You are on page 1of 6

የትምህርተ አበው መግቢያ

አበው የሚባሉት የቤተክርስቲያን አባቶች ከሐዋርያት በኋላ የተነሱ፣ የጌታችንን እና የመድኀኒታችንን የማዳን
ሥራ ከሐዋርያት በመቀጠል በትምህርቶቻቸው እና በስራዎቻቸው ያስቀጠሉ፣ በማዕረጋቸው እና በቅድስናቸው
ሐዋርያትን የሚያክሉ፣ ወንጌልን አንደ ዘመናቸው ሁኔታ እያብራሩ ክርስትና እና የክርስትና ሕይወት እዚህ
እንዲደርስ ያደረጉ መሰረት የጣሉ የቤተ ክርስቲያን ጸሀፊዎች፣ አባቶች ቅዱሳን ናቸው

ሐዋርያነ አበው፣ ነገስታትን ተቃውመው ስለ ክርስትና ጥብቅና የጻፉ አበው፣ የግኖስቲኮችን እና ፍልስፍናን
አስተምህሮ ተቃውመው የክርስትናን ትክክለኛነት የጻፉ አባቶች፣ ከዘመነ ሰማዕታት በኋላ የተነሱ ቅዱሳን
አባቶች፣ ገዳማውያን አባቶችን ያጠቃልላል፡፡

እነዚህ አባቶች በተለያየ ዘመን የተነሱ፣ ከተለያየ ቦታ የተገኙ፣ እንዲሁም የተለያየ ቋንቋ የሚናገሩ፣
በዘመናቸውም የተለያየ ዓይነት ፈተና እና ጥያቄን የተጋፈጡ፣ በወቅቱም ተገቢውን መልስ እና ትምህርት
አስተምረው ያለፉ፣ የቤተክርስቲያን ሕይወት የሆነውን መጽሐፍ ቅዱስ፣ ዶግማ እና ሥርዓት (ትውፊት)
ያዘጋጁ እናም ተጠብቆ እንዲቆይ ስርዓት የሰሩ በግልም በሕብረትም ሆነው ቤተክርስቲያን በዘመናቸው
የነበረውን ፈተና እንድትሻገር ያደረጉ ናቸው፡፡

የሩቅ ምስራቅ የታናሽ ኢሲያ፣ የሶርያ አባቶች፣ ከወደ ሮም የተነሱ አባቶች፣ ከአፍሪካ (ሊቢያ፣ እስክንድርያ፣
ኢትዮጵያ) የግሪክ ቋንቋ፣ የላቲን ቋንቋ፣ የሶርያ ቋንቋ፣ የግዕዝ ቋንቋ ለምሳሌ (በቅዱስ ቀሌምንጦስ
እንደተጻፈ የሚነገረው ኢትዮጵያዊው መጽሐፈ ቀሌምንጦስ፣ የእመቤታችንን ሞት፣ ትንሣኤና እርገት)
የሚናገሩ ስራዎች፣ መጽሐፈ ሄኖክ …

በትምህርተ አበው ውስጥ መማር የሚኖርብን የአበውን ሥራ ብቻ ሳይሆን በዘመናቸው የነበረውን


የቤተክርስቲያን ችግር ከነ ምክንያቱ መረዳት አለብን፡፡ በመሆኑም መናፍቃኑን፣ ሐሳባቸውን፣ ለሐሳባቸው
ምክንያት የሆነውን ነገር እና በክርስትና ውስጥ የሚመለሰው መልስ ለምን አላረካም እንዳላቸው ማየት
አለብን፡፡ ይህንን ስንመለከት ነው፣ የአባቶቻችንን መልስ የምንረዳው፡፡

የዶሴቲስቶች፣ የኢቢዮናይቶች፣ አስተምህሮ ችግር መንስኤ ግኖስቲካውያን ለምን ቁሱን ዓለም ሌላ ፈጣሪ
ፈጠረው ይላሉ፣ ከፊል ግኖስቲካዊ ይዘት ያላቸው በሐዋርያት ስም የተጻፉ ጽሑፎች ውስጥ ያለውን እውነት
እንዴት መለየት ይቻላል፣ በአርጌንስ አስተምህሮ ውስጥ ያለው ስህተት የፍልስፍና ተጽእኖ ያመጣው እንደሆነ፣
የአቡሊናርዮስ፣ የንስጥሮስ፣ የአውጣኪ
ከዛ ባሸገር የቤተክርስቲያን አባቶች ያሳለፉዋቸውን ውጣ ውረዶች፣ የቤተክርስቲያን አባቶች ሆነው ቆይተው
ስለ ቤተክርስቲያን ከነገስታት ጋር ሲታገሉ ቆይተው፣ በዘመናቸው ካሉ ማናፍቃን ጋር ቤተክርስቲያንን ወግነው
ሲከራከሩላት ቆይተው በኋላም ወደ ምንፍቅና የሄዱትን የቤተክርስቲያን ሰዎች ማንነት እና ትምህርት
እንመለከታለን፡፡

አብዛኞቹ የቤተክርስቲያን ሰዎች፣ መናፍቃንን ጨምሮ በተለይ ከኒቂያ ጉባኤ በፊት የነበሩት አባቶች
ሕይወታቸውን በሰማዕትነት እንዳሳለፉ፡፡ በተለይ ከቤተክርስቲያን የተለዩት በቤተክርስቲያን ውስጥ በነበሩበት
ዘመን ያበረከቱት ኦርቶዶክሳዊ ስራዎች እንዳላቸው፣ ከፊሎቹ አሁን ድረስ በሀሰት እንደተወነጁሉ የሚጠቀሱ
ይገኙባቸዋል፡፡ ለምሳሌ ታቲያን፣ ጠርጡለስ፣ አርጌንስ፣ አቡሊናርዮስ፣ አውሳቢዮስ፣ ንስጥሮስ፣ …

በቤተክርስቲያን ውስጥ በተለያየ ምክንያት የሚፈጠሩ ቁርሾዎች ወደ ሚቀጥሉት የቤተክርስቲያን አባቶች


ሕይወት እንዴት እንደሚዛመት እና ለብጥብጥ ምክንያት እንደሚሆን የነገስታት ጣልቃ ገብነት
ቤተክርስቲያንን እንዴት እንደጠቀመ እና እንደጎዳም እናያለን፡፡

የሜሊጢሳውያን ወደ ክርስትና እንዲመለሱ መደረግ፣ የነገስታት ንጉስ ቆስጠንጢኖስን ጨምሮ ከአርዮሳውያን


ጋር የነበራቸው ወዳጅነት፣ ኦርቶዶክሳውያን አባቶች ሲጋዙ አርዮሳውያን በመንበራቸው መቀመጥ፣ የአንዳንድ
አባቶች ከነገስታት ጋር ያላቸው ወዳጅነትነት እና ጠላትነት የፈጠሯቸው ችግሮች ለምሳሌ አውሳብዮሳውያን
ከአትናቴዎስ ጋር፣ ቀጶዶቅያውያን ከእስክንድራውያን ጋር፣ አስክንድራውያን ከአንጾኪያውያን ጋር፣
እስክንድራውያን ከቁስጥንጥንያ ጋር ያላቸው ቅሬታ ታሪካዊ ብቻ ሳይሆን ሃይማኖታዊ ሆኖም የተገለጠበት
ሁኔታ ይታያል፡፡ አንዱ የሌላውን በጥርጣሬ የሚያይበት

ከመጀመሪያው ጀምሮ የኢኣማንያን አስተምህሮ፣ የግኖስቲካውያን አስተምህሮ፣ የአይሁዳውያን፣ እንዲሁም


የፍልስፍና አስተምህሮ ቤተክርስቲያንን እንዴት ሲፈትን እንደነበረ፣ በዚህ ዘመን የነበሩ አባቶች ደግሞ
ክርስትናን ብቻ ሳይሆን የነዚህን ተገዳዳሪ አመለካከቶች አስተምህሮ ጭምር በደንብ መረዳት የግድ አስፈላጊ
እንደነበር አሁንም ለሚነሱ ጥያቄዎችም ሆነ ኑፋቄዎች በመጀመሪያ የነዚህን አባቶች ስራ መመልከት
ከግማሽ መንገድ በላይ እንደመጓዝ እንደሆነ፣ በመቀጠል በዘመናችን ለሚነሱ ሳይናሳዊም ሆነ ምንፍቅናዊ
ጥያቄዎች መጀመሪያ የነሱን አመለካከት መረዳት አስፈላጊ ብቻ ሳይሆን አስገዳጅ እንደሆነ ማወቅ
ይኖርብናል

ለምሳሌ ታቲያን፣ ሔሬኔዎስ እና ጠርጡለስ የግኖስቲካውያንን አስተምህሮ በደንብ የሚያውቁ መሆናቸው፣


አርጌንስ እና የቀጶዶቂያ አባቶች የፍልስፍና አስተምህሮን በደንብ መማራቸው ከሌሎች አባቶች በተሸለ
በዘመናቸው ለነበረው ተቃርኖ የተሸለ መልስ እንዲሰጡ አድርቸዋል፡፡
በመሆኑም የታሪክ መምህራን የቤተክርስቲያን ታሪክ ጸሐፊ የሚባሉትን አባቶች ብቻ ሳይሆን የሁሉንም
አባቶች ስራ ማወቅ እንደሚኖርብን፡፡ በእየአንዳንዱ አባቶች ስራ ውስጥ ታሪክም የሚገለጽ መሆኑን መገንዘብ
ይኖርብናል

ለምሳሌ የአውሳብዮስ የቤተክርስቲያን ታሪክን፣ የሔሬኔዎስን፣ የሶቅራጥስን…በተጨማሪም የቅዱስ


አትናቴዎስ ደብዳቤዎች፣ የቅዱስ ባስልዮስ ደብዳቤዎች የቅዱስ ጎርጎሬዎስ ዘእንዚናዙ እና የቅዱስ ቄርሎስ
ለንጉስ ተቃወሞ የተጻፉ ደብዳቤዎች

የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጓሜ እና ቀኖና አስተማሪዎችም እንደዚሁ በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን አንድምታ ላይ


ብቻ ሳይሆን፣ የተለያዩ ቅዱሳን አባቶች በዘመናቸው የጻፏቸውን የትርጓሜ ስራዎች ማንበብ ተገቢ ነው

ለምሳሌ የአርጌንስ የትርጓሜ ስራዎች በተለይ የዮንስ ወንጌል እስከአሁንም አቻ የማይገኝለት፣ የቅዱስ
ኤፍሬም፣ የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ የቅዱስ ጎርጎሬዎስ ዘኑሲስ፣ የቅዱስ ቄርሎስ፣ የቅዱስ አትናቴዎስ
ትርጓሜዎች፣ እንዲሁም በየጉባኤው እና በየ አባቶች የተደረጉ ቀኖናዎች፣ ለምሳሌ የቅ.አትናቴዎስ መጽሐፍ
ቅዱሳዊ ቀኖና፣ የኒቂያ ጉባኤ ጳጳሳትን ስለመሾም የሚናገረውን ቀኖና መረዳት ዛሬ በቤተክርስቲያናችን
የተፈጠረው ጉድ እንዳይፈጠር ያደርግ ነበር፡፡ ከሀገር ስብከት ሀገረ ስብከት መቀየር፣ ያለ ሲኖዶስ ፈቃድ
ጳጳስ መሾም የተከለከለ መሆኑን

የዶግማ እና የቀኖና መምህራንም፣ በቤተክርስቲያን ያለውን የዶግማ አስተምህሮ ዕድገት፣ ጅማሮ እና አሁን
የደረሰበትን አገላለጽ፣ በየጊዜው ዶግማውን እና የቤተክርስቲያን አስተዳደር እና ሕይወትን ለመጠበቅ
የተደረጉ ቀኖናዊ አስተምህሮዎችን እና ውሳኔዎችን ከአበው ትምህርት መፈተሸ ያስፈልጋል

ዋና ዋና የሚባሉት የቤተክርስቲያን ዶግማዎች በተለይ ሚስጢረ ሥላሤ እና ሚስጢረ ሥጋዌ ለነገረ ድኅነት
ያላቸው ትልቅ ቦታ እና ለመንፈሳዊ ዕድገት ያላቸው ቦታ

የቤተክርስቲያን ሁሉም አስተምህሮ ማለት ይቻላል በየጊዜው እየተብራራ እየተሸሻለ ነው ዛሬ ላይ የደረሰው፣


የዶግማ የበለጠ ግልጽ መኆን፣ የጸሎተ ሃይማኖት በሂደት መሻሻል፣ የካህናት ኃላፊነት፣ የምዕመናን ኃላፊነት
(የስርዓት መጻሕፍት)፣ የቤተክርስቲያን ሚስጢራት አፈጻጸም

ዛሬ ጥያቄ ለሚያነሱ መናፍቃን በተለይ አርዮሳውያን መልስ የሚሆን ስራዎች በ1ኛ እና በ2ኛው ጉባኤ
ጥንቅቅ ብለው መሰራታቸው (የቅዱስ አትናቴዎስ፣ የቀጶዶቂያ አባቶች)
የቤተክርስቲያን ሚስጢራትን፣ ምግባራትንም የምናስተምር ሰዎች፣ የቤተክርስቲያን አባቶችን ሕይወት
መረዳት፣ ወደደረሱበት ማንነት ለማደግ ምን ዐይነት መንፈሳዊ ልምምድ ሲያደርጉ እንደነበር፣ ለእኛም
በዚህ ዘመን እንመራበት ዘንድ እንደምሳሌ ያቆዩልን ስራዎቻቸውን ማየት ተገቢ ነው፡፡

ሚስጢራተ ቤተክርስቲያን ከሐዋርያት ዘመን ጀምሮ እንዴት ይፈጸሙ እንደነበር፣ እንዴት እንደተሻሻሉ፣
በሚሰጢራተ ቤተክርስቲያን ውስጥ ስለሚገኘው ጸጋ፣ ለመንፈሳዊ ዕድገት ያላቸው አስፈላጊነት እና አስተዋጽኦ
በዲድስቅልያ፣ በጠርጡለስ፣ በዮስጢኖስ፣ በቄርሎስ ዘኢየሩሳሌም ስራዎች እና በቅዱስ ጎርጎሬዎስ ዘኑሲስ
ስራዎች ውስጥ ይታያሉ

የሙሴ ሕይወት፣ መሀልይ መሀልይ እና የአቡነ ዘበዘማያት ጸሎቶች ትርጓሜዎች፣ የሐዋርያነ አበው ሕይወት
እና አሟሟት፣ የነ ቅዱስ ጎርጎሬዎስ ዘእንዚናዙ፣ የነ ቅዱስ ኤፍሬም፣ የነ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የእነ
አባ እንጦንስ እና የሎሎች መነኮሳት አባቶች የአርጌንስ ሕይወት ጭምር ለመንፈሳዊነት ያለውን ምሳሌነት
ያስተምራሉ

ባጠቃላይ በቤተክርስቲያን ዘመን ውስጥ እስከዚህ ዘመን ድረስ የተነሱ የቤተክርስቲያን አባቶችን መለስ
ብለን ማየት ለእራሳችን ብቻ ሳይሆን ለሌሎች ሰዎች ጭምር ሊተርፍ በሚችል መንገድ አልፎ ተርፎ በኛ
ዘመን ስለ አበው እና ሥራዎቻቸው የተጻፉ ስራዎችን ማየት ማንበብ ተገቢ ነው፡፡
ነገረ/ትምህርተ አበው
ትምህርቱን በ3/4 ዘመን ከፍለን ለማየት እንሞክራን

➢ ቅድመ ኒቂያ የነበሩ አባቶች


o ሐዋርያነ አበው
o የቤተክርስቲያን ጠበቆች ተብለው የሚጠሩ አበው
➢ ከኒቂያ እስከ ኬልቄዶን የነበሩ ቅዱሳን አበው
➢ ከኬልቄዶን በኋላ የተነሱ አበው
➢ መነኮሳት አበው

ሐዋርያነ አበው (150 ዓ.ም)

በዚህ ዘመን በትምህርተ አበው ሊዳሰሱ የሚገባቸው

➢ በዘመኑ የነበሩ የቤተክርስቲያን ፈተናዎች


o የሮም መንግስት (በቤተክርስቲያን ጠበቆች የተጻፉ ሥራዎች)
o የአይሁድ እምነት
o የአይሁድ ክርስቲያኖች (ኢቢዮናይት)
o የአረማውያን ክርስቲያኖች
▪ ዶሴቲስት
▪ ግኖስቲኮች
➢ ግኖስቲኮች በተለያዩ ሐገር ያሉ አመለካከታቸውም የተለያዩ ብዙ ሲሆኑ (እንደ ዛሬ ፕሮቴስታንት) በአንድ
መሪ የሚመሩ የተበታተኑ ዓይነት አማኞች ናቸው
➢ ሌላው የዚህ ዘመን መለያ እነዚህ ወገኖች መጽሐፍ ቅዱስን በመቃወም የራሳቸው መማሪያ መጻሕፍት
ያዘጋጁ መሆናቸው ነው (የአዲስ ኪዳን አፖክሪፋ እዚህ ውስጥ ይጠቀሳል)

የሐዋርያነ አበው ኃላፊነት

ምዕመናንን ማጽናናት፣ ነገስታትን መቃወም፣ እና በወቅቱ ለነበሩ መናፍቃን ተገቢውን መልስ መስጠት
ቤተክርስቲያን በቀጣይ በተመሳሳይ ችግር እንዳትረበሽ ስርዓት መዘርጋት ዋና ኃላፊነተቻው ነበር፡፡ በመሆኑም
ክርስትና ከዚህ ዘመን ጀምሮ በብዙ ነገሩ ተወልዶ እንደሚያድግ ህጻን የሚድህበት ዘመን ነው ማለት ነው፡፡

ቅዳሴው፣ ሚስጢራተ ቤተክርስቲያን እና አፈጻጸማቸው፣ ዶግማው እና ቀኖናው ‹‹ሀ›› ብሎ በሚገጥመው ፈተና ልክ


እየደረጀ የሚሔድበት አጋጣሚ ነው ሚታየው፡፡

ሐዋርያነ አበው እነማን ናቸው

የሐዋርያት ደቀመዝሙር የነበሩ 7 አባቶች ሲሆኑ በአብዛኛው የጴጥሮስ የዮሐንስ እና የጳውሎስ ደቀመዛሙርት
ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ እነዚህ አባቶች ሌሎች ሐዋርያትን እንዳዩ ይመሰክራሉ፡፡

ከዚህ በተጨማሪ በዚህ ዘመን የተሰሩ ሥራዎች አሉ፡፡

ዲዲስቅልያ

አመክንዮ ዘሐዋርያት

ቅዱስ አግናጢዎስ

ቅዱስ ቀሌምንጦስ
ቅዱስ ፓሊካርፕ

ኖላዊ ሔርማስ

ቅዱስ በርናባስ

ፓፕያስ

ለዲዮግናጠስ የተጻፈ ደብዳበ

ሰማዕቱ ጁስቲኒያን

ታትያስ

ጠርጡለስ

ቅዱስ ሔሬኔዎስ

አርጌንስ

አውሳቢዮስ ዘቂሳርያ

You might also like