Professional Documents
Culture Documents
A Minute With God
A Minute With God
ፀሎት ምንድነው
ፀሎት ምን አይደለም
የፀሎት ጥቅም
እንዴት እንፀልይ
ሳያቋርጡ መፀለይ
የፀሎት የቃልና የእምነት ግንኙነት
ተግባራዊ እይታ
የህብረት ምንነት
የጤነኛና ጤነኛ ያልሆነ ህብረት መገለጫዎች
የጤናማ ህብረት ጥቅም
ህብረት ያለማድረግ ጉዳቶች
ከነማን ጋር ህብረት ላድርግ
ከአስቸጋሪ ሰዎች ጋር ህብረት ማድረግ በእግዚአብሄር እይታ
ህብረትና ፍቅር
ተግባራዊ እይታ
በመፅሃፍ ቅዱስ ውስጥ የእግዚአብሄር ቃል የሚለው ሃረግ የአምላካችንን ማንነት በሚያሳይ ሁኔታ የተለያዩ
ትርጉሞችን ይዞ ይገኛል። ከእነዚህም ውስጥ፦
2) በነቢያት በኩል ወደሰዎች የሚላከው የእግዚአብሄር ቃል፦ በመፅሃፍ ቅዱስ ውስጥ እግዚአብሄር
ነቢያትን ተጠቅሞ ቃሉን ወደህዝቡ አድርሷል፤
የሰው ልጆች የእግዚአብሄርን ማንነት ወደማወቅ መድረስ የሚችሉት ቃሉን ሲያውቁ ብቻ ነው። ምክኒያቱም
እግዚአብሄር በቃሉ ውስጥ ከእርሱ ጋር እንዴት መኖር እንደሚቻል እንዲሁም ለህዝቡ ያለውን አላማና ለሰው
ልጆች ያለውን ፍቅር ገልጧል። አንድ ክርስቲያን በህይወት ዘመኑ ሁሉ ከአምላኩ ጋር ጥሩ ግንኙነት እንዲኖረው
ከፈለገ ከቃሉ ጋር የማያቋርጥ ግንኙነት ሊኖረው ያስፈልጋል፤ ማለትም የየእለት እንቅስቃሴው የእግዚአብሄር ቃል
በሚያዘው መሰረት ይሆን ዘንድ መፅሃፍ ቅዱስን በየእለቱ ማንበብና ያነበበውን መኖር ይገባዋል። ሰው የህይወት
ምልልሱ በቃሉ መሰረት ሲሆን በእግዚአብሄር ቃል ተሞልቷል ይባላል።
ሃጢአት ከእግዚአብሄር ጋር ያለንን ህብረት በማበላሸት መልካም ኣገልጋዮች እንዳንሆን የማድረግ ሃይል አለው፤
ቃሉን ዘወትር የምናነብና የምንመገብ ከሆነ ግን የሃጢኣትን ምንነት፣ መገለጫዎቹንና እግዚአብሄርን መበደል
የሚያመጣውን መዘዝ ጠንቅቀን በማወቅ ጌታን በፍርሃት እናገለግላለን። በሃጢኣት ውስጥ ሆኖ የሚያገለግል
ሰው የእግዚአብሄር ክብር ከኣገልግሎቱ እንደሚሸሽ መፅሃፍ ቅዱስ በስፋት ይነግረናል (ሕዝ 44:10-16) ። ስለዚህ
ቃሉን መሞላት ጌታን እንዳንበድል ያደርገናል።
ጥያቄ 1:1
ጥያቄ 1.3
“የዚህ ሕግ መጽሐፍ ከአፍህ አይለይ፥ ነገር ግን የተጻፈበትን ሁሉ ትጠብቅና ታደርግ ዘንድ በቀንም በሌሊትም
አስበው፤ የዚያን ጊዜም መንገድህ ይቀናልሃል ይከናወንልሃልም” (ኢያ1:8)።
ጥያቄ 1.4
ከመፅሃፍ ቅዱስ ታሪኮች ላይ የእግዚአብሄርን ቃል ጠንቅቀው በማወቃቸው ስኬታማ የሆኑ ሰዎችን በማንሳት
ተወያዩ።
ማጠቃለያ
እግዚአብሄር ለሰው ልጆች ያለውን ፍቅር እና አላማ በሙሉ የገለጠው በቃሉ ውስጥ በመሆኑ ቃሉን የተሞላ
ሰው ከጌታ ዘንድ የታሰበለትን የህይወት አቅጣጫ በቀላሉ ማግኘት ይችላል። ከላይ ከተገለፁት የቃሉ
ጠቀሜታዎችም በተጨማሪ እግዚአብሄር ቃል አማኞችን በሌሎችም ብዙ መንገዶች ይጠቅማቸዋል።ለምሳሌ
ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ በገባው ተስፋ መሰረት፦ በቃሉ የሚኖር ሰው ኣብ እና ወልድ ከእርሱ ጋር ይኖራሉ፤
እንዲሁም መንፈስ ቅዱስ ያስተምረዋል (ዮሃ 14፡23፥26)፣ ልመናው ይደረግለታል (ዮሃ 15፡7)፣ እግዚአብሄር
ለራሱ ይቀድሰዋል (ዮሃ 17፡17፣ኤፌ5፡25፥27)። ስለዚህ ክርስቲያን የእግዚአብሄርን ቃል ለመሞላት ዘወትር
መትጋት ይኖርበታል።
ጥያቄ 1.5
መዝሙር 119 ስለ እግዚአብሄር ቃል ጠቀሜታ ብዙ ያብራራል። ከዚህ ክፍል ውስጥ ከላይ ያልተዘረዘሩ የቃሉ
ጥቅሞችን በማውጣት ፃፉ።
መፅሃፍ ቅዱስ ቃሉ በሙላት እንዲኖርብን በ ቆላ 3፡16 ላይ ይነግረናል፤ ምክኒያቱም እርስ በርስ ለመማማርም
ሆነ ከእግዚአብሄር ጋር ህብረት ለማድረግ ቃሉ ወሳኝ ነው፤
ጠቃሚ ነጥቦች
አንድ ርእስ ማንበብ ከጀመርን እስከታሪኩ ማብቂያ ድረስ ለማንበብ መታገስ አለብን፣
ለምሳሌ የተራራው ስብከት በመባል የሚጠራውንና ከማቴዎስ ምእራፍ 5-7 ድረስ ያለውን
ክፍል ማንበብ ጀምረን ምእራፍ 6 ላይ ብናቆም ሙሉ ትምህርቱን ማግኘት አንችልም።
ስለዚህ መፅሃፍ ቅዱስን በእርጋታና በማስተዋል ማንበብ ይጠበቅብናል።
ማሰላሰል ማለት አንድን ነገር ለረጅም ሰአት ደጋግሞ ማሰብ፣ አንድን ሃሳብ ይዞና ፀጥ ባለ ቦታ ላይ ሆኖ
ማውጣትና ማውረድ እንዲሁም ለረጅም ጊዜ በጥልቀት ማሰብ የሚሉ ትርጉሞች አሉት። በእብራይስጥ ትርጉሙ
ደግሞ
ዳዊት በመዝሙሩ፦ አቤቱ፥ ሕግህን እንደ ምን እጅግ ወደድሁ፤ ቀኑን ሁሉ እርሱ ትዝታዬ
ነው። (መዝ119፡97) በማለት የእግዚአብሄርን ቃል ደጋግሞ ማሰብ የጌታን ድምፅ የመውደዳችን
ምልክት መሆኑን ይጠቁመናል። ሰው በአእምሮው እንዲመላለስ የሚፈቅደው ደስ የሚያሰኘውንና
ምቾት የሚሰጠውን ነገር እንዲሁም ትኩረቱን የሚስበውን ነው፣ ስለዚህ ቃሉን ማሰላሰላችን ቃሉን
መውደዳችንን እና ለቃሉ ያለንን አመለካከት ያሳያል።
ጠቃሚ ነጥቦች
ከምናነበው ክፍል የተወሰኑ ቁጥሮችን ወይም ኣንድን ታሪክ አውጥተን ማሰላሰል እንችላለን።
ለምሳሌ፦ ኤፌ 1፥5 ላይ ያለውን “በበጎ ፈቃዱ እንደ ወደደ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ ሥራ ለእርሱ
ልጆች ልንሆን አስቀድሞ ወሰነን።” የሚለውን ክፍል ይዘን እያሰላሰልን መዋል ይቻላል፣ እንዲሁም
1ሳሙ ምእራፍ 1 ላይ ያለውን ታሪክ በመውሰድ የታሪኩን ይዘት ማሰላሰል ይቻላል።
ቃሉን ስናሰላስል የተለያዩ ጥያቄዎችን ለራሳችን ማንሳት እንችላለን፤ ለምሳሌ ቃሉ የተፃፈው ለማን
ነው? ለኔስ ምን ያስተምረኛል? በምን መልኩ ልተገብረው እችላለሁ? ለሌሎች ወዳጆቼ በምን መልኩ
ላካፍላቸው እችላለሁ? ወዘተ የሚሉ ጥያቀዎችን ማንሳትና መልሶቹን መፈለግ እንችላለን
ቃሉን ለማሰላሰል የምንመርጠው ስፍራ ፀጥ ያለና ሃሳብ የሚበታትኑ ነገሮች የሌሉበት ቢሆን
ይመረጣል፤ በምናሰላስልበት ጊዜ ማህበራዊ ሚዲያ፣ስልኮችና ሌሎች መፃህፍትን ከአጠገባችን ብናርቅ
ይመረጣል። እንዲሁም ብቻችንን የእግር ጉዞ እያደረግን፣ ትራንስፖርት ውስጥ ሆነን ወዘተ ማሰላሰል
ይቻላል።
ቃሉን ማሰላሰል የተወሰነ የአእምሮ ልምምድ ይጠይቃል። ስለዚህ በየጊዜው አእምሯችንን ማሰላሰልንና
በአንድ ሃሳብ ላይ ማተኮርን ማሰልጠን ሊጠበቅብን ስለሚችል ይህንኑ በትእግስት መለማመድና
መፀለይ አለብን።
ጥያቄ1.6
በቃሉ መሰረት መፀለይ የሚያስገኛቸውን ሌሎች ጥቅሞች መፅሃፍ ቅዱስን መሰረት በማድረግ
ግለፁ።
ኢየሱስ በ ሉቃ8፡5-15 ላይ እንዳስተማረው በቃሉ የሚኖር ሰው ብዙ ፍሬን ያፈራል። በዚህ ክፍል ላይ ሊያፈሩ
ያልቻሉትም ጭምር ቃሉ እንደሰሙ ነገር ግን በመልካም የተቀበሉት ብቻ እንዳፈሩ ተፅፏል።እንዲሁም በ ማቴ7፡
24-27 ላይ ቃሉን ሰምቶ የሚያደርግ ሰው በአለት ላይ ቤቱን እንደሰራ ሰው አድርጎ መስሎታል።
ያእቆብም በመልእክቱ ቃሉን ሰምቶ የማያደርግ በመስታወት ያየውን ፊቱን እንደሚረሳ ሰው ማንነቱን
እንደሚስት ይነግረናል፣ (ያዕ 1፡22-24)
ያእቆብ ቃሉን የሚያደርግ ሰው በስራው የተባረከ ይሆናል በማለት ያስተምራል፤ (ያዕ 1፡25) እንዲሁም መፅሃፍ
ቅዱስ ቃሉን የሚያደርግን ሰው እግዚአብሔር እንደሚሰማው ያስተምረናል፤(ዮሃ 9፡31)።
በዚህ ሁሉ ውስጥ የምንረዳው ነገር የእግዚአብሔርን ቃል አክብሮ ለመኖር የራስ ውሳኔና ፅናት ወሳኝ መሆኑን
ነው።
ጥያቄ፦1.7
የእግዚአብሔርን ቃል መፈፀም የራስ ውሳኔን እና ፅናትን የሚጠይቅ መሆኑን የሚጠቁሙ ሌሎች የመፅሃፍ
ቅዱስ ትምህርቶችንና ታሪኮችን እያነሳችሁ ተወያዩባቸው።
ለ) ህይወቱ የተረጋና በእግዚአብሄር እቅድ መሰረት አይሆንም፦ የእግዚአብሄር ቃል ለሰው ልጆች የህይወት
ምሪት የሚሰጥ የእግዚአብሄር ስጦታ ነው። ሰው በዚህ ቃል የተሞላ ምልልስ ከሌለው ከእግዚአብሄር አላማ ጋር
በቀላሉ ስለሚተላለፍ ህይወቱ የተረጋጋና ሰላም የሌለበት ይሆናል።
ጥያቄ 1.8፦
(ሆሴ4:4-10) ላይ ያለውን ክፍል አንብቡና ህዝቡ ለምን ጥፋት እንደተፈረደበት እንዲሁም ይህ ትንቢት በዚህ
ዘመን ላለነው ለኛ ምን ሊያስተምረን እንደሚችል ተወያዩበት።
ተግባራዊ እይታ