Professional Documents
Culture Documents
5
5
መግቢያ
ልባችሁን ጠብቁ
የፍቅራችን ምንጭ ከየት ነው? ፍቅር ተወልዶ የሚያድግበት የሰውነታችን ክፍልስ ማን ነው? ልብ
ነው፡፡
ለዚህም ነው በምሳሌ 4፡23 እንዲህ ተብሎ የተጻፈው "አጥብቀህ ልብህን ጠብቅ፥ የሕይወት
መውጫ ከእርሱ ነውና።"
ይህን ሰምታችኋልን?
ከሁሉም አብልጣችሁ ልባችሁን ጠብቁ!
ይህ ክፍለ ምንባብ(ጥቅስ) የሥጋ ልባችሁን የሚያመለክት አይደለም፡፡
የሥጋ ልባችሁ ወደ ተለያዩ የሰውነታችሁ ክፍሎች ደምን የሚረጭ ጡንቻ ነው፤ ከሐሳብ፣
ምክንያትና ከስሜታችሁ ጋር እምባዛም ግንኑነት የለውም፡፡
ልባችን ምንን ይወክላል (ያመለክታል )
ዋነኛው መሥፈርት
እግዚአብሔር አዲስን ንጉሥ በእስራኤል እንዲሾም ነቢዩ ሳሙኤልን በላከው ጊዜ፣ ዋነኛው
መሥፈርት የፊት መልክ፣ ልምድ፣ አልፎ ተርፎም ተሰጥዖ አልነበረም፡፡
ለተወሰነ ጊዜ ያህል፣ ሳሙኤል ለሥራው ትክክለኛውን ሰው እንዳገኘ ተሰምቶት ነበር፡፡
እግዚአብሔር ግን ሳሙኤልን፦ "ፊቱን የቁመቱንም ዘለግታ አትይ ሰው እንዲያይ እግዚአብሔር
አያይምና ናቅሁት፤ ሰው ፊትን ያያል፥ እግዚአብሔር ግን ልብን ያያል አለው።" (1ሳሙ 16፡7)፡፡
ጌታን ማገልገል እና በሰዎች ላይ የሕይወት ለመውጥን ማምጣጥ የምትፈልጉ ከኾነ፣ በጣም አስፈላጊ
የሆነው ነገር ልባችሁ እንጂ የእናንተ ተሞክሮ ወይም ብቃት-ችሎታ አይደለም፡፡
የእግዚአብሔር የልቡን ፈቃድና ሐሳብ የምታድርጉ ሰዎች ለመሆን ምረጡ!
1) ወሲብ
2) ገንዘብ
3) ሥልጣን
ሰይጣን በጣም ብልኅና የጦርነት ስልት ዐዋቂ መሪ እንደመሆኑ መጠን የወደቀውን የሥጋ
ጠባያችንን ይጠቀማል፡፡ እኛን አባብሎ ለማጥመድም በሥጋ መሻቶቻችን በኩል ይወተውተናል፡፡
ደካማ የሆነውን ጎናችንን ያውቃል፤ በዚያም ገብቶ ጥቃቱን ይሰነዝርብናል፡፡
ገንዘብ የምንወድ ከሆነ በሀብት ይፈትነናል፡፡
ጒጒታችን ሥልጣንና ታዊቂነት የሆነ እንደሆነ ደግሞ ሹመትና ሽልማት እንደሚሰጠን አድርጎ ቃል
ይገባልናል፡፡
በፍትወተ ሥጋ የምንቃጠል ከሆነ ደግሞ ምናባዊውንና በልጭልጩን ዓለም ያቀርብልናል፡፡
እግዚአብሔር ለሕይወታችን ካለው ቅዱስ ዓላማ ለማጨናገፍ ጠላት አደንዛዥ ዕፆች፣ መጠጥ፣
ጥንቈላ/መተት/፣ ዓመጽ የሞላባቸው ፊልሞች፣ ወሲብ ነክ ድረ-ገጾች ብሎም ሁሉንም የማሰናከያ
ዘዴዎችን ሁሉ ያለእረፍትና ያለማቋርጥ ለመጠቀም ይጥራል፡፡
ጠላት የሚጠላውና የሚፈራው ነገር
ዲያብሎስ እንደ ፍቅር አድርጎ የሚጠላው ነገር የለም፤ ምክንያቱም ፍቅር የሆነው ኢየሱስ ክርሰቶስ
የርሱ ዋነኛ ወደረኛው ነውና፡፡
ስለዚህ ዲያብሎስ እንደ ፍቅር አድረጎ የሚፈራው አንዳች ነገር የለም፣ ምክንያቱም፡-
1) ልብን ሊፈውስና ሊያድስ የሚችል ብቸኛው ኃይል ፍቅር ነውና፡፡
2) የእግዚአብሔርን ሕዝብ ታላቁን ተልዕኮ እንዲያከናውኑና ሰዎችን ሁሉ ደቀመዛምርት እንዲያደርጉ
ማስከተት፣ አንድ ማድረግና ኀይልን ማስታጠቅ የሚቻለው ፍቅር ብቻ ነውና ነው፡፡
ጠላት ፍቅራችንን ለማጥፋትና ለማቀዝቀዝ፣ የተሰበረና ድንዙዝ ልብ ለማኖር በጣም መጨነቁ
አያስደንቅም፡፡
ምክንያቱም:-
የልባችንን ገዥ መንፈስ ቅዱስን ስናደርግ፣ የጠፋብንን ፍቅር፣ ደስታ፣ እና ሰላም ማደስ ይጀምራል፡፡
ነገር ግን ይህ ሂደት ጊዜን ሊወስድ ይችላል - የእኛንም ፈቃደኝነት ይጠይቃል፡፡
እዚህ ላይ ጥያቄው፡-
በእኛ ውስጥ ሥራውን እንዲያከናውን ለመንፈስ ቅዱስ ትክክልኛውን ሁኔታ እንዴት
ልናመቻችለት እንችላለን?
ልባችን ጽኑና ጤናማ መሆኑን ማረጋገጥ የምንችለው እንዴት ነው?
በሌላ አነጋገር ልባችንን መጠበቅ የምንችለው እንዴት ነው?
አድርግ አታድርግ
መልካም ልማዶችን መገንባት ሲባል ቅድሚያ ለሚሰጣቸው ነገሮች ቅድሚያ መስጠት ማለት ነው፡፡
በጊዜ ሰሌዳችን ውስጥ በጣም ቅድሚያ ሊሰጣቸው ለሚገቡ ነገሮች ትኲረት ሰጥተን እንሠራለን፡፡
ሮሜ 12፡2 "በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ
በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ።" በማለት በጥብቅ ያሳስበናል፡፡
እንዲህ ዓይነቱ መታደስ በየዕለቱ የሚያስፈልገን ነገር ነው፡፡ ይህም እውን ሊሆን የሚችለው፣ ጊዜ
ሰጥተን በጸሎትና መጽሐፍ ቅዱስን በማንበብ ከሰማያዊው አባታችን ጋር ስንገናኝ ብቻ ነው፡፡
የእግዚአብሔር ቃል እውነት እና ሕይወትን ለልባችን ይናገረናል፣ እንዲሁም ደግሞ የጠላትን ውሸት
ይገልጥልናል፡፡
መንፈስ ቅዱስ የኛን ሐሳብ በርሱ ሐሳብ ሲተካቸው፣ ከጭነቀት ነጻ እንሆንና ርሱ ራሱ
የእግዚአብሔርን ፈቃድ እንድናደርግ ኀይልን ያስታጥቀናል፡፡
መጥፎ ልምዶችን ማስወገድ ማለት ጊዜያችንንና ትኲረታችንን ሰርቀው አደጋ ላይ ለሚጥሉን ነገሮች
እምቢ -አሻፈረኝ ማለት ነው፡፡
መቼስ ሳምንቱን እንዴት እንደምታሳልፉት እናንተዉ ታውቃለችሁ፡፡
ምናልባትም፡-