You are on page 1of 192

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን

በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ

ማኅበረ ቅዱሳን

በወላይታ ሀገረ- ስብከት

የወላይታ ሶዶ ማዕከል

በዋዱ ቁስቋም ማርያም ቤተ ክርስቲያን

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ

በትምህርት እና ሐዋርያዊ አገልግሎት ክፍል

ለሁለተኛ ዓመት ለዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ኮርስ በሀንዳውት መልክ የተዘጋጀ

የኮርሱ ርዕስ፡- የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት

በቤተ ክርስቲያን ላይ በተለያየ ቦታ አና ጊዜ ለሚነሱ ጥያቄዎች መልስ ይሆን ዘንድ ከቤተ


ክርስቲያን ሊቃውንት ካስተማሯቸው መጻሕፍቶች፣ ከሰበኳቸው ስብከቶች እና ከለቀቋቸው
ከድረገጽ ጹሑፎች እንዲሁም ከተለያየ ጊዜ ከተማርኳቸው ኮርሶች መካከል የወሰድኩት፡፡

አዘጋጅ፡- ዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ


(በኤሌክትሪካል እና ኮምፕዩተረ ምህንድስና የዚህ ዓመት ምሩቅ)
አድራሻ፡- 09 42 40 76 60 (ስልክ ቁጥር)
:- ashewolde21@gmail.com (ኢሜል አድርሻ)
: - Ashenafi woldyes (ፌስ ቡክ አካውንት)
: - ዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (ቴሌ ግራም)

ሐምሌ 06/2011 ዓ.ም


ወላይታ ሶዶ፣ኢትዮጵያ
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ምስጋና (Acknowledgement)
በቅድሚያ በጅማሪም በፍጻሜ የማይለይ እንዲሁም ያለተለየኝ የምሥጢራት እና የሥርዓት ሁሉ
መሠረት እና ባለቤት፤ ከሃያ ሁለቱ ሥነ- ፍጥረታት አልቆ፣ አስውቦ፣ ለርስቱ ለመውረስ
ከሰባቱ ባሕርያት ለፈጠረው ለሰው ልጅ ምሥጢራትና ሥርዓትን ያደለ ለልዑል እግዚአብሔር
አምጣ ወልዳ እርሷም አሳድጋ ብርሃን የሰጠችን የድነታችን መሠረት፣ የብርሃን መገኛ ምሥራቅ
ለንጽሕተ ንጽኋን፣ ለቅድስተ ቅዱሳን፣ ወላዲተ አምላክ፣ ለቅድስት ድንግል ማርያም
የእኛን ጸሎት ወደ እግዚአብሔር የእግዚአብሔርን ምኅረት ወደ እኛ የሚያመጡ ቅዱሳን በሙሉ
ደከመኝ ሰለችኝ ሳይሉ ቤታቸውን ጥለው ከእኛ ጎን በመሆን በሀዘን በደስታችን ላልተለዩን
ምክራቸውንና ተግሳጻቸው ዘወትር ለሕይወታችን ብርሃን ለሆነው ለዋዱ ቁስቋም ማርያም
ቤተክርስቲያን አባቶች ካህናት በሙሉ
ወጣቱን በነጣቂ ተኩላዎች እንዳይበላ ግቢ ጉባያትን በማቋቋም ዘወትር ጠዋትና ማታ መንፈሳዊ
ማዕድን በመዘርጋት ሌተ ቀን ለሚተጋው ማኅበረ ቅዱሳን
ዘወትር ስብከትን በማዘጋጀት እና መጽሐፍትን በመጻፍ፣ በጉባኤ፣ በማኅበራዊ ሚዲያና እና
ድረገጾች ለምታስተምሩ እና አፋጣኝ ምላሽ ለምትሰጡ መምህራነ ቤተ ክርስቲያን

ዘወትር ከጎኔ በመሆን ለጹሁፉ መሳካት ለደከምከው እና ልዩ ምክርህ ላልተለየኝ መንፈሳዊ


ወንድሜ ሞቲ ደቻሳ
ዘወትር በሐሳብ እና በጎደለኝ ለነገር ሁሉ ቀድመው በመገኘት ለሚያግዙኝ መንፈሳዊ ወንድሞቼ
ዲ/ን ዕርገተ ቃል፣ ዲ/ን ሸለማ፣ ዲ/ን አካሉ፣ ዲ/ን ኃይለገብርኤል፣ ዲ/ን ኢሳይያስ፣ አሳየ፣
ባንቲደሩ፣ ቀለብ፣ ወሰኑ፣ የዶርም ጓደኞቼ በተለይ መኮነን፣ ንጉስ፣ መለሠ፣ ዘየደ
ከጎኔ በመሆን በመንፈሳዊ ሕይወት እንዳደክም ለሚያበረታቱኝ ለመፈሳዊት እህቶቼ ሎዛ፣
ሰናይት፣ ጌጤ፣ ፀሀይነሽ፣ ወሰንየለሽ፣በላይ፣ ደብሬ፣ ብልጫ፣ ብፅይት፣ ባለም፣ አቅልሲያ፣
አመተ ማርያም፣ ብርሃኔ፣መለሠ፣ ……….
በተለይ ደግሞ በግቢ ቆይታዬ ለዚህ ደረጃ እንድደርስ ለደከሙልኝ በሕይወቴ አንድ ምዕራፍ
ለመሻገር የረዱኝ ናቸው፡፡ ተሰማ፣ አለምነህ፣ ዙርያሽ እና ወለተ ሥላሴ
ጹሁፉን ወደ ተንቀሻቃሽ ስልክ መተግበሪያ (Mobaile APP) ለቀየረልኝ ለመንፈሳዊ ወንድሜ
ወንድምአገኝ ጥላሁን ከዚህ በላይ ጥበቡን ይግለጽልህ
ለጽሑፉ መጻፍ ምክንያት ለሆናችው እና ኮርስን ሳስተምር ሳትንቁኝ ለተከታተላችሁ ለሁለተኛ
ዓመት ለዩኒቨርስቲ እና ለአጠቃላይ ለግቢ ጉባኤው የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እንቁ ፍሬዎች
በማኅበረ ቅዱሳን ወላይታ ሶዶ ማዕከል፣ የግቢ ጉባኤው ሥራ አስፈጻሚዎች እና ንዑሳ በሙሉ
እነምዲሁም ለዋዱ ቁስቋም ማርያም ቤተክርስቲያን ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ለነገሮች ሁሉ
መሳካት ተቀዳሚ ናቸውና፡፡
ስማችሁን ያልጠቀስቁኝ ነገር ግን ከጎኔ ለነበራችሁ ዋጋችሁ በሰማይ መዝገብ ይጻፍላችሁ፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | II
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

መግቢያ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን
ይህን ጽሑፍ እንድጽፍ ያነሳሳኝ ነገር ቢኖር በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የኤሌክትሪካል ምህንድስና
ትምህርቴን ስከታተል ለአምስት ተከታታይ ዓመታት በዓለም ወጥመድ ገብቼ እንዳልቀር እና ሰው
መሆኔን እንዳልረሳ በዋናው ግቢ ጉባኤ በዋዱ ቁስቋም ማርያም ቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ
ሕይወትን እየመገቡኝ ቆይቻለሁ፡፡ በዚህም ቆይታዬ መካከል በአገልግሎት ተመሳስለውን የነበሩ ነገር
ግን ከኛ የተለዩ ወገኞች በሥርዓተ እና በምስጢራተ ቤተ ክርስቲያን ዙርያ የማደናገርያ ጥያቄዎች
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እንቁ ፍሬዎች ሲጠይቋቸው እና ብዙዎቹም በጥያቄያቸው እየተደናገሩ
ሃይማኖታቸውን ሲክዱና ሲቀይሩ በመመልከቴ፡፡ አንድም ምዕመናንም ሥርዓተ እና ምሥጢራተ
ቤተክርስቲያንን ባለመጠንቀቅ (ባለማወቅ) ሲስቱ በመመልከቴ፡፡ በተጨማሪም በ2011ዓ.ም ለሁለተኛ
ዓመት ለዩኒቨርስቲ ለአሮቶዶክስ ተዋሕዶ ተማሪዎች የቤተክርስቲያን ምሥጢራት እና ሥርዓት
የሚለው ኮርስ እያስተማርኩኝ ነበርና ኮርሱ በሀንዳውት መልክ ለማዘጋጀት አስቤ ነው፡፡ በተለይ
ደግሞ ብዙዎች ወቅታዊ ለሆኑ ጥያቄዎች መልስ የያዙ መጽሐፍትን በተመጣጣኝ ዋጋ እና
በፈለጉት ቦታ ባለማግኘታቸው መልስ ለመስጠት እየተቸጋገሩ ስለሆነ ምንአልባት ልታግዛቸው
ትችላለች በሚል አስተሳሰብ ለማዘጋጀት ተነሳሳሁኝ፡፡ ለዚህም እንዲረዳኝ በማኅበረ ቅዱሳን
የተዘጋጀው የኮርሱ መጽሐፍ፣ በቤተ ክርስቲያን ላይ በተለያየ ቦታ አና ጊዜ ለሚነሱ ጥያቄዎች
መልስ ይሆን ዘንድ ከቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት ካስተማሯቸው መጻሕፍቶች፣ ከሰበኳቸው ስብከቶች
እና ከለቀቋቸው ከድረገጽ ጹሑፎች እንዲሁም ከተለያየ ጊዜ ከተማተርኳቸው ኮርሶች መካከል
ወሰድኩኝ፡፡ በተጨማሪም መንፈሳዊ ወንድሜ ወንድማገኝ ጥላሁንን በመጠየቅ ይህን ጽሑፍ ወደ
ተንቀሻቃሽ ስልክ መተግበሪያ (Mobaile APP) ቀይሮልኛል፡፡ ስለሆነም ውድ አንባቢያን ሆይ በዚህ
ጹሑፍ ብቻ ለሁሉም ጥያቄዎች መልስ ላታገኙ ትችላላችሁና የተለያዩ የሊቃውንት እና የመምህራነ
ቤተክርስቲያን መጽሕፍትን ለይተን በመመልከትና በማንበብ እንድታዳብሩ በተለይ ደግሞ በአሁኑ
ሰዓት የቤተ ክርስቲያን የብብት እሳት የሆኑባትን ተሐድሶ መናፈቃን አና የአሕዛብ ጥያቄ መልስ
በመስጠት እንድትመክቱ እያልኩኝ በእግዚአብሔር ስም እማጸናችኋለሁ፡፡ በቀጣይ የቅዱሳን አምላክ
ቅዱስ እግዚአብሔር ዕውቀት፣ ጥበብና ማስተዋሉን ቢገልጽልን ወላዲተ አምላክ ጥላ ከለላ ብትሆነን
በሌላ ርዕሰ ጉዳይ ላይ በሰፊው እንገኛኛለን ብዬ አስባለሁኝ፡፡ አስከዛው ሠላመ እግዚአብሔር
አይለየን፡፡
ማሳሰቢያ፡- ይህ ጽሑፍ ግድፈት፣ ደሀጸ ብታገኙበት ፈጥኜ ስጽፈው ስቼ ነውና አርሙኝ፡፡ ሐሳብ
አስታያት ጥያቄ ካላችሁ በአድራሻዬ አግኙኝ፡፡

መልካም ንባብ!!!
አዘጋጅ ዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | III
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

መቅድም (Abstract)
“አንተም ሁነህ አስተካክለው” (አቡነ ጎርጎርዮስ) ቅድስት ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ደም
ከተመሠረተችበት ጊዜ አንስቶ ለልጆቿ ቅዱስ ቃሉን እየመገበች ምሥጢራትን እየፈጸመችና
በሥነ ምግባራት ሠናያት እያነፀች ባሕረ ዓለምን ቀዝፋ ወደ ዕረፍት ወደብ እያሻገረች
/እያደረሰች/ የምትገኝ መንፈሳዊት መርከብ ናት፡፡ ይኽችም በኢየሩሳሌም (በጸኑት)፣ በይሁዳ
(አምነው፤ እየወደቁና እየተነሡ በሚታገሉት) ፣ በሰማርያ (አምነው በካዱት) እና በምድር
ዳርቻ (ፈጽመው ባላመኑት) መካከል በምታደርገው ሐዋርያዊ አገልግሎት የምትመራበት
መንፈሳዊ ሥርዓትም ባለቤት ናት። እግዚአብሔር አምላካችን በሰዎች መካከል ማደር
በፈለገ ጊዜ በሰማይ ባለ መቅደሱ አምሳል ደብተራ ኦሪትን እንዲሠራ ሙሴን አዘዘው።
(ዘጸ፳፭፥፰፳፰) ንዋያተ ቅድሳቱና ሥርዓተ ደብተራ ኦሪቱም በዚያው አምሳል የተከናወነ
እንዲሆን ፈቀደ፡፡ “ፊተኛይቱም ደግሞ የአገልግሎት ሥርዓትና የዚህ ዓለም የሆነው መቅደስ
ነበራት” (ዕብ ፱፥፩) መቅደሰ ሰሎሞንም በደብተራ ኦሪት አምሳል ሲሠራ ድንኳኑ ሕንፃ
ከመሆኑ በስተቀር ንዋየ ቅድሳቱና ሥርዓቱ ተመሳሳይ ነበር፡፡ ቤተ መቅደሱ ተሠርቶ
በተፈጸመበት ወቅት ንጉሥ ሰሎሞን የእስራኤልን ጉባኤ በመረቀበት አንቀጽ “በመንገዱም
ሁሉ እንሄድ ዘንድ ለአባቶቻችንም ያዘዛትን ትእዛዙንና ሥርዓቱን እንጠብቅ ዘንድ ልባችንን
ወደ እርሱ ይመልስ።” (ነገ ቀዳ ፰፥፶፰) በመቅደሰ ሰሎሞን ይፈጸም የነበረው ሥርዓተ
አምልኮ አባቶቻቸው በደብተራ ኦሪት ይፈጽሙት በነበረው ሁኔታ መቀጠሉን ያሳያል።
ቤተክርስቲያንም በመቅደሰ ሰሎሞን አምሳል ተሠርታለች። ይህም ውጭያዊ የሕንፃ
አሠራሯን ብቻ ሳይሆን ውስጣዊ የአምልኮ ሥርዓቷን ሁሉ የተመለከተ ነው። ከሥርዓት
ውጪ እንዳሻቸው በመሄድ ቤተ ክርስቲያንን የሚያውኩትንም “ያለ ሥርዓት የሚሄዱትን
ገሥጹአቸው” ፤ (፩ተሰ፭፥፲፬)። “ወንድሞቻችን ሆይ በሠራንላችሁ ሥርዓት ሳይሆን በተንኮል
ከሚሄዱት ወንድሞች ሁሉ፥ ትለዩ ዘንድ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እናዝዛችኋለን። በማለት
ማስተማሩን ማስተዋል ይገባል ደገኛውን ሥርዓት ይዞ መጓዝ እንደሚገባም” አሁንም
ወንድሞቻችን ሆይ ጸንታችሁ ቁሙ፤ በቃላችንም ቢሆን ወይም በመልእክታችን
ያስተማርናችሁንና የሠራንላችሁን ሥርዓት ያዙ” (፪ተሰ ፪፥፲፭) በማለት አሳስቧል።
ቤተክርስቲያን በየጊዜው የፈጸመችውና የምትፈጽመው መንፈሳዊ አገልግሎት ሁሉ
ሥርዓትን በመከተል የተከናወነና የሚከናወን መሆኑ ግልጽ ነው። የቤተ ክርስቲያኒቱ
ሁለንተናዊ ሕይወት የሆነው ይህ ሥርዓተ አምልኮ ሳይበረዝና ሳይከለስ፣ ሳይጨመርበትና
ሳይቀነስለት እንዲጓዝ ለማድረግ ካህናት ሰባክያነ ወንጌል እና ምእመናን የበኩላቸውን
(የድርሻቸውን) ማበርከት ይጠበቅብናል፡፡ ምክንያቱም ዲያቆኑ ሀቢብ ጊዮርጊስ ፓትርያሪኩን
አቡነ ሺኖዳን አስገኘቷልና፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | IV
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ማውጫ
ምስጋና (Acknowledgment) ........................................................................................ II
መቅድም (Abstract) .................................................................................................... III
1. አንቀጸ መድኃኒት ቤተ ክርስቲያን .............................................................................. 1
1.1 የቤተ ክርስቲያን የቃሉ ትርጉም .......................................................................... 1
1.2 የቤተ ክርስቲያን አመሠራረት .............................................................................. 2
1.3 የቤተ-ክርስቲያን ዓላማ ........................................................................................ 3
1.4 ቤተ ክርስቲያን የማን ነች? ለማን ተሰጠች? ......................................................... 3
1.5 የቤተ ክርስቲያን ኦርቶዶክሳዊነት .......................................................................... 3
1.6 ቤተ ክርስቲያን ከሌሎች ዕምነቶች የሚለያት ......................................................... 4
1.7 የቤተ ክርስቲያን ባሕርያት ................................................................................... 4
1.8 የቤተ ክርስቲያን ምሳሌ በሐዲስ ኪዳን .................................................................. 9
1.9 የሕንጻ ቤተ እግዚአብሔር አጀማመር ................................................................. 10
1.10 የቤተክርስቲያን ሥሪት .................................................................................... 11
1.11 የሕንጻ ቤተክርስቲያን አተካከል ........................................................................ 14
1.12 የሕንጻ ቤተ-ክርስቲያን አሰራር (ዲዛይን) ........................................................... 14
1.13 የቤተ መቅደስ ክፍሎች.................................................................................... 15
1.14 በቤተ ክርስቲያንና በዙሪያዋ የሚገኙ /የማይንቀሳቀሱ/ ንዋያተ ቅድሳት ............... 16
1.15 በቤተክርስቲያን ውስጥ የሚሰሩሌሎች ቤቶች.................................................... 18
1.16 ቤተ ክርስቲያን ስትባረክ .................................................................................. 18
1.17 ለምን ወደ ቤተክርስቲያን እንሔዳለን? .............................................................. 19
2. ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ......................................................................................... 21
2.1 ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን የቃሉ ትርጉም ............................................................. 21
2.2 የሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን መሠረት .................................................................... 21
2.3 የሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን አስፈላጊነት ................................................................ 22
2.4 የሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ምንጮች ................................................................... 23
2.4.1 መጽሐፍ ቅዱስ .......................................................................................... 23
2.4.2 ሐዋርያት የሠሯቸዉ የሥርዓት መጻሕፍት ................................................. 28
2.5 Passion week ሰሙነ ሕማማት ...................................................................... 30
2.6 በበዓለ ሃምሳ ንስሓ ለምን ተከለከለ? .................................................................. 32
2.7 የሰሙነ ሕማማት ሥርዓት ............................................................................... 34
2.8 የዐብይ ጾምሥራዓት ከሌሎች አፅዋማት ለምን ተለየ? .......................................... 36

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | V
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

2.9 ሴት የወንድን ልብስ አትልበስ ............................................................................ 37


2.10 እህቶቻችን ለምን አይሰብኩም? ........................................................................ 39
3. ምሥጢራተና ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ከነገረ ድኅነት ጋር ያላቸው ግንኙነት ............. 41
3.1 መዳን ማለት ምን ማለት ነው? ......................................................................... 41
3.2 ሰው የዳነው እንዴት ነው .................................................................................. 41
3.3 ለመዳን የሚያስፈልጉ መሠረታዊ ነገሮች ............................................................ 42
3.4 ዕፀ በለስ ለምን ተፈጠረች .................................................................................. 43
3.5 ያለ ድንግል ማርያም አማላጅነት ዓለም ሁሉ አይድንም፡፡ .................................... 44
3.6 ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ከነገረ ድኅነት ጋር ያላቸው ግንኙነት ....................... 45
3.7 ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ከነገረ ድኅነት ጋር ያላቸው ግንኙነት ............................. 46
4. ምሥጢረ ጥምቀት ................................................................................................. 47
4.1 የምሥጢረ ጥምቀት የቃሉ ትርጉም................................................................... 47
4.2 የምሥጢረ ጥምቀት አመሠራረት ...................................................................... 48
4.3 የጥምቀት ምሳሌዎች......................................................................................... 49
4.4 የጥምቀት አከፋፈል (ዓይነቶች) .......................................................................... 51
4.5 ለጥምቀት የተወሰነ ዕድሜ ................................................................................. 53
4.6 የሕጻናት ጥምቀት............................................................................................. 53
4.7 የሕጻናት ጥምቀት መብትን ይጋፋልን? .............................................................. 56
4.8 የቄደር ጥምቀት ................................................................................................ 56
4.9 ጥምቀት አንዲት (የማትደገም) መሆኗን ............................................................. 57
4.10 በማን ስም ልንጠመቅ ይገባል .......................................................................... 58
4.11 የጥምቀት አፈጻጸም ........................................................................................ 59
4.12 ለምን በውኃ እንጠመቃለን ................................................................................ 62
4.13 የዉኃና የመንፈስ ኅብረት ................................................................................ 63
4.14 ስመ ክርስትና (የክርስትና ስም)......................................................................... 64
4.15 ማዕተብ (ክር) ማሰር ....................................................................................... 66
4.16 የክርስትና አባትና እናት .................................................................................. 66
4.17 የጥምቀት ጠቀሜታዎች .................................................................................. 67
4.18 ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለምን ተጠመቀ .................................... 70
4.19 የጥምቀት በዓል አከባበር ................................................................................. 71
5. ምስጢረ ሜሮን ...................................................................................................... 73
5.1 የቅብዓ ሜሮን ትርጉም...................................................................................... 73

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | VI
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

5.2 የቅብዐ ሜሮን አገልግሎት ................................................................................. 73


5.3 የቅብዐ ሜሮን ምሣሌዎች .................................................................................. 74
5.4 የቅባዐ ሜሮን አዘገጃጀት .................................................................................... 74
5.5 ቅብዐ ሜሮን በብሉይ ኪዳን ............................................................................... 75
5.6 ቅብዐ ሜሮን በአዲስ ኪዳን................................................................................. 75
5.7 የቅባዐ ሜሮን አመሠራረት ................................................................................ 76
5.8 የቅብዐ ሜሮን አፈጻጸም..................................................................................... 76
5.9 ቅብዐ ሜሮን የሚያስገኘው ጸጋ .......................................................................... 79
6. ምስጢረ ቁርባን ...................................................................................................... 80
6.1 የምስጢረ ቁርባን የቃሉ ትርጉም ....................................................................... 80
6.2 የምሥጢረ ቁርባን አገልግሎት ........................................................................... 80
6.3 ቅዱስ ቁርባን በምሳሌና በትንቢት ....................................................................... 81
6.4 የምሥጢረ ቁርባን አመሠራረት ......................................................................... 82
6.5 ሥርዓተ ቅዳሴ.................................................................................................. 84
6.5.1 ሥርዓተ ቅዳሴ ሦስት ክፍሎች አሉት .......................................................... 84
6.5.2 ለማስቀደስ ከመሄድ አስቀድሞ የሚደረግ ዝግጅት ......................................... 84
6.5.3 በቅዳሴ ጊዜ ስለሚደረጉና ሰለማይደረጉ ሥርዓት ........................................... 86
6.6 ከቅዱስ ቁርባን በፊትና በኋላ መደረግ ሥላለበት ሥርዓት.................................... 87
6.6.1 ቅድመ ቁርባን መደረግ ያለበት ሥርዓት....................................................... 87
6.6.2 ቅዱስ ቁርባንን ከተቀበሉ በኋላ የሚደረግ ጥንቃቄ ......................................... 92
6.7 ምሥጢረ ቁርባን የሚያስገኘው ጸጋ.................................................................... 93
6.8 ቁርባን በብሉይ ኪዳንና በሐዲስ ኪዳን ልዩነቱና አንድነቱ ..................................... 94
6.9 የአዲስ ኪዳን ታቦት .......................................................................................... 95
6.10 አርባ አራቱ ታቦት የሚለው መነሻ ታሪክ ....................................................... 104
7. ምሥጢረ ተክሊል .............................................................................................. 107
7.1 ሥራዓተ ተክሊል ............................................................................................ 107
7.2 የምሥጢረ ተከሊል የቃሉ ትርጉም .................................................................. 108
7.3 የምሥጢረ ተክሊል አመሠራረት ..................................................................... 108
7.4 የጋብቻ አመሰራረት ......................................................................................... 109
7.5 የጋብቻ ዓላማዎች ........................................................................................... 110
7.6 ወጣትነትና ስሜቶቻቸው ................................................................................. 111
7.6.1 የዐፍላ ጉልምስና ምልክቶች ....................................................................... 113

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | VII
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

7.6.2 ለዐቅመ ሔዋን የመድረስ ምልክቶች ........................................................... 117


7.7 ከጋብቻ በፊት እንዴት እንኑር ......................................................................... 121
7.8 መተጫጨት ማጫ መስጠት እንዳደረግ የተከለከለ ጋብቻ ................................... 122
7.9 የእጮኝነት ጊዜ ............................................................................................... 125
7.9.1 በእጮኝነት ወቅት ሊጠነቀቁባቸው የሚገቡ መሠረታዊ ነገሮች ..................... 126
7.9.2 በምንተጫጭበት ወቅት ብዙ ጊዜ የማናስተውላቸው ስህተቶች ..................... 127
7.10 ከጋብቻ በፊት ............................................................................................... 130
7.10.1 የትዳር ጓደኛ ለመምረጥ መሠረታዊ የሆኑ ኦርቶዶክሳዊ መመዘኛዎች ....... 130
7.10.3 በድንግልና መኖርና የሚያስገኘው ክብር .................................................... 132
7.10.4 ማሕተመ ድንግልና ምን ማለት ነው ....................................................... 131
7.10.5 ድንግልና እና ሥርዓተ ተክሊል ............................................................... 133
7.11 በጋብቻ ጊዜ .................................................................................................. 137
7.11.1 የሥርዓተ ተክሊል መስፈርቶች ምንድን ናቸው? ...................................... 137
7.11.2 የሥርዓተ ተክሊል አፈጻጸም.................................................................... 139
7.11.3 በምስጢረ ተክሊል የሚገኝ ክብርና ጸጋ .................................................... 141
7.12 ከጋብቻ በኋላ ................................................................................................ 142
7.12.1 ባሎች ለሚስቶቻቸው ሊያሳዩአቸው የሚገባ ፍቅር .................................... 143
7.12.2 በጋብቻ ውስጥ ግብረ ሥጋ ግንኙነት የማይፈጸምባቸው ቀናት ................... 144
7.12.3 ፍቺ የሚፈቅድባቸው ምክንያቶች ............................................................. 146
8. ምሥጢረ ንስሓ ................................................................................................... 148
8.1 የምሥጢረ ንስሓ የቃሉ ትርጉም ..................................................................... 148
8.2 የምሥጢረ ንስሐ አመሠራረት ......................................................................... 149
8.3 ንስሐ ለምን አስፈለገ? ..................................................................................... 149
8.4 የምሥጢረ ጥምቀት አፈጻጸም ......................................................................... 151
8.4.1 የንስሐ ሃዘን /ጸጸት/ ................................................................................. 152
8.4.2 ኑዛዜ ....................................................................................................... 152
8.4.3 ፍትሐትና ቀኖና ....................................................................................... 153
8.5 የሚያስገኘው ጸጋ ............................................................................................ 154
9. ምሥጢረ ክህነት .................................................................................................. 156
9.1 የምሥጢረ ክህነት የቃሉ ትርጉም ................................................................... 156
9.2 የምሥጢረ ክህነት አመሠራረት ....................................................................... 157
9.3 የካህናት ዐበይት ተግባራት............................................................................... 159

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | VIII
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

9.4 በብሉይ ኪዳንና በሐዲስ ኪዳን ክህነት መካከል ያለ ልዩነት ................................ 162
9.5 የክህነት ሥልጣን ደረጃዎች ............................................................................. 162
9.6.1 ሥርዓተ ሲመተ ኤጲስ ቆጶስ ..................................................................... 164
9.6.2 ሥርዓተ ሲመተ ቀሳውስት ........................................................................ 167
9.6.3 ሥርዓተ ሲመተ ዲያቆናት ........................................................................ 168
9.7 የቤተ ክርስቲያን አባቶች አገልግሎታቸውን በአግባቡ እንዲፈጸሙ ...................... 169
9.8 የቤተ ክርስቲያን አባቶች በፈተና ቢወድቁስ? ..................................................... 170
9.9 ሊቀ ካህናት አለን ሲል ምን ማለቱ ነው ........................................................... 173
9.10 ሴቶች ለምን ካህናት አይሆኑም? ................................................................... 174
9.11 ምሥጢረ ክህነት የሚያስገኘው ጸጋ................................................................ 175
10. ምሥጢረ ቀንዲል .............................................................................................. 177
10.1 የምሥጢረ ቀንዲል የቃሉ ትርጉም ................................................................ 177
10.2 የምሥጢረ ቀንዲል አመሠራረት .................................................................... 178
10.3 የምሥጢረ ቀንዲል አፈጻጸም ........................................................................ 179
10.4 በየብልቃጡ እየተሞላ የሚሸጠው “ዘይት” ምስጢረ ቀንዲልን ይተካልን? .......... 180
10.5 ምሥጢረ ቀንዲል የሚያስገኘው ጸጋ .............................................................. 180
ማጠቃላያ (ምክረ አበው) ........................................................................................... 183

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | IX
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

1. አንቀጸ መድኃኒት ቤተ ክርስቲያን


1.1 የቤተ ክርስቲያን የቃሉ ትርጉም

ቤተ-ክርስቲያን ማለት ከሁለት ቃላት የተገኘ ሲሆን ትርጉምም ቤት ማለት ቤተ ኖረ የሚል


ፍቺ ሲኖረው የሰዎች መኖርያ፣ መጠለያ፣ መሸሸግያ ፣ማረፍያ፣ ማደርያ ከድንጋይ፣ ከጭቃ
የተሰራየሚል ፍቺ ይይዛል፡፡ ክርስቲያን ማለት ደግሞ የክርስቶስ ተከታይ በስሙ የተጠራ
(ሀብተ ወልድና ስመ ክርስትና ያለው)፣ ያመነና የተጠመቀ ማለት ነው፡፡ ቤተ ክረስቲያን
ስንል ደግሞ አምኖ የተጠመቀ የክርስቶስ ተከታይ መኖርያ፣ መጠለያ፣ መሸሸግያና ማረፍያ
ማለት ነው፡፡ አንድም ክርስቲያኖች ለአምላካቸው መስዋዕይት በማቅረብ፣ በጸሎት፣
በስግደት፣ በጾም ከእግዚአብሔር ጋር የሚነጋገሩበትና አምልኮተ እግዚአብሔርን
የሚፈጽሙበት ቤት ማለት ነው፡፡ ፍ.ነገ አንቀጽ 1 ቤተ ክርስቲያን ግን የጸሎት ቤት
ትባላለች፡፡ ቤተ-ክርስቲያን የክርስቶስ ወገኖች ለጸሎትና ለስግደት ለቁርባን የሚሰበሰቡባት፣
ቃለ እግዚአብሔርን የሚሰሙበት፣ ፈጣሪያቸው እግዚአብሔርን የሚያመሰግኑበት፣ ምግባር
ትሩፋት የሚሠሩበት፣ ስለ ኃጢአታቸው ይቅርታ የሚጠይቁበት፣ ንስሓ የሚገቡበትና ሥጋ
ወደሙን የሚቀበሉበት ታቦትና መስቀል ሥዕል ያለበት የክርስቲያን ቤት ባለ ሦስት ክፍል
ማለት ነው፡፡

ምሥጢራዊ /ፍካሬያዊ/ በሆነ መንገድ ሲፈታ ደግሞ የክርስቲያንን ሃይማኖት የሚያመለክት


ይሆናል፡፡ የክርስትና እምነትን የተቀበሉ ምእመናን በጉባኤ /በጋራ/ና በተናጠል የሚጠሩበት
ስያሜ ሆኖ ይፈታል፡፡ ይህ የበለጠ ሲተነተን ደግሞ ቤተ-ወገን፣ ዘር፣ የክርስቲያን ትውልድ
ተብሎ ይተረጎማል፡፡ ይህም ለምሳሌ “ቤተ-ያዕቆብ” ሲል የያዕቆብ ወገን፣ የያዕቆብ ዘር፣
የያዕቆብ ትውልድ፣ ተብሎ ይተረጐማል። ከዚሁ በመነሣት ቤተ ክርስቲያንም የክርስቲያን
ወገን፣ የክርስቲያን ዘር፣ ትውልድ ተብሎ ይተረጎማል፡፡ ይህም ከላይ እንደገለጽነው
በተቀደሰው ቤት የተቀደሰውን አምልኮና አገልግሎት የሚፈጽመውንና የሚፈጸምለትን አካል
የሚያመለክት ይሆናል፡፡ ይህ የትርጓሜ ስልት አብሮን የኖረና የተለመደ አካሄድ ነው፡፡ ከላይ
ካየነው በተጨማሪ ቤተ እስራኤል፣ ቤተ ዳዊት፣ ቤተ ክህነት፣ ቤተ መንግሥት የሚለውን
ማየት ለዚህ በቂ ማስረጃ ነው፡፡

ቤተ ክርስቲያን የሚለው ቃል መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ያለው ነው። ለአጠቃላይ


ዕውቀትም የሚከተለውን መመልከት ይቻላል፡፡ በግሪኩ ኤክሌስያ (Ecclessia) በሚል ቃል
ነው የሚታወቀው። ይህ ቃል በቅዱስ ጳውሎስ መልእክታት ፷፪ ጊዜ፣ በሐዋርያት ሥራ ፳፫
ጊዜ፣ በዮሐንስ ራእይ ፳ ጊዜ፣ በማቴዎስ ወንጌል ፫ ጊዜና በሌሎች መልእክታት ፮ ጊዜ
በድምሩ ፻፲፬ ጊዜ በመጽሐፍ ቅዱስ ተገልጾ እናገኘዋለን፡፡ ይህም ቤተ ክርስቲያን የመጽሐፍ

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 1
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ቅዱስ ዋነኛ የትኩረት ነጥብ መሆኑን ይጠቁመናል። ቤተ ክርስቲያን አትበየንም ነገር ግን


ብዙ ጊዜ በመገለጫዎቿ አካለ ክርስቶስና ማኅደረ እግዚአብሔር የሆኑት ሁሉ አንድነት
ጉባኤ ተብላ ትጠራለች፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዳለው ራሷ ክርስቶስ በባሕርዩ
ተመርምሮ የማይደረስበት ሆኖ ሳለ ጥቂት እንኳ እናውቅ ዘንድ በብዙ ስም እንደሚጠራው
ሁሉ ቤተ ክርስቲያንም የተለየ ማንነቷን በሚያሳዩ ብዙ ምሳሌያዊ ስሞች ትጠራለች፡፡
ተራራ፣ ሙሽራ፣ ድንግል፣ ሴት ልጅ፣ መካኒቱ ሴት፣ ንግሥት፣ እመቤት፣ ገረድ፣ ገነት፣
የእርሻ መሬት (ባለ ብዙ ምርት) ፣ አበባ፣ በልግ፣ ሁሉንም ትባላለች፡፡

ቤተ ክርስቲያን ስለሚለው ድርብ ቃል እያንዳንዱ ምእመን የራሱ የሆነ ግንዛቤ ይኖረዋል፡፡


ስለዚህ ረቂቅነትን ከግዙፍነት፣ መታየት መጨበጥና ከመሰወር፣ መወሰንን ከምልዓት ጋር
እንደ ራሷ እንደ ጌታዋ እንደ ክርስቶስ የያዘች ስለሆነች ምሥጢር ትባላለች እንጂ፡፡ በቤተ
ክረስቲያን የሚፈጸመው ሥረዓተ አምልኮት በሙሉም ምሥጢር ነው፡፡ ይህም ማለት
በአመክንዮና በፍልስፍና የማይደረስበት ረቂቅ ጸጋ እግዚአብሔር የሚገኝበት፤ አፍአዊ በሆነ
ነገር ሁሉ ልንተረጉመው የማንችለው ስለሆነ ምሥጢር ልትባል ትችላለች፡፡ ምሥጢራቷም
ለመንጻት፣ ለማየት ለመብቃት፣ እና ለባሴ ክርስቶስ ለመሆን በደረጃ የሚያደርሱ ናቸው፡፡

በአጠቃላይ ቤተ-ክርስቲያን፡-
 በክርስቶስ ደም በቅዱስ ጴጥሮስ የምስክርነት ቃል ዐለት ላይ ተመስርታለች
 በምድር ያለች የእግዚአብሔር ቤተ-መንግስትና የፀጋዉ ግምጃ ቤት ናት
 ምዕመናንን ከእግዚአብሔር ጋር የምታገናኝ ድልድይ ናት
 ለመጀመሪያ ጊዜ በፊልጵስዮስ የተመሰረተች ናት
 ከመላዉ ዓለም በጥፋት ዉስጥ ያሉትን የምትዋጅ የድነት ወደብ መርከብ ናት

1.2 የቤተ ክርስቲያን አመሠራረት


ቤተ ክርስቲያንን የመሠረታት ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ በቂሳርያ ሳሉ
ደቀመዛሙርቱን “ሰዎች የሰውን ልጅ ማን ይሉታል?” በማለት በጠየቃቸው ጊዜ ሐዋርያት
እንደገለጹት ሰዎች ስለእሱ ማንነት የሰጡት መልስ ትክክለኛ አልነበረም፡፡ “እናንተስ እኔ
ማን እንደሆንሁ ትላላችሁ?” በማለት ደቀ መዛሙርቱ ሲጠየቁ ግን ቅዱስ ጴጥሮስ የሰጠው
ፈጣን መልስ የክርስቶስን ማንነት በሚገባ የገለጠ ነበር፡፡ “አንተ ክርስቶስ የሕያው
እግዚአብሔር ልጅ ነህ” የሚለውን ምላሽ ሰጠ፡፡ በዚህ ጊዜ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “…
አንተ ዓለት ነህ፤ በዚች ዓለትም ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እመሠርታታለሁ፡፡” (ማቴ. ፲፮፥፲፫-
፲፰)። በማለት ቃል ኪዳን ገባ፡፡ይህም ማለት በማይናወጽ ጽኑ መሠረት ማለትም ወልድ
ዋሕድ በምትል እምነት /ትምህርት/ ላይ የክርስትና ሃይማኖትና ቤተ ክርስቲያን መታነፅዋን
ያሳያል፡፡ በዓለት ላይ የተመሠረተ ቤት በነፋስ በጎርፍና በልዩ ልዩ ፈተና እንደማይፈርስ
ሁሉ በቅዱስ ጴጥሮስ የምስክርነት ቃል ላይ ክርስቶስ የመሠረታት ራሱን አሳልፎ የሰጠላት
በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)
ገጽ | 2
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ቤትም በኑፋቄ ነፋስና በክህደት ጉርፍ የማትንበረከክ ልዩ ልዩ የፈተና ማዕበላትን ተቋቁማ


ልጆቿን ወደ ዕረፍት ወደብ መንግሥተ ሰማያት የምታደርስ መሆኗን ያስገነዝበናል። (ማቴ
፯፥፳፬-፳፮)።

1.3 የቤተ-ክርስቲያን ዓላማ


1. ቤተ-ክርስቲያን በምድር ያለች የእግዚአብሔር መንግሥት ስለሆነች ለህዝብ ብዛትና
ለሀገር ስፋትን ለአዝመራ በረከትን፣ ለአስተዳደር ፀጥታን የምትሰጥ እንዲሁም
በጠቅላላዉ ለዓለም ሰላምን፣ ፍቅርን፣ አንድነትን እግዚአብሔር እንዲሰጥ መጸለይ፡፡
2. ለኃጥአት ርቆ የነበረዉን ሰዉ ማቅረብ፣ ከእግዚአብሔር ጋር ለማስታረቅ
በምዕመናንና በእግዚአብሔር መካከል መገናኛ ድልድይ መሆን፡፡
3. ምስጢራትን ለሚፈልጉ ሰዎች ስርዓትንና ዘመንን ሳይወስኑ ማደል፣ ጸጋን፣
ልጅነትን፣ ሀብትን፣ ረድኤትን ከእግዚአብሔር መስጠት
4. ቤተክርስቲያን የፀጋዉ ግመጃ ቤት ትባላለችና ከመናፍቃን ጋር እየተዋጋች
እዉነተኛዉን እምነት እየጠበቀች ድኅነት ለምዕመናን ማደል
5. የእርሷ መሪዎች ፍጹም መንፈሳዉያን በማድረግ የምትመራበትን ሕግ ፍጹም
መንፈሳዊ ሕግ ማድረግ

1.4 ቤተ ክርስቲያን የማን ነች? ለማን ተሰጠች?


ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋውን ቆርሶ፣ ደሙን አፍስሶ፣ አሮጌውን
የምሥጢር ሥርዓት አድሶ በቅዱሳን ነቢያት ትንቢትና በቅዱሳን ሐዋርያት ትምህርት፣
የክህነት ሥልጣንና አገልግሎት /ሥራ/ ላይ ቅድስት ቤተ ክርስቲያኑን መሥርቷታል፡፡ (ሐዋ.
፳፥፳፰ ኤፌ. ፪፥፳) ዮሐ. ፳፥፳፩-፳፪ ማቴ. ፲፰፥፲፰)። ክርስቲያን ልጆቻቸውም በዚህች ቤተ
ክርስቲያንም ጥላ ሥር ለቅዱሳን አበውና እማት አንድ ጊዜ የተሰጠች ሃይማኖትን
አጽንተው እየተጋደሉ ይኖሩባታል። (ይሁ ፫.) በኋላም ወደ መንግሥተ ሰማያት
ይሸጋገሩባታል፡፡ ስለዚህ ቤተ ክርስቲያን ሀብተ ወልድና ስመ ክርስትና ላላቸው ክርስቲያኖች
ሁሉ ቤታቸው ናት፡፡ ማናቸውም ዓይነቶች ምድራዊ ልዩነቶች በቤተ ክርስቲያን አባልነት፣
በክርስቶስም አካልነት ጣልቃ የመግባት አቅም አይኖራቸውም፡፡ የፖለቲካ፣ የብሔር
(ብሔረሰብ)፣ የቋንቋ፣ የቀለም፣ የጤና፣ የኢኮኖሚ፣ የሥልጣንና የመሳሰሉት ልዩነቶች ሁሉ
በቤተ ክርስቲያን ዘንድ ተቀባይነት የላቸውም። ቤተክርስቲያን በሁሉም ያለች፣ የሁሉምና
ለሁሉም ናት፡፡ በቤተ ክርስቲያኒቱ ትምህርት እስካመነ ድረስ በሌሎች ልዩነቶች ምክንያት
ለይታ የምታቀርበውና የምታርቀው የተለየ ወገንና አባል የላትም።

1.5 የቤተ ክርስቲያን ኦርቶዶክሳዊነት


ኦርቶዶክሳዊነት Orthodox Doxa – belief and glorification፣ Right doctrine and
right glorification ይህም ማለት የርትዕት ሃይማኖት እና የርቱዕ አምልኮተ እግዚአብሔር

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 3
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

አንድነት ነው ማለት ነው ይላሉ፡፡ (Metropolitan of Nafpaktos Hierotheos) ፡፡


ስለዚህም ኦርቶዶክሳዊነት ማለት ትክክለኛ እምነት እና እውነተኛና ትክክለኛ አምልኮተ
እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡ ምክንይቱም ያለ ትክክለኛ እምነት ትክክለኛ አምልኮት ሊኖር
አይችልም፤ ያለ ትክክለኛ አምልኮት ደግሞ የፈጣሪና የፍጡር ግንኙነት ወይም ውሕደት
ሊኖር አይችልም፤ ያለ ግንኙነት ደግሞ ደኅነት ሊኖር አይችልም፡፡ ያለ ድኅነት ደግሞ
ሃይማኖት ትርጉም ሊኖረው አይችልም፡፡ ስለዚህ የነገር ሁሉ መጀመሪያው ትክክለኛውን
እምነትና አምልኮተ እግዚአብሔር ማግኘት ይሆናል ማለት ነው፡፡

ለሰው እምነቱ የማያድነው ከሆነ ደግሞ እምነቱ ትክክል አይደለም ማለት ነው፡፡ ስለዚህ
ትክክለኛው እምነትና ትክክለኛው አምልኮተ እግዚአብሔር የቱ ነው ወይም የኦርቶዶክሳዊነት
መገለጫዎች ምን ምን ናቸው የሚለውን ጥያቄ እንድናነሣ ቤተ ክርስቲያን ተብላ
የምትጠራው አካለ ክርስቶስም እነዚህን ማሟላት አለማሟላቷን ለመመርመር እንገደዳለን፡፡
ለምን ይህ ከሌለ ያች ቤተ ክርስቲያን አካለ ክርስቶስ ሳትሆን እንደ ማንኛውም ሰዎች
የሚያቋቁሟቸው ተቋማት ድርጅት ብቻ ትሆናለችና፡፡ ስለዚህ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን
ስንል ኦርቶዶክሳዊነትን ገንዘብ ያደረገች አካለ ክርስቶስ ማለት ነው፡፡ አካለ ክርስቶስ ከሆነች
ኦርቶዶክሳዊ ናት፤ ኦርቶዶክሳዊ ሆና አካለ ክርስቶስ ያልሆነች የለችም፤ ልትኖርም
አትችልም፡፡

1.6 ቤተ ክርስቲያን ከሌሎች ዕምነቶች የሚለያት


 በተቀደሰዉ ቤት (በዉስጧ) የሚኖሩ የተቀደሱ ንዋያት ስላሏት ታቦተ
(እግዚአብሔር፣ መስቀለ ክርስቶስ፣ ቅዱሳት መጻሕፍት፣ ቅዱሳት ሥዕላት፣ ንዋያተ
ቅዱሳት፣ የማኅሌት/ዝማሬ ንዋያትና የመሳሰሉት ናቸው፡፡)
 በተቀደሰዉ ቤት የሚፈፀሙ ሰባቱ ምስጢራተ ቤተ-ክርስቲያን ስላላት
 በተቀደሰዉ ቤት የሚቀርብ አገልግሎት ስላላት (ማኅሌት፣ ሰዓታት፣ ኪዳን፣ ቅዳሴ፣
መዝሙር፣ ቅኔ፣ ስብከተ ወንጌልና የመሳሰሉት ሁሉ ናቸው፡፡

1.7 የቤተ ክርስቲያን ባሕርያት


የቤተ ክርስቲያን ባሕርያት ማለት የእውነተኛው ቤተ ክርስቲያን መታወቂያ (መገለጫ)
የሆኑ ምልክቶቿ ናቸው፡፡ በአንቀጸ (ጸሎተ) ሃይማኖት ከሠፈሩት አስተምህሮዎችና
ውሳኔዎች መካከል አንዱ የቤተ ክርስቲያንን ባሕርያትና ደረጃዎች በግልጽ የሚያስቀምጠው
ዐረፍተ ነገር ነው፡፡ ይህም “ከሁሉ በላይ በምትሆን ሐዋርያት በሰበሰቡዋት በአንዲት ቅድስት
ቤተ ክርስቲያን እናምናለን፡፡” የሚለው ነው። ከዚህ ክፍለ ንባብ በመነሣት የቤተ ክርስቲያንን
ባሕርያት እንደሚከተለው እናብራራለን፡፡ በዚህ ዐረፍተ ነገር /ኃይለ ቃል/ ውስጥ የቤተ
ክርስቲያን ባሕርያት በተሟላ መንገድ በሥርዓት ተሰድረውና ተሟልተው እናገኛቸዋለን፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 4
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ሀ/ አንዲት፡- እግዚአብሔር አንድ ነው፤ የክርስቶስም ማዳን አንዲት ናት፤ ተስፋ


የምናደርጋት መንግሥተ ሰማያት አንዲት ናት፤ የምንቀበለው የክርስቶስ ቅዱስ ሥጋና
ክቡር ደምም አንድ ነው፡፡ በአጭር አገላለጽ የተገለጠው እውነት ከነማብራሪያው አንድ ነው፡፡
ይህን የምታስተምር ቤተ ክርስቲያንም አንዲት ናት፡፡ የክርስቶስ አካል ስለሆነች አንዲት
ናት፡፡ የክርስቶስ አካል አይከፈልምና ቤተ ክርስቲያን አንዲት እንጂ ብዙ አይደለችም፡፡ ይህቺ
አንዲት ቤተ ክርስቲያን ተአምኖዋ በአንድ እግዚአብሔር ስለሆነ መለያየት አይስማማትም፡፡
ምእመናኗም አንድ ትምህርት ይማራሉ፤ አንድ እምነት ያምናሉ፤ አንድ ጥምቀት
ይጠመቃሉ፡፡ ሰዎች ወይም መላእክት ከእርሷ ውጪ ወጥተው በክሕደት በኃጢአት ሊሔዱ
ይችላሉ፡፡ ነገር ግን ሌላ ቤተ ክርስቲያን ሊመሠርቱ አይችሉም፡፡ እንመሥርት ቢሉም
የመሠረቱት ስብስብ ቤተ ክርስቲያን ተብለው ሊጠሩበት አይችሉም ምክንያቱም ከክርስቶስ
የተለየች ቤተ ክርስቲያን የለችምና፡፡ ሰዎች በተለያየ መንገድ ከአንዲቷ ማኅበር ቢወጡም
ቤተ ክርስቲያን ተከፋፈለች አይባልም፡፡ አንተ ዐለት ነህ በዚች ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን
እሠራታለሁ አለ እንጂ ቤተ ክርስቲያኖቸን አሠራቸዋለሁ አላለም፡፡ ማቴ 16፤ 18
በአጥቢያዎች መብዛት በሲኖዶሶች መብዛት የተነሣ የተከፋፈለች ልትሆን አትችልም፡፡
አስተዳደራዊና የአገልግሎት አሠጣጡ ተከፋፈለ እንጂ ክርስቶስ አልተከፋፈለምና
ብሔራዊነትን መሠረት አድረጋም አትሠራም፤ በሁሉ ያለች ለሁሉ የተሰጠች መሆኗን ረስቶ
በአንድ መንግሥት አስተዳደር ሥር ብቻ መወሰን በራሱ ኑፋቄ ነው፡፡ አንድነቷ በእምነትና
በምሥጢራት የሚገኝ እንጂ በአስተደደርና በመሳሰለው ሊደረስበት ሊገኝም አይችልም፡፡
ቤተ ክርስቲያን በውስጧ ቅዱሳን መላእክትን እንዲሁም በብሔረ ሕያዋን፣ በብሔረ ብፁዓን፣
በገነት፣ በዐጸደ ሥጋና በዐጸደ ነፍስ ያሉትን ምእመናን ሁሉ የምትይዝ አንዲት ኅብረት
ናት፡፡ (ዕብ. ፲፪፡፳፪-፳፬) ፡፡ በዐጸደ ነፍስ ያሉት ምእመናን በንስሓ የተመላለሱ፣ ሩጫቸውን
የጨረሱና ድል ያደረጉ ሲሆኑ፥ በዐጸደ ሥጋ ያለን ደግሞ ሩጫችንን ገና ያልጨረስንና
በተጋድሎ ውስጥ የምንገኝ ነን፡፡ ሐዋርያው እንዲህ እንዳለ፡- “እንዲሁ ብዙዎች ስንሆን
በክርስቶስ አንድ አካል ነን” (ሮሜ. ፲፪፡፭) ፡፡ በቤተ ክርስቲያን ምንነትና ማንነት ላይ ያለን
ልዩነት ለጠቅላላ ነገረ ሃይማኖት መለያየት ምክንያት ስለሚሆን ይሆናሉ፡፡ ይህን
የሚያስረዱ ሁለት ማሳያዎችን በማንሣት እንመልከት፡፡

፩. በካቶሊካውያን ዘንድ አንድ ሰው የፖፑን የክርስቶስ እንደራሴነት ካልተቀበለ የካቶሊክ


ቤተ እምነት አባል አይሆንም፡፡ በኦርቶዶክሳዊ ትምህርት ግን ቅዱሳን መላእክት እንዲሁም
በብሔረ ሕያዋን፣ በብሔረ ብፁዓን፣ በገነት፣ በዐጸደ ሥጋ ያለንና በዐጸደ ነፍስ የሚኖሩ
ምእመናን አንድ የምንሆነው በክርስቶስ ኢየሱስ አካልነት ነው፡፡ ይህም በቅዱስ ሥጋውና
በክቡር ደሙ የምናገኘው ጸጋ ነው፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 5
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

፪. በፕሮቴስታንቱ ዓለም ያለውን ስንመለከት ደግሞ በዐጸደ ሥጋ ያሉትና በዐጸደ ነፍስ


ያሉት አማኞች የተለያዩ ናቸው፤ እርስ በርሳቸው አይተዋወቁም፡፡ በሌላ አገላለጥ እንደ እነሱ
አባባል “ቤተ ክርስቲያን የሚታዩ አባላት ብቻ ያሏት ተቋም ናት” ፡፡ የቅዱሳንን ምልጃ
የማይቀበሉትም ስለዚሁ ነው፡፡ ይህም ሐዋርያው ጳውሎስ ከላይ ከነገረን (ዕብ. ፲፪፡፳፪-፳፬)
የእውነት መሠረት የተለየ ትምህርት ነው፡፡ ዳግመኛም ይህ የፕሮቴስታንቶቹ አስተምህሮ
(አይቻልም እንጂ) ስሙ ይክበር ይመስገንና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አንድ ያደረገ፡፡

ለዚህም ትምህርተ ሃይማኖታቸው አንድ የሆነውን አምስቱን እኀትማማች አብያተ


ክርስቲያናትን አብነት ማድረግ እንችላለን። በተለያየ ፓለቲካዊና መልክዓ ምድራዊ
አቀማመጥ እንደመገኘታቸው አምስቱም ልዩ ልዩ የቤተ ክርስቲያን አስተዳደር መጠነኛ
ልዩነት ያለው የአፈጻጸም ሥርዓት አላቸው፡፡ ይህም ወደ ክርስትና የመጡበትን የቀደመ
የአምልኮ ሕይወት መሠረት ያደረገ ነው። ይሁን እንጂ የክህነት መሠረታቸው ከክርስቶስ
የተገኘ አንድ ሐዋርያዊ ሥልጣንና መንበር ነው፡፡ ትምህርታቸው በነቢያት ትንቢት፣
በክርስቶስ ፈጻሚነትና በሐዋርያት ስብከት ላይ የተመሠረተ አንድ ነው፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ
ያለውን እውቀት በመቀበል፣ በመመስከርና በመኖር በምሥጢራትም ጸጋ እግዚአብሔርን
በማደል አንድ ናቸው። በየጊዜው የተነሱ ልዩ ልዩ ኑፋቄያትን በመቃወምና መናፍቃንንም
በማውገዝ ልዩነት የለባቸውምና የአንዲት ቤተ ክርስቲያን ቅርንጫፎች ናቸው።።

ለ/ ቅድስት፡- ቤተ-ክርስቲያንን የመሰረታትና በተቀደሰ ደሙ ያነጻት ቅዱስ ስለ ሆነ


ማደሪዉም በዕዉነት ቅድስት ናት፡፡ ይህችም በበዓለ ሃምሳ ቅድስና የበሕሪ ገንዘቡ የሆነዉን
መንፈስ ቅዱስን በተቀበለች ጊዜ ፈፅሞ ቀድሷታል፡፡ በውኃ መታጠብና ከቃሉ ጋር አንጽቶ
እንዲቀድሳት ስለ እርስዋ ራሱን አሳልፎ ሰጠ፤ ኤፌ 5 ፤26 የቅዱሳን አንድነት ናት፤ ያለ
ቅድስናም ሊቀላቀሉባት አይችሉም፡፡ ስለዚህም ልጆቼን ከዕዳ አውጥልኝ እያለች
ትለምንላቸዋለች፡፡ አንድም በአንቀጸ ሃይማኖት የሰፈረው ሁለተኛው የቤተ ክርስቲያን
መገለጫ ቅድስት የሚለው ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያንን የመሠረታት፣ በተቀደሰው ደሙ ያነጻት
ክርስቶስ ቅዱስ ስለሆነ ማደሪያውም በእውነት ቅድስት ናት፡፡ (ኤፌ. ፭፥፳፮)፡፡

በበዓለ ሃምሳ ቅድስና የባሕርይ ገንዘቡ የሆነውን (የቅድስና ባለቤት) መንፈስ ቅዱስን
በተቀበለች ጊዜም ፈጽሞ ቀድሷታል፡፡ የቅዱስ እግዚአብሔር የተቀደሰች ማደሪያው
በመሆኗም የቅድስናና የጸጋው ሁሉ መዝገብ ለመሆን ችላለች፡፡ የአገልጋዮቿ (የአባላቷ)
በኃጢኣት መሰነካከል ቅድስናዋን አያረክሰውም፤ መንፈሳዊ ውበቷንም አያቆሽሸውም ፡፡
ይልቁንም እነሱን በንስሐ አንጽታ ወደ ቀደመ ክብራቸው እንዲመለሱ በቅድስና
ታከብራቸዋለች፡፡ ለእርሷ የሚቀርበው መሥዋዕትና አገልግሎት ሁሉ የተቀደሰ ነው፡፡ “እርሱ

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 6
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

አካሉ የሆነች ቤተ ክርስቲያን ራስ ነው፤” (ቈላ. ፩፥፲፰)። ተብሎ እንደተጻፈው ራሷ ቅዱስ


በመሆኑ አካሉ የሆነች ቤተ ክርስቲያንም ቅድስት ነች፡፡

“ነገር ግን የጠራችሁ ቅዱስ እንደሆነ እንዲሁ እናንተም በአካሔዳችሁ ሁሉ ቅዱሳን ሁኑ፡፡


“እኔ ቅዱስ ነኝና ቅዱሳን ሁኑ” የሚል ተጽፏልና፡፡” (፩ጴጥ. ፩፥፲፭-፲፯) በማለት ቅዱስ
ጴጥሮስ ያስተላለፈልን መልእክት ፍጻሜውን ሊያገኝ የሚችለው በዚችው ቅድስት ቤተ
ክርስቲያን በኩል ብቻ ነው። ለዚህ የተጠሩ የምድራውያን (በአጸደ ሥጋ ያሉ) ክርስቲያኖችና
የሰማያውያን (በአጸደ ነፍስ ያሉ) ቅዱሳን ኅብረት መሆኗም የቅድስናዋ ሌላው መታወቂያዋ
ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያንን የናቁና በብልሹ ሥነ ምግባር በድፍረትም የተመላለሱ ቢገኙ እንደ
ዳታን አቤሮንና ቆሬ (ዘኁ ፲፮) ፣ እንደ ሐናንያና ሰጲራም (ሐዋ ፭፥፩-፲፭) ፣ በእግዚአብሔር
ቸርነትና ትዕግሥት ከተጎበኙ በኋላ ይቀጡና ይወገዳሉ እንጂ ቤተ ክርስቲያን በኃጢአታቸው
አትረክስም፡፡ አንድ አካባቢ ያለች አንዲት አጥቢያ ለሌላው ተግሣጽ ብትጠፋም እንኳን ቤተ
ክርስቲያን ግን የሲኦል አበጋዞች ሳያሸንፏት በቅድስናዋ ትቀጥላለች። (ማቴ ፲፮፥፲፰) ።

ሐ. ኩላዊት (ዓለም አቀፋዊት)፡- ሦስተኛው የቤተ ክርስቲያን መታወቂያ በአንቀጸ ሃይማኖት


“ከሁሉ በላይ በምትሆን” ተብሎ የተገለጸው ኲላዊነቷን የተመለከተ አንቀጽ ነው፡፡ ይህም
ቤተ ክርስቲያን ምንም ዓይነት የቀለም፣ የጤና ሁኔታ፣ የትምህርት ደረጃ፣ የቋንቋ፣ የጾታ፣
የሀብት፣ የመልክአ ምድርና ማንኛውም ልዩነት ሳያግዳት በየትኛውም ሀገር የምትገኝ ዓለም
አቀፋዊት ቤተ እግዚአብሔር መሆኗን የሚያሳይ ነው፡፡ ቆላ 3÷1 “በእርሱ ዘንድ አይሁዳዊ፣
ግሪካዊ፣ የተገዘረ፣ ያልተገዘረም፣ አረመኔም፣ ባላገርም፣ ቤተሰብና አሳዳሪ ማለት የለም ነገር
ግን ክርስቶስ በሁሉም ዘንድ ነዉ፡፡” በማለት ኩላዊነቷ ከቦታ አንጻር ብቻ ሳይሆን ከጊዜም
አንጻር መሆኑን ያስረዳል፡፡ በሁሉም ያለች (በቦታ የማትወሰን) ፣ ሁሉንም እውነት
አጠቃልላ የያዘች (ኦርቶዶክሳዊት እንደማለት ያለም ነው) ፣ ለሁሉም አማኞች የምትሰጠው
ሕይወትም አንድ ዓይነት ነው (ጥምቀቱ፣ ቁርባኑ፣ ጸበሉ፣ ተክሊሉ፣ …)፣ አማኞቿም
የሚኖሩት ኩላዊት በሆነው አእመሮዋና አስተሳሰቧ፡፡ ዓለም አቀፋዊነት ሙሉ በሙሉ
ምድራዊ የሆነችዉን የዚህች መሬት(ዓለም) ዜጎች የሚያቅፍ የምድራዊ ህብረት መገለጫ
ሲሆን ኩላዊነት ግን ምድራዉያንና ሰማዉያን የቤተክርስቲያን አባላት (የቅዱሳን አንድነት)
ጨምሮ የሚያቅፍ ላቅ ያለ ትርጉም ያለዉ የቤተክርስቲያን አንዱ ባሕርይ (መገለጫ) ነዉ፡፡
የሰዉን ልጆች ሁሉ ወደ ድኅነት የምትጠራ፣ የምተቀበል፣ የምትመግብ፣ የምታሳድግና
ለፍሬ የምታበቃ እመብዙኃን (የብዙዎች እናት) በምድር ያለች የእግዚአብሔር ቤተ-
መንግሥት እንዲሁም ሰማይና ምድርን የምታገናኝ በመሆኗ ኩላዊተ ናት፡፡

ኵላዊት (ካቶሊክ፣ Universal) የሚለው አገላለጽ በምዕራባውያን (በካቶሊካውያን) አስተሳሰብ


የተለየ ትርጕም አለው፡፡ በምዕራባውያን ዘንድ ለቤተ ክርስቲያን ኵላዊት መሆን ዋናው

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 7
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

መሠረቱ ለሮሙ ፖፕ መታዘዝ ነው፡፡ በእነርሱ አስተሳሰብ መሠረት የማይሳሳትና የክርስቶስ


ወኪል አድርገው ለሚቈጥሩት ለፖፑ የማትገዛ ቤተ ክርስቲያን ኵላዊት አይደለችም፡፡
በምሥራቃውያንና በኦሬንታል ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ደግሞ ቤተ ክርስቲያንን
ኵላዊት የሚያሰኛት ሥላሴ በአንድነት በሦስትነት የሚመለኩባት፣ ከሐዋርያት ጀምሮ
ባልተቋረጠ ክትትል ጳጳስ ያላትና የክርስቶስ ሥጋና ደም የሚፈተትባት መሆኗ ነው፡

ኵላዊትነት በምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን አንድነት (በተለይም በቅዱስ ቊርባን) እንጂ


በፖፕ አንድ መሆን አይደለምና፡፡ ቅዱስ አግናጥዮስ ምጥው ለአንበሳ ወደ ስሚርናስ በላከው
መልእክቱ እንደተናገረው፥ ቤተ ክርስቲያን ኵላዊት (ፍጽምት፣ ርትዕት፥ ሁሉንም የምትይዝ)
የምትባለው ቅዱስ ሥጋውና ክቡር ደሙ የሚፈተትባት በመሆኗ ነው፡፡ ዚህ ቅዱስ
ምሥጢር አማካይነት በየትኛውም ሥፍራ የምንኖር ክርስቲያኖች (በግብፅም፣
በኢትዮጵያም፣ በሰማይም፣ በምድርም) አንድ ወደ መሆን፣ ወደ ፍጽምና፣ ወደ እውነት
እንመጣለን፡፡ በመሆኑም ያለዚህ ምሥጢር ቤተ ክርስቲያን ኵላዊት አትባልም፡፡ በዚህም
የሐዋርያውያነ አበው ትምህርት መሠረት ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን “አማናዊ
አይደለም፤ አምሳል ነው” የሚሉ ሰዎች ስብስባቸው ቤተ ክርስቲያን እንዳልሆነ እንረዳለን፡፡
“በእርሱ ዘንድ አይሁዳዊ፣ ግሪካዊ፣ የተገዘረ፣ ያልተገዘረም፣ አረመኔም፣ ባላገርም፣ ቤተሰብ
እና አሳዳሪ ማለት የለም፤ ነገር ግን ክርስቶስ ለሁሉ በሁሉም ዘንድ ነው፡፡” (ቈላ. ፫፥፲፩)

የቤተ ክርስቲያን ዓለም አቀፋዊነት ኲላዊነት ከቦታ አንጻር ብቻ የሚታይ ሳይሆን ከጊዜም
አንጻር የሚብራራ ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን በቦታ ብቻ ሳይሆን በጊዜም የማትወሰን በመሆኗ
በብሉይ ኪዳን የነበሩትን አበውና እማት ጨምሮ ከሐዋርያት ጀምሮ እስከ ምጽአት ያሉትን
ምእመናን ልጆቿን ሁሉ አካታ /ሁሉንም በማጠቃለል/ የያዘች እናት ናት፡፡ የቤተ ክርስቲያን
አባሎቿ በሁለት ይከፈላሉና፡፡ የመጀመሪያዎቹ በአጸደ ሥጋ ያሉት ተዋጊዎች፣ ሰልፈኞች
የሆኑት ሲሆኑ፤ ሁለተኞቹ ደግሞ በአፀደ ነፍስ የሚገኙ አሸናፊዎች፣ ድል አድራጊዎች
የሆኑት ናቸው፡፡ በዚህም መሠረት የቤተ ክርስቲያን ኲላዊነት በሰማይም በምድርም፣
በብሉይ ኪዳንም በሐዲስ ኪዳንም ያሉትን ሁሉ የሚያጠቃልል መሆኑን ማስተዋል ይገባል፡፡
ከላይ እንደገለጽነው የቤተ ክርስቲያን መሥራቿና ራሷ ክርስቶስ በሰማይ፣ በምድርና
በሁሉም ቦታ ይኖራል፡፡ እሱ የሌለበትና የማይኖርበት ቦታ እንደሌለ (እንደማይኖር) ሁሉ
አካሉ ቤተ ክርስቲያንም የሌለችበትና የማትኖርበት ቦታ አይኖርም፡፡

ኲላዊነቷ (ዓለም አቀፋዊነቷ) የሚመነጨው ከዚህ እውነት ነው፡፡ ኲላዊነት ቤተ ክርስቲያን


እንዲህ የሁሉ እናት ሆና በሞት የለያዩትን፣ በቦታና በጊዜ የተራራቁትን በመንፈስ ቅዱስ
ጸጋ አቀራርባ በአንድ ጊዜና ቦታ እንደምታድማቸው፤ (እንደምትሰበስባቸው) የሚያሳይ
ምሥጢራዊ ቃል ነው። ዓለም አቀፋዊነት ሙሉ ለሙሉ ምድራዊ የሆነችውን የዚችን
መሬት (ዓለም) ዜጎች የሚያቅፍ የምድራዊ ኅብረት መገለጫ ሲሆን ኲላዊነት ግን
በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)
ገጽ | 8
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ምድራውያንና ሰማያውያን የቤተ ክርስቲያን አባላት (የቅዱሳንን አንድነት) ጨምሮ


የሚያቅፍ ላቅ ያለ ትርጉም ያለው የቤተ ክርስቲያን አንዱ ባሕርይ (መገለጫ) መሆኑን
ማስተዋል ይገባል።

መ/ ሐዋርያዊት፡- በአንቀጸ ሃይማኖት “ሐዋርያት በሰበሰቧት” ተብሎ መገለጹ ቤተ


ክርስቲያን ሐዋርያዊት መሆኗን የሚያስረዳ ኃይለ ቃል ነው፡፡ ከክርስቶስ በኋላ በሐዋርያት
ትምህርትና ስብከት ተስፋፍታለችና የሐዋርያት ትምህርት ተቀብላ ስታስተምር ትኖራለችና
የመሪዎቿ የጳጳሳት ሥልጣነ ክህነት ሳይቋረጥ ከሐዋርያት የተያያዘነዉና የሐዋርያት ጉባኤ
ተብላ ትጠራለች፡፡ ምክንያቱም አምላካችን ክርስቶስ ያወቁትን፣ ያመኑበትን፣ ያዩትን፣
የሰሙትን፣ በእጆቻቸው የዳሰሱትን ለዓለም እንዲያስተምሩና እንዲመሰክሩ የቤተ
ክርስቲያንን ተግባርና ሓላፊነት ለቅዱሳን ደቀ መዛሙርቱ ሰጥቷቸዋል፡፡ (፩ጢሞ፩፥ ፭) ፡፡
እነርሱን የሰማ እርሱን እንደሚሰማ፤ እነርሱን እንቢ ያለም እነርሱን እንቢ እንደሚል ገልጾ
በቤተ ክርስቲያን ላይ ባለ ሙሉ ሥልጣን አድርጎ ሾሟቸዋል፡፡ (ማቴ. ፲፥፵። ማር. ፱፥፴፯
ሉቃ. ፲፥፲፮ ዮሐ. ፲፫፥፳) እነርሱም ድውያነ ሥጋን በተአምራት፣ ድውያነ ነፍስን በትምህርት
እየፈወሱ ዓለምን ዕጣ በዕጣ ተካፍለው በወንጌል መረብነት ምእመናንን በውቅያኖስ
ከተመሰለው ዓለም ሰበሰቡ፡፡

“ሐዋርያዊት” የሚለው ቃል ለእውነተኛይቱ ቤተ ክርስቲያን መገለጫ ባሕርይዋ፣ አርማና


ምልክቷ ነው፡፡ ትውፊቷ፣ ትምህርቷ፣ ሥርዓቷና ሥልጣነ ክህነቷ ከአባቶቻችን ከሐዋርያት
ተያይዞ የመጣና ሰንሰለቱ ያልተቋረጠ፣ ዛሬ ከኛ ዘመን የደረሰና ነገም እስከ ምጽአት የሚጓዝ
በመሆኑ ቤተ ክርስቲያን ሐዋርያዊት ተብላለች፡፡ እነዚህን የቤተክርስቲያን ባሕርያት ማወቅ
ምእመናን በቤተክርስቲያን እንዲኖሩ ኋላም የመንግሥተ ሰማያት እድምተኞች እንዲሆኑ
ያነሳሳቸዋል። ሐዋርያዊ ትውፊት፣ ትምህርት፣ ሥርዓትና ሥልጣነ ክህነት ሳይኖር ቤተ
ክርስቲያን ልትኖር አትችልምና።

1.8 የቤተ ክርስቲያን ምሳሌ በሐዲስ ኪዳን


1. ገነት- አዳም ትዕዛዘ እግዚአብሔርን አፍርሶ ከመበደሉ በፊት በቤተ እግዚአብሔር በገነት
ይኖር ነበር። በገነትም እግዚአብሔር ለአዳም ያለው ፍቅሩ ጠባቆቱ ተገልጦበታል። አዳምም
በጸሎት ሕይወት ኖሮበታል። ይህቺ የአዳም የመጀመርያ ቤቱ ገነት ለቤተ ክርስቲያን ምሳሌ
ናት። (Church The House of God)

2. ሐመረ ኖኅ (የኖኅ መርከብ): - ሰዎች በበበደላቸው ምክንያት በጥፋት ውሃ ሲደመሰሱ


ኖኅና ቤተሰቡ ከጥፋት የዳኑባት ናት ቤተ ክርስቲያንም ከባሕረ እሳት ከሞተ ነፍስና
ከግብርናተ ዲያብሎስ የምታድን የቤተ ክርስቲያን ምሳሌ ናት። ዘፍ. 6:1-12፤ ዘፍ. 7:1-24

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 9
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

3. ክሕነተ መልከጼዲቅ: - መልከ ጼዲቅ የሳሌም ንጉስ የእግዚአብሔር ካህን አብራምን


ባገኘ ጊዜ ሕብስትና ወይንን አቅርቦ አብራምን ባርኮታል። አብራምም ለዚህ ታላቅ ካህን
ካለው ሁሉ አስራትን አበርክቶለታል። ዘፍ. 14:18-20 ካህኑ መልከ ጼዲቅ የኢየሱስ
ክርስቶስ ምሳሌ አብራም ያቀረበው ኅብስትና ወይን ዛሬ ካህናት በቤተ ክርስቲያን
ለሚያቀርቡት መስዋተ አዲስ ምሳሌ ነበር። መዝ. 109(110):1-4፤ ዕብ. 7:1-28

4. ቤቴል (ቤት ኤል) ፡- ያዕቆብ በፍኖተ ሎዛ ምስጢረ እግዚአብሔርን ያየባት ቤትኤልና


በዚህ ቦታ ላይ መላዕክተ እግዚአብሔር ሲወጡባትና ሲወርዱባት ያያት የብርሃን መሰላል
የእመቤታችንና የቤተ ክርስቲያን ምሳሌ ናት። ዛሬም መላዕክቱ የምዕመናንን ጸሎትና
ትሩፋት ይዘው ወደ እግዚአብሔር ፊት ይወጣሉ ፥ይወርዳሉ። ምዕመናንንም በረድኤቶ
ለመጠበቅ ከመውጣት ከመውረድ አላቋረጡምና።

5. ደብረ ሲና: - ደብረ ሲና ሊቀ ነቢያት ሙሴ 40ቀንና ሌሊትን ጾሞ ሕገ እግዚአብሔር


የተጻፈበትን ጽላት የተቀበለበት ፣ እስራኤል ዘስጋ ሕገ እግዚአብሔርን ጠብቀው ሕዝበ
እግዚአብሔር የተባሉበት ርስተ እግዚአብሔር (መንግስተ ሰማያትን) ለሚወርሱባት ቤተ
ክርስቲያን ምሳሌ ናት።

6. ደብተራ ኦሪት: - ደብተራ ኦሪት ታቦተ ሕግ የኖረባት ሌዋውያን ሕግ የተማሩባትና


ስርዓተ አምልኮ የፈጸሙባት ድንኳን ናት። በዚህም ድንኳን ሰውና እግዚአብሔር ይገናኙባት
ስለነበር የመገናኛ ድንኳን ተብላለች። ዘዳ. 33:7-10

7. ቤተ መቅደስ ምኩራብ (ሲናጎግ): - እንደ ደብተራ ኦሪት ሁሉ እግዚአብሔር


የተመለከበት ህንጻ ነው። ምኩራብ ከክ.ል. በፊት በ956 ዓመት በሰሎሞን ነበር። እጅግ
ባማረና በተዋበ መልኩ የተሰራው ይህ ቤተ መቅደስ ከክ.ል. በፊት በ586 በናቡከደነጾር
እስራኤላውያን ወደ ባቢሎን በተማረኩበት ጊዜ ተመዘበረ ተቃጠለ ፈረሰ። እስራኤል ከመጡ
በኋላም በዘሩባቤል ተጀምሮ ተጠናቋል። ምኩራብ አንድ ብቻ አይደለም ከዘሩባቤል በኋላም
በነሄሮድስ አግሪጳ ሌላ ምኩራብ እንደተሰራ ሌሎች ምኩራብ እንደነበሩ ይታወቃል። (ዋቢ: -
ትምህርተ ሃይማኖት ርትዕት ገጽ:73-74)

1.9 የሕንጻ ቤተ እግዚአብሔር አጀማመር

እግዚአብሔር አምላካችን በዘመናት ሁሉ በወደደው ቦታና ሁኔታ መመስገን ፈቃዱ ነው።


እስራኤልን ከግብጽ ምድር እንዲያወጣ በመረጠውና ታላቅ ነቢይ በሆነው በሙሴ በኩል
“መቅደስ ትሠራልኛለህ በመካከላቸውም አድራለሁ። በተራራው እንዳሳየሁህ ሁሉ፥ እንደ
ማደሪያው ምሳሌ፥ እንደዕቃውም ሁሉ ምሳሌ ለእኔ ትሠራለህ፤ እንዲሁ ትሠራለህ።” /ዘጸ

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 10
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

፳፭፥፰‐፲፡፡/ የሚል መመሪያ አስተላልፏል። በዚህ መመሪያ መሠረት ነቢዩ ሙሴ ደብተራ


ኦሪትን ለመሥራት እንደቻለ የታወቀ ነው፡፡

በአሠራር ሒደቱም ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲደረግ እግዚአብሔር አምላክ ለሙሴ በተደጋጋሚ


“በተራራው ላይ እንዳሳየሁህ ምሳሌ እንድትሠራ ተጠንቀቅ!” የሚል ኃይለ ቃል ይናገረው
ነበር። /ዘጸ፳፭፥፵፤ ፳፮፥፴፤ ፳፯፥፰።/ ይህም ደብተራ ኦሪት እግዚአብሔር ለሙሴ በደብረ ሲና
ተራራ ላይ ባሳየው መቅደሰ ብርሃን (የብርሃን (ሰማያዊ) መቅደስ ሥርዓትና አምሳል (ምሳሌ)
የተዘጋጀች መሆኗን ያረጋግጥልናል። በዚህ መሠረትነትም መቅደሰ ሰሎሞን በደብተራ ኦሪት
አምሳልና ሥርዓት፣ ቤተክርስቲያንም በመቅደሰ ሰሎሞን አምሳልና ሥርዓት የተሠሩ
(የተዘጋጁ) መሆናቸውን እንረዳለን። ይህም በመንፈሳዊ ስሌት ሲሰላ ቤተክርስቲያን ራሷ
በሰማያዊው (ብርሃናዊው) መቅደስና ሥርዓት አምሳል የተሠራች፥ በምድር ላይ ያለች
አማናዊት የእግዚአብሔር መንግሥት እንደሆነች አጉልቶ ያሳያል። (ራእይ ፲፩፥፲፱፤፰፥፫‐፭፡፡)

ቤተ ክርስቲያን የእግዚአብሔርና የክርስቲያኖች የጋራ ቤት ስለሆነች ምእመናን በዚያ


ከፈጣሪያቸውና ከአባታቸው ከእግዚአብሔር ጋር ይገናኛሉ። ቤተ ክርስቲያን እግዚአብሔር
በሕዝቡ መካከል በረድኤቱ፣ በፍቅሩ፣ በቸርነቱና በአካሉ /ሥጋ ወደሙ/ ሊያድርባት
የመረጣት ናትና። “የእግዚአብሔር ተራራ የለመለመ ተራራ ነው፣ የጸና ተራራና የለመለመ
ተራራ ነው። የጸኑ ተራራዎች ለምን ይነሣሉ? እግዚአብሔር ያድርበት ዘንድ የወደደው
ተራራ ይህ ነው፤ እግዚአብሔር ለዘለዓለም ያድርባቸዋልና። የብዙ ብዙ ሺህ የእግዚአብሔር
ሰረገላዎች ደስተኞች ናቸው። እግዚአብሔር በመቅደሱ በሲና በመካከላቸው ነው።” /መዝ፷፯፥
፲፭‐፲፰/፣ “ወደ መቅደሱ ተራራ ወሰዳቸው፥ ቀኙ ወደ ፈጠረችው ተራራ፤” (መዝ፸፯፥፶፬፡፡)
ደብረ ሲና ሰማያዊው ንጉሥ እግዚአብሔር በሰማያዊው መቅደስና ሥርዓት ሆኖ ለሙሴ
የታየባት፣ ያስተማረባትና ከሕዝቡ ጋር መሆኑን ያረጋገጠባት መቅደሱ ነበረችና።
ቤተክርስቲያንም ከመቅደሰ ሰሎሞንም ሆነ ከደብተራ ኦሪት በእጅጉ የምትከብርና የምትበልጥ
መሆኗን ማወቅ አለብን፡፡ /፪ቆሮ፫፥፯‐፲፪፡፡ ዕብ ፰፥፩‐ፍጻሜው።/

1.10 የቤተክርስቲያን ሥሪት

ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን መሠረተ ቃሉ ቤቴ የጸሎት ቤት ይባላል /ቤቴሰ ቤተጸሎት ትሰመይ/


የሚለው /ኢሳ. ፶፮፥፮-፯፤ ኤር. ፯፥፲፩፤ ማቴ. ፳፩፥፲፫፤ ማር. ፲፩፥፲፯፤ ሉቃ. ፲፱፥፵፮፤ ዮሐ. ፪፥
፲፮-፲፯/ ሲሆን ቤተ ክርስቲያን የዋዛ የፈዛዛ፣ የሳቅ የስላቅ፣ የጨዋታ፣ የመብል፣ የመጠጥ
ቤት ሳትሆን፤ ምዕመናን ኃጢአት ቢሠሩ ሰለ ኃጢአታቸው የሚያዝኑባት የሚያለቅሱባት
ንጹሕ የሆነ የእግዚአብሔርን ቃል ካህናት የሚያስተምሩባት፣ ምዕመናን የሚማሩባት የግል
ጸሎት፣ የማኅበር ጸሎት የሚጸልዩባት፣ በኅብረት የሚያስቀድሱባት ሥጋ ወደሙ
የሚቀበሉባት፣ የኃጢአት ሥርየት የሚያገኙባት፣ ሕፃናት በአርባ ቀንና በሰማንያ ቀን

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 11
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

በጥምቀተ ክርስትና አማካኝነት ከሥላሴ የጸጋ ልጅነት የሚቀበሉባት፣ ኢአማንያን የነበሩ


በመምህራን ትምህርት አምነው ክርስቲያን የሚሆኑባት፣ ለክህነትም ሆነ ለአባልነት የዘር
ሐረግ የማይቆጠርባት ዓለም አቀፋዊት የእግዚአብሔር ቤት ናት፡፡

አንዲት ቤተ ክርስቲያን ስትመሠረት ጀምሮ ሥርዓት አላት። የምትመሠረተው ባንድ ግለሰብ


ስም ሳይሆን በካህናትና በምዕመናን ጥያቄ በሀገረ ስብከቱ ኤጲስ ቆጶስ ፈቃድና ትእዛዝ
ነው፤ ካለኤጲስ ቆጶስ ፈቃድ ከመጽሐፉ ትዕዛዝ ወጥቶ አንዱ ቢያቋቁም ወይም ቢሠራ ቤተ
ክርስቲያን ናት ብለው ለዘለዓለሙ በዛች ቤተ ክርስቲያን አይቁረቡባት፤ እንደገበያ፣
እንደእንስሳት በረት ፈት ሆና ትኑር ይላል። /ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ ፩-፫/።

ቤተክርስቲያን ለመሥራት ፈቃድ ከተገኘ በኋላ ስለ አሠራሯ የሚከተለው ሥርዓት


ተሠርቶላታል። ቤተ ክርስቲያኗ ስትሠራ ደጆችና መስኮቶች አውጡላት ዛፍ ቅረጹላት ሐረግ
ሳቡላት እንደሚል በተቻለ መጠን ሊያስጌጧት ይገባል የመንግሥተ ሰማያት ምሳሌ
ናትና። በሰማይ ፀሐይ፣ ጨረቃ፣ ከዋክብት እንዲያበሩ፣ ሰባቱ ሰማያት ብሩሃን እንዲሆኑ
ቤተ ክርስቲያንም ብርህት ትሁን፤ ይልቁንም ክቡራት መጻሕፍት ሐዲሳት፣ የጳውሎስ
መልእክታት፣ የሐዋርያት መልእክታት፣ ግብረ ሐዋርያት በሚነበቡበት ጊዜ የበራች ትሁን፣
እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ ያለውም ይህንኑ ያመለክታል። /ማቴ. ፭፥፲፬/። ቅዱስ ወንጌል
በሚነበብበት ጊዜ ግን ፈጽማ የበራች ትሁን፤ እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ ያለው ይሻል። /ዮሐ.
፱፥፭/፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለአምልኮተ እግዚአብሔር
የምትገለገልባቸው አብያተ ክርስቲያናት ሥሪት በሦስት ምድብ /ክፍል/ የታወቁ ናቸው።

፩. ገዳም

ገዳም የታላቁን ነቢይ የኤልያስንና (፩ነገ.፲፯፥፩‐፰፡፡) የመጥምቁ የቅዱስ ዮሐንስን (ማቴ፫፥፬፡፡)


አኗኗርና ሕይወት አርአያ አድርገው የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ፍለጋ (ማቴ፬፥፩‐፲፪፡፡)
የተከተሉ መናንያን መነኮሳት የሚጋደሉበት የተቀደሰ ቦታ ነው። ትምህርተ ክርስቶስን
መሠረት አድርገው (ማቴ፲፥፴፯‐፵፡፡) እንደ ሐዋርያት (ማቴ፲፱፥፳፯‐ፍጻሜው፡፡) ሁሉን ትተው
የተከተሉት እነዚህ መናንያን መነኮሳት በጾም፣ በጸሎት፣ በስግደትና በልዩ ልዩ ተጋድሎ
ጸንተውና ከዓለም ርቀው ይኖሩበታል። በገዳም የሚኖሩት መነኮሳትና መነኮሳይያት
እንዲሁም በአመክሮ ላይ ያሉ ጥቁር ራሶች ብቻ ናቸው፡፡ መናንያን ከፈተና ይጠበቁ ዘንድ
የወንዶችና የሴቶች ገዳም ብዙውን ጊዜ የተለያየ ነው፡፡ አንዳንድ ገዳማት ብቻ ሁለቱንም
ጾታዎች በአንድነት የያዙ ሆነው ይገኛሉ፡፡

በገዳም ተወስነው የሚኖሩ መነኮሳት ገዳሙ የሚያዛቸውን ከመፈጸም ውጪ የኔ የሚሉት


ንብረት የሌላቸውና በራሳቸውም እንኳን ሊያዝዙ ከቶ አይችሉም። የምናኔ መመሪያቸውም
“ነፍሴን ለእግዚአብሔር፤ ሥጋዬን ለማኅበር አስገዛለሁ (ሰጥቻለሁ)፤” የሚል ነው፡፡ የገዳሙ
በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)
ገጽ | 12
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

መምህር ወይም አበምኔት ወይም አስተዳዳሪ የሚሾመው በዕድሜ፣ በመልካም ጠባይ፣


በገድል፣ በትሩፋትና በመሳሰሉት የተሻለው አባት ከመነኮሳቱ መካከል ተመርጦ ነው፡፡
በአንዳንድ ጥንታውያን ገዳማት የገዳሙ መምህር “የአጎዛ መምህር” (ዕብ፲፩፥፴፯) በመባል
ይጠራል። በሴቶች ገዳም የምትሾመው የመነኮሳይያቱ የበላይ ተጠሪ ደግሞ “እመ ምኔት”
ትባላለች ።

የአበምኔቱ ረዳቶች አፈመምህር፣ መጋቢ፣ እጓል መጋቢ፣ ሊቀ ረድእ፣ ሊቀ ዲያቆን ወዘተ


በመባል ይጠራሉ። ገዳማውያን መነኮሳት/ይያት/ በማኅበር እየሠሩ፣ እየጸለዩ፣ እየተመገቡ፣
አንድ ዓይነት ልብስ እየለበሱ ወዘተ በመኖር የሚጋደሉ ናቸው። ቤተ ክርስቲያን ልዩ ለሆነ
አገልግሎት ካልጠራቻቸው ወይም ገዳሙ ለተለየ ተልዕኮ፣ ለተወሰነ ጊዜ ካላካቸው በስተቀር
መነኮሳት በአታቸውን ጥለው ከገዳማቸው እንዲወጡ አይፈቀድላቸውም። እነርሱም ይህ
የምናኔ ዓላማ ገብቷቸውና ፈቅደው ስለሚመነኩሱ በአታቸውን ጥለው ለመውጣት
አይፈልጉም።

፪. ደብር፦

ደብር ከፍ ያለ ቦታ ተራራ ኮረብታ ማለት ነው። ከጥንት ጀምሮ እግዚአብሔር ብዙ ጊዜ


በተራራ ላይ ራሱንና ምሥጢራቱን ለወደዳቸውና ለመረጣቸው ሰዎች ይገልጥ ነበር።
(ዘጸ፲፱፥፩‐ፍጻሜው፤ ፳፬፥፩-ፍጻሜው ማቴ፲፯፥፩‐፲፤ ፳፬፥፫) ተራራ በቅዱሳን አበውና እማት፣
በጻድቃን በሰማዕታትም ሁሉ ይመሰላል። የእመቤታችንን የዘር ግንድ (ሐረግ) በተመለከተ
ነቢዩ ዳዊት ሲናገር “መሠረቶችዋ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው” (መዝ፹፮፥፩) በማለት
የተናገረው ለዚህ በቂ ማሳያ ነው።

ደብር ከሌሎቹ አገልግሎቶች በተጨማሪ ከዓመት እስከ ዓመት ስብሐተ እግዚአብሔር


ማለትም ስብሐተ ነግህ፣ መዝሙርና ቅዳሴ የማይቋረጥበት ነው። በደብርም በልዩ ምክንያት
ከተፈቀደላቸው መነኮሳት ጀምሮ ሕጋውያኑ ካህናት ያገለግሉበታል። ደብር በዓለም ውስጥ
በተለይም በከተማ አካባቢ የሚተከል እንደመሆኑ ምእመናን ዘወትር ያገለግሉበታል፤
ይገለገሉበታል። የደብር አስተዳዳሪ አለቃ ይባላል። የሚሾመውም እንደ አድባራቱ ሥርዓት
ከመነኮሳት ወይም ከሕጋዊያን ቀሳውስት ወይም ከመምህራን ነው፡፡ የደብር አስተዳዳሪ
የሆነው አባት እንደ ደብሩ ስያሜ ንቡረ እድ፣ ሊቀ ሥልጣናት፣ ሊቀ ሊቃውንት፣ መልአከ
ገነት፣ መልአከ ፀሐይ እየተባለ ይጠራል። አጠቃላይ አገልግሎቱ በሰበካ ጉባኤ ይመራል፡፡

፫. ገጠር

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በኢየሩሳሌም ዙሪያና በፍልስጥኤም ባሉ ገጠሮችና መንደሮችም


እየተዘዋወረ ያስተምር ነበር። ከነዚህም መንደሮች የተውጣጣ ፭ ገበያ ያህል ሕዝብ

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 13
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ይከተለው ነበር። (ማቴ፲፬፥፲፫‐፳፪፡፡) ሐዋርያትንና ሰባ ሁለቱን አርድዕትም የመንግሥትን


ወንጌል ያስተምሩና ድውያኑን ሁሉ ይፈውሱ ዘንድ በምድረ እስራኤል ሁሉ ልኳቸዋል።
(ማቴ ፲፥፭‐፯፡፡) (ሉቃ፲፥፩፡፡) ይህንን መሠረት በማድረግ ወንጌልን ለዓለም ሕዝብ ሁሉ
ለማድረስና ምሥጢራትንም በመፈጸም አማንያንን የሥላሴ ልጆች ለማድረግ ይቻል ዘንድ
በየገጠሩ ሁሉ ቤተ ክርስቲያን ታንጿል፤ ይታነፃልም። እንዲህ ያለችው ቤተ ክርስቲያን
“ገጠር” የሚል መጠሪያ ተሰጥቷታል።

የገጠር ቤተክርስቲያን መገለጫ የቦታው ገጠርነት (ከከተማ ወጣ ማለቱ) ብቻ ሳይሆን ከላይ


በደብር የጠቀስናቸው አገልግሎቶች በተሟላ ሁኔታ ዘወትር የማይሰጡባት መሆኑ ነው፡፡
እነዚህም በዕለተ ሰንበት፣ በወርኃዊና ዓመታዊ በዓላት ብቻ የሚቀደስባቸው ናቸው። የቤተ
ክርስቲያኑ አስተዳዳሪ እንደ ችሎታውና ዕውቀቱ አለቃ፣ መሪጌታ፣ ወይም ገበዝ ይባላል።
እንደ ደብር ይህም በሰበካ ጉባኤ ይመራል፡፡

1.11 የሕንጻ ቤተክርስቲያን አተካከል


እግዚአብሔር ከባሕርይ ምልዓቱ የተነሳ የማይኖርበት ቦታ ባይኖርም ውሱን ፍጥረታት
የሆንን እኛ ለሕሊናችን በሚስማማ ሁኔታ በውሱን ቦታ እንድናመልከው አዞናል፡፡ ለእኛ
መሰባሰቢያ ብቻ ሳይሆን እርሱም በረድኤትና በጸጋ ላለመለየቱ የቃል ኪዲን ቦታ በመሆኑ
ነው፡፡ እስራኤልን ‹‹በመካከላችሁ አድር ዘንድ ቤተ መቅደስን ስሩልኝ›› ያላቸው ለዚህ ነውና፡
፡ ዘጸ 25፤9 ሰዎችም ምሕረትና ይቅርታ ሲፈልጉ ወዲዚህ ቦታ ይመጡ ነበር፡፡
‹‹እግዚአብሔርን የፈለገ ሁሉ ከሰፈር ውጭ በመገናኛው ድንኳን ይወጣ ነበር›› ዘጸ 33፤7
ከዚህ የተነሳ ቤቱ ቤተ እግዚአብሔር ተብሎ ተጠራ 2ዜና 36፤18 በሐዋ 17፤24 ሊይ
‹‹የሰማይና የምድር ንጉስ ነውና የሰው እጅ በሰራው መቅደስ አይኖርም›› የሚለውን
ጠቅሰው ቤተ ክርስቲያን አያስፈልግም የሚሉ አሉ፡፡ ነገር ግን በዚያ ብቻ ተወስኖ አይኖርም
ለማለት የገባ ቃል ነው፡፡ ‹‹እግዚአብሔር በመረጠው ተራራ በዚያ ያድራል›› መዝ 67፤16
የቤተክርስቲያን ሥራ ፈቃድ ቤተክርስቲያን ለመትከል ሲፈልግ የክፍሉን ኤጲስ ቆጶስ ፈቃድ
ማግኘት ያስልጋል፡፡ አሊያ ቤተክርስቲያን መስራት አይቻልም /ፍት መን አን 1 ቁጥር 3/

1.12 የሕንጻ ቤተ-ክርስቲያን አሰራር (ዲዛይን)

1. ክብ ቅርጽ ፡- በሀገራችን በስፋት የምንጠቀምበት ሲሆን ክብ ቅርጽ ያለው ሶስት ቦታ


የሚከፈልና ሶስት በሮች ያሉት ነው፡፡ ቤተ ንጉስ ቅርጽ ይባላል፡፡ ነገስታት በቤተ
መንግስታቸው አምሳል ሰርተውታልና፡፡ እኛ ምድራዊ ነገስታት ነን ስልጣናችንም ጊዜያዊ
ነው፡፡ አንተ ግን ሰማያዊ ስልጣንህም ዘላለማዊ ነው እንዲህ ያለ ያማረ ቤት ይገባሃል ሲሉ፡
፡ አንድም ክብ መሆኑ ፍጹምነትና ያሳያል፡፡ ለዛም ነው የቅደሳን ስዕላቸው ሲሳል ፊታቸው

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 14
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

፤ ዓይናቸው ክብ የሚደረገው፡፡ ሃይማኖትን ከምግባር አስተባብረው ይዘዋልና፡፡ ከታሪክ


እንደምንረዲው በፊልጵስዮስ የተሰራችው የመጀመሪያዋ ቤተ ክርስትያን ክብ ቅርጽ ነበራት፡፡

2. ሰቀላማ ወይም ሞላላ ቅርጽ ፡- ይህ አራት ማዕዘን ያለው ሞላላ የሆነና ከፍ ብሎ


የሚታነጽ ነው፡፡ ክፍሎቹ በመጋረጃ ይከፈላሉ፡፡ አሰራሩም የተወሰደው ከደብተራ ኦሪት፣
ከሠሎሞን ቤተ-መቅደስ፣ እሌኒ በኢየሩሳሌም ካሰራችዉ ቤተ-ክርስቲያን (በመቅደሱ ስም
በጎልጎታ፣ በልደቱ ስም በቤተልሔም እንዲሁም በመሳሰሉት ቅዱሳት መካናት) ነው፡፡
የሐዲስ ኪዲን ሊቃውንት ሞላላ ቅርጽ ያለውን ይህን ቤተ ክርስቲያን ጌታችን የፈጸመውን
የድኅነት ሥራ እንድናስብበት ከመስቀል ጋር ያያይዙታል፡፡ እንደመጠኑ ከአንድ በላይ
ጉሊላት ሊኖረው ይችሊል፡፡ ለምሳሌ በሀገራችን የቀሞዉ ጉዲት ያፈረሰችዉ የአክሱም
ጽዮንና ደብረዳሞ ቤተ-ከርስቲያን እንዲሁም መንበረ ፀባኦት ቅድስት ሥላሴ

3. ዋሻ ቅርጽ ፡- የጥንት ክርስትያኖች በዘመነ ሰማዕታት ከአለውያን ነገስታት ሸሽተው በዋሻ


ሲሸሸጉ የቤተ ክርስቲያን አይነት ነው፡፡ በሩ አንድ ሲሆን በውስጡ ያሉት ክፍልች ብዙ ጊዜ
የሚለያዩት በመጋረጃ ነው፡፡ ጉሊላት የለውም፡፡ የሚታነጸው ተራራ በመፈልፈል አሌያም
ከተራራ የተነጠለ ዓለት በመፈልፈል ነው፡፡

1.13 የቤተ መቅደስ ክፍሎች

የቤተ መቅደስ ክፍሎች ቅኔ ማህሌት፣ ቅድስትና መቅደስ ሲባሉ እነዚህ ክፍሎች ጎልተው
የሚታዩት ክብ ቅርጽ ባላቸው ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ነው፡፡ በተጨማሪም የቤተክርስቲያን
የውስጥ ክፍሎች ሦስት ናቸው ፡፡ የእነዚህም ምሳሌነታቸው

1. በሶስቱ ዓለማተ መላሰዕክት (ኢዮር፣ ራማና ኤረር)


2. በሶስቱ መዓረጋተ ክህነት (ዱቁና፣ ቅስና ኤጲስ ቆጶስ)
3. በሶስቱ ጾታ ምእመናን ካህናት፣ ወንዶችና ሴቶች)

ሀ. ቅኔ ማህሌት፡- ስያሜው ከግብሩ የተወረሰ ነው፡፡ መዘምራን ካህናት መዝሙር


የሚዘምሩበት ቅኔ የሚቀኙበት ዲዊት የሚያስተዛዝሉበት ክፍል ሲሆን በመስዕ /ሰሜን
ምስራቅ/ ንዑስ ማእዘን በኩል ቀሳውስትና ዲያቆናት በመንፈቀ ሌሊት ሰዓት በነግህ ኪዳን
ያደርሱበታል፡፡ ወንዶች ምዕመናን ቆመው የሚያስቀድሱበት ነው፡፡ በጥንት ዘመን ሥርዓተ
ጥምቀት የየሚፈጸመው በዚሁ ክፍል ነበር፡፡ ለጥምቀት ቁርባን ያልበቁ በትምህርት በንሰሓ
ያሉ ንዐሰ ክርስቲያን /አዲስ አማኞች/ ዲያቆኑ ጻዖ ንዑሰ ክርስቲያን ብሎ እስከ ሚያውጅበት
ሰዓት ድረስ ይቆያሉ በኋላም ቃጭል ተመትቶ አዋጅ ሲታወጅ ይወጣሉ፡፡ በዚህ ክፍል በላብ
/ደቡብ ምስራቅ/ ንዑስ ማእዘን በኩል የሚገኘው ቦታ የሴቶች መቋሚያ ነው፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 15
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ለ. ቅድስት፡- ቀጥተኛ ትርጉሙ ልዩ የተለየ ማለት ሲሆን የቤተክርስቲያኑ ማእከላዊ ቦታ


ነው፡፡ ይህ ክፍል ካህናት በድርገት ጊዜ ምእመናንን የሚያቆርቡበት ነው፡፡ በስብከተ ወንጌሌ
ጊዜ መምህራን ቆመው የሚያስተምሩብት ክፍል ነው፡፡ በተክሊልና በቁርባን አንድ ለሚሆኑ
ሙሽሮች ጸሎት የሚደርስበትና በካህናት እጅ የሚባረኩበት ክፍል ነው፡፡ በስቅለት ዕለት
ጸሎት ይደረግበታል፡፡ የማይቆርቡ ምእመናን በዚህ ክፈል ማስቀደስ የለባቸውም

ሐ. መቅደስ፡- በብለይ ኪዳን ቅድስተ ቅደሳን ከሚባለው ጋር የሚነጻር ነው፡፡ የቃል ኪዲኑ
ታቦት በክብር ያርፍበታል፡፡ ሌሎች ነዋያተ ቅድሳት ይቀመጡበታል፡፡ ስልጣነ ክህነት
ካላቸው በስተቀር ማንም መግባት አይችሉም፡፡ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ብፁዓን
ሊቀጳጳሳትና ኤጲስ ቆጶሳት ያስቀድሱበታል፡፡ በምዕራብ በሰሜንና በደቡብ ሶስት በሮች
ሲኖሩት እያንዳንዱ መንጦላዕት አለው፡፡ በምስራቅ አቅጣጫ የማይከፈት መስኮት
ይበጅለታል፡፡ ለእመቤታችን የድንግልናዋ ምሳሌ ነው፡

1.14 በቤተ ክርስቲያንና በዙሪያዋ የሚገኙ /የማይንቀሳቀሱ/ ንዋያተ ቅድሳት


፩. አዕማድ /ምሰሶዎች/፡- እነዚህ በቤተክርስቲያን ውስጣዊ ክፍል ተተክለው ጣሪያውን
በመሸከም ግድግዳውን የሚያግዙ ናቸው። ምሳሌነታቸው

ሌሊትና ቀን ሳያርፉ በእግዚአብሔር ፊት ለምስጋና የሚቆሙ ቅዱሳን


መላእክትን ያሳስባሉ። /ራእ ፬፥፰‐፲/።
በአገልግሎት ጸንተው እግዚአብሔርን ሌሊትና ቀን ሳያርፉ ያገለገሉትንና ደስ
ያሰኙትን ሐዋርያት ያሳያሉ። /ገላ ፱/።

፪. ጉበን ወይም ደረጃ፡- ጉበን ወይም ደረጃ ወደ ቤተ ክርስቲያን የሚያደርስ /የሚያገባ/ ከፍ


ከፍ እያለ የሚጓዝ መንገድና መግቢያ ነው። ምሳሌነቱ ፡- “የእውነትና የሕይወት መንገድ
እኔ ነኝ በእኔ በኩል ካልሆነ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም።” /ዮሐ፲፬፥፮፡፡/ ብሎ የተናገረ
የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ ይህም እኔን የባህርይ ልጅ /ተወላዲ/ ሳይል አብን
የባሕርይ አባት /ወላዲ/ ሊለው የሚችል የለም፤ ማለቱ ነው። እርሱን አርአያና አብነት
አድርገን የምንኖር ከሆነ ወደ ሰማያዊ መንግሥቱ ያገባናል።

፫. የቤተ ክርስቲያን ክዳን ሣር መሆኑ፡- ምሳሌነቱ ፦ ሄሮድስ በጭካኔ ያስፈጃቸውን


የቤተልሔም ሕፃናት ያመለክታል፡፡ /ማቴ ፪፥፲፮‐፲፱፡፡/ የሣር ክዳን መጠኑ ይህን ያህላል
የማይባል ብዙ እንደሆነ ሁሉ ሕፃናቱም ምንም እንኳን ለመቆጠር ቢችሉም እጅግ ብዙ
ናቸውና። በዚህ ተመስለዋል:

፭. ምፅዋት ፦ ምሳሌነቱ፦ በዓልም በሌሊት ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን የማይለዩትን ቅዱሳን


መላእክት ያሳስባል: ዕፅዋቱ በቤተክርስቲያን ግቢ በብዛት እንደሚታዩ በቤተ ክርስቲያን

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 16
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

የሚኖሩ ቅዱሳን መላእክትም እጅግ ብዙ ናቸው: ዕፅዋቱ አምረውና ተውበው ለቤተ


ክርስቲያን ሞገስ ሆነው እንደሚታዩ ሁሉ ቅዱሳን መላእክትም የቤተ ክርስቲያንና
የምእመናን መንፈሳዊ ሞገሶች ናቸው። /መዝ፺፥፲፩፡፡/ እንደ ዕፅዋቱ የምእመናን ጥሬ ከላይ
ከሆናቸው ያሳያል።

፮. ማር፦ ምሳሌነቱ፦ የቅድስተ ሥላሴም ነው: ማር የሕፃኑን ግድግዳና ጣሪያ አገናኝቶና


አጽንቶ እንደሚያቆመው ቅድስት ሥላሴም ቤተ መቅደስ በሆነው የክርስቲያን ሰውነት ላይ
አድረው በሃይማኖትና በምግባር አጽንተውት እንደሚኖሩ ያመለክታል።

፯. ግድግዳና ምሳሌነቱ፦ የነቢያት ነው: ግድግዳና ለቤተክርስቲያን ውስጣዊ ክፍሎች


መጸለያና ከአንተ ወደ አንዱ የመሸጋገሪያ እንደሆነ ሁሉ ነቢያትም ዘመናት ወደ ዘመናት
/ከመ ፍዳ ወደ ዓመት ምህረት/ ለተደረገው ሽግግር ትንቢት ተናጋሪዎች መሆናቸውን
ያሳያል። /ማቴ፫፥፩‐፯፡፡/

፰. የተፈጠረ ድንጋዮችና የለዘቡ እንጨቶች፡- ምሳሌነታቸው ፦ የሰማዕታት ነው።


ደንጊያዎችና ዕንጨቶች ተወቅረውና ተጠርበው ለቤተ ክርስቲያን መሥሪያ እንደሚውሉ
ሁሉ ሰማዕታትም በእሳት እየተፈተኑ በስለት እየተመተሩ ለመንግሥተ እግዚአብሔር የበቁ፥
ለምእመናንም የሚተርፉ እንደሆኑ ያመለክታል፡፡ /ዕብ ፲፩፥፴፮‐፴፱፡፡/

፱. ልደት ምሳሌነቱ፦ ቀራንዮ ነው: ጉልላትንና ከላዩ ላይ ያለውን መስቀል ለሚመለከት


ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዕለተ ዓርብ ለድኀነተ ዓለም በቀራኒዮ ኮረብታ /አደባባይ/
መሰቀሉን እንዲያስብ ያደርገዋል። /ዮሐ ፲፱፥፲፯፡፡/

፲. ጣሪያውን ጣሪያ ያሉ ሻኩራዎች ምሳሌነታቸው፦ ቅዱሳን መላእክት ነው: ሻኩራዎች


ሌሊትና ቀን ነፋስ እየተወዛወዙ ድምፅ እንደሚሰጡ ቅዱሳን መላእክትም በአጸደ
ቤተክርስቲያን ሌሊትና ቀን ያሸበሽባሉ፤ ይዘምራሉ: /ዘፍ፳፰፥፲፩‐፲፰፡፡/

፲፩. የሰውን እንቁላል፡- ይህ አሁን ከችግር አኳያ እየቀረ የመጣ ቢሆንም በጥንታውያኑና
ገጠራማ አካባቢ በሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት የተለመደ ነው: በጉልላቱ ላይ በሚቆመው
መስቀል ዙሪያ የሰጎን እንቁላል ይደረጋል። ምሳሌነቱ /ምሥጢራዊ ትርጉም/፦ የሰጎን
እንቁላሏን ለመፈልፈል የምታበቃው በመታቀፍ ሳይሆን ሳታቋርጥ /ሳትንቀሳቀስ/ በማየት
ነው። ምግብ ሲያስፈልጋት እንኳን ወንዱን በቦታዋ ተክታ ነው። የቤተክርስቲያን ልደት ላይ
እንቁላሏ መሰቀሉ ሰጎን ያለማቋረጥ እንቁላልዋን እንደምትመለከት እግዚአብሔርም
ፍጥረቱን የማይረሳ በጸጋውና በረድኤቱ ከፍጥረቱ የማይለይ መሆኑን ያመለክታል።
እንቁላሉ በእግዚአብሔርና በምእመናን መካከል ያለውን የጠበቀ ግንኙነት ያስረዳል /፪ዜና ፯፥
፲፮፡፡ ኢሳ፵፱፥፲፭፡፡/

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 17
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ሰጎኗ ዓይኗን ለአፍታም ያህል እንኳን ካነሳች፥ እንቁላሉ ይለወጣል፤ ማለትም ይበላሻል፤
አይፈለፈልም: እንደዚሁም እግዚአብሔር መግቦቱንና ጠብቆቱን /ረድኤቱን/ ለአፍታም ያህል
ቢያቋርጥ ምእመናን /የሰው ልጆች/ ሕይወት አይኖራቸውም: አንድም ታሪኩ ምእመናን
እንደ ሰጎን ዓይነ ልቦናቸውን ወደ እግዚአብሔር፣ ወደ ቤተክርስቲያን፣ ወደ መስቀሉ፣ ወደ
እመቤታችን፣ ወደ ቅዱሳኑ ሁሉ እንዲያደርጉ ይጋብዛል። ዓይነ ልቡናውን ከእግዚአብሔር፣
ከቤተ ክርስቲያን፣ ከቅዱስ መስቀሉ፣ ከእመቤታችን፣ ከቅዱሳን ሁሉ ላይ ነህ /ከቀይ/
መንፈሳዊ ሕይወታቸው እንደሚበላሽ ፍጻሜያቸውም እንደማያምር ያሳያል። /ዮሐ ፲፱፥፳፭/

፲፪. ሦስቱ በታች፡ እነዚህ በታች ወደ ቤተክርስቲያን የሚያስገቡና በምሥራቅ፣ በሰሜንና


በደቡብ የሚገኙ ናቸው። በምሥራቅ ካህናት፣ በሰሜን ወንዶችና በደቡብ ሴቶች
ይገቡባቸዋል።

፲፫. ቤተልሔም፡- ከቤተ ክርስቲያን በስተምሥራቅ የሚሠራው ይህ ቤት መሥዋዕተ ወንጌል


(ሥጋውና ደሙ ማትም ኅብስቱና ወይኑ የሚዘጋጅበት ክፍል ነው: ምሳሌነቱ፦ ጌታችን
ኢየሱስ ክርስቶስ የተወለደበት ዋዉ /ጎኔ/ ነው።

፲፬. ቤተ ወርቅ፡- ይህ ክፍል አገልግሎት በኋላ ካህናት ረዳት አድርገን እህል ውሃ


የሚቀምሱበት ነው። ይህም በልማዳዊ አጠራር ደጀ ሰላም የሚባለው ነው። ምሳሌነቱ፦
የገነት ነው: ገነት ለቅዱሳን ጊዜያዊ የዕረፍት ቦታ /የነፍስ ማረፊያ/ እንደሆነች ሁሉ ቤተ
ምርፋቅም ለአገልጋይ ካህናት ጊዜያዊ የዕረፍት ክፍል መሆኗን ያሳያል።

1.15 በቤተክርስቲያን ውስጥ የሚሰሩሌሎች ቤቶች

1. ቤተሌሔም፡- ከቤተ ክርስቲያኑ በምስራቅ በኩል የሚሰራ ሲሆን ዱያቆናቱ ኅብስቱንና


ወይኑን ያዘጋጁበታል፡፡
2. የግብር ቤት፡- ከቤተ ክርስቲያኑ በደቡብ በኩል ተሰርቶ ለመስዋዕት የሚቀርበው
መገበሪያ የሚሰየምበት ነው፡፡
3. እቃ ቤት፡- ከቤተ ክርስቲያኑ በሰሜን በኩል ተሰርቶ ንዋያተ ቅዱሳት ይቀመጡበታል
4. ደጀሠላም፡- ከቤተ ክርስቲያኑ በምዕራብ በኩል ይሰራል፡፡

በተጨማሪም የሙታን በድን የሚያርፍበት፣ ጸሎተ ፍትሀት የሚፈጸምበት ቤት፣


ማጥመቂያ ቤት፣ የሰበካ ጽ/ቤት፣ ሰንበት ት/ቤት እና ሌሎችም አቅም በፈቀደ መልኩ እንደ
አስፈላጊነቱ ተያይዞ ይሰራል፡፡

1.16 ቤተ ክርስቲያን ስትባረክ

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 18
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ቤተ ክርስቲያን ሕንፃዋ ተፈጽሞ በምትባረክበትና በምትቀደስበት ጊዜ ከኤጲስ ቆጶሱ ጋር


ሰባት ቀሳውስት አብረውት ሊኖሩ ይገባል፣ ታቦቱም በሚባረክበት እንደዚሁ ሊሆን ይገባል፣
ኤጲስ ቆጶሱ እግዚአብሔር ሰውን የሚያከብርበት ራሱን የሚያስመስልበት ነውና ደስ
በሚያሰኝ በቅብዐ ቅዱስ በሜሮን ያክብራት ያትማት፣ ታቦቱንም በመቅደስ ውስጥ በመንበር
ያስቀምጡባት ከታቦቱ ጋራ የዮሐንስን ወንጌል ያኑሩ ከደቀ መዛሙርቱም በጌታ ኢየሱስ
አጠገብ የሚቀመጥ ጌታ የሚወደው ቅዱስ ዮሐንስን ነበርና። /ዮሐ. ፲፫፥፳፫/ ።

ታቦቱም ሲቀረጽ ከላይ አልፋ፣ ቤጣ፣ የውጣ፣ ወኦ/ወዖ/ ይቀረጻል። ቀጥሎ እመቤታችንን፣
ከእመቤታችን ቀጥሎ ዮሐንስን፣ ቀጥሎ ቤተ ክርስቲያኑ የሚተከለው ታቦት መልአክም
ቢሆን፣ ሰማዕትም ቢሆን፣ ጻድቅም ቢሆን ይቀረጻል። እነዚህ ከላይ የተጠቀሱት ካልተሟሉ
ታቦቱን ሊቀድሱበት አይገባም።

ከቤተ ክርስቲያን የገባ ዕቃ የወርቅ፣ የብር፣ ፃሕል ጽዋእ እርፈ መስቀል ቢሆን ንዋየ
ቅድሳት ነው ተብሎ አቡነ ዘበሰማያት ከተደገመበት በኋላ ከቤታቸው ወስደው በፃሕሉ
ፈትፍተው ሊበሉበት በጽዋው ቀድተው ሊጠጡበት አይገባም። ደፍረው ቢያደርጉ ሥርዓት
ማፍረስ ነውና ይህን ያደረገ ቢኖር በአንድ ሁለት ተቀጥቶ ንሰሐውን እሰኪፈጽም
ከምዕመናን ይለይ። /ዳን. ፭፥፩-፴፩/።

በቤተ ክርስቲያንም ኤጲስ ቆጶሳት፣ ካህናት፣ ዲያቆናትና ምዕመናን እንዴት መቆም


እንዳለባቸው ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን እንደሚከተለው ይገልጻል። ኤጲስ ቆጶሳት የቤተ
ክርስቲያን አዛዚያን እንደመሆናቸው በታቦቱ ፊት ይቁሙ፣ ቀሳውስትም መምህራን
እንደመሆናቸው ከኤጲስ ቆጶሳት ቀጥለው ይቁሙ፣ ሊቀ ዲያቆናትም ከኤጲስ ቆጶስ አጠገብ
ይቁሙ፣ ዲያቆናትም አገልጋዮች እንደመሆናቸው ከቀሳውስት ቀጥለው ይቁሙ፣ ከዲያቆናት
ቀጥለው ሕዝቡ ሁሉ ባንድ ቦታ ይቁሙ፣ የሚበቃ ቦታ ቢኖር ሕፃናት በአንድ ወገን
ለብቻቸው ይቁሙ፣ የሚበቃ ቦታ ከሌለ ግን ከአባቶቻቸው ጋራ ተስገው ይቁሙ፣
እንደዚሁም ሴቶች ባንድ ወገን /ቦታ/ ለብቻቸው ይቁሙ፣ ቦታ ቢገኝ ሕፃናት ሴቶች ባንድ
ወገን ለብቻቸው ይቁሙ፣ ቦታ ባይኖር ግን ሕፃናቱ በፊት እናቶች በኋላ ይቁሙ፣ ደናግላን
ሴቶችና ባልቴቶች ግን ከሴቶች በላይ ይቀመጡ ። /ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ ፲፪ ድስቅ ፲፪
ኒቅያ ፷፩/።

1.17 ለምን ወደ ቤተክርስቲያን እንሔዳለን?

ማቴ 1820 ሁለት ወይም ሦስት በስሜ በሚሰበሰቡበት በዚያ በመካከላቸው እሆናለው፡፡


ስላለ በአንድነት አግዚአብሔር በክብር በሚገለጥበት ቦታ ጸሎት በማድረግ፡፡ ሐዋ18;22
አባቶቻችን ሐዋርያት ወደ ቤተ ክርስቲያን ይሄዱ ስለነበር አናም እነርሱን አብነት አድርገን፡፡
አንድም ምስጢራተ ቤተክርስቲያን ለመሳተፍ (ለመቁረብ) ዮሐ 5;54 እና ስግደት፣ አምልኮ
በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)
ገጽ | 19
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ለመፈፀም እና ለማመስገን ከክርስቲያኖች ሕብረት (ከምዕመናን ጋር አብሮ) በጸሎት


ለመሳተፍ ከተከበረው ቦታ በረከት ለማግኘት፡፡ ምክንያቱም የእግዚአብሔር ስም
የሚከበርበት፣ የሚመሰገንበት ቅዱሳን የሚወደሱበት፣ የአምላክ ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደሙ
የሚፈተትበት ቦታ ስለሆነ፡፡ መዝ29;2 የስሙን ክብር ለእግዚአብሔር አምጡ በቅድስናው
ስፍራ ለእግዚአብሔር ስገዱ፡፡

ቦታ ምን ያህል የተቀደሰ አንደሚሆን ዘፍ 3;5 ሙሴ ወደ ደብረ ሲና ነበልባሉ ከሐመልማሉ


እየተዋሀደ ሲነድ ባየ ጊዜ ወደዚያ ቦታ ሲሔድ የቆምክባት ቦታ የተቀደሰች ናታና ጫማህን
ከእግርህ አውልቅ ብሎታል ስለዚህ ሥጋወደሙ የሚፈተትባት የክብሩ መገለጫ ታቦት
ባለበት ቦታ ማመንና የተቀደሰ ቦታ ይሁን፡፡ ሉቃ 1፡8-10 ካህኑ ዘካረያስ (መቅደሱን)
ሲያጥን በነበርበት ጊዜ …በዕጣኑም ጊዜ ህዝቡ ሁሉ በውጭ ቆመው ይፀልዩ ነበር፡፡

አኛም ቅዳሴው ሲኖር ኪዳኑ ሲኖር ብንጸልይ አብረን ከካክናቱ እና ከህዝቡ ጋር


እግዚአብሔር ብናመሰግን ክብር እናገኛለን እንጂ የሚጎዳን ምንድነው? ማቴ 26;41 “ወደ
ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ፀልዩ” የተባለ አይደለምን? ወደ ቤተ ክርስቲያን እንዴት ሄዱ ጸሎት
እንዳታደርሱ፣ ቅዳሴና ኪዳን እንዳታደረሱ ሁሌም የሚተጋ ሰይጣን ነው፡፡ 2ተሰ2;9-10
“በአመፅም መታለል ሁሉ እንደ ሰይጣን አሰራር ነው”፡፡ መዝ 122;1 “ወደ እግዚአብሕር
ቤት እንሂድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ”፡፡ መክ 5;1 ”ወደ እግዚአብሔር ቤት በገባህ ጊዜ እግርህን
ጠብቅ ለመስማት መቅረብ ከሰነፎች መስዋዕት ይበልጣልና”፡፡ እግዚአብሔር በክብሩ
የሚገለፅበት ታቦቱ ስላለ እግዚአብሔርን ለማመስገን ወደ ቤተ ክርስቲያን እንሄዳለን፡፡ መዝ
5፡3 “በማለዳ ድምፄን ትሰማለህ በማለዳ ከፊትህ እቆማለሁ እጠብቃለሁም፡፡ ሉቃ 24:53
“ሐዋርያት ዘወትርም እግዚአብሔርን እያመሰገኑና እየባረኩ በመቅደስ ኖሩ” ቤተ
ክርስቲያንን መሳለም ይገባል ወይ? አዎ ይገባል፡- ሐዋ 18; 22 ቅዱስ ጳውሎስ ወደ ቂሳርያ
በደረሰ ጊዜ ወጥቶ ለቤተክርስቲያን ሰላምታ ከሰጠ በኃላ ወደ አንፆኪያ ወረደ፡፡ በትምህርተ
መስቀል አምሳል አያማተብን ለቤተክርስቲያን ሰላምታን የምናከርበው ሐዋርያትን አብነት
አድርገን ነው;; መዝ 5;6 አንተን በመፍራት ወደ ቤትህ አገባለሁ ወደ ቅዱስ መቅደስህም
አሰግዳለሁ;; ሕዝ 46፡3 አንዲሁም መዝ 132;7

ማስገንዘቢያ፡- የቤተክርስቲያን ፍቺ ከሕንፃዉና ከምዕመናን ጉባኤ አንጻር ብናስቀምጠዉ


የተለያዩ ናቸዉ ማለት አይደለም፡፡ ምክንያቱም ሕንፃ ቤተክርስቲያኑ ያለምዕመናን ጉባኤ
(ማኅበረ ካኅናት ወማኅበረ መዕመናን) እንደዚሁም ማኅበረ ምዕመናንና የማኅበረ ካኅናት
ጉባኤ ይብዛም ይነስም ያለ ሕንፃ ቤተ-ክርስቲያን ሊታሰብና ሊነገርም ስለማይችል
በተጨማሪም ያለሕንፃ ቤተ-ክርስቲያን መንፈሳዉያን ዜጎች ክርስቲያኖች የመንግስተ ሰማይ
ዐድምተኞች ሊሆኑ አይችሉም፡፡ ሁለቱም የተሰናሰሉ ናቸዉ፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 20
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

2. ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን
2.1 ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን የቃሉ ትርጉም
ሥርዓት ማለት “ሠርዐ-ሠሪ” ከሚዉ የግዕዝ ግስ የወጣ ሲሆን ትርጉሙ ደንብ፣ ሕግ፣
አሰራር፣ መርሐግብር፣ ዕቅድ፣ ሕገ፣ ደንብ ማለት ነዉ፡፡ ቤተ ክርስቲያን የሥርየተ
ኃጢአት፣ የኖላዊነት (እረኝነት)፣ የማስተማር፣ የማስተዳደርና ምሥጢራትን የመፈጸም
ሥራ ለማከናወን የምትችልበት ሥርዓትም ባለቤት ናት፡፡ ይህም አንዲቷ፣ ሐዋርያዊቷና
ኩላዊቷ ቅድስት ቤተ-ክርስቲያን ከክርስቶስ የተቀበለችዉን የክህነት አገልግሎት አፈጻጸም
ማለትም የሥርየተ ኃጢአት፣ የኖላዊነት (እረኝነት)፣ የማስተማር፣ የማስተዳደርና
ምስጢራትን የመፈጸም ሥራ ማከናወን የምትችልበት እና በምዕመናን የሚተገበር መንፈሳዊ
ሥራና የእያንዳንዱ ምዕመናን መንፈሳዊ ሕይወት ከልደት እስከ ዕረፍት…… ደንብ፣
አሠራር፣ መርሐግብር፣ ሕግና፣ መመሪያ ማለት ነዉ፡፡

ይህም ሥርዓት በክርስቶስ ደም የተመሰረተች ቤተ-ክርስቲያን አምልኮቷን የምትፈጽምበት


ሕዝበ እግዚአብሔርን የምትጠብቅበት ጸጋ የሚሰጥ ቅዱስ ሥርዓት ነዉ፡፡ በተጨማሪም
ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን በምንልበትም ጊዜ በተቀደሰው ቤት (ሕንፃ) ለሚከናወነው
አገልግሎት፣ በምእመናን ጉባኤ ለሚተገበረው መንፈሳዊ ሥራና በእያንዳንዱ ምእመን
ሕይወት ከልደት እስከ ዕረፍት ለሚፈጸመው መንፈሳዊ እንቅስቃሴ ሁሉ መመሪያ ማለት
ነው፡፡ ለምዕመናን የሃይማኖት ማጽኛ መሠረት፣ መለያ እንዲሁም በቅዱሳት መጻሕፍት
የተገለጠ ቅዱስ ሥርዓት አምልኮ ነዉ፡፡ እነዚህም ሥርዓት ሐዋርያትና ሊቃዉንት በየጊዜዉ
ለቤተ-ክርስቲያን መተዳደሪያ የወሰኑትን የደነገጉት ሕግ ነዉ፡፡

2.2 የሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን መሠረት


የሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን መሠረት ሥርዓተ ቤተ መቅደስ ሲሆን፤ የሥርዓተ ቤተ መቅደሱ
መሠረት ደግሞ ሥርዓተ ደብተራ ኦሪቱ ነው፡፡ የሥርዓተ ደብተራ ኦሪት መሠረቱ ደግሞ
ሥርዓተ መቅደስ ሰማያዊ መሆኑን እግዚአብሔር ራሱ ነግሮናል፡፡ “በተራራው እንዳሳየሁህ
ሁሉ፣ እንደ ማደሪያው ምሳሌ፣ እንደ ዕቃውም ሁሉ ምሳሌ ለእኔ ትሠራለህ፤ እንዲሁ
ትሠራለህ፡፡” (ዘጸ. ፳፭፥፱ ፣ ፳፮-፴፣ ፳፯፥፰)፡፡ በማለት ሙሴን እንዳዘዘው የተጻፈው
የሚገልጽልን ይህንኑ እውነታ ነው፡፡ ይህን ሰማያዊ መቅደስ ዮሐንስ ወንጌላዊም በራእዩ
ማየቱን ነግሮናል፡፡ “ከዚህም በኋላ በሰማይ ያለው የእግዚአብሔር መቅደስ ተከፈተ፤
የእግዚአብሔር የሕጉ ታቦትም በመቅደሱ ታየች፤” (ራእ. ፲፩፥፲፱) እንዲል፡፡ ሙሴ ወደ
ተራራው በወጣ ጊዜ እግዚአብሔር ሰማያዊውን የብርሃን መቅደስ” ዕፁብ ድንቅ የሆኑ ንዋየ
ቅዱሳትንና የአገልግሎቱን ሥርዓት እንዲያይና እንዲሰማ ፈቅዶለታል፡፡ ለዚህም ነው
በተደጋጋሚ “በተራራው ላይ ባሳየሁህ ምሳሌ እንድትሠራ ተጠንቀቅ፡፡” እያለ የሚያሳስበው፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 21
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊም “ሰማይ ተከፈተ” በማለት ዓይነ ልቡናው በርቶለት ምሥጢራትም
ተገልጠውለት ሰማያዊን የብርሃን ቤተ መቅደስ ከታቦተ እግዚአብሔርና ንዋያተ ቅዱሳት
ጋር ማየቱን ነው የገለጠልን፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ መቅደሱንና ታቦተ እግዚአብሔርን ብቻ
ሳይሆን ያየው የካህናተ ሰማይ የቅዱሳን መላእክትን የአገልግሎት ሥርዓትም ነው፡፡ (ራእ.
፰፥፩-፮)፡፡ ቅዱሳን ነቢያትም ቢሆኑ በአገልግሎት ዘመናቸው ይህንኑ ሰማያዊ የአገልግሎት
ሥርዓት እግዚአብሔር በገለጠላቸው መጠን ማየትና መስማት ችለዋል፡፡ (ኢሳ. ፮፥፩-፮፡፡ ሕዝ.
፩፥፩-ፍጻ፡፡) ቤተ ክርስቲያን ምሥጢራትን የምትፈጽምበትና አገልግሎቱን የምታከናውንበት
ሥርዓት በቀጥታ ከሰማያዊው የብርሃን መቅደስ የተገኘ (የተቀዳ) መሆኑን ማስተዋልና
ሥርዓቷን አክብሮ መጓዝ ይገባል፡፡

2.3 የሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን አስፈላጊነት


የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት (ሥራ) ይቅርና ማንኛውም በዚህ ዓለም ውስጥ የሚከናወን
ተግባር ያለ ሥርዓት ሊጀመር፣ ሊሠራና ሊፈጸም አይችልም፡፡ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ካለ
ዘንድ ጠቀሜታውን ማወቅ፣ ማክበርና ለተፈጻሚነቱ ሁሉም የድርሻውን ማበርከት
ይጠበቅበታል፡፡ የሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን አስፈላጊነት በሚከተለው መልኩ ሊገለጽ ይችላል፡፡

፩ኛ. የቤተ ክርስቲያንን ልጆች በአንድ መስመር ለመምራት፣ ወጥና ዘላቂ በሆነ መንገድ
እንዲጓዙ ለማስቻል ሥርዓት ያስፈልጋል፡፡ ለምሳሌ፡- ቤተ ክርስቲያን በየትኛውም ክፍለ
ዓለም ብትታነፅም /ብትሠራም/፣ በየትኛውም ዓይነት ቋንቋ ብትገለገልም፣ አገልግሎቷን
ለየትኛውም ዓይነት ሕዝብ ብታቀርብም መሠረተ እምነቷ፣ የምሥጢራት አፈጻጸሟና
ሁለንተናዊ አገልግሎቷ ወጥና ዘላቂ (የማይቀያየር) በሆነ ሥርዓት መመራቱ የግድ ነው፡፡
ይህ ካልሆነ ግን አስተማሪውና ተማሪው፣ ተናጋሪውና ሰሚው፣ ቀዳሹና አስቀዳሹ፣
አገልጋዩና ተገልጋዩ፣ እረኛውና በጉ፣ ጀማሪውና ተከታዩ … ወዘተ ስለማይታወቅ
የተደበላለቀ (ውጥንቅጡ የወጣ) ይሆናል፡፡ ለዚህ ነው ቅዱስ ጳውሎስ “ነገር ግን ሁሉን
በአገባብና በሥርዓት አድርጉ፤” (፩ቆሮ ፲፬፥፵) በማለት ያስተማረው፡፡

፪ኛ. የክርስቶስ አካላት፣ የቤተ ክርስቲያንም አባላት የሆኑት ካህናትና ምእመናን አንድ ልብና
አንድ አሳብ ለመሆን የሚችሉት አንድ ዓይነት ሥርዓት ሲኖራቸውና ሲመሩበት ነው፡፡
አለበለዚያ አንዱ ሲያስተምር አንዱ የሚዘምር፣ አንዱ ሲጀምር አንዱ የሚጨርስ፣ አንዱ
ሲያበራ አንዱ የሚያጠፋ፣ አንዱ ሲከፍት አንዱ የሚዘጋ … ወዘተ ይሆንና ቤተ ክርስቲያን
ትርምስና ሁከት መለያየትም የሚነግሥባት ቤት ትሆናለች፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ
“የተጻፈው ሁሉ በመታገሳችንና መጻሕፍትን በማመናችን ተስፋችንን እናገኝ ዘንድ እኛ
ልንማርበት፤ የትዕግስትና የመጽናናት አምላክ እግዚአብሔር እንደ ኢየሱስ ክርስቶስ ፈቃድ
እርስ በርሳችን አንድ ሀሳብ መሆንን ይስጠን፤ ሁላችን አንድ ሆነን በአንድ አፍ በጌታችን
በኢየሱስ ክርስቶስ እግዚአብሔርን እናመሰግነው ዘንድ፡፡” (ሮሜ 15-4-7) በማለት
በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)
ገጽ | 22
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

እንደተናገረው ክርስቲያኖች አንድ ሀሳብ መሆንና አንድ ሆነው በአንድ አፍ እግዚአብሔርን


ማመስገን የሚችሉት ወጥ በሆነ ሥርዓት መመራት ሲችሉ ነው፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት ይህን
ስለተረዱ ነው፡፡ በእግዚአብሔር መንፈስ ተቃኝተው ስምንቱን የሥርዓት መጻሕፍት
የሠሩልን ዳግመኛም ቅዱስ ሉቃስ “ያመኑትም ሁሉ አንድ ልቡና አንዲት ነፍስ ሆነው
ይኖሩ ነበር፡፡” (ሐዋ 4፡32) በማለት የጻፈልንን ብንመረምረው አንድ ልብና አንዲት ነፍስ
የመሆን ምሥጢሩ በሥርዓት መመራት መተባበርም መሆኑን ለመረዳት አያዳግትም፡፡

፫ኛ. የሃይማኖትን ምሥጢራት ለመፈጸም የሚቻለው ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ሲኖር ብቻ


ነው፡፡ ሥርዓት የሃይማኖት መግለጫ ነውና፡፡ ሥርዓት የሌለው ሃይማኖት ፈጽሞ ሊኖር
አይችልም፡፡ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ብቻ ሳይሆኑ ማንኛውም የቤተ ክርስቲያን
አገልግሎት የሚከናወንበት የራሱ የሆነ ሥርዓት አለው፡፡ በመሠረተ እምነት ደረጃ
የምናምነውን በተግባር የምንገልጸው ሥርዓት ሲኖር ብቻ ነው፡፡ እግዚአብሔር አምላክ
ጥንትም በብሉይ ኪዳን ኋላም ሰው ሆኖ ቤተ ክርስቲያኑን በመሠረታት ጊዜ ያለ ሥርዓት
ያከናወነውና እንድናከናውንም ያዘዘን አንዳች ነገር የለም፡፡ ለምሳሌ ከብሉይ ኪዳን
የፋሲካውን በግ በተመለከተ የተጻፈውን ብንመለከት ጠቦቱ የሚያዝበት ወሩና ቀኑ፣
የተመጋቢዎች ቁጥር፣ የጠቦቱ ዓይነትና መጠኑ፣ የሚታረድበት ሰዓት፣ ደሙ የሚቀባበት
ቦታና አቀባቡ፣ የምግቡ አዘገጃጀት፣ የመብሊያው ሰዓት፣ የአመጋገቡ ሂደትና የተመጋቢዎቹ
ዝግጅት በዝርዝር መታዘዙ ሥርዓት መሆኑንና አዛዡም እግዚአብሔር መሆኑን ማስተዋል
ይገባል፡፡ (ዘፀ 12፡6-15)፡፡ በሐዲስ ኪዳንም ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “አሁንም
ወንድሞቻችን ሆይ ጸንታችሁ ቁሙ፤ በቃላችንም ቢሆን ወይም በመልእክታችን
ያስተማርናችሁንና የሠራንላችሁን ሥራዓት ያዙ፡፡” (2 ተሰ. 2፡15)፡፡ በማለት ሐዋርያት
ለወንጌል አገልግሎት የሚበጅ ሥርዓት መሥራታቸውንና ክርስቲያኖችም ይህን ሥርዓት
መጠበቅ እንዳለባቸው አስገንዝቧል፡፡

2.4 የሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ምንጮች


በዋናነት የሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ምንጭ ነው ብላ ቤተ ክርስቲያን የምታስተምረው
መጽሐፍ ቅዱስን ነው፡፡ መጻሕፍ ቅዱስ፣ የሐዋርያት ሲኖዶሳት፣ ሥርዓተ ጽዮን፣
አብጥሊስ፣ ትእዛዝ፣ ግጽው፣ ዲድስቅልያና ቀሌምንጦስ የሚባሉትን ያካትታል፡፡
በተጨማሪም ፍትሕ መንፈሳዊና የሦስቱ ጉባኤያት ውሳኔዎች (ኒቂያ፣ ቁስጥንጥንያ፣
ኤፌሶን) ፣ ከአራተኛዉ መ/ክ/ዘ ጀምሮ እስከ አሁን በየጊዜዉ የተነሱት የቤተ-ክርስቲያን
ሊቃዉንት የጻፏቸዉ ልዩ ልዩ መጻሕፍት የሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ምንጮች ናቸው፡፡

2.4.1 መጽሐፍ ቅዱስ


መጽሐፍ ቅዱስ ማለት ከሁለት ቃላት የተገኘ ሲሆን መጽሐፍ እና ቅዱስ የሚሉትን ቃላት
ይይዛል፡፡ መጽሐፍ ማለት በአንድ ጥራዝ ስር የተሰበሰበ ጹሑፍ ማለት ሲሆን ቅዱስ ማለት

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 23
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ደግሞ የተለየ፣ የተከበረ ማለት ነው፡፡ አንድም መጽሐፍ ቅዱስ ማለት በአንድ ጥራዝ
የተሰበሰበ የተለየና የተከበረ ፅሁፍ ማለት ነው፡፡ ስለምን ቅዱስ ተባለ ትሉኝ እንደሆነ፡-

1. አስገኚው እግዚአብሔር ቅዱስ ስለሆነ፡፡ ዘሌ 19፡2፤1ጴጥ 1፡15


2. ሰዎችን ወደ ቅድስና የሚያደርስ ስለሆነ፡፡ራዕ 2፡7
3. በእግዚአብሔር መንፈስ ተነድተው ቅዱሳን አባቶች የጻፉት ስለሆነ 2ጴጥ 1፡20 ትንቢት
ከቶ በሰው ፈቃድ አልመጣም ዳሩ ግን ቅዱሳን አባቶች በመንፈስ ቅዱስ ተነድተው ጻፉት፡፡
4. የሰው ልጅ ከመፈጠሩ በፊትና ወደፊት ስለሚመጣው ነገር በእርግጠኝነት ስለሚናገር ዘፍ
1፡1፣ ኢሳ 7፡14፣ ሮሜ 8፡28፣ ራዕ 1፡7፡፡
5. የሚያነቡትና የሚሰሙትን ስለሚባርክ ራዕ 1፡3፡፡
6. ዘመን የማይሽረው ስለሆነ፡፡ ማቴ 24፡35 ሰማይና ምድር ያልፋል ቃሌ ግን አያልፍም፡፡
ኢሳ 40፡8 የአምላካችን ቃል ለዘላለም ጸንታ ትኖራለች፡፡
7. ክብረ ቅዱሳንን ስለሚገልጥ (ስለሚናገር) መዝ 45፡5 ልዑል ማደሪያውን ቀደሰ፡፡ ሮሜ 8፡
28 እግዚአብሔርን ለሚወዱት እንደ ሀሳቡም ለተጠሩ እግዚአብሔር የመረጣቸው፣
ያጸደቃቸው ማን ይከሳቸዋል፡፡
8. በእድሜ እርሱን የሚበልጠው ስለሌለ፡-የመጀመርያው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል የተጻፈው
መጽሐፈ ሔኖክ ነው፡፡ የተጻፈውም በ400 ዓመተ ዓለም ነው፡፡
9. ሁልጊዜ ሲነበብ ስለማይሰለችና ብዘሁ ሚስጥራትን የያዘ ስለሆነ ቅዱስ ተባለ፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔርን ለሚያመልኩ፤ በሃይማኖት መንገድ ለሚጓዙ ሰዎች
የሕይወት መመሪያ ይሆን ዘንድ እግዚአብሔር በመረጣቸው አባቶች አማካይነት የተጻፈ
ቅዱስ መጽሐፍ ነው፡፡ ይህ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ቅዱስ እንደሌሎቹ
መጽሐፍት በተገኘበት አጋጣሚ ፣ ቦታና ጊዜ የሚነበብ አይደለም፡፡ ነገር ግን አንባቢው
አንብቦት ፍጹምና ለበጎ ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ እንዱሆን፣ መንፈሳዊውን ትምህርት
ለመማር፣ ራስን ለመገሰጽና ልቦናውን አቅንቶ በጽድቅ ስራ የተጋ ይሆን ዘንድ ልዩ የሆነ
ውስጣዊና አፍአዊ ዝግጅት ማድረግ ይኖርበታል፡፡ ‹‹የእግዚአብሔር ሰው ፍጹምና ለበጎ ስራ
ሁሉ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ ለትምህርትና
ለተግሳጽ ፣ ልብንም ለማቅናት፣ በጽድቅም ላለው ምክር ደግሞ ይጠቅማል›› እንዳለ ቅዱስ
በጳውሎስ፡፡ 2ኛጢሞ 3፤16፡፡

2.4.1.1 መጽሐፍ ቅዱስ ለማንበብ የሚደረግ ቅደመ ዝግጅት


1. አፍአዊ ዝግጅት፡- አፍአዊ ዝግጅት የሚባለው አንባቢው ለማንበብ ከመቅረቡ በፊት
ከልቡናውና አዕምሮው ውጭ ሊዘጋጀውና ሊያመቻቸው የሚገባውም ሁሉ ያጠቃልላል፡፡

2. መጽሐፍ ቅዱስን ማግኘት (መኖሩን ማረጋገጥ) ፡- ሰው ሁሉ የሚያነበው (ማንበብ


የሚችለው) የሚነበብ መጽሐፍ ሲኖር ነው፡፡ በመሆኑም እግዚአብሔርንና ፍቃድን ማወቅና

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 24
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

መፈጸም እንዲሁም ነገረ ሃይማኖትን ነገረ ቅዱሳንን መረዳት የሚፈልግ ሰው አስቀድሞ


መጽሐፍ ቅዱስ ማግኘት አለበት፡፡ የእግዚአብሔርን ድምጽ ለመስማት፣ በቃለ እግዚአብሔር
ለመቀደስ፣ የሚጠበቅበትን ኃሊፊነት ለመወጣት፣ መንፈሳዊ ሕይወቱ ምን እንደሚመስል
ለመረዳት፣ በእምነት ለማደግ፣ በመከራ ለመጽናት፣ በተስፋ ለማደር፣ ከክፋት ለመራቅና
ለመጠበቅ የሚፈልግ ክርስቲያን የራሱ የሆነ በፈለገው ሰዓት በቅርብ ሊያገኘው የሚችል
መጽሐፍ ቅዱስ ሊኖረው ይገባል፡፡ በተቻለ አቅም መጽሐፍ ቅደስ እንደ ጣት ቀለበት እንደ
አንገትም ማዕተብ ከእርሱ ባይለየው መልካም ነው፡፡

3. ማንበቢያ ቦታና ጊዜ መምረጥ፡- አንባቢው ለንባብ ከመቅረቡ በፊት የሚያነብበትን ጊዜና


ቦታ መምረጥ አለበት፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ያለው ቃል የእግዚአብሔር ቃል ነው፡፡ መጽሐፍ
ቅዱስን ማንበብ ከእግዚአብሔር ጋር መነጋገር ነውና፡፡ በመሆኑም አንድ ሰው መጽሐፍ
ቅዱስን ገልጦ ከማንበቡ በፊት ከእግዚአብሔር ጋር የሚያደርገውን ንግግር ሊያቋርጡ
የሚችል ነገሮች በአካባቢው እንዲይከሰቱ፣ ቦታና ጊዜ መምረጥ ይጠበቅበታል፡፡ ብዙ
ጫጫታና ግርግር የሌለባቸው ቦታዎች፣ ለተለየ ጉዲይ ያልተያዙ ለመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ
ብቻ የተያዘ ጊዜያት ያስፈልጋል፡፡

4. ማስተዋሻ ማዘጋጀት፡- አበው ‹‹በቃል ያለ ይረሳል በጹሁፍ ያለ ይወረሳል›› እንዳሉ


መጽሐፍ ቅዱስን በቃል ብቻ ማነብነብ ለጊዜው በአንባቢው ኅሊና ውስጥ ከሚፈጥረው
ስሜት በስተቀር ሊረሳ ይችላል፡፡ ይህ እነዳይፈጠር አንባቢው ያነበበውን እንዳይረሳው
ከሚያነበው ውስጥ የሚገነዘበውን የሚጽፍበት ማስታወሻ ማዘጋጀት ይኖርበታል፡፡

5. ውስጣዊ ዝግጅት፡- ውስጣዊ ዝግጅት የተባለው አንድ ሰው ቅዱሳት መጻሕፍን ለማንበብ


ከመመቀመጡ በፊት በልቦናው ሊያደርገው የሚገባ ዝግጅት ነው፡፡

6. የማንበብ ፍላጎትና ጉጉት፡- አንባቢው አስቀድሞ የማንበብ ፍላጎትና ጉጉት በውስጡ


ሊኖረው ይገባል፡፡ ይህ ደግሞ የቅደሳት መጻሕፍት ጥቅም ከመረዳት የሚመጣ ነው፡፡
መጽሐፍ ቅዱስን ማንበብ ከእግዚአብሔር ጋር መነጋገር ነው፡፡ ለሰው ደግሞ ከእግዚአብሔር
ጋር ከመነጋገር በላይ ክብር የለውም፡፡ ከዚህ በላይ በቅደሳት መጽሐፍት የተጻፉት ቃላት
የተሰበረውን የሚጠግኑ፣ ያዘነውን የሚያጽናኑ፣ በኃጢአት ያደፈውን የሚቀድሱ፣ የጽድቅ፣
የሰላምና የፍቅር መንገድ የሚያሳዩ ናቸው፡፡ ይህን እውነታ የተረዳ ሰው ቅደሳት
መጻሕፍትን ለማንበብ ከፍተኛ ፍላጎትና ጉጉት ያድርበታል፡፡ መዝ 118፤103፣ መዝ 118፤
72፡፡ በመሆኑም አንባቢው አስቀድሞ በሙሉ ፍላጎትና ጉጉት ለማንበብ የተዘጋጀ መሆኑን
ማስተዋል፡፡

7. መረጋጋት፡- የቅደሳት መጻሕፍትን ምሥጢር ለመረዳት ከሚያስችሉ ነገሮች መካከል


አንዱ መረጋጋት ነው፡፡ የተረጋጋ ልቡና ነገረ እግዚአብሔርን ለማስተዋል ፣ ሰማያዊውን
በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)
ገጽ | 25
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ምስጢር ለመረዳት ይችላል፡፡ በመሆኑም ማንኛውም ሰው ተቻኩሎ ፣ ተናዶ ፣ኅሊናው


በሀሳብ ተይዞ ሳለ ቅዱሳት መጻሕፍትን ከማንበብ ይልቅ የሚረጋጋበትን ሁኔታ ቢፈጥር
ይመረጣል፡፡ ምክንያቱም ሳይረጋጋ ቢያነብ ኅሊናው ከሚያነበው ኃይለ ቃል ጋር ስለማይገናኝ
በስተመጨረሻ ልቡናው ከምሥጢር ባዶ ይሆናል፡፡ መረጋጋትና ማስተዋል በሌለበት ምንባብ
ውስጥ ምሥጢረ እግዚአብሔር ሊገለጥ አይችልምና፡፡ ምሳ1፤33 ፣ ምሳ 18፤15፡፡

8. ድካምን ማራቅ፡- ከሥራ ብዛት፣ ከጤና መታወክ የተነሳ የአእምሮም ሆነ የስጋ ድካም
የሚፈጠርበት ወቅት አለ፡፡ በዚህ ወቅት ቅዱሳት መጻሕፍትን ለማንበብ ከመቅረብ ይልቅ
የሚሰማውን ድካም ዕረፍት በመውሰድ ማሳለፍ ይገባል፡፡

9. ጸሎት፡- ከእግዚአብሔር ጋር የምንገናኝበት፣ ኃይለ እግዚአብሔርን ጸጋ እግዚአብሔርን


ለማግኘት ወደእርሱ የምንቀርብበት ረቂቅ መንገድ ነው፡፡ በመሆኑም መጽሐፍ ቅዱስን
የሚያነብ ሰው እግዚአብሔር መንፈስ ቅደስ ምሥጢሩን እንዲገልጽለትና ከስሕተት
እንዲሰውረው አጥብቆ መጸለይ አለበት፡፡

10. ፈሪሓ እግዚአብሔርን ገንዘብ ማድረግ፡- መጽሐፍ ቅዱስን ማንበብ ማለት


እግዚአብሔርን ማነጋገር ነው፡፡ በመሆኑም አንባቢው በመጽሐፍ ቅዱስ አማካይነት
እያነጋገረ ያለውን እግዚአብሔርን መፍራት ይጠበቅበታል፡፡ የጥበብ መጀመሪያው
እግዚአብሔርን መፍራት ነውና፡፡ ምሳ 9፤10፡፡ መፍራት ይገባል ሲባል ፍርሀቱ
እግዚአብሔርን ከማክበር የተነሳ የሚመነጭ መሆን አለበት፡፡

11. ከመረዳት ጋር ማንበብ፡- መጽሐፍ ቅዱስ የሚነበበው ነገረ እግዚአብሔር፣ፈቃደ


እግዚአብሔርን ለማወቅና ነፍስን መንፈሳዊውን ምግብ ቃለ እግዚአብሔርን መግቦ
ከእግዚአብሔር ጋር ሊኖራት የሚገባትን አንድነት ለማጠናከር ነው፡፡ ይህን አላማ ተግባራዊ
ለማድረግ ደግሞ የግድ ምሥጢሩን መረዳት ያስፈልጋል፡፡ መጻሕፍትን ማወቅ ማለት
ምንበብ ብቻ ሳይሆን መረዳትም ጭምር ነውና፡፡

2.4.1.2 Sola scripture (scriptur alone) ስልሳ ስድስቱ መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ


ይህ አስተሳሰብ የመጣው በተሐድሶ እንቅስቃሴ (በሪፎርምኔሽን) አስተሳሰብ በአስራ
ስደስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ነው፡፡ ተሐድሶ (ሪፎርምኔሽን) ማለት the sixsthy centure
religious movement of churche’s (ለአስራ ስድስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የሃይማኖት
እንቅስቃሴ ማለት ሲሆን የፕሮቴስታንት ቸርቾች ለመመስረት የሚደረግ እንቅስቃሴ) ማለት
ነው፡፡ ለዚህም ነው ስልሳ ስድስቱ ብቻ ሲሉ የሥርዓት መጽሐፍ፤ ትውፊት፣ አዋልድ
መጽሐፍ እና የትርጓሜ መጽሐፍት አያስፈልጉም የሚሉን፡፡ አንድም መጽሐፍ ቅዱስ
ማንም ሰው እንደፈለገው ሊተረጉመውና ሁሉም ሰው ካህን ስለሆነ ሊያየው ይችላል የሚል

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 26
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

አስተሳሰብ ነው፡፡ ይህም አስተሳሰብ እንዲመጣና ስልሳ ስድሰቱ ብቻ እንዲሉ ያደረጋቸው


መጽሐፍ ቅዱስ በተለያየ ጊዜ ተተርጉሞ ተጽፏል፡፡

1.ኦሪት ዘሌዋውያን፡- ይህም ሙሴ በነበረበት ሰዓት የተጻፈ መጽሐፍ ነው፡፡ ዘዳ 9፡9

2. ኦሪት ዘሳምራዊያን ፡- ይህም ካህነ ሳምራውያን ምናሴ በዛ ዘመን የነበሩ ሳምራዊያን ያለ


መጽሐፍ ቅዱስ መምራት አትችልም ባሉት ጊዜ አጽፈውታል፡፡ ይህም ከኦሪት ዘሌዋውያን
ጋር እኩል ቁጥር አለው፡፡

3. አሪት ዘሰባው ሊቃናት፡- ቅደመ ልደተ ክርስቶስ በ275 ክፍለ ዘመን በንጉስ በበጥሊሞስ
አማካይነት ከኢብሩ ወደ ግሪክ አስተርጉሟል፡፡

4. ቭልጌት ትራንዜሽን፡- ቅደመ ልደተ ክርስቶስ በ481 ክፍለ ዘመን ጄሮም ወደ ላቲን
የተረጎመበት ነው፡፡ ወደ ላቲን ሲተረጉም ቆርጦ ይጥላል፡፡ ለምን ቢባል ከ63 እስከ 68
መ/ክ/ዘ በክርስቲያኖች ላይ በነበረው ስድት ምክንያት አይሁድ በጉባኤያቸው (በሸንጓቸው)
ተሰባስበው የክርስቶስ ሰም ያለበትን በሙሉ ቆርጠው ጣሉት፡፡ ለዚህም ነው ጄሮም አይሁድ
ስላልተጠቀሙበት ቆርጬ ጥዬዋለው ያለው፡፡ ዛሬም በፕሮቴስታንቱ ዓለም የሚያራምዱትና
የሚቀበሉት ይህንኑ ነው፡፡

5. ዴልስ ክሮስ፡- ይህም ከልደተ ክርስቶስ በኋላ 1949 አስከ 1956 በውጮች አቆጣጠር
በሙት ባሕር ዳርቻ የተገኙ ናቸው፡፡ ይህም የሙሴ አሪት፤የሰማርያውያን ኦሪት፣የሰባው
ሊቃናት ትርጓሜ እንዲሁም የሔኖክም መጽሐፍ ጭምር የያዘ ነው፡፡

ሌላኛው ስልሳ ስድስቱ ብቻ እንቀበላለን የሚሉ ከሆነ ጥያቄ ያስነሳብናል፡፡ ለምሳሌ ጥቂቶቹን
ብንመለከት፡- መላዕክት መቼ ተፈጠሩ፣ ዲያብሎስ ከየት መጣ እንዴትስ ሳተ፣ቃዬል ከየት
አምጥቶ ሚስት አገባ፣ማቴ 27፡9 ያለው በ30 ብር እንደሚሸጡት የነብዩ የኤርምያስ ትቢት
የት ነው ያለው፣ይሁዳ 1፡14 ላይ ያለው የሔኖክ ትንቢት የት ነው ያለው፡፡ እነዚህ በስልሳ
ስድስቱ የሉም ነገር ግን የሚገኙት 81 ላይ ነው የሚገኘው፡፡

2.4.1.3 ኦርቶዶክሳዊ የመሐፍ ቅዱስ አረዳድ


ቤተ ክርስቲያን መጽሐፍ ቅዱስ ወደ እርሷ የምታመጣ ሳትሆን እርሷ ወደ መጽሐፍ ቅዱስ
የምትመጣ ናት፡፡ ኦርቶ ማለት ቀጥተኛ ማለት ስለሆነ ቀጥተኛ የመጽሐፍ ቅዱስ አረዳድ
ትረዳለች፡፡ ከእነዚህ መካከል የተወሰኑት ስንመለከት፡-

1. ከኦሪት ዘፍጥረት እስከ ራዕየ ዮሐንስ ያሉት ሳትነጣጥል በአንድ ዓይነት ትቀበላለች፡፡
ምክንያቱም በማኅፀነ ብሉይ የነበረው በሐዲስ ኪዳን ተዋልዷል፡፡ አንድም ብሉይኪዳን
የሐዲስ ኪዳን መንገድ ይጠርግ ነበር፡፡ ገላ 4፡4 ፣ሲራ 4፡፡ እንዲሆም አዲስ ኪዳን ክርስቶስ
መጥቶ የመሰረታት ሳትሆን የገለጣት ናት፡፡ ዘፍ 3፡20 አዳም መልካሙና ደጉን ያውቅ
በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)
ገጽ | 27
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ዘንድ ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ፡፡ ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ ማለቱ ወልደ እግዚአብሔር የስውን
ስጋ እንደሚለብስ ሲገልጽ ነው፡፡ ዮሐ1፡1 በመጀመርያ ቃል ነበር፡፡ በተጨማሪም ምስጢሩን
ለመረዳት ብሉይኪዳን ያስፈልጋል፡፡ ምክንያቱም ብሉይ ኪዳን ለአዲስ ኪዳን መሠረት
ስለሆነ፡፡

2.. መጽሐፍ ቅዱስ የምንለካበት መንገድ ምስጢረ ስጋዊና ምስጢረ ስላሴ ነው፡፡ ስላሴ
ማለት ሦስትነት ማለት ነው፡፡ ቅድስት ስላሴ ማለት ደግሞ ልዩ የሆነች ሦስትነት ማለት
ነው፡፡ ምክንያቱም በሦስትነት ውስጥ አንድነት ስላለባት ይህም በአብ ልብነት ሦስቱም
ያስባሉ ፣በወልድ ቃልነት ይናገራሉ፣ በመንፈስ ቅዱስ እስትንፋስነት ሕያው ይኖራሉ፡፡ ዕብ
1፡2 እግዚአብሔር ዘመናትን በፈጠረበት (በተናገረበት) በልጁ ተናገረን፡፡ መለኮት ማለት
መለከ ገዛ፣ ግዛት ማለት ነው፡፡ ዮሐ 15፡26 ከአብ ዘንድ የምልክላችሁ አጽናኝ መንፈስ
በመጣ ጊዜ ስለኔ ይመሰክራል፡፡

3. በመንፈሳዊ ልብ ማንበብ ፡- 1ጲጥ 1፡20 ይህን ዕወቅ ትንቢት ከቶ ከሰው ፈቃድ


አልመጣምና… መጽሐፍ ቅዱስ ለዚህ ዓለም የመጨረሻ መልስ ነው፡፡ ምክንያቱም ሰማይና
ምድር ያልፋል ቃሌን ግን አያልፍም ይለናልና 1ቆሮ 1፡1 ዓለም በጥበቧ ክርስቶስን
ስላላወቀች ላልተረዱት ለዓለም ክርስቶስ ሆነ ብሎ ማስተማር ሞኝነት ነው፡፡ ሌላው
መጽሐፍ ቅዱስን በመንፈሳዊ ዓይን ማየት ስናቆም ተሐድሶነት (ክህደትን) እንጀምራለን፡፡

4. ፊደሉ፣ ቃሉ፣ ዓረፍተ ነገሩ በራሱ ብቻውን ሙሉ አይደለም፡፡ ዮሐ 8፡12 እኔ የዓለም


ብርሃን ነኝ የሚከተለኝ የሕይወት ብርሃን ይሆንለታል በጨለማም አይመላለስም፡፡ ማቴ 5፡
10 እናንተ የዓለም ብርሃን ናችው በተራራ ያለች ከተማ ልትሰወር አይቻላትም፡፡ በክርስትና
መኖር ማለት በራሱ በተራራ ላይ መውጣት ነው፡፡

2.4.2 ሐዋርያት የሠሯቸዉ የሥርዓት መጻሕፍት


1) መጽሐፈ ድድስቅልያና አራቱ መጻሕፍተ ሲኖዶሳት (ትዛዘ ግጽዉ፣ አብጥሊስና
ሥርዓተ ጽዮን)
2) ሁለቱ ኪዳናት (መጽሐፈ ኪዳን ቀዳማዊና ካልዕ)
3) መጽሐፈ ቀለሜንጦስ፡- የጴጥሮስ ደቀመዝሙር በሮም ኤጲስቆጶስ
1. መጽሐፈ ትዕዛዝ፡- በቁሙ ከሥራ አስቀድሞ የሚሰጥ፣ የሚጻፍ፣ የሚነገር ሕግ ሥርዓት
(አድርግ አታድርግ) የሚል ፍቃድና ደንብ ነዉ፡፡ ምልክቱ (በአኅጽሮተ ቃል ልዩ መጠሪያዉ)
ረስጠብ ይባላል፡፡ ከ72 በላይ አኝቀጾች አሉት፡፡ እነዚህም አንቀጾች ስለ ሊቃነ ጳጳሳት
ሥርዓት፣ ሢመት አተገባበር፣ ስለ መሥዋዕት አቀራረብ፣ ስለ ነዋያተ ቅድሳት ክብር፣ ስለ
ሥርዓተ ጥምቀት፣ ስለ ሥጋ ወደሙ ክብር ይዘዋል፡፡ ለምሳሌ፡- ረስጠብ 1÷2 ስለ ሊቃነ
ጳጳሳት አጠቃላይ ሥርዓት ይናገራል፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 28
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

2.. መጽሐፈ ግጸዉ፡- ሐዋርያት ለቀለሜንጦስ የሰጡት ሁለተኛ መጽሐፍ ነዉ፡፡ ምልክቱ
ረስጠጅ ነው፡፡ የእግዚአብሔርን ህልዉና ከማስረዳት ጀምሮ ስለ ምስጢረ ሥጋዌ፣ አጠቃላይ
ኢየሱስ ክርስቶስ በኢየሩሳሌም ስለ ማስተማሩና ስለ ሠራቸዉ ሥራዎች ይናገራል፡፡ 27
ያህል አንቀጾች አሉት፡፡ ረስጠጅ 30 ስለ መስዋዕትና አቀራረቡ የናገራል

3. መጽሐፈ አብጥሊስ፡- አብጥሊስ ማለት ቀኖና ማለት ነዉ፡፡ 46 የብሉይ ኪዳንና 35


የሐዲስ ኪዳን በአጠቃላይ 81 መጽሐፍት ሙሉ ዝርዝር ይዞ የገኛል፡፡ መጠሪያ(መሪ)
ምልክቱ ረስጠአ (ረስጣ) ነው፡፡ ስለ ኤጲስቆጶሳት፣ ስለ ካህናት፣ ስለ ዲያቆናትና ምዕመናን
አጠቃላይ ድርሻና መንፈሳዊ ሕይወት በሥፋትና ስለ ምስጢረ ንስሓ አሰጣጥና
አተገባበርየሚያስረዳና ትምህርተ ሃይማኖትን፣ ሥርዓተ ቤተ-ክርስቲያንን አስፈላጊነት
የናገራል፡፡ ምሳሌ ረስጣ 8 ምዕመናን ቤተ-ክርስቲያን ገብተዉ ሥርዓተ ቅዳዉን መከታተል
እነደሚገባቸዉ፡፡

4. መጽሐፈ ሥርዓተ ጽዮን፡- ሐዋርያት ለስብከተ ወንጌል ወደ ዓለም ከመላካቸዉ በፊት


በጸርሐ ጽዮን ተሰብስበዉ የሰሩትና የደነገጉት የቤተ-ክርስቲን ሥርዓት ሕግና ትምህርት
ነዉ፡፡ መሪ ምልክቱ ዓይን ነዉ፡፡ ስለ በዓለ አስተርእዮ (ኤጲፋኒያ፣ ስለ እሁድ ሰንበት በዓል
አከባበር ስለ ገሃድ ጾም ያትታል፡፡ የቀኖናቱ ብዛትም 30 የሚደርሱ ናቸዉ፡፡

5. መጽሐፈ ኪዳን፡- ኪዳን ማለት በቁሙ ዉል፣ ስምምነት፣ የፍቅርና የአንድነት መሐላ፣
ሰላማዊ ሕግ፣ ትምህርት፣ ምስጋና ማለትም ሁለቱን ወገን (እግዚአብሔርና ሰዉ ሰዉና
ሰዉን) የሚያደርግ ነዉ፡፡ ለሰዉ ረብና ጥቅም የሚሆን በተስፋ የቆሙ ቢጠብቁት በረከት
የሚያሰጥ ቢያፈርሱት ጉዳትና ጠብ የሚያመጣ ብዙ በረከት የሚያሰጥ ነዉ፡፡ መጽሐፈ
ኪዳን ኢሱስ ክርስቶስ የሐዋሪያት ቃል ከትንሳኤ እስከ ዕርገት ያስተማራቸዉ እየጠቁት
የመለሰላቸዉ ነዉ፡፡ ይህንንም ከዕርገት በኋላ በጥንታ…. ሐዋርያት ጽፈዉታል፡፡

5.1 መጽሐፈ ኪዳን ቀዳማዊ፡- ዮሐንስ፣ ጴጥሮስና ማቴዮስ ጌታችን እያጻፋቸዉ ጽፈዉታል፡
፡ 59 አንቀጾች አሉት፡፡ ስለ ሥርዓተ ቤተ-ክረስቲያን፣ የዘወትር ኪዳናት፣ ትምህርተ
ኅቡአት፣ እግዚአብሔር ዘብርሃናት፣ቅዳሴ እግዚእ፣ በእንተ ቅድሳት ያተተ ነዉ፡፡ ይዘቱ
ሥርዓተ ጸሎትና ሥርዓተ ቅዳሴ ነዉ፡፡ዘጠኙ ኪዳናት የምንላቸው፡-

ኪዳን ዘመንፈቀ ሌሊት፡- ለከ እግዚኦ ለገባሬ ኩሉ፣ አምላከ ብርሃን ወላዴ


ሕይወት፣ ንሤልስ ለከ ዘንተ ስብሐት
ኪዳን ዘነግህ፡- እግዚአብሔር አብ ወሃቤ ብርሃን፣ እግዚኦ ኢየሱስ ክርስቶስ
ስምዓነ ቅዱስ፣ ንሤልስ ለከ ቅዱስ ስብሐት
ኪዳን ዘሰርክ፡- ለከ ለአብ ዘኢይማአሰነ መደኃኔ ነፍስነ፣ ንዌድሰከ እግዚኦ፣
ለከ ዘእም ልብነ
በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)
ገጽ | 29
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

5.2 መጽሐፈ ኪዳን ካልዕ፡- ወጥ ሆኖ የተዘጋጀ ሲሆን በውስጡ፡- ስለ ካህናት ሹመትና


አገልግሎት፣ ስለ ንዑሰ ክርስቲያን ጥምቀትና ቁርባን፣ የጥጦስን፣ የሐሳዊ መሲሕን
ነገር መግለጽ፣ ስለ ክርስቶስና ስለ ዳግም ምጽአት የናገራል፡፡ ሐሳዊ ማለት "እኔ
ክርስቶስ ነኝ" ብሎ የሚመጣ አባቱ ከነገደ ዔሳዉ እናቱ ከነገደ ዳን እንደሆነ የሚነገርለት
የዓመፅና የክፋት ሰዉ ነዉ፡፡

6. መጽሐፈ ዲድስቅሊያ፡- ዲድስቅልያ ትምህርት ማለት ነዉ፡፡ 43 አንቀጾች የያዘ መድብለ


ትምህርት ወተግሣጽ ነዉ፡፡ ስለ ሰዉ ልጅ ሕይወትና ሞት፣ ስለ ፍቅረ ሰብ እና
እግዚአብሔር፣ ስለ ምስጢረ ጥምቀት፣ ስለ ጾምና ጸሎት፣ ስለ ምስጢረ ቁርባን፣ ስለ
ካህናት ክብርና አገልግሎት፣ ስለ ሥርዓተ ቤተክርስቲያን ዉስጥ ስለ ሚፈፀሙ ምስጢራት
ይናገራል፡፡

7. መጽሐፈ ቀለሜንጦስ፡- ቀለሜንጦስ ቅዱስ ጴጥሮስ ስለ ጌታችን ከተናረዉ ወስዶ


የጻፈዉ፡፡ መጠሪያዉ ጴጥ ሲሆን ይዘቱ ሥርዓተ ቅዳሴያዊ ቅርጽ አለዉ፡፡ ስለ ጽላተ ኪዳን
ቡራኬ ማለት ከኤጲስቆጶስ አዲስ ቤተ-መቅደስ የሚከበርበት ሥርዓት፣ ሥርዓተ ጥምቀትንና
በእጅ መንሳና መተያያ ጥምቀት እንደማይፈቀድ፣ ስለ ሥርዓተ ቁርባን፣ በቀኖናዊ ክፍሉም
ስለ ሰምዓታትና ስለ ክብረ በዓላት፣ ስለ ሰንበተ ክርስቲያን የዕረፍት ቀን መሆን
በተጨማሪም በሰሙነ ሕማማት የምእመናን ከተግባረ ሥጋ ማረፉ ግዴታ ስለመሆኑ
ያትታል፡፡

2.5 Passion week ሰሙነ ሕማማት


ይህ ሳምንት የዐብይ ጾም የመጨረሻው ሳምንት ነው። በላቲን በግሪክና በኢንግሊዝኛ እንዲህ
ተብሎ ይጠራል፦ Holy Week (Latin: Hebdomas Sancta or Hebdomas Maior,
"Greater Week"; Greek: Ἁγία καὶ Μεγάλη Ἑβδομάς, Hagia kai Megale
Hebdomas, "Holy and Great Week") in Christianity is the week just before
Easter. (ቅዱስ ሳምንት በላቲን Hebdomas sancta ወይም Hebdomas Maior በመባል
ይጠራል ይህም ማለት ታላቁ ሳምንት ማለት ነው። በግሪክ Hagia Kai Magale
Hebdomas ሲባል ትርጓሜው ቅዱስና ታላቁ ሳምንት ይባላል። በክርስትና ከትንሣኤው
በፊት ያለው ሳምንት ነው። ከሰርክ ሆሳዕና ጀምሮ እስከ ትንሣኤው ይዘልቃል። በሐዋርያት
የሕግ መጽሐፍ ላይ የጾም ቀናትን በጥንቃቄ እንድንጠብቃቸው ታዟል (Apostolic
constitution v 18,19)

ከሦስተኛው መቶ አጋማሽ እስከ አራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን በጾም ወቅት ከሥጋ መታቀብ
እንዳለብንና ዓርብንና ቅዳሚት ስዑርን ፍጹም ጾም እንድንጾም ታዟል። ይህ ማለት አኹን
ሥጋ ተፈቅዷል ለማለት ሳይኾን ጥንትም ጀምሮ በጾም ሥጋን መብላት የተከለከለ ነው

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 30
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ለማለት ነው። የአሌክሳንድርያው ዲዮናስዮስ ስለ ጾም በገለጠው ቀኖናዊ መልእክቱ ዘጠና


አንድ የጾም ቀናትን በጥንቃቄ መጠበቅ አስቀድሞ የተሠራ ጠቃሚ ሕግ መኾኑን በዘመኑ
ገልጧል Apostolical Constitutions v.18 ሰሙነ ሕማማት በተለየ ኹኔታ ጊዜ ተሰጥቶት
የክርስቶስን ሕማም ለመሳተፍ የምንዘክረው ልዩ ሳምንት ቢኾንም ከዚያ ሳምንት ውጭ
መከራ ክርስቶስ አይታሰብም ለማለት እንዳይደለ መረዳት እጅግ ተገቢ ነው።

የክርስቶስን ሕማማት ማሰብ የክርስትና መሠረት ነው። ክርስትና ከክርስቶስ መከራ ውጭ


ኾኖ አይገለጥም። እውነተኞች ምእመናንን ስለ እውነት ብለው የክርስቶስን መከራ
ይሳተፉታል። ስማችሁ የለም የሚለው መጽሐፍ ደግሞ ስለ ሰሙነ ሕማማት መነሻ እንዲህ
የሚል መረጃን ይሰጠናል፡፡ የሕማማትን ወቅት ከመጀመርያው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ
ክርስቲያኖች ያከብሩት እንደነበር የሚያሳዩ ጥንታውያን መዛግብት አሉ፡፡ በሕግ ደረጃ
ክርስቲያኖች በሰሙነ ሕማማት ከማንኛውም ሥራ ነጻ ሆነው፣ ፍርድ ቤቶችም ተዘግተው
እንዲከበሩ የወሰነው ደግሞ ታላቁ ቆስጠንጢኖስ ነው፡፡ እስከ አራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን
አዳዲስ ክርስቲያኖች ለመጠመቅ ይመርጡት የነበረው ጊዜ የትንሣኤን ቀን ነበር፡፡ ለዚህም
ሁለት ዓይነት ምክንያቶች ነበሯቸው፡-

የመጀመርያው ሰሙነ ሕማማትን በልዩ ሁኔታ ጾመው በትንሣኤው ቀን መጠመቁ ልዩ


የሆነ መንፈሳዊ ኃይል ስለሚሰጥ ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ እንደ ሐዋርያው ቅዱስ
ጳውሎስ ትምህርት መጠመቅ ከክርስቶስ ጋር ሞቶ ከክርስቶስ ጋር መነሣት ነው። በዚህ ልዩ
ሳምንት ካህናትና ምእመናን በነግህ፣ በሠልስት፣ በቀትር፣ በተሰዓትና በሠርክ ወደ ቅድስት
ቤተ ክርስቲያን በመጓዝ ስለ ጌታችን ኢየስስ ክርስቶስ ሕማማተ መስቀል የሚያዘክረውን
ምዕራፍ ከቅዱሳት መጻሕፍት በማንበብና በመጸለይ ሕማሙንና ሞቱን ይዘክራሉ፣ ቅዱስ
ያሬድ በመጨረሻው ሳምንት በየዕለቱ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ላይ የተፈጸመውን ነገረ
መስቀል በተመለከተ ያዘጋጀውን መዝሙር ይዘምራሉ፤ አብዝተው ስግደትን ይሰግዳሉ፡፡ ይህ
ኹሉ እንዳለ ኾኖ ይህ ሳምንት ቅዱስ ሳምንት ታላቅ ሳምንት እየተባለ መጠራቱ ተገቢ
ነው። ቅድስና የባሕርይ ገንዘቡ የኾነ ጌታ እኛን ለመቀደስ የእኛን ሕማም ተቀብሏልና።

እርሱ ላይ ይደርሱ የነበሩት እያንዳንዶቹ መከራዎች እኛን ከባርነት ወደ ነፃነት ለማሸጋገር


የተደረጉ የካሣ ሥራዎች ናቸው። ርቱዐ ሃይማኖት የዚህችን ዕለት ታላቅነት ለመግለጥ
እንዲህ ነበር ያለው፦ ከጾምናቸው ዕለታት ኹሉ ወርቅ ከብር እንዲሻል በሰማይ በሕማማት
የምንጾመው አንዲቷ ዕለት ትበልጣለች። ይህ አባት መልሶ የዕለቷን ታላቅነት ለማመልከት
በሰሙነ ሕማማት የቻለ ቀንም ሌሊትም ለሰባት ቀን ይጹም፤ የማይችል ሦስት ቀን ይጾም
ማንኛውም ክርስቲያን ከዳቦ፣ ከጨው፣ ከውኃ በቀር አይመገብ፤ ከሲዖል እስከ ሚወጣበት
ማንም ቢኾን አይሥራ። ሦስት ዕለት መጾም የማይቻለው ምጽዋዕት ይስጥ፤ ችግረኛ ከኾነ
አብዝቶ ይስገድ። ጌታችን በተሰቀለባት ዕለት ግን ለመጾም ያልደረሱ የተጠመቁ ሕፃናትም
በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)
ገጽ | 31
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ከጠዋት እስከ ምሽት ይጹሙ በዚህ ቀን ከክርስቶስ ጋር መከራ የሚቀበል ክርስቲያን ብፁዕ
ነው። "አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ እኛ ሲል የተቀበላቸውን መከራዎች
የምናስብበትን ሳምንት እንዴት ልናከብር እንደሚገባ ገለጸልን።

የሐዋርያት ቀኖናም በዚህ ሳምንት ውስጥ ያሉትን ሥርዓቶች አስመልክቶ እንዲህ ይላል
«ይልቁንም በእነዚህ በስድስቱ ቀኖች መጾም የሚችል ቢኖር ሁለት ሁለት ቀን ይጹም፡፡
የማይችል ግን አንድ አንድ ቀን ይጹም፡፡ ሌሎችን ቀኖች እስከ ዘጠኝ ሰዓት ይጹሙ፤
እችላለሁ የሚል ግን ፀሐይ እስኪገባ ይጹም፡፡ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ተሰብስባችሁ
መጻሕፍተ ኦሪትን እና መጻሕፍተ ነቢያትን፣ የዳዊትንም መዝሙር እያነበባችሁ በምስጋና
በጸሎት ዶሮ እስከሚጮኽ ድረስ የሌሊቱን ሰዓት ጠብቁ፡፡ ባለመፍራት እንዳይጠፋ ውስጣዊ
ሰውነቱን ይመርምር፡፡ ጾምን ከመፍታታቸው በፊት ገላቸውን ይታጠቡ፤ ሁሉም መብራት
የሚያበሩ ይሁኑ፡፡ የቻለ ዓርብ እና ቅዳሜ ሁለት ቀን ይጹም፤ ሁለት ቀን መጾም የማይችል
በሽተኛ ቢሆን ግን ቀዳም ሥዑርን ይጹም፡፡ የኀዘን ቀን ስለሆነች፡፡ እንጀራ እና ጨውም
አይቅመስ፡፡

በዚህ ሳምንት ውስጥ የእኛ በደል ያመጣብንን ርግመንና ፍዳ በማሰብ እኛ ምን ያህል


ከእግዚአብሔር ራሳችንን እንዳራቅንና እግዚአብሔር ደግሞ ምን ያህል እንዳፈቀረን
መከራውን ኹሉ በእኛ ቦታ ተገብቶ እንደተቀበለልን እያሰብን አካሎቻችንን ያን መከራ
እንዲሳተፉ በእውነተኛ ፍቅር ተመሥርተን በጾምና ጸሎት በስግደትም ለክርስቶስ መከራ
እናስገዛቸዋለን። አንድ ምእመን የታመመ ቢሆን ወይም ክርስቲያን በሌለበት አገር ሆኖ
ሳያውቅ የሕማማት ሰሞን ቢያልፍበት ወይንም በደዌ ውስጥ ሆኖ ቢቀርበት ከበዓለ ሃምሳ
በኋላ ሰውነቱን በማድከምም ደስታን ያድርግ፡፡ ምክንያቱም በበዓለ ሃምሳ ንስሓ መግባት
ተከልክሏልና፡፡

2.6 በበዓለ ሃምሳ ንስሓ ለምን ተከለከለ?


በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ያለ ምክንያት የሚደረግ ያለ ምሥጢርም የሚከወን ምንም ነገር
የለም:: የሃይማኖትን ትምህርት አብዝተን በተማርን ቁጥር የምናውቀው አለማወቃችን
ነውና ምንም ያህል ብንማር፣ የአዋቂነት መንፈስም ቢሰማን ከመጠየቅ ወደ ጐን አንበል::
መጠየቅ ለበጐ እስከሆነ ድረስ ሁሌም መልካም ነው:: ግን ልብን እያጣመሙ ቢያደርጉት
ደግሞ ገደል ይከታል:: በዓለ ሃምሳ ድንገት እንደ እንግዳ ደርሶ፣ እንደ ውሃ ፈሶ የመጣ
ሥርዓት አይደለም:: ይልቁኑ ምሳሌ ተመስሎለት በብሉይ ኪዳንም ሲከወን የነበረ እንጂ::
እንደሚታወቀው እስራኤል ከግብጽ ባርነት በ9 መቅሰፍት፣ በ10ኛ ሞተ በኩር ወጥተው፣
በ11ኛ ስጥመት ጠላት ጠፍቶላቸው ወደ ምድረ ርስት ተጉዘዋል:: ቅዱስና የእግዚአብሔር
ሰው ሙሴም ከእግዚአብሔር እየተቀበለ ብዙ ሥርዓቶችን ለቤተ እስራኤል አስተምሯል::
እነዚህ ሥርዓቶች ሁሉ ለሐዲስ ኪዳን ምሥጢረ ድኅነት ጥላና ምሳሌዎችም ነበሩ::
በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)
ገጽ | 32
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

በኦሪት ዘሌዋውያን ላይ ጌታ እንዲህ ይላል: - "ከሰንበት ማግስት ፍጹም ሰባት ጊዜ ሰባት


ቀን ቁጠሩ እስከ ሰባተኛ ሰንበት ማግስት ድረስ አምሳ ቀን ቁጠሩ:: አዲሱንም የእህል ቁርባን
ወደ እግዚአብሔር አቅርቡ::" (ዘሌ. 23:15) ይህም "በዓለ ሰዊት (የእሸት በዓል)" የሚባል
ሲሆን ከፋሲካ 7 ሱባኤ (49 ቀን) ተቆጥሮ በሰንበት (ቅዳሜ) ማግስት (እሑድ ቀን) በዓለ
ሃምሳ ይውላል፡፡ በዓሉ በግሪክኛው "ዸንጠቆስቴ (Pentecost)" ይባላል፡፡ "በዓለ ሃምሳ" እንደ
ማለት ነው፡፡ ለዚያም ነው ቅዱስ መጽሐፍ የመንፈስ ቅዱስ ለሐዋርያት በዚህ ቀን
መሰጠትን ሊነግረን ሲጀምር "ወአመ ተፈጸመ መዋዕለ ዸንጠኮስቴ…. " የሚለው፡፡ (ሐዋ.
2:1) በዓለ ሃምሳ (50ው ቀናት) በብሉይ "የእሸት በዓል" ቢባሉም ለሐዲስ ኪዳን ግን
"የሰዊት (እሸት) መንፈሳዊ" ዕለታት ናቸው፡፡ ጌታ መድኃኔ ዓለም ስለ እኛ መከራ ተቀብሎ:
ሙቶ ከተነሳ በሁዋላ 50 ያሉት ቀናት የዕረፍት: የተድላ የመንፈሳዊ ሐሴት ቀናት ናቸው::
በእነዚህ ዕለታት ማዘን፣ማልቀስ፣ ሙሾ ማውረድ፣ ንስሃ መግባት ወዘተ አይፈቀድም::
ምክንያቱም

1. ለእኛ ካሣ በጌታችን መፈጸሙን የምሰናስብባቸው ቀናት ናቸውና:: በእነዚህ ዕለታት


ብናዝን "አልተካሰልንም" ያሰኛልና::
2. በዚህ ጊዜ መስገድ: መጾም "ክርስቶስ በከፈለልን ዋጋ ሳይሆን በራሴ ድካም
(ተጋድሎ) ብቻ እድናለሁ" ከማለት ይቆጠራልና::
3. "ፍስሐ ወሰላም ለእለ አመነ - ላመን ሁሉ ደስታና ሰላም ተደረገልን" ተብሎ በነግህ
በሠርክ በሚዘመርበት ጊዜ ማዘን ሲጀመር ካለማመን ሲቀጥል ደግሞ "ደስታው
አይመለከተኝም" ከማለት ይቆጠራልና::
4. 50ውም ቀናት እንደ ዕለተ ሰንበት ይቆጠራሉና:: መጾምና መስገድ በዓል ያስሽራልና::
5. ዋናው ምሥጢር ግን እነዚህ 50 ዕለታት የአዝማነ መንግስተ ሰማያት (የሰማያዊው
ዕረፍት) ምሳሌዎች ናቸው::

ስለዚህ በእነዚህ ቀናት መጾም፣ መስገድ "መንግስተ ሰማያት ውስጥ ከገቡ በሁዋላ ድካም፣
መውጣት መውረድ አለ" ያሰኛልና ነው:: በዚያውም ላይ "ኢታጹርዎሙ ጾረ ክቡደ (ከባድ
ሸክም አታሸክሙ)" የተባለ ትዕዛዝ አለና ቅዱሳን አበው በጾም የተጐዳ ሰውነት ካልጠገነ
ወጥቶ ወርዶ : ሠርቶ መብላት ይቸግረዋልና ሰውነታችን እንዲጠገን : ይህንን በፈሊጥ
ሠርተዋል:: ስለዚህም:- "ሐጋጌ አጽዋም እምስቴ:: ወሠራዔ መብልዕ በዸንጠኮስቴ::" እያልን
አበውን እናከብራለን:: (አርኬ) ስለዚህ በበዓለ ሃምሳ ጾም፣ ስግደት፣ ንስሃ፣ ሐዘን፣ ልቅሶ፣
የለም::

<<ግን ይህንን ተከትሎውን ቀን ሙሉ ሆድ እስኪተረተር ከበላን ጉዳቱ ሥጋዊም


መንፈሳዊም ይሆናል>> አበው እንደነገሩን "እንደ ልባችሁ ብሉ" ሳይሆን የተባለው "ጦም
አትዋሉ" ነው:: ለምሳሌ:- በልቶ ጠጥቶ ከሚመጣ ኃጢአት፣ ክፋትና ፈተና ለመጠበቅ
በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)
ገጽ | 33
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

50ውን ቀናት ጥሬ የሚበሉ አሉ፣ ጠዋት ተመግበው ከ24 ሰዓት በሁዋላ ጠዋት የሚመገቡ
አሉ፣ መጥነው ጥቂት በልተው አምላካቸውን የሚያመሰግኑ አሉ፣ ነዳያንን አጥግበው
እነርሱ ከነዳያን ትራፊ የሚቀምሱ አሉ:: እኛም ከእነዚህ መካከል የሚስማማንን መርጠን
ልንከውን በተለይ ደግሞ በጸሎት ልንተጋ ይገባል:: አልያ ብሉ ተብሏል ብለን ያለ ቅጥ
ብንበላ : ብንጠጣ እኛው ራሳችን የሰይጣን ራት መሆናችን ነውና ልብ እንበል::
ማስተዋልንም ገንዘብ እናድርግ:: "እንደ ሥጋ ፈቃድ የሚኖሩ የሥጋን ነገር ያስባሉና:: እንደ
መንፈስ ፈቃድ የሚኖሩ ግን የመንፈስን ነገር ያስባሉ:: ስለ ሥጋ ማሰብ ሞት ነውና:: ስለ
መንፈስ ማሰብ ግን ሕይወትና ሰላም ነው:: ስለ ሥጋ ማሰብ በእግዚአብሔር ዘንድ ጥል
ነውና:: ለእግዚአብሔር ሕግ አይገዛምና:: መገዛትም ተስኖታል:: በሥጋ ያሉትም
እግዚአብሔርን ደስ ሊያሰኙት አይችሉም::" (ሮሜ. 8:5)

2.7 የሰሙነ ሕማማት ሥርዓት


ሰሙነ ሕማማትን፡- ከሌሎች የዐቢይ ጾም ሳምንታት ልዩ የሚያደርገው ሥርዓት አለ፡፡
በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተክርስቲያናት ሥርዓትና ደንብ መሠረት በሰሙነ ሕማማት
ከጸሎተ ሐሙስ በስተቀር ቅዳሴ አይቀደስም በሐሙስ ቢቀደስም ምእመናን ቅዳሴውን
የስርቆት ቅዳሴ ይሉታል ደውል እየተደወለ ቃጭል እየተቃጨለ ስለማይገባ፤ ስብሐተ ነግህ
አይደረስም፤ ጸሎተ ፍትሐት አይጸለይም ጸሎተ አስተስርዮም አይደረግም፡፡ ጥምቀተ
ክርስትናም አይፈጸምም፡፡ ከላይ የተዘረዘሩት የቤተ ክርስቲያን ሥርዓቶች አስቀድሞ በዕለተ
ሆሣዕና ይከናወናሉ፡፡ በተጨማሪም ማንኛውም ክብረ በዓል በዚህ ሳምንት ቢውል ከትንሣኤ
በኋላ ይከበራል፡፡ ይህም በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ የጸና ኦርቶዶክሳዊ
ሥርዓት ነው፡፡ ይህ ኹሉ የሚከናወነው የክርስቶስን ሕማም በምሳሌ ወይም በትምህርት
ከመግለጥ ይልቅ በተግባርም እየተሳተፍን እንድንጾምና እንድንጸልይ ቀድሞ የነበርንበት
የርግመን ዘመናችን የተለወጠልን በምን ዓይነት መከራ እንደኾነም በአካሎቻችን እንድንሥል
ለማድረግም ነው።

ሰሙነ ሕማማት ዘመነ ፍዳን በአዳም ምክንያት የወደቀብንን ርግማን የምናስታውስበትና


ከዚያም ጭንቅና መከራ የተላቀቅነው በወልደ እግዚአብሔር ሥጋዌና ስለእኛ ሲል
በተቀበላቸው መከራዎች እንደኾነ ተረድተን እስከ ሕይወታችን ኅልፈት ድረስ በሕሊናችን
ቀርጸን በልባችን አትመን እንድንኖር ለማድረግ ነው። ይህ ሳምንት ዘመነ ፍዳን የምናስብበት
ሳምንት ስለኾነ በዘመነ ምሕረት የሚደረጉ ሥርዓቶች ማለትም መስቀል መሳለም፣ ፍትሀት
ክርስትናና ሌሎችም ሕግጋት አይፈጸሙበትም። መረዳት ያለብን መሠረታዋ ነገር ይህ
ሳምንት ያለፈውን ዘመን ፍዳችንን እንዳንረሳና ያዳነንም የተቀበለልንን ሕማምና የካሣ ሥራ
እንድንዘክር ሥርዓት የተሠራበት ሳምንት እንጂ ሙሉ በሙሉ አኹን ያለነው በዘመነ ሐዲስ

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 34
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

አይደለም ለማለት እንዳይደለ የታወቀና የተረዳ ስለኾነ አንዳንድ የሐዲስ ኪዳን ሥርዓቶች
ሲደረጉ ብናይ እንዴት ልንል አይገባንም።

አንዳንድ ምእመናን መስቀል በካህናት እጅ ተይዞ ቡራኬ በዚህ ሳምንት ስለማይሰጥበት


በአንገታችን ላይ ያለውንም መስቀል ማውለቅ አለብንን? ብለው ጥያቄ ያነሣሉ ይህ በእርግጥ
በሥርዓት መጽሐፍ ያልተጻፈ ስለኾነ እንዲያ ማድረግ ተገቢ አይደለም። በአንገታችን
የምናስረው መስቀል በቤተክርስቲያን ጉልላት ላይ ያለውን መስቀል ይመስላልና። ሕማማት
ነው ተብሎ መስቀሉ ከጉልላቱ ላይ እንደማይወርድ ጉልላት ከተባለ ከምእመናንም አንገት
ላይ መስቀል መውረድ የለበትም።

ክርስቶስ በሕማማቱ የፈጸመውን የፍቅር ጉዞ በእውነተኛ ፍቅር ውስጥ ገብተው የተመለከቱ


የክርስቶስ ወዳጆች ጫማን ሳይጫሙ በባዶ እግር ኾነኽ መስቀልን በተሸከምክ ጊዜ ለተጓጓዙ
እግሮችህ ክብር ይገባቸዋል፤ ወደ ዕፀ በለስ የገሰገሱ የአዳምን እግሮች ሊክሱና ሊያድኑ
ደምተዋልና ብለው እግሮቻቸውን እሾኽ እየወጋው ድንጋይ እየመታው በባዶ እግራቸው
ሰሙነ ሕማማትን በመቆየት እግራቸውን ከክርስቶ እግር መከራ የሚያሳትፉ አሉ።
አንዳንዶቻችን ደግሞ ወደ ክርስቶስ ፍቅር ውስጥ መግባትን ያልወደድን ዓለምን ከእርሱ
ይልቅ አስበልጠን የወደድን ኾነን ሳለን ከጫማ ውጭ ያላኖርነውን እግር ከጫማ ውጭ
ስናደርገው ከስስነቱ የተነሣ ወዲያውኑ ሲደማብን ከእንግዲህ ወዲህ እንዲህ አላደርግም ብለን
በልባችን የምንቆርጥ ሰዎች አለን ይህ በፍቅር ሳይነኩ ጀምረው በፍቅር ሳይነኩ
የሚፈጽሙት የአንዳንዶቻችን የሰሙነ ሕማማቱ ትዕይንት ነው።

ርቱዐ ሃይማኖት ሰባት ቀን ጹሙ ያለውን የሚፈጽሙ የክርስቶስ ማኅደር የኾኑ አባቶች


እንዳሉ ኹሉ በራሳችን ዝለትና ለኃጢአት ካለን ዝንባሌ የተነሣ አንዲትን ቀን መቆየት
እያቃተን የቀኗን ማለቅ በጉጉት የምንጠብቅ ደካሞችም አንጠፋም። ሕማማትን የክርስቶስን
መከራ በፍቅር ለመሳተፍና አብሮ ለመቀበል እንጂ መጨረሻ ላይ ሲያመን በሕማማት ጊዜ
እንዲህ አድርጌ እኮ ነው ለማለትና ለመዘባበት አይደለም። ሌላው ይሁዳ (Judas Iscariot)
ስሙን የገለበጠና የፍቅርን አምላክ በማስመሰል ሰላምታ አሳልፎ የሰጠ ሰው ስለኾነ ይሁዳዊ
ግብርን ለመቃወምና ለማውገዝ በዚህ ሳምንት መሳሳም አይቻልም። በለቅሶ ቤት ሀዘን እንጂ
ደስታ የለምና በልቅሷችን ሳምንት በምድራዊ ደስታ ልናጌጥ አይገባምና። የሰላም ምንጭ
የሰላም መገኛ በክፉዎች ምክንያት ሰላማዊ ያልኾነ ሥራ እየተሠራበት የምን ሰላም አለና
ነው ከሕማማቱ በፊት ባለ መንፈስ ውስጥ ኾነን ሰላም የምንባባለው? በኢየሩሳሌም በዚህ
ሳምንት ውስጥ ያለችውን ዐርብ ዕለት ዐሥራ አራቱን ምዕራፋት መስቀሉን ተሸክመው
ይጓዛሉ። የክርስቶስን ሕማምና እንግልት በገቢር ያለፈባቸውን ምዕራፋት በማለፍ
ይሳተፋሉ።

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 35
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

በዚህ ታላቅ ሳምንት ውስጥ የክርስቶስን መከራ በማሰብ ገጹ የጠቆረውን ዮሐንስ ወንጌላዊን
ወደ መምሰል ማደግና ከኹሉም አብልጣ በስቃዮቹ ውስጥ በእናትነት ፍቅሯ እየደማች
የተሰቃየችውን ንጽሕትና ቅድስት እናታችን ድንግል ማርያምን መርሳት አይገባንም። ወደ
ክርስቶሰ የሕማማቱ ቤት መግቢያ በሮች እኚህ ናቸውና። በዚህ ሳምንት ውስጥ ክፉ ሥራ
የማይወዳጁትን አይሁድ ከሮማዊያን ጋር አወዳጅቶ በአምላካችን ላይ ስቃይን እንዳደረሱበት
እያሰብን ክፉ ከተባለው የክፋት ምንጭ (the father of evil) ጋር ተወዳጅተን የክርስቶስን
ስቃይ የረሳንባቸውን ጊዜያት በማዘከር ልናነባ ይገባናል። በዚህ ሳምንት ውስጥ ጌታን
አሳልፎ ከሰጠው ከይሁዳ ወገን እንኾን? ወይንስ ይህን ሰውዬ አላውቀውም ካለው ከጴጥሮስ?
የፈጸማቸውን ድንቅ የአምላክነት ሥራውን በትዕቢት ዕውርነት ምክንያት ከሚመለከቱት
አይሁድ ወገን እንኾን ወይስ ጌታን ለመስቀል ከወደዱት ከሮማዊያን ወታደሮች? በእርግጥ
በኖርንባቸው የዕድሜ ልኬታችን ውስጥ በጌታችን ላይ ከተነሣሡትና መከራን ካደረሱበት
ሰዎች አንዱን መኾናችንን መርምረን ይኾን? አምላካችን እግዚአብሔር በሕማማቱ ወደ
ፍቅሩ ይክተተን፡፡

2.8 የዐብይ ጾምሥራዓት ከሌሎች አፅዋማት ለምን ተለየ?


አጽዋማት ስንመለከታቸው ሰባት ናቸው፡፡ ከእነዚህም አጽዋማት መካከል የዐብይ ጾም
አንዱና ዋነኛው ነው፡፡ ዐብይ ማለት ታላቅ፣ ከፍተኛ፣ የበላይ ማለት ነው፡፡ ለምን ዐብይ
ተባለ ብንል ጌታችን መደኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶ የጾመው ጾም ስለሆነ እንዲሁም አበው
ነብያት እነ ሙሴ፣ ኤልያስ፣ ዳንኤል፣ ሕዝቅኤል አርባ ቀንና ሌሊት ያለ ምግብና ያለ ውኃ
የጾሙት ስለሆነ ዐብይ ተባለ፡፡ ነብያት ክርስቶስን ይወርዳል ይወለዳል ብለው በተስፋ
የጠበቁት ነው፡፡ አንድም የጌታችን ጾም ዋዜማ ነበር፡፡ አንድም የዐብይ ጾም 40 ቀንና ሌሊት
የጾመው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዐብይ ታላቅ ስለሆነ እና ፈጣሪ የሰራው
ሕግና ስርዓት ስለሆነ ዐብይ ተባለ፡፡ የዚህ ጾም ሥርዓት ስንመለከት በሐዋርያት ሲኖዶስ
በረስጣ በፍትህ መንፈሳዊ ተፅፏል፡፡ ሌሎች አጽዋማት ስንመለከተው ዘጠኝ ዘጠኝ ሠዓት፣
ገሃድ አስራ ሦስት ሠዓት፣ ከሕረቃል (ዘወረደ) ሰኞ አስከ አርብ አስራ ሁለት፣ ከቅድስት
ሰኞ እስከ ኒቆድሞስ አርብ አስራ አንድ ሠዓት፣ ከሆሳዕና ሰኞ እስከ ረዕቡ አስራ ሦስት
ሠዓት፤ ከጾሎተ ሐሙስ አስከ ትንሳኤ (አክፍሎት) አርባ ስምንት ሠዓት ይጾማሉ፡፡

ቅዳሜና እሑድ ምንም እንኳን ከጥሉላት ምግብ ብንከለከልም አይጾሙም፡፡ ጾሙ ስንጾመው


ሁሉን ነገር በሀዘን፤ በምፅዋት፣ በብዙ ስግደት ነው፡፡ በቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ቅዱስ
ያሬድ በጸደይ፣ በክርምት፣ በበጋ፣ በበልግ በተለየ መልኩ እራሱ የቻለ ቀለም በጾመ ድጓ
አስቀምጦለታል፡፡ በዐብይ ጾም ከበሮ፣ ጽናጽል፣ መስቀል፣ እልልታ፣ ጭብጨባ የለም፡፡
ምክንያቱም ቅዱስ ያሬድ በጾመ ድጓው ያዘጋጀለት በዝማሜ እና በዘንግ ብቻ ነወ፡፡ በዚህ
ጾም የሚደርሱት ውዳሴ ማርያም ዘወትር፣ መስተጋብዕ ጠዋት፣ አርባይት እሑድ፣ አርያም

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 36
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

በእየለቱ፣ ሠለስት በእየሠዓቱ ነው፡፡ ቅዳሴው ግዕዝ ነው፣ ሌሊት ሠዓታት ይቆማል፣
ስብሐተ ነግህ አይቋረጥም በተጨማሪም የገዳም አባቶች ወደ ዋሻ (ወደ ባዕታቸው) ገብተው
ይጾሙታል፡፡ በዚህ ጾም ወቅት የሚውሉ በዓላት ተለዋጭ ይደረግላቸዋል ምክንያቱም
በበዓል ፍስሐ ደስታ ስለሚደረግ እና በዐብይ ጾም ግን በሐዘን እንድንጾማ ስለታዘዝን ነው፡፡

2.9 ሴት የወንድን ልብስ አትልበስ


በኦሪት ዘዳግም ምዕ ፳፪፥፭ ፦ ሴት የወንድን ልብስ አትልበስ፣ ወንድም የሴትን ልብስ
አይልበስ፤ ይህን የሚያደርግ በአምላክህ በእግዚአብሔር ዘንድ የተጠላ ነውና። በማለት
እግዚአብሔር ፈቃዱን በሊቀ ነቢያት በቅዱስ ሙሴ በኩል ነግሮናል። አምላካችን
እግዚአብሔር ለእኛ የሚነግረን ነገር ኹሉ እጅግ ጠቃሚ ነው። በመኾኑም ከጥርጥር
መንፈስ ወጥተን ልንቀበለው ይገባናል። በዚህ ንባብ ውስጥ ያለው ትርጓሜው
እንደሚከተለው ነው፦

፩ ወንድ የሴትን ልብስ አይልበስ ሴትም የወንድን ልብስ አትልበስ። ወንድ የራሱ የኾነ
ልብስ አለው፤ ሴትም የራሷ የኾነ ልብስ አላት፤ በመኾኑም አንዱ የአንዱን ልብስ አይልበስ
የሚለው ቃል ከእግዚአብሔር የተሰጠ በመኾኑ ከእግዚአብሔር አልፎ መልካም የኾነውን
ማወቅ የሚችል ስለሌለ፤ ትዕዛዙን ከልብ ኾነን ልንቀበል ይገባናል። ክርስቲያን የኾነ ኹሉ
ተቃራኒ ልብስ አይልበስ፤ ይህ ከአምላኩ የሚለየው ነውና። እዚህ ጋ በጣም የሚያስደንቀው
ብዙ ሴቶች ሱሪ ማድረግ ምን ችግር አለው ይላሉ፦ ግን በቅንነት ኾነን ብናስብ ሱሪ
የወንዶች ልብስ መኾኑ በኹሉ ዘንድ ተቀባይነት ያለው እውነታ ነው።

ሱሪ ወንዶች ቀሚስን ሴቶች ይልበሱ የሚለውን ሥርዓት መቼ እንደተወሰነ፣ ከማን


ሥርዓት እንደተላለፈ ለማወቅ ብዙ ጥናቶችና ምርምሮች ማድረግ ይጠበቅብናል። ይህን
ጥናትና ምርምር ለማድረግ ደግሞ ወደ ጥንቱ ተጉዘን ሃይማኖታዊ ባህላዊ ታረካዊ የኾኑ
ቅርሶችን መጻሕፍትን መመልከት ግድ ይለናል። የሰው ልጅ ሕግ ሳይሰራ በሕገ ልቡና
የሚኖር ስለነበር መጥፎ ነገሮችን ከመሥራት ሕግ ሳይወጣለት በልቡናው ሕግ እየተመራ
ይከለከል ነበር። በቤት ውስጥም ኾነ በውጪ የሚሠራውን ሥራ በቡድን በነጠላ እየተለየ
መሥራት ጀመረ። ወንዶች የዱር አውሬን ለማደንም ኾነ ከሚደርስባቸው ጥቃት ለመከላከል
በውጭ ያለውን ሥራ ሲሠሩ በቤት ያለውን ሥራ ደግሞ ሴቶች ይሠሩ ነበር። በዚህ ጊዜ
ነበር ወንዶች ለመሮጥ ለመታጠቅ ለማምለጥ ለመዝለል ያመቻቸው ዘንድ ሱሪን መልበስና
ማዘጋጀት የጀመሩት። ሴቶቸም በቤት እየተሸፋፈኑ እየተሸለሙ በቤት ያለው ሥራ
መሥራት የጀመሩት።

ይህ በሕገ ልብና ነው። ወንዶችን በተለይ ካህናት ሱሪን ይልበሱ የሚል ምስክር ግን አለ ዘጸ
፴፱፥፳፰። ከዚህም ካህናት ወንዶች ስለኾኑ ሱሪ እንዲለብሱ ከተባለ ሴቶች ሴት በመኾናቸወ

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 37
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ሱሪ ልልበስ ማለት አይችሉም ማለት ነው። ሴቶች ኾይ ሱሪ አትልበሱ የሚል የለምና


እንለብሳለን አትበሉ ልበሱ የሚል ጽሑፍም የለምና። ይልቁኑ ሴት የወንድን ልብስ
አትልበስ ከተባለ ከወንድ ወገን የኾኑት ካህናት ሱሪን ይልበሱ የሚል በመጽሐፍ ከተገኘ
ሱሪን አለመልበስ እንጂ መሞገት ጥቅም የለውም። በሌላ በኩል ረዥም ዕድሜ ያላቸው
በታሪክና በባህል ላይ ያተኮሩ መጻሕፍት ላይ ያሉ ሥዕሎችን ስንመለከት ወንዶች ሱሪ
ሴቶች ቀሚስ ለበብሰው ነው የምናገኛቸው። የተለያዩ ጥንታዊ ካላንደሮችም ኾነ ፖስተሮች
ስንመለከት ሱሪ ወንዶች ቀሚስ ሴትች ለብሰው ነው የምንመለከተው።

እኅቶቼ ኾይ እንኳንስ ሱሪ ቀርቶ ቀሚስም ቢኽን ከሥርዐት ውጭ ከኾነ መልበስ


እንደማይቻል አታውቁምን? አኹን የምናያቸው ግልጥልጥ ያሉ ልብሶች፣ በጣም አጫጭር
ቀሚሶች፣ ውጥርጥር የሚያደርጉ ልብሶችን መልበሳችኹ አንደኛ እናንተንም
ያስጨንቃችኃል፣ ኹለተኛ አምላካችንንም ያሳዝነዋልና፡፡ ጥንቱን አዳምና ሔዋን በገነት
እያሉ እግዚአብሔር የጸጋ ብርሃን አልብሷቸው ነበር ኾኖም አዳም ትዕዛዙን ጠብቆ ሊቆይ
አልቻለም። በዚህም ምክንያት የለበሰውን የጸጋ ልብስ አጥቶ፤ በስተመጨረሻም በኃጢአቱ
ምክንያት ገነትን የሚያህል ቦታ እግዚአብሔር የሚያልል ጌታ ትቶ ወደ ምድረ ፋይድ ነው
የወረደው። አዳም ዕርቃኑን መኾኑን ሲያይ ቅጠል ቢያገለድምም ይህ ለርሱ ዘላቂ ልብስ
ሊኾነው አልቻለም። እግዚአብሔር ግን በቸርነቱ መልሶም ቢኾን ምን መልበስ እንዳለበት
እና አዳምንም ከማልበስ ቸል አላለም። የቁርበት ልብስን አለበሰው እንጂ ዘፍ ፫፥፳፩።

፪ በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትርጉም መሠረት ሴት የወንድን ልብስ አትልበስ ማለት


በሴትነቷ ያላትን ክብር ትወቅ፣ የወንድነትን ባሕርይ አትላበስ፤ ወንድ ልኹን አትበል።
ወንድም ወንድነቱን ያክብር እንጂ ሴት ልኹን አይበል፤ የሴትነትን ባሕርይ አይላበስ፤ ሴት
መኾንን አይሻ ወንድ በመኾኑ ወንድነቱን አክብሮ ይጠብቅ እንጂ ማለት ነው። በዚህ
ትርጓሜ መንፈስ ውስጥ ኾነን የሴቶችን ሱሪ እናድርግ ጥያቄ ብንጠይቅ መልሱ የሚኾነው
ሴት ኾይ ሴትነትሽን አክብሪ ለወንድ የተፈቀደውን በማድረግ ወንድነትን አትሺ ይኾናልና
መልሱ ጠንቀቅ ማለቱ ተገቢ ነው። አኹን ባለንበት ዘመን ብዙ ወንዶች ከወንድነት ይልቅ
ሴትነትን የወደዱ ይመስላል እነርሱ ባይናገሩትም የሚያደርጉት ሥራ ውስጣቸው በምን
እንደተሞላ ፍንትው አድርጎ ያሳየናል። የወንዶች ፀጉራቸውን እንደሴት ማድረጉ
ሥሉጥነትን የሚገልጽ ሳይኾን ድኩምነትን የሚያስረዳ ነው። በሴትነት የሚደረገውን ኹሉ
እኔ ላድርግ የሚል ወንድም የወንድነትንም ነገር ኹሉ እኔ ላድርግ የምትል ሴት ኹለቱም
በእግዚአብሔር ዘንድ በሥራቸው የተጠሉ ናቸው።

፫ ሴት የሴትነቷን ሓላፊነት ትወጣ ወንድም የወንድነቱን ሓላፊነት ይወጣ ማለት ነው።


ወንድ ሴት አይደለምና ዘር ልቀበል አይበል፤ ሴትም ወንድ አይደለችምና ዘር ላቀበል
አትበል። መውለድ የሴት እንጂ የወንድ አይደለምና ወንድ ኾይ ፀንሼ ልውለድ አትበል
በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)
ገጽ | 38
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ይህን ማድረግ አትችልምና። ጡት ማጥባት ከእግዚአብሔር ለእናቶች የተሰጠ ነውና ወንድ


ኾይ ካላጠባው አትበል። ማጥመቅ፣ ማቁረብ ለወንዶች ካህናት አባቶቻችን የተሰጠ ሓላፊነት
ነውና ሴቶች ኾይ ቄስ ኾኜ ካላቆረብኩ ካላጠመቅኹ አትበይ፤ እርሱ የወንድ ካህናት
ሓላፊነት ነውና። የሴቶች ካህን ካልኾንኩ ባይነት የወንዶችን እናት ካልኾንኩ ባይነትን
እግዚአብሔር አልወደደምና አንመኘው። ሊኾንም አይችልምና ተስፋም አናድርገው። ሴቶችን
ለእናትነት ካህናትን ለክህነት የመረጠው ጠቢበ ጠቢባን ልዑል አምላክ ነውና እንቀበለው።

፬ የሴት የወንድን ልብስ ካልለበስኩ ባይነትና የወንድ የሴትን ልብስ መልበስ የፓጋንነት
መለያ ነውና ሴት የወንድ ልብስ አትልበስ ወንድም እንዲሁ። በዘመነ ነቢያት የነበሩ ሰዎች
ከእግዚአብሔር ሕግ በመውጣት ከአምልኮታቸው ጋር በተያያዘ መልክ ለሚያመልኩት ጣዖት
ወንዶች የሴቶችን ልብስ በመልበስ፤ ጠጉራቸው በማሳደግ፤ ሴቶችም የወንድን ልብስ
በመልበስ ይታዩ ነበር። ከዚህ ከጣዖታዊ ሥርዐት ጋር በተያያዘ መልኩ ሴቶች የወንድን
ልብስ በመልበስ ወንዶችም የሴቶችን ልብስ በመልበስ ይዘፍኑ ይጨፍሩ ነበር።

2.10 እህቶቻችን ለምን አይሰብኩም?


በመፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሴት እህቶቻችን ትንቢት ሲናገሩ እንሰማለን እርግጥ ሴቶች
ትንቢት ይናገራሉ ፡፡ ሴቶች ትንቢት ይናገራሉ ማለት ይሰብካሉ ማለት አይደለም ለምሳሌ
በብሉይ ኪዳን እና በሀዲስ ኪዳን ጌታ በልጅነቱ እመቤታችን ቤተመቅደስ ይዛው በሔደች
ጊዜ ነቢያት ሴቶች ነበሩ ይህ ማለት ትንቢት መናገር እንጂ ስራቸው ማስተማር ወይም
መስበክ አልነበረም ፤ ቅዱስ ጳውሎስ ሴት ልጅ ለወንድ ልጅ መሰናከያ ስለሆነች/ አዳምን
ያሳተችው ሴት ስለሆነች (ይህም ሲባል ሄዋን ከዲያቢሎስ በእባብ አማካኝነት ተምራ
የመጣችውን ለአዳም ነግራለች ማለትም አስተምራለች፣ ሰብካለች በዚህም ለአዳም መሰናክል
ሆናለች/ እንዳትሰብክ ከልክሏል አውደምህረት ወጥታ ብትሰብክ ወንዶች በሷ ይሰናከላሉ
የሴት ድምፅ ደስ የሚለው ወንድ ቃሉን ሳይሆን ድምጿን አዳምጦ ይሔዳል ወንድ በሴት
የሚሰናከልበት ብዙ ነገር አለ።

መፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ በብሉይም ሆነ በሀዲስ ኪዳን አንድ ሴት ሰበከች ተብሎ አልተፃፈም
ጌታም እንዲሰብኩ የመረጠው ከ 12ቱ ሐዋርያት ውስጥ ሴት የለችም እንደውም ሐዋርያቱ
በይሁዳ ፋንታ እጣ ሲያወጡ ማቴዎስ ሲደርሰው በእጣው ሴት አልተካተተችም
ወንጌላቱንም ሆነ መልእክታቱን የጻፉት ወንዶች ናቸው የጻፉትም የሰበኩትን ነው አንድም
ቦታ ሴት ስትሰብክ አልታየም ሴት የራሷ አገልግሎት ነበራት ለምሳሌ ሊዲያ የቅዱስ
ጳውሎስን መልእክታት ለተፃፈበት አገር ይዛ ትሔድ ነበር ይህም ድንቅ አገልግሎት ነበር
በመዝሙር በምስጋና ይሳተፋሉ በገንዘብም ቤተክርስቲያንን ይረዱ ነበር፡፡ ቅድስት
ቤተክርሰቲያናችንም መፅሐፍ ቅዱስን አብነት አድርጋ ሴት ልጅ እንድትሰብክ አትፈቅድም፡፡
1ኛ ጢሞ 2፥11 "ሴት በነገር ሁሉ እየተገዛች በዝግታ ትማር" 1ኛ ቆሮ 14፥35 "ለሴት
በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)
ገጽ | 39
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

በማኅበር መካከል መናገር ነውር ነውና፥ ምንም ሊማሩ ቢወዱ በቤታቸው ባሎቻቸውን
ይጠይቁ።" ይህ ሴት እህቶቻችን መስበክ የሌለባቸው በጉባኤ /በአውደምህረት/ወንዶች
ባሉበት በአካል እንደሆነ ልብ ማለት ያስፈልጋል፡፡ በአንድ አካል ብዙ ብልቶች እንዳሉ
የብልቶቹም ሥራ አንድ እንዳይደል ሁሉ ወንድና ሴትም በአንድ አካል ያሉ የተለያዩ
ብልቶች ናቸው። አገልግሎታቸውም /የሥራ ድርሻቸውም እንዲሁ የተለያየ ነው። ወንድ
ራስ ሲሆን ሴት ደግሞ ልብ ትሆናለች ሴቶች የራሳቸውን ወንዶችና ሴቶች ልጆች ያስተምሩ
ዘንድ ችሎታው አላቸው።

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 40
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

3. ምሥጢራተና ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ከነገረ ድኅነት ጋር


ያላቸው ግንኙነት
3.1 መዳን ማለት ምን ማለት ነው?
1. በኃጢኣት ምክንያት ከመጣው ፍዳ (ሞት) ነጻ መውጣት፡- ዘፍ 6፤9 ኖህ ከጥፋት ውኃ
መዳኑ ሎጥ በሰዶምና በገሞራ ላይ በደረሰው እሳትና የዲን ቃጠሎ መዳኑ፣ ዘፍ 19
ያዕቆብና ልጆቹ ወደ ግብጽ በመውረድ ከረሃብ መዳናቸው፣ ንዕማን በዮርዳኖስ ታጥቦ
ከበሽታ መዳኑ፣ ደቀመዛሙርቱ ባሕር ላይ ሲጓዙ ስለ ኃይለኛ ማዕበል በተነሳባቸው ጊዜ ጌታ
ሆይ አድነን ብለው ድነዋል፡፡ ማቴ 23፡27፣ በአጠቃላይ ከተለያዩ ፍዳዎች መዳን 2ጢሞ 4፡
18
2.. የእግዚአብሔር ትዕዛዝ በማፍረስ ምክንያት ከደረሰብን ተደራራቢ ውድቀቶች፣ ቅጣቶች፣
ከፀጋ መራቆትንና የባሕሪ መጎስቆል እንዲሁም ኋላም ከእግዚአብሔር ልዩ ምክር በኢየሱሰ
ክርስቶስ ሥጋዌ በመንፈስ ቅዱስ የተሰጠው መዳን ይባላል፡፡
3. እግዚአብሔርን ማወቅ ማለት ነው፡፡ ሮሜ 1፡18 እግዚአብሔር ስለ ገለጠላቸው ስለ
እግዚአብሔር ሊታወቀው የሚቻለው በእነርሱ ዘንድ ግልጽ ነው፡፡
4. መዳን ማለት እንደ አዲስ መፈጠር ማለት ነው፡፡ ማቴ 19፡16 በአረጀ ልብስ አዲስ እራፊ
የሚያኖር የለም መጣፈያውን ልብሱን ይቦጫጭቀዋልና መቀደዱን የባሰ ይሆናል፡፡ 2ቆሮ5፡
17 ማንም ቢሆን በክርስቶስ አዲስ ፍጥረት ነው፡፡
5. በቅድስና ማደግ ነው፡፡ 2ቆሮ 3፡18 ከክብር ወደ ክብር እንለወጣለን እንዳለው መዳን
የተገደበ አይደለም የሚያድግ ነው እንጂ ፊሊ 3፡13 እኔ ገና እንዳልያዝሁት እቆጥራለው
ነገር ግን አንድ ነገር አደርጋለው በኋላዬ ያለውን አየረሳሁ በፊቴ ያለውን ለመያዝ
እዘረጋለው

3.2 ሰው የዳነው እንዴት ነው


ነገረ ድኅነት በክርስቶስ ሰው መሆንና ቤዛነት ለሰው ልጆች ሁሉ እንዲያው በነጻ የተሰጠ
የሕይወት ፈቃድ ነው። ይህን የሕይወት ፈቃድ ለሰው ልጆች ሁሉ እንድትሰጥ ሥልጣንና
ኃፊነት የሰጠው ደግሞ ለቤተ ክርስቲያን ነው፡፡ ሰው የዳነው በእግዚአብሔር ስጦታ ነው፡፡
ኤፌ 2፡3 ፡፡ ዮሐ 3፡16 በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ
እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንዲያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዷልና፡፡ ሮሜ
5፡10 ጠላቶቹ ሳለን በልጁ ሞት ይቅር አለን፡፡ ነገረ ድኅነት በክርስቶስ ሰው መሆንና ቤዛነት
ለሰው ልጆች ሁሉ እንዲያው በነጻ የተሰጠ የሕይወት ፈቃድ ነው። ይህን የሕይወት ፈቃድ
ለሰው ልጆች ሁሉ እንድትናኝ (እንድትሰጥ) ሥልጣንና ሓፊነት የሰጠው ደግሞ ለቤተ
ክርስቲያን ነው፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 41
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

3.3 ለመዳን የሚያስፈልጉ መሠረታዊ ነገሮች


1.ማመን (ዕምነት)፡-) የእግዚአብሔር ቸርነት በሙሉ ስለእኛ መሆኑን አምኖ በእምነት
መቀበል፡፡ የሐ 3፡14 በእርሱ የሚያምን የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይተፋ
የሰው ልጅ ይሰቀል ዘንድ ይገባዋል፡፡ እግዚአብሔር በቅዱሳት መጻሕፍት የገለጠውን በሙሉ
አንድም ሳያጎድሉና ሳይጨምሩ ሳይበርዙ በዕምነት መቀበል፡፡ ዮሐ 4፡22 እናንተስ
ለማታውቁት ትሰግዳላችሁ፡፡ ማቴ 10፡42 ማንም ከእነዚህ ከተናናሾቹ መካከል ለአንዱ
ቀዝቃዛ ፅዋ ውኃ ብቻ በደቀማዛሙርት ስም የሚያጣጣ ቢኖር እውነት እላችኋለሁ ዋጋው
አይጠፋበትም፡፡

2.. ምስጢራትን መፈጸም፡- ማር 16፡16 ያመነ የተጠመቀ ይድናል፡፡ ሐዋ 2፡37 በኢየሱስ


ክርስቶስ ስም ተጠመቁ፡፡ ጥምቀት ለምን ያገለግላል፡-

ሀ). ለስርየት፡-1ጲጥ 3፡21 ይህም ውሃ ደግሞ የጥምቀት ምሳሌ ሆኖአሁን ያድናል

ለ). ልጅነትን ለማግኘት፡-ዮሐ 3፡5 ሰው ሁሉ በውሃና በመንፈስ ካልተጠመ የእግዚአብሔርን


መንግስት ሊያይ አይችልም፡፡ ሮሜ 8፡15 አባ አባ ብለን የምንጮህበትን የልጅነት መንፈስ
ተቀበላችሁ፡፡

ሐ). ከክርስቶስ ከሞቱና ከትንሣኤው ለመሳተፍችን ምሳሌ፡-ሮሜ 6፡3 ሞቱ በሚመስል ሞት


ከእርሱ ጋር ከተባበርን ትንሣኤው በሚመስልትንሣኤ ከእርሱ ጋር እንተባበራለን፡፡ ቆላ 2፡12
በጥምቀት ከእርሱ ጋር ተቀበራችሁ በጥምቀት ደግሞ ከሙታን ባስነሳው በእግዚአብሔር
አሰራር በማመናችሁ ከእርሱ ጋር ተነሳችሁ፡፡

መ). ክርስቶስን ለመልበስ፡- ገላ 3፡27 ከክርስቶስ ጋር አንድ መሆንን የተጠመቃችሁ


ሁላችሁም ክርስቶስን ለብሳችኋል፡፡ምክንያቱም ያልተጠመቀ እራቆቱን እንዳለ ነው፡፡ 2ቆሮ
5፡3 ለብሰን ራቆታችንን አንገኝ፡፡

3. ቅዱስ ስጋውና ክቡር ደሙን መቀበል፡፡ ዮሐ 6፡54 ሥጋዬን የሚበላ ደሜን የሚጠጣ
የዘላለም ሕይወት አለው እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሰዋለው

4. በተቀበሉት ፀጋ መዳን መጽናትና መጋደል፡- ዕብ 2፡1 ስለዚህ ከሰማነው ነገር ምናልባት


እንውሰድ ለእርሱ ለእርሱ አብዝተን ልንጨነቅ ያስፈልጋል፡፡ 1ቆሮ 10፡12 የቆመ
የሚመስለው እንዳይወድቅ ይጠንቀቅ፡፡ ዕብ 4፡11 ወደ እዚያ ዕረፍት ለመጋባት እንትጋ፡፡
1ጢሞ 6፡11 የዘላለምን ሕይወት ያዝ፡፡

5. ቅዱስ ቃሉን መስማት፡፡ ዮሐ 5፡24 እውነት እላችኋለው ቃሌን የሚሰማ በላከኝም


የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 42
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

6. ስለ ሃይማኖት ሰማዕትነት በመቀበል፡፡ ዮሐ 12፡25 ነፍሱን የሚወዳት ያጠፋታል


ነፍሱንም በዚህ ዓለም የሚጠላ የዘላለም ሕይወት ይጠብቃታል

7.ሁሉን ትቶ በመከተል (በምናኔ)፡፡ ማቴ 19፡29 ስለ ስሜ ቤቶችን ወይንም ወንድሞችን


ወይንም እኅቶችን ወይም አባትን ወይም እናትን ወይም ሚስትን ወይም ልጆችን ወይም
እርሻን የተወ ሁሉ መቶ እጥፍ ይቀበላል የዘላለምንም ሕይወት ይወርሳል ፡፡

8. ትዕዛዛቱን በመጠበቅ፡፡ ማቴ 19፡16 ወደ ሕይወት መግባት ብትወድ ግን ትዕዛዛትን


ጠብቅ

9. ክርስቲያናዊ መልካም ስራ መስራት፡- ሮሜ 2፡13 በእግዚ አብሔር ፊት ሕግን


የሚያደርጉ ይጸድቃሉ፡፡ ሮሜ1፡16 ቅዱስ ጳውሎስ ለሮሜ ሰዎች
የሚጠበቅበትን እንዳደረገላቸው፡፡ ያዕ 2፡14ስራ የተለየው ዕምነት የተሞተ ነው

3.4 ዕፀ በለስ ለምን ተፈጠረች


1. አዳም ለእግዚአብሔር ያለው ፍቅር ይገልጥ ዘንድ፡፡ እግዚአብሔር ለአዳም ያለው ፍቅር
በተለያየ መልኩ ገልጦታል ለምሳሌ በአርአያው በመፍጠር፣ የሁሉም ፍጥረት ገዥ
በማድረግ፣በገቢር በመፍጠርና ሕያው ነፍስ በመስጠት እና የተለያዩ ፀጋዎችን በመስጠት
ፈጥሮታል፡፡ እግዚአብሔር ይህን ሁሉ ያደረገለት ስለ ፍቅሩ ነው እንጂ አዳም ሰርቶ
ስለደሞዙ አነበረም፡፡ አዳም ደግሞ ለእግዚአብሔር ያለው ፍቅር በምን ይግለጥ አንድ ዕድል
ያስፈልገዋል፡፡ ያም የተከለከለውን ዕፀ በለስን መጠበቅ ነው፡፡ ያቺን በመተው አዳም
ለእግዚአብሔር ያለው ፍቅር ያለው ፍቅር ከተከለከለችው የዛፍ ፍሬ በላይ መሆኑን
እንዲያሳይ ይህቺን ትዕዛዝ አስቀመጠለት፡፡ ዮሐ 14፡21 ትዕዛዜን በእርሱ ዘንድ ያለችው
የሚጠብቃትም የሚወደኝ እርሱ ነው፡፡ የእግዚአብሔር ወዳጅ ለመባል ሁለት ነገር
ያስፈልጋል፡- የእግዚአብሔር ትዕዛዝ ያለው ሰው እና የእግዚአብሔር ትዕዛዝ የሚጠብቅ
ማለት ነው፡፡

2. አዳም ፍጡርነቱን (ፈጣሪ ያለው መሆኑን) እንዳይዘነጋ (እንዲያዘክር)

3. አዳም የተሰጠውን ነጻነት ይታወቅ ዘንድ ነው

4. እግዚአብሔር ለአዳም የሰጠው ክብርና ታላቅ ቦታ ይታወቅ ዘንድ፡፡አንድ ሰው ኃላፊነት


የሚሰጠው ለሚወደውና ለሚያምነው ኃላፊነት መወጣት ይችላል ለሚለው ሰው ነው፡፡
ስለዚህ እግዚአብሔር አምላክም ይንን ጠብቅ ሲለው በትልቅ ቦታና ለትልቅ ዓላማ
እንደተፈጠረ ታውቋል ማለት ነው፡፡ በዋናነት ግን ማስታወስ ያለብን ሰዎች በልጆቻቸው
መንገድ ላይ የሚያሰናክል እንቅፋት እንደማያስቀምጡ ሁሉ እግዚአብሔር አምላክ ለሰዎች

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 43
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ፍቅርን የሰጠ አምላክ ስለሆነ አዳምን የሚጎዳ ነገር አያስቀምጥበትም፡፡ ማቴ 7፡11 እናነተ
ክፍዎች ስትሆኑ ለልጆቻቹን መልካም ስጦታን መስጠትን ካወቃችሁ በሰማያት ያለው
አባታችሁን ለሚለምኑት እንዴት አብዝቶ መልካም ነገርን ይሰጣቸው ይሆን ፡፡ ስለዚህ ዕፀ
በለስ የተፈጠረችው ለመልካም ነገር ነበር፡፡ ነገር ግን አዳምና ሔዋን እግዚአብሔር አምላክ
የሰጣቸውን ትዕዛዝ ትተው በዲያብሎስ ባዶ ስብከት ተታለው እግዚአብሔር የሚያህል
አምላክ ትተው ዲያብሎስን አምነው ሕጉንና ትዕዛዙን ጣሱ (አፈረሱ)፡፡ በኋላ የሰው
ውድቀት መጣ ፡፡ እንግዲህ የእግዚአብሔር አምላክ ሰው መሆን ያስፈለገውም የሰው ልጅ
ውድቀት ነው፡፡

3.5 ያለ ድንግል ማርያም አማላጅነት ዓለም ሁሉ አይድንም፡፡


ይህን ቃል ስንመለከተው አንድ ፍቺ ብቻ የሚሰጠው ሳይሆን በልዩ ልዩ አቅጫጫ ሊታይ
የሚገባው ብዙ ሚስጢራት ጠቅልሎ የያዘ ዐረፍት ነገር ነው፡፡ ፍቺው እንደምንድን ነው
ትሉኝ እንደሆነ፡- ሉቃ 1፡38 እንደ ቃልህ ይሁንልኝ፡፡ የአባታችን የአዳም የቀደመ ኃጢአት
ለልጆች ተርፎ ዓለሙ ሁሉ በኃጢአት በረት በተዘጋት በሰይጣን ቁራኝነት በተያዘበት
የሚያድነው ባጣበት በጨለማው ዘመን ከልጅ ልጅ ተወልጄ አድንኃለሁ የሚለውን አምላካዊ
ቃል ብቻ የድኅነት መንገድ ነውና የዘመኑ መቅረብና የአምላክ ሰው መሆን ይናፍቅ ነበር፡፡
በመሆኑም በየጊዜው የተነሱ ደጋግ አበው ከዘመኑ በደረስን ብለው ተመኝተዋል፡፡ ነብያት ና
ውረድ ተወለድ አድነን እያሉ በትንቢት አንደበት ጮኽዋል፡፡ ይህ ብቻ አይደለም ከእርሷ
እወለዳለው ብሎ የተናገረላት ያቺን መለኮትን ለመሸከም የአምላክ እናት ለመሆን
የተገባችውን ደገኛዋ እመቤት ከአዳም ጀምሮ በናፍቆት ሲጠብቋት ነበር፡፡ አንቲ ውእቱ
ተስፋሁ ለአዳም አመ ይሰደድ እም ገነት እነ ቅዱስ ዳዊት ደግሞ በሱባኤ
እንድትገለጥላቸው ጠይቀው ሳይደርሱባት በሩቅ ተሳለሟት (ናሁ ሰማዕናሁ) ብሎ
መስክሯል፡፡ እመቤታችን ከሌለች ክርስቶስ፤ ክርስቶስ ከሌለ ክርስትና የለምና ንጽሕይት ዘር
በማጣት ድኅነት ሳናገኝ ዕጣ ፈንታችን ፅዋ ተርታችን እንደ ሰዶምና ገሞራ ይሆን ነበር
በማለት የተናገረው ለዚህ ነው፡፡ ኢሳ1፡9 ስለዚህ ለሰው ልጆች ድኅነት ድንግል ማርያም
ታስፈልግ ነበር፡፡

እነሆ ሱባኤ ተፈጸመ ዘመኑም ደረሰ ምክንያተ ድኂናችን ከእሴይ ሥር ከዳዊት ዘር


ከናዝሬት ገሊላ ሀገር ተገኘች፡፡ ወስማ ለእይቲ ድንግል ማርያም (የዚህች ድንግል ስሟ
ማርያም ነው)፡፡ ሉቃ 1፡27 በዚያን ወራት መላኩ ቅዱስ ገብርኤል ከእግዚአብሔር ዘንድ
ተላከ፡፡ እግዚአብሔር አምላክ ለእናትነት ከመረጣት በቀጥታ በማኅጸኗ ማደር ሲችል ለምን
መላኩ ወደርሷ ላከ ካልን ድኅነት ውስጥ የእርሷም ፈቃድ እንዳለው እናስተውላለን፡፡ ሁሉን
ማድረግ ሲችል በእርሷ ይሁንታ ድኅነተ ዓለም እንዲፈጸም ፈቃዱ ሆነ፡፡ መላኩ አደግድጎ
እጅ ነሳት የመውለዷም ነገር አበሰራት፡፡ የመከራከር ሳይሆን የመረዳት ጥያቄ ጠየቀችው፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 44
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

መላኩም ለጥያቄው መልስ ሲሰጥ ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለም ብሎ ሲደመድም


እመቤታችን የዓለም ድኅነት ቁልፍ የሆነ ልመና ቃል በመናገር ይሁንታዋን ሰጠች (ይኩነኒ
በከመ ትቤለኒ) ፡፡ ልክ ይህን ቃል ካንደበቷ ሲወጣ አካላዊ ቃል የዕለት ፅንስ ሆኖ በማኅፀኗ
ተቀረጸ፡፡ በዚህም የድኅነተ ዓለም መሠረት ተጣለ፡፡ ምን አልባት እመቤታችን ይህን ቃል
ሳትናገር ብትዘገይ ኖሮ የሰው ልጆች ድኅነት በዚያው ልክ ይዘገይ ነበር፡፡

ምክንያቱም አምላክ ቃሏን ጠብቆ ነውና ያደረባት፡፡ ታዳያ ከዚህ ምን እንረዳለን እንደቃል
ይሁንልኝ የሚለውን የልመና ቃሏ ከፍጥረት መዳን ጋር የሚገናኝ ከሆን መላኩም
ሲያበስራት ካንቺ የሚወለደው ከሦስቱ አካል አንዱ ቅዱስ ነው፡፡ የዓለም መዳኃኒት ኢየሱስ
ይባላል፡፡ እንደ ቃልህ ይሁንና አምላክ ከእኔ ተወልዶ፣ ተሰቅሎ፣ ሞቶ፣ ሰውን ከዲያብሎስ
ቁራኝነት ያለቀው፣ በልጁ ብርሃንነት የ5500 ዘመን ድቅድቅ ጨለማ ይገፈፍ ፣ነፍሳት
ከሲኦል ወደገነት ይመልስ የሚል መልዕክት ያለው የምልጃ ቃል ለደቂቀ አዳም አቀረበች፡፡

ገና በቤተ መቅደስ ሳለች የነብዩ የኢሳያስ ትንቢት አንብባ የተመኘችውን እናትነት ሳይሆን
ባርያ መሆንን ነበር፡፡ ዓላማዋ ፍላጎቷ ሰው አንዲድን እንጂን ክብርን እንድታገኝ እንዳል
አለሆኑን በዚሁ ይታወቃል፡፡ ታዲያ እግዚአብሔር ትህትናዋ አይቶ መረጣት፡፡ እርሷም
ፍጥረት ከዳነልኘማ ይሁን አድርገው ብላ አምላክን ጠየቀች፡፡ ልክ ልጇ በጌቴ ሴማኒ በጸለየ
ጊዜ ይህች ጽዋ በእኔ ትለፍ ብሎ የሞትን ጽዋ ከአዳም ዘር ሁሉ እንዳሳለፈ እናቱም ከእኔ
ተወለድና ጽዋን ከሰው ልጆች ሁሉ አሳልፍ ብላ በመማለድ ሲጠባበቅ የነበረውን ቃሏን
ሰጠቸው፡፡ ታዲያ ያለዚህ ምልጃ ያለዚህ ፈቃድ የክርስቶስ ልደት የሰው ልጆች ድኅነት
እርግጥ ይሆን ነበር? ስለዚህ ያለድንግል ማርያም አማላጅነት ዓለም ሁሉ አይድንም፡፡

1.ዓለም የእመቤታችን አማላጅነት ካልተቀበለ አይድንም ነው፡፡ በዓለም ያሉ ሰዎች ሁሉ


እመቤታችን አታማልድም ሲሉ ክርስቶስን አማላጅ ያደርጉታል፡፡ ምክንያቱም አማላጅ
እንደሚያስፈልግ ሁላችን እናውቃለን፡፡ ስለዚህ እመቤታችን አታማልድም ሲሉ ቅዱሳን
ናቸው ወይም ክርስቶስ ነው፡፡ ማነው አማለጅ የሚል ጥያቄ ያስነሳል፡፡ አንድም
ስለእመቤታችን አማላጅነትና ክብር ማወቅ ግዴታ ነው ምክንያቱም የመዳናችን ቁልፍ ጉዳይ
ስለሆነ ነው፡፡

2.ዓለም ሁሉ ሐጢአተኛ ነው ማለት ነው፡፡ ዓለም ሁሉ በሀጢአት ውስጥ ስላለ የቅዱሳን


ጸሎት ልመና ምልጃ ግዴታ አስፈላጊ ነው፡፡ ለዚህም ከቅዱሳን ሁሉ በላይ ጸሎቷ ልመናዋ
የሚሰማላት የንጽሕይት ድንግል አማላጅነት ዓለም ሁሉ ሊቀበል ይገባል፡፡

3.6 ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ከነገረ ድኅነት ጋር ያላቸው ግንኙነት


ቃለ ወንጌልን በመስማት የሚጀምረው የሰው ልጆች ድኅነት በእምነት የሚመሠረት ቢሆንም
የተሟላ የሚሆነው ግን ምሥጢራትን በመፈጸም ነው፡፡ ይህም ድኅነት በአንድ ጊዜ ተጀምሮ

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 45
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

የሚያልቅ ባለመሆኑ በሰው ልጆች ምድራዊ ሕይወት ሁሉ ከሰይጣን፣ ከእኩያት ኃጣውእና


ከፍትወታት እኩያት ጋር በሚደረግ ረጅም መንፈሳዊ ተጋድሎ የሚረጋገጥ ነው፡፡ በዚህ
መንፈሳዊ ጉዞ ውስጥ ሁሉ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን የሚኖራቸው ሚና ከፍተኛ ነው፡፡

በዚህ መሠረት አንድ ሰው መዳን ከፈለገ ቃለ እግዚአብሔርን መስማት፣ ማመን፣ መጸለይ፣


ሌሎች ትእዛዛትን መፈጸምና የምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ተካፋይ መሆን ይኖርበታል፡፡
“… በፍርሃትና በመንቀጥቀጥ ሆናችሁ ለድኅነታችሁ ሥሩ፡፡” (ፊልጵ. ፪፥፲፪፡፡) እንደተባለ፤
ሁላችንም የምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ተሳታፊ ለመሆን መትጋት ይኖርብናል፡፡
ምክንያቱም “ቃሉን የምታደርጉ ሁኑ እንጂ ራሳችሁን እያሳታችሁ የምትሰሙ ብቻ
አትሁኑ፡፡” (ያዕ. ፩፥፳፪፡፡) ተብሎ ተጽፏልና፡፡ ክርስቶስን ማመናችንና መቀበላችን
የሚረጋገጠው፣ በጸጋው መዳናችንም የሚታወቀው ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያንን በመፈጸም
ብቻ መሆኑን ማመን ይኖርብናል፡፡ ይህንንም የምናገኘው በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ብቻ
ስንሆን ነው፡፡ ከቤተ ክርስቲያን ውጪ መሆንና ራስን በራስ ግላዊ አስተያየትና ፍልስፍና
ከቤተ ክርስቲያን ምሥጢራት ገለልተኛ ማድረግ ከድኅነት መስመር መራቅ ነው፡፡ ነገረ
ድኅነትና ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ቀጥተኛ የሆነ ግንኙነት አላቸው፡፡ ያለ ምሥጢራተ
ቤተ ክርስቲያን ድኅነት ፈጽሞ አይታሰብምና፡፡ ለማሳያ ያህልም ብንመለከት “ያመነ
የተጠመቀ ይድናል፡፡” (ማር. ፲፮፥፲፮፡፡) “ሥጋዬን የሚበላ፣ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም
ሕይወት አለው፤ እኔም በኋለኛይቱ ቀን አነሳዋለሁ፡፡” (ዮሐ. ፮፥፶፬፡፡) ለመዳንና የዘላለም
ሕይወት ባለቤት ለመሆን የምንችለው ምሥጢረ ጥምቀትን ቁርባንን ስንፈጽም መሆኑን
ከጥቅሶቹ መልእክት እንማራለን።

3.7 ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ከነገረ ድኅነት ጋር ያላቸው ግንኙነት


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንንም ከነገረ ድኅነት አንጻር ብንመረምር በተመሳሳይ ሁኔታ ቀጥተኛ
ግንኙነት እንዳላቸው እንገነዘባለን፡፡ ያለ ሥርዓት የሚፈጸሙ የቤተ ክርስቲያን ምሥጢራት
የሌሉ እንደመሆኑ መጠን ያለ ሥርዓት ቤተ ክርስቲያን የምትሰጠው ድኅነትም የለም፡፡
መድኃኔዓለም ክርስቶስ ለድኅነተ ዓለም የተጓዘባቸው መንገዶችና የመሠረታቸው
ምሥጢራት ሁሉ የተከናወኑት በዘፈቀደ ሳይሆን በአገባብና በሥርዓት መሆኑ ይታወቃል፡፡
የአዲስ ኪዳን መሥዋዕት የሆነውን የቅዱስ ቁርባንን አመሠራረት ለአብነት ብናይ
የሥርዓትንና የነገረ ድኅነትን ቀጥተኛ ግንኙነት መረዳት እንችላለን፡፡ መጀመሪያ ኅብስቱን
መባረኩና መቁረሱ ይበሉም ዘንድ አስቀድሞ ራሱ በልቶ ለደቀ መዙሙርቱ መስጠቱ፣
ወይኑንም አክብሮ ጠጥቶ ማጠጣቱ ራሱን የቻለ ታላቅ ሥርዓት ነው፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 46
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

4. ምሥጢረ ጥምቀት
4.1 የምሥጢረ ጥምቀት የቃሉ ትርጉም

ጥምቀት ፡- አበው በምሳሌ፤ ነቢያትም በትንቢትና በብዙ ኅብረ አምሳል ቀድመው


ካዩዋቸውና ከተናገሩላቸው የቤተ ክርስቲያን ምሥጢራት መካከል የመጀመሪያው ምሥጢረ
ጥምቀት ነው። ቃሉም “አጥመቀ” (አጠመቀ) ከሚለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ሲሆን
ትርጉሙም በተከማቸ ውሃ ውስጥ መነከር፣ መዘፈቅ፣ ገብቶ መውጣት ማለት ነው፡፡
በምስጢራዊ (በሃይማኖታዊ) ፍቺው በተጸለየበት ውሃ (ማየ ኅይወት) ውስጥ በሥላሴ (በአብ
በወልድ በመንፈስ ቅዱስ) ስም ሦስት ጊዜ ብቅ ጥልቅ ብሎ የመውጣት ሂደት ነው።
አንድም ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ ከማኅፀነ ዮርዳኖስ ተወልደን የሥላሴን ልጅነት (ሀብተ
ወልድና ስመ ክርስትና) የምናገኝበት፣ዳግመኛ ተወልደን ወደ እግዚአብሔር መንግስት
የምንገባበት፣ ከኃጢያት ነፃ የምንሆንበት፣ ከዲያቢሎስ አገዛዝ አርነት የምንወጣበት
የምስጢር ዓይነት ነው፡፡

በቅዱሳት መጻሕፍት እንደተገለጸው በነብየ እግዚአብሔር በቅዱስ ሕዝቅሌል ሕዝ 36፡25


“ጥሩ ውሀንም ጥምቀትን እረጫችኋለሁ እናንትም ትጠራላችሁ ከርኩስነታችሁም ሁሉ
ከጣኦቶቻችሁ ሁሉ አጠራችኋለሁ አዲስ ልብ እሰጣችኋለው” በማለት የዚህን ምስጢር
ክብርነት በረከትነት አምልቶ አስፍቶ ተናገሯል፡፡ በዚህ ሀሳብ ሌሎች ንፁሐን አበው
ሀዋርያት ተባብረውታል፡፡ የሐዋ.2፡38 ፣ 1ቆሮ 6፡11 ፣ ዮሐ. 3፡5 ፣ ኤፌ 5፡26 ፣ ገላ 3፡
27 ፣ ቲቶ 3፡5 እነሆ ኖኅ የዳነበትን መርከብ ቅዱስ ጴጥሮስ የጥምቀት ምሳሌ እንደሆነ
ገልጾታል፡፡ 1ጴጥ 3፡21 ምዕመናን ከኃጢአት ከጥፋት የሚድኑት በጥምቀት ነውና ቅዱስ
ጳውሎስም እስራኤል ከግብጽ የባርነት ቀንበር ተላቀው የኤርትራን ባሕር ተሻግረው
ወደምድረ ርስት ያደረጉትን ጉዞ የጥምቀትን ምሳሌ አድርጎ አመስጥሮታል፡፡ 1ኛቆሮ 10፡1-2
ምዕመናን ባህረ ኃጢያትን ተሻግረው ምድረ ርስተ መንግስተ ሰማያትን የሚወርሱት
በጥምቀት ነው፡፡

ጥምቀት እንዲሆን ያደረገ እርሱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ኢየሱስም እንዲህ ሲል መለሰ፦
እውነት እውነት እልኻለሁ ማንም ከውኃና ከመንፈስ ቅዱስ ያልተወለደ ወደ እግዚአብሔር
መንግሥት ይገባ ዘንድ አይችልም። (ዮሐ. ፫፡፭) እንግዲህ ሂዱና በአብና በወልድ በመንፈስ
ቅዱስ ስም አሕዛብን ሁሉ አስተምሩ፤ አጥምቋቸውም። (ማቴ. ፳፰፡፲፱) ያመነ የተጠመቀ
ይድናል፤ ያላመነ ግን ይፈረድበታል። (ማር. ፲፮፡፲፮) ከእግዚአብሔር መወለዳችን
የእግዚአብሔርን ርስት መንግሥተ ሰማያትን ለመውረስ ነው።

ሐዋርያት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ከተማሩ በኋላ ጥምቀት ኃጢአት ማስተስረያና

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 47
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

የልጅነት መቀበያ መሆኑን ሲያስተምሩ እንዲህ ብለዋል፦ ጴጥሮስም አላቸው፦ ንስሐ ግቡ


ኃጢአታችሁም ይሰረይ ዘንድ እያንዳንዳችሁ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ፤ የመንፈስ
ቅዱስንም ስጦታ ትቀበላላችሁ፡፡ ሐዋ. ፪፡፴፰ ኢየሱስ ክርስቶስ በውኃ መታጠብና ከቃሉ ጋር
አንጽቶ እንዲቀድሳት ስለ እርስዋ ራሱን አሳልፎ ሰጠ፤ (ኤፌ. ፭፡፳፭) ነገር ግን
የመድኃኒታችን የእግዚአብሔር ቸርነትና ሰውን መውደዱ በተገለጠ ጊዜ እንደ ምሕረቱ
መጠን ለአዲስ ልደት በሚሆነው መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ በመታደስ አዳነን እንጂ እኛ
ስላደረግነው በጽድቅ ስለ ነበረው ሥራ አይደለም።

የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት ደግሞ ስለ ጥምቀት እንዲህ ሲሉ አስተምረዋል፦ ኃጢአትን


ለማስተስረይ በምንጠመቃት አንዲት ጥምቀትም እናምናለን። (ሃይ. አበው ዘሠለስቱ ምዕት)
ጥምቀት የኃጢአት መደምሰሻና የእግዚአብሔርን ልጅነት ማግኛ መሆኑን ስናምን ለዚህ
እምነታችን መሠረቱ ከብዙ በጥቂቱ የጠቀስነው የነቢያት ትንቢትና የጌታችን የኢየሱስ
ክርስቶስ ትምህርት፣ የሐዋርያትና የሊቃውንትም ትምህርት ነው። የምንጠመቅበት ውኃም
ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ቀኝ ጎን የፈሰሰ ውኃ ነው። ይኽን ውኃ የምናገኘው በጸሎት
በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ነው። አጥማቂው ካህን በመጠመቂያ ውኃ ላይ መጽሐፈ ክርስትናን
(ጸሎተ ክርስትናን) ይጸልይበታል፤ አሐዱ አብ ቅዱስ፤ አሐዱ ወልድ ቅዱስ፤ አሐዱ ውእቱ
መንፈስ ቅዱስ ብሎም በመስቀል ይባርከዋል። በዚህ ጸሎትና ቡራኬ የተጸለየበት ውኃ
በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ተለውጦ ከጌታ ጎን የፈሰሰ ውኃ ሆኖ ይከብራል።

4.2 የምሥጢረ ጥምቀት አመሠራረት


የምሥጢራት ሁሉ መግቢያ በር የሆነው ምሥጢረ ጥምቀት መሥራችሁ ራሱ ጌታችንና
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ ነገር ግን ከጌታችን ጥምቀት በፊት አይሁድ
ለመንጻትና ለኃጢአት ሥርየት የሚጠመቁት “ጥምቀት” ነበራቸው፡፡ ይኸውም እግዚአብሔር
በረድኤት የሚገለጥባቸው የተቀደሱ ዕለታትና ቦታዎች ሁሉ ሰውነትንና ልብስን ማጠብ
የእግዚአብሔር ቤት ማገልገያ የሆኑ ዕቃዎችን ሁሉ ማጠብ ማንጻት ሥርዓትና ልማድ
ነበር፡፡ ይህም የእግዚአብሔርም ፈቃድ ያለበት አሠራር ነበር፡፡ ወደ እግዚአብሔር ቤት
ከመቅረባቸውና ለተቀደሰው አገልግሎት ከመግባታቸው አስቀድመው እግሮቻቸውንና
እጆቻቸውን የመታጠብ ግዴታም ነበራቸው፡፡ ሰውነታቸውን ከአፍአዊ (ከውጫዊ) እድፍ
በማጠብና ንጹሕ በማድረግ በባሕርይ ንጹሕና ቅዱስ በሆነው አምላክ ፊት ውስጣዊ
ሕይወትን ንጹሕ አድርጎ የመቅረብን ሥርዓትና ምሥጢር የሚያመለክት መንፈሳዊ
ሥርዓት ነበር፡፡

ጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጥምቀትን የመሠረተው በሦስት


መንገድ ነው። መጀመሪያ በተግባር ራሱ ተጠምቆ እንድንጠመቅ አስተምሮናል፤ አርአያም

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 48
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ሆኖናል (ማቴ 3፡13)፡፡ ሁለተኛም በትምህርቱ “ያመነ የተጠመቀ ይድናል” (ማር 16፡16)
እንዲሁም “እውነት እውነት እልሃለሁ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔር
መንግሥት ሊያይ አይችልም” (ዮሐ 3፡3-6) በማለት ጥምቀት ለድኅነት አስፈላጊ መሆኑን
አስተምሯል፡፡ ሦስተኛም ለቅዱሳን ሐዋርያት በሰጣቸው ትዕዛዝ “እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን
ሁሉ በአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችሁ ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው”
(ማቴ 28፡19-20) በማለት ምስጢረ ጥምቀትን መስርቶልናል።

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቲያስ በ፴ ዓመቱ በዮርዳኖስ ወንዝ በእደ ዮሐንስ


ተጠምቆ ምሥጢረ ጥምቀትን የመሠረተበት መሠረታዊ ምክንያት አለው፡፡ የዚህም
ምክንያቱ አዳም የ፴ ዓመት ጎልማሳ ሆኖ ተፈጥሮ ሳለ በድሎ ገነትን ያህል ቦታ፣
እግዚአብሔርን ያህል ጌታ አጣ። በዚህም በደል ምክንያት ከክብሩ ተዋርዶ ነበርና ወደ
ቀደመ ክብርህና አገርህ መለስኩህ ሲል አዳም በተፈጠረበት ዕድሜ ተጠምቆ እንደካሰለት
ለማጠየቅ በ፴ ዓመቱ ተጠመቀ። በዚህም መሠረት ከሱ ጀምሮ ዘሩን (ትውልዱን) በሙሉ
እንዳዳናቸው ለማረጋገጥ ሥርዓተ ጥምቀትን ሠርቶ ለቤተ ክርስቲያን ሰጠ፡፡ ይህንንም
መሠረት በማድረግ ሃይማኖታቸው የቀና ቅዱሳን አባቶች “ወነአምን በአሐቲ ጥምቀት
ለሥርየተ ኀጢአት፣ ኀጢአትን በምታስተሠርይ በአንዲት ጥምቀት እናምናለን” በማለት
መሠረተ እምነትን ደንግገዋል፡፡ ሕፃናትን በሙሉ ማለትም ወንዶችን በተወለዱ በ፵ ቀናቸው
ሴቶችን ደግሞ በተወለዱ በ፹ ቀናቸው ይጠመቃሉ፡፡ ይህም ለአንዳንዶች እንደሚመስላቸው
ከመጽሐፍ ቅዱስ ያልተገኘ አዲስ ሥርዓት አይደለም፡፡ አዳም በተፈጠረ በ፵ኛው ቀን
ሔዋንም በተፈጠረች በ፹ኛው ቀን በይባቤ መላእክት ታጅበው ገነት መግባታቸውን መሠረት
ያደረገ ሥርዓት ነው እንጂ፡፡ (ኩፋ. ፬፥፱-፲፬) በተጨማሪም እግዚአብሔር አምላካችን ሴት
ልጅ ከሕርስ ስለምትነጻበት፣ ወደ መቅደስ ስለምትገባበትና የተወለደውን/ችውን/
በእግዚአብሔር ፊት ማቆም ስለሚችሉበት ጊዜ ሲናገር ለወንድ ልጅ ፵ ቀን ለሴት ልጅም ፹
ቀን መቆየት እንደሚያስፈልግ ሥርዓት ሠርቷል። (ዘሌ. ፲፪፥፩-ፍጻሜው) ቀደም ብሎም
የእግዚአብሔር ወገን የመሆን የቃል ኪዳን ምልክት የሆነው ግዝረት ሕፃናት በተወለዱ
በስምንተኛው ቀን ይፈጸም ነበር፡፡ (ዘፍ. ፲፯ ፥፩‐ፍጻሜው)

4.3 የጥምቀት ምሳሌዎች

1. አብርሃም ዮርዳኖስን ተሻግሮ ወደ መልከጼዴቅ መሔዱ፡- አብርሃም የምእመናን


መልከጼዴቅ የኢየሱስ ክርስቶስ ዮርዳኖስ ደግሞ የማየ ገቦ ምሳሌ ናቸው (ዘፍ. 14፡17) ፡፡

2. ኢዮብ በዮርዳኖስ ተጠምቆ ከደዌው መፈወሱ፡- ይህም ምእመናን ተጠምቀው ከደዌ ሥጋ


ከደዌ ነፍስ የመፈወሳቸው ምሳሌ ነው፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 49
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

3. ንዕማን ሶርያዊ ተጠምቆ ከለምጽ መዳኑ (2ነገ. 5፡14)፡- ይኸውም ምእመናን ተጠምቀው
ከመርገመ ሥጋ ከመርገመ ነፍስ የመዳናቸው ምሳሌ ነው፡፡

4. የኖኅ መርከብ (ዘፍ. 7፥13)፡- ይኽንንም ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ “ጥቂቶች ማለት
ስምንት ነፍሳት በውኃ የዳኑባትን መርከብ ሲሠራ በኖኅ ዘመን የእግዚአብሔር ትዕግሥት
በዘገየ ጊዜ ቀድሞ ክደውት ለነበሩት ሰበከላቸው፡፡ አሁንም እኛን በዚያው አምሳል በጥምቀት
ያድነናል ሥጋን ከዕድፍ በመታጠብ አይደለም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመነሣቱ
በእግዚአብሔር እንድናምን መልካም ግብርን ያስተምረን ዘንድ ነው እንጂ” (1ጴጥ. 3፥20)
በማለት ገልጾታል፡፡ የጥፋት ውሃ በኖኅ ዘመን በበደላቸው ተጸጽተው ንስሓ ያልገቡ
ሰዎችንና (ከኖኅና ቤተሰቡ እንዲሁም ለዘር እንዲቀሩ ከተደረጉት ፍጥረታት በቀር) በምድር
የሚኖሩትን ሁሉ ያጠፋው ማየ አይኅ(የጥፋት ውሃ) የጥምቀት ምሳሌ ሲሆን ፤ ከጥፋት
ውሃ የዳኑት ኖኅና ልጆቹ ፤ ከክርስቶስ ጎን ለጥምቀታችን በፈሰሰው ትኩስ ውሃ በጥምቀት
ከእግዚአብሔር ተወልደው ከፍርድ ለሚድኑ ምዕመናን ምሳሌ ነው።

5. ለአብርሃም ሕግ ሆኖ የተሰጠው ግዝረት፡- አብርሃም ከአረጀ በኋላ ቢገረዝም ልጆቹ ግን


በተወለዱ በስምንተኛው ቀን እንዲገረዙ እግዚአብሔር ትዕዛዝ ሰጥቶ ነበር (ዘፍ. 17፥9)
“በሰው እጅ ያልተደረገ መገረዝን በእርሱ ሆናችሁ ተገረዛችሁ፡፡ በጥምቀትም ከእርሱ ጋር
ተቀብራችኋል በእርስዋም ከሙታን ለይቶ ባስነሣው በእግዚአብሔር ረዳትነትና በሃይማኖት
ከእርሱ ጋር ተነሥታችኋል” (ቈላ. 2፥11)፡፡ ግዝረት ለጊዜው ለእስራኤል ዘሥጋ መለያ
ሲሆን፤ ፍጻሜው ግን ሊመጣ ላለውና ለእሥራኤል ዘነፍስ ምዕመናን መክበሪያ ለሆነው
ለጥምቀት ምሳሌ ነው ።

6. የእስራኤል የኤርትራ ባህርን (ቀይ ባህርን) መሻገር (ዘፀ 14፡21፣ 1ቆሮ 10፡1)፡- ሙሴ
የክርስቶስ፤ ባህሩን የከፈለባት በትር የመስቀል፤ ባሕረ ኤርትራ የፍርድና የሲኦል፤
በተከፈለው ባሕር የተሻገሩት እስራኤል በመስቀሉ ላይ በፈሰሰው ደሙ በጥምቀት ከእግዚአ
ብሔር ተወልደው ባሕረ ኃጢአትን የሚሻገሩ ምዕመናን ምሳሌ ነው። ኢያሱ የዮርዳኖስን
ባሕር ክፍሎ እስራኤል መሻገራቸውም እንዲሁ የጥምቀት ምሳሌ ነው (ኢያ 3፡14 4፡15)።
ኢያሱ የክርስቶስ፤ ዮርዳኖስ የጥምቀት፤ ዮርዳኖስን የተሻገሩ እስራኤል በክርስቶስ አምነው
በመጠመቅ የዳኑ ምዕመናን ምሳሌ ነው።

7. የዮሐንስ ጥምቀት (ማቴ 3፡1)፡- ዮሐንስ ህዝቡን የንስሓ ጥምቀት እያጠመቃቸው ከቆየ
በኋላ ጌታ በሚመጣበት ጊዜ ግን እነሆ የእግዚአብሔር በግ በማለት ወደ ጌታ መርቷቸዋል
ስለዚህ የዮሐንስ ጥምቀት ምሳሌ ሆኖ ለአማናዊዉ የጌታ ጥምቀት የሚያዘጋጅ ነው፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 50
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

4.4 የጥምቀት አከፋፈል (ዓይነቶች)

1. የንስሓ ጥምቀት

የንስሓ ጥምቀት ልጅነትን ላገኙ ሰዎች ሕይወት ፈተና ለሚደርስባቸው ድካምና ጉስቁልና
ፈውስ እንዲሆን የሚሰጥ ሊደጋገምም የሚችል የጥምቀት ዓይነት ነው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ
መጥምቅ ያጠምቀው የነበረ ጥምቀት የንስሓ ጥምቀት ማሳያ ነው፡፡ ምንም እንኳን ዮሐንስ
ጥምቀትን ያጠምቅ የነበረ ቢሆንም የዮሐንስ ጥምቀት ልጅነትን የሚያሰጥ ጥምቀት
አልነበረም፡፡ የዮሐንስ ጥምቀት የንስሐ ጥምቀት ነበር፡፡

የዮሐንስ ጥምቀትን አቅምንም ሊቃውንተ ቤተ ክርስትያን እንዲህ ሲሉ ይገልጹታል፡፡ እድፍ


ቆሻሻ የያዘው ልብስ በውኃ ታጥቦ ነጽቶ ሽቱ ይርከፈከፍበታል፡፡ ገላም ሲያድፍ በውኃ ታጥቦ
ጽዱ ልብስ ይለብሳል፡፡ እንደዚሁም ሁሉ የዮሐንስ ጥምቀት ተጠማቂዎቹ ኋላ በክርስቶስ
ጥምቀት የሚሰጠውን መንፈስ ቅዱስን ለመቀበል በቅተው እንዲገኙ ከኃጢአት
መለየታቸውንና ተለየን ማለታቸውን የሚገልጽ ምልክት ነበር፡፡ ራሱም አንዲህ ሲል
መስክሯል “እኔ ለንስሐ በውኃ አጠምቃችኋለሁ ከኔ በኋላ የሚመጣው እርሱ ግን በእሳት
ያጠምቃችኋል” (ማር 1፡4-8 ማቴ 3፡11 ሉቃ 3፡16 ሐዋ 19፡4)፡፡

በነቢዩ ሕዝቅኤልም ‹‹ጥሩ ውኃንም እረጭባችኋለሁ እናንተም ትጠራላችሁ፥


ከርኵሰታችሁም ሁሉ ከጣዖቶቻችሁም ሁሉ አጠራችኋለሁ። አዲስም ልብ እሰጣችኋለሁ
አዲስም መንፈስ በውስጣችሁ አኖራለሁ፤ የድንጋዩንም ልብ ከሥጋችሁ አወጣለሁ፤
የሥጋንም ልብ እሰጣችኋለሁ። መንፈሴንም በውስጣችሁ አኖራለሁ በትእዛዜም
አስሄዳችኋለሁ፥ ፍርዴንም ትጠብቃላችሁ ታደርጉትማላችሁ። ለአባቶቻችሁም በሰጠኋት
ምድር ትኖራላችሁ፤ ሕዝብም ትሆኑኛላችሁ እኔም አምላክ እሆናችኋለሁ›› (ሕዝ 36፡25-
28) ተብሎ የተtነገረውም የንስሐ ጥምቀትን የሚያመለክት ነው፡፡

2. የደም ጥምቀት፡-

ሲሆን ይህ የሰማዕታት የጥምቀት ዓይነት ነው። የክርስትናን እምነት በመማር ላይ ሳሉ


ወይም ተምረው ሳይጠመቁ ወይም ሁለቱንም ሳያውቁ ክርስቲያኖች ስለ ክርስቶስ ብለው
መሥዋዕት መሆናቸውን ተመልክተው “ኢየሱስ ክርስቶስ እውነተኛ አምላክ ነው፤
የክርስቲያኖች እምነት እውነተኛ ነው” በማለት መስክረው በሰማዕትነት የሚሞቱ ሰዎች
ደማቸው /ስቃያቸው/ በእግዚአብሔር ቸርነት እንደ ጥምቀት ይቆጠርላቸዋል። ልጅነትን
ያገኙበታል፤ ኃጢአታቸውም ይሰረይላቸዋል።

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 51
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

3. የልጅነት ጥምቀት

አስቀድመን በሥጋ ከእናትና አባታችን በዘር በሩካቤ እንደተወለድንና የሥጋ ልጅነትን


እንዳገኘን ሁሉ በማየ ገቦ ስንጠመቅ ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ እንወለዳለን፡፡ ይህንን
አስመልክቶ ጌታችን “ከሥጋ የሚወለድ ሥጋ ነው፥ ከመንፈስ የሚወለድ መንፈስ ነው” ብሎ
ከማስተማሩ በፊት “ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ
አይችልም” በማለት (ዮሐ.3፥3 እና 6) በምሥጢረ ጥምቀት ሀብተ ወልድና ስመ ክርስትና
ስለመገኘቱ አስተምሯል፡፡ ሐዋርያውም በጥምቀት ስላገኘነው የልጅነት ጸጋ አስመልክቶ
ሲናገር “አባ አባት ብለን የምንጮኸበትን (የምንጣራበትን) የልጅነትን መንፈስ ተቀበላችሁ
እንጂ እንደገና ለፍርሃት የባርነትን መንፈስ አልተቀበላችሁምና፡፡ የእግዚአብሔር ልጆች
መሆናችንን ያ መንፈስ ራሱ ከመንፈስ ጋር ይመሰክራል” ብሏል (ሮሜ.8፥15-16)፡፡

ጌታችንም ለተቀበሉት ሁሉ በስሙም ላመኑበት በጠቅላላው የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ


ዘንድ ሥልጣንን ሰጥቷቸዋል፡፡ እነርሱም ከእግዚአብሔር ተወለዱ እንጂ ከደም ወይም
ከሥጋ ፈቃድ ወይም ከወንድ ፈቃድ አለመወለዳቸው ተገልጿል (ዮሐ.1፥11-13)፡፡ እንግዲህ
እኛ ክርስቲያኖች ሁለት ልደታት እንዳሉን እናስብ፡፡ ይኸውም መጀመሪያው ከሥጋ እናትና
አባታችን የተወለድነው ሲሆን፤ ሁለተኛው ደግሞ ከእግዚአብሔር የምንወለደው ነው፡፡
ከተወለድን በኋላ እድገታችን በሁለቱም ወገን መሆን ያስፈልጋዋል፡፡ ሰው ሥጋዊም
መንፈሳዊም ነውና፡፡ ገላ 3፡26 ፡ ቲቶ 3፡5 ፡ 1ኛጴጥ 1፡23

ልጅነት የምታሰጠዋ ጥምቀት አንዲት ናት (ኤፌ 4፡4-5)፡፡ ነገር ግን በሦስት ዋና ዋና


መንገዶች ልትፈጸም ትችላለች። የውሃ ጥምቀት በካህናት አማካኝነት በተጸለየበት ውሃ
ውስጥ በሥላሴ ስም ተጠምቀን በመንፈስ ቅዱስ ግብር ከእግዚአብሔር የምንወለድበት ነው
(ዮሐ 3፡3-6)፡፡ ጥምቀት በመርኃ ደረጃ በውኃ የሚፈጸም ነው፡፡ ውኃው በጸሎት በተባረከ
ጊዜ ልጅነትን የሚሰጥ የእግዚአብሔር መንፈስ ስለሚያድርበት በእምነት ሆኖ በውኃ
የሚጠመቅ ከውኃና ከመንፈስ ቅዱስ ይወለዳል፡፡ ጥምቀት የእግዚአብሔር ቸርነት መገለጫ
ነው፡፡ ማንም ሰው ደሃ እንኳ ቢሆን ቢያንስ ውኃ ይኖረዋልና በጸጋ ከእግዚአብሔር
እንወለድ ዘንድ በውኃ መጠመቅ ይገባል፡፡

በውኃ መጠመቅ እየቻሉ መጠመቅን እንደተራ ነገር አድርገው የሚያቃልሉ ሰዎች ኤሳው
እንዳቃለላት ብኩርና ባለማወቅ የእግዚአብሔርን ጸጋ ያቃልላሉ፡፡ በአንጻሩ ደግሞ በፍጹም
ልብ የክርስትናን ትምህርት አምነው ከመጠመቃቸው በፊት በሰማዕትነት የሚያርፉ
ሰማዕታት እግዚአብሔር ባወቀ የልጅነትን ጥምቀት ከመንፈስ ቅዱስ ወይም ከእሳት
ይቀበላሉ፡፡ የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት ማለት ደግሞ በውሃ ሳንጠመቅ እግዚአብሔር በፍቃዱ

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 52
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ጸጋውን በመላክ የሚሰጠን ልደት ነው። ለዚህም ምሳሌ የሚሆነን ቅዱሳን ሐዋርያት
የተጠመቁት ጥምቀት ነው (ሉቃ 3፡16 ፡ ሐዋ 1፡5 ፡ ሐዋ 2፡1-4 ፡ 1ኛ ቆሮ 12፡13)፡፡

4.5 ለጥምቀት የተወሰነ ዕድሜ

በሐዋርያት ስብከት ያመኑና በማንኛውም የዕድሜ ክልል የሚገኙ ሁሉ ይጠመቁ ነበር


(ሐዋ16፡15፣ 1ቆሮ 1፡15) ። በኋላ ግን ወላጆቻቸው ሊያስተምሯቸው ቃል እየገቡ
ልጆቻቸውን ወንዶችን በአርባ ሴቶችን በሰማንያ ቀናቸው ማጥመቅ ተጀመረ ። ለዚህም
መሠረቱ የእስራኤል ልጆች በተወለዱ ወንድ በአርባ ሴት በሰማንያ ቀናቸው ወላጆቻቸው
መባዕ (ስጦታ) ይዘውላቸው ወደ ቤተ መቅደስ እየሄዱ በእስራኤልነት (የዜግነት) መዝገብ
እያስመዘገቡ የተስፋዋ ምድር ከነዓን ባለመብቶች (ወራሾች) ያደርጓቸው እንደነበረ ነው (ዘሌ
12፡1-10)፡፡ አዳም በተፈጠረ በ40 ቀኑ፣ ሔዋንም በተፈጠረች በ80 ቀኗ ወደ ርስታቸው
ገነት እንደገቡ ሕጻናትም በ40 እና በ80 ቀናቸው ተጠምቀው የሰማያዊት ኢየሩሳሌም
አምሳል ወደሆነችው ወደ ቤተክርስቲያን ይገባሉ፡፡

በኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ህጻናት ወላጆቻቸው እንዲሁም ክርስትና እናት ወይም አባት


ሃይማኖታቸውን ሊያስተምሯቸው ሃላፊነት ወስደው የክርስትና አባት ወይም እናት
በተጨማሪ ቃል ገብተው ክርስትና በመነሳት (በመጠመቅ) የወላጆቻቸውን ርስት መንግስተ
ሰማያትን ይወርሳሉ። ከአርባ እና ከሰማንያ ቀን በኋላ የሚመጡ ተጠማቂዎች ግን
ሃይማኖታቸውን ተምረው ካመኑ በኋላ በማንኛውም የዕድሜ ክልል መጠመቅ ይችላሉ።
በሕይወት እስካሉ ድረስ መቸም ቢሆን ከመጠመቅ የሚያግዳችው ነገር የለም።

4.6 የሕጻናት ጥምቀት


በሐዲስ ኪዳን መጻሕፍትም የሕፃናትን ጥምቀት በተመለከተ በርካታ ማስረጃዎች አሉ፡፡
ሐዋርያት አባቶቻችን ያመኑትን ባጠመቁ ጊዜ እንደ ክርስቶስ ፴ ዓመት እስኪሞላቸው
የሚጠብቁ አልነበረም፡፡ ሁሉንም (ሕፃናትንም ጭምር) በተገኙበት ዕድሜ በማጥመቅ ሀብተ
ወልድና ስመ ክርስትና ያሰጧቸው ነበር እንጂ፡፡ (ሐዋ. ፲፥፵፯-ፍጻሜ፤ ፲፩፥፲፬፤ ፲፮፥፲፭፡፴-
፴፬፤ ፩ቆሮ. ፩፥፲፮፡፡) ከዚህም በተጨማሪ ጌታችን ኢየሱስም “ሕፃናትን ተውአቸው፤ ወደ
እኔም ይመጡ ዘንደ አትከልክሉአቸው፤ መንግሥተ ሰማያት እንደ እነዚህ ላሉት ናትና፡፡”
(ማቴ. ፲፱፥፲፬-፲፮) በማለት አዝዞናል። እሱ ከፈቀደላቸው በኋላ እግዚአብሔር የተቀበላቸውን
“ዕድሜያችሁ ገና ነውና ዘወር በሉ” በማለት እኛ ልንከለክላቸው አንችላለንን? እግዚአብሔር
የተቀበላቸውን እኛ መከልከል እንደማንችል መረዳት ያስፈልጋል፡፡ ሕፃናት ሳያውቁ ከእናት
አባታቸው በሥጋ እንደተወለዱ ሁሉ እንደዚሁም ሳያውቁ (ሳያምኑ) በወላጆቻቸው እምነት
መንፈሳዊ ልደትን በጥምቀት ያገኛሉ ማለት ነው፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 53
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

አለማወቅና ሕፃንነት እግዚአብሔር የሚሰጠውን ድኅነተ ሥጋ፣ ድኅነተ ነፍስ ሊገድበው


አይችልም፡፡ ሌላው ቀርቶ እግዚአብሔር ሕፃናትን ከእናታቸው ማኅፀንም ሳይቀር
እንደሚመርጣቸውና እንደሚቀድሳቸው መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል፡፡ (ኤር.፩፥፭፣ ሉቃ.፲፥፵፬)
ከዚህም ሁሉ ጋር ቤተ ክርስቲያን ሕፃናትን ክርስትና ስታነሣ ከወላጆቻቸው በተጨማሪ
ለወንዶቹ የክርስትና አባት፣ ለሴቶቹም የክርስትና እናት ተቀብላ በክርስትና ሃይማኖት
ኮትኩተው እንዲያሳድጓቸው አደራ (ሓላፊነት) ሰጥታና ቃል አስገብታ ነው፡፡(ፍትሐ ነገሥት
አንቀጽ ፫፥፳-፳፮)።

በቤተ ክርስቲያናችን ሌላው ቀርቶ ሕጻናት ፵ እና ፹ ቀናቸው ሳይሞላ ለሞት የሚያሰጋ


ሕመም ቢታመሙ በሞግዚት ቤተ ክርስቲያን ወስደው እንዲያጠምቋቸው ታዟል፡፡ (ፍትሐ
ነገሥት አንቀጽ ፫፥፴፬)። ቢሞቱም ባገኙት ልጅነት ይድናሉ፤ ቢድኑም ጥምቀት አንዲት
ስለሆነች በዚያው ከብረው ይኖራሉ፡፡ ይህንንም አውቆ የማሳወቁ ተግባር የመምህራንና
የካህናት አባቶች መሆኑ መዘንጋት የለበትም። አንድ ሰው በክርስትና ሃይማኖት አምኖ
ካልተጠመቀ (ዳግመኛ ካልተወለደ) እንደማይድንና መንግሥተ እግዚአብሔርን
እንደማይወርስ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አስተምሮናል፡፡ (ማር. ፲፮፥፲፭-፲፮፣ ዮሐ. ፫፥፩-፯፣
ሮሜ. ፮፥፫-፭)፡፡

እምነት ከሁሉ ነገር ቢቀድምም አዲስ የሆነውን ክርስቲያናዊ ሕይወት ለማግኘትና ለመዳን
ጥምቀት ደግሞ ከምሥጢራት ሁሉ ቀድሞ ለአዲሱ አማኝ ይፈጸምለታል፡፡ ምሥጢረ
ሜሮንና ምሥጢረ ቁርባንም በዕለቱ (ወዲያወኑ) ተፈጽመውለት ተጠማቂው ሰው የክርስቶስ
አካል፥ የቤተ ክርስቲያን አባል ይሆናል ማለት ነው፡፡ ከዚህ ውጪ አንድ ሰው በክርስቶስ
አምኛለሁ፣ አመልከዋለሁም እያለ ጥምቀት አያስፈልገኝም ቢል ሊድን አይችልም፡፡
በክርስቶስ ያመነ ሰው ትምህርቱን ሁሉ መቀበልና መፈጸም ይጠበቅበታልና፡፡ “ዳግመኛ
ከውኃና ከመንፈስ ቅዱስ ያልተወለደ ሰው ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም፡፡”
(ዮሐ.3፡5፡፡) በማለት ያስተማረን ራሱ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ነው፡፡ ይህን አምላካዊ
መመሪያ ሳይፈጽሙ በክርስቶስ አምናለሁ ማለት ፈጽሞ አብሮ ሊሔድ አይችልም፡፡ ስለዚህ
በክርስቶስ ያመነ እወደዋለሁም የሚል ሰው ትእዛዛቱን በመፈጸም እንደሚድን መርሳት
አይኖርበትም፡፡

ቤተ-ክርስቲያን ሕፃናትን ክርስትና ስታነሣ ከወላጆቻቸዉ በተጨማሪ ለወንዶች ክርስትና


አባት ለሴቶች የክርስትና እናት ተቀብላ በሃይማኖት ኮትኩተዉ እንዲአሳድጓቸዉ አደራ
(ኃላፊነት) አደራ ሰጥታ ቃል ታስገባለች፡፡ ፍት. አንቀፅ 3÷2-26 ሕጻናት 40 እና 80
ቀናቸዉ ሳይሞላ ለሞት የሚያሰጋ ሕመም ቢታመሙ በሞግዚት ቤተ-ክርስቲያን ወስደዉ
እንዲያጠምቋቸዉ ታዟል፡፡ ፍት. አንቀፅ 3÷34 አንድ ሰዉ በክርስቶስ አምኛለሁ

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 54
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

አመልከዋለሁም እያለ ጥምቀት አያስፈልገኝም ቢል ሊድን አይችልም፡፡ ምክንያቱም


በክርስቶስ ያመነ ሰዉ ትምህርቱን ሁሉመቀበልና መፈጸም ይጠበቅበታል፡፡

ሥጋዌ ልደት ከወንድና ከሴት እንደሆነ ሁሉ መንፈሳዊ ልደትም ከዉኃና ከመንፈስ ቅዱስ
ነዉ፡፡ በዚህም የመንፈስ ቅዱስ ልጆች እንባላለን እንጅ የዉኃ ልጆች አንባልም፡፡ ምክንያቱም
የምንከብረዉ ከዉኃዉ ሳይሆን በመንፍስ ቅዱስ ስለሆነ ነዉ፡፡ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ
ቤተክርስቲያን ሕጻናትን በ40 እና በ80 ቀን ስታጠምቅ ምስጢራትን፣ ምሳሌዎችን፣
ትውፊትን እንዲሁም የጌታንና የሐዋርያትን አስተምህሮ መሠረት አድርጋ ነው፡፡ ቅዱስ
ዮሐንስ አፈወርቅም እንደሚናገረው ቤተ ክርስቲያን ሕጻናትን የምታጠምቀው ኃጢአት በደል
አለባቸው ብላ ሳይሆን ከለጋነት ዕድሜያቸው ጀምረው ፍቅሩን እያጣጣሙ እንዲያድጉ
የሚያስችላቸውን የእግዚአብሔር ልጅ የመሆንን ጸጋ ልትሰጣቸው ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን
ሕጻናትን የምታጠምቀው ያውቃሉ ወይም አያውቁም ብላ አይደለም፡፡ የቤተሰቦቻቸውን
እምነትና ፈቃድ ምስክር በማድረግ ነው እንጂ፡፡ በተጨማሪም ቤተክርስቲያን ሕጻናትን
የማጥመቋ ዋነኛ ምክንያቷ መጽሐፍ ቅዱስን መርኅ (መሠረት) አድርጋ ነው፡፡ ለምሳሌ
ያህል ብንመለከት፡-

አዳምና ሔዋን በተፈጠሩ በ40 እና በ80 ቀናቸው ወደ ገነት መግባታቸው (ኩፋ 4፡9)
እስራኤል መስዋዕት ይዘው በ40 እና በ80 ቀን ወደ ቤተመቅደስ እንዲመጡ
መታዘዛቸው (ዘሌ 12፡1-8)
በኦሪቱ ሕፃናትም አዋቂዎችም ተገርዘው የተስፋው ወራሾች ነበሩና ይህም የጥምቀት
ምሳሌ ነው (ዘፍ 17፡1-5 ቆላ 2፡11-12)
በባህረ ኤርትራ የተሸገሩት ሕፃናትም ጭምር ነበሩና ይህም የጥምቀት ምሳሌ ነው
(1ኛ ቆሮ 10፡1-2)፡፡
ወደ ኖኅ መርከብ የገቡት መላው ቤተሰብ ነውና ይህም የጥምቀት ምሳሌ ነው (ዘፍ
7፡1-17 1ኛ ጴጥ 3፡20-22)፡፡
ሕፃናት በማኅፀን ሳሉ መንፈስ ቅዱስ ከሞላባቸው ሲወለዱ እንዳይጠመቁ
የሚከለክለቸው ምንድን ነው (ሉቃ 1፡15 ኤር 1፡4-5)፡፡
ሐዋርያትም ካስተማሩ በኋላ ቤተሰቡን ሙሉ ያጠምቁ ነበር (ሐዋ 10፡44-48 11፡
13-14 16፡15 16፡43)፡፡
ጌታችንም “ሰው ዳግመኛ ከውኃና ከመንፈስ ቅዱስ ካልተወለደ…” ያለው ሕፃናትንም
ይመለከታል (ዮሐ 3፡8)፡፡
ጌታችንም “ሕጻናት ወደ እኔ ይመጡ ዘንድ አትከልክሏቸው” ብሏል (ማቴ 19፡14)፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 55
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

4.7 የሕጻናት ጥምቀት መብትን ይጋፋልን?

ጥምቀተ ክርስትና ሁል ጊዜ ተጠማቂው ተጠይቆ ላይፈጸም ይችላል፡፡ ይህም የሚሆነው


ተጠማቂው ሕጻን የሆነ እንደሆነ ብቻ ነው፡፡ ለሕጻናት የሚያስፈልጋቸውን እናደርግላቸዋለን
እንጂ ፈቅደዋል (አልፈቀዱም) በሚል ግብዝነት ተይዘን ከጽድቅ ጉዞ እንዲለዩ አናደርግም፡፡
ይሁንና አንዳንዶች የሕጻናትን ጥምቀት መብተን መጋፋት አስመስለው ሳይረዱ ይናገራሉ፡፡
ለምሳሌ የመጀመሪያው ሰው አዳም የተፈጠረው የሠላሳ ዓመት ጎልማሳ ሆኖ ነበር፡፡
እግዚአብሔር አዳምን ከፈጠረው በኋላ በአፍንጫው የሕይወት እስትንፋስን እፍ ብሎበታል፡፡
ይህም እፍታ ለአዳም የልጅነትን ጸጋ ያገኘበት ጥምቀቱ ነበር፡፡ ነገር ግን ይህን ታሪክ
በያዘው የኦሪት ዘፍጥረት መጽሐፍ ላይ እግዚአብሔር ለአዳም የልጅነት ጸጋውን ከመስጠቱ
በፊት እንደ ጠየቀው አይናገርም፡፡ ታዲያ እንዴት የሠላሳ ዓመቱ ጎልማሳ አዳም
ያልተጠየቀውን ጥያቄ የአርባ ቀን ልጅ ጠይቁ ማለት ይቻላል? እግዚአብሔር አዳምን
አልጠየቀውም ማለት አስገደደው ማለት አይደለም፡፡ ቤተ ክርስቲያንም ሕጻናትን በቀጥታ
እነርሱን አልጠየቀችም ማለት አስገድዳቸዋለች ማለት አይደለም፡፡ አዳም የኋላ ኋላ በፈቃዱ
ፈጣሪውን ክዶ ልጅነቱን እንዳጣ እንዲሁ የእግዚአብሔርን አባትነት ያልፈለጉትም
አድገውም ቢሆን የመካድ መብታቸው የተጠበቀ ነው፡፡

4.8 የቄደር ጥምቀት


ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የልጅነት ጥምቀትን አንድ ጊዜ ትፈጽማለች፡፡ "አንድ ጌታ አንድ
ሃይማኖት አንዲት ጥምቀት" ኤፌ.4:5 ከሌላ ቤተ እምነት የነበሩ ሰዎች ቢመለሱ አስተምራ
አሳምና ታጠምቃለች፡፡ ቀድሞ በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን ተጠምቆ ኋላ
ግን ወደ ሌላ እምነት ቢገባ ተናዞ (ንስሐ ገብቶ) በማየ ጸሎት (መጽሐፈ ቄደር ተደግሞለት)
ይረጫል እንጂ ድጋሚ አይጠመቅም፡፡ ቄደር የንስሐ እጽበት ነው ፡፡ ያደፈ ልብስ
እንደሚታጠብ ሁሉ ይህም ሰው ንጽሕት እምነቱን አሳድፏልና ከኃጢአቱ ለመታጠቡ
ምልክት ይሆን ዘንድ በማየ ጸሎት ይታጠባል፡፡ በዓረብኛ ቀድር ይባላል፡፡ ትርጉሙም እድፍ
ርኩስ ማለት ነው፡፡ መጽሐፉ ወደ ግዕዝ ከተተረጎመ በኋላ ቄድር ተብሏል፡፡

በአሕመድ ግራኝ ወረራ ጊዜ በ16ቱ ዓመታት በተቆጣጠረው ቦታ ሁሉ የሚኖር ትልቅም


ይሁን ትንሽ ካልሰለመ ለመኖር አይችልም ነበር፡፡ ከዚህም የተነሳ ብዙ ሕዝብ ሰልሟል፡፡
የሰለመውን ሕዝብ እንደገና ወደ ክርስትና ለመመለስ መጽሐፈ ቄደርን ከዓረብኛ ወደ ግዕዝ
ተተርጉሟል፡፡ ቄደር የንስሐ ጸሎት ማለት ነው፡፡ አንዳንድ መምህራን ቄደርን ከዮሐንስ
ጥምቀት ጋር ያያይዙታል፡፡ የዮሐንስ ጥምቀት የንስሐ እንደሆነ በመጽሐፍ ቅዱስ
ተጠቅሷል፡፡ ስለዚህም ነው የቄደር ጥምቀትን ከዮሐንስ ጥምቀት ጋር የሚያያይዙት፡፡ በቤተ
ክርስቲያን ስደት ከተጀመረ አንስቶ ስደት ፈርተው ከሃይማኖታቸው የወጡትን ሁሉ

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 56
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ለመመለስ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ይህን መጽሐፍ አዘጋጅተዋል፡፡ በመጽሐፉ መጀመርያም


"መጽሐፈ ቄደር ሃይማኖቱን ለካደ ወይም ላረከሰ ወንድም ይሁን ሴት የወንድ መነኩሴም
ይሁን የሴት መነኩሲት የቤተ ክርስቲያን መምህራን ያዘጋጁት ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን በዚሁ
መጽሐፍ ተጠቅማ የጠፉትን በጎቿን መልሳለች፡፡ በመጽሐፉ የሰፈረው ጸሎት ይደገምና
ውሃው በተመለሱት ሰዎች ላይ ይረጫል (ይጠመቁታል)፡፡ ከመንፈስ ቅዱስ ካልተወለደ
የእግዚአብሔር ን መንግሥት ሊያይ አይችልም» ዮሐ.3፡5 በማለት በጥምቀት ልጅነት
በልጅነት ድህነት እንደሚገኝ አስረድቶአል፡፡

4.9 ጥምቀት አንዲት (የማትደገም) መሆኗን

ጥምቀት የማትደገም፣ የማትከለስ አንዲት ናት፡፡ ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ ልጅነትን
የምናገኝባት ጥምቀት የማትደገምና የማትከለስ አንዲት ብቻ መሆንዋን ሲያስተምር ‹‹አንድ
ጌታ አንድ ሃይማኖት አንዲት ጥምቀት…አለ›› ብሏል (ኤፌ.4÷5)፡፡ ሃይማኖታቸው የቀና
318ቱ ሊቃውንትም ‹‹ኃጢአትን በምታስተሠርይ በአንዲት ጥምቀት እናምናለን፡፡›› ብለው
አስተምረዋል፡፡ “ኃጢአት በሚሠረይባት አንዲት ጥምቀት እናምናለን” እንዲል፡፡ ከወላጆቻችን
በሥጋ የምንወለደው አንድ ጊዜ ብቻ እንደሆነ ሁሉ ከውሃና ከመንፈስም ከእግዚአብሔር
የምንወለደውም (የምንጠመቀው) አንድ ጊዜ ብቻ ነው። የጥምቀት ምሳሌ የነበረው ግዝረት
አንድ ጊዜ ብቻ እንደነበረ ሁሉ ጥምቀትም አንድ ጊዜ ነው (ቆላ 2 ፥ 11)። ከጌታ ሥጋና
ደም የምንሳተፍበት ምሥጢር በመሆኑ ጌታም የሞተውና የተነሳው አንድ ጊዜ ነውና አንድ
ጊዜ ብቻ እንጠመቃለን (ሮሜ 6፡3)።

በዚህ የተነሣ ኣርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አንድ ጊዜ ያጠመቀችውን ድጋሚ


አታጠምቅም፡፡ ነገር ግን አማናዊቷን ጥምቀት ቀድሞም አልፈጸሙምና ከቤተ ክርስቲያናችን
ውጪ በሌላ በማናቸውም ሁኔታ ‹‹ተጠምቀን ነበር›› የሚሉትን ወደ ቤተ ክርስቲያናችን
ሲቀርቡ በሥርዓቷ መሠረት አስተምራ አሳምና ታጠምቃቸዋለች፡፡ በሌላ መልኩ ደግሞ በእኛ
ቤተ ክርስቲያን ከተጠመቀ በኋላ በሌላ ሃይማኖት ገብቶ እንደገና ቢጠመቅ ወይም ከሌላ
እምነት ተከታይ ጋር ጋብቻ ቢመሠርት በንስሓ ከተመለሰ በኋላ መጽሐፈ ቄደር ተጸልዮለት
ይጠመቃል። ይህ ግን ሁለተኛ ጥምቀት ሳይሆን የንስሓ ጥምቀት ይባላል። ቄደር የንስሐ
እጽበት ነው፡፡ ያደፈ ልብስ እንደሚታጠብ ሁሉ ይህም ሰው ንጽሕት እምነቱን አሳድፏልና
ከኃጢአቱ ለመታጠቡ ምልክት ይሆን ዘንድ በማየ ጸሎት ይታጠባል፡፡ ከኦሪየንታል አብያተ
ክርስቲያናት (Oriental Churches) በቀር በሌላ ማንኛውም ቤተክርስቲያን ከተጠመቀ በኋላ
አምኖ የሚመጣ ሰው ቢኖር እንደገና ይጠመቃል።

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 57
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

4.10 በማን ስም ልንጠመቅ ይገባል


ሐዋርያዊትና ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰዎች የእግዚአብሔርን ልጆች ይሆኑ
ዘንድ በሥላሴ ስም ታጠምቃለች፡፡ ይህም ጌታ ራሱ ለሐዋርያቱ ‹‹ሂዱና አሕዛብን ሁሉ
በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም አጥምቋቸው፡፡›› (ማቴ. 28÷19) ብሎ የሰጠውን
አምላካዊ ቃል መሠረት በማድረግ ነው፡፡ ስለዚህ ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ደም
ከተመሠረተችበት ዘመን አንስቶ በሥላሴ (በአብ፣ በወልድ፣ በመንፈስ ቅዱስ) ስም መጠመቅ
የድኀነት በር ቁልፍ መሆኑን ስታስተምርና ተግባራዊ ስታደርግም ኖራለች፡፡ ይህንን
የወንጌል ቃል የሚያጣምሙ ከኛ የተለዩ ወገኖች በኢየሱስ ስም ብቻ መጠመቅ አለብን እንጂ
በአብ፣ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም መጠመቅ የለብንም ይላሉ፡፡ ለዚህም ማስረጃ አድርገው
ለማቅረብ የሚሞክሩት የሐዋርያው የቅዱስ ጴጥሮስን አነጋገር ነው፡፡

ቅዱስ ጴጥሮስ በበዓለ ሃምሳ ከየሃገሩ ለተሰበሰቡት አይሁድ የምሥራቹን ቃል ድምጹን ከፍ


አድርጐ ባሰማቸው ጊዜ ልባቸው ተነካ፡፡ ስለዚህም ‹‹ምን እናድርግ›› ብለው ሊያደርጉት
የሚገባቸውን እንዲነግራቸው ጠየቁት፡፡ እርሱም ‹‹ንስሐ ግቡ፣ እያንዳንዳችሁ በኢየሱስ
ክርስቶስ ስም ተጠመቁ አላቸው›› (የሐዋ ሥራ 2÷38)፡፡ ሐዋርያው ‹‹በኢየሱስ ክርስቶስ
ስም ተጠመቁ›› ብሎ ማስተማሩ ለምን ነበር? ለምን ጌታ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ
ስም አጥምቁ ያለውን ተከትሎ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ተጠመቁ አላለም?
የሚል ጥያቄ ለሚያነሣ ሁሉ ምክንያቱ እንደሚከተለው ነው፡፡

በበዓለ ሃምሳ ከየሃገሩ የተሰበሰቡት አይሁድ ከጥንት ጀምሮ በነቢያት አንደበት ይወርዳል
ይወለዳል እየተባለ የተነገረለትን መሲሕን ተስፋ ያደርጉ ነበር፡፡ ሐዋርያውም ያ የተስፋው
ቃል ዛሬ መፈጸሙንና በተስፋው ቃል መሠረት ከድንግል ማርያም በሥጋ ተወልዶ 33
ዓመተ ከ3 ወር በምድር ላይ ተመላልሶ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ የሰውን ልጅ በደሙ የዋጀው
ኢየሱስ ክርስቶስ ትንቢት የተነገረለት ሱባዔ የተቆጠረለት መሆኑን አምነው በሰው
ካልተጠመቁ በስተቀር አብርሃም አባታችን እግዚአብሔር አምላካችን በሚለው እምነት ብቻ
አምነው ጌታን በሰቀሉት አይሁድ መንገድ የሚጓዙ ከሆነ እንደማይድኑ በመሲሕ አምነው
በስሙም ከተጠመቁ ግን እንደ ሚድኑ ሊያስተምራቸው ስለፈለገ የጌታን ስም ለይቶ ጠራ፡፡
በዚህም የጌታን አዳኝነትና መሲሕነት አምነው እንዲቀበሉ በአጽንዖት መናገሩ ነው፡፡

ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ ብቻ ሳይሆን ሌሎችም ሐዋርያት ከላይ በተጠቀሰው ምክንያት ቤዛ


የሆነልንን ጌታ ሰው ሁሉ አምኖ እንዲድን በየሄዱበት የጌታን አዳኝነትና የባሕርይ
አምላክነት አሰተምረዋል፡፡ የስብከታቸው ማዕከል የነበረው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነበር፡፡
ምክንያቱም ክህደቱ ጸንቶ የነበረው በጌታ የባሕርይ አምላክነት ላይ ነበርና፡፡ በዚህ የተነሣ
የእርሱን አዳኝነትና የባሕርይ አምላክነት ለማሳመን ጌታን የስብከታቸው ማዕከል አደረጉ፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 58
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

4.11 የጥምቀት አፈጻጸም

ተጠማቂው ንዑሰ ክርስቲያን ከሆነ መሠረታዊ የሃይማኖት ትምህርቶችን ተምሮ እምነቱ


የተመሰከረለት መሆን አለበት። ሕጻናት የሆኑ እንደሆኑ ግን ለሕጻናቱ የክርስትና እናትና
አባት ሊሆኑ የመጡት ሰዎች ስለሕጻናቱ እምነት መስክረውላቸው እንዲጠመቁ ይደረጋል።
በሚጠመቅበት ጊዜ በውሃ ውስጥ ሶስት ጊዜ ብቅ ጥልቅ ማለት አለበት ፤ የክርስቶስ ሞትና
ትንሳኤ ምሳሌ ነውና። ተጠማቂው የሚጠመቀው በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም ነው
(ማቴ 28 ፥ 19)። ተጠማቂዎች ባለትዳሮች ከሆኑና ቤተሰብም ካላቸው ሁሉም ተምረው
አምነው በአንድነት መጠመቅ አለባቸው። ከተጠመቀ በኋላ መቁረብ (ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር
ደሙን መቀበል) ይገባል። ይህ ካልሆነ ጥምቀቱ ሕያው አይሆንም። እንዲያጠምቁ ስልጣን
ያላቸው ከክህነት ደረጃዎች ውስጥ ኢጲስቆጶስና ቀሳውስት ብቻ ናቸው፡፡ ይህም ጌታችን
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የማጥመቅ ስልጣንን የሰጠው ለአስራ አንዱ ሐዋርያት ብቻ
ስለሆነ ነው (ማቴ 28፡19)፡፡ ዲያቆናት እንዲያጠምቁ አልተፈቀደላቸውም (ማቴ 28፡19 እና
ፍት ነገ አንቀጽ 3)። ክህነት በሌለው ሰው የተከናወነ ጥምቀት እንደ እጥበት እንጂ እንደ
ጥምቀት አይቆጠርም፡፡ በዚህ መንገድ “የተጠመቀ” ሰው ልጅነት የምታስገኘዋን እውነተኛዋን
ጥምቀት መጠመቅ አለበት፡፡

ጥምቀት በመድፈቅ ወይም በመንከር ነው እንጂ በመርጨት (በንዝሐት) አይፈጸምም፡፡


ምሳሌውን፣ ምስጢሩንና ሥርዓቱን ያፋልሳልና፡፡ ጥምቀት ማለት መነከር ማለት ስለሆነ
ውኃ ውስጥ ገብቶ መውጣትን ያመለክታል፡፡ ስለዚህም በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ሦስት ጊዜ ውኃ ውስት ገብቶ በመውጣት ይከናወናል (ማቴ 28፡19)፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስም
የተገለጠው በመንከር የተከናወነው ጥምቀት ነው፡፡ “ሰረገላውም ይቆም ዘንድ አዘዘ፥ ፊልጶስና
ጃንደረባው ሁለቱም ወደ ውኃ ወረዱ፥ አጠመቀውም። ከውኃውም ከወጡ በኋላ የጌታ
መንፈስ ፊልጶስን ነጠቀው፤ ጃንደረባውም ሁለተኛ አላየውም፥ ደስ ብሎት መንገዱን ይሄድ
ነበርና (ሐዋ 8፡38-39)” በሚለው ቃል ውስጥ “ከውኃ ከወጡ በኋላ” የሚለው
የሚያመለክተው ጃንደረባው የተጠመቀው ውኃ ውስጥ ገብቶ እንደነበር ነው፡፡ “እንግዲህ
ክርስቶስ በአብ ክብር ከሙታን እንደ ተነሣ እንዲሁ እኛም በአዲስ ሕይወት እንድንመላለስ፥
ከሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ በጥምቀት ከእርሱ ጋር ተቀበርን። ሞቱንም በሚመስል
ሞት ከእርሱ ጋር ከተባበርን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ደግሞ ከእርሱ ጋር
እንተባበራለን (ሮሜ 6፡4-5 ቆላ 2፡12)” በሚለው ቃል ውስጥ መቀበር መቃብር ውስጥ
መግባትን፣ ትንሣኤ ደግሞ ከመቃብር መውጣትን እንደሚያመለክት ጥምቀትም በውኃ
ውስጥ ገብቶ (በመነከር) መውጣትን ይጠይቃል፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 59
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

በአራቱም ወንጌላት የጌታችን ጥምቀትም በውኃ ውስጥ ገብቶ በመውጣት መሆኑ ተጽፏል፡፡
“ኢየሱስም ከተጠመቀ በኋላ ወዲያው ከውኃ ወጣ፤ እነሆም፥ ሰማያት ተከፈቱ
የእግዚአብሔርም መንፈስ እንደ ርግብ ሲወርድ በእርሱ ላይም ሲመጣ አየ (ማቴ 3፡16)”
በሚለው ቃል ውስጥ “ከውኃ ወጣ” የሚለው የጌታችን ጥምቀት የተከናወነው በመነከር
እንደነበር ያሳያል፡፡ በተጨማሪም በሥጋ መወለድ በእናት ማኅፀን ውስጥ ቆይቶ መውጣትን
የሚያመለክት እንደሆነ ሁሉ “ከውኃና ከመንፈስ ቅዱስ መወለድም” እንዲሁ ውኃ ውስጥ
ገብቶ መውጣትን (መነከርን) ይጠይቃል፡፡ ስለዚህም ነው ጥምቀት “ዳግመኛ መወለድ”
የተባለው (ዮሐ 3፡3)፡፡ ዋና ዋናዎቹ የምሥጢረ ጥምቀት አፈጻጸም ሥርዓትን የሚመለከቱ
ነጥቦች ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ናቸው፡፡

፩. ንዑሰ ክርስቲያን የሚጠመቁት የትንሣኤ ዕለት ከሆነ ተገቢውን ትምህርት ቀድመው


ተምረውና ንስሐ ገብተው በሰሙነ ሕማማት ሐሙስ ልብሳቸውን አዘጋጅተውና
ሰውነታቸውን ታጥበው በመጾም ቅዳሜ ሌሊቱን እሑድ ይጠመቃሉ፡፡ በሌላ ቀን ከሆነ
ደግሞ በዋዜማው ታጥበውና ጾመው ይዘጋጁና የመቁረቢያ ልብሳቸውን በንጽሕና
አዘጋጅተው በዕለቱ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሔደው ይጠመቃሉ፡፡

፪. ኤጲስ ቆጶሱ (ቄሱ) የሚጠመቁትን ሰብስቦ ራሳቸውን ወደ ምሥራቅ እንዲያዘነብሉ


ያዛቸዋል፡፡ እጁንም በላያቸው ዘርግቶ ይጸልይላቸዋል፡፡

፫. መሐላውን አስምሎ ማለትም ሰይጣንን አስክዶና ክርስቶስን አሳምኖ ከፈጸመ በኋላ


በዐራቱም መዓዘን ለአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሰግዶ በፊታቸው ላይ እፍ
ይልባቸዋል፡፡ አካላቸውንም አማትቦ ይባርካል፡፡

፬. ጥምቀቱ በትንሣኤ ከሆነ በዶሮ ጩኸት ጊዜ፤ በሌላ ቀንም ከሆነ መጠመቂያው ሰዓት
ሲደርስ ተጠማቂዎችን በመካነ ጥምቀቱ ያቆማቸዋል፡፡ ያውም ካልሆነ ካህኑ ማዩን ቸቸ
በብርት አድርጎ ሥርዓተ ጸሎቱን ያደርሳል፡፡

፭. ከሰይጣን ቁራኝነት በሚለይበት በቅብዓ ቅዱሱ ላይ ጸልዮ ለተራዳኢው ቄስ ይሰጥና


ከተጠማቂዎች በስተግራ ያቆመዋል፡፡

፮. ልጅነት በሚያሰጠውና መንፈስ ቅዱስን በሚያሳድረው በሜሮኑ ላይ ይጸልይና


ለሁለተኛው ቄስ ሰጥቶ ከተጠማቂዎች በስተቀኝ ያቆመዋል፡፡

፯. ተጠማቂዎችን በማዘዝ ፊታቸውን ከምሥራቅ ወደ ምዕራብ፤ ከምዕራብ ወደ ምሥራቅ


ይመልሳቸውና በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ማመናቸውን ያረጋግጣል::

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 60
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

፰. አንዱ ቄስ የተጠማቂዎችን እጅ እየያዘ ሕፃናትም ከሆኑ ዲያቆኑ (ቄሱ) አቅፎ ከምዕራብ


ወደ ምሥራቅ ይመልሳቸዋል፡፡ ይህም ሰይጣንን ክደው በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ
ስም ማመናቸውን በምሳሌ የሚያረጋግጥበት መንገድ ነው፡፡ ምዕራብ የማኅደረ
ዲያብሎስ ምሥራቅም የማኅደረ ሥላሴ ምሳሌዎች ናቸውና፡፡ (ነጽሩ ውስተ ጽባሕ….)

፱. ከዚህ በኋላ ቅብዐ ቅዱሱን ቀብቶ ያጠምቃቸዋል፡፡ ሲያጠምቃቸውም ልብሳቸውንና


ማንኛውንም ጌጣ ጌጥ አውልቀውና ሴቶችም ሹርባቸውን ፈትተው ነው፡፡ ከዚያም
በመጠመቂያው ፫ ጊዜ ብቅ ጥልቅ ያደርጋቸዋል፡፡ ምቹ መጠመቂያ ከሌለም ማዩን
በላያቸው ላይ ሦስት ጊዜ እያፈሰሰ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
አጠምቅሃለሁ/ሻለሁ/፤ እያለ ያጠምቃቸዋል፡፡ ከመጠመቂያው በወጡም ጊዜ በንፍሐት
ልጅነትን ያሳድርባቸዋል፡፡

፲. ሴት በምትጠመቅበት ዕለት የወር አበባ (ግዳጅ) ከመጣባት እስክትነጻ ሳትጠመቅ


ትቆያለች፡

፲፩. ተጠማቂዎች መናገር ከቻሉ ራሳቸው፤ ካልቻሉም የክርስትና አባት (እናት) የሆኑት
ክርስቲያኖች የተጠማቂውን አውራ ጣት ይዘው ጸሎተ ሃይማኖትን በማንበብ
ሃይማኖታቸውን ይመሰክራሉ፡፡

፲፪. ሥርዓተ ቅዳሴውን አድርሰው፣ መጽሐፈ ክርስትናውን ደግመው ማዩን ከባረኩ በኋላ
ነው ማጥመቅ የሚጀምሩት፡፡ የ፵ እና የ፹ ቀን ሕፃናት ከተጠመቁ በኋላ ንዑሰ
ክርስቲያን ወንዶችና ሴቶች ይጠመቃሉ፡፡

በሚያጠምቁበትም ጊዜ “አጠምቀከ/ኪ በስመ አብ፣ አጠምቀከ/ኪ በስመ ወልድ፣


አጠምቀከ/ኪ በስመ መንፈስ ቅዱስ፤ ስምከ/ኪ ይኩን እገሌ/ሊት” በማለት ሲሆን
አስቀድመው መስቀል ግንባሩ ላይ አድርገው የሰየሙትን ስመ ክርስትና የሚያጸኑት
በዚያው ሰዓት ነው ማለት ነው፡፡

፲፫. ከተጠመቁ በኋላ ካህኑ ሜሮን ይቀባቸዋል፡፡ የተዘጋጀላቸውን ነጭ ልብስ ለብሰው ቅዳሴ
አስቀድሰው ሥጋውን ደሙን ይቀበላሉ፡፡ በሜሮን ከከበሩም በኋላ ሦስት ኅብረ ቀለማት
ያሉት ማተብ ይታሰርላቸዋል፡፡ ኅብረ ቀለማቱም ነጭ፣ ቀይ፣ ጥቁር(ቢጫ) ናቸው፡፡
ምሳሌነት አለው በአንድ መገመዱ የሥላሴን አንደነት ሦስተ መሆኑ……

፲፬. የክርስትና አባት/እናት አብረው ጾመውና ተገቢውን ዝግጅት አድርገው በዕለቱ ሥጋውን
ደሙን ይቀበላሉ፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 61
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

፲፭. በዕለቱ ክርስትና የተነሡ (የተጠመቁ) ሕፃናትና ንዑሰ ክርስቲያን የነበሩ አዳዲስ የቤተ
ክርስቲያን ልጆች ከሌሎች ቆራብያን አስቀድመው ቅዱሱን ቊርባን ይቀበላሉ፡፡

፲፮. ወንዶች ሴቶችን፣ ሴቶችም ወንዶችን ክርስትና አያነሡም፡፡

፲፯. የምትጠመቀዋ ንዑሰ ክርስቲያን ሴት ከሆነች ቅብዓ ቅዱሱንም ሆነ ሜሮኑን ኤጲስ


ቆጶሱ/ቄሱ/ ልብስ እንደለበሰች ከአንገት በላይ ከቀባት በኋላ ዓይኑን ተሸፍኖ ወይም
በመጋረጃ ተጋርዶ ዲያቆናዊት ማለትም ዕድሜዋ የገፋ ከስልሳ ዓመት በላይ የሆነችና
የምታገለግል መነኩሲት እጁን ይዛ እየመራቸው ሌሎቹን ሕዋሳት ይቀባታል፡፡

፲፰. የተጠማቂዎችን ራስ የሚያጠልቅ ማይ (ውኃ) በቤተ ክርስቲያን የማይገኝ ከሆነ ማዩን


በእጁ እየታፈነ (እየዘገነ) በሥላሴ ስም ያጥምቃቸዋል፡፡

4.12 ለምን በውኃ እንጠመቃለን


ጥምቀት በዉኃ የሆነዉ በዓናችን የምናየዉ ዉኃ በአካላችን ላይ ሲፈስ የማናየዉ መንፈስ ቅዱስ
እንደሚያድርብን ለመግለጽ ነዉ፡፡ አንድም ዉኃ ከመንፈስ ቅዱስ መወለዳችንን እና የምንወለደበትነ
ቀን የሚያሳይ ነዉ፡፡ አንድም የሞትና የትንሣኤን ምስጢር ለመግጽ ነዉ፡፡ ወደ ዉኃዉ ዉስጥ ገብቶ
መጠመቅ ወደ መቃብር የመዉረድ ፣ ከዉኃ መዉጣትም ከመቃብር የመዉጣርት፣ የትንሣኤ ምሳሌ
ነዉ፡፡ ጌታችን በመንፈስ ቅዱስ እንድንወለድ ያዘዘን እርሱ በግብረ መንፈስ ቅዱስ ስለተወለደ ነዉ፡፡
ማቴ1÷20 ከመንፈስ ቅዱስ የተወለዱትን ተከታዮቹን ወንድሞቼ ይላቸዋል፡፡ ዮሐ 20÷17

በጥንተ ፍጥረት መንፈስ እግዚአብሔር በውኃ ላይ ረብቦ እንደነብር መጽሐፍ ቅዱስ


እንዲህ ሲል ይገልጻል፡- ‹‹የእግዚአብሔርም መንፈስ በውኃ ላይ ሰፍፎ ነበር›› (ዘፍ.1÷2)፡፡
እንዲሁም በውኃ፣ በሕይወትና በመንፈስ ያለውን ግንኚነት ማስተዋል ይገባል፡፡ ልዑለ ባሕርይ ጌታ
በነቢዩ በኤርምያስ አንደበት እንዲህ ሲል ተናግራል ‹‹ሕዝቤ ሁለቱን ክፉ ነገሮች አድርገዋልና እኔን
የሕያውን ውኃ ምንጭ ትተውኛል…›› (ኤር.7÷13)፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ትምህርቱ
በእኔ የሚያምን መጽሐፍ እንዳለ የሕይወት ውኃ ወንዝ ከሆዱ ይፈልቃል ብሎ አስተምሯል
(ዮሐ.7÷39)፡፡ ለሳምራዊቷ ሴትም ‹‹እኔ ከምሰጠው ውኃ የሚጠጣ ሁሉ ግን ለዘላለም አይጠማም፡፡
እኔ የምሰጠው ውኃ በእርሱ ውስጥ ለዘላለም ሕይወት የሚፈልቅ የውኃ ምንጭ ይሆናል እንጂ
አላት›› (ዮሐ.4÷14)፡፡ ከላይ በተገለጸው መሠረት ውኃ የሕይወት ምልክት ነው፡፡

በተለያዩ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች እንደምናነበው ውኃ ለሰማያዊው መንግሥት፣ ለዘላለም ሕይወት


ምሳሌ ሆኖ ተገልጿል፡፡ ‹‹እርሱም በውኃ ፈሳሾች ዳር አንደተተከለች ፍሬዋን በየጊዜው እንደምትሰጥ
ቅጠልዋም እንደማይረግፍ ዛፍ ይሆናል›› (መዝ. 1÷3) እና የመሳሰሉትን ሁሉ እናገኛለን
(ራእይ.2÷16፣ 22÷1፣ 22÷17)፡፡ እንግዲህ ውኃ ከክፉ ኀሊና ለመንጻታችንና ለመቀደሳችን
ማረጋገጫ መሆኑን ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ ሲል አስተምሯል፡- ‹‹ከክፉ ሕሊና ለመነጻት

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 62
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ልባችንን ተረጭተን፣ ሰውነታችንንም በጥሩ ውኃ ታጥበን፣ በተረዳንበት እምነት በቅን ልብ እንቅረብ››


(ዕብ.10÷22)፡፡

 ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተጠመቀው በውኃ ነው እኛም እርሱን አብነት በማድረግ በውኃ
ልንጠመቅ ይገባናል (ማቴ.3÷13-16)፡፡
 ጌታችን ለኒቆዲሞስ ‹‹እውነት እውነት እልሃለሁ ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ
እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም›› ስላለ እኛም የጌታን ትእዛዝ ለመፈጸም በውኃ
እንጠመቃለን (ዮሐ.3÷5)፡፡
 ሐዋርያት ከጌታ በተማሩት መሠረት ያጠመቁት በውኃ ነው፡፡ ጴጥሮስም መልሶ ‹‹እነዚህ እንደ
እኛ ደግሞ መንፈስ ቅዱስን የተቀበሉ እንዳይጠመቁ ውኃን ይከለክላቸው ዘንድ የሚችል ማን
ነው? አለ›› (የሐዋ.10÷46ና 47)፡፡ ፊልጶስና ጃንደረባው ሁለቱም ወደ ውኃ ወረዱ
አጠመቃቸውም (የሐዋ.8÷28)፡፡
 ውኃ የሰውነትን እድፍ እንደሚያጠራ ሁሉ እንዲሁም ጥምቀት የነፍስን እድፍ ያስወግዳል
 ውኃ መልክን ያሳያል እኛም በመጠመቅ የሥላሴን ምሥጢር በዓይነ ኅሊናችን እናያለን፡፡
 ለንጊኖስ የተባለው ሐራዊ (ወታደር) የጌታን ቀኝ ጎን በጦር በወጋው ጊዜ ትኩስ ደምና ውኃ
ባንድነት ፈሷል (ዮሐ. 19÷34)፡፡ ደሙ ለመጠጣችን፣ ውኃው ለጥምቀታችን መሆኑን ሲያጠይቅ
ነው፡፡ ይህንንም ፍቁረ እግዚእ ዮሐንስ እንዲህ ሲል ገልጾታል ‹‹በውኃና በደም የመጣ ይህ ነው፡፡
እርሱም ኢየሱስ ክርስቶስ በውኃና በደሙ እንጂ በውኃው ብቻ አይደለም፡፡የሚመሰክሩት መንፈሱና
ውኃው ደሙም እንጂ በውኃው ብቻ አይደለም፡፡ የሚመሰክሩተ መንፈሱና ውኃው ደሙም ሦስት
ናቸውና፡፡ ሦስቱም በአንድ ይስማማሉ›› (1ዮሐ.5÷6-8)፡፡
 ውኃ በሁሉም ቤት ይገኛል፡፡ በሀብታሙም በድኃውም ጥምቀትም ላመነ ሁሉ የተፈቀደ መሆኑን
ለማጠየቅ በውኃ ሆኗል፡፡ ስለዚህም በውኃ ብቻ እንጠመቃለን፡፡ ሥርዓተ ጥምቀቱን የሚፈጽመው
ካህን አሐዱ አብ ቅዱስ፣ አሐዱ ወልድ ቅዱስ፣ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ ብሎ በእግዚአብሔር
ቃል ሲባርከው ውኃው ተለውጦ በዕለተ ዓርብ ከጌታችን ቀኝ ጐን የፈሰሰውን ውኃ ይሆናል፡፡

4.13 የዉኃና የመንፈስ ኅብረት


ኅብረታቸዉ የተከሰተዉ ዓለም በተፈጠረ በመጀመሪያዉ ቀን ነዉ፡፡ ዘፍ 1÷2
“የእግዚአብሔር መንፈስ በዉኃዉ ላይ ሰፍሮ ነበር” በዉኃዉ ላይ መስፈፉ ፀጋ መንፈስ
ቅዱስ በዉኃ (ጥምቀት) ለዘመነ ሐዲስ ሰዎች የሚሰጥ መሆኑን ለማሳየት ነበር፡፡ ሳዊሮስ
ዘአንጾኪያ “በጥበብ በሥርዓት ስለ እኛ ከተፈጸመዉ ከዚህ ስራ (ከጥምቀት) አስቀድሞ
መንፈስ ቅዱስም በዉኃ ላይ ይሰፍፍ ነበር” ሃይማኖተ አበዉ 87÷16፣ ሕዝ 36÷25-26
“ጥሩም ዉኃም እረጭባችኃለሁ እናንተም ትጠራላችሁ ከርኩሰታችሁም ሁሉ
ከሐጢያታችሁም ሁሉ አጠራችኃለሁ አዲስም ልብ እሰጣቹኋለሁ አዲስም መንፈስ
ለዉስጣችሁ አኖራለሁ፡፡”

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 63
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

4.14 ስመ ክርስትና (የክርስትና ስም)


ስም አንድ ሰው ከሌላው ተለይቶ የሚታወቅበት ነው። በኢትዮጵያ ሁለት አይነት ስም አለ፡፡
አንዱ በጥምቀት በቤተ ክርስቲያን የሚወጣለት (የክርስትና ስም) ሲሆን ሌላው ደግሞ
ከቤተሰብ የሚወጣለት ስም (የዓለም ስም) ነው፡፡ በቀደሙት ዘመናት ክርስቲያኖች በክርስትና
ስም ብቻ ይጠሩ ነበር፡፡ በዓለም ስም መጠራት መቼ እንደተጀመረ በትክክል ባይታወቅም
የኢትዮጵያ ክርስቲያኖች ተደጋግሞ መከራ የደረሰባቸው ስለሆነ ክርስቲያኖችን የሚያሳድድ
ጠላት በመጣ ቁጥር የክርስትና ስማቸውን እየደበቁ ለመዳን የፈጠሩት ዘዴ ሳይሆን
እንዳልቀረ አባ ጎርጎርዮስ በመጽሐፋቸው ያስረዳሉ፡፡ ተጠማቂው የክርስትና ስም
የሚወጣለት ቄሱ በሚያውቀው የዕለቱን በዓል ምክንያት አድርጎ ነው፡፡ ለምሳሌ፦ የጌታ
በዓል ሲሆን ኃይለ መድኅን ገብረ ኢየሱስ የእመቤታችን በዓል ሲሆን ተክለ ማርያም ወልደ
ማርያም እየተባለ የክርስትና ስም ይሰጣል(ይሰየማል)፡፡

አባትና እናት የሚያወጡለት ስም የተጸውኦ ስም ይባላል፡፡ በጥምቀት ጊዜ የሚወጣለት ስም


ደግሞ የክርስትና ስም ይባላል፡፡ በጥምቀት ሀብተ ወልድና ስመ ክርስትና ይገኝበታል፡፡
በክርስቶስ የሚያምን ሰው ክርስቲያን ሲባል እምነቱ ደግሞ ክርስትና ይባላል። ክርስቲያን
ማለት የክርስቶስ ወገን የሆነ ማለት ነው። በመሆኑም በክርስቶስ አምነን በሥላሴ ስም
መጠመቃችንን የሚገልጸው ስም ስመ ክርስትና ይባላል። ስያሜውም ተጠማቂው
ከተጠመቀበት ዕለት ጋር ተያይዞ ሊሰየም ይችላል። በመንፈሳዊ አገልግሎት ስንሳተፍ ስመ
ክርስትናችንን እንጠቀማለን፡፡

የክርስትና ስም መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትውፊት ያለው ነው፡፡ ስም መስጠት (መሰየም)


በእግዚአብሔር ዘንድ የሚያስፈልግ የተፈቀደ እና የተወደደ እንደሆነ ከመጽሐፍ ቅዱስ
እንረዳለን፡፡ ሔዋን ከአዳም የጎን አጥንት ስትገኝ አዳም "ሴት "ብሎ ጠራት ስጋሽ ከስጋዬ
አጥንትሽ ከአጥንቴ ማለት ነውና፡፡ ዘፍ 2:23 በምክረ ከይሲ ተታለው ከሳቱ ከወደቁ በኋላ
አዳም ሚስቱን ሔዋን ብሎ ጠርቷታል፡፡ የሕያዋን እናት ማለት ነው፡፡ ዘፍ 3:20 ሔዋን
ተብላ ስሟን በግብር መግለጥ አልተቻላትም ህያዋንን ሳይሆን ሙታንን ወልዳ ነበርና፡፡
ይህስ በትንቢት መነፅርነት ስም ከግብር የተስማማላት ከዘሩ የምትወለደው እመቤታችንን
ሲያመለክት ነው፡፡ አዳም ለሚስቱ ስም ሲያወጣላትና ሲቀይርላት የስምንና የስምን ትርጉም
አስፈላጊነት ያሳየናል፡፡

እግዚአብሔር አምላክም ለአንድ ድርጊት መታሰቢያ እና የሚሰየመውን ሰው ተልእኮን


ለማሳየት የቅዱሳንን ስም ሲለውጥ በመጽሐፍ ቅዱስ እንመለከታለን፡፡ ለአብነት ያህል፡-
ከአብርሃምና ከሳራ ጋር የገባውን ቃል ኪዳን ሲያመለክት (ሲያሳስብ) "አብራምን ወደ
አብርሃም " ዘፍ 17:5 "ሦራን" ወደ "ሣራ" ለውጧል፡፡ ዘፍ 17:15 አብርሃም የብዙዎች
(የብዙ ህዝብ) አባት ሣራም የብዙዎች እናት ይሆናሉና፡፡ የአባቶች አለቃ ያዕቆብም ስሙ
በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)
ገጽ | 64
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ተለውጦ እስራኤል መባልን አግኝቷል፡፡ "ከእንግዲህ ወዲህ ስምህ እስራኤል ይባል እንጂ
ያዕቆብ አይባል፡፡" ዘፍ 32:28 በአዲስ ኪዳንም መድኃኒ ዓለም ክርስቶስ የዮና ልጅ
ስምዖንን ጴጥሮስ ብሎታል፡፡ ማቴ 16:18 ከሌሎች ሐዋርያት ጋር ስለ ተሰጠው ኀላፊነት
የሚገልፅ ነውና፡፡ በቀደመ ግብሩ ክርስቲያኖችን ያሰድድ የነበረው ሳውል ስሙ ተለውጦ
ጳውሎስ ተብሏል፡፡ ሐዋ 13:7 ነቢዩ ኢሳይያስም "በቤቴና በቅጥሬ ውስጥ ከወንዶችና ሴቶች
ልጆች የሚበልጥ መታሰቢያና ስም እሰጣቸዋለሁ፡፡ የማይጠፋ የዘላለም ስም እሰጣቸዋለሁ፡፡"
ኢሳ 56:5 እንዳለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ይህን አማናዊ ቃል መሰረት አድርጋ ከምዕመን
ክርስቲያን እስከ ህንፃ ቤተ ክርስቲያን ድረስ በቅዱሳን ስም እንዲጠራ ታደርጋለች፡፡

ዳግመኛም "የፃድቅ መታሰቢያ ለዘላለም ይኖራል፡፡" መዝ 111(112):6 በማለት ክቡር ዳዊት


ነግሮናል፡፡ "የፃድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነው፡፡" ምሳ 10:7 በረከትን እናገኛለን በስማቸው
በመጠራትም መታሰቢያቸውን እናደርጋለን፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅም ቅዱሳንን
የምናከብርበት እና የቅዱሳን ወዳጆች መሆናችንን የምናይበት መንገድ እንደሆነ ገልፆአል፡፡
“So let the name of the saints enter our homes through the naming of our
children, to train not only the child but the father, when he reflects that he is
the father of John or Elijah or James; for, if the name be given with
forethought to pay honor to those that have departed, and we grasp at our
kinship with the righteous rather than with our forebears, this too will greatly
help us and our children. Do not because it is a small thing regard it as
small; its purpose is to succor us.” (➕ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ➕)

በወንጌል "የራሱን በጎች በየስማቸው ጠርቶ ይወስዳቸዋል፡፡" ዮሐ 10:3 በሚለው ቃል


መሰረት በግ ጠባቂ በጎቹን መልካቸውን፣ ቀንዳቸውን፣ አካላቸውን በሚገልጥ ስም
እንዲሰይማቸው ኢየሱስ ክርስቶስም ደቀ መዛሙርቱን ሐዋርያት፤ ሰብአ አርድእት
ብሏቸዋል፡፡ ከሐዋርያትም አንዳንዶችን በአዲስ ስም ሰይሟቸዋል፡፡ ለምሳሌ፦ ስምዖንን
ጴጥሮስ ፤ ዲዲሞስን ቶማስ፤ ልብድዮስን ታዴዎስ ይህንንም የጌታችንን ቃል አብነት
አድርጋ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ከማኅፀነ ዮርዳኖስ ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ የተወለዱ
ልጆቿን በክርስትና ስም አክብራ ለመንግስቱ የበቁ ይሆኑ ዘንድ ታዘጋጃቸዋለች፡፡ በመሆኑም
የክርስትና ስም መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሰረት ያለው የእግዚአብሔር ፈቃድ የሚገለጥበት ነው፡፡
ሁላችን የክርስቶስ አካል የሆንን ብልቶች ነን፡፡ "ነገር ግን ብልቶች እርስ በርሳቸው ይተሳሰቡ
ዘንድ እንጂ በአካል መለያየት እንዳይሆን" 1ኛ ቆሮ 12:25 እንደተባለ እርስ በርሳችን
በፀሎት እንተሳሰብ፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 65
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

4.15 ማዕተብ (ክር) ማሰር

ማዕተብ የሚለው ቃል ዐተበ ካለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም አመለከተ


ማለት ነው። ስለዚህ ማዕተብ ማለት ምልክት ማለት ነው። በሃይማኖት አምነው ለተጠመቁ
ክርስቲያኖች የሚሰጥ ምልክት (መታወቂያ) ወይም ማኅተም ነው። ስለ ማዕተብ በመጽሐፍ
ቅዱስ የተለያየ ምሳሌዎች ተጠቅሰዋል። በብሉይ ኪዳን የነበሩ አባቶች ለእምነታቸው
መገለጫ ምልክት ነበራቸው። ለምሳሌ ለአበ ብዙኃን አብርሃም ግዝረት ተሰጥቶት ነበር
(ሮሜ 4፡13 ፡ ዘፍ 17፡9-14)። ማዕተብ ክርስቶስ በገመድ መታሰሩንና መጎተቱን
የሚያስታውስ ምልክትም ነው፡፡ “ክርስቶስ ደግሞ ፍለጋውን እንድትከተሉ ምሳሌ ትቶላችሁ
ስለ እናንተ መከራን ተቀብሎአልና (1ኛ ጴጥ 2:21)።” እንተባለ የክርስቶስን መከራ
እናስብበታለን (ዮሐ 18፡12-24) ማዕተብ በሦስት ዓይነት ቀለም መሆኑ የሦስትነት (የሥላሴ)
ምሳሌ ነው። ሦስቱ ክሮች ደግሞ በአንድ ተገምደው መሠራታቸው የአንድነቱ ምሳሌ ነው።
ክርስቲያን ማዕተብ በማሰሩ ስለ ክርስቲያንነቱ ሳያፍር ይመሰክርበታል፤ አጋንንትን ድል
ይነሣበታል፡፡ ተጸልዮበት ተባርኮ የሚታሠር ነውና ከቤተክርስቲያን በረከት ያገኝበታል፡፡
ማዕተብ ማሰርን ያስጀመረው ቅዱስ ያዕቆብ ዘእልበረዳኢ ክርስቲያኖችን ከመናፍቃን
ለመለየት ማዕተብ ያስርላቸው እንነበር በመጻሕፍት ተጽፏል፡፡

4.16 የክርስትና አባትና እናት

በ40 እና በ80 ቀናቸው ለሚጠመቁ ሕጻናት ስለ እምነታቸው ባለው ነገር ሁሉ ኃላፊነት


የሚወስዱ የክርስትና አባትና እናት እንዲኖራቸው ያደረጉት በ4ኛው መ/ክ/ዘ የነበረው የቤተ
ክርስቲያናችን የመጀመሪያው ኢጲስ ቆጶስ አባ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ናቸው። ዓላማውም
መንፈሳዊ ዝምድናን (አበ ልጅነትን) ማጠናከሪያ መንገድ ነው። በአበ ልጅነት የተዛመዱ
ሰዎች በጋብቻ መዛመድ አይችሉም። በሥጋ የተዛመዱ ከ7ተኛ የዝምድና ሐረግ በኋላ
መጋባት የሚፈቀድ ሲሆን በአበ ልጅ ግን የተዛመደ የቁጥር ገደብ የለውም (ፈጽሞ መጋባት
አልተፈቀደለትም) ፡፡ ይህም የሚያሳየው ከሥጋ ዝምድና ይልቅ ክብር የሚሰጠው
ለመንፈሳዊ ዝምድና መሆኑን ነው። ከክርስትና አባትነትና እናትነትን የሚከለክሉ ነገሮች
አሉ፡፡ እነዚህም የሥጋ ዝምድና ያላቸው፣ የጋብቻ ዝምድና ያላቸው፣ ዕድሜያቸው
ለማስተማር ለማሳመን ያልደረሰ፣ እምነት ትምህርት ችሎታ የሌላቸው፣ እምነታቸው
ከተጠማቂው ጋር ተመሳሳይ ያልሆነ ናቸው፡፡ የጾታ ሁኔታ በተመለከተ ወንድ ወንድን ሴት
ሴትን ያነሣል እንጂ ወንድ ሴትን፡ ሴት ወንድን ክርስትና ማንሣት አይፈቀድላቸውም፡፡
የክርስትና አባትና እናት ክርስትና ያነስዋቸው ልጆች በሥጋ ከወለድዋቸው ልጆች ሳይለዩ
ሕጻናቱ ዕድሜያቸውም ለትምህርት ሲደርስ መሠረታዊ የሃይማኖት ትምህርት የማስተማር

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 66
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ግዴታ እንዳለባቸው ቃል ይገባሉ። በገቡት ቃል መሠረት በተግባር የመተርጎም ኃላፊነት


አለባቸው።

4.17 የጥምቀት ጠቀሜታዎች

በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ከኒቂያ ጉባኤ በኋላ ከተነሱት አባቶች አንዱ “በፊተኛው
ትንሣኤ ዕድል ያለው ብፁዕና ቅዱስ ነው ሁለተኛው ሞት በእነርሱ ላይ ሥልጣን የለውም”
(ራእይ20:6) የሚለውን የወንጌላዊው ዮሐንስን አባባል በተረጎመበት የእግዚአብሔር ከተማ
በሚለው መጽሐፉ ላይ “ፊተኛው ትንሣኤ” የተባለው ሀብተ ወልድና ስመ ክርስትና
የምናገኝበት ጥምቀት እንደሆነ ገልጿል፡፡ ክርስቶስን መሠረት ያደረገ እምነት ሁሉ “ሰው
ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም” (ዮሐ. 3፡3)
የሚለው የጌታ ትምህርት መመሪያው ሊሆን ግድ ነው፡፡ ጌታችን እንዳስተማረውም
ያለጥምቀት ድኅነት የለም፡፡ በምስጢረ ጥምቀት በሚታየው አገልግሎት የሚገኘው
የማይታይ ጸጋ ግን ብዙ ነው፡፡ የሚከተሉት በጥምቀት የሚገኙ የማይታዩ ጸጋዎች ናቸው፡፡

1. ድኅነት

የድኅነት ባለቤት መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በግልጽ እንደተናገረው ዘላለማዊ ድኅነትን


ለማግኘት የሚሻ ሁሉ ወልድ ዋሕድ በምትለው ሃይማኖት አምኖ መጠመቅ ግድ ይለዋል፡፡
ስለዚህም ጌታችን ከሙታን ከተነሳ በኋላ ለደቀ መዛሙርቱ ‹‹ያመነ የተጠመቀ ይድናል፤
ያላመነ ግን ይፈረድበታል›› (ማር 16፡16) በማለት በጥምቀት ድኅነት እንደሚገኝ
አረጋግጧል፡፡ ከጌታ ከቃሉ የተማረ ቅዱስ ጴጥሮስ የመምህሩን ትምህርት መሠረት አድርጎ
“ጥቂቶች ማለት ስምንት ነፍስ በውኃ የዳኑበት መርከብ ሲዘጋጅ፤ የእግዚአብሔር ትዕግስት
በኖኅ ዘመን በቆየ ጊዜ ቀድሞ አልታዘዙም፡፡ ይህም ውኃ ደግሞ ማለት ጥምቀት ምሳሌው
ሆኖ አሁን ያድነናል የሰውነትን እድፍ ማስወገድ አይደለም” በማለት ጥምቀት የሰዉነትን
እድፍ ማስወገድ ሳይሆን ዉስጣዊ እድፍ (ኃጢአትን) የሚያስወግድ ምስጢር መሆኑን
ያስረዳል፡፡ (1ኛ ጴጥ. 3፡20-21)

መዳን ስንል የእግዚአብሔርን መንግሥት ወርሶ የዘላለም ሕይወት ባለቤት መሆን ማለት
ነው፡፡ ለስም አጠራሩ ክብር ምስጋና ይግባውና መድኃኒዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ የሌሊት
የትምህርት መርኃ ግብር ትምህርቱን በተመስጦ ኅሊና በሰቂለ ልቡና ይከታተል ለነበረው
ለኒቆዲሞስ የድኅነት በሩ ጥምቀት እንደሆነ ገልጾለታል “እውነት እውነት እልሃለሁ ሰው
ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግስት ሊገባ ይችልም” (ዮሐ.3፡
5)፡፡ ይህ ታላቅ ቃልም ጥምቀት ለድኅነት አስፈላጊ መሆኑን ያሳያል፡፡ ከጌታችን ጎን
በተገኘዉ በዉኃዉና በደሙ ልጅነትና ሥርየት ኃጢአት እናገኛለን፡፡ በማየ ገቦዉ

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 67
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

እንጠመቃለን፣ ደሙን ደግሞ በምሥጢረ ቁርባን እንቀበለዋለን ሐዋ 1÷38 “ንስሐም ግቡ


ኃጢአታችሁም ይሰረይ ዘንድ ኢያንዳንዳችሁ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ” ማቴ
28÷19-20 “የሰዉ ልጅ ይድን ዘንድ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሊጠመቅ
ይገባዋል፡፡” ማር 16÷16 “ያመነ የተጠመቀ ይድናል ያላመነ ግን ይፈረድበታል” ቲቶ 3÷5
ለአዲስ ልደት ለሚሆነዉ መታጠብና (በጥምቀት) ለመንፈስ ቅዱስ መታደስ አዳነን

2. የእግዚአብሔርን ልጅነት ማግኘት (ዳግም ልደት)

ጥምቀትን ዳግም ልደት ያስባለው ከሥጋ ልደት የተለየ በመሆኑ ነው፡፡ በአዳምና በሔዋን
ስህተት ምክንያት አጥተነው የነበረውን የልጅነት ጸጋ የምናስመልሰው በውኃ በምናደርገው
ጥምቀት ነው፡፡ ዳግም ከሥላሴ የምንወለደው በውኃ በምናደርገው ጥምቀት ነው፡፡
ምክንያቱም በጥምቀት የሚገኘዉ ልደት የማይጠፋና የማያዳግም ዘልዓለማዊ የልጅነት
ማኅተም ነዉ፡፡ 1ኛ ጴጥ 1÷23 “ዳግኛ የተወለዳችሁት ከሚጠፋ ዘር አይደለም፣ በሕያዉና
ለዘላለም በሚኖር በእግዚአብሔር ቃል ከማይጠፋ ዘር ነዉ እንጂ፡፡” ገላ 4÷6-7 “ልጆችም
ስለሆናችሁ እግዚአብሔር አባ አባትብሎ የሚጮኽ የልጁን መንፈስ በልባችሁ ዉስጥ ላከ፡፡
ስለዚህ ከእንግዲህ ወዲህ ልጅ ነህ አንጅ ባሪያ አይደለህም፡፡” ሮሜ 8÷15-17 “አባ አባት
ብለን የምንጮኽበትን የልጅነት መንፈስ ተቀበላችሁ እንጂ እንደገና ለፍርሃት የባርነትን
መንፈስ አልተቀበላችሁምና የእግዚአብሔር ልጆች መሆናችንን ያ መንፈስ ራሱ
ከመንፈሳችን ጋር ይመሰክራል፡፡”

3. መንግሰተ ሰማያት መዉረስ

በጥምቀት የምናገኘዉ የእግዚአብሔር የልጅነት ጸጋ የእግዚአብሔርን መንግስት ለመዉረስ


የምንችል ባለተስፋዎች እንድንሆን ያደርገናል፡፡ “ዳግመኛ ካልተወለደ ነገር የእግዚኣብሔርን
መንግስት ሊያይ አይችልም፡፡” ልጅነታችን መንግስቱን የምንወርስ ለመሆናችን መያዣ
(ዐርበን) ነዉ፡፡ “የመንፈስ መያዣሰጠን” 2ኛ ቆሮ 5÷5 ገላ 4÷7 “ልጅ ከሆንን ወራሾች
ደግሞ ነን፣ማለት የእግዚአብሔር ወራሾች ነንአብረን ደግሞ እንድንከብር ጥምቀት አብረን
መከራ ብንቀበል ከክረስቶስ ጋር አብረን ወራሾች ነን፡፡

4. ሥርየተ ኃጢአት:

“ወነአምን በአሐቲ ጥምቀት ለሥርየተ ኃጢአት” (ጸሎተ ሃይማኖት) ሊቃውንተ


ቤተክርስቲያን ባወጡት አንቀጸ ሃይማኖት ላይ ካሰፈሩት አንቀጽ አንዱ በጥምቀት ሥርየተ
ኃጢአት እንደሚገኝ “ወነአምን በአሐቲ ጥምቀት ለሥርየተ ኀጢአት፣ ኀጢአትን
በምታስተሠርይ በአንዲት ጥምቀት እናምናለን” የሚለው ነው፡፡ እነዚህ አባቶች በቅዱስ
መጽሐፍ የሰፈረውን በአንዳንድ የቤተክርስቲያን የውስጥ ጠላቶች አማካይነት ወደ
በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)
ገጽ | 68
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ቤተክርስቲያን ሾልኮ የገባን የስህተት ትምህርት ለማጥራት፣ እምነትን ለማጽናትና


ምእመናንን ከውዥንብር ለመታደግ አንቀጸ ሃይማኖትን ወስነዋል፡፡ ይህ የአበው ውሳኔ
መጽሐፍ ቅዱስን መሠረት ያደረገ መሆኑን ከብዙ ማስረጃዎች የምንገነዘበው እውነታ ነው፡፡
ለምሳሌ ያህል፡ በድንቅ አጠራሩ ለአገልግሎት የተጠራው ቅዱስ ጳውሎስ ከኃጢአቱ ይነጻ
ዘንድ “አሁንስ ለምን ትዘገያለህ? ተነሣና ስሙን እየጠራህ ተጠመቅ ከኃጢአትህም ታጠብ”
መባሉን አስተውሉ (የሐዋ. ሥራ 22፡16)፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በበዓለ ሃምሣ
ተሰብስበው ለነበሩት በትምህርቱ ልቡናቸው በተነካ ጊዜ “ምን እናድርግ?” ብለው ሲጠይቁት
የመለሰላቸው “ንስሐ ግቡ ኃጢአታችሁ ይሰረይ ዘንድ እያንዳንዳችሁ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም
ተጠመቁ” ብሏቸው ነበር (የሐዋ. ሥራ 2፡37-38)፡፡

5. ክርስቶስን መምሰል

“ጥምቀት ክርስቶስን በሞቱ የምንመስልበትና በትንሣኤው የምንተባበርበት ነው” (ሮሜ6፡3-4)


ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “ከክርስቶስ ኢየሱስ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ የተጠመቅን ሁላችን
ከሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ እንደ ተጠመቅን አታውቁምን? እንግዲህ ክርስቶስ በአብ
ክብር ከሙታን እንደተነሣ እንዲሁ እኛ በአዲስ ሕይወት እንድንመላለስ ከሞቱ ጋር አንድ
እንሆን ዘንድ በጥምቀት ከእርሱ ጋር ተቀበርን” (ሮሜ. 6፡3-4) በማለት በጥምቀት ክርስቶስን
እንደምንመስለው ተናግሯል፡፡ ማጥመቅ በፈሳሽ ውኃ ነው፤ ጥልቅ ውኃ በማይገኝበት ጊዜ
ግን ውኃ በሞላበት ገንዳ ይፈጸማል፡፡ ይህም ካልሆነ ውኃ ቀድቶ የተጠማቂውን መላ አካል
ውኃው እንዲያገኘው በማድረግ በእጅ እየታፈኑ ያጠምቁታል፡፡ በጥምቀት ጊዜ የተጠማቂው
አካል በውኃ እንዲጠልቅ መደረጉ “ከሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ በጥምቀት ከእርሱ ጋር
ተቀበርን” (ሮሜ. 6፡4) የሚለውን በገቢር ለመግለጽ ነው፡፡ እንዲሁም ተጠማቂው ከውኃ
ውስጥ ብቅ ማለቱ “በጥምቀት ደግሞ ከሙታን ባስነሣው በእግዚአብሔር ሥራ በማመናችሁ
ከእርሱ ጋር ተነሳችሁ” (ቆላ. 2፡12) ያለውን እንዲሁ በድርጊት ለማሳየት ነው፡፡

አጥማቂው ካህን “አጠምቀከ/ኪ በሥመ አብ አጠምቀከ/ኪ በሥመ ወልድ አጠምቀከ/ኪ


በሥመ መንፈስ ቅዱስ” እያለ ሦስት ጊዜ ብቅ ጥልቅ እያደረገ ድርጊቱን ሦስት ጊዜ
መፈጸሙ በሥላሴ አንድነትና ሦስትነት አምኖ መጠመቁን ለማጠየቅ ሲሆን እንዲሁም
የጌታን ሦስት መዓልት ሦስት ሌሊት በመቃብር አድሮ መነሳቱንና ተጠማቂዎችም ኋላ
በትንሣኤ ዘጉባኤ “ንቃ መዋቲ” የሚለው አዋጅ ሦስት ጊዜ በሚታወጅበት ጊዜ በቀዋሚ
አካል በምትናገር አንደበት ከራስ ጠጉራቸው እስከ እግር ጥፍራቸው ከቁጥር ሳይጎድሉ
ከሰውነታቸው ሳይከፈሉ ወንድ በአቅመ አዳም ሴት በአቅመ ሔዋን መነሳታቸውን ለማዘከር
ነው፡፡ ስለዚህ ጥምቀት “ከክርሰቶስ ጋር ከሞትን ከእርሱ ጋር ደግሞ በሕይወት እንድንኖር
እናምናለን” (ሮሜ. 6፡8) በሚለው የሐዋርያው ቃለ ትምህርት መሠረት ጥምቀት ጌታችን

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 69
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ኢየሱስ ክርስቶስን በሞቱ የምንመስልበት በትንሣኤውም የምንተባበርበት ታላቅ ምሥጢር


ነው፡፡

6. የክርስቶስ አካል መሆን፡-

“ጥምቀት የክርስቶስ አካል መሆናችን የሚረጋገጥበት ነው” (ገላ 3፡27) በዘመነ ብሉይ
የአብርሃም ወገኖች የአብርሃም ልጆች መሆናቸው ይረጋገጥ የነበረው በግዝረት ነበር፡፡
ግዝረት በኦሪቱ የእግዚአብሔር ሕዝብ መለያ ነበር፡፡ ያልተገረዘ ሁሉ ከሕዝቡ ተለይቶ
እንዲጠፋ የእግዚአብሔር ትዕዛዝ ነበር (ዘፍ. 17፡14)፡፡ ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ
በአምሳልነት ሲፈጸም የኖረው ግዝረት በዘመነ ሐዲስ በጥምቀት መተካቱን “በክርስቶስ
ገዛሪነት የኃጢአትን ሕዋስ ሰንኮፍ ቆርጦ በመጣል ሰው ሰራሽ ያይደለ ግዝረትን
የተገዘራችሁበት፤ በጥምቀት ከእሱ ጋር ተቀበራችሁ ከሙታን ለይቶ ባስነሣው
በእግዚአብሔር ረዳትነትም በሃይማኖት ከእሱ ጋር ለመኖር በእስዋ ተነሣችሁ” (ቆላ. 2፡11-
12) በማለት አበክሮ ያስገነዝባል፡፡ ግዝረት ለሕዝበ እግዚአብሔር የአብርሃም የቃል ኪዳን
ተሳታፊዎች የመሆናቸው መለያ ምልክት እንደነበር ሁሉ ጥምቀት ደግሞ በጌታ በኢየሱስ
ክርስቶስ ለሚያምኑ ሁሉ የጸጋው ግምጃ ቤት ከሆነችው ቅድስት ቤተክርስቲያን ውስጥ
የሚገኘው ጸጋ ተሳታፊ ያደርጋቸዋል፡፡ በጥምቀት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር አንድ
እንሆናለን፡፡ “ከክርስቶስ ኢየሱስ ጋር አንድ ትሆኑ ዘንድ የተጠመቃችሁ ሁሉ ክርስቶስን
ለብሳችኋልና” (ገላ. 3፡27) በማለት ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እንደተናገረው በጥምቀት
ከእግዚአብሔር ጋር አንድ እንሆናለን፡፡ እንግዲህ እግዚአብሔር ያደሰውን አዲሱን ሰውነት
የምንለብሰውና የክርስቶስ ተከታዮች የምንሆነው በጥምቀት ነው፡፡

4.18 ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለምን ተጠመቀ

ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጥር 11 ቀን በዮሐንስ እጅ በባሕረ


ዮርዳኖስ ተጠመቀ፡፡ ሉቃ. 3፡21፡፡ እርሱ የባሕርይ አምላክ ሲሆን ራሱን ዝቅ አድርጎ
በአገልጋዩ እጅ ተጠመቀ፡፡ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመጠመቁ፡-

ሀ/ የዕዳ ደብዳቤያችንን ደመሠሠልን፡- በአዳምና በሄዋን መተላለፍ ምክንያት አዳምና ሄዋን


የ እግዚአብሔር ን ልጅነት ርስታቸው ገነትን አጥተው በሞት ጥላ ሥር ወደቁ፡፡
የ እግዚአብሔር ልጆች የነበሩ የሳጥናኤል ባሪያዎች ሆኑ፤ ዲያብሎስ በተንኰሉ የሰው
ልጆችን ለዘለዓለሙ ለመኰነን «አዳም ገብሩ ለዲያብሎስ ሄዋን ዓመቱ ለዲያብሎስ» የሚል
የሰው ልጆች መቅጫ የሚሆን ጽሑፍ በዮርዳኖስ እና በሲኦል አስቀምጦ ነበር፡፡ ጌታችን
አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮርዳኖስ በተጠመቀ ጊዜ በዮርዳኖስ የነበረውን
የዕዳ ደብዳቤያችንን ደምስሶ አጠፋልን፡፡ ስለዚህ ነው ቅዱስ ዮሐንስ «የዲያብሎስን ሥራ

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 70
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ያፈርስ ዘንድ የ እግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ»1ኛዮሐ.3፡9 በማለት የመሠከረው ቅዱስ


ጳውሎስም ለገላትያ ምዕመናን በጻፈላቸው መልእክቱ «በነጻነት ልንኖር ክርስቶስ ነጻ አወጣን»
ሕገላ.5፡1ሕ በማለት ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የዕዳ ደብዳቤያችን
ደምስሶ ከሞት የባርነት አገዛዝ ነጻ እንዳወጣን አስረድቶአል፡፡

ለ/ በጥምቀቱ ወለደን፡- አዳምና ሄዋን ከተፈጠሩባት ኤልዳ ከምትባል ቦታ አዳም በ4ዐ ቀን


ሄዋን በ8ዐ ቀን በይባቤ መላእክት ወደ ገነት ገብተው ነበር፡፡ ኩፍሌ 4፡9-13፡፡ ሕጉን
በተላለፉ ጊዜ ከገነት ወጥተው፣ ልጅነታቸውን አጥተው በጉስቁልና ወድቀው
ሲኖሩ እግዚአብሔር ዘጠና ዘጠኙን ነገደ መላእክት ትቶ ሰውን ለመፈለግ አምላክ ሰው ሆነ
የአዳምን ልጅነት ለመመለስ በዮርዳኖስ ተጠመቀ፡፡ «ኀዲጎ ተሥዐ ወተሰዐተ ነገደ ቆመ
ማዕከለ ባህር» ዘጠና ዘጠኙን ነገደ መላእክት ትቶ ሰውን ለመፈለግ አምላክ ከባህር ውስጥ
ቆመ በማለት ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ በድጓው እንደገለጸው አምላክ በውሃ ተጠምቆ
ጠፍተን የነበርነውን ፈለገን፤ ፈልጐም አዳነን፤ የመጀመሪያ የልጅነት ጸጋችንን መለሰልን፤
ወራሾቹም አደረገን፡፡ «ያዘዝኋችሁን ሁሉ ብታደርጉ ወዳጆቼ ናችሁ» ዮሐ.15፡14፡
፡ እግዚአብሔር ወልድ በጥምቀቱ ወለደን «ወለደነ ዳግመ እመንፈስ ቅዱስ ወማይ» እንዲል
በጥምቀቱ ሀብተ ልደት ጸጋ መንፈስ ቅዱስን ሠጠን፤ ጥምቀትን መዳኛ የመንግሥተ
ሰማያት መግቢያ በር አደረገው፤ ያለጥምቀት ሰው መዳን አይችልምና፡፡

ሐ. በጥምቀቱ አህዛብና ሕዝብን አንድ አደረገ

ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተጠመቀው በዮርዳኖስ ወንዝ ነው፡፡


የዮርዳኖስ ምንጭ ከላይ አንድ ሲሆን ለሁለት ይከፈልና ዝቅ ብሎ አንድ ይሆናል፡፡ ጌታችን
ከመገናኛው ተጠምቆአል ይህም ሕዝብና አህዛብ በጥምቀቱ አንድ እንደሆኑ ያስረዳል፡፡ በጌታ
ጥምቀት ሕዝብና አህዛብ አንድ እንደሆኑ «ከክርስቶስ ጋር አንድ ትሆኑ ዘንድ
የተጠመቃችሁ ሁሉ ክርስቶስን ለብሳችኋልና አይሁዳዊ፣ ግሪካዊ፣ ባሪያ፣ ጨዋ፣ ወንድ፣
ሴት የለም ሁላችሁም በክርስቶስ አንድ ሰው ናችሁ» በማለት የሰው ዘር ልዩነት በጌታችን
በአምላካችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ሁሉ ተወግዶ ሰው እኩል መሆኑን እና
በጥምቀት አንድ ሰው መሆኑን አስረድቶአል፡፡ ገላ. 3፡27፡፡

4.19 የጥምቀት በዓል አከባበር

የጥምቀት በዓል አከባበር በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጌታችን


አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ሰው ልጆች ድኅነት ከዮሐንስ እጅ ይጠመቅ
ዘንድ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ ያደረገውን አምላካዊ ጉዞ ለማሰብ ታቦታቱ በካህናትና
በምእመናን ታጅበው ወደ ባህረ ጥምቀት ተጉዘው አምሳለ ዮርዳኖስ በሆነውና በተዘጋጀላቸው

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 71
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ስፍራ ያርፋሉ፡፡ ሌሊቱን በሙሉ በማኅሌትና በቅዳሴ በዓሉ እየተከበረ ያድርል፡፡ ጧት


የበረከት ጥምቀት ከተፈጸመ በኋላ በደማቅና በልዩ ልዩ ሥነ ሥርዐት
በስብሐተ እግዚአብሔር በዓሉ ይከበራል፡፡ ታቦታቱም በማኅሌትና በእልልታ ታጅበው ወደ
መንበራቸው ይመለሳሉ፡፡ ይህ ዕለት ነጻ የወጣንበት የዕዳ ደብዳቤያችንን የተደመሰሰበት
ከ እግዚአብሔር ጋር አንድ የሆንበት ዕለት ስለሆነ ልዩ በሆነ ደስታ እናከብረዋለን፡፡ ይህንን
ታላቅ በዓል በምናከብርበት ጊዜ በክርስቶስ የተደመሰሰው ኃጢአትን አስወግደን እንደ
ልብሳችን ልባችንን በንስሐ አጥበን ንጹሐን ሆነን ፈቃደ ሥጋችንን ለፈቃደ ነፍሳችን
አስገዝተን እግዚአብሔር ን ከሚያሳዝን ከኃጢአት፣ ከተንኰል፣ ከዘረሕነት፣ወዘተ ሁሉ ርቀን
ለነፍሳችን በሚጠቅም በፍፁም መንፈሳዊ ሥርዓት በዓሉን ልናከብር ይገባናል፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 72
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

5. ምስጢረ ሜሮን
5.1 የቅብዓ ሜሮን ትርጉም
ሜሮን ማለት የጽርዕ ቋንቋ ነው ትርጉሙም መዓዛ ያለው የሚያውድ ፣ የሚጣፍጥ፣ ልብ
የሚመስጥ ፣ ጣዕም ያለው መልኩ ጽርየቱ ዘይት ነው፡፡ በግሪክ ሲሆን ደግሞ ትርጉሙም
ቅብዕ ማለት ነው፡፡ በግዕዝ ቅብዕ፣ ቅብዐ ሜሮን ይባላል፡፡ አንድም ሜሮን ማለት ቅዱስ
ቅብዕ / ዘይት ማለት ነው ፡፡ ቅብዐ ቅዱስ፣ የተባረከ ሽቱ፣ ብፁዓን ጳጳሳት ከበለስንና ከዕፀወ
ዕጣን ከአስጳዳቶስ ከሌላም ከብዙ ዓይነት ሽቱ፣ ተገቢውን ሥርዓተ ጸሎት ፈጽመው
የሚያወጡት ሲሆን በሚመለከተው ጳጳስ አማካኝነት በየሀገረ ስብከቱ ላሉ አብያተ
ክርስቲያናት ሁሉ በነጻ የሚታደል ነው፡፡ ይህም ለመንፈሳዊ አገልግሎት ብቻ የሚውል
የተቀደሰ ቅባት ነው። (መጽ. ሰዋ. ወግስ መመዝ. ቃላት ሐዲስ ገጽ ፮፻፰፡፡) ስለ ቅብዐ
ሜሮን ቅዱስ መጽሐፍን የፃፉ ሰዎች የመንፈስ ቅዱስን ስጦታ ቅብዐት ይሉታል፡፡ 2ቆሮ 1፡
21 ዮሐ 2፡20 ቅብዕን በመንፈስ ቅዱስ ማህተምን ይሉታል፡፡ ኤፊ 1፡13 ፣4፡30 ይህ ቅብዓ
ማህተመ ሕይወት በመሆኑ ለአገልግሎት ይውላል፡፡

5.2 የቅብዐ ሜሮን አገልግሎት


ምሥጢረ ሜሮን ጥቅሙና አገልግሎቱ በብሉይ ኪዳን ለእግዚአብሔር የኾነው ኹሉ
የሚታተምበት፣ ያደፈው የረከሰው የሚቀደስበት ቅብዕ ነው፡፡ እግዚአብሔርን ለማገልገል
የሚሾሙ ሌዋውያን ካህናት /አራት ሽቱ አምስተኛ ዘይት/ የሚቀቡት ዕብፅ ይህ ነበር፡፡
የእግዚአብሔርን ሕዝብ እስራኤልን የሚጠብቁ የእግዚአብሔር እንደራሴዎች ነገሥታትም
“መሢሐን” የሚባሉት በዚህ ተቀብተው ስለሚነግሱ ነው፡፡ “መሢሕ” ማለት ቅቡዕ የተቀባ
ማለት ነውና፡፡

የቃል ኪዳኑ ታቦት (ፅላት) ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብቶ በመንበረ ክብሩ ላይ በመቀመጥ


አገልግሎት እንዲሰጥ አስቀድሞ በዚህ በተቀደሰ ቅብዓ ሜሮን ተባርኮ መሰየም አለበት።
ተሰርቆ ወይም በሌላ፤ ክብሩ በማይጠበቅበትና ተገቢ ባልሆነ ቦታ ቢቆይም ከተመለሰ በኋላ
እንደገና መባረክ አለበት። ቤተ ክርስቲያን ከታነጸ በኋላ፤ በውስጡ ሙሉ የቤተ ክርስቲያን
አገልግሎት ከመስጠቱ በፊት በቅብዓተ ሜሮን መባረክ አለበት። በቅብዓተ ሜሮን ካልተባረከ
ቤተ ክርስቲያን ሊባል አይችልም። ይኸም ብቻ አይደለም የቤተመቅደስ ንዋያተ ቅድሳትን
አስቀድሞ በዚህ መታተም አለባቸው፡፡ ከተቀቡ በኋላ ለቤተ መቅደስ እንጂ ለተራ
አገልግሎት አይውሉም ከብሉይ ኪዳን በፊት የነበረው አካሔዱን ከእግዚአብሔር ጋር
ያደረገው ከአሥሩ አንዱ ሔኖክ ከመሰወሩ በፊት ሜሮን ተቀብቶ እንደ ተሰወረና ልማደ
ሰብእ እንደ ጠፉለት ይነገራል፡፡ በተጨማሪም የቅብዐ ሜሮን አገልግሎት ለአንድ ዓይነት
ተግባር ብቻ አይደለም፡፡ በብሉይ ኪዳን እንዳየነው ሁሉ በሐዲስ ኪዳንም ቅብዓ ሜሮን
ሦስት ዓይነት አገልግሎቶች አሉት፡፡ እነዚህም፡-

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 73
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

፩ኛ. ጸጋ መንፈስ ቅዱስን ለመቀበል፡- አዳዲስ አማንያን (ተጠማቂዎች) ከተጠመቁ በኋላ


በሜሮን ተቀብተውና ከብረው ሀብተ መንፈስ ቅዱስ እንዲያድርባቸው ያደርጋል፡፡

፪ኛ. የእግዚአብሔር አገልጋዮች (ካህናት)ን ለመሾም፡- ካህናት አባቶች የእግዚአብሔርን ቤተ


ክርስቲያን ወይም ሕዝብ ለማገልገል የሚችሉበትን ሥልጣን (ሹመት)፣ ማስተዋል (ጥበብ)፣
ኃይል ብርታት) ፣ ትዕግሥትና ጽናት የሚያጎናጽፋቸውን ጸጋ መንፈስ ቅዱስ ለመቀበል
እንዲችሉ በሚሾሙበት ጊዜ በሜሮን ይቀባሉ (ይከብራሉ)፡፡

፫ኛ. ለአዲስ ሕንፃ ቤተ ክርስቲያንና ለንዋየ ቅድሳት ማክበሪያ፡- አዲስ ሕንፃ ቤተ


ክርስቲያንና ንዋየ ቅድሳቱ የእግዚአብሔር ገንዘቦች እንዲሆኑ በሜሮን ተቀብተው እንዲከብሩ
ይደረጋል፡፡

5.3 የቅብዐ ሜሮን ምሣሌዎች


1. ያዕቆብ በሐዉልቱ ላይ የቀባዉ ዘይት፡- "ይህች ቦታ የሰማይ ደጅ ናት፡፡ በቦታዉ
የእግዚአብሔር ቤት እንደሚሰራ ትንቢት ተናግሮ ተንተርሶት ያደረዉን ድንጋይ አንስቶ
ሐዉልት አድርጎም አቆመዉ፡፡በላዩም ዘይት አፈሰሰበት፡፡" ዘፍ 28÷1-22 አባታችን
ያዕቆብ፡- የሐዲስ ኪዳን ካህናት ምሳሌ፣ ዘይቱ፡-የምስጢረ ሜሮን ምሣሌ፣ ያቦታ ዘይቱ
ፈስበት እንደከበር፡-በቅደብዓ ሜሮን ፀጋ እግዚአብሔር ያድራል በተጨማሪም በልጅነት
ፀጋዉ ተጠማቂዉ የከብራል፡፡

2. የሙሴ የተቀሰ ዘይት(ቅብዓት)፡- "ይህ ለልጅ ልጆችህ የተቀደሰ ቅብዓት ይሁንልኝ" ዘፀ


30÷31 ከቤተ አሮን የተወለደ ወንድ ልጅ እግዚአብሔርን በክህነት ያገለግል ዘንድ
ቅዱሱን ቅባት ቀብቶ ሀብተ ክህነትን ገንዘብ የደርግ ነበር፡፡

5.4 የቅባዐ ሜሮን አዘገጃጀት


የምዕመናን ሁለተኛ ልደት ከውኃና ከከመንፈስ ስለኾነ ምዕመናን በውሀ ሲጠመቁ ከውሀ፣
ሜሮን ሲቀቡ ከመንðፈ ቅዱስ ይወለዳሉ፡ ስለ ሜሮን አወጣጥ የሜሮን አፈላል በጥንታዊት
ቤተ ክርስቲያን ትውፊት እንደሚታወቀው ጌታ ከተገረፈባቸው እና ከተሰቀለባቸው ዕፀዋት
ተሰብስቦ ተነጥሮ ከተነጠረ በኋላ ኤጲስ ቆጶሳት ተሰብስበው ምህላና ጸሎት ያደርሱበታል
ይቀድሱበታል፡፡ በኋላም በአንብሮተ ዕድ ባርከው ወደ የሀገረ ስብከታቸው ይከፋፈሉታል፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለብዙ ዓመታት ሜሮን የሚመጣላት
ከእስክንድርያ ቤተ ክርስቲያን ነበር፡፡ አሁን ነጻነቷን ካገኘት በኋላ ግን ፈልሀተ ሜሮን
አስፈላጊ ሲኾን ስለ መንበረ ማርቆስ ክብር የኢትዮጵያ ጳጳሳት ወደ ካይሮ እየተላኩ ከግብጽ
ጳጳሳት ጋር ኹነው የፍልሀተ ሜሮንን ሥርዓት ይፈጽማሉ፡፡ የኢትዮጵያንም ድርሻ
ተካፍለው ያመጣሉ፡፡ በግብጽ የሚደረገው ፍልሀተ ሜሮን ሁል ጊዜ በሰኔ ወር
የመጀመሪያው ፍልሀተ ሜሮን ተደረገ የሚባለው በሰኔ ስምንት ቀን ነውና በመለካውያን

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 74
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ዘንድ ሜሮን የሚፈላው በጸሎተ ሐሙስ ዕለት በቅዳሴ ላይ ነው፡፡ ግሪኮች የቁስጥንጥንያ
መንበር ለማክበር ሲሉ ጳጳሶቻቸውን ወደ ቁስጥንጥንያ ልከው በዚያ ፍልሀተ ሜሮን
ያደርጋሉ፡፡

5.5 ቅብዐ ሜሮን በብሉይ ኪዳን


በብሉይ ኪዳን ዘመን የነበሩ ካህናት የሚሾሙት፤ ሕዝበ እስራኤልን የሚያስተዳድሩ
የእግዚያብሔር እንደራሴዎች ነገስታትን መሲሀን የሚባሉት በዚህ ቅብ ተቀብተው
ስለሚነግሱ ነው፡፡ ዘፍ 20፡23፣ 1ኛ ሳሙ 10፡1፣ ዘዳ 28፡41፣ 1ኛ ሳሙ 9፡6፣ 1ኛ ነገስት
1፡34፣ ዘፀ 28፥41፣ ዘፀ 29፥7፣ ዘሌ 4፥3፣ ዘሌ 6፥20፣ ዘሌ 8፥2፣ በዚህ የብሉይ ኪዳን
ዘመን ካህናቱም ሆኑ ነገሥታቱ የሚቀቡት ከእስራኤል ዘሥጋ መካከል ተመርጠው
የእግዚአብሔርን ህዝብ ለማገልገል ሲሆን፤ ቅብዓ ክህነቱም ሆነ ቅብዓ መንግስቱ
አገልግሎታቸውን በማስተዋልና በታማኝነት እንዲፈጽሙ የሚያተጋቸው የእግዚአብሔር ፀጋ
የሚተላለፍበት መንገድ ነው። በዚህ ዓይነት የመሪነት ቦታ የያዙ ካህናትና ነገሥታት
ከእግዚአብሔር የሚሰጣቸውን ትእዛዝ በመቀበል ለእግዚአብሔር እየታዘዙና ሕዝባቸውን
በቅንነት እያገለገሉ አልፈዋል።

5.6 ቅብዐ ሜሮን በአዲስ ኪዳን

የአዲስ ኪዳኑ ቅብዐ ሜሮን መነሻው ከላይ እንደገለጽነው ይህ የብሉይ ኪዳኑ ቅብዐ ዘይት
አጠቃቀምና አገልግሎት ነው፡፡ በብሉይ ኪዳን ለታላቅ መንፈሳዊ አገልግሎት ይውል
እንደነበረው የተቀደሰ ቅብዓት በሐዲስ ኪዳንም መንፈሳዊ ዓላማውን ሳይለቅ አገልግሎቱ
ቀጥሏል ። 1 ዮሐ 2፥17 ፈቅዶና መመሪያ ሰጥቶ ያስጀመረውም ራሱ እግዚአብሔር ነው፡፡
ካህናትን በቅብዐ ሜሮን አክብሮ ሥልጣነ ሐዋርያትን ማስተላለፍ ጥንታዊ የተለመደና የከበረ
የቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ነው፡፡ በምሥጢረ ተክሊልም ሙሽራውና ሙሽሪት በቅብዓ ሜሮን
ታትመው ይከብራሉ፡፡ በመጽሐፈ ተክሊል ከሌሎቹ የሥርዓተ ተክሊል አፈጻጸሞች ጋር
የአቀባብ ሥርዓቱና በቅብዐ ሜሮኑ ላይ የሚጸለየው ጸሎት ሠፍሮ ይገኛል፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ በሐዲስ ኪዳን በቅብዐ ሜሮን የሚታደለውን የመንፈስ ቅዱስ ስጦታ
መሆኑን “እናንተስ ከቅዱሱ ያገኛችሁት ቅብዐት አላችሁ ሁሉንም ታውቃላችሁ፡፡ እውነትን
የምታውቁ ስለሆናችሁ፣ ውሸትም ሁሉ ከእውነት እንዳልሆነ ስለምታውቁ እንጂ እውነትን
እንደማታውቁ አድርጌ እጽፍላችኁም፡፡” (፩ዮሐ. ፪፥፳-፳፪፡፡) በማለት አስተምሮናል፡፡
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ከዚህ አሳብ ጋር ተመሳሳይ የሆነ መልእክት “ከእናንተ ጋር
በክርስቶስ ስም የሚያጸናንና የቀባን እግዚአብሔር ነው፡፡ ደግሞም ያተመንና የመንፈስ
ቅዱስን ፊርማ በልቦናችን የሰጠን እርሱ ነው፡፡” በማለት አስተላልፎልናል፡፡ (፪ ቆሮ. ፩፥፳፩-

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 75
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

፳፫፡፡) ሐዋርያት በጸሎተ ሐሙስ ማታ በህጽበተ ዕግር አማካኝነት ተጠምቀዋል። ዮሐ 13 ፥


4 መንፈስ ቅዱስን የተቀበሉት ግን ጌታችን ባረገ በሃምሳኛው ቀን ነበር። የሐዋ 2፥1

በሐዋርያት ጊዜ ማንኛውም ያመነ ሰው ከተጠመቀ በኋላ የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ የሚቀበለው


በሐዋርያት አንብሮተ ዕድ ማለት ሐዋርያት እጃቸውን ሲጭኑበት ነበር፡፡ የምዕመናን ቁጥር
ሲበረከት ኤጲስ ቆጶሳትም በየቦታው ሜሮን እያፈሉ በሜሮኑ ላይ እየቀደሱ ወደ የአብየተ
ክርስቲያናቱ እንዲልኩና፣ የሚጠመቁ ምዕመናንም በእነሱ አንብሮተ ዕድ ፈንታ ሜሮን
እንዲቀቡ በሎዶቅያ ጉባኤ ተወሰነ፡፡ በአንብሮተ ዕድ ፈንታ ሜሮን እንዲተካ ሥርዓት
የተሰራው ቅዱሳት መጻሕፍትን መሠረት በማድረግ ነው፡፡ ቅብዓ ሜሮን በብሉይ ኪዳን
በምሳሌነት ይሰራበት ከነበረው ሌላ አዲስ ኪዳን የጻፉ ቅዱሳን ሰዎችም የመንፈስ ቅዱስን
ስጦታ ቅብዓት ይሉት ነበር፡፡ ቅብዕን የመንፈስ ቅዱስ ማህተም ይሉታል፡፡ ማህተም ያለበት
ኹሉ የማንነቱ እንደሚታወቅ ምዕመናንም የመንፈስ ቅዱስ ገንዘቦች መኾናቸው
የሚታወቀው የሚረጋገጠው በጥምቀት በቅብዓ ሜሮን ሲታተሙ ነውና፡፡

5.7 የቅባዐ ሜሮን አመሠራረት


ምሥጢረ ሜሮንን የመሠረተልን ራሱ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡
መጥምቀ መለኰት ቅዱስ ዮሐንስ “እኔ ለንስሐ በውኃ አጠምቃችኋለሁ፤ ጫማውን
ለመሸከም የማይገባኝ ከእኔ በኋላ የሚመጣው እርሱ ግን ከእኔ ይልቅ ይበረታል፤ እርሱ
በመንፈስ ቅዱስ በእሳትም ያጠምቃችኋል፤” (ማቴ. ፫፥፲፩፡፡) በማለት እንደመሰከረለት
በመንፈስ ቅዱስና በእሳት የሚያጠምቅ እሱ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ብቻ ነው፡፡
ለሐዋርያትም ተስፋ እንዳደረገላቸው በበዓለ ሃምሳ ከአብ የሠረፀ መንፈስ ቅዱስን ላከላቸው፤
በመንፈስ ቅዱስ አጠመቃቸው፡፡ (ሐዋ. ፩፥፭፤ ፪፥፩-፲፬፡፡) በደቀ መዛሙርቱ ላይ እፍ
ባለባቸው ጊዜ ደግሞ የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ ተቀበሉ፡፡ (ዮሐ. ፳፥፳፩-፳፬) ከዕርገቱ በፊትም
ደቀ መዛሙርቱን እስከ ቢታንያ አውጥቶ እጁን አንሥቶ በላያቸው ጭኖ ባርኳቸዋል፡፡
በዚሁ መሠረትም ቅዱሳን ሐዋርያት የተቀበሉትን የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ ለተከታዮቻቸው
በአንብሮተ ዕድ ያድሉ ነበር፡፡ አዳዲስ ተጠማቂዎችም በሐዋርያትና በተከታዮቻቸው
አንብሮተ እድ እየተደረገላቸው በልጅነት ይከብሩ ነበር። (ሐዋ፰፥፲፬-፲፯፤ ፲፱፥፭-፮) ከጊዜ በኋላ
ተጠማቂዎች እየበዙ ሲመጡ ለአባቶቻችን እግዚአብሔር ገልጾላቸው ቅብዐ ሜሮኑን
በአንብሮተ እድ እያከበሩ ለአብያተ ክርስቲያናት በማከፋፈል ምሥጢረ ሜሮን በአንብሮተ
እድ ምትክ እንዲፈጸም ማድረግ ጀመሩ፡፡ ይህንንም ሥርዓት የቤተ ክርስቲያን አባቶች
በሎዶቅያ ጉባኤ ወስነው አጸኑ፡፡

5.8 የቅብዐ ሜሮን አፈጻጸም


ቅብዐ ሜሮን በዋነኛ ምሥጢራዊ አገልግሎቱ ከምሥጢረ ጥምቀት አፈጻጸም አይለይም፡፡
በእኛ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት ከላይ እንደገለጥነው የሜሮን አቀባብ ወዲያ

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 76
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ከጥምቀት አያይዞ ይፈጸማል፡፡ ይህም ማለት ተጠማቂው ሰው ጥምቀት ከተፈጸመለት በኋላ


ሳይውል ሳያድር ወዲያውኑ ጥምቀቱን እንደተቀበለ ሜሮን ይቀባል፡፡ ሜሮን ሲቀባም
በመንፈስ ቅዱስ መጠመቁን፣ ከውኃና ከመንፈስ ቅዱስ መወለዱንን፣ መንፈስ ቅዱስን
እንዳደረበት ይረጋገጥለታል፡፤ ተጠማቂው ተጠምቆ ሜሮን መቀባቱ መንፈስ ቅዱስን
መቀበሉን ያመለክታል፡፡

የአቀባቡም ሥርዓት የተጠመቀው ሕጻን እንደኾነ በክርስትና ዋሱ እቅፍ እንዳለ ይቀባል፡፡


አዋቂ እንደኾነ ከማጥመቂያው ወጥቶ እንደቆመ ቄሱ ሜሮኑን በአውራ ጣቱ እየጠለፈ
“እቀብአከ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ እያለ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
በትዕምርተ መስቀለ ያትመዋል በመጀመሪያ ግንባሩን ያትመዋል አዕምሮው የተባረከ
እንዲኾን ግራ ቀኝ አይኖቹን ያትመዋል ዓይኖቹ የእግዚአብሔርን እውነት እንዲያዩ፣ ግራ
ቀኝ ጆሮቹን ያትመዋል ጆሮዎቹ የእዚአብሔርን ቃል እንዲሰሙ፣ አፉን ከናፍሩን
ያትመዋል፣ እውነት እንዲናገር የእግዚአብሔርን ጥበብ እንዲማር፣ ደረቱን ያትመዋል፡፡
ልቡ ቅን እንዲያስብ፣ ግራ ቀኝ እጆቹን ይቀባዋል፡፡ እጆቹ ለመልካም ሥራ እንዲፋጠኑ፣
ግራ ቀኝ እግሮቹን ይቀባዋል እግሮቹ ወደ መልካም ሥራ እንዲፋጠኑ፡፡ በአጠቃላይ መላ
ሰውነቱን ይቀባዋል በኋላ ሰውነቱ የእግዚአብሔር ማደሪያ እንዲሆን፡፡

በሜሮን የሚታተሙ በሜሮን የሚቀደሱ አዲስ ክርስቲያኖች ብቻ አይደሉም፡፡ አዲስ ቤተ


ክርስቲያን ተሰርቶ ካለቀ በኋላ አገልግሎት የሚጀመርበት በሜሮን ከተቀባ በኋላ ነው፡፡ የቤተ
ክርስቲያን የውስጥ ንዋያተ ታቦት፣ ጻህል፣ ጽዋ፣ ዕርፈ መስቀል፣ መሶበ ወርቅ፣
ማዕጠንት፣ ማህፈድ፣ መንበር፣ እነዚህና የመሳሰሉትም ለአገልግሎት ከመቅረባቸው በፊት
በሜሮን ይታተማሉ ልዩ ጸሎትና ቡራኬም ይፈጸምባቸዋል ከዚያ በኋላ ተራ ሥራ
አይሰራባቸውም፡፡ በግሪክና በሌሎች መለካውያን አቀባቡ ከእኛው ጋር ተመሳሳይነት አለው
ከጥምቀት ጋር አያይዘው ይቀባሉ ሲቀቡ ግን “ማህተመ ፀጋ ዘመንፈስ ቅዱስ ዝውእቱ”
እያሉ ነው የሚቀባው ቄሱ ነው፡፡ በዚህም መሠረት በእኛ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ
ክርስቲያናት የተወሰኑትን የአቀባብ ሥርዓቶች ከዚህ በታች እንመልከት፡፡

በዕለተ ጥምቀት ሜሮን በጳጳሳት ከተባረከ በኋላ ለአገልግሎት የተሰየመው ቄስ


በእጁ ይዞ ይጸልይበታል፡፡ መጽሐፈ ክርስትናንም ይደግማል (ያነባል)::
የተጠማቂውን ፴፮ ሕዋሳት በታዘዘው መሠረት ክፍል ክፍሉን እየለየ ይቀባል፡፡
ቅብዐ ሜሮኑን በአውራ ጣቱ እየጠቀሰ (እያስነካ) በትእምርተ መስቀል አምሳል
እቀብዐከ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ እያለ ተጠማቂውን ይቀባዋል፡፡
በሥርዓተ ጥምቀት እንደገለጽነው ንዑሰ ክርስቲያን ሴት ከሆነች ልብስ ለብሳ
ከአንገቷ በላይ ኤጲስ ቆጶሱ (ቄሱ) ይቀባታል፡፡ በኋላም ከአንገት በታች ያሉትን

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 77
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ቀሪ ሕዋሳት ጳጳሱ ወይም ቄሱ ተጋርዶ (ተሸፍኖ) ዲያቆናዊት የቄሱን እጅ ይዛ


እየመራች ይቀባታል፡፡

የተጠማቂው ፴፮ቱ ሕዋሳት በሜሮን ሲከብሩ በሥርዓተ ቤተክርስቲያን


የአቀባባቸው ቅደም ተከተል የታወቀ ነው፡፡ ከላይ እንደገለጽነው ሁሉም
በትእምርተ መስቀል አምሳል የሚታተሙ (የሚቀቡ) ናቸው።

 ግንባሩን ግራና ቀኝ ሁለት ቦታ ይቀባና በፊቱ ላይ እፍ ይገልበታል..........1


 ሁለቱን የአፍንጫ በሮች፣ …...…………………………...….………......2
 ሁለቱን ከናፍር፣ ……………….………………………………………...2
 ሁለቱን ጆሮዎች፣ …………………...……...…...……………………....2
 ሁለቱን ዓይኖች፣ …………………….………….…………………….….2
 ደረቱን፣..……………………………….……………………………….....1
 ልቡን፣ ………………………………………………...………………….1
 ከመሐል አናት እስከ ወገብ ያለውን አካል፣ ………….………….……….1
 መሐል ጀርባውን፣ ………….…………………………………………….1
 እንብርቱን፣ ……………………………………………………………….1
 ሁለቱን እጆች፣ …………….………………………………………….….2
 የእጆቹን መገናኛዎች፣ …………………………………………………....2
 ትከሻዎቹን፣……………………….……………………………………….2
 ማጅራቱን፣………………………...………………...…………………….1
 አንገቱን፣ ….………………………………………………………...……1
 ክርኖቹን፣ …………….………………………………………...….….….2
 የእጆቹን ውጪያዊ ክፍሎች (መዳፎች)፣ …………….............….………2
 የእጆቹን ውስጣዊ ክፍሎች (መዳፎች)፣ …………….….………………...2
 የእግር መገናኛዎቹን (መዳፎች)፣ …………...…….………...……………2
 ጉልበቶቹን፣ …………...………………….….…...………………...…….2
 የእግሮቹን ውጪያዊ ክፍሎች (ጣቶች)፣ ………….…………….........….2
 የእግሮቹን ውስጣዊ ክፍሎች (ጣቶች)፣ ………....…………….….…...…2
በድምሩ 36 ሕዋሳት ይሆናሉ፡፡

እነዚህን ሕዋሳት በቅደም ተከተል ከቀባ በኋላ በተጠማቂው ላይ እጁን ጭኖ “በሰማያውያን


በረከት የተባረክህ ሁን” እያለ ይባርከዋል፡፡ ሠላሳ ስድስቱ የተጠማቂው ሕዋሳት በዚህ መልክ
በቅብዐ ማሮን ታትመው የእግዚአብሔር ገንዘቦች (ማደሪያዎች) ይሆናሉ፡፡ ከተጠማቂዎች
ሌላ ቅብዐ ሜሮን ለሁለት ምሥጢራት ማክበሪያነት (ማተሚያነት) ያገለግላል፡፡ እነዚህም
ምሥጢረ ክህነትና ምሥጢረ ተክሊል ናቸው፡፡ በምሥጢረ ክህነት ካህናት ከቄሱ ጀምሮ ወደ
ላይ ያሉት ማለትም ጳጳስና ቄስ በቅብዐ ሜሮን ከብረው ካህናተ እግዚአብሔር ይሆናሉ፡፡
ይህም በብሉይ ኪዳን “እኔንም በክህነት እንዲያገለግሉኝ ትቀድሳቸው ዘንድ የምታደርግላቸው
ነገር ይህ ነው፤ የቅብዐትንም ዘይት ወስደህ በራሱ ላይ ታፈሰዋለህ፤ ትቀባውማለህ፡፡
ልጆቹንም ታቆርባቸዋለህ፤ ቀሚሶችንም ታለብሳቸዋለህ፤ በመታጠቂያም ታስታጥቃቸዋለህ፤
ቆብንም ታደርግላቸዋለህ፤ ለዘለዓለም ሥርዓትም ክህነት ይሆንላቸዋል፡፡ እንዲሁም የአሮንና
የልጆቹን እጆች ትቀባቸዋለህ፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 78
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

5.9 ቅብዐ ሜሮን የሚያስገኘው ጸጋ


አካሉ አንድ ሲሆን ስጦታው ልዩ ልዩ የሆነ መንፈስ ቅዱስ (፩ቆሮ. ፲፪፥፬፡፡) ምእመናንን
ለልዩ ልዩ አገልግሎት የሚያዘጋጃቸው፣ የሚሰጠውን ሀብተ ወልድና ስመ ክርስትና
የሚያጸናው በዚሁ ዕለት በሜሮን አማካኝነት በሚቀበሉት (በሚያድርባቸው) የመንፈስ ቅዱስ
ጸጋ ነው፡፡ (፩ቆሮ፲፪፥፳፯-ፍጻ) (ሐዋ ፰፥፲፬-፲፰) አዲሱ ተጠማቂ የቤተ ክርስቲያን ልጅ፣
የእግዚአብሔር ማደሪያ ስለሚሆንም ለተፈጠረበት ዓላማ የሚሠራ ሆኖ ይዘጋጃል፡፡
የክርስቶስ አካልነቱ የቤተ ክርስቲያንም አባልነቱ የተረጋገጠ ክርስቲያን ይሆናል፡፡

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “ሥጋችሁም ለእግዚአብሔር ነው እንጂ ለዝሙት አይደለም፤


እግዚአብሔርም ለሥጋችሁ ነው፡፡ ሥጋችሁ የክርስቶስ አካል እንደሆነ አታውቁምን?
እንግዲህ የክርስቶስን አካል ወስዳችሁ የአመንዝራ አካል ታደርጉታላችሁን? አይገባም፡፡
ከአመንዝራ ጋር የተገናኘ ከእርስዋ ጋር አንድ አካል እንዲሆን አታውቁምን? መጽሐፍ፣
“ሁለቱ አንድ አካል ይሆናሉ” ብሎአልና፡፡ ከእግዚአብሔር ጋር የተዋሐደ ግን ከእርሱ ጋር
አንድ መንፈስ ይሆናል፡፡ ሥጋችሁ ከእግዚአብሔር ለተቀበላችሁት በእናንተ አድሮ ላለ
ለመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንደሆነ አታውቁምን? ለራሳችሁ አይደላችሁም፡፡ በዋጋ
ተገዝታችኋልና፤ ስለዚህም እግዚአብሔርን በሥጋችሁ አክብሩት፡፡” (፩ቆሮ. ፮፥፲፫-ፍጻ፡፡)
በማለት ያስተማረን ይህን የሚያጎላና ሌሎች ምሥጢራትንም አካቶ የያዘ ነው፡

ከማኅፀነ ዮርዳኖስ ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ ተወልደን የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ መሆን


የጀመርነው ከተጠመቅንበትና በሜሮን ከከበርንበት ዕለትና ሰዓት ጀምሮ የእግዚአብሔርን
የክብር ዕቃ፣ ማደሪያ መቅደሱንም በጥንቃቄ የማይዙና የሚያቃልሉ ሁሉ የሚቀጡ
መሆኑን ማወቅ ያስፈልጋል፡፡ የመቅደሱ ባለቤት እግዚአብሔር ለቤቱና ለሥርዓቱ ቀናዒ
ነው፡፡ መቅደሱ የኃጢአት ሸቀጥ ማራገፊያና መነገጃ ሲሆን ዝም ብሎ አያይም፡፡ (ማቴ. ፳፩፥
፲፪-፲፰) ንጉሡ ብልጣሶር አባቱ ናቡከዳናፆር ከኢየሩሳሌም ቤተ መቅደስ ማርኮ በቤተ
መንግሥቱ ዕቃ ቤት በክብር ያኖራቸውን ንዋያተ ቅድሳት አስመጥቶ በማቃለል ጣዖታትን
እያመለኩ እንዲበሉባቸውና እንዲጠጡባቸው አደረገ፡፡ እንዲህ አድርጎ በንዋየ ቅድሳቱ
በተሳለቀባቸው ዕለትም ተገድሎ አደረ፡፡ (ዳን. ፭፥፩-ፍጻ፡፡) እግዚአብሔርንና የሱ የሆኑትን
ሁሉ የማያከብሩ ሰዎች ለማይገባ አዕምሮ ተላልፈው እንደሚሰጡ ማወቅ ጠቃሚ ነው፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 79
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

6. ምስጢረ ቁርባን
6.1 የምስጢረ ቁርባን የቃሉ ትርጉም
ቁርባን የሚለው ቃል መሠረቱ ከዕብራይስጥ ቋንቋ የመጣ ሲሆን “ስጦታ” የሚል ትርጉም
ይኖረዋል፡፡ ከምሥጢራት አንዱ መሆኑ ሕብስቱ ተለውጦ የክርስቶስ ሥጋ ጽዋው ተለውጦ
የክርስቶስ ደም ሲሆን አይታይም፡፡ ነገር ግን እምነት ያለው ሁሉ በእምነት መነጽር
ይመለከተዋል፡፡ ይህም ማለት እንደ ኦሪቱ ቁርባን ሰው ለእግዚአብሔር ያቀረበውን ስጦታ
ብቻ የሚያመለክት ሳይሆን እግዚአብሔርም በተለየ ሁኔታ ለሰዎች ደኅንነት ለዓለም ሁሉ
የሰጠውን በሥጋና በደም የመጣውን የልጁን ስጦታ ያስገነዝባል። ስለዚህም ለዓለም
መድኃኒት ሆኖ የተሰጠው በጸሎተ ኀሙስ ማታ ወደ ጌታ ሥጋና ደም የተለወጠው
ኅብስትና ወይን ዛሬም በጸሎተ ቅዳሴ የጌታን ሥጋና ደም ሆኖ የሚቀርበው ቅዱስ ቁርባን
ይባላል። እርሱም ከእግዚአብሔር የተሰጠ የተቀደሰ ስጦታና መሥዋዕት ነው።

አንድም ምሥጢረ ቁርባን ስንል ክርስቶስ ስለ እኛ ኃጢአት በመስቀል ላይ መሥዋዕት ሆኖ


በሥጋው በመሞቱ የዓለምን ኃጢአት ያስወገደበት፣ የዘላለም ሕይወትን ያሰገኘበት፣
የመዳናችን መሠረት፣ የጸጋችን ሁሉ ምንጭ የሆነውን የቅዱስ ሥጋውንና የክቡር ደሙን
የማዳን ጸጋ የሚያመለክት ታላቅ የክርስትና ሃይማኖት ምሥጢር ነው። ክርስቶስ እንደ
መሥዋዕትም እንደ ዐቢይ ሊቀ ካህናትም በመሆን ሁለቱንም በአንድ ጊዜ ፈጽሟል (ዕብ ፯፣
፳፡፳፰) ፡፡ እንደ ዐቢይ ሊቀ ካህናትነቱ በመስቀል ላይ የተቆረሰው ሥጋውን የፈሰሰው
ደሙን የኃጢአት መሥዋዕት አድርጎ ለእግዚአብሔር በማቅረቡ ሰውን ከራሱና
ከእግዚአብሔር ጋር አስታራቀ፣ የጥልንም ግድግዳ አፈረሰ፣ የተራራቀውን አቀራረበ።
እንግዲህ ለኃጢአታችን መሥዋዕት ሆኖ ከእግዚአብሔር የተሰጠንን እኛ ደግሞ ከምስጋና
ጋር መልሰን ለእርሱ እናቀርባለን።

6.2 የምሥጢረ ቁርባን አገልግሎት


የምሥጢራተ ቤተክርስቲያንና የአገልግሎቶች ሁሉ የማረጋገጫ ማኅተም ነው፡፡ ይህም
ማለት ማንኛውም ምሥጢር በቤተክርስቲያን ከተፈጸመ በኋላ በምሥጢረ ቊርባን
ካልተፈጸመ (ካልታተመ) የቤተ ክርስቲያን ምሥጢር ሊባል አይችልም፡፡ በተጨማሪም
በቤተክርስቲያን የሚከናወኑ አገልግሎቶች ሁሉ ማለትም ማኅሌቱ፣ ሰዓታቱ፣ መዝሙሩ፣
ቅኔው፣ ኪዳኑና የመሳሰሉት ሁሉ ፍጻሜያቸውን የሚያገኙት በቅዳሴ ነው፡፡ ቅዳሴውም
የምሥጢረ ቊርባን መክበሪያ የጸሎታት ሁሉ ቁንጮ የሆነ፤ የምስጋናና የጸሎት ሥርዓት
ነው፡፡ ቁርባን ማለት በአንድ በኩል ለእግዚአብሔር የሚቀርበውን መሥዋዕት በሌላ በኩል
ደግሞ እኛ ወደ እግዚአብሔር የምንቀርብበትን፣ የምንቀራረብበትንና የምንዋሐድበትን ሁኔታ
ያሳየናል። ልንቀርብና የመለኮታዊውንም ጸጋ ተሳታፊ ልንሆን የምንችለው በምሥጢረ
ቁርባን አማካኝነት ኅብስቱና ወይኑ ወደ ክርስቶስ ሥጋና ደም ተለውጦ ስንቀበለው ነውና

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 80
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ምሥጢር መሆኑን ከዚህ ላይ እናስተውላለን። ሥጋውና ደሙ የተሰጠን በነፃ ያለ ዋጋ


ሳይገባን በችሮታ ነውና፡፡ መስዋዕት ማቅረብ የተጀመረው በአዳም ጊዜ ሲሆን ከአዳም እስከ
ሙሴ የተነሱ አበው ሁሉ በህገ ልቦና ለእግዚአብሔር መስዋት ይሰው ቁርባን ያቀርቡ ነበር፡፡
መስዋዕታቸው ከእንሰሳ ቁርባናቸው ከእህልና ከአትክልት ማለት ከስንዴ እህል፣ ከወይን ፍሬ
የሚቀርብ ነው፡፡

ዘመነ ኦሪት በብሉይ ኪዳን በሙክራብ የተሰዋ እንሰሳት ሁሉ በአዲስ ኪዳን በቤተክርስቲያን
ለሚሰዋው ሁሉ የክርስቶስ ሥጋና ደም ምሳሌ ነበር፡፡ መልከ ጼዴቅ ያበረከተው ኅብስተ
አኮቴት ጽዋዐ በረከት ለአምላክ የሥጋውና የደሙ ምሳሌ ሆነው አልፈዋል፡፡ በሐዲስ ኪዳን
ግን አማናዊው ቊርባን (መሥዋዕት) ሰዎች የሚያቀርቡት (የሚሰጡት) መባዕ ሳይሆን
መድኃኔዓለም ክርስቶስ ዓለሙን ለማዳን በቀራንዮ ዐደባባይ በአባቱ ፈቃድ፣ በመንፈስ ቅዱስ
ፈቃድ፣ በራሱም ፈቃድ በመስቀል ላይ ለዓለሙ ሁሉ ያቀረበው (የሰጠው) ቅዱስ ሥጋውና
ክቡር ደሙ ነው፡፡

ይህም በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ካህናት በቅዳሴ ጊዜ የሚያቀርቡት ኅብስት የክርስቶስ ሥጋ


ወይኑም የክርስቶስ ደም በመሆን የሚፈተት የሚቀዳ አማናዊ የአዲስ ኪዳን ቁርባን ነው፡፡
ሥጋውንና ደሙን ግን በየጊዜው እንቀበላለን ይኽ መኾኑ ግን አንድ ጊዜ የሆነው የጌታችን
ሞቱ በየጊዜው ለምናምነው ምእመናንና በየጊዜው በድለን ለምንመለስ ኃጥአን ቤዛ በመሆን
ሲሰጠን ይኖራልና ስለዚህ ነው። ሥጋውንና ደሙን መቀበልም እግዚአብሔርን ፈርቶ
ከሠሩት ኃጢአት ተጸጽቶ ማረኝ ብሎ አልቅሶ ለወደፊቱም ከኃጢአት ተለይቶ ነው፤ ፩ኛ
ቆሮ. ፲፩፥፳፰። ያለፍርሃት በድፍረት ያለንጽሕና በኃጢአት ሆኖ ቢቀበሉት ማለት ከሟርት፣
ከስርቆት፣ ከዝሙት፣ ከሐሜት፣ ከፌዝና፣ ከቧልት ሳይለዩ ቢቀበሉት ግን የገሃነም ፍርድን
ያመጣል እንጂ ከኃጢያት ፍርድ አያነፃም፤ ፩ኛ ቆሮ. ፲፩፥፳፯ ዕብ. ፲፥፳፱ ቸሩ እግዚአብሔር
ኃጢአትን ድል የምንነሣበት ረድኤቱን ይስጠን የምስጢረ ቁርባንን ነገር በዚህ እናበቃለን::

6.3 ቅዱስ ቁርባን በምሳሌና በትንቢት


በብሉይ ኪዳን ታሪክ ውስጥ ለሥጋውና ለደሙ ማለት ለምሥጢረ ቁርባን የተመሰሉ
ምሳሌዎች አሉ። በጠቅላላ የኦሪት መሥዋዕት ሁሉ ለወንጌሉ መሥዋዕት ምሳሌነት
ቢኖራቸውም ዋና ዋናዎቹን ብቻ እንጠቅሳለን።

የልዑል እግዚአብሔር ካህንና የሳሌም ንጉሥ ያቀረበው የኅብስትና የወይን


መሥዋዕት ለክርስቶስ ዘላለማዊ ሊቀ ካህናትነትና ለሥጋው ወደሙ ዓይነተኛ ምሳሌ
ሆኖ ይነገራል (ዘፍ ፲፬፤፲፰ ዕብ ፭፣፮ እና ፲፣፯፥፲፯)።

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 81
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ከቀሳፊ የሞት መልአክ አድኖ ከግብጽ ባርነት ነፃ ያወጣቸው የፋሲካ በግ ደም


መረጨትና ሥጋውም ተጠብሶ መበላቱ የእግዚአብሔር በግ ለተባለው ለክርስቶስ
አዳኝነትና ለምሥጢረ ቁርባን ምሳሌ ሆኗል (ዘፀ ፲፪፤፩፡፶፩ ፩ኛ ቆሮ ፭፣፯)።
እሥራኤላውያን በምድረ በዳ ይመገቡት የነበረው ከሰማይ የወረደው መና ዛሬ
ምእመናን ለነፍሳቸው ምግብ የሚቀበሉት የሥጋውና የደሙ ምሳሌ ነው (ዘፀ ፲፮፣
፲፮፥፳፫ ዮሐ ፮፣፵፱፥፶፩)።
ጥበብ ያዘጋጀችው ማዕድ፣ ያረደችው ፍሪዳ፣ የጠመቀችው የወይን ጠጅ፣
የላከቻቸው አገልጋዮቿ የተጠሩት ሰዎች ሁሉ ምሳሌነት እንዳላቸው ይነገራል።
ጥበብ የክርስቶስ፣ ማዕድ የሥጋው የደሙ፣ አገልጋዮች የካህናት፣ ተጋባዦች
የምእመናን ምሳሌ ናቸው ተብሎ ይተረጎማል (ምሳ ፱፤፩፥፭)። ይህን የመሳሰሉ
ሌሎች ምሳሌዎችም አሉ (ዘሌዋ ፪፤ ፳፫፣፲፫፥፲፬ ሲራክ ፳፬፣፲፱፥፳፩)።

በትንቢትም ስለ እውነተኛው ቁርባን ተነግሯል። “ከፀሐይ መውጫ ጀምሮ እስከ መግቢያዋ


ድረስ ስሜ በአሕዛብ ዘንድ ታላቅ ይሆናልና፤ በየሥፍራውም ለስሜ እጣን ያጥናሉ ንጹሕም
ቁርባን ያቀርባሉ” (ሚል ፩፣፲፩)። ይህ ስለ ወንጌል መሥዋዕት የተነገረ እንጂ ስለ ኦሪት
መሥዋዕት አይደለም። ምክንያቱም የኦሪት መሥዋዕት በኢየሩሳሌም ከተማ በቤተመቅደስ
ብቻ እንጂ በሌላ ቦታ እንዳይፈጸም በሕግ የተከለከለ ነው። እንግዲህ ነቢዩ ሚልክያስ ንጹሕ
ቁርባን ያለው እስከ ዓለም ዳርቻ ድረስ ለአሕዛብ ወንጌል በተሰበከበት ሥፍራ ቤተ ክርስቲያን
በተቋቋመበት ቦታ ሁሉ የሥጋውና የደሙ ንጹሕ መሥዋዕት መቅረቡን የሚያመለክት
ነው። ሌላው ደግሞ የኢሳይያስ ትንቢት ነው። “እናንተ የተጠማችሁ ሁሉ ወደ ውኃ ኑ
ገንዘብም የሌላችሁ ኑና ግዙ ብሉም፣ ኑ ያለ ገንዘብም ያለ ዋጋም የወይን ጠጅና ወተት
ግዙ በረከትንም ብሉ” (ኢሳ ፶፭፣፩፥፪)። ይህ የነቢዩ ቃል በመብልና በመጠጥ ስለሚመጣው
ስለ ምሥጢረ ቁርባን በትንቢትና በምሳሌ እንደ ተነገረ ይታመናል።

6.4 የምሥጢረ ቁርባን አመሠራረት


ምሥጢረ ቁርባንን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሕማማቱና ከሞቱ በፊት በዋዜማው ኀሙስ
ማታ መሥርቶታል፡፡ ይህም ሰዓት በአይሁድ የቀን አቆጣጠር ወደ ዓርብ ይታሰባል።
መጀመሪያ የሥጋውና የደሙን ምሥጢር ሲያሳይ እንዲህ ነበር ዓልአዛር በተባለው ሰው
ቤት ጌታችን ከደቀ መዛሙርቱ ጋር መጀመሪያ የኦሪትን መሥዋዕት ሠውቶ በልቷል።
ወዲያው የበሉትን የኦሪት መሥዋዕት በተአምራት ከሆዳቸው አጥፍቶ ሰዎች ለእራት
ካመጡለት ኅብስት አንዱን አንሥቶ ያዘና ወደ አባቱ ጸለየ። ኅብስቱንም በሥልጣኑ ለውጦ
ሥጋውን አድርጎ ይህ ስለ እናንተ የሚሰጥ ሥጋዬ ነውና እንኩ ብሉ ብሎ ለደቀ መዛሙርቱ
ሰጣቸው መታሰቢያዬንም ይህ አድርጉት ብሎም አስተማራቸው። ቀጥሎም ወይን በጽዋ
ቀድቶ ያዘና ጸለየ ወይኑንም ለውጦ ደሙ አድርጎ ይህ ስለእናንተ የሚፈስ ደሜ ነው እንኩ

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 82
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ጠጡ ብሎ ሰጣቸው፤ ሉቃ. ፳፪፥ ፲፱–፳ ማቴ. ፳፮፥ ፳፮ ማር. ፲፬፥ ፳፪ የኦሪትን መሥዋዕት
አሳልፎ መሥዋዕተ ወንጌልን መሥርቷል።

በዚያችም ምሽት የኦሪቱን በግ መሥዋዕትነት አበቃ፤ ከእንግዲህ ወዲህ እውነተኛው


የእግዚአብሔር በግ ይሠዋል። እርሱም የክርስቶስ ሥጋና ደም ነው። ስለዚህ በማዕዱ ዙሪያ
ለተሰበሰቡት ሐዋርያቱ በብሉይ ኪዳን ምሳሌ የተመሰለለትን: ትንቢት የተነገረለትን አዲሱን
ቃል ኪዳን ጌታ በራሱ ሥጋና ደም መሠረተ።

“ኢየሱስ እንጀራና ኅብስትን አንስቶ ባረከ። ቆርሶ ለደቀመዛሙርቱ ሰጠና እንካቹ ብሉ፤ ይህ
ሥጋዬ ነው አለ። ጽዋንም አንሥቶ አመስግኖም ሰጣቸው። እንዲህም አለ ሁላችሁም
ከእርሱ ጠጡ፤ ስለ ብዙዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው”
በማለት ምሥጢረ ቁርባንን መሠረተ /ማቴ ፳፮፣፳፮-፳፰/። ኪዳን ማለት ከእግዚአብሔር ጋር
የምንገባው ቃል ኪዳን የሚያመለክት ነው። “እውነት እውነት እላችኋለሁ እውነተኛ እንጀራ
ከሰማይ የሚሰጣችሁ አባቴ ነው እንጂ ከሰማይ እንጀራ የሰጣችሁ ሙሴ አይደለም፤
የእግዚአብሔር እንጀራ ከሰማይ የሚወርድ ለዓለምም ሕይወትን የሚሰጥ ነውና አላቸው።
ዮሐ. ፮፥ ፴፪–፴፫

በመቀጠልም ሥጋዬ እውነተኛ መብል ደሜም እውነተኛ መጠጥ ነውና። ሥጋዬን የሚበላ
ደሜንም የሚጠጣ በእኔ ይኖራል እኔም በእርሱ እኖራለሁ።ሕያው አብ እንደ ላከኝ እኔም
ከአብ የተነሣ ሕያው እንደምሆን፥ እንዲሁ የሚበላኝ ደግሞ ከእኔ የተነሣ ሕያው ይሆናል።
ከሰማይ የወረደ እንጀራ ይህ ነው፤ አባቶቻችሁ መና በልተው እንደ ሞቱ አይደለም፤ ይህን
እንጀራ የሚበላ ለዘላለም ይኖራል፡፡ ዮሐ. ፮፥ ፶፭–፶፰ ጌታችን ይህን ነገር በቃሉ
ሲነግራቸው መጀመሪያ ለሰሙት ሰዎች በሥራ እስኪያሳያቸው ድረስ ሊታመን የማይችል
ረቂቅ ነገር ነበር። ኋላ ግን ሠርቶ ባሳያቸው ጊዜ ተረድተው አምነውበታል። በዕለተ ዓርብ
የቆረሰውን ሥጋ፣ ያፈሰሰውንም ደም አስቀድሞ በዋዜማው ኅብስቱንና ወይኑን ለውጦ
ኅብስቱን ፲፫ ቦታ ፈትቶ (ቆራርሶ)፣ አብነት ለመሆንና ለማስደፈር ራሱ በራሱ እጅ ተቀብሎ
ለቀደ መዛሙርቱ አቀበላቸው፡፡ በመስቀል ላይ ለአንዴና ለዘለዓለሙ የፈጸመው ይህ
አምላካዊ የማዳን ሥራ እስከምጽአት ድረስ ለዓለሙ ሁሉ በሥርዓተ ቅዳሴ ከብሮ
እንዲታደልም (እንዲዳረስም) ሐዋርያት አባቶቻችንን አዘዛቸው፡፡

የምሥራቹን ቃል እንዲያስተምሩ፣ በስሙ ሥርየተ ኃጢአትን እንዲሰጡና ሌሎች


ምሥጢራትንም እንዲፈጽሙ የሚያስችል ሥልጣነ ክህነትን ሰጣቸው፡፡ (ማቴ. ፳፰፥፲፱-፳፡፡
ሉቃ. ፳፪፥፲፬-፳፤ ፳፬፥፵፬-፶፡፡ ፩ቆሮ. ፲፩፥፳፫-፳፯፡፡) በዚሁ መሠረትም ሐዋርያት ቃሉን
አስተምረው ካሳመኑ በኋላ እያጠመቁና በአንብሮተ እድ መንፈስ ቅዱስን እያሳደሩ ምሥጢረ
ቁርባንን እየፈጸሙ በማቁረብ ተተኪዎቻቸውንም በዚሁ ሥርዓት በማጽናት ቤተ

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 83
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ክርስቲያንን እንዲህ በማስፋፋት ኖሩ፡፡ የዚህ ሥልጣን አገልግሎትና ሓላፊነት ባለቤትም


ቅድስት ቤተክርስቲያን ብቻ ናት፡፡ ይህንንም አውቃ ስትፈጽመው ኖራለች፤ እየፈጸመችም
ትገኛለች፤ እስከ ዕለተ ምጽአት ድረስም ስትፈጽመው ትኖራለች፡፡

6.5 ሥርዓተ ቅዳሴ


ቅዳሴ ማለት መቅስ፣አቀዳደስ፣ቀደሰ፣ቡራኬ፣ምስጋና የቁርባን ጸሎት ማለት ነዉ፡፡ ከምስጢረ
ቁርባን ጋር የተያያዘ ሲሆን ለሌሎች ምስጢራትመ የሚስጢርነታቸዉ ማረጋገጫ ማኅተም
ነዉ፡፡ምክንያቱም ያለሥጋ ወዳሙ ምስጢራቱ ምሉዕ ሊሆኑ አይችሉምና፡፡

6.5.1 ሥርዓተ ቅዳሴ ሦስት ክፍሎች አሉት


1. የዝግጅት (ግባተ መንጦላዕት) ፡- የሚቀርበዉ ጸሎት ከመጋረጃ ዉጭ በመቀረደስ
አፍኣ የሚጸለይ ነዉ፡፡ ሚመጠን ግርምት ዛቲ ዕለት እስከሚለዉ የሚያካትት ነዉ፡፡
የዝግያ ልዑካኑና (ሰሞነኞቹን) ብቻ የሚመለከት ነዉ፡፡
2. የንባብ(የትምህርት) ቅዳሴ፡-ምዕመናንንም የሚያሳትፍ ነዉ፡፡ የመጽሐፈ ቅዳሴ
ምንባባት የሚቀርቡበትና ትምህርተ ወንጌልም የሚሰጥበት ነዉ፡፡
3. ፍሬ ቅዳሴ፡- የሥርዓተ ቅዳሴ የመጨረሻ ክፍል ነዉ፡፡ ሕብስቱና ሥጋ ወደሙ
የሚለወጥበትን ጊዜ የሚመለከት ጸሎትና ቡራኬ የያዘ ነዉ፡፡

6.5.2 ለማስቀደስ ከመሄድ አስቀድሞ የሚደረግ ዝግጅት


1ኛቆሮ 14÷40 "ሁሉም ነገር በአግባብና በሥርዓት ይሁን" ስለ ሆነም ወደ ቅድስት ቤተ-
ክርስቲያን በተለይ በዕለተ ሰንበት፣ በዐብይት በዓላት፣ በቅዱሳን ክብረ በዓላትና በዘመነ ጾም፡
ቅዳሴ ማስቀደስ፣ ቁርባን ለመቁረብ፣ ከጸሎተ ቅዳሴዉ በረከትን ለማግኘት ቅድሰት ቤተ-
ክርስቲያን ስንመጣ

የሕሊና ዝግጅት፡- ወደ እግዚአብሔር ፊት ስንቀርብ በጎ ሕሊና እንዲኖረን ያደርጋል፡፡ ሮሜ


13÷5 ምሳ 23÷26 “ልጅ ሆይ ልብህን ስጠኝ” ስድስቱን ዕለታት በሥራ የባከነዉን
ልቡናችንን ስብስብ አድርጎ ማሳረፉና ወደ ቤተ-መቅደስ ልቡናችንን ሕሊና ሰብስበን እንዴት
መግባት እንዳለብን መክ 5÷1 "ወደ ቤተ-ክርስቲያን በገባህ ጊዜ እግርህን ጠብቅ"

ሐሳባችንን ለመሰብሰብ የሚረዱን፡- 2ኛ ጢሞ 3÷12-16"የእግዚአብሔር ሰዉ ለፍጹምና ለበጎ


ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ
ለትምህርትና ለተግሳጽ ልብን ለማቅናት ለጽድቅም ላለዉ ምክር ደግሞ ይጠቅማል፡፡" ከዚህ
የምንረዳዉ፡-

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 84
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

 ቅዱሳት መጽሐፍትን ማንበብ፡፡ ሮሜ 15÷4-5


 መንፈሳዊ መልዕክት ያላቸዉን ኦርቶዶክሳዊ መዝሙሮችን ማድመጥ ፍጹም እምነት
የሚገኘዉ ቃለ እግዚአብሔርን በመስማት ስለሆነ፡፡ ሮሜ" እምነት ከመስማት ነዉ
መስማትም በእግዚአብሄር ቃል ነዉ"
 መንፈሳዊ ፊልሞችን መመልከት፡፡ ምሳ 4÷25 "ዓይኖችህ የቀና ነገርን ይመልከቱ"

የሰዉነታችንን ንጽሕና መጠበቅ፡- ተፈጥሮአዊ አካላችን ጥሩ ጠረን እንዲኖረዉ ሰዉነታችንን


በሰንበት ዋዜማ በመታጠብ ያስፈልጋል፡፡ ወደ እግዚአብሔር ለመቅረብ የሻቱ ሕዝበ
እስራኤልን ሙሴ እንዲህ ብሎ እንዲዘጋጁ እንዳዘዛቸዉ፡- ዘፀ 15÷19 "ሰዉነታችዉን አነጹ
ሕዝቡም ልብሳቸዉን አጠቡ፡፡" የካልሲያችንን የጫማችንን ንጽህና መጠበቅ እንደ ግዴታ
አድርገን መዉሰድ፡፡ "መሰናከያ ለሚያመጣ ለዚያ ሰዉ ወየዉለት" ማቴ 18÷17

መንፈሳዊ አለባበስ ስርዓትን መጠበቅ፡- የሰዉነታችንን ንጽህና ከመጠበቅ ጋር የአለባበስ


ሥርዓትን መጠበቅ የገባል፡፡ ቅዱስ ያዕቆብ የቅድስት ቤተ-ክርስቲያን አምሳል ወደ ምትሆን
ወደ ቤቴል መሥዋዕት ይሠጥ ዘንድ ትዕዛዝ በደረሰዉ ጊዜ ቤተሰቡን፡- "ንጽሕ ሁኑ
ልብሳችሁንም ለዉጡ" ዘፍ 35÷2፣ ዘዳ 32÷7 "አባትህን ጠይቀዉ እርሱ ይነግርሃል"
ለምድራዊ ሰርግ ተራ ልብስ ለብሰን ብንሄድ እንኳን ከበሬታ አናገኝም ምክንያቱም አክብሮ
የጠራንን ቤተሰብ አልመሰልንምና፡፡ ማቴ 22÷12 ቤተ-ክርስቲያን መንፈሳዊ ተድላ፣ደስታ
የምንቋደስባት ናትና ነቀፋ የሌለበት የመርዓዊ ንጉስሥ ክርስቶስ ንጽሕት የሰርግ ቤት
ስለሆነች ነጠላ፣ጋቢያችንን በመስቀሊያ አጣፍተን ከፈጣሪያችን ፊት በሰማያዉያን አምሳል
ለምስጋና ቢቆም ለእግዚአብሔርም ክብር ነዉ ለአስቀዳሾችም ሞገስ ነዉ፡፡

ለቅዳሴ ሲሄዱ ሊለበሱ የማየገባቸዉ፡- ማንኛቸዉም የሌሊት ልብስ፣ ለሠርግ ለተለያዩ


ጥሪዎች የሚለበሱ አልባሳት፣ የሰዉነታችንን የአካል ቅርጽ አጉልተዉ የሚያሳዩ ልብሶች

በምንጣፍ አንድ ከመሆን መታቀብ፡- በዕለቱ (ሌሊት) ለነፍስ ፈቃድ ሥጋን ማስገዛት፡፡ ምሳ
12÷13 "ለሰዉ የከበረ ሃብት ትጋቱ ነዉ" በተራክቦ የደከመና የዛለ አዕምሮ የዞ ወደ ቤተ
መቅደስ መግባት አይገባም፡፡ 1ኛ ቆሮ 7÷5 "ለጸሎት ትተጉ ዘንድ ተስማምታችሁ ለጊዜዉ
ካልሆነ በስተቀር እርስበርሳችሁ አትከላከሉ፡፡" ፍት. ነገ 24÷7 "እግዚአብሔርን ለማገልገል
ከሆነ ግን በምንጣፍ በአልጋ አንድ ከመሆን (የአካል ተዋሕዶ) ከመፈጸም መጠበቅ አለብን፡፡"

ወርሃዊ ልማደ አንስት በተከሰት ጊዜ መታቀብ፡- ፍት. ነገ አንቀጽ 5631 "እናቶችና እህቶች
ወርሃዊ ልማደ አንስት በተከሠተ ጊዜ ወደ ቅድስት ቤተ-ክርስቲያን ዉስጥ በመግባት ራስን
ማብቃትና ለጸሎት ለቅዳሴ እንዲሁም ሥርዓተ አምልኮ ለመፈጸም ራስን ማዘጋጀት አግባብ
አየደለም፡፡" ልማደ አንስት እንደ ብሉይ ኪዳኑ መርገም አይደለም፡፡ "ዲያቢሎስ ያሳሳታት

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 85
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ሔዋንን ነጻ አወጣት" (የሰኞ ዉዳሴ ማርያም) "ሔዋን ከመርገመ ሥጋ ከመርገመ ነፍስ ነፃ


ካደረጋት ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋዉን ክብሩን
እንዳይነሳን ለምኝልን አዕምሮዉን ጥበቡን ሣይብን አሳድሪብን" ቅዱስ ኤፍሬም

በቅዳሴ ጊዜ የሚስቅ ሰው ቅዱስ ባስልዮስ በጻፈው በ፸፪ኛው አንቀጽ ካህን ቢሆን የሚያቀብል
ነውና ሥጋ ወደሙን ከተቀበለና ካቀበለ በኋላ ወጥቶ አንድ ሱባዔ ይቀጣ ይጹም ይስገድ፣
የሳቀው ሕዝባዊ ቢሆን ግን ሥጋ ወደሙን ሳይቀበል ያን ጊዜ ፈጥኖ ይውጣ ይላል። ምነው
ፍርድ አበላለጠ ካህኑን ተቀብሎ ወጥቶ ይቀጣ አለ፤ ሕዝባዊውን ሳይቀበል ወጥቶ ይሂድ
አለ ቢሉ ካህኑ የሚቆመው ከውስጥ ነው ሲስቅ የሚያየው የለም። ካህኑ በቅዳሴ ጊዜ
ቅዳሴውን ጥሎ ወጥቶ ሲሄድ ባዩት ጊዜ ቄስ እገሌ አባ እገሌ በመሥዋዕቱ ምን
አይተውበታል ብለው መሥዋዕቱን ሳይቀር ይጠራጠሩታል፤ ስለዚህ ነው። ምዕመኑ ግን
ሲስቅ ሁሉ ያየዋልና ለሌላ መቀጣጫ እንዲሆን፤ በቤተ መቅደስ የማይወደድ ሌላ ነገር
አይናገር፤ በቤተ መቅደስ ጭንቅ፣ ደዌ ሳያገኘው አንዱን ስንኳ ምራቁን እንትፍ አይበል።
ነገር ግን ደዌ ቢያስጨንቀው ድምፅ ሳያሰማ ምራቁን በመሐረቡ ተቀብሎ ያሽሸው።

6.5.3 በቅዳሴ ጊዜ ስለሚደረጉና ሰለማይደረጉ ሥርዓት


በቤተ ክርስቲያንና በቅዳሴ ጊዜ ማንም ማን ዋዛ ፈዛዛ ነገር የሚናገር አይኑር፣ ቤተ
ክርስቲያን በፈሪሃ እግዚአብሔር ሆነው የሚጸልዩባት የጸሎት ቦታ ናትና ቅዳሴው ሳይፈጸም
አቋርጦ መውጣት አይቻልም፣ አይፈቀድም፣ በጣም ጭንቅ ምክንያት ወይም በሕመም
ምክንያት ከሆን ግን ክቡር ወንጌል ከተነበበ በኋላ ሊወጣ ይችላል። በቅዳሴ ጊዜ ካህናት
የሚቀድሱባቸው አልባሳት ነጫጭ ይሁን ነጭ ልብስ ደስ እንዲያሰኝ በሥጋ ወደሙ የተገኘ
ክብርም ደስ ያሰኛልና፣ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ባህርየ መለኮቱን በገለጸ ጊዜ ልብሱ
እንደበረድ ነጭ ሆኗል። መላእክትም ወርኃ ሰላም ወርኃ ፍስሐ ነው ሲሉ የልደት፣
የትንሣኤ፣ የዕርገት ነጫጭ ልብስ ለብሰው ታይተዋል።

አንድ ሰው እንኳ ጫማ አድርጎ ከቤተ መቅደስ አይግባ ልዑል እግዚአብሔር የምትቆምባት


ደብረ ሲና የከበረች ናትና ጫማህን አውልቅ ብሎ ለሙሴ ተነግሮታልና። /ዘጸአት ፫-፭/።
በቅዳሴ ጊዜ ተሰጥዖውን የማያውቅ ደግሞ በአንክሮ፣ በተዘክሮ፣ በአንቃእድዎ፣ በንጹሕ
ልቡና፣ በሰቂለ ሕሊና ሆኖ ሕሊናው ወደ ዓለማዊ እንዳይወስደው መቆጣጠር አለበት።
ቅዱስ ወንጌል ከተነበበ በኋላ ካህኑ ለሕዝቡ ተርጉሞ ይንገራቸው ያስተምራቸው እጁንም
በሚታጠብበት ጊዜ የተጣላችሁ ሳትታረቁ፣ የሰው ገንዘብ የወሰዳችሁትን ሳትመልሱ ሥጋ
ወደሙን ብትቀበሉ ሥጋው እሳት ሆኖ ይፈጃችኋል ደሙ ባህር ሆኖ ያሰጥማችኋል። ነገር
ግን የወሰዳችሁትን የሰው ገንዘብ መልሳችሁ፣ ከተጣላችሁት ታርቃችሁ ኃጢአት ብትሰሩ
ንስሐ ገብታችሁ ብትቀበሉት ግን መድኃኒተ ሥጋ መድኃኒተ ነፍስ ይሆናችኋል። በረከተ
ሥጋውን በረከተ ነፍሱን ያድላችኋል ብሎ ይንገራቸው ያስተምራቸው ይላል።

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 86
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ካህኑ ሥጋ ወደሙን በፈተተበት እጁ ሕዝቡን ፊታቸውን ይባርካቸው። ቀሳውስት ግን እጅ


በእጅ ተያይዘው እርስ በርሳቸው ይባረኩ። ቀዳሹ ካህን ቀሳውስትን ሲያሳልም “የጴጥሮስን
ሥልጣን ባንተ አለ” ይበል፣ ተሳላሚው ቄስም “መንግሥተ ሰማያት ያውርስህ ከሾመ
አይሻርህ” ይበል። ለዲያቆናትም “ልዑል እግዚአብሔር ያክብርህ ይባርክህ፣ ለማስተማር
ዓይነ ልቡናህን ያብራልህ፣ ምሥጢሩን ይግለጥልህ” እያለ ይባርካቸው። ለምዕመናንም
“ልዑል እግዚአብሔር ያክብርህ፣ ይባርክህ፣ ገጸ ረድኤቱን ይግለጽልህ” እያለ ይባርካቸው።
ለሴቶችም “ልዑል እግዚአብሔር ይባርክሽ፣ ያክብርሽ ገጸ ረድኤቱን ይግለጽልሽ” ብሎ በእጁ
ይባርክ።

6.6 ከቅዱስ ቁርባን በፊትና በኋላ መደረግ ሥላለበት ሥርዓት


በጥምቀት ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ ከማኅፀነ ዮርዳኖስ ዳግም ተወልደን መንግስተ ሰማያትን
ለመውረስ /ዮሐ.3፥5/ የተዘጋጀን ክርስቲያኖች ሕያዋን እንሆን ዘንድ ዘወትር መንፈሳዊውን
መብል ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን መቀበል አለብን። ዮሐ.6፥26። ሥጋዊ መብልና
መጠጥ ዘወትር እንደሚያሻን ሁሉ አምላካችንንም ዘወትር እንድንሻው ቅዱስ ሥጋውንና
ክቡር ደሙን በሚበላና በሚጠጣ ሰጥቶናል። ዮሐ.6፥3 ስለዚህም ምዕመናን ዘወትር ከቅዱስ
ሥጋውና ከክቡር ደሙ የተለየ ሕይወት ሊኖረን አይገባም። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ
በቀዳማዊ ቆሮንቶስ መልዕክቱ 11፥26 ሳይገባው ይህን እንጀራ የበላ ወይም

የጌታን ጽዋ የጠጣ ሁሉ የጌታ ሥጋና ደም አለበት ሰው ግን ራሱን ይፈትን እንዲሁም


ከእንጀራው ይብላ ከጽዋውም ይጠጣ ሳይገባ የሚበላና የሚጠጣ የጌታን ሥጋ ስለማይለይ
ለራሱ ፍርድ ይበላልና ይጠጣልምና። በማለት እንዴት ወደ ቅዱስ ቁርባኑ መቅረብ
እንዳለብን ተናግሯል። ወደ ቅዱስ ሥጋው ክቡር ደሙ ቅድመ ቁርባን ጊዜ ቁርባንና ድኅረ
ቁርባን ልንፈፅመው የሚገባውን ሥርዓት ማወቅ ተገቢ በመሆኑ በሦስት ከፍለን
እንመለከታለን።

6.6.1 ቅድመ ቁርባን መደረግ ያለበት ሥርዓት


ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን ከምንቀበልበት ሰዓት አስቀድሞ ባሉት ዐሥራ ስምንት
ሰዓታት። ልንፈፅመው የሚገባውን ሥርዓት ያሳያል። በቅድመ ቁርባን የማፈፀሙ
ሥርዓቶች፦

ከሩካቤ ሥጋ መከልከል፦ ቀዳሲያንና ሥጋውንደሙን የሚቀበሉ ምዕመናን በጋብቻ ተወስነው


የሚኖሩ ከሆነ ሥጋ ወደሙን ከመቀበላቸው ሦስት ቀናት አስቀድሞ ከሩካቤ ሥጋ መከልከል
አለባቸው። "ጋብቻ ክቡር መኝታውም ንፁሕ" /ዕብ 13፥4/ እንዳለ በሕግ የሆነ ሩካቤ ኃጢአት
ሆኖ አይደለም። ካህኑ /አቀባዩ/ ክርስቶስን መስለው ምዕመኑም /ተቀባዩም/ ሐዋርያትን

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 87
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

መስሎ የሚቀርብ በመሆኑ ነው። አንድም በመሰረቱ ግብሩ የሥጋ እንደመሆኑ መጠን
ስለሚቀበሉት ምስጢር ክብር መንፈሳዊ ጥንቃቄ ለማድረግ ነው።

በንስሐ መታደስ፦ የሚያቀብሉና የሚቀበሉ ሰዎች ከንስሐ አባታቸው ጋር በመመካከርና


የንስሐ አባታቸውን ፈቃድ ማግኘት አለባቸው። የበደሉትን ሳይክሱ፣ የወደዱትን
ሳይመልሱ፣ ከቂም ከበቀል ሳይነጹ፣ ክፉ ኅሊናን ሳያርቁ ወደ ሥጋወደሙ መቅረብ
አይገባቸውም።

ለዐሥራ ስምንት ሰዓታት መጾም፦ ጌታ በምሴተ ሐሙስ በሦስት ሰዓት በአይሁድ ጭፍሮች
ተይዞ እስከ አርብ 9 ሰዓት ድረስ ያለውን ጊዜ በማሰብ 18 ሰዓታት የተመገቡት ከሆዳቸው
ጠፍቶ ለአፋቸው ምረት፣ ለሆዳቸው ባዶነት እስኪሰማቸው እንዲጾሙ ቤተክርስቲያን
ታስተምራለች። ይሁን እንጂ አንዳንድ ሰዎች ከቅንነት አንጻር ይህን ያህል ሰዓት መቆየት
ባለመቻላቸው ሥጋደሙን ለመቀበል ቤተክርስቲያን መጥተው ሲታመሙ እና ራሳቸውን
ስተው ሲወድቁ ይታያል። እንዲህ አይነቱን ችግር ለማቃለል ከንስሐ አባታቸው ጋ
በቅድሚያ ሊማከሩበት ይገባል። "ጴጥሮስ በሁለተኛው ቀሌምንጦስ በ46ኛው አንቀጽ ጠንቅቆ
ሳይጾም ማንም ማን ሥጋ ወደሙን አይቀበል። ከወንዶችም ከሴቶችም ወገን ማንም ምን
የቀመሰ ቢኖር፣ ከቀመሰ በኋላ ሥጋውን ደሙን ቢቀበል፣ ተደፋፍሮ ይህንን ቢያደርግ
ለዘለዓለም ከምዕመናን በውግዘት ይለይ።"

ለመቀበል በተዘጋጁበት ዕለት ሰውነትን አለመታጠብ ፡- ምክንያቱም ሲታጠቡ ውኃ ወደ አፍ


በቀላሉ ሊገባ ስለሚችል ነው። በተመሳሳይ ሁኔታ ጥርስ መፋቅም መድማትን ሊያስከትል
ይችላል። ስለዚህ ሰውነትን መታጠቡ፣ ጥርስ መፋቁ፣ ጢም መላጨቱ ከመቀበሉ 18 ሰዓት
በፊት ማድረግ፣ የሚለብሱትን ልብስ ንጹሕ አድርጎ ማዘጋጀት ይገባል። በአምልኮ ጦዖት
ልቦና ጊዜ ቁርባን ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን ለመቀበል በቀረብንበት ጊዜ የሚፈፀምን
ሥርዓት ያሣያል። ካህናቱ ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን ለመቀበል ድርገት ሲወርዱ
ምእመናን በስግደት እጅ ሊነሱ ይገባል። ሥጋ ወደሙን ለመቀበል በየማዕረጋቸው ተሰልፈው
የሚቀርቡ ምእመናን እጃቸውን በትእምርተ መስቀል አመሳቅለው፣ ምእመናን ደግሞ
ክንብንባቸውን ገልጠው ሊቀርቡ ይገባል። ይህም ትምህርተ ትህትና ነው።

ሐዋርያት በመጀመርያው ቀሌምንጦስ በ23ኛው ሠለስቱ ምእት በኒቅያ በጻፉት መጻሕፍት


በ17ኛ አንቀጽ...‹ወይዘምሩ በጊዜ ተመጥዎ ቁርባን ኵሎሙ ምእመናን ሁሉ ቅዱስ ሥሉስን
ይጸልዩ› አሉ፡፡ ሓዋርያት በመጀመርያው ቀሌምንጦስ በ23ኛው ባስልዮስ በጻፈው መጻሕፍ
በ99ኛው አንቀጽ ካህን በሚያቀብልበት ጊዜ ኃጢአታችንን ለማስተስረይ ለኃጢአት ለሞት
አሳልፎ የሰጠው የክርስቶስ ሥጋ ይህ ነው ይበል፡፡ የሚቀበልም ሰው አሜን ይበል፡፡
ዳግመኛም ጽዋን ይዞ ደምን የሚያቀብል ካህን ስለእኛ የፈሰሰው የክርስቶስ ደም ይህ ነው

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 88
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ይበል፡፡ ደሙንም የሚቀበል ሰው ሁለት ጊዜ አሜን ይበል፡፡ በፍጹም ፍርሐትና ንጽሕና


ይቀበለው፡፡ ደሙን ሲቀበል ሁለት ጊዜ አሜን ማለቱ ደማዊት ነፍስን ነባቢት ነፍስን ሲያይ
አንድም የሥጋውን ጨምሮ ነው፡፡

እንደተቀበሉ አፋቸውን በእጃቸው ሊሸፍኑ ይገባል፡፡ ይኸውም ሥጋ ወደሙ እንዳይነጥብ


ለመጠንቀቅ ነው፡፡ የተቀበሉትንም ሥጋ ወደሙ በትናጋቸው መካከል አድርገው /በአፋቸው
መካከል አዘዋውረው/ በቀስታ ወደ ጉሮሮአቸው ሊልኩት ይገባል እንጂ እንደምድራዊ
ኅብስት በጥርሳቸው ሊያኝኩት አይገባም፡፡ በጥርሳቸው መካከልና በላንቃቸው ተጣብቆ የቀረ
እንዳይኖር የቅዳሴ ጠበል ሊጠጡ ይገባል፡፡ አንዳንደ ሰዎች አፋቸውን ለረጅም ሰዓት ይዘው
መቆየት አይችሉም፡፡ ስለዚህ የሚበሉ ነገሮችን ይዘው ገብተው ከተቀበሉ በኋላ
ቤተክርስቲያን ውስጥ ሲመገቡ ይስተዋላሉ፡፡ ይህ በጣም ትልቅ ስህተትና ድፍረት ነው፡፡
ምክንያቱም እጃቸውን በአፋቸው ላይ እንዲያኖሩ የታዘዙት በአፋቸው ያለውን ቅዱስ
ሥጋውን ክቡር ደሙን ከጉሮሮአቸው አጥርተው እስኪያወርዱ ድረስ አንድም ለአክብሮተ
ሥጋ ወደሙ ነው፡፡

በቤተ ክርስቲያን ውስጥም አፍን ለማደፍ ዘቢብ ወይም ሌላ ማናቸውንም ነገር እንዲበሉ
ሥርዓት ያስቀመጠ መጽሃፍ የለም፡፡ ቅዳሴ ጠበሉ እሱ አፍ ማደፊያ ነው፡፡ ምእመናን
ምእመናት አባቶችን አብነት ለማድረግ ሲገባቸው በራሳቸው መንገድ ከሥርዓት የወጣ ነገር
መፈጸም አይገባቸውም፡፡ ቤተሰቦቻቸውም ማደፊያ የሚሆን ነገር ይዘው ውጪ
እንዲጠብቋቸው አልያም በእናቶች የሚታደለውን ዳቤና ንፍሮ ተቀብለው አፋቸውን ማደፍ
ይችላሉ፡፡ ስለዚህ ይህን ዓይነቱን ስህተት የሚፈጽሙ ሰዎች ሊታረሙ ይገባል፡፡

6.6.1.1 ለመቁረብ የሚያበቁና የማያበቁ ምክንያቶች


ሀ. ከምዕመናን በስተቀር ያላመኑ ሰዎች ሥጋዉንና ደሙን ሊቀበሉ አይገባቸዉም

ለ. ቅዳሴ ሲቀደስ ያልነበረ፣ ያላስቀደሰ፣ ካህኑም ማቁረብ ምዕመኑም መቁረብ አይገባቸዉም

ሐ. በንስሐ የተለየ ሰዉ ለሞት የሚያበቃ ደዌ በታመመ ጊዜ ሥዉን ደሙን ከመቀበል


አይከልክሉት ቢድንም አንተ ንስሐ ይገባሃል ንስሐን ተቀበል ብለዉ ሥጋዉን ደሙን
ከመቀበል አይከልክሉት፡፡ ፍት. ነገ አንቀጽ 13

መ. በሚገባ ሳይጾሙ ሥጋ ወደሙን መቀበል አይገባም፡፡ ፍት.ነገ አንቀጽ 13

ሰ. ከቂም በቀል ያለበት የዝሙትና የስካር መንፈስ ያለበት ሰዉ የህን ሁሉ በንስሐ ሳያርቅ
መቀበል አይገባዉም፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 89
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

6.6.1.2 ሥጋ ወደሙን ሳያምኑ ቢቆርቡ የሚያስከትለዉ ጉዳት


ሳይገባው ራሱን ሳይፈትን ሳይመረምር የሚቆርብ ፣የጌታን ሥጋ ስለማይለይ ለራሱ ፍርድ
ይበላልና፣ በማለት ይኸው ሐዋርያ ያስጠነቅቀናል። “ስለዚህ ሳይገባው ይህን እንጀራ ኅብስት
የበላ ወይም የጌታን ጽዋ የጠጣ ሁሉ የጌታ ሥጋና ደም ዕዳ አለበት። ሰው ግን ራሱን
ይፈትን፣ እንዲሁም ከእንጀራው ከኅብስቱ ይብላ ከጽዋውም ይጠጣ፤ ሳይገባው የሚበላና
የሚጠጣ የጌታን ሥጋ ስለማይለይ ለራሱ ፍርድ ይበላልና፣ ይጠጣልምና። ስለዚህ በእናንተ
ዘንድ የደከሙና የታመሙ ብዙዎች አሉ አያሌዎችም አንቀላፍተዋል። ራሳችንን
ብንመረመር ግን ባልተፈረደብንም ነበር፤ ነገር ግን በተፈረደብን ጊዜ ከዓለም ጋር እንዳንኮነን
በጌታ እንገሠጻለን” /፩ኛ ቆሮ ፲፩፣፳፯-፴፪/።

6.6.1.3 ለመቁረብ የሚደረግ ጥንቃቄ /ዝግጅት/


ምእመናን ሥጋ ወደሙን ለመቀበል በሚፈልጉበት ወቅት ሊፈጽሟቸው የሚገቡ ዝግጅቶች
አሉ። ሥጋዊ ማዕድስ እንኳን ከመበላቱ በፊት የራሱ የሆነ ዝግጅት አሉት። ሰማያዊው
ማዕድማ ምን ያህል ጥንቃቄ ይፈልግ ይሆን!? /ማቴ ፳፪፥፲፪፡፡/ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
በሰርግ ቤት ምሳሌነት በርካታ ትምህርቶችን አስተምሯል። ካስተማራቸው ትምህርቶች
መካከል በተጠቀሰው ወንጌልና ምዕራፍ ከቁጥር ፩ ጀምሮ የሰፈረውን ታሪክ ስናነበው ከርእሰ
ጉዳያችን ጋር በተያያዘ የሚከተሉትን ነጥቦች እናገኛለን። “መንግሥተ ሰማያት ለልጁ ሰርግ
ያደረገ ንጉሥን ትመስላለች፤” በማለት ይጀምራል። ወደ ሰርጉ ከታደሙት መካከል
አንደኛው ለሰርጉ ቤት ክብር የሚመጥን ዝግጅት ሳያደርግ በዘፈቀደ በመግባቱ የደረሰበት
ችግርና ቅጣት ቁጥር ፲፪ ጀምሮ ስናነብ የምናገኘው ነው። ንጉሡ ተጋባዦችን ሊጎበኝ
/ሊያይ/ ወደ ሰርጉ ቤት በገባ ጊዜ ያ ሰው የሰርግ ልብስ ሳይለብስ በመገኘቱ ነው ተግሣጹም
ቅጣቱም ያገኘው። ይህም ምድራዊው ሰርግም እንኳን ቢሆን የራሱ የሆነ የአለባበስ፣
የአቀማመጥ፣ የአመጋገብና የክንውን ሥርዓትና ጊዜ እንዳለው ያሳየናል።

የሰርጉ ቤት የቤተ ክርስቲያንና የመንግሥተ ሰማያት ምሳሌ ሲሆን የሰርጉ ባለቤት ደግሞ
የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ነው፡፡ ታዳሚዎቹም የምእመናነ ክርስቶስ ምሳሌዎች
ናቸው። ድግሱ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በጸሎተ ቅዳሴ በየጊዜው የምታዘጋጀው ቅዱስ
ሥጋውና ክቡር ደሙ ነው። ይህም ዝም ተብሎ በዘፈቀደ ማንም ባሻው ጊዜ እየተነሣ
ያለምንም ዝግጅት የሚመገበው ተራ ምግብ አይደለም። ተግሣጹም ሆነ ጽኑዕ ቅጣቱ
እንዳያገኘን ባግባቡ ተዘጋጅተን በካህናት እጅ የሚሰዋውን መሠዋዕተ ሐዲስ መቀበል
ይኖርብናል፡፡ ዋና ዋናዎቹ የዝግጅቱ አካላትም የሚከተሉት ናቸው።

ባለፈ ኃጢአት መጸጸት፣ መናዘዝና ቀኖና ተቀብሎ በትሕትናና በፍቅር መፈጸም፤


ዳግም ላለመበደልም ወስኖ መጋደል፤

ወደ ልባችን የኃጢአትን አሳብ እንዳያስገቡ አካላዊ ስሜቶችን ሁሉ መግዛት፤


በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)
ገጽ | 90
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ሰውነትን /አካልን/ በዋዜማው በአግባቡ መታጠብና አቅም በፈቀደ መጠን ተገቢውን


ልብስ (ከተቻለ ነጭ) አዘጋጅቶ መልበስ፤

በዋዜማው ቀለል ያለ ምግብ መመገብ ፣ለ፲፰ ሰዓታት ከምግበ ሥጋ መከልከል፣

ሕጋዉያን (ባለ ጋብቻ) ቆራቢያን ከሩካቤ ሥጋ ለ፫ ቀናት መታቀብ፣

ከሕልመ ሌሊትና ከወር አበባ እንዲሁም ከሚደማና ከሚያዥ ቁስል ነጻ መሆንን


ማረጋገጥ፣

በወሊድ ጊዜ ሴቶች ለወንድ ልጅ ፵ ቀን ለሴትም ልጅ ፹ ቀን የሞላቸው መሆኑን


መገንዘብ፣

ሥርዓተ ጸሎተ ቅዳሴ ከመጀመሩ በፊት መድረስ የሚሉትና የመሳሰሉት ዝግጅቶች


አስፈላጊ ናቸው። ከጤንነት ጋ በተያያዘ የጾም ሰዓትን በተመለከተ ከመምህረ ንስሐ
ጋር በመመካከር በፈቃደ ካህን የሚስተካከል ይሆናል።

 የማይላመጥ የአድማስ ድንጊያ ነዉ፡፡ በዚህም የሚያስ ከትለዉነ የመከራ ጽናት


ለመናገር ነዉ፡፡ የድንጊያ ንፍሮ (የብረት ቆሎ) ማላመጥ እንደማይቻልም በአግባቡ
ሆነዉ ካልተቀበሉት የሚያስከትለዉም መከራ ጽኑዕ ነዉ፡፡
 በኃጢአት ላይ ኃጢአትን የሚጨምር ከማስተስረይ ቀርቶ በደለኛ ያደርጋል፡፡
 ደዌ ሥጋ ደዌ ነፍስን ያመጣል፣ በመከራ ላይ መከራን ያመጣል
 እንደ ባቢሎን እሳት የሚያቃጥል የሚግጥ እሳት ይሆናል፡፡
 ልቡናን በኃጢአት ያደነድናል እንደ ይሁዳ ለሌላ በደል ያዘጋጃል

6.6.1.4 የቆራቢያን የአቆራረብ ቅደም ተከተል


1. ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት፣ሊቃነ ጳጳሳት፣ጳጳሳት(ኤጲስቆጶሳት)
2. ቀሳዉስት ወዲያቆናት
3. ወዶች በየማዕረጋቸዉ
4. ሴቶች በየክብራቸዉ
5. በዕለቱ የተጠመቁ ከምእመናን የቀድማሉ (ወነወዶች መጀመሪያ ናቸዉ)
6. ንዑሰ ክርስቲያን ተጠማቂያን እንደየእድሜያቸዉ (ከትንሽ ወደ ትልቅ)
7. በድንግልና ኖረዉ የመነኮሱ መነኮሳት
8. ከመነኮሱ ከ20 ዓመት በላይ የሆናቸዉ መነኮሳት
9. ንፍቀ ዲያቆናት፣አናጉንስጥሰዉያን፣መዘምራን፣
10. በሕግ ኖረዉ የመነኮሱ መነኩሳት
11. በሕግ ጸንተዉ ያሉ ሕጋዊያን

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 91
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

12. በንስሐ ተመልሰዉ የመነኮሱ መነኩሳት


13. ንስሐ የገቡ ሕዝባዉያን በየማዕረጋቸዉ ቅድሱን ቁርባን ይቀበላሉ
14. ለሴቶች የ80 ቀን ሕጻናት ቅድሚያይኖራቸዋል
15. ንዑሰ ክርስቲያን ተጠማቂዎች
16. በድንግልና ኑረዉ የመኮሱ ድናግል
17. የቀሳዉስት ሚስቶች
18. በሕግ ኖረዉ የመነኮሱ መነኮሳት
19. የዲያቆናት ሚስቶች
20. በንስሐ ተመልሰዉ የመነኮሱ መነኮሳት
21. የንፍቅ ዲያቆናት፣የአናጉስጢሳዊያንና የመዘምራን ሚስቶች
22. በሕግ ጸንተዉ ያሉ ሕጋዉያን፣ በመጨረሻ ንስሐ የገቡ ሕዝባዉያን ሴቶች
(ሚስቶች)

6.6.2 ቅዱስ ቁርባንን ከተቀበሉ በኋላ የሚደረግ ጥንቃቄ


 ከተቀበሉ በኋላ ወዲያዉ ቅዳሴ ጠበል መጠጣት አይገባም ቆመዉ ያስቀደሱበት
ቦታ በመሔድ ድርገት እስኪወርድ ድረስ መቆየት፡፡
 በአፍ ዉስጥ ትንኝና የመሳሰሉት ተሐዋስያን እንዳይገቡ አፍን በመሐረብ
መሸፈን
 ከሰርዎተ ሕዝብ አስቀድሞ ሥጋ ወደሙን የተቀበሉ ሁሉ በጸሪቀ መበለት
አፋቸዉን አያድፉ ቅዳሴ ከአፋቸዉ አይንጠብ፡፡
 ከቤተ መቅደስ ሳይጋፉ በቀስታ ወጥቶ በደጀ ሰላም (ጸሪቀ መበለት) ቀምሶ አፍን
ማደፍ
 በዕለቱ ቆራቢያን እንዲፈጽሟቸው የማይፈቀዱ ተግባራት በከፊል

ገላን (ሰውነትን) መታጠብ፣ ከልብስ መራቆት፣ መስገድ


መንበርከክ፣ ምራቅን እንትፍ ማለት፣ መበጣት መቆረጥመታገም
መተኮስ፣ የእጅና ይእግር ጥፍር መቆረጥ፣ ፀጉርን መላጨት፣ ሩቅ
መንገድ መሔድ፣ መፍረድ፣ መክሰስ፣ መካሰስ፣ ወደ መታጠቢያ
ቤት መሄድ፣ ያለ መጠን መብላት፣ መጠጣት፣ ለሦስት ቀናት
ያህል ግብረ ሥጋ፣ ይህን የመሳሰሉትን ሁሉ ማድረግ አይገባም፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 92
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

6.7 ምሥጢረ ቁርባን የሚያስገኘው ጸጋ

በብሉይ ኪዳን እግዚአብሔር በሙሴ አማካኝነት ከቤተ እሥራኤል ጋር ቃል ኪዳን የገባው


በእንሰሳት ደም ነበር /ዘፀ ፳፬፣፩-፲፩/። ያን ጊዜ ቤተ እሥራኤል ቃል የገቡት ሕገ ኦሪትን
ሊፈጽሙ አሠርቱ ትእዛዛትን ሊጠብቁ ሥርዓቱን ሊያከብሩ ነበር። እግዚአብሔር ደግሞ በበኩሉ
አምላካቸውና ጠባቂያቸው ሊሆን፣ ምድረ ርስትንም ሊያወርሳቸው ተሰፋ ሰጣቸው፣ ቃል
ገባላቸው። በወንጌል ግን እግዚአብሔር ቃል ኪዳን የገባው በልጁ ደም ነው። እግዚአብሔርም
የፈጸመልን አዲሱ ኪዳን ከብሉይ ኪዳን እጅግ የላቀ ነው። ምክንያቱም በክርስቶስ የሐዲስ ኪዳን
ደም ኃጢአታችን ተወግዶልናል፤ ከእግዚአብሔር ታርቀናል፤ የእግዚአብሔርን ልጅነት
አግኝተናል፤ እግዚአብሔርም አባት ሆኖን የመንግሥቱ ወራሾች እንድንሆን አብቅቶናል።

ቃል ኪዳን ከገባንበት ዋናው ነገር በቆረብንና ቅዳሴ ባስቀደስን ቁጥር የበደላችንንና


የኃጢአታችንን ሥርየት ያገኘንበትን፣ ከእግዚአብሔር የታረቅንበትን የክርስቶስን ሕማምና ሞት
ማሰብና ማስታወስ ነው። ስለዚህ ነው ጌታችን ኅብስቱን አንስቶ ባርኮና ቆርሶ ለሐዋርያቱ
ከሰጣቸው በኋላ “ስለ እናንተ የሚሰጠው ሥጋዬ ይህ ነው፤ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት”
ብሎ ያላቸው /ሉቃ ፳፪፣፲፱/። መታሰቢያዬ የተባለው ስለ ሕማምና ሞቱ መሆኑንና ይህንንም
የሞቱን ዜና የመስቀሉን ነገር ጌታ እስኪመጣ ድረስ በምሥጢረ ቁርባን አማካኝነት እንደሚነገር
ከሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎሰ እንማራለን /፩ኛ ቆሮ ፲፩፣፳፫፡፳፮/። ዛሬም በጸሎተ ቅዳሴ “ንዜኑ
ሞተከ እግዚኦ” የተባለውን እያዜምን እናስታውሰዋለን

በምንቆርብበትም ጊዜ የምናየው የተፈጥሮ ኅብስትና ወይን ብቻ መስሎን እንዳንሳሳት


የማይታየው መለኮት የተዋሐደው የጌታ ሥጋና ደም መሆኑን አምነን መቀበል አለብን።
አለበለዚያ በራሳችን ላይ ፍርድን እናመጣለን። የሚታየው ኅብስትና ወይን በክርስቶስ ቃል
ኪዳን፣ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል፣ በካህኑ ጸሎትና በጸሎተ ቅዳሴ ነፍስ የተለየው፣ መለኮት
የተዋሐደው ሥጋ ወልደ እግዚአብሔርና ደመ ወልደ እግዚአብሔር ወደ መሆን ይለወጣል።
ምእመናን ይህን አምነውና ንስሐ ገብተው ሲቀበሉ በወንጌል የተጻፈውን የማይታይ ጸጋ
ለማግኘት ይችላሉ። ከእነዚህም ዋና ዋናዎቹ ቅዱስ ቁርባንን በመቀበል የሚገኙ ጸጋዎች፦

 ሥርየተ ኀጢአት፣ (ማቴ፳፮፥፳፮-፳፰፡፡)


 የዘላለም ሕይወት፣ (ዮሐ ፮፥፶፬፡፡)
 የኃጢአት ልጓም ሆኖ ማገልገል፣ (ዮሐ ፮፥፴፭፤፶፭፡፡)

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 93
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

 ከክርስቶስ ጋር አንድ መሆን፣ (ዮሐ ፮፥፶፫፡፡)


 ፍትወታትን ድል መንሳት፣ (ያዕ ፬፥፯፡፡)
 ፍላጎትን ለመቆጣጠርና ራስን መግዛት፣ (፪ጢሞ፥፩፥፯፡፡)
 የፍቅር ሰዎች መሆን፣ (፩ ዮሐ፬፥፯‐ፍጻሜው፡፡)
 የትዕግሥትን ጸጋ ለመቀበል፣ (ዕብ ፬፥ፍጻሜው፡፡)

6.8 ቁርባን በብሉይ ኪዳንና በሐዲስ ኪዳን ልዩነቱና አንድነቱ


በብሉይ ኪዳን ታሪክ መሥዋዕትና ቁርባን ለእግዚአብሔር ማቅረብ የተጀመረው ከአባታችን
ከአዳም ጀምሮ ነው፡፡ በዘመነ አበው የነበሩ አባቶች እስከሙሴ ድረስ በሕገ ልቡና መርምረው
እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ መሥዋዕት አቅርበው ተመስግነውበታል፡፡ ያማረ የተወደደ
መሥዋዕት ማቅረብ ያልቻሉ ደግሞ በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነት ሳያገኙ ቀርተዋል፡፡ (ዘፍ.
፬፥፫-፮፡፡) ከሙሴ ጀምሮ ባለው ዘመን ደግሞ እግዚአብሔር በሙሴ አማካኝነት እስራኤልን
ባዘዘው መሠረት ከሥጋ (ከእንስሳ) ወገን የሆነውን መሥዋዕት፣ ከአዝርዕትና ከአትክልት ወገን
የሆነውን ደግሞ ቁርባን እያሉ በመጥራት ለእግዚአብሔር ያቀርቡት ነበር፡፡ መሥዋዕቱና
ቁርባኑም የዘወትር፣ የመባቻ፣ የሰንበት፣ የበዓል፣ የፈቃድ፣ የምስጋና፣ የመድኃኒት፣ የንስሐ፣
የብፅዓት፣ የቅንዓት እየተባሉ ይጠሩ ነበር፡፡ (ዘኁ@8÷1-ፍጻ፣@9÷1ፍጻ፡፡)

የዘወትሩን መሥዋዕት ካህናት የዓመቱን መሥዋዕት ደግሞ ሊቀ ካህናት፤ ያቀርቡት ነበር፡፡


ካህናቱም አስቀድመው ስለራሳቸው በደል በመቀጠልም ስለ ሕዝቡ ኃጢአት በእግዚአብሔር ፊት
መሥዋዕት ያቀርቡ ነበር፡፡ ከመጋረጃ ውጪ በቅድስት ካህናቱ መሥዋዕት ሲያቀርቡ ሊቀ
ካህናቱ ግን ከመጋረጃ ውስጥ በዓመት አንድ ቀን በቅድስተ ቅዱሳን መሥዋዕቱን ያቀርብ ነበር፡፡
መሥዋዕቱም ሆነ ቁርባኑ ከሰዎች ለእግዚአብሔር የሚቀርብና ጊዜያዊ ኃጢአትን ለማስተሥረይ
ብቻ የሚችል ነበር፡፡ (ዕብ፱÷፮-፰፡፡) የሐዲስ ኪዳኑ መሥዋዕት ግን አስቀድመን እንደገለጽነው
እግዚአብሔር ዓለሙን ሁሉ እስከ ሞት ድረስ የወደደበትና ለሰው ልጆች ሁሉ የተሰጠ የፍቅር
ስጦታ ነው፡፡ (ዮሐ ፫፥፲፮፡፡)

በብሉይ ኪዳን ዘመን የነበሩ አበው ሁሉ ያቀረቡት መሥዋዕትና ቁርባን፣ በአዳምና በሔዋን
በደል በሰው ልጆች ሁሉ ላይ ተፈርዶ የነበረውን መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ ሊያስወግድ
አልቻለም ነበር፡፡ እግዚአብሔር አምላካችን ይህንን መርገም ያጠፋበት፤ የጥሉንም ግድግዳ
ያፈረሰበት አማናዊ መሥዋዕት ክርስቶስ በመስቀል ላይ የቆረሰውና ያፈሰሰው ቅዱስ ሥጋው

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 94
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ክቡር ደሙ መሆኑም ይታወቃል፡፡ የሁለቱ ኪዳናት መሥዋዕት አንድነታቸው ካህናት በቤተ


መቅደስ ስለራሳቸውና ስለሰዎች በእግዚአብሔር ፊት የሚያቀርቡት መሆኑ ነው፡፡

6.9 የአዲስ ኪዳን ታቦት


ታቦት ቃሉ የግእዝ ሲሆን ትርጓሜውም ማደሪያ ማለት ነው። ታቦት በብሉይ ኪዳን ታላቅ
መንፈሳዊ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየ ቅዱስ ንዋይ ሲሆን በሐዲስ ኪዳንም የራሱ የሆነ
አገልግሎት ያለው የከበረ መንፈሳዊ የክብር መገልገያ ነው። የብሉይ ኪዳን ታቦትና የአዲስ
ኪዳን ታቦት በቅርጽና በይዘት፣ በዓላማና በአገልግሎት ፈጽሞ የተለያዩ ናቸው።

የብሉይ ኪዳን ታቦት በይዘቱ ትልቅ የሆነና አራት መያዣዎች ያሉት ሲሆን በአራት ሰዎች
የሚያዝ ነው። አገልግሎቱ ደግሞ አሰርቱ ትእዛዛት የተጻፈባቸውን ሁለት ጽላቶች
ለማስቀመጫነት የሚጠቅም ነው። ታቦት የሚለው ቃል ማደሪያ የሚል ትርጉምንም ያገኘው
ከዚሁ ይሰጥ ከነበረው የማደሪያነት አገልግሎት አንጻር የተሰጠ ስያሜ ነው። ይህንን የከበረ
የሕግ ማደሪያ(ታቦት) ይሰሩና በወርቅ ይለብጡት ዘንድ ለሙሴና ለአሮን ያዘዛቸው ራሱ
እግዚአብሔር ነው። ዘፀ 25፥8 እግዚአብሔር ያለ ዓላማና ያለ ምክንያት አንዳችም ነገር ሰዎች
ይሰሩ ዘንድ አያዝም።

በዘመነ ብሉይ የታቦቱ መኖር ታላቁ ዓላማ እስራኤላውያን ከግብጽ ወጥተው ወደ ከነዓን ሲጓዙ
መንፈስ የሆነውንና በሥጋዊ ዓይን የማይታየውን እግዚአብሔርን በእውነትና በመንፈስ
ለማምለክ የእምነት ደረጃቸውና የአምልኮ ልምምዳቸው ገና ስለነበር በሚታየው ታቦት ፊት
የማይታየውን እግዚአብሔርን ያመልኩት ዘንድ አዕምሯቸውን የሚያግዝ በፊታቸው
የሚያልፍ፣ የሚታይና ግዘፍ ያለው ነገር መኖር ስለነበረበት እግዚአብሔር ታቦት በመካከላቸው
ይኖር ዘንድ ወደደ። የሰው ልጅ አእምሮ በሃይማኖት አድጎና በእምነት ጎልምሶ በመንፈስ
ማምለክ እስካልጀመረ ድረስ ከኅሊና በላይ ረቂቅ የሆነውን እግዚአብሔርን ለማምለክ በዓይኑ
ፊት የሚታዩና የሚዳሰሱ ኅሊናውን ለአምልኮ የሚያግዙ መንፈሳዊ ንዋያት ያስፈልጉታል።
በዚህም ምክንያት ነበር የሕጉ ማደሪያ በሆነው በታቦት ላይ የሠራዊት ጌታ ራሱን በክብር
እየገለጠ ኃልዎቱን በማሳየት ለክብር የመረጠው ሕዝብ እግዚአብሔር የሚባል አምላክ እንዳለ
በእርግጠኝነት እንዲያምንና ለእርሱ በፍቅር እየተንበረከከ የእጆቹን በረከት እንዲመገብ
እንዲሁም ከአሕዛብ ጣዖታት ራሱን እንዲጠብቅ ያደርግ የነበረው።

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 95
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

"በዚያም ከአንተ ጋር እገናኛለሁ፤ የእስራኤልንም ልጆች ታዝዝ ዘንድ የምሰጥህን ነገር ሁሉ


በምስክሩ ታቦት ላይ ባለው በሁለት ኪሩቤል መካከል፥ በስርየት መክደኛውም ላይ ሆኜ
እነጋገርሃለሁ።" (ዘጸ 25:22) ስለዚህም የብሉይ ኪዳን ታቦት የእግዚአብሔር የክብሩ መገለጫ
ዙፋንና ኃልዎቱን ማስረጃ የክብር ንዋይ ስለነበር ሕዝቡ ታቦቱ ወዳለበት ወደ መገናኛው
ድንኳን እየሄደ በክብር ደመና የሚገለጠውን እግዚአብሔርን በፍቅር ያመልክ ነበር። በሕዝቡና
በእግዚአብሔር መካከል የነበረው ግንኙነትም እንደ አባትና ልጅ የቅርብ ነበር እንጂ
እግዚአብሔር መንፈስ እንደ መሆኑ ለሕዝቡ ፈጽሞ ከሕሊናቸው የራቀ አልነበረም።

ወደ አዲስ ኪዳን ስንመጣ የአዲስ ኪዳን ታቦት በይዘትና በመጠን በአገልግሎት እና በዓላማ
እንደ ብሉይ ኪዳኑ ሳይሆን የከበረውን የክርስቶስ ሥጋና ደም በከበረ ቅዱስ ንዋይ ላይ
ለመፈተት የምንጠቀምበት ክቡር ምስዋዕ ነው። በአዲስ ኪዳን እግዚአብሔር ራሱን የገለጠው
በአንድ ልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋዌ በኩል ነው ። መልአኩ ለቅድስት ድንግል ከአንቺ
የሚወለደው ቅዱሱ የእግዚአብሔር ልጅ ነው ብሎ ካበሰረ በኋላ ባሕርያችንን ባሕርይው አድርጎ
በአጭር ቁመትና በጠባብ ደረት ተወስኖ በምድራችን በሥጋ የተገለጠው ቅዱሱ የእግዚአብሔር
ልጅ ከብሉይ ኪዳኑ ታቦት በላቀ ሁኔታ የእግዚአብሔርን ክብር ገልጦልናል፣በአባቱ እቅፍ
ያለው የበኩር ልጅ አባቱን ተርኮልናል።

የእግዚአብሔርን መኖርና መግቦቱን በግልጽ የክርስቶስ ሰው መሆን ዓለም እንዲረዳው


አድርጎታል። ዓይንና ልባችን ወዴትም እንዳያይ ፈጣሬ ፍጥረታት መጋቤ ዓለማት አንዱ
እግዚአብሔር ብቻ እንደሆነ ልባችንን ገልጦ አስተምሮናል። ቅዱስ ጳውሎስ እንዳለ። "ከጥንት
ጀምሮ እግዚአብሔር በብዙ ዓይነትና በብዙ ጎዳና ለአባቶቻችን በነቢያት ተናግሮ ሁሉን ወራሽ
ባደረገው ደግሞም ዓለማትን በፈጠረበት በልጁ በዚህ ዘመን መጨረሻ ለእኛ ተናገረን።" ዕብ 1፥1
ስለዚህ የብሉይ ኪዳኑን ታቦት ክብርና ዋና ዓላማ ክርስቶስ ኢየሱስ ጠቅልሎ ወስዶታል
የእግዚአብሔርን ክብርና መግቦት በልጁ በኩል የበለጠ ተገልጦልናል።

"መቼም ቢሆን እግዚአብሔርን ያየው አንድ ስንኳ የለም፤ በአባቱ እቅፍ ያለ አንድ ልጁ እርሱ
ተረከው።" (የዮሐንስ ወንጌል 1:18) ሌላው የብሉይ ኪዳን ታቦት አገልግሎት ሕጉ ለተጻፈበት
ጽላት ማደሪያ ነበር ዛሬ የአዲስ ኪዳን ታቦት ላይ በየቤተ ክርስቲያኑ ስመ እግዚአብሔር
ይጻፍበታል እንጂ አስርቱ ትእዛዛት አይጻፍበትም ምክንያቱም ሕጉን በልባችን ላይ እንደ
ሚጽፈው በቅዱስ ቃሉ አስረግጦ ነግሮናል። ክርስትና ደግሞ ከፊደል ሕግ በላይ በመንፈስ ሕግ

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 96
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

የምንኖርበት የቅድስና ሕይወት ነው። "እናንተም በሕያው እግዚአብሔር መንፈስ እንጂ በቀለም
አይደለም፥ ሥጋ በሆነ በልብ ጽላት እንጂ በድንጋይ ጽላት ያልተጻፈ፥ በእኛም የተገለገለ
የክርስቶስ መልእክት እንደ ሆናችሁ የተገለጠ ነው።" (2ቆሮ3:3)

በዚህ በአዲስ ኪዳን ዘመን እግዚአብሔርን በእውነት እና በመንፈስ እናመልካለን ፣በአንድ ልጁ


በኢየሱስ ክርስቶስ ሞትና ትንሳኤ ያገኘነውን ሕይወትና ጽድቅ በልባችን እያሰብን በኅሊናችን
ሕያው ሆኖ የሚኖረውን የእግዚአብሔርን ክብር ለፍጥረት ሁሉ ስናውጅ እንኖራለን። ታዲያ
የአዲስ ኪዳን ታቦት አስፈላጊነት ለምንድነው? ቢባል። መልሱ አጭርና ግልጽ ነው የኃጢአት
ሥርየት ያገኘንበትንና ወደ ዘለዓለም ሕይወት የተሻገርንበት የከበረው የክርስቶስ ቅዱስ ሥጋና
ክቡር ደም መፈተቻ አድርገን እንጠቀምበታለን ።

ዛሬ በቤተ መቅደስ የሚፈተተው ሥጋና ደም በእለተ አርብ ከፈሰሰው የኪዳን ደም ጋር


በእምነት ሕብረት የምንፈጥርበት ስለሆነና ሥጋዬን የበላ ደሜን የጠጣ የዘለዓለም ሕይወት
ያገኛል ያለውን መለኮታዊ ቃል በተግባር የምንፈጽምበት ስለሆነ ለከበረው መንፈሳዊ መስዋዕት
የከበረ ቅዱስ መሰዊያ ስለሚያስፈልግ ታቦቱን በክብር እንጠቀምበታለን። አንዳንድ ሰዎች
ከእውቀት ማነስ የተነሳ የአዲስ ኪዳኑን ታቦት ሲያጣጥሉና ሲነቅፋ ባልተገራ አንደበትም ጣዖት
ነው ሲሉ እንሰማለን ፈጽሞ ስህተት ነው። የከበረው የክርስቶስ ስም የተጻፈበት ታቦት ጣዖት
አይባልም።እንኳንስ መንፈሳዊ ምግባችንን ለምንፈትትበት ቅዱስ ምስዋዕ ለሥጋዊ ምግባችን
እንኳን ማዕድ የምናስቀምጥበትን ገበታ በክብር እንይዛለን ።

የከበረው የክርስቶስ ደምና ሥጋ ለሚቀርብበት ቅዱስ መሰዊያማ የበለጠ ክብር ልንሰጥ ይገባል።
አንዳንዶች እኛ ኢትዮጵያውያን ከሌላው የዓለም ማኅበረሰብ ይልቅ በልዩ ሁኔታ ከታቦት ጋር
ያለንን ልዩ ሕብረት በመመልከት ሌሎች ሀገሮች የማይጠቀሙትን እናንተ ኦርቶዶክሳውያን
እንዴት ትጠቀማላችሁ ይሄ ወንጌልን አለመረዳት ኦሪታዊነት ነው ይላሉ በጣም ስህተት ነው።
ታሪክን ወደ ኋላ መለስ ብለን በንን የሚለያይ ነው፡፡ ከዚህም በጥልቀት ልናጠና ይገባል ሌሎች
ሀገራት ክርስትናን የተከተሉትና ወንጌልን የተቀበሉት ቀድሞ ከነበሩበት ከጣዖት አምልኮ
በሐዋርያት ስብከትና በብዙ ድንቅ ተአምራት ተላቀው ወጥተው ነው። እኛ ኢትዮጵያውያን ግን
ወደ ሕገ ወንጌል የተሻገርነውና ክርስትናን የተቀበልነው ቀድሞ ከነበርንበት ከሕገ ኦሪት ወጥተን
ነው። ታሪክ በግልጽ እንደሚያስረዳን ከእስራኤል ቀጥሎ በብሉይ ኪዳን ሕግና መንፈሳዊ
ሥርዓት እግዚአብሔርን ስታመልክ የኖረች ብቸኛዋ ሀገር ኢትዮጵያ ነች ። ሌላው ዓለም

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 97
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ጣዖት በሚያመልክበትና በየጋራውና በየወንዙ እንግዳ አማልክትን በሚከተልበት የጨለማ ዘመን


የአብርሃም አምላክ እያለች እግዚአብሔርን ታመልክ የነበረች ቅድስት ሀገር ሀገረ እግዚአብሔር
ኢትዮጵያ ነች። ስለሆነም ለታቦት ክብር መስጠታችን ከጥንት ጀምሮ ሲወርድ ከመጣው
የአምልኮ ትውፊታችን ጋር የተያያዘ ነው እንጂ እንደ ውሃ ፈሳሽ እንደ እንግዳ ደራሽ የሆነ
ዘመን ላይ የተፈጠረ ክስተት አይደለም። ሌሎች ሀገራት ግን ከጣዖት አምልኮ የመጡ
በመሆናቸው እንደ ኢትዮጵያ ያለ ሥርዓት የላቸውም። ይሁን እንጂ አዲስ ኪዳንን ከተቀበሉ
በኋላ በየቤተመቅደሳቸው የክርስቶስን ሥጋና ደም የሚፈትቱበት እንደ ታቦት ለመሰዊያነት
የሚጠቀሙበት የከበረ ንዋይ አላቸው።

ልብ እንበል የክርስቶስ ሥጋና ደም መሠጠቱን የሚያምን አንድ ክርስቲያን ይህ የከበረ ሥጋና


ደም እንደ ተራ ማዕድ በየቦታው ፣ በየጠረጴዛው ሊቀርብ ይችላል ብሎ ለማሰብ እጅግ
ይከብደዋል፡፡ ስለዚህም ቤተ ክርስቲያን ዘመነ ሰማዕታት አልፎ ስደትዋ እስካበቃበት ዘመን
ድረስ በሒደት እየተሻሻለ በመጣ የቤተ መቅደስ ሥርዓት የሐዲስ ኪዳኑን መሥዋዕት በክብር
ለመሠዋትና ለምእመናን ለማቀበል በቅታለች፡፡ የበግና የፍየል ደም ይሠዋ በነበረበት የኦሪት
ዘመን እንኳን ለብቻው ትልቅ መሠዊያ ተዘጋጅቶ፣ መሠዊያው ተቀድሶ ሰው በማይገባበት
በመገናኛው ድንኳን ውስጥ በክብር ተቀምጦ ነበር፡፡ በድንኳኒቱ ውስጥ የሚያገለግሉት አሮንና
ልጆቹም የተለየ ልብስ ለብሰው የበጉን ደም በመሠዊያው ዙሪያ ባለው ቀርነ ምሥዋዕ
(የመሠዊያ ቀንድ) ላይ እየቀቡ ሥርዓቱን ይፈጽሙ ነበር፡፡

ለበግና ለፍየል መሥዋዕት ይህ ሁሉ ክብር ከተሠጠ እንደ በግ ስለ ሁላችን ኃጢአት ራሱን


መሥዋዕት አድርጎ ያቀረበው የእግዚአብሔር በግ ኢየሱስ ክርስቶስ ፣ እንደ ሊቀ ካህናትነቱ
እጁን በመስቀል ላይ ዘርግቶ የሰዋውና ዓለም እንዲድንበት እንካችሁ ብሉ ብሎ የሠጠን
የኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋና ደም መሥዋዕት ሆኖ የሚቀርብበት መሠዊያ ምንኛ የከበረ ይሆን?
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሥጋ ወደሙ ‹መሠዊያ› የምትለው ታቦት
በቅርጽም ፣ በአገልግሎትም ፣ በክብርም በኦሪት እግዚአብሔር ለሙሴ ከሠጠው ታቦት ጋር
አንድ አይደለም፡፡ የቀደመው ታቦት በአራት ካህናት የሚያዝ በውስጡ ጽላት የሚቀመጥበት
ሲሆን የአሁኑ ታቦት ግን የጽላት ቅርጽ ያለው ጽሌ (ሰሌዳ) ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያኒቱ የሐዲስ
ኪዳኑን ታቦት በሦስት ስያሜ ትጠራዋለች - የቃልኪዳኑ ታቦት ፣ ጽላት እና መሠዊያ ብላ፡፡
የቃልኪዳኑ ታቦት የሚባለው እግዚአብሔር ከእስራኤል ጋር ስላደረገው ስለ ቀድሞ ቃልኪዳን
ሳይሆን ‹‹ሥጋዬን የሚበላ ደሜን የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው›› ተብሎ ስለተሠጠው እና

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 98
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

‹‹ስለብዙዎች የኃጢአት ይቅርታ የሚፈስሰው የሐዲስ ኪዳን ደሜ ነው›› ብሎ ጌታችን ስለ


ሠጠን አዲሱ ኪዳን ነው፡፡ (ማቴ. 26፡26-30) የቃልኪዳኑ ታቦት የሚባለው በሥጋ ወደሙ
ስለተሠጠን ሐዲስ ኪዳን ነው፡፡ ታቦት መባሉ ደግሞ እግዚአብሔር በረድኤት የሚያድርበት፣
በሥጋ ወደሙ ደግሞ በአካል የሚገለጥበት ዙፋን ስለሆነ ነው፡፡ ጽላት (ሰሌዳ) የሚባለው
ዐሠርቱ ትእዛዛት ተጽፈውበት አይደለም፡፡ የሕግ ሁሉ ፈጻሚ የሆነው የመድኃኔዓለም ክርስቶስ
‹‹አልፋና ኦሜጋ›› የሚለው የከበረ ስሙ በታቦቱ ላይ ስለተጻፈ ነው፡፡

(ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን /ሊቀ ካህናት ክንፈ ገብርኤል አልታዬ/ ፣ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን


ታሪክ /ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ/) አንዳንድ ሰዎች ‹‹የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ታቦት ከኦሪቱ
ጋር አይመሳሰልም›› ብለው እንደ ትልቅ መከራከሪያ ሲያውጁ ማየት እጅግ ያስገርማል፡፡ አንዴ
‹ኦሪታዊት ነሽ› አንድ ጊዜ ደግሞ ‹‹ለምን እንደ ኦሪቱ አልሆንሽም›› ብሎ ንትርክ ግራ ያጋባል፡፡
የኦሪቱን ያልመሰለው አሁን ያለነው ሐዲስ ኪዳን ላይ ስለሆነና የታቦቱ አገልግሎት የተለየ
ስለሆነ ነው፡፡ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ እንዲህ ሲሉ ያብራራሉ ‹‹የኦሪት ጽላት እግዚአብሔር
በደመና ተከናንቦ ሙሴንና አሮንን የሚያነጋግርበት ለእስራኤል ብቻ በረድኤት የሚገለጥበት
ዙፋን ነበር፡፡ ይህ ግን (የሐዲስ ኪዳኑ ታቦት) የአምላክ ሥጋና ደም የሚፈተትበት ጌታችን
ሥጋዬን የበላ ደሜን የጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው ሥጋዬን ብሉ ደሜን ጠጡ እያለ
ያመኑትን የሚጠራበት የምሕረት ምሥዋዕ (መሠዊያ) ነው፡፡ ክብርና ስግደትም የሚደረግለት
ለዚህ ነው፡፡›› (የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ ገጽ 109)

በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓት መሠረት በታቦታቱ ሁሉ ላይ የተጻፈው ‹‹አልፋና


ኦሜጋ›› የሚለው የመድኃኔዓለም ክርስቶስ ስም ነው፡፡ በተጨማሪም የእግዚአብሔር ኅቡዕ
ስሞች ታቦት ላይ ይጻፋል አልፋ፣ወዖ፣ቤጣ ፣የውጣ ፣ኢየሱስ ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር
ሕያው የሚሉ ምሥጢራዊ ትርጉም ያላቸው ስሞች ይጻፋሉ።ታቦት ሲወጣ በአክብሮት
እጅነስተን የምንበረከከው ከስሞች ሁሉ በላይ ለሆነው ታላቅ ስም ነው። ከስሙ ጋር ደግሞ
በሁሉም ታቦታት ላይ የሚከተለው ጥቅስ በግእዝ ተጽፏል፡፡ ‹‹ከመ ለስሙ ለኢየሱስ ክርስቶስ
ይስግድ ኲሉ ብርክ ዘበሰማያት ወዘበምድር›› ‹‹ይህም በሰማይና በምድር ከምድርም በታች
ያሉት ሁሉ በኢየሱስ ስም ይንበረከኩ ዘንድ›› የሚል ነው፡፡

(ፊል 2፡10) በታቦቱ ፊት የሚሰግድ ሰው ለምን እንደሚሰግድ በታቦቱ ላይ የሚጻፈው ይህ


ጥቅስ ያስረዳናል፡፡ ምክንያቱ ‹‹ጉልበት ሁሉ ለኢየሱስ ስም ይሰግዱ ዘንድ›› ስለሚገባ ነው፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 99
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

የክርስቶስ ሥጋ እንደሚቆረስ ደሙ እንደሚፈስስ የሚያምን ሰው በዚህ መሠዊያ ፊት


በፍርሃት ለክርስቶስ ይሰግዳል፡፡ ሥጋ ወደሙን ‹‹ተራ መታሰቢያ ብቻ ነው›› የሚል ሰው ግን
በመሠዊያው ፊት እንዲሰግድና መሠዊያውን እንዲያከብር አንጠብቅም፡፡ የኢየሱስ ክርስቶስን
ስም በታቦቷ ጽፋ ክብር የምትሠጥ የሐዲስ ኪዳን ቤተ ክርስቲያን ልጆች ስለሆንን
እግዚአብሔርን እናመሰግናለን፡፡ የታቦቱ ሌላ መጠሪያ የመሠዊያ ታቦት (ታቦተ ምሥዋዕ)
የሚል ሲሆን ቅዱስ ጳውሎስ ስለዚህ መሠዊያ ‹‹መሠዊያ አለን በድንኳኒቱ የሚያገለግሉ
ከእርሱ ሊበሉ መብት የላቸውም›› በማለት ስለ ሐዲስ ኪዳኑ መሠዊያ ይነግረናል፡፡

(ዕብ. 13፡10) ይህ መሠዊያ በኦሪት ድንኳን የሚያገለግሉ የአሮን ልጆች ከእርሱ ሊበሉ መብት
የሌላቸው ለእኛ ክርስቲያኖች ብቻ በመሠዊያው ያለውን ሥጋና ደም እንድንበላ የተሠጠን
ታቦተ ምሥዋዕ (Christian Alter) ነው፡፡ የታቦትን የሐዲስ ኪዳን አገልግሎት ስንናገር
የሚቃወሙ ሰዎች ከሚያነሡት ተደጋጋሚ ትችት አንዱ "ታቦት ያላት የኢትዮጵያ ቤተ
ክርስቲያን ብቻ ናት›› የሚል ነጥሎ የመምታት ጥረት ነው፡፡ በተለይም የግብፅ ቤተ
ክርስቲያንን በመጥቀስ ‹‹ግብፆች ታቦት የላቸውም›› የሚል ንግግር ይዘወተራል፡፡ ለዚህ ጉዳይ
እኛ መልስ ከምንሠጥ የራሳቸው የግብፃውያንን ምላሽ ብቻ ማስቀመጥ ይቀልለናል፡፡ ግብፃውያን
ከኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ታቦት ጋር አቻ የሆኑ ሁለት ንዋያተ ቅድሳት አሏት፡፡ አንደኛው
የመሠዊያው ጽላት (ሰሌዳ) /Alter Board/ ሲሆን ሁለተኛው ታቦት /Ark/ ነው፡፡

ቄስ ታድሮስ ማላቲ የተባሉት የቤተ ክርስቲያኒቱ እውቅ ጸሐፊ ‹‹Church The House of
God›› በተሰኘው መጽሐፋቸው ላይ ስለ የመሠዊያው ሠሌዳ (Alter Board) አሠራር ሲናገሩ
‹‹ይህ የመሠዊያ ጽላት አንድ መስቀል ወይም ብዙ መስቀሎች ይሳሉበታል ፤ አልፋና ኦሜጋ
ተብሎ ይጻፍበታል ፤ ከዚያም መዝ. 86፡1 ላይ ያለው መሠረቶቿ የተቀደሱ ተራሮች ናቸው
የሚለው የመዝሙረ ዳዊት ቃል ይጻፍበታል፡፡›› ይሉና ስለ አሠራሩ ሲናገሩ ‹‹የግብፅ ቤተ
ክርስቲያን መሠዊያው ስለሚሠራበት ቁስ የተደነገገ ሕግ የላትም ፤ እስከ አራተኛው ክፍለ
ዘመን ድረስ ከእንጨት ብቻ ይሠራ ነበር፡፡ ከዕብነ በረድና ከድንጋይም ሊቀረጽ ይችላል፡፡››
ይህንን ካሉ በኋላም እግረ መንገዳቸውን ስለ ኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ታቦተ ምሥዋዕ
ሲናገሩ፡፡

‹‹ከእንጨት የሚሠራ ታቦተ ምሥዋዕ እስካሁን ድረስ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን አገልግሎት


መሥጠቱን ቀጥሏል›› (Wooden Alters continue in use in the Ethiopian Church at

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 100
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

the present time) ብለው ያጠቃልላሉ፡፡ ይህ ስለ መሠዊያ እንጂ ስለ ታቦት አይናገርም፡፡ ስለ


ታቦት በእኚሁ ጸሐፊና በቤተክርስቲያኒቱ በኦፊሴላዊ ድኅረ ገጽ ላይ የሚከተለው ተጽፏል። "In
the middle of the Alter, there is a wooden box, called in Coptic 'pi totc' which
means 'a seat' or 'a throne', and is used as a Chalice-Stand. Usually it is
cubicle in shape, about thirty centimetres high and twenty-five centimetres wide,
the top is closed with high flaps. The beautiful carving is inlaid with ebony and
ivory and is decorated with four small icons. It can be only the Lord in the last
supper, St Mary, Archangel Michael, St. Mark and then the patron Saints. It is
called 'the Throne' for it represents the presence of the Crucified Lord. Its name
also corresponds to the 'Ark of the Old Testament', for it contained the Tablets
of Law written with the finger of God to declare God's covenant with man. The
new Ark now contains the true Blood of Christ, as the New covenant, that fulfils
the Law and the prophets. ››

(‹‹ከመሠዊያው መካከል የሚቀመጥ የእንጨት ሳጥን ሲኖር ይህ በኮፕት ቲቶት ተብሎ


የሚሠራ ሲሆን ትርጉሙም ‹መንበር› ወይም ዙፋን ማለት ነው፡፡ ጽዋው የሚቆመውም በዚህ
ላይ ነው፡፡ ቅርጹ ክበባዊ ሲሆን 13/25 ሴንቲሜትር ነው፡፡ ከላይ በጨርቅ ይሸፈናል፡፡ በጥቁርና
ነጭ ኽብረ ቀለማት ያጌጠ ሲሆን አራት ሥዕላት በዙሪያው ይደረጋሉ፡፡ ሥዕላቱ የጌታችን
ጸሎተ ሐሙስ ሥዕል የእመቤታችን ፣ የቅዱስ ሚካኤልና የሚታሰበው ቅዱስ ሥዕላት ናቸው፡፡
‹ዙፋን› ተብሎ የሚጠራው የተሰቀለው ጌታ እንደሚያድርበት በማሰብ ነው፡፡ ይህ ስያሜም
‹ከብሉይ ኪዳኑ ታቦት› ጋር የሚመሳሰል ነው፡፡ ያ ታቦት እግዚአብሔር ከሕዝቡ ጋር ያደረገው
ቃልኪዳን የተጻፈባቸው የሕግ ጽላት ያሉበት ነበር፡፡ አሁን ያለው አዲሱ ታቦት ግን
እውነተኛውን የክርስቶስ ደም የያዘ ሲሆን ክርስቶስም ሕግንና ነቢያትን ፈጽሞ አዲሱን ኪዳን
የሠጠን ነው፡፡››

ይህ ማብራሪያ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ስለ እኛ ቤተ ክርስቲያን ታቦት ከሠጡት ማብራሪያ ጋር


ምንም አይለያይም፡፡ ይህን እንደ ማሳያ ጠቀስን እንጂ ታቦቱ ዑደት ባለማድረጉ እና በሥርዓቱ
ይለያያል እንጂ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ለሥጋ ወደሙ መሠዊያ ነው ብላ ከምታከብረው
ታቦት ጋር በክብርና በአገልግሎት አቻ የሆኑ በቅብዐ ሜሮን የሚከብሩና በመንበር የሚቀመጡ
ንዋያተ ቅድሳት በሁሉም አብያተ ክርስቲያናት አሉ፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 101
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ባለንበት ዘመን በሥጋ ወደሙ እውነተኛነት ከማያምኑ ሰዎች ጋር ስለ መሠዊያው አስፈላጊነት


በመከራከር ብዙ ጊዜ ሲባክን ይታያል፡፡ የኢየሱስ ክርስቶስ ስም የተጻፈበትን ታቦት ‹ጣዖት› ነው
የሚሉ ‹ክርስቲያኖች› እያየን እንደነቃለን፡፡ ‹‹ጉልበት ሁሉ ለኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይንበርከክ››
ተብሎ የተጻፈበት ‹ጣዖት› እንዴት ይኖራል? ‹‹አልፋና ኦሜጋ›› የሚል ጣዖት አለ? ወንጌል
በላዩ ላይ የተቀመጠበት ፣ በቅብዐ ሜሮን የከበረ ፣ ሥጋ ወደሙ የሚፈተትበት ታቦት እንዴት
ጣዖት ተብሎ ይጠራል? አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ
ተብሎ በሥላሴ ስም የሚቀደስበትን ታቦት ባዕድ አምልኮ ለማለት መድፈር እንዴት
ያስደነግጣል፡፡

አንዳንዶች ‹ታቦት ተሰርቆ ተሸጠ› የሚሉ ዜናዎችን በማራገብ ታቦቱ ኃይል የለውም ሊሉን
ይሞክራሉ፡፡ እንኳን የክርስቶስ ስም የተጻፈበት ታቦት ቀርቶ ራሱ ክርስቶስ በሠላሳ ብር ተሸጦ
ከሊቶስጥራ እስከ ቀራንዮ እየተተፋበት፣ እየተደበደበ ተጎትቶ ተሰቅሎ የለምን? ክብር ይግባውና
ኃይል የለውም ሊባል ይችላል? ‹‹ታቦቱን ገልጠን እናሳያለን›› ብለው እየፎከሩ ቤተ ክርስቲያንን
ያዋረዱ የሚመስላቸው፣ በታቦቱ እግዚአብሔርን የምታመልከውን ቤተ ክርስቲያን ታቦት
ታመልካለች ብለው ያላለችውን በግድ ብላለች ብለው ድርቅ የሚሉ ሰዎች ስናይ ከማዘን ውጪ
ምን እንላለን? ቤተ ክርስቲያን ታቦትን የምትሸፍነው ስለሚፈተትበትና ስለ ሚሠዋበት
የጌታችን ሥጋና ደም ክብር እንጂ ቢገለጥ የምታፍርበት ነገር ኖሮ አይደለም፡፡ ቢገለጥ
የሚታየው የመድኃኔዓለም ክርስቶስና የቅዱሳኑ ስም ነው፡፡

ጌታዋ ዕርቃኑን በመሰቀሉ ያላፈረች ቤተ ክርስቲያን ስሙ በተጻፈበት ታቦት አታፍርም፡፡


የተከበራችሁ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ ጽድቅና ድኅነታችን በወንጌል ነው። በወንጌል ሕይወት
እየተመላለስን መንፈሳዊ ትውፊታችንን፣ ሃይማኖታዊ በዓላቶቻችንን እና የማንነት መገለጫ
ቅርሳችንን አጥብቀን ልንይዝ ይገባል። ዛሬ ሰለጠንን የሚሉት ምዕራባውያን ወንጌልን
ተረድተናል በሚል የጀመሩት የአምልኮ ነጻነት መንፈሳዊ ትውፊቶቻቸውን ጠራርጎ አጥፍቶ
ዛሬ ላይ እጅግ በሚያሳዝን ሁኔታ ትውልዱን ሥርዓት አልባ አድርገውት መንፈሳዊ መዓዛ
ተለይቷቸው በመጨረሻም አብዛኞቹ ቤተ መቅደሶች የሚያመልክባቸው ትውልድ ጠፍቶ ወደ
ጭፈራ ቤት፣ መጠጥ መሸጫና ቡቲክነት እንደተቀየሩ በአውሮፓና አሜሪካ ላይ ዓይናችን እያየ
ነው። ትውልዱም እግዚአብሔር የለም በሚል ፍልስፍና ተጠልፎ ለሰይጣናዊ አምልኮ ተጋልጦ
ይገኛል።

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 102
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ስለዚህ ሁሉን በሩቅ አጥሮ መያዝ ስለሚገባ አባቶቻችን በመንፈስ ቅዱስ ምሪት ያቆዩልንን
መንፈሳዊ ክብራችንን፣ሥርዓትና አምልኳችንን ሁሉ ጠንቅቀን ልንጠብቅ ይገባል። ክብራችንን
እያቀለልን ወንጌል ገብቶኛል ማለት ፍጹም የተሳሳተ አመለካከትና ፍጻሜው የማያምር ሕይወት
ነው። አንዳንዶች አለቦታው የሚጠቀስ ጥቅስ በመጥቀስ ታቦት ተሽሯል ሲሉም እንሰማለን ።
ይህ የሚያሳየው የግለሰቦቹ በዘመንና በትርጉም ተከፍሎ የሚጠናውን መጽሐፍ ቅዱስ
በጥልቀት አለማጥናታቸውን ነው። ቃሉ እንዲህ የሚል ነው። "በበዛችሁምጊዜ በምድርም ላይ
በረባችሁ ጊዜ፥ ይላል እግዚአብሔር፥ በዚያ ዘመን።

የእግዚአብሔር የቃል ኪዳኑ ታቦት ብለው ከእንግዲህ ወዲህ አይጠሩም፤ ልብ አያደርጉትም፥


አያስቡትምም፥ አይሹትምም፥ ከእንግዲህ ወዲህም አይደረግም። "(ትንቢተ ኤርምያስ 3:16)
ይህንን ቃል በጣም በጥንቃቄ ልናስተውል ይገባል ነብዩ ኤርምያስ በዘመኑ ለነበሩ
እስራኤላውያን ይህንን ቃል የተናገረው የሰላም ዘመን መቅረቡን ጦርነትና ስደት ከእነርሱ
መራቁን ለማብሰር ነው።እስራኤላውያን በታሪካቸው እንደምናጠናው መከራና ችግር
ሲመጣባቸው ታቦቱን አውጡልንና ይዘን እንጓዝ ይሉ ነበር አሁን እንደዚያ የምትጨነቁበት
ዘመን አይሆንም ሲላቸው ነው ነብዩ የእግዚአብሔርን የቃልኪዳኑ ታቦት ብለው አይጠሩም
ያለው እንጂ ታቦት ጭራሽ አያስፈልግም ለማለት አይደለም።

ልብ ካልን ሲጀምር በበዛችሁ ጊዜ በምድር ላይም በረባችሁ ጊዜ ብሎ የሚጀምረው ዘመነ ሰላም


እንደ ቀረበላቸው የሚያስረዳ ነው። ደግሞ በጣም ማስተዋል ያለብን ኤርምያስ የነበረው
ከክርስቶስ ልደት ስድስት መቶ ዓመታት ቀድሞ ነው ። እስከ ክርስቶስ መወለድ ይህን ሁሉ
ዘመን የእስራኤል ሕዝብና ካህናት ያለ ታቦት ኖሩ ብለን ከአምልኮ ውጭ እንደ ነበሩ ማሰብ
ትልቅ ስህተት ነው። አንዳንድ ሰዎች ደግሞ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ እኛ ነን ስለዚህ ታቦት
ማለት ማደሪያ ስለሆነ በዚህ ዘመን አያስፈልግም ይላሉ ይህ ጥራዝ ነጥቅነት ነው። የእኛ
የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያነትና የሥጋወ ደሙ መፈተቻ ታቦት ምንም የሚያገናኘው ነገር የለም።
ነገሮችን በጥንቃቄ ልንመረምርና ክብራችንን መንፈሳዊ እሴቶቻችንን አጥብቀን ልንጠብቅ
ለትውልድም ልናስተላልፍ ይገባል። መንፈስ ቅዱስ ለሁላችንም ትሑት ልቡና ያድለን።
እባካችሁ ሰዎች ከተስሳተ አመለካከት እንዲመለሱ ትምህርቱን ለሌሎችም ሼር አድርጉት።

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 103
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

6.10 አርባ አራቱ ታቦት የሚለው መነሻ ታሪክ


በሙሴ ዘመን የነበረው ታቦት አንድ ነው፤ አሁን ለምን በዛ? ጎንደር በኢትዮጵያ የመንግሥት
ታሪክ ከአክሱምና ላሊበላ ቀጥሎ ታላቋ የመንግሥት ማዕከል ነበረች፡፡ በመንግሥት ማዕከልነት
የተቆረቆረችው በአፄ ፋሲል (1624-1660 ዓ.ም) ነው፡፡ ጎንደር የመንግሥት ማዕከል ብቻ
ሳትሆን በጊዜው የመንፈሳዊ ትምህርት ማዕከልም ነበረች፡፡ በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን
የመጻሕፍት ትርጓሜና የአቋቋም ትምህርት/ዜማ/ ይበልጥ የተስፋፋውና በየሀገሩ ያሉ
ሊቃውንት በመናገሻ ከተማዋ ጎንደር በነገሥታቱ አማካይነት በመሰባሰባቸው ሲሆን ከዚያን
ዘመን ጀምሮ እስከዛሬ ድረስ መንፈሳዊ ትምህርት በስፋት የሚሰጥባት የትምህርት ማዕከል
ለመሆን ችላለች፡፡

በአሁኑ ሰዓት በሰሜን ጎንደር በሚገኙ 21 ወረዳዎች ከ2117 ያላነሱ ገዳማትና አብያተ
ክርስቲያናት ሲኖሩ በዋና ከተማዋ ደግሞ ከ92 ያላነሱ አብያተ ክርስቲያናት ይገኛሉ፡፡ በአብነት
ት/ቤት ረገድም የመጻሕፍት ጉባዔያት፣ የአቋቋም ምስክር፣ የቅኔ አብያተ ጉባዔያት እንዲሁም
የዜማ ት/ቤቶች በከተማዋ እና በዙሪያዋ በሚገኙ ወረዳዎች ይገኛሉ፡፡ በአሁኑ ሰዓት በከተማዋ
ከ92 ያላነሱ አብያተ ክርስቲያናት ቢኖሩም በአብዛኛው ስማቸው ደጋግሞ የሚነሳው የ44ቱ ብቻ
ነው፡፡ አንዳንዳን ሰዎች በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙት የአብያተ ክርስቲያናት ታቦታት ስያሜ
ብዛት ሲመስላቸው ሌሎች ደግሞ በጎንደር በጥምቀት በዓል ወደ ጥምቀተ ባህር የሚወርዱትን
ብቻ ሲሉ ይደመጣሉ፡፡ አርባ አራቱ ታቦታተ ጎንደር ከቤተ መንግሥቶቹ በተጨማሪ ታሪካዊዋ
ጎንደር የምትታወቅበት ቅርስ ነው፡፡

ጎንደር ከተማ በአፄ ፋሲል የመንግሥት ከተማ ከመሆኗ አስቀድሞ የአካባቢው ነዋሪዎች
ተክለዋቸው የነበሩ አብያተ ክርስቲያናት ነበሩ፡፡ ለምሳሌ ቀሐ ኢየሱስ፣ አርባዕቱ እንስሳ፣ አበራ
ጊዮርጊስ በምሳሌነት ይጠቀሳሉ። ጎንደር የመንግሥት ከተማ ከሆነችበት እስከ ጎንደር ዘመን
ማክተሚያ ፈፃሜ መንግሥት አፄ ተክለ ጊዮርጊስ (1772-1777) ድረስ 18 ነገሥታት የነገሱ
ሲሆን እነዚህም አብዛኛዎቹ አብያተ ክርስቲያናትን አሠርተዋል፡፡ እንግዲህ 44 የሚባሉት
አብያተ ክርስቲያናት ጎንደር የመንግሥት ከተማ ከመሆኗ አስቀድሞ የተተከሉበትን ጨምሮ
እስከ ፈፃሜ መንግሥት ተክለ ጊዮርጊስ (1772-1777) ድረስ የተተከሉትን ብቻ ሲሆን
ቁጥራቸውም 44 ነው፡፡ ከዚያ ወዲህ ከዘመነ መሳፍንት እስከ አሁን የተተከሉ በርካታ አብያተ
ክርስቲያናት ቢኖሩም ከ44ቱ የሚቆጠሩ አይደሉም፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 104
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

በአጠቃላይ አርባ አራቱ ታቦታተ ጎንደር በጎንደር ዘመን በጎንደር ከተማና አካባቢው የሚገኙና
የነበሩ 44 አብያተ ክርስቲያናት ጥቅል ስም ነው፡፡ ስለዚህ አርባ አራቱ ታቦት ሲባል ይህን
ታሪክ ተከትሎ የመጣ ስያሜ እንጂ በቤተ-ክርስትያናችን ስፍር ቁጥር የሌላቸው ታቦታት ነው
ያሉት! ምክንያቱም ሁልጊዜም አዲስ ቤተ ክርስቲያን በሚሰራበት ጊዜ ታቦት ተቀርጾ በላዩ ላይ
"ኢየሱስ ክርስቶስ አልፋ ኦሜጋ" ተብሎ ይጻፍበታል። ኢየሱስ ፊተኛውና ኃለኛው፤
መጀመሪያውና መጨረሻው ማለት ነው ፡፡ ይህ ቃል ከተጻፈበት በኋላ በሊቀ ጳጳስ እጅ ተባርኮና
ሜሮን ተቀብቶ በመንበሩ ይሰየማል (ይቀመጣል)፣ በቅዳሴም ጊዜ ሕብስቱና ወይኑ ወደ ቤተ
መቅደስ ሲገባ ቄሱ ሥርዓተ ቅዳሴውን የሚያከናውነው ሕብስቱን ሥጋ መለኮት፣ ወይኑን ደመ
መለኮት ወደ መሆን የሚለውጠው በዚህ በታቦቱ ላይ አክብሮ በሚጸልየው ጸሎት ነው ፡፡
ሥጋዬን ብሉ ደሜንም ጠጡ እያለ ያመኑትን ሁሉ የሚጠራበት የምሕረት ምሥዋዕ (መሠዊያ)
ነው፡፡ ታቦት በሐዲስ ኪዳን እውነተኛው የሕይወት ምግብ የክርስቶስ ሥጋና ደም
የሚቀርብበትና የሚፈተትበት መሠዊያ ነው። ስለዚህ ታቦት በአርባ አራት ቁጥር ብቻ
የሚወሰን ሳይሆን እልፍ አዕላፍ መሆኑን ልብ ልንል ይገባል! "ለሚጠይቋቹ ጥያቄ ሁሉ
እንዴት መልስ መመለስ እንዳለባቹ ታውቁ ዘንድ ንግግራቹ ሁል ጊዜ በጨው እንደተቀመመ
በፀጋ ይሁን" ቆላስይስ 4:6 ብዙ ጊዜ ከኦርቶዶክስ እምነት ውጪ ያሉ ሰዎች የሚያነሱት ጥያቄ
እግዚአብሔር ለሙሴ የሰጠውን ጽላት እንዲያስቀምጥበት ሥራ ያለው ታቦት አንድ ብቻ ነው
ዛሬ ግን በጣም ብዙ ነው ለምን ይሄ ሆነ? ይላሉ። ለዚህ ጥያቄ ምላሻችን ሁለት ነው።

አንደኛ እግዚአብሔር በሙሴ ዘመን ሰጥቶት የነበረው ጽላት በጊዜው ለነበረው ሕዝብ
ማምለኪያ ነው። በአንድ በተወሰነ ቦታ ተሰብስቦ በሙሴና በአሮን መሪነት ያመልክ ለነበረው
የተወሰነ ሕዝብ አንድ ታቦት በቂው ነበር። ሕዝብ ሲበዛና እግዚአብሔርን የሚያመልከው አማኝ
በየቦታው ሲሰፋ ግን ጽላቱን ማብዛት የግድ ነው።ለዚህም ነው እግዚአብሔር ለሙሴ እኔ
የሰጠሁህን ዓይነት ጽላት ቅረጽ ብሎ ፈቃድ የሰጠው ዛሬም እንደ ሙሴ ያሉ የሃይማኖት
አባቶች ይህንን ቅዱስ ንዋይ ያዘጋጃሉ። "ጽላቶቹም የእግዚአብሔር ሥራ ነበሩ፤ ጽሕፈቱም
በጽላቶች ላይ የተቀረጸባቸው የእግዚአብሔር ጽሕፈት ነበረ።" (ኦሪት ዘጸአት 32:16) "
እግዚአብሔርም ሙሴን አለው። ሁለት የድንጋይ ጽላቶች እንደ ፊተኞች አድርገህ ጥረብ።"
(ኦሪት ዘጸአት 34:1)

ሁለተኛው ምክንያት፤ ታቦታትን ማብዛት መጽሐፍ ቅዱስን ከማብዛት ጋር ተመሳሳይ በመሆኑ


ነው። መጽሐፍ ቅዱስ ጥንት ሲዘጋጅ አንድ ብቻ ነበር። ዛሬ ግን በቢልየን ደረጃ ያውም

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 105
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

በተለያዩ ቋንቋዎች ተዘጋጅቶ በዓለም ዙሪያ ተባዝቶ ይገኛል። መጽሐፍ ቅዱስ ለምን በዛ?
የሚል ጠያቂ ካለ መልሱ አጭርና ግልጽ ነው። እግዚአብሔርን የሚያመልከው ሕዝብና በቃሉ
ሕይወት ማግኘት ያለበት አማኝ ስለበዛ መጽሐፉም ተባዝቷል። ይህንን ማድረግ ደግሞ ምንም
ስህተት የሌለበት የተቀደሰ ተግባር እንደሆነ ሁሉ። ታቦታት ቢብዙና እግዚአብሔርን
የሚያመልከው ሕዝብ ባለበት፣ አብያተ ክርስቲያን በታነጸበት ቦታ ሁሉ ቢቀመጥ ስህተት
አይደለም። ታቦት አይመለክም የምናመልከውና የምንሰግደው በታቦቱ ላይ ለተጻፈው አልፋና
ኦሜጋ ለሆነው በደሙ ቤዛ ለሆነን ጌታ ለኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 106
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

7. ምሥጢረ ተክሊል
መግቢያ

ቤተ ክርስቲያን ልጆቿ ለእግዚአብሔር መንግሥት ለመብቃት በሚያደርጉት መንፈሳዊ ጉዞ


ሁለት የኑሮ አማራጮች አቅርባላቸዋለች፡፡ አንደኛው ፍጹም የሆነ የድንግልና ሕይወትን ጠብቆ
በመኖር የሚገባበትና በተጋድሎ የሚኖርበት የምንኩስና ሕይወት ሲሆን ሁለተኛው በተቀደሰ
ጋብቻ ክብደ ዓለምን በመቋቋም እየተጋገዙ የሚጓዙበት ሕይወት ነው፡፡

7.1 ሥራዓተ ተክሊል


በመተጫጨትና በቃል ኪዳን የተመሰረተው ጋብቻ በተክሊልይፈጸማል፡፡ ክርስቲያናዊ ጋብቻ
ትክክለኛነቱ የሚታወቀው በተክሊልና በስጋወደሙ ሲፈጸም ነው፡፡ ተክሊል ማለት አከበረ ፤
ከለለ ካለው ግስ የወጣ ቃል ነው፡፡ ይኸውም ክቡር ማለት ነው፡፡ ጋብቻ በቤተ ክርስቲያን
ውስጥ በቃል ኪዳንና በቡራኬ በጸሎተ ተክሊልና በቅዱስ ቁርባን ሲፈጸም ምስጢር አለው፡፡
በሚታይ ምልክቶችና ስርአቶች የማይታይ ጸጋ እናገኝበታለን፡፡ ኤፌ 5፤32

ይህ ማለት “ተከለለ” ተቀናጀ ከሚለው የግዕዝ ግስ የተገኘ ነው፡፡ በሥርዓተ ጋብቻ ቅደም
ተከተል መሰረት በመተጫጨት እና በቃል ኪዳን የተመሰረተ ጋብቻ በተክሊል ይፈጸማል፡፡
ቤተክርስቲያን ምስክርነት የሚፈጸመው ጸጋ መንፈስ ቅዱስን የሚያሰጥ ስለሆነ ነው፡፡
ክርስቲያናዊ ጋብቻ ትክክለኛነቱም የሚታወቀው በተክሊል ሥጋወ ደሙ ሲፈጸም ነው፡፡
ክርስቲያናዊ ጋብቻ ትክክለኛነቱም የሚታወቀው በትክሊል ሥጋወ ደሙ ሲፈጸም ነው፡፡ ዘፍ 1፡
27-28 ፣ 2-18 ማቴ 19-4 እነዚህን ምሥጢራተ ቤተክርስቲያን አውቀን ተረድተን
የእምነታችን ፍጻሜ የሆነውን አምላካችንን ለተፈጠርንለት ዓላማ በመገዛት የነፍሳችንን መዳን
ልናረጋግጥ ይገባል፡፡

በሁለት ክርስቲያኖች በአንድ ወንድና በአንዲት ሴት ፈቃድ በቤተሰቦቻቸውም መልካም ፈቃድ


ለሚደረግ ጋብቻ ቤተክርስቲያን የምትፈጽመው ሥርዓት ነው፡፡ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኝ ፣
ደናግላን እና በዝምድና ሰባት ትውልድ የራቁ መሆን አለባቸው ፡፡ የሚፈጸመውም አንድ ጊዜ
ብቻ ነው፡፡

ለዚህም ቸሩ አምላካችን እግዚአብሔር እንዲረዳን የወላዲተ አማላክ አማላጅነት እንዳይለየን


የጻድቃን ፀሎት የቅዱሳን በረከት እንዳይለየን ፈቃዱ ይሁንልን አሜን!!!

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 107
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ምሥጢረ ቁርባን ማለት ክርስቶስ ስለ እኛ ኃጢአት በመስቀል ላይ መሥዋዕት ሆኖ በሥጋው


በመሞቱ የዓለምን ኃጢአት ያስወገደበት፣ የዘላለም ሕይወትን ያሰገኘበት፣ የመዳናችን
መሠረት፣ የጸጋችን ሁሉ ምንጭ የሆነውን የቅዱስ ሥጋውንና የክቡር ደሙን የማዳን ጸጋ
የሚያመለክት ታላቅ የክርስትና ሃይማኖት ምሥጢር ነው።

7.2 የምሥጢረ ተከሊል የቃሉ ትርጉም


ተክሊል ከለለ ጋረደ ካለው የግዕዝ ግሥ የተገኘ ነው። ተክሊል ማለት መከለል፣ መወሰን፣
መጋረድ፣ መለየት፣ ማለት ሲሆን። በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ለሚጋቡ ምዕማናን
የሚፈጸምላቸው ሥርዓት ነው። ጋብቻ በሰው ልጆች ታሪክ ውስጥ የመጀመሪያው ሲሆን
እግዚአብሔር ወንድና ሴት አድርጎ ከፈጠራቸው በኋላ ምድርን ሙሏት ብሎ አዘዛቸው። ዘፍ 1:
27 ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ሴትና ወንድ በጋብቻ እየተሳሰሩ ልጆችን በመውለድ መባዛት ጀመሩ።

7.3 የምሥጢረ ተክሊል አመሠራረት


እግዚአብሔር አምላካችን ጋብቻን በአዳምና በሔዋን መካከል ሲመሠርት አንድ ወንድ ላንዲት
ሴት፥ አንዲት ሴትም ለአንድ ወንድ ብቻ መሆኑን በተግባር ገልጾልናል፡፡ ይህም ለክርስቲያናዊ
ጋብቻ ቋሚ የዘለዓለም መመሪያ መሆኑን በሚገባ ማስተዋል ይገባል። ጋብቻውም
የተመሠረተው በተመሳሳይ ጾታ መካከል ሳይሆን በሁለት ተቃራኒ ጾታዎች መካከል መሆኑንም
ያሳየን ራሱ እግዚአብሔር ነው። /ዘፍ፪፥፲፰-ፍጻሜ፡፡) ግብረ ሰዶማውያን ለሚያነሱት መሠረት
የለሽ ጥያቄ ይህን ከሰብአዊ ተፈጥሮአችን አኳያ መመርመር በራሱ መልስ ይሰጣል። የጋብቻን
መሠረታዊ ዓላማዎች የተመለከትንም እንደሆነ ሦስት መሠረታዊ (ዐበይት) ነጥቦችን
ያስታውሰናል። ይህ የተቀደሰ የጋብቻ ሥርዓት /ምሥጢረ ተክሊል/ ሙሽራይቱንና ሙሽራውን
ከሥጋዊ ሕይወት ለመውጣትና ወደ መንፈሳዊ ሕይወት ለመድረስ የሚያደርጉትን ጉዞ የተቃና
በማድረግ ሦስቱን ዓላማዎች ጠብቀው እንዲጓዙ ያስችላቸዋል።

አንዳንዶች እንደሚመስላቸው ይህ ምሥጢር ለሙሽራይቱና ለሙሽራው ጊዜያዊ የሆነ ሥጋዊ


ፍላጎት መፈጸሚያ፣ ለሰው ፊት መታያና ለቀረፃ ማሳመሪያ የሚውል የካሜራ ፍጆታ
አይደለም፡፡ ዕጮኞሞች ሳይገባቸውና ሳይገባቸው (“…ገባ አንዱ ጠብቆ አንዱ ላልቶ ይነበብ)
ከማን አንሼ በማለት የሚገቡበት ኑሮም አይደለም። ተገቢውን የክርስትና ትምህርት የወሰዱ
ወደፊት የምንገልጠውን የጋብቻ መስፈርት የሚያሟሉና ሦስቱን የጋብቻ ዓላማዎች
ተረድተውና አምነው የወሰኑ ዕጩዎች /ጥንዶች/ የሚፈጽሙት አንድነት ነው።

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 108
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

በጋብቻ አመሠራረት ሂደት “እግዚአብሔር አምላክም አለ፦ ሰው ብቻውን ይኖር ዘንድ መልካም
አይደለም፤ የሚረዳውን ጓደኛ እንፍጠርለት እንጂ።” (ዘፍ ፪፥፲፰፡፡) የሚለው ኃይለ ቃል መነሻና
መሠረት ነው። ይህም የጋብቻ መሥራቹና ፈቃዱ እግዚአብሔር መሆኑንና የተመሠረተውም
በመጀመሪያዎቹ አባታችንና እናታችን /በአዳምና በሔዋን/ መካከል እንደነበር ያስረዳል፡፡
“ምሥጢረ ተክሊል” በሐዲስ ኪዳን የተሰጠው መጠሪያ ስም ነው። ተክሊል “ከለለ” ከሚለው
የግእዝ ግስ የሚወጣ /የሚገኝ/ ሲሆን ትርጉሙም ጋረደ ፣አጠረ፣ ከበበ፣ አከበረ፣ አጀበ፣ ፈጽሞ
አስጌጠ፣ ሸለመ፣ አክሊል አቀዳጀ፣ ማለት ነው።

ምሥጢረ ተክሊል በሰፊው ሲብራራ ደግሞ የሙሽራውንና የሙሽራይቱን የጋብቻ ቃል ኪዳን


በሃይማኖት የሚያጸና፣ የጋብቻ ግዴታን ለመወጣት የሚያስችል፣ በፍቅር የሚያስተሳስርና
ዘላቂ አነድነትን የሚያስገኝ የጸጋ ምሥጢር ነው፡፡ የሚሰጠውም ምንጊዜም ቢሆን እንደሌሎቹ
ምሥጢራት ከቅዱስ ቁርባን ጋር ነው። ይህ የጋብቻ ሥርዓት፣ የጋብቻ ኪዳን፣ ስምምነትና
ውል በታወቀ በቂ ማክንያት ካልሆነ በቀር ፈጽሞ የማይፈርስ ጽኑዕ አንድነት ነው። ቅድስት
ቤተክርስቲያን ለሙሽራው /መርዓዊ/ እና ለሙሽሪት /መርዓት/ የምትፈጽመው ይህ መንፈሳዊ
የጋብቻ ሥርዓት በክርስቶስና በቤተ ክርስቲያን መካከል ላለው ጽኑዕ አንድነትና ዘላለማዊ ፍቅር
ምሳሌ የሚሆን /የሆነ/ ታላቅ ምሥጢር ነው። (ኤፌ ፭፥፴‐፴፫፡፡)

በሐዲስ ኪዳንም ዘመን መጀመሪያ አካባቢ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በገሊላ ቃና በተዘጋጀው
የጋብቻ ሥርዓት ላይ በመገኘት ክርስቲያናዊ ጋብቻን አክብሯል። በዶኪማስ ቤት ከእናቱ
ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያምና ከደቀ መዛሙርቱ ከሐዋርያት ጋር ተገኝቶ ጋብቻን
ፈጽሞ ባርኮታል። የታወቀና የተገለጠ የመጀመሪያ ተአምሩንም በእመቤታችን ምልጃ የፈጸመው
በዚሁ ሰርግ ቤት መሆኑ ይታወቃል። (ዮሐ ፪፥፩‐፲፪፡፡)

7.4 የጋብቻ አመሰራረት


ጋብቻ ከሕግጋተ እግዚአብሔር አንዱ ነው፡፡ ስለሆነም ጋብቻ በኦሪትም ፤ በወንጌሌም ሕግ
ተሰርቷል፡፡ እግዚአብሔር በድንግልና ሊኖሩ ከፈለጉ ሰዎች በቀር ሁሉ በጋብቻ እንዲኖር
ጥንቱን በአዳምና በሔዋን ጋብቻን መሰረተ፡፡ ዘፍ 2፤18፡፡ የአዳምና የሔዋን ጋብቻ የሕጋዊ
ጋብቻ መሰረት ነው፡፡ ለአዳም ብዙ ሴቶች አለመፈጠራቸው፣ አንድ ወንድ አንድ ሴት እንጂ
አያሌ ሴቶች አለመፈቀዳቸውን ፤ ለሔዋንም እንዲሁ መሆኑን ያመለክታል፡፡ ጋብቻ
ከእግዚአብሔር የተሰጠ ህግ በመሆኑ ማንም ሰው ሚስቱን እዳይፈታ በኦሪትም ሆነ በወንጌል

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 109
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ተከልክሏል፡፡ ይህም በመሆኑ በኦሪት የነበሩ ሰዎች ሚስቶቻቸውን በመርዝ ፣ አፍ በማፈንና


ልብን በማሸት መግደል ጀመሩ፡፡ ይህ ክፋታቸው እየበዛ በመሔዱ ሙሴ የጋብቻን ህግ
የማሻሻል ተገደደ ፤ የተሻሻለው ህግ ፍቺን ሚፈቅድ ሲሆን ስርዓቱ ግን ጠበቅ ያለ ነበር፡፡ ባል
ሊፈታት ከፈለገ በደብዳቤ ፅፎ በአደባባይ አንብቦና ነውሯን አጋልጦ እንዲፈታት ሙሴ በኦሪት
ስርዓት ሠራ፡፡ በሐዲስ ኪዳን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ጋብቻ ፈሪሳውያን ጠይቀውት
ሲያስተምር ‹‹እግዚአብሔር አንድ ያደረገውን ሰው መለየት ስለማይገባው ባሌ በማናቸውም
ምክንያት ሚስቱን ሊፈታ አይገባውም›› ባላቸው ጊዜ የሙሴን ህግ አንስተው በጥያቄ መልክ
አቀረቡለት፡፡ እሱም ሙሴ ሕጉን ያሻሻለው ስለሌባቸው ክፋት እንጂ ቀድሞ እንዲህ አሌነበረም
፤ ካላመነዘረች በስተቀር ማንም ሰው ሚስቱን እንዳይፈታ የተፈታችውንም እንዳያገባ ጌታችን
በወንጌል አዘዘ፡፡ ዘፍ 1፤27 ፣ ዘፍ 2፤24 ፣ ዘዳ 2፤4 ፣ ማቴ 19፤3-12 ፣ ማቴ 5፤31-32

7.5 የጋብቻ ዓላማዎች

ሀ. ለመረዳዳት፡- “ሰው ብቻውን ይሆን ዘንድ አግባብ አይደለም የሚመቸውን ረዳት እንፍጠርለት
። ዘፍ 2 ፥ 18 ።” ብሎ እግዚአብሔር እንደተናገረ ፤ ሰው በኑሮው ሁሉ እንዳይቸገር
የውስጡን ሀሳብ የሚያካፍለው ፣ ችግሩን የሚጋራውና ራሱን የሚወክልለት የህይወት አጋሩን
እየመረጠ ጋብቻ ይመሠርታል ።

ሀ. ዘር መተካት፦

እግዚአብሔር አምላክ ባዘዘው (በፈቀደው) መሠረት የመጀመሪያው የጋብቻ ዓላማ ልጆችን


መውለድ ዘርን መተካትና ማብዛትና ትውልድ እንዲቀጥል /እንዳይቋረጥ/ ማድረግ ነው። (ዘፍ፩፥
፳፯፡፡) አዳምን ያለዘርና ያለልደት ከዐራቱ ባሕርያተ ሥጋና ከሦስቱ ባሕርያተ ነፍስ የፈጠረው
እግዚአብሔር ከአዳም ጎን አንዲት አጥንት ነሥቶ ፈጠራት ቀጣዩ የሰው ልጅ ትውልድ ግን
ከጋብቻ ፍሬ (ከዘር ከሩካቤ በሚገኝ ውጤት) ላይ የተመሠረተ እንዲሆን ፈቀደ። በዚህም
መሠረት ጥንዶቹ (ወላጆች) ልጆችን በመውለድ የእግዚአብሔር ሥራ፣ ፈቃድና ትእዛዝ
ተባባሪዎችና ፈጻሚዎች ይሆናሉ ማለት ነው። ትዳርን አማራጫቸው ያደረጉ ክርስቲያኖች
ሁሉ ይህንን ትእዛዘ እግዚአብሔር ማክበር ይኖርባቸዋል።

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 110
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ለ. እርስ በርስ መረዳዳት፦

ሁለተኛው የጋብቻ ዓላማ (አስፈላጊነት) ባለ ትዳሮቹ በኑሮአቸው ሁሉ እርስ በርሳቸው


መረዳዳት እንዳለባቸው የሚገልጸው ነው። ይህንንም ትእዛዝ የሰጠው እግዚአብሔር አምላካችን
ነው፡፡ (ዘፍ፪፥፲፰‐፳፭፡፡) ሔዋንን ከመፍጠሩ በፊት የተናገረው ኃይለ ቃል የአዳምና የሔዋን
ተግባር አንዱ ለሌላው ምቹ ረዳት መሆን እንደሚገባው የተገለጸበት ነው። እሱ እግዚአብሔር
የባረከው ትዳር ስለሆነም አዳምና ሔዋን በዘመናቸው ሁሉ እየወደቁ እየተነሡም የሚረዳዱና
የሚደጋገፉ ሆነዋል፡፡ ባለትዳሮች እርስ በርሳቸው በመረዳዳትና በመደጋገፍ ካልኖሩ የዚህን
ዓለም ከባድ የኑሮ ቀንበር መሸከም አይችሉም። በዚህ ዓለም የሚፈራረቀው ውጣ ውረድ፣
መከራም ሆነ ደስታ በተናጠል አይገፋም። ጋብቻ የመሠረቱ ክርስቲያኖች ሁሉ ቅድስናቸውን
ጠብቀው በረድኤተ እግዚአብሔር፣ በድንግል ማርያም አማላጅነትና በቅዱሳን ሁሉ ጸሎት
ተጠብቀው በፍቅርና በአንድነት ጸንተው እየተረዳዱ መኖርን መዘንጋት የለባቸውም። ጋብቻ
ያልመሠረቱ ክርስቲያን ወጣቶችም ዓላማው ገብቷቸውና በዚህ መንፈስ ተቃኝተው ከወዲሁ
ራሳቸውን ለቅዱስ ጋብቻ ማዘጋጀት አለባቸው።

ሐ. ከዝሙት ጠንቅ ለመዳን፦

ጋብቻ ቅድስናውን ጠብቆ እንዲዘልቅ የሥጋ ፍትወትን (ፍላጎትን) መቆጣጠር ወሳኝነት አለው።
ይህ ደግሞ የጋብቻ ዓይነተኛ ዓላማ ነው። በዝሙት ጠንቅ ከሚመጣው የሥጋ ደዌ /በሽታ/፣
የመንፈስ ጭንቀት፣ የትዳር መናጋትና የልጆች መበተን የሚዳነው ይህን ዓላማ በአግባቡ
በመረዳትና በማስተናገድ ነው፡፡ ስለዚህም ፈቃደ ሥጋ ከጥንዶቹ በአንዳቸው በጸና (በተነሣ) ጊዜ
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እንዳስተማረው በጸሎት ለመትጋት እንዲቻል ለጊዜው በመስማማት
ካልሆነ በስተቀር እርስ በርሳቸው እንዳይከላከሉ ቤተ ክርስቲያን ታስተምራለች። (፩ቆሮ፯፥፩‐፯፡፡)
በዚሁ በተጠቀሰው ምዕራፍ ውስጥ የምንማረው ሌላው ቁም ነገር በምኞት ከመቃጠል እና
ተያያዥ ከሆኑ ችግሮች ሁሉ ለመዳን ጋብቻ ፍቱን መድኃኒት መሆኑን ነው። ጋብቻ በመሠረቱ
ጥንዶች መካከል የሚደረግ ተራክቦም ከጋብቻ በፊትና ከጋብቻ ውጪ እንደሚደረገው ግብረ
ሥጋ ግንኙነት የረከሰና ፈጻሚዎቹንም የሚያረክስ አይደለም። (ዕብ፲፫

7.6 ወጣትነትና ስሜቶቻቸው


የወጣቶች ስብዕና ላይ ሰሜት ኃይለኛ ጉልበት አለው፡፡ ስሜት ደግሞ በመከተሉ ሁለት ነገሮች
በአንዱ ካልተወሰኑ መረጋጋት አያገኝም፡፡ መንፈሳችንና አዕምሮችንን ለእግዚአብሔር ሲገዛና

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 111
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

እና ስሜቶቻችን እና ቁሳዊ ፍላጎታችንን በልክ ስናደርግ መረጋጋት እናገኛለን፡፡ የወጣትነት


ዘመን ዕድሜ ከስንት እስከ ስንት እንደሆነ በተለያዩ ሰዎች የሚለያያ ቢሆንም በቅድስት ቤተ
ክርስቲያን አስተምህሮ ለአቅመ አዳምና ለአቅመ ሔዋን ማለትም ከ15 ለወንዶች 18 በላይ
ይባላል፡፡ በወጣትነት ዘመን ምኞት፣ ከመንፈሳዊነት መራቅን፣ ስጋዊ መሆንን የሚያይልበት
ወቅት ነው፡፡ ይህም ደግሞ እኩይ ፍትወት ይባላል፡፡ 2ጢሞ 2፡22 ከክፉ የጎልማሳነት ምኞት
ነው፡፡ የወጣትነት ዘመን የሚመኙበት ሳይሆን የሚሰሩበት ዘመን ነው፡፡ ያዕ 1፡14 ነገር ግን
ሰው በራሱ ምኞት ሲሳብና ሲታለል ይፈተናል እንጂ እግዚአብሔር በክፉ አይፈትንም፡፡ በዚህ
ወቅት ወጣቶች በርካታ አካላዊና ስነ ልቦናዊ ለውጦች ያስተናግዳሉ፡፡

በወጣትነት ሁሉም ነገር ያምራል ሀብት፣ ትዳር፣ ትምህርት፣ መታወቅን 1ጲጥ 4፡1-2 እንደ
እግዚአብሔር ፈቃድ እንጂ እንደ ሰው ምኞት እንዳትኖሩ፡፡ በወጣትንነት ጊዜ ያሉ ለውጦች
ስንመለከት ጠባያዊ ለውጦች፣ የአስተሳሰብ፣ የስሜት፣ የሀሳብ፣ የፍላጎት ለውጦች ይይዛል፡፡
በተጨማሪም ለተቃራኒ ጾታ የሚኖረው ፍላጎት (አመለካከት) ጎልቶ ይታያል፡፡ እነዚህ
ስሜቶችም ይሁን ለውጦች በራሳቸው ችግር አይደሉም ስነ ተፈጥሯዊ ናቸውና ነገር ግን ሰው
አካላዊ ዕድገቱን ከወጣትነት ደረጃ ደርሶ እነዚህ ለውጦች ላይ ሲደርስ መንፈሳዊ ዕድገቱን
ቀጫጫ ከሆነ(ከተመናመነ) ወይም አካላዊ እድገቱን በአግባቡ መምራት የሚችልበት ደረጃ
ካልደረሰ ሰው ሰውነቱ ቀርቶ እንስሳዊ ወደ መሆን ደረጃ ላይ ይደርሳል ማለት ነው፡፡ አንድም
በሁለቱም ጾታዎች ውስጣዊ ተግዳሮቶች መካከል ደግሞ የሚከተሉትን የጠባይ ለውጦች
በእዚህ በወጣትንት እድሜ ይከሰታሉ፡፡

የስሜት መረበሽና በቀላሉ መጨነቅ፣ የተረጋጋ አመለካከት ማጣትና መዋዠቅ፣ ነገሮችን


ከሚገባው በላይ ችላ ማለት፣ ስለ ራስና ስለ ሌሎች የተዘበራረቀ አመለካከት መኖር፣ በቀላሉ
በጓደኛ ግፊት መጋለጥ ፣ ትኩረትን መሻት፣ በዐይን ፍቅር መሻት፣ ሲወደሱ በቀላሉ መደሰት
ሲነቀፉ ደግሞ በቀላሉ ማዘን፣ ቅብጥብጥነት (ፋሽን መከተል)፣ ሩቅ ነገር አርቆ ለመጨበጥ
መሞከርና ሲያጡ በቀላሉ ተስፋ መቁረጥ እንዲሁም ብዙ ነገሮች ለመሞከር መጣር፣ በመርኃ
ግብር ያለ መመራት (ጊዜን በአግባቡ አለመጠቀም)፣ ለትምህርት ትኩረት ካለመስጠት የውጤት
መዋዠቅ፣ በመንፈሳዊ ሕይወት መዛል እና በአገልግሎት ትጋት መቀነስ፣ ራስን ዝቅና ከፍ
አድርጎ መመልከት ናቸው፡፡ እነዚህም ለውጦች የሰራው እግዚአብሔር ነው፡፡ ለሰው ልጆች
አነዋወሩም ሕግ የሰጠ እራሱ ነው፡፡ የጓደኛ ተጽዕኖ አካባቢ እና የተሳሳቱ ትምህርቶች
አስተሳሰቦች ዋነኞች ናቸው፡፡ በእነዚህም ለውጦች ግፊት ምክንያት ያልተፈለጉ ድርጊቶች

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 112
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ውስጥ ሊገባ ይችላል፡፡ ምክንያቱም ሕጉንና የሰው ልጅ ተፈጥሮ አይጣላም ይስማማል


ይገናዘባል እንጂ ፡፡ አንድም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በመዋዕለ ስጋዌ
ካስተማረን ነገሮች አንዱ በጥቂቱ ማደግን ነው፡፡

7.6.1 የዐፍላ ጉልምስና ምልክቶች

 ይህ ወቅት በፆታ የመብሰል ምልክቶች ይታዩበታል፡፡


 የአጥንቶች እድገትና የጡንቾች መለጠጥ የቅንብር ጉድለቶች ይስተዋላሉ፡፡
 የአዳም ፍሬ በመባል የሚታወቀዉ (ማንቁርት) አድጎ ይታያል፡፡
 የድምፅ ጅማቶች ሳይታሰብ ቀጭን ማዉጣትና የድምፅ መጎርነን
 ብጉር የሚያበጉሩ አሉ
 በብብት፣በደረት፣በብሽሽት (የአባላ ዘርዕ) አከባቢ ጸጉር ማብቀል
 ከራስ እስከ ጽሕም በግራና በቀኝ የሚወርድ ለጊዜዉ ለስለስ ያለና ስለ ጠጉር(ሪዝ)
ማቆጥቆጥ ሴት እስኪመስሉ ልጭት አድርጎ ማንሳት አይገባም፡፡ "ነገር ግን ጽሕማችንን
ስንላጭ የወንድነት መልካችንን ወደሌላ ማለትም ሴት ወደ መምሰል እንለወጥ ዘንድ
አይገባንም፡፡" ፍት. ነገ 11
 የሰዉነት ጠረን መለወጥ
 የዘር ፍሰት (ሕልመ ሌሊት) ማየት መጀመር

7.6.1.1 ሕልመ ሌሊት

በአፍላ ጉልምስና ወቅት አባለ ዘርዕ ወደ ሙሉ የእድገት ደረጃ መድረስ ብቻ ሳይሆን


መሥራትም ይጀምራል፡፡ ከንዑስ መሌሊት (ኀፍረተ አካል) ዘርዓ ብእሴ የሚባል የአፍንጫ
ዘመል(ንፍጥ) የሚመስል ፍሳሽ ነገር ነዉ፡፡ ወንድና ሴት ግንኙነት በሚያደርጉበት ጊዜ ወደ
ሴቲቱ ማኅፀን በመግባት ፅንስ እንዲፈጠር የሚያደርግ ፍሳሽ ንጥረ ነገር ነዉ፡፡ ለዘር የበቁ
ወጣቶች ተንተዉ ሳለ በተለቀ እንቅልፍ ሆነዉ ሕልም በሚያልሙበት ወቅት ይታያቸዋል፡፡
የዚህ ዓይነት ሕልም ሕልመ ጽምረት (የመስቆርርት ሕልም) ይባላል፡፡ ሕልሙን ያየ ሰዉ
ዝንየት መታኝ (ሕልመ ሌሊት) አገኘኝ ይላል

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 113
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

7.6.1.2 ሕልመ ሌሊት ኃጢአት የሚሆነዉ መቼት ነዉ

አጋንንት የሰዉን ልጆች በልዩ ልዩ መንገድ በክፋት ይወጋቸዋል፡፡ የሰዉ ልጆች


ሲያንቀላፉ አጋንንት ግን ለቅጽበት እንኳን አያሸልብም፡፡
አጋንንት የሰዉን ልጅ በተኛበት ክፉ ሕልም ምትሐት በማሳየት ይፈትኑታል፡፡
 የተራቆተ የሴት ገላ በማሳት
 ወንድና ሴት አለሌና ባዝራ እየሆኑ ሲጫወቱና ሲደራረጉ
ከዚህም የተነሳ እርሱም በዝሙት ሐሳብ ይሳብና በሕልሙ ዝሙት ፈጽም ያድራል፡፡
ይህ ድርጊት ጸዋግ (ኅሡም) ሕልም ይባላል፡፡ ክፉ(ጥፉ) ሕልም ማለት ነዉ፡፡ መጽሐፈ
መነኮሳት "ሰይጣናት የሰዉ ልጅ ቀን ቀን ክፉ ሐሳብ በማሳሰብና በማሠራት በሌሊት
ደግሞ ዝሙት የሞላበት አጸያፊ ሕልም ለማሳየት ይዋጉታል፡፡"
ሰይጣናት ያቀረቡለት ረቂቅ ፈተና ከመቃወም ይልቅ ደስ እያለዉ የሚያጣጥም፡፡
ከመደሰትና ከመቆጨት ይልቅ በደስታ ስለ ዝሙት በደስታ የሚያሰላስል
የሚዳራ፣የሚዛለል
ወደ ዝሙት ከሚያመሩ ማናቸዉም ነግር የማይሸሽ
እነዚህ ነቅቶ ሳለ ያልተቃወማቸዉን ያህል ኃጢአት ሆነዉ ይቆጠሩበታል፡፡
"በቀን ነቅቶ ሳለ ኃጠአትን ወደ ሚቀበልና ገልጾ የማይናዘዛት ለዚያ ሰዉ የረከሰች ሐሳቡ
ሕልሙ ኃጢአት ሆና ትቆጠርበታለች፡፡"
"በንስሐ ሥራ የማይደክም (ንስሐ የማይገባ) በቀደመዉ ኃጢአቱ እግዚአብሔርን ይቅር
በለኝ የማይለዉ ለዚያ ሰዉ የሚያጸይፍ ሕልሞች ዕዳ በደል ሆነዉ የቆጠሩበታል፡፡"
ከሥራ ብዛት ሕልም ሊታይ ይችላል
መክ 3 "ሕልም በስራ ብዛት ይታያል"
ከምኞት ብዛት ሊከሰት ይችላል፡፡ ክፉ ምኖት በሕልምም ቢሆን ያረክሳል
ይሁ 1÷8 "እያለሙ ሥጋቸዉን ያረክሳሉ"
አብዝቶ በመመገብ የሚከሰት ሕልመ ሌሊት ሐጢአት ይሆናል
መዝ 103÷15"እኅልም ጉልበትን ያጠነክራል" ለቁመተ ሥጋ ያህል ብቻ መመገብ
አለበት፡፡
 ለሥጋ መገዛት የሚሻዉንም ሁሉ ጥሮ ግሮ ማቅረብ የገዛ ሰዉነትን ማምለክ
ነዉ፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 114
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

 በሰዉነት ላይ የዝሙት ፆር ጸንቶ ሳለ አብዝቶ መመገብ የሚቃጠል ክርን ሰም


እንደመቀባት ነዉ፡፡ መ. መነኮሳት “አብዝቶ መመገብ ከወጣትነት ጋር የሐጢአት
ሐሳብን በግድ እንዲመጣ ያደርጋል"
 አብዝቶ መመገብና ለመብል መሳሳት የኃጢአት ምንጭና ኃጢአት ሆነዉ
ይቆጠራሉ፡፡ ሕዝ 16÷49"እነሆ የእህትሽ የሰዶም ኃጢአት ይህ ነበር ትዕቢት፣
እንጀራ መጥገብ፣መዝለልና ሥራ መፍታት በእርሷና በሴቶች ልጆቿ ነበር"
 ሳይጠነቀቅ ቀርቶ አብዝቶ ከመመገቡ የተነሣ ኅልመ ሌሊት ያገኘዉ ሰዉ እንደ
ኃጢአት ይታሰብበታል፡፡ ማር የሳቅ 20÷2 መ. መነኮሳት "ከሰዉነቱ እንደ
ምነጭ የሚነቃ ርኩስ ዘር በዝቶ ሳለ ፈሰሰ ጎስቋላ ምንጣፉ፣ልብሱ፣በዝሙት
ደስ ተሰኘ ሥጋዉ፣ ሁለንተናዉ የረከሰ ነዉ፡፡ ሥጋ ሁልጊዜ ያነቃዋልና ዘር
የሚፈሰዉ በሌሊት ብቻ አይደለም፡፡ ሕሊናዉንም ያረክሰዋል፡፡"
አንድ ሰዉ በንቁ ልቡና ሳለ ወደ ኃጢአት የሚመሩትን ነገሮች ተግቶ እየተቃወመ ነግረ ግን
በተኛና ባንቀላፋ ጊዜ ዝንየት ቢገኘዉ በተራክቦ፣ ዘር በማፍሰስ ያት ሕልሙ ዕዳ ሆና
አትቆጠርበትም፡፡ ሰይጣን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን፡-የኔን ወገኖች አጋንንት
ባንተ ወገኖች ላይ አሰለትናቸዋለዉ፣ነገር ግን ወገኖቼ የአንተን ወገኖች አይችሏቸዉምና ድል
ይሆናሉ፡፡ እነርሱ ምንም ባችሏቸዉ እኔ ግን "በሕልመ ሌሊት አስሕቶሙ" (በሕለመ ሌሊት
አስታቸዋለሁ) አለዉ፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደግሞ ሲል መለሰለት "ጭንጋፍ አባቱን
ለመዉረስ ከቻለ ሕልመ ሌሊትም በወገኖቼ ላይ እዳ ሆና ትቆጠርባቸዋለች" ይህ ማለት
ተስዕሎተ መልክዕ ያልተፈጸመለት ጭንጋፍ አባቱን መስሎና አሕሎ ባለ መገኘቱ የአባቱ
የሆነዉን ነገር መዉረስ እንደማይቻለዉ እንዲሁም በተግባር ያልተፈጸመች ሕልመ ሌሊትም
እንደ ተግባር ኃጢአት ተቆጥራ አታስኮንንም ማለት ነዉ፡፡

7.6.1.3 ዝንየትና መንፈሳዊ ሥርዓቱ

ሕልመ ሌሊት ያገኘዉ ሰዉ በዚያዉ ሠጋ ወደሙ መቀበል (መቁረብ) አይችልም


ወደ ቤተ-ክርስቲያን መግባት ይከለከላል
መግባት የሚቻለዉ ልብሱን ቀይሮ ካጠበና ከላዉን ከታጠበ በኋላ በማግስቱ ነዉ፡፡
ወደ ቤተ-ክረስቲያን መግባት አይቻልም ሲባል ወደ ቤተ-መቅደስ መግባት አይቻልም
ማለት ነዉ፡፡ ጸሎት ማድረግ፣ትምህርትና የመሳሰሉትነ መንፈሳዊ ተግባራት
የመጀመሪያወን ቅፅር በመግባት በዕለቱ ሊያከናዉን ይችላል፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 115
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

በመኝታ ወቅት ሕልመ ሌሊትን ጨምሮ ልዩ ልዩ ነገሮች ሊከሠቱ ስለ ሚችሉ በቤተ


መቅደስ መኝታ ፈጽሞ የተከለከለ ነዉ፡፡
"የነግሁንና የመንፈቀ ሌሊቱን ጸሎት እጃቸዉን ከታጠቡ በኋላ ይጸልዩ በዚያ ሰዓት ዉኃ
ባያገኙ እፍ ብለዉ ከአፋቸዉ በሚወጣዉ ምራቅ እጃቸዉን አሻስተዉ ያማትቡ፡፡" ፍት.
ነገሥት ትርጓሜዉ "ይህ የመንፈስ ቅዱስ ስጦታ ነዉና ከራስህ እስከ እግርህ ድረስ
ንፁሕ ትሆናለህ፡፡ ካልተጠራጠሩ የዮርዳኖስ ዉኃ በአፍ ሊገኝ ይችላል፡፡" መጽሐፈ
ሰዓታት መግቢያ
ሩካቤ የፈጸሙ ባልና ሚስት መተጣጠብን ምንያት በማድረግ ከመጸለይ ወደ ኋላ ማለት
ለባቸዉም፡፡ ሩካቤያቸዉ ንጹሕ ስለ ሆነ ካልታጠብን አንጸልይም አይበሉ፡፡ ዘር
የመጣበትንን የነጠበበትን አካል (ኀፍረተ አካልን) ብቻ መታተብ ይበቃቸዋል፡፡
ያላገቡ ወጣቶች ግን ሕልመ ሌሊት ሲያገኛቸዉ መላ ሰዉነታቸዉን መታተብ አለባቸዉ

7.6.1.4 የሕልመ ሌሊት መፍትሔ

1. ሕልምን ደስ እየተሰኙ ደጋግመው አለማሰብ

ተግቶ ለመጸለጥ፣ ለማሰቀደስ፣ ለመቁረብ በወሰኑ ጊዜ ሕልመ ሌሊት እንቅፋት እየሆነ


ይፈተኑበታል፡፡ "ሌሊት በሕልም ከሴት ጋር ተገናኘህ መስሎኽ ዘር ቢወርድህ በመዓልት
አታስባት" መጽሐፈ መነኮሳት

2. ሕልመ ሌሊት በምታይበት ጊዜ ከነዚህ ቸል ብለህ ተመላልሰህ አትተች ፈጥነህ


ተነስተህ ታጥበህ ጸሎት አድርስ
 ቢቻል መስገድ ባይቻል ግን ይቅር በለኝ፣አድነኝ፣እርዳኝ እያልክ ወደ እግዚብሔር
ለምን፡፡
3. ዉኃ በብዛት አለመጠጣት
ፍልክስዮስ "እንደ ዉኃ ጥም ለመዓልት ሕልም ኃጢአትን የሚያጠፋ የለም ዉኃን
ካልስለህ ሰዉነትህን አስጨንቀዉ" ፊል ክፍል 3
"ርኩስ መንፈስ ግን ከሰዉ በወጣ ጊዜ ዕረፍት እየፈለገ ዉኃ በሌለበት ቦታ ያልፋል
አየገኝምም በዚያን ጊዜም ወደ ወጣሁበት ቤቴ እመለሳለሁ ይላል ቢመጣም ባዶ ሆኖ
ተጠርጎና አጊጦ ያገኘዋል" ማቴ 12÷43-45
በሕልመ ሌሊት በተደጋጋሚ እንደ ተጠቃ ወደ ዝሙት በሚመራ ማናቸዉም ነገር ሽሽ፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 116
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

በመሸ ጊዜ የምታያቸዉ ንባቦች መርምረህ ለፍትወት የሚያጋልጡትን ሽሻቸዉ፡፡ ደጋግ


መንፈሳዊ መጽሐፍት ለማንበብ ትጋ፡፡
ከመኝታህ በፊት ጠግቦ ላለመተኛት ሞክር፡፡ ትኩስና የሞቁ ነገሮች ላለመዉሰድ ተጣጣር
"በሰላም እተኛለዉ አንቀላፋለዉ"
ምስጢራችንን ለመያዝ የታመነና በምነግረዉ ነገር ራሱ ወደ ፈተና ሊገባ የማይችል
ለህይወቱ ብዙ ተሞክሮ ያለዉ መንፈሳዊ መምህርና አበዉ ካህናት እተማከሩ
በሚያቀርቡት የመፍትሔ ሐሳብ መያዝ
"ከወንድሞች መካከል በአንዱ እንዲህ ሆነበት፡፡ ወዳጅን ሰይጣናት የሚያሳስቡት ሕልመ
ኃጢአት በታሰበዉ ጊዜ እረዳዋለሁ ብሎ ከወዳጁ ጋር ወደ በአት ሄደ፡፡ የመንፈሳዊ
ወንድሙ ፈተና ወደ እርሱ ከዚያኛዉ ይልቅ በዝቶ መጣበት፡፡ምክንያቱም ያሰዉ ሕልመ
ሌሊትን ለመቃወም የማይችልና ገና ከፍጹምነት ያልደረሰ ነበር" ፊልክ ክፍል 7

7.6.2 ለዐቅመ ሔዋን የመድረስ ምልክቶች

የተለያዩ የአካል ለዉጦች ያሳያሉ(ይታይባቸዋል)


በኮረዳነት አመታት ፈጣን የሆነ የመት ማደግና የክብደት መጨመር ከመከሰቱ ሌላ
የሽንት መርዘም፣የትክሻ መስፋትና የአንገት መወፈር ይመጣሉ፡፡
በአንዳንድ ሴቶች ብጉር በሰዉነታቸዉ ይታያል
የፊት ቅርጽም ቀስ በቀስ እየተለወጠ መሔድ
በብብትና በብሽሽት አከባቢ ከሚታየዉ የጸጉር መብቀል ጋር ዳሌዎች ይሰፋሉ፡፡
የሚኖራቸዉ ሰፋ ያለ ዳሌ ወለዲን ብቻ ሳይሆን ከወለዱ በኋላ ሕጻናቸዉን
ለማዘዝና ለማቀፍ ምቹ ይሆንላቸዋል፡፡
መኃ 8÷8 "እኛ ጡት የሌላት ታናሽ እህት አለችን" ለትንሽ ሴት ልጅ
ጡት ማጎጥጎጥ
ሁለቱ ጡቶች ልጅ በምትወልድበት ጊዜ ለሕፃኑ ምግብ የሚሆነዉ ወተት
ማመንጨት ይጀምራሉ፡፡ በተጨማሪም ባሏ የሚደሰተዉ ጡቶቿን ለመሳም
በመነካካትና በመዳበስ ነዉ፡፡ ስለዚህ እዉነተኛ ባሏን የምታስደስትበት እግዚአብሔር
የሰጣት ብርቅ ሕዋስ ነዉ፡፡
ምሳ 5÷19 "ጡቷ ሁልጊዜ ታርካህ በፍቅሯም ሁልጊዜ ጥገብ"
ሕዝ 23÷8 "የድንግልናዋንም ጡቶች ዳብሰዉ ነበር"

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 117
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

 የጡት መጠኑ የቀነሰ መስሎ የገንዘብ አቅም ባይኖራቸዉ ዕንኳ ምናምን


እየወታተፉ እነርሱ ልከኛ ያሉትን ጡት ለማስመሰል ይደክማሉ፡፡
 የጡት መጠን የቀነሰ መስሏቸዉ ነፍሰቸዉ እስክትመጣ ድረስ በጡት መያዣ
ሲወጥሩ ስተዋላሉ፡፡
"ሌላ መልክ አትሻ (መነቀስ፣መጠቆር) በተፈጥሮ ያገኘኸዉ በቃሃል" ሠለስቱ ምዕት
 ጡት በቀላሉ ሊጎዳ የሚችል ሕዋስ መሆኑን ባለሙያዎች ይናገራሉ
 ለጡት ካንሰርና ለተለያዩ ደዌዎች ይጋለጣሉ
 ሕፃናትን ከማጥባት መቦዘን ይህ ማለት "ልጆቿን ለሞግዚቶች አትስጥ
ምክንያቱም መከራን ማሳቀቅና ዝሙትን መዉደድና እግዚአብሔር ሰጠዉን
ምግብ መውደድ ስለሆነ ግፍ ነዉ፡፡" ጡት የተፈጠረዉ ልጆቿን ለማሳደግ
ምግብ ለመስጠት ነዉ
የወር አበባ መታየት ይጀምራሉ

6.6.2.1 የወር አበባ ስያሜዎች

1. በሴቶች የሚሆነዉ ልማድ (ልማደ አንስት)


ዘፍ 16÷11 "አብርሃምና ሣራም በዕድሜያቸዉ ሸምግለዉ ፈፅመዉ አርጅተዉ ነበር፤
በሴቶችም የሚሆነዉ ልማድ ከሣራ ተቋርጦ ነበር፡፡"
2. በሴቶች የሚደርስ ግዳጅ
ዘፍ 31÷35 "በፊትህ ልቆም ስላልቻልኩ አትቆጣብኝ በሴቶች የሚደርስ ግዳጅ
ደርሶብኛል፡፡"
3. በየወሩ የሚታይ አበባ፡፡ አበባ የተባለበት ምክንያት ሴቶች ረሳቸዉ በዕፅ በየወሩ
የሚያዩት ደም በአበባዉ፤የሚወልዷቸዉ ልጆች በፍሬዉ መሰላሉ፡፡
"ለአንድ ተክል አበባዉ ቀድሞ ፍሬዉ እንደሚከተል ለሴቶች ልጆችም በጀመሪያ የወር
አበባ ቀድሞ ይታያቸዉና በኋላ ለልጅ መዉለድ ይበቃሉ፡፡ አንድ ተክል አበባዉ ከረገፈና
ቅጠሉ ከደረቀ በኋላ ፍሬ እንደሚስገኝ ሴቶች ልጆችም በእርጅና ምክንያት ደም
ከቆረጡ(ካረጡ) በኋላ መዉለጃ ጊዜያቸዉ አልፏልና ልጅ ለማግኘት አይችሉም፡፡
ምክንቱም ሴቶች በየወሩ የሚያዩት አበባ ነዉና፡፡" መጽሐፈ ሥነፍጥረት ዘዓርብ
4. ደመ ትክቶ ፡- ሕዝ 18÷7-9 "አደፋም ወዳለባት ሴት ባይቀርብ ….እርሱ ጻድቅ ነዉ
ፈጽሞ በሕይወት ይኖራል፡፡ ይላል እግዚአብሔር"

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 118
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

5. ደመ ጽጌ (የአበባ ደም)፡- ያበቡ(በአበባነት) ዘመን ያሉ ሴቶች የሚያስገኙት ደም እንደ


ማለት ነዉ፡፡ ደም መባሉ፡- የወንድ ዘር ካላገኘ ከማኅፀን ግድግዳ ፍራሽ ጋር በደም
መልክስለሚፈስና የኋለኛዉ ማንነት ደምነት ስለሆነ ነዉ፡፡
 ከኦቫሪ(ከዘር ከረጢት) ቤወሩ የሚለቀቅ የወንድ ዘዘር ካላገኘ ኦቫ (የሴት ዘር)
ከእንቁላል ጋር በየወሩ በደም መልክ ይፈሳል፡፡
 በእርግዝና ወቅት የቋረጥና ልጅ ከወለደች በኋላ ጤናማ ሂደቱን የቀጥላል
 ሚስትና እናት ለመሆን (ለመድረሷ) ፈጣሪ የመደበላት ፀጋ የሕይወት ሚና ነዉ

7.6.2.2 የወር አበባ መቼት

መቼት ማለት መቼና የት ማለት ነዉ

 አዳምና ሔዋን በኃጢአት ከወደቁ በኋላ ከገነት ዉጭ ነዉ፡፡


 በገነት እያሉ ደመ ጽጌ የነበረ ቢሆንም ደሟ በአፍአ አይታይም ነበር
 ከበደሉ በኋላ በየወሩ እንዲፈስ እግዚአብሔር ፈረደባት
 ዝናም መዝነብ የጀመረዉ ከሰዶም ጥፋት ወዲህ ነዉ፡፡ ዘፍ 8÷22
ዉስጥ ለዉስጥ ያረካት የነበረዉ ዉኃ ዝናም ሆኖ እየመጣ ምድርን ከዉች
ያጨቀያት ጀመር
ምድር፡- የሔዋን ምሳሌ ናት፡፡ ሰዉ ምድር ይባላልና
ዝናም፡- የወር አበባ ምሳሌ
ዉስጥ ለዉስጥ ሄድ የነበረዉ ዉኃ ከጊዜ በኋላ በዉጭ ተገልቶ ምድርን
ማጨቅየቱ ለሔዋን ባሕርይ የነበረ ደም ከጊዜ በኋላ በአፍአ መታየት
መጀመሩን ያስረዳል

7.6.2.3 በወር አበባ ወቅት የሚያጋጥም የሕመም ስሜት

 የጡንቻና የአጥንት መልፈስፈስ (ድካም) ማጋጠም


 የጀርባ (የወገብ ሕመም) ፣ማቅለሽለሽ፣የጡት ሕመም
 ሆድ ቁርጠት፣ምራቅ ማስተፋት
 የምግብ መንሸራተት ችግር፣ራስምታት፣የሙቀት መጨመር
 የምግብ ፍላጎት ማጣት፣ብርድ ብርደ የማለት

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 119
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

በዚህ ጊዜ

 በቂ እረፍት ስፈልጋታል፡፡
 ቀልጣፋ የተግባርና የእንቅስቃሴ ሰዉ ሆኖ መገነት ያስፈልጋል
 ትዝብት ላይ እስከ መዉደቅ የሚያደርስ መቅበጥበጥ
 የመደበር፡- በቀላሉ በሆነ ባልሆነ መከፋት
 በወር አበባ ላይ የሚገኙ ሴቶችን በሚገባ መንከባከብ ያስፈልጋል፡፡
ዘፍ 31÷35 "ላባ የተባለ ሰዉ የጥፋት ዕቃ በሚፈልግበት ጊዜ በወር አበባ ላይ ትገኝ
የነበረችዉን ልጅ ራሔልን ከተቀመጠችበት ቦታ ላለማስነሣት የተቀመጠችበትን ስፍራ
ከመበርበር ተቆጥቧል፡፡ ምክንያቱም "በፊትህ ልቆም ስላልቻልኩ አትቆጣብኝ በሴቶች
የሚደርስ ግዳጅ ደርሶብኛል""

7.6.2.4 በወር አበባ ወቅት ያሉ ሥርዓቶች

 ጸሎት መጸለይ ይቻላል፣ማስቀደስም ይቻላል


 ቅዱሳት መጽሀፍትን ማንበብ ይቻላል
 ለዝክርና ለጽድቅ ጠሚሆን ማንኛዉንም ሥራ ማለትም ስነዴ መልቀም አሻሮ መቁላት፣
እንኩሮ ማነከር ይቻላል፡፡
የወር አበባ መርገም ሳይሆን አድፍ(እዳሪ) ነዉ
ለምሳሌ እንደ ዘሕል(ንፍጥ)፣ሽንት፣ምራቅ፣ዓይነ ምድር፣ላብ…

7.6.2.5 በወር አበባ ወቅት የሚከለከሉ ነገሮች

1. ሩካቤ፡- በደም ወራት የሚደረግ ሩካቤ ለአባላዘር፣ለልክፍት፣ለኢንፌክሽን በቀላሉ


ያጋልጣል
የሰዉ ልጅ ክቡር ነዉ፡፡ በደም ወቅት እያለች ሩካቤ መፈጸም ክቡር ዘርን እዳሪ ከሆነ
ከደም ጋር ማዋሃድ ነዉና፡፡
ዘሌ 18÷19 "እርሷም በመርገም ርኩሰት ሳለች ኀፍተ ሥጋዋን ትገልጽ ዘንድ ወደ ሴት
አትቅረብ"
ዘሌ 20÷18 "ማንኛዉም ሰዉ ከባለ መርገም ሴት ጋር ቢተኛ ኀፍረተ ሥጋዋን ቢገልጥ
እርሷም የደሟን ፍሳሽ ገልጣለችና ሁለቱም ከሕዝባቸዉ መካከል ተለይተዉ ይጥፉ፡፡"

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 120
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

2. መጠመቅ፡- 1ኛ ጴጥ 3÷21" ይህ ውኃ ደግሞ ማለት ጥምቀት ….. የሰውነት እድፍ


ማስወገድ አይደለም፡፡ ለእግዚአብሔር የበጎ ኅሊና ልመና ነው እንጂ፡፡"
የሥጋ ንጽሕና ለነፍስ ንጽሕናና ለንስሓ የመዘጋጀት ምልክት (ምሳሌ) ነው፡፡ "
በምትጠመቀው ሴት በምትጠመቅበት ቀን እድፍ ቢመጣባት እስክትነጻ ድረስ ትቆይ"
ፍት.አን 11፡፡ ነገር ግን ጸበሉን መተሸሸት እና መጠጣት ይቻላል፡፡
3. መቁረብ፡- " ከግዳጇ ያልነጻችውን ሴት በደሟ ወራት ከቤተ ክርስቲያን አግብቶ
ሥጋወደሙን የቀበላት ከማዕረግ ይሻር" ፍት. አን 6፡፡
4. ቤተ መቅደስ መግባት፡ ፍት. አን 6" ንጽሕናዋን ያለፈጸመች ወላድ እና ከደመ ጽጌዋ
ያልነጻች ሴት ቤተ መቅደስ አትግባ"
 ቤተ ክርስቲያን መሔድ ትችላለች፡- ሄዳ በመጀመረያው ቅጽር መጸለይ፣
መማርና ማንኛውንም መንፈሳዊ ተግባራት መፈጸም ትችላለች
 ቤተ መቅደስ መግባት የማይቻለው፡-
 ድካምና ልዩ ልዩ ሕመም ስለሚከሰት ነው፡፡ በቤተ ክርስቲያን ደግሞ ወዲህ እና ወዲያ
ሳይሉ እና ሳይንቆራጠጡ መንፈሳዊውን ሥርዓተ ጸሎት ማድረስ ይገባል
 በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ለሚጸልየው ሰው ልቡና እንዳይታወክ
 እዳሪ እና እድፍ ስለሆነ ሳይነጹ መግባት ጸያፍ ነገር ይዞ እንደመግባት ይቆጠራል፡፡
 ሰውም ቢሆን ወደ ቤተ እግዚአብሔር ሲሔድ ከስጋዊ እድፍ ንጹሕ መሆን ይኖርበታል
 መቅደሱን እንድንፈራ አምላካችን ስላዘዘን፡፡ መቅዱስን መፍራት ደግሞ እግዚአብሔርን
መፍራት ነውና፡፡ መዝ 5÷7
 እናታችን ሔዋን ደመ ዕፀ በለስን በማፍሰሷ ከገነት ተባራለችና፡፡ የቀደመውን ዘመን
ለማስታወስ ይረዳ ዘንድ እና ቤተ መቅደስ የገነት ምሳሌ ስለሆነች፡፡
 ቤተ ክርስተያን በክርስቶስ ደም የተመሰረተች ስለሆነ በውስጧ ሊፈስ የሚገባው በደሙ
የዋጃት የክርስቶስ ደም ብቻ ነው፡፡ መዝ 5÷7፣ 1ጢሞ 3÷14

7.7 ከጋብቻ በፊት እንዴት እንኑር


የጋብቻ መቅድም መተጫጨት ነው፡፡ የመተጫጨት ባህልና ሥርዓት ፍቃድና ስምምነትን
ዕድሜን ፤ የስጋዊና መንፈሳዊ ዝምድናን ፤ የሃይማኖትን አንድንትን ዘርዝሮ ይገልጣል፡፡
ተጋቢዎች ከተዋወቁ ፣ እርስ በእርሳቸው ከተስማሙና ከተፈቃቀዱ ለወላጆቻቸው አሳውቀው
ፈቃድና ስምምነትን ካገኙ በኋላ የውዴታ ቃላቸውን በመጀመሪያ ለንስሓ አባታቸው ወይም

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 121
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ለቤተክርስቲያኑ አስተዳዳሪ ወይም ለክፍለ ኤጲስ ቆጶስ በመናገር ወደ ጋብቻ ቃሌኪዳን


ይሔዳሉ፡፡ ዕድሜን በተመለከተ ወንዶች ከ20 ዓመት በላይ ሴቶች ከ15 ዓመት በላይ
ሲሆናቸው መተጫጨትና መጋባት ይፈቀድላቸዋል፡፡ ፍት.መን.24 ም3. ክፍል 2፡፡ በዝምድና
በኩል ጋብቻን የሚከለክል ዝምንድና ሶስት ዓይነት ነው፡፡ ስጋዊ ዝምድና ፣ የጋብቻ ዝምድናና
መንፈሳዊ ዝምድና ናቸው፡፡ ስጋዊ ዝምድና በፍትሐ ነገስት በአንቀጽ 24፡842-853 ተዘርዝሮ
እንደተገለጸው ስጋዊ ዝምድና የሚጠበቀው እስከ ሰባት ትውልድ ነው፡፡
ይህም በአንድ ጎን ሰባት በአንድ ጎን ሰባት ከተቆጠረ በኋላ ስምንተኛዎቹ መጋባት ይችላል፡፡
አንድ ጥሩ መንፈሳዊ የሆነ/ች ወንድም (እህት) ጋር አብሮ ለማገልገል በእህትነትና
በወንድምነት መቀራረበን መልመድ ይኖርብናል፡፡ ነገር ግን ይህን በምናደርግበት ጊዜ የተለያዩ
ክፉ ወጥመዶች ያገኙናል ለምሳሌ፡- ክፉ ፊልሞች፣ለፈተና በሚያጋልጥ ሁኔታዎች ውስጥ
መቀመጥ ፤የጓደኛ ተጽእኖ ስለ ራሰቸው ሕይወትና ኃጢኣት ልምድ ደጋግመው በማውራት
የሰዎችን ልብ መስረቅ፡፡ እኛም እነዚህ ፈተናዎችን እንዳሉ ተመልክተን አቀራረባችንን በጥንቃቄ
ማደረግ አለብን፡፡ አንድም እግዚአብሔር ያዘጋጀልንን የምናገኝበት ጊዜ እስኪደርስ ድረስ ፡-
1. በትግስት መጠበቅ ዕብ 10፡36 መክ 3፡1
2. እንደ ፈቃዱ እንመላለስ 2ጢሞ 2፡22 ሮሜ 6፡12 መክ 12፡1
3. ያለ ሐሳብ እንኑር ሉቃ 21፡34 1ጴጥ 5፡6-7
4. በጾምና በጸሎት መትጋት ማቴ 26፡41 ፊል 4፡6 ዮሐ15፡14
5. ከጋብቻ በፊት ከእጮኝነት ዘመን እንዴት እንደ ሚዘልቅ ማወቅ
6. ስለሚስጥረ ተክሊል እና ሌሎች ስርዓት ማወቅ
7. በትዳር ውስጥ ችግር ቢኖር እንዴት መፍታት እንደሚቻል ማወቅ

7.8 መተጫጨት ማጫ መስጠት እንዳደረግ የተከለከለ ጋብቻ

1. የሥጋ ዘመድ ጋብቻ፡-


ወደላይ፡- ወላጆች አያቶች፣ቅድመአያቶች
ወደታች፡- ልጆች የልጅ ልጆች
ወደጎን፡- ያባቶች ወንድሞች፣ያባቶችዕኅቶች የእናት እህቶችና ወንድሞች፣ወንድሞች፣
የወንድሞች ሌጆች፣ከአባቶችና ከአያቶች ስለተወለዱ የተለያዩ ዘመዶች፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 122
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

የአባት ወንድም ልጅ አራተኛ ትዉልድ ናት፡፡

አባቴ እኔን ወለደ፣ ሁለት

አያቴ አባቴን ወለደ

አያቴ የአባቴን ወንድም ወለደ ሁለት

የአባቴ ወንድም ልጁን ወለደ

2. ከህግ ወገን የዘመድ ጋብቻ

እነዚህም የሌሎች ልጆች በጥምቀት ክርስትና የተነሱ ናቸዉ፡፡ ኒቂያ 23÷25 "ክርስትና
አንሺዉና ተነሺዉ ከሁለተኛዉ ጋር አይጋቡ ወላጆቹም፣ወነወድሞቹም፣ልጆቹም፣ልጅ ልጆቹም
የሚስቱ ከሌላ ልጆችም ወገን ንዱ ልጆች ከሁለተኛ ልጁ ጋራ አይጋቡ ሴት ልጆን ባሏ
ክርስትና ላነሳዉ ወንድ አታግባ" ወንድም እንደዚሁልጁን ሚስቱ ክርስትና ላነሳችዉ ወንድ
አያጋባ፡፡ ከእነዚህ ሁሉ በመካከላቸዉ መንፈሳዊ ተዛመዶ ሆኗል፡፡

3. አብሮ በመኖር የተዛመዱ ሰዎች ጋብቻ

ምንመ እነርሱ በሞግዚትናት ስር ቢወጡ አሳዳጊዎቻቸዉም ቢያዩ እነዚህ ጡት መጥባትን


በመሳተፉ ወይም በልጆች መዕረግ በማሳደግ ያሉ ናቸዉ፡፡

ልጆቻቸዉም ወላጆቻቸዉም እነርሱ ቢሆኑ አባቶቻቸዉም ያባቶቻቸዉን አባቶችም ያባቶችን


ወንድሞች የእናቶቻቸዉን ወንድሞች እና እህቶች ያባት ሚስት ያባት ሚስት (የእንጀራ
እናት) አባት ልጅ ትሆናለች ብሎ ያሳደጋትን ልጅ አያግባ፡፡

4. በትዉልድ ያይደለ በግቢ ስለሚዛመዱ ሰዎች መጋባት


 ያባቶች ሚስቶች፣ወንድ አያቶቻቸዉ እኅቶቻቸዉእናቶቻቸዉ ሴት አያቶቻቸዉ
 የልጆች ሚሲቶች፣ልጆቻቸዉ፣እኅቶቻቸዉ፣እናቶቻቸዉ፣ሴቶች አያቶቻቸዉ
 የወንድሞች ሚስቶች ልጆቻቸዉ፣እሕቶቻቸዉ፣እናቶቻቸዉ፣ሴቶች አያቶቻቸዉ
 የሴት ዘመዶች አያቷ፣እናቷ፣ያባቷ እኅት፣የእናቷ እኅት፣እኅቷ፣ልጇ፣የልጅ ልጇ
ናቸዉ፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 123
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

5. ሊያገባት ከሾሙት ጋር አደራ ያስጠበቁት ሰዉ ጋብቻ

የኸዉም እርሱ ልጅ ወንድሙም ከገንዘቧ ሁሉ ጋር 26 ዓመት ከሆናት በኋላ ከሂሳብ ወገን


የሚጋባ አደራዉን ከፈጸመ በኋላ ያግባት

6. የጌታ ሚስት ባሏ ነፃ ያወጣዉ ባሪያ ሚስት ልቶን መልካም አይደለም


7. የእርሱ ወገወን ያልሆነችዉን አማኝ ያልሆነችዉን ማግባት አይገባም
8. ለጋብቻ ከሚያስፈልገዉ ሩካቤ የሚከለክል(ከእናቱ ማሕፀን ጀምሮ በተፈጥሮ እንደስልብ
ያለ ቢሆን) ሩካቤ የማይቻለዉ ስለሆነ ጋብቻን ይከለክላል
 ፍናፍነታም (የወንድና የሴት አካል በአንድነት በ አንድ ቦታ ያለበት ሰዉ)
 ስትም ሩካቤ የሚከለክል ትርፍ አጥንት ያለባት ቢትሆን
 ስልብ፣እብድ፣የሚቆራርጡ ደዊያት እንደ ደዌ ሥጋ
9. በዝሙት ሥራ በአግባቡ የፈረዱበትን ለመፍታት በሚገባ የፈቷትንም ማግባት
10. ሁለት(ሦስት) ጋብቻ ማግባት አይገባም
11. መነኮሳይትን ማፍባት አይቻልም
12. እድሜዋ ከ60 ዘመን ያለፈዉን ማግባት አይቻልም
13. የባሏን ሞት የሀዘን ወራት ያልፈጸመች ሴት ማግባት አይቻልም ሙሉ ዓመት (10
ወር) ነገር ግን መተጫቸትና ቃል ማሰር ይቻላል
14. ከወንድና ከሴት እያንዳንዱ ካልወደዱ ሌላ ሊያገባቸዉ አይገባም

ማጨት ቃልኪዳን መግባት ከጋብቻ የሚቀድም ተስፋ ነዉ፡፡ በደኩም ያለ ደብዳቤ ሊሆን
ይችላል፡፡ ዕድሜዉ ከ7 ዓመት ላለፈ ሕፃን አይጩለት፡፡ የወንዶች አካለ መጠን ፍጻሜ 20
ዓመት ያም ባይሆን 25 ዓመት ነዉ፡፡ የሴቶችም 12 ዓመት ያም ባይሆን15 ዓመት፡፡ የጋብቻ
አንድነት ግን በካሕናት መኖር በላያቸዉ በሚጸልትጸሎት ካልሆነ በቀር አይሆንም ኤፈጸምም፡፡
አንድ አካል እንደ ሆኑ ቅዱስ ቁርባን ያቀብላቸዋል፡፡ ሁለተኛ የሚያገቡ ወንዶች ካሕናት ቢሆኑ
ከሹመታቸዉ ይሻሩ፡፡ ከዚያም በኋላ ቢደግሙ የረከሱ ይሆናሉ፡፡ 1ኛቆሮ 7÷39"ሴት ባሏ
በሕይወት እያለ በሕግ የታሰረች ናት ባሏ ቢሞት ግን ነፃ ናት፡፡

እግዚአብሔርን ከሚያምኑ ወገን የወደደችዉን ልታገባ ይገባታል፡፡ በምክሬ ብትፀና ብፅዕት ናት፤
መታገስ ሲሳናት ግን ታግባ፡፡" የሚጋቡ ፈቶች ቢሆኑ ተክሊል አያድርጉላቸዉ፡፡በረከተ ተክሊል
ለድንግል ወንድና ለድንግል ሴት የገባልና፡፡ ሮሜ 7÷3"ሴት ባሏ በሕይወት ሳለ ሌላ ሰዉ

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 124
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ብታገባ ሴሰኛ ሕግ አፍራሽም ሆነች፡፡" ያመነች ሴት ያለመነ ወንድ ብታገባ ከምዕመናን ትለይ፡፡
1ኛቆሮ 6÷12-15"ያላመነች ሚስት ያለችዉ ወንድም ቢኖር ከእርሱ ጋር ልትኖር ብትወድ
አይፍታት ያመነች ሴትም ያለመነ ባል ቢኖራት እርሱም ከእርሷ ጋር ሊኖር ቢወድ ባሏን
አትፍታዉ ያላመነ ወንድ ባመነች ሴት ይከብራልና፡፡ እንደዚሁም ያላመነች ሴት ባመነ ወንድ
ትከብራለች፡፡ ያላመነዉ መለየትን ቢወድ ግን ይለያይ፡፡"

ጋብቻ ከሚሻርበት ገንዘብ ከተነገረበት ሚስት መፍታት አይቻልም፡፡ ማቴ 19÷3-10 "ሳትሰስን


ሚስቱን የሚፈታ ሁሉ እሱ ዘማ አደረጋት ባሏ የፈታትንም ያገባ አመነዘረ" እግዚአብሄር አንድ
ያደረጋቸዉን ሰዉ ሊለያ አይችልም፡፡ 1ኛቆሮ 7÷11-18"ባል ከሚስቱ ጋር ይኑር ሴትም ከባሏ
ጋር ትኑር ያገቡትን ሰዎች እኔ የማዝዛቸዉ አይደለሁም የእግዚአብሔር ትእዛዝ ነዉ እንጂ፡፡
ሴት አትፍታ፡፡ ልትፈታ ብትወድ ግን ያለ ባል ትኑር ያም ባይሆን ከባሏ ጋር ትታረቅ፡፡
ወንድም ሚስቱን ሊፈታ አይገባዉም፡፡ ሰዉ ሆይ ከሚስትህ ጋራ የታሠርክ ቢትሆን ከእርሷ
መለየትን አትሻ፡፡ ከእነርሱ አንዱ ሁለተኛዉን እንቢ ሊለዉ አይገባም፡፡ 1ኛቆሮ 7÷3-7"ባል
ለሚስቱ ከእርሱ ላይ ለእርሷ የሚገባዉን ይስጥ ዳግመኛም ሚስት እንደዚሁ ለባሏ ታድርግ፡፡
ሴት በገዛ ስጋዋ ላይ ስልጣን የላትም ባሏ በራሱ ላይ የሰለጠነ ነዉ እንጂ፡፡ ከዚህ በኋላ ይህን
በፈጸማችሁ ጊዜ ወደፍቃዳችሁ ተመለሱ፡፡ የምትሹትን ስላጣችሁ ሰይጣን ድል እንዳይነሳችሁ፡፡
ለደካሞች እንደ ሚነግረ ይህን እላችኋለኋለሁ፡፡ በቁርጥ ትእዛዝ አይደለም"፡፡ በግዳጅና
በአራስነት ወራት ተከለከለ ነዉ፡፡ ዐባለ ዘርዕን ከጥፋት ወገን ስለሚገኘዉ ነዉ፡፡ ከዚህም የተነሳ
በማሕፀን የተፀነሱትን ልጆች የሥጋ ደዌ ስለሚያገኛቸዉ ነዉ፡፡

7.9 የእጮኝነት ጊዜ
የእጮኝነት ጊዜ የጋብቻ ጊዜ እንዳለመሆኑ መጠን የተቃራኒ ጾታ ግንኙነትን ሳናደርግ በሐሳብ
የምንግባባበት ጠባይ ለጠባይ የምንጠናናበት በማናቸውም ጉዳዮች ሳንተፋፈር የምንነጋገርበት
ጠንከርም ሲል ቤተሰቦቻችንን የምናስተዋውቅበት የቅድመ ጋብቻ አንዱ ክፍል ነው በመሆኑም
ቅድስናን (ክብረ ንጽሕናን) የሚያሳጡንን የረዘመ የእጮኝነት ጊዜ ማስቆጠር በምንገናኝበት ጊዜ
ከሰው የተደበቀ ቦታን መምረጥ እንዲሁም ሕይታችንን የሚያለመልመውን ቃለ እግዚአብሔር
በሕብረት አለመመገብ ናቸው፡፡ ሌላውና የመጨረሻው የእጮኝነት ጊዜአችንን የተሳካ
የሚያደርግልን እና ለቅዱሱ ጋብቻ የሚያበቃን

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 125
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

1ኛ. እግዚአብሔር እንደሚያየን ማመን እርሱ እንደሚያየን ካመንን እርስ በእርሳችን ሰው ኖረ


አልኖረ አንዳራም፡፡ 1ጴጥ 4፡1

2ኛ. የሚገባን ልብስ ማድረግ አካልን የሚግልጥ ልብስን አለማድረግ፡፡ 2ሳሙ 13፡19 ከጋለሞታ
ልብስ የተለየ ምሳ 7፡10 ባትን ከሚያሳይ ልብስ የተለየ ኢሳ 47፡2፤ የተገባ አለባበስ ጌጠኛ
(ንጹሕ) እና ደገኛ ልብስ ኢሳ 52፡1 ነብዩ ኤርሚያስ ሴቶች ስለምን የተገላለጠ ልብስ
እንደሚያደርጉ ሲገልጥ "በልብሽም እንዲህ ያለ ነገር ስለምን ደረሰብኝ ብትይ ከኃጢአትሽ ብዛት
የተነሳ የልብስሽ ዘርፍ ተገልጦአል ተረከዝሽም ተገፍፏል፡፡" ኤር13፡22

3ኛ. የሥጋ ስሜታችንን የሚያነሳሱ ፊልሞችን እና የመሳሰሉትን ነገሮች አለማየት

4ኛ. የዝሙት ጾርን በጾምና በጸሎት ማሸነፍ የእጮኝነት ጊዜአችንን የተሳካና ጣፋጭ
እግዚአብሔር ያለበት ያደርግልናል፡፡

7.9.1 በእጮኝነት ወቅት ሊጠነቀቁባቸው የሚገቡ መሠረታዊ ነገሮች


1. በእጮኝነት ወቅት ለወደፊት ከሚጠብቃቸው ኑሮ አኳያ አንጻር እጮኞዎች ሊያውቁት
ወይም ስንቅ ሊያደርጉት የሚገባቸው ጉዳይ ነው፡፡ ግልጽ ሆነው ሊነጋገሩባቸው ጉዳይ ቢኖር
ማግኘትና ማጣት፣ መደሰትና ማዘን፣ ዓለምና መከራ፣ መኖርና መሞት እንዳለ ብልህነት
በነፋስ ዕውቀት መገንዘብ ይገባቸዋል፡፡ ጥሩም ሆነ ክፉ እድላቸው በእግዚአብሔር አምላክ እንደ
ተያዘ መሆኑን ከልብ ተረድተው ክፉ እንዳይነካቸው ደግ እንዳያልፋቸው በቀና ሃይማኖት
ምግባር ሠርተው በጾም በጸሎት በምጽዋት በአገልግሎት በትርፍም መኖር አለባቸው፡፡
ማኅበራዊ ነሮንና የቤተሰብ አመራርን በአቅምና በቁጠባ መመራትን በታዣዥነት መለማመድ
አለባቸው፡፡ ከሌሎች መማርና መመከር አግባብ ነው፡፡ በግልጸኝነት አለመወያየትም
ትውውቃቸው ቀንሶ ያስቀረውና በኋላ ለምን ሆነ ሊያመጣና ለትዳር መስመር እንቅፋት
ሊፈጥርባቸው ይችላል፡፡ ሁሉም ባይሆንም ያለው ተጨባጭ ነገር ሁሉ ተገልጾ በይሁኔታው
መታለፍ ይኖርበታል፡፡

2. በእጮኝነት ወቅት ለፈቃደ ስጋ ሳይሸነፉ ለሌላ ወገንም ፈተና (መሰናኪያ) ሳይሆን እንዴት
ባለ ጥንቃቄ ያሳልፋል፡፡ ሌላኛው ነገር ከራሳቸውም ሆነ ከአካባቢ ለሚመጣው ፈተና መቋቋም
ያለባቸው ብቻቸውን አለመገናኘት አለመሆን የጋብቻውን ጊዜ በትግስት በጾም በጸሎት በስግደት

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 126
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

መጠበቅ ና ንስሐ አባት መያዝና ሁሉንም ማመከር ነው፡፡ መተጫጨታቸውን ግልጽ በማድረግ
ሳይጠጋጉ በጣምም ሳይራራቁ ምልክት ሳያሳዩ በእሀትነትና በወንድምነት ደረጃ መጓዝ መኖርም
ነው፡፡ከዚህ በተረፈ ስለማይመለከተው ሌላ ሰው ብዙ አለመጨነቅ ወሳኝ አቋም ነው፡፡

3. ከጀመርነው ጓደኛ ዘለቄናነት እንዲኖረው ፈቃደ እግዚአብሔር መጠየቅ (በስዕለትና


በአስተበቆት መለመን) ፡፡ አፈአዊ በሆነ ጉዳይ መረዳዳት በአመቺው መንገድና ሥርዓት ባለው
ሁኔታ እየተገናኙ መጠያየቅ፣ መተማመን፣ መናበብ፣ ሐሳቡን የሚወድና የሚጠላውን ወገን
ከሚያጠራጥር ድርጊትና ሐሳብ መራቅና መጠንቀቅ፡፡ የሰውን ነገር ሳያጣሩ አለመስማትና
ቅሬታን አለማሳደር እነዲሁም በተለያ ስጦታዎችና እርዳታ ወረተኛ አለመሆን፡፡

7.9.2 በምንተጫጭበት ወቅት ብዙ ጊዜ የማናስተውላቸው ስህተቶች


ጊዜያዊ ሀብትን ተመልክተን የምናደርገው መተጫጨት ፡- ይህ ሀብት አገኛለው የምፈልገውን
እበላለው እለብሳለው ሕይወትን በተሻለ ሁኔታ እመራለው ነፍሴ ሆይ ብይ ጥገቢ እንዳለው
ሰነፍ በመሆን ጋብቻን ለጥቅም መፈለግ ፍቅርን እንዳናይ እንደተጋረደብን ዘመናችንን ሁሉ
በተሰላቸና ፍጹም በተረበሸ መልኩ በጨለማ እንድንመራ ከማድረጉም በላይ ሰማያዊውን
የእግዚአብሔርን ጸጋ በምድራዊው ገንዘብ ለውጠናልና ደስታ የሰማይ ያህል ይርቅብናል
የሕይወት ትርጉሙ የማይገባን ከእንሰሳዊ ሕይወት ያልተሻለ በራሳችንም በፍሬዎቻችንም
የማንደሰት እንሆናለን፡፡

ለዚህ ስህተት የሚዳረጉትን ሰዎች በተመለከተ፡- "...ከእነርሱም ወገን ስለ ገንዘብ ብዛት ጋብቻን
የሚሻ አለ፡፡ ... ስለዚህም ስለ ገንዘብ ፍቅር የሚስቱን መልከ ጥፉነት የሚታገሥ አለ፡፡..."
(ፍት.ነገ. ትርጓሜ አን.24፡839 ገጽ211) ካስተዋልን ግን ገንዘብ እኮ ድግስን እንጂ ጋብቻን
አያሳካም ፍቅርን አይገዛም ይልቁንም ደገኛ ሀብት ቢኖረን ባለጸጋውን አምላክ እንደማምለካችን
መመካታችን በእርሱ ብቻ ይሆን ዘንድ ልባችን ቢመካ ሰላማችን እንደ ወንዝ በሆነ ነበር፡፡
ምክንያቱም ብንመካበት የተገባ የዘላለም መኖሪያች እና የሕይወታችን ትርጉም፤የመኖራችን
ዋስትና የሚሆን እንደ እግዚአብሔር ያለ ለእኛ ማንም የለም፡፡ ዘዳ 33፡26 መመካት
በእግዚአብሔር መሆን እንዳለበት ነብየ እግዚአብሔር ኤርሚያስ እንዲህ በማለት ያመጣዋል ፡-
"እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፡፡ ጠቢብ በጥበቡ አይመካ ኃያልም በኃይሉ አይመካ ባለ ጠጋም
በብልጥግናው አይመካ ነገር ግን የሚመካው ምሕረትንና ፍርድን ጽድቅንም በምድር ላይ

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 127
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

የማደርግ እኔ እግዚአብሔር መሆኔን በማወቁና በማስተዋሉ በዚህ ይመካ ደስ የሚያሰኙኝ


እነዚህ ናቸውና ይላል እግዚአብሔር፡፡" ኤር9፡23-24

ዛሬ የአመለካከት ድኅነት ሰማይን በነካበት ዘመን ሰው መሆናችን እስኪረሳን ጊዜያዊው


ኑሮአችን ዘላለማዊ ኑሮ እስኪመስለን ድረስ ያወረን እና እግዚአብሔርን እንዳናይ ታላቅ ጋሬጣ
የሆነብን ገንዘብ ነው፡፡ ሰው ለመጥላታችን ሰው ለመውዳዳችን ሚዛኑ እግዚአብሔር ሳይሆን
ገንዘብ ሆኗል “ገንዘብ ካለ በሰማይ መንገድ አለ” የሚለውን አባባል የሕይወታችን መርሕ
አድርገን እንደ ስምዖን መሰሪ ሰማያዊውን ጸጋ በገንዘብ ለማግኘት የምንሯሯጥ ያላስተዋል
ስንቶች ነን? ለእኛ ተክሊል ማድረግ የጓደኞቻችን የድፍረት ኃጢአት መመዘኛ የሆነብን፣ እነ
እገሌ አድርገዋል አይደል? ምን ሆኑ? በማለት የእግዚአብሔር የምሕረት ባለጠግነትን እንደ
ሞኝነት የምናይ ስንቶቻችን ነን? ይህ ግን መንፈስ ቅዱስን ማታለል ነውና ለጊዜው የተሳካልን
ቢመስለን ቀናተኛው እግዚአብሔር የስራችንን ሊሰጠን ዋጋውን በእጁ ይዞ ዘወትር በሕሊናችን
በኩል ይቆማል፡፡

ሰው ሰው ሆነ የሚባለው እንደ ሰው መኖር ሲችል ብቻ ነው፡፡ ይኸውም የእግዚአብሔር ፍቅር


የተሞላ ሰው ሲሆን ነው፤ እግዚአብሔር ያሉት ሁሉም ነገሮች አሉት ዳዊት ልጁ ሰሎሞንን
ሰው ስላልሆነ አይደለም "ልጄ ሆይ ሰው ሁን" ያለው ነገር ግን ሰው ማለት በእግዚአብሔር
አምሳል የተፈጠረ ክቡር እና የእግዚአብሔር ፍቅር የሚንጸባረቅበት የክብሩ ማደሪያ ነው፤
በመሆኑም በዚህ የእግዚአብሔር ቤተመቅደስ መንገስ ያለበት እግዚአብሔር ብቻ እንጂ
በደባልነት ገንዘብ ሊሆን አይገባም፡፡ ምክንያቱም ገንዘብ ቤተመቅደስ ልባችንን ከተቆጣጠረው
ክፋትን ብቻ የሚያበቅል ፍሬ የሌለው ሕይወትን እንድንመራ እንገደዳለን፡፡

እዚህ ላይ ቅዱስ ጳውሎስ በመንፈስ ለወለደው ለልጁ ለጢሞቴዎስ የመከረውን ቃል ማስታወስ


ወደድኩኝ፡- "ገንዘብን መውደድ የክፋት ሁሉ ሥር ነውና አንዳንዶችም ይህን ሲመኙ
ከሃይማኖት ተሳስተው በብዙ ስቃይ ራሳቸውን ወጉ አንተ ግን የእግዚአብሔር ሰው ሆይ ከዚህ
ሽሽ ጽድቅንና እግዚአብሔርን መምሰል እምነትንም ፍቅርንም፣ መጽናትንም፣ የዋህነትን
ተከታተል፡፡ መልካሙን የእምነት ገድል ተጋደል የተጠራህለትንም በብዙም ምስክሮች ፊት
በመልካም መታመን የታመንህለትን የዘላለምን ሕይወት ያዝ፡፡" 1ጢሞ6፡10-12 ገንዘብን
መውደድ ይህን ያህል ክፉ እና ከሐይማኖት መንገገድ የሚያስወጣ ቀይ መስመር ነው፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 128
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ወጪያዊ ውበት ተክለ ሰውነት ፡- ነገር ግን ይህን ብቻ እንደ መስፈርት በመቁጠር ስንቱን
ቆንጆ ላናገባቸው በእጮኝነት ጊዜ አስነወርናቸው? አንገታቸውን አስደፋናቸው? አላማውያን
የማያደርጉትን ነውር እርም የሆነ ነገር ፈጸምን? ጋብቻን ለመመስረትም ለመተጫጨትም
ተክለ ሰውነት አይከለከልም፤በተክለ ሰውነትም ምክንያት ጋብቻ አይፈርስም፡፡ ምሳ31፡30
ሁሉም ውብ ነው፤በእግዚአብሔር ጣቶች የተዘጋጀ የእግዚአብሔር ውጤት ነው፡፡ በዝሙት
የምናይ ከሆነ"ቆንጆና እሸት አይታለፍም" እያልን ካገኘነው ጋር አንሶላ እየተጋፋን
እግዚአብሔርን እናሳዝናለን፤ባለማስተዋል እንዲህ የምናደርግ ይህ የእግዚአብሔር ድምጽ ነውና
ንሠሐ ገብተን ሰው ልንሆን ይገባናል፡፡

በዚህ ውበት ተሳስበው የተተጫጩ ጥንዶች እግዚአብሔርን በማወቅም ይሁን ባለማወቅ


አላከበሩምና ለዝሙት ለማይረባም አእምሮ ተላልፈው ላለመሰጠታቸው ዋስትና አይኖራቸውም፡
፡ ቅዱስ ጳውሎስ እግዚአብሔርን ለማያከብሩ እና ተክለ ሰውነትን ተመልክተው አብረው
ለመኖር ላቀዱ ጥንዶች እንዲህ ሲል ያስጠነቅቃል፡-"ስለዚህም እግዚአብሔርን እያወቁ እንደ
እግዚአብሔርነቱ መጠን ስላላከበሩትና ስላላመሰገኑት የሚያመካኙት አጡ ነገር ግን በሀሳባቸው
ከንቱ ሆኑ የማያስተውለውም ልባቸው ጨለመ፡፡ ጥበበኞች ነን ሲሉ ደንቆሮወች ሆኑ..."ሮሜ1፡
20፤21

ይህ ብቻ አይደለም ለመመለስ እና እግዚአብሔርን ለማወቅ ባለመውደዳቸው ለማይረባ አእምሮ


አሳልፎ እንደሰጣቸው ሲናገር፡- "እግዚአብሔርን ለማወቅ ባልወደዱት መጠን እግዚአብሔር
የማይገባውን ያደርጉ ዘንድ ለማይረባ አእምሮ አሳልፎ ሰጣቸው ዓመፃ ሁሉ ግፍ መመኘት
ክፋት ሞላባቸው ቅናትን ነፍስ መግደልን ክርክርን ተንኮልን ክፉ ጠባይን ተሞሉ የሚያሾከሹኩ
ሐሜተኞች አምላክን የሚጠሉ..." ሮሜ1፡28-32 በእጮኝነት ከምንስትባቸው አንዱ ተክለ
ሰውነት በመሆኑ ከዝሙት የጸዳ እይታ እግዚአብሔር ሁሉንም ውብ አድርጎ እንደሰራ በማመን
ይንን እንደ መስፈርት እንዳንቆጥረው በመጠንቀቅ የእጮኛ ምርጫችንን ከወዲሁ ልናስተካክል
ይገባል፡፡ ውበት ሐሰት ነው ደምግባትም ከንቱ ነው እግዚአብሔርን የምትፈራ እርስዋ
ትመሰገናለች ነውና የሚለው ቃሉ የእኛ መስፈርት ከተሳሳተው ተክለ ሰውነት ወደ ትክክለኛው
እግዚአብሔርን ወደ መፍራት ሊሸጋገር ይገባል፡፡ ደግሞም አባቶቻችን "የሚያብለጨልጭ ሁሉ
ወርቅ አይደለም" የሚሉት ምክር ልብ ልንለው ይገባል፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 129
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

7.10 ከጋብቻ በፊት

የተጋቢዎቹ ስምምነት አስቀድመው በጋብቻው ሁለቱም ተጋቢዎች መተወዋቅ መስማማትና


መወሰን አለባቸው። ትዳርን ያህል ታላቅ ነገር በሌሎች ግፊትና ትእዛዝ መወሰን የለበትም።
እጮኛሞች ሲተዋወቁም በስህተት ውስጥ ወድቀው ሃይማኖታቸውን እንዳያስነቅፉ
ግንኙነታቸው ከዓለማውያን ሰዎች ልዩ መሆኑን መዘንጋት የለባቸውም። በመጠናናትም ጊዜ
ማለፍ የለበትም ጊዜ በረዘመ ቁጥር ሃሳብ ይለዋወጣልና። የሃይማኖት አንድነት ለጊዜው ቀላል
መስሎ የሚታየው የሃይማኖት ጉዳይ በኋላ ለመፍታት አስቸጋሪ ሊሆን ይችላል። በአንድ
ሃይማኖት የሚያምኑና ሥርዓቱን ጠብቀው የተጋቡ ከሆኑ ግን እንደ አንድ ያስባሉ
ሳይነጋገሩም በሀሳብ ይስማማሉ ይተሳሰባሉ። በእርግጥ የሌላ እምነት ተከታይ የሆነውን
አስተምሮ አሳምኖ ማግባት ይፈቀዳል። ነገር ግን እሰብካለሁ ሲሉ መሰበክ እንዳይመጣ ጥንቃቄ
ያስፈልጋል ።

የአእምሮና የአካል ብስለት እንደ ቤተ ክርስቲያ ትምሕርት የጋብቻ ዕድሜ ሴት ከአሥራ


አምስት፣ ወንድ ከሃያ ዓመት ጀምሮ ባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ሲሆን የአእምሮ ዝግጅት
ማለትም ከሃይማኖት አንጻር፣ ስለ ትዳር መማርና መረዳት፣ ከትዳር በኋላ ስለሚኖረው
ህይወት ግንዛቤ ማግኘት፣ ከጋብቻ በኋላ ከትዳር ጓደኛው የሚቀርበው ሰው እንደሌለ ማወቅ፣
ራስን ለትዳር ጓደኛ አሳልፎ ለመስጠት መወሰንና ወደፊት ሊከሰቱ የሚችሉ ችግሮችን
በትዕግሥት ለማሳለፍ መዘጋጀት ናቸው።

7.10.1 የትዳር ጓደኛ ለመምረጥ መሠረታዊ የሆኑ ኦርቶዶክሳዊ መመዘኛዎች


ጠባይ ደምግባት ፣ሙያ፣ ባልትና፣ ለሥራ ታታሪነት፣ ብርታት፣ ሙሉ አካልና ጤንነት /ቢቻል
መልክም/ ሃይማኖትና ሥነ-ምግባር፣ሥነ ሥርዓት፣ መሠረታዊ ዕውቀት፣ አቻነት እኩያ
አምሳያ መሆን ነው፡፡ በትውልድ በሃይማኖት በሀብትና በዕውቀት በጠባይም መመጣጠንና
መቀራረብ፡፡ ለመወሰን ምክረ አበው በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ አበው ሲናገሩ በሌሊት በሌሊት
ምንታውቆ ሴትን ጠብቆ ማትረፍ አይቻልም፡፡ ሴትና ዓለም አንድ ናቸው፡፡ 1ቆሮ 7፡29-34
በዚህ በተረፈ ቁርጠኝነት ነው፡፡ አለመፍራት፣ አለመጠራጠርና አለማወላወል ምሳ 12፡15 ምሳ
5፡3-77.9.2 ከጋብቻ በፊት ሩካቤ ለምን ተከለከለ?

ጋብቻ የአካልና የመንፈስ አንድነት ነው። "ሁለት አካል አንድ ልብ" የሚሆኑበት

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 130
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ድንቅና ሰማያዊ ምስጢር እንጂ በአካልም በመንፈስም የተለያዩ ሰዎች በአንድ ላይ የሚኖሩበት
የደባልነት ኑሮ አይደለም። ቅድመ ጋብቻ የሩካቤ ሥጋ ግንኙነት መፈጸም ዝሙት በመሆኑ
ከእግዚአብሔር ይለየናል። ማመንዘር ደግሞ ከእግዚአብሔር መንግስት የሚለይ ነው።
"አመንዝሮች...የእግዚአብሔርን መንግስት አይወርሱም" 1ኛ. ቆሮ 6:9 እንዲል። ቅዱስ ዮሐንስ
ወንጌላዊም "የሴሰኞች እድላቸው በዲንና በእሳት የሚቃጠል ባሕር ነው ይሀውም ሁለተኛ ሞት
ነው።" ራዕ. 20:8 በማለት ያስጠነቅቃል። የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት በጋብቻ የቡራኬ ስርዓት
ብዙ ተባዙ ምድርንም ሙሏት ዘፍ. 1:28 ከሚለውና የመጀመርያው ቡራኬና ከቃና ሰርግ ቤት
ምስጢር ወስደው በጋብቻ በዓል ጊዜ የሚፈጸም ልዩ የቡራኬ ጸሎት ሰርተዋል።

ቅዱስ አግናጥዮስ የተባለው የቤተ ክርስቲያን አባት የክርስቲያኖች ጋብቻ በኤጲስ ቆጶሱ ፈቃድ
ኤጲስ ቆጶሱ ባለበት እንዲፈጸም ስርዓት ሰርቷል። ሊቁ ጠርጡለስም ይህንን ትምህርት
በመደገፍ "የክርስቲያኖች ጋብቻ አማናዊ የሚሆነው በኤጲስ ቆጶስ ፈቃድ የሆነ እንደሆነ ነው።
ያለበለዚያ ግን ጋብቻ አይባልም።" ብሏል። እንዲያውም ይሀው ሊቅ "ቤተ ክርስቲያን
ሳታውቀው የሚፈጸም ጋብቻ ሁሉ ዝሙት እንጂ ጋብቻ አይባልም።" ብሏል።

7.10.2 ማሕተመ ድንግልና ምን ማለት ነው


ማሕተመ ድንግልና ማለት ሴት ከወንድ ጋር ሩካቤ አድርጋ አለማወቋን የሚያስረዳ የስራዋ
መገለጫ የአኗኗሯ መታዋቂያ ልዩ የተፈጥሮ ምልክትና የድንግልናዊ ኑሮዋ ዘውድ ነው። ይህ
መለኮታዊ ማሕተም በሴቶች አፈ ማህፀን ቀለበት በሚመስል ስስ ስጋነት በጉልህ ይታወቃል።
ብዙ ጊዜም ድንግልና ለሴቶች የሚነገረው በጉልህ ምልክት የሚታወቀው በእነርሱ ስለሆነ ነው።
ነገር ግን ድንግልና ለወንዶችም ተጠቃሽ መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ "ከሴቶች ጋር ያልረከሱ
እነዚህ ናቸው። ድንግሎች ናቸው።" ራዕ. 14:4 በማለት ይናገራል።

ድንግልና ማለት ደግሞ ወንድ የማታውቅ ከወንድ ጋር ሩካቤ ፈጽማ የማታውቅ ጥብቅ
ልጃገረድ ሴት ወይም ሴትን በምንጣፍ ተገናኝቶ የማያውቅ ወንድ ማለት ነው። በሰው ልጆች
ዘንድ ካለ ዘር መቀበል ማቀበልና ሰስሎተ ድንግልና (የድንግልና መወገድ) መኖሩ የታወቀ
ነው። ይህ ስለታወቀ ብቻ ሩካቤ ከተፈጸመ ማሕተመ ድንግልና አይኖርም ድንጋሌ ስጋ ካለ
ደግሞ ሩካቤ አልተፈጸመም በማለት ድምዳሜ ላይ አያደርስም።

1. ብዙ ጊዜ ሩካቤ አድርገው ድንጋሌ ስጋቸው ያልተወገደ እንደውም ማሕተመ


ድንግልናቸው ሳይገሰስ እስከ መጽነስ የደረሱ ብዙ ሴቶች ስላሉ ለዚህ ምስክር ናቸው።

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 131
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

2. ከዚህ በተጨማሪ ተፈጥሮአዊ ድንግልናቸው በሩካቤ ብቻ ሊገሰስ የማይቻል እየሆነ


በቀዶ ጥገና ሕክምና ማሕተመ ድንግልና እንዲወገድ የሚደረግላቸው ብዙ ሴቶች አሉ።

3. ከዚህ በተጨማሪ ማሕተመ ድንግልናን ከድንግልና ጋር ለይተን የምንመለከትበት ሁናቴ


አለ። ለምሳሌ: - ወንዶች እንደ ሴቶች ተጨባጭና ጉልህ የድንግልና ምልክት
ስለሌላቸው ከሴት ጋር ሩካቤ ፈጽመው የማያውቁ ሆነው ሳለ ድንግል አይደሉም
ለማለት አይቻልም።

ሩካቤን ፈጽመው የማያውቁ ሴቶች ሲወለዱ ጀምሮ ማሕተመ ድንግልና የሌላቸው ሊሆኑ
ይችላሉ። ወይም ከጊዜ በኋላ በከባድ የአካል እንቅስቃሴ፣ በአደጋ በሕክምና ወይም በእድሜ
ብዛት ምክንያት ማሕተመ ድንግልናቸው ሊፈርስባቸው ይችላል። እንዲህ ያሉ ሴቶች ማሕተመ
ድንግልናቸውን ቢያጡም ሩካቤ ፈጽመው እስካላወቁ ድረስ ደናግል መባላቸው የተጠበቀ ነው።
በሌላ በኩል ወንዶች ሩካቤ ፈጽመው ሳለ እንደ ሴቶች የሚገሰስ ማሕተመ ድንግልና
ስለሌላቸው ድንግልናቸው አልፈረሰም እንደማይባል ሁሉ ሴቶች ሩካቤ ስጋ እየፈጸሙ በልዩ
ልዩ ምክንያት ማሕተመ ድንግልናቸው ባይገሰስ መደበኛ ሩካቤ እስከፈጸሙ ድረስ ደናግላን
ሊባሉ አይችሉም። ለምሳሌ: - የሚያይ የሚመስል ዓይን እያላቸው በመፍዘዙ ምክንያት የማያዩ
ሰዎች የዓይን ምልክታቸው (ዓይን የሚባለው ሕዋስ ወይም መልክ) ጨርሶ ስላልጠፋ ብቻ
ዓይን አላቸው ይባላልን? እንደዚሁም ሁሉ ሩካቤ ፈጽመው ሳለ ማሕተመ ድንግልናቸው
ባለመጥፋቱ ብቻ ደናግል ሊባሉ አይችሉም። (ሕይወተ ወራዙት: 122-125)

በቤተ ክርስቲያን ባለው ሥርዓተ ጋብቻ መሰረት ድንግልናቸውን የጠበቁ ኦርቶዶክሳውያን


በሥርዓተ ተክሊል ጋብቻቸውን ሲፈጽሙ ሌላው ደግሞ ምንም እንኳ ምስጢረ ተክሊል
ባይፈፀምላቸውም በልዩ ልዩ ምክንያት ድንግልናቸውን ላፈረሱ አስቀድሞ በተክሊል ተጋብተው
በዝሙት ወይም በሞት ምክንያት ለፈቱ የመዓስባን ስርዓት ይፈፀምላቸዋል፡፡ አክሊል
ባይደረግላቸውም ሁለቱን አንድ የሚያደርግ የሚያፀናቸው ስጋውና ደሙ ስርዓት ለሁለቱም
ያለ ልዩነት የሚፈፀምላቸው ነው፡፡

7.10.3 በድንግልና መኖርና የሚያስገኘው ክብር


ድንግልና ስንመለከት በሁለት ከፍለን እናየዋለን፡፡ የመጀመሪያው እስከ ጋብቻ ድረስ ያለ
ሕይወት 2ቆሮ 6፡18 ከዝሙት ሽሹ ሰው የሚያደርገው ኃጢአት ሁሉ ከስጋ ውጪ ነው
ዝሙት የሚሰራ ግን በገዛ ስጋው ላይ ኃጢአትን ይሰራል፡፡ ሁለተኛው አስከ ሕይወት ፍጻሜ

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 132
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

የሚዘልቅ ማቴ 19፡7 1ቆሮ7 ይህ ሁሉ አይሆንም ለተሰጣቸው እንጂ ይህም ከመጀመርያ


ጀምሮ የሚቀጥልና ለማግባትም በደረሱበት አድሜ ላይ በጋብቻ በመኖር ዘር መተካትና ደስ
መሰኘትን መተውና እግዚአብ ሔር ለማገልገል መጽናት፡፡ ይህም ከፍ ያለ የመንፈሳዊ ሕይወት
ደረጃን የክርስቶስ ፍቅርና ውለታ በጥልቀት ማሰብና መረዳት ትልቅ ስብዕና ነው፡፡

1.እግዚአብሔርን ለማገልገል ፡- ሳየገቡ እንደ ነቢዩ ኤርሚያስ፣መጥምቁ ቅዱስዮሐንስና ቅዱስ


ጳውሎስ የመሳሰሉት በሙሉ ልብ እግዚአብሔር ለማገልገል ይጠቅማል፡፡ 1ቆሮ 7፡32-36
ድንግልናው በልብ ይጠብቅ ዘንድ ቢጸና መልካም አደረገ፡፡

2. እንደ መላዕክት ንጹሕ ሆኖ ለመኖር፡-2ጢሞ 1፡7 የሥጋ ፈቃድ ማሸነፍና መግታት መቻል
ሌሎችንም ፈተናዎች መታገስ የሚቻልበትን መንፈሳዊ ኃይልን ብርታትን ያጎናጽፋልና፡፡

3. ዝሙትና ርኩሰትን ድል ለማድረግ (በቅድስና ሰውነትን ለመጠበቅ) ፡- ቅዱስ ዮሐንስ በጽዮን


ተራራ ላይ በጉ የተባለ ክርስቶስን ከብበው ሰው ሊሰማው የሚቻለውን ምስጋና እየሰሙ እርሱ
ወደሚሔድበት ለመሔድ ስልጣን ያላቸው ተብለው በራዕይ ያያቸው 144ሺህ ደናግል
ድንግለናን መጠበቅ ያለው ክብር ያሳያል፡፡

4. የንጽሕናና የቅድስና ምሳሌ ነው፡- 2ቆሮ11፡2 ለአንዱ ንጹህ ድንግል ለክርስቶስ


አጭቼአችኋለው፡፡ ስለዚህ ወጣቶች ድንግልና ለመጠበቅ መትጋትና መጋደል ይኖርብናል፡፡

7.10.4 ድንግልና እና ሥርዓተ ተክሊል


ድንግልና የሚለውን ቃል አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ሲተረጉሙት፡- "በቁሙ ድንግልነት ድንግል
መሆን ክብርና ማኅተመ ሥጋ ንጽሐ ሥጋ" ብለዋል፡፡ ግልጽ ሲያደርጉት ደግሞ በደንገለ
ትርጉም ላይ እንዲህ ብለዋል፡-" ደነገለ አጥብቆ ጠበቀ ከለከለ ከሴት አራቀ ራሱን ወይም
ሌላውን" ይላል፡፡ ድንግልና የሚለውን አዲስ የአማረኛ መዝገበ ቃላትን ያዘጋጁት ሊቁ ደስታ
ተክለወልድ ሲገልጹ፡- " ድንግልና ፡- ድንግል መሆን መጠበቅ ወይም ክብርና" መጽሐፍ
ቅዱስም ስለ ድንግልና በብዙ ስፍራ ክብር መሆኑን ይገልጣል፡- "እርሱም ሚስትን በድንግልናዋ
ያግባ" ዘሌ21፡13 ገለዓዳዊው ዮፍታሔ አሞናውያንን በእጁ ይጥልለት ዘንድ ለእግዚአብሔር
ከድሉ በኋላ የሚያገኘውን መስዋዕት አድርጎ ሊያቀርብ ስለት በመሳሉ ከበሮ እየመታች
የተቀበለችው ልጁ ነበረችና መስዋዕት አድርጎ ከማቅረቡ በፊት ይህቺ ሴት ስለድንግልናዋ ሁለት
ወር ታለቅስ ዘንድ ወደ ተራራዎቹ መውጣቷ ለድንግልና ምን ያህል ክብር መስጠት እንዳለብን
የምንማርበት ሕይወት ነው፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 133
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

"ሁለት ወርም አሰናበታት ከባልንጀሮቿም ጋር ሄደች በተራራዎችም ላይ ለድንግልናዋ


አለቀሰች" ይህን ያህል ነው ድንግልና ሊከበር የሚገባው ለሞት እንኳን የተዘጋጀንበት
የሚያስጨንቅ ጊዜ ቢሆን ድንግልና ሊጠበቅ ይገባዋል ምክንያቱም ክብር ነውና የጌታ
ቤተመቅደስ ከጋብቻ በፊት በሚደረግ ዝሙት ይፈርስ ዘንድ የተገባ አይደለምና፡፡ መሳ11፡28-
40፤1ቆሮ6፡18-20 ደስታ ተክለ ወልድ ስለ ድንግል ትርጓሜ ሲተነትኑ በማይሰበር ብዕራቸው
ድንግል "ሴት ያላወቀ ወንድ ወንድ ያላወቃት ልጃገረድ (ዘሌ 21፡13)" ማለት ነው፡፡ ይሉና
ቀጠል አድርገው ድንግልናን ከእናትነት አስተባብራ የያዘች ቤዛዊተ ዓለም ድንግል ማርያምን
“ድንግል ማርያም ከመውለድ አስቀድሞ፣ በመውለድ ጊዜ፣ ከመውለድ በኋላ ድንግል የሆነች
ማርያም... በማለት ለደናግላን የዘላለም ምሳሌ መሆንዋን ጥልቅ በሆነ የነገረ ማርያም
ምሥጢር ይገልጣሉ፡፡ እውነት ነው ድንግል ማርያምን ከፈጣሪ በታች የሚመስላት አንዳች
ፍጡር የለም፡፡

ሥርዓተ ተክሊል ያለ ድንግልና የማይፈጸም ምሥጢር ነው፡፡ ስለዚህም ለተክሊል ክብር


እንድንበቃ ድንግልናችንን ልንጠብቅ ይገባል፡፡ ካልሆነ ግን ራሱን የብርሐን መልአክ
እስኪያደርግ ድረስ የሚለወጠው ዲያብሎስ በልዩ ልዩ ዝንጋዬ እንድንወድቅ ያደርገናል፡፡ ቅዱስ
ጳውሎስ ያለንን መንፈሳዊ ሀብት መጠበቃችን ዋጋ የሚያሰጥ መሆኑን በገለጸበት አውድ ፡-
"…መልካሙን ገድል ተጋድያለው ሃይማኖትን ጠብቄአለው…የጽድቅ አክሊል
ተዘጋጅቶልኛል ”2ጢሞ4፡7 እንዳለ፡፡ ለሃይማኖት መቆም ለሃይማኖት መቀደስ ለሃይማኖት
መጋደል እንዲገባ በስፋት ይገልጥልናል፡፡ እዚህ ላይ ማወቅ የሚገባን ድንግልና ሥርዓተ
ተክሊሉን ለማክበር ብቻ ሳይሆን እግዚአብሔርን ከመፍራት አንጻር እንደ ዕንቁ አክብረን
በመጠበቅ በዚህ ጉዳይ የሚመጣብንን የዲያብሎስ የሽንገላ ከንፈር፣ የመከራ ገፈት፣ የሥጋ
ፈቃድ ጦርነት፣ ከዓለም ብልጭልጭነት የተነሳ ከሚያመጡብን ሥቃይ እና መከራ በመጋደል
እንደ ሐዋርያው የጽድቅ አክሊላችንን ስለመቀበላችን የምናገኘውን ሕይወት ቤተክርስቲያን
በሚታይ አክሊል የማይታየውን የጽድቅ አክሊል በምሥጢረ ተክሊል መፈጸሟ የሠማይ
ሥርዓት በምድር ተሰራ የሚለውን በተግባር ማየታችን መሆኑን ነው፡፡

እንደ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ ድንግልና በሁለት ዓይነት መልኩ እንዳለ በተለያዩ ሉቃውንተ
ቤተክርስቲያን የብዕር ውጤቶቻቸው በስፋት ተገልጧል፡፡ ድንግልናን የሥጋ እና የነፍስ በማለት
በሁለት ከፍለን ልናየው እንችላለን፡፡ የደናግላን ምሳሌ የሆነች እመቤታችን ድንግል ማርያም

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 134
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

በሥጋም በነፍስም ድንግል ናት፡፡ አንዳንዴም የሕሊና ድንግልና የነፍስ ድንግልና ተብሎ ሊገለጽ
ይችላል፡፡ የ4ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ሊቅ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ፡ -“ድንጋሌ ሥጋ ለድንግሌ
ነፍስ መገለጫ፣ ጥላ ወይም አምሳል ነው፡፡” በማለት የሥጋ እና የነፍስ ድንግልና ያላቸውን
ትስስር በሚገባ ገልጽዋል፡፡ ይኸውም፡- ድንጋሌ ሥጋ ከግብረ ሥጋ ግንኙነት በመራቅ
የምንኖረው የቅድስና ሕይወት ሲሆን፤ ድንጋሌ ነፍስ ደግሞ ኃጢአታችንን ለካህናት አባቶቻችን
በመግለጽ በንሰሐ እየተመላለስን የምንኖረው ሰማያዊ ሕይወት ነው፡፡ እዚህ ላይ ከድንግል
ማርያም በስተቀር ሰው በሕሊናው ይበድላልና ዕለት ዕለት ንሰሐ ካልገባ በዚህ ንጹሕ ይሆን
ዘንድ የሚችል የለም፡፡

ሌላው ስለ ምሥጢረ ንሰሐ ታላቅነት በመጽሐፈ መነኮሳት እንዲህ ብሎ ያመጣዋል ፡-"ንስሐ


ግን የበደለን እንዳልበደለ ዘማዊን እንደ ድንግል ታደርገዋለች" የሚለውን ስለ ነፍስ ድንግልና
የተነገረውን ሐሳብ ለሥጋ ድንግልና እንደሆነ አስተምረውን በቤተመቅደሱ ሳይቀር ያለ
ድንግልና ተክሊል እንድናደርግ ያደፋፈሩን እና እኛም እስከ አሁን ድረስ "ማን በድንግልና
አገባ?" በሚለው ፈሊጥ ቤተመቅደሱን ባለመፍራት በተክሊል አግብተን ክብራችንን በነውራችን
የለወጥን ብዙዎች አለን እግዚአብሔር ይቅር ይበለን፡፡ ስንዱዋ እመቤት ቤተክርስቲያን በልዩ
ልዩ ምክንያት በፍቃዳችን ድንግልናችንን ላጣን በአማራጭነት የቁርባን ሥርዓትን እንድንፈጽም
አዘጋጅታልናለች፡፡ ዛሬ በቤተክርስቲያናችን የምንሰማውም ሆነ የምናየው የሚደረገውም ሆነ
የምናደርገው ውስጣችንን የሚያደማ እጅግ የሚያስከፋ እና አንገት የሚያስደፋ ነገር ነው፡፡

ድንግልና ለሴት ብቻ እንደ ግዴታ የተወሰነ ሕግ ይመስል የሴቷ ድንግልና እንጂ


የወንዱ የድንግልና ሕይወት ከግምት ውስጥ የማይገባበት፣
ይልቁንም ሳያፍሩ አርግዘው በተክሊል እንደ ደናግላን ሲያገቡ እንደ ማየት
የሚያስለቅስ፣
ሁለት ልጅ ወልደው በድንግልና የሚሰጠውን ክብር በገንዘብ ብዛት መንፈስ ቅዱስን
ሲያታልሉ አንዳች የማይሰማቸው ልበ ደንዳኖችን እንደማወቅ የሚያቆስል፣
ድንግልናቸው የተወሰደባቸው ሴቶች ሕይወታቸው ጨልሞ እግዚአብሔርንም ቤቱንም
እምነታቸውንም በመጥላት እየረገሙ ሲጮሁ ደፋሪዎቹ ግን ምንም እንዳላደረጉ
በተክሊል ሲጋቡ ማየት አይደለም መስማት እንኳን ምን ያህል ህሊናን ያደማል፣

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 135
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

የደካሞችን ስህተት ማመሳከሪያ በማድረግ ንሰሐ አባት እንኳን ሳይዙ መስካሪ


ሳይኖራቸው ለጊዜያዊ የውጭ ዕድል በድፍረት በከበረው በምሥጢረ ተክሊል ሲያገቡ
እንደማየት ምን የሚያስጨንቅ ጊዜ አለ?

አቡቀለምሲስ የተባለው ወንጌላዊው ዮሐንስ በራእይው፡- "ዓመፀኛው ወደፊት ያምጽ ርኩሱም


ወደ ፊት ይርከስ ጻድቁም ወደ ፊት ጽድቅ ያድርግ ፤ቅዱሱም ወደ ፊት ቀደስ አለ፡፡ እኔ በቶሎ
እመጣለሁ ለእያንዳንዱም እንደ ሥራው መጠን እከፍል ዘንድ ዋጋዬ ከእኔ ጋር ነው፣ አልፋና
ዖሜጋ ፊተኛውና ኋለኛው መጀመሪያውና መጨረሻው እኔ ነኝ፡፡"ራእ22፡12-13 እንዳለ እርሱ
የወደደውን ያድርግ፡፡ ቅዱሱን ጋብቻ በሥርዓተ ተክሊል ሌሎች ወገኖች የማያደርጉበት ብዙ
ምክንያት ቢኖርም በተለይ ከእኛ ሃይማኖት ውጪ የሆኑት ግን በዋናነት ጋብቻ ለእነርሱ
በተጋቢዎች መካከል እንደሚፈጸም ኮንትራት እንጂ የአንድነት ምሥጢሩን ብዙም ቦታ
አይሰጡትም፡፡ ይሁንና እኛ ግን መጽሐፍ ቅዱስ እንደ ነገረን ጋብቻ፡-

ሁለቱም አንድ ሥጋ የሚሆኑበት፣


አንድ ሐሳብ የሚያስቡበት፣
እንደ አንድ ልብ አሳቢ የሚናገሩበት፣
ባል ለሚስቱ ራሱን አሳልፎ የሚሰጥበት፣
በእግዚአብሔር መንፈስ አንድ የሚሆኑበትና እንደ እርሱ ፍቃድ የሚመላለሱበት፣
መኝታው ከዝሙት ንጹህ ይሆን ዘንድ በቃሉ መመሪያነት መኖር፣
እርሱ ሲፈቅድ ደግሞ የእርሱን ሥጦታ ልጆችን የምንቀበልበት የበረከት በር፣
እግዚአብሔርን በፍቅር ሆነን የምናመልከበት፣ እርስ በእርሳችን የምንረዳዳበት፣
በጸሎታችን ዲያብሎስን ድል የምናደርግበት ሕይወት ነው፡፡

ከድንግልና ጋር በተያያዘ በተክሊል ለማግባት ከሁኔታዎች አንጻር እንደ ደናግላን


በቤተክርስቲያን ምሥጢረ ተክሊል የምትፈጽምላቸው አሉ፡፡ ለምሳሌ፡-

 በሕክምና ምክንያት ድንግልናቸውን ለሚያጡ፣


 በተፈጥሮም ሲወለዱ ድንግልና ለሌላቸው፣
 ለአቅመ ሔዋን ሳይደርሱ በመደፈር ድንግልናቸውን ላጡ
 በከባድ ስራ ምክንያት የተነሳ ድንግልናቸውን ያጡ እነዚህ ያለፈቃዳቸው በመሆኑ እንደ
ደናግላን በተክሊል ማግባት ይችላሉ፡፡ፍ. ነገስት 24

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 136
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

7.11 በጋብቻ ጊዜ

በውሳኔ መጽናት የሁለቱም ወገን ዘመዶችና ጓደኞች የራሳቸው ፍላጎት እንዲሆንላቸው በማሰብ
ስለ ሠርጉ ፕሮግራም በማውጣት ከቤተ ክርስቲያን ውጭ እንዲደረግ ወይም ደግሞ በሁለቱም
በቤተ ክርስቲያንም (በሥርዓተ ተክሊል እንዲፈጸም በመዘምራን እንዲታጀቡ) እንደገናም
በዓለማዊ ሠርግ (በቬሎ እንዲወጡ፣ በባንድ እንዲታጀቡ) በማዋከብ ግራ ሊያጋቡ ይችላሉ ።
ነገር ግን የሚጋቡት አጃቢዎቹ ስላልሆኑ፣ መወሰን ያለበት በሙሽሮቹ ነው። ሙሽሮቹም
በውሳኔያቸው መጽናት አለባቸው። በውስጣቸው ያልተቆረጠ ዓለማዊ ፍላጎት ስላላቸውና
ከእግዚአብሔር ቃል ይልቅ ለቤተሰቦቻቸው ምክርና ትእዛዝ ክብር በመስጠት ሠርጉ
የተደበላለቀና ቅጥ ያጣ ብዙ ሰዎችንም የሚያሰናክል ሊሆን አይገባም ።

ጋብቻው በቅዱስ ቁርባን መሆን አለበት ሥርዓተ ተክሊል የሚፈጸምላቸው የሥጋ ድንግልና
ላላቸው ሲሆን ሌሎችም ክርስቲያኖች ጋብቻቸውን በቅዱስ ቁርባን ማድረግ ይችላሉ።
ክርስቲያናዊ ጋብቻ ያለ ቅዱስ ቁርባን አይደረግም። አንዳንድ ሰዎች ለፎቶ ግራፍና ለቪዲዮ
ሲሉ ብቻ ጋብቻቸውን በሥርዓተ ተክሊል ለማድረግ ያስባሉ፣ ይህ ተገቢ ስላልሆነ አስቀድመው
ስለ ጋብቻ ትምህርት በሚገባ መማርና ምርጫቸውን ከወዲሁ ማስተካከል ይገባቸዋል ።

7.11.1 የሥርዓተ ተክሊል መስፈርቶች ምንድን ናቸው?


ቤተ ክርስቲያን በተክሊል ተጋብተው በታወቀ ምክንያት ጋብቻቸው ለፈረሰባቸውና በማወቅም
ሆነ ባለማወቅ ድንግልናቸውን ላጡ /ላልጠበቁ /ምእመናን ልጆቿ በቅዱስ ቁርባን የምታጋባበት
ሥርዓት አላት። ይኸውም በንስሐ ታርመውና ተስተካክለው ለተመለሱ ክርስቲያኖች ከተክሊል
ጋብቻ የተቀደሰ ሥርዓት ጎን ለጎን በተለየ ሁኔታ የምታጋባበት መንፈሳዊ ሥርዓት ነው።
በሥርዓተ ጸሎቱ፣ አክሊል ባለመቀዳጀታቸውና ቅብዐ ሜሮን ባለመቀባታቸው ከሥርዓተ
ተክሊል አፈጻጸም ይለያል። የንስሐ ጸሎት ተደግሞላቸው የታዘዘው ሥርዓትም ተፈጽሞላቸው
ሥጋ ወደሙ ተቀብለው ይከብራሉ፡፡ በንስሐና በሥጋ ወደሙ ይባረካሉ።

በዓለማዊ ጋብቻ የተጋቡ ክርስቲያኖችም ጋብቻቸውን /ትዳራቸውን/ በንስሐና በሥጋ ወደሙ


የሚያስባርኩበት መስመር አለ፡፡ ቤተክርስቲያን ሁሉም ልጆቿ የቅድስናን ሕይወት
የሚያጣጥሙበት፣ በዚህ ዓለም ባመኑበት እምነት በሠሩትም ሥራ ከብረው መንግሥተ
ሰማያትን የሚወርሱበት መንገድ ባለቤት ነች። በዚህ መሠረት መጓዝን ትተው ድንግልና
የሌላቸው ሰዎች ለሰው ይምሰልና ለታይታ ብለው ለደናግል ብቻ የተፈቀደውን ሥርዓተ

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 137
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ተክሊል ቢያስፈጽሙ ከበረከት ይልቅ መርገምን ይቀበላሉ፡፡ ልብንና ኩላሊትን የሚመረምረውን


እግዚአብሔርን ማታለል ሞክረዋልና ሳይቀጡ አይቀሩም። እግዚአብሔር አምላካችን ከሁሉም
አዋቂነቱ ጋር ለቤቱና ለሥርዓቱም ቀናዒ፣ ፈራጅና ተበቃይም ነውና።

የመጀመሪያው ጋብቻ በእግዚአብሔር ፈቃድ በኤደን ገነት እንደተመሰረተ ሁሉ ዛሬም ሥርዓተ


ተክሊል የሚፈጸመው በቅድስት ቤተክርስቲያን ብቻ ነው፡፡ ይህም በዓለም ከሚደረገው ጋብቻ
ስለሚለይ ቅዱስ ጋብቻ ይባላል፡፡ በዚህ ደግሞ ይህንን የከበረ እና የተቀደሰ የምሥጢረ ተክሊል
ሰማያዊ ምስጢር ለመፈጸም ቤተክርስቲያን ለልጆቿ የራስዋ የሆነ ሥርዓት አዘጋጅታለች፡፡ ይህ
የሚጠበቅብን መስፈርት እንደ እግዚአብሔር ልጅነታችን ቀላል ነው፡፡ "ይህም በእግዚአብሔር
ዓይን ቀላል ነው" እንዲል " ለሚያምን ሁሉ ይቻላል"፡፡

1. በሃይማኖት አንድ መሆን፡-

ከሁሉም ማመን ይቀድማል፣ ከሁሉ መቀበል ይቀድማል፣ ከሁሉ የምናምነውን ማወቅ


ይቀድማል፣ ከሁሉም የምናየውን ማመን ይቀድማል፣ ከሁሉም መንፈሳዊ መሆን ይቀድማል፣
ከሁሉም መታመን ይቀድማል፣ በሃይማኖት አንድ መሆን ብቻም ሳይሆን እስከሞት ድረስ
ለመጋደል ራሳቸውን ያዘጋጁ ጥንዶች ሊሆኑ ይገባል፡፡ ይህ ካልሆነ ያላመነ ልብ ያለው ለጊዜው
እንኳን አመንኩ ቢል ከጋብቻው በኋላ አሻፈረኝ ብሎ ያለማመኑን እንደማመን ተቀብሎ
እግዚአብሔር የሌለበትን ኑሮ እንዲመራ ይገደዳልና ከሁሉም በፊት ማመን የተገባ ነው፡፡ ቅዱስ
ጳውሎስ አብዝቶ ስለ ትዳር ጽፎልናል ለምሳሌ ክርስቲያን እግዚአብሔርን ከማያውቅ ጋር
እንኳን ቅዱሱን ጋብቻ ይቅርና የባልንጀርነት ግንኙት እንዳያደርግ አስጠንቅቆ እንዲህ ሲል
ይመክራል፡-"አትሳቱ ክፉ ባልንጀርነት መልካሙን አመል ያጠፋል፡፡ በጽድቅ ንቁ ኃጢአትንም
አትስሩ እግዚአብሔርን የማያውቁ አሉና..."1ቆሮ15፡33

ተመልከቱ አንድ ሰው እግዚአብሔርን ካላወቀ እንዴት ሆኖ እኛ የምንኖረውን ሕይወት ሊኖር


ይችላል? እንዴት ሆኖ እግዚአብሔርን ስለ ማምለክ ይገባዋል? እንዴትስ ከኃጢአት ርቀህ ከእኛ
ጋር ኑር ስንለው እሺ ብሎ ለመኖር ይችላል? በዘመናችን የትዳር አንዱ አለመጽናት
የሐይማኖት ልዩነት መሆኑ ጸሐይ የሞቀው የአደባባይ ምሥጢር ነው፡፡ የፍቺውን ቁጥር
ለመገመት መዘጋጃ መሄድም አይጠበቅብንም፡፡ ሳንርቅ በየቤታችን ያለ ጉድ ነው፡፡ አንዳንዴ
ሁለቱም ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ነን እያሉ እርሱ ክርስቶስ አምላክ ነው ይላል፤ እርሷ ደግሞ

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 138
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ፍጡር ነው እንደውም ስለ እኛ እያማለደ ነው ትላለች፤ሁለቱም ለየራሳቸው ትክክል


መሆናቸውን አምነው ተቀብለዋል፡፡ ግን የተለያየ በፍጹም ሊገናኝ የማይችል እምነትና
አመለካከት ነው፡፡ ታድያ ያለባቸውን ልዩነት ወደ ትክክለኛው ማምጣት ሲገባቸው እምነት
የግል ነው ብለው ከአንድነት ወደ ሁለትነት ይሸጋገራል፡፡

7.11.2 የሥርዓተ ተክሊል አፈጻጸም


ሥርዓተ ተክሊል የሚፈጸመው ሁለቱም ደናግል ሆነው ሲገኙ ነው።
ሥርዓተ ተክሊል የሚፈጸመው በሁለቱ ተጋቢዎችና በወላጆቻቸው /አሳዳጊዎቻቸው/ ፈቃድ
መሠረት ነው፡፡ የሚጋቡትም ወንዶችና ሴቶች ለአካለ መጠን የደረሱና ማለትም ለወንድ ሃያ
ዓመት (20)፣ ለሴት አስራ አምስት (15) ዓመት ከሆናቸው ጀምሮ ያሉ እና በሃይማኖት
የተካከሉ /የተመሳሰሉ/ መሆን ይገባቸዋል:: ሥርዓተ ተክሊሉ የሚፈጸመውም በድንግልና
ለተወሰኑ እጮኛሞች ነው። ሥርዓቱ የሚፈጸመው ካህናትና ምእመናን በተሰበሰቡበት በጉባኤ
ነው እንጂ በስውር በድብቅ አይደለም። ከዚህ ውጪ የሚፈጸም የተክሊል ጋብቻ የለም።
የጋብቻው ሥርዓት በቤተ ክርስቲያን ቢፈጸምም በቅዱስ ቁርባን ያልታተመ ከሆነ የተክሊል
ጋብቻ ተፈጸመ ሊባል አይቻልም። የምሥጢራተ ቤተክርስቲያን ሁሉ ማኅተማቸውና
መክብባቸው ምሥጢረ ቁርባን ነውና። /ፍት.ነገ.፳፬፥፰፻፺፰‐፱፻፡፡)

ጋብቻ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በቃል ኪዳንና በቡራኬ፣ በጸሎተ ተክሊልና በቅዱስ ቁርባን
ሲፈጸም ምሥጢርነት ይኖረዋል። /ኤፌ. ፭፥፴፪፡፡/ በሚታዩ የአፈጻጸም ሥርዓቶችና ምልክቶች
የማይታይ ጸጋ እግዚአብሔ ይገኝበታልና። ምሥጢረ ተክሊል ከቤተ ክርስቲያን ውጪ በምንም
ዓይነት መንገድና በየትኛውም ቦታ አይፈጸምም፡፡ ከቤተ ክርስቲያን ከወጣ ካህናት ቢኖሩም
እንኳን በየትኛውም ቦታ አይፈጸምም፡፡ ቤተክርስቲያን ሳታውቀው የሚፈጸም ጋብቻ መንፈሳዊ
ጋብቻ ሊባል አይችልም፡፡ ሥርዓተ ተክሊሉ በሚፈጸምበት ዕለት የሚኖረው አፈጻጸም
የሚከተለውን ይመስላል፡፡

ሙሽራው ከሚዜዎቹና ከዘመዶቹ ጋር ወደ ቤተ ክርስቲያን ሄዶ በሰሜናዊው ማዕዘን ይቆማል።


ሙሽሪትም ከሚዜዎቿና ከዘመዶቿ ጋር ወደ ቤተክርስቲያን ገብታ በደቡባዊ ማዕዘን
ትቆማለች፡፡ ከዚያም በንስሐ አባታቸውና በሊቀ ዲያቆኑ አስተናባሪነት በቅድስት በተዘጋጀላቸው
የክብር ወንበር ላይ ይቀመጣሉ፡፡ ከእግራቸው ሥር ልዩ የክብር ምንጣፍ ይነጠፋል፡፡ ካህናቱ
ከፊት ለፊታቸው ካለው ጠረጴዛ ላይ በአንድነት የሚለብሱትን ነጭ ልብስ፣ ካባ፣ መጎናጸፊያ፣

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 139
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ተቀብተው የሚከብሩበትን ቅብዓ ቅዱስ፣ (ሜሮን) የሚቀዳጇቸውን አክሊላት፣ የሚያጠልቁትን


ቀለበትና የሚጨብጡትን መስቀል ያኖራሉ፡፡ ቀጥለውም ሥርዓተ ተክሊሉን አድርሰው
ቃልኪዳን በመገባባት እንደ ትእዛዙ ይፈጽሙላቸዋል። በመጨረሻም ቅዳሴ አስቀድሰው
ሥጋውን ይበላሉ፤ ደሙንም ይጠጣሉ፡፡

ሀ. መስቀል /ወንጌል/ ጨብጠው ቃል ኪዳን መግባታቸው

በሃይማኖት ጸንተው ለመኖር በሚያደርጉት ግብግብ የሚቀበሉትን ፈተና ያመለክታል፡፡


በመስቀሉ /በወንጌሉ/ ኃይልም ፈተናውን ድል እንደሚያደርጉት ያሳያል። መስቀልና ወንጌል
የድል አድራጊነት /የአሸናፊነት/ ምልክት ነውና።

ለ. አንድ ነጭ መጎናጸፊያ መጎናፀፋቸው፤

ሀብተ ወልድና ስመ ክርስትና ያላቸው የሥላሴ ልጆች መሆናቸውን ያጠይቃል። አንድ ልብስ
ለብሰው አንድ ክብር ወርሰው በዚህ ዓለም የመኖራቸውና በወዲያኛውም ዓለም አንዲት ርስት
መንግሥተ ሰማያትን ወርሰው ከክርስቶስ ጋር የሚኖሩ መሆኑን ያመለክታል፡፡ ነጭ ልብስ
/መጎናጸፊያ/ ክብርን፣ ትንሣኤንና የሚቀበሉትን የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ የሚያስረዳ ነውና፡፡

ሐ አንድ በሆነ ምሳሌያዊ ቀለበት የሁለቱንም አውራ ጣቶች ባንድ ማጣመራቸው፤

ቀለበቱ የሃይማኖት ምሳሌ ነው፡፡ ቀለበት በክብነቱና ፍጻሜ የለሽ በመሆኑ በቃል ኪዳን የጸናው
የተክሊል ጋብቻም ከሕይወት ፍጻሜ በስተቀር ማንም የማይለያየው መሆኑን ያሳያል።
በአንዲት ርትዕት ሃይማኖት የማይናወጽ መሠረት ላይ የታነጸ እንደመሆኑ የጠላት ነፋስ፣
የፈተና ጎርፍና ልዩ ልዩ ወቅታዊ የስሜት ማዕበላት /የማያፈርሱት/ መሆኑን ያመለክታል።

መ. በቅብዓ ቅዱስ (ሜሮን) ተቀብተው መክበራቸው

ቅብዐ ሜሮን በምሥጢረ ሜሮን እንዳየነው የመንፈስ ቅዱስ ማሳደሪያ ነው፡፡ በዚህም መሠረት
ረድኤተ መንፈስ ቅዱስ በትዳራቸው ዘመን ሙሉ የማይለያቸው መሆኑን ያጠይቃል።

ሠ. አክሊል መቀዳጀታቸው

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 140
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

አክሊል የድል አድራጊነት ምልክት እንደመሆኑ ድል አድራጊነታቸውን ያመለክታል። እስከ


ጋብቻቸው ዕለት ባሉት አፍላ የወጣትነት ቆይታዎች በርካታ ውጣ ውረዶችን በረድኤተ
እግዚአብሔር አልፈው፤ ድንግልናቸውን ጠብቀው፤ ለዚያች ዕለት በመድረሳቸው ቤተ
ክርስቲያን የምትሸልማቸው የክብራቸው መገለጫ ነው፡፡ በቀጣይ የሕይወት ዘመናቸው ደግሞ
በጾም፣ በጸሎት፣ በንስሐ፣ በሥጋ ወደሙና በመልካም ምግባራት ሁሉ ጸንተው እንዲኖሩ
ያስችላቸዋል። ትዳራቸውን በፈቃደ እግዚአብሔር ጠብቀው ከተጓዙ ሰማያዊውን የክብር አክሊል
የሚቀዳጁ መሆኑን ቤተ ክርስቲያን በምሥጢር የምታበሥርበት ሥርዓት ነው። በተጨማሪም
በተስፋ ልጆቿን የምታጸናበት የሕይወት መንገድ ነው።

7.11.3 በምስጢረ ተክሊል የሚገኝ ክብርና ጸጋ


ተክሊል ከምስጢራተ ቤተክርስቲያን አንዱ እንደመሆኑ ከቅዱስ ቁርባን ጋር ሲፈጸም ታላቅ
መንፈሳዊ ክብር ያስገኛል፡፡ማቴ 19፤6 ሙሽራውና ሙሽሪቱ በቅዱስ ጋብቻ አንድ ይሆናሉ፡፡
አንድም ሽንገላና ግብዝነት የሌለበት እውነተኛ ፍቅር ይኖራቸዋል፡፡ እንዲሁም መዝ 126፤3
የተባረኩ ሌጆችን ይወለዳሉ፡፡ በአጠቃላይ የመከባበርና የመፈቃቀድ ፣ የመዋደድና የመፈቃቀር
፣ የመረዳዳትና የመተማመን በሁሉ ነገር የመተማመን በሁሉ ነገር የመስማማት መንፈስ
በምስጢረ ተክሊል ያገኛሉ፡፡

ሀ. ሥጋዊና መንፈሳዊ አንድነት

ሁለቱ ተጋቢዎች ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዳስተማረን ከሁለትነት ወደ አንድነት


የሚመጡት በቅዱስ ጋብቻ /በምሥጢረ ተክሊል/ ነው፡፡ ይህ ጥምረት /አንድነት/ በጥበበ
እግዚአብሔር የሚከናወን ስለሆነ ሰዎች ሊለዩት እንዳይሞክሩ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል፡፡ /ማቴ
፲፱፥፮፡፡/ ይህም አንድነት በሥጋ ዓይን የሚታየው ሁለትነት ሳይጠፋ የሚከናወን የባልና ሚስት
ተዋሕዶ ስለሆነ ታላቅ ምሥጢር ነው። /ኤፌ ፭፥፴፪፡፡/ ይህም የአሳብ አንድነትና የጋራ
መተሳሰብን በማምጣት ይታወቃል። ጋብቻው በፈቃደ እግዚአብሔር ስለሚመራም ተጋቢዎች
የተረጋጋ ሕሊናና ሰላም ይኖራቸዋል፡፡ ማኅበረሰቡም ይህን በመረዳቱ “ባልና ሚስት ከአንድ
ባሕር ይቀዳሉ፤” እያለ አንድነታቸውን በሥነ ቃል ሲያውጅላቸው ይኖራል።

ለ/ እውነተኛና ዘላቂ ፍቅር

በባልና ሚስት መካከል የሚኖረው መተሳሰብ መቻቻልና ሰላም ሌላው የቅዱስ ጋብቻ ፍሬ ነው፡፡
የአንድነቱ መሠረት የሆነው እውነተኛ ፍቅር በተጋቢዎች መካከል ካለ ለጋብቻው ዘላቂነት

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 141
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ታላቅ አስተዋፅኦ ይኖረዋል፡፡ ጋብቻው የታነጸበት /የተመሠረተበት/ ሃይማኖት መሠረቱ


የማይነቃነቅ እምነት ሲሆነ የእውነተኛ ፍቅራቸውም መገኛ እሱው ነው፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ
ጳውሎስ እንዳስተማረንም በባልና ሚስት መካከል ሊኖር የሚገባው እውነተኛ ፍቅር በፍትወት
እንስሳዊት የተቃኘ አይደለም፡፡ በክርስቶስ እና በቤተክርስቲያን መካከል ካለው ጽኑ ፍቅር
የተቀዳ ነው እንጂ፡፡ (ኤፌ፭፥፳‐፴፪፡፡) ይህም እውነተኛ ፍቅር በፈሪሐ እግዚአብሔርና
በመተማመን ላይ የተመሠረተ ሆኖ አንዱ ላንዱ ራሱን መሥዋዕት አድርጎ እስኪሰጥ ድረስ
የሚያበቃ መሆኑን ያስገነዝበናል። ይህ እውነተኛ ፍቅር ጋብቻቸውን በተቀደሰው ሥርዓት
በቤተ ክርስቲያን ፈጽመው በቅዱስ ቁርባን ለታተሙ ባልና ሚስት እንዲሁም በንስሐና በሥጋ
ወደሙ ትዳራቸውን ላስባረኩ ጥንዶች መሆኑን ማስተዋል ያስፈልጋል።

ሐ. የተባረኩ ልጆች

እግዚአብሔርን የሚፈሩ ሰዎች በመንገዶቹም የሚጓዙ ሰዎች ምስጉኖች (ብፁዓን) እንደሚባሉ


ቅዱስ መጽሐፍ ይነግረናል፡፡ መገለጫዎቹንም ሲያብራራ እንዲህ ይላል: ‐ “የድካምህን ፍሬ
ትመገባለህ፣ ብፁዕ ነህ፣ መልካምም ይሆንልሃል። ሚስትህ በቤትህ እልፍኝ ውስጥ
እንደሚያፈራ ወይን ትሆናለች፤ ልጆችህም በማዕድህ ዙሪያ እንደ አዲስ የወይራ ተክል
ይሆናሉ፤ እነሆ እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው እንዲህ ይባረካል፡፡ እግዚአብሔር ከጽዮን
ይባርክህ በሕይወትህ ዘመን ሁሉ፤ የኢየሩሳሌምን መልካምነት ታያለህ፤ የልጆችህንም ልጆች
ታያለህ፤ በእስራኤልም ላይ ሰላም ይሁን።” (መዝ፻፳፮፥፩‐ፍጻሜው፡፡) የቀድሞዎቹ ነገስታቶች
ክርስትናቸውን አጥብቀው ይይዙ የነበሩ በመሆኑ ይተዳደሩበት የነበረውን መጽሐፍ ፍትሐ
ነገስት ማለታቸውን መቅድሙ ይገልፃል፡፡ ይህ መጽሐፍ ለሀገራችንም ሆነ ለዓለም ሕዝብ
የሕግ ምንጭ ሆኖ አሁን ደረስ የሚያገለግል ታላቅ መጽሐፍ ነው፡፡ ከአረበኛ ወደ ግእዝ
ቀጥሎም በእንግሊዝኛ እንዲሁም በ1962 ዓ.ም በግእዝ እና በአማረኛ የታተመው መጽሐፍ
አገልግሎቱን የዋለው ከ15ኛው መቶ ክፍለ ዘመን (ዓፄ ዘርአያዕቆብ 1444-1468) ጀምሮ ሲሆን
የኢትዮጵያ ሕገ መንግስት እስከ ረቀቀበት (1948 ዓ.ም) ድረስ በዚህ የሕግ መጽሐፍ ኢትዮጵያ
ትተዳደርበት እንደነበረ የታሪክ ሕያው ምስክርነትን መጥቀስ ይቻላል፡፡

7.12 ከጋብቻ በኋላ

ባልና ሚስት አንድ ስለሆኑ በመካከላቸው ሁለትነት መታየት የለበትም ሰው ከቤተሰቡ ጋር


የተዛመደው ስምምነቱ ተጠብቆለት ሳይሆን በተፈጥሮ ህግ ነው። እናትና አባቱን ይቀበላል

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 142
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

እንጅ ለመቀበል ድርድር ውስጥ አይገባም። ከእኛ በፊት የተደረጉ ነገሮችን በሙሉ አምነን
እንድንቀበል ተፈጥሮ ያስገድደናል። ትዳር ግን ተስማምቶ፣ ወዶና፣ ፈርሞ የሚገባበት ዘላቂ
ሕይወት ስለሆነ፣ ስምምነቱ እስከ ሕይወት ፍጻሜ የጸና ነው። “ሰው እናትና አባቱን ይተዋል
ወደ ሚስቱም ይጣበቃል ሁለቱም አንድ ይሆናሉ። ዘፍ 2፡24 ማቴ 19፡4” ባለው አምላካዊ ቃል
መሠረት በትዳራቸው ውስጥ ማንም ሊገባ አይፈቀድለትም። ወላጆችም ቢሆኑ ልጆቻቸው
ባይስማሙ ያስታርቃሉ፣ ይመክራሉ እንጅ ለእነሱ ስላልተስማማቸውና ግላዊ ጥቅማቸው
ስለቀረባቸው ብቻ ፍታት፣ ፍቺው እያሉ የልጆቻቸውን ትዳር መበጥበጥ የለባቸውም የብዙዎች
ትዳር የሚበተነው በቤተሰብ ጣልቃ ገብነት በመሆኑ ባለትዳሮች ይህን ጉዳይ አስቀድመው
ሊረዱት ይገባል ።

7.12.1 ባሎች ለሚስቶቻቸው ሊያሳዩአቸው የሚገባ ፍቅር


ቤተ ክርስቲያን ለክርስቶስ እንደምትገዛ ሚስትህ ለአንተ ትገዛልህ ዘንድ ትሻለህን? ክርስቶስ
ለቤተ ክርስቲያን እንዳደረገላት አንተም እንዲሁ ለሚስትህ አድርግላት፡፡ ሕይወትህን ስለ ርሷ
አሳልፈህ መስጠት ካለብህ ስለርሷ ሕይወትህን አሳልፈህ ስጥ፤ መከራም መቀበል ካለብህ
መከራን ለመቀበል አትሰቀቅ፡፡ አንተ ይህን ብትፈጽመው ስንኳ ክርስቶስ ለቤተ ክርስቲያን
ካደረገላት ጋር ሲነጻጸር የሚወዳደር አይደለም፡፡ ምክንያቱም አንተ ይህን ያደረግኸው ከአንተ
ጋር ፈጽማ ለተዛመደችህ ለአንዲት ሴት ነው፡፡ “እርሱ ግን ከእርሱ ለተመለሰችውና ለጠላቸው
ራሱን አሳልፎ ሰጠ፡፡” ርሱ ከርሱ የተመለሰችውንና የጠላችውን እንዲሁም ያቃለለችውን ገንዘቡ
ሲያደርጋት በማስፈራራት፣ በማስገደድ ወይም ይህን በመሳሰሉ ነገሮች አልነበረም፤ ነገር ግን
ኀዘን ባልተቀላቀለበት ፍጹም በሆነ ፍቅር በመሆን ነበር፡፡ አንተም ለሚስትህ እንዲሁ
አድርግላት አዎን! ምናልባት ሚስትህ አንተን ልታመናጭቅህ፣ ልትንቅህ፣ ልታፌዝብህም
ትችላለች፤ ቢሆንም ግን አንተ ለርሷ ካለህ አርቆ አሳቢነት ንጹሕ ፍቅርና ኀዘኔታ የተነሣ
ልትታገሣት ይገባሃል፡፡ ከሰው ሁሉ ጋር ተስማምቶ ለመኖርም ከእነዚህ የተሻሉ ነገሮች ፈጽሞ
አናገኝም፡፡ በተለይም ለባልና ለሚስት፡፡ አንድ ሰው አገልጋይ ባሪያውን በማስፈራራት ለመግዛት
ቢሞክር ለጥቂት ጊዜአት ሊገዛለት ይችላል፡፡ ሆኖም ይህ ባሪያ እንዲህ ዓይነት አገዛዝ
ስለማይመቸው ከእርሱ ፈጥኖ ይሸሻል፡፡

ነገር ግን አንድ ሰው የሕይወቱን አጋር፣ የልጆቹን እናት፣ የደስታው ሁሉ ምንጭ የሆነችውን


ሚስቱን በፍቅርና በፍጹም አክብሮት እንጂ ልክ እንደ ባሪያ በፍርሃት ሰንሰለት በማሰር ወይም
በማስጨነቅ ርሷን ሊገዛት መሞከር አይገባውም፤ ሚስት በባልዋ ምክንያት የምትሸበር ከሆነ

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 143
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

አንድነታቸው ምን ዓይነት አንድነት ነው? ከባሪያ ጋር እንደ መኖር ከሚስት ጋር መቀመጥ


ለባል የሚፈጥርለት ምን ዓይነት ደስታ ነው? አዎን ይልቁኑ አንተ ስለ ርሷ ስትል ብዙ
መከራዎችን መቀበል ሲገባህ በተቃራኒው በቁጣ ርሷን በማስጨነቅና በማሸበር ታስፈራራታለህን?
ክርስቶስ እንዲህ አላደረገም፡፡ “በውኃ መታጠብና ከቃሉ ጋር አንጽቶ አንዲቀድሳት ስለ ርሷ (ስለ
ቤተ ክርስቲያን) ራሱን አሳልፎ ሰጠ ፡፡ ከቃሉ እንደምንረዳው ቤተ ክርስቲያን (እኛ) አስቀድማ
ንጽሕት አልነበረችም፤ ጉድፍ ነበረባት፤ መልከ ጥፉም ነበረች፡፡ ስለዚህም ለእርሱ የተገባች
አልነበረችም፡፡ አንተ እንደ ቤተ ክርስቲያን የሆነችውን ሴት ሚስትህ ትሆን ዘንድ አትመርጥም፡
፡ ቤተ ክርስቲያን ከክርስቶስ የተለየችውን ያህል ከአንተ ፈጽማ የማትስማማውን ሴት ሚስትህ
ትሆን ዘንድ ወደ አንተ አታቀርባትም፡፡

እርሱ ግን እጅግ መልከ ጥፉ ብትሆንም አልጠላትም፣ አልተጸየፋትም፣ ስለ መልከ ጥፉነቷ


የተጻፈውን መስማት ትፈልጋለህን? ቅዱስ ጳውሎስ ስለ ርሷ ምን እንደሚል ስማ “ቀድሞ
ጨለማ ነበራችሁ” (ኤፌ. ፭፡፰) አላት፤ የገጽታዋን መጥቆር ትመለከታለህን? ከጨለማስ የበረታ
ጥቁረት ምን አለ? የአመሏን መክፋት ደግሞ ስማ “በክፋትና በምቀኝነት” ይልና “የምንኖር”
ይላል፤ ስለ ነውሮቿ ደግሞ “የማንታዘዝና የምንስት ለልዩ ልዩ ተድላ እንደ ባሪያዎች የምንገዛ”
ይላታል (ቲቶ. ፫፡፫) ፡፡ ነገር ግን ለርሷ ስለተደረገላት በጎነት ምን ማለት ይቻለኛል? ርሷ
ስንፍናን የተሞላችና ክፉ አንደበት የነበራት እንዲሁም በነውሮቿ ሁሉ ያደፈች ብትሆንም
እነዚህ ሁሉ ጠባዮቿ ከርሷ አላራቀውም፡፡

ነገር ግን ልክ የደስ ደስ እንዳላት ልጃገረድ በአፍቀሪም ዘንድ ለምትወደድ ውብ ሴት


እንደሚደረገው ርሱ ስለ ርሷ ራሱን አሳልፎ የሰጠ አይደለምን? ይህንንም በማድነቅ ቅዱስ
ጳውሎስ “ስለጽድቅ የሚሞት በጭንቅ ይገኛልና ስለ ቸር ሰው ግን ሊሞት ስንኳ የሚደፍር
ምናልባት ይገኛል” ይልና “ነገር ግን ኃጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቷልና” (ሮሜ. ፭፡
፯-፰) ብሎአል፡፡ በዚህ መልክ ርሷ ለርሱ ትሆን ዘንድ አቀረባት፤ በመንፈሳዊ ውበትም
አስጌጣት፤ ንጽሕት አደረጋት፤ ስለ ርሷም ራሱን አሳልፎ ለመስጠት ስንኳ የጨከነ ሆነ፡፡
(የትዳር አንድምታ እንደ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ አስተምህሮ ገጽ 17-19)

7.12.2 በጋብቻ ውስጥ ግብረ ሥጋ ግንኙነት የማይፈጸምባቸው ቀናት


• በአራስነት ወቅት (ለወንድ ፵፣ ለሴት ፹ ቀናት እስኪሞላ ያሉት ቀናት)፤
• የወር አበባ ጀምሮ እስኪጠራ (ሰባት ቀናት)፤
• ሥጋ ወደሙ ከመቀበል ቀድሞ ያሉ (ሦስት ቀናት)፤

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 144
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

• ሥጋ ወደሙ ከተቀበሉ በኋላ (ሦስት ቀናት)፤


• ሁለቱ ሰናብት (ሰንበቶች)፤
• ዐበይት በዓላት (ዓመታዊ የቤተ ክርስቲያን በዓላት)፤
• በየወሩ በ፲፪፣ በ፳፩ እና ፳፱ ያሉ (የግዝት በዓላት) ፤
• እርግዝና ሲገፋ፤
• ቢቻል በሰባቱ አጽዋማት፤ በተለይ ግን በዐቢይ ጾም፤ (ፍት. ነገ ፳፬፥፱፻፳፩‐፱፻፳፬፡፡)
ወጣቶች ለአቅመ አዳምና ሔዋን ደርሰው ማግባት ከፈለጉ የምሥጢረ ተክሊልን ጋብቻ
መምረጥ ለሥጋም ለነፍስም እንደሚበጅ መረዳት አለባቸው። አባቶቻችንና እናቶቻችን በፈቃደ
እግዚአብሔር በመታገዝ ከማግባታቸው በፊት ድንግልናቸውን ጠብቀው ማለትም ታቅበው
ይኖሩ ነበር፡፡ ከዚያ በኋላ በድንግልና በመጋባት የተባረከ የትዳር ጊዜን እንዳሳለፉ መርሳት
አይገባም። በፈቃደ እግዚአብሔር የሚመራ ሰው እግዚአብሔር መንገዶቹን ሁሉ ስለሚያቃናለት
አይቸገርም፡፡ የምትሆነውን የትዳር አጋር በወላጆቹ፣ በራሱና በወደደው ላይ አድሮ
ስለሚመርጥለት ባትመቸኝስ፥ ባይመቸኝስ በሚል ስጋት አይጨነቅም።

ቀድሜ መሞከር አለብኝ በሚል ድፍረትም ክብሩን የሚያሳጣውንና የሚያስቀጣውን ኃጢአት


አይሠራም። በማያዋጣ ሥጋዊ ጥበብ ሽፋን ሥጋዊ ፍትወቱን ከማርካት ይልቅ በጸሎት
ፈጣሪውን ወደ መጠየቅ ስለሚያዘነብል የተመካበት እግዚአብሔር ጎዶሎውን ሁሉ
ይሞላለታል። የሚመቻትን ረዳት እንደሚሰጠው ስለሚያምን እግዚአብሔር ይደሰትበታል።
ክርስቲያኖች ሁሉ ዓለማዊውን ፍልስፍናና ሙከራ (ትግበራ) ትተው በተወክሎ እግዚአብሔር
የትዳር አጋራቸውን መፈለግ፣ መምረጥ፣ ከእግዚአብሔር እጅ መቀበልና ትዳርን መመሥረት
ይጠበቅባቸዋል።

በተጨማሪም ሁለቱ እጮኛሞች በድብቅ ስለቆረቡ ወይም ምናልባትም የንስሐ አባታቸው


/ካህኑ/ ከተጠቀሰው ሥርዓት ውጪ ስላማማላቸው ሥርዓተ ተክሊል እንደተፈጸመና በሥርዓተ
ቤተክርስቲያን እንደተጋቡ እንደማይቆጠር ማስተዋል ያስፈልጋል። ብዙዎች ግን
ስለማይተማመኑና በተክሊል መጋባትን እንደመታሰር ስለሚቆጥሩት ከተቀደሰው የጋብቻ
ሥርዓት ይርቃሉ፡፡ በተጨማሪም ስለ ቅዱስ ጋብቻ (የተክሊል ጋብቻ) አስፈላጊነት፣ አፈጻጸምና
ክብር ባለማወቅም ዓለማዊውን ጋብቻ የሚመርጡ አሉ፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 145
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

7.12.3 ፍቺ የሚፈቅድባቸው ምክንያቶች

1. ሞት ከሁለቱ አንዳቸው በሞት ቢለዩ በሕይወት የቀረው ሌላ እንዲያገባ ተፈቅዶለታል ።


ነገር ግን ጋብቻው በአንድ ሃይማኖት ከሚኖሩና በቅዱስ ቁርባን መጋባት ከሚፈልጉ ጋር
መሆን አለበት። ሮሜ 7፡2 1 ቆሮ 7፡39

2. የጤና ጉድለት በትዳር ለመኖር እስከማይችሉበት ድረስ በእንዳቸው ላይ የጤና (በጾታዊ


አካላቸው ላይ) ችግር ካገጥማቸውና ለአብረው ለመኖር ካልተስማሙ መፋታት ይችላሉ።
ምክንያቱም ከጋብቻ መሠረታዊ ፍላጎቶች ከሆኑት ውስጥ አንዱ ስለተጓደለ ካልተስማሙ በቀር
አብረው ለመኖር አይገደዱም ።

3. የሃይማኖት ልዩነት አንዳቸው ከኦርቶክሳዊት ተዋሕዶ ሃይማኖት ወጥተው የሌላ እምነት


ተከታይ ከሆኑና ተመክረው መመለስ ካልቻሉ በሃይማኖቱ የጸናው ትዳሩን መፍታት
ይፈቀድለታል። ነገር የተለየው ተመልሶ ካመነና ይቅርታ ከጠየቀ የትዳር ጓደኛውም
ይቅርታውን ከተቀበለውና ከተስማማ በትዳራቸው መቀጠል ይችላሉ ።

4. ዝሙት ከሁለቱ አንዳቸው በዝሙት ከወደቁ ንጹሁ ሰው ትዳሩን መፍታት ይችላል። ነገር
ግን ወሬ በመስማትና በጥርጣሬ ሳይሆን በተጨባጭ ከተገኘ መሆን አለበት። ማቴ 5፡32
የቤትን ገመና ለውጭ ማውራት ነገረ ሰሪ የሆኑ ሰዎችን ሊያስገባ ይችላልና መጠንቀቅ
ያስፈልጋል። የትዳር መሠረቱ በእውነት መግባባትና መተማመን ስለሆነ በሁኔታዎች
መጠራጠርና መጨቃጨቅ አያስፈልግም። ባልና ሚስት በትዳራቸው በሚኖረው ማንኛውም
ዓይነት ኑሮ በመመካከርና በመወያየት መወሰን አለባቸው ።

ትዳር የሁለቱም የጋራ ሕይወት ስለሆነ ፤ መመሪያ አውጪና ተቀባይ መሆን የለባቸውም ።
ገቢያቸውም ሆነ ወጪያቸው በጋራ መ ወሰን አለበት። ትዳሩ እውነት የሚሆነው እነዚህ
ሲሟሉ ነውና ። የባለትዳሮችን አንድነት የበለጠ የሚያረጋግጡት የሚወልዷቸው ልጆች ናቸው
ልጆች የሁለቱም እኩል ሀብቶች ስለሆኑ ያቀራርቧቸዋል። ትዳራቸውንም ማክበር ያለባቸው
የሚወዷቸው ልጆቻቸው እንዳይበታተኑባቸው በማሰብ ጭምር መሆን አለበት። በመካንነት
ምክንያት መውለድ ያልቻሉት ባለትዳሮችም እግዚአብሔር ለእነሱ የወሰነላቸው የተሻለ መሆ
ኑን በማሰብ ማመስገን ይገባቸዋል እንጅ በአምላክ ሥራ ገብተው ማማረር አይገባቸውም።
የተወለደውም ቢሆን ካልተባረከ ሊሞት ወይም መጥፎ ልጅ ሊሆን ይችላል። እግዚአብሔር

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 146
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

አውቆ ያደረገውን አምላካዊ ጥበብ ባለማወቅና ያሰቡት ስላልተሳካላቸው ብቻ ራሳቸውን


የተረገመ አድርገው መቁጠር የለባቸውም እግዚአብሔር ያደረገው ሁሉ ለበጎ ነው ብሎ መቀበል
ይገ ባል። ገና ከማያውቋቸውና ካልተወለዱ ልጆች ይልቅ የሚወዱትና ከእግዚአብሔር አደራ
የተቀበሉት የትዳር አጋራቸው እን ደሚበልጥባቸውም በማስተዋል ማሰብ ይገባቸዋል። ዘፍ 30

ስለ ሰንበትም የእግዚአብሔርን ሥርዓት ጠብቁ በማለት አስጠንቅቋቸዋል፡፡ ዘሌ 8፡35 እነያሱ


ከማይቱን ሰባት ጊዜ የዞሩት ሥርዓቱ ስለሚያዛቸው ነው፡፡ ኢያ 6፡15 ሰሎሞን እግዚአብሔርን
በመውደዱ በኮረብታው የመስገድን የመሰዋትን እና የማጠንን ሥርዓት ከአባቱ ተምሮ
በሥርዓት ይፈጽም ነበር፡፡ 1ነገ 3፡3 ብዙ ብዙ መጥቀስ ይቻላል፡፡ የእግዚአብሔር ሥርዓት ቅን
መሆኑን የነገረን ይፈጽመው የነበረው ዳዊት ነው፡- "የእግዚአብሔር ሥርዓት ቅን ነው፤ልብንም
ደስ ያሰኛል የእግዚአብሔር ትእዛዝ ብሩህ ነው ዓይንንም ያበራል፡፡" መዝ 18(19) ይህ ብቻ
አይደለም እግዚአብሔር "የእስራኤል ልጆች ከእኔ ዘንድ በሳቱ ጊዜ የመቅደሴን ሥርዓት የጠበቁ
የሳዶቅ ልጆች ሌዋውያን ካህናት ያገለግሉኝ ዘንድ ወደ እኔ ይቀርባሉ..." ወደ እግዚአብሔር
የሚያቀርበን ልዩ መንገድ ሥርዓት መጠበቅ መሆኑን ገልጦልናል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ
ሲያጠቃልልልን ፡- "ነገር ግን ሁሉ በአግባብና በሥርዓት ይሁን፡፡"1ቆሮ14 መጽሐፍ ቅዱስም
ሆነ ልዩ ልዩ መጽሐፈ ሊቃውንት እንደሚመክሩን አንድ ሰው በሥርዓተ ተክሊል ጋብቻውን
ለመቀደስ ቢፈልግ ሊያሟላው የሚገባው መስፈርቶች አሉ፡፡ እነዚህን ስናይ መሰረታችን
መጽሐፍ ቅዱስ፤ፍትሐ ነገስት አንቀጽ 24 (የጋብቻ አንቀጽ) እና መጽሐፈ ተክሊል ይሆናል፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 147
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

8. ምሥጢረ ንስሓ
መግቢያ

እግዚአብሔር አምላካችን ለሰው ልጆች ሥጋዊ ደዌ ሕመም ፈውስ የሚሆኑትን መፈወሻ


መድኃኒት እንደሰጠን ሁሉ የነፍስ ደዌ ኃጢአትን የሚያርቅና ከሕመሙ የሚፈውስ መድኃኒት
ንስሐን ሰጥቷቸዋል: ደዌ የሆነው ኃጢአት በምድራዊ ኑሮአችው ሁሉ አብሮ እንደሚኖር
የታወቀ በመሆኑ መድኃኔዓለም ክርስቶስ መድኃኒቱንም አብሯቸው ይኖር ዘንድ ከሐኪሞች
ከካህናት ጋር በመካከላችው አኖረው፡፡

8.1 የምሥጢረ ንስሓ የቃሉ ትርጉም

ንስሐ ማለት ከጥምቀት በኋላ በሠሩት ኃጢአት ከልብ ማዘን፣ ወደ መምህረ ንስሐ ሄዶ
መናዘዝ (ኃጢአትን መናገር)፣ ጥፋትን ላለመድገም መወሰንና በእግዚአብሔር ቸርነት፥ በካህኑም
የማሰር የመፍታት ሥልጣን አምኖ አነሰ፣ በዛ ሳይሉ የተሰጠውን ቀኖና በደስታና በምስጋና
ተቀብሎ መፈጸም ነው። ከላይ በተገለጸው መሠረት ምሥጢረ ንስሐ ምእመናን ከኃጢአት
ቁራኝነት የሚላቀቁበትና አዲስ ሕይወትን የሚያገኙበት የድኅነተ ነፍስ መንገድ ነው፡፡ ሥርወ
ቃሉ “ነስሐ” የሚለው የግእዝ ቃል ሲሆን ትርጉሙም ንስሐ ገባ፣ ዐዘነ፣ ተጠጠተ፣ ተመለሰ፣
ክፉ ዐመሉን ተወ፣ ጠባዩን ለወጠ፣ ማለት ነው። (ኪ.ወ.ክፍሌ)

ንስሐ የግዕዝ ቃል ሲሆን ትርጉሙ ጸጸት ነው፡፡ ጸጸትነቱ ሰው በሠራው ኃጢአት ተጸጽቶ
ኃጢአቱ ይሰረይለት ዘንድ እግዚአብሔርን በሐዘን በለቅሶ ሲለምን እንጂ የጐልማሳ ሚስት
ሳልቀማ፣ የሰው ገንዘብ ሳልሰርቅ ቀረሁ … በማለት የሚጸጸተው ጸጸት አይደለም፡፡
ንስሐ ለተጠመቁ ሰዎች ከጥምቀት በኋላ የተሰጠች ሀብት ናት። በጥምቀት ከእግዚአብሔር
የምትገኝ የልጅነት ሁለተኛ ማዕረግ ናት፡፡ በሃይማኖት ገንዘብ ያደረግነው የመንግሥተ ሰማያት
አራቦን ማለትም መግዣ ናት። ንስሐ ለሚሿት ሰዎች የተከፈተች የይቅርታ በር ናት፡፡ በንስሐ
በርነት ከፈጣሪ ወደሚገኝ ቸርነት እንቀርባለን።

ይህ ቃል የግዕዝ ቃል ነው፡፡ ትርጉሙም በሰሩት ኃጢያት መጸጸት ምነው ባልሰራሁት


ባላደረኩት ብሎ ማልቀስ ወደ ኃጢያት ላለመመለስ መወሰን፣ በሕጉ ጸንቶ ለመኖር ቃል
መግባት፡፡ ክርስቲያን በጥምቀት ከአለም ክፉ ስራዎች ሁሉ የተለየ ነው፡፡ ህይወቱ ለክርስቶስ

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 148
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

የተሰጠ ነው፡፡ ሮሜ 12፡1 የመጨረሻው ግቡና ዓላማው ሥርየተ ኃጢያትን ማግኘት እና


የዘላለም ሕይወት መወረስ ነው፡፡ አካሉ የመንፈስ ቅዱስ ነው፡፡ 1ቆሮ 6-19

8.2 የምሥጢረ ንስሐ አመሠራረት

ምሥጢረ ንስሐን የመሠረተ ራሱ ጌታችን ነው። ለሰው ልጆች አዛኝ የሆነው መፍቀሬ ሰብ
ክርስቶስ የኛን ኃጢአት ሁሉ በሰውነቱ ተሸክሞ በሕማምና በሞቱ አንድ ጊዜ አድኖናል።
ይህንንም ጸጋ በምሥጢረ ጥምቀት አግኝተነዋል። ከዚህ በኋላ ለምንፈጽመው በደል ማስተስረያ
እንዲሆነን ለሐዋርያትና እነሱን ለሚከተሉት ካህናት ሥልጣንን በመስጠት ምሥጢረ ንስሐን
መሥርቶልናል። ኃጢአትን የማስተስረይ ሥልጣን የእግዚአብሔር ብቻ ሲሆን ለእኛ ጥቅምና
ደህንነት ሲል ለቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች ለጴጥሮስና ለሐዋርያት ተከታዮች ሰጥቷል። ቅዱስ
ጴጥሮስ ስለ እውነተኛ እምነቱ ከመሰከረ በኋላ ሥልጣነ ክህነትን ማለትም የመንግሥተ
ሰማያትን ቁልፍ ክርስቶስ ሰጥቶታል። እንዲህም ብሎታል «የመንግሥተ ሰማያትንም
መክፈቻዎች እሰጥሃለሁ በምድር የምታስረው ሁሉ በሰማያት የታሰረ ይሆናል፤ በምድርም
የምትፈታው ሁሉ በሰማያት የተፈታ ይሆናል» ማቴ. ፲፮፥፲፱

እንደዚሁም ይህን ሥልጣን ለሌሎች ሐዋርያትም ሰጥቷቸዋል። /ማቴ ፲፰፥፲፰/። ከትንሣኤው


በኋላም ለሦስተኛ ጊዜ ኃጢአትን የማስተስረይ ሥልጣን ሰጥቷቸዋል። «አብ እኔን እንደላከኝ
እኔም ደግሞ እልካችኋለሁ አላቸው። ይህንንም ብሎ እፍ አለባቸውና መንፈስ ቅዱስን ተቀበሉ።
ኃጢአታቸውን ይቅር ያላችኋቸው ሁሉ ይቀርላቸዋል፤ የያዛችሁባቸው ተይዞባቸዋል አላቸው።»
/ዮሐ. ፳፥፳፩-፳፫/። ስለዚህ ኃጢአትን የማስተስረይ ሥልጣን ለነሱ የተሰጠ ስለሆነ በሐዋርያት
እግር ለተተኩ ለቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ካህናት ኃጢአትን መናዘዝ ይገባል።

8.3 ንስሐ ለምን አስፈለገ?

የቀደመ በደልና ኀጢአት ይደመሰስ /ይሠረይ/ ዘንድ ንስሐ በእጅጉ አስፈላጊ ነው። ሐዋርያው
ቅዱስ ዼጥሮስ በበዓለ ሃምሳ በጽርሐ ጽዮን ዙሪያ ተሰብስበው ለነበሩ እጅግ በርካታ ሕዝቦች
የድኅነትን ትምህርት አስተማራቸው፡፡ በትምህርቱ የተመሰጡት እነዚያ ሰዎችም “ምን
እናድርግ?” ባሉ ጊዜ የተመለሰላቸው መልስ ከንስሐ ሕይወት ጋር የተያያዘ ነበር። (ሐዋ.፪፥
፲፬‐፵፩፡፡) በቤተ መቅደስ በር ላይ ይቀመጥ የነበረውን ድውይ /መሔድ የተሳነውን ሕሙም/
ቅዱስ ጴጥሮስና ቅዱስ ዮሐንስ በክርስቶስ ስም በፈወሱት ጊዜ መገረምና መደነቅ የሞላባቸው

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 149
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

አይሁድ ብዙ ነበሩ። ቅዱስ ጴጥሮስ ለእነዚህም በሥጋ ስለተገለጠው አምላክ ካስተማራቸው


በኋላ አለቆቻቸው በዓለማ ክርስቶስን በካዱትና በገደሉት ጊዜ ተባባሪዎቻቸው የሆናችሁት
እናንተ እንግዲህ ኀጢአታችሁ ይሰረይላችሁ ዘንድ ንስሐ ግቡ፤ ተመለሱም፤ (ሐዋ. ፫፥፲፱፡፡)
መባላቸውን እናነባለን። እነዚህ ሁለት ተያያዥ ኃይለ ቃላት (ነጥቦች) የንስሐን አስፈላጊነት
የሚያመለክቱ ናቸው፡፡ ንስሐ የማንኛውንም ምእመን ቁስለ ነፍስ የሚፈውስ መንፈሳዊ
መድኃኒት ነው::

“ሸማ ሲያድፍ በውሃ፤ ሰውነት ሲያድፍ በንስሐ” እንዲሉ:: ሀብተ ወልድና ስመ ክርስትና
የተቀበለ ሰው ከቀደመ ኃጢአቱ በጥምቀት ቢነጻም በቀረ ዘመኑ ከሚሠራቸው ጥፋቶች
በምሥጢረ ንስሐ እንዲነጻ ክርስቶስ ፈቀደለት፡፡ አስቀድሞ ለሐዋርያት ከዚያም ቀደም ባለው
ምዕራፍ እንዳየነው በተዋረድ ለተነሡና ለሚነሡ አገልጋዮች (ካህናት) ኃጢአትን ይቅር
የሚሉበትና የሚይዙበት /የሚፈቱበትና የሚያስሩበት/ ሥልጣንን ሰጣቸው፡፡ (ዮሐ፳፥፳፩‐፳፫
ማቴ፲፰፥፲፰) ይህም ማለት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ኃጢአትን የሚያስተሰርዩበትን ጸጋ፣
መንግሥተ ሰማያትንም ከፍተው የክርስቶስን መንጋ የሚያስገቡበት ቁልፍ ለካህናት አባቶቻችን
ሰጥቷቸዋል።” የመንግሥተ ሰማያትንም መክፈቻዎች እሰጥሃለሁ፤ በምድር የምታስረው ሁሉ
በሰማያት የታሰረ ይሆናል፤ በምድርም የምትፈታው ሁሉ በሰማያት የተፈታ ይሆናል” በማለት
እንደገለጸልን፡፡ (ማቴ፲፮፥፲፮‐፳፡፡)

በሉቃስ ወንጌል ምዕ፲፭፥፬- ፍጻሜው ያለውን ታሪክ ስንመለከት ከመንጋው ተነጥሎና ባዝኖ
በምድረ በዳ የጠፋውን በግ፣ በቤት ውስጥ የጠፋውን ድሪምና ከቤተሰቡ ተለይቶ ወጥቶ
የጠፋውን ታናሹን ልጅ እናገኛቸዋለን። ባለበጎቹ፣ ባለድሪሟና፣ የልጁ አባት በጠፋባቸው ነገር
እጅግ እንዳዘኑ፣ የጠፋባቸውን አጥብቀው እንደፈለጉና ባገኙትም ጊዜ ፍጹም ደስ እንዳላቸው
እናነባለን፡፡ እነዚህ ተገናዛቢ ታሪኮች ሁሉም የንስሐን ክብር፣ ኃይልና ምሥጢር ያሳዩናል፡፡
ከሀገርና ከወገን ተለይቶ፤ ከሃይማኖት፣ ከምግባር ምድረ በዳ በሆነ ቦታም መጥፋት አለ፡፡ በቤት
ውስጥ ሆኖ የትም ሳይወጡ ባሉበት ሁኔታ መጥፋት አለ:: ከሞላ ከተትረፈረፈ፥ ሰላምና ፍቅር
ከሰፈነበት ቤት አሻፈረኝ ልቀቁኝ ብሎ ወጥቶም መጥፋት አለ፡፡

ባለንብረትና ወላጅ አባት የሆነ ሰው ደግሞ ያ ነገር የጠፋበትን መንገድና ሁኔታ እያሰላሰለ
ከመናደድ ይልቅ የሚገኝበትን መንገድ በማሰብ ፍለጋው ላይ ተግቶ ይሠራል:: ባገኘው ጊዜ
ደግሞ ባለው ነገርና አቅም ሁሉ ደስታውን ይገልጻል። በመንፈሳዊ የሕይወት ጉዞም ሰዎች

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 150
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

በተመሳሳይ እይታ በልዩ ልዩ መንገድ ከእግዚአብሔር እጅ ሊወጡ፤ ከመንፈሳዊት ቤታቸውም


ሊኮበልሉ /ሊጠፉ/ ይችላሉ:: እግዚአብሔር አምላካችን ግን የኀጥኡን ሰው ሞቱንና ጥፋቱን
አይሻም፤ መመለሱን እንጂ። “በውኑ ኃጢአተኛ ይሞት ዘንድ እፈቅዳለሁን? ይላል ጌታ
እግዚአብሔር፤ ከመንገድ ሊመልስና በሕይወት ይኖር ዘንድ አደለምን?” እንዲል፡፡ (ሕዝ ፲፰፥
፳፫፡፡)

ከላይ የጠቀስነውን ምሳሌያዊ ትምህርት ያስተማረው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ


ነው። በዋናነት የጠፋውን በግ አዳምን የፈለገውና ባገኘውም ጊዜ ደስ ብሎት በትከሻው
የተሸከመው እሱ ክርስቶስ ነው። ምሳሌዎቹም ይህን የምሥጢረ ሥጋዌ ታሪክ አጉልተው
የሚናገሩ ናቸው:: በተጨማሪም ምሳሌዎቹ በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ከሀገር ወጥተውም ሆነ
በሀገር ቤት /በቤት /ውስጥ/፣ በቤተሰብ ቁጥጥር ሥር ሆነውም ይሁን ከቤት ወጥተው
/ከቤተሰብም ተለይተው/ በኃጢአት የጠፉትንና የሚጠፉትን ሁሉ ይናገሯቸዋል፡፡ እነዚህ የጠፉ
አካላት ራሳቸውን ፈልገው እንዲያገኙና በሕይወት እንዲኖሩ ይጋብዟቸዋል።

ሌሎች ስለጠፉት የሚገዳቸው ክርስቲያኖች ሁሉና የሚመለከታቸው አካላትም የጠፉ


ወገኖቻቸውን ፈልገው እንዲያገኟቸውና ሐሴት እንዲያደርጉ ይጎተጉቷቸዋል:: በሰውም ሆነ
በእግዚአብሔር ዘንድ የጠፉበት ምክንያት፣ የጠፉበት ቦታ፣ የጠፉበት ሁኔታና የጠፉበት ጊዜ
ሚዛን የሚደፋ ጉዳይ አይደለም። ሚዛን የሚደፋውና በሁሉም ዘንድ በእጅጉ የሚፈለገው
የጠፋው ነገር ፍለጋ፣ መገኘትና ወደ ቀደመ መኖሪያና ቦታው መመለሱ ነው። በግልጽ አነጋገር
ለክርስቲያኖችና ለቤተ ክርስቲያን መሠረታዊው ጉዳይ ኀጥአን በንስሐ የመመለሳቸው ነገር
ነው።

8.4 የምሥጢረ ጥምቀት አፈጻጸም

እንግዲህ ንስሐ ገብተን፣ የኃጢአትን ስርየት አግኝተን፣ ከሰውና ከእግዚአብሔር ጋር ታርቀን


በጽድቅ ጎዳና ለመራመድና በደህንነት ጸጋ ለመኖር እንድንችል ቢያንስ ሦስት ነገሮችን መፈጸም
አለብን። የመጀመሪያው የንስሐ ሃዘን ማለትም እውነተኛና ልባዊ ጸጸት በቅድሚያ እንዲኖረን
ያስፈልጋል። ሁለተኛው ኑዛዜ ሲሆን ሦስተኛው ደግሞ ስለኃጢአታችን የሚሰጠንን የንስሐ
ቅጣት የሚያመለክት የቀኖናን ሥርዓት መፈጸምና እንደዚሁም በካህኑ በኩል የምናገኘው
የፍትሐት ጸጋ ነው።

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 151
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

8.4.1 የንስሐ ሃዘን /ጸጸት/

ንስሐ የሚገባ ሰው በመጀመሪያ ኃጢአቱን እያስታወሰ ሰውና ፈጣሪውን መበደሉን እያሰበ


የሚያደርገው ሃዘን ወደ ንስሐ የሚወስድ እውነተኛ ሃዘን ስለሆነ ሃዘኑን እግዚአብሔር
ይቆጥርለታል። «የሚያዝኑ ብፁዓን ናቸው፣ መጽናናትን ያገኛሉና» /ማቴ. ፭፥፬/ የተባለው
የራሳቸውንና የሌላውን ኃጢአት እያሰቡ የሚያዝኑትን ተነሳሒያን ያመለክታል። ንስሐ ማለት
ጸጸትን የሚያመለክት ቢሆንም ቁጭትና ቅንዓት የሞላበት የዓለማዊ ጸጸት ሳይሆን እውነተኛው
ሃዘንና መመለስ መሆኑን በቅድሚያ መገንዘብ ይኖርብናል።

ስለእውነተኛው ሃዘን ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እንደሚከተለው ያስተምረናል። «አሁን


ስለንስሐ ስላዘናችሁ ደስ ብሎኛል እንጂ ስላዘናችሁ አይደለም፤ በምንም ከእኛ የተነሳ እንዳትጎዱ
እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ አዝናችኋልና። እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የሆነ ሃዘን ጸጸት
የሌለበትን፣ ወደ መዳንን የሚያደርሰውን ንስሐ ያደርጋልና፤ የዓለም ሃዘን ግን ሞትን
ያመጣል።» /፪ኛ ቆሮ. ፯፥፱-፲/። እንግዲህ እውነተኛውን ሃዘን ከእንባ ጋር አድርጎ በንጹህ
ልቦናና ጸሎት ለእግዚአብሔር በማቅረብ ተነሳሒው እንደገና ላለመበደል መወሰን ይኖርበታል።
ውሳኔውንም ለመፈጸም የሚያስችለውን የመንፈስ ቅዱስን ረድኤት በማግኘት ሁልጊዜ ተግቶ
መጸለይ አለበት፡፡

8.4.2 ኑዛዜ

ከዚህ ቀጥሎ ተነሳሒው ኃጢአቱን ሥልጣነ ክህነት ላለው ካህን ይናዘዛል። ኑዛዜ ማድረግ
በቅዱሳት መጻሕፍት የታዘዘ ነው። «ከነዚህ ነገሮች በአንዲቱ በደለኛ ቢሆን፥ የሠራውን ኃጢአት
ይናዘዛል። ስለሠራው ኃጢአት ለእግዚአብሔር የበደልን መስዋዕት ያመጣል፤ … ካህኑ
ስለኃጢአቱ ያስተሰርይለታል። … እርሱም ይቅር ይባላል።» /ዘሌ. ፭፥፭-፮፣፲/። ከዚህ ጥቅስ
የኃጢአትን ስርየት ለማግኘት ለካህን መናዘዝ እንደሚገባ እንማራለን። ስለዚህ ኃጢአታችንን
ለአናዛዡ ካህን ከበደሉ ዓይነትና ሁኔታ ጋር ማስረዳት ይገባናል። ስንናዘዝም ከእንባና ከጸጸት
ጋር ሆነን ከካህኑ ጋር አብሮ እግዚአብሔር እንደሚሰማን አምነን በእውነት መናገር
ያስፈልገናል።

በሽታውን የሰወረ መድኃኒት አያገኝም ተብሏልና ለነፍስ ቁስል ሐኪም ለሆነው ለካህኑ
ኃጢአታችንን ከሰወርን ለነፍስ የሚሆነውን ፈውስ ለማግኘት አንችልም።«ኃጢአቱን የሚሰውር

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 152
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

አይለማም፤ የሚናዘዝባትና የሚተዋት ግን ምሕረትን ያገኛል።» /ምሳ. ፳፰፥፲፫/ ተብሎ


ተጽፏልና ስለዚህ እርስ በርሳችን በቂም በቀል ሳንያያዝ የበደልነውን እየካስን፣ የበደለንን ይቅር
እያልን ብንናዘዝና የሰማዩን አባታችን በጸሎት ብንጠይቀው ምሕረትና ፈውስን ይሰጠናል። ነገር
ግን እኛ ማንንም አልበደልንም ኃጢአትም የለብንም ብንል እግዚአብሔርን ሐሰተኛ ማድረጋችን
ስለሆነ እንጠንቀቅ። ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ እንዳለው «ኃጢአት የለብንም ብንል ራሳችንን
እናስታለን፣ እውነትም በኛ ውስጥ የለም። በኃጢአታችን ብንናዘዝ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን
ከዓመፃም ሁሉ ሊያነጻን የታመነና ጻድቅ ነው። ኃጢአትን አላደረግንም ብንል ሐሰተኛ
እናደርገዋለን ቃሉም በኛ ውስጥ የለም።» /፩ኛ ዮሐ. ፩፥፰-፲/።

8.4.3 ፍትሐትና ቀኖና

እንግዲህ ተነሳሒው በእውነት ኃጢአቱን አውቆ ለካህኑና በስውር ለሚያየውና ለሚሰማው


ለእግዚአብሔር ከተናዘዘ በኋላ ከካህኑ ሁለት ነገሮችን ይቀበላል። እነሱም ፍትሐትና ቀኖና
ናቸው። ፍትሐት ማለት ከኃጢአት እስራት የሚፈታበት ነው። ቀኖና ማለት ለኃጢአቱ ምክርና
ተግሳጽ የሚያገኝበትን፣ በንስሐ ቅጣት የሚቀበልበትን፣ ካሳ መቀጫ የሚከፍልበትን ሁኔታ
የሚያመለክት ነው። ፍትሐት የሚሰጠው ካህኑ የንስሐውን ጸሎት ሥነ ሥርዓት ከፈጸመ በኋላ
«እግዚአብሔር ይፍታህ» ሲል ተናዛዡ ወይም ተነሳሒው ከኃጢአቱ እስራት ይፈታል።
ከእግዚአብሔርም ይቅርታን ያገኛል። ንስሐ የገባው ሰው ከኃጢአቱ ተፈትቶ ከእግዚአብሔር
ጋር መታረቁ ታላቅ ጸጋ ነው። እንግዲህ ፍትሐት የተቀበለ ተነሳሒ ሁሉ ኃጢአቱ የተሰረየለት
ስለሆነ ከዘላለም የሞት ቅጣት ነፃ ይሆናል።

ምንም እንኳን ተነሳሒው ከዘላለም የሞት ቅጣት ቢድንም ዓይነቱና መጠኑ የተለያየ ጊዜያዊ
ቅጣት መቀበል ይገባዋል። ይህም የንስሐ ቀኖና ይባላል። ጊዜያዊ ቅጣት ወይም ቀኖና
ያስፈለገበት ምክንያት ኃጢአትን መሥራት ምን ያህል አደገኛ እንደሆነ ለተነሳሒው ለማሳሰብና
ዳግመኛ እንዳይበድል ለማስጠንቀቅ እንዲሁም ደግሞ ሥጋን በመገሰጽ ለነፍሱ የጽድቅንና
የደህንነትን ጎዳና ለማስተማር ነው። ምንጊዜም ፍቅሩና ምሕረቱ ከኛ ጋር ቢሆንም
እግዚአብሔር በአባትነቱ ላጠፋነው ጥፋት በጊዜያዊ ቅጣት ይቀጣናል። መልካም አባት ልጁን
እንደሚገስጽና እንደሚቀጣ ዓይነት ይቀጣናል። /ዕብ. ፲፪፥፭-፲፩/። እንግዲህ ያልተገራ ልቦና ካለን
ለእግዚአብሔር በማስገዛት የኃጢአታችንንም ቅጣት በደስታ በመቀበል የበለጠ ጸጋና ረድኤትን
እናገኛለን። «በዚያን ጊዜ ያልተገረዘው ልባቸው ቢዋረድ፣ የኃጢአታቸውንም ቅጣት ቢቀበሉ እኔ

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 153
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ለያዕቆብ የማልኩትን ቃልኪዳኔን አስባለሁ … ምድሪቱንም አስባለሁ።» ተብሎ ተጽፏልና /ዘሌ.


፳፮፥፵፩-፵፪/።

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም በዝሙት የተከሰሰውን የቆሮንቶሱን ሰው በሥጋው እንዲቀጠፍ


ፈርዶበታል። «እንደዚህ በሠራው ላይ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አሁን
ፈርጄበታለሁ … መንፈሱ በጌታ በኢየሱስ ቀን ትድን ዘንድ እንደዚህ ያለው ሰው ለሥጋው
ጥፋት ለሰይጣን እንዲሰጥ ፍርዴ ነው።» /፩ኛ ቆሮ. ፭፥፩-፭/። ይኸው ሐዋርያ ለሁለተኛ ጊዜ
በጻፈው መልእክቱ ከላይ የተጠቀሰው የቆሮንቶስ ሰው ቅጣቱ የሚበቃው ስለሆነ ማኅበረ
ክርስቲያኑ ይቅርታ እንዲያደርጉለት ጠይቋል። «እንደዚህ ላለ ሰው ይህ ከናንተ የምትበዙት
የቀጣችሁት ቅጣት ይበቃዋልና እንደዚህ ያለው ከልክ በሚበዛ ሃዘን እንዳይዋጥ ይልቅ
ተመልሳችሁ ይቅር ማለትና ማጽናናት ይገባችኋል። ስለዚህ ፍቅርን እንድታጸኑ
እለምናችኋለሁ፤ ስለዚህ ደግሞ ጽፌ ነበርና» /፪ኛ ቆሮ. ፪፥፮-፲፩/። እንግዲህ የሐዋርያውን
ምክር ሰምተን ዛሬ የምንገኘው ክርስቲያኖችን በበደላችን ምክንያት ካህኑ የሚሰጠንን ምክርና
ተግሳጽ አዳምጠን የንስሐውንም ቅጣት ማለትም ቀኖናውን ተቀብለን በደስታ ብንፈጽመው
መንፈሳዊ ደህንነታችን ይጠበቃል። መንፈሳዊ ግዴታችንንም እንወጣለን።

በቤተ ክርስቲያናችን ቀኖና የሚሰጠው እንደ ተነሳሒው የኃጢአት ዓይነትና ሁኔታ ታይቶ
ነው። ካህኑ የተነሳሒውን የኑሮ ሁኔታና ያጋጠመውን ፈተና በማስመልከት ምክርና ትምህርት
ይሰጠዋል። እንደመልካም የነፍስ ሐኪምም እንደበሽታው ሁኔታ ካህኑ አስፈላጊውን የነፍስ
መድኃኒት ይሰጠዋል። የቀኖና አሰጣጥ መንገዱና ዓይነቱ ብዙ ነው። ለአንዳንዱ ተነሳሒ የቃል
ምክርና ተግሳጽ ብቻ የሚበቃው አለ። ለሌላው ጾም ብቻ ወይም ከስግደት ጋር ቀኖና
ይሰጠዋል። ልዩ የንስሐ ጸሎት፣ ምጽዋት፣ ለተበደለው ወገን ካሳ መክፈል፣ ለችግረኞች
አገልግሎት መስጠት አስፈላጊም ከሆነ ለተወሰነ ጊዜ ከቁርባን መለየት ወይም ልዩ ልዩ
አስቸጋሪ ነገሮችን መፈጸም ወይም ለቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊና ማኅበራዊ ኑሮ የሚጠቅሙ
የጉልበትም ሆነ የአዕምሮ ሥራ መሥራትና የመሳሰሉት ሁሉ ከቀኖና ቤተ ክርስቲያን
ይቆጠራሉ።

8.5 የሚያስገኘው ጸጋ

በንስሐ ሕይወት መመላለስ በተነሳሕያን ሕይወት የሚታዩ ጉልህ ፍሬዎች አሉት:: የአፈጻጸም
ሥርዓቱን ጠብቆ በተገለጸው መሠረት የተገበረ ሰው ከምንም በላይ ታስሮበት ከነበረው ኃጢአት

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 154
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

የተፈታ ይሆናል፡፡ ይህ ነጻነት በምሥጢረ ንስሐ የሚገኝ ፍሬ (ጸጋ) ነው። ተነሳሒው በኑሮው
ሁሉ ትሑት እንዲሆንም ይረዳዋል። በዚህም ከትዕቢት ተላቆ ራሱን በማዋረድ ክርስቶስን
ወደሚመስልበት ሕይወት ለማደግ ይችላል:: ሌላው ተነሳሒው የሚያገኘው ጥቅም ኀጢአትን
የሚጸየፍበትና የሚጠላበትን ኃይል መጎናጸፍ ነው፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ ኃጢአተኞችን ግን
የሚወድበት ስለ እነርሱም የሚያለቅስበት ጸጋ ያገኛል:: ይህም በሌሎች ኀጢአት (ላይ)
በመፍረድ ከሚመጣ አምላካዊ ፍርድ ለመዳን ያስችለዋል። በራሱ ኀጢአት ከልቡ ያዘነና
የተጸጸተ ሰው ለኀጢአተኞች ከማዘን ውጪ በእነርሱ ላይ የማይጠቅሙ (የፍርድ) ቃላትን
ሊያስብና ሊናገር አይችልምና።

ንስሐ የገባ ሰው ስለኃጢአቱ የሚያዝነው ሐዘን ከላይ እንደገለጽነው እንደ ቤተ ፈት “በዚህ ጊዜ


ተሾሜ ይህን እበላ፤ ይህንንም እጠጣ ነበር፤ ወይኔ ዛሬ ግን ይኼ ሁሉ ቀረብኝ፤” እንደሚለው
ያለ አይደለም። እንደ አባታችን አዳም “የእግዚአብሔር ሕጉን አፍርሼ ፈጣሪዬን አሳዘንኩት።”
እያለ ነው የሚያዝነው። እንዲህ ያለው ሰው ከንስሐ በኋላ ዘወትር ጭምትና ሰላማዊ፣
የማይከራከርና ዝምተኛ በመሆን ሕገ እግዚአብሔርን እያሰላሰለ የሚኖርበትን ጸጋ ያገኛል
ሕይወቱንም ወደ ተሻለ መንፈሳዊ ደረጃ ከፍ ማድረግ በሚያስችል ፍቅረ እግዚአብሔር እርከን
ላይ ያወጣል፡፡ በፍቅረ እግዚአብሔር የተቃኘ ሰው ደግሞ በንስሐ መመላለስን ስለማይሰለችና
ስለማይዘናጋ የበዛ ኃጢአቱ ይሰረይለታል፡፡ (ሉቃ ፯፥፵፯)

የበዛ ኃጢአቱ የተሰረየለት ምእመንም ሳይገባው የተደረገለትን ይቅርታ ዘወትር ስለሚያስብ ልቡ


በፍቅረ እግዚአብሔር እሳት እየጋመ መሔዱ አይቀሬ ነው። ንስሐ የገባ ሰው ዓይኖቹ
አጥርተው ስለሚያዩ ቀድሞ በኃጢአቱ ምክንያት ማየት ያልቻለውን የተከፈተ የገነት ደጅ
ይመለከታል፡፡ ይህ በራሱ በንስሐ አማካኝነት የተገኘ ጸጋ ነው፡፡ በተጠረገለት የንስሐ ጎዳና
ስለሚጓዝም አዲስ የመንፈሳዊ ሕይወት ምዕራፍ ይጀምራል። በዚህም ለራሱም ጭምር ሊረዳው
ወደማይችል ጥልቅ ተመስጦ የሚያስገባ አዲስ መንፈሳዊ ዓለምን ማጣጣም ይከፈታል።
በዚህም ምክንያት የመንፈሳዊ ጽናቱ /ጥንካሬው/ ምንጭ በንስሐ ሕይወት መመላለሱ እንደሆነ
ማስተዋል ይጀምራል፡፡ ከዚያም ንጽሕናን ገንዘብ ለማድረግ እየታገለ በተቀደሰ ሕይወት
ለመኖርና ከንስሐ ሕይወት ሰገነት ላለመውረድ እየታገለ ይጓዛል።

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 155
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

9. ምሥጢረ ክህነት
9.1 የምሥጢረ ክህነት የቃሉ ትርጉም
ይህ ቋንቋ የግዕዝ ቋንቋ ነው፡፡ ተክህነ አገልገለ ከሚለው ግስ የወጣ ነው፡፡ 18 1ቆሮ 4፡1 ማር
28፡20 ክህነት ለእግዚአብሔር የሚቀርብ የተቀደሰ አገልግሎት ማለት ነው፡፡ የክህነት
አገልግሎት የተጀመረው በላይ በሰማይ ነው ፡፡ ክህነት የአገልግሎት ስም ሆኖ የቤተክርስቲያን
ከፍተኛ መንፈሳዊ ማዕረግ ነው፡፡ ሃያ አራቱ መላእክት (ካህናተ ሰማይ) የእግዚአብሔር
አገልጋዮች ይባላሉ፡፡ ያለ እረፍት ‹ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ የነበረና ያለ የሚመጣው ሁሉንም
የሚገዛ› እያሉ ሲያመሰግኑ ይኖራሉ፡፡ አንድም ክህነት መንፈሳዊ አገልግሎት ነው፡፡
አገልግሎቱም በሰውና በእግዚአብሔር መካከል የሚፈጸም ነው። የክህነት ሥልጣን ምድራውያን
መሪዎችና ዳኞች የማይሾሙትና የማይሽሩት ሰማያዊ ሹመት ነው። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
ለደቀ መዛሙርቱ የማሰርና የመፍታት ሥልጣን በመስጠት ነው ምሥጢረ ክህነትን ያጸናው።
ቤተክርስቲያን የምሥራቹን ቃል ለዓለም በማዳረስ ምእመናንን የምትጠራቸው በካህናት
አማካኝነት ነው። ምሥጢራቷን የምታከናውነውና የእግዚአብሔር ጸጋ ለሚገባቸው ሰዎች
የምታድለው በሐዲስ ኪዳን ካህናት በኩል ነው፡፡ የካህናት አገልግሎት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
በመሠረተው (በሠራው) ሥርዓት መሠረት የሚጓዝ ነው።

እግዚአብሔር አዳምንም ፈጥሮ በልጅነት አክብሮ ነብይና ካህን አድርጎ ሾሞ በኦሪት በወንጌል
ሥርዓት እስኪወሰን ድረስ ከአዳም ጀምሮ እስከ ሙሴ የነበሩ አበው በበረከት አበው
ከእግዚአብሔር እየተሾሙ ትንቢትን ክህነት ከቅዱሱ መንፈስ እየተቀበሉ (እየተሾሙ)
በነብይነታቸው ያለውን የሚመጣውን ሲገልጽ ሲያስተምሩ በሀብተ ክህነታቸው መስዋዕት
ሲቀርቡ ነበር፡፡ ክህነት በዘመነ ኦሪት ለሌዊ ነገድ ከተሰጠ በኋላ ሲወርድ ሲወራረድ እስከ
ክርስቶስ ደርሷል፡፡ ታላቁ ሊቀ ካህናት እየሱስ ክርስቶስ እንደ ብሉይ ኪዳን መስዋዕት እንሰሳ
ሳሆን እራሱን መስዋዕት፣ እርሱ ሰዋዒ ሆኖ ወደ መቅደስ ገብቷል፡፡ ዮሐ 20፡22 ማሬ 18፡
ኦሪት ከተሰጠች በኋላ የመጀመሪያው ካህን ሆኖ የተሾመው አሮን ይባላል፡፡
እውነተኛውን( አማናዊውን) ክህነት የመሰረተው ጌታችንና መድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ነው፡
፡ ዕብ 6፣26-28 ‹‹ካህኑ የሰራዊት ጌታ የእግዚአብሔር መልክተኛ ነውና ከከንፈሮቹ (ከአንደበቱ)
ዕውቀትን ይጠብቁ ዘንድ ይገባቸዋል ፤ ሰዎችን ሕግን ከአፉ ይፈልጉ ዘንድ ይገባቸዋል፡፡››

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 156
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

9.2 የምሥጢረ ክህነት አመሠራረት


አማናዊው የሐዲስ ኪዳን ክህነት ከመጀመሩ በፊት በብሉይ ኪዳንም ክህነትና አገልግሎቱ
በስፋት ይታይ ነበር። በሕገ ልቡና ዘመን ከአዳም ጀምሮ እስከ ሙሴ ድረስ የተመረጡ አበው
ለቤተሰቦቻቸው የክህነትን ተግባር ይፈጽሙ ነበር። ክህነት እግዚአብሔር የሚገለገልበት ልዩ
ጥሪና ስጦታ እንደመሆኑ መጠን እነዚህ አባቶች ራሳቸውንና ቤተሰቦቻቸውን ከእግዚአብሔር
ጋር በማገናኘት ይህን አገልግሎት ይፈጽሙ ነበር። ለማስረጃ ያህልም የሚከተሉትን መመልከት
ይቻላል።

“በዚያችም ቀን አዳም ከኤዶም ገነት ሲወጣ ለበጎ መዓዛ ነጭ ዕጣን፣ ቀንዓትና ልባንጃ
ስንቡልም ኀፍረቱን በሸፈነበት ቀን በጥዋት ፀሐይ ሲወጣ ዐጠነ።” ኩፋ. ፭፥፩ ይህም
አባታችን አዳም በተፈጠረበት ወቅት እግዚአብሔር ካሳደረበት ፯ት ሀብታት አንዱ ሀብተ
ክህነት መሆኑን የምንረዳበት አንዱ ማስረጃ ነው፡፡”

“አቤልም ደግሞ ከበጎቹ መጀመሪያ የተወለደውንና ከሰቡት አቀረበ፤ እግዚአብሔርም ወደ


አቤልና ወደ መሥዋዕቱ ተመለከተ፤” (ዘፍ፬፥፬፡፡)

“ኖኅም ለእግዚአብሔር መሠዊያውን ሠራ፤ከንጹሕም እንሰሳ ሁሉ፣ ከንጹሕም ወፎች


ወሰደ፤ በመሠዊያውም ላይ መሥዋዕትን አቀረበ፤ እግዚአብሔርም አምላክም መልካሙን
መዓዛ አሸተተ፡፡” (ዘፍ፰፥፳‐፳፩፡፡)

“እግዚአብሔርም ለአብራም ተገለጠለትና “ይህችን ምድር ለዘርህ እሰጣለሁ።” አለው።


አብራምም ለእርሱ ለተገለጠለት ለእግዚአብሔር በዚያ መሠዊያውን ሠራ፡፡… በዚያም
ለእግዚአብሔር መሠዊያን ሠራ የእግዚአብሔርንም ስም ጠራ፡፡” (ዘፍ፲፪፥፯)

ስለ ይስሐቅም “በዚያም ለአምላኩ ለእግዚአብሔር መሠዊያን ሠራ፤ የእግዚአብሔርንም ስም


ጠራ፡፡” ተብሏል። (ዘፍ ፳፮፥፳፭፡፡)

ስለ ያዕቆብ ደግሞ እንዲህ የሚል ጽሑፍ አለ፤ “በዚያም መሠዊያውን ሠራ፤ የዚያንም ቦታ
ስም ቤቴል ብሎ ጠራው፡፡’’ (፴፭፥፯፡፡)

በዘመነ አበው ከነበሩት የክህነት አገልግሎቶች ላቅ ያለ ስፍራ የሚሰጠው የመልከጼዴቅ


ክህነትና አገልግሎት ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ስለ እርሱ የተጻፉት ኃይለ ቃላት እንዲህ ነው
የሚሉት፡፡ “የሳሌም ንጉሥ መልከጼዴቅም እንጀራንና የወይን ጠጅን አወጣ፤ እርሱም የልዑል

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 157
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

እግዚአብሔር ካህን ነበረ፡፡” (ዘፍ፲፬፥፲፱) ፣ “እንደ መልከ ጼዴቅ ሹመት፥ አንተ ለዘለዓለም ካህን
ነህ ብሎ እግዚአብሔር ማለ አይጸጸትም፡፡” (መዝ ፻፱፥፬፡፡) ይህም ኀይለ ቃል መልከጼዴቅ
የልዑል እግዚአብሔር ካህን ብቻ ሳይሆን የወልደ እግዚአብሔርም ምሳሌ መሆኑን
ያመለክታል። ቅዱስ ጳውሎስ ይህንን ኀይለ ቃል ሲያብራራ እንዲህ ነበር ያለው፤ “የሳሌም
ንጉሥ፣ የልዑል እግዚአብሔርም ካህን የሆነ ይህ መልከ ጼዴቅ፥ አብርሃም ነገሥታትን ድል
ነስቶ በተመለሰ ጊዜ ከእርሱ ጋር ተገናኝቶ ባረከው፤ አብርሃምም ከገንዘቡ ሁሉ ከዐሥር አንድ
ሰጠው፤… ክህነቱ የወልደ እግዚአብሔር ምሳሌ ሆኖ ለዘለዓለም ይኖራል።” (ዕብ፯፥፩‐፬፡፡)
ለጊዜው ይህን ያህል ጠቀስን እንጂ ሙሉው ምዕራፍ የመልከ ጼዴቅን ክህነትና ክብር
ከክርስቶስ ጋር እያነጻጸረ ያቀረበበት ክፍል ነው።

ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስም በቅዳሴው ምዕራፍ ፫ ላይ በሰፊው ያቀረበውን ምስክርነት


መመልከት ይቻላል። የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ የሆነ መልከጼዴቅ አበ ብዙኃን ከተባለ
ከአብርሃም ዐሥራት መቀበሉ፤ አብርሃምም ዐሥራት መስጠቱ ታላቅነቱንና ክብሩን ያሳያል
ይህም ምሳሌነት ወልደ እግዚአብሔር ክህነት በመልከጼዴቅ ክህነት ዘምሳል ጸንቶ መኖሩን
ያሳያል፡፡ መልከጼዴቅ በስንዴና በወይን ቁርባን ማመስገኑ (ማስታኮቱ)፣ ሹመቱን ከእገሌ
ተሾመው መባል አለመቻሉና ሹመቱ ለእገሌ አለፈ አለመባሉ የትውልድ ቁጥር ካለመኖሩ ጋር
ተደምሮ ክርስቶስን አስመስሎታል፡፡ ርእሰ አበው የተባለ አብርሃምም ለሱ አሥራት አውጣጥቶ
ማቅረቡ የምእመናን ምሳሌ ያደርገዋል፡፡ ይህ ታሪክ ደገኛ ምሳሌ ሆኖ አማናዊቱን የአዲስ ኪዳን
ክህነት ክብር ከማሳየቱም በላይ ምእመናን ለካህናት አባቶች መታዘዝ እንደሚገባቸው
ያስተምራል፡፡ (ትርጓሜ ዕብራውያን ምዕራፍ ፯)

ከሙሴ ጀምሮ ባለው ዘመነ ኦሪትም እግዚአብሔር ከአሥራ ሁለቱ ነገዶች መካከል አንዱ
በክህነት እንዲያገለግለው መምረጡን እንረዳለን። (ዘጸ ፳፱፥፩‐፲ ዘሌ፰፥፲፪፤ ፳፩፥፩‐ፍጻሜ፡፡ ዘኁ፩፥
፶‐፶፪፤ ዘኁ፩፥፶‐፶፪፤ ዘኁ፫፥፩‐፲፬፡፡) ከተመረጠው የሌዊ ነገድ መካከልም አሮንና ልጆቹን የበለጠ
አክብሮና አቅርቦ በክህነት እንዲያገለግሉት መፍቀዱን ከላይ የጠቀስናቸው ማስረጃዎች
ይነግሩናል። አሿሿማቸውን፣ ዝርዝር አገልግሎታቸውንና መሥዋዕታቸውን በተመለከተም
በኦሪት ዘጸአት ፳፰፡፳፱፣ ዘሌዋዉያን ፰፡፲ እና ዘኁልቁ ምዕራፍ ፫‐፬ ተጽፎ እናገኛለን፡፡

እንደሚታወቀው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጊዜያዊውን የብሉይ ኪዳን


አገልግሎት (ክህነት) እና መሥዋዕት አሳለፈው። እርሱ ራሱ መሥዋዕት፣ መሥዋዕት አቅራቢ

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 158
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ሊቀ ካህንና መሥዋዕት ተቀባይ አምላክ ሆኖ የሐዲስ ኪዳኑን አማናዊ ክህነት መሠረተልን።


በአዲስ ሥርዓት፣ መሥዋዕትና ኪዳን የመሠረተው ይህ ምሥጢረ ክህነት ምእመናንን ወደ
እግዚአብሔር መንግሥት የሚያቀርብ (የሚያስገባ) ሆነ፡፡ ለደቀ መዛሙርቱ የሰጣቸው
የማስተማር፣ የማጥመቅ፣ የማቁረብ ኃጢአትን የማስተስተሥርይ፣ ሥልጣን በደሙ
የመሠረታትን ቤተክርስቲያን ማለትም ምእመናንን እንዲጠብቁለትና እንዲመሩለት ነው፡፡ (ሐዋ.
፳፥፲፯-፳፰ ዮሐ፳፩፥፲፭‐፳፡፡)

9.3 የካህናት ዐበይት ተግባራት


፩/ ለጸሎት መትጋትና ትምህርተ ወንጌልን ለመላው ዓለም ማዳረስ፤ (ማቴ፳፰፥፲፱‐፳፡፡ ማር፲፮፥
፲፭፡፡ ሐዋ፩፥፰፤ ፮፥፩‐፬፡፡)

፪ኛ/ የሕዝቡን ኃጢአት ማስተሥረይና ወደ ቅድስና ጎዳና መምራትና፤ /ዮሐ፳፥፳፫፡፡/

፫ኛ/ መንጋውን /ምእመናነ ክርስቶስን/ የመጠበቅና የማስተዳደር ሥራ ነው። (ዮሐ፳፩፥፲፭‐፲፰፡፡


፩ኛጴጥ ፭፥፩‐፭፡፡)

ምንም እንኳን ለሐዲስ ኪዳን ክህነት እንደ ብሉይ ኪዳን ለክህነት አገልግሎት የተለየ ዘርና
ነገድ ባያስፈልገውም ሁሉም የሰው ዘር ካህን ሊሆን እንደማይችል ግልጽ ነው፡፡ ጌታችን
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይከተሉት ከነበሩት ፭ ገበያ ሕዝብ መካከል ለክህነት
አገልግሎት መጀመሪያ የመረጣቸው ዐሥራ ሁለቱን ሐዋርያት እንጂ ሁሉንም ተከታዮች
አልነበረም። (ማቴ ፲፥፩‐፭፡፡ ማር፫፥፲፫‐፲፱፡፡ሉቃ፮፥፲፪‐፲፮፡፡) እዚህ ላይ ልንመለከተው የሚገባን
በብሉይ ኪዳን ለቤተ እስራኤልና በሐዲስ ኪዳን ለክርስቲያኖች የተሰጠ ተመሳሳይ ይዘት ያለው
ቃልኪዳን አለ፡፡ ይህንንም በንጽጽር እንደሚከተለው እናየዋለን ።

 “ለያዕቆብ ቤት እንዲህ በል፤ ለእስራኤል ልጆች እንዲህ ንገር፤… አሁንም ቃሌን


በእውነት ብትሰሙ፥ ኪዳኔንም ብትጠብቁ፥ ምድር ሁሉ የእኔ ናትና ከአሕዛብ ሁሉ
የተመረጠ ርስት ትሆኑልኛላችሁ፤ እናንተም የክህነት መንግሥት፤ የተቀደሰም ሕዝብ
ትሆናላችሁ፡፡” (ዘፀ፲፱፥፫‐፯፡፡)

 “እናንተ ግን ከጨለማ ወደሚደነቅ ብርሃን የጠራችሁን የእርሱን በጎነት እንድትነግሩ


የተመረጠ ትውልድ የመንግሥትና የክህነት ወገን፥ ቅዱስ ሕዝብ፥ ለርስቱም የተለየ ወገን
ናችሁ፤ እናንተ ቀድሞ ወገኖች አልነበራችሁም፤ አሁን ግን የእግዚአብሔር ወገኖች

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 159
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ናችሁ፤ እናንተ ምሕረት ያገኛችሁ አልነበራችሁም፤ አሁን ግን ምሕረትን


አግኝታችኋል።” (፩ኛ ጴጥ፪፥፱‐፲፩) ቀደም ሲልም “በሰው ወደ ተናቀ በእግዚአብሔር
ዘንድ ግን ወደ ተመረጠውና ክቡር ወደ ሆነው ወደ ሕያው ድንጋይ ወደ እርሱ ቅረቡ።
ደግሞ እንደ ሕያዋን ድንጋዮች ሆናችሁ በኢየሱስ ክርስቶስ ለእግዚአብሔር ደስ
የሚያሰኝ መንፈሳዊ መሥዋዕትን ታቀርቡ ዘንድ ቅዱሳን ካህናት እንድትሆኑ መንፈሳዊ
ቤት ለመሆን ተሠሩ፡፡ (፩ጴጥ፪፥፬‐፮) እነዚህ ከላይ እንደገለጥነው ተመሳሳይ ምሥጢር
የያዙ ኃይለ ቃላት ሆነው እናገኛቸዋለን ።

 “ለወደደን ከኃጢአታችንም በደሙ ላጠበን ለአባቱም ለእግዚአብሔር ነገሥታትና ካህናት


ላደረገን ለእርሱ ከዘለዓለም እስከ ዘለዓለም ድረስ ክብርና ኀይል ይሁን፤ አሜን፡፡ (ራእ፩፥
፭‐፯፡፡)

 “ከእነርሱም ለአምላካችን ነገሥታትና ካህናትን ሾምህ፤ በምድርም ሁሉ ይነግሣሉ፡፡”


(ራእ፭፥፲፡፡) የሚሉትም ከላይኞቹ ኃይለ ቃላት ጋር የተዛመዱ ናቸው፡፡

በኦሪቱ እንደተጻፈ መልእክቱ ለቤተ እስራኤል ሁሉ ነው፡፡ በካህናት አገልግሎት ለምትወደስ፣


ለምትመሰገን የእግዚአብሔር መንግሥት መመረጣቸውን፤ ካህናት ከእነሱ ማኅፀንና አብራክ
እንደሚወለዱና ከሌላው የዓለም ሕዝብ ሁሉ ተለይተው የእግዚአብሔር ማደሪያዎች
እንደሚሆኑ የሚገልጽ ነው፡፡ ከዚህ ውጪ ሁሉንም እስራኤላዉያን ካህናት ናቸው ማለቱ
አልነበረም፡፡ ይህማ እንዳይሆን ከመካከላቸው የሌዊን ነገድ በተለይም ደግሞ አሮንንና ልጆቹን
በክህነት እንዲያገለግሉት እግዚአብሔር መምረጡን ባልነገረንም ነበር።

በሐዲስ ኪዳንም ያሉት ከላይ የጠቀስናቸው ማስረጃዎች በተመሳሳይ ሁኔታ ሁሉም


ክርስቲያኖች ካህናት ናቸውና ካህናት አያስፈልጉም ለማለት የተጻፉና የተነገሩ አይደሉም።
የእግዚአብሔርን አምላክነትና ቸርነት ለሚያምኑ ሁሉ ለመንገር፣ በሕይወትም ለመመስከር
የተጠሩ አገልጋዮች መሆናቸውን ነው የሚናገሩት። ክርስቲያኖች የተመረጡ የመንግሥተ
እግዚአብሔር ዜጎችና በካህናት ጥበቃ (እረኝነት) ሥር ያሉ መንጎች /ወገኖች/ መሆናቸውን ነው
የሚናገሩት። የክርስቲያኖች አገልግሎትም የተቀደሰ እና በእግዚአብሔር ዘንድ የተወደደ
መሆኑን እንጂ ሁሉም ምሥጢራተ ቤተክርስቲያንን የሚፈጽሙ የቤተ ክርስቲያን የውስጥ
አገልጋዮች ናቸው ማለት አይደለም፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 160
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

በብሉይ ኪዳን ዘመን በሙሴ ምስፍናና በአሮን ክህነት ላይ የሚያጉረመርሙ፤ “ሁሉም ቅዱሳን
ናቸውና እናንተ አበዛችሁት” የሚሉ ተቃዋሚዎች ተነሥተው ነበር። (ዘኁ ፲፮፥፩‐ፍጻሜ፡፡)
በምዕራፉ ውስጥ በግልጽ እንደተቀመጠው ከእግዚአብሔር የተከፈለው የተቃዋሚዎች ዕጣ
ፈንታ “ትክክል ናችሁ!” የሚል መልስና “በረከት” ሳይሆን ታይቶ የማይታወቅ ጥፋትና
ጉስቁልና ነበር። ዳግመኛ ተመሳሳይ መገዳደር በካህናት ላይ እንዳይነሣ ለማድረግም
እግዚአብሔር በሙሴ አማካኝነት ፲፪ ቱንም ነገዶች የሚወክሉ የአባቶቻቸውን በትር ስማቸውን
ጽፎ ወደ መቅደስ እንዲያስገባ አደረገ። እስራኤላውያን ሁሉም የእግዚአብሔር ሕዝቦች ሆነው
ሳለ አሁንም ክህነትን ለአሮንና ለአባቱ ለሌዊ ቤት ማጽናቱን በተዓምር መሰከረ። ቀድሞ
በሰጠው ምልክት መሠረትም የአሮን ስም የተጻፈባት የአባቱ የሌዊ በትር አቆጥቁጣ /ለምልማ/
አብባና የበሰለ ለውዝ አፍርታ ተገኘች። መላው የእስራኤል ልጆችም አዩና አመኑ። (ዘኁ ፲፯)

እግዚአብሔርም ሙሴን እንዲህ ብሎ አዘዘው፤ “ማጉረምረማቸው ከእኔ ዘንድ እንዲጠፋ፥


እነርሱም እንዳይሞቱ፥ ለማይሰሙ ልጆች (ለሚያምፁብኝ) ምልክት ሆና ትጠበቅ ዘንድ የአሮንን
በትር በምስክሩ ፊት አኑር።” (ዘኁ፲፯፥፲፡፡) ሊቀ ነቢያት ሙሴና አሮንም እንደታዘዙት ያችን
የለመለመች በትር በቤተ መቅደስ ውስጥ በቅድስተ ቅዱሳን አኖሯት፡፡ ይህንንም መጽሐፍ
ቅዱስ ለእኛ ምስክርና ተግሣጽ ይሆነን ዘንድ ሲተርክልን ይኖራል። (ሮሜ ፲፭፥፬፡፡) በራእይ
ዮሐንስ ፩፥፭‐፯ የሰፈረውን መልእክት ብናይ “ነገሥታትና ካህናት አደረገን” ይላል። ይህ ማለት
ግን ሁላችንም ነገሥታት፤ ሁላችንም ካህናት ነን ማለት አይደለም። የመንግሥተ እግዚአብሔር
ታዳሚነታችንን እንዲሁም “ተክህነ‐አገለገለ” ማለት እንደሆነ ሁሉ እግዚአብሔርን ለማገልገል
መጠራታችንን የሚያሳይ መሆኑን ማስተዋል ያስፈልጋል፡፡

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 161
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

9.4 በብሉይ ኪዳንና በሐዲስ ኪዳን ክህነት መካከል ያለ ልዩነት

ተራ.ቁ የብሉይ ኪዳን ክህነት የሐዲስ ኪዳን ክህነት


፩ ጊዜያዊ ነበር። ዘላለማዊ ነው፡፡

፪ ከእስራኤል መካከል ለአንድ ነገድ ብቻ -ብቁ ሆነው ለተገኙ የሰው ልጆች ሁሉ


የተሰጠ የተፈቀደ

፫ አገልግሎቱ በቤተ እስራኤል ብቻ የተወሰነ አገልግሎቱ ለመላው የሰው ልጆች ሁሉ

፬ -ሥጋዊ ፈውስ ብቻ ይሰጥ ነበር ፈውሰ ሥጋ ወነፍስ የሚሰጥ ነው

፭ ጊዜያዊ የኃጢአት ሥርየትን ያሰጥ ነበር ፍጹም የሆነ ሥርየተ ኃጢአትን ያሰጣል

፮ መሥዋዕቱ የእንሰሳ ሥጋና ደም ነበር መሥዋዕቱ የዘለዓለም ሕይወት የሆነ


የክርስቶስ ሥጋና ደም ነው

፯ ሌዊንና አሮንን መሠረት ያደረገ ነበር ክርስቶስን መሠረት ያደረገ ነው

9.5 የክህነት ሥልጣን ደረጃዎች


፩. ጵጵስና /ኤጲስ ቆጶስና /፡- ይህ መዓርገ ክህነት ለከፍተኛው የቤተክርስቲያን አገልጋይ
የሚሰጥ ሥልጣን ሲሆን የመዓርጉ ባለቤት ኤጲስ ቆዾስ /ጳጳስ/ ይባላል። ቅዱሳት መጻሕፍት
ይህን መዓርገ ክህነት በተመለከተ ምን ይላሉ?

“ጵጵስናን /ኤጲስ ቆጶስነትን/ ሊሾም የሚወድ መልካም ሥራን ወደደ።” (፩.ጢሞ.፫)

“አሁንም በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተክርስቲያን ትጠብቁ ዘንድ መንፈስ


ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ።”
(ሐዋ ፳፥፳፰፡፡)

“ጳጳስ እንደ እግዚአብሔር መጋቢ የማይነቀፍ ሊሆን ይገባዋል።” (ቲቶ ፩፥፯፡፡)

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 162
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

“ኤጲስ ቆጶስ ሆይ በሥራው ሁሉ ራስህን በንጽሕና አጽና። የሹመትህንም መዓርግ


እወቅ። በሕዝቡ ዘንድ በሹመትህ እንደ እግዚአብሔር ነህና። ለሕዝቡ፣ ለነገሥታት
ሁሉ፣ ለመኳንንቱ፣ ለካህናቱ ለአባቶችና ለተማሩት ልጆቻቸው፣ ከትእዛዝህ በታች
ላሉት ሁሉ፣ አለቃ ሁነሃልና። በቤተክርስቲያን ተቀመጥ። በቃልህም አስተምር።
(ፍት.ነገ አን፭፥፻፲፰)

“ስለ ኤጲስ ቆጶስም፣ ለአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ኤጲስ ቆጶስ ሆኖ የሚሾመው


የምእመናን ጠባቂ፣ ነውር የሌለበት፣ ንጹሕና ቸር፣ የዚህንም ዓለም ጭንቀት
የማያስብ፣ ፶ ዓመት የሞላው፣ የጎልማሳነት ኀይልን ያለፈ፣ ነገር የማይሠራ፣
በወንድሞችም መካከል ሐሰትን የማይናገር ይሆን ዘንድ እንደሚገባው በጌታችን
በኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ ሰማን። (ዲድስቅልያ ፬፥፩፡፡)

፪. ቅስና፦ ይህ ከመዐርጋተ ክህነት አንዱ ሲሆን ባለሙያውና ተሿሚው ቄስ ወይም ቀሲስ


ይባላል። ትርጓሜውም የቤ/ክ አገልጋይ ማለት ነው። ቅስናን በተመለከተም ቅዱሳት መጻሕፍት
የሚሰጡት ምስክርነት ብዙ ነው። ጥቂቶቹን ብቻ እንደሚከተለው እናያለን።

“ለቤተ ክርስቲያንም ቀሳውስትን ሾሙ፣ ጾሙ፣ ጸለዩም፣ ለሚታመኑበት


ለእግዚአብሔርም አደራ ሰጡአቸው። (ሐዋ ፲፬፥፳፫) “ወደ ኢየሩሳሌም በደረሱ ጊዜም
ምእመናንና ሐዋርያት ቀሳውስትም ተቀበሏቸ” (ሐዋ፲፭፥፬)

” በየከተማውም ሲሄዱ ሐዋርያትና ቀሳውስት በኢየሩሳሌም ያዘዙትን ሥርዓት


አስተማሩአቸው። አብያተ ክርስቲያናትም በሃይማኖት ጸኑ፤ ዕለት ዕለትም ቁጥራቸው
ይበዛ ነበር።” (ሐዋ፲፮፥፬‐፮፡፡) በመልካም የሚያስተዳድሩ ቀሳውስት ይልቁንም በመስበክና
በማስተማር የሚደክሙ እጥፍ ክብር ይገባቸዋል።” (፩ጢሞ፭)

“ከእናንተ የታመመ ሰው ቢኖር በቤተክርስቲያን ያሉ ቀሳውስትን ይጥራና ይጸልዩለት።”


(ያዕ፭፥፲፬፡፡)

“መልካም የሆኑትን የአምላክን መጻሕፍት ነገር፣ ይልቁንም አራቱን ወንጌላት ያላወቀ


አንዱ ስንኳ ቄስ አይሁን፤ አምስት ሰዎች ያልመሰከሩለት አንዱ ስንኳ ቄስ አይሁን።”
(ፍት.ነገ.አነ.፮፥፪፻፲፪፡፡)

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 163
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

፫. ድቁና፦ ይህ የመጨረሻው (ታችኛው) መዓርግ ክህነት ነው። ቃሉ “ዲያኮንያ” ከሚለው


የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም “ረዳት፣ አገልጋይ” ማለት ነው። ይህንንም መዓርገ
ክህነት በተመለከተ ቅዱሳት መጻሕፍት ምን እንደሚሉ ደግሞ እንመለከታለን ።

“ከኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያዎች ከጳውሎስና ከጢሞቴዎስ ፥ በፊልጵስዩስ ለሚኖሩ


ከቀሳውስት፣ ከኤዺስ ቆጶሳትና ከዲያቆናት ጋር በኢየሱስ ክርስቶስ ላሉ ቅዱሳን ሁሉ።”
(ፊልጵ.፩፥፩፡፡)

“እንዲሁም ዲያቆናት ጭምቶች፣ ቃላቸው የማይለወጥ፣….” (፩ጢሞ፫፥፰፡፡) ዲያቆናትም


ልጆቻቸውንና የቤታቸውን አስተዳደር በመልካም እየገዙ፣እያንዳንዳቸው የአንዲት ሴት
ባሎች ይሁኑ።” (፩ጢሞ፫፥፲፪፡፡)

“ዲያቆናት መልካም ሥራን በመዓልትም በሌሊትም በቦታው ሁሉ የሚሠሩ ይሁኑ።”


(ፍት ነገ. አን. ፯፥፪፻፶፰፡፡) ከዚህም በተጨማሪ ሐዋርያት ሰባቱን ዲያቆናት በፈቃደ
እግዚአብሔር እንደሾሙ ተገልጾልናል። እነዚህ ሁሉ ምስክሮች መዐርጋተ ክህነት፣ ተፈላጊ ሥነ
ምግባራትና ሥርዓተ ክህነትን የተመለከቱ ምሥጢራት ሁሉ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሆናቸውን
ማሳያ ናቸው። ከተጠቀሱት ውጪ በተገለጹት ዐበይት የክህነት ደረጃዎች ሥርና መካከል
ሌሎች በቤተክርስቲያናችን አገልግሎት የታወቁ ንዑሳን የሥልጣን መዓርጋት አሉ፡፡
ዲያቆናዊት፣ ንፍቅ ዲያቆን፣ አናጉንስጢስ /አንባቢ/፣ መዘምር፣ ዘማሪ /ማኅሌታዊ/፣ ዐጸውተ
ኀዋኅው፣ ሊቀ ዲያቆን፣ ቆሞስ፣ ሊቀ ጳጳስና ፓትርያርክ የሚባሉት ናቸው።

9.6 የምስጢረ ክህነት አፈጻጸም

9.6.1 ሥርዓተ ሲመተ ኤጲስ ቆጶስ

መስፈርታት /መመዘኛዎች/

“ጵጵስና ሊሾም የሚወድ መልካም ሥራን ወደደ የሚለው ቃል የታመነ ነው፤ ነገር ግን
ጵጵስናን የሚሾም እንዲህ ሊሆን ይገባዋል፡፡

1. የማይነቀፍ፤

2. አንዲት ሴት ያገባ፦ ይህ እስከ ኒቅያ ጉባኤ ድረስ የተተገበረ ሲሆን በ318ቱ ቅዱሳን አባቶች
ጉባኤ ጳጳስ ድንግላዊ እንዲሆን በመወሰኑ አሁን እየተፈጸመ ያለው ይህኛው /ድንግላዊ

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 164
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

የሚለው/ ነው። ሌሎቹ መስፈርቶች ግን ሳይለወጡ እንዳሉ የቀጠሉ ናቸው፡፡ ባለትዳሩ


ድንግላዊ በሆነው የተቀየረበትም ምክንያትም የሚከተለው ነው፡፡

3. ካህኑ ባለትዳር በመሆኑ ምክንያት ሙሉ ጊዜውንና ትኩረቱን ለቤተ ክርስቲያን ማድረግ


እያቃተው በመምጣቱ ነው፡፡ የቤተ ክርስቲያን ሥራ በሙሉ ልብ፣ ትኩረትና ጊዜ ሊሠራ
የሚገባው በመሆኑ በተለይ በመሪነት ያሉት ጳጳሳት ይህን ያሟሉ እንዲሆኑ በማስፈለጉ
በ፫፻፳፭ ዓ.ም የቤተ ክርስቲያን አባቶች በኒቂያ ጉባኤ ጳጳሳት ድንግላውያን እንዲሆኑ ወሰኑ፡፡
ለዚህም ውሳኔያቸው፡- “ነገር ግን ያለ አሳብ ልትኖሩ እወዳለሁ፡፡ ያላገባው ጌታን እንዴት ደስ
እንደሚያሰኘው የጌታን ነገር ያስባል፤ ያገባ ግን ሚስቱን እንዴት ደስ እንደሚያሰኛት የዓለምን
ነገር ያስባል፤ ልቡም ተከፍሏል፡፡” (፩ቆሮ ፯፥፴፪-፴፬) በማለት ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ
ያስተማረውን ትምህርት መሠረት አድርገዋል፡፡

ካህኑ በሚስቱ ላይ ልጆች ሲጨመሩበት ልቡን ምን ያህል ሊከፍልበት እንደሚችል ተረድተው


መላ ዘመኑን በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት እግዚአብርሔርን እንዴት ሊያስደስተው እንደሚችል
እንዲያስብና የሚያስጨንቀው የአብያተ ክርስቲያናት ጉዳይ ብቻ እንዲሆን ለማስቻል ይህን
ወስነዋል፡፡ (፪ቆሮ. ፲፩፥፳፰፡፡) ትጉህ፤ ብልህ፤ እንደሚናገረው የሚሠራ፤ እንግዳ ተቀባይ፤ ራሱን
የጠበቀ፤ የሚያስተምርና የሚገሥጽ፤ የማይሰክር፤ ለመማታት /ለማውገዝ/ እጁን /አንደበቱን/
የማያፈጥን፤ ትዕግሥተኛ፤ የማይጣላ፤ ገንዘብ የማይወድ፤ ቤቱን በመልካም የሚያስተዳድር፤
በፍጹም ንጽህና የሚታዘዙ ልጆች ያሉት፤ አዲስ አማኝ /ክርስቲያን/ ያልሆነና መልካም ምስክር
ያለው ሊሆን እንደሚገባ ተጽፏል። (፩ጢሞ ፫፥፩‐፰፡፡)

“ለአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ኤጲስ ቆጶስ ሆኖ የሚሾመው የምእመናን ጠባቂ ሆኖ ነውር


የሌለበት፤ ንጹሕና ቸር፤ የዚህን ዓለም ጭንቀት የማያስብ፤ ፶ ዓመት የሞላው፤ የጎልማሳነት
ኃይልን ያለፈ፤ ነገር የማይሠራ፤ በወንድሞች መካከል ሐሰትን የማይናገር ይሆን ዘንድ
እንደሚገባው በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ ሰማን (ዲድስቅልያ ፬፥፩፡፡) የሚማር ይሁን፤
ሰላምን የሚያደርግ ይሁን፤ ቂም ክፋትና ዐመፅ የሌለበት ልበ ንጹሕ ይሁን፤ በጎ ሥራን
ለመሥራት ትጉህ መንፈሳዊ ይሁን፤ የማይሳሳት፤ የማይቆጣ፤ የማይበቀል፤ ጸብና ክርክር
የሌለው፤ የማይኮራ፤ ገንዘብ የማይወድ፤ የማይሳደብ ይሁን፤ በዚህ ዓለም ጉዳይና በሥጋው
ነውር የሌለበት ይሁን፤ የሚራራና የሚመጸውት ይሁን፤ ሰውን ወዳጅ የሆነ፤ እንግዳን
የሚቀበል፤ ፊት አይቶ የማያዳላ፤ እውነተኛ ፈራጅ የሆነ፤ ጥበብ ያለው፤ ለመስጠት እጁን

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 165
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

የሚዘረጋ፤ ረዳት የሌለውን የሚቀበል፤ ድሆችን፥ ደሀ አደጎችንና ባልቴቶችን የሚወድ ይሁን”።


(ዲዲስቅልያ ፬፥፰‐፲፭፡፡)

የአሿሿም ሥርዓት

ኤጲስ ቆጶስ በዕለተ እሑድ ይሾም። በሚሾምበትም ቀን ካህናትና ምዕመናን ይገኙ ሕዝቡና
ካህናቱም መክረውለት ይሾም፤ እጃቸውን በእርሱ ላይ ሊያኖሩ የመጡ ኤጲስ ቆጶሳቱም “እኛ
በዚህ በተመረጠ በእግዚአብሔር ባሪያ ላይ እጃችንን እናስቀምጣለን፤ እያሉ በአብ በወልድ
በመንፈስ ቅዱስ ስም እጃቸውን ያስቀምጡ። ነውር በሌለባትና አንዲት በሆነች በማይገለጥ
በሕያው እግዚአብሔር ቤተክርስቲያን በጸናች ሥርዓት ይጸና ዘንድ፣ የቀና ፍርድን ለመፍረድ፣
ምስጋናን፣ ለመግለጥ ልጅነትን ለማሰጠት፣ ለታመነች ትምህርት፤ ይኸውም ነገረ መስቀሉን
ለማስተማር ከሥሉስ ቅዱስ ዘንድ በጉባኤ በቤተክርስቲያን የተሾመ ነው።

ከዚህም በኋላ ከእነርሱ ቀዳሚ የሆነው ኤጲስ ቆጶስ እጁን ይጫንበት የሹመቱንም ጸሎት
ያድርስ፤ ሕዝቡም “አሜን” ይበሉ። ከዚህ በኋላ ኤጲስ ቆጶሳቱ እጅ ይንሡት ሕዝቡና ካህናቱም
ይገባዋል! ይገባዋል! ይበሉ። ሁሉም እጅ ይንሱት። በእንተ ሰላምን ይጸልዩለት ከዚህ በኋላ
ሊነበብ የሚገባውን ክፍለ መጽሐፍ ቅዱስ ያንብቡ፡፡ አከታትለውም ቅዳሴውን ይፈጽሙ
አስቀድሞ እርሱ ሥጋውንና ደሙን ይቀበል። ከዚያም በየማዕረጋቸው ለሁሉም ሥጋውና
ደሙን ያቀብላቸው። በሰላምም ያሰናብታቸው። እስከ ሦስተኛው ቀን ድረስ በጌታ ትንሣኤ
አምሳል ፫ ቀን መንፈሳዊ በዓል ያክብሩ።

ሁሉም ከተመረጡ በኋላ ሕዝቡና ቀሳውስቱ ዲያቆናቱ ኤጲስ ቆጶሳቱም በዕለተ እሑድ
ይሰብሰቡ። ከእርሱ የሚበልጠው “አለቃ ይሆናችሁ ዘንድ የመረጣችሁት ይህ ነውን?” ብሎ
ቀሳውስቱንና ዲያቆናቱን ይጠይቃቸዋል። አዎን ቢሉ “የከበረችው ሹመት ለዚህ ትገባዋለችን?”
ይበል፤ “በሚገባና በተረዳ ሥርዓት አኗኗርን አጽንቷልን? ምንም በደል አልተገኘበትምን?”
ይበል እነርሱም መልሰው እንደዚህ እንደሆነ ቢናገሩ በማድላት ያይደለ በእውነት ሹመት
ይገባዋል፡፡ በሦስተኛውም ደግሞ “ለዚህ ሹመት በእውነት ይገባዋልን?” ብሎ ይጠይቃቸው።
ነገር ሁሉ በሁለት ወይም በሦስት ምስክር ይጸናልና በሦስተኛውም ጊዜ ይገባዋል ቢሉ ሁሉም
እጃቸውን ዘርግተው ያጨበጭባሉ። ይህንንም በስምምነት ካደረጉ በኋላ ጸጥታ ይሁን።

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 166
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ዲያቆናትም ቅዱሳት ወንጌላትን ገልጠው በተሾመው ራስ ላይ ይያዙ፤ ኤጲስ ቆጶሳትም ለርሱ


በሚገባው ወንበር ያስቀምጡት፤ ሁሉም ከተቀበሉት እግዚአብሔርም ይቀበለዋል። በሦስት
ኤጲስ ቆጶሳት ይሾም፤ እንደዚህ ይሾም። በራሱ ላይ ወንጌልን ተሸክመው የበለጠው ኤጲስ
ቆጶስ እንደዚህ (ለሲመቱ የተዘጋጀውን ጸሎት) ይጸልይ። ጸሎቱን ከጨረሰ በኋላ እጁን
ይጫንበት። ይሳለመውም። መንፈስ ቅዱስም ይመላበት (ያድርበት) ዘንድ በፊቱ ላይ እፍ
ይበልበት። ከዚህ በኋላ የቀሩት ካህናት ሁሉ እጅ ይንሱት፡፡ ሕዝቡ ግን እጁን ይሳሙት ከዚህ
በኋላ ቅዳሴውን ይፈጽሙ። (ፍት. ነገ. አንቀጽ፭፥፻፳‐፻፮፡፡) ከዚህ በተጨማሪ

ኤጲስ ቆጶሳቱ አዲሱን ኤጲስ ቆጶስ ከመሾማቸው በፊት እጃቸውን ይታጠባሉ። /ፍትነገ.
አን፬፡፡/
ተሿሚውን ኤጲስ ቆጶስ መስቀል ያስይዙታል።
ኤጲስ ቆጶስ በአንድ ኤጲስ ቆጶስ አይሾምም። ከርእሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ ጋር ሁለት ወይም
ሦስት ሊቃነ ጳጳሳት /ጳጳሳት/ አንብሮተ እድ በማድረግ ይሾማሉ። /አብጥሊስ ፪፡፡/
ኤጲስ ቆጶስ የሚሾመው በሚሾምበት ሀገር ካህናትና ምእመናን ምርጫና በርእሰ ሊቃነ
ጳጳሳቱ ፈቃድ ነው። /አብጥሊስ ፪፡፡/
መራጮችም (ቢያንስ) 30 ዘመን (ዓመት) የሆናቸው ናቸው።

9.6.2 ሥርዓተ ሲመተ ቀሳውስት


መመዘኛዎች

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለጊዜው ለረድኡና ኤጲስ ቆጶስ አድርጎ ለሾመው ለቲቶ ለፍጻሜው
ደግሞ ለቤተክርስቲያን መመሪያ እንዲሆን ያስቀመጠው /ያስተላለፈው/ የቀሳውስት መስፈርት
የሚከተለውን ይመስላል፡፡ የአንዲት ሚስት ባል፤ የማይነቀፍ፤ የሚያምኑ ልጆች ያሉት፤
ስለመዳራት ወይም ስለአለመታዘዝ የማይከሰስ ማንም ቢኖር ሹመው፡፡ (ቲቶ ፩፥፭‐፯)
በተጨማሪም በፍትሐ ነገሥት አባቶቻችን (የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት) በጉባኤ የወሰኑአቸው
መመዘኛዎች ቀርበዋል፡፡ ጥቂቶቹን እነሆ፡- በራሱ ፈቃድ የሚኖር አይሁን፤ ቂመኛ፣ አብዝቶ፣
የሚጠጣ፣ ለመማታት (ለመገዘት) እጁን (አንደበቱን) የሚያፈጥን አይሁን፤ እንግዳ መቀበልን
የሚወድ፤ በጎ ሥራን የሚወድ፤ ንጹሕ፥ ጻድቅ፥ ቸር የሆነ፤ ከፍትወታት ሰውነቱን ወስኖ ገትቶ
የያዘ፤ የሃይማኖት ትምህርት ነገርን በማስተማር የሚተጋ፤ ያልታዘዘ ትርፍን የሚወድ
አይሁን። የእውነት ትምህርትን በማስተማር ማረጋጋት የሚችል፤ የሚክዱትንና
የሚተናኮሉትን የሚከራከራቸው ይሁን እንጂ፤ ሠላሳ ዓመት የሆነው፤ መልካም የሆኑትን

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 167
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

የአምላክ መጻሕፍትን ነገር ይልቁንም አራቱን ወንጌላት ያወቀ፤ አምስት ሰዎች የመሰከሩለት፤
(ፍት.ነገ. አነ ፮፥፪፻፲‐፪፲፫)

አፈጻጸም

ኤጲስ ቆጶሳት አንብሮተ እድ ይሾማሉ፤

ቀሳውስት ዙሪያቸውን ከበው ይዳስሷቸዋል፤

ለኤጲስ ቆጶስ ሹመት እንደተነገረው ይጸልዩለት፡፡ (ፍት.ነገ.አን ፮፥፲፫፡፡)

9.6.3 ሥርዓተ ሲመተ ዲያቆናት


መመዘኛዎች

ዲያቆናትን ለመሾም የሚቻልባቸው መመዘኛዎች በቅዱስ ጳውሎስ መልእክት ውስጥ በሰፊው


ሰፍረዋል። ለማሳያ ያህል የሚከተለውን መመልከት እንችላለን:: እንዲሁም ዲያቆናት:-
ጭምቶች፤ ቃላቸው የማይለወጥ፤ የወይን ጠጅ መጠጣትን የማያበዙ፤ ከንቱ ትርፍንም
የማይወድዱ ይሁኑ፤ የሃይማኖትንም ምሥጢር በንጹሕ ልብ የሚጠብቁ ሊሆኑ ይገባል፤
እነርሱም አስቀድመው ይፈትኑአቸው ከዚህም በኋላ ያለነቀፋ ከሆኑ ያገልግሉ፤ የአንዲት ሴት
ባሎች የሆኑ፤ ልጆቻቸውንና የቤታቸውን አስተዳደር በመልካም የሚገዙ በማለት ይዘረዝራል።
“በመልካም ለሚያገለግሉት ከፍተኛውን ሹመት ይስጧቸው፤ ኢየሱስ ክርስቶስን በማመን ብዙ
ባለሟልነት አለና”። (፩ጢሞ፫፥፰‐፲፩፡፡) በማለት ያጠቃልላል። በፍትሐ ነገሥትም ከቀረቡት
መመዘኛዎች መካከል ለየት ያሉ የሚመስሉትን ብቻ መርጠን እናቀርባለን። ርኩስ የሆነውን
የትርፍ ድርሻ አይውደዱ፤ የሚራሩ፣ የዋሃን፣ የማያንጎራጉሩ ይሁኑ፤ ቁጡዎች አይሁኑ፤
ለባለጸጎች ፊት የሚያደሉ ነዳያንን የሚያሳዝእኑ ወይን አብዝተው የሚጠጡ አይሁኑ፤ ስለበጎ
ምሥጢራት ምርመራ የሚሰንፉ አይሁኑ ፤ከሶስት ሰዎች የተመረጡና የተመሰከረላቸው
ይሁኑ፤ ሃያ አምስት ዓመት የሆናቸው፤ (ፍት.ነገ. ፯፥፪፻፴፱‐፪፻፵፮፡፡)

አፈጻጸም

“ዲያቆኑን በምትሾምበት ጊዜ በእርሱ ላይ እጅህን አኑርና (አስቀምጥና) ጸልይ። ሁሉም


ቀሳውስትና ዲያቆናት ቁመው ሳሉ አስቀድመን እንደተናገርንና እንዳልን ይመረጥ። ከዚህ በኋላ

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 168
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ኤጲስ ቆጶሱ ብቻ እጁን ይጫንበት። ቀሳውስት የሚተባበሩበትን ቅስና ይህ ዲያቆን ይቀበል


ዘንድ አይሾምምና፤ የኤጲስ ቆጶሱን ትእዛዝ ይሠራ ዘንድ ነው እንጂ። (ፍት.ነገ.አን.፯፥፪፻፵፱)

9.7 የቤተ ክርስቲያን አባቶች አገልግሎታቸውን በአግባቡ እንዲፈጸሙ


1. የቤተ ክርስቲያን ጸሎት፡-
እያንዳንዳችን ክርስቲያን ሆነን ለመኖር፣ ዓለምን አሸንፈንና ፈተናን ተቋቁመን ለመኖር ምን
ያህል የእግዚአብሔር እርዳታ እንደሚያስፈልገን በእውነተኛው የክርስትና ጠባብ ጐዳና ትንሽ
የተጓዘ ሰው ሁሉ ያውቀዋል፡፡ ጻድቁ ኢዮብ እንዳለው «የሰው ሕይወቱ በምድር ላይ ብርቱ
ሰልፍ ነው፡፡» ስለዚህ በየሰዓቱ «አቤቱ ወደ ፈተና አታግባን» እያልን እንጸልያለን፡፡ /ማቴ 6፥
13/ የራስን ሕይወት ለማዳን ይህን ያህል የእግዚአብሔር ጸጋና ጸሎት የሚያስፈልግ ከሆነ
ከራስ አልፎ ሰዎችን ለማዳንማ ምን ያህል ጸሎትና የእግዚአብሔር እርዳታ ያስፈልግ ይሆን?
ሰው የራሱን መዳን በፍርሃትና በመንቀጥቀጥ የሚፈጽም ከሆነ፣ ብዙ መከራን መቀበል
የሚጠበቅበት ከሆነ፣ በቤተ ክርስቲያን ላይ ተሹሞ ለማገልገል የተነሳ፣ ብዙ ነፍሳትን
ከዲያብለስ ነጥቆ ወደ ክርስቶስ በረት ለማስገባት የሚዋጋ የክርስቶስ ወታደርማ ምን ያህል
መከራን መቀበልና ፈተናን መጋፈጥ ይጠበቅበት ይሆን? ስለዚህም ሐዋርያው ቅዱስ
ጳውሎስ«ለሌሎች ከሰበኩ በኋላ እኔ ደግሞ የተጣልኩ እንዳልሆን ራሴን በመጐሰም
አስገዛለሁ»ይላል።/1ኛ ቆሮ 9፥27/ ይህንን የምታውቅ ቤተ ክርስቲያን ሁለት መሠረታዊ
መመሪያዎች አሏት፡፡

የመጀመሪያው ለክህነት የሚመረጡ ሰዎች ጠንካራ ክርስቲያኖች፣ ዲያብሎስን የመዋጋትና


በእግዚአብሔር ኃይል ድል የማድረግ ልምድ ያላቸው እንዲሆኑ ያስፈልጋል ይህንንም ቅዱስ
ጳውሎስ «አዲስ ክርስቲያኖች አይሁኑ በማለት ጠቅለል አድርጐ ተናግሮታል።1ኛ ጢሞ 3፡6
በተለይ ከፍተኛው የክህነት ደረጃ /ለጵጵስና/ የሚመረጡ ሰዎች ከመነኮሳት መካከል እንዲሆኑ
ቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ሰርታለች፡፡ እውነተኞች መነኮሳት ጌታ በምድረ በዳ ድል ያደረገውን
ዲያብሎስ በምድረ በዳ ድል የሚያደርጉ፣ ለኃጢአት ሁሉ ስር የሆነውን ዓለምን መውደድን
አሸንፈው በምድር ሰማያዊ ኑሮ የሚኖሩ፤ ለክህነት አገልግሎት የተመቹ ናቸው፡፡ ለክህነት
አገልግሎት ከሚመረጡት በኩል የሚጠበቅ ነው፡፡

ከምዕመናንስ ምን ይጠበቃል? እነዚህ አባቶች ሕይወታቸውን ለምዕመናን ጥበቃ መስዋዕት


እንዳደረጉ ምዕመናንም ስለነዚህ አባቶች አዘውትረው ሊጸልዩ ይገባል፡፡ ለዚህ ነው ሐዋርያው

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 169
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

«ወንድሞች ሆይ ስለእኛ ደግሞ ጸልዩ» ያለው፡፡ /2ኛ ተሰ 5፥25/ ቤተ ክርስቲያናችን


በእያንዳንዱ ሥርዓተ ጸሎት ለአበው እንጸልይ ዘንድ ታሳስበናለች፡፡ በቤተ ክርስቲያን ቅዳሴ
ሲቀደስ «ጸልዩ በእንተ ሊቃነ ጳጳሳት፣ ስለሊቃነ ጳጳሳት ጸልዩ» ይላል ዲያቆኑ፤ እኛም
እንጸልያለን፡፡ በቅዳሴአችን ጊዜ «አቤቱ ለቤተ ክርስቱያን አባቶች ፍቅርን ስጥ።» እያልን
እንጸልያለን። ስለዚህ ኢያሱና ሆር ሙሴን ይጸልይ ዘንድ ሁለት እጁን ደግፈው እንደያዙት
እኛም አባቶቻችን በጸሎታቸው፣ በአገልግሎታቸው ይጸኑ ዘንድ ኢያሱና ሆርን በጸሎት
ልንደግፋቸው ይገባል፡፡ ኢያሱና ሆር ሲደክሙ የሙሴ እጅ ይታጠፍ ነበር፤ እስራኤልም ይሸነፉ
ነበር፡፡ እኛም በጸሎታችን መደገፋችንን ካቆምን የአባቶች የአገልግሎት፣ የጸሎት እጅ ሊታጠፍ
ይችላል፡፡ በዚህም የእስራኤል ዘነፍስ ጉባኤ ቤተ ክርስቲያን በአማሌቅ (የዲያብሎስ ሠራዊት)
ትታወካለች፡፡

2. አስራት በኩራት ማውጣት ፦


በብሉይ ኪይን ከአስራ ሁለት ነገዶች አንዱ የሌዊ ነገድ ርስት አልተሰጠውም ነበር፡፡
ምክንያቱም የሌዊ ነገድ የካህናት ነገድ በመሆኑና ለካህናት ደግሞ ርስታቸው እግዚአብሔር
በመሆኑ ነበር፡፡ ስለዚህ ምዕመናን ለእግዚአብሔር ከሚያመጡት አስራት በኩራት ለካህናቱ
ይሰጣቸው ነበር፡፡ ይህም ለአዲስ ኪዳን ካህናትም ይሰራል፡፡ ካህናት አባቶች ቤተ ክርስቲያንን
እንዲያገለግሉ፣ የተሰጣቸውን የአገልግሎት ሥልጣን በአግባቡ እንዲወጡ ከፈለግን እኛ
በገንዘባችን፣ በዕውቀታችን፣ በጉልበታችን ልናግዛቸው ይገባል፡፡ አስራት በኩራት ከአንድ
ክርስቲያን የሚጠበቅ ትንሹ ስጦታ ነው፡፡ አያሌ ክርስቲያኖች ከዚህ ያለፈ ነገር ለቤተ
ክርስቲያን ሲሰጡ ኑረዋል፡፡ ይህን የሚያደርጉት ለቤተ ክርስቲያን መስጠት ለራስ መስጠት
መሆኑን ስለሚያውቁ ነው፡፡ እግዚአብሔርማ መች የኛን ገንዘብ ይፈልጋል፤ እኛው
እንገለገልበት ዘንድ፣ ካህናቱ በዚያ እየተደገፉ መንጋቸውን በሰላም ይጠብቁ ዘንድ ነው፡፡

9.8 የቤተ ክርስቲያን አባቶች በፈተና ቢወድቁስ?


በክርስትና ፈተና መምጣቱ አይቀርም በተለይም ይህ ፈተና በአባቶች ዘንድ ጠንከር ይላል፡፡
«መንጋው ይበተን ዘንድ» ዲያብሎስ «እረኛውን» ለመምታት ስለሚጥር ነው፡፡ ይህ ፈተና
በአባቶች ላይ ውጤቱ የተለያየ ነው፡፡ ደገኞቹ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ዲያብሎስን ድል
አድርገው፣ አላውያን ነገሥታትን ድል ነስተው፣ ሩጫቸውን በታላቅ ድል ፈጽመው፣
እግዚአብሔርን አስደስተውና ምዕመናንን አገልግለው ያልፋሉ፡፡ ሌሎቹም እንደየአቅማቸው
በተሰጣቸው ጸጋ አገልግለው ያልፋሉ፡፡ እስከዚህ ድረስ መልካሙን ጦርነት ተዋግተው

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 170
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ያሸነፉትን ጠቅሰን ተናገርን እንጂ፡፡ በዚህ ፈተና ድል የሚነሱ፣ መንጋው ይበተን ዘንድ
ዲያብሎስ መትቶ የሚጥላቸው፣ ከዚያም በኋላ ከራሳቸው አልፎ ምዕመናንንም
የሚያሰናክልባቸው አባቶችም ጥቂት አይደሉም፡፡

የአባቶች በፈተና መውደቅ ክብደቱ የተለያየ ነው፡፡ አባቶቻችን እንደኛው ሥጋ ለባሽ ፍጡር
ናቸውና የጋራ ድካማችን ይጋራሉ፡፡ በዚህም ምክንያት በየዕለቱ ጥቃቅን ስህተቶችን
መፈጸማቸው አይቀርም፡፡ ቅዱሳን አባቶች እንደሚሉት «ማንም በዚህች ምድር ላይ ለአንድ ቀን
ቢውል እግዚአብሔርን ሳይበድል የሚውል የለም»፡፡ ስለዚህ አባቶችም በፈተና ቢወድቁ
አይገርምም፡፡ ቤተ ክርስቲያናችንም ንስሓን ለሁሉም ትፈቅዳለች፡፡ እያንዳንዳቸው ካህናት
አባቶች ለሌሎች የንስሐ አባት ቢሆኑም ለራሳቸው ደግሞ የንስሐ አባት ሊኖራቸው ይገባል፡፡
ስለዚህ አባቶቻችን በትንሽም በትልቅም ኃጠአት ቢወድቁ ንስሐቸውን እግዚአብሔር ይቀበላል፤
ምዕመናንም የኃጢአትን አስቸጋሪነት እያወቁ ያዝኑላቸዋል ይጸልዩላቸዋል እንጅ
አይፈርዱባቸውም፡፡ ነገር ግን ክህነትን የሚያስነጥቁ ኀጢአቶች አሉ፡፡

አባቶች በእነዚህ ኃጢአቶች ቢወድቁና ንስሐ ቢገቡ ኃጢአታቸው ይቅር ይባላል፤ ክህነታቸው
ግን አይመለስም፡፡ በእነዚህ ኃጢአቶች የተሰነካከሉና ንስሐ የገቡ አባቶች እንደምዕመናን ሆነው
ወደ ቅድስና የማደግ ፀጋ ሳይነፈጋቸው በቤተ ክርስቲያን በጾም በጸሎት በሰላም ይኖራሉ፡፡
ከዚህ የከፋው የአባቶች ፈተና ግን ታላላቅ ኃጢአቶችን /ለምሳሌ፡- እንግዳ ትምህርት
ማስተማር፣ ምንፍቅና፣ ዝሙት.../ ሰርተው ንስሐ አለማግባት ነው፡፡ እንዲያውም በተቃራኒው
የተወሰኑ የዋሃን ምዕመናንን ተከታይ በማድረግ ቤተ ክርስቲያንን እንደሚያውኩ በቤተ
ክርስቲያን ታሪክ ይታወቃል፡፡ ቤተ ክርስቲያንን የከፋፈሉት ታላላቆቹ መናፍቃን በቤተ
ክርስቲያን የክህነት ማዕርግ የነበራቸው /አርዮስ ቄስ ነበር፤ ንስጥሮስ የቁስጥንጥንያ ሊቀ ጳጳስ
ነበር.../ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ናቸው፡፡

በክፉ ኃጢአታቸው ጸንተው የሚኖሩትን፣ ይባስ ብለውም ምዕመናንን የሚከፋፍሉትን አባቶች


ቤተ ክርስቲያን ከማኅበሯ ስትለያቸው /ስታወግዛቸው/ ኖራለች፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ «ክፉውን
ከመካከላችሁ አውጡት» እንዳለ የቤተ ክርስቲያንን ማኅበር የሚያውኩትን፣ የንጉሠ ሠላም
የክርስቶስን አደራ ተቀብለው በምዕመናን መካከል መለያየትን የሚዘሩትን «አባቶች» ቤተ
ክርስቲያን ስትለያቸው ኖራለች፡፡ እንግዲህ በቤተ ክርስቲያን አባቶች ላይ ያለው ፈተና ሥጋ

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 171
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ለባሽ ሁሉ ከማያመልጣቸው ጥቃቅን ኃጢአቶች ከቤተ ክርስቲያን እስከሚለዩት ከባድ


ኃጢአቶች ይደርሳል ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ምዕመናን አባቶች በፈተና ወድቀው ሲመለከቱ፡-

1. ለአባቶች በፈተና መውደቅ የእኛ እጅ ሊኖር እንደሚችል ማወቅ


ከላይ ቀደም ብለን እንደጥቀስነው አባቶች ጠንክረው የአገልግሎት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ
የምዕመናንም ጸሎት የእነርሱም ብርታት አስፈላጊ ነው፡፡ ይህንንም በመረዳት በቤተ ክርስቲያን
በሚከናወነው ጸሎት ሁሉ ለአበው እንጸልይ ዘንድ ሥርዓት ሰርታለች፡፡ ስለዚህ አበው በፈተና
ሲወድቁ ምዕመናን ራሳችንን መፈተሽ ይገባናል፡፡ «በየቅዳሴው ለአባቶች የምንጸልየው ጸሎት
የት ሄደ? እግዚአብሔር ጸሎታችንን ለምን አልሰማም? » ብለን ራሳችንን መጠየቅ ይገባል፡፡

በህዝበ እስራኤል ኃጢአት ታቦተ ጽዮን ተማርካ እንደነበር፣ ነቢያቱም በባቢሎን ተማርከው
እንደነበረ አሁንም አባቶቻችን የተማርኩት በእኛ ኃጢአት ምክንያት ይሆንን? ብሎ ራስን
መጠየቅ ይገባል፡፡ አባቶች ራሳቸውንና ቤተሰቦቻቸውን የሚያስተዳድሩበት፣ ገዳማት ተጠናክረው
ለጸሎትና መልካም አባቶችን ለማፍራት እንዲተጉ ረድተናቸዋል ወይ? አባቶች በፈተና ሲወድቁ
እጃችን በእነርሱ ላይ የምንቀስር ሁላችን ወደ ፈተና እንዳይገቡ በምን ረዳናቸው? በጸሎታችን
እናስባቸዋለን ወይ? አስራት በኩራት እናወጣለን ወይ? «የሚያስተምሩንና አርአያ የሚሆኑን
አባቶች ብናገኝ እናደርግ ነበር» ልንል እንችላለን፡፡ ነገር ግን ይህ ግማሽ ምክንያት እንጅ ሙሉ
ስላልሆነ እኛም እነርሱም /ካህናቱም/ ከበደል አናመልጥም፡፡«ሁላችንም በድለናል»ማለት
ይሻለናል።

2. መፍረድ አይገባም
«እንዳይፈረድብህ አትፍረድ» ይላል /ማቴ 7፥1/ ለመፍረድ ማንም ስልጣን አልሰጠንም፡፡ ኧረ
ለመሆኑ አባቶች የተሸከሙትን ፈተና ሞክረን አይተነዋል ወይ? እኛ ብንሆን እንደነርሱ
እንደማንሆን ምን ማረጋገጫ አለን? አባቶቻችን ዓለምንና ክብርን ንቀው፣ ራሳቸውን
ለምንኩስናና ራስን የመካድ ኑሮ አሳልፈው ሰጡ፡፡ ከእነርሱ መካከል የተውትን ክብር የናፈቁ፣
የካዱት እኔነታቸው እያሸነፋቸው ይኖራሉ፡፡ በእነዚህ አባቶች ላይ እጆቻችን የምንቀስር
ስንቶቻችን ይህንን ክብርንና ራስን የመካድ ኑሮ ሞክረነው እናውቃለን፡፡ አብዛኞቻችን
የምዕራባውያንን የተንደላቀቀ ኑሮ የለመድን፣ የምንኩስናንና የተጋድሎን ኑሮ እንኳን
የምንሞክረው ቀርቶ ስንሰማው የሚያንገሸግሸን፣ አንዳንዴም የምንቀላለድበት አይደለምን?
ታዲያ እንዴት ሞክረውት የተሸነፉትን ለመውቀስና ለመኮነን እንፈጥናለን?

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 172
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ምናልባት «ብንማርና አባቶች የሚገባውን ሁሉ ቢያደርጉልን እንደተባለው እንሆን ነበር» እንል


ይሆናል፤ አይሁድም «በአባቶቻችን ዘመንስ በነበርን ኑሮ ነቢያትን ባልገደልን ነበር» ሲሉ ጌታ
ገሠጻቸው እንጅ በዚያ አላመሰገናቸውም፡፡ ማቴ 23፥30 ይህንን ፍርድ ለእግዚአብሔር ትተን
ለራሳችን መዳን ብንሠራ ግን መልካም ይሆናል፤ ፍርዱን ግን ለእርሱ እንተወው «በቀል የእኔ
ነው»፡፡ ይህ ማለት ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን ሲታወኩ ዝም ትላለች ማለት አይደለም፡፡ በቤተ
ክርስቲያን ለምዕመናን መገልገል እንቅፋት የሚሆኑና የሚፈጥሩ አባቶች ከቤተ ክርስቲያን
የሚለዩበት ሥርዓት አለ፡፡ ምዕመናን በአገልግሎት ተዋረድ አማካኝነት ችግራቸውንና
አቤቱታቸውን ለሚመለከተው አካል ማድረሳቸውም ችግር አይደለም፡፡ ችግሩ በየመንገዱና
በየቀልዱ አባቶችን በመስደብና በእነርሱ ላይ ለማላገጥ የውሸት «መንፈሳዊነታችን» ለመግለጥ
ስንጥር ነው፡፡ ከእውነት ለቤተ ክርስቲያን የሚቆረቆር ሰው የአባቶችን ውድቀት እየከፋውና ልቡ
እያዘነበት በግድ ያወራዋል እንጅ፤ የካም ልጅ በኖህ ስካር እንደሳቀው በአባቶቹ «ስካር»
አይዝናናም፤ አይቀልድም፡፡

3. ችግር ያለባቸውንና ቤተ ክርስቲያን የለየቻቸውን አባቶች አለመከተል


እውነተኛ ክርስቲያን ለቤተ ክርስቲያን አንድነትና ሠላም የሚታዘዝ ነው፡፡ አንዳንድ አባቶች ወደ
ቤተ ክርስቲያን በንስሐ ተመልሰው በሰላም መኖር ሲያቅታቸው ምዕመናንን መከፋፈልና
የራሳቸውን «ቡድን» በመሰብሰብ ተከታይ ማፍራት ይጀምራሉ፡፡ በዚህም አንዳንድ የዋሃን
ምዕመናንን ከቤተ ክርስቲያን አንድነት እንዲለዩና እንዲወጡ መክፈል ይሞክራሉ፡፡ በዚህ ጊዜ
ምዕመናን ከሁሉም በላይ ለቤተ ክርስቲያን ልንታዘዝ ይገባል፡፡ ማንም ቢሆን አባትነትን
የሰጠችው ቤተ ክርስቲያን እስከሆነች ድረስ አባትነቱን የመንጠቅ መብት አላት፡፡ ቤተ
ክርስቲያን አባትነቱን የነጠቀችውን ሰው መከተል ግን የቤተ ክርስቲያንን ሉዓላዊ ስልጣን
መናቅ ነው፡፡

9.9 ሊቀ ካህናት አለን ሲል ምን ማለቱ ነው


ዕብ 8፡1‹‹በሰማያት በግርማው ዙፋን ቀኝ የተቀመጠ እንዲህ ያለ ሊቀ ካህናት አለን›፡
፡›በመጀመርያ መያዝ ያለብን በዙፋን መቀመጥ መፍረድ እንጅ ማማለድ አይደለም፡፡ አምላካችን
ኢየሱስ ክርስቶስ የካህናት አለቃ ሊቀ ካህናት ቢባል ካህናትን የሚሾማቸው የሚሽራቸው
መሠረታቸውም እርሱ ነውና የካህናት አለቃ ነው፡፡ እንዲሁም ኢየሱስ ክርስቶስ የካህናት አለቃ
ሲባል እንደ ብሉይ ኪዳን ሊቀ ካህናት ዕለት ዕለት ወደ እግዚአብሔር ለሰዎች ምልጃን
የሚያቀርብ መስዋዕትን የሚሰዋ ሳይሆን ለዓለም ሐጢአት አንድ ጊዜ እራሱ መስዋዕት፣ እራሱ

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 173
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

መስዋዕት አቅራቢ፣ እራሱ መስዋዕት ተቀባይ ሆኖ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ በቀራንዮ አደባባይ


በመስቀል ላይ ደሙ የፈሰሰ ሥጋው የተቆረሰ ነው እንጂ እንደ ብሉኪዳን ካህናት አይደለም፡፡
ዕብ 7፡27 ‹‹እርሱ እንደነዚያ ሊቀ ካህናት/እንደ ብሉይ ኪዳን ካህናት/ አስቀድሞ ሰለራሱ
ሐጢአት በኋላም ስለ ህዝቡ ሐጢአት ዕለት ዕለት መስዋዕት ሊያቀርብ አያስፈልገውም፤
እርሱን ባቀረበ ጊዜ ይህን አንድ ጊዜ ፈጽሞ አድርጓልና››፡፡

ሰለዚህ የዘለዓለም ሊቀ ካህናት የተባለው እርሱ አንድ ጊዜ በፈጸመው ቤዛነት በእርሱ ወደ


እግዚብሔር የሚመጡትን ወንጌልን አምነው ስርዓቱን የሚፈጽሙትን፤ንስሓ ገብተው ሥጋውና
ደሙን ለሚቀበሉ ሁሉ ድህነት ህይወት እየሆናቸው አንድ ጊዜ የፈጸመው የማዳን ሥራ
ለዘለዓለም ሊቀ ካህናት ይባላል፡፡ ለዚህ ነው ዕብ 7፡20-21 ‹‹እነርሱም ያለመሃላ ካህናት
ሆነዋልና፤ እርሱ ግን ጌታ አንተ እንደ መልክአ ጼዴቅ ሹመት ለዘለዓለም ካህን ነህ ብሎ
ማለ››፡፡ ሊቀ ካህኔ ማለት ግን አላዋቂነትም ክህደትም ነው ደግሞም አይባልም አይልምም፡፡
በአጠቃላይ ኢየሱስ ክርስቶስ ሊቀ ካህናት ቢባል እንደ ብሉይ ኪዳን ካህናት ምልጃን የሚያቀርብ
ሳይሆን ሓጢአትን የሚያስተሰርይ (ይቅር የሚል)ነው፡፡ ለዚህ ነው 1ዮሐ2፡2 ‹‹እርሱም
የሓጢአታችን ማስተስሪያ ነው ለኃጢአታችን ብቻ አይደለም ነገር ግን ለዓለሙ ሁሉ እንጂ››
ለመሆኑ የብሉይ ኪዳን ካህናት እራሳቸውን ሰውተዋልን? ታዲያ ያለሰው እራሱን መስዋዕት
ካቀረበው ክርሰቶስ ጋር እንድ ዓይነት አማላጅ ማለት የከፋ ክህደት እነደሆነ ልታውቅ ይገባሃል፡
፡ የኦሪት ካህናት በየዓመቱ ወደ ቅድስት መስዋእትን ይዘው እንደገቡት የሚገባ አይደለም
ካልሆነ ደግሞ አዳኝ እንጅ አማላጅ ወይም ለማኝ አይደለም፡፡ ዕብ9፡25

9.10 ሴቶች ለምን ካህናት አይሆኑም?


በገሃድ እንደሚታወቀው ሥልጣነ ክህነት ለሴቶች ብቻ ሳይሆን ለሁሉም ወንዶች እንኳን ቢሆን
አይሰጥም። በብሉይ ኪዳን ከአሥራ ሁለቱ ነገደ እስራኤል መካከል የክህነት አገግሎት ለሌዊ
ነገድ፤ ከዚያም ለአሮንና ለልጆቹ የተፈቀደ ሲሆን ሌሎቹ ግን መቅደሱን እንዳይዳፈሩ
ተከልክለዋል፡፡ ክህነትን በዐመፅ ለመቀማት ያሰቡት ቆሬ ዳታንና አቤሮን ከነቤተሰቦቻቸውና
ንብረታቸው ጥፋትን መጎናፀፋቸው ይታወሳል። (ዘኁ ፲፮፥፩‐ፍጻሜ፡፡) እግዚአብሔር አምላካችን
ሙሴን የአሥራ ሁለቱንም ነገድ አባቶች በትር ማታ ወደ ቤተመቅደስ አግብቶ ጠዋት
እንዲያወጣ አዘዘው፡፡ በክህነት ያገለግለው ዘንድ የመረጠው በትር ላይ ምልክት
እንደሚያሳየውም አክሎ(ጨምሮ) ነግሮታል። ቀደም ብለን እንደገለጽነውም የአሮን በትር
ለምልማ አብባና አፍርታ በመገኘቷ የእስራኤል ማጉረምረማቸው ለጊዜውም ቢሆን ጸጥ ብሎ

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 174
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ነበር። ያቺ የአሮን በትርም ለማጉረምረማቸው ምስክር ትሆን ዘንድ በምስክሩ ታቦት አጠገብ
እንድትቀመጥ መታዘዙም ይታወቃል፡፡ (ዘኁ ፲፯፥፩‐፲፪፡፡) በዚህ ሁሉ የክህነት አገልግሎት ታሪክ
ውስጥ ሴቶች ሱታፌ እንዳልነበራቸው መረዳት ተገቢ ነው።

በአዲስ ኪዳንም ቢሆን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የክህነትን ምሥጢር በመሠረተ ጊዜ የማሰርና
የመፍታት ሥልጣንን ሰጥቶ ምሥጢራትን እንዲፈጽሙ የፈቀደላቸው ከተከተሉት መካከል
ወንዶች ማለትም ቀደም ብሎ ፲፪ቱ ሐዋርያት፤ ከዚያም ፸፪ቱ አርድዕትና የመሳሰሉት ናቸው።
ለሁሉም አማኝ ማለትም ለወንዶችም ሆነ ለሴቶች አለመፈቀዱን ቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ
ይነግሩናል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ደቀ መዝሙሩ ጢሞቴዎስን ፈጥኖ እጁን በመጫን ካህናትን
እንዳይሾም ማስጠንቀቁ ለዚህ አንድ ማሳያ ነው፡፡ ሁሉም ካህናት መሆን የሚችሉ ቢሆን ኖሮ
እንዲህ ያለ ማስጠንቀቂያና ትምህርት አይሰጥም ነበር (፩ጢሞ ፭፥፳፪፤ ፫፥፩‐፲፬፡፡) ከላይ
እንደገለጽነው የሐዲስ ኪዳን ትምህርት ከብሉይ ኪዳን ክህነት የሚለየው የዘር ተከፍሎ
ስለሌለበት ነው። ውድ አንባቢ ሆይ እዚህ ላይ መረዳት ያለብን እግዚአብሔር ከወንዶች መካከል
እሱ ባወቀ በመረጣቸው ብቻ ሥልጣነ ክህነትን ፈቅዶ ሌሎችን የከለከለበት ምክንያት
የማይታወቅ መሆኑን ነው። እግዚአብሔርን “ይህን ለእገሌ ፈቅደህ ይህንን ለነእገሌ ለምን
ከለከልክ?” ማለት የማይቻል መሆኑ መረሳት የለበትም፡፡ (ኢሳ ፵፥፲፩‐፲፭፡፡) የሥልጣነ ክህነት
አለመፈቀድ ማለት የቅድስና ሕይወትና የመንግሥተ ሰማያት በር መዘጋት ወይም መከልከል
ስላልሆነ በተሰጠውና በተፈቀደው የአገልግሎት መስመር እግዚአብሔርንና ቤተክርስቲያንን
ተግቶ ማገልገል ለቅድስና ሕይወት እንደሚያበቃ ማወቅ ይገባል። ከዚህ ውጪ “ሴቶች ክህነት
ለምን ተከለከሉ?” በማለት እግዚአብሔርን መሞገት ምንም ዓይነት ዕርባና የለውም። (ኢሳ፵፥
፱‐፲፩) ወደ እግዚአብሔር መንግሥት የሚያስገቡ መንገዶች በርካታ መሆናቸውንና እነዚህም
ለሴቶችም ጭምር የተፈቀዱ የአገልግሎት መስመሮች መሆናቸውን መዘንጋት አይገባም።
(፪ቆሮ፲፪፥፩‐ፍጻሜው)

9.11 ምሥጢረ ክህነት የሚያስገኘው ጸጋ


ጳጳሳት አባቶቻችን በሚያደርጉት ጸሎትና አንብሮተ እድ በካህናት በኩል የሚተላለፈው ጸጋ
እግዚአብሔረ በእጅጉ ታላቅ ነው፡፡ በሚታየው አገልግሎት የማይታየው ጸጋ በሦስቱም የክህነት
ደረጃዎች እንደየአቅማቸው ይሰጣል። (፪ጢሞ፩፥፮) በካህኑ ላይ የሚያድርበት ይህ ጸጋ
እግዚአብሔር ሥልጣንና ተግባሩን የሚያስፈጽምለትና ለምእመናን የሚያበረክተውን አገልግሎት
የሚያሠምርለት ነው፡፡ ካህናት እንደ ነቢያት ቃለ እግዚአብሔርን የማስተማር፣ እንደ

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 175
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ካህንነታቸውም ኃጢአትን የማስተሥርይና ምሥጢራትን የመፈጸም እንዲሁም እንደ ንጉሥ


/መሪ/ የክርስቶስን መንጋ የመጠበቅና የማስተዳደር ሥልጣን አላቸው። ለካህናት አባቶቻችን
ክርስቶስን የሚመስሉበት ታላቅ የአገልግሎት ሕይወት የሚያጎናጽፋቸው ነው።

ምክንያቱም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱ እንደ አናጉንስጢስ በቤተ መቅደስ መጻሕፍትን


አንብቧል። (ሉቃ ፬፥፮) እንደ አጻዌ ኀዋኅው የቤተ መቅደስን በሮች ጠብቋል። (ማቴ፳፩፥፲፪)
እንደ ዲያቆን ዝቅ ብሎ ታዟል አገልግሏል። (ዮሐ ፲፫፥፭፱፡፡ ማቴ፳፥፳፱፡፡ ሉቃ፳፪፥፳፮፡፡) እንደ
ሊቀ ዲያቆን አገልጋዮችን አስተባብሯል፤ አሰማርቷል። (ማቴ፲፥፮‐፭፡፡ ማር፲፮፥፲፭፡፡) እንደ ካህን
/ቄስ/ ሥጋ ወደሙን ፈትቶ ቆርቦ አቁርቧል። (ማር፲፬፥፳፪‐፳፮) እንደ ጳጳስ ሕዝቡን ሰብስቦ
አስተምሯል፤ የተበታተኑትን ሰብስቧል። (ማቴ ፱፥፴፮‐፴፰ ዮሐ፰፥፰፩‐፰፯) እንደ ፓትርያርክ
እጁን ጭኖ ሥልጣነ ክህነት ሰጥቷል። (ሉቃ፳፬፥፶ ዮሐ፳፥፳፪‐፳፫ ማቴ፲፰፥፲፰) ክርስቶስን
ከመምሰል የሚበልጥ ምንም ጸጋ ፈጽሞ ስለሌለ ለካህናት የተሰጠ ጸጋ ለአማኞች ሁሉ ከተሰጠ
የልጅነት ጸጋ ይበልጣል፡፡ ከልጅነት ጸጋ በተጨማሪ ለጨለማው ዓለም ብርሃን፣ ለአልጫው
ዓለም ጨው በመሆን የተለያየውን ዓለም በክርስቶስ አንድ እንዲያደርጉ ተመርጠዋልና።

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 176
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

10. ምሥጢረ ቀንዲል


መግቢያ

ይህ ምሥጢር ከጥንት ጀምሮ በቤተክርስቲያን ይፈጸም እንደነበር የታወቀ ነው:: ከላይ


እንዳየነው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያትን፣ ሐዋርያትም ተከታዮቻቸውን፣ አዘዋቸው
ነበርና። ኢጶሊጦስ ዘሮም የተባለው አባት /፫መ/ክ/ዘ/ “ሐዋርያዊ ትውፊት” በተባለው መጽሐፉ
በምሥጢረ ቀንዲል አፈጻጸም ጊዜ ይጸለይ የነበረውን ጸሎት አስፍሮታል:: ይህም
የሚያመለክተው ምሥጢረ ቀንዲል በቤተ ክርስቲያን ይፈጸም የነበረው ከጥንት /ከምሥረታዋ/
ጀምሮ መሆኑን ነው።

በጸሎት ድዉያንን የመፈወስ ተግባር በብሉይ ኪዳን ዘመንም እንደነበር ቅዱሳት መጻሕፍት
ምስክሮቻችን ናቸው። (ዘሌ. ፲፫፥፩‐ፍጻሜው፡፡) በድፍረት የእግዚአብሔር አገልጋይ በሆነው
በወንድሟ በሙሴ ላይ ካህኑ አሮንን በማስተባበር ሐሜት በመሰንዘሯ በለምጽ በሽታ
የተመታችው ማርያም እኅተ ሙሴ የዳነችው በወንድሟ በሊቀ ነቢያት ሙሴ ጸሎት ነበር።
“ሙሴም ወደ እግዚአብሔር እየጮኸ አቤቱ እባክህ አድናት አለው።” /ዘኁ ፲፪፥፩‐፲፮፡፡/
“የተባለው ይህንን ያረጋግጥልናል። የቀንዲል መብራቶችም በደብተራ ኦሪት እንደነበሩ መጽሐፍ
ቅዱስ ይነግረናል። (ዘጸ ፵፥፬፡፡) እነዚህ ሁሉ አማናዊ ለሆነው ምሥጢረ ቀንዲል ምሳሌዎችና
መነሻዎች መሆናቸውን ማስተዋል ይገባል::

ከምሥጢረ ቀንዲል ጋር ፈጽሞ የሚስማማ ሌላ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃም አለ:: ይህን


አስመልክቶ መጽሐፈ ሲራክ ላይ እንዲህ የሚል ተጽፏል። “…ልጄ ሆይ በሽታህን ቸል
አትበል፤ ወደ እግዚአብሔርም ጸልይ፤ እርሱም ይፈውስሃል:: ኃጢአትን ተዋት፣ እጅህን
አቅና፣ ልቡናህንም ከኃጢአት ሁሉ አንጻ፤ መባህን አግባ የመታሰቢያውንም የስንዴ ዱቄት
ስጥ።” (ሲራ. ፴፰፥፩‐፲፮፡፡) ከእግዚአብሔር የምትገኝ ፈውሰ ሥጋን ለማግኘት ንስሐ መግባትና
ለእግዚአብሔር መባዕ ማስገባት እንደሚገባ ልብ ይሏል፡፡

10.1 የምሥጢረ ቀንዲል የቃሉ ትርጉም

ይህ ቃል የላቲን ቋንቋ ነው ትርጉሙም ፍፁም መብራት ማለት ነው፡፡ ከሰባቱ ሚስራት አንዱ
ቀንዲል ነው፡፡ በብሉይ ኪዳን ዘይት የፈውስ ምልክት ነው፡፡ በደዌ ዳኛ በአልጋ ቁራኛ ተይዘው
የሚሰቃዩ ህሙማን ወይም በድንገተኛ አጋጣሚ የመቁሰል አደጋ የደረሰባቸው ቁስለኞች

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 177
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

እየተቀቡ ይፈወሱ ነበር፡፡ ኢሳ 1፡6 ሉቃ 10፡34 ራዕ 3፡18 ማር 6፡13 ይህ ቅብዓተ በሐዲስ


ኪዳን ለሚጠመቁ ከሚደረግ ቅብዐ ሜሮን ጋር ግንኙነት የለውም ራሱን የቻለ ሕሙማነ ሥጋ
ብቻ ሳይሆን ሕሙማነ ነፍስ ኃጥአን የሚቀቡት ፈውስ የሚያገኙበት ነው፡፡ ማር 6፡13 ያዕ 5፡
13-15 ራዕ 1፡17፡፡ ቀንዲል (ቅብዓ ቅዱስ) በመጽሐፍ ቅዱስ ዘይት እተተባለ ይጠራል።
የሚጋጀውም ከንጹህ ወይራ ዘይት ሲሆን ህሙ ማነ ሥጋና ህሙማነ ነፍስ እየተቀቡ
የሚፈወሱበት የተቀደሰ ቅባት ነው። በዚህም የተቀደሰ ቅባት (ዘይት) በብሉይ ኪዳን ዘመን
የነበሩ ሰዎች በሚታመሙ ጊዜ እየተቀቡ ይፈወሱበት ነበር። ኢሳ 1፥6 ሉቃ 10፥34 በሐዲስ
ኪዳንም ሐዋርያት ህሙማነ ሥጋንና ህሙማነ ነፍስን ቅብዓ ቅዱስ እየቀቡ ከነበረባቸው ደዌ
ፈውሰዋቸዋል ። ማር 6 ፥ 13 በቀጣይም ፡ ምዕመናን ፡ በሚታመሙበት ጊዜ ፤ ካህናት
እንዲጸልዩላቸውና ቅብዓ ቅዱስ (ዘይት) ቀብተው እንዲፈውሷቸው ታዝዘዋል ። ያዕ 5 ፥ 14

10.2 የምሥጢረ ቀንዲል አመሠራረት


ካንድል /Candle/ የሚለውን የላቲን ቃል መሠረት ያደረገው “ቀንዲል” ትርጉሙም “መብራት”
ነው። ምሥጢረ ቀንዲል ማለት ካህኑ ለታመሙ ክርስቲያኖች በሚያደርገው ጸሎት፣
በሚሰጠው ቡራኬና በሚቀባውም ዘይት /ቅብዐ ቅዱስ/ አማካኝነት በእግዚአብሔር ቸርነት
የሚገኘውን የሥጋና የነፍስ ድኅነትና ፈውስ የሚያመለክት ምሥጢር ነው። መጽሐፈ ዘይት፣
ጸሎተ ዘይት፣ ቅብዐ ድውያን ማለትም ይሆናል፡፡ ስሙን ከድርጊቱ አግኝቶታል። ጸሎቱ
ሲፈጸም መብራት አብርቶ ነውና፡፡ የምሥጢረ ቀንዲል መሥራች ጌታችንና መድኃኒታችን
ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ይኸውም ለቅዱሳን ሐዋርያቱ ድውያንን እንዲፈውሱ፣ ሙታንን
እንዲያስነሡ፣ ልሙፃንን እንዲያነጹ፣ አጋንንትን እንዲያወጡና ኃጢአትን ሁሉ እንዲያስተሠርዩ
ሥልጣንን በሰጣቸው ጊዜ ነው። “ዐሥራ ሁለቱንም ወደ እርሱ ጠርቶ ሁለት ሁለት አድርጎ
ላካቸው፤ በርኩሳን መናፍስት ላይም ሥልጣን ሰጣቸው፤ ወጥተውም ሁሉ ንስሐ ይገቡ ዘንድ
ሰበኩ፤ብዙ አጋንንትንም አወጡ፤ ብዙ ድውያንንም ዘይት እየቀቡ ፈወሷቸው።” (ማር፮፥፯‐፲፬፡፡)
እንዲል፡፡ ከሰባቱ ምሥጢራተ ቤተክርስቲያን አንዱ ለመሆን የበቃበት ምክንያት በሚታይ
አገልግሎት ከሚታይ ፈውሰ ሥጋ ጋር የማይታይ ፈውሰ ነፍስም ስለሚገኝበት ነው፡፡ ከእናንተ
የታመመ ሰው ቢኖር በቤተ ክርስቲያን ያሉ ቀሳውስትን ይጥራና ይጸልዩለት፤ በጌታችን
በኢየሱስ ክርስቶስ ስም የተጸለየበትንም ዘይት ይቅቡት፤ የሃይማኖት ጸሎትም ድውዩን
ይፈውሰዋል፤ እግዚአብሔርም ያስነሣዋል፤ ኃጢአትንም ሠርቶ እንደሆነ ይሠረይለታል። (ያዕ
፭፥፲፬‐፲፮፡፡) በማለት ቅዱስ ያዕቆብ ምስክርነቱን የሰጠን ለዚህ ነው።

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 178
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

10.3 የምሥጢረ ቀንዲል አፈጻጸም


ቀንዲል:‐ ቅብዓ ቅዱስ /የተለየ የከበረ ዘይት (ቅባት) እየተባለ ይጠራል። ይህም ከወይራ ዛፍ
በጸሎት በመታገዝ በረድኤተ እግዚአብሔር የሚዘጋጅ /የሚወጣ /ዘይት ነው። በተዘጋጀለት
የክብር ዕቃ /ብልቃጥ/ ተደርጎ በከርሰ መንበር ወይም በዕቃ ቤት በክብር ይቀመጣል። የቀንዲሉ
አዘጋጅና ባለቤት ምሥጢሩንም ፈጻሚዋ ቤተ ክርስቲያን ናት፡፡ ከምእመናን ወገን የታመሙ
ሲኖሩ ወደ ቤተክርስቲያን ወደ ካህኑ ይመጣሉ። የማይችሉ የሆኑ እንደሆነ ካህኑን /ካህናቱን/
ወደ ቤታቸው ይጠራሉ፡፡ ካህኑ /የንስሐ አባቱ/ ሕሙሙን ምእመን በማጽናናት ኃጢአቱን
እንዲናዘዝ/ ንስሐ እንዲገባ/ ያደርገዋል:: በመቀጠልም ባቅሙ የሚችለውን ቀኖና እንዲፈጽም
ያዘዋል:: ከዚያም ካህኑ /የንስሐ አባቱ/ ከሌሎች ካህናት ጋር ሆኖ ምሥጢሩን ለታማሚው
ለመፈጸም ይዘጋጃል፡፡ ከዚያም ቀንዲሉን /መብራቱን/ አብርቶ መጽሐፈ ቀንዲልን በመጠቀም
የታዘዘውን ጸሎት ይጸልዩለታል። በጸሎቱ ፍጻሜም የሕመምተኛውን ሕዋሳት በተለይ
የታመመውን ክፍል በተጸለየበት ቅብዐ ቅዱስ በመስቀል አምሳል /ምልክት/ ይቀቡታል::
በመጨረሻም ከማእሰረ ኃጢአት የሚፈታበትን ሥርዓት /ኑዛዜ/ ይፈጽሙለታል። ይህም
ለታመመው ምእመን ፈውሰ ሥጋ፣ ፈውሰ ነፍስን ያድለዋል።

ሥርዓተ ቀንዲልን የሚፈጽሙት ሰባት ኤጲስ ቆጶሳት ወይም ቀሳውስት ሆነው ነው። እነዚህ
ሰባት መሆናቸው ሰባት ቁጥር በዕብራውያን ፍጹም ቁጥር እንደመሆኑ በምሥጢረ ቀንዲል
ፍጹም ሥርየትና ፈውስ መገኘቱን ለማጠየቅ ነው። እነሱም /ካህናቱ/ ቅዱስ ዮሐንስ በራእዩ
ያያቸው የሰባቱ የወርቅ መቅረዞችና መብራቶች ምሳሌ ናቸው። (ራእ፩፥፳፡፡) ከላይ እንደገለጽነው
ኃጢአቱን ለተናዘዘው ምእመን በቀረበው ንጹሕ ዘይት ላይ የታዘዘው ጸሎት ይደረሳል። ሰባቱም
ካህናት በየተራ በታመመው ራስ ላይ የታዘዙትን የወንጌል ክፍላት ያነባሉ ወንጌል ከተነበበ
በኋላም ሰባቱም እጃቸውን በሕመምተኛው ላይ ጭነው የታዘዙትን ጸሎታት ይጸልዩለታል፡፡

በመጨረሻም አስቀድመን እንደተናገርነው በሰባት እንጨቶች ጫፍ ላይ ጥጥ በመጠምጠም ተራ


በተራ በተጸለየበት ቅብዐ ዘይት እየነከሩ አምስቱን የስሜት ሕዋሳት /ዓይኑን፣ ጆሮውን፣
አፍንጫውን፣ አፉንና እጁን በመስቀል ምልክት ይቀቡታል፡፡ የዚህም ምክንያት በዓይኑ አይቶ፣
በጆሮው ሰምቶ፣ ባፍንጫው አሽትቶ፣ በአፉ ተናግሮና በእጁ ዳሶ ለሠራው ኃጢአት ሥርየት
እንዲሆነው ነው። አእምሮ የሚገኝበት የአምስቱ የስሜት ሕዋሳት ማዕከልና የማስተዋል
/የማሰብ/ ኃይል የሚገኝበት ክፍል ነውና፤ በዋናነት ግንባርም ይቀባል፡፡ የልብ ማረፊያ ነውና
ደረቱም ይቀባል፡፡ ሰውነቱን ሁሉ ሊበክል የሚችል የርኩሰት ቁስል /ቁስለ ነፍስ/ የሚመነጭ

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 179
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ከሱ ነውና ፈጽሞ እንዲፈወስ እነዚህ ሁሉ ይቀባሉ፡፡ ከቀሳውስት በታች ያሉ ዲያቆናት ግን


ለካህናት ከመታዘዝና ከመራዳት በስተቀር ይህንን ምሥጢር መፈጸም እንደማይችሉ የታወቀ
ነው። ስለዚህ የሚመለከታቸው የቤ/ክርስቲያኒቱ አባቶች ከምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን አንዱ
ሆኖ ስለሚቆጠረው ምሥጢረ ቀንዲል ተፈጻሚነትና ቀጣይነት አንድ መላ ማለት (መፍትሔ
መፈለግ) አለባቸው፡፡ በጽሑፍና በቃል ከመቆጠር ባለፈ እንደ ስድስቱ ምሥጢራተ
ቤተክርስቲያን በተግባር ተፈጽሞ እንዲታይ ማድረግ ይገባል:: ምእመናንም ይህን ምሥጢርና
አፈጻጸሙን በማወቅ ለተግባራዊነቱ የድርሻቸውን ማበርከት አለባቸው።

10.4 በየብልቃጡ እየተሞላ የሚሸጠው “ዘይት” ምስጢረ ቀንዲልን ይተካልን?


ይህ ምሥጢር በአሁኑ ጊዜ በአብዛኛው አብያተ ክርስቲያናት እየተፈጸመ አይደለም::
አስተምህሮው እንዲህ ነው፣ እንዲህ ይደረጋል፣ ከማለት ውጪ ሲተገበር አይታይም::
በምትኩም ከአስተምህሮአችን ውጪ የሆኑ ተግባራት ሲፈጸሙ ይታያል:: “ከኢየሩሳሌም
የመጣ፣ ባህታዊ እገሌ የጸለዩበት፣ አጥማቂ እገሌ የባረኩት፣…ቅብዓ ቅዱስ ነው፤ ወዘተ”
እየተባለ በየስፍራው የሚቸበቸብ ዘይት ማየት የተለመደ ሆኗል:: ይህንንም እንዳንድ ግንዛቤ
የሌላቸው ምእመናን እየገዙ “ቅብዓ ቅዱስ” በማለት በራሳቸው ጊዜ በቤታቸው እያኖሩ የሚቀቡ
በዚህም ምክንያት ከፈውስ ይልቅ ተጨማሪ ደዌ የሚሸከሙ ሆነዋል፡፡ እነዚህ ሰዎች
ከትክክለኛው መስመር ያፈነገጡ በመሆናቸው በነፍሳቸው ከበረከት ይልቅ መርገምን
ተከናንበው ድርብ ጉዳት የሚጎዱ ከመሆናቸውም በላይ ከክርስቲያን ትምህርትም የራቁና የወጡ
ሆነዋል:: ይህ ግን በእውነቱ ከሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ውጪ የሆነ ጸያፍ ተግባር መሆኑን
በመረዳት የሳቱ ሰዎች ወደ እውነተኛው የቤተ ክርስቲያን ትምህርትና ሥርዓት መመለስ
ይኖርባቸዋል። በምንም አይነት ሁኔታ በየቦታው በቤተ ክርስቲያን ግቢም እንኳን ቢሆን
የሚሸጡ ዘይቶች ይህን ቅዱስ ምሥጢር መተካት አይችሉም፡፡ ደጋግመን እንደተናገርነው
ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ፈጽሞ በገንዘብ የሚሸጡና የሚገዙ አደሉም፡፡

10.5 ምሥጢረ ቀንዲል የሚያስገኘው ጸጋ

ቅብዓ ቅዱስ በማንኛውም ዓይነት በሽታ በተለይ በቁስል ለተመቱና ጆሯቸው ለታመመባቸው
ሰዎች እንዲሁም ደዌ ነፍስ ላደረባቸውና ረድኤተ እግዚአብሔር አጋዥ እንዲሆናቸው ፣
ከኃጢአታቸውም እንዲነጹ የፈለጉ ምዕመናን ካህኑ ጸሎተ ቀንዲል ጸልዮ በሚቀባቸው ጊዜ
ከነበረባቸው የሥጋና በሽታና የነፍስ ደዌ (ኃጢአት) ይፈወሳሉ። ነገር ግን በሚቀቡበት ጊዜ

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 180
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

እግዚአብሔር በዚህ የተቀደሰ (ዘይት) ቅብዓ ቅዱስ ላይ አድሮ ካደረባቸው ደዌ


እንደሚያድናቸው በፍጹም ልባቸው ማመን አለባቸው። ቅብዓ ቅዱስ የሚቀቡ አምነው
የተጠመቁ ክርስቲያኖች ሲሆኑ ከመቀበቀታቸው በፊት ንስሐ መግባትና ራሳቸውን መቀደስ
አለባቸው። ሥርዓቱ የሚፈጸመው በካህናት ሲሆን በመጀመሪያ ጸሎቱ ቤተ ክርስቲያን ወይም
ታማሚው በተኛበት ቦታ ዙሪያ ያም ባይሆን በካህኑ ጸሎት ቤት ከተጸለየበት በኋላ የታመመው
(የቆሰለው) ቦታ ላይ ይቀባል። እንደሌሎቹ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ሁሉ በሚታይ
አገልግሎት፣ አገልጋይና መገልገያ ንዋያተ ቅዱሳት የማይታየውን ጸጋ እግዚአብሔር ያስገኛል።
እነዚህንም ጸጋች በሁለት ከፍለን እናያቸዋለን። ምሥጢሩ የሚፈጸምላቸው ህሙማን የሥጋና
የነፍስ ደዌ ያላባቸው በመሆናቸው ፈውሱም የሥጋና የነፍስ ተብሎ በሁለት ይከፈላል፡፡

ሀ. ፈውሰ ሥጋ ፦

ሰው ማለት ከአራቱ ባሕርያተ ሥጋና ከሦስቱ ባሕርያተ ነፍስ የተፈጠረ እንደመሆኑ በዚህ
ዓለም ሲኖር በሥጋውና በነፍሱ የሚቀበላቸው ሕማማት አሉ። ያንዱ መታመም ሌላኛውንም
ይጎዳል፤ ማለትም የሥጋ መታመም ነፍስን፣ የነፍስም መታመም ሥጋን ስለሚያውከው
ቤተክርስቲያን መንፈሳዊውን ሕክምና በተናጠል አትፈጽምም፡፡ አንዱ ተፈውሶ አንዱ ከታመመ
ከላይ እንደገለጽነው የተፈወሰውም ታማሚ መሆኑ አይቀርምና ምእመናን ይህን ድርብ ሕክምና
ታክመው ፈውሰ ሥጋ፣ ፈውሰ ነፍስ እንዲያገኙ የምታደርግበት መንገድ ምሥጢረ ቀንዲል
ይባላል።

ከላይ በአፈጻጸሙ እንደገለጽነው ምሥጢረ ቀንዲል በታዘዘው መሠረት የተፈጸመለት ታማሚ


ምእመን ከሕማመ ሥጋው ይፈወሳል። ሁሉንም ልጆቹን እንዳይታመሙ የሚጠብቃቸው፣
በሆነ ምክንያት በታመሙም ጊዜ የሚፈውሳቸው እግዚአብሔር ነው። “አንተ የአምላክህን
የእግዚአብሔርን ቃል አጥብቀህ ብትሰማ፣ በፊትህም መልካምን ብታደርግ፣ ትእዛዙንም
ብታደምጥ፣ ሥርዓቱንም ሁሉ ብትጠብቅ፣ በግብፃዊያን ላይ ያመጣሁትን በሽታ
አላደርስብህም፤ እኔ ፈዋሽህ እግዚአብሔር ነኝ::” (ዘጸ፲፭፥፳፮፡፡) እንደተባለ:: ሰው ሆኖ በዚህ
ዓለም ላይ የሚመላለስ ክርስቲያን ሁሉ ሥጋዊ ጤንነቱ በበሽታ በተናጋ ጊዜ ድውያንን ሁሉ
ይፈውሱ ዘንድ ሥልጣን ወደ ተሰጣቸው ካህናት ቀርቦ መታከም ይኖርበታል:: “እኔ እስከ ዓለም
ፍጻሜ በዘመኑ ሁሉ ከእናንተ ጋር እኖራለሁ::” (ማቴ. ፳፰፥፳፡፡) ብሏቸዋልና። መድኃኔዓለም
ክርስቶስ በሰጣቸው ሥልጣን መሠረት ሕመምተኛውን ይፈውሰዋል:: በተለይም በክርስቲያናዊ

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 181
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ሕይወቱ ጠንክሮ እግዚአብሔርን ደስ ለማሰኘት የሚተጋ ሰው ካለ ደዌው እንዳይጸናበትና


እንዳያስመርረው እግዚአብሔር ከሱ ጋር ሆኖ ያቀልለታል:: አስፈላጊ በሆነ ሰዓትና ቦታም
በምሥጢረ ቀንዲል ይፈውሰዋል:: /መዝ ፵፥፩‐፭፡፡/ ይህ ምሥጢር በፍጹም እምነት
“ይደረግልኛል!” ብሎ በማመን ከተፈጸመ ሕሙማንን ከደዌ ዳኛ ከአልጋ ቁራኛ ይገላግላቸዋል።

ለ. ፈውሰ ነፍስ

በምሥጢረ ቀንዲል የሚገኝ ሁለተኛው ጸጋ ፈውሰ ነፍስ ነው:: የሚታመመው ሥጋ ብቻ


ስላልሆነ /ነፍስም ስለምትታመም/ እንደ ሥጋ ሁሉ እሷም ፈውስ ያስፈልጋታል። ነፍስን
የሚያቆስላትና የሚያሳምማት ደግሞ ኀጢአት ነው። ከላይ እንደገለጽነው አንዱ አካል ተፈውሶ
ሌላኛው አካል በሽተኛ ከሆነ ሰውየው ጤነኛ ሆነ ማለት አይቻልምና፤ ሁለቱንም እንደ
ሕመማቸው ዓይነትና ጽናት ተመጣጣኝ የሆነ ሕክምና ሰጥቶ መፈወስ ይገባል። ስንዱዋ
ቤተክርስቲያን የአካለ ሥጋና የአካለ ነፍስ ውሑድ የሆነውን /ሰውን/ በጠቀስነው መሠረት
እያከመች ኖራለች፤ ትኖራለችም፡፡ መንፈሳዊ ሐኪሞቿም ካህናት ናቸው፡፡ ሥልጣናቸው
የሁለቱንም አካላት (የሥጋንና የነፍስን) ሕመም ለማከም የሚያስችል ሀይል ያለው ነውና::

ሕመምተኛው ሰው የእግዚአብሔርን ቸርነት አምኖ ኀጢአቱን በተናዘዘ ጊዜ ኃጢአቱ መክሰም


ትጀምራለች። ካህኑ በሚሰጠው መንፈሳዊ ትምህርት መሠረት ከኃጢአት ጋር ያለውን ሰንሰለት
ቆርጦ በጣለና እግዚአብሔርን ኃጢአት እየሠራ ላለማሳዘን በወሰነ ጊዜ ደግሞ በምሥጢረ ንስሐ
እንደገለጽነው ከማእሰረ ኃጢአት የተፈታ ይሆናል:: የንስሐው፣ የኑዛዜዉና የቀኖናው
አስፈላጊነትም ለፈውስ ነፍስ ነው:: እግዚአብሔር አምላካችን የነፍሳችንን ድኅነትና ፈውስ
ከሥጋችን ድኅነትና ፈውስ የበለጠ ስለሚፈልግ ለፈውሰ ነፍስ ከፍተኛ ትኩረት እንድንሰጥ
ይፈልጋል። ቅዱስ ጴጥሮስም “ክርስቶስ ስለ እኛ በሥጋው ከተሰቀለ እናንተም ይህቺን ዐሳብ
ጋሻ አድርጋችሁ ኑሩ፤ በሥጋው መከራ የተቀበለ ከኃጢአት ድኖአልና።” (፩ጴጥ፬፥፩፡፡) በማለት
የተናገረው ከያዝነው ፍሬ አሳብ ጋር የተጣጣመ መልዕክት ያለው ነው። ይህም ምሥጢር
የሚስማማው የሥጋን ሕመምና መከራ እንደጸጋ ቆጥረውና ተቀብለው ለሚታገሡት ነው።
የምሥጢረ ቀንዲልም ዋናው ትኩረት የሥጋ ፈውስ መስጠት አለመስጠት ላይ ሳይሆን
ሕመምተኛው ፈውሰ ሥጋ እንኳን ባያገኝ በሽታውን በአኮቴት /በትዕግሥትና በምስጋና/
ተቀብሎ ከነፍስ ሕማምና ከሥጋ ሞት እንዲድን ማድረግ ላይ ነው።

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 182
የቤተክርስቲያን ምስጢራትና ሥርዓት የኮርስ ሃንዳውት 2011 ዓ.ም

ማጠቃላያ (ምክረ አበው)


ወገኖቼ መንፈሳዊ ትውፊታችንን፣ ታሪካችንና ሃይማኖታችንን አጥብቀን እንያዝ። ዛሬ
በአውሮፓና በአሜሪካ ሰለጠንን፣ ወንጌል በራልን ብለው ሲመጻደቁ የነበሩና መንፈሳዊ
ትውፊታቸውን አራግፈው የጣሉ የፕሮቴስታንት ቤተ እምነቶች የአምልኮ መቅደሶቻቸውን
ዘግተው ወደ ዓለማዊነትና ወደ ለየለት የክህደት ዓለም ውስጥ ገብተዋል። ቤተ መቅደሶቻቸውን
ቡና ቤት፣ ልብስ መሸጫ ቡቲክና፣ የመኖሪያ አፓርትመንት አድርገውታል። ዛሬ ሃይማኖት
የለሽ ትውልድ ፈጥረው ወጣቶቻቸው የሰይጣን እምነት ተከታዮች፣ ሰዶማውያን፣ የአደንዛዥ
ዕፅ ሱሰኞች፣ ዘወትር የጌታ ስቅለት የሚታሰብበትን ዕለተ አርብ በስካርና በጭፈራ የሚያነጉ
የርኩሰት ተባባሪዎች ሆነዋል። በአጭሩ ታቦትን ሲቃወሙ የነበሩ የፕሮቴስታንት
ፓስተሮቻቸውና ተከታዮቻቸው በአብዛኛው ሃይማኖት የለሾች ከሃድያን /ATHEIST/ ሆነው
ቀርተዋል። ወገኖቼ ኢትዮጵያውያን እባካችሁ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን
አጥባቃችሁ ያዙ ትውልዱን ከክርስቶስ ጋር በፍቅር አጣብቃ፣ በምግባርና በሃይማኖት ይዛ
የቆየች ወደፊትም የምትኖር ብቸኛዋ የክርስቶስ ሙሽራ ይህችው እናት ቤተክርስቲያን ነች።
ዛሬ በሐሰተኛ ነቢይትና በአጭበርባሪ ፓስተሮች በስሜት የሚነዳው ሕዝብ ለጊዜው ነው
ከተወሰኑ ዓመታት በኋላ ሁሉ ነገራቸው እያስጠላው፣ ሌብነታቸው እያንገፈገፈው ሲመጣ
አንቅሮ ይተፋቸዋል፤ የሚያሳዝነው ግን ከቤተክርስቲያንም ወጥቶ ኦርቶዶክስን እየረገመ ስለኖረ
ተመልሶ መምጣት ስለሚከብደው ጨፋሪና ዘማዊ፣ በፍልስፍና ልቡ የተጠለፋ ከሀዲ ትውልድ
ሆኖ ይቀራል። እባካችሁ ከቤተክርስቲያን ኮብልላችሁ የወጣችሁ ኦርቶዶክሳውያን አገልጋዮችና
ምዕመናን ወደ እናት ቤተክርስቲያናችሁ ተመለሱ። የሚያብረቀርቅ ሁሉ ወርቅ አይደለም።
ኢየሱስ፣ ኢየሱስ ያለ ሁሉ ኢየሱስ የሚያውቀው አይደለም ከቶውን አላውቃችሁም የሚባሉ
በጣም ብዙ ናቸው። ወደ እናት ቤተ ክርስቲያን ላለመመለስ የካህናቱን ድክመትና፣ የመሪዎቹን
ስንፍና አትመልከቱ የተሰቀለውን ክርስቶስ ብቻ ተመልከቱ። ቤተክርስቲያኒቱ ላይ ጣት
ከመቀሰርና ከማጥላላት ይልቅ ዶግማዋ ምን እንደሆነ በጥልቀት መርምሩ፣ በነገረ መለኮት
ዙሪያ እና በምሥጢራት ያላት ጥልቅ አስተምህሮ ምን እንደሆነ ሊቃውንቱን ቀርባችሁ ጠይቁ።
የዶክትሪን መጻሕፍቷን መርምሩ። በጥራዝ ነጠቅ ዕውቀት ብቻ ቤታክርስቲያኒቱ ላይ ዘለፋ
አትናገሩ። የእውቀት ደረጃዬ ምን ያህል ነው ብላችሁ በመጀመሪያ ራሳችሁን ፈትሹ። ምን
ያህል መጻሕፍቶቿን አንብቢያለው ብላችሁ አዕምሯችሁን መዝኑ፡፡ የረቀቀውን አጉልቶ፣
የራቀውን አቅርቦ ምሥጢርን የሚገልጽ የምሥጢራት ሁሉ መሠረት ለሆነው ለአምላካችን

ለቅዱስ እግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፡፡ ይቆየን………….

በዲያቆን አሸናፊ ወልደኢየሱስ (በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ በዋናው ግቢ ግቢ ጉባኤ ትምህርት ክፍል)


ገጽ | 183

You might also like