You are on page 1of 46

ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

ምዕራፍ ስድስት
፩- የቅዱሳት ሥዕላት ትርጉም፤
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ትምህርተ ሃይማኖት እና ትውፊት ቅዱሳት ሥዕላት
ማለት፤ በአብያተ ክርስቲያናት ግድግዳ፡ በሸራ፡ በብራና፡ በወረቀት እና በመስቀሎች ላይ በቀለም ወይም
በጭረት ባለ ሁለት ጎን (two dimensional) ሆነው የሚሠሩ የልዑል እግዙአብሔርን፡ የእመቤታችንን፡
የቅዱሳን መላዕክትን፡ የጻድቃንን እና የሰማዕታትን ማንነት የሚገልጥ መንፈሳዊ ጥበብ ነው። ሥጋዊውን
ዓለም ከሚያንጸባርቁ መንፈሳዊ መልዕክት ከሌላቸው ሌሎች ሥዕላት ፈጽመው ስለሚለዩ ቅዱሳን
ሥዕላት ይባላሉ።

፪-የቅዱሳት ሥዕላት አመጣጥ፤


፪-፩ በብሉይ ኪዳን
ሥዕል በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ለያ዗ው ቦታ መሠረቱ የሁሉ አስገኝ የሆነው አምላካችን እግዙአብሔር
አስቀድሞ ለነቢዩ ሙሴ ሥዕለ ኪሩብን በሥርየት መክደኛው ታቦት ላይ እንዲያ዗ጋጅ ማ዗ዘ ነው።
ለዙህም መሠረት በ዗ጸ. ም. ፳፭፡ቁ ፳፪ ‚በዙያም ካንተ ጋር እገናኛለሁ የእስራኤልንም ልጆች ታዜዜ ዗ንድ
የምሰጥህን ነገር ሁሉ በምስክሩ ታቦት ላይ ባለው በሁለት ኪሩቤል መካከል በስርየት መክደኛው ላይ ሆኜ
አነጋግርሃለሁ‛ ብሎ መናገሩ ነው። እግዙአብሔርም የተናገረውን የማያስቀር ነውና ሊቀ ነቢያት ሙሴን
በሥዕለ ኪሩብ መካከል ሆኖ ድምጹን አሰምቶታል።
፪-፪ በሐዲስ ኪዳን
ከሐዋርያዊ ተልዕኮውና የሕክምና ሞያው በተጨማሪ የሥዕል ጠቢብ የነበረው ቅዱስ ሉቃስም ምስለ
ፍቁር ወልዳን (እመቤታችን ከልጇ ከወዳጇ ጋር ሆና) በመሳል ለትውልድ አቆይቶልናል። በተጨማሪም
ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ለጢባርዮስ ቄሳር የጌታችንን ሥነ-ስቅለት ሥዕል አ዗ጋጅቶ ሰጥቶታል።

፫- ቅዱሳት ሥዕላት በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን


የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የራሷ የሆነ ፊደል፡ ሥነ ጽሁፍ፡ ዛማ፡ ኪነ ህንፃ… ወ዗ተ
እንዳሏት ሁሉ የራሷ የሆነ የሥነ ሥዕል ጥበብም ያላት ስንዱ እመቤት ናት። ከጥንተ ክርስትና
የአክሱማውያን ዗መን ጀምሮ ሥዕል በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ቦታ እንደነበረው የአርኪዮሎጂ ግኝቶችና
የጥንት አብያተ ክርሰቲያናት ፍርስራሾች ያመለክታሉ። በተለይ በ዗መነ አክሱም ተሠርተው በከፊል
የፈረሱ እና ከመፍረስ የተረፉ እንደ አብርሃ ወአጽብሐ፡ ውቅሮ ቅዱስ ቂርቆስ፡ ደብረ ዳሞ ገዳም፡ መርጡለ
ማርያም፡ ወ዗ተ ያሉት አብያተ ክርስቲያናት የያዞቸው
ሥዕሎች የ዗መኑን የሥዕል ጥበብ አሻራ ያሳያሉ። በተለይ በመካከለኛው መቶ ክፍለ ዗መን የኢትዮጵያ
ቤተ ክርስቲያን የሥዕል ጥበብ ያደገበት ዗መን ነበር። በአሁኑ ወቅት በአብዚኞቹ አብያተ ክርስቲያናት
የምናገኛቸው ሥዕላት በዙህ ዗መን የተሠሩ ናቸው።

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 1


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

፬- የቅዱሳት ሥዕላት ጥቅም፡


፬-፩ ለሥርዓተ አምልኮ
ቅዱሳት ሥዕላት ሰውንና እግዙአብሔርን የሚያገናኙ መንፈሳዊ ሀብቶች ናቸው። በሥዕል ፊት ቆሞ
መጸለይ፡ ወይንም መስገድ ሥዕሉን አምላክ ማድረግ አይደለም። ነገር ግን የሥዕሉን ባለቤት በሥዕሉ ፊት
ሆኖ በመማጸን በረከቱን ለማግኘት የሚፈጸም ሥርዓት ነው። ሥዕሉ ለባለቤቱ መታሰቢያ ነው። ‚የጻድቅ
መታሰቢያ ለበረከት ነው ተብሎ እንደተጻፈ‛ ምሳ. ፲፡፯ የሥዕሉን ባለቤት አቅርቦ ያሳየናል። ገድሉን፣
ተአምራቱንና ቃል ኪዳኑን ያስታውሰናል። በመንፈስም ድልድይ ሆኖ ከሥዕሉ ባለቤት ያገናኘናል።
ሙሴና አሮን ወደ ደብተራ ኦሪት ገብተው በታቦቱና ሥዕለ ኪሩብ ፊት እየሰገዱ ከእግዙአብሔር ትዕዚዜ
ይቀበሉ ነበር ዗ኁ. ፲፮፡፵፭
፬-፪ ለትምህርት
ቅዱሳት ሥዕላት ሲሣሉ የሥዕሉን ባለቤት ዐቢይ ገድልና ተአምራት በሚያጎላ መልኩ ነው። ስለሆነም
ማንኛውም ምእመን የሥዕሉን ባለቤት መንፈሳዊ ተጋድሎ በቀላሉ እንዲረዳ ያደርገዋል። ለምሳሌ የጻድቁ
አባታችን የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ሥዕል ሲሣል ለ22 ዓመታት 8 ጦሮችን ከግራ ከቀኝ ከፊት ከኋላ
አስተክለው ሲጸልዩ አንድ እግራቸው በቁመት ብዚት መቆረጡን እንዲሁም ስለ ቅድስናቸው ከተሰጣቸው
ስድስት የብርሃን ክንፎች ጋር ተደርጎ ይሣላል። ክህነታቸውን ለመግለጽም የእርፍ መስቀልና ጽና ይ዗ው
ይሣላል። የሥዕሉ ባለቤት እንዲታወቅም በሥዕሉ ላይ አጭር የጽሑፍ መግለጫ ይቀመጣል። ‛዗ከመ ጸለየ
አቡነ ተክለሃይማኖት‛ እንዲል። በዙህ ሥዕል ምእመናን የጻድቁን ተጋድሎ ይማሩበታል፤ አርአያም
ያደርጉታል።

 ኦርቶዶክሳዊ የቅዱሳት ሥዕላት አሣሣል


ቅዱሳት ሥዕላት "ቅዱስ" እና "ሥዕላት" ከሚሉት ቃላት የተገናኘ ወይም የተሰናሰለ ቃል ሲሆን፤ሥዕል
በቁሙ፣ መለክ፣ የመልክ ጥላ፣ንድፍ፣አምሳል፣ንድፍ ውኃ፣በመጽሔት፣ በጥልፍ፣በስፌት ወይም በቀለም
በወረቀት ገዜፎ ተጽፎ፤ከእብን ከእፅ ከማዕድን ታንጦ፡ተቀርጦ ተሸልሞ አጊጦ የሚታይ የሚዳሰስ ነገር
ነው።
ዳግመኛም የቅዱሳንን ታሪክና ማንነት በጊዛው ላልነበርን በመንፈስ ዓይን ፤እንድናይ ስለሚያደርጉን፤
አንድም ሥጋዊውን ዓለም ከሚያንጸባርቁ ዓለምውያን ሥዕላት ፈጽመው የተለዩ በመሆናቸው፤አንድም
የቅዱሳኑ ቅድስና ሥዕላቱን ቅዱስ ስላሰኛቸው፤አንድም በሥዕላቱ አድሮ እግዙአብሔር ስለሚፈጽማቸው
ገቢረ ተዓምራት የተነሳ ሥዕላቱ "ቅዱሳት ሥዕላት" ተብለው ይጠራሉ።
ይህ ደግሞ ኦርቶዶክሳዊያን ቅዱሳት ሥዕላት በእግዙአብሔር ፈቃድ ሐዋርያዊ ቀኖናን ተከትለው የሚሳሉ
የቤትክርስቲያን ንዋያተ ቅዱሳት ናቸው እንጂ እንዴው በ዗ፈቀደ የሚ዗ጋጁ የኪነጥበብ ስራወች
አለመሆናቸውን ያስገነዜባል።
የቤተክርስቲያንን ሥላት ልዩ ከሚያደርጓቸው ገጽታወች መካከል አንዱ ትምህርተ ሃይማኖትን ጠብቀው
መሳላቸ ነው።ዓላማቸው ወንጌልን ለመስበክ ለማስተማሪያነት ስለሆነ ሰፊውን ትምህርተ ሃይማኖት
በሥዕል የሚገልጡ መሆን አለባቸው።
ትምምህርተ ሃይማኖትን ያልጠበቁ ሥዕላት ከሆኑ ግን የሚያስተምሩት ትምህርት ኑፋቄ ስለሚሆን
ቤተክርስቲያን አትቀበላቸውም።ለምሳሌ ቅድስት ሥልሴ ሲሳሉ አንድነታቸውና ሦስትነታቸው በሥዕል

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 2


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

ይገለጣል።አንድነታቸውን ለመግለጽ ነደ እሣት የሚሆኑ ኪሩቤል በተሸከሙት አንድ መንበር


እንደተቀመጡ ልብሳቸው ሳይነጣጠል፤ሦስትነታቸውን ዓለምን በቀኝ እጃቸው እንደያዘ ፣የሦስቱም ፊት
ወደ አንድ አቅጣጫ እየተመለከቱ አካላቸው ገጽታቸው በተመጣጣኝ ሁኔታ ይሣላል።
የጌታ ትንሳኤ ሲሳል መግነዜ ፍቱልኝ መቃብር ክፈቱልኝ አለማለቱን ለመግለፅ የተ዗ጋ መቅብር ይታያል።
በትንሳኤው ብርሃን ዓለምን የቀደሰ ነውና ብርሃን ጨለማውን ሲገልጥ የሚያሳይ ተደርጎ ይሳላል።ሆኖም
ግን በአንዳንድ የምዕራባውያን አብያተ ክርስቲያናት ሥዕላት ላይ የምንመለከተው የተከፈተ መቃብር
ወይም መላእክት የመቃብሩን በር ለጌታችን ሲከፍቱለት የሚያሳይ ሥዕል ነው።
ይህም በስልጣኑ አልተነሳም የሚል ትርጓሜን ይሰጣል።ይህ ደግሞ ትምህርተ ሃይማኖትን ስለሚፋልስ
ቤተክርስቲያን አትቀበለውም።በኢትዮዽያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርቲያን ቀኖና መሰረት
የቤተክርስቲያን ቅዱሳት ሥዕላት መልክና ቁመና ሲሣሉ ራሱን የቻለ ህግና ሥርዓት አለው።
ቅዱሳት ሥላት ሲሣሉ በገሀዱ ዓለም የተለመደውን (realistic) የአሣሣል ዗ይቤ አይከተሉም።ምክንያቱም
የሥዕላቱ ዓለማ መንፈሳዊነትን መግለፅና ውክልና (religious symbols) እንጂ እውነተኛ መልካቸው
እንዲህ ነው ለማለት ስለማይሳል ነው።
የሚከብሩት በነፍሳቸው ባገኙት ክብር እንጂ በሥጋቸው ግዜፈትና ርቀት አይድለምና ።ከዙህ በተጨማሪ
ጠይም፣ ጥቁር፣ ነጭ፣ቀይ፣ረጅም፣አጭር፣ወፍራም ወይም ቀጭን ወ዗ተ በሚለው ላይም አያተኩሩም።
የቅዱሳት ሥዕላት ፊት ሲሳል ሰፊና ክብ ተድርጎ ይሳላል።
ሰፊና ክብ መሆኑ የፍጹምነት ምሳሌ አንድም መላ ሕይወታቸውን ለጽሎትና ለተመስጦ እንዳዋሉ
ለመግለጽ ነው።ትልቅ፣ክብና ሰፊ ተደርገው መሳላቸው ለውክልና እንጂ ይህንን ይመስላሉ ለማለት ግን
አይደለም።
ቅዱሳት ሲሣሉ ዓይናቸው ጎላጎላ ተደርጎ ይሣላል።ጎላ ጎላ ማለቱ ክፉውን ከደጉ፣ጨለማውን ከብርሃኑ
ለይተው በተቀደሰው ጎዳና በፍጹም አስተዋይ ልቡና የተጓዘ መሆናቸውን ለማመልከት፤አንድም
ሥጋዊውንና መንፈሳዊውን ፣ረቂቁንና ግዘፉን ዓለም በግልፅ የማየት ጸጋ እንዲሁም ከሰው ልጆች ሕሊንና
አእምሮ በላይ የሆነውን ረቂቅ መለኮታዊ ምስጢር በስፋት በማወቅ አቅምና ጣዕሙን የመረዳት ችሎታ
ከቸሩ አምላክ በልግስና እንደተሰጣቸው እናስተውላለን።
ከዙህ በተጨማሪ ዓይናቸው ጎላ ጎላ ማለቱ የተመልካቹን ምዕመን ልብ ለመሳብ፣ለመመሰጥ፣
የመደመምን ስሜትና ፈሪሃ እግዙአብሔርን ለመፍጠር ይጠቅማል።ዓይኖቻቸው የሚያዩትም ወድ አንድ
አቅጣጫ ብቻ ነው ።ይህም አንዲት መንግስተ ሰማያትን በአይነ ህሊና በመመልከት ለክብር እንደበቁ
ለማመልከት ነው።
ዳግመኛም አንዲት ርትዕት ኦርቶዶክስ ተውህዶ ሃይማኖትን ሳይፈሩና ሳያፍሩ ያለ ጥርጥር ተቀብለውና
መስክረው የኖሩ መሆንቸው እንዲሁም ጥርጥር በልባቸው አለመኖሩን ያጠይቃል።የተረዳች የቀናች
ሃይማኖትን ጥብቀው ያስጠበቁ በክብር ወደ ዗ላለም ርስት ያቀኑ በመሆናቸው ወደ አንድ አቅጣጫ
እየተመለከቱ ይሳላሉ።ዓይን የሰውነት መብራት ናት እንዲል። (ማቴ 6፡22) በሥዕሉ ባለቤት ራስ ዘሪያ ላይ
የምንመለከተው ጸዳለ ብርሃን (አክሊለ ብርሃን) ደግሞ ቤበተክርስቲያናችን የቅድስና ማዕረግ
እንደተሰጣቸው ያጠይቃል።

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 3


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

ነገር ግን በቅድስት ስላሴና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ላይ የሚደረገው ፀዳለ ብርሃን የእግዙአብሔር
ቅድስና የባህርይው መሆኑን እንደሚገልፅ መረዳት ያስፈልጋል።እኔ እግዙአብሔር አምልካችሁ ቅዱስ ነኝና
እናንተም ቅዱሳን ሁኑ እንዲል። (዗ሌ 19፡2፣ 1ዼጥ 1፡15-16)
በአጠቃላይ ሥዕሎቻችን በኪነ ጥበብ ዗ርፍ የተለመደውን የተለያዩ ህዋሳተ አካልን ትክክለኛ መጠን
ላይጠብቁ ይችላሉ።ይህ የሚሆነው ደግሞ ሥዕላቱ ውክልና ሃይማኖታዊ ምልክቶች በመሆናቸው፤
አንድም ሥዕላቱ የሚሳሉት ቅዱሳን ይህንን ይመስላሉ ይህንን ያክላሉ ለማለት አይደለምና ፤አንድም
የሚያስተዋዉቁን ከመንፈሳዊው ዓለምና ጣዕመ ጻጋ ጋር እንጂ ከምድራዊው ዓለም ጋር ባለመሆኑ ነው።
በመሆኑም በቅዱሳት ሥዕላቱ ላይ ሊተላለፍ የተፈለገውን ልዩና ጥልቅ መንፈሳዊ መልክእክት በመረዳት
ተገቢውን አክብሮት መስጠት ይገባል። በቤተክርስቲያናችን ቀኖና መሰረት አብዚኛውን ጊዛ
የምንጠቀማቸው ቀለማት፦ ሰማያዊ፣ቀይ፣አርንጓዴ፣ቢጫና ነጭ ሲሆኑ ቀለማቱ ራሱን የቻለ
ምስጢር ወይም ትርጉም አላቸው ።
1) ሰማያዊ፦ ሰማያዊውን ሃብት ገን዗ብ ለማድረግ በፈቃደ ነፍስ መመራትን ለማመልከት እንዲሁም
በመንፈስ ፍሬወች ፈቃደ ሥጋን በፈቃደ ነፍስ ድል ማድረጋቸውን፤አንድም ትህትናን ያሳያል። ቅዱሳን
በትሕትና ለመኖራቸው ማሳያ ነው ።በመሆኑም ይህ ቀለም መንፈሳችን በእምነት መንገድና በትህትና
የመንፈስ ፍሬዎችን ገን዗ብ በማድረግ እንድንጓዜ ያስታውሰናል።
2) ቀይ፦ ሰማዕትነትን ያሳያል።ይህም ቅዱሳን ነፍሳቸውን ለመከራና ለሞት አሳልፈው ስለክርስቶስና
ስለቤተክርስቲያን ብለው መስጠታቸውን ለማመልከት ይህን ቀለም እንጠቀመዋለን።የመስዋዕትነት የነፃ
አውጭነት ምልክት ነው።ጌታችን በሸንጎ ፊት ቆሞ የለበሰው ልብስ ቀይ ሐር እንደነበር። (ማር 15፡16-17፣
ኢያ2፡18)
3) ቢጫ ፦ ይህ ቀለም እውነተኛነትንና ብርሃንነትን ይገልፃል።እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ እንዲል
(ማቴ5፡14) ከዙህ በመነሳት ቤተክርስቲያን የቅድስና ማዕረግ ላይ የደረሱትን ቅዱሳት እውነተኞችና
የዓለም ብርሃን ናችሁ ስትል በራሳቸው የብርሃን አክሊል በቢጫ አድርጋ ትሥላለች።
4) አረንጓዴ፦ ከልምላሜ ከፀደይ ጋር ስለሚያያዜ መንፈስዊ ትርጉሙ መታደስን አዲስ ሕይወትን፣
ድህነትንና ተስፋን ያሳያል።በዙህ መሰረት አረንጓዴነትና ሕይወት ተወራራሽ ይሆናሉ።
5) ነጭ፦ የድል አድራጊነት የንፅህና እና የፍጹምነት ምሳሌ ነው።ቅዱሳን ዓለምንና ምኞቱን ድል ያደረጉ
ልበ ንጹሃን በመሆናቸው ነጭ ልብስ ለብሰው ይሳላሉ።ነጭ ልብስ ለብሰዋል ፤ከአለቆቹም አንዱ "እነዙህ
ነጫጭ የለበሱት እነማን ናቸው? ከየት መጡ?" አለኝ።እኔም "አቤቱ አንተ ታውቃለህ" አልኩት። እርሱም
"እኒህ ከጽኑ መከራ ነጻ የወጡ ልብሳቸውንም በበጉ ደም አጥበው ያነጹ ናቸው።"አለኝ። መለኮታዊ
ክብርንም ያሳያል።ለምሳሌ በደብረታቦርና በትንሳኤ ሥዕሎች ላይ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነጭ ልብስ
ለብሶ ይሣላል።
በትውፊታዊ አሣሣል ቅዱሳት ሥዕላት ድርሰት ላይ የቅዱሳኑ አቋማቸው (በሥዕሉ ላይ የሚገኝበት
ሥፍራ)የተወሰነ ነው።ለምሳሌ የስነ ስቅለት ሥዕል ከሆነ ጌታችን ቀይ ግልድም አድርጎ፤አንገቱን ወደ ቀኝ
አ዗ንብሎ፤አክሊሊ ሦክ እንደደፋ፤በቀኙ እመቤታችን በግራው ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ሆነው።በእግረ
መስቀሉ አፅመ አዳም እንዲታይ ተደርጎ ይሣላል።
ምስለ ፍቁር ወልዳ ከሆነ ደግሞ እመቤታችን ጌታን ታቅፋ ከተሳለች በኋላ በግራ በቀኝ ቅዱስ ገብር ኤልና
ቅዱስ ሚካኤል ይሣላሉ።ሆኖም ግን ይህ ሁሉም የሥዕል ድርሰት ላይ የቅዱሳን አቋማቸው የተወሰነ ነው

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 4


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

ማለት ግን አይደለም።ስለዙህ ቅዱሳት ሥዕላት ከላይ የተጠቀሱትን ቀኖናን ተከትለው ይሣሉ ዗ንድ
ይገባል።

ምዕራፍ ሰባት
1. ሥርዓተ ጥምቀት
ጥምቀት የሚለውን ቃል አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ሲተረጉሙ ‚ጥምቀት‛ በቁሙ፡- ‚ማጥመቅ፣
መጠመቅ፣ አጠማመቅ፣ ጠመቃ፣ የማጥመቅና የመጠመቅ ሥራ፣ ኅፅበት፣ በጥሩ ውኃ የሚፈጸም‛
በማለት ተርጉመውታል።

ጥምቀት አንድ ምዕመን እንደገና ከመንፈስ ቅዱስ ልደት የሚያገኝበትና የቤተ ክርስቲያን አባል
የሚሆንበት የመጀመሪያው መግቢያ በር ነው። ምሥጢረ ጥምቀትን የመሠረተው ጌታችን አምላካችንና
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።

በዮሐንስ ወንጌል ፫፣ ፭ ላይ ‚እውነት እውነት እልሃለሁ፣ ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ


እግዙአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም። ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ነው፣ ከመንፈስም የተወለደ መንፈስ
ነው። ዳግመኛ ልትወለዱ ያስፈልጋችኋል ስላልሁህ አትደነቅ‛ በማለት የአይሁድ አለቃ ለነበረው ለኒቆዲሞስ
ጌታችን ያስተማረውን ትምህርት ልብ ላለው ጥምቀት በጌታችን ትምህርት መመሥረቷን ይስረዳል።

በሰው ልጅ ዗ላለማዊ ድኅነት ውስጥ ትልቁን ድርሻ የሚይ዗ው ሥርዓተ ጥምቀት ከሌሎቹ ምሥጢራተ
ቤተ ክርስቲያን በቀዳሚነት የሚፈጸምና የማይደገም ሥርዓት ነው። ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ ‚አንዲት
ጥምቀት‛ በማለት የሥርዓተ ጥምቀትን አለመደገም ገልጦ ተናግሯል (ኤፌ.፬፣ ፭)።

በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ተመዜግቦ እንደሚገኘው፥ በቁስጥንጥንያ በ ፫፻፹፩ ዓ.ም. የተሰበሰቡ ፩፻፶
የሃይማኖት አባቶቻችን ‚ወነአምን በአሐቲ ጥምቀት ለሥርየተ ኃጢአት፣ ኃጢአትን በምታስተሠርይ
በአንዲት ጥምቀት እናምናለን‛ በማለት የጥምቀትን አንድ መሆንና ኃጢአትን በደልን የምታርቅ
ስለመሆኗ በእግዙአብሔር መንፈስ ቅዱስ ተመርተው ተናግረዋል፤ ሃይማኖታቸውንም ገልጠዋል።

1. ጌታችን የተጠመቀው ለምንድነው?

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 5


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

የሥርዓተ ጥምቀትን ትርጉምና የመሠረተው ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለመሆኑ በአጭሩ
ከገለጽን፤ ጌታችን የተጠመቀው ለምንድር ነው? የሚል ጥያቄ ቢነሣ ጌታችን እርሱ ባወቀ ጥምቀትን
የፈጸመበት ዋነኛ ምክንያቶች እንደ ሊቃውንት አባቶቻችን አስተምህሮ በሦስት መንገዶች ይታያል።
እነዙህም፦

1) ምሥጢረ ሥላሴን/ሦስትነቱን ያስረዳን ዗ንድ (ማቴ. ፫፣ ፲፫-፲፯)


2) ለትምህርት፡ ለትህትናና ለአርዓያነት (ዮሐ. ፲፫፣ ፩-፲፯ እና ፩ኛ ጴጥ. ፪፣ ፳፮)
3) ጥምቀታችንን ይባርክልን ዗ንድ (ማቴ. ፬፣ ፩-፲) ናቸው።
2. የሰው ልጆች ሥርዓተ ጥምቀት እንዲፈጸምልን የሚያስፈልገው ለምንድነው?
 የልጅነት ጸጋን እናገኝ ዗ንድ፡ ዮሐ. ፩፣ ፭
አስቀድመን በሥጋ ከእናትና አባታችን በ዗ር በሩካቤ እንደተወለድንና የሥጋ ልጅነትን እንዳገኘን ሁሉ
በጥምቀት (በማየ ገቦ ስንጠመቅ) ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ እንወለዳለን። ይህንን አስመልክቶ ጌታችን
‚ከሥጋ የሚወለድ ሥጋ ነው፣ ከመንፈስ የሚወለድ መንፈስ ነው‛ ብሎ ከማስተማሩ በፊት ‚ሰው ዳግመኛ
ካልተወለደ በቀር የእግዙአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም‛ ያለው (ዮሐ. ፫፣ ፫ እና ፮)። በምሥጢረ
ጥምቀት ሀብተ ወልድና ስመ ክርስትና ስለመገኘቱ አስተምሯል።

ሐዋርያውም በጥምቀት ስላገኘነው የልጅነት ጸጋ አስመልክቶ ሲናገር ‚አባ አባት ብለን የምንጮኸበትን
ወይም የምንጣራበትን የልጅነትን መንፈስ ተቀበላችሁ እንጂ እንደገና ለፍርሃት የባርነትን መንፈስ
አልተቀበላችሁምና። የእግዙአብሔር ልጆች መሆናችንን ያ መንፈስ ራሱ ከመንፈስ ጋር ይመሰክራል‛ ብሏል
(ሮሜ.፰፣ ፲፭-፲፮)። ጌታችንንም ለተቀበሉት ሁሉ በስሙም ላመኑበት በጠቅላላው የእግዙአብሔር ልጆች
ይሆኑ ዗ንድ ሥልጣንን ሰጥቷቸዋል። እነርሱም ከእግዙአብሔር ተወለዱ እንጂ ከደም ወይም ከሥጋ ፈቃድ
ወይም ከወንድ ፈቃድ አለመወለዳቸው ተገልጿል (ዮሐ.፩፣ ፩-፲፫)።

 ሥርየተ ኃጢያትን ለማግኘት፡ ሐዋ. ፪፡ ፴፯-፴፰


በጌታችን ትምህርት መሰረት (ዮሐ. ፫፣ ፭) ሰዎች ከነበረባቸው ኃጢአት ይነፁ ዗ንድ እና ወደ እግዙአብሔር
መንግስት ይገቡ ዗ንድ ሥርዓተ ጥምቀት ተሠርታለች። ጌታችን ሞትን ድል አድርጎ በተነሣ በ፶ኛው ቀን
የመንፈስ ቅዱስ ጸጋና ሀብቱ በቅዱሳን ሐዋርያት ላይ ማደሩን የሰሙ አይሁድ ከቅዱሳን ሐዋርየት ዗ንድ
ቀርበው የሚናገሩትን ቃለ እግዙአብሔር መስማት ጀመሩ። ቅዱሳን ሐዋርያትም የጌታችን የኢየሱስ
ክርስቶስን የባሕርይ አምላክነቱን በኃይለ ሥልጣኑ ሞትን ድል አድርጎ መነሣቱንና ወደ ሰማይ ማረጉን
ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 6
ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

ነገሯቸው።አይሁድም ይህንን በሰሙ ጊዛ ልባቸው ተነካ ጴጥሮስንና ሌሎችንም ሐዋርያት ‚ወንድሞች ሆይ


ምን እናድርግ?‛ አሏቸው። ጴጥሮስም ‚ንስሐ ግቡ ኃጢአታችሁም ይሰረይ ዗ንድ እያንዳንዳችሁ በኢየሱስ
ክርስቶስ ስም ተጠመቁ፤ የመንፈስ ቅዱስንም ስጦታ ትቀበላላችሁ‛ አላቸው። ይህ የሐዋርያው ቃል
የሚያስረዳን የጥምቀትን መድኀኒትነት ነው። አስቀድመን እንደገለጥነው አባቶቻችን በሃይማኖት
መግለጫቸው ‚ወነአምን በአሐቲ ጥምቀት ለሥርየተ ኀጢአት፥ ኀጢአትን በምታስተሠርይ በአንዲት
ጥምቀት እናምናለን‛ ማለታቸው ጥምቀት ከደዌ ነፍስ የምታድን መሆኗን መመስከራቸው ነው።

 ዗ላለማዊ ድህነትን እናገኝ ዗ንድ ነው፡ ማር. ፲፮፣ ፲፭-፲፮


የሰው ልጅ ድኅነት ቅጽበታዊ አለመሆኑ የታወቀ ነው። ይሁንና የድኅነት በር ከፋችና ሌሎችን ምሥጢራተ
ቤተ ክርስቲያን ለመፈጸም የሚያበቃን ሚስጢር ጥምቀት ነው። ጥምቀት ለድኅነት አስፈላጊ መሆኑን
ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቅዱሳን ደቀ መዚሙርቱ በሰጣቸው ሐዋርያዊ
መመሪያ ውስጥ በግልጥ ተቀምጧል። ‚ሑሩ ውስተ ኲሉ ዓለም ወስብኩ ወንጌለ ለኲሉ ፍጥረት። ዗አምነ
ወ዗ተጠምቀ ይድኅን ወ዗ሰ ኢአምነ ይደየን። ወደ ዓለም ሂዱ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ። ያመነ
የተጠመቀ ይድናል ያላመነ ግን ይፈረድበታል‛ (ማር. ፲፮፣ ፲፭-፲፮)።

ስለዙህ ጌታችን ባስተማረው መሰረት ማንኛውም ሰው ወደመንግስተ ሰማያት መግባት ይችል ዗ንድ
በሥርዓተ ጥምቀት ከውሃና ከመንፈስ ቅዱስ መወለድና የእግዙአብሔር ልጅ መሆን ይገባዋል። እንግዲህ
እኛ ክርስቲያኖች ሁለት ልደታት እንዳሉን እናስብ። ይኸውም የመጀመሪያው በሥጋ ከእናትና አባታችን
የተወለድነው ሲሆን፤ ሁለተኛው ደግሞ ከእግዙአብሔር የምንወለደው ነው፡፡ ከተወለድን በኋላ እድገታችን
በሁለቱም ወገን መሆን ያስፈልገዋል። ሰው ሥጋዊም መንፈሳዊም ነውና። እንግዲህ በጥምቀት ያገኘነውን
ጸጋና ክብር ሁላችን ልናስብ ያስፈልገናል። ይህንንም ክብራችንን መጠበቅ ያሻናል።

3. የጥምቀት ሥርዓት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያናን


በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ወንድ በተወለደ በአርባ ቀኑ ሴት በተወለደች በሰማንያ ቀኗ የጥምቀት ሥርዓት
ይፈጸምላቸዋል። የህጻኑ ጤንነት የሚያሰጋ ከሆነ ከዙህ ቀን በፊትም ሊፈጸም ይችላል። በችግርና በሌላ
ምክንያት ከተጠቀሰው ቀን ቢ዗ገይ ቤ/ክ የመጡትን ወደኋላ አትመልስም ታጠምቃለች። በ ፵ እና በ ፹
ቀን የሆነበት የመጀመሪያው ምክንያት አዳም በተፈጠረ በ ፵ ቀን ሔዋን በተፈጠረች በ ፹ ቀን ገነት
እንዲገቡ ስለተፈቀደላቸው ነው (ኩፋ ፬፣ ፱)።

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 7


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

ሌላው ደግሞ በኦሪት ሕግ ወንድ በተወለደ በ ፵ ቀን ሴት በ ፹ ቀን ከወላጆቻቸው ጋር ወደ ቤተ መቅደስ


ሄደው ቡራኬ ተቀብለው በርግብና በዋኖስ ደም ተረጭተው ከዕብራውያን መዜገብ ገብተው ይመለሱ
ነበር።

በኦሪት ይደረግ የነበረው ሥርዓት ለሐዲስ ምሳሌ በመሆኑ በዙሁ በኦሪት ልማድ መሰረት ልጆችም
እንደየጾታቸው በ ፵ እና በ ፹ ቀን በመጠመቅ የጸጋ ልጅነት ያገኛሉና ነው (዗ሌ ፲፪፣ ፩=፰፤ ሉቃ ፪፣ ፳፪)።
ሐዋርያትም በአገልግሎት ዗መናቸው የክርስቶስን ትምህርት በመከተል የእድሜ ልዩነት ሳያደርጉ ሕዜብን
ሁሉና በአንድ ቤት የሚገኙ የቤተሰብ አባላትን በሙሉ ያጠምቁ ነበር (የሐዋ ፲፣፴፫ ፤ ፩ቆሮ ፩፣፲፮)

4. የህፃናት ጥምቀት
የሕፃናት የ40 ቀንና የ80 ቀን ጥምቀት ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ለሚስጥረ ጥምቀት አፈጻጸም ብርቱ
ጥንቃቄ ታደረጋለች፡፡ ሰው ሁሉ በጥምቀት አማካኝነት የሚሰጠውን ጸጋ እንዲያገኝ አሰፈላጊውን ጥረት ሁሉ
ትፈጽማለች፡፡ ሰዎች ሳይጠመቁ እንዳይሞቱ በማለት ሕጻናትን የምታጠምቀው በቅዱሳት መጸሕፍት
በተረዳችው መሠረት እንደሆነ ከዙህ ቀጥለን ለማየት እንሞክራለን፡፡

መጽሐፈ ኩፋሌ፡- 4፡9 ከተፈጠረባት ምድር ለአዳም አርባ ቀን ከተፈጸመለት በኃላ ይገዚትም ይጠብቃትም
዗ንድ ወደ ገነት አሰገባው፡፡ ሚስቱንም በሰማንያ ቀን አሰገባት፡፡

ይላልና ለአዳምና ለሔዋን ንጹሕ ጠባይዕ ሳይድፍባቸው ከመንፈስ ቅዱስ የጸጋ ልጅነት ተቀብለው በ40ና
በ80 ቀን ገነት እንድገቡ ዚሬም ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እግዙአብሔር መጀመረያ በሠራው ሥራዓት መሠረት
በአዳም አለመታ዗ዜ ምክንያት የተወሰደውን ልጅነት ለማሰመለሰ ሕጻናት ወንዶችን በ40 ቀን ሕፃናት
ሴቶችን በ80 ቀን ዕድሜያቸው ታጠመቃለች፡፡

1) ሕጻናት የ዗ላለምን ሕይወት እንዲያገኙ ወላጆቻቸውና ቤተ ክርስቲያን የሚሹት ነው፡፡ የሐ ፡- 3፡5 ሰው


ከወኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር የእግዙአብሔርን መንግስት ሊያይ አይችልም፡፡ ስለዙህ ሕጻናት
በወላጆቻቸው እምነት የተነሳ የወላጆቻቸውን እምነት የእነርሱ እምነት በማድረግ ገና በሕጻንነት
ጊዛያቸው ከእግዙአብሔር መንግስት ውጭ እንዳይሆኑ ታጠምቃቸዋለች፡፡ ዳሩ ግን ሳይጠመቁ
ቢሞቱ ጌታ እንደተናገረው መንግስተ ሰማይን አያዩአትም፡፡ እንደ ጌታ ትምህርት የሚንሄድ ከሆነ ሰው
ብሎ ባጠቃላይ ሕጻናትን አዋቂዎችን ሁሉ ጨምሮ ተናገረ እንጂ ከሕጻናት በሰተቀር አላለም፡፡ ሰው
ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር የእግዙአብሔርን መንግስት ሊያይ አይችልም፡፡
2) ሕጻናት በመጠመቃቸው የቤተ ክርስቲያን አባል ስለሚሆኑ የእግዙአብሔር ጸጋ ተካፋዮች ይሆናሉ፡፡ ገና
ከሕጻንነታቸው ጀምሮ የቤተ ክርስቲያንን ሕይወት ይለማመዳሉ፡፡ በዙህ ፈንታ ከሕጻንነታቸው ጊዛ
ጀምረው ከእግዙአብሔር ጸጋ ተራቁተው የሚያድጉ ከሆነ ለመጥፎ ሕይወት ይዳረጋሉ፡፡

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 8


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

3) ለሕጻናት በሚደረግ ጥምቀት መጽሐፍ ቅዱስ አይቃወምም እንደውም ይደግፋል፡፡ ማር ፡- 10፡14


ሕጻናትን ወደ እኔ ይመጡ ዗ንድ ተዉ አትከልክሉአቸው እንዲሁም ጌታችን ያመነ የተጠመቀ ይድናል
ሲል በዙያን ዗መን ገና ወንገል መሰበክ በጀመረበት ላሉት ሰዎች የተነገረ ሲሆን ከክህደታቸውና
ከጥርጥራቸው ተመልሰው የሚመጡ ሁሉ አምነው መጠመቅ እንዳለባቸው የሚያሰገነዜብ ነው፡፡

4) ሕጻናት የእግዙአብሔር ልጆች ሊሆኑ እንደሚገባ ጌታችን ሲገልጽ ማቴ ፡- 19፡14 ሕጻናት ወደ እኔ


ይመጡ ዗ንድ ተዉአቸው አትከልክሏቸው መንግሰተ ሰማያት እንደ እነርሱ ላሉት ናትና ብሏል፡፡ በዙህ
የጌታ ትምህርት መሠረት ቤተ ክርስቲያንም የመሪዋንና የመሥራችዋን የክርስቶስን መርሕ በማድረግ
ወላጆቻቸው ታቅፈው ወደ ቤተ ክርስቲያን ይ዗ው በመምጣት ተጠምቀው የእግዙአብሔር ልጆች
የቤተ ክርስቲያን አባላት እንዲሆኑ ሲያደረጉ እርሷ ከልካይ አትሆንም፡፡ ጌታ ተዉአቸው ይምጡ
ልጅነትን ፤ ጸጋን፤ በረከቱን ያግኙ ብሏልና፡፡ ሕፃናት ንጹሐነ አእምሮ መሆናቸውን ጌታ ሲያሰተምር
እንደ ሕፃናት ካልሆናችሁ መንግሰተ ሰማይ አትገቡም ብሏል፡፡
5) መጽሐፍ ቅዱስ ሕፃናት መጠመቃቸውን ያሰተምረናል፤
 ሐዋ ፡- 16፡33 በእሥር ቤቱ በተደረገው ተአምር የተደነቀውና ወደ ክርስትና እምነት የተሳበው የወኀኒ
ጠባቂ ጳውሎስና ስላስ ካሰተማሩትና ካሳመኑት በኋላ ከነቤተሰቡ መጠመቁ ተገልጾአል፡፡ እንግዲህ
የተሰበከውና ያመነው የወኀኒ ጠባቂው ስሆን የተጠመቁት ግን ሕፃናትን ጨምሮ መላው ቤተሰቡ ነው፡፡
 ሐዋ ፡- 16፡15 ልብዋን ጌታ የከፈተላትና ቃሉን አድምጣ ሕይዋትውን ለክርስቶስ የሰጠችው ልድያ
ባመነች ጊዛ የተጠመቀችው ብቻዋን ሳይሆን ከመላው ቤተሰብዋ ጋር ነው፡፡ ከቤተሰቡ መካከል ሕፃናት
መኖራቸው የማይቀር ነው፡፡
 1ቆሮ ፡- 1፡16 ቅዱስ ጳውሎስ የእስጢፋኖስንም ቤተሰቦች ደግሞ አጥምቄያለሁ በማለት የእስጢፋኖስን
መላ ቤተሰብ ማጥመቁን ገልጾአል፡፡ እንዙህ የእስጢፋኖስ ቤተሰቦች ሁሉ ትልልቆች ብቻ ናቸውን?
ሕጻናት የሉበትም ይሆን?
 ሐዋ.ሥራ 2 ላይ እንደተገለጸው በበዓለ ሃምሳ ከ3000 ያላነሱ ሰዎች በጴጥሮስ ተሰበኩ፡፡ ከእንዙያ
ውስጥ ብዘዎቹ መጠመቃቸው ተገልጸዋል፡፡ የተጠመቁት ግን አዋቂዎች ብቻ መሆናቸውን የሚገልጽ
ቃል የለም፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሕጻናትን ጥምቀት የሚነቅፍ ባንዱም ክፍል ተጽፎ አናገኝም፡፡
እስከ አሁን እንደተገለጸው መጽሐፍ ቅዱስ የሕፃናትን ጥምቀት ያልነቀፈ ሲሆን በብሉይ ኪዳን የጥምቀት
ምሳሌ የነበሩትን ስንመለከት ይበልጥ የሕጻናትን ጥምቀት ትክክልኛነት ያረጋግጡልናል፡፡

ግዜረት የጥምቀት ምሳሌ ነው፡፡ ሕፃናት በተወለዱ በስምነተኛው ቀን ይገረዘ ነበር፡፡ (዗ፍ ፡- 17፡12)፡፡

እንግዲህ ሕፃናቱ የሚገረዘት በወላጆቻቸው እምነት እንጅ እነርሱ ዐውቀው ግረዘን ብለው አይደለም፡፡
የእስራኤል ቀይ ባሕርን ማቋረጥ የጥምቀት ምሳሌ መሆኑ በ1ቆሮ 10፡2 የተገለጸ ስሆን ባሕሩን ያቋረጡት
ዐዋቂዎች ብቻ ሳይሆኑ ሕፃናትም ጭምር ናቸው፡፡ ከባርነት ከፈርዖን አገዚዜ ነፃ የወጡት ሕፃናቱም ጭምር
ናቸው፡፡ እስራኤል ከቡኩረ ሞት የዳኑበት የአንድ አምት ጠቦት በግ ደግሞ ምሳሌነቱ የጌታ መሆኑ የተወቀ
ስሆን በዙያን ጊዛ በበጉ ደም አማካኝነት ከሞት የዳኑት የታ዗ዘትን እሺ ብለው የፈጸሙት ዐዋቂዎች ብቻ
ሳይሆኑ የእነርሱም ልጆቹም ጭምር ናቸው፡፡ እንግዲህ በወላጆቻቸው እምነት ሕፃናቱ መዳናቸውን
ልናሰተውል ይገባል፡፡

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 9


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

ስለዙህ ሕፃናት በአእምሮ ባለበሰሉበትና ስለጥምቀታቸው አምነው ተቀብያዋለሁ ሳይሉ የሚደረገው


ጥምቀት እውነተኛ ጥምቀት አይደለም የሚሉ በእግዙአብሔር ቃል መሠረት ከላይ እንደተገለጸው ሁሉ
መሳሳታቸው የተረጋገጠ ነው፡፡

እግዙአብሔር ሰውን ይመረጣል እንጂ ሰው እግዙአብሔርን አይመርጥም፡፡ ራሱ ባለቤቱ እንዳሰተማረው


ሁሉ እኔ መረጥኋችሁ እንጂ እናንተ አልመረጣችሁኝም ብሏል (ዮሐ. 15፡16)፡፡ ድኀነት በእግዙአብሔር ቸርነት
የሚገኝ እንጂ በሰው ትምህርት እና እውቀት የሚሸመት ወይም የሚገበይ ዕቃ አይደለም፡፡

ስለሆነም ቤተ ክርስቲያናችን ሕፃናትን ማጥመቋ ከመጽሐፍ ቅዱስና ከቀደሙት አበው ባገኘችው ትምህርት
መሠረት ነው፡፡

ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሕጻናትን በ40 እና በ80 ቀን ስታጠምቅ ምስጢራትን፣ ምሳሌዎችን፣


ትውፊትን እንዲሁም የጌታንና የሐዋርያትን አስተምህሮ መሠረት አድርጋ ነው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅም
እንደሚናገረው ቤተ ክርስቲያን ሕጻናትን የምታጠምቀው ኃጢአትበደል አለባቸው ብላ ሳይሆን ከለጋነት
ዕድሜያቸው ጀምረው ፍቅሩን እያጣጣሙ እንዲያድጉ የሚያስችላቸውን የእግዙአብሔር ልጅ የመሆንን
ጸጋ ልትሰጣቸው ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን ሕጻናትን የምታጠምቀው ያውቃሉ ወይም አያውቁም ብላ
አይደለም፡፡ የቤተሰቦቻቸውን እምነትና ፈቃድ ምስክር በማድረግ ነው እንጂ፡፡

1) አዳምና ሔዋን በተፈጠሩ በ40 እና በ80 ቀናቸው ወደ ገነት መግባታቸው (ኩፋ 4፡9)፡፡
2) እስራኤል መስዋዕት ይ዗ው በ40 እና በ80 ቀን ወደ ቤተመቅደስ እንዲመጡ መታ዗ዚቸው (዗ሌ 12፡
1-8)፡፡
3) በኦሪቱ ሕፃናትም አዋቂዎችም ተገር዗ው የተስፋው ወራሾች ነበሩና ይህም የጥምቀት ምሳሌ ነው
(዗ፍ 17፡1-5 ቆላ 2፡11-12)፡፡
4) በባህረ ኤርትራ የተሸገሩት ሕፃናትም ጭምር ነበሩና ይህም የጥምቀት ምሳሌ ነው (1ኛ ቆሮ 10፡1-
2)፡፡
5) ወደ ኖኅ መርከብ የገቡት መላው ቤተሰብ ነውና ይህም የጥምቀት ምሳሌ ነው (዗ፍ 7፡1-17 1ኛ ጴጥ
3፡20-22)፡፡
6) ሕፃናት በማኅፀን ሳሉ መንፈስ ቅዱስ ከሞላባቸው ሲወለዱ እንዳይጠመቁ የሚከለክለቸው ምንድን
ነው (ሉቃ 1፡15 ኤር 1፡4-5)፡፡
7) ሐዋርያትም ካስተማሩ በኋላ ቤተሰቡን ሙሉ ያጠምቁ ነበር (ሐዋ 10፡44-48 11፡13-14 16፡15 16፡
43)፡፡
8) ጌታችንም “ሰው ዳግመኛ ከውኃና ከመንፈስ ቅዱስ ካልተወለደ…” ያለው ሕፃናትንም ይመለከታል
(ዮሐ 3፡8)፡፡
9) ጌታችንም “ሕጻናት ወደ እኔ ይመጡ ዗ንድ አትከልክሏቸው” ብሏል (ማቴ 19፡14)፡፡
በአንዳንዶች ዗ንድ የሕጻናት ጥምቀት ለዳግም ልደት ወይስ ለጥንተ አብሶ ስርየት? የሚል ጥያቄ ይነሳል፡፡
በዙህ ላይ የጥንተ አብሶ ትርጉም ጋር በተያያ዗ የተለያየ አመለካከት አለ፡፡ አንዳንዶች የሕጻናት ጥምቀት
ጥንተ አብሶን ለማጥፋትና ልጅነትን ለማግኘት ነው ይላሉ፡፡ ሌሎች ደግሞ በጥንተ አብሶ ምክንያት
የተጎዳውን የሰውን ባህርይ ለመጠገንና ልጅነትን ለማግኘት ነው ይላሉ፡፡ ሌሎች ደግሞ ጥንተ አብሶ
በክርስቶስ ጠፍቶልናል፤ የሕጻናት ጥምቀት ለዳግም ልደት ብቻ ነው ይላሉ፡፡ በአጠቃላይ ግን ሕጻናት ዳግም
ልደትን ያገኙ ዗ንድ መጠመቅ እንዳለባቸው ሁሉም ይስማማል፡፡

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 10


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

5. የሕጻናት ጥምቀት መብትን ይጋፋልን?


ጥምቀተ ክርስትና ሁል ጊዛ ተጠማቂው ተጠይቆ ላይፈጸም ይችላል፡፡ ይህም የሚሆነው ተጠማቂው ህጻን
የሆነ እንደሆነ ብቻ ነው፡፡ ለህጻናት የሚያስፈልጋቸውን እናደርግላቸዋለን እንጂ ፈቅደዋል (አልፈቀዱም)
በሚል ግብዜነት ተይ዗ን ከጽድቅ ጉዝ እንዲለዩ አናደርግም፡፡ ይሁንና አንዳንዶች የሕጻናትን ጥምቀት
መብተን መጋፋት አስመስለው ባለመረዳት ይናገራሉ፡፡ ለምሳሌ የመጀመሪያው ሰው አዳም የተፈጠረው
የሠላሳ ዓመት ጎልማሳ ሆኖ ነበር፡፡ እግዙአብሔር አዳምን ከፈጠረው በኋላ በአፍንጫው የሕይወት
እስትንፋስን እፍ ብሎበታል፡፡ ይህም እፍታ ለአዳም የልጅነትን ጸጋ ያገኘበት ጥምቀቱ ነበር፡፡ ነገር ግን ይህን
ታሪክ በያ዗ው የኦሪት ዗ፍጥረት መጽሐፍ ላይ እግዙአብሔር ለአዳም የልጅነት ጸጋውን ከመስጠቱ በፊት
እንደ ጠየቀው አይናገርም፡፡ ታዲያ እንዴት የሠላሳ ዓመቱ ጎልማሳ አዳም ያልተጠየቀውን ጥያቄ የአርባ ቀን
ልጅ ጠይቁ ማለት ይቻላል? እግዙአብሔር አዳምን አልጠየቀውም ማለት አስገደደው ማለት አይደለም፡፡ ቤተ
ክርስቲያንም ሕጻናትን በቀጥታ እነርሱን አልጠየቀችም ማለት አስገድዳቸዋለች ማለት አይደለም፡፡ አዳም
የኋላ ኋላ በፈቃዱ ፈጣሪውን ክዶ ልጅነቱን እንዳጣ እንዲሁ የእግዙአብሔርን አባትነት ያልፈለጉትም
አድገውም ቢሆን የመካድ መብታቸው የተጠበቀ ነው፡፡

6. የጥምቀት አፈጻጸም
ተጠማቂው ንዑሰ ክርስቲያን ከሆነ መሠረታዊ የሃይማኖት ትምህርቶችን ተምሮ እምነቱ የተመሰከረለት
መሆን አለበት። ሕጻናት የሆኑ እንደሆኑ ግን ለሕጻናቱ የክርስትና እናትና አባት ሊሆኑ የመጡት ሰዎች
ስለሕጻናቱ እምነት መስክረውላቸው እንዲጠመቁ ይደረጋል። በሚጠመቅበት ጊዛ በውሃ ውስጥ ሶስት ጊዛ
ብቅ ጥልቅ ማለት አለበት ፤ የክርስቶስ ሞትና ትንሳኤ ምሳሌ ነውና። ተጠማቂው የሚጠመቀው በአብ
በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም ነው (ማቴ 28 ፥ 19)። ተጠማቂዎች ባለትዳሮች ከሆኑና ቤተሰብም
ካላቸው ሁሉም ተምረው አምነው በአንድነት መጠመቅ አለባቸው። ከተጠመቀ በኋላ መቁረብ (ቅዱስ
ሥጋውንና ክቡር ደሙን መቀበል) ይገባል። ይህ ካልሆነ ጥምቀቱ ሕያው አይሆንም። እንዲያጠምቁ
ስልጣን ያላቸው ከክህነት ደረጃዎች ውስጥ ኢጲስቆጶስና ቀሳውስት ብቻ ናቸው፡፡ ይህም ጌታችን
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የማጥመቅ ስልጣንን የሰጠው ለአስራ አንዱ ሐዋርያት ብቻ ስለሆነ ነው
(ማቴ 28፡19)፡፡ ዲያቆናት እንዲያጠምቁ አልተፈቀደላቸውም (ማቴ 28፡19 እና ፍት ነገ አንቀጽ 3)።
ክህነት በሌለው ሰው የተከናወነ ጥምቀት እንደ እጥበት እንጂ እንደ ጥምቀት አይቆጠርም፡፡ በዙህ
መንገድ ‚የተጠመቀ‛ ሰው ልጅነት የምታስገኘዋን እውነተኛዋን ጥምቀት መጠመቅ አለበት፡፡

ጥምቀት በመድፈቅ ወይም በመንከር ነው እንጂ በመርጨት (በንዜሐት) አይፈጸምም፡፡ ምሳሌውን፣


ምስጢሩንና ሥርዓቱን ያፋልሳልና፡፡ ጥምቀት ማለት መነከር ማለት ስለሆነ ውኃ ውስጥ ገብቶ
መውጣትን ያመለክታል፡፡ ስለዙህም በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሦስት ጊዛ ውኃ ውስት ገብቶ
በመውጣት ይከናወናል (ማቴ 28፡19)፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስም የተገለጠው በመንከር የተከናወነው ጥምቀት
ነው፡፡ ‚ሰረገላውም ይቆም ዗ንድ አ዗዗፥ ፊልጶስና ጃንደረባው ሁለቱም ወደ ውኃ ወረዱ፥ አጠመቀውም።
ከውኃውም ከወጡ በኋላ የጌታ መንፈስ ፊልጶስን ነጠቀው፤ ጃንደረባውም ሁለተኛ አላየውም፥ ደስ
ብሎት መንገዱን ይሄድ ነበርና (ሐዋ 8፡38-39)‛ በሚለው ቃል ውስጥ ‚ከውኃ ከወጡ በኋላ‛
የሚለው የሚያመለክተው ጃንደረባው የተጠመቀው ውኃ ውስጥ ገብቶ እንደነበር ነው፡፡ ‚እንግዲህ
ክርስቶስ በአብ ክብር ከሙታን እንደ ተነሣ እንዲሁ እኛም በአዲስ ሕይወት እንድንመላለስ፥ ከሞቱ ጋር
አንድ እንሆን ዗ንድ በጥምቀት ከእርሱ ጋር ተቀበርን። ሞቱንም በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር
ከተባበርን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ደግሞ ከእርሱ ጋር እንተባበራለን (ሮሜ 6፡4-5 ቆላ 2፡

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 11


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

12)‛ በሚለው ቃል ውስጥ መቀበር መቃብር ውስጥ መግባትን፣ ትንሣኤ ደግሞ ከመቃብር መውጣትን
እንደሚያመለክት ጥምቀትም በውኃ ውስጥ ገብቶ (በመነከር) መውጣትን ይጠይቃል፡፡

በአራቱም ወንጌላት የጌታችን ጥምቀትም በውኃ ውስጥ ገብቶ በመውጣት መሆኑ ተጽፏል፡፡ ‚ኢየሱስም
ከተጠመቀ በኋላ ወዲያው ከውኃ ወጣ፤ እነሆም፥ ሰማያት ተከፈቱ የእግዙአብሔርም መንፈስ እንደ
ርግብ ሲወርድ በእርሱ ላይም ሲመጣ አየ (ማቴ 3፡16)‛ በሚለው ቃል ውስጥ ‚ከውኃ ወጣ‛ የሚለው
የጌታችን ጥምቀት የተከናወነው በመነከር እንደነበር ያሳያል፡፡ በተጨማሪም በሥጋ መወለድ በእናት
ማኅፀን ውስጥ ቆይቶ መውጣትን የሚያመለክት እንደሆነ ሁሉ ‚ከውኃና ከመንፈስ ቅዱስ መወለድም‛
እንዲሁ ውኃ ውስጥ ገብቶ መውጣትን (መነከርን) ይጠይቃል፡፡ ስለዙህም ነው ጥምቀት ‚ዳግመኛ
መወለድ‛ የተባለው (ዮሐ 3፡3)፡፡ ዋና ዋናዎቹ የምሥጢረ ጥምቀት አፈጻጸም ሥርዓትን የሚመለከቱ
ነጥቦች ከዙህ በታች የተ዗ረ዗ሩት ናቸው፡፡

1) ንዑሰ ክርስቲያን የሚጠመቁት የትንሣኤ ዕለት ከሆነ ተገቢውን ትምህርት ቀድመው ተምረውና
ንስሐ ገብተው በሰሙነ ሕማማት ሐሙስ ልብሳቸውን አ዗ጋጅተውና ሰውነታቸውን ታጥበው በመጾም
ቅዳሜ ሌሊቱን እሑድ ይጠመቃሉ፡፡ በሌላ ቀን ከሆነ ደግሞ በዋዛማው ታጥበውና ጾመው ይ዗ጋጁና
የመቁረቢያ ልብሳቸውን በንጽሕና አ዗ጋጅተው በዕለቱ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሔደው ይጠመቃሉ፡፡
2) ኤጲስ ቆጶሱ (ቄሱ) የሚጠመቁትን ሰብስቦ ራሳቸውን ወደ ምሥራቅ እንዲያ዗ነብሉ ያዚቸዋል፡፡
እጁንም በላያቸው ዗ርግቶ ይጸልይላቸዋል፡፡
3) መሐላውን አስምሎ ማለትም ሰይጣንን አስክዶና ክርስቶስን አሳምኖ ከፈጸመ በኋላ በዐራቱም
መዓ዗ን ለአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሰግዶ በፊታቸው ላይ እፍ ይልባቸዋል፡፡ አካላቸውንም
አማትቦ ይባርካል፡፡
4) ጥምቀቱ በትንሣኤ ከሆነ በዶሮ ጩኸት ጊዛ፤ በሌላ ቀንም ከሆነ መጠመቂያው ሰዓት ሲደርስ
ተጠማቂዎችን በመካነ ጥምቀቱ ያቆማቸዋል፡፡ ያውም ካልሆነ ካህኑ ማዩን እንደ ገበቴ በተሰራ ብርት
አድርጎ ሥርዓተ ጸሎቱን ያደርሳል፡፡
5) ከሰይጣን ቁራኝነት በሚለይበት በቅብዓ ቅዱሱ ላይ ጸልዮ ለተራዳኢው ቄስ ይሰጥና ከተጠማቂዎች
በስተግራ ያቆመዋል፡፡
6) ልጅነት በሚያሰጠውና መንፈስ ቅዱስን በሚያሳድረው በሜሮኑ ላይ ይጸልይና ለሁለተኛው ቄስ
ሰጥቶ ከተጠማቂዎች በስተቀኝ ያቆመዋል፡፡
7) ተጠማቂዎችን በማ዗ዜ ፊታቸውን ከምሥራቅ ወደ ምዕራብ፤ ከምዕራብ ወደ ምሥራቅ
ይመልሳቸውና በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ማመናቸውን ያረጋግጣል::
8) አንዱ ቄስ የተጠማቂዎችን እጅ እየያ዗ ሕፃናትም ከሆኑ ዲያቆኑ (ቄሱ) አቅፎ ከምዕራብ ወደ
ምሥራቅ ይመልሳቸዋል፡፡ ይህም ሰይጣንን ክደው በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ማመናቸውን በምሳሌ የሚያረጋግጥበት መንገድ ነው፡፡ ምዕራብ የማኅደረ ዲያብሎስ ምሥራቅም
የማኅደረ ሥላሴ ምሳሌዎች ናቸውና፡፡ (ነጽሩ ውስተ ጽባሕ….)
9) ከዙህ በኋላ ቅብዐ ቅዱሱን ቀብቶ ያጠምቃቸዋል፡፡ ሲያጠምቃቸውም ልብሳቸውንና ማንኛውንም ጌጣ
ጌጥ አውልቀውና ሴቶችም ሹርባቸውን ፈትተው ነው፡፡ ከዙያም በመጠመቂያው ፫ ጊዛ ብቅ ጥልቅ
ያደርጋቸዋል፡፡ ምቹ መጠመቂያ ከሌለም ማዩን በላያቸው ላይ ሦስት ጊዛ እያፈሰሰ በአብ በወልድ
በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠምቅሃለሁ/ሻለሁ/፤ እያለ ያጠምቃቸዋል፡፡ ከመጠመቂያው በወጡም ጊዛ
በንፍሐት ልጅነትን ያሳድርባቸዋል፡፡
10) ሴት በምትጠመቅበት ዕለት የወር አበባ (ግዳጅ) ከመጣባት እስክትነጻ ሳትጠመቅ ትቆያለች፡

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 12


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

11) ተጠማቂዎች መናገር ከቻሉ ራሳቸው፤ ካልቻሉም የክርስትና አባት (እናት) የሆኑት ክርስቲያኖች
የተጠማቂውን አውራ ጣት ይ዗ው ጸሎተ ሃይማኖትን በማንበብ ሃይማኖታቸውን ይመሰክራሉ፡፡
12) ሥርዓተ ቅዳሴውን አድርሰው፣ መጽሐፈ ክርስትናውን ደግመው ማዩን ከባረኩ በኋላ ነው ማጥመቅ
የሚጀምሩት፡፡ የ፵ እና የ፹ ቀን ሕፃናት ከተጠመቁ በኋላ ንዑሰ ክርስቲያን ወንዶችና ሴቶች
ይጠመቃሉ፡፡በሚያጠምቁበትም ጊዛ ‚አጠምቀከ/ኪ በስመ አብ፣ አጠምቀከ/ኪ በስመ ወልድ፣
አጠምቀከ/ኪ በስመ መንፈስ ቅዱስ፤ ስምከ/ኪ ይኩን እገሌ/ሊት‛ በማለት ሲሆን አስቀድመው
መስቀል ግንባሩ ላይ አድርገው የሰየሙትን ስመ ክርስትና የሚያጸኑት በዙያው ሰዓት ነው ማለት
ነው፡፡
13) ከተጠመቁ በኋላ ካህኑ ሜሮን ይቀባቸዋል፡፡ የተ዗ጋጀላቸውን ነጭ ልብስ ለብሰው ቅዳሴ አስቀድሰው
ሥጋውን ደሙን ይቀበላሉ፡፡ በሜሮን ከከበሩም በኋላ ሦስት ኅብረ ቀለማት ያሉት ማተብ
ይታሰርላቸዋል፡፡ ኅብረ ቀለማቱም ነጭ፣ ቀይ፣ ጥቁር(ቢጫ) ናቸው፡፡ ምሳሌነት አለው በአንድ
መገመዱ የሥላሴን አንደነት ሦስተ መሆኑ……
14) የክርስትና አባት/እናት አብረው ጾመውና ተገቢውን ዜግጅት አድርገው በዕለቱ ሥጋውን ደሙን
ይቀበላሉ፡፡
15) በዕለቱ ክርስትና የተነሡ (የተጠመቁ) ሕፃናትና ንዑሰ ክርስቲያን የነበሩ አዳዲስ የቤተ ክርስቲያን ልጆች
ከሌሎች ቆራብያን አስቀድመው ቅዱሱን ቊርባን ይቀበላሉ፡፡
16) ወንዶች ሴቶችን፣ ሴቶችም ወንዶችን ክርስትና አያነሡም፡፡
17) የምትጠመቀዋ ንዑሰ ክርስቲያን ሴት ከሆነች ቅብዓ ቅዱሱንም ሆነ ሜሮኑን ኤጲስ ቆጶሱ/ቄሱ/ ልብስ
እንደለበሰች ከአንገት በላይ ከቀባት በኋላ ዓይኑን ተሸፍኖ ወይም በመጋረጃ ተጋርዶ ዲያቆናዊት
ማለትም ዕድሜዋ የገፋ ከስልሳ ዓመት በላይ የሆነችና የምታገለግል መነኩሲት እጁን ይዚ እየመራቸው
ሌሎቹን ሕዋሳት ይቀባታል፡፡
18) የተጠማቂዎችን ራስ የሚያጠልቅ ማይ (ውኃ) በቤተ ክርስቲያን የማይገኝ ከሆነ ማዩን በእጁ እየታፈነ
(እየ዗ገነ) በሥላሴ ስም ያጥምቃቸዋል፡፡

7.ይህ ሥርዓት ለምን በውሃ ይፈጸማል?


‹‹ከክፉ ሕሊና ለመነጻት ልባችንን ተረጭተን፣ ሰውነታችንንም በጥሩ ውኃ ታጥበን፣ በተረዳንበት እምነት
በቅን ልብ እንቅረብ›› (ዕብ.10÷22)፡፡
 ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተጠመቀው በውኃ ነው እኛም እርሱን አብነት በማድረግ በውኃ
ልንጠመቅ ይገባናል (ማቴ.3÷13-16)፡፡
 ጌታችን ለኒቆዲሞስ ‹‹እውነት እውነት እልሃለሁ ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ
እግዙአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም›› ስላለ እኛም የጌታን ትእዚዜ ለመፈጸም በውኃ
እንጠመቃለን (ዮሐ.3÷5)፡፡
 ሐዋርያት ከጌታ በተማሩት መሠረት ያጠመቁት በውኃ ነው፡፡ ጴጥሮስም መልሶ ‹‹እነዙህ
እንደ እኛ ደግሞ መንፈስ ቅዱስን የተቀበሉ እንዳይጠመቁ ውኃን ይከለክላቸው ዗ንድ
የሚችል ማን ነው? አለ›› (የሐዋ.10÷46ና 47)፡፡ ፊልጶስና ጃንደረባው ሁለቱም ወደ ውኃ
ወረዱ አጠመቃቸውም (የሐዋ.8÷28)፡፡
 ውኃ የሰውነትን እድፍ እንደሚያጠራ ሁሉ እንዲሁም ጥምቀት የነፍስን እድፍ ያስወግዳል

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 13


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

 ውኃ መልክን ያሳያል እኛም በመጠመቅ የሥላሴን ምሥጢር በዓይነ ኅሊናችን እናያለን፡፡


 ለንጊኖስ የተባለው ሐራዊ (ወታደር) የጌታን ቀኝ ጎን በጦር በወጋው ጊዛ ትኩስ ደምና ውኃ
ባንድነት ፈሷል (ዮሐ. 19÷34)፡፡ ደሙ ለመጠጣችን፣ ውኃው ለጥምቀታችን መሆኑን
ሲያጠይቅ ነው፡፡ ይህንንም ፍቁረ እግዙእ ዮሐንስ እንዲህ ሲል ገልጾታል ‹‹በውኃና በደም የመጣ
ይህ ነው፡፡ እርሱም ኢየሱስ ክርስቶስ በውኃና በደሙ እንጂ በውኃው ብቻ አይደለም፡፡
የሚመሰክሩት መንፈሱና ውኃው ደሙም እንጂ በውኃው ብቻ አይደለም፡፡ የሚመሰክሩተ
መንፈሱና ውኃው ደሙም ሦስት ናቸውና፡፡ ሦስቱም በአንድ ይስማማሉ›› (1ዮሐ.5÷6-8)፡፡
 ውኃ በሁሉም ቤት ይገኛል፡፡ በሀብታሙም በድኃውም ጥምቀትም ላመነ ሁሉ የተፈቀደ መሆኑን
ለማጠየቅ በውኃ ሆኗል፡፡ ስለዙህም በውኃ ብቻ እንጠመቃለን፡፡ ሥርዓተ ጥምቀቱን የሚፈጽመው
ካህን አሐዱ አብ ቅዱስ፣ አሐዱ ወልድ ቅዱስ፣ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ ብሎ በእግዙአብሔር
ቃል ሲባርከው ውኃው ተለውጦ በዕለተ ዓርብ ከጌታችን ቀኝ ጐን የፈሰሰውን ውኃ ይሆናል፡፡

8.የዉኃና የመንፈስ ኅብረት


ኅብረታቸዉ የተከሰተዉ ዓለም በተፈጠረ በመጀመሪያዉ ቀን ነዉ፡፡ ዗ፍ 1÷2 ‚የእግዙአብሔር
መንፈስ በዉኃዉ ላይ ሰፍሮ ነበር‛ በዉኃዉ ላይ መስፈፉ ፀጋ መንፈስ ቅዱስ በዉኃ (ጥምቀት)
ለ዗መነ ሐዲስ ሰዎች የሚሰጥ መሆኑን ለማሳየት ነበር፡፡ ሳዊሮስ ዗አንጾኪያ ‚በጥበብ በሥርዓት ስለ እኛ
ከተፈጸመዉ ከዙህ ስራ (ከጥምቀት) አስቀድሞ መንፈስ ቅዱስም በዉኃ ላይ ይሰፍፍ ነበር‛ ሃይማኖተ
አበዉ 87÷16፣ ሕዜ 36÷25-26 ‚ጥሩም ዉኃም እረጭባችኃለሁ እናንተም ትጠራላችሁ
ከርኩሰታችሁም ሁሉ ከሐጢያታችሁም ሁሉ አጠራችኃለሁ አዲስም ልብ እሰጣቹኋለሁ አዲስም
መንፈስ ለዉስጣችሁ አኖራለሁ፡፡‛

2. ሥርዓተ ሜሮን
ቅብዐ ሜሮን በዋነኛ ምሥጢራዊ አገልግሎቱ ከምሥጢረ ጥምቀት አፈጻጸም አይለይም፡፡ በእኛ
በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት ከላይ እንደገለጥነው የሜሮን አቀባብ ወዲያ ከጥምቀት አያይዝ
ይፈጸማል፡፡
ይህም ማለት ተጠማቂው ሰው ጥምቀት ከተፈጸመለት በኋላ ሳይውል ሳያድር ወዲያውኑ ጥምቀቱን
እንደተቀበለ ሜሮን ይቀባል፡፡ ሜሮን ሲቀባም በመንፈስ ቅዱስ መጠመቁን፣ ከውኃና ከመንፈስ ቅዱስ
መወለዱንን፣ መንፈስ ቅዱስን እንዳደረበት ይረጋገጥለታል፡፤ ተጠማቂው ተጠምቆ ሜሮን መቀባቱ
መንፈስ ቅዱስን መቀበሉን ያመለክታል፡፡
የአቀባቡም ሥርዓት የተጠመቀው ሕጻን እንደኾነ በክርስትና ዋሱ እቅፍ እንዳለ ይቀባል፡፡ አዋቂ እንደኾነ
ከማጥመቂያው ወጥቶ እንደቆመ ቄሱ ሜሮኑን በአውራ ጣቱ እየጠለፈ ‚እቀብአከ በስመ አብ ወወልድ
ወመንፈስ ቅዱስ እያለ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም በትዕምርተ መስቀለ ያትመዋል፡፡

 በመጀመሪያ ግንባሩን ያትመዋል አዕምሮው የተባረከ እንዲኾን ግራ ቀኝ አይኖቹን ያትመዋል ዓይኖቹ


የእግዙአብሔርን እውነት እንዲያዩ፣ ግራ ቀኝ ጆሮቹን ያትመዋል ጆሮዎቹ የእዙአብሔርን ቃል

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 14


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

እንዲሰሙ፣ አፉን ከናፍሩን ያትመዋል፣ እውነት እንዲናገር የእግዙአብሔርን ጥበብ እንዲማር፣


ደረቱን ያትመዋል፡፡ ልቡ ቅን እንዲያስብ፣ ግራ ቀኝ እጆቹን ይቀባዋል፡፡ እጆቹ ለመልካም ሥራ
እንዲፋጠኑ፣ ግራ ቀኝ እግሮቹን ይቀባዋል እግሮቹ ወደ መልካም ሥራ እንዲፋጠኑ፡፡ በአጠቃላይ መላ
ሰውነቱን ይቀባዋል በኋላ ሰውነቱ የእግዙአብሔር ማደሪያ እንዲሆን፡፡
በዕለተ ጥምቀት ሜሮን በጳጳሳት ከተባረከ በኋላ ለአገልግሎት የተሰየመው ቄስ በእጁ ይዝ ይጸልይበታል፡፡
መጽሐፈ ክርስትናንም ይደግማል (ያነባል):: የተጠማቂውን ፴፮ ሕዋሳት በታ዗዗ው መሠረት ክፍል
ክፍሉን እየለየ ይቀባል፡፡

ቅብዐ ሜሮኑን በአውራ ጣቱ እየጠቀሰ (እያስነካ) በትእምርተ መስቀል አምሳል እቀብዐከ በስመ አብ
ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ እያለ ተጠማቂውን ይቀባዋል፡፡ በሥርዓተ ጥምቀት እንደገለጽነው ንዑሰ
ክርስቲያን ሴት ከሆነች ልብስ ለብሳ ከአንገቷ በላይ ኤጲስ ቆጶሱ (ቄሱ) ይቀባታል፡፡ በኋላም ከአንገት በታች
ያሉትን ቀሪ ሕዋሳት ጳጳሱ ወይም ቄሱ ተጋርዶ (ተሸፍኖ) ዲያቆናዊት የቄሱን እጅ ይዚ እየመራች ይቀባታል፡
፡ የተጠማቂው ፴፮ቱ ሕዋሳት በሜሮን ሲከብሩ በሥርዓተ ቤተክርስቲያን የአቀባባቸው ቅደም ተከተል
የታወቀ ነው፡፡ ከላይ እንደገለጽነው ሁሉም በትእምርተ መስቀል አምሳል የሚታተሙ (የሚቀቡ) ናቸው።

 ግንባሩን ግራና ቀኝ ሁለት ቦታ ይቀባና በፊቱ ላይ እፍ ይልበታል


 ሁለቱን የአፍንጫ በሮች፣
 ሁለቱን ከናፍር፣
 ሁለቱን ጆሮዎች፣
 ሁለቱን ዓይኖች፣
 ደረቱን፣
 ልቡን፣
 ከመሐል አናት እስከ ወገብ ያለውን አካል፣
 መሐል ጀርባውን፣
 እንብርቱን፣
 ሁለቱን እጆች፣
 የእጆቹን መገናኛዎች፣
 ትከሻዎቹን፣
 ማጅራቱን፣
 አንገቱን፣
 ክርኖቹን፣
 የእጆቹን ውጪያዊ ክፍሎች (መዳፎች)፣
 የእጆቹን ውስጣዊ ክፍሎች (መዳፎች)፣

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 15


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

 የእግር መገናኛዎቹን (መዳፎች)፣


 ጉልበቶቹን፣
 የእግሮቹን ውጪያዊ ክፍሎች (ጣቶች)፣
 የእግሮቹን ውስጣዊ ክፍሎች (ጣቶች)፣
በድምሩ 36 ሕዋሳት ይሆናሉ፡፡ እነዙህን ሕዋሳት በቅደም ተከተል ከቀባ በኋላ በተጠማቂው ላይ እጁን
ጭኖ ‚በሰማያውያን በረከት የተባረክህ ሁን‛ እያለ ይባርከዋል፡፡ ሠላሳ ስድስቱ የተጠማቂው ሕዋሳት በዙህ
መልክ በቅብዐ ማሮን ታትመው የእግዙአብሔር ገን዗ቦች (ማደሪያዎች) ይሆናሉ፡፡ ከተጠማቂዎች ሌላ
ቅብዐ ሜሮን ለሁለት ምሥጢራት ማክበሪያነት (ማተሚያነት) ያገለግላል፡፡ እነዙህም ምሥጢረ ክህነትና
ምሥጢረ ተክሊል ናቸው፡፡ በምሥጢረ ክህነት ካህናት ከቄሱ ጀምሮ ወደ ላይ ያሉት ማለትም ጳጳስና ቄስ
በቅብዐ ሜሮን ከብረው ካህናተ እግዙአብሔር ይሆናሉ፡፡ ይህም በብሉይ ኪዳን ‚እኔንም በክህነት
እንዲያገለግሉኝ ትቀድሳቸው ዗ንድ የምታደርግላቸው ነገር ይህ ነው፤ የቅብዐትንም ዗ይት ወስደህ በራሱ
ላይ ታፈሰዋለህ፤ ትቀባውማለህ፡፡ ልጆቹንም ታቆርባቸዋለህ፤ ቀሚሶችንም ታለብሳቸዋለህ፤
በመታጠቂያም ታስታጥቃቸዋለህ፤ ቆብንም ታደርግላቸዋለህ፤ ለ዗ለዓለም ሥርዓትም ክህነት
ይሆንላቸዋል፡፡ እንዲሁም የአሮንና የልጆቹን እጆች ትቀባቸዋለህ፡፡

3. ሥርዓተ ቁርባን
ቁርባን የሚለው ቃል መሠረቱ ከዕብራይስጥ ቋንቋ የመጣ ሲሆን ‚ስጦታ‛ የሚል ትርጉም ይኖረዋል፡፡
ከምሥጢራት አንዱ መሆኑ ሕብስቱ ተለውጦ የክርስቶስ ሥጋ ጽዋው ተለውጦ የክርስቶስ ደም ሲሆን
አይታይም፡፡ ነገር ግን እምነት ያለው ሁሉ በእምነት መነጽር ይመለከተዋል፡፡ ይህም ማለት እንደ ኦሪቱ
ቁርባን ሰው ለእግዙአብሔር ያቀረበውን ስጦታ ብቻ የሚያመለክት ሳይሆን እግዙአብሔርም በተለየ
ሁኔታ ለሰዎች ደኅንነት ለዓለም ሁሉ የሰጠውን በሥጋና በደም የመጣውን የልጁን ስጦታ ያስገነዜባል።

ስለዙህም ለዓለም መድኃኒት ሆኖ የተሰጠው በጸሎተ ኀሙስ ማታ ወደ ጌታ ሥጋና ደም


የተለወጠው ኅብስትና ወይን ዚሬም በጸሎተ ቅዳሴ የጌታን ሥጋና ደም ሆኖ የሚቀርበው ቅዱስ ቁርባን
ይባላል። እርሱም ከእግዙአብሔር የተሰጠ የተቀደሰ ስጦታና መሥዋዕት ነው።
 የምሥጢረ ቁርባን አገልግሎት
የምሥጢራተ ቤተክርስቲያንና የአገልግሎቶች ሁሉ የማረጋገጫ ማኅተም ነው፡፡ ይህም ማለት
ማንኛውም ምሥጢር በቤተክርስቲያን ከተፈጸመ በኋላ በምሥጢረ ቊርባን ካልተፈጸመ (ካልታተመ)
የቤተ ክርስቲያን ምሥጢር ሊባል አይችልም፡፡ በተጨማሪም በቤተክርስቲያን የሚከናወኑ አገልግሎቶች
ሁሉ ማለትም ማኅሌቱ፣ ሰዓታቱ፣ መዜሙሩ፣ ቅኔው፣ ኪዳኑና የመሳሰሉት ሁሉ ፍጻሜያቸውን
የሚያገኙት በቅዳሴ ነው፡፡ ቅዳሴውም የምሥጢረ ቊርባን መክበሪያ የጸሎታት ሁሉ ቁንጮ የሆነ፤
የምስጋናና የጸሎት ሥርዓት ነው፡፡

ቁርባን ማለት በአንድ በኩል ለእግዙአብሔር የሚቀርበውን መሥዋዕት በሌላ በኩል ደግሞ እኛ ወደ

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 16


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

እግዙአብሔር የምንቀርብበትን፣ የምንቀራረብበትንና የምንዋሐድበትን ሁኔታ ያሳየናል። ልንቀርብና


የመለኮታዊውንም ጸጋ ተሳታፊ ልንሆን የምንችለው በምሥጢረ ቁርባን አማካኝነት ኅብስቱና ወይኑ
ወደ ክርስቶስ ሥጋና ደም ተለውጦ ስንቀበለው ነውና ምሥጢር መሆኑን ከዙህ ላይ እናስተውላለን።
ሥጋውና ደሙ የተሰጠን በነፃ ያለ ዋጋ ሳይገባን በችሮታ ነውና፡፡

መስዋዕት ማቅረብ የተጀመረው በአዳም ጊዛ ሲሆን ከአዳም እስከ ሙሴ የተነሱ አበው ሁሉ በህገ ልቦና
ለእግዙአብሔር መስዋት ይሰው ቁርባን ያቀርቡ ነበር፡፡ መስዋዕታቸው ከእንሰሳ ቁርባናቸው ከእህልና
ከአትክልት ማለት ከስንዴ እህል፣ ከወይን ፍሬ የሚቀርብ ነው፡፡

዗መነ ኦሪት በብሉይ ኪዳን በሙክራብ የተሰዋ እንሰሳት ሁሉ በአዲስ ኪዳን በቤተክርስቲያን ለሚሰዋው
ሁሉ የክርስቶስ ሥጋና ደም ምሳሌ ነበር፡፡ መልከ ጼዴቅ ያበረከተው ኅብስተ አኮቴት ጽዋዐ በረከት
ለአምላክ የሥጋውና የደሙ ምሳሌ ሆነው አልፈዋል፡፡ በሐዲስ ኪዳን ግን አማናዊው ቊርባን
(መሥዋዕት) ሰዎች የሚያቀርቡት (የሚሰጡት) መባዕ ሳይሆን መድኃኔዓለም ክርስቶስ ዓለሙን ለማዳን
በቀራንዮ ዐደባባይ በአባቱ ፈቃድ፣ በመንፈስ ቅዱስ ፈቃድ፣ በራሱም ፈቃድ በመስቀል ላይ ለዓለሙ ሁሉ
ያቀረበው (የሰጠው) ቅዱስ ሥጋውና ክቡር ደሙ ነው፡፡
 የምሥጢረ ቁርባን አመሠራረት
ምሥጢረ ቁርባንን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሕማማቱና ከሞቱ በፊት በዋዛማው ኀሙስ ማታ
መሥርቶታል፡፡ ይህም ሰዓት በአይሁድ የቀን አቆጣጠር ወደ ዓርብ ይታሰባል። መጀመሪያ የሥጋውና
የደሙን ምሥጢር ሲያሳይ እንዲህ ነበር ዓልአዚር በተባለው ሰው ቤት ጌታችን ከደቀ መዚሙርቱ ጋር
መጀመሪያ የኦሪትን መሥዋዕት ሠውቶ በልቷል።

ወዲያው የበሉትን የኦሪት መሥዋዕት በተአምራት ከሆዳቸው አጥፍቶ ሰዎች ለእራት ካመጡለት ኅብስት
አንዱን አንሥቶ ያ዗ና ወደ አባቱ ጸለየ። ኅብስቱንም በሥልጣኑ ለውጦ ሥጋውን አድርጎ ይህ ስለ እናንተ
የሚሰጥ ሥጋዬ ነውና እንኩ ብሉ ብሎ ለደቀ መዚሙርቱ ሰጣቸው መታሰቢያዬንም ይህ አድርጉት ብሎም
አስተማራቸው። ቀጥሎም ወይን በጽዋ ቀድቶ ያ዗ና ጸለየ ወይኑንም ለውጦ ደሙ አድርጎ ይህ ስለእናንተ
የሚፈስ ደሜ ነው እንኩ ጠጡ ብሎ ሰጣቸው፤ ሉቃ. ፳፪፥ ፲፱–፳ ማቴ. ፳፮፥ ፳፮ ማር. ፲፬፥ ፳፪
የኦሪትን መሥዋዕት አሳልፎ መሥዋዕተ ወንጌልን መሥርቷል።
በዙያችም ምሽት የኦሪቱን በግ መሥዋዕትነት አበቃ፤ ከእንግዲህ ወዲህ እውነተኛው የእግዙአብሔር በግ
ይሠዋል። እርሱም የክርስቶስ ሥጋና ደም ነው። ስለዙህ በማዕዱ ዘሪያ ለተሰበሰቡት ሐዋርያቱ በብሉይ
ኪዳን ምሳሌ የተመሰለለትን: ትንቢት የተነገረለትን አዲሱን ቃል ኪዳን ጌታ በራሱ ሥጋና ደም መሠረተ።
‚ኢየሱስ እንጀራና ኅብስትን አንስቶ ባረከ። ቆርሶ ለደቀመዚሙርቱ ሰጠና እንካቹ ብሉ፤ ይህ ሥጋዬ ነው
አለ። ጽዋንም አንሥቶ አመስግኖም ሰጣቸው። እንዲህም አለ ሁላችሁም ከእርሱ ጠጡ፤ ስለ
ብዘዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው‛ በማለት ምሥጢረ ቁርባንን
መሠረተ /ማቴ ፳፮፣፳፮-፳፰/።

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 17


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

ኪዳን ማለት ከእግዙአብሔር ጋር የምንገባው ቃል ኪዳን የሚያመለክት ነው። ‚እውነት እውነት እላችኋለሁ
እውነተኛ እንጀራ ከሰማይ የሚሰጣችሁ አባቴ ነው እንጂ ከሰማይ እንጀራ የሰጣችሁ ሙሴ አይደለም፤
የእግዙአብሔር እንጀራ ከሰማይ የሚወርድ ለዓለምም ሕይወትን የሚሰጥ ነውና አላቸው። ዮሐ. ፮፥
፴፪–፴፫ በመቀጠልም ሥጋዬ እውነተኛ መብል ደሜም እውነተኛ መጠጥ ነውና። ሥጋዬን የሚበላ
ደሜንም የሚጠጣ በእኔ ይኖራል እኔም በእርሱ እኖራለሁ።

ሕያው አብ እንደ ላከኝ እኔም ከአብ የተነሣ ሕያው እንደምሆን፥ እንዲሁ የሚበላኝ ደግሞ ከእኔ የተነሣ
ሕያው ይሆናል። ከሰማይ የወረደ እንጀራ ይህ ነው፤ አባቶቻችሁ መና በልተው እንደ ሞቱ አይደለም፤ ይህን
እንጀራ የሚበላ ለ዗ላለም ይኖራል፡፡ ዮሐ. ፮፥ ፶፭–፶፰ ጌታችን ይህን ነገር በቃሉ
ሲነግራቸው መጀመሪያ ለሰሙት ሰዎች በሥራ እስኪያሳያቸው ድረስ ሊታመን የማይችል ረቂቅ ነገር ነበር።

ኋላ ግን ሠርቶ ባሳያቸው ጊዛ ተረድተው አምነውበታል። በዕለተ ዓርብ የቆረሰውን ሥጋ፣ ያፈሰሰውንም


ደም አስቀድሞ በዋዛማው ኅብስቱንና ወይኑን ለውጦ ኅብስቱን ፲፫ ቦታ ፈትቶ (ቆራርሶ)፣ አብነት
ለመሆንና ለማስደፈር ራሱ በራሱ እጅ ተቀብሎ ለቀደ መዚሙርቱ አቀበላቸው፡፡ በመስቀል ላይ ለአንዴና
ለ዗ለዓለሙ የፈጸመው ይህ አምላካዊ የማዳን ሥራ እስከምጽአት ድረስ ለዓለሙ ሁሉ በሥርዓተ ቅዳሴ
ከብሮ እንዲታደልም (እንዲዳረስም) ሐዋርያት አባቶቻችንን አ዗ዚቸው፡፡

የምሥራቹን ቃል እንዲያስተምሩ፣ በስሙ ሥርየተ ኃጢአትን እንዲሰጡና ሌሎች ምሥጢራትንም


እንዲፈጽሙ የሚያስችል ሥልጣነ ክህነትን ሰጣቸው፡፡ (ማቴ. ፳፰፥፲፱-፳፡፡ ሉቃ. ፳፪፥፲፬-፳፤ ፳፬፥፵፬-፶፡፡
፩ቆሮ. ፲፩፥፳፫-፳፯፡፡) በዙሁ መሠረትም ሐዋርያት ቃሉን አስተምረው ካሳመኑ በኋላ እያጠመቁና
በአንብሮተ እድ መንፈስ ቅዱስን እያሳደሩ ምሥጢረ ቁርባንን እየፈጸሙ በማቁረብ ተተኪዎቻቸውንም
በዙሁ ሥርዓት በማጽናት ቤተ ክርስቲያንን እንዲህ በማስፋፋት ኖሩ፡፡ የዙህ ሥልጣን አገልግሎትና
ሓላፊነት ባለቤትም ቅድስት ቤተክርስቲያን ብቻ ናት፡፡ ይህንንም አውቃ ስትፈጽመው ኖራለች፤
እየፈጸመችም ትገኛለች፤ እስከ ዕለተ ምጽአት ድረስም ስትፈጽመው ትኖራለች፡፡

4. ሥርዓተ ቅዳሴ
ቅዳሴ ማለት መቅስ፣አቀዳደስ፣ቀደሰ፣ቡራኬ፣ምስጋና የቁርባን ጸሎት ማለት ነዉ፡፡ ከምስጢረ ቁርባን ጋር
የተያያ዗ ሲሆን ለሌሎች ምስጢራትመ የሚስጢርነታቸዉ ማረጋገጫ ማኅተም ነዉ፡፡ምክንያቱም ያለሥጋ
ወዳሙ ምስጢራቱ ምሉዕ ሊሆኑ አይችሉምና፡፡
 ሥርዓተ ቅዳሴ ሦስት ክፍሎች አሉት
1. የዝግጅት (ግባተ መንጦላዕት) ፡- የሚቀርበዉ ጸሎት ከመጋረጃ ዉጭ በመቀረደስ አፍኣ
የሚጸለይ ነዉ፡፡ ሚመጠን ግርምት ዚቲ ዕለት እስከሚለዉ የሚያካትት ነዉ፡፡ የዜግያ ልዑካኑና
(ሰሞነኞቹን) ብቻ የሚመለከት ነዉ፡፡

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 18


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

2. የንባብ(የትምህርት) ቅዳሴ፡- ምዕመናንንም የሚያሳትፍ ነዉ፡፡ የመጽሐፈ ቅዳሴ ምንባባት


የሚቀርቡበትና ትምህርተ ወንጌልም የሚሰጥበት ነዉ፡፡
3. ፍሬ ቅዳሴ፡- የሥርዓተ ቅዳሴ የመጨረሻ ክፍል ነዉ፡፡ ሕብስቱና ሥጋ ወደሙ የሚለወጥበትን ጊዛ
የሚመለከት ጸሎትና ቡራኬ የያ዗ ነዉ፡፡
 ለማስቀደስ ከመሄድ አስቀድሞ የሚደረግ ዝግጅት
1ኛቆሮ 14÷40 "ሁሉም ነገር በአግባብና በሥርዓት ይሁን" ስለ ሆነም ወደ ቅድስት ቤተ- ክርስቲያን
በተለይ በዕለተ ሰንበት፣ በዐብይት በዓላት፣ በቅዱሳን ክብረ በዓላትና በ዗መነ ጾም፡ ቅዳሴ ማስቀደስ፣
ቁርባን ለመቁረብ፣ ከጸሎተ ቅዳሴዉ በረከትን ለማግኘት ቅድሰት ቤተ- ክርስቲያን ስንመጣ
 የሕሊና ዝግጅት፡-
ወደ እግዙአብሔር ፊት ስንቀርብ በጎ ሕሊና እንዲኖረን ያደርጋል፡፡ ሮሜ 13÷5 ምሳ 23÷26 ‚ልጅ ሆይ
ልብህን ስጠኝ‛ ስድስቱን ዕለታት በሥራ የባከነዉን ልቡናችንን ስብስብ አድርጎ ማሳረፉና ወደ ቤተ-
መቅደስ ልቡናችንን ሕሊና ሰብስበን እንዴት መግባት እንዳለብን መክ 5÷1 "ወደ ቤተ-ክርስቲያን በገባህ
ጊዛ እግርህን ጠብቅ" ሐሳባችንን ለመሰብሰብ የሚረዱን፡- 2ኛ ጢሞ 3÷12-16"የእግዙአብሔር ሰዉ
ለፍጹምና ለበጎ ሥራ ሁሉ የተ዗ጋጀ ይሆን ዗ንድ የእግዙአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ
ለትምህርትና ለተግሳጽ ልብን ለማቅናት ለጽድቅም ላለዉ ምክር ደግሞ ይጠቅማል፡፡" ከዙህ የምንረዳዉ፡-

 ቅዱሳት መጽሐፍትን ማንበብ፡፡ ሮሜ 15÷4-5


 መንፈሳዊ መልዕክት ያላቸዉን ኦርቶዶክሳዊ መዜሙሮችን ማድመጥ ፍጹም እምነት
የሚገኘዉ ቃለ እግዙአብሔርን በመስማት ስለሆነ፡፡ ሮሜ" እምነት ከመስማት ነዉ
መስማትም በእግዙአብሄር ቃል ነዉ"
 መንፈሳዊ ፊልሞችን መመልከት፡፡ ምሳ 4÷25 "ዓይኖችህ የቀና ነገርን ይመልከቱ"
 የሰዉነታችንን ንጽሕና መጠበቅ፡-
ተፈጥሮአዊ አካላችን ጥሩ ጠረን እንዲኖረዉ ሰዉነታችንን በሰንበት ዋዛማ በመታጠብ ያስፈልጋል፡፡
ወደ እግዙአብሔር ለመቅረብ የሻቱ ሕዜበ እስራኤልን ሙሴ እንዲህ ብሎ እንዲ዗ጋጁ እንዳ዗ዚቸዉ፡- ዗ፀ
15÷19 "ሰዉነታችዉን አነጹ ሕዜቡም ልብሳቸዉን አጠቡ፡፡" የካልሲያችንን የጫማችንን ንጽህና መጠበቅ
እንደ ግዴታ አድርገን መዉሰድ፡፡
"መሰናከያ ለሚያመጣ ለዙያ ሰዉ ወየዉለት" ማቴ 18÷17 መንፈሳዊ አለባበስ ስርዓትን መጠበቅ፡-
የሰዉነታችንን ንጽህና ከመጠበቅ ጋር የአለባበስ ሥርዓትን መጠበቅ የገባል፡፡ ቅዱስ ያዕቆብ የቅድስት
ቤተ-ክርስቲያን አምሳል ወደ ምትሆን ወደ ቤቴል መሥዋዕት ይሠጥ ዗ንድ ትዕዚዜ በደረሰዉ ጊዛ
ቤተሰቡን፡- "ንጽሕ ሁኑ ልብሳችሁንም ለዉጡ" ዗ፍ 35÷2፣ ዗ዳ 32÷7 "አባትህን ጠይቀዉ እርሱ
ይነግርሃል" ለምድራዊ ሰርግ ተራ ልብስ ለብሰን ብንሄድ እንኳን ከበሬታ አናገኝም ምክንያቱም አክብሮ
የጠራንን ቤተሰብ አልመሰልንምና፡፡ ማቴ 22÷12 ቤተ-ክርስቲያን መንፈሳዊ ተድላ፣ደስታ የምንቋደስባት
ናትና ነቀፋ የሌለበት የመርዓዊ ንጉስሥ ክርስቶስ ንጽሕት የሰርግ ቤት ስለሆነች ነጠላ፣ጋቢያችንን
በመስቀሊያ አጣፍተን ከፈጣሪያችን ፊት በሰማያዉያን አምሳል ለምስጋና ቢቆም ለእግዙአብሔርም ክብር

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 19


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

ነዉ ለአስቀዳሾችም ሞገስ ነዉ፡፡


 ለቅዳሴ ሲሄዱ ሊለበሱ የማየገባቸዉ፡-
ማንኛቸዉም የሌሊት ልብስ፣ ለሠርግ ለተለያዩ ጥሪዎች የሚለበሱ አልባሳት፣ የሰዉነታችንን የአካል ቅርጽ
አጉልተዉ የሚያሳዩ ልብሶች

 በምንጣፍ አንድ ከመሆን መታቀብ፡-


በዕለቱ (ሌሊት) ለነፍስ ፈቃድ ሥጋን ማስገዚት፡፡ ምሳ 12÷13 "ለሰዉ የከበረ ሃብት ትጋቱ ነዉ" በተራክቦ
የደከመና የዚለ አዕምሮ የዝ ወደ ቤተ መቅደስ መግባት አይገባም፡፡ 1ኛ ቆሮ 7÷5 "ለጸሎት ትተጉ ዗ንድ
ተስማምታችሁ ለጊዛዉ ካልሆነ በስተቀር እርስበርሳችሁ አትከላከሉ፡፡" ፍት. ነገ 24÷7
"እግዙአብሔርን ለማገልገል ከሆነ ግን በምንጣፍ በአልጋ አንድ ከመሆን (የአካል ተዋሕዶ) ከመፈጸም
መጠበቅ አለብን፡፡"
 ወርሃዊ ልማደ አንስት በተከሰት ጊዜ መታቀብ፡-
ፍት. ነገ አንቀጽ 5631 "እናቶችና እህቶች ወርሃዊ ልማደ አንስት በተከሠተ ጊዛ ወደ ቅድስት ቤተ-ክርስቲያን
ዉስጥ በመግባት ራስን ማብቃትና ለጸሎት ለቅዳሴ እንዲሁም ሥርዓተ አምልኮ ለመፈጸም ራስን
ማ዗ጋጀት አግባብ አየደለም፡፡" ልማደ አንስት እንደ ብሉይ ኪዳኑ መርገም አይደለም፡፡

"ዲያቢሎስ ያሳሳታት ሔዋንን ነጻ አወጣት" (የሰኞ ዉዳሴ ማርያም) "ሔዋን ከመርገመ ሥጋ ከመርገመ
ነፍስ ነፃ ካደረጋት ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋዉን ክብሩን
እንዳይነሳን ለምኝልን አዕምሮዉን ጥበቡን ሣይብን አሳድሪብን" ቅዱስ ኤፍሬም በቅዳሴ ጊዛ የሚስቅ
ሰው ቅዱስ ባስልዮስ በጻፈው በ፸፪ኛው አንቀጽ ካህን ቢሆን የሚያቀብል ነውና ሥጋ ወደሙን ከተቀበለና
ካቀበለ በኋላ ወጥቶ አንድ ሱባዔ ይቀጣ ይጹም ይስገድ፣ የሳቀው ሕዜባዊ ቢሆን ግን ሥጋ ወደሙን
ሳይቀበል ያን ጊዛ ፈጥኖ ይውጣ ይላል።

ምነው ፍርድ አበላለጠ ካህኑን ተቀብሎ ወጥቶ ይቀጣ አለ፤ ሕዜባዊውን ሳይቀበል ወጥቶ ይሂድ
አለ ቢሉ ካህኑ የሚቆመው ከውስጥ ነው ሲስቅ የሚያየው የለም። ካህኑ በቅዳሴ ጊዛ ቅዳሴውን ጥሎ
ወጥቶ ሲሄድ ባዩት ጊዛ ቄስ እገሌ አባ እገሌ በመሥዋዕቱ ምን አይተውበታል ብለው መሥዋዕቱን
ሳይቀር ይጠራጠሩታል፤ ስለዙህ ነው። ምዕመኑ ግን ሲስቅ ሁሉ ያየዋልና ለሌላ መቀጣጫ እንዲሆን፤
በቤተ መቅደስ የማይወደድ ሌላ ነገር አይናገር፤ በቤተ መቅደስ ጭንቅ፣ ደዌ ሳያገኘው አንዱን
ስንኳ ምራቁን እንትፍ አይበል። ነገር ግን ደዌ ቢያስጨንቀው ድምፅ ሳያሰማ ምራቁን በመሐረቡ
ተቀብሎ ያሽሸው።

 በቅዳሴ ጊዜ ስለሚደረጉና ሰለማይደረጉ ሥርዓት


በቤተ ክርስቲያንና በቅዳሴ ጊዛ ማንም ማን ዋዚ ፈዚዚ ነገር የሚናገር አይኑር፣ ቤተ ክርስቲያን በፈሪሃ

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 20


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

እግዙአብሔር ሆነው የሚጸልዩባት የጸሎት ቦታ ናትና ቅዳሴው ሳይፈጸም አቋርጦ መውጣት አይቻልም፣
አይፈቀድም፣ በጣም ጭንቅ ምክንያት ወይም በሕመም ምክንያት ከሆን ግን ክቡር ወንጌል ከተነበበ
በኋላ ሊወጣ ይችላል።
በቅዳሴ ጊዛ ካህናት የሚቀድሱባቸው አልባሳት ነጫጭ ይሁን ነጭ ልብስ ደስ እንዲያሰኝ በሥጋ ወደሙ
የተገኘ ክብርም ደስ ያሰኛልና፣ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ባህርየ መለኮቱን በገለጸ ጊዛ ልብሱ እንደበረድ
ነጭ ሆኗል። መላእክትም ወርኃ ሰላም ወርኃ ፍስሐ ነው ሲሉ የልደት፣ የትንሣኤ፣ የዕርገት ነጫጭ
ልብስ ለብሰው ታይተዋል።

አንድ ሰው እንኳ ጫማ አድርጎ ከቤተ መቅደስ አይግባ ልዑል እግዙአብሔር የምትቆምባት ደብረ ሲና
የከበረች ናትና ጫማህን አውልቅ ብሎ ለሙሴ ተነግሮታልና። /዗ጸአት ፫-፭/። በቅዳሴ ጊዛ ተሰጥዖውን
የማያውቅ ደግሞ በአንክሮ፣ በተ዗ክሮ፣ በአንቃእድዎ፣ በንጹሕ ልቡና፣ በሰቂለ ሕሊና ሆኖ ሕሊናው
ወደ ዓለማዊ እንዳይወስደው መቆጣጠር አለበት።

ቅዱስ ወንጌል ከተነበበ በኋላ ካህኑ ለሕዜቡ ተርጉሞ ይንገራቸው ያስተምራቸው እጁንም በሚታጠብበት
ጊዛ የተጣላችሁ ሳትታረቁ፣ የሰው ገን዗ብ የወሰዳችሁትን ሳትመልሱ ሥጋ ወደሙን ብትቀበሉ ሥጋው
እሳት ሆኖ ይፈጃችኋል ደሙ ባህር ሆኖ ያሰጥማችኋል። ነገር ግን የወሰዳችሁትን የሰው ገን዗ብ
መልሳችሁ፣ ከተጣላችሁት ታርቃችሁ ኃጢአት ብትሰሩ ንስሐ ገብታችሁ ብትቀበሉት ግን መድኃኒተ
ሥጋ መድኃኒተ ነፍስ ይሆናችኋል። በረከተ ሥጋውን በረከተ ነፍሱን ያድላችኋል ብሎ ይንገራቸው
ያስተምራቸው ይላል።
ካህኑ ሥጋ ወደሙን በፈተተበት እጁ ሕዜቡን ፊታቸውን ይባርካቸው። ቀሳውስት ግን እጅ በእጅ
ተያይ዗ው እርስ በርሳቸው ይባረኩ።
 ቀዳሹ ካህን ቀሳውስትን ሲያሳልም ‚የጴጥሮስ ሥልጣን ባንተ አለ‛ ይበል፣ ተሳላሚው ቄስም
‚መንግሥተ ሰማያት ያውርስህ ከሾመ አይሻርህ‛ ይበል።
 ለዲያቆናትም ‚ልዑል እግዙአብሔር ያክብርህ ይባርክህ፣ ለማስተማር ዓይነ ልቡናህን
ያብራልህ፣ ምሥጢሩን ይግለጥልህ‛ እያለ ይባርካቸው።
 ለምዕመናንም ‚ልዑል እግዙአብሔር ያክብርህ፣ ይባርክህ፣ ገጸ ረድኤቱን ይግለጽልህ‛ እያለ
ይባርካቸው። ለሴቶችም ‚ልዑል እግዙአብሔር ይባርክሽ፣ ያክብርሽ ገጸ ረድኤቱን ይግለጽልሽ‛ ብሎ
በእጁ ይባርክ።
 ከቅዱስ ቁርባን በፊትና በኋላ መደረግ ሥላለበት ሥርዓት
በጥምቀት ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ ከማኅፀነ ዮርዳኖስ ዳግም ተወልደን መንግስተ ሰማያትን ለመውረስ
/ዮሐ.3፥5/ የተ዗ጋጀን ክርስቲያኖች ሕያዋን እንሆን ዗ንድ ዗ወትር መንፈሳዊውን መብል ቅዱስ ሥጋውንና
ክቡር ደሙን መቀበል አለብን። ዮሐ.6፥26።
ሥጋዊ መብልና መጠጥ ዗ወትር እንደሚያሻን ሁሉ አምላካችንንም ዗ወትር እንድንሻው ቅዱስ ሥጋውንና
ክቡር ደሙን በሚበላና በሚጠጣ ሰጥቶናል። ዮሐ.6፥3 ስለዙህም ምዕመናን ዗ወትር ከቅዱስ ሥጋውና
ከክቡር ደሙ የተለየ ሕይወት ሊኖረን አይገባም።

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 21


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በቀዳማዊ ቆሮንቶስ መልዕክቱ 11፥26 ሳይገባው ይህን እንጀራ የበላ ወይም
የጌታን ጽዋ የጠጣ ሁሉ የጌታ ሥጋና ደም አለበት ሰው ግን ራሱን ይፈትን እንዲሁም ከእንጀራው ይብላ
ከጽዋውም ይጠጣ ሳይገባ የሚበላና የሚጠጣ የጌታን ሥጋ ስለማይለይ ለራሱ ፍርድ ይበላልና
ይጠጣልምና። በማለት እንዴት ወደ ቅዱስ ቁርባኑ መቅረብ እንዳለብን ተናግሯል። ወደ ቅዱስ ሥጋው
ክቡር ደሙ ቅድመ ቁርባን ጊዛ ቁርባንና ድኅረ ቁርባን ልንፈፅመው የሚገባውን ሥርዓት ማወቅ ተገቢ
በመሆኑ በሦስት ከፍለን እንመለከታለን።
 ቅድመ ቁርባን መደረግ ያለበት ሥርዓት
ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን ከምንቀበልበት ሰዓት አስቀድሞ ባሉት ዐሥራ ስምንት ሰዓታት።
ልንፈፅመው የሚገባውን ሥርዓት ያሳያል።
በቅድመ ቁርባን የማፈፀሙ ሥርዓቶች፦
ከሩካቤ ሥጋ መከልከል፦ ቀዳሲያንና ሥጋውንደሙን የሚቀበሉ ምዕመናን በጋብቻ ተወስነው የሚኖሩ
ከሆነ ሥጋ ወደሙን ከመቀበላቸው ሦስት ቀናት አስቀድሞ ከሩካቤ ሥጋ መከልከል አለባቸው። "ጋብቻ
ክቡር መኝታውም ንፁሕ" /ዕብ 13፥4/ እንዳለ በሕግ የሆነ ሩካቤ ኃጢአት ሆኖ አይደለም።

ካህኑ /አቀባዩ/ ክርስቶስን መስለው ምዕመኑም /ተቀባዩም/ ሐዋርያትን መስሎ የሚቀርብ በመሆኑ ነው።
አንድም በመሰረቱ ግብሩ የሥጋ እንደመሆኑ መጠን ስለሚቀበሉት ምስጢር ክብር መንፈሳዊ ጥንቃቄ
ለማድረግ ነው።በንስሐ መታደስ፦ የሚያቀብሉና የሚቀበሉ ሰዎች ከንስሐ አባታቸው ጋር በመመካከርና
የንስሐ አባታቸውን ፈቃድ ማግኘት አለባቸው። የበደሉትን ሳይክሱ፣ የወደዱትን ሳይመልሱ፣ ከቂም
ከበቀል ሳይነጹ፣ ክፉ ኅሊናን ሳያርቁ ወደ ሥጋወደሙ መቅረብ አይገባቸውም።
ለዐሥራ ስምንት ሰዓታት መጾም፦ ጌታ በምሴተ ሐሙስ በሦስት ሰዓት በአይሁድ ጭፍሮች ተይዝ እስከ
አርብ 9 ሰዓት ድረስ ያለውን ጊዛ በማሰብ 18 ሰዓታት የተመገቡት ከሆዳቸው ጠፍቶ ለአፋቸው ምረት፣
ለሆዳቸው ባዶነት እስኪሰማቸው እንዲጾሙ ቤተክርስቲያን ታስተምራለች።
"ጴጥሮስ በሁለተኛው ቀሌምንጦስ በ46ኛው አንቀጽ ጠንቅቆ ሳይጾም ማንም ማን ሥጋ ወደሙን
አይቀበል። ከወንዶችም ከሴቶችም ወገን ማንም ምን የቀመሰ ቢኖር፣ ከቀመሰ በኋላ ሥጋውን ደሙን
ቢቀበል፣ ተደፋፍሮ ይህንን ቢያደርግ ለ዗ለዓለም ከምዕመናን በውግ዗ት ይለይ።"
ለመቀበል በተ዗ጋጁበት ዕለት ሰውነትን አለመታጠብ ፡- ምክንያቱም ሲታጠቡ ውኃ ወደ አፍ በቀላሉ
ሊገባ ስለሚችል ነው። በተመሳሳይ ሁኔታ ጥርስ መፋቅም መድማትን ሊያስከትል ይችላል። ስለዙህ
ሰውነትን መታጠቡ፣ ጥርስ መፋቁ፣ ጢም መላጨቱ ከመቀበሉ 18 ሰዓት በፊት ማድረግ፣
የሚለብሱትን ልብስ ንጹሕ አድርጎ ማ዗ጋጀት ይገባል።

ሥጋ ወደሙን ለመቀበል በየማዕረጋቸው ተሰልፈው የሚቀርቡ ምእመናን እጃቸውን በትእምርተ መስቀል


አመሳቅለው፣ ምእመናን ደግሞ ክንብንባቸውን ገልጠው ሊቀርቡ ይገባል። ይህም ትምህርተ ትህትና ነው።
ሐዋርያት በመጀመርያው ቀሌምንጦስ በ23ኛው ሠለስቱ ምእት በኒቅያ በጻፉት መጻሕፍት በ17ኛ
አንቀጽ...‹ወይ዗ምሩ በጊዛ ተመጥዎ ቁርባን ኵሎሙ ምእመናን ሁሉ ቅዱስ ሥሉስን ይጸልዩ› አሉ፡፡

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 22


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

ሓዋርያት በመጀመርያው ቀሌምንጦስ በ23ኛው ባስልዮስ በጻፈው መጻሕፍ በ99ኛው አንቀጽ ካህን
በሚያቀብልበት ጊዛ ኃጢአታችንን ለማስተስረይ ለኃጢአት ለሞት አሳልፎ የሰጠው የክርስቶስ ሥጋ ይህ
ነው ይበል፡፡ የሚቀበልም ሰው አሜን ይበል፡፡

ዳግመኛም ጽዋን ይዝ ደምን የሚያቀብል ካህን ስለእኛ የፈሰሰው የክርስቶስ ደም ይህ ነው ይበል፡፡


ደሙንም የሚቀበል ሰው ሁለት ጊዛ አሜን ይበል፡፡ በፍጹም ፍርሐትና ንጽሕና ይቀበለው፡፡ ደሙን
ሲቀበል ሁለት ጊዛ አሜን ማለቱ ደማዊት ነፍስን ነባቢት ነፍስን ሲያይ አንድም የሥጋውን ጨምሮ ነው፡፡
እንደተቀበሉ አፋቸውን በእጃቸው ሊሸፍኑ ይገባል፡፡
ይኸውም ሥጋ ወደሙ እንዳይነጥብ ለመጠንቀቅ ነው፡፡ የተቀበሉትንም ሥጋ ወደሙ በትናጋቸው መካከል
አድርገው /በአፋቸው መካከል አ዗ዋውረው/ በቀስታ ወደ ጉሮሮአቸው ሊልኩት ይገባል እንጂ
እንደምድራዊ ኅብስት በጥርሳቸው ሊያኝኩት አይገባም፡፡ በጥርሳቸው መካከልና በላንቃቸው ተጣብቆ
የቀረ እንዳይኖር የቅዳሴ ጠበል ሊጠጡ ይገባል፡፡
አንዳንደ ሰዎች አፋቸውን ለረጅም ሰዓት ይ዗ው መቆየት አይችሉም፡፡ ስለዙህ የሚበሉ ነገሮችን ይ዗ው
ገብተው ከተቀበሉ በኋላ ቤተክርስቲያን ውስጥ ሲመገቡ ይስተዋላሉ፡፡ ይህ በጣም ትልቅ ስህተትና
ድፍረት ነው፡፡ ምክንያቱም እጃቸውን በአፋቸው ላይ እንዲያኖሩ የታ዗ዘት በአፋቸው ያለውን ቅዱስ
ሥጋውን ክቡር ደሙን ከጉሮሮአቸው አጥርተው እስኪያወርዱ ድረስ አንድም ለአክብሮተ ሥጋ
ወደሙ ነው፡፡
በቤተ ክርስቲያን ውስጥም አፍን ለማደፍ ዗ቢብ ወይም ሌላ ማናቸውንም ነገር እንዲበሉ ሥርዓት
ያስቀመጠ መጽሃፍ የለም፡፡ ቅዳሴ ጠበሉ እሱ አፍ ማደፊያ ነው፡፡ ምእመናን ምእመናት አባቶችን አብነት
ለማድረግ ሲገባቸው በራሳቸው መንገድ ከሥርዓት የወጣ ነገር መፈጸም አይገባቸውም፡፡ ቤተሰቦቻቸውም
ማደፊያ የሚሆን ነገር ይ዗ው ውጪ እንዲጠብቋቸው አልያም በእናቶች የሚታደለውን ዳቤና ንፍሮ
ተቀብለው አፋቸውን ማደፍ ይችላሉ፡፡ ስለዙህ ይህን ዓይነቱን ስህተት የሚፈጽሙ ሰዎች ሊታረሙ ይገባል፡
 ለመቁረብ የሚያበቁና የማያበቁ ምክንያቶች
 ከምዕመናን በስተቀር ያላመኑ ሰዎች ሥጋዉንና ደሙን ሊቀበሉ አይገባቸዉም
 ቅዳሴ ሲቀደስ ያልነበረ፣ ያላስቀደሰ፣ ካህኑም ማቁረብ ምዕመኑም መቁረብ አይገባቸዉም
 በንስሐ የተለየ ሰዉ ለሞት የሚያበቃ ደዌ በታመመ ጊዛ ሥዉን ደሙን ከመቀበል አይከልክሉት
ቢድንም አንተ ንስሐ ይገባሃል ንስሐን ተቀበል ብለዉ ሥጋዉን ደሙን ከመቀበል አይከልክሉት፡፡
ፍት. ነገ አንቀጽ 13
 በሚገባ ሳይጾሙ ሥጋ ወደሙን መቀበል አይገባም፡፡ ፍት.ነገ አንቀጽ 13
 ከቂም በቀል ያለበት የዜሙትና የስካር መንፈስ ያለበት ሰዉ የህን ሁሉ በንስሐ ሳያርቅ መቀበል
አይገባዉም፡፡

 ሥጋ ወደሙን ሳያምኑ ቢቆርቡ የሚያስከትለዉ ጉዳት


ሳይገባው ራሱን ሳይፈትን ሳይመረምር የሚቆርብ ፣የጌታን ሥጋ ስለማይለይ ለራሱ ፍርድ ይበላልና፣

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 23


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

በማለት ይኸው ሐዋርያ ያስጠነቅቀናል። ‚ስለዙህ ሳይገባው ይህን እንጀራ ኅብስት የበላ ወይም የጌታን
ጽዋ የጠጣ ሁሉ የጌታ ሥጋና ደም ዕዳ አለበት። ሰው ግን ራሱን ይፈትን፣ እንዲሁም ከእንጀራው
ከኅብስቱ ይብላ ከጽዋውም ይጠጣ፤ ሳይገባው የሚበላና የሚጠጣ የጌታን ሥጋ ስለማይለይ ለራሱ ፍርድ
ይበላልና፣ ይጠጣልምና። ስለዙህ በእናንተ ዗ንድ የደከሙና የታመሙ ብዘዎች አሉ አያሌዎችም
አንቀላፍተዋል። ራሳችንን ብንመረመር ግን ባልተፈረደብንም ነበር፤ ነገር ግን በተፈረደብን ጊዛ ከዓለም
ጋር እንዳንኮነን በጌታ እንገሠጻለን‛ /፩ኛ ቆሮ ፲፩፣፳፯-፴፪/።
 ለመቁረብ የሚደረግ ጥንቃቄ /ዝግጅት/
ምእመናን ሥጋ ወደሙን ለመቀበል በሚፈልጉበት ወቅት ሊፈጽሟቸው የሚገቡ ዜግጅቶች አሉ። ሥጋዊ
ማዕድስ እንኳን ከመበላቱ በፊት የራሱ የሆነ ዜግጅት አሉት። ሰማያዊው ማዕድማ ምን ያህል ጥንቃቄ
ይፈልግ ይሆን!? /ማቴ ፳፪፥፲፪፡፡/ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሰርግ ቤት ምሳሌነት በርካታ
ትምህርቶችን አስተምሯል።
ይህም ዜም ተብሎ በ዗ፈቀደ ማንም ባሻው ጊዛ እየተነሣ ያለምንም ዜግጅት የሚመገበው ተራ ምግብ
አይደለም። ተግሣጹም ሆነ ጽኑዕ ቅጣቱ እንዳያገኘን ባግባቡ ተ዗ጋጅተን በካህናት እጅ የሚሰዋውን
መሠዋዕተ ሐዲስ መቀበል ይኖርብናል፡፡ ዋና ዋናዎቹ የዜግጅቱ አካላትም የሚከተሉት ናቸው።
 ባለፈ ኃጢአት መጸጸት፣ መና዗ዜና ቀኖና ተቀብሎ በትሕትናና በፍቅር መፈጸም፤
 ዳግም ላለመበደልም ወስኖ መጋደል፤
 ወደ ልባችን የኃጢአትን አሳብ እንዳያስገቡ አካላዊ ስሜቶችን ሁሉ መግዚት፤
 ሰውነትን /አካልን/ በዋዛማው በአግባቡ መታጠብና አቅም በፈቀደ መጠን ተገቢውን ልብስ
(ከተቻለ ነጭ) አ዗ጋጅቶ መልበስ፤
 በዋዛማው ቀለል ያለ ምግብ መመገብ ፣ለ፲፰ ሰዓታት ከምግበ ሥጋ መከልከል፣
 ሕጋዉያን (ባለ ጋብቻ) ቆራቢያን ከሩካቤ ሥጋ ለ፫ ቀናት መታቀብ፣
 ከሕልመ ሌሊትና ከወር አበባ እንዲሁም ከሚደማና ከሚያዥ ቁስል ነጻ መሆንን ማረጋገጥ፣
 በወሊድ ጊዛ ሴቶች ለወንድ ልጅ ፵ ቀን ለሴትም ልጅ ፹ ቀን የሞላቸው መሆኑን መገን዗ብ፣
 ሥርዓተ ጸሎተ ቅዳሴ ከመጀመሩ በፊት መድረስ የሚሉትና የመሳሰሉት ዜግጅቶች አስፈላጊ
ናቸው። ከጤንነት ጋ በተያያ዗ የጾም ሰዓትን በተመለከተ ከመምህረ ንስሐ ጋር በመመካከር
በፈቃደ ካህን የሚስተካከል ይሆናል።
የማይላመጥ የአድማስ ድንጊያ ነዉ፡፡ በዙህም የሚያስከትለዉን የመከራ ጽናት ለመናገር ነዉ፡፡ የድንጊያ
ንፍሮ (የብረት ቆሎ) ማላመጥ እንደማይቻልም በአግባቡ ሆነዉ ካልተቀበሉት የሚያስከትለዉም
መከራ ጽኑዕ ነዉ፡፡
 በኃጢአት ላይ ኃጢአትን የሚጨምር ከማስተስረይ ቀርቶ በደለኛ ያደርጋል፡፡
 ደዌ ሥጋ ደዌ ነፍስን ያመጣል፣ በመከራ ላይ መከራን ያመጣል
 እንደ ባቢሎን እሳት የሚያቃጥል የሚግጥ እሳት ይሆናል፡፡
 ልቡናን በኃጢአት ያደነድናል እንደ ይሁዳ ለሌላ በደል ያ዗ጋጃል

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 24


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

 የቆራቢያን የአቆራረብ ቅደም ተከተል


1. ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት፣ሊቃነ ጳጳሳት፣ጳጳሳት (ኤጲስቆጶሳት)
2. ቀሳዉስት ወዲያቆናት
3. ወዶች በየማዕረጋቸዉ እና በስርዓተ ተክሊል የሚጋቡ ሙሽሮች ይቀድማሉ
4. ሴቶች በየክብራቸዉ
5. በዕለቱ የተጠመቁ ከምእመናን የቀድማሉ (ወነወዶች መጀመሪያ ናቸዉ)
6. ንዑሰ ክርስቲያን ተጠማቂያን እንደየእድሜያቸዉ (ከትንሽ ወደ ትልቅ)
7. በድንግልና ኖረዉ የመነኮሱ መነኮሳት
8. ከመነኮሱ ከ20 ዓመት በላይ የሆናቸዉ መነኮሳት
9. ንፍቀ ዲያቆናት፣አናጉንስጥሰዉያን፣መ዗ምራን፣
10.በሕግ ኖረዉ የመነኮሱ መነኩሳት
11.በሕግ ጸንተዉ ያሉ ሕጋዊያን
12.በንስሐ ተመልሰዉ የመነኮሱ መነኩሳት
13.ንስሐ የገቡ ሕዜባዉያን በየማዕረጋቸዉ ቅድሱን ቁርባን ይቀበላሉ
14.ለሴቶች የ80 ቀን ሕጻናት ቅድሚያይኖራቸዋል
15.ንዑሰ ክርስቲያን ተጠማቂዎች
16.በድንግልና ኑረዉ የመኮሱ ድናግል
17.የቀሳዉስት ሚስቶች
18.በሕግ ኖረዉ የመነኮሱ መነኮሳት
19.የዲያቆናት ሚስቶች
20.በንስሐ ተመልሰዉ የመነኮሱ መነኮሳት
21.የንፍቅ ዲያቆናት፣የአናጉስጢሳዊያንና የመ዗ምራን ሚስቶች
22.በሕግ ጸንተዉ ያሉ ሕጋዉያን፣በመጨረሻ ንስሐ የገቡ ሕዜባዉያን ሴቶች (ሚስቶች)

 ቅዱስ ቁርባንን ከተቀበሉ በኋላ የሚደረግ ጥንቃቄ


 ከተቀበሉ በኋላ ወዲያዉ ቅዳሴ ጠበል መጠጣት አይገባም ቆመዉ ያስቀደሱበት ቦታ በመሔድ
ድርገት እስኪወርድ ድረስ መቆየት፡፡
 በአፍ ዉስጥ ትንኝና የመሳሰሉት ተሐዋስያን እንዳይገቡ አፍን በመሐረብ
መሸፈን
 ከሰርዎተ ሕዜብ አስቀድሞ ሥጋ ወደሙን የተቀበሉ ሁሉ በጸሪቀ መበለት አፋቸዉን አያድፉ ቅዳሴ
ከአፋቸዉ አይንጠብ፡፡
 ከቤተ መቅደስ ሳይጋፉ በቀስታ ወጥቶ በደጀ ሰላም (ጸሪቀ መበለት) ቀምሶ አፍን ማደፍ
 በዕለቱ ቆራቢያን እንዲፈጽሟቸው የማይፈቀዱ ተግባራት በከፊል

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 25


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

ገላን (ሰውነትን) መታጠብ፣ ከልብስ መራቆት፣ መስገድ መንበርከክ፣ ምራቅን እንትፍ ማለት፣ መበጣት
መቆረጥ መታገም መተኮስ፣ የእጅና ይእግር ጥፍር መቆረጥ፣ ፀጉርን መላጨት፣ ሩቅ መንገድ መሔድ፣
መፍረድ፣ መክሰስ፣ መካሰስ፣ ወደ መታጠቢያ ቤት መሄድ፣ ያለ መጠን መብላት፣ መጠጣት፣ ለሦስት
ቀናት ያህል ግብረ ሥጋ፣ ይህን የመሳሰሉትን ሁሉ ማድረግ አይገባም፡፡

5.ሥራዓተ ተክሊል
ቤተ ክርስቲያን ልጆቿ ለእግዙአብሔር መንግሥት ለመብቃት በሚያደርጉት መንፈሳዊ ጉዝ ሁለት የኑሮ
አማራጮች አቅርባላቸዋለች፡፡ አንደኛው ፍጹም የሆነ የድንግልና ሕይወትን ጠብቆ በመኖር የሚገባበትና
በተጋድሎ የሚኖርበት የምንኩስና ሕይወት ሲሆን ሁለተኛው በተቀደሰ ጋብቻ ክብደ ዓለምን በመቋቋም
እየተጋገዘ የሚጓዘበት ሕይወት ነው፡፡

በመተጫጨትና በቃል ኪዳን የተመሰረተው ጋብቻ በተክሊል ይፈጸማል፡፡ ክርስቲያናዊ ጋብቻ ትክክለኛነቱ
የሚታወቀው በተክሊልና በስጋወደሙ ሲፈጸም ነው፡፡ ተክሊል ማለት አከበረ ፤ ከለለ ካለው ግስ
የወጣ ቃል ነው፡፡ ይኸውም ክቡር ማለት ነው፡፡ ጋብቻ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በቃል ኪዳንና
በቡራኬ በጸሎተ ተክሊልና በቅዱስ ቁርባን ሲፈጸም ምስጢር አለው፡፡ በሚታይ ምልክቶችና ስርአቶች
የማይታይ ጸጋ እናገኝበታለን፡፡ ኤፌ 5፤32
በጋብቻ አመሠራረት ሂደት “እግዚአብሔር አምላክም አለ፦ ሰው ብቻውን ይኖር ዗ንድ መልካም
አይደለም፤ የሚረዳውን ጓደኛ እንፍጠርለት እንጂ።‛ (዗ፍ ፪፥፲፰፡፡) የሚለው ኃይለ ቃል መነሻና መሠረት
ነው። ይህም የጋብቻ መሥራቹና ፈቃዱ እግዙአብሔር መሆኑንና የተመሠረተውም በመጀመሪያዎቹ
አባታችንና እናታችን /በአዳምና በሔዋን/ መካከል እንደነበር ያስረዳል፡፡ ‚ምሥጢረ ተክሊል‛ በሐዲስ
ኪዳን የተሰጠው መጠሪያ ስም ነው። ተክሊል ‚ከለለ‛ ከሚለው የግእዜ ግስ የሚወጣ /የሚገኝ/ ሲሆን
ትርጉሙም ጋረደ ፣አጠረ፣ ከበበ፣ አከበረ፣ አጀበ፣ ፈጽሞ አስጌጠ፣ ሸለመ፣ አክሊል አቀዳጀ፣ ማለት ነው።
ምሥጢረ ተክሊል በሰፊው ሲብራራ ደግሞ የሙሽራውንና የሙሽራይቱን የጋብቻ ቃል ኪዳን በሃይማኖት
የሚያጸና፣ የጋብቻ ግዴታን ለመወጣት የሚያስችል፣ በፍቅር የሚያስተሳስርና ዗ላቂ አነድነትን
የሚያስገኝ የጸጋ ምሥጢር ነው፡፡

የሚሰጠውም ምንጊዛም ቢሆን እንደሌሎቹ ምሥጢራት ከቅዱስ ቁርባን ጋር ነው። ይህ የጋብቻ


ሥርዓት፣ የጋብቻ ኪዳን፣ ስምምነትና ውል በታወቀ በቂ ምክንያት ካልሆነ በቀር ፈጽሞ የማይፈርስ
ጽኑዕ አንድነት ነው። ቅድስት ቤተክርስቲያን ለሙሽራው /መርዓዊ/ እና ለሙሽሪት /መርዓት/
የምትፈጽመው ይህ መንፈሳዊ የጋብቻ ሥርዓት በክርስቶስና በቤተ ክርስቲያን መካከል ላለው ጽኑዕ
አንድነትና ዗ላለማዊ ፍቅር ምሳሌ የሚሆን /የሆነ/ ታላቅ ምሥጢር ነው። (ኤፌ ፭፥፴‐፴፫፡፡)

በሐዲስ ኪዳንም ዗መን መጀመሪያ አካባቢ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በገሊላ ቃና በተ዗ጋጀው የጋብቻ
ሥርዓት ላይ በመገኘት ክርስቲያናዊ ጋብቻን አክብሯል። በዶኪማስ ቤት ከእናቱ ከእመቤታችን ከቅድስት

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 26


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

ድንግል ማርያምና ከደቀ መዚሙርቱ ከሐዋርያት ጋር ተገኝቶ ጋብቻን ፈጽሞ ባርኮታል። የታወቀና
የተገለጠ የመጀመሪያ ተአምሩንም በእመቤታችን ምልጃ የፈጸመው በዙሁ ሰርግ ቤት መሆኑ
ይታወቃል። (ዮሐ ፪፥፩‐፲፪፡፡)
 ከጋብቻ በፊት እንዴት እንኑር

የጋብቻ መቅድም መተጫጨት ነው፡፡ የመተጫጨት ባህልና ሥርዓት ፍቃድና ስምምነትን ዕድሜን ፤
የስጋዊና መንፈሳዊ ዜምድናን ፤ የሃይማኖትን አንድንትን ዗ርዜሮ ይገልጣል፡፡ ተጋቢዎች ከተዋወቁ ፣
እርስ በእርሳቸው ከተስማሙና ከተፈቃቀዱ ለወላጆቻቸው አሳውቀው ፈቃድና ስምምነትን ካገኙ በኋላ
የውዴታ ቃላቸውን በመጀመሪያ ለንስሓ አባታቸው ወይም ለቤተክርስቲያኑ አስተዳዳሪ ወይም ለክፍለ
ኤጲስ ቆጶስ በመናገር ወደ ጋብቻ ቃልኪዳን ይሔዳሉ፡፡

ዕድሜን በተመለከተ ወንዶች ከ20 ዓመት በላይ ሴቶች ከ15 ዓመት በላይ ሲሆናቸው መተጫጨትና
መጋባት ይፈቀድላቸዋል፡፡ ፍት.መን.24 ም3. ክፍል 2፡፡ በዜምድና በኩል ጋብቻን የሚከለክል ዜምንድና
ሶስት ዓይነት ነው፡፡ ስጋዊ ዜምድና ፣ የጋብቻ ዜምድናና መንፈሳዊ ዜምድና ናቸው፡፡ ስጋዊ ዜምድና
በፍትሐ ነገስት በአንቀጽ 24፡842-853 ተ዗ርዜሮ እንደተገለጸው ስጋዊ ዜምድና የሚጠበቀው እስከ ሰባት
ትውልድ ነው፡፡
ይህም በአንድ ጎን ሰባት በአንድ ጎን ሰባት ከተቆጠረ በኋላ ስምንተኛዎቹ መጋባት ይችላል፡፡ አንድ
ጥሩ መንፈሳዊ የሆነ/ች ወንድም (እህት) ጋር አብሮ ለማገልገል በእህትነትና በወንድምነት
መቀራረበን መልመድ ይኖርብናል፡፡ ነገር ግን ይህን በምናደርግበት ጊዛ የተለያዩ ክፉ ወጥመዶች
ያገኙናል ለምሳሌ፡- ክፉ ፊልሞች፣ለፈተና በሚያጋልጥ ሁኔታዎች ውስጥ መቀመጥ ፤የጓደኛ ተጽእኖ ስለ
ራሰቸው ሕይወትና ኃጢኣት ልምድ ደጋግመው በማውራት የሰዎችን ልብ መስረቅ፡፡ እኛም እነዙህ
ፈተናዎችን እንዳሉ ተመልክተን አቀራረባችንን በጥንቃቄ ማደረግ አለብን፡፡ አንድም እግዙአብሔር
ያ዗ጋጀልንን የምናገኝበት ጊዛ እስኪደርስ ድረስ ፡-
1. በትግስት መጠበቅ ዕብ 10፡36 መክ 3፡1
2. እንደ ፈቃዱ እንመላለስ 2ጢሞ 2፡22 ሮሜ 6፡12 መክ 12፡1
3. ያለ ሐሳብ እንኑር ሉቃ 21፡34 1ጴጥ 5፡6-7
4. በጾምና በጸሎት መትጋት ማቴ 26፡41 ፊል 4፡6 ዮሐ15፡14
5. ከጋብቻ በፊት ከእጮኝነት ዗መን እንዴት እንደ ሚ዗ልቅ ማወቅ
6. ስለሚስጥረ ተክሊል እና ሌሎች ስርዓት ማወቅ
7. በትዳር ውስጥ ችግር ቢኖር እንዴት መፍታት እንደሚቻል ማወቅ
 የተከለከለ ጋብቻ
1. የሥጋ ዗መድ ጋብቻ፡-
ወደላይ፡- ወላጆች አያቶች፣ቅድመአያቶች ወደታች፡- ልጆች የልጅ ልጆች
ወደጎን፡- ያባቶች ወንድሞች፣ያባቶች ዕኅቶች የእናት እህቶችና ወንድሞች፣ወንድሞች፣ የወንድሞች ልጆች፣
ከአባቶችና ከአያቶች ስለተወለዱ የተለያዩ ዗መዶች፡፡

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 27


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

የአባት ወንድም ልጅ አራተኛ ትዉልድ ናት፡፡ አባቴ እኔን ወለደ፣ሁለት አያቴ አባቴን ወለደ
አያቴ የአባቴን ወንድም ወለደ ሁለት የአባቴ ወንድም ልጁን ወለደ
2. ከህግ ወገን የ዗መድ ጋብቻ
እነዙህም የሌሎች ልጆች በጥምቀት ክርስትና የተነሱ ናቸዉ፡፡ ኒቂያ 23÷25 "ክርስትና አንሺዉና
ተነሺዉ ከሁለተኛዉ ጋር አይጋቡ ወላጆቹም፣ወድሞቹም፣ልጆቹም፣ልጅ ልጆቹም የሚስቱ ከሌላ ልጆችም
ወገን አንዱ ልጆች ከሁለተኛ ልጁ ጋራ አይጋቡ ሴት ልጆን ባሏ ክርስትና ላነሳዉ ወንድ አታግባ"
ወንድም እንደዙሁ ልጁን ሚስቱ ክርስትና ላነሳችዉ ወንድ አያጋባ፡፡ ከእነዙህ ሁሉ በመካከላቸዉ
መንፈሳዊ ተዚመዶ ሆኗል፡፡
3. አብሮ በመኖር የተዛመዱ ሰዎች ጋብቻ
ምንመ እነርሱ በሞግዙትናት ስር ቢወጡ አሳዳጊዎቻቸዉም ቢያዩ እነዙህ ጡት መጥባትን በመሳተፉ
ወይም በልጆች መዕረግ በማሳደግ ያሉ ናቸዉ፡፡ ልጆቻቸዉም ወላጆቻቸዉም እነርሱ ቢሆኑ አባቶቻቸዉም
ያባቶቻቸዉን አባቶችም ያባቶችን ወንድሞች የእናቶቻቸዉን ወንድሞች እና እህቶች ያባት ሚስት
ያባት ሚስት (የእንጀራ እናት) አባት ልጅ ትሆናለች ብሎ ያሳደጋትን ልጅ አያግባ፡፡
4.በትዉልድ ያይደለ በግቢ ስለሚዛመዱ ሰዎች መጋባት
 ያባቶች ሚስቶች፣ወንድ አያቶቻቸዉ እኅቶቻቸዉእናቶቻቸዉ ሴት አያቶቻቸዉ
 የልጆች ሚሲቶች፣ልጆቻቸዉ፣እኅቶቻቸዉ፣እናቶቻቸዉ፣ሴቶች አያቶቻቸዉ
 የወንድሞች ሚስቶች ልጆቻቸዉ፣እሕቶቻቸዉ፣እናቶቻቸዉ፣ሴቶች አያቶቻቸዉ
 የሴት ዗መዶች አያቷ፣እናቷ፣ያባቷ እኅት፣የእናቷ እኅት፣እኅቷ፣ልጇ፣የልጅ ልጇ ናቸዉ፡፡
5. ሊያገባት ከሾሙት ጋር አደራ ያስጠበቁት ሰዉ ጋብቻ
የኸዉም እርሱ ልጅ ወንድሙም ከገን዗ቧ ሁሉ ጋር 26 ዓመት ከሆናት በኋላ ከሂሳብ ወገን የሚጋባ
አደራዉን ከፈጸመ በኋላ ያግባት
6. የጌታ ሚስት ባሏ ነፃ ያወጣዉ ባሪያ ሚስት ልቶን መልካም አይደለም
7. የእርሱ ወገወን ያልሆነችዉን አማኝ ያልሆነችዉን ማግባት አይገባም
8. ለጋብቻ ከሚያስፈልገዉ ሩካቤ የሚከለክል (ከእናቱ ማሕፀን ጀምሮ በተፈጥሮ እንደስልብ ያለ
ቢሆን) ሩካቤ የማይቻለዉ ስለሆነ ጋብቻን ይከለክላል ጃንደረባ ሆኑ የተፈጠረ
 ፍናፍነታም (የወንድና የሴት አካል በአንድነት በ አንድ ቦታ ያለበት ሰዉ)
 ሴትም ሩካቤ የሚከለክል ትርፍ አጥንት ያለባት ብትሆን
 ስልብ፣እብድ፣የሚቆራርጡ ደዊያት እንደ ደዌ ሥጋ ያለበት ቢሆን ወይም ብትሆን
9. በዝሙት ሥራ በአግባቡ የፈረዱበትን ለመፍታት በሚገባ የፈቷትንም ማግባት
10.ሁለት (ሦስት) ጋብቻ ማግባት አይገባም
11.መነኮሳይትን ማግባት አይቻልም
12.እድሜዋ ከ60 ዗መን ያለፈዉን ማግባት አይቻልም
13.የባሏን ሞት የሀ዗ን ወራት ያልፈጸመች ሴት ማግባት አይቻልም ሙሉ ዓመት (10 ወር) ነገር ግን
መተጫቸትና ቃል ማሰር ይቻላል
14. ከወንድና ከሴት እያንዳንዱ ካልወደዱ ሌላ ሊያገባቸዉ አይገባም

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 28


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

ማጨት ቃልኪዳን መግባት ከጋብቻ የሚቀድም ተስፋ ነዉ፡፡ በደኩም ያለ ደብዳቤ ሊሆን ይችላል፡፡
ዕድሜዉ ከ7 ዓመት ላለፈ ሕፃን አይጩለት፡፡ የወንዶች አካለ መጠን ፍጻሜ 20 ዓመት ያም ባይሆን 25
ዓመት ነዉ፡፡ የሴቶችም 12 ዓመት ያም ባይሆን15 ዓመት፡፡ የጋብቻ አንድነት ግን በካሕናት መኖር
በላያቸዉ በሚጸልይ ጸሎት ካልሆነ በቀር አይሆንም አይፈጸምም፡፡ አንድ አካል እንደ ሆኑ ቅዱስ ቁርባን
ያቀብላቸዋል፡፡ ሁለተኛ የሚያገቡ ወንዶች ካሕናት ቢሆኑ ከሹመታቸዉ ይሻሩ፡፡ ከዙያም በኋላ ቢደግሙ
የረከሱ ይሆናሉ፡፡ 1ኛቆሮ 7÷39"ሴት ባሏ በሕይወት እያለ በሕግ የታሰረች ናት ባሏ ቢሞት ግን ነፃ ናት፡፡
 የሥርዓተ ተክሊል አፈጻጸም
ሥርዓተ ተክሊል ያለ ድንግልና የማይፈጸም ምሥጢር ነው፡፡ ስለዙህም ለተክሊል ክብር እንድንበቃ
ድንግልናችንን ልንጠብቅ ይገባል፡፡ ካልሆነ ግን ራሱን የብርሐን መልአክ እስኪያደርግ ድረስ
የሚለወጠው ዲያብሎስ በልዩ ልዩ ዜንጋዬ እንድንወድቅ ያደርገናል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ያለንን መንፈሳዊ
ሀብት መጠበቃችን ዋጋ የሚያሰጥ መሆኑን በገለጸበት አውድ ፡- "…መልካሙን ገድል ተጋድያለው
ሃይማኖትን ጠብቄአለው…የጽድቅ አክሊል ተ዗ጋጅቶልኛል ‛2ጢሞ4፡7 እንዳለ፡፡

ሥርዓተ ተክሊል የሚፈጸመው ሁለቱም ደናግል ሆነው ሲገኙ ነው። ሥርዓተ ተክሊል የሚፈጸመው
በሁለቱ ተጋቢዎችና በወላጆቻቸው /አሳዳጊዎቻቸው/ ፈቃድ መሠረት ነው፡፡ የሚጋቡትም ወንዶችና
ሴቶች ለአካለ መጠን የደረሱና ማለትም ለወንድ ሃያ ዓመት (20)፣ ለሴት አስራ አምስት (15)
ዓመት ከሆናቸው ጀምሮ ያሉ እና በሃይማኖት የተካከሉ /የተመሳሰሉ/ መሆን ይገባቸዋል::

ሥርዓተ ተክሊሉ የሚፈጸመውም በድንግልና ለተወሰኑ እጮኛሞች ነው። ሥርዓቱ የሚፈጸመው


ካህናትና ምእመናን በተሰበሰቡበት በጉባኤ ነው እንጂ በስውር በድብቅ አይደለም። ከዙህ ውጪ
የሚፈጸም የተክሊል ጋብቻ የለም።

የጋብቻው ሥርዓት በቤተ ክርስቲያን ቢፈጸምም በቅዱስ ቁርባን ያልታተመ ከሆነ የተክሊል ጋብቻ
ተፈጸመ ሊባል አይቻልም። የምሥጢራተ ቤተክርስቲያን ሁሉ ማኅተማቸውና መክብባቸው
ምሥጢረ ቁርባን ነውና። /ፍት.ነገ.፳፬፥፰፻፺፰‐፱፻፡፡)

ጋብቻ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በቃል ኪዳንና በቡራኬ፣ በጸሎተ ተክሊልና በቅዱስ ቁርባን ሲፈጸም
ምሥጢርነት ይኖረዋል። /ኤፌ. ፭፥፴፪፡፡/ በሚታዩ የአፈጻጸም ሥርዓቶችና ምልክቶች የማይታይ ጸጋ
እግዙአብሔ ይገኝበታልና። ምሥጢረ ተክሊል ከቤተ ክርስቲያን ውጪ በምንም ዓይነት መንገድና
በየትኛውም ቦታ አይፈጸምም፡፡

ከቤተ ክርስቲያን ከወጣ ካህናት ቢኖሩም እንኳን በየትኛውም ቦታ አይፈጸምም፡፡ ቤተክርስቲያን


ሳታውቀው የሚፈጸም ጋብቻ መንፈሳዊ ጋብቻ ሊባል አይችልም፡፡ ሥርዓተ ተክሊሉ በሚፈጸምበት ዕለት
የሚኖረው አፈጻጸም የሚከተለውን ይመስላል፡፡

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 29


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

 ሙሽራው ከሚዛዎቹና ከ዗መዶቹ ጋር ወደ ቤተ ክርስቲያን ሄዶ በሰሜናዊው ማዕ዗ን ይቆማል።


 ሙሽሪትም ከሚዛዎቿና ከ዗መዶቿ ጋር ወደ ቤተክርስቲያን ገብታ በደቡባዊ ማዕ዗ን
ትቆማለች፡፡
 ከዙያም በንስሐ አባታቸውና በሊቀ ዲያቆኑ አስተናባሪነት በቅድስት በተ዗ጋጀላቸው የክብር ወንበር
ላይ ይቀመጣሉ፡፡
 ከእግራቸው ሥር ልዩ የክብር ምንጣፍ ይነጠፋል፡፡ ካህናቱ ከፊት ለፊታቸው ካለው ጠረጴዚ
ላይ በአንድነት የሚለብሱትን ነጭ ልብስ፣ ካባ፣ መጎናጸፊያ፣ ተቀብተው የሚከብሩበትን ቅብዓ
ቅዱስ፣ (ሜሮን) የሚቀዳጇቸውን አክሊላት፣ የሚያጠልቁትን ቀለበትና የሚጨብጡትን መስቀል
ያኖራሉ፡፡
 ቀጥለውም ሥርዓተ ተክሊሉን አድርሰው ቃልኪዳን በመገባባት እንደ ትእዚዘ ይፈጽሙላቸዋል።
በመጨረሻም ቅዳሴ አስቀድሰው ሥጋውን ይበላሉ፤ ደሙንም ይጠጣሉ፡፡
ሀ. መስቀል /ወንጌል/ ጨብጠው ቃል ኪዳን መግባታቸው
በሃይማኖት ጸንተው ለመኖር በሚያደርጉት ግብግብ የሚቀበሉትን ፈተና ያመለክታል፡፡ በመስቀሉ
/በወንጌሉ/ ኃይልም ፈተናውን ድል እንደሚያደርጉት ያሳያል። መስቀልና ወንጌል የድል አድራጊነት
/የአሸናፊነት/ ምልክት ነውና።
ለ. አንድ ነጭ መጎናጸፊያ መጎናፀፋቸው፤
ሀብተ ወልድና ስመ ክርስትና ያላቸው የሥላሴ ልጆች መሆናቸውን ያጠይቃል። አንድ ልብስ ለብሰው
አንድ ክብር ወርሰው በዙህ ዓለም የመኖራቸውና በወዲያኛውም ዓለም አንዲት ርስት መንግሥተ
ሰማያትን ወርሰው ከክርስቶስ ጋር የሚኖሩ መሆኑን ያመለክታል፡፡ ነጭ ልብስ /መጎናጸፊያ/ ክብርን፣
ትንሣኤንና የሚቀበሉትን የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ የሚያስረዳ ነውና፡፡

ሐ አንድ በሆነ ምሳሌያዊ ቀለበት የሁለቱንም ጣቶች ባንድ ማጣመራቸው፤


ቀለበቱ የሃይማኖት ምሳሌ ነው፡፡ ቀለበት በክብነቱና ፍጻሜ የለሽ በመሆኑ በቃል ኪዳን የጸናው የተክሊል
ጋብቻም ከሕይወት ፍጻሜ በስተቀር ማንም የማይለያየው መሆኑን ያሳያል። በአንዲት ርትዕት
ሃይማኖት የማይናወጽ መሠረት ላይ የታነጸ እንደመሆኑ የጠላት ነፋስ፣ የፈተና ጎርፍና ልዩ ልዩ ወቅታዊ
የስሜት ማዕበላት /የማያፈርሱት/ መሆኑን ያመለክታል።
መ. በቅብዓ ቅዱስ (ሜሮን) ተቀብተው መክበራቸው
ቅብዐ ሜሮን በምሥጢረ ሜሮን እንዳየነው የመንፈስ ቅዱስ ማሳደሪያ ነው፡፡ በዙህም መሠረት ረድኤተ
መንፈስ ቅዱስ በትዳራቸው ዗መን ሙሉ የማይለያቸው መሆኑን ያጠይቃል።
ሠ. አክሊል መቀዳጀታቸው
አክሊል የድል አድራጊነት ምልክት እንደመሆኑ ድል አድራጊነታቸውን ያመለክታል። እስከ ጋብቻቸው
ዕለት ባሉት አፍላ የወጣትነት ቆይታዎች በርካታ ውጣ ውረዶችን በረድኤተ እግዙአብሔር አልፈው፤
ድንግልናቸውን ጠብቀው፤ ለዙያች ዕለት በመድረሳቸው ቤተ ክርስቲያን የምትሸልማቸው የክብራቸው

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 30


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

መገለጫ ነው፡፡ በቀጣይ የሕይወት ዗መናቸው ደግሞ በጾም፣ በጸሎት፣ በንስሐ፣ በሥጋ ወደሙና
በመልካም ምግባራት ሁሉ ጸንተው እንዲኖሩ ያስችላቸዋል። ትዳራቸውን በፈቃደ እግዙአብሔር ጠብቀው
ከተጓዘ ሰማያዊውን የክብር አክሊል የሚቀዳጁ መሆኑን ቤተ ክርስቲያን በምሥጢር የምታሥተምርበት
ሥርዓት ነው። በተጨማሪም በተስፋ ልጆቿን የምታጸናበት የሕይወት መንገድ ነው።

ከጋብቻ በኋላ አንድ ክርስቲያን እነዚህን ነገሮች መጠበቅ አለበት


 በአራስነት ወቅት (ለወንድ ፵፣ ለሴት ፹ ቀናት እስኪሞላ ያሉት ቀናት)፤
 የወር አበባ ጀምሮ እስኪጠራ (ሰባት ቀናት)፤
 ሥጋ ወደሙ ከመቀበል ቀድሞ ያሉ (ሦስት ቀናት)፤
 ሥጋ ወደሙ ከተቀበሉ በኋላ (ሦስት ቀናት)፤
 ሁለቱ ሰናብት (ሰንበቶች)፤
 ዐበይት በዓላት (ዓመታዊ የቤተ ክርስቲያን በዓላት)፤
 በየወሩ በ፲፪፣ በ፳፩ እና ፳፱ ያሉ (የግዜት በዓላት) ፤
 እርግዜና ሲገፋ፤/ወይም እርግዜና እንዳለ ከታወቀበት ጊዛ ጀምሮ የመጀመሪያዎቹ 3 እና 4 ወራት
በኋላ/
 ቢቻል በሰባቱ አጽዋማት፤ ካልሆነ ግን በዐቢይ ጾም፤ (ፍት. ነገ ፳፬፥፱፻፳፩‐፱፻፳፬፡፡) ከሥጋ
ፍቃድ መከልከል ያስፈልጋል ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ነው፡፡

በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ከድንግልና ጋር በተያያ዗ በተክሊል ለማግባት ከሁኔታዎች አንጻር እንደ ደናግላን
በቤተክርስቲያን ምሥጢረ ተክሊል የምትፈጽምላቸው አሉ፡፡ ለምሳሌ፡-
 በሕክምና ምክንያት ድንግልናቸውን ለሚያጡ፣
 በተፈጥሮም ሲወለዱ ድንግልና ለሌላቸው፣
 ለአቅመ ሔዋን ሳይደርሱ በመደፈር ድንግልናቸውን ላጡ
 በከባድ ስራ ምክንያት የተነሳ ድንግልናቸውን ያጡ እነዙህ ያለፈቃዳቸው በመሆኑ እንደ ደናግላን
በተክሊል ማግባት ይችላሉ፡፡ፍ. ነገስት አንቀጽ 24

ፍቺ የሚፈቅድባቸው ምክንያቶች

1) ሞት ከሁለቱ አንዳቸው በሞት ቢለዩ በሕይወት የቀረው ሌላ እንዲያገባ ተፈቅዶለታል ። ነገር


ግን ጋብቻው በአንድ ሃይማኖት ከሚኖሩና በቅዱስ ቁርባን መጋባት ከሚፈልጉ ጋር መሆን አለበት።
ሮሜ 7፡2 1 ቆሮ 7፡39
2) የጤና ጉድለት በትዳር ለመኖር እስከማይችሉበት ድረስ በእንዳቸው ላይ የጤና (በጾታዊ አካላቸው
ላይ) ችግር ካገጥማቸውና ለአብረው ለመኖር ካልተስማሙ መፋታት ይችላሉ። ምክንያቱም ከጋብቻ
መሠረታዊ ፍላጎቶች ከሆኑት ውስጥ አንዱ ስለተጓደለ ካልተስማሙ በቀር አብረው ለመኖር
አይገደዱም ።
3) የሃይማኖት ልዩነት አንዳቸው ከኦርቶክሳዊት ተዋሕዶ ሃይማኖት ወጥተው የሌላ እምነት ተከታይ
ከሆኑና ተመክረው መመለስ ካልቻሉ በሃይማኖቱ የጸናው ትዳሩን መፍታት ይፈቀድለታል። ነገር

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 31


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

የተለየው ተመልሶ ካመነና ይቅርታ ከጠየቀ የትዳር ጓደኛውም ይቅርታውን ከተቀበለውና


ከተስማማ በትዳራቸው መቀጠል ይችላሉ ።
4) ዜሙት ከሁለቱ አንዳቸው በዜሙት ከወደቁ ንጹሁ ሰው ትዳሩን መፍታት ይችላል። ነገር ግን
ወሬ በመስማትና በጥርጣሬ ሳይሆን በተጨባጭ ከተገኘ መሆን አለበት። ማቴ 5፡32 የቤትን
ገመና ለውጭ ማውራት ነገረ ሰሪ የሆኑ ሰዎችን ሊያስገባ ይችላልና መጠንቀቅ ያስፈልጋል።
የትዳር መሠረቱ በእውነት መግባባትና መተማመን ስለሆነ በሁኔታዎች መጠራጠርና
መጨቃጨቅ አያስፈልግም። ባልና ሚስት በትዳራቸው በሚኖረው ማንኛውም ዓይነት ኑሮ
በመመካከርና በመወያየት መወሰን አለባቸው ።

6.ሥርዓተ ንስሓ
እግዙአብሔር አምላካችን ለሰው ልጆች ሥጋዊ ደዌ ሕመም ፈውስ የሚሆኑትን መፈወሻ መድኃኒት
እንደሰጠን ሁሉ የነፍስ ደዌ ኃጢአትን የሚያርቅና ከሕመሙ የሚፈውስ መድኃኒት ንስሐን ሰጥቷቸዋል:
ደዌ የሆነው ኃጢአት በምድራዊ ኑሮአችው ሁሉ አብሮ እንደሚኖር የታወቀ በመሆኑ መድኃኔዓለም
ክርስቶስ መድኃኒቱንም አብሯቸው ይኖር ዗ንድ ከሐኪሞች ከካህናት ጋር በመካከላችው አኖረው፡፡

ንስሐ ፦ ነስሐ ተፀፀተ ካለው የተገኘ ሲሆን ፤ ንስሐ ማለት በሠሩት ኃጢአት መፀፀት ፣ ማ዗ን ፣ ወደ
እግዙአብሔር ለመመለስ መወሰን ማለት ነው። ንስሐ ከ዗ለዓለማዊ ፍርድ የሚያድን ፤ ዗ማዊውን እንደ
ድንግል ፤ ሌባውን መጽዋች የሚያደርግ በፊት ከተሠራው ኃጢአት ንጹህ አድርጎ ፤ ከእግዙአብሔር ጋር
አንድ የሚያደርግ ምሥጢር ነው

የንሥሐ አፈጻጸም
እንግዲህ ንስሐ ገብተን፣ የኃጢአትን ስርየት አግኝተን፣ ከሰውና ከእግዙአብሔር ጋር ታርቀን በጽድቅ
ጎዳና ለመራመድና በደህንነት ጸጋ ለመኖር እንድንችል ቢያንስ ሦስት ነገሮችን መፈጸም አለብን።
የመጀመሪያው የንስሐ ሃ዗ን ማለትም እውነተኛና ልባዊ ጸጸት በቅድሚያ እንዲኖረን ያስፈልጋል።
ሁለተኛው ኑዚዛ ሲሆን ሦስተኛው ደግሞ ስለኃጢአታችን የሚሰጠንን የንስሐ ቅጣት የሚያመለክት
የቀኖናን ሥርዓት መፈጸምና እንደዙሁም በካህኑ በኩል የምናገኘው የፍትሐት ጸጋ ነው።
1. የንስሐ ሃ዗ን /ጸጸት/
ንስሐ የሚገባ ሰው በመጀመሪያ ኃጢአቱን እያስታወሰ ሰውና ፈጣሪውን መበደሉን እያሰበ የሚያደርገው
ሃ዗ን ወደ ንስሐ የሚወስድ እውነተኛ ሃ዗ን ስለሆነ ሃ዗ኑን እግዙአብሔር ይቆጥርለታል። «የሚያዜኑ
ብፁዓን ናቸው፣ መጽናናትን ያገኛሉና» /ማቴ. ፭፥፬/ የተባለው የራሳቸውንና የሌላውን ኃጢአት እያሰቡ
የሚያዜኑትን ተነሳሒያን ያመለክታል። ንስሐ ማለት ጸጸትን የሚያመለክት ቢሆንም ቁጭትና ቅንዓት
የሞላበት የዓለማዊ ጸጸት ሳይሆን እውነተኛው ሃ዗ንና መመለስ መሆኑን በቅድሚያ መገን዗ብ
ይኖርብናል።
ስለእውነተኛው ሃ዗ን ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እንደሚከተለው ያስተምረናል። «አሁን ስለንስሐ
ስላ዗ናችሁ ደስ ብሎኛል እንጂ ስላ዗ናችሁ አይደለም፤ በምንም ከእኛ የተነሳ እንዳትጎዱ እንደ
እግዙአብሔር ፈቃድ አዜናችኋልና። እንደ እግዙአብሔር ፈቃድ የሆነ ሃ዗ን ጸጸት የሌለበትን፣ ወደ

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 32


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

መዳንን የሚያደርሰውን ንስሐ ያደርጋልና፤ የዓለም ሃ዗ን ግን ሞትን ያመጣል።» /፪ኛ ቆሮ. ፯፥፱-፲/።
እንግዲህ እውነተኛውን ሃ዗ን ከእንባ ጋር አድርጎ በንጹህ ልቦናና ጸሎት ለእግዙአብሔር በማቅረብ
ተነሳሒው እንደገና ላለመበደል መወሰን ይኖርበታል። ውሳኔውንም ለመፈጸም የሚያስችለውን የመንፈስ
ቅዱስን ረድኤት በማግኘት ሁልጊዛ ተግቶ መጸለይ አለበት፡፡
 መፀፀት/ስንል/ምን ማለት ነው?
አንድ ክርስቲያን በድፍረትም ይሁን በስህተት ‚የሠራው በደል‛ መጻሕፍት በማንበብ ፣ ከመምህራን
ተምሮ ፣ የስብከት ካሴት አዳምጦ ፤ ህሊናው ወቅሶት ፣ ወይም በሌላ በአንድ ምክንያት ስህተት መሆኑን
ከተረዳ በኋላ ተፀፅቶ ከእግዙ አብሔር ለመታረቅ (በደሉን ለማስተስረይ) የሚያደርገው ጉዝ ንስሐ ይባላል ።
በሠራው በደል ሳይፀፀት ፤ ለጊዛው ህሊናውን ስለረበሸው ብቻ ንስሐ የሚገባ ሰው ፤ ከስሐውን በኋላ ወደ
ቀደመ ሕይወቱ ሊመለስ ይችላል ። ምክንያቱም ፡ ንስሐ የገባው ፡ በሠራው በደል ከልቡ ተፀፅቶ ሳይሆን ፤
በስሜት ተነሳስቶ ነውና ፤

1) ኃጢአትን መጥላት፡-በበደላችን ከተፀፅትን በኋላ የሰራነውን በደል መጥላትና ወደፊትም


መሥራት እንደሌለብን ራሳችንን ማሳመንና ከኃጢዓት መንገድ መራቅ ማለት ነው ።
2) ከንስሐ በኋላ ስላለው ሕይወት መወሰን፡-አንድ ምዕመን ንስሐ ከመግባቱ በፊት ለወደፊቱ
የሚኖረውን ሕይወት አስቀ ድሞ መመርመርና መወሰን ይገባዋል የእግዙአብሔን ቃል ስንሰማ
ለጊዛው ልባችን ሊነካ ፣ ምን እናድርግ ልንል እንችላለን ። የሐ ሥ 2 ፥ 37 ። ነገር ግን ከተወሰነ
ጊዛ በኋላ ዓለሙን ወደመምሰል እንደማንመለስ አስቀድመን ራሳችንን መመርመር አለብን ።
ብዘዎቹ በስሜት ወደ ክርስትና ከገቡ በኋላ ፤ በጊዛያዊ ነገር ተታለው በድንገት ከሃይማኖት
መንገድ ወጥተዋልና ።

በንስሐ ጊዜ
አንድ ምዕመን ካለፈ በደሉ በንስሐ ታጥቦ በአዲስ ሕይወት ራሱን ለማስተካከልና ከእግዙአብሔር ጋር
ለመኖር ከወሰነ በኋላ የንስሐ አባት ሊኖረው ይገባል ። ጌታችን ‚ካህናትን‛ ራሱን ወክለው መንጋውን
እንዲጠብቁ ‚በምድር ያሰራችሁት በሰማይ የታሰረ በምድር የፈታችሁት በሰማይ የተፈታ ይሁን‛ (ማቴ 8
፥ ዮሐ 21 ፥ 15 ። ማቴ 16 ፥ 19) በማለት መንጋውን እንዲጠብቁ ሾሟቸዋልና። አንድ ክርስቲያን
በሕይወት ሲኖር ፤ የእግዙአብሔርን መንገድ የሚመራው ፤ ሲሳሳት ንስሐውን ተቀ ብሎ ቀኖና በመስጠት
ከእግዙአብሔር የሚያስታርቀው የንስሐ አባት የግድ ሊኖረው ይገባል።

ንስሐ የሚገባው ምዕመን በካህኑ ፊት በሚቀርብበት ጊዜ የሚከተሉትን ማሟላት


አለበት
1) የሠራውን ስህተት በሙሉ ማስታወስ ፡-ቀኖናው የሚሰጠው እንደ በደሉ ዓይነት ስለሆነ
የሠራውን ማስታወስ አለበት ፤ በቃሉ የሚረሳው ከሆነም በጽሁፍ መመዜገብ ያስልጋል ።
2) ሳይቀንሱ (ሳይከፍሉ) በሙሉ መናገር ፡-‚ይህን ብናገር ሰው ምን ይለኛል ?‛ ብሎ ከባዱን
(የሚያሳፍረውን) ነገር መደበቅ የለበትም። ሲሰራው ያላሳፈረውን ሲናገረው ሊያፍርበት
አይገባም። አንድ ጊዛ ተናግሮ ከህሊናው ካላስወጣው ሁሌም ሲረብ ሸው ይኖራልና።
“እናንተ ሸክማችሁ የከበደ ወደ እኔ ኑ ሸክማችሁን አራግፋለሁ” ማቴ 11 ፥ 28
ተብሏልና በትክክል አስታውሶ መና዗ዜና የኃጢአትን ሸክም ማራገፍ ይገባል። ስለ በደላችን በምንና዗ዜበት
ጊዛ ግን ፤ ከዕገሌ ጋር ፤ በዙህ ጊዛ ፤ በዙህ ቦታ ፤ ይህን አድርጌያለሁ እያልን ፤ ቦታውን ፤ ጊዛውን የሌላ

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 33


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

ሰው ስም በዜርዜር እንድንናገር አንገደድም ፣ የሠራነውን በደል ብቻ ‚ጣዖት አምልኬያለሁ ፤ ሠርቄያለሁ ፤


አመንዜሬያለሁ‛ በማለት በጥቅሉ መናገር እንችላለን ።

2. ኑዛዜ
ከዙህ ቀጥሎ ተነሳሒው ኃጢአቱን ሥልጣነ ክህነት ላለው ካህን ይና዗ዚል። ኑዚዛ ማድረግ በቅዱሳት
መጻሕፍት የታ዗዗ ነው። «ከነዙህ ነገሮች በአንዲቱ በደለኛ ቢሆን፥ የሠራውን ኃጢአት ይና዗ዚል። ስለሠራው
ኃጢአት ለእግዙአብሔር የበደልን መስዋዕት ያመጣል፤ካህኑ ስለኃጢአቱ ያስተሰርይለታል።እርሱም ይቅር
ይባላል።» /዗ሌ. ፭፥፭-፮፣፲/። ከዙህ ጥቅስ የኃጢአትን ስርየት ለማግኘት ለካህን መና዗ዜ እንደሚገባ
እንማራለን። ስለዙህ ኃጢአታችንን ለአናዚዡ ካህን ከበደሉ ዓይነትና ሁኔታ ጋር ማስረዳት ይገባናል።
ስንና዗ዜም ከእንባና ከጸጸት ጋር ሆነን ከካህኑ ጋር አብሮ እግዙአብሔር እንደሚሰማን አምነን በእውነት
መናገር ያስፈልገናል።

በራሳችን ድካም የሠራነውን በደል ‚ዕገሌ አሳስቶኝ‛ እያሉ ሌላውን ሰው ስለ እኛ ስህተት ተጠያቂ ማድረግ
ሳይሆን ፣ አንደበታችንን ከሳሽ ህሊናችን ምስክር አድርገን በመጨከን ራሳችንን በእግዙአብሔር ፊት
መክሰስ ነው ። አምላካችን የልባችንን መመለስ ፣ አይቶ የሰራነውን በደል ሁሉ እንዳልተሠራ አድርጎ
ያነጻናል ። በደልን በንስሐ ይቅር ማለት የእግዙአብሔር የቸርነት ሥራ ነውና።

በሽታውን የሰወረ መድኃኒት አያገኝም ተብሏልና ለነፍስ ቁስል ሐኪም ለሆነው ለካህኑ ኃጢአታችንን
ከሰወርን ለነፍስ የሚሆነውን ፈውስ ለማግኘት አንችልም።«ኃጢአቱን የሚሰውር አይለማም፤
የሚና዗ዜባትና የሚተዋት ግን ምሕረትን ያገኛል።» /ምሳ. ፳፰፥፲፫/ ተብሎ ተጽፏልና ስለዙህ እርስ
በርሳችን በቂም በቀል ሳንያያዜ የበደልነውን እየካስን፣ የበደለንን ይቅር እያልን ብንና዗ዜና የሰማዩን
አባታችን በጸሎት ብንጠይቀው ምሕረትና ፈውስን ይሰጠናል። ነገር ግን እኛ ማንንም አልበደልንም
ኃጢአትም የለብንም ብንል እግዙአብሔርን ሐሰተኛ ማድረጋችን ስለሆነ እንጠንቀቅ።
ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ እንዳለው «ኃጢአት የለብንም ብንል ራሳችንን እናስታለን፣ እውነትም በኛ ውስጥ
የለም። በኃጢአታችን ብንና዗ዜ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመፃም ሁሉ ሊያነጻን የታመነና ጻድቅ ነው።
ኃጢአትን አላደረግንም ብንል ሐሰተኛ እናደርገዋለን ቃሉም በኛ ውስጥ የለም።» /፩ኛ ዮሐ. ፩፥፰-፲/።
3. ፍትሐትና ቀኖና
እንግዲህ ተነሳሒው በእውነት ኃጢአቱን አውቆ ለካህኑና በስውር ለሚያየውና ለሚሰማው ለእግዙአብሔር
ከተና዗዗ በኋላ ከካህኑ ሁለት ነገሮችን ይቀበላል። እነሱም ፍትሐትና ቀኖና ናቸው። ፍትሐት ማለት
ከኃጢአት እስራት የሚፈታበት ነው።

ቀኖና ማለት ለኃጢአቱ ምክርና ተግሳጽ የሚያገኝበትን፣ በንስሐ ቅጣት የሚቀበልበትን፣ ካሳ መቀጫ
የሚከፍልበትን ሁኔታ የሚያመለክት ነው። ፍትሐት የሚሰጠው ካህኑ የንስሐውን ጸሎት ሥነ ሥርዓት
ከፈጸመ በኋላ «እግዙአብሔር ይፍታህ» ሲል ተናዚዡ ወይም ተነሳሒው ከኃጢአቱ እስራት ይፈታል።

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 34


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

ከእግዙአብሔርም ይቅርታን ያገኛል።

ንስሐ የገባው ሰው ከኃጢአቱ ተፈትቶ ከእግዙአብሔር ጋር መታረቁ ታላቅ ጸጋ ነው። እንግዲህ ፍትሐት
የተቀበለ ተነሳሒ ሁሉ ኃጢአቱ የተሰረየለት ስለሆነ ከ዗ላለም የሞት ቅጣት ነፃ ይሆናል።ምንም እንኳን
ተነሳሒው ከ዗ላለም የሞት ቅጣት ቢድንም ዓይነቱና መጠኑ የተለያየ ጊዛያዊ ቅጣት መቀበል ይገባዋል።

ይህም የንስሐ ቀኖና ይባላል። ጊዛያዊ ቅጣት ወይም ቀኖና ያስፈለገበት ምክንያት ኃጢአትን
መሥራት ምን ያህል አደገኛ እንደሆነ ለተነሳሒው ለማሳሰብና ዳግመኛ እንዳይበድል ለማስጠንቀቅ
እንዲሁም ደግሞ ሥጋን በመገሰጽ ለነፍሱ የጽድቅንና የደህንነትን ጎዳና ለማስተማር ነው። ምንጊዛም
ፍቅሩና ምሕረቱ ከኛ ጋር ቢሆንም እግዙአብሔር በአባትነቱ ላጠፋነው ጥፋት በጊዛያዊ ቅጣት
ይቀጣናል።

መልካም አባት ልጁን እንደሚገስጽና እንደሚቀጣ ዓይነት ይቀጣናል። /ዕብ. ፲፪፥፭-፲፩/። እንግዲህ ያልተገራ
ልቦና ካለን ለእግዙአብሔር በማስገዚት የኃጢአታችንንም ቅጣት በደስታ በመቀበል የበለጠ ጸጋና ረድኤትን
እናገኛለን። «በዙያን ጊዛ ያልተገረ዗ው ልባቸው ቢዋረድ፣ የኃጢአታቸውንም ቅጣት ቢቀበሉ እኔ ለያዕቆብ
የማልኩትን ቃልኪዳኔን አስባለሁ … ምድሪቱንም አስባለሁ።» ተብሎ ተጽፏልና /዗ሌ. ፳፮፥፵፩-፵፪/።
አንድ ምዕመን ንስሐ ከገባ በኋላ የሚከተሉትን በቅደም ተከተል ማድረግ አለበት?
1. የተቀበለውን ቀኖና በትክክል መፈጸም

ቀኖና የግሪክ ቃል ሲሆን : መለኪያ ማለት ነው ። ካህኑ ለበደለው ምዕመን እንደ ሃይማኖቱ ጽናት ፣ እንደ
አእምሮው ስፋት ፤ የሠራውን በደል መጥኖ ቀኖና ከሰጠው በኋላ እንደታ዗዗ው መፈጸም አለበት ። የነነዌ
ሰዎች ፣ ት. ዮና 3 ፥1 ። ንጉሡ ህዜቅያስ ፣ ኢሳ 38 ፥ 1 ። ቅዱስ ጴጥሮስ ሉቃ 22 ፥ 54 ። እና ሌሎችም
ይቅርታን ያገኙት ፤ በበደላቸው ተጸጽተው በማልቀሳቸውና ንስሃ በመግባታቸው ነው ። በንስሐ ወቅት ፡
መሬት ላይ መተኛት ምግብ መቀነስ ፣ ከዓለማዊ ነገሮችና ለመንፈሳዊ ሕይወት ከማይመቹ ጓደኞች መራቅ
ያስፈልጋል ። በንስሐ ጊዛ እንዳናደርግ ከታ዗ዜነው ነገር ራሳችንን በመግዚት መቆጠብ አለብን ፤
እግዙአብሔር በቸርነቱ ወደ ድኅነት ከጠራን በኋላ እንደገና ተመልሰን ወደተውነው ድካማችን መመለስ
የለብንም። የጊዛውን ሳይሆን የመጨረሻውን ማሰብ አለብን ። 2 ጢሞ 4 ፥10 ። መዜ 6 ፥6 ።

2. በደላችን በንስሐ እንደሚሰረይልን ማመን

ክርስቶስ ደሙን ያፈሰሰው በደላችንን ለመደምሰስ ስለሆነ ከበደላችን ሊያነጻን የታመነ አምላክ ነው ።
ከሠራነው ብዘ ኃጢአት አንጻር የሚሰጠን ቀኖና ትንሽ መስሎ ቢታየንም ። ማሰብ ያለብን የራሳችንን
በደል ሳይሆን የእግዙአብሔርን ቸርነት ነው ። ከእኛ በደል የእግዙአብሔር የቸርነት ሥራው እጅግ
ይበልጣልና የታ዗ዜነውን ፈጽመን የቀረውን እንደቸርነትህ ማለት ይገባል ። ‚የታ዗ዚችሁትን ባደረጋችሁ ጊዛ
የማንጠቅም ባሪያዎች ነን በሉ‛ ተብለናልና ። ሉቃ 17 ፥ 10 ።

3. በሥጋውና በደሙ መታተም (መቁረብ)

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 35


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

አንድ የተራበ ሰው እጁን ስለታጠበ ብቻ አይጠግብም ። የግድ ምግብ መብላት አለበት ። ንስሐ ማለት
መታጠብ ፣ ከእድፍ (ከኃጢአት) መንጻት ማለት ሲሆን ፤ ድኅነት የሚገኘው የ዗ለዓለም ሕይወት
የሚሰጠውን ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን በመቀበል ነው ። ዮሐ 6፥33 ። ብዘዎቹ መቁረብን እንደ
ትርፍ ነገርና በዕድሜ የተገደበ (ለሽማግሌ ብቻ) አድርገው ስለሚቆጥሩት ለመቀበል ሲ዗ጋጁ አይታዩም ።
ነገር ግን ክርስቲያን የሆነ ሁሉ ቅዱስ ቁርባን የግድ ያስፈልገዋል ። ቀኖና የተቀበልንበት በደላችን
የሚሰረየው ሥጋውን ስንበላ ፣ ደሙንም ስንጠጣ ነውና ።

4. ሁሌም ለንስሐ መ዗ጋጀት

ንስሐ ከገባንና ከቆርብን በኋላ እንደገና በኃጢአት ልንወድቅ እንችላለን። አምለካችን ‚ለምን ንስሐ
አልገባህም እንጅ ለምን ኃጢአት ሠራህ? አይልምና‛ ሁለተኛ ስንበድል ሀፍረት ሳይሰማንና ከኃጢአት
መላቀቅ ካልቻልሁ በየጊዛው የንስሐ አባቴን ከማስቸግር አርፌ ብቀመጥ ይሻለኛል በማለት ፡ ሁሉንም
እርግፍ አድርገን እንድተወው ፡

ክፉ ሀሳብ በአምሯችን ሊፈታተነን ይችላል ። ነገር ግን ከንስሐ በኋላ እንደ መላእክት በቅድስና ብቻ
እንኖራለን ማለት ሳይሆን ‚ጻድቅ ሰባት ጊዛ ይወድቃል ፤ ሰባት ጊዛ ይነሳል‛ ምሳ 24፥ 16 ። እንደተባለ ፡
አምላካችን ብንወድቅ ሊያነሳን ፤ ብንጠፋ ሊፈልገን ፤ ብንርቅ ሊያቀርበን ፤ በኃጢአት ብንረክስ ሊቀድሰን
(እንደ ባ዗ቶ ሊያጠራን) የታመነ አምላክ ስለሆነ ተስፋ ሳንቆርጥ ፤ በኃጢአታችን ሳንደበቅ ፤ ዗ወትር ለንስሓ
መ዗ጋጀት አለብን። ኢሳ 1 ፥ 18 ።

7.ምሥጢረ ክህነት/ሥርዓተ ክህነት/


ካህን ፦ ተክህነ አገለገለ ። ካለው የግዕዜ ቃል የተገኘ ሲሆን ፤ ካህን ማለት የእግዙአብሔር አገልጋይ ፤
የምዕመናን አባት ፤ ጠባቂ ፤ መጋቢ ማለት ነው ።

ምሥጢረ ክህነት በብሉይ ኪዳን


የክህነት አንዱ መገለጫው መስዋዕት ማቅረብ ሲሆን ፤ ለመጀመሪያ ጊዛ ለዙህ አገልግሎት የተመረጠውና
ካህን ተብሎ የተጠራው መልከ ጼዴቅ ነው ። ዗ፍ 14፥18 ። በኋላም እግዙአብሔር በቃል ኪዳኑ ታቦት ፊት
በቤተ መቅደስ እግዙአብሔርን የሚያገለግል የሕዜቡን ኃጢአት እየተቀበለ ከእግዙአብሔር የሚያስታርቅ
ካህን እንዲመርጥ ሙሴን ስላ዗዗ው ከመልከ ጼዴቅ በኋላ አሮን ተሾመ ።

ከአሮን እስከ ዮሐንስ መጥምቅ ደረስ ረጅሙን የብሉይ ኪዳን ዗መን ከአሮን ዗ር ብቻ የሚወለዱት ቅብዓ
ክህነት እየተቀቡ በካህንነት እያገለገሉ አልፈዋል ።

ነገር ግን በ዗ር ሐረግ ላይ የተመሠረተው ክህነት ለሐዲስ ኪዳኑ ክህነት ምሳሌ ስለነበረ ፍፁምና ዗ላቂ
አልነበረምና መስዋዕቱም ሆነ የአመራረጡ ሂደት በሌላ ተተካ ።

዗ላቂ ያልሆነበትና በሌላ የተተካበት ምክንያት

 ክህነቱ በ዗ር ብቻ የተገደበ ስለነበረ በሐዲስ ኪዳን ህጉንና ሥርዓቱን አሟልቶ ለተገኘ ለማንኛውም
ሕዜብ የተፈቀደ ሆነ ። ክርስቶስ የመጣው ለዓለም ሁሉ ነውና ።

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 36


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

 መስዋዕታቸው ፍጹም ድኅነት የማያሰጥ በመሆኑ በክርስቶስ ሥጋና ደም ተተካ ። ዮሐ 6 ፥ 32 ።


 አገልግሎቱ ለጊዛው ከሥጋ መቅሰፍት ከማዳን ያላለፈ ነበረ ፤ በሐዲስ ኪዳን ግን በምድርም
በሰማይም ማሰር በሚችሉ ፣ በነፍስም በስጋም ላይ ሥልጣን ባላቸው ካህናት ተተካ ። ማቴ 18 ፥
18 ።

ምሥጢረ ክህነት በሐዲስ ኪዳን


በብሉይ ኪዳን የመጨረሻው ካህን መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ሲሆን ፤ ከእሱ በኋላ የብሉይ ኪዳን
ክህነት አልፏል ። ጌታችን ወደ ዮርዳኖስ ሄዶ በዮሐንስ እጅ በመጠመቅ ፡ ካህኑ በሚገኝበት ቦታ ቤተ
ክርስቲያን ድረስ ሄደን በካህኑ እጅ መጠመቅ እንዳለብን አስተምሮናል ። ማቴ 3 ፥13 ።

ጌታችን ሲያስተምር ስለ ካህናት በብዘ ቦታ ተናግሯል ። ሂድና ራስህን ለካህን አሳይ ። ማቴ 8 ፥ 4 ። አንተ
ብፁዕ ነህ ፡ የመንግስተ ሰማያትንም መክፈቻ እሰጥሃለሁ… ። ማቴ 16 ፥ 17 ። እውነት እላችኋለሁ
በምድር ያሰራችሁት በሰማይ የታሰረ ፣ በምድር የፈታችሁት በሰማይ የተፈታ ይሆናል ። ማቴ 18 ፥ 18 ።
ይህን የተናገረው በመዋዕለ ስብከቱ ሲሆን ከሙታን ከተነሳ በኋላም ለሐዋርያት አረጋግጦላቸዋል ። ሂዱና
በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም አጥምቋቸው ። ማቴ 28 ፥ 19 ።..እፍ አለባቸውና መንፈስ ቅዱስን
ተቀበሉ ። ዮሐ 20 ፥ 22 ። በመጨረሻም ቅዱስ ዼጥሮስን ‚….ስምዖን ሆይ በጎቼን ጠብቅ ፤ (ለጊዛው አስራ
ሁለቱን ሐዋርያት ፡ ለፍጻሜው ወላጆችን) ፣ ጠቦቶቼን ጠብቅ ፤ (ለጊዛው ሰብዓ አርድዕትን ፡ ለፍጻሜው
ወጣቶችን) ፣ ግልገሎቼን ጠብቅ (ለጊዛው ሰላሳ ስድስቱ ቅዱሳት አንስትን ፡ ለፍጻሜው ህጻናትን)‛ በማለት
ሐዋርያትን ዸዸሳት ፣ ቅዱስ ዼጥሮስን የመጀመሪያ ሊቀ ዻዻሳት አድርጎ ሾመው ። ዮሐ 21 ፥ 15 ። ከዙህ
ጊዛ ጀምሮ ቤተ ክርስቲያን በሊቀ ዸዸስና በዸዸሳት በሚመራ መንፈሳዊ ጉባኤ (ቅዱስ ሲኖዶስ) አማካኝነት
እየተመራች አገልግሎቷን ታካሂዳለች ።

 የክህነት ደረጃዎች
 ሊቀ ዻሳሳት
ሊቃነ ዸሳሳት ‚ፓትርያርክ‛ እየተባለም ይጠራል ። በአንዲት ቤተ ክርስቲያን (በአንድ ሲኖዶስ) ላይ የበላይ
ሆኖ የሚሾም የሁሉም አባት ነው ። የሐዋ ሥራ 20 ፥ 28 ። በሕዜብና በካህናት ከተመረጠ በኋላ በዻሳሳት
ይሾማል ። ፍት ነገ 5 ። ረስጣ 2 ። ፓትርያርክ ያወገ዗ውን ዻዻስ አይፈታውም ። መንፈሳዊ ሥልጣኑ
ከሁሉም በላይ ነውና። (ሲኖ 51) ፓትርያርክ በመላዋ ቤተ ክርስቲያን በጸሎት ጊዛ ስሙ ይጠራል ።

ኤዺስ ቆዾስ
ዻዻስ በአንድ ሀገረ ስብከት አባት ሆኖ የሚሾም ነው ። ሲያገለግል በነበረበት አካባቢ ባሉ ምዕመናን
ጥቆማና ድምጽ በርዕሰ ሊቃነ ዻሳሳቱና በሲኖዶስ ፈቃድ ይሾማል። (ፍት ነገ 5 : አብጥ 2) በአንድ ዻዻስ
ብቻ አይሾምም። (ፍት ነገ 5 : ረስ 58 : ዲድ 34) ዻዻስ በሀገረ ስብከቱ በጸሎት ጊዛ ስሙ ይጠራል። (ፍት 5
: ክፍ 4) አዲስ ጽላት ፣ አዲስ ቤተ ክርስቲያን ፣ ይባርካል ። ለቄስ ለዲያቆን ሥልጣነ ክህነት ይሰጣል ። (1
ጢሞ 5 ፥ 2 : ፍት ነገ አን 5 ክፍ 4 )

ሥርዓት ሢመት

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 37


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

 ኤጲስ ቆጶሳቱ አዲሱን ኤጲስ ቆጶስ ከመሾማቸው በፊት እጃቸውን ይታጠባሉ። /ፍትነገ. አን፬፡፡/
 ተሿሚውን ኤጲስ ቆጶስ መስቀል ያስይዘታል።
 ኤጲስ ቆጶስ በአንድ ኤጲስ ቆጶስ አይሾምም። ከርእሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ ጋር ሁለት ወይም ሦስት ሊቃነ
ጳጳሳት /ጳጳሳት/ አንብሮተ እድ በማድረግ ይሾማሉ። /አብጥሊስ ፪፡፡/
 ኤጲስ ቆጶስ የሚሾመው በሚሾምበት ሀገር ካህናትና ምእመናን ምርጫና በርእሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ
ፈቃድ ነው። /አብጥሊስ ፪፡፡/
ቀሳውስት
ቅስና የሚቀበሉት በዲቁና ክህነት በማገልገል ላይ ያሉ ሲሆኑ ፤ በሁለት መንገድ ይሾማሉ ።

1. በምንኩስና የተወሰነ ያላገባ ጌታን እንዴት እንደሚያገለግል የጌታን ነገር ያስባል ( 1 ቆሮ 7 ፥ 32 )


በማለት ቅዱስ ዻውሎስ እንደተናገረ ፤ በምንኩስና ለመኖር የፈለገ አስቀድሞ ወደ ገዳም ሄዶ
የምንኩስናን ሕይወት መማርና አባቶችን እያገለገለ በተግባር ማየት አለበት ። በገዳም የሚሰጠውን
አገልግሎት ከፈጸመ በኋላ ፤ አበምኔቱ ሲፈቅድለት ሥርዓተ ገዳሙ በሚያዜ዗ው መሠረት መዓርገ
ምንኩስና ይቀበላል ። (ይመነኩሳል)ከምንከስና በኋላ ለክህነት የሚያበቃውን ትምህርት ተምሮ
በየደረጃው ያሉትን የሥልጣነ መዓርጋት። በድንግልና ከመነኮሰና በትም ሕርቱም ሆነ በግብረ ገብነቱ
በቂ ሆኖ ከተገኘ እስከ መጨረሻው የቤተ ክርስቲያን መዓርግ ‚ጵጵስና‛ ሊደርስ ይችላል ።
2. በህግ የተወሰኑ ዲያቆናት በአንድ ህግ ከተወሰኑ ፤ በኋላ ለቅስና የሚያበቃ ትምህርትና ሥነ ምግባር
ካላቸውና በሚያገለግ ሉበት አጥቢያ ሕዜብ ድምጽ ከተደገፉ ፤ ሊቀ ዻዻሱ ብቃታቸውን መዜኖ የቅስና
መዓርግ ይሰጣቸዋል። (ፍገ ፡ 6)

ሰላሳ ዓመት ያልሆነው ቅስና አይሾምም ። ፍት ነገ ፡ 6 ። የቀሳውስት የአገልግሎት ድርሻ አስተምሮ


ማጥመቅ ፤ ንስሐ መቀበልና መና዗ዜ ፣ (ማሰርና መፍታት) ፤ ቀድሶ ማቁረብ ፤ ማስተማር…. ናቸው ።

ካህን የመጀመሪያ ሚስቱ ከሞተችበት ፤ መነኩሴም ምንኩስናውን ከተወው በኋላ የቅስና (የክህነት) ሥራ
መሥራት አይፈ ቀድለትም ። ከማኅበረ ምዕመናን ግን አይለይም ።

ዲያቆናት
ዲያቆናት ካህናትን የሚራዱና የሚላላኩ ሲሆኑ ፤ በአገልግሎታቸው መሠረት የሚከተሉት ደረጃዎች
አሏቸው

1. ዲያቆን፡-አስቀድሞ ሃይማኖቱን የተረዳ ፣ በምዕመናን ዗ንድ በግብረ ገብነቱ የታወቀና


የተመሰከረለት ፣ ለዲቁና አገልግሎት የሚያበቃውን ትምህርት ጠንቅቆ የተማረ ፤ ሆኖ ሲገኝ
በአንብሮተ ዕድ (እጅ በመጫን) ይሾማል ። የተለየ ብቃትና ችሎታ ከሌለው በቀር ዕድሜው ከሃያ
አምስት ዓመት በታች የሆነ ዲቁና አይሾምም ። ዲያቆን ከመጀመሪያ (ከህግ) ሚስቱ ከተፋታና ሌላ
ካገባ ፣ ሃይማኖቱን ለውጦ በመናፍቃን ከተጠመቀ ፣ ከክህነቱ ይሻራል ። ፍት ነገ ፡ 7 ። ክፍል ፡ 5 ።
ዲያቆናት መቅደስ ይገባሉ ፤ ነገር ግን መንበርና ታቦት ፣ (ከተለወጠ በኋላ) ሥጋውንና ደሙን
በእጃቸው አይነኩም ። ዲያቆናት ለተልእኮ የሚፋጠኑ ፣ በትህትና የሚላላኩ ፣ በኑሯቸው ለሌላው
አርአያ መሆን ይገባቸዋል ።
2. ንፍቀ ዲያቆን፡- የዲያቆን ረዳት ሲሆን ፤ መንፈሳዊ ሕይወቱ ፣ ግብረ ገብነቱና የሃይማኖቱ ጽናት
በሚያገለግልበት አጥቢያ ካህናትና ምዕመናን የተመሠከረለት ። ፍት ነገ 8 ። ንፍቀ ዲያቆን በቃል ብቻ

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 38


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

ይሾማል ፤ አንብሮተ ዕድ ‚እጅ በማጫን‛ አይደረግለትም ። ፍ ነ 8 ክፍ 2 ። የዲያቆን ረዳት


እንደመሆኑ መጠን በሥራው ሁሉ ያግ዗ዋል እንጅ ንዋየ ቅድሳት አይነካም ። ፍት ነገ 8 ። ዶክ 45 ፣
46 ። ጥፋት ሠርቶ ከተገኘ ከክህነቱ ይሻራል ። ፍት ነገ ፡ 8 ፡ ክፍል ፡ 4 ።
3. አናጉንስጢስ፡-አገልግሎቱ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ መጻሕፍት ማንበብ ሲሆን ፤ ትምህርቱና በግብረ
ገብነቱ ከታየ በኋላ ተመ ርጦ ይሾማል ። ፍት ነገ 8 ክፍል1 ። አናጉንስጢስ አንብሮተ ዕድ
አይደረግለትም በቃል ብቻ ይሾማል ። ፍት ነገ 8 ፡ ክፍ ፡ 2 ። በአገልግሎት ጊዛ ዲያቆናት በቅዳሴ
ሠዓት የሚለብሱትን ልብሰ ተክህኖ አይለብስም ። ፍት ነገ 8 ፡ ክፍ 3 ። አናጉንስጢስ ጥፋት
ከተገኘበት ከሥራ ታግዶ ከዓመት በኋላ ይመለሳል ። ከጥፋቱ ካልታረመ ከአገልግሎቱ ይሻራል ። ፍት
8 ክፍል 4 ። ሚስቱ ከሞተችበት ሌላ አግብቶ ማገልገል ይችላል ። ፍት ፡ 4 ፡ ክ ፡ 5 ።
4. መ዗ምራን፡-በቡራኬ ይሾማሉ ። ፍ ነገ ፡ 8 ክፍ ፡ 2 ። ከመዜሙረ ዳዊት ፣ በሀገራችን የቅዱስ ያሬድን
ዜማሬም ይ዗ምራሉ ። በሚ዗ምሩበት ጊዛ ልብሰ ተክህኖ አይለብሱም ። ፍት ገነ ፡ 8 ክፍ ፡ 3 ።
መ዗ምራን ሚስታቸው ከሞተችባቸው ሌላ ማግባት ይችላሉ ። ፍት ነገ ፡ 8 ክ ፡ 5 ። በሀገራችን
መ዗ምራን ማለት የማኅሌት ትምህርት የተማሩትን ሲሆን ፤ እነዙህም ሥልጣነ ክህነት (ዲቁና ቅስና ፣
ከዙያም በላይ) ካላቸው በሁለቱም (በማኅሌትም በክህነታቸውም) ማገልገል ይችላሉ ። የሰንበት
ት‚ምህርት መንፈሳውያን ወጣቶችም መ዗ምራን ይባላሉ ።
5. አጻዌ ኆኅት፡-በቃል ብቻ ይሾማል አገልግሎቱ በር መክፈትና መዜጋት ሲሆን ልብሰ ተክህኖ
አይለብስም ። ፍት ነገ 8 ፡ ክፍ ፡ 3 ። ሚስቱ ከሞተችበት ሌላ አግብቶ ማገልገል ይችላል ። ፍት ነገ ፡ 8 ፡
ክፍ ፡ 3 ።
6. ሴቶች ዲያቆናውያት ፡-በትዳር ተወስነው የኖሩ ፣ ልጆቻቸውን በሥርዓት ያሳደጉ ፣ በቅዱስ ቁርባን
የተወሰኑ ፣ ለአገልግሎት የ ሚፋጠኑ ፣ 8 ዓመት የሆናቸው ፤ ዲያቆዊት ሆነው በቃል ይሾማሉ ። 1
ጢሞ 5 ፥ 9 ። ፍት ፡ ነ 8 ፡1 ። ዲድ 17 ።አገልግሎታቸው
o ከካህናቱ ወደ ሴቶች ይላላካሉ ፤ ሴቶች ክርስትና ሲነሱ ፤ ካህኑ እጃቸውን ይዝ ከአንገተችው በታች
ቅብዓ ሜሮን ይቀባሉ ።
o አይባርኩም ፤ ቄስና ዲያቆን የሚሠራውን የክህነት ሥራ አይሠሩም በሴቶች በር ቆመው
ይቆጣጠራሉ ።
o እንደ ዲያቆኑ ተንሥኡ ጸልዩ አይሉም ቅስና አይሾሙም ጉባዔ በጸሎት አይከፍቱም ። (ፍነ 8 ክፍ 1)

እነዙህም ፤ ፈቃደ እግዙአብሔር ሆኖ ከሌላው ምዕመን ተለይተው እነሱ ወደ ቤተክርስቲያን ስለቀረቡ ፤


ምዕመናን በሥጋ ድካም ቢሳሳቱ ፤ ከሚያገለግሉት ጓደኞቻቸው መካከልም የተሳሳተ ወንድማቸው ቢኖር
ሊመክሩት ፤ ሊያጽናኑት ይገባል እንጅ ፤ የራሳቸውን ጽድቅ የወንድማቸውን ስህተት እያወሩ ፤ ለሚድኑት
መሰናክል መሆን የለባቸውም። (ሉቃ 18 ፥ 9)

8.ሥርዓተ ጸሎት

ጸሎት ጸለየ፡- ለመነ፣ ጠየቀ አማለደ፣ ማለደ ካለው የግዕዜ ቃል የወጣ ቃል ነው፡፡ ጸሎት ማለት ጠቅለል
አድርገን ስንመለከተው ከእግዙአብሔር ጋር መነጋገር እግዙአብሔርን ማመስገን መለመን፣ መጠየቅ፣
መማለድ፣ መማፀን ነው፡፡ ‚ጸሎት ብሂል ተናግሮ ምስለ እግዙአብሔር፡፡‛ አባታችን አዳምም ከመላእክት
ተምሮ በየሰዓቱ ይጸልይ ያመሰግን ነበር፡፡ ዲያብሎስ በእባብ አድሮ ወደ አዳም በመጣ ጊዛ ጸሎት እያደረገ
ስለነበር ዲያብሎስን ድል ነሥቶታል ሔዋንን ግን ሥራ ፈትታ እግሯን ዗ርግታ ስለአገኛት ድል ነስቷታል፡፡

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 39


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

ጸሎት ሰማእታት ከነደደ እሳት፣ ከተሳለ ስለት፣ ከአላውያን መኳንንት፣ ከአሕዚብ ነገሥታት ከዲያብሎስ
ተንኮል እና ሽንገላ ዲያብሎስ በእነርሱ ላይ ከአጠመደው አሽከላ የዳኑበት ጋሻ ነው፡፡ ኤፌ.6፥10 21 ጸሎት፣
ሰው አሳቡን ለእግዙአብሔር የሚገልጥበት እግዙአብሔርም የሰውን ልመና ተቀብሎ ፈቃዱን
የሚፈጽምበት ረቂቅ ምስጢር ነው፡፡

የጸሎት መሠረቱ ‚ዕሹ ታገኛላችሁ ለምኑ ይሰጣችኋል ደጁ ምቱ ይከፈትላችኋል‛ የሚለው የጌታችን


ትምህርት ነው ማቴ.7፥7 ጸሎት፡- በሦስት ክፍል ይከፈላል

 ጸሎተ አኰቴት
 ጸሎተ ምህላ
 ጸሎተ አስተብቊዖት

ጸሎተ አኰቴት፡-
ማለት እግዙአብሔርን ከሁሉም አስቀድሞ ስለተደረገልን ነገር በማመስገን የሚጀመር ጸሎት ነው ይህም
ዓይነት ጸሎት የቅዱስ ባስልዮስን የምስጋና ጸሎት የመሰለ ነው፡፡ ‚ነአኲቶ ለገባሬ ሠናያት ላዕሌነ
እግዙአብሔር መሐሪ‛

‚ለእኛ በጎ ነገርን ያደረገ ይቅርባይ እግዙአብሔር አምላካችንን እናመሰግነዋለን‛ ይልና ምክንኀያቱን ሲገልጥ
ጠብቆናልና፥ አቅርቦናልና፥ ወደ እርሱም ተቀብሎናልና፥ እስከዙችም ሰዓት አድርሶናልና‛ ይላል፡፡ /ሥርዐተ
ቅዳሴ/ ይህ ጸሎት የምስጋና ጸሎት /ጸሎተ አኰቴት/ ይባላል፡፡

ቅዱስ ጳውሎስም ይህንን የምስጋና ጸሎት ለፊልጵስዮስ ክርስቲያኖች ሲጽፍላቸው ‚ነገር ግን በሁሉ ነገር
ጸልዩ ማልዱም እያመሰገናችሁም ልመናችሁን ለእግዙአብሔር ግለጡ‛ ይላል፡፡ ፊል.4፥6 ዳግመኛም
‚ስለእናንተ በኢየሱስ ክርስቶስ ከእግዙአብሔር ዗ንድ ለእናንተ ስለተሰጣችሁ ጸጋ ዗ወትር እግዙአብሔርን
አመስግነዋለሁ‛ 1ቆሮ.1፥4 ብሎ ከመለመን አስቀድሞ እግዙአብሔርን ማመስገን አስፈላጊ መሆኑን
አስተምሯል፡፡ በዙህ መሠረት ሰው የተደረገለትን በጎ ነገር ሁሉ በማሰብ ፈጣሪውን ማመስገን
ከማመስገንም ቀጥሎ የሚያስፈልገውን ከፈጣሪው መለመን አስፈላጊ ነው፡፡

ጸሎተ ምህላ፡-
ጸሎተ ምህላ ስለፈውሰ ሕሙማን ስለ ሀገርና ስለነገሥታት ስለ ጳጳሳት፣ ካህናት ዲያቆናት፣ ምዕመናን
ሕይወት ቸነፈር፣ ጦርነት፣ ረሀብ፣ ድርቅ ወይም ሌላ አስጊ ነገር በሆነ ጊዛ በብዚት፣ በማኅበር የሚጸለይ
ጸሎት ነው፡፡ የምህላ ጸሎት ሲጸለይ በእስራኤል ላይ ቸነፈር በተነሣ ጊዛ አሮን በሽተኞን ባንድ ወገን
ጤነኞችን ባንድ ወገን አድርጎ የክህነት ልብሱን ለብሶ ማዕጠንተ ወርቁን ይዝ በራስህ የማልክላቸውን
አብርሃምን፣ ይስሐቅን፣ ያዕቆብን አስበህ የወገኖችህን ኀጢአት ይቅር በል‛ እንደጸለየላቸው ነው፡፡ ዗ኁ.16፥
46-50

ዚሬም ካህናት ከጠቀስናቸው አስጊ ነገሮች ማንኛውም በሀገር ላይ ቢመጣ ወደ ሀገር እንዳይገባ ገብቶ
ቢሆን ከፍ ያለ ጉዳት እንዳያመጣ የክህነት ልብስ ለብሰው ማዕጠንቱ ይ዗ው ሥዕለ ማርያም፣ መስቀል
አቅርበው ማኅበረ ክርስቲያንን ሰብስበው፣ ኢየሱስ ክርስቶስን ‚ስለእኛ ከድንግል ማርያም መወለድህን
ስለእኛ መሠቀል መሞትህን አስበህ የህዜብን ኀጢአት ይቅር በል ከመዓት ወደ ምሕረት ተመለሰ‛ እያሉ
በምህላ ይጸልያሉ፡፡

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 40


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

የምህላ ጸሎት መአትን መቅሰፍትን ይመልሳል ጦርን፣ ቸነፈርን ያስታግሳል መሠረቱም፡፡‚ጾም ለዩ ምህላ
ስበኩ‛ ያለው ቃል ነው፡፡ ይህ ጸሎት በሰላም ጊዛ ሰላሙ ዗ላቂ እንዲሆን በጦርነት ጊዛ ለመከላከያነት ዋና
መሣሪያ ነው፡፡ ስለዙህ አጥብቀን ልንከተለው ይገባል፡፡

የምህላ ጸሎት ነገሠታት ከዘፋናቸው ወርደው ወንድ ሙሽራ ሴት ሙሽራ ከጫጉላቸው፣ ከመጋረጃቸው
ለምግብ የደረሱ ልጆች ከምግብ ለምግብ ያልደረሱ ከጡት ተከልክለው ሕዜብ ሁሉ ምንጣፍ ለብሰው
አመድ ነስንሰው የሚጸልዩት ከፍተኛ ጸሎት ነው ኢዩ.2፥12-18፣ ዮና.3፥5

ጸሎተ አስብቊዖት
ይህ ጸሎት አንድ ሰው ስለሚፈልገው ነገር ቦታ ለይቶ ሱባኤ ገብቶ የሚጸልየው ጸሎት ነው፡፡ ይህ ጸሎት
በተለይ ጣዕመ ጸጋን በቀመሱ በተባሕትዎ፣ በምናኔ በገዳም በሚኖሩ አበው ዗ንድ የተለመደና የሚደረግ
ጸሎት ነው፡፡ ወጣንያን እግዙአብሔርን ጠይቀው አድርግ አታድርግ የሚል መልስን አይጠብቁም፡፡ ፍጹማን
አባቶች ግን እግዙአብሔር ጠይቀው አድርግ ወይም አታድርግ የሚል ፈቃደ እግዙአብሔርን ሳይቀበሉ
የሚያደርጉት ነገር የለምና ቦታ፣ ጊዛ ወስነው ፈቃደ እግዙአብሔር ይጠይቃሉ፡፡ ይህ ጸሎተ አስተብቊዖት
ይባላል፡፡ ይህም ማለት መላልሶ ደጋግሞ ያለ ዕረፍት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ የሚደረግ ጸሎት ነው፡፡
ለምሳሌ ትልቁ መቃርስ ዓለምን ዝሮ ለመጎብኘት ለተከታታይ አምስት ዓመታት እግዙአብሔርን ከለመነ
በኋላ እየዝረ መካነ ቅዱሳንን እንዲጎበኝ ከእግዙአብሔር ፈቃድ አግኝቷል በዙህም ከእርሱ ከገድል በትሩፋት
የሚበልጡ መናንያን በማግኘቱ መነኮሳትማ እነርሱ እንጂ እኔ ምንድን ነኝ? እያለ ራሱን እየወቀሰ
እንደተመለሰ በመጽሐፈ መነኮሳት ተጽፎ እናገኛለን፡፡ በቤተ ክርስቲያናችን ‚መስተበቊዕ‛ የሚባል የጸሎት
ክፍል፡፡ አለ ይህ ጸሎት በካህናት አባቶቻችን ስለሙታን፣ ስለሕያዋን፣ ስለነገሠታት፣ ስለ ጳጳሳት ስለ ንዑሰ
ክርስቲያን፣ ስለ ምእመናን መባዕ ስለሚያቀርቡ ስለነጋድያን፣ ስለዜናም ስለ ወንዝች የሚጸለይ ትልቅ ቦታ
የሚሰጠው የጸሎት ክፍል ነው፡፡

ጠቅላላውን በቤተ ክርስቲያን የሚጸልዩ ጸሎታት ጸሎተ ፍትሐት፣ ጸሎተ ተክሊል፣ ጸሎተ ህሙማን፣ ጸሎተ
ቅዳሴ፣ ጸሎተ ሰዓታት፣ የግል ጸሎት፣ የማኅበር ጸሎት በተጨማሪም ጸሎተ ንዋየ ቅዱሳት እነዙህ ሁሉ ከላይ
ከ዗ረ዗ርዓቸው ሦስቱ የጸሎት ክፍሎች አይወጡም፡፡ ከጸሎተ አኰቴት ከጸሎተ ምህላ፣ ከጸሎተ
አስተበቊዖት ይመደባሉ፡፡ እነዙህን ጸሎታት በሰቂለ ኅሊና በአንቃዕድዎ /ዐይንን ወደ እግዙአብሔር
በማንሳት/ መጸለይ ታላቅ ዋጋ የሚያሰጥ ከሰይጣን ወጥመድ የሚታደግ ሕይወትን የሚስተካከል
ከእግዙአብሔር ጋር የሚያስታርቅ አጋንንትን የሚያርቅ ኀይለ እግዙአብሔርን ለሚጸልየው የሚያስታጥቅ
መላእክትን የሚያስመስል ነው፡፡

ሰባቱ የጸሎት ጊዜያት


1. የጸሎት ጊዜያት

ልበ አምላክ ነቢየ ልዑል ቅዱስ ዳዊት‛ስብዓ ለእለትየ እሴብሐከ በእንተ ኵነኔ ጽድቅከ ፣ስለ ጽድቅህ ፍርድ
በቀን ሰባት ጊዛ አመሰግንሃለው‛/መዜ 118-164/ብሎ እንደተናገረ ክርስቲያን የሆነ ሁሉ ሰባት ጊዛ
በየእለቱ እንዲጸልይ ቤተ ክርስቲያን ታስተምረናለች፡፡ሰባቱ የጸሎት ጊዛያትም የሚከተሉት ናቸው፡፡

1.1 ጸሎተ ነግህ

ቅዱስ ዳዊት ‚አምላኬ አምላኬ በማለዳ ወደ አንተ እገሰግሳለሁ‛ መዜ 62÷11 እንዳለ ሌሊቱ አልፎ ቀኑ
ሲተካ፣ከመኝታችን ስንነሳ ምንጸልየው የጸሎት ዓይነት ጸሎተ ነግህ ይባላል፡፡በዙህ ጊዛ የሚከተሉትን

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 41


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

ምስጢራት እያሰብን መጸለይ ይገባናል፡፡ ሌሊቱን አሳልፎ ቀኑን ስለተካልን እያመሰገንን ወጥተን እስክንገባ
በሰላም ጠብቆ ውሎአችንን የተባረከ እንዲያደርግልን እንጸልያለን። የመጀመሪያው ሰው አዳም
የተፈጠረበትም ሰዓት በመሆኑ ያንን እያሰብን እንጸልያለን፡፡ የሰውን ልጅ በመዓልትና በሌሊት የሚጠብቁ
መላእክት ለተልዕኮ ሲፋጠኑ የሚገናኙበት ሰዓት ነው፡፡የሌሊቱ መልአክ ሲሄድ የቀኑ መልአክ ሲቀርብና
ሲተካ የሚገናኙበት በመሆኑ በዙህም ሰዓት እንጸልያለን፡፡ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ
ሰው ልጆች በደል በጲላጦስ አደባባይ የቆመበት ሰዓት በመሆኑ እንጸልያለን።

1.2 ጸሎተ ሠለስት (3 ሰዓት)

ከነግህ በመቀጠል የምንጸልየው ጸሎት ጸሎተ ሠለስት (የሦስት ሰዓት) ጸሎት ይባላል፡፡ይህ የጸሎት ጊዛ
ሔዋን የተፈጠረችበት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የቅዱስ ገብርኤልን ብሥራት የሰማችበት
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ሰው ልጆ ሲል በጲላጦስ አደባባይ የተገረፈበት ነቢዩ ዳንኤል
ፊቱን ወደ ኢየሩሳሌም አቅጣጫ መልሶ የቤቱን መስኮት ከፍቶ የጸለየበት ለአባቶቻችን ሐዋርያት መንፈስ
ቅዱስ የወረደበት /በኢየሩሳሌም ጸንተው በመቆየታቸው ከእግዙአብሔር ዗ንድ ይህንን ታላቅ ጸጋ
የተቀበሉበት /ሰዓት ነው፡፡

1.3 ቀትር (6 ሰዓት)

በእለቱ እኩሌታ ላይ የምናገኘው ይህ ሰዓትም እንደዙሁ የጸሎት ጊዛ ነው፡፡ይህም ጊዛ ሰይጣን አዳምን


ያሳተበት በዕፀ በለስ ምክንያት ለስሕተት የተዳረገውን አዳምን ለማዳን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ
ክርስቶስ በቀራንዮ አደባባይ የዋለበት የቀን እኩሌታ በመሆኑ የፀሐይ ሙቀት የሚያይልበት የሰው ልጅ
ለድካም የሚዳረግበት በዙህም ምክንያት አጋንንት የሚበረታቱበት ጊዛ ነው። ስለዙህ የአዳምን ስሕተት፣
የዳግማዊ አዳም የኢየሱስ ክርስቶስ መሰቀልና መሞት፣እያሰብን የቀን እኩሌታ በመሆኑ መዳከማችንን
ተገን አድርጎ አጋንንት እንዳይሰለጥንብን እየለመንን እንጸልያለን፡፡

1.4 ተሰዓተ ሰዓት (9 ሰዓት)

዗ጠኝ ሰዓት ላይ አራተኛውን ጸሎት እናደርሳለን።በዙህ ጊዛ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ


አዳምን ነጻ ለማውጣት በፈቃዱ ቅዱስ ሥጋውን ከቅድስት ነፍሱ የለየበት ሰዓት ነው። ቅዱሳን መላእክት
የሰው ልጆችን በጎም ሆነ ክፉ ተግባር ወደ ፈጣሪ የሚያሳርጉበት ነው ቆርኖሌዎስ የተባለ መቶ አለቃ
በጸሎት ጸንቶ ደጅ ሲጠና ከሰነበተ በኋላ ከፈጣሪው ምላሽ ያገኘበት ሰዓት ነው (ሐዋ 10÷ 9) በዙህ ጊዛ
የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን መከራ እና ሞት አያሰብን ቅዱሳት መላእክት ከፈጣሪያቸው
እንዲያስታርቁን እየለመንን የቆርኖሌዎስ እድል እንዲገጥመን እየተማጸንን እንጸልያለን፡፡

1.5 ጸሎተ ሰርክ (11 ሰዓት)

አምስተኛው የጸሎት ጊዛ የሠርክ ጸሎት ነው፡፡ስለዙህ የጸሎት ሰዓት ቅዱስ ዳዊት እንዲህ ይላል፡፡‛ጸሎቴን
እንደ ዕጣን በፊትህ ተቀበልልኝ እጅ መንሳቴም እንደ ሠርክ መሥዋዕት ትሁን‛ (መዜ 140 ÷2) ጌታችን
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዓለምን ለማዳን በፈቃዱ ነፍሱን ከሥጋው ከለየ በኋላ ወደ መቃብር
የወረደበት ሰዓት ነው፡፡ (ማቴ. 27÷ 57)

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 42


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

1.6 ጸሎተ ንዋም (የመኝታ ጊዜ ጸሎት)

ይህ ጊዛ ዕለቱን በሰላም አሳልፈን ለሌሊቱ ዕረፍት የምን዗ጋጅበት ነው፡፡በሰላም ላዋለን ፈጣሪ በሰላም
አሳድረን ብለን ራሳችንን በእምነት የምናስረክብበት ነው፡፡ እኛ ተኝተን የሚሆነውን አናውቅም እርሱ ግን
የማያንቀላፋ እረኛ ስለሆነ ይጠብቀናል።ስለዙህ ከመተኛታችን በፊት ሊሌሊቱን እንዲባርክልን እንጸልያለን።
በዙህ ጊዛ፡- ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ ዚሙርቱን በጌቴሴማኒ ጸሎት አስተምሯቸዋል፡፡
ቀኑ አልፎ በሌሊቱ ይተካል ስለዙህ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለጸሎት ማስተማሩን እያሰብን እንጸልያለን፡፡
ሰላም አሳድረንም ብለን ለፈጣሪ ራሳችንን በእምነት አደራ እናስረክባለን፡፡

1.7 መንፈቀ ሌሊት (እኩለ ሌሊት)

እኩለ ሌሊትም እንደ ቀናቱ የጸሎት ሰዓታት የተለያዩ ትርጉሞች አሉት ። ቅዱሰ ዳዊት ‘’መንፈቀ ሌሊት
እትነሣእ ከመ እግነይ ለከ በእንተ ኵነኔ ጽድቅከ‛‚ስለ ጽድቅህ ፍርድ በእኩለ ሌሊት አመሰግነህ ዗ንድ
እነሳለሁ‛/መዜ 118-62/በማለት ይህ ሰዓት ከእግዙአብሔር ጋራ የሚነጋገርበት እንደሆነ ገልጿል፡፡ ጌታችን
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቤተልሔም ዋሻ የተወለደበት ሰዓት ነው። ሞትን ድል አድርጎ በታላቅ
ኃይልም የተነሳው በሌሊት ነው። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግመኛ ለፍርድ ሚመጣበትም
ሰዓት ነው። ከዙህ የተነሳ ለእኛ ሲል ከሰማየ ሰማያት መውረዱን፣ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም
ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ መወለዱን በማሰብ ሞትን ድል እንደተነሳልንም አስበን በማመስገን
ዳግመኛ ለፍርድ ሲመጣ በቀኙ ከሚያቆማቸው ወገን እንዲያደርገን እየለመንን በዙህ ሰዓት እንጸልያለን፡፡

ሰባቱን የጸሎት ጊዜያት ጠብቀን መጸለይ ካልተቻለንስ?

በሰባቱ የጸሎት ሰዓታት የታቻለንን ያህል እንድንጸልይ ታ዗ናል፡፡እነዙህን የጸሎት ሰዓታት በገዳም ያሉ
መነኮሳት በየበረሃው የሚዝሩ ባሕታውያን ይጠብቋቸዋል፡፡ ይጸልዩባቸዋልም፡፡በከተማ በሥራ ምክንያት
ሩጫ በዜቶበት በሁሉም ሰዓት መጸለይ የማይችል ክርስቲያን ግን ቢያንስ በማለዳ ከእንቅልፉ ሲነሳ እና
ማታ ወደ መኝታው ሲያመራ መጸለይ ይገባዋል።ጠዋት እና ማታ በመጸለይ ከፈጣሪ ጋራ ያለው የአባትና
ልጅ ግንኙነት እንዳይቋረጥ ማድረግ ይገባዋል፡፡

ምን እንጸልይ?
በመደበኛነት ልንጸልያቸው የሚገቡ ጸሎታት / በቤተክርስቲያናችን አባቶች በገዳማቱ በአድባራቱ
የሚ዗ወተሩ እለታዊ ጸሎታት/ እነኚህ ናቸው፡፡

1.መዝሙረ ዳዊት

መዜሙረ ዳዊት በገዳማት ከሚኖሩ አበው መነኮሳት ባህታውያን ጀምሮ በካህናት፣ምእመናን በሁሉም
዗ንድ በየእለቱ የሚጸለይ ጸሎት ነው።አባቶች ከፊደል ቆጠራው ቀጥሎ ዳዊቱን ያጠኑና ከዙህ ጊዛ ጀምረው
እየደገሙት፣እየጸለዩበት ይኖራሉ።ዳዊት ሳይደግሙ ወደ ዕለታዊ ተግባራቸው አይሰማሩም።መዜሙረ
ዳዊት እንደሌሎች ጸሎታት ሁሉ በየዕለቱ ተለይቶ የሚጸለይ አለው።ቀጥለን እንመልከት ሰኞ ከ 1 – 30
ማክሰኞ ከ 31 – 60፣ረቡዕ ከ 61 – 80፣ሐሙስ ከ 81 – 110፣አርብ ከ 111 – 130፣ቅዳሜ ከ 131 – 150
እሁድ- ጸሎተ ነቢያት እና መኃልየ መኃልይ ዗ሰሎሞን ይጸለያል፡፡

አንድ ንጉሥ መዜሙረ ዳዊትን ስንጸልይ ለዕለቱ የታ዗዗ውን ሃያ እና ሰላሳ መዜሙር ማድረስ ባንችል
እንኳን አንድ ንጉሥ ማድረስ ይገባናል። አንድ ንጉሥ የሚባለው፡-አስር መዜሙር ነው፡፡ለምሳሌ ሰከኞ

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 43


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

አንድ ንጉስ ለማድረስ ከፈቀዱ ከ 1 – 10 ያለውን ያደርሳሉ፡፡ከማክሰኞ ከሆነ ደግሞ ከ 30 -40 ያውን
የመጀመሪያውን አስር መዜሙር ያደርሳሉ ማለት ነው፡፡ይህን ሁሉ ማድረስ ያልተቻለው ግን የተወሰኑ
መዜሙራትን መርጦ በየእለቱ ያደርሳል፡፡

2. ውዳሴ ማርያም

ውዳሴ ማርያም ከተቻለ የሰባቱን ዕለታት ካልተቻለ የእለቱን ማድረስ ተገቢ ነው።የ዗ወትር ጸሎት ካደረስን
በኋላ የዕለቱን ውዳሴ ማርያም አድርሰን ይዌድስዋ መላዕክትን ደግመን ከእመቤታችን በረከት ተሳታፊ
መሆን ተገቢ ነው፡፡ በዋልድባ የሚኖሩ መነኮሳት ውዳሴ ማርያም ከቅዳሴ ማርያም ሳያደርሱ ውለው
አያድሩም፡፡በየአብነት ትምህርት ቤቱ የሚገኙ መምህራንና ተማሪዎች እና በየገዳማት ያሉ መነኮሳት ሁሉ
ውዳሴ ማርያምን በየዕለቱ ያደርሳሉ፡፡እኛም ከአበው ተምረን ማታ ከመኝታ በፊት ወይም ጠዋት ስንነሳ
ይህን ጸሎት ማድረስ ተገቢ ነው፡፡

3. ወንጌል ዗ዮሐንስ

የዮሐንስ ወንጌልን በየምዕራፍ ከፋፍለን በየእለቱ ማንበብ ሌላው ጸሎት ነው፡፡አባቶች ይህንን ጸሎት
በየእለቱ እያደረሱ ብዘ ተጠቅመውበታል።

4.ሌሎች ጸሎታት

ውዳሴ አምላክ፣ ሰኔ ጎለጎታ፣ መልክአ ኢየሱስ፣ መልክአ ማርያም ፣ በመዜገበ ጸሎት እንዲሁም በመዜሙረ
ዳዊት መጽሐፍት ላይ ያሉትን ሌሎች ጸሎታት፣እንዲሁም ገድላት፣ተአምራትን፣እንደ ችሎታችን በየዕለቱ
እናደርሳለን፡፡ ቢያንስ ግን ይህ ሁሉ ባይሆንልን ከላይ የጠቀስነውን የመዜሙረ ዳዊትና ፣ውዳሴ ማርያምን
ጸሎት ማድረስ ይገባናል፡፡

9.ሥርዓተ ቀንዲል
ቅብዓ ቅዱስ /የተለየ የከበረ ዗ይት (ቅባት) እየተባለ ይጠራል። ይህም ከወይራ ዚፍ በጸሎት በመታገዜ
በረድኤተ እግዙአብሔር የሚ዗ጋጅ /የሚወጣ /዗ይት ነው። በተ዗ጋጀለት የክብር ዕቃ /ብልቃጥ/
ተደርጎ በከርሰ መንበር ወይም በዕቃ ቤት በክብር ይቀመጣል።

የቀንዲሉ አ዗ጋጅና ባለቤት ምሥጢሩንም ፈጻሚዋ ቤተ ክርስቲያን ናት፡፡ ከምእመናን ወገን


የታመሙ ሲኖሩ ወደ ቤተክርስቲያን ወደ ካህኑ ይመጣሉ። የማይችሉ የሆኑ እንደሆነ ካህኑን
/ካህናቱን/ ወደ ቤታቸው ይጠራሉ፡፡ ካህኑ /የንስሐ አባቱ/ ሕሙሙን ምእመን በማጽናናት ኃጢአቱን
እንዲና዗ዜ/ ንስሐ እንዲገባ/ ያደርገዋል::

በመቀጠልም ባቅሙ የሚችለውን ቀኖና እንዲፈጽም ያ዗ዋል:: ከዙያም ካህኑ /የንስሐ አባቱ/ ከሌሎች
ካህናት ጋር ሆኖ ምሥጢሩን ለታማሚው ለመፈጸም ይ዗ጋጃል፡፡ ከዙያም ቀንዲሉን /መብራቱን/
አብርቶ መጽሐፈ ቀንዲልን በመጠቀም የታ዗዗ውን ጸሎት ይጸልዩለታል።

በጸሎቱ ፍጻሜም የሕመምተኛውን ሕዋሳት በተለይ የታመመውን ክፍል በተጸለየበት ቅብዐ ቅዱስ

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 44


ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

በመስቀል አምሳል /ምልክት/ ይቀቡታል:: በመጨረሻም ከማእሰረ ኃጢአት የሚፈታበትን ሥርዓት


/ኑዚዛ/ ይፈጽሙለታል። ይህም ለታመመው ምእመን ፈውሰ ሥጋ፣ ፈውሰ ነፍስን ያድለዋል።

ሥርዓተ ቀንዲልን የሚፈጽሙት ሰባት ኤጲስ ቆጶሳት ወይም ቀሳውስት ሆነው ነው። እነዙህ ሰባት
መሆናቸው ሰባት ቁጥር በዕብራውያን ፍጹም ቁጥር እንደመሆኑ በምሥጢረ ቀንዲል ፍጹም
ሥርየትና ፈውስ መገኘቱን ለማጠየቅ ነው። እነሱም /ካህናቱ/ ቅዱስ ዮሐንስ በራእዩ ያያቸው የሰባቱ
የወርቅ መቅረዝችና መብራቶች ምሳሌ ናቸው። (ራእ፩፥፳፡፡) ከላይ እንደገለጽነው ኃጢአቱን ለተና዗዗ው
ምእመን በቀረበው ንጹሕ ዗ይት ላይ የታ዗዗ው ጸሎት ይደረሳል። ሰባቱም ካህናት በየተራ በታመመው ራስ
ላይ የታ዗ዘትን የወንጌል ክፍላት ያነባሉ ወንጌል ከተነበበ በኋላም ሰባቱም እጃቸውን በሕመምተኛው
ላይ ጭነው የታ዗ዘትን ጸሎታት ይጸልዩለታል፡፡

በመጨረሻም አስቀድመን እንደተናገርነው በሰባት እንጨቶች ጫፍ ላይ ጥጥ በመጠምጠም ተራ በተራ


በተጸለየበት ቅብዐ ዗ይት እየነከሩ አምስቱን የስሜት ሕዋሳት /ዓይኑን፣ ጆሮውን፣ አፍንጫውን፣ አፉንና
እጁን በመስቀል ምልክት ይቀቡታል፡፡ የዙህም ምክንያት በዓይኑ አይቶ፣ በጆሮው ሰምቶ፣ ባፍንጫው
አሽትቶ፣ በአፉ ተናግሮና በእጁ ዳሶ ለሠራው ኃጢአት ሥርየት እንዲሆነው ነው።

አእምሮ የሚገኝበት የአምስቱ የስሜት ሕዋሳት ማዕከልና የማስተዋል /የማሰብ/ ኃይል የሚገኝበት
ክፍል ነውና፤ በዋናነት ግንባርም ይቀባል፡፡ የልብ ማረፊያ ነውና ደረቱም ይቀባል፡፡ ሰውነቱን ሁሉ
ሊበክል የሚችል የርኩሰት ቁስል /ቁስለ ነፍስ/ የሚመነጭ ከሱ ነውና ፈጽሞ እንዲፈወስ እነዙህ ሁሉ
ይቀባሉ፡፡ ከቀሳውስት በታች ያሉ ዲያቆናት ግን ለካህናት ከመታ዗ዜና ከመራዳት በስተቀር ይህንን
ምሥጢር መፈጸም እንደማይችሉ የታወቀ ነው።

10.ማጠቃላያ (ምክረ አበው)


ወገኖቼ መንፈሳዊ ትውፊታችንን፣ ታሪካችንና ሃይማኖታችንን አጥብቀን እንያዜ። ዚሬ በአውሮፓና
በአሜሪካ ሰለጠንን፣ ወንጌል በራልን ብለው ሲመጻደቁ የነበሩና መንፈሳዊ ትውፊታቸውን አራግፈው
የጣሉ የፕሮቴስታንት ቤተ እምነቶች የአምልኮ መቅደሶቻቸውን ዗ግተው ወደ ዓለማዊነትና ወደ ለየለት
የክህደት ዓለም ውስጥ ገብተዋል። ቤተ መቅደሶቻቸውን ቡና ቤት፣ ልብስ መሸጫ ቡቲክና፣
የመኖሪያ አፓርትመንት አድርገውታል። ዚሬ ሃይማኖት የለሽ ትውልድ ፈጥረው ወጣቶቻቸው
የሰይጣን እምነት ተከታዮች፣ ሰዶማውያን፣ የአደንዚዥ ዕፅ ሱሰኞች፣ ዗ወትር የጌታ ስቅለት
የሚታሰብበትን ዕለተ አርብ በስካርና በጭፈራ የሚያነጉ የርኩሰት ተባባሪዎች ሆነዋል።

በአጭሩ ታቦትን ሲቃወሙ የነበሩ የፕሮቴስታንት ፓስተሮቻቸውና ተከታዮቻቸው በአብዚኛው


ሃይማኖት የለሾች ከሃድያን /ATHEIST/ ሆነው ቀርተዋል። ወገኖቼ ኢትዮጵያውያን እባካችሁ የኢትዮጵያ
ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን አጥባቃችሁ ያዘ ትውልዱን ከክርስቶስ ጋር በፍቅር አጣብቃ፣
ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 45
ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

በምግባርና በሃይማኖት ይዚ የቆየች ወደፊትም የምትኖር ብቸኛዋ የክርስቶስ ሙሽራ ይህችው እናት
ቤተክርስቲያን ነች።

ዚሬ በሐሰተኛ ነቢይትና በአጭበርባሪ ፓስተሮች በስሜት የሚነዳው ሕዜብ ለጊዛው ነው ከተወሰኑ


ዓመታት በኋላ ሁሉ ነገራቸው እያስጠላው፣ሌብነታቸው እያንገፈገፈው ሲመጣ አንቅሮ ይተፋቸዋል፤
የሚያሳዜነው ግን ከቤተክርስቲያንም ወጥቶ ኦርቶዶክስን እየረገመ ስለኖረ ተመልሶ መምጣት
ስለሚከብደው ጨፋሪና ዗ማዊ፣ በፍልስፍና ልቡ የተጠለፋ ከሀዲ ትውልድ ሆኖ ይቀራል። እባካችሁ
ከቤተክርስቲያን ኮብልላችሁ የወጣችሁ ኦርቶዶክሳውያን አገልጋዮችና ምዕመናን ወደ እናት
ቤተክርስቲያናችሁ ተመለሱ።

የሚያብረቀርቅ ሁሉ ወርቅ አይደለም። ኢየሱስ፣ ኢየሱስ ያለ ሁሉ ኢየሱስ የሚያውቀው አይደለም


ከቶውን አላውቃችሁም የሚባሉ በጣም ብዘ ናቸው። ወደ እናት ቤተ ክርስቲያን ላለመመለስ የካህናቱን
ድክመትና፣ የመሪዎቹን ስንፍና አትመልከቱ የተሰቀለውን ክርስቶስ ብቻ ተመልከቱ። ቤተክርስቲያኒቱ
ላይ ጣት ከመቀሰርና ከማጥላላት ይልቅ ዶግማዋ ምን እንደሆነ በጥልቀት መርምሩ፣ በነገረ
መለኮት ዘሪያ እና በምሥጢራት ያላት ጥልቅ አስተምህሮ ምን እንደሆነ ሊቃውንቱን ቀርባችሁ ጠይቁ።

የዶክትሪን መጻሕፍቷን መርምሩ። በጥራዜ ነጠቅ ዕውቀት ብቻ ቤታክርስቲያኒቱ ላይ ዗ለፋ አትናገሩ።


የእውቀት ደረጃዬ ምን ያህል ነው ብላችሁ በመጀመሪያ ራሳችሁን ፈትሹ። ምን ያህል
መጻሕፍቶቿን አንብቢያለው ብላችሁ አዕምሯችሁን መዜኑ፡፡

ሰንበት ትምርት ቤት ከሕጻንነት እድሜያችን ጀምሮ እስከ እርጅና ዗መናችን የማንለያት የጥበብና የፍቅር
ቤታችን ናት የቅደስት ቤተ ክርስቲያንን ሥርዓት የሀይማኖታችንን ዶግማና ቀኖና ጠንቅቀን እድናውቅ
የምታደርገን የጥበብ ማሕደር የቅደስት ቤተ ክርስቲያን አንዷ የወንጌል ማደረሻ ክፍል ነች፡፡ስለዙህ ለንጸና
በእውነት ልንመላለስ ለነፍሳችንም ለስጋችንም የሚበቃ ጥበብን እድንቀስም አደራ እላለሁ!!!

የረቀቀውን አጉልቶ፣ የራቀውን አቅርቦ ምሥጢርን የሚገልጽ የምሥጢራት ሁሉ መሠረት ለሆነው


ሥርዓትን የሠራልን ለአምላካችን ለቅዱስ እግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፡፡እናታችን ቅድስት ድንግል
ማርያም በምልጃዋ አትለየን የመላእክቱ ጥበቃ የቅዱሳኑ በረከት የሰማዕታቱ ጽጋ መንፈስ ቅዱስ አይለየን
አሜን!!አሜን!!አሜን!!
ይቆየን………….

ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት 2014 ዓ.ም. Page 46

You might also like