሐዘን ጦር ይወጋል፡፡ ሕዝቡ “ንዜኑ ሞተከ
እግዚኦ፣ ወትንሣኤከ ቅድስተ፣ ነአምን ዕርገተከ፣ ወዳግመ ምጽአተከ፣ ንሴብሐከ
ወንትአመነከ፤ አቤቱ ሞትህን፣ ልዩ የሚሆን ትንሣኤህንም እንመሰክራለን (እንናገራለን)፤
ዕርገትህንና ዳግመኛ ዓለምን ለማሳለፍ መምጣትህን እናምናለን፤ አምነንም
እናመሰግንሃለን።” እያሉ ከቄሱ ጋር አብረው ቅድስት የሆነች እምነታቸውን ይመሰክራሉ፡፡
ጸሎተ ፈትቶ
ይህ ጸሎት ካህኑ ሥጋውን እየፈተተ የሚጸልየው ነው፡፡ ይኸውም፡- “ከወዳጁ ከአልዓዛር
ቤት ግብር አግብቶ ሳለ ለበረከት ካመጡለት ከኅብስቱና ከወይኑ ከፍሎ “ዝ ውእቱ ሥጋየ፤
ዝ ውእቱ ደምየ፤ ይህ ሥጋዬ ነው፤ ይህ ደሜ ነው፡፡” ብሎ አክብሮ ለውጦ ትኩስ ሥጋ
ትኩስ ደም አድርጎ ሰጣቸው፡፡ የፍታቴው ሥርዓትም ከክርስቶስ /ከምሥጢረ ሥጋዌ/ ሙሉ
ጉዞ ጋር የተሰናሰለ ምሳሌነት ያለው ነው፡፡ አሁን በዚህ ቦታና ጊዜ ግን ልንገልጸው
አይቻለንም፡፡ ከዚህ በመቀጠል ዲያቆኑ “ጸልዩ” ብሎ ሲያዝ ሕዝቡ ከካህናቱ ጋር በጋራ
“አቡነ ዘበሰማያት”ን በዜማ ይደግመዋል፡፡ አያይዞም “በከመ ምሕረትከ አምላክነ ወአኮ
በከመ አበሳነ፤ አቤቱ ሥጋህን ደምህን መስጠትህ እንዳንተ እንደቸርነትህ ነው እንጂ እንደ
ኃጢአታችን አይደለም፡፡ እንደ ኃጢአታችንማ ባልተገባንም ነበር፡፡ አንድም
ኃጢአታችንን ይቅር የምትለን እንዳንተ እንደ ቸርነትህ ነው እንጂ እንደኛ እንደ
ኃጢአታችን አይደለም፡፡ እንደ እኛስ እንደ ኃጢአታችን ባልተገባንም ነበር፡፡ አንድም
71
መከራውን የምታመጣብን ቅሉ እንዳንተ እንደቸርነትህ ነው እንጂ፤ እንደኛ እንደ
ኃጢአታችን አይደለም፡፡ እንደ እኛስ እንደ ኃጢአታችን ቢሆን ኖሮ ፈጥኖ፣ በዝቶ
በተደረገብን ነበር፡፡” የሚለውን ጸሎት ሦስት ጊዜ መላልሰው እየተቀባበሉ ያደርሱታል፡፡
ይህም በራሱ ምሥጢረ ሥላሴን ያሳያል፡፡
72
እንገዛለን፡፡/ሐዋርያት በሱ አምነው ቤታቸውን፣ ንብረታቸውን ጥለው
እንደተከተሉት፤ አንድም በመስቀል ተሰቅለው እንደመሰሉት እንመስለው ዘንድ፡፡/
73
ዲያቆኑ፦ “ስግዱ ለእግዚአብሔር በፍርሃት፤ በፈሪሃ እግዚአብሔር ሁናችሁ ስገዱ፡፡”
ይላል፡፡ ጸሎተ ንስሐ ሊደገምላቸው ስለሆነ ሰግደው እንዲያስደግሙ እያዘዛቸው ነው፡፡
አስቀድሞ ፍትሐት ዘወልድንና በእንተ ቅድሳትን ወድቀው እንዳስደገሙ፡፡ ሕዝቡም
“ቅድሜከ እግዚኦ ንሰግድ ወንሴብሐከ፤ አቤቱ ወድቀን (ሰግደን) እናመሰግንሃለን፤
(እያመሰገንህ እንሰግዳለን)፤” እያሉ ይሰግዳሉ፡፡
ጸሎተ ንስሐ
ዲያቆኑ፦ ስገዱ ካለና ሕዝቡም ከሰገዱ በኋላ ሠራዒው ቄስ (ካህን) ጸሎተ ንስሐ
ይደግምላቸዋል። ከዚህ ጸሎት የሚገኝ ጥቅም ብዙ ነው፡፡ ጸሎቱ “በደልን፣ ተመለስንም”
ላሉ ሁሉ የሚጸለይ ነው። ስለዚህም ጸሎቱ መናዘዣ ነው። ተናጋሪውም ቅዱስ ባስልዮስ
ነው። “እኔ ከንሰሐ ሕይወት ውጪ ነኝ” ብሎ ወድቆ (ሰግዶ) የማያስደግም ምእመንም ሆነ
ካህን ሊኖር አይችልም።
ካህኑ ጸሎተ ንስሐ ከደገመ በኋላ ዲያቆኑ “ነጽር፤ አስተውል” ይላል ካህኑም “ቅዱሳት
ለቅዱሳን፤ ሥጋ ወደሙ የተሰጠ ከኃጢአት ለነጹ ለበቁ ነው፤ በቅቻለሁ የሚል ይምጣ
ይቀበል።” በማለት ያውጃል ፡፡ሕዝቡም “አሐዱ አብ ቅዱስ፣ አሐዱ ወልድ ቅዱስ፣ አሐዱ
ውእቱ መንፈስ ቅዱስ” በማለት ይመልሳል።
በመቀጠል ዲያቆኑ “እለ ውስተ ንስሐ ሀለውክሙ አትሕቱ ርእሰክሙ፤ በደልን፤ ተመለሰን
በማለት ያላችሁ ርእሰ ልቡናችሁን ዝቅ ዝቅ አድርጉ፤” በማለት በድጋሚ ያዝዛል። ካህኑም
እግዚአብሔር ልቡናቸውን ያዋረዱትን ሁሉ እንዲምራቸው ይጸልይላቸዋል።
ምስክርነት
ሠራዒው ካህን በዚህ ክፍለ ጸሎት ስለ ምሥጢረ ተዋሕዶ (ሥጋዌ) በተለይም ስለ ቅዱስ
ሥጋውና ደሙ የሃይማኖት ምስክርነት ያቀርባል። በዚህ ምስክርነትም እማሬዎች አሉበት።
ምስክርነቱም ፦
75
• ክርስቶስ ወዶና ፈቅዶ በጲላጦስ ፊት በእውነት (ለእምነት) የመሰከረ ስለመሆኑ፣
ምእመናንም (ካህናትም ጭምር) እንደ ካህኑ “አሜን፣ አሜን ፣አሜን ፤ነአምን” በማለት
ሃይማኖታዊ ምስክርነታቸውን በተመሳሳይ ሁኔታ ይሰጣሉ።
ለቁርባን መዘጋጀት
76
ከዚህ ቀጥሎ ያለው የቅዳሴ ክፍል ያስቀደሰ ሁሉ ቁርባን ለመቀበል የሚዘጋጅበት ክፍል
ነው። ካህኑ “እግዚአብሔር አምላኪየ ናሁ ሥጋ ወልድከ መሥዋዕት ዘያሠምረከ፤ ፈጣሪዬ
እግዚአብሔር ሆይ ደስ የሚያሰኝህ መሥዋዕት የልጅህ ሥጋ እነሆ” በማለት ይጀምርና
ኃጢአቱን (የራሱን)ይቅር ይልለት ዘንድ ሥጋ ወደሙን እያማፀነ ይጸልያል። ከዚህ
በማያያዝ ምእመናንም ቅዱስ ቁርባን ከመቀበላቸው በፊት ሊጸልዩት የሚገባ ጸሎት
ይደገማል ።”ኦ እግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ አኮ ዘይደልወኒ ትባዕ ታሕተ ጠፈረ ቤትየ
ርኩስት፤ አቤቱ ፈጣሪዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፥በኃጢአት በተታታ ሰውነቴ ማደር
የሚገባህ አይደለም”። የሚለውን ጸሎት ምእመናን እየደገሙ ይቀበላሉ።
❖ ትሕትና፣ ተአምኖ ኃጣውእ፣ ምልጃ፣ ነገረ መስቀል፣ ነገረ ማርያም፣ ነገረ መላእክት፣
ነገረ ቅዱሳንና ክብረ ሥጋ ወደሙ ከዚህ ጸሎት አንጻር የሚገኙበትን አንቀጽ
ለማዛመድ ይሞክሩ።
ከዚህ በኋላ ቀሪ ጸሎታት ተሟልተው ከቀረቡ በኋላ ሰዓቱ ሲደርስ ከሠራዒው ጀምሮ
ልዑካኑ ካህናቱና ምእመናኑ በየተራቸው ቅዱሱን ቁርባን ይቀበላሉ። ልዑካኑ እንደተቀበሉ
ሃይማኖተ አበው ይነበባል፡፡ ከዚያም ስለ ሥጋውና ደሙ ክብር የተዘጋጀው መልክዐ
ቁርባን በዜማ ይደርሳል። የዚህ ጸሎት መጀመሪያ “ሰላም ለኪ” የሚለው ነው።የቆራቢያን
የአቆራረብ ቅደም ተከተልም እንደሚከተለው ነው፦
• ወንዶች በየመዓርጋቸው፤
• ሴቶች በየክብራቸው፤
• የቀሳውስት ሚስቶች፤
• የዲያቆናት ሚስቶች፤
ሠርሆተ ሕዝብ
በሥርዓተ ቅዳሴው መጨረሻ ላይ ራሱን የቻለ የመሰናበቻ ሥርዓትና ጸሎት አለ። ቀደም
ብሎም ሐዳፌ ነፍስና አንብሮተ እድ የሚባሉ ስለ ሁሉም የሚቀርቡ ጸሎታትና
ምስጋናዎች ይቀርባሉ። ካህኑ የማሰናበቻውን ጸሎትና ቡራኬ ከፈጸመ በኋላ ዲያቆኑ እትዉ
በሰላም ብሎ ሕዝቡን ያሰናብታል፡፡ ዲያቆኑ ከማሰናበቱ በፊት ንፍቁ ቄስ እመቤታችን
ቅድስት ድንግል ማርያምን ፣ሊቃነ መላእክትን ፣ዐርባዕቱ እንስሳን ፣አርእስተ አበውን፣
መጥምቀ መለኮትን፣ ዐርባዕቱ ወንጌላዊያንን፣ አሥራ ሁለቱ ሐዋርያትን፣ ጻድቃን
ሰማዕታትን፣ እያማፀነ በነሱ ጸሎት፣ በነሱ ምልጃ ጠብቃቸው እያለ ይለምናል፡፡
በመቀጠልም “አድንኑ አርእስቲክሙ ቅድመ እግዚአብሔር አምላክነ፤ በፈጣሪያችን
በእግዚአብሔር ፊት ራሳችሁን ዝቅ ዝቅ አድርጉ፤” በማለት ዲያቆኑ ሕዝበ ክርስቲያኑን
ለቡራኬ ያዘጋጃቸዋል። ከቡራኬ በኋላም “እትዉ በሰላም፤ በሰላም ግቡ፤” ብሎ
ያሰናብታቸዋል። “በሕይወት በጤንነት እሾህ ሳይወጋችሁ፥ እንቅፋት ሳይመታችሁ፤ወደ
ቤታችሁ ግቡ፤” ይላል። ምሥጢሩ ግን ሥጋውን ደሙን በመቀበላችሁ ኃጢአታችሁ
ተሠረየላችሁ፤ ባንድነት ወደ መንግሥተ ሰማያት ግቡ፤” ማለቱ ነው። “ዕትዉ” የ “ንዑ
ኃቤየ” ምሳሌ ነውና።
80
ሳይለብስ በመገኘቱ ነው ተግሣጹም ቅጣቱም ያገኘው። ይህም ምድራዊው ሰርግም እንኳን
ቢሆን የራሱ የሆነ የአለባበስ፣ የአቀማመጥ፣ የአመጋገብና የክንውን ሥርዓትና ጊዜ
እንዳለው ያሳየናል።
የሰርጉ ቤት የቤተ ክርስቲያንና የመንግሥተ ሰማያት ምሳሌ ሲሆን የሰርጉ ባለቤት ደግሞ
የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ነው፡፡ ታዳሚዎቹም የምእመናነ ክርስቶስ ምሳሌዎች
ናቸው። ድግሱ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በጸሎተ ቅዳሴ በየጊዜው የምታዘጋጀው ቅዱስ
ሥጋውና ክቡር ደሙ ነው። ይህም ዝም ተብሎ በዘፈቀደ ማንም ባሻው ጊዜ እየተነሣ
ያለምንም ዝግጅት የሚመገበው ተራ ምግብ አይደለም። ተግሣጹም ሆነ ጽኑዕ ቅጣቱ
እንዳያገኘን ባግባቡ ተዘጋጅተን በካህናት እጅ የሚሰዋውን መሠዋዕተ ሐዲስ መቀበል
ይኖርብናል፡፡ ዋና ዋናዎቹ የዝግጅቱ አካላትም የሚከተሉት ናቸው።
81
በዕለቱ ቆራቢያን እንዲፈጽሟቸው የማይፈቀዱ ተግባራት በከፊል ከዚህ በታች የቀረቡት
ናቸው፡፡
• ከልብስ መራቆት፣
• መስገድ መንበርከክ፣
• መበጣት መቆረጥ፣
• መታገም መተኮስ፣
• ፀጉርን መላጨት፣
• ሩቅ መንገድ መሔድ፣
፭.የሚያስገኘው ጸጋ
❖ ውድ ተሳታፊ ሆይ ቅዱስ ቁርባን መቀበል ለምን ለምን ይጠቅማል?
የሚታየው ኅብስትና ወይን በክርስቶስ ቃል ኪዳን፣ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል፣ በካህኑ ጸሎትና
በጸሎተ ቅዳሴ ነፍስ የተለየው፣ መለኮት የተዋሐደው ሥጋ ወልደ እግዚአብሔርና ደመ
ወልደ እግዚአብሔር ወደ መሆን ይለወጣል። ምእመናን ይህን አምነውና ንስሐ ገብተው
ሲቀበሉ በወንጌል የተጻፈውን የማይታይ ጸጋ ለማግኘት ይችላሉ። እነዚህም፦
ማጠቃለያ
ምሥጢረ ቁርባን የመንግሥተ ሰማያት መግቢያ ማረጋገጫ ማኅተም ነው፡፡ ለዚህም
ነው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “እውነት እውነት እላችኋለሁ የሰውን ልጅ ሥጋ
ካልበላችሁ ደሙንም ካልጠታችሁ የዘላለም ሕይወት የላችሁም፤ ሥጋዬን የሚበላ
ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው፤ እኔም በኃለኛይቱ ቀን አነሣዋለሁ፡፡”
በማለት በግልጽ ያስተማረን፡፡ (ዮሐ 6፥%3-%5ÝÝ፡፡) ክርስቲያኖች ሁሉ ይህን ርእሰ
ጉዳይ በተመለከተ ቆም ብለው በርጋታ ሊያስቡበት ይገባል፡፡ ክርስቲያኖች ተብለው
በስሙ መጠራታቸው ብቻውን የሕይወት ባለቤት ሊያደርጋቸው አይችልም፡፡
መድኃኔዓለም ክርስቶስ እንዳስተማረን እሱ የወይን ግንድ ክርስቲያኖችም
ቅርንጫፎቹ ናቸው፡፡ ከግንዱ ከክርስቶስ የተወለደ ሆኖ ሳለ የቃለ እግዚአብሔር
እንዲሁም የሥጋውና የደሙ ምግብ የተቋረጠበት ቅርንጫፍ /ክርስቲያን/ ደግሞ
ጠውልጎ መድረቁ አይቀርም፡፡ ከደረቀና ከግንዱ ተቆርጦ ከተጣለም ለእሳት
የተዘጋጀ ይሆናል፡፡ በሕይወቱ እንዳይጠወልግ፣ እንዳይደርቅና እንዳይቃጠል
የሚፈልግ ምእመን ሁሉ ከግንዱ ጋር ሊኖር፤ ከግንዱ ከክርስቶስ የሚገኘውን
የሕወት ምግብም ሳያቋርጥ ንስሐ እየገባ ሊመገብ ያስፈልገዋል፡፡ እያስቀደሱ
ጥቂቶች ብቻ ማዕዱን ከበው ሲመገቡ ማየት ብቻውን ለተራበች ሰውነት /ነፍስ/
የሚፈይደው አንዳች ቁም ነገር የለውም፡፡ (ዮሐ 05፥1-0፡፡Ý) በዚህ ምዕራፍ
ያነበብነውን ሁሉ ከራሳችን ተግባራዊ ሕይወት ጋር በማመዛዘን ወደ ቅዱስ ቁርባን
ለመቅረብ የምንችልበት መሣሪያ ማድረግ ይጠበቅብናል፡፡
ዋቢ መጻሕፍት
• ዲ/ን ያሬድ ገ/መድኅን፤ ኆኅተ ሰማይ፤ ማኀበረ ቅዱሳን፤
፲፱፻፺፮፤ አ/አ።
84
ምዕራፍ ፮
ምሥጢረ ክህነትና አፈጻጸሙ
መግቢያ
ከ@2ቱ ፍጥረታት መካከል የፍጥረታት ሁሉ ዘውድ የሚባለው የሰው ልጅ ነው፡፡ ከሰው
ልጆች መካከልም እግዚአብሔር የተወሰኑትን መርጦ መሥዋዕት እንዲያቀርቡ፣ ዕጣን
እንዲያሳርጉና በመቅደሱ እንዲያገለግሉ አደረገ፡፡ እነዚህ ሰዎችም ካህናት /አገልጋዮች/
ተብለው ይጠራሉ፡፡ እግዚአብሔር ሙሴን “አንተም ወንድምህን አሮንን ከእርሱም ጋር
ልጆቹን ከእስራኤል ልጆች መካከል ለይተህ በክህነት ያገለገሉኝ ዘንድ ወደ አንተ
አቅርብ፡፡” በማለት ያዘዘውን ማየት ለዚህ ጥሩ ማሳያ ነው፡፡ በብሉይ ኪዳንም ሆነ በሐዲስ
ኪዳን የክህነት መሠረቱ የእግዚአብሔር ጥሪ ነው፡፡ በዚህ ምዕራፍ በዝርዝር
የምንመለከተው ምሥጢረ ክህነትን ነው፡፡ በምዕራፉ ሥርም አመሠራረቱን፣
አስተምህሮውን፣ አፈጻጸሙንና የሚያስገኘውን ጸጋ በተገቢው ሁኔታ ለማብራራት
ተሞክሯል፡፡
85
፮.፩ አመሠራረት
አማናዊው የሐዲስ ኪዳን ክህነት ከመጀመሩ በፊት በብሉይ ኪዳንም ክህነትና
አገልግሎቱ በስፋት ይታይ ነበር። በሕገ ልቡና ዘመን ከአዳም ጀምሮ እስከ ሙሴ
ድረስ የተመረጡ አበው ለቤተሰቦቻቸው የክህነትን ተግባር ይፈጽሙ ነበር። ክህነት
እግዚአብሔር የሚገለገልበት ልዩ ጥሪና ስጦታ እንደመሆኑ መጠን እነዚህ አባቶች
ራሳቸውንና ቤተሰቦቻቸውን ከእግዚአብሔር ጋር በማገናኘት ይህን አገልግሎት
ይፈጽሙ ነበር። ለማስረጃ ያህልም የሚከተሉትን መመልከት ይቻላል።
86
ይህም ኀይለ ቃል መልከጼዴቅ የልዑል እግዚአብሔር ካህን ብቻ ሳይሆን የወልደ
እግዚአብሔርም ምሳሌ መሆኑን ያመለክታል። ቅዱስ ጳውሎስ ይህንን ኀይለ ቃል
ሲያብራራ እንዲህ ነበር ያለው፤ “የሳሌም ንጉሥ፣ የልዑል እግዚአብሔርም ካህን
የሆነ ይህ መልከ ጼዴቅ፥ አብርሃም ነገሥታትን ድል ነስቶ በተመለሰ ጊዜ ከእርሱ
ጋር ተገናኝቶ ባረከው፤ አብርሃምም ከገንዘቡ ሁሉ ከዐሥር አንድ ሰጠው፤… ክህነቱ
የወልደ እግዚአብሔር ምሳሌ ሆኖ ለዘለዓለም ይኖራል።” (ዕብ፯፥፩‐፬፡፡) ለጊዜው
ይህን ያህል ጠቀስን እንጂ ሙሉው ምዕራፍ የመልከ ጼዴቅን ክህነትና ክብር
ከክርስቶስ ጋር እያነጻጸረ ያቀረበበት ክፍል ነው። ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስም
በቅዳሴው ምዕራፍ ፫ ላይ በሰፊው ያቀረበውን ምስክርነት መመልከት ይቻላል።
፮.፪.አስተምህሮ
የተከበሩ አንባቢ ሆይ-upÉT>Á የሚከተሉትን ጥያቄዎች ለመመለስ ይሞክሩ፡፡
እነዚህም፦
88
እነዚህንም ተግባራት የሚያከናውኑት በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ምሥጢራተ ቤተክርስቲያን
ከመፈጸምና ከማገልገል ጋር ነው።
ምንም እንኩዋን ለሐዲስ ኪዳን ክህነት እንደ ብሉይ ኪዳን ለክህነት አገልግሎት
የተለየ ዘርና ነገድ ባያስፈልገውም ሁሉም የሰው ዘር ካህን ሊሆን እንደማይችል ግልጽ
ነው፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይከተሉት ከነበሩት ፭ ገበያ ሕዝብ
መካከል ለክህነት አገልግሎት መጀመሪያ የመረጣቸው አስራ ሁለቱን ሐዋርያት እንጂ
ሁሉንም ተከታዮች አልነበረም። (ማቴ ፲፥፩‐፭፡፡ ማር፫፥፲፫‐፲፱፡፡ሉቃ፮፥፲፪‐፲፮፡፡)
89
በኦሪቱ እንደተጻፈ መልእክቱ ለቤተ እስራኤል ሁሉ ነው፡፡ በካህናት አገልግሎት
ለምትወደስ፣ ለምትመሰገን የእግዚአብሔር መንግሥት መመረጣቸውን፤ ካህናት ከእነሱ
ማኅፀንና አብራክ እንደሚወለዱና ከሌላው የዓለም ሕዝብ ሁሉ ተለይተው የእግዚአብሔር
ማደሪያዎች እንደሚሆኑ የሚገልጽ ነው፡፡ ከዚህ ውጪ ሁሉንም እስራኤላዉያን ካህናት
ናቸው ማለቱ አልነበረም፡፡ ይህማ እንዳይሆን ከመካከላቸው የሌዊን ነገድ በተለይም ደግሞ
አሮንንና ልጆቹን በክህነት እንዲያገለግሉት እግዚአብሔር መምረጡን ባልነገረንም ነበር።
90
በብሉይ ኪዳንና በሐዲስ ኪዳን ክህነት መካከል ያለ ልዩነት
ተራ.ቁ የብሉይ ኪዳን ክህነት የሐዲስ ኪዳን ክህነት
፩ ጊዜያዊ ነበር። ዘላለማዊ ነው፡፡
91
በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የታወቁ ሦስት የክህነት ሥልጣን ደረጃዎች አሉ።እነዚህም
ጵጵስና ፣ቅስናና ድቁና ናቸው። እነዚህ የሥልጣን ደረጃዎችም ከየትም የተገኙና የተፈጠሩ
ሳይሆኑ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሆናቸውን እንደሚከተለው እናያለን፡፡
፪.ቅስና፦
ይህ ከመዐርጋተ ክህነት አንዱ ሲሆን ባለሙያውና ተሿሚው ቄስ ወይም ቀሲስ ይባላል።
ትርጓሜውም የቤ/ክ አገልጋይ ማለት ነው። ቅስናን በተመለከተም ቅዱሳት መጻሕፍት
የሚሰጡት ምስክርነት ብዙ ነው። ጥቂቶቹን ብቻ እንደሚከተለው እናያለን።
92
• ”በየከተማውም ሲሄዱ ሐዋርያትና ቀሳውስት በኢየሩሳሌም ያዘዙትን ሥርዓት
አስተማሩአቸው። አብያተ ክርስቲያናትም በሃይማኖት ጸኑ፤ ዕለት ዕለትም
ቁጥራቸው ይበዛ ነበር።” (ሐዋ፲፮፥፬‐፮፡፡) በመልካም የሚያስተዳድሩ ቀሳውስት
ይልቁንም በመስበክና በማስተማር የሚደክሙ እጥፍ ክብር ይገባቸዋል።”
(፩ጢሞ፭፥፲፯፡፡)
፫.ድቁና፦
ይህ የመጨረሻው (ታችኛው) መዓርግ ክህነት ነው። ቃሉ “ዲያኮንያ” ከሚለው የግሪክ
ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም “ረዳት፣ አገልጋይ” ማለት ነው። ይህንንም መዓርገ ክህነት
በተመለከተ ቅዱሳት መጻሕፍት ምን እንደሚሉ ደግሞ እንመለከታለን ።
• ዲያቆናዊት፣
93
• ንፍቅ ዲያቆን፣
• አናጉንስጢስ /አንባቢ/፣
• ዐጸውተ ኀዋኅው፣
• ሊቀ ዲያቆን፣
• ቆሞስ፣
• ሊቀ ጳጳስና
፮.፫. አፈጻጸም
94
ምሥጢረ ክህነት እንደሌሎቹ ምሥጢራት ሁሉ ራሱን የቻለ የአፈጻጸም ሥርዓት አለው።
ይህንንም በሦስቱ ዐበይት የክህነት ደረጃዎች አንጻር ብቻ እንመለከታለን።
“ጵጵስና ሊሾም የሚወድ መልካም ሥራን ወደደ የሚለው ቃል የታመነ ነው፤ ነገር ግን
ጵጵስናን የሚሾም እንዲህ ሊሆን ይገባዋል፡፡
• የማይነቀፍ፤
95
“ለአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ኤጲስ ቆጶስ ሆኖ የሚሾመው የምእመናን ጠባቂ ሆኖ
ነውር የሌለበት፤ ንጹሕና ቸር፤ የዚህን ዓለም ጭንቀት የማያስብ፤ ፶ ዓመት የሞላው፤
የጎልማሳነት ኃይልን ያለፈ፤ ነገር የማይሠራ፤ በወንድሞች መካከል ሐሰትን የማይናገር
ይሆን ዘንድ እንደሚገባው በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ ሰማን (ዲድስቅልያ
፬፥፩፡፡) የሚማር ይሁን፤ ሰላምን የሚያደርግ ይሁን፤ ቂም ክፋትና ዐመፅ የሌለበት ልበ
ንጹሕ ይሁን፤ በጎ ሥራን ለመሥራት ትጉህ መንፈሳዊ ይሁን፤ የማይሳሳት፤
የማይቆጣ፤ የማይበቀል፤ ጸብና ክርክር የሌለው፤ የማይኮራ፤ ገንዘብ የማይወድ፤
የማይሳደብ ይሁን፤ በዚህ ዓለም ጉዳይና በሥጋው ነውር የሌለበት ይሁን፤ የሚራራና
የሚመጸውት ይሁን፤ ሰውን ወዳጅ የሆነ፤ እንግዳን የሚቀበል፤ ፊት አይቶ የማያዳላ፤
እውነተኛ ፈራጅ የሆነ፤ ጥበብ ያለው፤ ለመስጠት እጁን የሚዘረጋ፤ ረዳት የሌለውን
የሚቀበል፤ ድሆችን፥ ደሀ አደጎችንና ባልቴቶችን የሚወድ ይሁን”። (ዲዲስቅልያ
፬፥፰‐፲፭፡፡)
የአሿሿም ሥርዓት
ሁሉም ከተመረጡ በኋላ ሕዝቡና ቀሳውስቱ ዲያቆናቱ ኤጲስ ቆጶሳቱም በዕለተ እሑድ
ይሰብሰቡ። ከእርሱ የሚበልጠው “አለቃ ይሆናችሁ ዘንድ የመረጣችሁት ይህ ነውን?” ብሎ
ቀሳውስቱንና ዲያቆናቱን ይጠይቃቸዋል። አዎን ቢሉ “የከበረችው ሹመት ለዚህ
ትገባዋለችን?” ይበል፤ “በሚገባና በተረዳ ሥርዓት አኗኗርን አጽንቷልን? ምንም በደል
አልተገኘበትምን?” ይበል እነርሱም መልሰው እንደዚህ እንደሆነ ቢናገሩ በማድላት ያይደለ
በእውነት ሹመት ይገባዋል፡፡ በሦስተኛውም ደግሞ “ለዚህ ሹመት በእውነት ይገባዋልን?”
96
ብሎ ይጠይቃቸው። ነገር ሁሉ በሁለት ወይም በሦስት ምስክር ይጸናልና በሦስተኛውም
ጊዜ ይገባዋል ቢሉ ሁሉም እጃቸውን ዘርግተው ያጨበጭባሉ። ይህንንም በስምምነት
ካደረጉ በኋላ ጸጥታ ይሁን። ዲያቆናትም ቅዱሳት ወንጌላትን ገልጠው በተሾመው ራስ ላይ
ይያዙ፤ ኤጲስ ቆጶሳትም ለርሱ በሚገባው ወምበር ያስቀምጡት፤ ሁሉም ከተቀበሉት
እግዚአብሔርም ይቀበለዋል።
በሦስት ኤጲስ ቆጶሳት ይሾም፤ እንደዚህ ይሾም። በራሱ ላይ ወንጌልን ተሸክመው የበለጠው
ኤጲስ ቆጶስ እንደዚህ (ለሲመቱ የተዘጋጀውን ጸሎት) ይጸልይ። ጸሎቱን ከጨረሰ በኋላ
እጁን ይጫንበት። ይሳለመውም። መንፈስ ቅዱስም ይመላበት (ያድርበት) ዘንድ በፊቱ
ላይ እፍ ይበልበት። ከዚህ በኋላ የቀሩት ካህናት ሁሉ እጅ ይንሱት:: ሕዝቡ ግን እጁን
ይሳሙት:: ከዚህ በኋላ ቅዳሴውን ይፈጽሙ። (ፍት.ነገ .አንቀጽ፭፥፻፳‐፻፮፡፡)
ከዚህ በተጨማሪ
• ኤጲስ ቆጶስ ከአንድ ኤጲስ ቆጶስ አይሾምም። ከርእሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ ጋር ሁለት
ወይም ሦስት ሊቃነ ጳጳሳት /ጳጳሳት/ አንብሮተ እድ በማድረግ ይሾማሉ። /አብጥሊስ
፪፡፡/
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለጊዜው ለረድኡና ኤጲስ ቆጶስ አድርጎ ለሾመው ለቲቶ
ለፍጻሜው ደግሞ ለቤተክርስቲያን መመሪያ እንዲሆን ያስቀመጠው /ያስተላለፈው/
የቀሳውስት መስፈርት የሚከተለውን ይመስላል::
97
ገትቶ የያዘ፤ የሃይማኖት ትምህርት ነገርን በማስተማር የሚተጋ፤ ያልታዘዘ ትርፍን
የሚወድ አይሁን። የእውነት ትምህርትን በማስተማር ማረጋጋት የሚችል፤ የሚክዱትንና
የሚተናኮሉትን የሚከራከራቸው ይሁን እንጂ፤ ሠላሳ ዓመት የሆነው፤ መልካም የሆኑትን
የአምላክ መጻሕፍትን ነገር ይልቁንም አራቱን ወንጌላት ያወቀ፤ አምስት ሰዎች
የመሰከሩለት፤ (ፍት.ነገ.አነ ፮፥፪፻፲‐፪፲፫፡፡)
አፈጻጸም
በዚሁ መመዘኛ መሠረት በፍትሐ ነገሥት ስለቀሳውስት የአሿሿም ሥርዓት የሚከተለው
ሰፍሮ ይገኛል።
አፈጻጸም
98
የዲያቆናትን ሹመት በተመለከተ ፍትሐ ነገሥት ላይ እንዲህ የሚል ተጽፏል::
፬.የሚያስገኘው ጸጋ፦
የተከበሩ አንባቢ ሆይ የሚከተለውን ጥያቄ ለመመለስ ይሞክሩ
ማጠቃለያ:-
ቅዱሳት መጻሕፍት የካህናትን ሥራ በእረኝነት ተግባር መስለው ያስተምራሉ፡፡ የእረኛው
መዘናጋት በጎችን ለተኩላዎችና ለቀበሮዎች የተጋለጡ እንደሚያደርጋቸው ሁሉ የካህናት
መዘናጋትም በበግ የተመሰሉ ምእመናንን ለክህደትና ለኑፋቄ የተመቻቹ ያደርጋቸዋል፡፡
ሕዝቡ በኃጢአቱ ቢፈረድበትም ካህናትም ተጠያቂ መሆናቸው አይቀርም፡፡ መንጋው
የአራዊት ንጥቂያ ቢሆን፣ አለቅት ቢይዘው፣ ሳይጠግብ ቢመለስ፣ ከሌላ ማሳ ገብቶ ቢያጠፋ
በዚህም ምክንያት ወቀሳና ክስ ቢከተል፣ /ቢመጣ/ ዋናው ተጠያቂ እረኛው መሆኑ የታወቀ
ነው፡፡ በምእመናን ጥፋት፣ ክህደት፣ ሥርዓት የለሽ መሆን፣ ንስሐ አለመግባትና ከቅዱስ
ቁርባንና ከመልካም ምግባራት ሁሉ መራቅ ቀጥተኛ ተጠያቂው ካህኑ ስለሆነ ካህናት
እንዲጠነቀቁና ሓላፊነታቸውን እንዲወጡ እነዚሁ መጻሕፍት ያስጠነቅቃሉ፡፡ (ሕዝ
፴፫፥፯‐፲፤ ፴፬፥፩‐ፍጻሜ፡፡) በምድር ላይ ያለች የእግዚአብሔር ቤተ መንግሥት ቤተ
ክርስቲያን ናት፡፡ አስተናጋጆች /አስተናባሪዎች/፣ መጋቢዎች፣ መሳፍንትና መኳንንት
ይሆኑት ዘንድ ንጉሡ እግዚአብሔር የሾማቸው ደግሞ ካህናትን ነው፡፡ በምድር ላይ ከዚህ
የተሻለ ቀርቶ የሚወዳደር ምን ዓይነት ሥልጣን ይኖራል? ካህን ሆኖ ከመሾምስ
የሚበልጥና የሚወዳደር ምን ዓይነት ሥራና አገልግሎት አለ? በእውነቱ ካህናት በምድር
ላይ ያሉ የእግዚአብሔር መላእክት ናቸው፡፡ እነሱን ማክበር መውደድና መታዘዝ
እግዚአብሔርን የሚያስደስት መሆኑን መረዳት ከምእመናን ይጠበቃል፡፡ ካህኑ ክህነቱ
ሲያቃልላት ከእግዚአብሔር እንደሚለይ ሁሉ ምእመናንም ካናትን ሲያቃልሉ
ከእግዚአብሔር ይጣላሉ::
ዋቢ መጻሕፍት
102
ምዕራፍ ሰባት
ምሥጢረ ንስሐና አፈጻጸሙ
መግቢያ
እግዚአብሔር አምላካችን ለሰው ልጆች ሥጋዊ ደዌ ሕመም ፈውስ የሚሆኑትን መፈወሻ
መድኃኒት እንደሰጠን ሁሉ የነፍስ ደዌ ኃጢአትን የሚያርቅና ከሕመሙ የሚፈውስ
መድኃኒት ንስሐን ሰጥቷቸዋል:: ደዌ የሆነው ኃጢአት በምድራዊ ኑሮአችው ሁሉ አብሮ
እንደሚኖር የታወቀ በመሆኑ መድኃኔዓለም ክርስቶስ መድኃኒቱንም አብሯቸው ይኖር
ዘንድ ከሐኪሞች ከካህናት ጋር በመካከላችው አኖረው::
103
፯∙፩ አመሠራረት
የምሥጢረ ንስሐን አመሠራረት ከማየታችን በፊት ምነነቱን ባጭሩ እንገልጻለን።
ንስሐ ማለት ከጥምቀት በኋላ በሠሩት ኃጢአት ከልብ ማዘን፣ ወደ መምህረ ንስሐ
ሄዶ መናዘዝ (ኃጢአትን መናገር)፣ ጥፋትን ላለመድገም መወሰንና በእግዚአብሔር
ቸርነት፥ በካህኑም የማሰር የመፍታት ሥልጣን አምኖ አነሰ፣ በዛ ሳይሉ የተሰጠውን
ቀኖና በደስታና በምስጋና ተቀብሎ መፈጸም ነው። ከላይ በተገለጸው መሠረት
ምሥጢረ ንስሐ ምእመናን ከኃጢአት ቁራኝነት የሚላቀቁበትና አዲስ ሕይወትን
የሚያገኙበት የድኅነተ ነፍስ መንገድ ነው፡፡ ሥርወ ቃሉ “ነስሐ” የሚለው የግእዝ
ቃል ሲሆን ትርጉሙም ንስሐ ገባ፣ ዐዘነ፣ ተጠጠተ፣ ተመለሰ፣ ክፉ ዐመሉን ተወ፣
ጠባዩን ለወጠ፣ ማለት ነው። (ኪ.ወ.ክፍሌ ገጽ ፮፻፶፭፡፡)
፯.፪. አስተምህሮ
❖ (በሉቃ ፲፭፥፬-ፍጻሜው) ስናነብ ከምናገኛቸው ሦስቱ የጠፉ ነገሮች መካከል
ከርስዎ ሕይወት ጋር የሚመሳሰለውን ለይተው ለማወቅ ይሞክሩ ።
104
ኃይልና ምሥጢር ያሳዩናል:: ከሀገርና ከወገን ተለይቶ፤ ከሃይማኖት፣ ከምግባር ምድረ በዳ
በሆነ ቦታም መጥፋት አለ:: በቤት ውስጥ ሆኖ የትም ሳይወጡ ባሉበት ሁኔታ መጥፋት
አለ:: ከሞላ ከተትረፈረፈ፥ ሰላምና ፍቅር ከሰፈነበት ቤት አሻፈረኝ ልቀቁኝ ብሎ ወጥቶም
መጥፋት አለ፡፡ ባለንብረትና ወላጅ አባት የሆነ ሰው ደግሞ ያ ነገር የጠፋበትን መንገድና
ሁኔታ እያሰላሰለ ከመናደድ ይልቅ የሚገኝበትን መንገድ በማሰብ ፍለጋው ላይ ተግቶ
ይሠራል:: ባገኘው ጊዜ ደግሞ ባለው ነገርና አቅም ሁሉ ደስታውን ይገልጻል። በመንፈሳዊ
የሕይወት ጉዞም ሰዎች በተመሳሳይ እይታ በልዩ ልዩ መንገድ ከእግዚአብሔር እጅ
ሊወጡ፤ ከመንፈሳዊት ቤታቸውም ሊኮበልሉ /ሊጠፉ/ ይችላሉ:: እግዚአብሔር አምላካችን
ግን የኀጥኡን ሰው ሞቱንና ጥፋቱን አይሻም፤ መመለሱን እንጂ። “በውኑ ኃጢያተኛ
ይሞት ዘንድ እፈቅዳለሁን? ይላል ጌታ እግዚአብሔር፤ ከመንገድ ሊመልስና በሕይወት
ይኖር ዘንድ አደለምን?” እንዲል፡፡ (ሕዝ ፲፰፥፳፫፡፡)
የቀደመ በደልና ኀጢአት ይደመሰስ /ይሠረይ/ ዘንድ ንስሐ በእጅጉ አስፈላጊ ነው።
ሐዋርያው ቅዱስ ዼጥሮስ በበዓለ ሃምሳ በጽርሐ ጽዮን ዙሪያ ተሰብስበው ለነበሩ እጅግ
በርካታ ሕዝቦች የድኅነትን ትምህርት አስተማራቸው:: በትምህርቱ የተመሰጡት እነዚያ
ሰዎችም “ምን እናድርግ?” ባሉ ጊዜ የተመለሰላቸው መልስ ከንስሐ ሕይወት ጋር የተያያዘ
ነበር። (ሐዋ.፪፥፲፬‐፵፩፡፡) በቤተ መቅደስ በር ላይ ይቀመጥ የነበረውን ድውይ /መሔድ
የተሳነውን ሕሙም/ ቅዱስ ጴጥሮስና ቅዱስ ዮሐንስ በክርስቶስ ስም በፈወሱት ጊዜ
መገረምና መደነቅ የሞላባቸው አይሁድ ብዙ ነበሩ። ቅዱስ ጴጥሮስ ለእነዚህም በሥጋ
ስለተገለጠው አምላክ ካስተማራቸው በኋላ አለቆቻቸው በዓለማ ክርስቶስን በካዱትና
በገደሉት ጊዜ ተባባሪዎቻቸው የሆናችሁት እናንተ እንግዲህ ኀጢአታችሁ ይሰረይላችሁ
ዘንድ ንስሐ ግቡ፤ ተመለሱም፤ (ሐዋ. ፫፥፲፱፡፡) መባላቸውን እናነባለን። እነዚህ ሁለት
ተያያዥ ኃይለ ቃላት (ነጥቦች) የንስሐን አስፈላጊነት የሚያመለክቱ ናቸው፡፡ ንስሐ
የማንኛውንም ምእመን ቁስለ ነፍስ የሚፈውስ መንፈሳዊ መድኃኒት ነው::
105
ንስሐን ስናስብ ምንጊዜም ኀጢአትን ማሰባችን አይቀርም:: ምክንያቱም አንድ ሰው
የሠራው ኀጢአት በእግዚአብሔር በሌሎች፣ በራሱና በቤተ ክርስቲያን ላይ የተፈጸመ
ጥፋት ነውና:: ኀጢአት ባይኖር ኖሮ ንሰሐ ባላስፈለገም ነበርና:: ኀጢአትን በምናስብበት
ጊዜ ደግሞ ምንጩን መነሻውንና የሚያባብሱትን ነገሮች መመርመራችን የግድ ነው::
ይህም መንፈሳዊ ሕይወታችንን እንዳያውክብን ቀድመን ለመጠንቀቅ ማለትም አርቆ
ለማጠር ይጠቅመናል፡፡ ኀጢአት ከ፯ ዓመት ጀምሮ በማንኛውም የዕድሜ ክልል
ይፈጸማል:: በተለይ ደግሞ በሃይማኖት መኖርን እንደ እስረኝነት በሚቆጥር፣ አዳዲስ
ነገሮችን ሁሉ ለመሞከር በሚደፍርና ሌላው ያየውን ካላየ ሞቶ የሚያድር የሚመስለው
ትውልድ የኃጢአት ተጋላጭነቱ ከፍተኛ ነው:: ለዚህ ተጋላጭ የሆነው ወጣት ስሜቶቹን
መፈተሽ ይኖርበታል። ስሜቶቹ በምን እንደተቃኙና እንዳሻቸው ቢለቀቁ ውጤታቸው ምን
ሊሆን እንደሚችል ማስተዋል በእጅጉ ይጠቅመዋል፡፡ መረን መለቀቅ (ዝርው መሆን)
ከመንፈሳዊ ሕይወት አንጻር ሲመዘን ምን ሊባል እንደሚችል ቀድሞ ማሰብ ይገባዋል::
ይህን ማድረጉ ከኃጢአት ተላቆ ወደ ጽድቅ ከተማ የሚያደርገውን ጉዞ ያቀላጥፋለታል::
ያዘነበት፣ የተጸጸተበት፣ የተናዘዘበትና የተሠረየለት ኀጢአት ዳግመኛ ደጁን እንዳያንኳኳ፤
ቢያንኳኳም እንኳን አስተናጋጅ እንዲያጣ፤ ቢሰናከልም ፈጥኖ የሚፀፀትበትንና
የሚናዘዝበትን ኃይል ያደርግለታል:: በዚህም ምክንያት የኀጢአት ምንጮቹንና
የሚያባብሱ ጉዳዮችን ለይቶ (አውቆ) መጋደል /መዋጋት/ በክርስቲያኖች መንፈሳዊ ጉዞ
ውስጥ የንስሐ ሕይወት አካል ይሆናል ማለት ነው።
፯∙፫∙ አፈጻጸም
❖ አንድ ወጣት ከአንዲት ተማሪ ጋር ድቀት አገኘውና ልጅቱ ፀነሰች፤መፅነሷን
ሲሰማ ባደረገው ነገር እጅግ ተጸጽቶ ቤ/ክ ሄደና ለእግዚአብሔር አየተናዘዘ
አለቀሰ:: ይህ ልጅ ንስሐ ገባ ማለት ይቻላልን? ለምን? /እንዴት?
በንስሐ ሂደት ሁለተኛው ደረጃ ኀጢአትን መተው ነው። ኀጢአትን መተው ሲባልም
የኀጢአትን እርሾ ከኅሊናና ከልቡና ጨርሶ /ፈጽሞ/ ማጥፋት ነው፡፡ ይህም ኀጢአትን
ከማሰብ መለየት ማለት ነው፡፡ ምክንያቱም ሰው ምንም እንኳን ኀጢአቱን በገቢር
/በተግባር/ ባይፈጽምም በልቡ ፍቅረ ኀጢአት ከነገሠ/ /ኀጢአት በልቡ ከተመላለሰ/ ንስሐ
አያስፈልገውም አይባልም። ይህ ሰው የእግዚአብሔርን ሕግ ለመጠበቅ ብሎ ኀጢአትን
በገቢር ባይሠራም ኀጢአትን አልጠላምና ኀጢአትን ትቷል ሊባል አይችልም፡፡ በልቡናው
የኀጢአት ፍቅርና ቅሪት ስላለ ፀፀቱና ንስሐው ልቡናው ከኀጢአት እስኪነጻ መሆን
አለበት።
ቀጣዩ ተግባር ተነሳሒው ከካህኑ ምክርና ተግሣጽ የሚያገኝበት፤ ቀኖና /የንስሐ ቅጣት/
የሚቀበልበትና ካሣ /መቀጫ/ የሚከፈልበት ክፍል ነው፡፡ ካህኑ የሚሰጠው ቀኖና እንደ
ኅጢአቱ መጠን ተለክቶ የተሰጠ ማወራረጃ ማካካሻ ሳይሆን እንደተነሳሒው አቅም፣ እንደ
ካህኑ ሥልጣንና እንደ እግዚአብሔር ቸርነት የሆነ የድኅነት ምክንያት ሆኖ የሚቀርብ
ነው:: ቀኖናውም የጾም፣ የጸሎት፣ የስግደት፣ የምጽዋት ሊሆን ይችላል። ቀኖናው
ከተጠቀሱት ውስጥ በከፊል፣ በተጠናጠል ወይም በጠቅላላው የያዘ ሊሆን ይችላል።
ኀጢአቱን የሚደመስሰው የቀኖናው መብዛትና ማነስ ሳይሆን በካህኑ ሥልጣን ላይ የተገለጸ
የእግዚአብሔር ቸርነትና ርኁራኄ ነው:: ቀኖናው ግን ለቸርነቱ ምክንያት የሚሆን
የተነሳሒውን ፍላጎት፣ ጥረት፣ እምነት፣ ፀፀት እንዲሁም የካህኑን ሥልጣን መሠረት ያደረገ
ነው፡፡ ቀኖናውም ለተነሳሒው የመታዘዙና የመፀፀቱ ማሳያ (መገለጫ) ተደርጎ ይወሰዳል።
የኀጢአትና የዐመፅ መሣሪያ የነበሩ ብልቶቹ የጽድቅ መሣሪያ ሆነው ለመለወጣቸውም
ማረጋገጫ ነው። ተነሳሒው በታዛዥነት ቀኖናውን ተቀብሎ ሲፈጽም፣ ልቡናው በጸጸት
ሲሰበር፣ ኃጢአትን ሲጠላና ሰይጣንን ሲክድ እግዚአብሔር ይደሰትበታል፡፡ በመጨረሻም
ቀኖናውን ፈጽሞ ለመምህረ ንስሐው ንስሐውን በመንገር ፍትሐት ዘወልድ ተደግሞለት
ካህኑ “እግዚአብሔር ይፍታህ!” ሲለው ከኃጢአት የተፈታና ነጻ የወጣ ይሆናል፡፡
ወዲያውኑም ሥጋውን በልቶ፣ ደሙንም ጠጥቶ ከማኅበረ ምእመናን ይቀላቀላል። ቀደም
አድርገን እንደገለጽነውም ልቡ በጥልቅ ሐዘን በተሰበረና በተፀፀተ ጊዜ ለመናዘዝ የተነሣው
ዳግመኛ ያንን ኃጢአት ላለመሥራት ወስኖ ነው:: ሥጋውንና ደሙን ተቀብሎ ከማኅበረ
ምእመናን ከተቀላቀለ በኋላ በእግዚአብሔር አጋዥነት ውሳኔውን ለማስከበር ይታገላል።
አሁንም ዳግመኛ ከተሳሳተ ከላይ የተመለከትነው የንስሐ ሂደት ዳግመኛ ይቀጥላል::
ኃጢአት መሥራቱ በድፍረት አይሁን እንጂ ኃጢአት ምንጊዜም በንስሐ ይሰረያል።
፯∙፬ የሚያስገኘው ጸጋ
❖ ደግሜ ያንን ኃጢአት ልሠራው ስልምችል ላለመሥራት እንዴት
እወስናለሁ? ኃጢአት ላለመሥራት መወሰን ይቻላልን?
ማጠቃለያ
110
ዋቢ መጻሕፍት
111
ምዕራፍ ስምንት
ምሥጢረ ተክሊልና አፈጻጸሙ
መግቢያ
ቤተ ክርስቲያን ልጆቿ ለእግዚአብሔር መንግሥት ለመብቃት በሚያደርጉት መንፈሳዊ
ጉዞ ሁለት የኑሮ አማራጮች አቅርባላቸዋለች፡፡ አንደኛው ፍጹም የሆነ የድንግልና
ሕይወትን ጠብቆ በመኖር የሚገባበትና በተጋድሎ የሚኖርበት የምንኩስና ሕይወት ሲሆን
ሁለተኛው በተቀደሰ ጋብቻ ክብደ ዓለምን በመቋቋም እየተጋገዙ የሚጓዙበት ሕይወት ነው::
112
• የምሥጢረ ተክሊልን አፈጻጸምና የሚያስገኘውን ጸጋ ይረዳሉ።
፰.፩. አመሠራረት
በጋብቻ አመሠራረት ሂደት “እግዚአብሔር አምላክም አለ፦ ሰው ብቻውን ይኖር ዘንድ
መልካም አይደለም፤ የሚረዳውን ጓደኛ እንፍጠርለት እንጂ።” (ዘፍ ፪፥፲፰፡፡) የሚለው
ኃይለ ቃል መነሻና መሠረት ነው። ይህም የጋብቻ መሥራቹና ፈቃጁ እግዚአብሔር
መሆኑንና የተመሠረተውም በመጀመሪያዎቹ አባታችንና እናታችን /በአዳምና በሔዋን/
መካከል እንደነበር ያስረዳል:: “ምሥጢረ ተክሊል”
ሸለመ፣ አክሊል አቀዳጀ፣ ማለት ነው። ምሥጢረ ተክሊል በሰፊው ሲብራራ ደግሞ
የሙሽራውንና የሙሽራይቱን የጋብቻ ቃል ኪዳን በሃይማኖት የሚያጸና፣ የጋብቻ ግዴታን
ለመወጣት የሚያስችል፣ በፍቅር የሚያስተሳስርና ዘላቂ አነድነትን የሚያስገኝ የጸጋ
ምሥጢር ነው፡፡ የሚሰጠውም ምንጊዜም ቢሆን እንደሌሎቹ ምሥጢራት ከቅዱስ ቁርባን
ጋር ነው። ይህ የጋብቻ ሥርዓት፣ የጋብቻ ኪዳን፣ ስምምነትና ውል በታወቀ በቂ ማክንያት
ካልሆነ በቀር ፈጽሞ የማይፈርስ ጽኑዕ አንድነት ነው። ቅድስት ቤተክርስቲያን ለሙሽራው
/መርዓዊ/ እና ለሙሽሪት /መርዓት/ የምትፈጽመው ይህ መንፈሳዊ የጋብቻ ሥርዓት
በክርስቶስና በቤተ ክርስቲያን መካከል ላለው ጽኑዕ አንድነትና ዘላለማዊ ፍቅር ምሳሌ
የሚሆን /የሆነ/ ታላቅ ምሥጢር ነው። (ኤፌ ፭፥፴‐፴፫፡፡) በሐዲስ ኪዳንም ዘመን
መጀመሪያ አካባቢ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በገሊላ ቃና በተዘጋጀው የጋብቻ ሥርዓት
ላይ በመገኘት ክርስቲያናዊ ጋብቻን አክብሯል። በዶኪማስ ቤት ከእናቱ ከእመቤታችን
ከቅድስት ድንግል ማርያምና ከደቀ መዛሙርቱ ከሐዋርያት ጋር ተገኝቶ ጋብቻን ፈጽሞ
ባርኮታል። የታወቀና የተገለጠ የመጀመሪያ ተአምሩንም በእመቤታችን ምልጃ የፈጸመው
በዚሁ ሰርግ ቤት መሆኑ ይታወቃል። (ዮሐ ፪፥፩‐፲፪፡፡)
፰∙፪∙ አስተምህሮ
ከላይ የምሥጢረ ተክሊል አመሠራረት ላይ እንዳየነው እግዚአብሔር አምላካችን ጋብቻን
በአዳምና በሔዋን መካከል ሲመሠርት አንድ ወንድ ላንዲት ሴት፥ አንዲት ሴትም
ለአንድ ወንድ ብቻ መሆኑን በተግባር ገልጾልናል፡፡ ይህም ለክርስቲያናዊ ጋብቻ ቋሚ
የዘለዓለም መመሪያ መሆኑን በሚገባ ማስተዋል ይገባል። ጋብቻውም የተመሠረተው
113
በተመሳሳይ ጾታ መካከል ሳይሆን በሁለት ተቃራኒ ጾታዎች መካከል መሆኑንም ያሳየን
ራሱ እግዚአብሔር ነው። /ዘፍ፪፥፲፰-ፍጻሜ፡፡) ግብረ ሰዶማውያን ለሚያነሱት መሠረት
የለሽ ጥያቄ ይህን ከሰብአዊ ተፈጥሮአችን አኳያ መመርመር በራሱ መልስ ይሰጣል።
የጋብቻ ዓላማዎች
❖ እግዚአብሔር ጋብቻን ፈቅዶ ለሰው ልጆች የሰጠበት ምክንያት (ዓላማ)
ምንድን ነው?
እግዚአብሔር አምላክ ከአዳምና ከሔዋን ጀምሮ ጋብቻን ለሰው ልጆች ባርኮ የሰጠበት
መሠረታዊ ዓላማ ከዚህ በታች እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡
ሀ. ዘር መተካት፦
እግዚአብሔር አምላክ ባዘዘው (በፈቀደው) መሠረት የመጀመሪያው የጋብቻ ዓላማ ልጆችን
መውለድ ዘርን መተካትና ማብዛትና ትውልድ እንዲቀጥል /እንዳይቋረጥ/ ማድረግ ነው።
(ዘፍ፩፥፳፯፡፡) አዳምን ያለዘርና ያለልደት ከዐራቱ ባሕርያተ ሥጋና ከሦስቱ ባሕርያተ
ነፍስ የፈጠረው እግዚአብሔር ከአዳም ጎን አንዲት አጥንት ነሥቶ ፈጠራት ቀጣዩ የሰው
ልጅ ትውልድ ግን ከጋብቻ ፍሬ (ከዘር ከሩካቤ በሚገኝ ውጤት) ላይ የተመሠረተ እንዲሆን
ፈቀደ። በዚህም መሠረት ጥንዶቹ (ወላጆች) ልጆችን በመውለድ የእግዚአብሔር ሥራ፣
ፈቃድና ትእዛዝ ተባባሪዎችና ፈጻሚዎች ይሆናሉ ማለት ነው። ትዳርን አማራጫቸው
ያደረጉ ክርስቲያኖች ሁሉ ይህንን ትእዛዘ እግዚአብሔር ማክበር ይኖርባቸዋል።
• እርግዝና ሲገፋ፤
115
• ቢቻል በሰባቱ አጽዋማት፤ በተለይ ግን በዐቢይ ጾም፤ (ፍት.ነገ
፳፬፥፱፻፳፩‐፱፻፳፬፡፡) ከዚህ ውጪ፤ እንግዳ ክስተቶች ሲፈጠሩ ከንስሐ አባት ጋር
መነጋገርና መጨረስ ይገባል።
ወጣቶች ለአቅመ አዳምና ሔዋን ደርሰው ማግባት ከፈለጉ የምሥጢረ ተክሊልን ጋብቻ
መምረጥ ለሥጋም ለነፍስም እንደሚበጅ መረዳት አለባቸው። አባቶቻችንና እናቶቻችን
በፈቃደ እግዚአብሔር በመታገዝ ከማግባታቸው በፊት ድንግልናቸውን ጠብቀው ማለትም
ታቅበው ይኖሩ ነበር:: ከዚያ በኋላ በድንግልና በመጋባት የተባረከ የትዳር ጊዜን እንዳሳለፉ
መርሳት አይገባም። በፈቃደ እግዚአብሔር የሚመራ ሰው እግዚአብሔር መንገዶቹን ሁሉ
ስለሚያቃናለት አይቸገርም:: የምትሆነውን የትዳር አጋር በወላጆቹ፣ በራሱና በወደደው ላይ
አድሮ ስለሚመርጥለት ባትመቸኝስ፥ ባይመቸኝስ በሚል ስጋት አይጨነቅም። ቀድሜ
መሞከር አለብኝ በሚል ድፍረትም ክብሩን የሚያሳጣውንና የሚያስቀጣውን ኃጢአት
አይሠራም። በማያዋጣ ሥጋዊ ጥበብ ሽፋን ሥጋዊ ፍትወቱን ከማርካት ይልቅ በጸሎት
ፈጣሪውን ወደ መጠየቅ ስለሚያዘነብል የተመካበት እግዚአብሔር ጎዶሎውን ሁሉ
ይሞላለታል። የሚመቻትን ረዳት እንደሚሰጠው ስለሚያምን እግዚአብሔር ይደሰትበታል።
ክርስቲያኖች ሁሉ ዓለማዊውን ፍልስፍናና ሙከራ (ትግበራ) ትተው በተወክሎ
እግዚአብሔር የትዳር አጋራቸውን መፈለግ፣ መምረጥ፣ ከእግዚአብሔር እጅ መቀበልና
ትዳርን መመሥረት ይጠበቅባቸዋል። በተጨማሪም ሁለቱ እጮኛሞች በድብቅ ስለቆረቡ
ወይም ምናልባትም የንስሐ አባታቸው /ካህኑ/ ከተጠቀሰው ሥርዓት ውጪ ስላማማላቸው
ሥርዓተ ተክሊል እንደተፈጸመና በሥርዓተ ቤተክርስቲያን እንደተጋቡ እንደማይቆጠር
ማስተዋል ያስፈልጋል። ብዙዎች ግን ስለማይተማመኑና በተክሊል መጋባትን
እንደመታሰር ስለሚቆጥሩት ከተቀደሰው የጋብቻ ሥርዓት ይርቃሉ፡፡ በተጨማሪም ስለ
ቅዱስ ጋብቻ (የተክሊል ጋብቻ) አስፈላጊነት፣ አፈጻጸምና ክብር ባለማወቅም ዓለማዊውን
ጋብቻ የሚመርጡ አሉ፡፡
፰∙፫ አፈጻጸም
የተከበሩ አንባቢ ሆይ ይህን ርእስ ከማብራራታችን በፊት የሚከተሉትን ጥያቄዎች
ለመመለስ ይሞክሩ?
116
❖ ሥርዓተ ተክሊል የሚፈጸመው ሁለቱም ደናግል ሆነው ሲገኙ ነው።
ድንግልናቸውን በልዩ ልዩ ሁኔታ ላጡ ወጣቶች /ወንዶችም ሴቶችም/ ቤተ
ክርስቲያን የምታስተናግድበት መንፈሳዊ ሥርዓት አላትን? ካለ ምንድነው?
117
-በሃይማኖት ጸንተው ለመኖር በሚያደርጉት ግብግብ የሚቀበሉትን ፈተና ያመለክታል::
በመስቀሉ /በወንጌሉ/ ኃይልም ፈተናውን ድል እንደሚያደርጉት ያሳያል። መስቀልና
ወንጌል የድል አድራጊነት /የአሸናፊነት/ ምልክት ነውና።
ቀለበቱ የሃይማኖት ምሳሌ ነው:: ቀለበት በክብነቱና ፍጻሜ የለሽ በመሆኑ በቃል ኪዳን
የጸናው የተክሊል ጋብቻም ከሕይወት ፍጻሜ በስተቀር ማንም የማይለያየው መሆኑን
ያሳያል። በአንዲት ርትዕት ሃይማኖት የማይናወጽ መሠረት ላይ የታነጸ እንደመሆኑ
የጠላት ነፋስ፣ የፈተና ጎርፍና ልዩ ልዩ ወቅታዊ የስሜት ማዕበላት የማያናዋውጡት
/የማያፈርሱት/ መሆኑን ያመለክታል።
ቅብዐ ሜሮን በምሥጢረ ሜሮን እንዳየነው የመንፈስ ቅዱስ ማሳደሪያ ነው:: በዚህም
መሠረት ረድኤተ መንፈስ ቅዱስ በትዳራቸው ዘመን ሙሉ የማይለያቸው መሆኑን
ያጠይቃል።
ሠ. አክሊል መቀዳጀታቸው
118
• በጋብቻ ሕይወት ውስጥ ከባድ ፈተና ነው ብለው የሚያስቡት ምንድነው? እንዴት?
፰∙፬ የሚያስገኘው ጸጋ
❖ በምሥጢረ ተክሊል ተጋቢ ጥንዶቹ የሚያገኙት ጸጋ ምንድን ነው?
ሐ.የተባረኩ ልጆች
ዋቢ መጻሕፍት
• ማ/ቅ፤ ትምህርተ ሃይማኖት ርትዕት፤ ማኀበረ ቅዱሳን፤ ፲፱፻፺፫
አ/አ።
121
• ክርስቲን ሻዮ፤ መ/ሰ ዳኛቸው ካሳሁን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ
ተዋህዶ ቤ/ክ ትውፊትና መንፈሳዊ ሕይወት፤ ማኀበረ ቅዱሳን፤
1999፤ አ/አ።
ምዕራፍ ዘጠኝ
ምሥጢረ ቀንዲልና አፈጻጸሙ
መግቢያ:‐
ይህ ምሥጢር በአሁኑ ጊዜ በአብዛኛው አብያተ ክርስቲያናት ከቁጥር ሟሟያነት የዘለለ
ተግባራዊ አፋጻጸም የማይታይበት ነው፡፡ የቀደሙ አባቶቻችን ይህንንም ምሥጢር እንደ
ሌሎቹ ምሥጢራት በአግባቡ ይፈጽሙት እንደ ነበር ቅዱሳት መጻሕፍት ይመሰክራሉ::
የቤተ ክርስቲያን አባቶች በፈቃደ እግዚአብሔር የሠሩት የምሥጢረ ቀንዲል አፈጻጸም
ከአመሠራረቱ ጀምሮ የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮና የሚያስገኘው ጸጋም በዚህ ምዕራፍ
ተብራርቶ ቀርቧል፡፡ ከሰባቱ የቤተ ክርስቲያን ምሰሶዎች ወይም ምሥጢራት ይህም እንደ
ስድስቱ ሁሉ ጸንቶ እንዲቆም በማድረግ ሒደት አንባቢያን ሁሉ የበኩላቸውን እንዲወጡ
ይህ ጽሑፍ አስተዋጽዖ ያበረክታል ተብሎ ታምኖበታል::
፱∙፩ አመሠራረት
122
ካንድል /Candle/ የሚለውን የላቲን ቃል መሠረት ያደረገው “ቀንዲል” ትርጉሙም
“መብራት” ነው። ምሥጢረ ቀንዲል ማለት ካህኑ ለታመሙ ክርስቲያኖች በሚያደርገው
ጸሎት፣ በሚሰጠው ቡራኬና በሚቀባውም ዘይት /ቅብዐ ቅዱስ/ አማካኝነት በእግዚአብሔር
ቸርነት የሚገኘውን የሥጋና የነፍስ ድኅነትና ፈውስ የሚያመለክት ምሥጢር ነው።
መጽሐፈ ዘይት፣ ጸሎተ ዘይት፣ ቅብዐ ድውያን ማለትም ይሆናል:: ስሙን ከድርጊቱ
አግኝቶታል። ጸሎቱ ሲፈጸም መብራት አብርቶ ነውና::
❖ ፱∙፪. አስተምህሮ
ይህ ምሥጢር ከጥንት ጀምሮ በቤተክርስቲያን ይፈጸም እንደነበር የታወቀ ነው:: ከላይ
እንዳየነው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያትን፣ ሐዋርያትም ተከታዮቻቸውን፣ አዘዋቸው
ነበርና። ኢጶሊጦስ ዘሮም የተባለው አባት /፫መ/ክ/ዘ/ “ሐዋርያዊ ትውፊት” በተባለው
መጽሐፉ በምሥጢረ ቀንዲል አፈጻጸም ጊዜ ይጸለይ የነበረውን ጸሎት አስፍሮታል:: ይህም
የሚያመለክተው ምሥጢረ ቀንዲል በቤተ ክርስቲያን ይፈጸም የነበረው ከጥንት
/ከምሥረታዋ/ ጀምሮ መሆኑን ነው።
፱∙፫. አፈጻጸም
❖ ቤተክርስቲያን ምሥጢረ ቀንዲል የምትፈጽምላቸው ሕሙማን ምን ዓይነት ሕመም
ለታመሙት ነው?
የተከበሩ የምዕራፉ አንባቢ ሆይ:‐ የዚህን ጥያቄ መልስ በማስታወሻዎ ለመጻፍ ይሞክሩ
ቀንዲል:‐ ቅብዓ ቅዱስ /የተለየ የከበረ ዘይት (ቅባት) እየተባለ ይጠራል። ይህም ከወይራ
ዛፍ በጸሎት በመታገዝ በረድኤተ እግዚአብሔር የሚዘጋጅ /የሚወጣ /ዘይት ነው።
በተዘጋጀለት የክብር ዕቃ /ብልቃጥ/ ተደርጎ በከርሰ መንበር ወይም በዕቃ ቤት በክብር
ይቀመጣል። የቀንዲሉ አዘጋጅና ባለቤት ምሥጢሩንም ፈጻሚዋ ቤተ ክርስቲያን ናት፡፡
ከምእመናን ወገን የታመሙ ሲኖሩ ወደ ቤተክርስቲያን ወደ ካህኑ ይመጣሉ። የማይችሉ
የሆኑ እንደሆነ ካህኑን /ካህናቱን/ ወደ ቤታቸው ይጠራሉ፡፡ ካህኑ /የንስሐ አባቱ/ ሕሙሙን
ምእመን በማጽናናት ኃጢአቱን እንዲናዘዝ/ ንስሐ እንዲገባ/ ያደርገዋል:: በመቀጠልም
ባቅሙ የሚችለውን ቀኖና እንዲፈጽም ያዘዋል:: ከዚያም ካህኑ /የንስሐ አባቱ/ ከሌሎች
ካህናት ጋር ሆኖ ምሥጢሩን ለታማሚው ለመፈጸም ይዘጋጃል፡፡ ከዚያም ቀንዲሉን
/መብራቱን/ አብርቶ መጽሐፈ ቀንዲልን በመጠቀም የታዘዘውን ጸሎት ይጸልዩለታል።
በጸሎቱ ፍጻሜም የሕመምተኛውን ሕዋሳት በተለይ የታመመውን ክፍል በተጸለየበት ቅብዐ
ቅዱስ በመስቀል አምሳል /ምልክት/ ይቀቡታል:: በመጨረሻም ከማእሰረ ኃጢአት
የሚፈታበትን ሥርዓት /ኑዛዜ/ ይፈጽሙለታል። ይህም ለታመመው ምእመን ፈውሰ ሥጋ፣
ፈውሰ ነፍስን ያድለዋል።
124
ኃጢአት ሥርየት እንዲሆነው ነው። አእምሮ የሚገኝበት የአምስቱ የስሜት ሕዋሳት
ማዕከልና የማስተዋል /የማሰብ/ ኃይል የሚገኝበት ክፍል ነውና፤ በዋናነት ግንባርም
ይቀባል:: የልብ ማረፊያ ነውና ደረቱም ይቀባል፡፡ ሰውነቱን ሁሉ ሊበክል የሚችል
የርኩሰት ቁስል /ቁስለ ነፍስ/ የሚመነጭ ከሱ ነውና ፈጽሞ እንዲፈወስ እነዚህ ሁሉ
ይቀባሉ፡፡ ከቀሳውስት በታች ያሉ ዲያቆናት ግን ለካህናት ከመታዘዝና ከመራዳት
በስተቀር ይህንን ምሥጢር መፈጸም እንደማይችሉ የታወቀ ነው።
፱∙፬. የሚያስገኘው ጸጋ
❖ በምሥጢረ ቀንዲል የሚገኘው ጥቅም ምንድን ነው?
125
የሥጋና የነፍስ ደዌ ያላባቸው በመሆናቸው ፈውሱም የሥጋና የነፍስ ተብሎ በሁለት
ይከፈላል፡፡
ሀ. ፈውሰ ሥጋ ፦
ሰው ማለት ከአራቱ ባሕርያተ ሥጋና ከሦስቱ ባሕርያተ ነፍስ የተፈጠረ እንደመሆኑ በዚህ
ዓለም ሲኖር በሥጋውና በነፍሱ የሚቀበላቸው ሕማማት አሉ። ያንዱ መታመም
ሌላኛውንም ይጎዳል፤ ማለትም የሥጋ መታመም ነፍስን፣ የነፍስም መታመም ሥጋን
ስለሚያውከው ቤተክርስቲያን መንፈሳዊውን ሕክምና በተናጠል አትፈጽምም:: አንዱ
ተፈውሶ አንዱ ከታመመ ከላይ እንደገለጽነው የተፈወሰውም ታማሚ መሆኑ አይቀርምና
ምእመናን ይህን ድርብ ሕክምና ታክመው ፈውሰ ሥጋ፣ ፈውሰ ነፍስ እንዲያገኙ
የምታደርግበት መንገድ ምሥጢረ ቀንዲል ይባላል።
ፈውሰ ነፍስ
በምሥጢረ ቀንዲል የሚገኝ ሁለተኛው ጸጋ ፈውሰ ነፍስ ነው:: የሚታመመው ሥጋ ብቻ
ስላልሆነ /ነፍስም ስለምትታመም/ እንደ ሥጋ ሁሉ እሷም ፈውስ ያስፈልጋታል። ነፍስን
የሚያቆስላትና የሚያሳምማት ደግሞ ኀጢአት ነው። ከላይ እንደገለጽነው አንዱ አካል
ተፈውሶ ሌላኛው አካል በሽተኛ ከሆነ ሰውየው ጤነኛ ሆነ ማለት አይቻልምና፤ ሁለቱንም
እንደ ሕመማቸው ዓይነትና ጽናት ተመጣጣኝ የሆነ ሕክምና ሰጥቶ መፈወስ ይገባል።
ስንዱዋ ቤተክርስቲያን የአካለ ሥጋና የአካለ ነፍስ ውሑድ የሆነውን /ሰውን/ በጠቀስነው
መሠረት እያከመች ኖራለች፤ ትኖራለችም:: መንፈሳዊ ሐኪሞቿም ካህናት ናቸው፡፡
ሥልጣናቸው የሁለቱንም አካላት (የሥጋንና የነፍስን) ሕመም ለማከም የሚያስችል ሀይል
ያለው ነውና::
126
ሕመምተኛው ሰው የእግዚአብሔርን ቸርነት አምኖ ኀጢአቱን በተናዘዘ ጊዜ ኃጢአቱ
መክሰም ትጀምራለች። ካህኑ በሚሰጠው መንፈሳዊ ትምህርት መሠረት ከኃጢአት ጋር
ያለውን ሰንሰለት ቆርጦ በጣለና እግዚአብሔርን ኃጢአት እየሠራ ላለማሳዘን በወሰነ ጊዜ
ደግሞ በምሥጢረ ንስሐ እንደገለጽነው ከማእሰረ ኃጢአት የተፈታ ይሆናል:: የንስሐው፣
የኑዛዜዉና የቀኖናው አስፈላጊነትም ለፈውስ ነፍስ ነው:: እግዚአብሔር አምላካችን
የነፍሳችንን ድኅነትና ፈውስ ከሥጋችን ድኅነትና ፈውስ የበለጠ ስለሚፈልግ ለፈውሰ ነፍስ
ከፍተኛ ትኩረት እንድንሰጥ ይፈልጋል። ቅዱስ ጴጥሮስም “ክርስቶስ ስለ እኛ በሥጋው
ከተሰቀለ እናንተም ይህቺን ዐሳብ ጋሻ አድርጋችሁ ኑሩ፤ በሥጋው መከራ የተቀበለ
ከኃጢአት ድኖአልና።” (፩ጴጥ፬፥፩፡፡) በማለት የተናገረው ከያዝነው ፍሬ አሳብ ጋር
የተጣጣመ መልዕክት ያለው ነው። ይህም ምሥጢር የሚስማማው የሥጋን ሕመምና
መከራ እንደጸጋ ቆጥረውና ተቀብለው ለሚታገሡት ነው። የምሥጢረ ቀንዲልም ዋናው
ትኩረት የሥጋ ፈውስ መስጠት አለመስጠት ላይ ሳይሆን ሕመምተኛው ፈውሰ ሥጋ
እንኳን ባያገኝ በሽታውን በአኮቴት /በትዕግሥትና በምስጋና/ ተቀብሎ ከነፍስ ሕማምና
ከሥጋ ሞት እንዲድን ማድረግ ላይ ነው ።
ማጠቃለያ
የዚህ ዓለም መንግሥታት ለሚያስተዳድሩት ሕዝብ ይበጃል ያሉትን ሁሉ ከማድረግ
ወደ ኋላ አይሉም፡፡ ለምሳሌ የሕዝቡን ጤና በተመለከተ በርካታ የጤና ተቋማት በየጊዜው
እየገነቡ አገልግሎታቸውን የተሟላ ለማድረግ ሲጣጣሩ ይታያል:: የፀጋው ግምጃ ቤት
የሆነች ቤተ ክርስቲያንም የምእመናንን አጠቃላይ ምድራዊ ኑሮ የምታስተናግድባቸው
የምትመራባቸውና የምታስተዳድርባቸው የጠሩና የበቁ ምሥጢራት አሏት፡፡ ከነዚህ ውስጥ
አንዱ ምሥጢረ ቀንዲል ሲሆን ይህም ከላይ እንደተገለጸው ቤተክርስቲያን የምእመናንን
ሥጋዊና መንፈሳዊ ጤንነት የምትጠብቅበት የተቀደሰ መንገድ ነው:: ይህን ምሥጢር
በተሟላ ሁኔታ በአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ተደራሽ እንዲሆን (እንዲሰጥ) ማድረግ
ይገባል:: ይሁን እንጂ ይህ ሲተገበር አይታይም ቤተ ክርስቲያን ከዓለማውያኑ የዚህ ዓለም
መንግሥታት ታንሳለችን? አታንስም፤ ትበልጣለች እንጂ፡፡ ይህ ከሆነ ደግሞ ታላቅነቷንና
ብልጫዋን እንደቀድሞው አገልግሎቷን የተሟላ በማድረግ ማሳየት ይጠበቅባታል፡፡ ለዚህም
የተለየ ክፍልን ብቻ ተጠያቂ ሳናደርግና ሳንጠብቅ ሁላችንም በጋራ በመንቀሳቀስ ይህን
ምሥጢር በታዘዘው መሠረት እውን ለማድረግ መነሣት አለብን::
ዋቢ መጻሕፍት
• ማ/ቅ፤ ትምህርተ ሃይማኖት ርትዕት፤ ማኀበረ ቅዱሳን፤ ፲፱፻፺፫፤
አ/አ።
127
• የኢት/ኦ/ተ/ቤ/ክ፤ ፍትሐ ነገሥት ንባብና ትርጓሜው፤ ትንሣኤ
ማሳተሚያ ድርጅት፤ ፲፱፻፺፤ አ/አ።
128
ምዕራፍ አሥር
በዓላት
ከተማሪዎች የሚጠበቅ አጠቃላይ ውጤት ተማሪዎች ይህን ምዕራፍ ካጠናቀቁ በኋላ ፦
በብሉይ ኪዳን ይከበሩ የነበሩ በዓላትን የአከባበር ሥርዓት በዝርዝር ሳይሆን በጥቅል
በማየት እንጀምራለን። በዚህ ዘመን በዐላት እንዲከበሩ ያዘዘው እግዚአብሔር ሲሆን
ለያንዳንዱ ክብረ በዓል የአከባበር ሥርዓቱንም ደንግጎ ሰጥቷል። ዋና ዋናዎቹ
ትእዛዛትም ተግባረ ሥጋን መተው (ዘሌ፳፫፥፫‐፴‐፴፪፡፡) ተገቢ መሥዋዕት ማቅረብ
(ዘኁ ፳፰፥፩-ፍጻሜው፡፡) በተለይ በሦስቱ ዐበይት በዓላት (የቂጣ፣ የመከር፣ የአዝርዕት
132
መክተቻ (የዳስ በዓል) ወደ ቤተ መቅደስ መውጣትና በዚያም ባዶ እጅ አለመታየት
(ዘጸ፳፫፥፲፬‐፲፰፡፡ ዘዳ፲፮፥፲፮‐፲፰፡፡) ምስጋና ማቅረብ (፩ኛ ዜና መዋ ፲፮፥፩‐፴፯፡፡
መዝ ፹፥፩‐፭፡፡) እና የመሳሰሉት ናቸው።
• ሐሜት፣ ዋዛ ፈዛዛ፣
133
• ክርስቲያናዊውን ባህል ማጣጣልና የመሳሰሉት ሁሉ
የማይገቡ ናቸውና ክርስቲያኖች ከነዚህ መራቅ
ይኖርባቸዋል።
ዋዜማ
ዋዜማ ሁለት ተያያዥ የሆኑ ፍቺዎች አሉት::
፩.በቁሙ፤ መጀመሪያ ዜማ፤ ከበዓሉ በፊት ማታውን የሚዜምና የሚመራ መዝሙር፤ ቅኔ።
፪.ድራር፤ ንዑስ በዓል፤ ማኅትው የሚቆምበት፤ ዋዜማ የሚመራበት ቀን፤ (ማኅትው የነግህ
መዝሙር ነው። (ኪ.ወ.ክ. ገጽ፬፻፲፰፡፡)
በዕለቱ
ከላይ ለመግለጽ እንደሞከርነው የበዓላቱ አከባበር እንደየበዓላቱ ዓይነት ልዩ ልዩ ነው።
ለዋዜማው የሚቀርበውን ስብሐተ እግዚአብሔር ለሁሉም በጋራ የሚደረስና እንደ በዓሉ
ሁኔታ ልዩ ልዩ የምስጋና ስልትና ሥርዓት እንዳለው ባየነው መሰረት ማለት ነው።
ሥርዓተ በዓላትን በጥቅሉ ስናያቸው በዕለቱ ያላቸውን አከባበር በሁለት ከፍለን ማየት
እንችላለን ።
፲.፬. ዋና ዋና በዓላት
135
ክቡር አንባቢ ሆይ፦
ይህንን ርእሰ ጉዳይ በዝርዝር ከማየታችን በፊት የሚከተለውን ጥያቄ ለመመለስ ይሞክሩ።
2.ብርሃን
3.ኖላዊ
4.በዓለጌና
5.ግዝረት
6.ልደተ ስምኦን
7. ቃና ዘገሊላ
8. ደብረ ዘይት
9.መስቀል
136
ለ.የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም በዓላት
እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ እመቤታችን ቅድስት
ድንግል ማርያም ፴፫ ዓመታዊና ወርኃዊ በዓላት አሏት።(መቅድመ ተአምረ ማርያም፡፡)
በዚህ ጽሑፍ ከነዚህ በዓላት መካከል ዋና ዋና የሚባሉ አምስቱን ብቻ እንዘረዝራቸዋለን ።
2. ዕረፍቷ፡- ጥር ፳፩ ቀን፤
ከነዚህ በዓላት በተጨማሪ ለሁሉም ክርስቲያን የጋራ የሆኑ የግዝት በዓላት አሉ።እነዚህም
ከእመቤታችን በተጨማሪ ወር በገባ በ፲፪ የቅዱስ ሚካኤልና በ፳፱ የጌታችን የኢየሱስ
ክርስቶስ ልደት መታሰቢያ ናቸው:: በየአጥቢያዎቹ የሚከበሩ ልዩ ልዩ ተጨማሪ በዓላትም
አሉ።እነዚህ ግን በአጥቢያው ካህናትና ምእመናን ደረጃ ብቻ የተወሰኑ ናቸው። ከነዚህ
ውጪ የሆኑት በዓላት ሁሉ ምእመናን በግላቸው (በፈቃዳቸው) ከተደረገላቸው ድንቅ ሥራ
ተነሥተው በፍቅርና በፍላጎት የሚፈጽሙት መሆኑ መታወቅ አለበት:: እነዚህን
ቤተክርሰቲያናችን ምእመናን በግድ እንዲያከብሯቸው ያላዘዘቻቸው (በግዝት
ያልሠራቻቸው) ናቸው።
ዑደት ታቦተ እግዚአብሔር እንደ ዕለቱ በዓል ማንነት ከመንበረ ክብሩ እየተነሣ በታላቅ
ክብርና ምስጋና ቤተ መቅደሱን የሚዞርበት እግዚአብሔርም ህዝቡን የሚባርክበት ሥርዓት
ነው። በዑደቱ ጊዜም ከልሂቅ እስከደቂቅ የተማረ ያልተማረ ሳይባል ሁሉም እንደ ችሎታው
እግዚአብሔርንና መታሰቢያ የተደረገለትን ቅዱስ ያመሰግናል::በዓላትን በዑደት የማክበር
መሠረታዊ ዓላማውም ምእመናን በቅዱሳን አማካኝነት የሚታደለውን በረከተ እግዚአብሔር
እንዲያገኙና ለመንግሥተ እግዚአብሔር የሚያበቃቸውን ቃለ እግዚአብሔር እንዲማሩ
ለንስሐም እንዲዘጋጁ ማድረግ ነው።ቤተ ክርስቲያኑን ሦስት ጊዜ በመዞርም ምሥጢረ
137
ሥላሴን ይሰብካሉ ሦስት ጊዜ መሆኑ የሦስትነት ግብሩ (ድርጊቱ) አንድ ዓይነት መሆኑ
(አለመለወጡ) ያንድነት ምሳሌ ሆኖ ይመሠጠራልና።አፈጻጸሙም ቀደም ብለን ባጭሩ
በገለጽነው መሠረት ይሆናል።
ጥምቀት (ኤጲፋንያ)
በኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓት መሠረት እንደ ደመራ
(መስቀል) በዓል ሁሉ በዓለ ጥምቀትም የአደባባይ በዓል ነው:: በሁለቱ መካከል ያለው
ልዩነት የአከባበሩ ሥርዓት ልዩ ልዩ ውበት ያለው መሆኑና በደመራ በዓል ካህናቱ ይዘው
የሚወጡት መስቀል ሲሆን በጥምቀት (ኤጲፋንያ) ደግሞ ወደ ጥምቀተ ባሕር ይዘው
የሚወርዱት በየአጥቢያው የሚገኙ ታቦታትን መሆኑ ነው። መስቀል ወደ አደባባይ
የሚወጣው በበዓሉ ዋዜማ በደመራው ዕለት ከሰዓት በኋላ እንደሆነ ሁሉ ታቦታቱም
ከመንበረ ክብራቸው ወጥተው ወደ ባሕረ ጥምቀት የሚወርዱት በበዓሉ ዋዜማ በከተራ
ነው:: ሌላው የሚያመሳስላቸው ነጥብ ደግሞ ሁለቱም በዓላት የሚከበሩት እንደ ሌሎቹ
የጌታ በዓላት ሁሉ የእግዚአብሔርን የማዳን ሥራ ለመመስከር መሆኑ ነው።
ምእመናን በታላቅ ጉጉት ከሚጠብቋቸው በዓላት አንዱ በሆነው በዚህ በዓል ታቦታቱ
በምስጋና፣ በዕልልታ፣ በሆታ ታጅበው ወደ ባሕረ ጥምቀት ይወርዳሉ:: አስቀድሞ በባሕረ
ጥምቀቱ እንደ አካባቢው ተጨባጭ ሁኔታ ዳስ ተጥሎ ወይም ድንኳን ተተክሎ እና ከተራ
ተከትሮ /ውሃ ተገድቦ/ ይጠብቃል። ታቦታቱ ከዛ ሲደርሱ ቀሪው የምስጋናና የልመና
(የምህላ) ሥርዓት ይፈጸማል። በመቀጠልም በተዘጋጀው ጊዜያዊ ማረፊያ (መቅደስ)
ታቦታቱና ንዋያተ ቅድሳቱ እንዲገቡ ይደረጋል። ይህ ዕለትና ቦታ በዓመት ውስጥ
ቤተክርስቲያን ከመደበኛው ቦታዋ ውጪ ሥርዓተ ቅዳሴ የምታከናውነበትና ምሥጢራትን
የምታድልበት ብቸኛና ልዩ ዕለትና ቦታ ነው።
ልዩ የዑደት ሥርዓት
በአክሱም ጽዮን ማርያም ከጥንት ጀምሮ የነበረና አሁንም ያለ ልዩ የዑደት ሥርዓት እዚህ
ላይ መጠቀስ ይኖርበታል ብለን እናምናለን:: ይሀ ሥርዓተ ዑደት የሚከናወነው በየወሩ ለ፯
ተከታታይ ቀናት ከመባቻ (፩) እስከ ሥላሴ (፯) ድረስ ነው። ከሌሊቱ ፲፩ ሰዓት ጀምሮ
የአክሱም ከተማ ካህናትና ምእመናን በብዛት ወጥተው ጧፋ እያበሩ ታቦተ እግዚአብሔርን
የሚያከብሩበትና የሚባረኩበት ልዩ የዑደት ሥርዓት ነው። ከመቅደሱ የወጣው ታቦትም
በካህናቱ ከብሮ የከተማውን እምብርትና ዋነኛ ክፍል እየባረከ ዞሮ የሚመለስበት በየወሩ
138
ለ፯ ቀናት የሚከናወን አስደሳች ሥርዓት ነው። የዑደቱ መሠረታዊ ዓላማ እመቤታችንን
ድንግል ማርያምንና በእሷም በኩል እግዚአብሔርን በምህላ (እግዚኦታ) መማፀን ነው።
በግራና በቀኝ እየተቀባበሉ (እያስተዛዘሉ) ከተለመደው አደባባይ ደርሰው ምህላውን በልዩ
ልዩ ጸሎታት አጠናክረው በአቡነ ዘበሰማያት ያሳርጋሉ። በዚያም ትምህርተ ወንጌል
ተሰጥቶ በታላቅ ክብር ወደ ቤተክርስቲያን ይጓዛል። ቀሪውን ዑደት በቤተ ክርስቲያኒቱ
ዙሪያ ከፈጸሙ በኋላም ታቦቱ ወደ መንበረ ክብሩ ይመለሳል:: ይህም ከላይ እንደገለጽነው
በአክሱም ጽዮን ከዓመት ዓመት የማይታጎል (የማይቋረጥ) ሥርዓተ ዑደት ከጥንት ጀምሮ
የነበርና ዛሬም በመፈጸም ላይ ያለ ክርስቲያናዊ ዕሴትና ሥርዓተ አምልኮ ነው። አንዳንድ
ገዳማትና አድባራትም ይህን ትውፊት ይዘው ታቦት አውጥተው ዑደት ባያደርጉም በየወሩ
ለ፯ ቀናት ምህላ ያደርጋሉ።
ለዚህ ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት እንዲቻል ባንድ ወቅት አክሱማውያን “እኛ የዓለም
ቅርስ ጠባቂዎች ነን።” ያሉትን መነሻ ማድረግ ይኖርብናል። አዎ በእውነቱ ከሆነ
አክሱማውያን ዓለም በመላው ዓይኑን አቅንቶ ጆሮውን ከፍቶና ልቡን አጓጉቶ
የሚጠብቃትን ታቦተ ጽዮንን ከሙሉ ታሪኳና ሥርዓቷ ጋር እየጠበቁ ያሉ ቀናዕያን
ክርስቲያኖች ናቸው። በሌላ አነጋገር እነሱ የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ መንፈሳዊ
ቅርሶች ባለቤቶች ብቻ ሳይሆኑ ተገቢውን ክብር በመስጠት ከእግዚአብሔር ጋር
የኖሩና የሚኖሩም ናቸው። እነሱ የቤተ ክርስቲያንና የእግዚአብሔር አደራ
ተቀባዮች፣ ተንከባካቢዎች፣ ጠባቂዎችና ለተተኪው ትውልድ አስተላላፊዎች ናቸው።
ከነዚህ ከተቀበሏቸውና ከጠበቋቸው ቅርሶችና ዕሴቶች መካከልም አንዱ ከላይ
የገለጽነው ሥርዓተ ዑደት ነው።
ሀ.መንፈሳዊ ጠቀሜታዎች
139
• ከበዓሉ ባለቤት (ከቅዱሱ፣ ከቅድስቷ) የቃል ኪዳን በረከትና ረድኤት ለማግኘት፤
/መዘ ፻፲፩፥፮። ምሳ፲፥፯፡፡/
ለ.ማኀበራዊ ጠቀሜታዎች
• የሀገርና የዜጎችን መልካም ገጽታ ለመጠበቅና ለማዳበር፤
140
• በብዙ ወጪና ድካም ከበዓሉ ቦታ ደርሰው ቅዳሴ ሳያስቀድሱና ሥጋ ወደሙ
ሳይቀበሉ የሚመለሱ “እግረኛ ምእመናን” በብዛት መታየታቸው፤
ማጠቃለያ
ከቀረበው ማብራሪያ ቅዱሳት በዓላትን በተመለከተ በቂ ማብራሪያ እንዳገኙ እምነታችን
ነው፡፡ አንዳንዶች እንደሚመስላቸው የድህነት መንስኤ ሳይሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎች
ያሉት መሆኑን ለማሳየት ተሞክ…ል፡፡ ከምንም በላይ ሰው ሠራሽ ሳይሆኑ እግዚአብሔር
ፈቅዶ የሠራልን ለመሆናቸው በሰፊው መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ ያላቸው የማይዳሰሱ
መንፈሳዊ ቅርሶች ናቸው፡፡ በቅዱሳት በዓላት ስንፍናቸውን ለመሸፈን በዓል አክባሪ
መስለው ሥራ ፈተው የሚውሉ አንዳንድ ግለሰቦች ቢኖሩ (ካሉ) የግላቸው የግንዛቤ ችግር
ከመሆን አልፎ ቤተ ክርስቲያንን አያስጠይቅም፡፡ ቤተ ክርስቲያን የምትጠየቀው ልጆቿን
ካላስተማረች ብቻ ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን እያስተማረች ምእመናን በራሳቸው መንገድ
እየተÕዙ በዓላትን የስንፍና መሸሸጊያ ካደረጉ ደግሞ ተጠያቂዎቹ እነሱው ስለሆኑ
በፈጣሪያቸው ዘንድም የሚቀጡ ይሆናሉ:: በቤተ ክርስቲያን ትምህርት መሠረት በዓላትን
በአግባቡና በሥርዓቱ የሚያከብሩት ደግሞ ዋጋ የሚያገኙበትና የሚከበሩበት ይሆናል::
ዋቢ መጻሕፍት፦
141
• የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ፤ መጽሐፍ ቅዱስ፤ የኢትዮጲያ መጽሐፍ ቅዱስ
ማኀበር፤ ፳፻፤ አ/አ።
142
ምዕራፍ ፲፩
ሕንጻ ቤተክርስቲያንና ንዋያተ ቅድሳት
መግቢያ
በዚህ መጽሐፍ የመጀመሪያው ምዕራፍ ላይ ስለ ቤተ ክርስቲያን በቂ መረጃ
ማግኘት የሚያስችል ጽሑፍ ማቅረባችን ይታወሳል በዚህኛው ምዕራፍ የምናየው
የዚያኛውን አሳብ በመድገም ሳይሆን ቀጣይ የሆኑ ጉዳዮችን በማንሳት ይሆናል
ከላይ በጠቀስነው ዋና ርእስ ሥር
143
ከተማሪዎች የሚጠበቅ አጠቃላይ ውጤት፦
ተማሪዎች ይህን ትምህርት /ምዕራፍ/ ካጠናቀቁ በኋላ፦
145
ቤተክርስቲያን ዙሪያዋ ክብ ሆኖ (ሙሉ ክብ ወይም ማዕዘናማ ክብ) ባለ አንድ
ጉልላት ናት። በፊልጵስዩስ ከተማ ሰኔ ሃያ ቀን በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ድንቅ
ተአምር በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ስም የተመሠረተችው
የመጀመሪያዋ ቤተክርስቲያን ክብ ቅርጽ እንደነበራት የቤተክርስቲያን ታሪክ
ያስረዳል። ይህች ቤተ ክርስቲያን በተሠራች ማግስት ሰኔ ሃያ አንድ ቀን በጌታችን
ኢየሱስ ክርስቶስ የከበረች መሆኗም ይታወቃል:: በቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ
መሠረት የቤተክርስቲያን ክብነት ፍጹምነቷን የሚያመለክት ነው። ይህ ማለትም
የእምነቷን፣ የአስተምህሮዋን፣ የሕጓን፣ የሥርዓቷንና የአገልግሎቷን ፍጹምነትና
ልጆቿን ለፍጹምነት ማዕረግ የምታበቃ መሆኗን የሚያመለክት ነው። ይህችኛዋ ቤተ
ክርስቲያን ሦስት ክፍሎችና ሦስት በሮች ያላት ስትሆን ሦስቱን የመላእክት ዓለም
(ኢዮር፤ ራማ፤ ኤረር)፣ ሦስቱን መዐርጋተ ክህነት (ጳጳስ፤ ቄስ፤ ዲያቆን)፣ ሦስቱን
ጾታ ምእመናን (ካህን፤ ወንድ፤ ሴት) እና ሦስቱን የገነት በሮች የሚያመለክቱ
አማንያን (እውነተኛ) ምሳሌዎች ናቸው።
፪. ሰቀላማ ወይም ሞላላ ቅርጽ፦ ይህኛው ቤተክርስቲያን አራት ማዕዘን ቅርጽ ያለው፣
ሞላላ የሆነና ከፍ ብሎ የሚታነፅ ነው። ይህ ዓይነቱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በአሁኑ ጊዜ
በተለይ በከተሞች በከፍተኛ ደረጃ በመስፋፋት ላይ ያለ ሲሆን አሠራሩም የተወሰደው
ንጉሥ ሰሎሞን ካሠራው ቤተ መቅደስ ነው። ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ይህን ዓይነቱን
የቤተ መቅደስ አሠራር ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ
የፈጸመውን የድኅነት ሥራ የሚያዘክር ነው ይላሉ። አሠራሩን ብዙ ጊዜ መሠረቱን
በመስቀል ቅርጽ አውጥተው ግድግዳውንም በዚያው ላይ በመገንባት መስቀልኛ
ቤተክርስቲያን የሚያደርጉት ለዚህ ነው። ይህ ዓይነቱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን ከ፩ በላይ
ጉልላትና ከሦስት በላይ በሮች ይኖሩታል። ውስጣዊ ክፍሎቹ የሚከፋፈሉት ደግሞ
በመጋረጃ ይሆናል።
146
፫. ዋሻ ቅርጽ፦ ከዓላውያን ነገሥታት ስቃይና መከራ ለማምለጥ በየዘመኑ የተነሡ
ክርስቲያኖች በየዋሻውና በየፍርኩታው ይሸሸጉ ነበር፡፡ በዚያን ዘመን አምልኮአቸው
እንዳይቋረጥ በየዋሻው ይማማሩና መሥዋት ይሠው ነበር:: በዚህ ሁኔታ የተጀመረው
የዋሻ ቤተክርስቲያን ምንም ጉልላት የለውም:: እንደ ሰቀላማው የቤተክርስቲያን ቅርፅ
ሦስቱ የቤተ ክርስቲያን ክፍሎች የሚለዩት በመጋረጃ ነው፡፡ አንዳንድ ተፈጥሮአዊ
የዋሻ አብያተ ክርስቲያናት ቢኖሩም በሀገራችን በብዛት ተመዝግበው የሚገኙት በእነ
ቅዱስ ላሊበላ የተሠሩ ሰው ሠራሽ (ፍልፍል) የዋሻ አብያተ ክርስቲያናት ናቸው።
ሐ. የቤተክርስቲያን ሥሪት
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለአምልኮተ እግዚአብሔር
የምትገለገልባቸው አብያተ ክርስቲያናት ሥሪት በሦስት ምድብ /ክፍል/ የታወቁ
ናቸው። እነርሱም፦
፩. ገዳም
ገዳም የታላቁን ነቢይ የኤልያስንና (፩ነገ.፲፯፥፩‐፰፡፡) የመጥምቁ የቅዱስ ዮሐንስን
(ማቴ፫፥፬፡፡) አኗኗርና ሕይወት አርአያ አድርገው የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ፍለጋ
(ማቴ፬፥፩‐፲፪፡፡) የተከተሉ መናንያን መነኮሳት የሚጋደሉበት የተቀደሰ ቦታ ነው።
ትምህርተ ክርስቶስን መሠረት አድርገው (ማቴ፲፥፴፯‐፵፡፡) እንደ ሐዋርያት
(ማቴ፲፱፥፳፯‐ፍጻሜው፡፡) ሁሉን ትተው የተከተሉት እነዚህ መናንያን መነኮሳት በጾም፣
በጸሎት፣ በስግደትና በልዩ ልዩ ተጋድሎ ጸንተውና ከዓለም ርቀው ይኖሩበታል። በገዳም
የሚኖሩት መነኮሳትና መነኮሳይያት እንዲሁም በአመክሮ ላይ ያሉ ጥቁር ራሶች ብቻ
ናቸው:: መናንያን ከፈተና ይጠበቁ ዘንድ የወንዶችና የሴቶች ገዳም ብዙውን ጊዜ
የተለያየ ነው:: አንዳንድ ገዳማት ብቻ ሁለቱንም ጾታዎች በአንድነት የያዙ ሆነው
ይገኛሉ::
147
የአበምኔቱ ረዳቶች አፈመምህር፣ መጋቢ፣ እጓል መጋቢ፣ ሊቀ ረድእ፣ ሊቀ ዲያቆን
…ወዘተ በመባል ይጠራሉ። ገዳማውያን መነኮሳት/ይያት/ በማኅበር እየሠሩ፣ እየጸለዩ፣
እየተመገቡ፣ አንድ ዓይነት ልብስ እየለበሱ ወዘተ በመኖር የሚጋደሉ ናቸው። ቤተ
ክርስቲያን ልዩ ለሆነ አገልግሎት ካልጠራቻቸው ወይም ገዳሙ ለተለየ ተልዕኮ፣
ለተወሰነ ጊዜ ካላካቸው በስተቀር መነኮሳት በአታቸውን ጥለው ከገዳማቸው እንዲወጡ
አይፈቀድላቸውም። እነርሱም ይህ የምናኔ ዓላማ ገብቷቸውና ፈቅደው ስለሚመነኩሱ
በአታቸውን ጥለው ለመውጣት አይፈልጉም። በ፪ኛው መቶ ክ/ዘመን አባ ጳኩሚስ
ባዘጋጁት ሥርዓተ ምንኩስና /ገዳም/ መሠረት በመጋደል የሚኖሩ መናንያነ ዓለም
ናቸውና።
፪. ደብር፦
ደብር ከፍ ያለ ቦታ፥ ተራራ፥ ኮረብታ ማለት ነው። ከጥንት ጀምሮ እግዚአብሔር ብዙ
ጊዜ በተራራ ላይ ራሱንና ምሥጢራቱን ለወደዳቸውና ለመረጣቸው ሰዎች ይገልጥ
ነበር። (ዘጸ፲፱፥፩‐ፍጻሜው፤ ፳፬፥፩-ፍጻሜው። ማቴ፲፯፥፩‐፲፤ ፳፬፥፫፡፡) ተራራ
በቅዱሳን አበውና እማት፣ በጻድቃን በሰማዕታትም ሁሉ ይመሰላል። የእመቤታችንን
የዘር ግንድ (ሐረግ) በተመለከተ ነቢዩ ዳዊት ሲናገር “መሠረቶችዋ በተቀደሱ ተራሮች
ናቸው፡፡” (መዝ፹፮፥፩፡፡) በማለት የተናገረው ለዚህ በቂ ማሳያ ነው። ጌታችንም ከላይ
እንዳየነው በተራራ ላይ ይጸልይ፤ ክብሩን ይገልጥና ምሥጢራትን ለደቀ መዛሙርቱ
ይነግር ነበር። ይህንና ይህን ከመሳሰሉት መነሻዎች አኳያ ቤተ ክርስቲያን አንደኛውን
ሥሪት ደብር ብላ ጠርታዋለች።
፫. ገጠር
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በኢየሩሳሌም ዙሪያና በፍልስጥኤም ባሉ ገጠሮችና
መንደሮችም እየተዘዋወረ ያስተምር ነበር። ከነዚህም መንደሮች የተውጣጣ ፭ ገበያ
ያህል ሕዝብ ይከተለው ነበር። (ማቴ፲፬፥፲፫‐፳፪፡፡) ሐዋርያትንና ሰባ ሁለቱን
አርድዕትም የመንግሥትን ወንጌል ያስተምሩና ድውያኑን ሁሉ ይፈውሱ ዘንድ በምድረ
148
እስራኤል ሁሉ ልኳቸዋል። (ማቴ ፲፥፭‐፯፡፡) (ሉቃ፲፥፩፡፡) ይህንን መሠረት በማድረግ
ወንጌልን ለዓለም ሕዝብ ሁሉ ለማድረስና ምሥጢራትንም በመፈጸም አማንያንን
የሥላሴ ልጆች ለማድረግ ይቻል ዘንድ በየገጠሩ ሁሉ ቤተ ክርስቲያን ታንጿል፤
ይታነፃልም። እንዲህ ያለችው ቤተ ክርስቲያን “ገጠር” የሚል መጠሪያ ተሰጥቷታል።
149
የተለዩ ናቸው። ምክንያቱም የቆሙለት ውክልና /የሚወክሉት አካል/ ቅዱስ በመሆኑና ስለ
እግዚአብሔር የሚመሰክሩ የረቀቁ መምህራን በመሆናቸው ነው።
ከዚህ በላይ የጠቀስናቸው ማስረጃዎች የሚያሳዩት በብሉይ ኪዳን ዘመን በደብተራ ኦሪትም
ሆነ በመቅደሰ ሰሎሞን ሥዕለ ኪሩብ በየመጋረጃው ላይ ሳይቀር ይጠለፍ ይቀረጽ እንደነበር
ነው። በዚህ መልክ ለአምልኮተ እግዚአብሔር ከፍተኛ ጠቀሜታ እየሰጡ ከዘመናችን
ደርሰዋል። በሐዲስ ኪዳንም ቅዱሳት ሥዕላት በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት በስፋትና
በብዛት ለአምልኮተ እግዚአብሔር መግለጫ እንዲሆኑ ተደርገዋል። በቤተ ክርስቲያን ታሪክ
እንደተገለጸው ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ለሮሙ ንጉሥ ለጢባርዮስ ቄሳር የጌታችንን ሥነ-
ስቅለት ሥሎ እንደሰጠውና እንደተጽናናበት ታውቋል። ቅዱስ ሉቃስ ወንጌላዊ ደግሞ
“ምስለ ፍቁር ወልዳ” በመባል የሚታወቀውን የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማርያምን
ሥዕለ አድኅኖ በመሣል ለሐዲስ ኪዳን የቅዱሳት ሥዕላት አገልግሎት ፈር ቀዳጆች
ለመሆን እንደቻሉ ታውቋል።
150
ከሁሉ የሚቀድመውና ለቅዱሳት ሥዕላት አሣሳል የመድኃኔዓለም ፈቃድ ተደርጎ ሊወሰድ
የሚችለው ክርስቶስ በመከራው ሰዓት በድንቅ ተአምር በጨርቅ ላይ ያተመው ሥዕል ነው።
ይህም ያገለግሉትና ይከተሉት ከነበሩት ደናግል (ቅዱሳት አንስት) አንዷ ቤሮኒካ ከራሱ
የሚወርደው ደሙ ፊቱን ቢሸፍነው እንዲጠርግበት በሰጠችው የሐር ጨርቅ (መሐረም) ላይ
ፊቱን በጠረገበት ጊዜ የታተመው ሙሉ የፊቱን ገጽታ የሚያሳየው ሥዕል ነው። “ቅዱሱ
ፊት” በመባል የሚታወቀው ይህ ሥዕል የሰው እጅ የሠራው አይደለም። በሌላ ታሪክም
የኤዴሳው ንጉሥ አብጋር ታሞ ሳለ ጌታችን መጥቶ እንዲፈውሰው መልእክተኛ ቢልክ
ጌታችን በሐር ጨርቅ የፊቱን መልክ አትሞ (በተአምር ሥሎ) የላከለት እንደሆነ
ሊቃውንት ያስተምራሉ፡፡ ፲፪ ዓመት ደም ሲፈሳት የነበረችው ሴት (ማር.፭፥፳፭‐፴፭፡፡)
ከተፈወሰች በኋላ ለጌታ ውለታ መታሰቢያ እንዲሆንላት በግቢዋ ያቆመችው ከነሐስ
የተሠራ ሥዕልም ሌላው ማረጋገጫ እንደሆነ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ጸሐፊያን ገልጸዋል።
ለ.መልክእ
• በሥዕሉ ባለቤት አናት /ራስ/ ዙሪያ አክሊለ ብርሃን ይደረጋል። ይህም ሰማያዊ
ክብራቸውን ያሳያል፡፡ (ሠራዊተ መላእክት በብዛት ሲሣሉ ላይደረግ ይችላል።)
151
• ዐይናቸው የጎላና ወደ አንድ አቅጣጫ የሚመለከት ይሆናል። ይህም የጎላች፣
የተረዳች ርትዕት (ቀጥተኛ) የክርስትና ሃይማኖትን ያለ ጥርጥር መቀበላቸውንና
ማቀበላቸውን ያመለክታል።
ሐ.ቀለም
በቤተ ክርስቲያናችን የሥዕል አሣሣል ጥበብ መሠረት ቅዱሳት ሥዕላትን ለመሣል ጥቅም
ላይ የሚውሉ /የሚታዩ/ ቀለማት በአብዛኛው የሚከተሉት ናቸው::
152
• ለማስታወስ አንድ ወቅት የተከናወነው ክርስቲያናዊው ክስተት ከምእመናን ልቡና
እንዳይጠፋና በወቅቱ ያሉ ያህል ሆኖ እንዲሰማቸው ለማድረግ ቅዱሳት ሥዕላት
ከፍተኛውን ሚና ሲጫወቱ ኖረዋል፤ ይኖራሉ።
153
፲፩.፫ ንዋየ ቅድሳት
የተከበሩ አንባቢ ሆይ፡-
154
፪.ጉበን ወይም ደረጃ
ምሳሌነቱ፦
፭.ዕፅዋት፦
፮.ማገር፦
ምሳሌነቱ፦
ምሳሌነቱ፦
ምሳሌነታቸው ፦
፱.ጉልላት
ምሳሌነቱ፦
ምሳሌነታቸው፦
ይህ አሁን ከችግር አኳያ እየቀረ የመጣ ቢሆንም በጥንታውያኑና ገጠራማ አካባቢ በሚገኙ
አብያተ ክርስቲያናት የተለመደ ነው:: በጉልላቱ ላይ በሚቆመው መስቀል ዙሪያ የሰጎን
እንቁላል ይደረጋል።
156
እግዚአብሔርም ፍጥረቱን የማይረሳ በጸጋውና በረድኤቱ ከፍጥረቱ የማይለይ መሆኑን
ያመለክታል። እንቁላሉ በእግዚአብሔርና በምእመናን መካከል ያለውን የጠበቀ ግንኙነት
ያስረዳል /፪ዜና ፯፥፲፮፡፡ ኢሳ፵፱፥፲፭፡፡/
ሰጎኗ ዓይኗን ለአፍታም ያህል እንኳን ካነሳች፥ እንቁላሉ ይለወጣል፤ ማለትም ይበላሻል፤
አይፈለፈልም:: እንደዚሁም እግዚአብሔር መግቦቱንና ጠብቆቱን /ረድኤቱን/ ለአፍታም
ያህል ቢያቋርጥ ምእመናን /የሰው ልጆች/ ሕይወት አይኖራቸውም:: አንድም ታሪኩ
ምእመናን እንደ ሰጎን ዓይነ ልቦናቸውን ወደ እግዚአብሔር፣ ወደ ቤተክርስቲያን፣ ወደ
መስቀሉ፣ ወደ እመቤታችን፣ ወደ ቅዱሳኑ ሁሉ እንዲያደርጉ ይጋብዛል። ዓይነ ልቡናቸውን
ከእግዚአብሔር፣ ከቤተ ክርስቲያን፣ ከቅዱስ መስቀሉ፣ ከእመቤታችን፣ ከቅዱሳኑ ሁሉ ላይ
ካነሡ /ከነቀሉ/ መንፈሳዊ ሕይወታቸው እንደሚበላሽ ፍጻሜያቸውም እንደማያምር
ያሳያል። /ዮሐ ፲፱፥፳፭‐፳፰፡፡/
፲፫. ቤተልሔም
፲፬. ቤተ ምርፋቅ
157
ቃጭል /መረዋ/ ደግሞ ከውስጥ በቅዳሴ ሰዓት በመናበብ /አንዱ አንዱን በመከተል/
አገልግሎት ይሰጣሉ።
ምሳሌነቱ፦
ምሳሌነቱ፦
158
1. በቤተ ክርስቲያን የቅዳሴ አገልግሎት ገባሬ ሠናይ ካህን ቄሱ “ከደማችሁ ንጹሕ ነኝ!”
እያለ መናጻቱ ጲላጦስ ክርስቶስ ከመሰቀሉ በፊት “እኔ ከዚህ ጻድቅ ሰው ደም ንጹህ ነኝ!”
በማለት ለመናገሩ ምሳሌ ነው::
መ. ጽንሐሕ፦ ይህ የዕጣን ማጠኛ ቅዱስ ንዋይ ነው። በብሉይ ኪዳንም በአሠራር ደረጃ
ልዩነት ቢኖረውም የዕጣን መሠዊያ ከማይነቅዝ ዕንጨት ተሠርቶ በወርቅ ተለብጦ
አገልግሎት ይሰጥ ነበር። /ዘጸ፴፥፩‐፲፩፤ ፴፯፥፳፭‐፳፱፡፡/
• ፍሕም፦ የመለኮት፤
159
ምሳሌነቱ ፦
• ሙዳዩ የእመቤታችን፤
• ዕጣን የጌታ፤
• ካህኑ ከቅዳሴ በፊት መርጦ የሚያስቀምጠው ፭ ቆቀር /ፍሬ/ ዕጣን:- የ፭ቱ ኪዳናት
ማለትም የቁርባነ አቤል፣ የመሥዋዕተ ኖኅ፣ የኂሩተ አብርሃም፣ የመብዐ ይስሐቅ፣
የተልእኮተ ሙሴ ወአሮን ምሳሌ ነው፡፡ (መጽሐፈ ቅዳሴ ገጽ ፴፪ ቁጥር ፳፩ እና
ገጽ ፮ ቁጥር ፵፩-፵፫፡፡)
በሌላ በኩል ደግሞ ሌላው እንደላይኛው ሆኖ ኤልያስ ለምእመናን ምሳሌ ይሆናል። (፩ነገ
፲፱፥፬‐፱፡፡ ቅዳሴ ማርያም፡፡)
ምሳሌነቱ፦ የእመቤታችን፤
ምሳሌነቱ ፦
- ዐውዱ፦ የቤተልሔም
- ዐውዱ ላይ የሚነጠፈው ማኅፈድ:- እመቤታችን ጌታን በወለደች ጊዜ ያለበሰችው
ቈጽለ በለስ፤
- ጻሕል፦ ጌታ የተወለደበት የከብቶች በረት፤
:- የእመቤታችን የሰውነቷ፤
አንድም፦
ዐውድ፦ የጎልጎታ
161
የታችኛው ማኀፈድ፦ የመግነዝ፤
• ተቅዋም፦ የእመቤታችን፤
አ. ደወል /መጥቅዕ/
ሀ. የተጋብኦ ደወል
162
ምሳሌነቱ፦ የትንቢተ ነቢያት ነው:: ደውሉ ካህናትና ምእመናንን ቀስቅሶ
ለአገልግሎት /ለጸሎት/ እንደሚዘጋጅ፤ ነቢያትም የሕዝቡን ልብ እየቀሰቀሱ፤
ከአምልኮተ ጣኦት ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር እየመለሱ፤ ለአዲስ ኪዳን
አገልግሎት እንዲዘጋጁ ያደርጉ እንደነበር ያሳያል።
ሐ. የወንጌል ደወል
ምሳሌነቱ፦
የስብከተ ዮሐንስ፣ የሐዋርያትና የሰብአ አርድዕት ልቅሶ ነው። (ሉቃ፫፥፫‐፯፡፡) ይህ
ደወል ከተደወለ በኋላ ያለው የቅዳሴ ክፍል ፍሬ ቅዳሴ ይባላል:: ይህም መሥዋዕተ
ወንጌል የሆነው የክርስቶስ ሥጋውና ደሙ የሚቀርብበት ነው:: ደወሉ ሐዋርያትና
አርድእት ቅዱሳት አንስትም ጌታችን በተሰቀለ ጊዜ ያዘኑትን ሐዘን፥ ያለቅሱትንም
ለቅሶ፣ ያፈሰሱትንም ዕንባ የሚያስታውስ ነው።
መ.የእግዚኦታ ደወል
ሠ.የድርገት ደወል
163
ካህናትም በቅዳሴ ጊዜ ነፍስ የተለየውን መለኮት ያልተለየውን (የተዋሐደውን)
የክርስቶስን ሥጋና ደም እንዲያቀብሉ ደወል ይደወላል:: ሐዋርያትና ሰብአ
አርድእት ጸጋ መንፈስ ቅዱስን ተቀብለው ወንጌልን በመላው ዓለም አስተምረዋል፤
ሰብከዋል። ዞረው ማስተማራቸውንና በስብከታቸው የሰው ልጆች ሁሉ ከሞት ወደ
ሕይወት መሸጋገራቸውን ለማሰብና ምእምናንም ዛሬ በደወሉ ድምፅ የዘለዓለም
ሕይወት ወደሚያገኙበት፥ የክርስቶስ ሥጋና ደም እንደሚቀርቡ ለማመልከት ነው::
የመዝሙር ጥቅም
ከብሉይ ኪዳን ዘመን ጀምሮ በሰው ልጆች ሕይወት ውስጥ ጉልህ ሥፍራ ያለው መዝሙር
/በዜማ ስልት በወጉ የተዘጋጀ ምስጋና/ በርካታ ጥቅሞች አሉት:: ከምንም በላይ
እግዚአብሔር አምላክንና በእርሱ ፈቃድም ለመረጣቸው ቅዱሳንና ቅዱሳት ሁሉ ምስጋና
164
በማቅረብ መባረክ /መቀደስ/ ዋናው ጥቅም ነው። በተጨማሪም ለማሳያ የሚሆኑ ጥቅሶችን
ብንጠቅስ፦ደዌያት እንዲከለከሉ /እንዲገሠጹ/፤ /፩ሳሙ ፲፮፥፳፩‐ ፍጻሜው፡፡/ የጠላት
ወጥመድ እንዲበጣጠስ፣ እግር ብረቶችና ሰንሰለቶች እንዲወላልቁና እስረኞችም ነጻ
እንዲወጡ፤ /ሐዋ፲፮፥፳፭‐፴፭፡፡/ መዝሙር በምእመናን የዕለት ተዕለት ክርስቲያናዊ
ሕይወት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው መጽሐፍ ቅዱስ በዝርዝር ይነግረናል።
፩ መጽሐፈ ድጓ፦
ይህ የምስጋና መጽሐፍ በዓመቱ ውስጥ ያሉ የበዓላትና የሰናብት መዝሙራትን ሰብስቦ
የያዘ ነው:: ድጓ ማለትም እስትጉቡእ /ስብስብ/ የቤተ ክርስቲያን ድግ /ትጥቅ/ ከቅዱሳት
መጻሕፍት ተለቅሞ የወጣ ድርሳን፣ መዝሙረ ሐዲስ ማለት ነው:: ድጓ በውስጡ አራት
ታላላቅ ክፍሎች አሉት:: እነርሱም:-
ሀ/ የዮሐንስ ድጓ፤
ለ/ የአስተምህሮ ድጓ፤
ሐ/ ጾመ ድጓና
ምሳሌነታቸው፦
➢ የአራቱ ክፍላተ ዘመን ማለትም “መፀው፣ ሐጋይ፣ ጸደይና ክረምት” ለሚባሉት ነው፡፡
እንዲሁም:-
➢ በብሉይ ኪዳን የነበሩ የአራቱ ክፍላተ ዘመን፣ “ዘመነ አበው፣ ዘመነ መሳፍንት፣ ዘመነ
ነገሥታትና ዘመነ ካህናት” ይሆናሉ፡፡ አንድም:-
➢ በሐዲስ ኪዳን የነበሩና ያሉ ያራቱ ክፍላተ ዘመን ዘመነ “ሐዋርያት፣ ዘመነ
ሐዋርያውያን አበው፣ ዘመነ ሰማዕታት እና ዘመነ ሊቃውንት” እንዲሁም
➢ የአራቱ ወንጌላውያን “ማቴዎስ፣ ማርቆስ፣ ሉቃስና ዮሐንስ” ነው።
፪/መጽሐፈ ዝማሬ፦
ዝማሬ ዘመረ አመሰገነ ከሚለው የግእዝ ቃል የሚወጣ ስም ነው:: በነጠላው መዘመር፣
አዘማመር፣ ዝመራ፣ ዜማ፣ የኅብረት ምስጋና፣ የሚል ፍቺ ይኖረዋል:: አገልግሎቱ ሥርዓተ
ቅዳሴ በሚፈጸምበት ወቅት ከድርገት በኋላ የሚቃኝ፣ የሚዜም፣ የሚዘመርና የቅዳሴውን
አካሄድና ዓላማ ተከትሎ የሚጓዝ ምስጋና ነው:: የሚዘመረውም በሳምንት (ሰንበት)፣ በወርና
በክብረ በዓላት ወቅት ነው:: አከፋፈሉንም በተመለከተ በሦስት ዋና ዋና ክፍሎች
ይመደባል። እነርሱም፦ዝማሬ፣ አኮቴትና ምሥጢር ይባላሉ:: በውስጡም ሦስት ንዑሳን
ክፍሎች አሉት:: እነርሱም በበኩላቸው ኅብስት ጽዋዕና መንፈስ በመባል ይታወቃሉ:: ቅ/
ያሬድ በሦስት ክፍላት /አርእስት/ የዘመረበት የራሱ የሆነ ምሥጢራዊ ፍቺም አለው፡፡
166
ምሳሌነቱ፦ ጌታችን ፫ መዓልት፣ ፫ ሌሊት በከርሰ መቃብር ለማደሩ ነው።
፫.መጽሐፈ መዋሥዕት
የቃሉ ትርጉም በሁለት መንገድ ሊገለጥ (ሊፈታ) ይችላል። ይኸውም በአንድ በኩል:-
፬.መጽሐፈ ምዕራፍ
ማረፊያ ወይንም ማሳደሪያ የሚል ትርጉም የሚኖረው ይህ መጽሐፍ የዘወትርና የጾም
ተብሎ በ ፪ ታላቅ ክፍሎች የቀረበ ምስጋና ነው። የሁለቱም ክፍሎች መሠረታቸው የቅ/
ዳዊት መዝሙርና የራሱ የቅ/ ያሬድ ድጓ ነው፡፡ በዓመቱ ውስጥ ባሉት ሳምንታትና በዓላት
እግዚአብሔርን ለማመስገን አገልግሎት ላይ የሚውለው የዘወትር ምዕራፍ ነው:: የጾም
ምዕራፍ ደግሞ በጾመ ሁዳዴ /ዐቢይ ጾም/ እና በረቡዕና ዓርብ ጾም እንዲሁም በምሕላ
ቀኖች እግዚአብሔርን መለመኛና ማመስገኛ ነው።
፲/አንብር /ር/፦ መድኃኔዓለም ክርስቶስ የማዳን ሥራውን ፈጽሞ በማረግ በአባቱ ዕሪና
/ክብርና ትክክልነት/ መቀመጡን ያስረዳል።
ምሳሌነቱ፦ የወልድ ነው፤ ወልደ እግዚአብሔር ወልደ ማርያም ኢየሱስ ክርስቶስ ሰውን
ለማዳን ጽኑዕ መከራ በመቀበሉ ተመስሏልና::
169
ቤተክርስቲያንን፣ ትምህርቷን፣ ዜማዋን፣ ቅርሷን፣ ታሪኳንና ትውፊቷን፣ መርሳት /መተው/
እንደማይገባና ከዚህ ዓለም ጥቅሞች፣ ከሥጋዊ ፍላጎቶችና ከደስታዎች ሁሉ በላይ
ቤተክርስቲያንንና የጠቀስናቸውን መንፈሳዊ ሀብቶች መውደድ እንደሚገባ ከዚህ ኃይለ
ቃል መረዳት ይችላል።
ለምሳሌ፦ ከቅዱስ ያሬድ የዜማ ድርሰቶች ዋናውን ድጓን ብንመለከት በ፬ ወቅቶች /ክፍለ
ዘመናት/ ተከፋፍሎ መዜሙን እንረዳለን። እነሱም፦
170
መ. ዜማው በመጽሐፍ ቅዱሳዊ ምሳሌና ምሥጢር የተሞላ መሆኑ ሌላው ልዩ ጠባዩ ነው።
የዜማው መሠረቶችም፦ መጻሕፍተ ብሉያት፣ መጻሐፍተ ሐዲሳት፣መጻሕፍተ
ሊቃውንት፣መጻሕፍተ መነኮሳት፣አዋልድ መጻሕፍትና ትውፊት ናቸው።
ምሳሌነቱ፦
- ዕጣን፦ የጌታ
- ጽምፅ፦ የምስጋናዋ፤ የመስንቆ ጭራ (ክር) በዕጣን ታሽቶ ድምጽ እንደሚሰጥ፣
እመቤታችንም ጌታን ወልዳ ወላዲተ አምላክ ለመባል በቅታለች። ጌታን ፀንሳ
ሳለችም “ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ያመሰግኑኛል።” (ሉቃ፩፥፵፰፡፡) በማለት
ተናግራለች::
፫. በገና ከመጀመሪያዎቹ የዝማሬ መሣሪያዎች አንዱ ነው፡፡ /ዘፋ ፬፥፳፩፡፡/ ቅዱስ ዳዊት
በገና እየደረደረና እግዚአብሔርን እያመሰገነ ንጉሥ ሳኦልን ከደዌው /ከያዘው ርኩስ
መንፈስ/ ይገላግልበት የነበረ የዜማ መሣሪያ ነው። /፩ሳሙ፲፮፥፲፮፡፡/ ካህናተ ሰማይ
ቅዱሳን መላእክት የቅዱሳን ጸሎት ከሆነ ዕጣን ከሞላበት የወርቅ ዕቃ /ጽናሐሕ/ ጋር በገና
ይዘው በአዲስ መዝሙር ሲያመሰግኑ ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ አይቷቸዋል። /ራእ
172
፭፥፰‐፲፡፡/ ይህም የዚህን የዝማሬ መሣሪያ ሰማያዊ ክብርና ተቀባይነት የሚያጎላልን
ይሆናል። በመጽሐፍ ቅዱስ ብዙ ጊዜ ጥቅም ላይ መዋሉ ተመዝግቧል:: /፩ ዜና ፲፭፥፳፩፡፡
፪ ዜና ፳፱፥፳፭‐፳፰። መዝ ፴፪፥፩‐፬፤ ፺፩፥፩‐፫፡፡/
• የሻኩራዎቹ ቁጥር፦
፮.ከበሮ፦
• ጠፍሩ - የተዋሕዶ፤
176
ሐ. የዕጣኑ ጢስ ወደ ላይ መውጣት በቤተክርስቲያን የሚቀርበው ጠቅላላ አገልግሎትና
ጸሎት ወደ እግዚአብሔር የማረጉ (የመቅረቡ) ምሳሌ ነው።
❖ በብሉይ ኪዳንና በሐዲስ ኪዳን ጽላት (ታቦት) መካከል ያለው አንድነትና ልዩነት
ምንድነው?
ታቦት
ሥርወ ቃሉን ስንመለከት ቤተ-አደረ ከሚለው ግስ ይወጣና ታቦት ማለት የጽላቱ
ማደሪያ፥ መኖሪያ የሚል ይሆናል። ይኸውም የእግዚአብሔር የክብሩ መገለጫ፥ የክብሩም
ዙፋን ነው:: በአሁኑ (አዲስ ኪዳን) የቤተ ክርስቲያን አጠቃቀም ታቦት ስንል ጽላት
ማለታችን ነው። ታቦት ወጣ ማለትም የጽላት ማደሪያው ወጣ ማለት አይደለም፡፡ ስመ
አምላክ የተጻፈበት አማናዊው የሐዲስ ኪዳን መሠውያ፣ የሥጋ ወደሙ ማክበሪያ፣ የጻሕሉና
የጽዋው ማኖሪያ የሆነው ጽላት ወጣ ማለታችን ነው እንጂ፡፡ ከዚህ በታች ታቦት እያልን
ስንጽፍም ጽላት ማለታችን እንደሆነ በመረዳት እንዲያነቡ እንጠይቃለን:: ታቦት
እግዚአብሔር ከሕዝቡ ጋር የመኖሩ /የመሆኑ/ ምልክት ነው። /ዘፀ ፳፭፥፩-፳፪፡፡/
177
እስራኤልን እየታደጋቸው፤ መንገዳቸውንና ማደሪያቸውንም እያዘጋጀላቸው ተጉዘዋል።
/ዘኁ፲፥፴፫፡፡ ኢያ፫፥፩-ፍጻሜው፤ ፮፥፩-ፍጻሜው፡፡/ በብሉይ ኪዳን ዘመን ሁሉ
የእግዚአብሔር የቃል ኪዳኑ ታቦት /ጽላት/ እየተባለ ይጠራ ነበር። /ዘዳ ፲፥፰፤
፴፩፥፱‐፳፭፡፡/
ይህ መሠውያው በሰማያዊው መቅደስም እንኳን አለ። /ራእ ፮፥፱፤ ፰፥፫፤ ፲፩፥፩፡፡/ በራእ.
፲፩፥፲፱ ላይ ያለው ደግሞ በግብሩ ብቻ እንደላይኞቹ መሠውያ እያለ ሳይሆን እንደ
ፊተኛው /በብሉይ ኪዳን ይጠራ እንደነበረው/ በመጥራት ወንጌላዊው ዮሐንስ ያየውን
እንዲህ በማለት አስፍሮታል። “ከዚህም በኋላ በሰማይ ያለው የእግዚአብሔር መቅደስ
ተከፈተ፣ የእግዚአብሔር የሕጉ ታቦትም በመቅደሱ ታየች፤ የመብረቅና የነጎድጓድ ድምፅ፥
178
የምድር መናወጥና ታላቅ በረዶም ሆነ።” እንዲል:: ምሥጢሩ ግን ያው እንደላይኛው
መሠውያ ማለትን ያስተረጉማል:: ለታቦትም ሲሰገድ፣ በታቦቱ አድሮ ድንቅ ሥራ
ለሚሠራው፣ ሥጋውንና ደሙን ለሚያምኑበት ሁሉ መድኃኒት አድርጎ ለሰጠው
ለእግዚአብሔር ነው የምንሰግደው፡፡ በሐዲስ ኪዳን ታቦት በምንልበት ጊዜ አማናዊት
ታቦት እመቤታችን ድንግል ማርያም አብራ ትዘከራለች። /መዝ ፻፴፩፥፰፡፡/ የብሉይ ኪዳን
መጻሕፍት ትርጓሜያት ታቦት የእመቤታችን ጽላት የልጇ (የክርስቶስ) በማለት
የሚያመሠጥሩትም ለዚህ ነው።
፲፩•፯ መስቀል
በአጠቃላይ መስቀል
፯. አዳም ከነልጆቹ ከሲዖል ረግረግ ነጻ የወጣበት የሕይወት መሰላል ነው። /ኤፌ ፪፥፲፬፡፡/
180
፱. ካህናትና ምእመናን መውጣት መግባታቸውን (መንገዳቸውን)፣ ምግባቸውንና
መጠጣቸውን፣ ሥራቸውንና ኑሮአቸውን ሁሉ የሚያስባርኩበት መንፈሳዊ መሣሪያና
የመጽናናት ምልክት ነው።
ይኸውም፦
የመስቀል ዓይነቶች
፪. የእጅ መስቀል፦ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት፣ ሊቃነ ጳጳሳት፣ ኤጲስ ቆጶሳትና ቀሳውስት ዘወትር
የሚይዙትና ምእመናንን የሚባርኩበት ነው።
181
የእንጨት መስቀል፦ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከ፯ ዓይነት ዕፅዋት
በተዘጋጀ መስቀል የመስቀሉ መታሰቢያ ነው::
የወርቅ መስቀል፦ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ንጽሐ ባሕርይ አምላክ የመሆኑ ማዘከሪያ
ነው።
የመዳብ መስቀል፦ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደሙ መፍሰስ ዓለምን የማዳኑ
/መዳብ ቀይ ነውና/ ማስታወሻ ነው።
መስቀል ከቅርጹ አንጻር ሲታይ በቤተ ክርስቲያናችን ከጥንት ጀምሮ ጥቅም /አገልግሎት/
ላይ የዋሉ የመስቀል ዓይነቶች ደግሞ እንደሚከተለው ሆነው ሊዘረዘሩ ይችላሉ።
• ዕፀ ሳቤቅ መስቀል፣
• ጽጌ ደንጎላ መስቀል፣
• ዕፀ ስርናይ መስቀል፣
• ለንጊኖስ መስቀል፣እና
ማጠቃለያ
በዚህ ዓለም ላይ አንድ ሰው የወላጆቹ ልጅ መሆኑ ከሚረጋገጥባቸው መንገዶች አንዱ
የወላጆቹን አኗኗራቸውን በወጉ የተረዳ መሆኑና የውጪውንና የውስጡን ንብረታቸውን
ሰፍሮ ቆጥሮ ማወቅ፣ መጠበቅና መጠቀም ሲችል ነው፡፡ ወላጆቹ እስካሉ አብሮአቸው
ይጠቀማል፤ ባረፉ ጊዜም እንዳየና እንደሰማ ሕይወታቸውንና የእነሱ የሆነውን ሀብታቸውን
ወርሶ ይኖራል፡፡
183
ዋቢ መጻሕፍት
• የኢት/ኦ/ተ/ቤ/ክ፤ ፍትሐ ነገሥት ንባብና ትርጓሜው፤ትንሣኤ
ማሳተሚያ ድርጅት፤ ፲፱፻፺፤ አ/አ።
184
• ክርስቲን ሻዮ፤ መ/ሰ ዳኛቸው ካሳሁን፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ
ተዋህዶ ቤ/ክ ትውፊትና መንፈሳዊ ሕይወት፤ ማኅበረ ቅዱሳን
1999፤ አ/አ።
ማጠቃለያ ፦
ወልደ እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ በቀራኒዮ አደባባይ ሥጋውን ቆርሶ ፥ ደሙን
አፍስሶ ዓለሙን ሁሉ አዳነ። በመዋዕለ ሥጋዌው ድውያነ ሥጋን በተአምራት ፥ ድውያነ
ነፍስን ደግሞ በትምህርት እየፈወሰ በምድረ እስራኤል ተመላለሰ። በዚህም ምሥጢራትን
በመመሥረት ሥርዓታቸውንም አከናውኖ ቤተ ክርስቲያንን አደራጀ። ከትንሣኤው በፊት
ያስተማረው ትምህርት፣ የሠራው ተአምራት “ወንጌል” ሲባል ከትንሣኤው በኋላ ያስተማረው
ትምህርት ደግሞ “ኪዳን” ይባላል። ሞትን በሞቱ አጥፍቶ ከሲዖል ባርነት ከሠይጣንም
ቁራኝነት የሰውን ልጅ ነጻ ቢያደርገውም “ነጻ ወጥቻለሁ!” ብሎ እንዳሻው እንዲኖር ግን
አልተፈቀደለትም።
186