Professional Documents
Culture Documents
ስድስተኛ ክፍል
Email
office@eotc-gssu.org
YouTube
https://www.youtube.com/channel/
UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg
Facebook
http://facebook.com/EOTC.GSSU
Telegram
https://t.me/EOTCNSSU
Website
https://eotc-gssu.org/a/
Twitter
https://twitter.com/tibeb_felege
Copyright ©
፳፲፭
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት
ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም
ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት
ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ
አስኪያጅ እና የባህርዳር ሁገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ምዕራፍ ሁለት
ቅዱሳን እነማን ናቸው?
፪.፩. ቅዱሳን ሰዎች.............................................................. ፲፮
፪.፪. ቅዱሳን መላእክት........................................................ ፲፱
፪.፫. ቅዱሳት መጻሕፍት..................................................... ፳
፪.፬. ቅዱሳት ሥዕላት ......................................................... ፳፩
፪.፭. ንዋያተ ቅድሳት.......................................................... ፳፪
፪.፮. ቅዱሳት መካናት ........................................................ ፳፫
የምዕራፉ ማጠቃለያ
፩
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
ምዕራፍ ሦስት
መዓርጋተ ቅዱሳን.................................................... ፳፰
፫.፩ ንጽሐ ሥጋ....................................................... ፴
፫.፪ ንጽሐ ነፍስ........................................................ ፴፬
፫.፫ ንጽሐ ልቡና...................................................... ፴፮
ምዕራፍ አራት
የቅዱሳን ምልጃ
፬.፩. ምልጃ ምንድን ነው?................................................. ፵፪
፬.፪. ምልጃ በአጸደ ሥጋ.................................................... ፵፬
፬.፪.፩. የቅዱሳን ምልጃ በዘመነ ብሉይ ........................ ፵፬
፬.፪.፪. የቅዱሳን ጻድቃን ምልጃ በሐዲስ ኪዳን............ ፵፱
፬.፫ አማላጅነት በዘመነ ሐዋርያት...................................... ፶
፬.፬. ቅዱሳን አማላጅነት በአጸደ ነፍስ (ከሞት በኋላ)........... ፶፪
ምዕራፍ አምስት
፪
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
ምዕራፍ አንድ
የነገረ ቅዱሳን ትምህርት መሠረታዊያን
ዓላማ
ተማሪዎች ይህንን ምዕራፍ ሲያጠናቅቁ
የመክፈቻ ጥያቄዎች
፫
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
፩.፩ መግቢያ
፩.፪ ትርጓሜ
“ነገረ ቅዱሳን” የሚለው ቃል ከሁለት ቃላት የተገኘ ጥምር ቃል ሲሆን
ትርጉሙም፦
. “ነገር” የሚለው ቃል በቤተክርስቲያን አንድን የመጽሐፍ ቅዱስ ወይም
የቤተክርስቲያን የትምህርት ዘርፍ ወይም አይነት አጉልቶ ለማሳየት
የሚውል ቃል ነው። ለምሳሌ፦ ነገረ መለኮት፣ ለገረ ማርያም፣ ነገረ
ቤተክርስቲያን. . .
• “ቅዱስ” የሚለው ቃል “ቀደሰ” ከሚለው የግዕዝ ቃል የተገኘነው።
ትርጉሙም ለየ፣አከበረ፣ አመሰገነ፣ አገነነ፣ መረጠ፣ አጠራ፣ አነጻ፣ ባረከ
ወዘተ … ማለት ነው፡፡በመሆኑም ቅዱስ ስንል የተለየ ፣ የተከበረ ፣
የተመረጠ ፣ የተመሰገነ ፣ የገነነ ፣ የጠራ የነጻ ማለት ነው።
. ስለዚህ ነገረ ቅዱሳን የተቀደሰ ሕይወት ስለኖሩ አባቶች እና እናቶች
ከልደታቸው እስከ ዕረፍታቸው ሕይወታቸውን፣ እንዲሁም ሌሎችም
ቅዱሳን ብለን ስለምንጠራቸው መካናት እና ንዋያት የምናጠናበትና
የምንማርበት የትምህርት ክፍል ነው።
፲፩
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
ከዚህ በተጨማሪ ፦
• ሰይጣን የብርሃን መልአክ መስሎ እንዳያስተን እንጠበቃለን።
• ቤተክርስቲያን መታሰቢያቸውን ለይታ ለመፈጸምና ለእኛ ለማሳወቅ
ያስችላታል።
• ምዕመናን በክርስቶስ የወይን ግንድነት ላይ ቅርንጫፍ በመሆን
ብዙ ፍሬ ያፈሩ የሃይማኖት አባቶቻቸውን አውቀው ከአታላዮች፣
ከአስመሳዮች፣ከሐሳውያን እንድንጠበቅ ይረዱናል፡፡
፲፫
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
፲፬
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
ምዕራፍ ሁለት
ዓላማ
ተማሪዎች ይህንን ምዕራፍ ሲያጠናቅቁ
የመክፈቻ ጥያቄዎች
፲፭
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
፲፰
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
የምድራውያን አንድነት የሆነችውን ቤተክርስቲያን በሃይማኖት
በመምራት መንጋውን ከተኩላ በመጠበቅ የክርስቶስን ትዕዛዝ የፈጸሙ
ቅዱሳን ናቸው፡፡
፪.፭.ንዋያተ ቅድሳት
፳፬
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
የማጠቃለያ ጥያቄዎች
ክፍለ አንድ - እውነት ወይም ሐሰት በማለት መልሱ።
፩ ቅዱሳን ተብለው የሚጠሩት ሰዎች ብቻ ናቸው።
፪ እግዚአብሔር ቅድስናን ለሁሉም ይሰጣል።
፫ ቅዱሳን መላእክት መልእክት ከእግዚአብሔር ወደ ሰው እንጂ
ከሰው ወደ እግዚአብሔር አይወስዱም።
፳፮
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
ምዕራፍ ሦስት
መዓርጋተ ቅዱሳን
ዓላማ
ተማሪዎች ይህንን ምዕራፍ ሲያጠናቅቁ
• ቅድስና በአንድ ግዜ የሚገኝ እና የሚደረስበት ሳይሆን የዕድሜ ዘመንን
ተጋድሎ እንደሚጠይቅ ይረዳሉ።
• ሦስቱን ዋና ዋና የቅድስና መዓርጋት ይዘረዝራሉ።
• አሥሩን መዓርገ ቅዱሳን ይዘረዝራሉ።
• ቅዱሳንን አብነት አድርገው ራሳቸውን ለቅድስና ሕይወት ያለማምዳሉ።
የመክፈቻ ጥያቄዎች
፳፯
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
መዓርጋተ ቅዱሳን
፫.፪ ንጽሐ ሥጋ
ይህ ደረጃ ወጣንያን በባሕርዩ ፍጹም ከሆነው እግዚአብሔር ፍጹም
ጸጋን ተቀብለው ለመክበር ቁርጥ ተጋድሎ የሚጀምሩበት ሕይወት
ነው። በዚህም ጊዜ ጠላት የተባለ ሰይጣን የተጋድሎ ሕይወታቸውን
የሚያቀጭጭ ፈተና ያመጣባቸዋል። እነርሱ ግን በፍጹም ተጋድሎ
በእግዚአብሔር ጸጋ ከአንዱ መዓርግ ወደ ሌላ መዓርግ ይሸጋገራሉ።
የንጽሐ ሥጋ መዓርጋት ሦስት ናቸው። እነሱም ጽማዌ፣ ልባዌ፣
ጣዕመ ዝማሬ ሲሆኑ፤እነዚህ መዓርጋት ላይ የደረሱ ቅዱሳን ሠላሳ ፍሬ
በሚያፈራው ዘር የተመሰሉት ናቸው፡፡
ሀ. ጽማዌ
ጽማዌ ማለት ዝምታ ጸጥታ ማለት ነው፡፡ቅዱሳን ይሄን የሚያደርጉት
በመናገር በማውራት ብዙ ኃጢአት፣ ብዙ ሰው ማስቀየም እና ማቁሰል
ስላለ፣ ራሳቸው አንደበታቸውን በመግዛት ከእግዚአብሔር እና ቅዱሳን
መላእክት እንዲሁም ቅዱሳን ሰዎች ጋር ብቻ በልቡናቸው የሚነጋገሩበት
ሕይወት ነው። አባ አርሳኔዎስ የሚባሉ አባት “ብዙ በተናገርኩ ቁጥር
እጸጸታለሁ፣ ዝም ስል ግን ጸጽቶኝ አያዉቅም” ብለዋል። ሰው በተናገረ
፴
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
ቁጥር አስቦበት ሰውን ለማስቀየምም ይሁን ሳያስበው ለመልካም
የተናገረው ሰዎችን ያስከፋል። ሰውን ተናግሮ ማስከፋት ደግሞ ኃጢአት
ነው። ዝም ማለት ግን ምንም አያስጸጽትም።
ቅዱስ ያዕቆብም በመልእክቱ እንዲህ ይላል። “አንደበት እሳት ነው።
አንደበት በብልቶቻችን መካከል ዓመጸኛ ዓለም ሆኗል፣ ሥጋን ሁሉ
ያሳድፋልና፣ የፍጥረትንም ሁሉ ሩጫ ያቃጥላል፣ በገሃነምም ይቃጠላል።”
(ያዕ ፫፥፮)
ለ. ልባዌ
ልባዌ ማለት ልብ ማድረግ፣ ማስተዋል፣ ዕውቀት፣ ማለት ነው፡፡
ከዚህ መዓርግ ላይ የደረሱ ቅዱሳን የሕሊና ጾር በተነሣባቸው ጊዜ
(ክፋ ምኞት ሲመጣባቸው) መስቀል ተክለው ይሰግዳሉ፡፡ሥጋዊ ነገርን
በማሰብ ጸጋቸው እንዳይነሣ ሕሊናቸው ነገረ መስቀልን ከማሰብ
እንዲለይ አይፈልጉም፡፡ በበአታቸው ጸንተው ቢኖሩም የሚፈልጉትን
ነገር ሁሉ እግዚአብሔር ፈጥኖ ይሰጣቸዋል፡፡ እንዲሁም ነፍስ ከሥጋ
ተለይታ ወዴት እንደምትሔድ ያያሉ፤መላእክት ሲወጡና ሲወርዱ፣
ተልእኳቸውንና እነማን እንደሆኑም ጭምር ስማቸውን ለይተው ያውቃሉ፡
፡አጋንንትንም የማየትና ለምን እንደተላኩ የማወቅ ጸጋ ይሰጣቸዋል፡፡
እግዚአብሔር ከሚሰውራቸው አንዳንድ ነገሮች በስተቀር ከጠፈር በታች
ያለውን ማናቸውንም ነገር ሳይጠይቁ ይረዳሉ፡፡ /፪ኛቆሮ ፲፪፥፩-፯/፡፡
፴፪
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
ሐ. ጣዕመ ዝማሬ
አባቶች እዚህ ማዕረግ ላይ ሲደርሱ የሚጸልዩትን ጸሎት አንድ በአንድ
ምስጢሩን ያውቃሉ፡፡የሚጸልዩትን ጸሎት ምሥጢሩን ተረድተው
በልቡናቸው እያመላለሱ ያለማቋረጥ እግዚአብሔርን ያመሰግናሉ፣
ይጸልያሉ። እያንዳንዷን ቃል ጣዕሟን አይጠግቧትም። የአቡነ ዘበሰማያት
ምስጢር አላልቅ ብሏቸው ለ፴ ዓመት የሚቆዩ አሉ፡፡
ሀ. አንብዕ
እዚህ መዓርግ ላይ የደረሱ ቅዱሳን የዕንባ ሀብት (አንብዐ ንስሐ) ይሰጣቸዋል፡
፡ ሳያቋርጡ ያነባሉ፤ ዐይናቸው ግን አይጠፋም፤ ዕንባቸው ሌሊትና ቀን
አያቋርጥም፤ አንብዐ ንስሐ መዓርግ ላይ የሚደርሱ ቅዱሳን አብዛኛውን
ጊዜ የሚጸልዩት በሕሊና ነው። ይኽም በሕሊናቸው የሚመላለስ ረቂቅ
ጸጋ ስለኾነ ኃጢአትን ያስወግድላቸዋል፡፡ እርጥብ እንጨትን በእሳት ላይ
ቢጥሉት እየነደደ ውኃ እንደሚወጣው ሁሉ በሀብተ አንብዕ ደረጃ ላይ
ያሉ ቅዱሳንም ሞተ ወልደ እግዚአብሔርን፣ ግፍዐ ሰማዕታትትን፣ምረረ
ገሃነመ እሳትን እያሰቡ በልቡናቸው ከሚቀጣጠለው መንፈሳዊ ጸጋ እሳት
የተነሣ የጸጋን ዕንባ ያነባሉ (ያፈሳሉ)፡፡ ማቴ ፭፥፬፡፡
ለ. ኩነኔ
ኩነኔ ማለት አገዛዝ፣ ግዛት ማለት ነው፡፡ እዚህ መዓርግ ላይ የደረሱ
ቅዱሳን የነፍስ ፈቃዳቸው የሥጋ ፈቃዳቸውን ይገዛል፤ ያሸንፋል፡፡ ገላ
፭፥፲፮ በሰው ሕይወት የሥጋና የነፍስ ፈቃዳት ሁልጊዜ ይቃረናሉ፡፡ ገላ
፴፬
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
፭፥፲፯ የነፍስ ፈቃድ እያሸነፈ ሔዶ ሥጋን በቁጥጥር ሥር የሚያውልበት፣
ነፍስ የመንፈስን ፈቃድ ብቻ መፈጸም የምትጀምርበት መዓርግ ኩነኔ
ነው፡፡የሥጋቸው ፈቃድ በፈቃደ ነፍሳቸው ላይ ምንም ዓይነት ተጽዕኖ
አይኖረውም፡፡በሐሳብም ከመበደል ይጠበቃሉ፡፡ የሲዖልንና የገሃነመ
እሳትን ኩነኔ እያሰቡ ያዝናሉ፡፡
ሐ. ፍቅር
እዚህ መዓርግ ላይ የሚደርሱ አባቶች ሁሉን የመውደድ ሀብት
ይሰጣቸዋል፡፡እነርሱንም ሁሉ ይወዳቸዋል፡፡ በእነዚህ አባቶች ዘንድ ይህ
ጌታ ነው፣ ይህ ባሪያ ነው፣ ይህ ወንድ ነው፣ይህች ሴት ናት፣ ይህ ደግ
ነው፣ ይህ ክፉ ነው፣ ይህ መልከ ቀና ነው፣ ይህ መልከ ክፉ ነው ማለት
የለም፡፡ እነዚህ ቅዱሳን ክርስቶስ ዓለሙን እንዲሁ ወዷል ብለው ሰውን
ሁሉ አስተካክለው ይወዳሉ፤ ለሁሉም ይራራሉ፤ የወጡትን በደኅና
አግባቸው፤ የሰው ልጆችን ከክህደት ወደ ሃይማኖት፣ ከገቢረ ኃጢአት
ወደ ገቢረ ጽድቅ መልሳቸው እያሉ ይጸልያሉ፡፡ ፩ኛ ቆሮ ፲፫፥፩-፲፫፣
ማቴ. ፭፥፵፬ አዕዋፋት እንስሳትና አራዊት አይጣሏቸውም፡፡ ዓመፀኞች
አጋንንት ጭምር ይታዘዙላቸዋል፡፡ መዝ. ፺(፺፩)፥፲፫፤፡
መ. ሑሰት
ሑሰት ማለት እንደ ፀሐይ ብርሃን ካሰቡበት ሁሉ መገኘት፤ በሌላ
ቦታ የሚሠራውን ባንድ ቦታ ሆኖ ማየት መቻል ሲሆን የሚደረገው
ሁሉ አይሰወራቸውም፡፡ ሁሉንም አንድ ቦታ ሆነው ማየት ይችላሉ።
ለምሳሌ በአንድ ተመሳሳይ ሰዓት በመላው ዓለም ቅዳሴ ቢቀደስ እነማን
እንደቀደሱ እነማን እንደቆረቡ በቅጽበት ያውቃሉ፡፡ በዚህ መዓርግ ሳሉ
ረቂቅ መንፈስ ቅዱስ ስለሚዋሐዳቸው ረቂቃን ይሆናሉ፡፡ በሥጋ ግዙፋን
ቢሆኑም ጠፈር፥ ደፈር ሳይከለክላቸው በመስተዋት ብርሃን እንደሚያልፍ
ማለፍ ይችላሉ፡፡ ፪ኛነገ. ፮፥፰-፲፫፤የሐዋ. ፭፥፩-፲፩፡፡
፴፭
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
ሀ. ንጻሬ መላእክት
ንጻሬ ማየት ማለት ነው፡፡ ንጻሬ መላእክት ማለት መላእክትን ማየት
ማለት ነው፡፡ ወጣንያንስ መላእክትን ያዩ የለምን፣ የልባዌ መዓርግ ላይ
የደረሱስ መላእክትን እያዩ እነማን እንደሆኑ ለምን እንደመጡ ያውቁ
የለምን? ቢሉ እነዚያ መላእክትን የሚያዩት በዚህ ዓለም ሆነው ነው፡፡
ንጻሬ መላእክት ላይ የደረሱ ግን መላእክትን በዓለማቸው እየገቡ፣ በዚህም
ዓለም ሆነው በተመስጦ እላይ የመላእክት ዓለም እየገቡ ነው፡፡ እነዚህ
ቅዱሳን ነፍሳቸው ብቻ ወይም ከነሥጋቸው ወደ መላእክት ዓለም ሂደው
እያንዳንዱን ከተማይ ጎበኛሉ፤ ዜማቸውንም ይሰማሉ፤ ምስጋናቸውም
ከመላእክት ጋር አንድ ሆኖ ቅዱስ፣ ቅዱስ፣ ቅዱስ እያሉ አብረው
ያመሰግናሉ፡፡ ረቂቃን የሆኑት መላእክት አካል ገዝተው ዳመና ዳመና
አክለው ይታዩዋቸዋል፡፡ከመላእክት መዓርግ ላይ ይደርሳሉ፤ የመላእክትን
መኖሪያና ክብር እያዩ ያደንቃሉ፤ በመላእክት ቋንቋ ይናገራሉ፡፡ ቅዱስ
ያሬድ በአካለ ሥጋ በምድር ሆኖ በአካለ ነፍስ የመላዕክትን ዜማ ከሰማይ
፴፮
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
ሰምቶ እንደመጣው እና ቅዱስ ጳውሎስ እስከ ሦስተኛው ሰማይ ድረስ
እንደተነጠቀው ማለት ነው፡፡ ‘‘ወደ ገነት ተነጠቀ፥ ሰውም ሊናገር
የማይገባውን የማይነገረውን ቃል ሰማ።’’ እንዳለ (፪ኛቆሮ.፲፪፥፪)፡፡ ከዚህ
መዓርግ በታች ያሉ ወጣንያን እንኳን በጸጋ በመላእክት ቋንቋ መናገር
ይችሉ የለምን? ቢሉ ልዩነቱ ወጣንያን ከፍቅር መዓርግ ላይ ሳይደርሱ
ነው፡፡ እነዚህ ግን ከፍቅር መዓርግ ደርሰው ነው፡፡ ይህ መዓርግ ከሑሰት
ይበልጣል፡፡ እዚህ መዓርግ ላይ የሚደርሱ ቅዱሳን ከጠላቶቻቸው
ከአጋንንት ይሰወራሉ፤ የመንግሥተ ሰማያትን ምስጢር ያውቃሉ፡፡
ለ. ተሰጥሞ ብርሃን
ዓሣ በባሕር ውስጥ ተሰጥሞ (ጠልቆ) እንደ ሚኖር፤ እዚህ መዓርግ ላይ
የሚደርሱ አባቶች ኅሊናቸው ጸጥ ይላል፤ ልዑል፣ ስፉሕ፣ ረቂቅ በሚሆን
ብርሃን ይሰጥማሉ (ይዋኛሉ)፤ሕይወታቸው ብሩህ ይሆናል፤ ሙሉ በሙሉ
ደስተኞች ይሆናሉ፡፡ ፪ኛ/ቆሮ ፮፥፲ ፣ ፊልጵ ፫፥፩/ አሞራዎችና ንስሮች
በአየር ባሕር ውስጥ እንደሚበሩ፣ዓሣዎች በባሕር ውስጥ እንደሚዋኙ
ተሰጥሞ መዓርግ ላይ የደረሱ ቅዱሳንም በላይ ባለ የብርሃን ውቅያኖስ
ውስጥ ይዋኛሉ፤ይንሳፈፋሉ፡፡ ይሄም የብርሃን ውቅያኖስ የእግዚአብሔር
ጸጋ ነው፡፡ በዚያ ብርሃን ልቦናቸው ይታጠባል፤ ፍጹም ሆነው የልብ
ንጽሕና ላይ ይደርሳሉ፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ በኤፌ ፭፥፲፫“ ሁሉ ግን በብርሃን
ሲገለጥ ይታያል፤ የሚታየው ሁሉ ብርሃን ነውና።” እንዲል።
፴፰
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
ማጠቃለያ ጥያቄዎች
ክፍል ፩፦ እውነት ወይም ሐሰት በማለት መልሱ።
፩ ቅድስና ምንም ዓይነት ደረጃ የለውም።
፪ የቅድስና የመጀምሪያው ደረጃ ዝምታ ወይም አርምሞ ነው።
፫ ቅዱሳን የንጽሓ ልቦና መዓርግ ላይ ሲደርሱ ወደ ንጽሓ ሥጋ
መዓርግ ይሸጋገራሉ።
ክፍል ፪፦ አዛምድ/ጅ
ረድፍ ሀ ገድፍ ለ.
፩ ከዊነ እሳት ሀ. ካሉበት ቦታ ሆኖ ሌላ ቦታ
የሚደረገውንየ ፈለጉትን ነገር ሁሉ ማወቅ
፪ ተሰጥሞ ብርሃን ለ. በተጋድሎ ፈቃድ ሥጋቸውን
ለፈቃደ ነፍሳቸው ማስገዛት
፫ ንጻሬ መላእክት ሐ.ዝምታ
፬ ሑሰት መ.የሚያገለግሏቸውን መላእክትን
በዓይነ ሥጋ ማየትና መስማት
፭ ፍቅር ሠ. በሚያስደንቀው የእግዚአብሔር
ብርሃን ውስጥ መዋኘት
፮ ኩነኔ ረ.ሁሉንም አስተካክሎ መውደድ
፯ አንብዕ ሰ. ያለ ማቋረጥ እንባቸውን የሚያፈሱ
፰ ጣዕመ ዝማሬ ሸ. ማስተዋል ልብ ማድረግ
፱ ልባዌ ቀ. ሳይሰለቹና ሳይቸኩሉ በንቁ ሕሊና
ማመስገን እና መጸለይ
፲ አርምሞ በ. ለአጋንንት የማያስቀርብና የሚያቃጥል
ሰውነት ይኖራቸዋል
፴፱
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
፵
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
ምዕራፍ አራት
የቅዱሳን ምልጃ
ዓላማ
ተማሪዎች ይህንን ምዕራፍ ሲያጠናቅቁ
የመክፈቻ ጥያቄዎች
፵፩
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
፵፪
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
ለ. ተማላጅ፥- ተማላጅ ማለት ምልጃ ተቀባይ ማለት ነው። የጸሎት ሁሉ
መድረሻ፣ ተቀባይ ቅዱስ እግዚአብሔር ነው። ቅዱስ እግዚአብሔር
ስንልም አብ ወልድ መንፈስቅዱስን ማለታችን ነው። ሦስቱ አካላት
ባንዲት ጌትነት፣ ሥልጣን፣ መለኮት፣ ፈቃድ በሰማይና በምድር የሚገኙ
ፍጥረታትን ሁሉ ልመና ተቀብለው የፈቃዳቸውን የቸርነታቸውን ሥራ
ይሠራሉ።
፵፫
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
፵፯
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
፶
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
. ማቴ ፲፥፵-፵፪ “እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፥ እኔንም የሚቀበል
የላከኝን ይቀበላል።ነቢይን በነቢይ ስም የሚቀበል የነቢይን ዋጋ
ይወስዳል፥ጻድቅንም በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል።”
. ዮሐ. ፳፥፳፫ “ኃጢአታቸውን ይቅር ያላችኋቸው ሁሉ ይቀርላቸዋል፤
የያዛችሁባቸው ተይዞባቸዋል አላቸው።”
ሐዋ. ፯፥፷ እስጢፋኖስም ጌታ ኢየሱስ ሆይ፥ ነፍሴን ተቀበል ብሎ
ሲጠራ ይወግሩት ነበር።ተንበርክኮም። “ጌታ ሆይ፥ ይህን ኃጢአት
አትቍጠርባቸው ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ።”
፶፩
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
፶፪
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
• “ሙታንስ በሚነሡበት ጊዜ በሰማያት እንደ እግዚአብሔር መላእክት
ሆነው ይኖራሉ እንጂ አያገቡም፣ አይጋቡምም። ስለ ሙታን መነሣት
ግን ስለ እናንተ ‘እኔ የአብርሃም አምላክ፥ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም
አምላክ ነኝ’ የሚልከ እግዚአብሔር ዘንድ ወደ እናንተ የተባለውን
አላነበባችሁምን? የሕያዋን አምላክ ነው እንጂ የሙታን አይደለም”
እንዲል፡፡ (ማቴ ፳፪ ፥ ፴፪)
ሉቃስ ፲፮ ፥ ፲፱ - መጨረሻ
<<ቀይ ልብስና ቀጭን የተልባ እግር የለበሰ አንድ ባለ ጠጋ ሰው ነበረ፥
ዕለት ዕለትም እየተመቸው በደስታ ይኖር ነበር። አልዓዛርም የሚባል
አንድ ድሀ በቍስል ተወርሶ በደጁ ተኝቶ ነበር፥ ከባለ ጠጋውም ማዕድ
፶፬
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
ከሚወድቀው ፍርፋሪ ሊጠግብ ይመኝ ነበር፤ ውሾች እንኳ መጥተው
ቍስሎቹን ይልሱ ነበር። ድሀውም ሞተ፥ መላእክትም ወደ አብርሃም
እቅፍ ወሰዱት፤ ባለጠጋው ደግሞ ሞተና ተቀበረ። በሲኦልም በሥቃይ
ሳለ አሻቅቦ አብርሃምን በሩቅ አየ አልዓዛርንም በእቅፉ። እርሱም እየጮኸ፦
አብርሃም አባት ሆይ፥ ማረኝ፥ በዚህ ነበልባል እሰቀያለሁና የጣቱን ጫፍ
በውኃ ነክሮ መላሴን እንዲያበርድልኝ አልዓዛርን ስደድልኝ አለ።
፶፮
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ሐዋርያትን “አንትሙ ውእቱ ብርሃኑ
ለዓለም - እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ” ያላቸው ብርሃንነታቸው በዚህ
በኃላፊው ዓለም ብቻ ተወስኖ እንዲቀር አይደለም፣አማላጅነታቸውም
በአጸደ ነፍስ ሳሉ ጭምር ነው እንጂ ከሞቱስ በኋላ ማማለድ የለባቸውም
እንዳይባል የሰው ልጅ በግርማ መንግሥት በክበበ ትስብዕት መጥቶ
በጌትነቱ በተገኘ ጊዜ እናንተም በ፲፪ መንበሮች ተቀምጣችሁ በ፲፪ቱ ነገደ
እስራኤል ላይ ትፈርዳላችሁ ብሎአቸዋል ማቴ. ፲፱፥፳፰፡፡ ከማማለድና
ከመፍረድስ የቱ ይቀላል?
ማጠቃለያ
በሥጋ የተለዩ፣ በነፍስ ግን ሕያዋን የኾኑ ቅዱሳን በሥጋ ለሞቱት ሰዎች
ያማልዳሉ፤በሥጋ ያልሞቱት ደግሞ በሥጋ ለሞቱት ‹‹አማልዱን›› እያሉ
ይጸልያሉ፡፡ ‹‹በዚያ ወራት የወዳጆቼ የጻድቃን ልመናቸው ወደ ሰማይ
ወጣች፤ከዚህ ዓለም በግፍ የፈሰሰ የጻድቁም ደም በመላእክት ጌታ ፊት
ተወደደ፡፡ በእነዚህ ወራቶች በሰማይ የሚኖሩ ጻድቃን በአንድ ቃል ኾነው
ተባብረው ያመሰግናሉ፤ ለሰው ፈጽመው ይለምናሉ፡፡ ፈጣሪያቸውን
ያመሰግናሉ፤›› ተብሎ እንደተጻፈ (ሄኖክ ፲፪፥፴፫)፡፡ ሙታን ለሕያዋን፣
ሕያዋን ለሙታን ይጸልያሉ ማለትም ይኸው ነው፡፡እግዚአብሔር
አምላካችን በቅዱሳን ጸሎትና ምልጃ ይጠብቀን፡፡
፶፯
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
የማጠቃለያ ጥያቄዎች
ክፍል ፩ - እውነት ወይም ሐሰት በማለት መልሱ
፩ ቅዱሳን በዚህ ዓለም በሥጋ እያሉ ብቻ ሳይሆን ካረፉ በኋላ በአጸደ
ነፍስም ያማልዳሉ።
፪ ቅዱሳን ሕያዋን እንጂ ሙታን አይደሉም።
፫ አምላካችን እግዚአብሔር ስለ ቅዱሳን ጸሎት እና ቃልኪዳን ሲል
ቅጣትን ያስወግዳል።
፬ አባታችን አብርሃም እየለመነው እግዚአብሔር ሰዶምና ገሞራን
ያጠፋቸው ምልጃውን አልቀበል ብሎ ነው።
፬ ቅዱሳን ከሞቱ እና ወደ ገነት ከሄዱ በኋላ እዚህ ዓለም ስለሚሆነው
ነገር አያውቁም።
፶፰
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
ምዕራፍ አምስት
ዓላማ
ተማሪዎች ይህንን ምዕራፍ ሲያጠናቅቁ
የመክፈቻ ጥያቄዎች
፶፱
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
፷
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
፷፩
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
፷፪
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
ሲፈጠር ጀምሮ ዕውር የነበርውን ሰው አምላክችን ኢየሱስ ክርስቶስ
መለኮት የተዋሐደውን ቅዱስ ምራቁን እንትፍ ብሎ በምራቁ ጭቃ
አደረገና የዚያን ዕውር ዓይኑን ቀባው:: ከቀባውም በኋላ “ሒድና
በሰሊሆም መጠመቂያ ታጠብ” አለው ዮሐ.፱፥፩:: ዕውሩም ሄዶ ታጠበና
እያየ ተመለሰ:: ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዕውሩን ጭቃ ከቀባው በኋላ
ለምን በሰሊሆም መጠመቂያ እንዲጠመቅ አዘዘው? ያዳነው ራሱ ነው::
እርሱ ራሱ አግኝቶትና ፈውሶት ሳለ ሄደህ ታጠብ ለምን አለው?
ጌታችን ይህንን ያደረገው ኃይሉን በጸበል ላይ ማሳደሩን ለመግለጽ ነው::
እግዚአብሔር ፈውስ የሚሰጥበት ቅዱስ ውኃ “ጸበል” መባሉም ጌታችን
የዚህን ዕውር ዓይን የፈጠረው መለኮት በተዋሐደው ቅዱስ ምራቁ
ለውሶ ጭቃ ባደረገው መሬትና ከሰሊሆም መጠመቂያ ከተገኘው ቅዱስ
ውኃ ድብልቅ በመሆኑ ነው:: እንዲሁም በጭቃ በተዋሐደ ቅዱስ ምራቁ
አማካይነት ኃይሉን ስላሳደረበት ነው::
፷፫
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
፸፪
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
የቅዱሳን ክብርና ቃልኪዳን
እግዚአብሔር አምላክ ቅዱሳን በሚፈጽሙት መንፈሳዊ ተጋድሎ
ምክንያት ስለሚደሰት የክብራቸው መገለጫ እንዲሆን እና ኃጥአን
በቅዱሳን ተማጽነው መልካም ሥራ ሠርተው መንግሥቱን እንዲወርሱ
፥በቅዱሳን ቃል ኪዳን ተጠቃሚ እንዲሆኑና የቅዱሳን ክብር ይገለጽ
ዘንድ ለቅዱሳኑ ቃል ኪዳን ይሰጣቸዋል፡፡ ‘‘ነቢይን በነቢይ ስም የሚቀበል
የነቢይን ዋጋ ይወስዳል፥ ጻድቅንም በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ
ይወስዳል። (ማቴ ፲ ፥ ፵፩) እንዲል
፸፯
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት ስድስተኛ ክፍል
ዋቢ መጻሕፍት
መጽሐፍ ቅዱስ ሰማንያ ወአሐዱ
ነገረ ቅዱሳን -፩፣ 2004 ዓ.ም፣ ቀሲስ ደጀኔ ሽፈራው
ነገረ ቅዱሳን ፣ መምህር ፈቃዱ ሳህሌ ፣ 2011 ዓ.ም. ፣ ማኅበረ
ቅዱሳን
፸፰
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
የሰንበት ት/ቤት አመራር እና መምህራን እንዲሁም
ተማሪዎችና ወላጆች በመጽሐፉ ላይ ያላችሁን
ማንኛውም አስተያየት እና ግብዓት በሚከተለው
አድራሻ ላኩልን
office@eotc-gssu.org
https://t.me/GSSUCurriculum_bot