Professional Documents
Culture Documents
Longing For GOD
Longing For GOD
ጥናት አራት፡-ፀሎት
ዳን 6፤3-23 1 ኛ ተሰ 5፤17
1. የፀሎት ትርጉም በአንተ እንዴት ይታያል?
2. በዳንኤል ላይ የተገኘ ሰበብ ፀሎት ብቻ እንደነበር
ሁሉ በምንም ሁኔታ ውስጥ መፀለይ እንደሚቻል
ያስተምረናል፡፡በ 1 ኛ ተሰ 5፤17 ላይ ጳውሎስ
ሳታቋርጡ ፀልዩ ሲል ምን ለማለት ፈልጎ
ይመስልሃል?
3. ስለሚያሳድዱን እና ስለሚጠሉን ሰዎች መፀለይ
በአንተ እይታ ምን ይመስላል/ማቴ 5፤44-45/?
ጳውሎስ በብዙ ቦታ ፀልዩልን፣ስለእናንተ
እፀልያለሁ፣ይፀልዩልን ዘንድ ሲል ምን
ሊያሰተምረን ወዶ ነው?
4. የፀሎት መሰናክሎች ምን ምን ናቸው?
5. ከላይ የተዘረዘሩት መሳናክሎች ተቋቁሞ የግል
የፀሎት ጊዜን በቋሚነት መያዝ ይቻላል?በዳንኤል
ህይወት ካየኸው ምን ትወስናለህ?
ጥናት አምስት፡-በእግዚአብሔር መታመን
ኢሳ 40፤27-31 ኢሳ 30፤18 መዝ 37፤9
1. እግዚአብሔርን እንዳናስብ የሚያደርጉ ብዙ
ነገሮች ገጥመውን እግዚአብሔር ያላየ ወይም
የተወን ሲመስለን የሚሰማ ስሜት ምን አይነት
ነው?
2. ነብዩ የእስራኤል ሰዎች ላነሱት ቅሬታ የሰጠው
መልስ ያሉበትን ሁኔታ እንዴት ሊያስረሳቸው
ይችላል/ኢሳ 40፤28-29/?
3. ስለ መተማመን ከመነሳቱ በፊት በቁ.28 ላይ
የተገለፁትን የእግዚአብሔር ማንነት መገለጫዎች
በቁ.29 ከተገለፀው አሰራሩ ጋር እንዴት
እንደሚያያዝ አብራራ፤
4. እግዚአብሔርን በመተማመን ሲል እንዲሁ
ከመጠበቅ ጋር ምድነው
ሚለየው፤”እግዚአብሔርን በመተማመን
የሚጠባበቁ” ተብለው የተጠቀሱ ሰዎች
“ብላቴኖች እና ጎበዛዝት” ተብለው ከተገለፁት
ጋር በምን መልኩ ነው የተነፃፀሩት?
5. በራሳቸው ብርቱ ወይም ጎበዝ ከሚባሉ ሰዎች
አንተን የሚለይህ ነገር ምንድነው?በእግዚአብሄር
ስለመታመንስ በመጪው ዘመን ምን ልታደርግ
ወስነሃል?