Professional Documents
Culture Documents
አጠቃላይ መግቢያ
• የቀደም አበው ታሪክ በቀጥታም ኾነ በተዘዋዋሪ
የቤተክርስቲያን ታሪክ ነው፡፡
• ቀደም አበው የነበራቸው የአምልኮ ሥርዓት፣ መንፈሳዊነት፣
እረኝነት፣ ትምህርት፣ ወዘተ ኹሉ ቤተክርስቲያን በእነዚህ
ነገሮች የነበራት አካሔድ እንዴት እንደ ነበረ የሚያስረዳ ነው፡፡
• የአበው መጻሕፍት ሲተረጎሙ በምዕራቡ ዓለምና በምሥራቁ
ዓለም ኹለት ተቃራኒ የኾነ ዓላማ ያለው ነው፡፡
– በምዕራቡ ዓለም መጻሕፍቱ የሚተረጎሙት ለመተቸት፣ ቋንቋውን
ለመመርመር፣ ትምህርቱን እንዲሁ እንደ ሳይንስ ለማጥናት ነው፡፡
– በምሥራቁ ዓለም ግን መጻሕፍቱ የሚተረጎሙት የአበውን ልብ
ብሎም የክርስቶስን ልብ አግኝቶ በዚያ መሠረት ወደ መሬት
አውርዶና ተግብሮ ለመዳን ነው፡፡
• ነገረ አበው (ፓተር - አባት፣ ፓትሮሎጂ - ነገረ አበው) የአበው ሕይወት፣
ተጋድሎ፣ ጽሑፍ (ትምህርት)፣ አባባሎች፣ እምነት ኹሉ የሚያጠና ነው፡፡
• ሕይወታቸው የሚጠናው ጽሑፋቸውንና አባባላቸውን በቀላሉ ለመረዳት
ይጠቅማል፡፡ በዙሪያቸው የነበረው ማኅበረሰብም ይህን ለመረዳት
አስፈላጊ ነው፡፡
• ያደረጉአቸው ተጋድሎዎችም ከሕይወታቸው የተለየ አይደለም፡፡
• በተለይም በእግዚአብሔር፣ በሰው፣ በቤ/ክ.፣ በነገረ ድኅነት፣ በሥነ
ፍጥረት፣ በዚህ ዓለምና በወዲያኛው ዓለም ያላቸው ትምህርት እጅግ
ወሳኙ ነው፡፡
• ስለዚህ ነገረ አበው ነገረ ቤተክርስቲያንን ለመረዳትና ወደ ቤ/ክ. ውስጥ
ገብተን አሳብዋን ለመረዳት በር (ደጅ) ነው፡፡
• አበው ብለው መጥራት የተጀመረው ከእነ አብርሃም፣ ይስሐቅ ያዕቆብ
አንሥቶ ነው፡፡ በሐዲስ ኪዳን ደግሞ አይሁድና አረማውያን ቅዱስ
ፖሊካርፐስን “የክርስቲያኖች አባት ይኼ ነው” ይሉት ነበር፡፡ ቅዱስ
አትናቴዎስም ቅዱስ ዲዮናስዮስን “አባት” ብሎ ጠርቶታል፡፡
• “አንድ ሰው ከሌላ ሰው አንደበት ሲማር ይህ ሰው የዚያ
አስተማሪው ሰው ልጅ ነው ይባላል፤ ኹለተኛው ደግሞ አባት
ይባላል” (ቅዱስ ሄሬኔዎስ፣ በእንተ መና.4፡41፣2)፡፡
• በነገረ አበው ትምህርት አንድ ሰው አባት ለመባል
– ጽሑፍ በመጻፍ ሱታፌ ያለው፣
– ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮ ያለው፡፡ በምዕራቡ ዓለም እነ
ጠርጡለስ፣ አርጌንስ፣ ታቲያን፣ ቀሌምንጦስ ዘእስክንድርያ፣
አውሳብዮስ ዘቂሳርያን ያካትታሉ፡፡
– የቅድስና ሕይወት
– ጥንታዊነት፡፡ ብዙውን ጊዜ እስከ 6ኛው መ.ክ.ዘ.፣ አንዳንዶች
እስከ 8ኛ መ.ክ.ዘ.፣ ሌሎች ደግሞ በየትኛውም ጊዜ ያሉ ናቸው
ይላሉ፡፡
የነገረ አበው ታሪክ
• የነገረ አበው አባት ተብሎ የሚጠራው አውሳብዮስ ዘቂሳርያ ነው፡፡ እርሱ በ326 ዓ.ም.
የአበውን አባባሎችና ጽሑፎች ተርጉሞ ጽፎአልና፡፡
ለምሳሌ፡- ሩሲያ፡ዩክሬን፡ሰርቪያ፡ቦሲኒያ፡ግሪክ
ሐዋርያነ አበው (ተላውያነ
ሐዋርያት)
• በዚህ ውስጥ የሚካተቱት በዋናነት፡-
– ቅዱስ አግናጥዮስ፡- 7 መልእክታት አሉት፡፡
– ሰርምኔስ በደረሰ ጊዜም ቅዱስ ፖሊካርፐስ መጥቶ ተጎንብሶ ሰንሰለቶቹን ስሞታል፡፡ ቅዱስ
አግናጥዮስም፡- “ቤተ ክርስቲያንን አደራ” ብሎታል፡፡
• ገሚሱ ያለቅሳል፡፡ ገሚሱ በቅዱሱ ጥብዓት በቅንአት ደስ ይሰኛል፡፡ ከፊሉ አዝኖ ተክዞ
ይመለከታል፡፡
• የአ/ኦ/ተ/ቤ/ክ. የዚህን ታላቅ ሰማዕት የዕረፍት ቀን ታኅሳስ 24 ቀን ታከብረዋለች፡፡ በሐምሌ ሰባት ስንክሳር
ላይ ታነሣዋለች፡፡
የቅዱስ አግናጥዮስ
ትምህርቶች
ሰባት መልእክታትን ጽፎአል
• የተወሳሰቡ አይደሉም፡፡
• ቅዱስ አግናጥዮስ ስለ ቤተ ክርስቲያን አንድነት ከፍተኛ የኾነ ትኩረት ሰጥቶ ያስተማረ ሲኾን
ቀጥሎ ያለውም ከትምህርቶቹ ውስጥ ተጠቃሽ ነው፡-
– “መከፋፈልና ቁጣ ባለበት በዚያ እግዚአብሔር አያድርም፡፡ በንስሐ ለሚመለሱት ግን በእውነት ወደ
እግዚአብሔር አንድነትና ወደ ቤተ ክርስቲያን ኅብረት ቢመለሱ ጌታ ይቅር ይላቸዋል፡፡ ምንም ዓይነት
ነገር በሁከትና በጠብ እንዳታደርጉ እመክራችኋለሁ፡፡ ለእርሱ አስተምህሮ እንደሚገባ ኢየሱስ
ክርስቶስ ባስተማረን መሠረት በፍቅርና በሰላም እንጂ” (ኤፌ.5)፡፡
• ቅዱስ ጳውሎስ እንደ ተናገረ ጳጳሳት፣ ካህናት ለእኛ እንደሚተጉ (ዕብ.13፡17) ምንም ነገር
ብናደርግ ያለ ጳጳሳት ልናደርግ እንደማይገባን፣ የምድራዊ መብልና መጠጥ ሳይኾን
የሰማያዊ ምሥጢር አገልጋዮች ስለ ኾኑ እነርሱን ደስ ማሰኘት እንደሚገባን፣ ከእነርሱ
ውጪም ቤተ ክርስቲያን የሌለን እንደ ኾንን አስተምሮአል (ትራ.2)፡፡
• ቅዱስ ፖሊካርፐስ የተወለደው ከክርስቲያን ቤተሰቦች በ70 ዓ.ም. በጥንታዊቷ ሰምርኔስ ከተማ
(ቱርክ ውስጥ የአሁኗ እዝሚር) ነው፡፡
• ይህች ካሊስቶ መጀመሪያ እንደ ባሪያ አድርጋ ገዝታዋለች፡፡ ባደገ ጊዜም የቤትዋን ንብረት አለቃ ኾነ፡፡
• ካሊስቶ በተመለሰች ጊዜም አንድ ሌላ ባሪያ ንብረትዋን ኹሉ ለሰዎች እንደ ሰጠባት ነገራት፡፡ ወደ
መጋዘኑ ስትመጣ ግን አንድም ሳይየጎድል ሙሉ ኾኖ አገኘችው፡፡
• ሠ) አገርን በተመለከተ
• አውሳብዮስ ዘቂሳርያም ከዚህ ተነሥቶ “ጊዜው ከ92 እስከ 101 ዓ.ም. ነው” ይላል፡፡
• 11 ምዕራፍም አለው፡፡
• ቅዱስ ቀሌምንጦስ መጽሐፉን ለመጻፍ ምክንያት የኾነው ነገር እንዲህ
በማለት ያስቀምጣል፡-
• በዕለተ እሑድ ሰማይና ምድር፣ መላእክትም አሥር ወገን ኾነው እንደ ተፈጠሩ፤
ከኹሉም መላእክት በማዕርግ የሚበልጠው የሳጥናኤል ወገን እንደ ነበረ፣ በዕለተ
ሰኑይ እግዚአብሔር በምድር ባሉ ውኆችና በሰማይ ባሉ ውኆች መካከል ልዩነትን
(ጠፈርን) እንዳደረገ፣ በዕለተ ሠሉስ ከሰማይ በታች ያሉ ውኆች በአንድ ቦታ
እንዲሰበሰቡ እንዳዘዘ እና የብሱም እንደ ታየ፣ አዝዕርትንም ዛፎችንም እንደ ፈጠረ፣
በዕለተ ረቡዕ ፀሐይ ጨረቃ ከዋክብት እንደ ተፈጠሩ፣ በዕለተ ሐሙስ ውኆች
የዓሣዎችን ዓይነት ያወጡ ዘንድ እንደ ታዘዙ፣ በነፋስ የሚበሩትንም አስደናቂ
ትላልቅ አንበሪዎችንም እንደ ፈጠረ፣ በዕለተ ዓርብ ከምድር አራዊትን እንስሳትን
እንደ ፈጠረ፣ በመጨረሻም ከአራቱ ባሕርያት ትንሽ ትንሽ ወስዶ ሰውን በአርአያውና
በምሳሌው እንደ ፈጠረ ሔዋንንም ከአዳም ከጎኑ ዐፅም እንዳስገኛት ይናገራል::
• እግዚአብሔር አዳምን (ሰውን) በማይነገር ክብር
እንደ ፈጠረው፤ የመለኮት ብርሃን በአዳም ፊት ያበራ
እንደ ነበር፣ የፊቱ ብርሃን ከፀሐይ የሚበልጥ ሰውነቱ እንደ ንጋት
ኮከብ የሚያበራ እንደ ነበር፣ እግዚአብሔር ለአዳም የምስጋና
አክሊል፣ ልብሰ መንግሥት፣ የግርማ ከፍተኛነት እንዳለበሰው፣
የመንግሥትን አክሊል እንዳቀዳጀው ንጉሥነትንና ነቢይነትን
እንደሰጠው፣ … መላእክት በታላቅ ግርማ እና ምስጋና ባዩት ጊዜ
እንደ ፈሩት፤ አራዊት እንስሳት አዕዋፍ እግዚአብሔር
የፈጠራቸው ፍጥረታት ኹሉ ተሰብስበው ለአዳም
እንደ ሰገዱለት … ሰይጣን የአዳምን ጸጋና ክብር አይቶ
እንደ ቀና የሚያስትበትንም ምክንያት ይፈልግ
እንደ ነበር ይናገራል /ምዕ.1፥14-49/፡፡
ለ) የአዳም ውድቀት
• ስለ ዕውቀት
• የመጽሐፉ ኹለተኛው ክፍል ደግሞ ለእነዚህ ኑፋቄዎች የተሰጠ ድንቅ ምላሽ ነው፡፡
አመክንዮአዊ በኾነ ምላሹም የ(ግ)ኖስቲካውያን ትምህርት በኹለት ጎራ ማለትም
በኹለት አማልክትና በብዙ አማልክት ኑፋቄነት እንደሚከፈል አሳይቶአል፡፡
– አዳም የበለጠ መንፈሳዊ ልኹን ብሎ የወደቀውም ያለ መንፈስ ቅዱስ መንፈሳዊ ልኹን በማለቱ
ነው፡፡
– እንዲህ ሲያደርግ መንፈሳዊነቱ በዚህ ዓለም ጀምሮ ፍጹም የሚኾነው በመንግሥተ ሰማያት
ነው፡፡
– በዚህ ዓለም ውስጥ ኾኖም ግን ክፉውንና ደጉን ለይቶ ማወቅ ይቻለዋል፡፡ የአሕዛብንና
የመናፍቃንን ስንፍና መለየት ይቻለዋል፡፡ ይህን ተጸይፎም ለእግዚአብሔር፣ ለክርስቶስና ለቤተ
ቅዱስ አቡሉዲስ ዘሮም
ሕይወቱና ትምህርቱ
• የቅዱሱ ታሪክ የተከናወነው ሮም ውስጥ ቢኾንም ሮማዊ ሳይኾን ግሪካዊ
ነው፡፡
• ማሠቃየቱንም በሰለቸ ጊዜ በእግሮቹ ውስጥ ታላቅ ደንጊያ አስሮ ከጥልቅ ባሕር የካቲት
አምስት ቀን 236 ዓ.ም. አሰጠመው፡፡
• በማግስቱ የካቲት ስድስት ሲኾንም የዚህ አባት ሥጋው በውሃ ላይ ተንሳፍፎ ተገኘ፡፡
ደንጊያውም በእግሮቹ እንደ ታሰረ ነበር፡፡
• አንድ ምእመንም ወስዶ በእርሱ ዘንድ አኖረው፡፡ በከበሩ ልብሶችም ገንዞ ሰወረው፡፡
• ወሬው በሮሜ አገሮች ኹሉ ተሰምቶ ስለ ነበር ንጉሡ ሊያቃጥለው ፈልጎት የነበረ ቢኾንም ያ
የቅዱስ አቡሉዲስ ሥራዎችና ትምህርቶች
• ቅዱስ አቡሉዲስ ብዙ ድርሳናትን ደርሶአል፡፡ ለምሳሌ ስለ እውነተኛዋ እምነት፣ ስለ ወልደ
እግዚአብሔር ሰው መኾን፣ እግዚአብሔርን ደስ ስለ ማሰኘት የተሰጠ ምክር ሠናይት
ይገኙበታል፡፡ እነዚህን በተመለከተም እ.ኤ.አ. በ1551 ዓ.ም. በሐውልት ውቅር ሥራዎቹ
ተዘርዝረው ተገኝተዋል፡፡
• ቀደም ብለን እንደ ገለፅነውም የቅዱስ ሄሬንዮስ ደቀ መዝሙር እንደ መኾኑ ለ32 መናፍቃን
መልስ ጽፎአል፡፡
• በ234 ዓ.ም. ላይም ከፍጥረተ ዓለም አንሥቶ እስከ እርሱ ዘመን የነበረውን ታሪክ ጽፎአል፡፡
• “ትውፊተ ሐዋርያት” የተሰኘና ዲድስቅልያን የመሰለ መጽሐፍም
ጽፎአል፡፡ ይህ ሥራ በተለይም በብዙዎች በኢትዮጵያ ያለው ቅጂ
እንደ ኾነ ያምናሉ፡፡
የአሳይመንቱ ይዘት
አበው 1. ታሪካቸው(የት እንደ ተወለዱ፣እናት እና አባታቸው፣
እድገታቸው……)(2%)
2. የሰሩዋቸውን ስራቸውን እና ከእግዚአብሔር ጋር የነበራቻውን
ግኑኝነት(10%)
3. የጻፎችው መጽሃፍት እና በዘመናቸው የነበረውን የተከናወኑ
1.ሰማዕቱ ጀስቲን እና ዐባይት ክስተቶች ያስተማረቸውን ዋናዋና ቁምነገሮችን
የቤተክርስቲያን ጠበቆች ማብራረት(10%)
2. ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ 4. በነበሩበት ዘመን የነበረው የቤተክርስቲያን ሁኔታና ለዛሬው
ያለው ፋይዳ(5%)
3. የምንኩስና መስራቾች 5. ያረፉበት ቀን፤ የተደረገላቸው ቃል ኪዳን ፤ የታነፀላቸው
ቤተክርስቲያን እና ቤተክረስቲያን በዐላቸውን የምታስብበት
4. ቅዱስ ያሬድ ቀን (3%)
5.አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ማሳሰቢያ፡-1. በጽሁፍ ይገባል
2.የተዘጋጀውጽሑፍታቀርባላችሁ (5%)
3. ቢያንስ ከ ሦስት በላይ መርጃ መጽሐፍት
መጠቀም እና መጻፍ አለበት