You are on page 1of 25

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ

ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን


ቦሌ ደብረ ሳሌም መድኀኔዓለምና መጥምቀ
መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ፈለገ ዮርዳኖስ ሰንበት
ት/ቤት መጋቢት ፳፻፲፫

የቤተክርስቲያን ታሪክ ትምህርት

በይትባረክ ሙላቱ
የዛሬው የትምሕርት ክፍለ ጊዜ የሚዳስሰው
❖ የቤተክርስቲያን ታሪክ ትምህርት መከለስና ማጠቃለል

 የቤተክርስቲያን ታሪክ ትምህርት ምንነት


➢ ቤተ ክርስቲያን ምን ማለት ነው?

➢ የቤተክርስቲያን ታሪክ ትምህርት ዓላማና ጥቅም

➢ የቤተክርስቲያን ታሪክ ምንጮች

➢ የቤተክርስቲያን ትርጉም (በዘይቤያዊ ፍቺ)


 ሕንፃ ቤተክርስቲያን

 የክርስቲያኖች አንድነት

 እያንዳንዱ ክርስቲያን

➢ የቤተ ክርስቲያን ባሕሪያት /ቅፅል ስሞች/


የዛሬው የትምሕርት ክፍለ ጊዜ የሚዳስሰው
➢ የቤተ ክርስቲያን ባሕሪያት /ቅፅል ስሞች/
 ቤተክርስቲያን አንዲት ናት

 ቤተክርስቲያን ቅድስት ናት

 ቤተክርስቲያን ዓለም አቀፋዊት (ኩላዊት) ናት

 ቤተክርስቲያን ሐዋርያዊት ናት

 የቤተክርስቲያን ዕድሜ
❖ ማኀበረ መላዕክት (ቤተክርስቲያን በዓለመ መላእክት)

❖ ከአዳም - ኢየሱስ ክርስቶስ ያለው የደጋግ አባቶች አንድነት

❖ ከክርስቶስ አሁን እስካለንበት ዘመን የሚደርሰው አንደነትን


ያጠቃለለ ነው፡፡
የቤተክርስቲያን ታሪክ ትምህርት መከለስና ማጠቃለል
 የቤተክርስቲያን ታሪክ ትምህርት ምንነት
የቤተክርስቲያን ታሪክ ትምህርት ምንነት

የቤተ ክርስቲያን ታሪክ  መግቢያ እና


 የዓለም መድረክ
በኢትዮጵያ ተብሎ ለ3 ይከፈላል፡፡
 መግቢያ፡- ከዓለመ መላዕክት እስከ እርገተ ክርስቶስ
 የዓለም መድረክ፡- ከእርገተ ክርስቶስ በኋላ እስከ የዓለም
አብያተ ክርስቲያናት አንድነት ንቅናቄ ማኅበር/ጕባኤ/
(ECUMENISM)
 በኢትዮጵያ፡- በሀገራችን የተዋህዶ ጉዞ ምን እንደሚመስል
ያሳያል፡፡
ቤተ ክርስቲያን ምን ማለት ነው?
 ቤተክርስቲያን፡ -የሚለው ከሁለት ቃላት በጥምረት
የተገኘ ሲሆን ቤተ ማለት በግእዝ አደረ ክርስቲያን
ደግሞ የክርስቶስ ማለት ነው፡፡ በዚህም
ቤተክርስቲያን የሚለው በቁሙ ሲፈታ የክርስቶስ
ማደሪያ ማለትን ያስገኛል፡፡
 "ቤተክርስቲያን" የምንለው የክርስቲያን ሃይማኖትን
ነው፡፡ ትርጕሙም ማደር፣ ወገን፣ ነገድ፣ ዘር፣ ጉባኤ፣
ማኅበር፣ ቤተሰብ ማለት ነው፡፡ ቤተክርስቲያን
የሚለው ቃል መሠረቱ ከግዕዝ ሲሆን የቃሉም መነሻ
ቤተ፣ አደረ፣ ፡፡
 ክርስቲያን፡- የሚለው ቃል ከክርስቶስ የተገኘ ቃል
ነው፡፡
የቤተክርስቲያን ታሪክ ትምህርት ዓላማና
ጥቅም
❖ የቤተክርስቲያናችንን ከፍተኛነትና ጠቃሚነትን
ለመገንዘብና ራስንም በእምነት ለማጽናት፣
❖ ባለፉት ዘመናት የተከሰቱ ችግሮችን ለማወቅና
በድጋሚ እንዳይከሰቱ የመፍትሔ ሃሳብ
ለመስጠት፣
❑ አዳም አባታችን የበደለውን በደል
❑ በኖህ ጊዜ የነበሩ ሕዝቦችን
❑ የግራኝ አህመድን
❑ የዩዲት ጉዲትንና የመሳሰሉትን
የቤተክርስቲያን ታሪክ ትምህርት ዓላማና
ጥቅም
❖ ቅዱሳን አባቶች በመከራና በፈተና ያሳዩትን
የሃይማኖት ፅናት በማየት እነርሱን ለመምሰልና
እኛም የድርሻችንን ለመወጣት እና
➢ ሰማዕታትን ፡- ቅ/ጊዮርጊስ፣ ቅ/አርሴማ
➢ ፃድቃን፡- አባታችን አቡነ ተክለ ሐይማኖት
➢ ደናግላን፣ መነኮሳትና የመሳሰሉት
❖ በመንፈሳዊ ጉዞአችን መንፈሳዊ ጥበብና ብልሃትን
ገንዘብ እንድናደርግ ይጠቅመናል፡፡
የቤተክርስቲያን ታሪክ ምንጮች
1. አሥራው መጻሕፍት/ብሉይ ኪዳንና ሐዲስ ኪዳን/ ፤
አዋልድ መጻሕፍት/በተለይ ገድላትና ድርሳናት/፤
እንዲሁም ትርጓሜ መጻሕፍት፡፡
2. የቤ/ክ አባቶች የጻፏቸው የታሪክ መጻሕፍት
/ለምሳሌ፡- ጊዮርጊስ ወልደ አሚድ፣ ዮሐንስ መደብር፣
ዜና እስክንድር፣…/
3. ታሪኩ በተፈጸመበት ቦታና ጊዜ ተገኝተው
የቤተክርስቲያንንና የዘመኑን ታሪክ የጻፉ ጸሓፊዎች
/ሩፊኖስ፣ሶቅራጥስ፣ዮሴፍ ወልደ ኮርዮን፣
አውሳብዮስ፣…/ የጻፏቸው መጻሕፍት፡፡
4. በየጊዜው የተደረጉ የቤተክርስቲያን ጉባኤዎች(ኒቂያ፣
ቊስጥንጥንያ፣ ኤፌሶን) እና ውሳኔዎቻቸው
የቤተክርስቲያን ታሪክ ምንጮች
5. በየጊዜው የተገኙና የሚገኙ የቤተክርስቲያን
መቃብራት፣ መቅደሶች፣ ስዕሎች፣ ገንዘቦች፣ ጽሑፎች፣
የአርኪዎሎጂ/የጥንታውያን ነገሮች ምርመራ/ እና
እነዚህን የመሳሰሉ ለማገናዘቢያነት የሚረዱ ቅርሶች፡፡
6. መንፈሳውያንም ሆኑ ዓለማውያን ነገሥታት ሰለ
ቤተክርስቲያን የደነገጓቸው ልዩ ልዩ ሕግጋት(ለምሳሌ፡-
ክብረ ነገሥት፣ ብዕለ ነገሥት፣ ታሪከ ነገሥት)
እንዲሁም
7. የቤተክርስቲያን ትውፊት መረጃዎች ያስፈልጉታል፡፡
1. ሕንፃ ቤተክርስቲያን

2. የክርስቲያኖች አንድነት

3. እያንዳንዱ ክርስቲያን
ሕንፃ ቤተክርስቲያን
➢ የክርስቲያኖች መገናኛ መሰብሰቢያ በዓት
➢ ክርስቲያኖች በአንድነት የሚጸልዩበት፣ የሚሰግዱበት፣
ሥጋ ወደሙን የሚቀበሉበት፣ ከእግዚአብሔር ጋር
የሚገናኙበት ቦታና የጸሎት ቤት ማለት ነው፡፡(ኢሳ 56÷7፤
ኤር 7÷10-11፤ ማር 11÷17፤ ሉቃ 19÷46)
➢ ቤተ ክርስቲያንም በፊልጵስዩስ ለመጀመሪያ ጊዜ በጌታችን
ፈቃድ ከተሰራ
➢ ቤተክርስቲያን
የክርስቲያኖች አንድነት
 የክርስቲያኖች አንድነት «ማኅበረ ምዕመናን» ማለት ነው
 ይህም በአንድ ጌታ በአንድ እምነት እና በአንድ ጥምቀት
አምነው የተጠመቁ፣ በክርስቶስ ክርስቲያን የተሰኙ፣
በዚህ ምድር በአንድ አሳብ እና ተስፋ የሚኖሩ፣
በመጪው ዓለምም በእግዚአብሔር መንግሥት
በዘለዓለማዊ አንድነት የሚኖሩ ክርስቲያኖችን
የሚያመለክት ነው፡፡ ማቴ 18÷20
ምሳሌ፡ -  ቤተክርስቲያን ዘኢትዮጵያ
 ከዓል፡ - በዓል ለማክበር ይሰባሰቡ የነበሩ
እስራኤላውያን ስያሜ (በዓል የዕብራውያን ቃል
ነው)
 ቤተክርስቲያን ዘእስክንድርያ
እያንዳንዱ ክርስቲያን
❖ እያንዳንዱን ምዕመን ማለታችን ነው፡፡ ይህም
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ የእግዚአብሔር ቤተ
መቅደስ መሆናችሁን አታውቁምን በማለት የገለፀው
ነው፡፡ (1ኛ ቆሮ 6÷19)፡፡
የቤተ ክርስቲያን ባሕሪያት /ቅፅል ስሞች/

 ቤተክርስቲያን አንዲት ናት

 ቤተክርስቲያን ቅድስት ናት

 ቤተክርስቲያን ዓለም አቀፋዊት (ኩላዊት) ናት

 ቤተክርስቲያን ሐዋርያዊት ናት
ቤተክርስቲያን አንዲት ናት
➢ቤተክርስቲያን በወርቅ፣ በአፈር፣ በከተማ፣ በገጠር
ብትሰራ ክብሯ አንድ ነው፡፡ ሮሜ 12÷5፡፡ «ብዙዎች
ስንሆን በክርስቶስ አንድ አካል ነን» እንዲል፡፡
➢ምዕመናን አንድ ልብ አንድ ሃሳብ ሆነው በውስጥ
የሚደረገውን ክብር ስለሚካፈሉ ቤተክርስቲያን
አንዲት ናት፡፡ የሚሰራባት ሥርዓት የሚፈፀምባት
ጸሎት አንድ ስለሆነ ቤተክርስቲያን አንዲት ናት፡፡ ገላ
4÷5
ቤተክርስቲያን ቅድስት ናት
• ቅድስና የባሕሪው የሆነው ጌታችን በደሙ
የመሰረታት ስለሆነች ቤተክርስቲያን ቅድስት
ትባላለች፡፡ ሐዋ 20÷28
• በኃጢያትና በክህደት ረክሰው የነበሩ
በእምነት በንስሃ ወደ እርሷ ገብተው
ይቀደሳሉና ቤተክርስቲያን ቅድስት ናት፡፡ መዝ
45÷4
ቤተክርስቲያን ዓለም አቀፋዊት (ኩላዊት) ናት
 ቤተክርስቲያን አንዲት ብትሆንም መንፈሳዊ ናትና
በሁሉ ያለች የሁሉም ናት ምክንያቱም እግዚአብሔር
በአንድ አካባቢ ሊወሰን አይቸልም፡፡
 ቤተክርስቲያን በዘር፣ በጎሳ በቋንቋ ተከፍላ የእገሌ
ናት የምትባል ሳትሆን የሁሉና በሁሉ ያለች ናት፡፡
ጌታችን በመስቀል ላይ የተሰቀለው ለሁሉም እንጂ
ለተወሰኑት ብቻ አይደለም፡፡ ማቴ 28÷19
ቤተክርስቲያን ሐዋርያዊት ናት
❖ የሐዋርያትን ትውፊት፣ ቀኖና፣ ትምህርት ይዛ
ስለምትገኝ ቤተክርስቲያን ሐዋርያዊት ናት፡፡ ኤፌ
2÷20፡፡

❖ በነብያትና በሐዋርያት መሠረት ላይ ታንፃችኋል


እንዲል ሐዋርያው፡፡ ይሁ1÷3፡፡

❖ የሐዋርያትን ገድል ይዛ በመገኘትና ዕረፍታቸውን


እየቆጠረች ስለምታስባቸው ሐዋርያዊት ትባላለች፡፡
የቤተክርስቲያን ታሪክ ትርጉም
• የቤተክርስትያን ታሪክ ማለት የክርስትና እምነት
ታሪክ ማለት ነው፡፡
• በቤተክርስትያን ታሪክ ትምህርታችን የክርስትና
እምነት የአምላክ መገለጥ ነው፡፡
➢ይሁን እንጂ በዘመንና በቦታ የተደረጉ ስለሆነ መቼ
እንዴት እንደሆነ የምናውቅበትና በጉዞው ሁሉ
የገጠሙትን ችግሮችና ምቾቶች የምንማርበት ነው፡፡
የቤተክርስቲያን ዕድሜ
1. ማኀበረ መላዕክት (ቤተክርስቲያን በዓለመ
መላእክት)

2. ከአዳም - ኢየሱስ ክርስቶስ ያለው የደጋግ


አባቶች አንድነት

3. ከክርስቶስ አሁን እስካለንበት ዘመን የሚደርሰው


አንደነትን ያጠቃለለ ነው፡፡
ማኀበረ መላዕክት (ቤተክርስቲያን በዓለመ
መላእክት)
➢ እግዚአብሔር መላእክትን በጨለማ ከፈጠረ በኃላ
ተሰወራቸው፡፡ እነርሱም ከእውቀት ጋር ስለተፈጠሩ
ማነው የፈጠረን ብለው መጠየቅ ጀመሩ፡፡ በዚህን ጊዜ
ከነሱ ላቅ በሎ ይገኝ የነበረው ሳጥናኤል እኔ ነኝ
የፈጠርኳችሁ በማለት ክርክር ተነስቶ መላእክት ለሦስት
ተከፈሉ፡፡
1. ከነሱ በቦታ ስለበለጠ ፈጥሮናል ያሉ፣
2. ነው ወይም አይደለም እያሉ መጠራጠር የጀመሩ፣
3. ዝም ያሉና
4. አምላካችን ራሱን እስኪገልፅልን ድረስ በያለነበት
ጸንተን እንቁም ያሉ ነበሩ፡፡
……የቀጠለ
❖ በመላእኩ በቅዱስ ገብርኤል ንግግር በመጽናት
እግዚአብሔርን ቅዱስ፣ ቅዱስ፣ ቅዱስ እያሉ
የሚያመሰግኑ ቅዱሳን መላእክት ህብረት
ስብስብ ቤተክርስቲያን ይባላል፡፡
ከአዳም - ኢየሱስ ክርስቶስ ያለው የደጋግ
አባቶች አንድነት
• ከአዳም እስከ አዲስ ኪዳን መመስረት ወቅት ያለው
በአራት የተከፈለ ዘመን ነው፡፡ እነዚህም፡-
1. ዘመነ አበው
2. ዘመነ መሳፍንት
3. ዘመን ነገሥት
4. ዘመነ ነብያት/ካህናት/ሲባሉ እያንዳንዱን
በዝርዝር እንደሚከተለው እንመለከታለን፡፡
ዘመነ አበው
መግቢያ
❖ የጽሑፍ ሕግ ሣይሰጣቸው በፊት የሰው ልጅ
በሕገልቦና ለእግዚአብሔር እንዴት ይታዘዙ ነበር
የሚለውን እንመለከታለን፡፡
❖ በእግዚአብሔር አምሳል የተፈጠረ ሰው
የእግዚአብሔርን ትዕዛዝ በመጣሱ ያጣውን ጸጋ
ምን እንደሆነ እንመለከታለን
❖ የሃያሁለቱን አርዕስተ አበው ታሪክ በቅደም
ተከተል በመተረክ፤ ክፉውንና በጎውን በንጽጽር
እናያለን
• ዘመነ አበው የሚባለው ከአዳም እስከ ሙሴ ድረስ
ያለው ዘመን ነው፡፡
• ዘመኑንም ሊቃውንት ከሁለት ከፍለው ያሳያሉ፡፡
ከአዳም እስከ ጥፋት ውኃ 2256 ዓ.ዓ እንዲሁም
ከኖኅ እስከ ሙሴ 1588 ዓ.ዓ በጥቅሉ 3844
ዓመታትን ያስቆጠረ ዘመን ነው፡፡

ይቆየን!!!!

You might also like