You are on page 1of 286

አንድ ክርስቲያን ከጌታ ጋር

የቅርብ ውይይት ማድረግ


የሚችለው መቼ ነው?
ተከታታይነት ባለው የማቴዎስ ወንጌል
ስብከቴ የመጀመሪያው ቅጽ ርዕስ ይህ ነው፡፡ በዚህ
ርዕስ ጌታ የተናገረውን እውነት ልሰብክላችሁ
ወስኛለሁ፡፡ አንድ ሰው ትንሽም ይሁን ትልቅ
ማናቸውም ግብ ላይ ይደርስ ዘንድ የመጀመሪያውን
ትክክለኛ እርምጃ መራመድ አለበት፡፡ የሁሉም
ክርስቲያኖች የመጨረሻ ግብ ጌታን መከተል ነው፡፡
እዚህ ግብ ላይ ለመድረስም አስቀድመው
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ማወቅ አለባቸው፡፡
ጌታን በትክክል መከተል የሚችሉት ያን ጊዜ ብቻ
ነውና፡፡
የማቴዎስ ወንጌል ከአራቱ ወንጌሎች አንዱ
እንደ መሆኑ በብዙ ክርስቲያኖች ዘንድ
ይታወቃል፡፡ ቀድሞውኑም ብዙ ጊዜ አንብባችሁት
ሊሆን ይችላል፡፡ ነገር ግን የማቴዎስ ወንጌል
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንደሚገኘው ልክ እንደ
ሌላው መጽሐፍ ሁሉ መነበብ ያለበት በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል መነጽር ነው፡፡ አንዳንድ
ክርስቲያኖች በማቴዎስ ወንጌል ውስጥ
በተመዘገቡት የጌታ የተራራው ስብከቶች በአያሌው
ይደነቃሉ፡፡ ከዚህ የተነሳ በዚህ ምልከታ ላይ
በመመስረት ብቻ የጌታን ፈቃድ ለመከተል
ይሞክራሉ፡፡ ነገር ግን እኔ ስለ እግዚአብሄር ጽድቅ
ለእናንተ በመስበክ ወደተሻለ መረዳት እንድትደርሱ
ላግዛችሁ እወዳለሁ፡፡ የእርሱ ዓላማ ይህ ነውና፡፡
ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ጥምቀት
ታውቃላችሁን? ጌታን የትና በማን አማካይነት
ልትገናኙት እንደምትችሉ ታውቃላችሁን? ግልጽ
የሆነ የእግዚአብሄር ጽድቅ መረዳት ኖሮዋችሁ
ኢየሱስን አዳኛችሁ አድርጋችሁ ለማመን
ትሻላችሁን? እነዚህ በዚህ መጽሐፍ ውስጥ
ከሚብራሩት እጅግ አስፈላጊ ጥያቄዎች አንዳንዶቹ
ናቸው፡፡
አንድ ክርስቲያን ከጌታ ጋር
የቅርብ ውይይት ማድረግ
የሚችለው መቼ ነው?

PAUL C. JONG

Hephzibah Publishing House


A Ministry of THE NEW LIFE MISSION
SEOUL, KOREA

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
አንድ ክርስቲያን ከጌታ ጋር የቅርብ ውይይት ማድረግ የሚችለው መቼ ነው?
በማቴዎስ ወንጌል ላይ የተሰጡ ስብከቶች (Ⅰ)
የተከለሰ ዕትም፤ የታተመው ©2015 በሄፍዚባህ ማተሚያ ቤት የታተመ፡፡
ሙሉ መብቱ በሕግ የተጠበቀ ነው፡፡ ከዚህ መጽሐፍ ባለቤት በጽሁፍ የተገኘ
ፈቃድ ሳይኖር የዚህን መጽሐፍ ማንኛውንም ክፍል ማባዛት ወይም በማንኛውም
መልኩ ወይም በማንኛውም መንገድ በኤሌክትሮኒክ ወይም በሜካኒካል ፎቶ ኮፒ
ማድረግን ጨምሮ በቅጂ መልክ ወይም መረጃን ይዞ በሚያጠራቅም ወይም
መረጃን ይዞ በሚያስቀር ማንኛውም መንገድ ማሰራጨት አይቻልም፡፡

ጥቅሶቹ በሙሉ የወሰዱት ከ1954ቱ የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ ነው፡፡


ISBN 978-89-282-0677-3
የሽፋን ስዕል፡ በሚን ሶ. ኪም
ንድፍ፡ በዮንግ አይ ኪም
ትርጉም፡ በካሳሁን አየለ
የታተመው በኮርያ ነው፡፡

Hephzibah Publishing House


A Ministry of THE NEW LIFE MISSION
P.O. Box 18 Yang-Cheon Post Office
Yang-Cheon Gu, Seoul, Korea

♠ Website: https://www.nlmission.com
https://www.bjnewlife.org
https://www.nlmbookcafe.com
♠ E-mail: newlife@bjnewlife.org

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
ማውጫ

መቅድም --------------------------------------------------------------- 9

ምዕራፍ 1

የኢየሱስ ክርስቶስ የትውልድ ግንድ


(ማቴዎስ 1፡1-6) ---------------------------------------------------- 13

እኛን ለማዳን የመጣውን ጌታችንን ኢየሱስን እናመስግነው


(ማቴዎስ 1፡18-25) ------------------------------------------------- 19

በመንፈስ ቅዱስ የተጸነሰው ኢየሱስ


(ማቴዎስ 1፡18-25) ------------------------------------------------ 29

ምዕራፍ 2

ጌታን በትክክል ልንገናኘው የምንችለው የት ነው?


(ማቴዎስ 2፡1-12) -------------------------------------------------- 47

ምዕራፍ 3

እውነተኛውን ወንጌልና የኢየሱስን የጽድቅ ምግባር አስፋፉ


(ማቴዎስ 3፡1-17) -------------------------------------------------- 57

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
ሐጢያቶቻችሁን ለመደምሰስ የመጣው ኢየሱስ
(ማቴዎስ 3፡1-17) -------------------------------------------------- 65

ምዕራፍ 4

በረከት ማለት እግዚአብሄርን መፍራትና አምላክን ማገልገል ነው


(ማቴዎስ 4፡1-11) ------------------------------------------------- 93

ምዕራፍ 5

የተራራው ስብከት
(ማቴዎስ 5፡1-16) ------------------------------------------------ 107

ምዕራፍ 6

ጌታ ስለ ጸሎት ያስተማረው ትምህርት (1)


(ማቴዎስ 6፡1-15) ------------------------------------------------ 125

ጌታ ስለ ጸሎት ያስተማረው ትምህርት (2)


(ማቴዎስ 6፡1-15) ------------------------------------------------ 144

ልቦቻችሁን በጌታ ላይ አድርጋችሁ ኑሩ


(ማቴዎስ 6፡21-23) ---------------------------------------------- 160

ስለ ሕይወታችሁ አትጨነቁ፤ ነገር ግን በእግዚአብሄር ብቻ እመኑ


(ማቴዎስ 6፡25-34) --------------------------------------------- 167

ለቀኑ ችግሩ ይበቃዋል


(ማቴዎስ 6፡34) ------------------------------------------------- 182

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
ምዕራፍ 7
በወንጌል ሐይል በማመን በጠባቡ ደጅ መግባት አለብን
(ማቴዎስ 7፡13-14) ---------------------------------------------- 191

በመጨረሻው ቀን ጌታ ቢተወን ምን እናደርጋለን?


(ማቴዎስ 7:21-23) ---------------------------------------------- 197

የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ መፈጸም የሚችለው እምነት


(ማቴዎስ 7፡20-27) --------------------------------------------- 205

ሰማይ መግባት የምንችለው የአብን ፈቃድ ስናውቅና


ስናምንበት ብቻ ነው
(ማቴዎስ 7፡21-27) ---------------------------------------------- 223

ገንዘባችሁን ብቻ ከሚሹ ሐሰተኛ ነቢያቶች ተጠንቀቁ


(ማቴዎስ 7፡13-27) ---------------------------------------------- 230

ምዕራፍ 8

የመንፈሳውያን ለምጻሞች ፈውስ


(ማቴዎስ 8፡1-4) ------------------------------------------------- 247

‹‹ቃል ብቻ ተናገር››
(ማቴዎስ 8፡5-10) ---------------------------------------------- 265

አስቀድማችሁ ጌታን ተከተሉ


(ማቴዎስ 8፡18-22) ---------------------------------------------- 277

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com
መቅድም
በመላው ዓለም የሚገኙ ብዙ ሰዎች የሐጢያት ስርየትን እየተቀበሉ ነው፡፡
ከዚህ የተነሳ ከጌታ ከኢየሱስ ጋር በሚያደርጉት ጉዞዋቸው የሚመሩዋቸውና
ምሪትን የሚሰጡዋቸው ሰዎች ያስፈልጉናል፡፡ የሐጢያቶቻቸውን ሁሉ ስርየት
የተቀበሉ ሰዎችን ወደ ቤተክርስቲያን ማምጣት ይገባናል፡፡ በእያንዳንዱ የዓለም
አገር ብዙ መሪዎች እንደሚነሱ አበክሬ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ የቢሮ ሠራተኞቼን
ሁሉ የእግዚአብሄር መልዕክተኞችና ሚሽነሪዎች አድርጌ በመላው ዓለም መላክ
ብችል እመኛለሁ፡፡ ሆኖም እነርሱ ወደ አገሮች ሁሉ ከተላኩ እዚህ በመቅረዙ
ጌጠኛ እጄታ የተመሰለውን የእግዚአብሄርን ሥራ የሚወክለውን የጽድቅ ወንጌል
ማን ይደግፋል? ስለዚህ እኔ በእርሱ/በእርስዋ አገር ውስጥ የአምላክን ሠራተኞች
እነዲያስነሳ ተስፋ አደርጋለሁ፤ እጸልያለሁም፡፡
ይህ መጽሐፍ ወደፊት ለሚነሱ የዳኑ መሪዎች የሚሆን ተከታታይ
የመንፈሳዊ ዕድገት የመጀመሪያው መጽሐፌ ነው፡፡ ጌታን ሳገለግል የእግዚአብሄር
ሕዝብ እንደሚነሳ አምናለሁ፡፡ ወደፊት የሚነሱ መሪዎችን ስጠብቅ አሁን
ለእናንተ የማቀርብላችሁን እነዚህን ስብከቶች በካሴት አዘጋጅቻለሁ፡፡ የነገዎቹን
መሪዎች ለማሰልጠን ዓላማ የታተሙትና የተተረጎሙት ስብከቶች ነፍስን
የሚመግቡ መልዕክቶችን ወደ ልባችሁ ያመጣሉ፡፡
እነዚህ ስብከቶች በእርግጥም ለሰዎች ሁሉ መንፈሳዊ ምግብ እንደሚሆኑ
አምናለሁ፡፡ ሁላችንም በሌሎች አገሮች ከሚኖሩ ምዕመናንና የእግዚአብሄር
ሠራተኞች ጋር ፊት ለፊት መገናኘት ስለማይቻለን ይህንን መጽሐፍ በማጋራት
አስቀድመው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ካመኑት ጋር መንፈሳዊ ሕብረት
ላደርግ እንደምችል ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ እርሱ የሕይወትን ምግብ በመመገብ
የእርሱ ሠራተኞች ስላደረገን ሁላችንም አመስጋኞች ነን፡፡
እስከ አሁን ድረስ በእንግሊዝኛ ቋንቋ 10 መጽሐፎችን አሳትመናል፡፡
መጽሐፎቹን ያነበቡ ብዙ ሰዎችም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን
የሐጢያት ስርየትን በመቀበላቸው አመስጋኞች መሆናቸውን ደርሰንበታል፡፡ አሁን
ደግሞ ለመንፈሳዊ ዕድገታቸው በሚሆኑት ስብከቶች አማካይነት እንደገና
የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ሕይወትን የሚሰጥ ብቸኛው በእውነት መሆኑን
እመሰክራለሁ፡፡ ውሎ አድሮም በዓለም ላይ የሚኖሩ ሰዎች ሁሉ የውሃውና

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


10 መቅድም

የመንፈሱ ወንጌል ብቸኛው እውነት መሆኑን በጥልቀት ወደ መረዳት ይደርሳሉ፡፡


አንድ ጊዜ እውነትን ከተረዱና በስሜት ላይ ያነጣጠረውን እምነታቸውን ከጣሉ
ልቦቻቸው የዘላለም ቤዛነት የሚገኝበት ብቸኛው መንገድ በሆነው የውሃና
የመንፈስ ወንጌል ይሞላሉ፡፡ ስለዚህ በመላው ዓለም የሚገኙ ሰዎች የክርስቶስ
ደቀ መዛሙርት ሆነው ይኖራሉ፡፡ አሁን የጠፉ ነፍሳቶችን የሚያድኑ መሳርያዎች
እንሆናለን፡፡ በአገራቱ ሁሉም ለጠፉት በጎችም በውሃውና በመንፈስ ወንጌል
ሐይል በማመን የእርሱን ሥራ እንሰራለን፡፡
እያንዳንዱ ተክል እንደሚያብብና ፍሬ እንደሚያፈራ ሁሉ የእውነተኛው
ወንጌል ሐይልም በእርሱ የሚያምኑትን የሚባርክ ብቻ ሳይሆን የእግዚአብሄር
ሠራተኞች ሆነው ሕይወታቸውን እንዲመሩም የሚፈቅድላቸው ነው፡፡ እነርሱም
በሥጋና በመንፈሳዊ ሕይወታቸው ይባረካሉ፡፡ አሁን በመላው ዓለም አገሮች
የሚገኙ የእግዚአብሄር ሠራተኞች የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በመስራት
እጅግ ብዙ ሰዎችን ከሐጢያቶቻቸው ያድናሉ፡፡ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
ስንሰብክ በማሸነፍ እንቀጥላለን፡፡ በዚህ በእውነተኛው የውሃና ወንጌል የምናምን
ምዕመናኖች በመሆናችንም ለእግዚአብሄር መንግሥት ብዙ ፍሬዎችን
እናፈራለን፡፡ የምንኖረው በመከር ዘመን ውስጥ ነው፡፡ የተትረፈረፉ የደህንነት
ፍሬዎችንም እናፈራለን፡፡ አሁን በእርሱ ቃሎች እናምናለን፡፡ እርሱን
እናመሰግናለን፤ እናከብረውማለን፡፡
እግዚአብሄር ቢፈቅድ እነዚህንና ብዙ ሌሎች ነገሮችን እንደርጋለን፡፡ እርሱ
እያንዳንዳችንን እንደሚባርከን አምናለሁ፡፡ እግዚአብሄር በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል ለሚያምን ሁሉ የተትረፈረፉትን መንፈሰዊና ሰማያዊ በረከቶች --
የሰማይን የተቀደሰ እምነትና የምድርን ስብ በረከቶች -- ይስጠው፡፡ 

ፖል ሲ. ጆንግ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ምዕራፍ
1

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት
ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
የኢየሱስ ክርስቶስ
የትውልድ ግንድ
‹‹ ማቴዎስ 1፡1-6 ››
‹‹የዳዊት ልጅ የአብርሃም ልጅ የኢየሱስ ክርስቶስ ትውልድ መጽሐፍ፡፡
አብርሃም ይስሐቅን ወለደ፤ ይስሐቅም ያዕቆብን ወለደ፤ ያዕቆብም ይሁዳንና
ወንድሞቹን ወለደ፡፡ ይሁዳም ከትዕማር ፋሬስንና ዛራን ወለደ፡፡ ፋሬስም ኤስሮምን
ወለደ፤ ኤስሮምም አራምን ወለደ፤ አራምም አሚናዳብን ወለደ፡፡ አሚናዳብም
ነአሶንን ወለደ፤ ነአሶንም ሰልሞንን ወለደ፡፡ ሰልሞንም ከራኬብ ቦኤዝን ወለደ፤
ቦኤዝም ከሩት ኢዮቤድን ወለደ፡፡ ኢዮቤድም እሴይን ወለደ፡፡ እሴይም ንጉሥ
ዳዊትን ወለደ፡፡››

እኛም የኢየሱስ ክርስቶስ የትውልድ ግንድ አካል ለመሆን በእርሱ ማዳን


ማመን ያስፈልገናል፡፡ በሌላ አነጋገር በእርሱ ማዳን ማመን የእርሱ የትውልድ ግንድ
አካል ለመሆን ብቸኛው መንገድ ነው፡፡
አባታችን እግዚአብሄር እኛን ለማዳን መላዕክቶቹን አልላከም፡፡ የላከው አንድ
ልጁን ነው፡፡ አባታችን እግዚአብሄር እኛን ከሐጢያቶቻችን ለማዳን የላከው ኢየሱስ
ክርስቶስን ነበር፡፡ እርሱ የእግዚአብሄር ልጅና አዳኛችን በሆነው በኢየሱስ የሚያምን
ማንም ሰው ለአንዴና ለመጨረሻ ለሐጢያቶቹ ሁሉ ይቅርታን እንደሚያገኝ ቃል
ገብቷል፡፡ በዚህ አገባብ ማቴዎስ 1፡1 እንዲህ ይላል፡- ‹‹የዳዊት ልጅ የአብርሃም ልጅ
የኢየሱስ ክርስቶስ ትውልድ መጽሐፍ፡፡›› እዚህ ላይ ‹‹የኢየሱስ ክርስቶስ ትውልድ››
የሚያመለክተው እኛ ኢየሱስ ክርስቶስን በሚያውቅና በሚያምን እምነት አማካይነት
ከጨለማው ሐይል ድነን የእግዚአብሄር ልጆች መሆን የምንችልበትን መንፈሳዊ
ዓለም ነው፡፡
ይህ ምንባብ ሐጢያተኛ ከሐጢያቶቹ ድኖ የእግዚአብሄር ልጅ ለመሆን ምን
እንደሚያስፈልገው ያብራራል፡፡ በሌላ አነጋገር አንድ ሰው የእግዚአብሄር ልጅ
ለመሆን አብርሃም የነበረው ዓይነት ተመሳሳይ እምነት ሊኖረው ያስፈልገዋል፡፡ ወደ
እግዚአብሄር መንግሥት ለመግባት ምን ዓይነት እምነት ያስፈልጋል? አብርሃም

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


14 የኢየሱስ ክርስቶስ የትውልድ ግንድ

እንዳደረገው ፈጽሞ በእግዚአብሄር ማመን ያስፈልገናል፡፡ እግዚአብሄርን ያስደሰተው


የአብርሃም እምነት ምንድነው? እርሱ በእግዚአብሄር ቃል ፈጽሞ አመነ፡፡ በሰውኛ
ተጠየቅ የማይቻለውን ተስፋ አደረገ፡፡ እርሱ ከሰው አስተሳሰብ ባሻገር እርሱ
እንደተናገረው በእግዚአብሄር ኪዳን አመነ፡፡ የእምነቱ ምልዓት ያ ነበር፡፡ የአብርሃም
ሚስት ልጅ የምትወልድበትን ዕድሜ አልፋ ልጅ መጸነስ ባይቻላትም አብርሃም ዘሩ
እንደ ሰማይ ከዋክብት እንደሚበዛ እግዚአብሄር ከእርሱ ገር የተጋባውን ኪዳን
አመነ፡፡ ስለዚህ እግዚአብሄር ይህንን ጽድቅ አድርጎ ቆጠረለት፡፡ በእርሱም ደስ
ተሰኘ፡፡ አብርሃም በእምነት የጻድቃን አባት የሆነው እንዲህ ነው፡፡
ዛሬም እናንተና እኔ አብርሃምን የምዕመናኖች ሁሉ አባት አድርገን
የምንመለከተው እርሱ እግዚአብሄር የተናገረውን በትክክል ስላመነ ነው፡፡
በተመሳሳይ መንገድ ወደ ኢየሱስ መንግሥት ለመግባት የአብርሃም ዓይነት እምነት
ያስፈልገናል፡፡ ሐጢያተኛ የሐጢያት ስርየት የሚያገኝበትና ጻድቅ ሰው የሚሆንበት
ብቸኛው መንገድ ይህ ነው፡፡ ኢየሱስን ጌታችንና አዳኛችን አድርገን በመቀበል ወደ
እግዚአብሄር መንግሥት መግባትና የእርሱን ማዳን መቀበል እንችላለን፡፡
የኢየሱስ ክርስቶስ የትውልድ ግንድ አካል ለመሆን ኢየሱስን አዳኛችን
አድርገን የምናምነው እንዴት ነው? በሌላ አነጋገር ለሐጢያተኞች በሆነው የእርሱ
ማዳን የምናምነው እንዴት ነው? ለእኛ በተሰጠን መሰረት በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል ማመን ያስፈልገናል፡፡
እግዚአብሄር አባታችን የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ ለመስወገድ ልጁን
ኢየሱስን መድህን አድርጎ ወደዚህ ዓለም ላከው፡፡ ስለዚህ ኢየሱስ በዮርዳኖሰ ወንዝ
በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅ ዘዴ የሐጢያተኞችን ሐጢያቶች በሙሉ
እንደወሰደ ማመን አለብን፡፡ እውነተኛውም እምነት እርሱ ለሐጢያቶቻችን
እንደተሰቀለ፣ በመስቀል ላይ እንደደማና እንደሞተ፣ ዳግመኛም ከሙታን እንደተነሳና
በእርሱም የሚያምኑትን ምዕመናኖች በሙሉ እንዳዳነ ማመን ነው፡፡ ‹‹ኢየሱስም፡-
አሁንስ ፍቀድልኝ እንዲህ ጽድቅን ሁሉ መፈጸም ይገባናልና አለው፡፡ ያን ጊዜ
ፈቀደለት፡፡ ኢየሱስም ከተጠመቀ በኋላ ወዲያው ከውሃ ወጣ፡፡ እነሆም ሰማያት
ተከፈቱ፡፡ የእግዚአብሄርም መንፈስ እንደ ርግብ ሲወርድ በእርሱ ላይም ሲመጣ
አየ፡›› (ማቴዎስ 3፡15-16)
ይህ ምንባብ ኢየሱስ በጥምቀቱ የዓለምን ሐጢያቶች የወሰደበት እውነት
ነው፡፡ እግዚአብሄር አባታችን ጌታችን ኢየሱስን ለሐጢያተኞች በመላክ ልቦቻችንን
እንደ በረዶ ለማንጻትና የእግዚአብሄርን መንግሥት በር ለመክፈት በአጥማቂው
ዮሐንስ በመጠመቅ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ እንዲወሰድ አደረገው፡፡ እኛም ቃሉን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የኢየሱስ ክርስቶስ የትውልድ ግንድ 15

በልባችን በመቀበል ጻድቃን መሆን እንችላለን፡፡ የእርሱ ቤተሰብ አባሎችም


እንሆናለን፡፡ ኢየሱስ በሰራው ሥራ የሚያምን ማንኛውም ሰው ከሐጢያተኛ ወደ
ሐጢያት አልባ ሰውነት መለወጥ ይችላል፡፡ የእግዚአብሄር ቤተሰብ ለመሆን መንገዱ
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ማመን ነው፡፡
አንድ ሐጢያተኛ የእግዚአብሄር ልጅ ይሆን ዘንድ ኢየሱስ የሐጢያተኞች
አዳኝ መሆኑን የሚያምን እምነት ሊኖረው ያስፈልጋል፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ
‹‹የዳዊት ልጅ›› ማለት ኢየሱስ የይሁዳ ዘር ነው ማለት ነው፡፡ በብሉይ ኪዳን
እግዚአብሄር የያዕቆብ ልጅ ከሆነው የይሁዳ ነገድ ነገሥታቶችን እንደሚያስነሳ ቃል
ኪዳን አድርጓል፡፡ (ዘፍጥረት 49፡10) ዳዊት ብሉይ ኪዳን ከተናገረለት የይሁዳ ነገድ
የመጣ ሰው ነው፡፡ ኢየሱስም ንጉሥ ሆኖ ከይሁዳ ነገድ ተወለደ፡፡ አብርሃም
እንዳደረገው እኛም የእግዚአብሄርን ቃል በማመን የንጉሣዊ ቤተሰብ አካል
እንሆናለን፡፡ በእምነት የኢየሱስ ክርስቶስ የትውልድ ግንድ አካል የሚሆን
ማንኛውም ሰው ቀድሞውኑም የእግዚአብሄር ልጅ ሆንዋል፡፡ አብርሃም ይስሐቅን
ወለደ፤ ይስሐቅም ያዕቆብን ወለደ፤ ያዕቆብም ይሁዳንና ወንድሞቹን ወለደ፡፡
እነርሱም ዘሮቻቸውን መውለድ ቀጠሉ፡፡ በእግዚአብሄር ቃል የሚያምኑ ሰዎች
የእግዚአብሄርን ልጆች በመውለድ ይቀጥላሉ፡፡
በእምነት የኢየሱስ የትውልድ ግንድ አካል የሆኑ ሁሉ የእግዚአብሄርን
ምህረት የተቀበሉ ሰዎች ናቸው፡፡ ስለ ራሳቸው የሚኮሩበት ምንም ነገር የላቸውም፡፡
እነርሱ ትሁትና ደካሞች ነገር ግን በእግዚአብሄር ቃል ያመኑ ናቸው፡፡ ስለዚህ
ከእውነተኛው ንጉሥ ጋር አንድ ቤተሰብ ሆኑ፡፡
እኛ በእምነት የእርሱ የትውልድ ግንድ አካል ለመሆን ይህንን ማወቅ
ያስፈልገናል፡፡ በኢየሱስ ክርስቶስ የትውልድ ግንድ ውስጥ ረዓብ የተባለች ጋለሞታ
እንደዚሁም ከአህዛቦች ሞዓባዊት የሆነች ሩት የምትባል ሴት ነበረች፡፡ ታዲያ
እንዴት አንዲት ጋለሞታ የኢየሱስ የትውልድ ግንድ አካል መሆን ቻለች? ረዓብ ወደ
እግዚአብሄር መንግሥት የገባችው በእግዚአብሄር ላይ ባላት እምነት ነው፡፡
ሐጢያተኛ የእግዚአብሄር ልጅ የሚሆንበት ብቸኛው መንገድ በቃሉ ማመን
እንደሆነ እግዚአብሄር ነግሮናል፡፡ ይህ ማለት እውነተኛ እምነት ጥሩ ሥራ
በመሥራት ጥሩ ሕይወትን መኖር ማለት ሳይሆን በእግዚአብሄር ቃል ማመን ነው፡፡
አንዲት ጋለሞታ እንደ እግዚአብሄር ፈቃድ መኖር የቻለችው እንዴት ነው?
እግዚአብሄር ብዙ ሐጢያቶች የሰራችውን ጋለሞታ የሚመስል ሰውን ሐጢያቶች
በሙሉ እንኳን በጌታ ማዳን ይቅር ብሎዋል፡፡ ጋለሞታ እንኳን በእግዚአብሄር
የደህንነት እውነት በማመን የእግዚአብሄር ልጅ መሆን ችላለች፡፡ ይህ ማለት በዚህ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


16 የኢየሱስ ክርስቶስ የትውልድ ግንድ

ዓለም ላይ የሚኖር እያንዳንዱ ሐጢያተኛ የእግዚአብሄር ልጅ መሆን ይችላል ማለት


ነው፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ በእርሱና በቃሉ ስለሚያምን እምነት ይነግረናል፡፡ በማቴዎስ 1
ላይ መጽሐፍ ቅዱስ እንደገና ስለ ትዕማር እምነት ይናገራል፡፡ ትዕማር ማነች?
እርስዋ ከአማትዋ ጋር የተኛች የይሁዳ ምራት ነበረች፡፡ ይህንን ከሥነ ምግባር አንጻር
ስንመለከተው ከአማትዋ ጋር የግብረ ሥጋ ግንኙነት ያደረገች ሴት እንዴት
የተቀደሰው የኢየሱስ የትውልድ ግንድ አካል መሆን ቻለች? ሆኖም ትዕማር
ለአማትዋ በተሰጠው ኪዳን በማመንዋ ድጋፍን አገኘች፡፡ እርስዋ አማትዋ
ባስተላለፈው ቃል በሚያምነው እምነት የኢየሱስ የትውልድ ግንድ አካል ሆነች፡፡
በእስራኤል በኩሩ ሲሞት ታናሹ የበኩሩን ሚስት መውሰዱ የተለመደ ነበር፡፡
በኩር የሆነው ልጅ ሲሞት ልጅ ከሌለው አማቱ የበኩር ልጁን ሚስት ለታናሹ ልጁ
የማጋባት ሐላፊነት አለበት፡፡ ትዕማር የይሁዳን የበኩር ልጅ አገባች፡፡ ነገር ግን
የበኩር ልጁ በእግዚአብሄር ፊት ክፉ ስለነበር እግዚአብሄር ገደለው፡፡ ስለዚህ
በእስራኤል ልማድ መሰረት ይሁዳ ሁለተኛውን ልጁን ለትዕማር ሰጠ፡፡ ነገር ግን
ሁለተኛው ልጅ ወራሹ ለእርሱ እንደማይሆን በማወቁ ዘሩን በምድር ላይ አፈሰሰ፡፡
እግዚአብሄርም ቀሰፈው፡፡ አማትየውም ሦስተኛ ልጁን ለምራቱ መስጠት ነበረበት፡፡
ነገር ግን ገና ልጅ ስለነበር ሦስተኛው ልጁ ሲያድግ እንደሚያጋባው ቃል ገባ፡፡
ትዕማር ሦስተኛውን ልጀ ጠበቀች፤ ሆኖም አማትዋ ልጁን ስላልሰጣት ትዕማር
ተንኮል አሰበች፡፡
በዓመቱ በጎች የሚሸለቱበት ቀን ደረሰ፡፡ ስለዚህ ትዕማር የመበለትነትዋን
ልብስ አውልቃ ራስዋን በዓይነ ርግብ ሸፍና በመንገድ ዳር ተቀመጠች፡፡ በእስራኤል
ያሉ ጋለሞታዎች ራሳቸውና ፊታቸው በዓይነ ርግብ መሸፈን ነበረበት፡፡ ይሁዳ
በጎቹን ለመሸለት ሲሄድ በመንገዱ ላይ ባያት ጊዜ ከእርስዋ ጋር ለመሆን ፈለገ፡፡
ስለዚህ መያዣ ይሆን ዘንድ ቀለበቱን፣ አምባሩንና በትሩን ሰጣት፡፡ ይሁዳ ይህች ሴት
ምራቱ እንደሆነች አላወቀም፡፡ ከጥቂት ወራቶች በኋላ የትዕማር ሆድ እየገፋ ሄደ፡፡
በወቅቱ መበለት ስለነበረች ይህ ሁኔታ ምንዝርና ሆኖ ታየ፡፡ በእስራኤል አመንዝራ
በድንጋይ ተወግሮ ወይም በእሳት ተቃጥሎ ይገደል ነበር፡፡ ይሁዳ በድንጋይ ተወግራ
እንድትሞት አቀደ፡፡ ነገር ግን ትዕማር በወቅቱ ‹‹ያረገዝሁት የዚህ በትርና ቀለበት
ባለቤት ከሆነው ሰው ነው›› አለች፡፡ እነዚህ ይሁዳ ለጋለሞታይቱ መያዣ አድርጎ
የሰጣት ነበሩ፡፡ ስለዚህ ይሁዳ አወቃቸው፡፡ ትዕማርም የቤተሰቡን የዘር ግን
የሚያስቀጥሉ ወንድ ልጆችን ወለደች፡፡
ይህም እግዚአብሄር በኪዳኑ ቃል የሚያምኑና በእርሱም የሚኖሩትን ሰዎች

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የኢየሱስ ክርስቶስ የትውልድ ግንድ 17

እንደሚባርክ ያሳያል፡፡ ስለዚህ የኢየሱስ የትውልድ ግንድ አካል የሆነ ማንኛውም


ሰው እንዲህ የሚሆነው በእግዚአብሄር ቃል ላይ ባለው እምነቱ ነው፡፡ ‹‹ይሁዳም
ከትዕማር ፋሬስንና ዛራን ወለደ›› ተብሎ በምንባቡ ላይ እንደተጻፈ ትዕማር መንታ
ልጆችን በመውለድ በይሁዳ በኩል በእግዚአብሄር ኪዳን ላይ ባላት እምነት
የኢየሱስን የትውልድ ግንድ አስቀጠለች፡፡ እዚህ ላይ ‹‹ስህተት ሰርተሻል›› በማለት
የወቀሱዋት እስራኤሎች አልነበሩም፡፡ እንዲያውም ይህ የተባረከ እምነት ነው
በማለት የትዕማርን እምነት አመሰገኑ፡፡ ልክ እንደዚሁ እግዚአብሄር በአምላክ ቃል
የሚያምኑ ሰዎችን እምነት ይቀበላል፡፡ ትዕማር የኢየሱስ የትውልድ ግንድ አካል
መሆን የቻለችው በእግዚአብሄር ኪዳን በማመንዋ ነው፡፡ እኛም በእግዚአብሄር ቃል
ብናምን የእርሱ ልጆች መሆን እንችላለን፡፡
መልካም ሥራዎችን በመስራት ጻድቃን አንሆንም፡፡ እያንዳንዱ ሐጢያተኛ
ጻድቅ መሆን የሚችለው በእግዚአብሄር ጽድቅ ወንጌል በማመን ከእግዚአብሄር ጋር
አንድ ቤተሰብ ሲሆን ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሄር ልጆች የሚያደርገን
የተቀደሰው ባህሪያችን እንዳልሆነ ይነግረናል፡፡ የእግዚአብሄር ልጆች የምንሆነው
በእግዚአብሄር የኪዳን ቃል ላይ ባለን እምነት ነው፡፡ የእግዚአብሄር ልጆች
የምንሆነውና ወደ ኢየሱስ መንግሥት የምንገባው የእግዚአብሄርን ቃል በሚያምነው
እምነታችን ነው፡፡ እኛ ጻድቃንና ሐጢያት አልባ የምንሆነው በኢየሱስ በማመን
እንደሆነ ማወቅና ማመን አለብን፡፡
ቅዱሳት መጻህፍትን እንደተጻፉት የሚያምን እምነት በእግዚአብሄር ጽድቅ
የሚያምን እምነት እንደሆነ መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል፡፡ ኢየሱስን ስንቀበል ጻድቃን
ለመሆን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ማመን ይኖርብናል፡፡ ብዙውን ጊዜ ‹‹ቅድስና››
የሚለው ቃል በዓለም ላይ ባሉ በሁሉም ሐይማኖቶች ውስ ጥቅም ላይ ይውላል፡፡
ነገር ግን በራሱ መንገድ የተቀደሰ ሰው ወደ እግዚአብሄር መንግሥት እንደማይገባ
ኢየሱስ ነግሮናል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስን እንመረምር፡፡ አብርሃም ለደህንነታቸው
ስለፈራ ሚስቱን እህት አድርጎ አቀረበ፡፡ ይስሐቅም ይህንኑ በሚስቱ ላይ አደረገ፡፡
አብርሃም ሚስቱን ሸጠ፡፡ ይስሐቅም ይህንኑ ያደረገ ሰው ነው፡፡ በምንባቡ ውስጥ
የተጠቀሱት ትዕማርና ረዓብ በእምነታቸው ባይሆን ኖሮ በኢየሱስ የትውልድ ግንድ
ውስጥ መካተት ከማይችሉ ሕዝቦች ምሳሌዎች አንዳንዶቹ ይሆኑ ነበር፡፡ በክርስትና
ውስጥ ቅድስና ማለት ቀስ በቀስ ቅዱስ መሆን ማለት ነው፡፡ ሆኖም ትዕማር
ከአማትዋ ጋር የግብረ ሥጋ ግንኙነት ነበራት፡፡ ረዓብም ጋለሞታ ነበረች፡፡ ሩት
ደግሞ አህዛብ ነበረች፡፡ ከእነዚህ ሴቶች ማናቸውም በሰው ምልከታ የኢየሱስ
የትውልድ ግንድ አካል ለመሆን ቦታ አልነበራቸውም፡፡ ነገር ግን እነርሱ ጻድቃን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


18 የኢየሱስ ክርስቶስ የትውልድ ግንድ

ተብለው የተጠሩትና የኢየሱስ የትውልድ ግንድ አካል የሆኑት በእግዚአብሄር ኪዳን


ላይ ባላቸው ፍጹም እምነት ነበር፡፡ የእግዚአብሄር ልጆች ወደመሆን የሚመራን
የእምነት ዓይነት ይህ ነው፡፡ እኛ በእግዚአብሄር የጽድቅ ቃል ኢየሱስ አዳኛችን
መሆኑን በሚያምነው እምነት የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ወደ ማወቅ
ደርሰናል፡፡ በሌላ አነጋገር እኛ ሐጢያት አልባ ሰዎች የሆንነው 0.0001% በመልካም
ሥራችን አይደለም፡፡ ሐጢያት አልባ ሰዎች የሆንነው፤ የእግዚአብሄር ልጅ የሆነውን
ኢየሱስን አዳኛችንና የተጻፈውን የእግዚአብሄርን ቃል ማለትም የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል በማመናችን ነው፡፡
ኢየሱስን ጌታችንና አዳኛችን አድርገን በመቀበል የእግዚአብሄር ልጆች
ሆነናል፡፡ ንጉሣችን እግዚአብሄር መንፈስ ቅዱስ ያላቸው ሰዎች የእርሱ ሕዝብ
እንደሆኑ ይነግረናል፡፡ እርሱ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምኑትን እንደ እኛ
ያሉ ሰዎች ‹‹ዳግመኛ የተወለዱ ልጆቼ›› ብሎ ይጠራናል፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ
የእግዚአብሄር ጻደቃን ልጆች ገና ከሐጢያቶቻቸው ካልዳኑት ተራ ሰዎች የተለዩ
ናቸው፡፡ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል የተቀበሉና የሚያምኑ ሰዎች
የሐጢያቶቻቸውን ስርየት ካልተቀበሉት ሰዎች የተለዩ ናቸው፡፡ እኛ አዳኛችን
የሆነውን ኢየሱስን በልባችን ውስጥ መድህን አድርገን በመቀበላችን ከሐጢያቶቻችን
ሁሉ ይቅርታን አግኝተናል፡፡ ጌታ ወደዚህ ዓለም መጥቶ በዮርዳኖስ ወንዝ
በአጥማቂው ዮሐንስ እንደተጠመቀና በመስቀል ላይ በመሞትም ደሙን እንዳፈሰሰ
ስለምናምን ቀድሞውኑም የሐጢያቶቻችንን ስርየት እንደተቀበልን እናውቃለን፡፡
ስለዚህ በእግዚአብሄር ልጅ አማካይነትና ያንንም እውነት በማመን የእግዚአብሄር
ልጆች ሆነናል፡፡
ሐሌሉያ! ይህንን የእግዚአብሄር ጽድቅ የሆነውን የውሃውንና የመንፈሱን
ወንጌል ስለሰጠን እግዚአብሄርን እናመሰግነዋለን፡፡ 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


እኛን ለማዳን የመጣውን
ጌታችንን ኢየሱስን
እናመስግነው
‹‹ ማቴዎስ 1፡18-25 ››
‹‹የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት እንዲህ ነበረ፡፡ እናቱ ማርያም ለዮሴፍ
በታጨች ጊዜ ሳይገናኙ በመንፈስ ቅዱስ ጸንሳ ተገኘች፡፡ እጮኛዋ ዮሴፍም ጻድቅ
ሆኖ ሊገልጣት ስላልወደደ በስውር ሊተዋት አሰበ፡፡ እርሱ ግን ይህን ሲያስብ እነሆ
መልአክ በሕልም ታየው፡፡ እንዲህም አለ፡- የዳዊት ልጅ ዮሴፍ ሆይ ከእርስዋ
የተጸነሰው ከመንፈስ ቅዱስ ነውና እጮኛህን ማርያምን ለመውሰድ አትፍራ፡፡
ልጅም ትወልዳለች፤ እርሱም ሕዝቡን ከሐጢአታቸው ያድናቸዋልና ስሙን ኢየሱስ
ትለዋለህ፡፡ በነቢይም ከጌታ ዘንድ እነሆ ድንግል ትጸንሳለች፤ ልጀም ትወልዳለች፤
ስሙንም አማኑኤል ይሉታል የተባለው ይፈጸም ዘንድ ይህ ሁሉ ሆኖአል፡፡
ትርጓሜውም እግዚአብሄር ከእኛ ጋር የሚል ነው፡፡ ዮሴፍም ከእንቅልፉ ነቅቶ የጌታ
መልአክ እንዳዘዘው አደረገ፡፡ እጮኛውን ማርያምንም ወሰደ፡፡ የበኩር ልጅዋንም
እስክትወልድ ድረስ አላወቃትም፡፡ ስሙንም ኢየሱስ አለው፡፡››

የገና በዓልን እናከብራለን፡፡ በዓሉ በዚህ ዓመት በዝምታ የተሞላና ቅዱስ


ሌሊት ይመስላል፡፡ ከተማይቱ ጸጥ ያለችና የተረጋጋች ሆናለች፡፡ የኢኮኖሚ ችግር
ስለተጋረጠብን የገና በዓል መብራቶችን ወይም ጌጦችን በመንገድ ላይ ማየት አዳጋች
ነው፡፡ ይህ በእነዚህ ቀናቶች ያለውን የኢኮኖሚ ችግር የሚያንጸባርቅ መሆን
አለበት፡፡ ይህም በዚህ ዓመት ሌላ የገና በዓል ስለሚኖረን እንዴት እምነታችንን
መጠበቅ እንደሚገባን ያስታውሰናል፡፡ ከማቴዎስ ወንጌል አንድ የአዲስ ኪዳን
ምንባብ እንመልከት፡፡
ቁጥር 21 እንዲህ ይላል፡- ‹‹ልጅም ትወልዳለች፤ እርሱም ሕዝቡን
ከሐጢአታቸው ያድናቸዋልና ስሙን ኢየሱስ ትለዋለህ፡፡›› ጌታችን በድንግል በኩል

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


20 እኛን ለማዳን የመጣውን ጌታችንን ኢየሱስን እናመስግነው

በዚህ ዓለም ላይ ተወልዶ ኢየሱስ ተብሎ ተጠራ፡፡ ‹‹ኢየሱስ›› የሚለው ስም


ሕዝቡን ከሐጢያታቸው የሚያድን ማለት ነው፡፡
እኛ አስቀድመን ኢየሱስን የተገናኘን ሰዎች የገና በዓልን ስንቀበል ደስተኞች
ነን፡፡ ነገር ግን የዚህን ቀን ትርጉም እስካላወቅን ድረስ የገና በዓል ማለት ምንም
ማለት እንዳልሆነ እንረዳለን፡፡ የገናን በዓል በጌታ ውስጥ ሆነን የምንቀበለው ከሆነ
ጌታ ለእናንተ ያለው ፍቅር የተትረፈረፈ እንደሆነ ማየት እንችላለን፡፡ የገና በዓል
የነገሥታት ንጉሥ የሆነውና አጽናፈ ዓለማትን የፈጠረው እግዚአብሄር ሕዝቡን
ከሐጢያቶቻቸው ለማዳን አንድያ ልጁን ወደዚህ ዓለም መላኩን ያመለክታል፡፡ እኛ
በእርሱ ውስጥ ስንሆን የገና በዓል እጅግ አስደሳችና የሚወደስ ቀን ይሆናል፡፡
እግዚአብሄርን ለማመስገን አንድን ቀን የገና በዓል አድርገን የለየነው ለዚህ
ነው፡፡ በእርግጥ ይህ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተገለጠው ትክክለኛው ቀን ሊሆን
አይችልም፡፡ አንዳንድ ሰዎች ይህ ቀን የጸሐይ አምላክ የሚመለክበት ቀን ነው
በማለት ይከራከራሉ፡፡ ሆኖም የገናን በዓል ትርጉም ማሳነስ አይገባንም፡፡ አንዳንድ
ሰዎች ኢየሱስ ተወልዶበታል ያልነው ቀን የተሳሳተ ቀን እንደሆነ ያምናሉ፡፡
ትክክለኛው ቀን መቼም ይሁን እርሱ ወደዚህ ዓለም ለምን እንደመጣ ለማስታወስ
የገናን በዓል ማክበር ይገባናል፡፡ የገናን በዓል ስናከብር ጌታን ስለ ፍቅሩና ከእርሱ
ስለተቀበልነው ደህንነት በጥልቀት ልናስብ ይገባናል፡፡ በክርስቶስ ውስጥ ሆነን
የጌታን ምጽዓት ልናከብርና ከሐጢያቶቻችን ሁሉ እንዳዳነን በማመንም እርሱን
ልናመሰግነው ያስፈልገናል፡፡ የገናን በዓል በተጨባጭ ለማክበር የገናን በዓል
አውነተኛ ትርጉም መረዳት ያስፈልገናል፡፡
የእሁድ አምልኮ አገልግሎትን እየሰጠን ነው፡፡ አሁን ከጠዋቱ 5፡12 ትናትናም
ከጠዋቱ 5፡12 ነበረ፡፡ ነገም ከጠዋቱ 5፡12 ይሆናል፡፡ ይህ ማለት ዓለም ጌታችን
እስኪመጣ ድረስ ትቀጥላለች ማለት ነው፡፡ ይህች ዓለም እግዚአብሄር
እስከሚያጠናቅቃት ድረስ ትኖራለች፡፡ ነገር ግን በጌታ ውስጥ ሆነን የገናን በዓል
እውነተኛ ትርጉም የማንረዳ ከሆንን ይህ የተለየ የአምልኮ አገልግሎት ከእኛ ጋር
የሚያገናኘው ምን አንዳች ነገር አለው? ጥር 25 ከጠዋት 5፡12 ማለት በዓመቱ
ውስጥ ከሚያልፈው ከሌላው ሰዓት የበለጠ ምንም ነገር የለውም ማለት ነው፡፡ ወደ
ዓመቱ ፍጻሜ ስንቃረብ በጌታ ያለንን እምነት ደግመን መፈተሸ ይገባናል፡፡ ጌታ
የሰጠንን ፍቅርና የተቀበልነውን ደህንነት ማስታወስ ያስፈልገናል፡፡ ሕይወትን
ጨምሮ በዚህ ዓለም ላይ ያለው እያንዳንዱ ነገርና የሚያልፈው እያንዳንዱ ጊዜ ያለ
ኢየሱስ ትርጉም የለውም፡፡
በሌላ በኩል የገናን በዓል በጌታ ውስጥ ሆነን ስንቀበለው ብዙ ትርጉም

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


እኛን ለማዳን የመጣውን ጌታችንን ኢየሱስን እናመስግነው 21

አለው፡፡ እኛ ከሐጢያቶቻችን ሁሉ የዳንነው እርሱ እኛን ለማዳን ስለመጣ ነው፡፡


እኛን ለማዳን ባይመጣ ኖሮ በእርግጥም ለጥፋት የተወሰንን እንሆን ነበር፡፡ ነገር ግን
ኢየሱስ በእኛ ምክንያት ተጠመቀ፤ ተሰቀለም፡፡ ሕዝቡን ከሐጢያቶቻቸው ለማዳን
በድንግል ማርያም በኩል ወደዚህ ዓለም መጣ፡፡ ስለዚህ ክርስቲያኖች እንደ
መሆናችን የገና በዓል በትክክል ቅዱስ ቀን ነው፡፡
ከዚህ የተነሳ የጌታችንን ልደት መላውን ዩኒቨርስ በፈጠረውና በሚቆጣጠረው
እንደዚሁም መጀመሪያውንና መጨረሻውን በሚያየው ጌታ ውስጥ ሆነን
ስንመለከተው ከእኛ ጋር የሚገናኝ አንድ ነገር አለው፡፡ ስለዚህ በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል አማካይነት የእርሱን እውነተኛ የፍቅር ሥራ ማየት ያስፈልገናል፡፡ ይህ ዓለም
የኖረው እግዚአብሄር ዩኒቨርስን ስለፈጠረ ነው፡፡ እግዚአብሄር ከዚህ ቀደም አንድ
ጊዜ እንዳደረገው ይህንን ዓለም እንደሚያጠፋው ተናግሮዋል፡፡ መጨረሻው ቅርብ
እንደሆነ ማየት እንችላለን፡፡ የጸደይን፣ የበጋን፣ የበልግንና የክርምትን ዑደተ ወቅቶች
በጌታ ውስጥ ሆነን ስንመለከት ‹‹ኦ! ይህ የእግዚአብሄር ሥራ ነው!›› ብለን ስሜቱ
እንደሚሰማንና እንደምንረዳ ሁሉ እርሱ እኛን ከሐጢያቶቻችን ሲያድነንም አዲስ
ዓለም እየፈጠረ እንደሆነ ስሜቱ ሊሰማን ይችላል፡፡
ይህ ዩኒቨርስ የሚንቀሳቀሰው ሁሉን ቻዩ አምላክ ይህንን ዩኒቨርስ
ስለሚቆጣጠረው መሆኑን እናውቅ ዘንድ እርሱ የራሱን ፍጥረት አሳይቶናል፡፡ ሰዎች
የሚያምኑት ራሳቸው በዓይናቸው በብረቱ ሲያዩ ነው፡፡ በእግዚአብሄር ውስጥ
ስንሆን እርሱ እንዴት እንደሚሰራ በግልጽ መረዳት እንችላለን፡፡ ነገር ግን በጌታ
ውስጥ ሆነን አራቱን ወቅቶች ስንመለከት የእግዚአብሄርን ቸርነት በጣም በግልጽ
ማየት እንችላለን፡፡ ሕይወታችንን በእግዚአብሄር ውስጥ ሆነን ስንመለከት
ሕይወታችንን በግልጽ ማየት እንችላለን፡፡ ይህንን በጌታ ውስጥ ሆነን ስንመለከት
ተራ ሰዎች እስኪሞቱ ድረስ 70 ወይም 80 ዓመት የጉስቁልና ሕይወት ይኖራሉ፡፡
እኛ በጉስቁልና ኖረን በጉስቁልና እንድንሞት ተወስነን ነበር፡፡ ጌታችን
በሐጢያቶቻችን ምክንያት ለጥፋት የተመደብነውን እኛን በአንድ ጊዜ ለማዳን
ወደዚህ ዓለም መጥቶ እንደተጠመቀ፣ እንደተሰቀለና በሦስተኛው ቀን ከሙታን
እንደተነሳ ማየት እንችላለን፡፡ እኛ በክርስቶስ ውስጥ ሆነን በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ድነን ከጥፋትና ከእርግማን ተነጥቀናል፡፡ ስለዚህ
ሁሉንም ነገር በክርስቶስ ውስጥ በእምነት ዓይኖች ማየት አለብን፡፡
አንዳንድ ሰዎች ማርያም ድንግል በመሆንዋ በእርግጥ ልጅ ሊኖራት መቻሉን
ይጠራጠራሉ፡፡ እንዲያውም አንዳንድ መጋቢዎችም እንኳን ኢየሱስ በድንግል
ማርያም በኩል መወለዱን ይጠራጠራሉ፡፡ የእርሱን ሥጋ መልበስ ቢሰብኩና

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


22 እኛን ለማዳን የመጣውን ጌታችንን ኢየሱስን እናመስግነው

ቢያከብሩም በተጨባጭ ግን ኢየሱስ በድንግል ማርያም በተዓምራዊ መንገድ


እንደተጸነሰና እንደተወለደ አያምኑም፡፡ እነዚህ ሰዎች በዚህ መንገድ ደደብነታቸውን
ያሳያሉ፡፡ እኛ የእግዚአብሄርን ሥራዎች በጌታ ውስጥ ሆነን በእምነት ዓይኖች
የማናይ ከሆነ ልናምናቸው አንችልም፡፡ ምንባቡ ኢየሱስ በመንፈሰ ቅዱስ ከተጸነሰ
በኋላ እንደተወለደና ከመወለዱ በፊትም እግዚአብሄር ለሕጻኑ ኢየሱስ ስም
እንዳወጣለት ይነግረናል፡፡
ኢየሱስ ከመወለዱ ከ700 ዓመታት በፊት እግዚአብሄር በነቢዩ ኢሳይያስ
በኩል ‹‹ድንግል ትጸንሳለች፤ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፤ ስሙንም አማኑኤል ብላ
ትጠራዋለች፡፡›› (ኢሳይያስ 7፡14) ይህ እግዚአብሄር ሰዎችን ለማዳን የሰው ሥጋ
ለብሶ ወደዚህ ዓለም የሚመጣ የሚናገር ትንቢት ነው፡፡ ይህንን በጌታ ውስጥ ሆነን
ስንመለከተው ይህ ሰዎችን ከሐጢያቶቻቸው ለማዳን የእግዚአብሄር ሥራ መሆኑን
ማየት እንችላለን፡፡ ይህም እግዚአብሄር ሰዎችን እንደፈጠረና ከሐጢያቶቻችንም
እንዳዳነን ማየትና ማመን እንችል ዘንድ ነው፡፡
ሆኖም ይህንን በሰዎች ዓይን ብቻ አይተን በሰው ተጠየቅ ለመረዳት
የምንሞክር ከሆንን ማመኑ አዳጋች ነው፡፡ ከዚህ የተነሳ አንዳንድ ሰዎች እግዚአብሄር
ሰዎችን በመፍጠር የተደሰተ ብቻ ሳይሆን መልካምና ክፉን ከምታስታውቀው ዛፍ
በልተው መከራ ውስጥ መዘፈቃቸውን ማየቱም በጣም አስቂኝ እንደሆነም
አስቦዋል፡፡ ነገር ግን ውድ ክርስቲያኖች ምድርና ሌሎች ፕላኔቶች በሙሉ
በተመደበላቸው ምህዋር ዙሪያ የመሽከርከራቸው ሚልኪ ዌይ የመኖሩ፣ ይህች
ምድርም ለሰው ሕይወት ፍጹም የሆኑ ሁኔታዎች ያሉዋት የመሆኑ፣ ቀንና ሌሊት
የመኖሩ፣ የዘመኑ ሳይንስ ሊያስተውለው በማይችላቸው ምስጢራዊ ሥራዎችና
የሕይወት ተዓምራቶች ትክክለኝነት እውነታ የቸርነት አምላክ እንዳለ ይነግረናል፡፡
ጌታ ወደዚህ ምድር በመጣ ጊዜ በመንፈስ ቅዱስ ተጸንሶ ተወለደ፡፡ ኪዳኑን
ለመፈጸምም ‹‹አማኑኤል›› ሆነ፡፡ በሌላ አነጋገር እርሱ የደህንነት መሰናዶውን
በዩኒቨርስ ፍጥረት ፊት በማኖር ለእኛ ለሰዎች ቃል ገብቶ ቃሉን ፈጽሞዋል፡፡ እርሱ
በድንግል በኩል ብቻ የመምጣቱ እውነታ ለእኛ በረከት ነው፡፡ ለዚህም
እግዚአብሄርን እናመሰግናለን፡፡
በኢየሱስ ስናምን ተጠራጣሪ መሆን አይገባንም፡፡ ስንጠራጠር ሁሉም ነገር
አጠራጣሪ መስሎ ይታያል፡፡ ለዚህ ምክንያቱ በሐጢያቶቻችን ስንታወርና
ተጠራጣሪዎች ስንሆን እምነታችን ምሉዕ ስለማይሆን ፍጹም የሆኑትን
የእግዚአብሄር መልካም ሥራዎች በሚገባ ማየት አለመቻላችን ነው፡፡ ነገር ግን ሙሉ
በሙሉ በእግዚአብሄር ስንታመን ዓይኖቻችን በመንፈስ ቅዱስ ይከፈቱና

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


እኛን ለማዳን የመጣውን ጌታችንን ኢየሱስን እናመስግነው 23

ከሐጢያቶቻችን ለመዳን ኢየሱስን መቀበል እንችላለን፡፡ እኛ በእግዚአብሄር ጽድቅ


የምናምን ሰዎች በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን ከሐጢያቶቻችን ድነናል፡፡ ምክንያቱም
በጌታ ጽድቅ ውስጥ ያሉትን የእርሱን ሥራዎች በተጨባጭ እንመለከታለን፡፡
ተጠቃሚዎች የሆንነው ይህንን በጌታ ጽድቅ ውስጥ በመመልከታችን ነው፡፡ ነገር
ግን በእግዚአብሄር ጽድቅ የማያምኑ ሰዎች የገናን በዓል የሚቀበሉት ምንም ትርጉም
የሌለው አድርገው ነው፡፡
ኢየሱስ ከእኛ ጋር ለመሆን አማኑኤል ሆኖ ወደዚህ ዓለም መጣ፡፡ በመንፈስ
ቅዱስ ተጸንሶ ሕጻን ኢየሱስ ሆኖ ተወለደ፡፡ በ30 ዓመቱ በመጠመቅም የሰዎችን
ሐጢያቶች ሁሉ ወስዶ የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ ተሸክሞ ተሰቀለ፡፡ ዳግመኛም
ከሙታን ተነሳ፡፡ ዳግመኛ የሚመጣ አማኑኤል አምላክ ሆነ፡፡ በመንፈስ ቅዱስ
የተጸነሰው ሕጻን ኢየሱስ ሆኖ የተወለደው፣ በመጠመቅም ሐጢያቶቻችንን
ለመውሰድ ያደገው፣ በመስቀሉ ደም ያዳነን፣ አሁንም በመንፈስ ቅዱስ መልክ
በልባችን ውስጥ የሚኖረውና የሚሰራው ጌታችን ነው፡፡ በእግዚአብሄር ጽድቅ
በሚያምነው የእምነት ልባችን ውስጥ የሚኖረው መንፈስ ቅዱስ የደህንነትን፣
የሰላምንና የበረከቶችን ጸጋ ሰጥቶናል፡፡ ኢየሱስ የዘላለም አዳኛችን የመሆኑን
እውነታ እንመን፡፡
የሆኖ ሆኖ ታህሳስ 25 (ወይም በኢትዮጵያ አቆጣጠር ታህሳስ 29) የጌታችንን
ኢየሱስ ልደት ለማክበርና ለእግዚአብሄር ምስጋና ለማቅረብ የምናስብበት ቀን ነው፡፡
ይህንን ቀን ማክበር በመቻላችን እግዚአብሄርን እናመሰግናለን፡፡ ታህሳስ 25 ላይ
ምንም የገና በዓል ባይኖር ምድር አሳዛኝ ስፍራ ትሆን ነበር፡፡ የሰው ዘርም ያለ
ኢየሱስ በተስፋ መቁረጥ ውስጥ ይኖር ነበር፡፡ ምንም የሚያስደስት ነገር አይኖርም
ነበር፡፡ የሰው ዘር የሐጢያተኞች አዳኝ፣ የሰዎች አዳኝ፣ ወደ ጥፋት የሚነጉዱ ሰዎች
አዳኝ ሆኖ ወደዚህ ዓለም በመምጣቱ አንድ እውነታ አዲስ ተስፋን ተቀብሎዋል፡፡
ያለፈው ጊዜ ምንም ያህል አስከፊ የነበረ ቢሆንም በጌታ ውስጥ ሆነን የወደፊቱን
ተስፋ እናደርጋለን፡፡
ኢየሱስ ባይመጣ ኖሮ በዚህ ዓለም ላይ ምን ተስፋ ይኖረን ነበር? እንደ
ሶቅራጥስ፣ ሳካያሙኒና ኮንፊሺየስ ያሉ የዚህ ዓለም ‹‹ጠቢባን›› እና ‹‹ቅዱሳን›› ምን
አደረጉልን? ከሞራል አስተምህሮቶች የበለጠ ምንም ነገር አልሰጡንም፡፡ በዚህ ዓለም
ላይ ጥሩ ሕይወትን መኖር የማይፈልግ ማን ነው? እነርሱ ከሐጢያቶቻችን፣
ከፍርድና ከጥፋት ደህንነትን ሊሰጡን አልቻሉም፡፡
እናንተንና እኔን ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ያዳነን ብቸኛው አካል ኢየሱስ ነው፡፡
እርሱ በጥምቀቱና በስቅለቱ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ለመደምሰስ ወደዚህ ዓለም

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


24 እኛን ለማዳን የመጣውን ጌታችንን ኢየሱስን እናመስግነው

መጣ፡፡ ከሐጢያቶቻቸው የሚድኑት የእግዚአብሄር ጽድቅ በሆነው የውሃውና


የመንፈሱ ወንጌል የሚያምኑ ሰዎች ብቻ ናቸው፡፡ በእግዚአብሄር ጽድቅ የማያምኑ
ሰዎች ዳግመኛ ሊወለዱ አይችሉም፡፡ ከዚህ ምልከታ አንጻር እውነተኛውን
የሐጢያት ስርየት የምንቀበለው ጌታ የነገሥታቶች ሁሉ ንጉሥ መሆኑን በማመንና
እርሱ ወደዚህ ዓለም መጥቶ እንደተጠመቀ፣ በመስቀል ላይ እንደሞተ፣ ከሙታን
እንደተነሳና አዳኛችን እንደሆነ በሚያምነው እምነት በማመን ነው፡፡ ጌታ እኛን
ለማዳን ወደዚህ ዓለም በመምጣቱ አዲስ ሕይወት አግኝተን ሰማይ መግባት
የሚችሉ የእግዚአብሄር ሰዎች ሆነናል፡፡
የሰው ዘር ታሪክ እርስ በርሳችን የምንነካከስበትና የምንዋዋጥበት ራስን ወደ
ማጥፋት የሚመራ ታሪክ ነው፡፡ ታሪካችን እስከ አሁን ድረስ እርስ በርስ የመነካከስ፣
የመተኛኘክና የመገዳደል ታሪክ ብቻ ነው፡፡ እርስ በእርስ የመገዳደሉ ሐጢያት
በሰው ዘር ታሪክ ውስጥ እጅግ ታላቅ የሆነው ሰው እርሱን በዮርዳኖስ ወንዝ
ባጠመቀው ጊዜ ወደ ጌታችን ተላለፈ፡፡ እርሱ ለሐጢያታችን በመሰቀሉም
ወዲያውኑ ከሐጢያታችን ዳንን፡፡ ኢየሱስ ግን ወደዚህ ዓለም መጥቶ በሰው ታሪክ
ውስጥ እጅግ ታላቅ በሆነው ሰው በዮርዳኖስ ወንዝ በመጠመቅ እርስ በርስ
ያነካከሱትንና ያገዳደሉትን የሐጢያተኞች ሐጢያቶች በሙሉ ወስዶ ራሱን
በመስቀል ላይ በመስጠትና በመሞት ከዓለም ሐጢያቶች ሁሉ ወዲያውኑ አዳነን፡፡
ይህንን እውነት ፈጥነን ማመን አለብን፡፡ ጌታ የደህንነትን ተስፋ የሰጠን እንደዚህ
ነው፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስን የሚያምነውንና የሚታመነውን እምነታችንን ከግል
ሕይወታችን ወይም ከመላው የሰው ታሪክ ውስጥ አውግዘን ማስወገድ አይገባንም፡፡
ያለ ኢየሱስ ክርስቶስ የሰው ዘር ታሪክ የሚባል ነገር ሊኖር አይችልም፡፡ በዚህ ዓለም
ላይ ያለ ኢየሱስ እውነተኛ የቤተሰብ ዕሴት የሚባል ነገር ሊኖር አይችልም፡፡ ያለ
ኢየሱስ እውነተኛ እምነት ወይም እውነተኛ ደህንነት የሚባል ነገር ሊኖር
አይችልም፡፡ ‹‹ሰባኪ ከሆንህ ጀምሮ ስትናገረው የነበረው ይህንኑ ነው›› ትሉ
ይሆናል፡፡ ነገሩ እንደዚያ አይደለም፡፡ ምሳሌ ልሰጣችሁ እወዳለሁ፡፡ ያለ ኢየሱስ
የሰው ዘረ ታሪክ የሚባል ነገር ሊኖር አይችልም ብያለሁ፡፡ ይህ አባባል እውነት
መሆኑን ወይም አለመሆኑን እንመርምር፡፡
ባለፉት ዘመናት ታላቋ ብሪታንያ ብዙ አገሮችን አሸንፋለች፡፡ ‹‹ጸሐይ
በብሪታንያ መንግሥት ውስጥ ፈጽሞ አትጠልቅም›› የሚል ሐረግ ተፈጠረ፡፡ በታላቋ
ብሪታንያ ጸሐይ የምትጠልቅባቸው የቀን ሰዓታቶች አልነበሩም፡፡ ጸሐይ የብሪታንያ
ቅኝ ግዛት በሆነ በአንድ አገር ስትጠልቅ በሌላኛው የብሪታንያ ቅኝ ግዛት በሆነው

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


እኛን ለማዳን የመጣውን ጌታችንን ኢየሱስን እናመስግነው 25

አገር ላይ ጸሐይ ትወጣ ነበር፡፡ ስለዚህ ጸሐይ ፈጽሞ በብሪታንያ ቅኝ ግዛት ውስጥ
አትጠልቅም፡፡ ታላቋ ብሪታንያ በዓለም ላይ ብርቱ የነበረችው እንደዚህ ነበር፡፡
ዓለምን በሐይል አሸንፈው ነበር፡፡ በዚያን ዘመን በታላቋ ብሪታንያ ብዙ
ፑሪታውያን ነበሩ፡፡ ኢየሱስን ጌታቸውና አዳኛቸው አድርገው ያመኑ እነዚህ
ፑሪታውያን ከታላቋ ብሪታንያ ሸሽተው ወደ አሜሪካ ሄዱ፡፡ ስለ እምነታቸው
በምታሰድዳቸው አገር ውስጥ መኖር አልቻሉም፡፡ ፑሪታውያን ከታላቋ ብሪታንያ
ሲሸሹ ጸሐይ አትጠልቅም የሚለው ዝናም እንደዚሁ ደበዘዘ፡፡ እነርሱ በዓለም ላይ
የነበራቸው ሐብትና ሥልጣንም ሞተ፡፡ ዛሬ የቀረላቸው ብቸኛው ዝና የጨዋዎች
አገር መሆን ብቻ ነው፡፡
ወደ አሜሪካ የሸሹት ፑሪታውያን ትክክል ይሁን ወይም አይሁን ወንጌላቸውን
ለቀረው ዓለም አሰራጩ፡፡ ይህ ሲሆን አሜሪካ በዓለም ላይ አዲስ ልዕለ ሐይል ሆና
ተነሳች፡፡ ይህ ምስጢር ነው ብላችሁ አታስቡምን? አሜሪካኖች ወንጌልን በኮርያ
አስፋፉ፡፡ አሁን የኮርያ ኢኮኖሚ አደገ፡፡ እኛም አሁን ‹‹የእስያ ደራጎን›› ተብለን
እንጠራለን፡፡ የደራጎን (ዘንዶ) ምልክት በመንፈሳዊ ምልክት ጥሩ ምልክት አለመሆኑ
እርግጥ ነው፡፡ ነገር ግን ለማያምኑ ሰዎች ደራጎን አምላካቸው አድርገው
የሚሰግዱለት ጠንካራ ምልክት ነው፡፡ የኮርያ የኢኮኖሚ ዕድገት ‹‹የእስያ ደራጎን››
ወይም ‹‹የእስያ ነብር›› የተባለው ለዚህ ነው፡፡
የዓለምን ታሪክ ስንመለከት ኢየሱስን ያገለገሉና ወንጌልን ያስፋፉ አገሮች
የኢኮኖሚ ተሐድሶ እንደነበራቸው ማየት እንችላለን፡፡፡ አንድ አገር ከኢየሱስ
ሲያፈነግጥና ምዕመናኖችን ሲያሳድድ ኢኮኖሚው ይሞታል፡፡ የአንድ አገር ብልጥግና
የሚደገፈው ያ አገር በሚያስፋፋው ወንጌል ነው፡፡
ማየት እንደምንችለው ኢየሱስ የዓለም ታሪክ ማዕከል ነው፡፡ ኢየሱስ በሰው
ዘር ታሪክ ውስጥ እጅግ የተባረከ ጌታና አዳኝ ነው፡፡ ኢየሱስ አሁንም ሕያው ነው፡፡
ዩኒቨርስንና የእናንተንና የእኔን ሕይወት ይገዛል፡፡ በልባችን ውስጥም ሰላምን
ይሰጠናል፡፡ ወደ እርሱ መመልከት፣ እርሱን ማምለክ፣ ስለተትረፈረፈው ጸጋውም
እርሱን ማመስገን አለብን፡፡ በዚህ ዓለም ላይ ሕይወታችንን ስንኖር ሁሉንም ነገር
በጌታ ውስጥ መመልከትና በጌታ ባለን እምነት መኖር አለብን፡፡ ያልኩት በጌታ
ውስጥ ነው! በዚህ ዓለም ላይ የሰውን ታሪክ ገጠመኞችና የኢኮኖሚ ለውጦችንም
በእምነት መነጽር መመልከት ያስፈልገናል፡፡ እያንዳንዱን ነገር በትክክል ማየት
የምንችለው ነገሮችን በኢየሱስ ክርስቶስ መነጽር ስናይ ብቻ ነው፡፡
ከሐጢያቶቻችንም ለመዳን ብቸኛው መንገድ ይህ ነው፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስ ለእኛ ማነው? እርሱ የነገሥታት ንጉሥ ነው፡፡ ንጉሡ የራሱን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


26 እኛን ለማዳን የመጣውን ጌታችንን ኢየሱስን እናመስግነው

ሕዝብ ለማዳን ወደዚህ ዓለም በመምጣቱ እውነታ አመስጋኞች ልንሆን ይገባናል፡፡


ንጉሣችሁ እናንተን ለማዳን ወደዚህ ዓለም መጥቷል፡፡ ልክ እንደ እናንተ የደከመ
ሥጋ ይዞ የመጣውን አምላክ ታመሰግኑታላችሁን?
አንዳንዶች ‹‹ምን የሚያስመሰግን ነገር አለ? እንዲህ ባለ ቀን አንድ ከሩዝ
የተሰራ ዳቦ በሾርባ መብላት፣ መጠጥ መጠጣት፣ ጊዜን መቅጨት ነው፡፡ አንድ ሰው
ለመጠጥ ቢጋብዘኝና ቢከፍልልኝ ምናልባት አመሰግነው ይሆናል፡፡…ምን
የሚያስመሰግን ነገር አለ?›› ይሉ ይሆናል፡፡ ይህ እንዲህ የሚሆነው ግለሰቡ ይህንን
በሰው ዕይታ ስላየው ነው፡፡ ውድ ክርስቲያኖች እውነተኛ ደስታ በማይረቡ ነገሮች
ውስጥ አይገኝም፡፡ የሚገኘው ጌታ ንጉሥ ሆኖ መጥቶ እናመሰግነው ዘንድ
ከሐጢያቶቻችሁ ያዳናችሁ መሆኑን በማወቅ ነው፡፡ ንጉሡ መጥቶ አዳነን፡፡
አመስጋኝ ልንሆን የሚገባን ለዚህ ነው፡፡ የነገሥታት ንጉሥ እኛን ለማዳን
በመምጣቱና እኛን በማዳኑ እውነታ አመስጋኞች ልንሆን ይገባናል፡፡ አንድ ሰው
በዕድሜያችን ሁሉ ያለብንን ዕዳ የሚከፍልልንን ገንዘብ ቢሰጠን በሰው ዕይታ
አመስጋኞች ልንሆን እንችላለን፡፡ ነገር ግን በተጨባጭ አመስጋኞች ልንሆን የሚገባን
የነገሥታት ንጉሥ ወደ ሲዖል እንወርድ ዘንድ የተወሰነብንን እኛን ለማዳን
በመምጣቱ ነው፡፡ ውድ ክርስቲያኖች ይህ እንዲህ ነው ወይስ አይደለም? --
በትክክል እንደዚሁ ነው፡፡
ራሳችንን በጌታ ውስጥ በትክክል ስንመለከት አመስጋኞች ነን፡፡ እኔ ወንጌልን
የምሰብከው እያንዳንዱን ነገር በጌታ ውስጥ በማየት፣ የጌታን በረከቶች በማመንና
በማመስገን ነው፡፡ እኔ እያንዳንዱን ነገር በጌታ ውስጥ ስለማይ ምንም ነገር
ባይኖረኝም እንኳን አመስጋኝና ያለኝ የሚበቃኝ ነኝ፡፡ ጌታ እኔን ለማዳን መምጣቱን
በጌታ ውስጥ ሆኜ ሳየው በጣም ያረካኛል፡፡ ይህንን በጌታ ውስጥ ሆነን ሳይሆን
በሰዋዊ ዓይኖቻችን ከጌታ ውጭ ሆነን የምናየው ከሆነ ምንም ነገር አያረካንም፡፡ ጌታ
የሰጠንን ደህንነት ተመልክተን በጌታ ውስጥ አመስጋኝ መሆን ይኖርብናል፡፡
እያንዳንዱን ነገር በጌታ ውስጥ ማየት ይኖርብናል፡፡ በእምነታችን ከሌሎች ጋር
መተባበር አለብን፡፡ በእምነታችንም ታሪክን መመርመር አለብን፡፡ እያንዳንዱን ነገር
የምንጋፈጠው በእምነታችን መሆን አለበት፡፡ ሌሎች ሰዎችን በጌታ ውስጥ ሆነን
ልናያቸው ይገባናል፡፡ የዓለምን ታሪክ በጌታ ውስጥ ሆነን ማየት ይኖርብናል፡፡
ዓለምን በእምነታችን ስንጋፈጠው በልባችን ውስጥ እውነተኛ ሰላምና በረከቶች
ይኖሩናል፡፡ ያንን ስናደርግ በእርግጥም በጌታ ሕይወት ሰላምና በረከቶች ይኖራሉ፡፡
አመስጋኞች የምንሆነው ለዚህ ነው፡፡
በማንኛውም ጊዜ በጌታ ውስጥ ስንመለከት ‹‹ሁልጊዜ ደስ ይበላችሁ፤

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


እኛን ለማዳን የመጣውን ጌታችንን ኢየሱስን እናመስግነው 27

ሳታቋርጡ ጸልዩ፤ በሁሉ አመስግኑ›› ለሚለው ትዕዛዝ ታማኝ መሆን እንችላለን፡፡


ይህንን በጌታ ውስጥ የማናየው ከሆነ ‹‹ሁልጊዜ እናለቅሳለን፤ ሳናቋርጥ እናለቅሳለን፤
በሁሉ እናለቅሳለን፡፡›› እናንተና እኔ እያንዳንዱን ነገር በጌታ ውስጥ ማየት አለብን፡፡
ይህንን የገና በዓል ስንቀበል የነገሥታት ንጉሥ እናንተን ለማዳን ስለመጣና
ስላዳናችሁ የሰውን ዘር ሐጢያቶች በሙሉም ስላስወገደ አመስጋኞች ልንሆን
ያስፈልገናል፡፡ ይህንን የገና በዓል በዚህ ዓይነት እምነት ልንቀበለውና አመስጋኞች
ልንሆን ያስፈልገናል፡፡
ውድ ክርስቲያኖች ለዚህ አመስጋኞች ልንሆን ይገባናል ወይስ አይገባንም?
አመስጋኞች ነን፡፡ ይህ ተረት ነው ወይስ እውነት? ይህ እውነት ነው፡፡ መጽሐፍ
ቅዱስ እንዲህ ይላል፡- ‹‹በነቢይም ከጌታ ዘንድ እነሆ ድንግል ትጸንሳለች፤ ልጀም
ትወልዳለች፤ ስሙንም አማኑኤል ይሉታል የተባለው ይፈጸም ዘንድ ይህ ሁሉ
ሆኖአል፡፡ ትርጓሜውም እግዚአብሄር ከእኛ ጋር የሚል ነው፡፡›› (ማቴዎስ 1፡22-23)
በዚህ ምድር ላይ ያላገባች ሴት ልጅ መውለድ ትችላለችን? ያላገባች ሴት
ከማግባቷ በፊት አስቀድማ ልትወልድ ትችላለች፡፡ ብዙ ሴቶች ከጋብቻ ውጭ ልጆች
አሉዋቸው፡፡ የሕጻናት ማሳደጊያ ጣቢያን በመጎብኘት ይህንን ማረጋገጥ እንችላለን፡፡
ብዙ ልጆች ትዳር በሌላቸው እናቶቻቸው ለሕጻናት ማሳደጊያ ተሰጥተዋል፡፡ በውጭ
አገራቶች የሚኖሩ ቤተሰቦች ከጋብቻ ውጭ የተወለዱ አንዳንድ ልጆችን በጉዲፈቻ
ወስደው ያሳድጋሉ፡፡ ያላገቡ ሴቶች ልጆች የሚወልዱባቸው አንዳንድ ሁኔታዎች
እንዳሉ እርግጥ ነው፡፡ ነገር ግን ያ አንዲት ድንግል ልጅ ከመውለድዋ የተለየ ነው፡፡
ምክንያቱም ያላገባች ሴት ከወንድ ጋር መገናኘት ትችላለችና፡፡
በምድር ላይ ከወንድ ጋር ግንኙነት ሳይኖራት ልጅ የወለደች ድንግል
የለችም፡፡ ‹‹አርቴፊሸል የዘር ፈሻሽ ቢሰጣት ይህ ሊሆን አይችልምን?›› ትሉ
ይሆናል፡፡ ሴት ማህጸን ያላት ወንድ በሌላ አነጋገር ማህጸነ ወንድ ናት፡፡ ስለዚህ
በእንግሊዝኛው ዉማን ተብላ ተጠርታለች፡፡ ማህጸን ያላት ሴት ልጀ ትወልዳለች፡፡
ወንድ ግን ሕጻን ለመውለድ ሴት ታስፈልገዋለች፡፡ ምክንያቱም ሰው ሕጻን
የሚፈጠርበትን የዘር ፍሬ ማህጸን ውስጥ መርጨት የሚችለው ወንድ ብቻ እንደሆነ
ያውቃል፡፡ ማርያምም ማህጸን የነበራት ሴት ነበረች፡፡ ነገር ግን ወንድ አልነበረም፡፡
ማርያም በመንፈስ ቅዱስ ብቻ ጸነሰች፡፡ ይህ ኢየሱስ ከመወለዱ ከ700 ዓመታት
በፊት የተተነበየ ነበር፡፡ ‹‹እነሆ ድንግል ትጸንሳለች፤ ወንድ ልጅንም ትወልዳለች፡፡
ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች፡፡›› መልአኩ ገብርኤል ማርያም ኢየሱስን
እንደምትጸንስ ከእግዚአብሄር የተላከውን የተለየ መልዕክት አስተላለፈ፡፡
መልአኩ እንዲህ አለ፡- ‹‹ብሩክ ሴት የእግዚአብሄር ጸጋ ከአንቺ ጋር ይሆናል፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


28 እኛን ለማዳን የመጣውን ጌታችንን ኢየሱስን እናመስግነው

ትልቅ ሰውም ትጸንሻለሽ፡፡›› ያን ጊዜ ማርያም፡- ‹‹ምንም ወንድ አላውቅም፤ እንዴት


ልጅ ሊኖረኝ ይችላል?›› ብላ ጠየቀች፡፡
‹‹ዘመድሽ ኤልሳቤጥ እርስዋ ደግሞ በእርጅናዋ ወንድ ልጅ ጸንሳለች፡፡››
የዘካርያስ ሚስት አልሳቤጥ በእርጅናዋ ወንድ ልጅ መጸነስዋ ወይም ድንግል ወንድ
ልጅ መጸነስዋ የተከናወነው በእግዚአብሄር የተለየ ችሮታ በኩል በትንቢቱ ፍጻሜ
መሰረት ነው፡፡
ከዚያም ማርያም ‹‹እነሆኝ የጌታ ባርያ እንደ ቃልህ ይሁንልኝ›› በማለት
መልአኩ ያመጣውን መልዕክት ተቀበለች፡፡ ሕጻኑም በማህጸንዋ ውስጥ አደገ፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ ይህ እውነት እንጂ ውሸት ስላልሆነ ይህንን የሚያምኑ
ብጹዓን ናቸው፡፡ እኛ በክርስቶስ የሆንን አንድያ ልጁን ስለሰጠን እንደሚገባው
አላመሰገንነውም፡፡
ነገር ግን ይህንን እውነት ለማያምኑ ሰዎች የገና በዓል የቤተክርስቲያንን በጀት
ለመሙላት የገና በዓል አሥራት ከሚከፈልበት ቀን ውጭ ሌላ ምንም ነገር
አይደለም፡፡ በገና በዓል አስመስሎ ‹‹ለገና በዓል የሚሆን ልዩ ስጦታ›› ተብሎ በመቶ
ሺህዎች የሚቆጠር ብር መሰብሰብ ይቻላል፡፡ ብዙ ሰዎች የተለየ ስጦታ የሰጡ ሰዎች
ተብለው ስማቸው ተወድሶዋል፡፡ እግዚአብሄር ግን በዚህ አይደሰትም፡፡
አምልኮዋችን ለማስመሰል ተብሎ የሚደረግ ጉባኤ ሳይሆን የኢየሱስን ልደት
በእውነት ለማክበርና እግዚአብሄርን ለማመስገን የተደረገ አምልኮ በመሆኑ አመስጋኝ
መሆን ይገባናል፡፡
ጌታ ከጥፋትና ከሐጢያት እኛን ለማዳን በመምጣቱና ከሐጢያቶቻችን ሁሉ
ስላዳነን እናመሰግነዋለን፡፡ በዓመቱ ውስጥ ከምናሳልፋቸው ቀኖች ሁሉ የገና በዓል
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ውስጥ ያለውን እጅግ የተባረከ የምስራች ለመቀበል
የምናስበው ቀን ነው፡፡ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በልባችን፣ ደህንነትንም
በጌታ ውስጥ ሆነን ከልባችን በማመን አመስጋኞች ልንሆን ይገባናል፡፡ እያንዳንዱን
ነገር በጌታ ውስጥ ባለ እምነት በማመንና በጌታ ውስጥ ባሉ ዓይኖች በማየት
መፍረድ ይኖርብናል፡፡ በቀጣዩ ዓመትም ደግሞ በእምነት መከተል ይኖርብናል፡፡
ሁላችሁም ጌታን ታመሰግናላችሁን? ጌታችን በእርግጥም የሚገርም ጸጋ
ሰጥቶናል፡፡ አሁን ጌታ ከእኛ ጋር ነው፡፡ እርሱን ማመስገን መጀመር ባለመቻላችንም
በጣም አመስጋኞች ነን፡፡ ለጌታችን ክብርን እንሰጣለን፡፡ 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በመንፈስ ቅዱስ የተጸነሰው
ኢየሱስ
‹‹ ማቴዎስ 1፡18-25 ››
‹‹የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት እንዲህ ነበረ፡፡ እናቱ ማርያም ለዮሴፍ
በታጨች ጊዜ ሳይገናኙ በመንፈስ ቅዱስ ጸንሳ ተገኘች፡፡ እጮኛዋ ዮሴፍም ጻድቅ
ሆኖ ሊገልጣት ስላልወደደ በስውር ሊተዋት አሰበ፡፡ እርሱ ግን ይህን ሲያስብ እነሆ
መልአክ በሕልም ታየው፡፡ እንዲህም አለ፡- የዳዊት ልጅ ዮሴፍ ሆይ ከእርስዋ
የተጸነሰው ከመንፈስ ቅዱስ ነውና እጮኛህን ማርያምን ለመውሰድ አትፍራ፡፡
ልጅም ትወልዳለች፤ እርሱም ሕዝቡን ከሐጢአታቸው ያድናቸዋልና ስሙን ኢየሱስ
ትለዋለህ፡፡ በነቢይም ከጌታ ዘንድ እነሆ ድንግል ትጸንሳለች፤ ልጅም ትወልዳለች፤
ስሙንም አማኑኤል ይሉታል የተባለው ይፈጸም ዘንድ ይህ ሁሉ ሆኖአል፡፡
ትርጓሜውም እግዚአብሄር ከእኛ ጋር የሚል ነው፡፡ ዮሴፍም ከእንቅልፉ ነቅቶ የጌታ
መልአክ እንዳዘዘው አደረገ፡፡ እጮኛውን ማርያምንም ወሰደ፡፡ የበኩር ልጅዋንም
እስክትወልድ ድረስ አላወቃትም፡፡ ስሙንም ኢየሱስ አለው፡፡››

ማቴዎስ ምዕራፍ 1 የኢየሱስን ልደት በዝርዝር ያብራራል፡፡ በሰውኛ ተጠየቅ


ፈጸሞ ከወንድ ጋር ያልነበረች ድንግል ልጅ ሊኖራት አይችልም፡፡ ዕርግዝና ሊመጣ
የሚችለው በአንድ ወንድና በአንዲት ሴት መካከል የግብረ ሥጋ ግንኙነት ሲደረግ
ብቻ ነው፡፡ ስለዚህ በዘመናት ሁሉ ታሪክ ውስጥ የዚህ ዓይነቱ ያልተለመደ ውልደት
ተረት ሆኖ የሚታይ ብቻ ነው፡፡ ሆኖም ይህ በእግዚአብሄር ዘንድ ተችሎ ነበር፡፡
ኢየሱስ የተወለደበትን ምክንያት በጥንቃቄ ከመረመርን ይህንን መረዳት
እንችላለን፡፡ በማንነቱ አምላክ የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ በድንግል ማርያም በኩል
የሰው መልክ ይዞ የተወለደው ሕዝቡን ከሐጢያቶቻቸው ሁሉ ለማዳን ነው፡፡ በሌላ
አነጋገር ሐጢያተኞችን ከሐጢያቶቻቸው ለማዳን እርሱ ራሱ አዳኝ ሆኖ መምጣቱ
ነበረበት፡፡ ሐጢያተኞችን ለማዳን ማስተሰርያ የሚሆን ሐጢያት አልባ ሰው
አስፈለገ፡፡ (1ኛ ዮሐንስ 2፡2) ያም ራሱ አምላክ የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ ነበር፡፡
ጋብቻ ለመፈጸም ቃል የገባች ድንግል ሴት ከጋብቻ በፊት ልጅ ብትወልድ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


30 በመንፈስ ቅዱስ የተጸነሰው ኢየሱስ

ድርጊቱ በማህበረሰቡ ዘንድ ያልተገባ ባህርይ እንደሆነ ተቆጥሮ ወቀሳን የሚያመጣ


ነበር፡፡ ይህ በዚያን ዘመን በአይሁዶች መካከል ሞት የሚገባው ሐጢያት ሊሆን
ይችል ነበር፡፡ የእስራኤል ሕግ ምንዝርናን የፈጸመ ማንኛውም ሰው እንዲወገር
ያዛል፡፡ ከላይ በተጠቀሰው በዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት መሰረት ማርያምና
ዮሴፍ ለማጋባት ቃል ተገባብተው ነበር፡፡ ዮሴፍና ማርያም እግዚአብሄርን የሚፈሩ
ነበሩ፡፡ ስለዚህ ባጋጠማቸው አስገራሚ ገጠመኝ እግዚአብሄርን በሚፈራ እምነት
የእግዚአብሄር ዕቅድ መከተልን ተማሩ፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ ይህንን ታሪካዊ ሁነት በኢሳይያስ 7፡14 ላይ በግልጽ
መዝግቦታል፡- ‹‹ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል፤ እነሆ ድንግል ትጸንሳለች
ወንድ ልጅም ተወልዳለች፡፡ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች፡፡›› እንደገናም
ኢሳይያስ 9፡6 እንዲህ ይላል፡- ‹‹ሕጻን ተወልዶልናልና ወንድ ልጅም ተሰጥቶናል፡፡
አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል፡፡ ስሙም ድንቅ፣ መካር፣ ሃያል አምላክ፣
የዘላለም አባት፣ የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል፡፡›› ይህም ተፈጽሞዋል፡፡
በሚክያስ 5፡2 ላይም እንዲህ ተመዝግቦዋል፡- ‹‹አንቺም ቤተልሔም ኤፍራታ
ሆይ አንቺ በይሁዳ አእላፋት መካከል ትሆኚ ዘንድ ታናሽ ነሽ፤ ከአንቺ ግን አወጣጡ
ከቀድሞ ጀምሮ ከዘላለም የሆነ በእስራኤልም ላይ ገዥ የሚሆን ይወጣልኛል፡፡›› ይህ
ምንባብ የኢየሱስን ውልደት በግልጽና በተጨባጭ ተንብዮአል፡፡
የሚክያስና የኢሳይያስ መጽሐፎች ነቢያቶቹ ሚክያስና ኢሳይያስ
የእግዚአብሄር ቃሎች በእነርሱ ላይ በመጡ ጊዜ በመንፈስ ቅዱስ ተመርተው
የመዘገቡዋቸው ትንቢቶች ናቸው፡፡ እነርሱ በእግዚአብሄር ትንቢት አማካይነት
ከእነርሱ ዘመን በኋላ 700 ዓመታቶች ቆይቶ ስለሚወለደው የኢየሱስ ክርስቶስ
ልደት አውቀው መዘገቡት፡፡
ከእነዚህ ምንባቦች በተጨማሪም የኢየሱስን ልደት በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ
የሚተነብዩ ብዙ ስፍራዎች በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አሉ፡፡ ይህ በእርግጥም
አስገራሚ ነው፡፡ የኢየሱስ ውልደት በራሱ በእግዚአብሄር የታቀደና የተተገበረ
ባይሆን ኖሮ አዳጋች ምስጢር ነበረ፡፡ ይህም እግዚአብሄር አብ የኢየሱስን ውልደት
ከዘላለም ጀምሮ ማለትም ምድር የምትባል ነገር ከመኖርዋ በፊት ከመጀመሪያው
እንዳቀደው ያረጋግጣል፡፡ (ምሳሌ 8፡23)
መጽሐፍ ቅዱስ በ39 የብሉይ ኪዳን መጽሐፎችና በ27 የአዲስ ኪዳን
መጽሐፎች በጠቅላላው በ66 መጽሐፎች የተዋቀረ ነው፡፡ ብሉይ ኪዳን በሕግ
መጽሐፎችና በትንቢት መጽሐፎች የተዋቀረ ሲሆን አዲስ ኪዳን በወንጌላት፣
በመልዕክቶችና በራዕይ የተዋቀረ ነው፡፡ ብሉይ ኪዳን በአብዛኛው የተጻፈው

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በመንፈስ ቅዱስ የተጸነሰው ኢየሱስ 31

በዕብራይስጥና በአራማይክ ሲሆን አዲስ ኪዳን የተጻፈው በግሪክ ነው፡፡


የዕብራይስጥ ቋንቋ ጉልበበቱ ግልጽ የሆነው ፍቺው ሲሆን የግሪክ ቋንቋ ብርታቱ
ደግሞ ስፋት ያለው የቃላት አጠቃቀሙ ነው፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ በብዙ ምዕተ ዘመናት ውስጥ በ1,600 ዓመታቶች በብዙ
የተለያዩ ስፍራዎች በሚኖሩ አርባ ሰዎች የተጻፈ ነው፡፡ ከዚህ የተነሳ
የተጣምሮአዊነቱ ተዓማኒነት ጠቅለል ያለ ምልክታ ነው፡፡ ነገር ግን ይህ በማንም
ሰው ዕውቀት የተጻፈ ሳይሆን በመንፈስ ቅዱስ ምሪት የተጻፈ ነበር፡፡ ስለዚህ ስለ
ኢየሱስ ውልደት የሚናገሩት ትንቢቶች በሙሉ በታሪክ ውስጥ ከሆኑት ሁነቶችና
እውነታዎች ጋር የተጣጣሙ ናቸው፡፡
2ኛ ጢሞቴዎስ 3፡15-17 እንዲህ ተጽፎዋል፡- ‹‹ከሕጻንነትህም ጀምረህ
ክርስቶስ ኢየሱስን በማመን መዳን የሚገኝበትን ጥበብ ሊሰጡህ የሚችሉትን
ቅዱሳት መጽሐፍትን አውቀሃል፡፡ የእግዚአብሄር ሰው ፍጹምና ለበጎ ሥራ ሁሉ
የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ የእግዚአብሄር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ ለትምህርትና
ለተግሳጽ ልብንም ለማቅናት በጽድቅም ላለው ምክር ደግሞ ይጠቅማል፡፡›› ይህ
ምንባብ መጽሐፍ ቅዱስ ተዓማኒና ደራሲውም ራሱ እግዚአብሄር እንደሆነ በግልጽ
ያረጋግጣል፡፡ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ውልደትና ሥራዎች የሚናገሩት ትንቢቶችና
ዘገባዎች የሚገኙት በኢሳይያስ መጽሐፍ ውስጥ ብቻ ሳይሆን በ66ቱም የብሉይና
የአዲስ ኪዳናት መጽሐፎች ውስጥ መሆኑን ማወቅ ይኖርብናል፡፡
ሉቃስ 24፡27 ይህንን መዝግቦዋል፡- ‹‹ከሙሴና ከነቢያትም ሁሉ ጀምሮ ስለ
እርሱ በመጽሐፍት ሁሉ የተጻፈውን ተረጎመላቸው፡፡›› በቁጥር 44 ላይም እንዲህ
ተመዝግቦዋል፡- ‹‹እርሱም፡- ከእናንተ ጋር ሳለሁ በሙሴ ሕግና በነቢያት
በመዝሙራትም ስለ እኔ የተጻፈው ሁሉ ይፈጸም ዘንድ ይገባል ብዬ የነገርኋችሁ
ቃሌ ይህ ነው አላቸው፡፡›› እነዚህ ምንባቦች ኢየሱስ ክርስቶስ መጽሐፍ ቅዱስ
የሚናገርለት ዋናው ገጸ ባህርይ መሆኑን ግልጽ ያደርጋሉ፡፡
በዘመናት ውስጥ ትንቢት የተነገረለትና የተመሰከረለት ኢየሱስ ሰው ሆኖ
በድንግል ማርያም በኩል የተወለደበት ምክንያቱ ምንድነው? ‹‹ኢየሱስ›› በሚለው
ስም ውስጥ የትውልዱ ዓላማና ትርጉም በግልጽ ተንጸባርቋል፡፡ ለነገሮች ስም
በምንሰጥበት ጊዜ በስሙ ውስጥ ትርጉምን እናስቀምጣለን፡፡ ኢየሱስም ‹‹ሕዝቡን
ከሐጢያታቸው የሚያድን›› የሚል ፍቺ አለው፡፡ እርሱ ከስሞች ሁሉ ኢየሱስ የሚል
ስም የተሰጠው የመሆኑ እውነታ የውልደቱን ዓላማ የሚያሳይ እርግጠኛ ምልክት
ነው፡፡
ሁሉን ቻዩ ፈጣሪ ዝቅ ብሎ በሰው መልክ ወደዚህ ዓለም መጣ፡፡ ይህም ለእኛ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


32 በመንፈስ ቅዱስ የተጸነሰው ኢየሱስ

ያለውን አስገራሚ ጸጋ ያሳየናል፡፡ ኢየሱስ ሰው ሆኖ የመጣው አብዝቶ ስለወደደን


ነው፡፡
ዮሐንስ 3፡16 እንዲህ ይላል፡- ‹‹በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት
እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሄር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን
እንዲሁ ወዶአልና፡፡›› ይህ ምንባብ የሚነግረን በኢየሱስ የሚያምን ማንም ሰው
ሰማይ መግባት እንደሚችል ነው፡፡
በዚህ ዓለም ላይ የገዛ ራሱን አንድያ ልጅ ለወንጀለኛ ብሎ መስዋዕት
የሚያደርግ ሰው የለም፡፡ ይህ በሰዎች ዘንድ የታወቀ ሆኖ ሳለ ፈጣሪ እንደ ትል
ለሚመስሉ ሰዎች የሰው ሥጋ ለብሶ የመወለዱ እውነታ ቅዱስ ሥላሴ አምላክ ምን
ያህል ይህንን ዓለም እንደወደደው ይነግሩናል፡፡ ስለዚህ ሰው የፈጣሪን ወሰን
የሌለው ፍቅር የማይቀበል ከሆነ በዚህ ግትርነቱ ኩነኔ ይገባዋል፡፡
ዮሐንስ 8፡24 እንዲህ ይላል፡- ‹‹እንግዲህ በሐጢአታችሁ ትሞታላችሁ
አልኋችሁ፡፡ እኔ እንደሆንሁ ባታምኑ በሐጢአታችሁ ትሞታላችሁና፡፡››
እዚህ ላይ ‹‹እኔ እንደሆንሁ ባታምኑ›› የሚለው ምንባብ ምን ማለት ነው? ይህ
ማለት ‹‹እግዚአብሄር አንዱንና ብቸኛውን ልጁን እንደላከና ያም አንዱና ብቸኛው
ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ መሆኑን ባታምኑ›› ማለት ነው፡፡ ኢየሱስ ወደዚህ ዓለም
የመጣበት ምክንያት በማቴዎስ ምዕራፍ 1 ላይ እንደተመዘገበው ሐጢያተኞችን
ከሐጢያቶቻቸው ሁሉ ለማዳን ነው፡፡
የብሉይና የአዲስ ኪዳን ሥራ የመንፈስ ቅዱስ ሥራ ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስ
ተጨባጭና ሕያው ነው፡፡ ኢየሱስ የዓለምን ሐጢያቶች ለመውሰድ ወደዚህ ዓለም
መምጣቱ፣ በመስቀል ላይ መሰቀሉና በሦስተኛው ቀን ከሙታን መነሳቱ ተጨባጭ
እንደሆነ ሁሉ መንፈስ ቅዱስም ልክ እንደ ኢየሱስ ሌላ አካል እውነተኛ የቅዱስ
አምላክ መንፈስ ነው፡፡ የእግዚአብሄር መንፈስ የሆነው መንፈስ ቅዱስ ራሱ
እንደዚሁ አምላክ ነው፡፡
ቀደም ብዬ የመጽሐፍ ቅዱስ ሥራ የመንፈስ ቅዱስ ሥራ እንደሆነ
ተናግሬያለሁ፡፡ ዘፍጥረት 1፡2 እንዲህ ይላል፡- ‹‹ምድርም ባዶ ነበረች፤ አንዳችም
አልነበረባትም፡፡ ጨለማም በጥልቁ ላይ ነበረ፡፡ የእግዚአብሄርም መንፈስ በውሆች
ላይ ሰፍፎ ነበር፡፡›› በዚህ ምንባብ ላይ የእግዚአብሄር መንፈስ መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡
መንፈስ ቅዱስ እግዚአብሄር አብና ኢየሱስ በተጨባጭ እንዳሉ ሁሉ አለ፡፡ መንፈስ
ቅዱስ ዛሬ ባነበብነው የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ውስጥም ተጠቅሶዋል፡፡ ‹‹እናቱ
ማርያምም ለዮሴፍ በታጨች ጊዜ ሳይገናኙ በመንፈስ ቅዱስ ጸንሳ ተገኘች፡፡›› ይህ
ምንባብ ኢየሱስ ከድንግል ማርያም በመንፈስ ቅዱስ እንደተጸነሰ ይነግረናል፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በመንፈስ ቅዱስ የተጸነሰው ኢየሱስ 33

ስለዚህ እግዚአብሄር አብ፣ ኢየሱስ ወልድና መንፈስ ቅዱስ በተጨባጭ ለእኛ


አንድ አምላክ ናቸው፡፡ ኢየሱስ አዳኛችን ሆኖ ወደዚህ ዓለም ይመጣ ዘንድ ኢየሱስ
አዳኝ ይሆን ዘንድ ያደረጉት እግዚአብሄር አብና መንፈስ ቅዱስ መተባበር
ነበረባቸው፡፡ ነገር ግን አንዳንድ ሰዎች ይህንን ክፍል ለማመን ስለሚቸገሩ ይህ
የማይዋጥ ነው በማለት ይህንን የሚያብራራ መረጃ ይፈልጋሉ፡፡ እኔም ለእነዚህ
ሰዎች እግዚአብሄር አብ፣ ኢየሱስ ወልድና መንፈስ ቅዱስ በሰሩዋቸው ሥራዎች
ውስጥ የሥላሴን ሥራ በዝርዝር ከመጽሐፍ ቅዱስ ልሰጣቸው እችላለሁ፡፡ እናንተ
በተጨባጭ በሕይወት እንደምትኖሩ ሁሉ ኢየሱስ፣ መንፈስ ቅዱስና እግዚአብሄር
አብም በተጨባጭ ይኖራሉ፡፡ ሁላችንም ሰዎች እንደሆንን ነገር ግን እያንዳንዱ
ግለሰብ ከሌሎች የተለየና የማይመሳሰል እንደሆነ ሁሉ በሥላሴ ውስጥ ያሉትም
የእያንዳንዳቸው ሚና የተለያየ ነው፡፡ ነገር ግን እነርሱ አንድ አምላክ ናቸው፡፡
መንፈስ ቅዱስ የመለኮት መንፈስ እንደሆነ እነግራችኋለሁ፡፡
የመለኮት መንፈስ የሆነው መንፈስ ቅዱስ አካል አለው፡፡ የራሱ ነጻ ባህርይም
አለው፡፡ የሰው ዘር አዳኝ የሆነው ኢየሱስ በማርያም በኩል ወደዚህ ዓለም የመጣው
በሥላሴ አምላክ ሥራ ነበር፡፡ ስለዚህ በደህንነት ሥራ ውስጥ አብ፣ ወልድና መንፈስ
ቅዱስ አብረው እንደሚሰሩ እናውቃለን፡፡ ኢየሱስ ወደ ሰማይ ከማረጉ በፊት ደቀ
መዛሙርቱን፡- ‹‹እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ፣ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ
ስም እያጠመቃችኋቸው…ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው›› (ማቴዎስ 28፡19) ብሎ
ያዘዛቸው ለዚህ ነው፡፡ ዩኒቨርስን የፈጠረው የእግዚአብሄር ሥራና እግዚአብሄር
የሰራው ሥራ በሙሉ በእግዚአብሄር አብ ብቻ ወይም በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ
ብቻ የተሰራ ሳይሆን እግዚአብሄር አብ፣ ኢየሱስ ወልድና መንፈስ ቅዱስ ስለ
ሥራዎቹ ሁሉ አንድ ላይ ተማክረው አብረው የሰሩት ሥራ ነው፡፡
እኛ ከሐጢያቶቻችንን የዳንነው አዳኙ ለእኛ የሰራውን በማመናችን ነው፡፡
ኢየሱስ እውነተኛ አካል እንደሆነ ሁሉ መንፈስ ቅዱስም ሌላው የመለኮት አምላክ
ባህርይ የሆነ እውነተኛ አካል ነው፡፡ ስለዚህ በዩኒቨርስ ውስጥ የተሰሩት ሥራዎች
በሙሉ የሥላሴ አምላክ ሥራ ናቸው፡፡ መንፈስ ቅዱስ በውሃውና በመንፈሱ
ወንገጌል በምናምን በእኛ ልብ ውስጥ ከማደሩም በላይ እውነትን እየነገረ
ያስተምረናል፡፡ በሕይወት መንገድም ይመራናል፡፡
ዮሐንስ ምዕራፍ 14ን እንመልከት፡፡ ዮሐንስ 14፡25-26 እንዲህ ይላል፡-
‹‹ከእናንተ ዘንድ ስኖር ይህን ነግሬአችኋለሁ፡፡ አብ በስሜ የሚልከው ግን መንፈስ
ቅዱስ የሆነው አጽናኝ እርሱ ሁሉን ያስተምራችኋል፡፡ እኔም የነገርኋችሁን ሁሉ
ያሳስባችኋል፡፡››

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


34 በመንፈስ ቅዱስ የተጸነሰው ኢየሱስ

መጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ቅዱስን አጽናኝ ብሎ የሚጠራው ለዚህ ነው፡፡ አብ


የሚልከው መንፈስ ቅዱስ ‹‹እርሱ ሁሉን ያስተምራችኋል፤ እኔም የነገርኋችሁን
ያሳስባችኋል፡፡›› አጽናኙ መንፈስ ቅዱስ እውነትን ያስተምረናል፡፡ እግዚአብሄር አብ
ምን እንደሚያስደስተውና ፈቃዱም ምን እንደሆነ ስለመሳሰሉት ነገሮች ሁሉ
ያስተምረናል፡፡ ጌታ ያስተማረውን የሚያስታውሰንም እንደዚሁ መንፈስ ቅዱስ
ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ‹‹ከእርሱ የተቀበላችሁት ቅባት በእናንተ ዘንድ ይኖራልና
ማንም ሊያስተምራችሁ አያስፈልግም›› (1ኛ ዮሐንስ 2፡27) ብሎ የሚነግረን ለዚህ
ነው፡፡ ይህ ማለት መንፈስ ቅዱስ በልባችን ውስጥ ስለሚኖር ስለ እግዚአብሄር
ያስተምረናል ማለት ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስ አጽናኝ የሆነው ለዚህ ነው፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ ኢየሱስ ክርስቶስንና መንፈስ ቅዱስን በስፋት ያብራራቸዋል፡፡
እንደ አራቱ ወንጌላት፣ የሐዋርያት ሥራ፣ የጳውሎስ መልዕክቶች፣ ያዕቆብ፣ ጴጥሮስና
ዮሐንስ የጻፉዋቸው መልዕክቶች እንደዚሁም የዮሐንስ ራዕይ መጽሐፍ ያሉ የአዲስ
ኪዳን መጽሐፎች በሙሉ የኢየሱስ ትምህርቶች ናቸው፡፡ በአራቱ ወንጌላት ዘመን
ኢየሱስ ራሱ አስተማረን፡፡ የወንጌል ዘመን ሲያልፍ ኢየሱስ ወደ ሰማይ አረገ፡፡
በበዓለ ሃምሳ ቀንም መንፈስ ቅዱስን እንደሚልክ ተስፋ ሰጠ፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ
የመንፈስ ቅዱስ ዘመን ሆንዋል፡፡
ይህ የመንፈስ ቅዱስ ዘመን ነው፡፡ እናንተና እኔ የምንኖርበት ይህ ዘመን
መንፈስ ቅዱስ የሚሰራበት ዘመን ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስም በውስጣችን አድሮ
ወንጌልን እንድናሰራጭ ያደርገናል፡፡ እውነትን እንድናስተውል ያግዘናል፡፡
ሐጢያቶቻችንን ይወቅሳል፡፡ የእግዚአብሄርን ፈቃድ በሚገባ እንድንከተል
ይመራናል፡፡ የሚጎድለንንም ይሞላልናል፡፡ ስህተት ምን እንደሆነ እንድናውቅም
ያግዘናል፤ ቃሉንም ያስታውሰናል፡፡
የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል የመንፈስ ቅዱስ ወንጌል ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስ
ሥራውን የሚሰራው ለምንድነው? ይህንን የሚሰራው ይህ የመንፈስ ቅዱስ ዘመን
ስለሆነ ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ዓለም ላይ ተወለደ፤ በጥምቀቱም
ሐጢያቶቻችንን ወሰደ፤ ፍርድን ተቀበለ፤ ወደ ሰማይ አረገ፡፡ አንድ ቀንም ተመልሶ
ይመጣል፡፡ ኢየሱስ እስከሚመለስ ድረስ መንፈስ ቅዱስ ከተጻፈው ቃል ጋር አብሮ
ይሰራል፡፡
መንፈስ ቅዱስ በእግዚአብሄር ቃል አማካይነት የሚሰራ አምላክ ነው፡፡
ማርያም የእግዚአብሄርን መልዕክት በተቀበለች ጊዜ መንፈስ ቅዱስ ሕጻኑን ኢየሱስን
እንድታገኝ ሰራ፡፡ መንፈስ ቅዱስ ሕጻኑ ኢየሱስ እንዲወለድ ያስቻለውን አቅም
የሰጠው የእግዚአብሄርን ቃሎች የሰማችው ማርያም ‹‹እነሆኝ የጌታ ባርያ እንደ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በመንፈስ ቅዱስ የተጸነሰው ኢየሱስ 35

ቃልህ ይሁንልኝ›› በማለት የእግዚአብሄርን መልዕክት በመቀበልዋ ነው፡፡ ስለዚህ


መንፈስ ቅዱስ በተተነበየው ውስጥ ይሰራል፡፡
ማቴዎስ 1፡22-23 እንዲህ ይላል፡- ‹‹በነቢይም ከጌታ ዘንድ እነሆ ድንግል
ትጸንሳለች፤ ልጀም ትወልዳለች፤ ስሙንም አማኑኤል ይሉታል የተባለው ይፈጸም
ዘንድ ይህ ሁሉ ሆኖአል፡፡ ትርጓሜውም እግዚአብሄር ከእኛ ጋር የሚል ነው፡፡››
መንፈስ ቅዱስ በተጻፈው ቃሉ ለሚያምኑ ሰዎች ይሰራል፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ በሉቃስ ውስጥ ለኤልሳቤጥ የተገለጠላት መልአኩ ገብርኤል
ለማርያምም ተገልጦ፡- ‹‹አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ፡፡ የምትወልጂውም
ልጅ ታላቅ ይሆናል!›› ብሎ እንደነገራት ይነግረናል፡፡ ታላቁ ልጅ አዳኙ ነው፡፡ ያን
ጊዜ ማርያም ደንግጣ ‹‹ወንድ ስለማላውቅ ይህ እንዴት ይሆናል?›› በማለት
ጠየቀችው፡፡ ገብርኤልም፡- ‹‹እነሆ ዘመድሽ ኤልሳቤጥ እርስዋ ደግሞ በእርጅናዋ
ወንድ ልጅ ጸንሳለች፡፡ ለእርስዋም መካን ትባል ለነበረችው ይህ ስድስተኛ ወር ነው››
ብሎ ነገራት፡፡ ያን ጊዜ ማርያም መልአኩ የሰጣትን የእግዚአብሄር ቃሎች ተቀብላ፡-
‹‹እነሆኝ የጌታ ባርያ እንደ ቃልህ ይሁንልኝ›› አለች፡፡ መልአኩም ከእርስዋ ተለየ፡፡
ኢየሱስም ከእርስዋ ተወለደ፡፡ ይህ መንፈስ ቅዱስ እንዴት እንደሚሰራ የሚያሳይ
ጥሩ ምሳሌ ነው፡፡
በዚህ ዘመን መንፈስ ቅዱስ አሁንም በልባችን ውስጥ እየሰራ በዓለም ላይ
ይገኛል፡፡ መንፈስ ቅዱስ የሚሰራው እንዴት ነው? በተጻፈው የእግዚአብሄር ቃል
ስናምን መንፈስ ቅዱስ በእግዚአብሄር ቃሎች አማካይነት ይሰራል፡፡ ኢየሱስን
ላልተቀበሉት ወንጌልን ስናሰራጭ በእርሱ ውስጥ የሚሰራው መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡
እናንተና እኔ ወንጌልንና የእግዚአብሄርን ቃል ስናሰራጭ በውስጣችን ያለው መንፈስ
ቅዱስ ገናም ዳግመኛ ባልተወለዱት ሰዎች ውስጥ ይሰራል፡፡ ወንጌል ሲሰራጭ
መንፈስ ቅዱስ ወንጌልን እንዲያስተውሉ በመርዳት በውስጣቸው ይሰራል፡፡ ይህንን
ሲሰሙና ሲያስቡት መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሄር ቃል ምን እንደሆነ
ያስተምራቸዋል፡፡ ወንጌልን እንዲያስተውሉትም ለመርዳት በውስጣቸው ሆኖ
ይሰራል፡፡ ከዚህ የተነሳ ሰዎች የሐጢያት ስርየትን ያገኛሉ፡፡ እግዚአብሄር በቃሎቹ
አማካይነት መረዳትን ስለሚሰጠን መንፈስ ቅዱስ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ
በተጻፈው መሰረት ይሰራል፡፡
እግዚአብሄር ደህንነታችንን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ያቀደው ከፍጥረት
በፊት ነው፡፡ ወልድ የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስም ወደዚህ ዓለም መጥቶ በውሃ
ጥምቀቱና በመስቀል ላይ ባፈሰሰው ደሙ አማካይነት ደህንነታችንን ፈጸመ፡፡
መንፈስ ቅዱስም እግዚአብሄር አብ ያቀደውንና ወልድ የፈጸመውን ደህንነት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


36 በመንፈስ ቅዱስ የተጸነሰው ኢየሱስ

አረጋገጠልን፡፡ መንፈስ ቅዱስ አጽናኝ በመሆን ‹‹በትክክል እያመናችሁ ነው፤


እንደዚያ እመኑ፡፡ ያ ትክክል ነው›› እያለ ጠንካራ እምነት እንዲኖረን ያግዘናል፡፡
ስለዚህ መንፈስ ቅዱስ ለእያንዳንዳችን አጽናኝና አስተማሪ ነው፡፡ የመንፈስ
ቅዱስ ዘመን የአዲስ ኪዳን ዘመን የሆነው ለዚህ ነው፡፡ የአዲስ ኪዳን ዘመን
የመንፈስ ቅዱስ ዘመን ነው፡፡ ስለዚህ እየኖርን ያለነው በመንፈስ ቅዱስ ዘመን
እንደሆነ ማወቅ አለብን፡፡
ማርያም እግዚአብሄር የሰጣትን ቃሎች ተቀብላ በመንፈስ ቅዱስ ልጅን
መጸነስዋ እውነት ነው፡፡ በመንፈስ ቅዱስ ሥራም ሕጻኑ ኢየሱስ በዓለም ላይ
ተወለደ፡፡ ይህንን ደህንነት የሰጠንን እግዚአብሄርን እናመሰግነዋለን፡፡ የመንፈስ
ቅዱስ ሥራ መዳን አስችሎናል፡፡
በመንፈስ ቅዱስ መጸነስ ማለት ደህንነታችን ከእግዚአብሄር ነው ማለት ነው፡፡
ይህ በአንድ ታላቅ የሐይማኖት መስራች የተደረገ ነገር አይደለም፡፡ እኛን ልጆቹ
ለማድረግ በእግዚአብሄር አብ፣ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ የተደረገ ነው፡፡
ከሐጢያቶቻችን የዳንነውና የሐጢያቶችን ስርየት የተቀበልነው እንደዚህ ነው፡፡
በመንፈስ ቅዱስ ስራ የዳንነው እውነታ የሆነው ለዚህ ነው፡፡ አመስጋኞች
የምንሆነውም ለዚህ ነው፡፡
በጥቅል አነጋገር ኢየሱስን አሳምረን እናውቀዋለን፤ ነገር ግን ስለ መንፈስ ቅዱስ
ብዙ አናውቅም፡፡ ሆኖም በተጨባጭ በውስጣችን የሚኖረው መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡
ኢየሱስ በመንፈስ ቅዱስ ውስጥ ነው፤ መንፈስ ቅዱስም በኢየሱስ ክርስቶስ ውስጥ
ነው፤ ወልድ በአብ ውስጥ ነው፤ አብም በወልድ ውስጥ ነው እንደተባለ ወደ ሰማይ
ከማረጉ በፊት ሐጢያቶቻችንን ያነጻው ኢየሱስ ነበር፡፡ አሁን ደግሞ በእምነታችን
በውስጣችን የሚኖረው መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ በተጨባጭ ወደዚህ
ዓለም መጣ፡፡ የእናንተንና የእኔን ሐጢያቶች በሙሉ ደመሰሰ፡፡ አሁን በኢየሱስ
ክርስቶስና በእግዚአብሄር ቃል በሚያምነው እምነታችሁ መንፈስ ቅዱስ በልባችሁ
ውስጥ ይኖራል፡፡ እናንተና እኔ በመንፈስ ቅዱስ ቁጥጥር ሥር ነን፡፡
ስለዚህ መንፈስ ቅዱስን በጣም በሚገባ ማወቅ አለብን፡፡ እናንተና እኔ
በውስጣችን የሚኖረውን መንፈስ ቅዱስ የምናሳዝነው ከሆነ እግዚአብሄርም
ያዝናል፡፡ የእርሱን መመሪያዎች በመከተል በእናንተና በእኔ ውስጥ የሚኖረውን
መንፈስ ቅዱስ ስናስደስት ደስተኞች ከመሆናችንም በላይ እግዚአብሄርም
ይደሰታል፡፡ ስለዚህ በልባችን ውስጥ በኢየሱስ ክርስቶስ የሚያምነው እምነታችን
መለወጥ እንዳይገባው በውስጣችሁ የሚኖረውን መንፈስ ቅዱስ ማወቅ
ያስፈልጋችኋል፡፡ መንፈስ ቅዱስን ስናውቅ ከእግዚአብሄር ጋር ተገቢ ግንኙነት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በመንፈስ ቅዱስ የተጸነሰው ኢየሱስ 37

ይኖረናል፡፡ መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን የሚሰራው በእኛ ፋንታም ለእግዚአብሄር


የሚማልደው የእግዚአብሄርን ፈቃድ እንድናውቅ የሚረዳንና በጽድቅ ጎዳናዎች
የሚመራን መንፈስ ቅዱስን ስናውቅ ብቻ ነው፡፡ ነገር ግን መንፈስ ቅዱስን የምናሳዝን
ከሆንን መንፈስ ቅዱስ ያዝናል፡፡ እንዲህም ይላል፡- ‹‹እንግዲህ የምትፈልገውን ሁሉ
አድርግ፤ በራስህ ተወጣው፡፡›› ያን ጊዜ እግዚአብሄር የተወን ያህል ይሰማናል፤
እንደቆሳለን፤ ግራ እንጋባለን፡፡ ከእግዚአብሄርም 9,000 ማይሎች ያህል የራቅን
መስሎ ይሰማናል፡፡ ስለዚህ በውስጣችን የሚኖረውን መንፈስ ቅዱስ በሚገባ ማወቅ
አለብን፡፡ ኢየሱስ በእናንተና በእኔ ውስጥ ባለው የመንፈስ ቅዱስ ሥራ አድኖናል፡፡
መንፈስ ቅዱስ መንገዳችንን ለመምራት አሁንም በውስጣችን ይሰራል፡፡
ይህ ገባችሁ? -- አዎ-- ይህንን የተረዳችሁት የሐጢያት ስርየትን
ስለተቀበላችሁና መንፈስ ቅዱስም አሁን በውስጣችሁ ስለሚኖር ነው፡፡ ያልዳኑና
በልባቸው ውስጥ መንፈስ ቅዱስ የሌላቸው ሰዎች የእግዚአብሄርን ቃል
ስለማያስተውሉ ቃሉ ኢ-ተጠያቂያዊ ነው ይላሉ፡፡ በመንፈስ ቅዱስ ምሪት ከተጻፈው
ከመጽሐፍ ቅዱስ የበለጠ ምንም ትክክለኛ ነገር የለም፡፡ መግቢያው፣ ዋናው አሳብና
ድምዳሜው በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ግልጽ ነው፡፡ ነገር ግን ገና ዳግመኛ
ያልተወለዱ ሰዎች የመጽሐፍ ቅዱስን ተዓማኒነት በፍጹም ማየት አይችሉም፡፡
ስለዚህ ኢየሱስ ‹‹እውር እውርን ሊመራው ይችላልን? ሁለቱስ ገደል ውስጥ
አይወድቁምን?›› (ሉቃስ 6፡39) በማለት እንደ እውራን የቆጠራቸው ለዚህ ነው፡፡
በአንድ ወቅት ከአንድ መጋቢ ጋር ተገናኘሁ፡፡ አንድ ቀን ይህ መጋቢ እንዲህ
አለኝ፡- ‹‹ኢየሱስ ከድንግል ማርያም ሥጋ እንዴት እንደተወለደ በሰውኛ ተጠየቅ
ልታብራራልኝ የምትችል ከሆንህ እኔም በእግዚአብሄር ቃል እንዳለ አምናለሁ፡፡››
ብዙ የሥነ መለኮት ምሁራን የዚህ ዓይነት እምነት ስላላው ይህም መጋቢ ይኸው
ዓይነት እምነት ነበረው፡፡ ወንድ የማታውቀው ድንግል እንዴት ልጅ ማርገዝ
እንደቻለች ማብራራት ብችል በኢየሱስ አምናለሁ በሚለው አባባሉ አዘንሁ፡፡
ስለዚህ ጠየቅሁት፡-
‹‹አንተ መጋቢ ነህን?››
‹‹አዎ እኔ መጋቢ ነኝ፤ በዩኒቨርሲቲም የአንድ ክርስቲያን የተማሪ ድርጅት
ዳይሬክተር ነኝ፡፡››
‹‹ዳይሬክተር? የዳይሬክተር ሚና ምንድነው?››
‹‹ሚናው ተማሪዎች እምነት ሊኖራቸው ይችል ዘንድ ክርስትናን
እንዲያስተውሉ መርዳት ነው፡፡››
‹‹ዳይሬክተር ሆነህ በኢየሱስ ክርስቶስ ውልደት አታምንምን? ኢየሱስ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


38 በመንፈስ ቅዱስ የተጸነሰው ኢየሱስ

በድንግል ማርያም በመንፈስ ቀዱስ እንደተጸነሰ፣ በዚህ ዓለም ላይ እንደተወለደና


ከሐጢያቶቻችን እንዳዳነን አታምንምን?››
‹‹አይ አላምንም፡፡››
‹‹እንግዲያውስ በመጀመሪያ በራስህ ልታፍር ይገባሃል፡፡ ሁለተኛ ለበጎችህ
እረኛ የሆንህ አንተ ራስህን መጋቢ ብለህ መጥራት አትችልም፡፡ አንተ ኑሮን ለመኖር
ብቻ ሙያተኛ የሆንህ መጋቢ ነህ፡፡››
እርሱም አንዲት ዶሮ የማይራቡ እንቁላሎችን ልትወልድ ትችላለች ነገር ግን
ከወንድ ጋር ሳይገናኙ ልጅ ማግኘት የማይቻል ነው› አለ፡፡
እኔም፡- ‹‹አንተ እውነተኛ መጋቢ ሳትሆን ኑሮን ለመግፋት የተቀጠርህ ነህ
ያልሁት ለዚህ ነው፡፡ ይህንን ሳትረዳ ወይም ይህንን ሳታምን ተማሪዎችን እንዴት
ወደ ኢየሱስ መምራት ትችላለህ? እየመራኸው ያለውን የክርስቲያን ተማሪ
ድርጅትህን መልቀቅ አለብህ፡፡ ወደ ኢየሱስ ልትመራቸው አትችልም፡፡
ሕይወታቸውን እያበላሸህ ነው›› አልኩት፡፡
ራሱን መጋቢ ብሎ የሚጠራ ሰው ኢየሱስ በመንፈስ ቅዱስ መወለዱን
አለመረዳቱ የሚያሳዝን ነው፡፡ እውነቱን ለመናገር መንፈስ ቅዱስ በውስጣችሁ
የማይኖር ከሆነ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተጻፈውን የኢየሱስን ውልደት
የምትረዱት እንዴት ነው? በዚህ ዘመን ሰው ሰራሽ ግብዓተ ነፍስ የሚባል ነገር አለ፡፡
ይህም ቢሆን ለጽንሰት የዘር ፈሻሽና እንቁላል ያስፈልገዋል፡፡ ታዲያ ከእነዚህ በአንዱ
ብቻ እንዴት መወለድ ይቻላል? የኢየሱስ ውልደት የተቻለው ይህ የእግዚአብሄር
ሥራ ስለነበር ነው፡፡
ሕጻኑ ኢየሱስ በመንፈስ ቅዱስ ሥራ በድንግል ማርያም በኩል የሚወለድ
የመሆኑ ክስተት ኢየሱስ ከመወለዱ ከ700 ዓመታት በፊት ተተንብዮ ነበር፡፡
በኢሳይያስ ላይ ‹‹እነሆ ድንግል ትጸንሳለች፤ ልጅም ትወልዳለች፤ ስሙንም አማኑኤል
ብላ ትጠራዋለች›› የሚለው ምንባብ ለምን ተጻፈ? እግዚአብሄር ለእኛ ያለውን
አስገራሚውን ዕቅዱን እንድናውቅ ሲፈልግ ብዙውን ጊዜ በሰው ሐይል በማይቻል
አንድ የተለየ ክስተት በኩል ይገልጠዋል፡፡
እስራኤል በጠላቶችዋ የተማረከችበትና በእስራኤል ያሉ ሕዝቦችም በሙሉ
ምርኮኛ ሆነው የተወሰዱበት ወቅት ነበር፡፡ ይህችን አገር መልሶ ከጠላት ማስለቀቅ
የማይቻል ነበር፡፡ ነገር ግን እግዚአብሄር ይህች አገር በ70 ዓመታት ውስጥ
እንደመትመለስ ተስፋ ሰጠ፡፡ ይህንን ያመነ ማንም ሰው አልነበረም፡፡ በእግዚአብሄር
እጅ ግን ተዓምር ሆነ፡፡
ልክ እንደዚሁ በነቢዩ ኢሳይያስ በኩል ‹‹እነሆ ድንግል ትጸንጻለች፤ ልጅም

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በመንፈስ ቅዱስ የተጸነሰው ኢየሱስ 39

ትወልዳለች፤ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች›› የሚለው አስገራሚ ተዓምር


በተጨባጭ ተግባራዊ ሆነ፡፡ ይህ በሰውኛ ተጠየቅ የማይቻል ነው፡፡ እግዚአብሄር
ግን እናንተንና እኔን ለማዳን ብርቱ በሆነው ሐይሉ የሰራው እንዴት ነው? እርሱ
ነቢያቶቹን ትንቢት እንዲናገሩ እንደላካቸው ሁሉ አሁንም መልዕክቶቹን
እንዲሰጡለት አገልጋይ ባሮቹን በመላክ በመልዕክቶቹ የሚያምነውን ማንኛውንም
ሰው ያድናል፡፡ ስለዚህ የእናንተና የእኔ ደህንነት የመንፈስ ቅዱስ ሥራ ነው፡፡
እኛ በሥላሴ አምላክ --እግዚአብሄር አብ፣ ኢየሱስ ወልድና መንፈስ ቅዱስ
ሥራዎች ድነናል፡፡ ስለዚህ አሁንም እንኳን እግዚአብሄር ቃሉን ለሚቀበል
ለማንኛውም ሰው መንፈስ ቅዱስን በመላክ የእግዚአብሄር ልጆች ያደርጋቸዋል፡፡
በዳንን ጊዜ የዳንነው ወይም መንፈስ ቅዱስን የተቀበልነው አንድ ሰው ‹‹ይህንን እሳት
ተቀበሉ›› ወይም ‹‹ይህንን መንፈስ ቅዱስ ተቀበሉ›› ብሎ ስለጮኸ ነውን?
አይደለም፡፡ መንፈስ ቅዱስ ሁልጊዜም በተጻፈው ቃል በኩል ይሰራል፡፡ ቃሉን እኛ
ራሳችን አነበብነው ወይም አንድ ሰው ለእኛ ሰበከልን በቃሉ ካመንን መንፈስ ቅዱስ
ቃሉን እንድናስተውል ሊረዳንና ሊያረጋግጥልን በውስጣችን ይሰራል፡፡ እግዚአብሄር
መንፈስ ቅዱስን በቃሉ ለሚያምኑ ሰዎች ስጦታ አድርጎ የሰጣቸው ለዚህ ነው፡፡
እናንተና እኔ በእርግጥም በመንፈስ ቅዱስ ሥራ አማካይነት አስገራሚ
ደህንነትን ተቀበለናል፡፡ እዚህ ላይ ድንግል ማርያም በቃሉ ላይ ባላት እምነት
ሕጻኑን ኢየሱስን ጸነሰች፡፡ እናንተም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን
ስለዳናችሁ ኢየሱስ ተመሳሳይ በሆነ መርህ እንደ መንፈስ ቅዱስ በውስጣችሁ ሊኖር
መጣ፡፡ በእግዚአብሄር ቃል ብታምኑ የሐጢያታችሁን ስርየት ትቀበላላችሁ፡፡
ከዚያም የእግዚአብሄር ልጅ ትሆናላችሁ፡፡ የእግዚአብሄር ልጅ ስትሆኑ መንፈስ
ቅዱስ በውስጣችሁ ይኖራል፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስ በመንፈስ ቅዱስ የመጣ የእግዚአብሄር ልጅ ነው፡፡
የእግዚአብሄር ልጅ የሱነው ኢየሱስ ሐጢያት አልነበረበትም፡፡ እርሱ በመጽሐፍ
ቅዱስ ትምህርት ውስጥ እንደተጻፈው በዚያው መንገድ በውስጣችን ይሰራል፡፡
ማርያም ከመልአኩ መልዕክትን በተቀበለች ጊዜ ቃል ሥጋ ሆነ፡፡ ሕጻኑ ኢየሱስ ሆኖ
ተወለደ፡፡ ቃሉ የሚሰራው እንደዚህ ነው፡፡ ኢየሱስም አዳኝ የሆነው እንደዚህ
ነው፡፡
‹‹የመንፈስ ቅዱስ ሥራ›› ስንል አንድ ሰው መንፈስ ቅዱስ ለማርያም ተገልጦ
‹‹ከአሁን ጀምሮ በአንቺ ውስጥ እሰራለሁ›› ብሎ በመናገር አንዳች አስማታዊ ነገር
እንደሰራ ያስብ ይሆናል፡፡ ነገሩ የሆነው እንደዚያ አይደለም፡፡ እግዚአብሄር ቃሉን
ሲልክ የእግዚአብሄርን ቃል ከተቀበልነው መንፈስ ቅዱስ ከእግዚአብሄር ቃል ጋር

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


40 በመንፈስ ቅዱስ የተጸነሰው ኢየሱስ

አብሮ በውስጣችን ይሰራል፡፡ ይኸው መርህ በኢየሱስ ውልደትና በእኛ ዳግመኛ


ውልደት ውስጥ ተግባራዊ ሆንዋል፡፡ የሐጢያቶቻችሁን ስርየት ስትቀበሉ የሆነውም
እንደዚሁ ነው፡፡ እኔ ዳግመኛ ስወለድ የተሰራውም ይኸው ነው፡፡ የእግዚአብሄርን
ቃል ስንቀበልና ስናምን ሐጢያቶቻችን በተጨባጭ ይደመሰሳሉ፡፡ መንፈስ ቅዱስም
ይህንን ያረጋግጥልናል፡፡
ኢየሱስና መንፈስ ቅዱስ የሚሰሩት እንደዚህ ነው፡፡ ይህ አስገራሚ
አይደለምን? ማርያም የእግዚአብሄርን ቃሎች ተቀበለች፡፡ ሕፃኑ ኢየሱስም ተወለደ፡፡
እናንተና እኔ በኢየሱስ ጥምቀትና በመስቀሉ ደም አማካይነት የመዳንን ቃል
ስንቀበል ምን ተከሰተ? ነፍሳችሁ ጻድቅ ሆና ዳግመኛ ተወልዳለች ወይስ
አልተወለደችም? ዳግም ተወልዳለች፡፡ በኢየሱስ ውስጥ መንፈስ ቅዱስ ነበረ ወይስ
አልነበረም? ነበረ፡፡ መንፈስ ቅዱስ ከውልደቱ ጀምሮ በኢየሱስ ውስጥ ነበረ፡፡
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ዳግመኛ እንድንወለድ በተደረግነው በእኛ ውስጥ
መንፈስ አለን? አለ፡፡ ተዓምሩ ተመሳሳይ ነው፡፡ ቃሉም ተመሳሳይ ነው፡፡
ኢየሱስ በመንፈስ ቅዱስ ሥራ የመወለዱን ቃል ተረድታችኋልን? --አዎ--
ሥራው ተመሳሳይ ነው፤ ደግሞም አስገራሚ ነው፡፡ ስለዚህ ኢየሱስን በመቀበል
የሐጢያቶቻችንን ስርየት ስንቀበል ይህ የመጨረሻው አይደለም፡፡ በእኛ ውስጥ
በተጨባጭ የሚኖረው መንፈስ ቅዱስ አስተማሪ ሆኖ ያስተምረናል፤ ይመራንማል፡፡
ስለዚህ በእኛ ላይ የሚሰለጥነው፣ የሚያስተምረንና የሚመራን መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡
እንግዲህ ብቻችንን አይደለንም፡፡ እግዚአብሄር መንፈስ ቅዱስ ሁልጊዜም
ከእናንተ ጋር ነው፡፡ እናንተም ከእግዚአብሄር ጋር ናችሁ፡፡ መንፈስ ቅዱስም በችግር
ወይም በመከራዎች ውስጥ በምንሆንበት ጊዜ በድክመቶቻችን ያግዘናል፡፡ እንዴት
መጸለይ እንደሚገባን ስለማናውቅ መንፈስ ራሱ በማይነገር መቃተት
ይማልድልናል፡፡ (ሮሜ 8፡26) ምን ማድረግ እንዳለብን ካላወቅን ‹‹መንገዱ ያ
ሳይሆን ይህ ነው›› ብሎ የሚያስተምረን መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡ እርሱ የእግዚአብሄርን
ቃል ያስታውሰናል፤ ያጽናናናል፤ ስናዝን ልባችንን ይደግፋል፤ ያጽናናንማል፡፡
ሁልጊዜም ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አብረን የምንሆነው በዚህ ሁኔታ ነው፡፡
እናንተና እኔ በጣም አስገራሚ ደህንነት አግኝተናል፡፡ አብ፣ ወልድና መንፈስ
ቅዱስ ይህንን ዩኒቨርስ ፈጠሩ፡፡ ስለዚህ እናንተና እኔ ይህንን ደህንነት ተቀብለን
የእግዚአብሄር ልጆች መሆን ችለናል፡፡ ይህንን ማወቅ አለብን፡፡
እግዚአብሄር ዓለምን ለምን ፈጠረ? እርሱ ዓለምን የፈጠረው እንደ እናንተና
እንደ እኔ የሐጢያታቸውን ስርየት የተቀበሉ ሰዎች የዚህ ስፍራ ጌታ እንዲሆኑ ነው፡፡
ደህንነታችን ከፍጥረት በፊት የታቀደው ለዚህ ነው፡፡ እናንተና እኔ ዛሬ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በመንፈስ ቅዱስ የተጸነሰው ኢየሱስ 41

ከሐጢያቶቻችን እንድንድን ይህ ደህንነት ከረጅም ጊዜ በፊት ታቀደ፡፡ ከፍጥረት


በፊት በታቀደው የእግዚአብሄር ችሮታ መሰረት እኛ ከሐጢያቶቻችን ከመዳናችንም
በላይ በውስጣችን መንፈስ ቅዱስ የሚኖርብን የእግዚአብሄር ልጆችም ሆነናል፡፡
ስለዚህ በተጨባጭ በእርሱ መንግሥት ውስጥ እንደ ነገሥታቶችና እንደ
ንግሥታቶች እየኖርን ያለን የእግዚአብሄር ልጆች ነን፡፡ በዚህ ዓለም ላይ ስንኖር
ነገሥታቶችና ንግሥታቶች ባንሆንም በእርሱ መንግሥት ውስጥ ግን የእግዚአብሄር
ልጆችና ነገሥታቶች እንደዚሁም ንግሥታቶች ነን፡፡ እኛ በጣም ተፈላጊ ሰዎች ነን፡፡
እውነተኛ በጣም ተፈላጊ ሰዎች ነን፡፡ እኛ በእርግጥም አስገራሚ ደህንነትን
የተቀበልን ተፈላጊ ሰዎች ነን፡፡
የገና በዓል አስገራሚ የሆነውና ትልቅ ትርጉም ያለው ለዚህ ነው፡፡ ሕጻኑ
ኢየሱስ በመንፈስ ቅዱስ ከተጸነሰ በኋላ ሲወለድ ማርያም የእግዚአብሄረን ቃሎች
በመቀበል ሕጻኑን ኢየሱስን ስትጸንስና ሕጻኑ ኢየሱስም በ10 ወር ውስጥ ሲወለድ
የደህንነታችን ሥራ ተጀመረ፡፡ ድንግል ማርያም የእግዚአብሄርን መልዕክት
ከተቀበለች በኋላ ጌታ ከእርስዋ ሲወለድ ‹‹ደስታ ለዓለም ጌታ መጥቷል›› ብለን
ዘመርን፡፡ ጌታ ከእግዚአብሄር ዘንድ የተላኩላትን የእግዚአብሄር ቃሎች
በተቀበለችው በድንግል ማርያም በኩል በተወለደበት ቀን ‹‹ደስታ ለዓለም ጌታ
መጥቷል›› ብለን ዘመርን፡፡ እኛ የዚህን አስገራሚ ሥራ ቀን እያከበርነው ነው፡፡
ትክክል ለመሆን ኢየሱስ የተወለደው እረኞች ከመንጎቻቸው ጋር ሌሊቱን
በሜዳ ባደሩበት ሞቃት ቀን እንጂ በሚያንቀጠቅጥ የአየር ጠባይ ባለው ቀን
አልነበረም፡፡ በትክክለኛው ቃል ላይ ጠቀሜታን ከማስቀመጥ ይልቅ መላው ዓለም
በመንፈስ ቅዱስ ከተጸነሰ በኋላ የደህንነትን በር የከፈተውንና በልባችን ውስጥ
የተቀበልነውን ደህንነት የሚያስታውሰውን ቀን ለማክበር የሚሰበሰብበትን ቀን
ወስነናል፡፡ ጠቃሚው ነገር ቀኑ ራሱ ሳይሆን ኢየሱስ ወደዚህ ዓለም የመምጣቱና
ማርያምም ሕጻኑ ኢየሱስ ይወለድ ዘንድ የእግዚአብሄርን ቃሎች የመቀበልዋ
እውነታ ነው፡፡
ይህንን ቀን ስናከብር አስገራሚውን ደህንነት ደግመን እናስባለን፡፡ በመንፈስ
ቅዱስ የተቀበልነውን ደህንነትና እርሱም በእኛ ውስጥ የሚኖር መሆኑን የምናስብ
ሆነን እንደገና መንፈስ ቅዱስን የሚያስደስቱ ሰዎች በመሆን ራሳችንን ማሰር
አለብን፡፡ ውድ ክርስቲያኖች እኛ አስገራሚ በሆኑ በረከቶች የተባረክን ሰዎች ነን፡፡
ማርያም ብሩክ ሆና ተቆጠረች፡፡ እናንተና እኔም እንደዚሁ ብሩካን ነን፡፡ ይህ
እውነት ነውን? --አዎ--፡፡
የገና በዓል ከተማይቱን በወንድ ጓደኞቻችን፣ በሴት ጓደኞቻችን፣

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


42 በመንፈስ ቅዱስ የተጸነሰው ኢየሱስ

በሐጢያተኞችና በቤተሰብ በአንድ እግርዋ የምናቆምበት ቀን ነውን? ወይስ ይህ ቀን


ጌታ እኛን ለማዳን ወደዚህ ምድር መምጣቱን ጥሩ ምግባሮችን በማድረግ
የምናከብርበትና የምናስብበት ጸጥ ያለ ሌሊትና ብጹዕ ሌሊት ነው? የጽድቅ
ምግባሮች የሚከናወኑበት ቀን ነው፡፡ እስቀድሜ እነግራችኋለሁ፡፡ እዚህ ያለ
ማንኛውም ሰው የገናን በዓል በተሳሳተ መንገድ እንደማይረዳና ወደ ጭፈራ ቤት
ባለመሄዱ በራሱ እንደማያዝን በዚህ ፍርሃት ሆኜ እነግራችኋለሁ፡፡ ‹‹እንደ ሌላው
ዓለም ወጥቼ የማልጠጣው ነገር ግን ቀኑን በዝምታ የማሳልፈው ለምንድነው?››
ብሎ የሚያስብና በበታችነት ስሜት የሚንገላታ ሰው ሊኖር እንደሚችል
የምነግራችሁ በፍርሃት ነው፡፡ የገናን በዓል ለማሳለፍ ተመራጩ መንገድ የቀኑን
ትርጉም በማሰላሰል በዝምታ ማሳለፍ ወይም አንዳንድ የጽድቅ ምግባሮችን
በማድረግ ማሳለፍ ነው፡፡ በዚህ የገና በዓል ወንጌልን ብናውጅና በውጤቱም አንድ
ሰው የሐጢያትን ስርየት ቢቀበል ከዚህ የበለጠ ሊታወስ የሚችል የገና በዓል
አይኖርም፡፡ ማርያም የእግዚአብሄርን ቃል በመቀበልዋ ኢየሱስ እንደተወለደ ሁሉ
ሐጢያተኞችም እንደ ሕጻኑ ኢየሱስ የምንሰብከውን የወንጌል ቃል በመቀበል በዚህ
ዓለም ላይ ጻድቅ ሰው ሊሆኑና ዳግመኛ ሊወለዱ ይችላሉ፡፡ በገና በዓል ወቅት ከዚህ
የበለጠ አንዳች ያማረ ትርጉም ሊኖር ይችላልን? የዚህ ዓይነት የጽድቅ የገና በዓል፤
የሚቻል ከሆነም ትርጉም ያለው የገና በዓል እንደሚኖራችሁ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡
በገና በዓል ወቅት በዙሪያችሁ ያዘነ ወይም ታመመ ሰው ስለመኖሩ
እንድትመለከቱ አደፋፍራችኋለሁ፡፡ የገና በዓል መላው ዓለም የሚያከብረው ዓውደ
ዓመት ነው፡፡ ሆኖም ይህ በዓል ለአንዳንድ ሰዎች በጣም የሐዘን ዓውደ ዓመት
ሊሆን እንደሚችል ማስታወስና ማመን አለብን፡፡ ስለዚህ ይህንን የገና በዓል ሌሎችን
የሚጠቅም የገና በዓል ልታደርጉት ትችላላችሁ፡፡
የገና በዓል የደስታና የምስጋና ቀን ነው፡፡ እኔን በሚመለከት በገና በዓል
ላሰራጫቻቸው እችል ዘንድ የወንጌል መጽሐፎቻችን ሕትመት ፈጥኖ እንዲጠናቀቅ
ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ የመጀመሪያው መጽሐፌ ነገ ወደ አሜሪካ እንደሚላክ
ሰምቻለሁ፡፡ በሚቀጥለው ዓመት ብዙ ሰዎች መጽሐፉን ማንበብ ይችሉ ዘንድ
በቅርቡ በአማዞን ዶት ኮም ላይ እንዲጫን እመኛለሁ፡፡ በቻይና ቋንቋ እየታተሙ
ያሉ መጽሐፎች ስላሉ በቀጣዩ ዓመት በሆንግ ኮንግና በቻይና መሰራጨት ይችሉ
ዘንድ ሕትመቱ ፈጥኖ እንዲጠናቀቅ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ ማርያም የእግዚአብሄርን
ቃሎች በመቀበል ሕጻኑን ኢየሱስን እንደጸነሰች ሁሉ ቻይኖችም ኢየሱስን
እንዲቀበሉና የሐጢያት ስርየትንም እንዲያገኙ እመኛለሁ፡፡ ይህ የእናንተም ተስፋ
አይደለምን? --አዎ--፡፡ በጣም በትርጉም የተሞላ የገና በዓልና የሚቻል ከሆነም

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በመንፈስ ቅዱስ የተጸነሰው ኢየሱስ 43

ከሌሎች ጻድቃን ሰዎች ጋር ያማረ የገና በዓል ይኖራችሁ ዘንድ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡
እግዚአብሄርን ስለ ደህንነታችንና በእኛ ላይ ስላለው ጥበቃው
እናመሰግነዋለን፡፡ በእያንዳንዱ የገና በዓል ወቅት ብዙ አደጋዎችን እናያለን፡፡
ከእነዚህ አደጋዎች እየጠበቀን ስላለ እግዚአብሄርን እናመሰግነዋለን፡፡ ሰክሮ
በመንዳት የሚከሰቱ ብዙ የመኪና አደጋዎች አሉ፡፡ ቅጥ ላጣው ተድላቸው ሲሉም
ገንዘብ ለማግኘት የሚፈልጉ ወጣቶች የሚፈጽሙዋቸው ወንጀሎችም አሉ፡፡ በገና
በዓል ወቅት ጠንቃቆች መሆን አለብን፡፡
ያለ ማቋረጥ የእርሱን ጥበቃ ለማግኘት፣ ወንጌልን ለማሰራጨት፣
ለመንግሥቱ፣ ለራሳችሁ ደህንነት፣ ለቤተክርስቲያኑ ደህንነት፣ አብረዋችሁ ላሉ
ክርስቲያኖች፣ እንደዚሁም ለብዙ ነፍሳቶች መዳን እንደምትጸልዩ ተስፋ
አደርጋለሁ፡፡ 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


44 በመንፈስ ቅዱስ የተጸነሰው ኢየሱስ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ምዕራፍ
2

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት
ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
ጌታን በትክክል ልንገናኘው
የምንችለው የት ነው?
‹‹ ማቴዎስ 2፡1-12 ››
‹‹ኢየሱስም በይሁዳ ቤተልሔም በንጉሡ በሄሮድስ ዘመን በተወለደ ጊዜ እነሆ
ሰብዓ ሰገል፡- የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ወዴት ነው? ኮከቡን በምሥራቅ አይተን
ልንሰግድለት መጥተናልና እያሉ ከምሥራቅ ወደ ኢየሩሳሌም መጡ፡፡ ንጉሡ
ሄሮድስም ሰምቶ ደነገጠ፤ ኢየሩሳሌምም ሁሉ ከእርሱ ጋር፡፡ የካህናትንም አለቆች
የሕዝቡንም ጻፎች ሁሉ ሰብስቦ ክርስቶስ ወዴት እንዲወለድ ጠየቃቸው፡፡
እነርሱም፡-
አንቺ ቤተልሔም የይሁዳ ምድር
ከይሁዳ ገዥዎች ከቶ አታንሺም፤
ሕዝቤን እስራኤልን የሚጠብቅ መስፍን
ከአንቺ ይወጣልና፡፡
ተብሎ በነቢይ እንዲህ ተጽፎአልና በይሁዳ ቤተልሄም አሉት፡፡
ከዚህ በኋላ ሄሮድስ ሰብዓ ሰገልን በስውር ጠርቶ ኮከቡ የታየበትን ዘመን
ከእነርሱ በጥንቃቄ ተረዳ፡፡ ወደ ቤተልሄምም እነርሱን ስድዶ፡- ሂዱ፤ ስለ ሕጻኑ
በጥንቃቄ መርምሩ፤ ባገኛችሁትም ጊዜ እኔ ደግሞ መጥቼ እንድሰግድለት ንገሩኝ
አላቸው፡፡ እነርሱም ንጉሡን ሰምተው ሄዱ፡፡ እነሆም በምሥራቅ ያዩት ኮከብ ሕጻኑ
ባለበት ላይ መጥቶ እስኪቆም ድረስ ይመራቸው ነበር፡፡ ኮከቡንም ባዩ ጊዜ በታላቅ
ደስታ እጅግ ደስ አላቸው፡፡ ወደ ቤትም ገብተው ሕጻኑን ከእናቱ ከማርያም ጋር
አዩት፤ ወድቀውም ሰገዱለት፡፡ ሣጥኖቻቸውንም ከፍተው እጅ መንሻ ወርቅና ዕጣን
ከርቤም አቀረቡለት፡፡ ወደ ሄሮድስም እንዳይመለሱ በሕልም ተረድተው በሌላ
መንገድ ወደ አገራቸው ሄዱ፡፡››

በዚህ ዓለም ላይ የሚኖሩ ብዙ ሰዎች አሉ፡፡ ከእነዚህ ሰዎች መካከል ብዙዎቹ


ኢየሱስ ጌታቸው መሆኑን የሚያስቡት በጽንሰ አሳብ ደረጃ ብቻ ነው፡፡ በአሜሪካ፣
በእስያና በአውሮፓ ብዙ ሰዎች በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን ከሐጢያቶቻቸው

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


48 ጌታን በትክክል ልንገናኘው የምንችለው የት ነው?

መዳን ይሻሉ፡፡ በማቴዎስ ምዕራፍ 2 ላይ እንደተጻፈው በኮከብ እየተመሩ ሕጻኑን


ኢየሱስን ለማግኘት እንደተጓዙት ነገር ግን ኢየሩሳሌም በደረሱ ጊዜ ግራ
እንደተጋቡት ሰብዓ ሰገሎች ግራ መጋባት የለብንም፡፡ ዛሬም ቢሆን ደህንነትን
ለማግኘት ከኢየሱስ ጋር ለመገናኘት አጥብቀው የሚፍጨረጨሩ ነገር ግን ፈጽሞ
ኢየሱስን የማያገኙ ሰዎች አሉ፡፡ ምክንያቱም ኢየሱስን መገናኘት የሚፈልጉት
በራሳቸው ውሱን እሳቤዎች መሰረት ነውና፡፡
በመላው ዓለም የሚገኙ ክርስቲያኖች የእግዚአብሄር ልጆች ይሆኑ ዘንድ
በውሃና በመንፈስ የመጣውን ኢየሱስን ከልባቸው መገናኘትና ከሐጢያቶቻቸው
መዳን ይኖርባቸዋል፡፡ ነገር ግን በተጨባጭ የሚታየው ይህ አይደለም፡፡ እንዲህ
የማይሆንበት ምክንያቱ እነዚህ ሰዎች የሚከተሉት የራሳቸውን ውሱን እሳቤዎች
እንጂ የእግዚአብሄርን ቃል ባለመሆኑ ነው፡፡ በዓለም ላይ የሚኖሩ ብዙ ሰዎች
የነገሥታትን ንጉሥ ያለ ምንም ችግር የማይገናኙት ‹‹ንጉሡ በኢየሩሳሌም ይወለዳል››
የሚል ውሱን እሳቤ ስላላቸው ነው፡፡
ነገር ግን እርሱ ምስኪን ሐጢያተኞችን ለማዳን ወደዚህ ዓለም መምጣት
ነበረበት፡፡ ስለዚህ ሰዎች በራሳቸው ውሱን እሳቤዎች ኢየሱስን ለመገናኘትና
ከሐጢያቶቻቸው ለመዳን ሲፍጨረጨሩ ደህንነትን አለማግኘታቸው የተለመደ
ነው፡፡ አሁንም እንኳን ብዙ ሰዎች ‹‹ወደዚያ ትልቅ ቤተክርስቲያን ብሄድ ኢየሱስን
ማግኘት ቀላል ይሆናል፡፡ ስብከትን ለመስማት ወደዚህ ትልቅ ቤተክርስቲያን ብሄድ
ትክክለኛውን የእግዚአብሄር ቃል እሰማለሁ›› ብለው የሚያስቡና እዚህ የተሳሳተ
መረዳት ውስጥ የሚወድቁ ብዙ ሰዎች አሉ፡፡ ሆኖም ነገሩ የእውነትን ቃል ስትሰሙ
በትልቅ ቤተክርስቲያን ውስጥ ወይም በትንሽ ቤተክርስቲያን ውስጥ መስማታችሁ
አይደለም፡፡ ሰዎች በራሳቸው ውሱን እሳቤዎች በሚሰብኩበት ጊዜ ሐጢያተኞች
እውነተኛውን ወንጌል እንዳይሰሙ፣ ከሐጢያቶቻቸውም እንዳይድኑና መንፈስ
ቅዱስን እንዳይቀበሉ ያግዳቸዋል፡፡
ትናትና የገና በዓል ዋዜማ ነበር፡፡ ዛሬ ደግሞ የገና በዓል ነው፡፡ በእነዚህ
ባለፉት ሁለት ቀናቶች ውስጥ የተሰበኩትን የገና በዓል ስብከቶች መለስ ብለን
ስናስባቸው አሁንም እንኳን ኢየሱስ ክርስቶስን ቢያምኑም ከልባቸው ያልተገናኙት
ብዙ ክርስቲያኖች መኖራቸው ልቤን ይሰብረዋል፡፡ ይህም ሰው ጌታን በራሱ ውሱን
እሳቤዎች መሰረት ሊገናኘው የማይችል የመሆኑን እውነት ደግሞ ያስታውሰናል፡፡
በገና በዓል ወቅት አንዳንድ ቤተክርስቲያኖች በመጠቅለያ የተጠቀለለ የሕጻኑን
ኢየሱስ ምስል ይሰሩና በግርግም ውስጥ ያስቀምጡታል፡፡ አንዳንድ
ቤተክርስቲያኖችም ድሆችን የመርዳት ዓላማ ይዘው በልግስና ጥሩ ነገርን ያደርጋሉ፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ጌታን በትክክል ልንገናኘው የምንችለው የት ነው? 49

ነገር ግን ኢየሱስ የተወለደበት ምክንያት የሰውን ዘር በሙሉ በልቡ ውስጥ ካሉት


ሐጢያቶች ሁሉ በማዳን የእግዚአብሄር ሕዝብ ማድረግ ነው፡፡
ሰብዓ ሰገል የራሳቸውን ውሱን እሳቤዎች በመከተላቸው ብዙ ችግሮች
እንደገጠሙዋቸው መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል፡፡ ይህም ለብዙ ሕጻናት መሞት
ምክንያት ሆነ፡፡ በነቢያት እንደተተነበየው ኢየሱስ የሚወለድበት ስፍራ
ቤተልሄም ቢሆንም ውሱን ከሆኑት እሳቤዎቻቸው የተነሳ የሚወለደው
በኢየሩሳሌም ነው ብለው አሰቡ፡፡ ውጤቱም ውዥንብርና የብዙ ሕጻናት ሞት
ሆነ፡፡ አሁንም ቢሆን ብዙ ሰዎች ኢየሱስ ክርስቶስን አዳኛቸው አድርገው
የሚያምኑት በራሳቸው ውሱን እሳቤዎቻቸው የእውነት ንጉሥ የሆነውን ኢየሱስ
ክርስቶስን መገናኘት እንደማይችሉ ማወቅ ያስፈልጋቸዋል፡፡
ዛሬ ብዙ ክርስቲያኖች በኢየሱስ ሲያምኑ ከበሽታዎቻቸው ሊፈውሱ ወይም
ባለጠጋ ሊሆኑ እንደሚችሉ ወደ ማሰብ ያዘነብላሉ፡፡ ይህ ግን ውሱን እሳቤያቸው
ነው፡፡ አንድ ሰው በሥጋዊ ስሜቶች ተነሳስቶ በኢየሱስ ቢያምን ደህንነቱን ወይም
መንፈስ ቅዱስን ሊያገኝ አይችልም፡፡ ሰዎች መንፈስ ቅዱስን የማይቀበሉት
ኢየሱስን አዳኛቸው አድርገው የሚያምኑት በራሳቸው ውሱን እሳቤዎች በመሆኑ
ነው፡፡
ብዙ ሰዎች በትልቅ ቤተክርስቲያን ውስጥ ሲያመልኩ የኦርጋንና አንድ
ትልቅ በአራት የተከፈለ የመዘምራን ቡድን ድምጽ ሲሰሙ እርካታ ይሰማቸዋል፡፡
ነገር ግን እግዚአብሄርን የምንገናኘው በትልቅ ቤተክርስቲያን ውስጥ ስናመልክ
ነው የሚለው እምነት ከማይረባውና ዓለማዊ ከሆነው እሳቤያችን የመነጨ
እምነት ስለመሆኑ መስማማት አለብን፡፡ ስለዚህ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
ያመጣውን ኢየሱስ ክርስቶስን በሰው እሳቤዎች ልንገናኘው እንደማንችል ማመን
አለብን፡፡ አሳዛኙ ነገር ደግሞ ሰዎች በመላው ዓለም በኢየሱስ ክርስቶስ ልደት
የሚደሰቱት የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ሳያውቁ በዓለም ደስታ መሆኑ
ነው፡፡
የኮሌጅ ካምፓሶችን ስንጎበኝ ብዙውን ጊዜ ወጣት ተማሪዎች
ጊታሮቻቸውን እየተጫወቱ ሲዘምሩና እግዚአብሄርን ሲያመልኩ እናያለን፡፡
እግዚአብሄርን የማምለክ ትዕይንት ውብ ነው፡፡ ነገር ግን የእነርሱን ምስጋናዎች
አብዝታችሁ በሰማችሁ ቁጥር በነፍሳቸው ውስጥ ያለው ጥማት አብልጦ
ሊሰማችሁ ይችላል፡፡ ነፍሳቸው እጅግ እንደተጠማች ሊታወቃችሁ ይችላል፡፡
ምክንያቱም እግዚአብሄርን በአንደበቶቻቸው ቢያመሰግኑትም በጉጉት ቢናፍቁም
የእውነትን አምላክ በመገናኘት ረገድ አልተሰካላቸውምና፡፡ ሆኖም ጌታን ያለ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


50 ጌታን በትክክል ልንገናኘው የምንችለው የት ነው?

ውሃውና ያለ መንፈሱ ወንጌል ለመገናኘት ያላቸው ምኞት ከምኞት የዘለለ ምንም


ነገር የለውም፡፡ በእግዚአብሄር እናምናለን ቢሉም የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
ስላላገኙ እግዚአብሄርን የሚሹት እንደ ሐጢያተኞች ሆነው ነው፡፡ ይህ ማለት
ዛሬ በክርስቲያን ቤተክርስቲያኖች ውስጥ ዳግመኛ ያልተወለዱ ሐጢያተኞች
እግዚአብሄርን ለመገናኘት በጥማት ተሞልተው መዝሙሮችን ይዘምራሉ ማለት
ነው፡፡
ነገር ግን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምኑ ሰዎች ሐጢያቶቻቸውን
በሙሉ ደምስሶ ካዳናቸው ጌታ ጋር ስለተገናኙ በምስጋና የተሞላ አምልኮን
ያቀርባሉ፡፡ ሐጢያተኞች ግን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ሳያውቁ
ለእግዚአብሄር አምልኮ ለማቅረብ ስለሚሞክሩ የምስጋና አምልኮን ማቅረብ
አይችሉም፡፡ ሐጢያተኞች አዳኙን ኢየሱስ ክርስቶስን ሊገናኙት አይችሉም፡፡
ምክንያቱም እርሱን ለመገናኘት የሚሞክሩት ከውሃውና ከመንፈሱ ወንጌል ውጪ
ነውና፡፡
አሁን ያለውን የክርስቲያን ቤተክርስቲያኖች ሁኔታ ስንመለከት ዛሬ
የክርስቲያን ቤተክርስቲያኖች ልክ እንደ ዓለማዊ ካምፓኒዎች እየሰሩ
ስለመሆናቸው ከዓለም በሚሰነዘሩት ነቀፌታዎች ከመስማማት በቀር ልናደርገው
የምንችለው ነገር የለም፡፡ ይህ ማለት ቤተክርስቲያኖቹ አስፈላጊ የሆኑትን
ተግባራቶችዋን እያደረገች አይደለም ማለት ነው፡፡ ዛሬ የክርስቲያን
ቤተክርስቲያኖች ግብ በገና በዓል በሚሰበሰብ አስራትና በምስጋና ስጦታ አስራት
ዓመታዊ መዋዕለ ንዋያቸውን ማሟላትና ዓመታዊ በጀታቸውን መበጀት ነው፡፡
የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ለዓለም እውነተኛ ሕይወትን የመስጠት
ሐላፊነት ስላለባት የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በማሰራጨት ላይ ማተኮር
አለብን፡፡ ነገር ግን እንደ እውነቱ ከሆነ አብዛኞቹ ቤተክርስቲያኖች ግባቸው
ዓለማዊ ዕሴቶችን መከተል በመሆኑ በብዙዎች ዘንድ ተነቅፈዋል፡፡ እንደዚሁም
መሞት የማይገባቸውን ነፍሳቶች በሐሰተኛ ወንጌሎቻቸው እየገደሉዋቸው ነው፡፡
(ሕዝቅኤል 13፡19) ሆኖም ችግሩ የክርስቲያን ቤተክርስቲያን መሪዎች
በቤተክርስቲያኖቻቸው ውስጥ ያለውን የመንፈሳዊ ንቅዘት አደጋ አለመገንዘባቸው
ነው፡፡
ውድ ክርስቲያኖች ሰብዓ ሰገል ኮከቡን መከተል ትተው የራሳቸውን
እሳቤዎች በመቀበላቸው ምን ተከሰተ? ብዙ ግራ መጋባት ነበር፡፡ ሰብዓ ሰገል
ከመጀመሪያው ኢየሱስን መገናኘት የተሳናቸው የራሳቸውን አስተሳሰቦች
በመከተላቸው ነው፡፡ በኋላ ግን የራሳቸውን አስተሳሰቦች ትተው በእግዚአብሄር

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ጌታን በትክክል ልንገናኘው የምንችለው የት ነው? 51

ቃል ላይ በመመስረት ኢየሱስን ተመለከቱ፡፡ በመጨረሻም አዳኙን ኢየሱስን


በተገቢው መንገድ ተገናኙት፡፡
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሰብዓ ሰገል ኢየሱስን በተገቢው መንገድ
መገናኘት የቻሉ ሰዎች የሆኑት ጸሐፍትንና ፈሪሳውያንን ጠይቀው በመጽሐፍ
ቅዱስ ውስጥ የተጻፉትን ትንቢቶች በመከተል ወደ ቤተልሄም በመሄዳቸው
ነው፡፡ ሰብዓ ሰገል ኢየሱስን መገናኘት የቻሉት የተጻፉትን የእግዚአብሄር ቃሎች
ስለተከተሉ ነው፡፡ ይህም የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በማወቅና በእርሱም
በማመን በመንፈሳዊ ሁኔታ እውነተኛውን አዳኝ ከመገናኘት ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡
ሰብዓ ሰገል የተጻፉትን የእግዚአብሄር ትንቢቶች ችላ ብለው ቢሆን ኖሮ ምንም
ያህል አበክረው ቢሞክሩም እንኳን ኢየሱስ መገናኘት አይችሉም ነበር፡፡ እኛ
ሁላችን የሐጢያቶቻችንን ሁሉ ይቅርታ ማግኘት የምንችለውና ለኢየሱስም
እውነተኛ እምነት የምናቀርበው የተጻፉትን የእግዚአብሄር ቃሎች አጥብቀን
ስንይዝና በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ስናምን ብቻ ነው፡፡ ሰብዓ ሰገል
ያሉዋቸውን ሦስት የእምነት ስጦታዎች ማቅረብ ችለዋል፡፡
ዳግመኛ የተወለደ ሰው ሁሉ ከእግዚአብሄር ዘንድ በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል የሚያምን የእምነት ቃል እንዳለው ልናውቅ ይገባናል፡፡ ሁላችንም
ኢየሱስን በትክክል መገናኘት የምንችለው የእግዚአብሄርን የውሃና የመንፈስ
ወንጌል በልባችን ስንቀበል እንደሆነ ማወቅ አለብን፡፡ በዘላለማዊው የውሃና
የመንፈስ ወንጌል ኢየሱስን በተጨባጭ ልንገናኘው፣ ልናመልከውና የእርሱን
ምሪት ልንቀበል እንችላለን፡፡ ሰብዓ ሰገል ከኢየሱስ ጋር መገናኘት የቻሉበት
ታሪክ እንደሚያሳየው ይህ የሆነው በተጻፈው የትንቢቶች ቃል በሚያምነው
እምነት ነው፡፡
በማቴዎስ 2፡6 ላይ የተጻፈው በብሉይ ኪዳን በሚክያስ 5፡2 ላይ የተጻፈው
ትንቢት ፍጻሜ ነው፡፡ ‹‹አንቺም ቤተልሔም ኤፍራታ ሆይ አንቺ በይሁዳ
አእላፋት መካከል ትሆኚ ዘንድ ታናሽ ነሽ፡፡ ከአንቺ ግን አወጣጡ ከቀድሞ ጀምሮ
ከዘላለም የሆነ በእስራኤልም ላይ ገዥ የሚሆን ይወጣልኛል፡፡›› እግዚአብሄር
በነቢዩ ሚክያስ በኩል የነገሥታት ንጉሥ የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ በቤተልሔም
እንደሚወለድ ተስፋ ሰጠ፡፡
ቤተልሔም ማለት ‹የዳቦ ቤት› ማለት ሲሆን ከተማይቱ በእስራኤል ውስጥ
ትንሽ የገጠር ከተማ ነበረች፡፡ ይህች ከተማ ዳዊት የተወለደባት ከተማ ነበረች፡፡
በዘፍጥረት መጽሐፍ ውስጥ ከአስራ ሁለቱ የያዕቆብ ልጆች አንዱ ለነበረው
ለይሁዳ ‹‹ይሁዳ ሆይ ዙፋንህ በዘሮችህ ይቀጥላል›› ብሎ እንደተነበየው ተስፋ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


52 ጌታን በትክክል ልንገናኘው የምንችለው የት ነው?

ሰጠው፡፡ ስለዚህ እግዚአብሄር ለይሁዳ በሰጠው ትንቢት መሰረት ጌታችን


በቤተልሔም ተወለደ፡፡ ጌታችን በእርግጥም የነገሥታት ንጉሥ ሆኖ የሰው ሥጋ
በመልበስ ወደዚህ ዓለም ተወለደ፡፡ ስለዚህ እግዚአብሄር በነቢያቶች በኩል
በሰጠው ተስፋና ትንበያ መሰረት ጌታችን ቤተልሄም በምትባል ትንሽ ከተማ
ውስጥ ተወለደ፡፡
ጌታችን እንዴት በተጻፈው ቃሉ መሰረት እንደሚሰራ አሳይቶናል፡፡ ጌታችን
በእውነት ይናገረናል፡፡ የተናገራቸውንም ቃሎች ይፈጽማል፡፡ ስለዚህ
እግዚአብሄርን አምነን ስንከተለው ብዙውን ጊዜ የራሳችንን እሳቤዎች መካድ
ያስፈልጋል፡፡ ጌታን ስንከተል በአስተሳሰቦቻችን ስህተት ማሰብ ስለሚቻል
ሁልጊዜም የራሳችንን አስተሳሰቦች መካድና በተጻፈው የእግዚአብሄር ቃል
የሚያምነውን እምነት መከተል አለብን፡፡
ሰብዓ ሰገል እንደገና በኮከብዋ ተመርተው ቤተልሔም በመድረስ ከሕጻኑ
ኢየሱስ ጋር ተገናኙ፡፡ በዓለም ላይ ያለ እያንዳንዱ ሰው ኢየሱስን እንዲገናኝ
የምንፈልግ ከሆንን የተጻፈውን የእግዚአብሄር ቃል ማስፋፋት አለብን፡፡ ኢየሱስን
ልንገናኘው የምንችለው የተጻፈውን የእግዚአብሄር ቃል በማመንና በመከተል
ብቻ ነው፡፡ ከተጻፈው የእግዚአብሄር ቃል ውጪ በራሳችሁ እሳቤዎች ኢየሱስን
አዳኝ አድርጋችሁ ልታውቁትና ልትገናኙት አትችሉም፡፡
የተጻፈውን የእግዚአብሄር ቃል ስናምንና ስንከተል ኢየሱስ ለእኛ
እንደተወለደ፣ የሰውን ዘር ሐጢያቶች ለመውሰድ በአጥማቂው ዮሐንስ
እንደተጠመቀ፣ የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ እንደወሰደ፣ በመስቀል ላይ
እንደደማና እንደሞተ፣ እንደተነሳ፣ ዳግመኛ ሲነሳም ደህንነታችንን እንደፈጸመ
ወደ ማወቅ እንመጣለን፡፡ የነገሥታት ንጉሥ የሆነውን ኢየሱስን ልንገናኝ
የምንችልበት ብቸኛው መንገድ ይህ ነው፡፡ አዳኙን ኢየሱስን ለመገናኘት
ኢየሱስን በተጻፈው የእግዚአብሄር ቃልና በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ማመን
ያለብን ለዚህ ነው፡፡ በተጻፈው የእግዚአብሄር ቃል ካልሆነ በቀር አዳኙን
ኢየሱስን መገናኘት እንደማንችል ማስታወስ አለብን፡፡
ሦስቱም ስጦታዎች ማለት ወርቅ፣ ዕጣንና ከርቤ ዋጋ ያላቸው ናቸው፡፡
ከርቤ የማይለወጠውን የእግዚአብሄር ቃል ያመለክታል፡፡ የእግዚአብሄር ቃል
እውነቱ ከሌለን በኢየሱስ ልናምን ወይም የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
ልንቀበል አንችልም፡፡ ሰብዓ ሰገሎች የወርቅና የዕጣን ሁለት ስጦታዎችን ብቻ
ሰጥተው ቢሆን ኖሮ ከሐይማኖታዊ ሰዎች በቀር ምንም ባልሆኑ ነበር፡፡ ይህም
ከሰብአዊ አስተሳሰቦች የመጣ የተሳሳተ እምነት እንጂ በእግዚአብሄር ዓይኖች

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ጌታን በትክክል ልንገናኘው የምንችለው የት ነው? 53

ትክክለኛ እምነት ባልሆነ ነበር፡፡ እኛም ደግሞ ለጌታ ሦስቱን ስጦታዎች መስጠት
የሚኖርብን መሆኑን ማጤን አለብን፡፡ ኢየሱስን መገናኘት የምንፈልግ ከሆነ
በመጀመሪያ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል መቀበል፣ የሐጢያቶችን ስርየት
መቀበልና እርሱን በእምነት ብቻ መከተል አለብን፡፡
ሰብዓ ሰገል የተጻፈውን ቃል ከተከተሉ በኋላ ኢየሱስን በቤተልሔም
ሲያገኙት ሕጻኑ ኢየሱስ በግርግም ውስጥ ተኝቶ ነበር፡፡ በሕጻኑ ኢየሱስ ፊት
ያጎነበሱት፣ ስጦታዎቻቸውን ያቀረቡትና እምነታቸውን የመሰከሩት ያን ጊዜ ብቻ
ነው፡፡ ጴጥሮስ ‹‹አንተ የሕያው እግዚአብሄር ልጅ ክርስቶስ ነህ›› ብሎ
እንደመሰከረ እነርሱም ምስክርነታቸውን መስጠት ቻሉ፡፡ ሰብዓ ሰገል በተጻፈው
ቃል ከመደገፍ ይልቅ በራሳቸው እሳቤዎች ላይ ተደግፈው ኢየሱስን ፍለጋ
በኢየሩሳሌም አውራጃ ቢዞሩ ኖሮ ከጌታ ጋር መገናኘት አይችሉም ነበር፡፡ ነገር
ግን ወደተጻፈለት ስፍራ በሄዱ ጊዜ ሕጻኑ ኢየሱስ እዚያ ነበር፡፡ በዚህ ዘመንም
ከልቡ ዳግመኛ መወለድ የሚፈልግ ማንኛውም ሰው የተጻፈውን የእግዚአብሄር
ቃል መከተልና በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን ዳግመኛ መወለድ
ያስፈልገዋል፡፡
ማንም ይሁን ሰው ዛሬም ኢየሱስን ለመገናኘት በተጻፈው ቃል ማመን
ያስፈልገዋል፡፡ በራሳችን እሳቤዎች የሚያምነውን የእምነት ዓይን ማስወገድ ነገር
ግን በተጻፈው ቃልና በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት ከሐጢያቶቻችን
ሁሉ ባዳነን ኢየሱስ በማመን ወደ አዳኙ መመለስ ያስፈልገናል፡፡ በዓለም ላይ
ያሉ ክርስቲያኖች በሙሉ ይህንን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በማወቅ ወደ
እግዚአብሄር መመለስ አለባቸው፡፡ አዳኙን ኢየሱስን የምናገኘው እንደዚህ ነው፡፡
ትክክለኛ እምነታችንን ለእግዚአብሄር አቅርበን ድጋፍ የምናገኝበት ብቸኛው
መንገድ ይህ ነው፡፡
ገና ኢየሱስ ክርስቶስን ያልተገናኙት በዓለም ያሉ ሰዎች በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል በማመን ወደ እግዚአብሄር መመለስ አለባቸው፡፡ ወደ
እግዚአብሄር ቃል መመለስና በእውነቱም በኩል ኢየሱስን መገናኘት አለብን፡፡
የተጻፈውን ቃል እንዳለ ስናምነውና ስንከተለው በትክክለኛ እምነት የሚያምኑ
ምዕመናን እንሆናለን፡፡ በዓለም ላይ ያሉ ሰዎች በሙሉ ወደ ውሃውና መንፈሱ
ወንጌል መመለስ ይገባቸዋል፡፡ ኦርቶዶክስ የእምነት ድርጅቶች ተብዬዎችን ወይም
ታላላቅ የቤተክርስቲያን ሕንጻዎችን ከመሻት ይልቅ ራሳችንን በማዋረድ
በተጻፈው ቃል በኩል የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል መቀበል አለብን፡፡
ኢየሱስ እንደሚመጣ መላው ዓለም ያወቀ ቢሆን አብዛኛው ሕዝብ ገናም

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


54 ጌታን በትክክል ልንገናኘው የምንችለው የት ነው?

ኢየሱስ ክርስቶስን አዳኙ አድርጎ አልተገናኘውም፡፡ እነዚህ ሰዎች አሁንም ድረስ


ኢየሱስን በዓለማዊ ቤተ መንግሥቶች ውስጥ ይፈልጉታል፡፡ ነገር ግን ወደ
ቤተልሔም መሄድ አለባቸው፡፡ ወደ ትንሽዋ የቤተልሔም ከተማ ሲሄዱ ኢየሱስን
ሊገናኙት ይችላሉ፡፡ እርሱን በሌላ በማንኛውም ስፍራ ሊያገኙት አይችሉም፡፡
ሕጻኑ ኢየሱስ ፈጽሞ በቤተ መንግሥት ውስጥ የለም፡፡ ውድ ክርስቲያኖች
ገባችሁ? ሕጻኑ ኢየሱስ ፈጽሞ ከሄሮድስ ጋር አልኖረም፡፡ ኢየሱስን ለመገናኘት
ወደ ቤተልሔም መሄድ አለብን፡፡ ይህ ማለት ኢየሱስን ለመገናኘት ወደ ዳቦ ቤት
ማለትም የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን መሄድ አለብን፡፡ ስለዚህ የዛሬዋ
ቤተልሔም ማለት ዳግመኛ የተወለዱ ሰዎች ያሉባት ቤተክርስቲያን ማለት ናት፡፡
ሰዎች ሁሉ በግልጽ ከሐጢያቶቻቸው መዳን የሚችሉት በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል እውነት የሚመጣውን የእግዚአብሄር ደህንነት በሚያምነው
እምነታቸው ብቻ ነው፡፡ ነገር ግን ብዙ ሰዎች ልክ ሰብዓ ሰገል እንዳደረጉት
ኢየሱስን በራሳቸው እሳቤዎች ለመገናኘት በመሞር አሁንም ድረስ ግራ በመጋባት
እየተቅበዘበዙ ነው፡፡ አንዳንድ ሰዎች ለ50 ዓመታት ፈልገውታል፡፡ ሌሎች ሰዎች
ደግሞ ከ70 ዓመታት በኋላ አሁንም ድረስ ይፈልጉታል፡፡
አዳኝ የሆነውን ሕጻኑን ኢየሱስን ያልተገናኙትን ሰዎች ነጥቀን በማውጣት
እነርሱም ደግሞ አዳኙን ኢየሱስን መገናኘት ይችሉ ዘንድ የውሃውንና የመንፈሱን
ወንጌል ልናቀርብላቸው ግዴታ አለብን፡፡ የእምነት ዓይኖቻችንን ሰፋ አድርገን
ከፍተን በስፋት ማየት አለብን፡፡ እኛ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በሁሉም
የዓለም ማዕዘናቶች ላሉ ሁሉ መስጠት አለብን፡፡ 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ምዕራፍ
3

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት
ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
እውነተኛውን ወንጌልና
የኢየሱስን የጽድቅ ምግባር አስፋፉ
‹‹ ማቴዎስ 3፡1-17 ››
‹‹በዚያም ወራት መጥምቁ ዮሐንስ መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ
ግቡ ብሎ በይሁዳ ምድረ በዳ እየሰበከ መጣ፡፡ በነቢዩ ኢሳይያስ፡-
የጌታን መንገድ አዘጋጁ
ጥርጊያውንም አቅኑ እያለ
በምድረ በዳ የሚጮህ ሰው ድምጽ
የተባለለት ይህ ነውና፡፡ ራሱም ዮሐንስ የግመል ጠጉር ልብስ ነበረው፡፡
በወገቡም ጠፈር ይታጠቅ ነበር፡፡ ምግቡም አንበጣና የበረሃ ማር ነበር፡፡ ያን ጊዜ
ኢየሩሳሌም ይሁዳም ሁሉ በዮርዳኖስ ዙሪያ ያለ አገር ሁሉ ወደ እርሱ ይወዩ
ነበር፡፡ ዳሩ ግን ከፈሪሳውያንና ከሰዱቃውያን ብዙዎች ወደ ጥምቀቱ ሲወጡ ባየ
ጊዜ እንዲህ አላቸው፡- እናንተ የእፉኝት ልጆች ከሚመጣው ቁጣ እንድትሸሹ ማን
አመለከታችሁ? እንግዲህ ለንስሐ የሚገባ ፍሬ አድርጉ፡፡ በልባችሁም፡- አብርሃም
አባት አለን እንደምትሉ አይምሰላችሁ፤ እላችኋለሁና፡- ከእነዚህ ድንጋዮች
ለአብርሃም ልጆች ሊያስነሣለት እግዚአብሄር ይችላል፡፡ አሁንስ ምሣር በዛፎች
ሥር ተቀምጦዋል፤ እንግዲህ መልካም ፍሬ የሚያደርግ ዛፍ ሀሉ ይቆረጣል፤ ወደ
እሳትም ይጣላል፡፡ እኔስ ለንስሐ በውሃ አጠምቃችኋለሁ፤ ጫማውን እሸከም ዘንድ
የማይገባኝ ከእኔ በኋላ የሚመጣው ግን ከእኔ ይልቅ ይበረታል፡፡ እርሱ በመንፈስ
ቅዱስ በእሳትም ያጠምቃችኋል፡፡ መንሹም በእጁ ነው፤ አውድማውንም ፈጽሞ
ያጠራል፤ ስንዴውንም በጎተራው ይከታል፤ ገለባውን ግን በማይጠፋ እሳት
ያቃጥለዋል፡፡ ያን ጊዜ ኢየሱስ በዮሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ፡፡
ዮሐንስ ግን፡- እኔ በአንተ ልጠመቅ ያስፈልገኛል፤ አንተም ወደ እኔ ትመጣለህን?
ብሎ ይከለክለው ነበር፡፡ ኢየሱስም መልሶ፡- አሁንስ ፍቀድልኝ፤ እንዲህ ጽድቅን
ሁሉ መፈጸም ይገባናልና አለው፡፡ ያን ጊዜ ፈቀደለት፡፡ ኢየሱስም ከተጠመቀ በኋላ
ወዲያው ከውሃ ወጣ፤ እነሆም ሰማያት ተከፈቱ የእግዚአብሄርም መንፈስ እንደ
ርግብ ሲወርድ በእርሱ ላይም ሲመጣ አየ፤ እነሆም ድምጽ ከሰማያት መጥቶ፡-
በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው አለ፡፡››

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


58 እውነተኛውን ወንጌልና የኢየሱስን የጽድቅ ምግባር አስፋፉ

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አጥማቂው ዮሐንስ እጅግ አስፈላጊ ገጸ ባህርይ


የነበረ መሆን አለበት፡፡ አጥማቂው ዮሐንስ የእስራኤል ሕዝብ ንስሐ እንዲገባ
ጮኸ፡፡ የኢየሱስንና የአጥማቂውን ዮሐንስን ሥራ በግልጽ ማስታወስ አለብን፡፡
ወደዚህ ዓለም የመጣው ኢየሱስ ከአጥማቂው ዮሐንስ ጋር አብሮ የእግዚአብሄርን
ፈቃድ በመታዘዝ የሰውን ዘር አዳነ፡፡ አጥማቂው ዮሐንስና ኢየሱስ ወደዚህ
ዓለም መጥተው የጽድቅ ምግባሮች አከናወኑ፡፡
አጥማቂው ዮሐንስ የእስራኤል ሕዝብ ወደ እግዚአብሄር እንዲመለሱ
ለመናቸው፡፡ በማቴዎስ 3፡7 ውስጥ ማየት እንደምችለው አጥማቂው ዮሐንስ
እያጠመቀ ሳለ ፈሪሳውያንንና ሰዱቃውያንን ወደ እርሱ ሲመጡ ባየ ጊዜ ‹‹እናንተ
የእፉኝት ልጆች ከሚመጣው ቁጣ እንድትሸሹ አመለከታችሁ?›› በማለት
በድፍረት ወቀሳቸው፡፡ ይህ አጥማቂው ዮሐንስ እንደ ነቢይ ሆኖ ‹‹እናንተ
የእፉኝት ልጆች ንስሐ ግቡ!›› በማለት የእስራኤልን ሕዝብ ወቀሰ፡፡ አጥማቂው
ዮሐንስ በእግዚአብሄር ፊት የጽድቅ ምግባሮችን ያደረገና የብሉይ ኪዳን ዘመንም
የመጨረሻው ነቢይ ነበር፡፡
አንዳንዶች አጥማቂው ዮሐንስ የእግዚአብሄር ነቢይ ሆኖ ሳለ ‹‹የእፉኝት
ልጆች›› የሚል እንዲህ ያለ አሳፋሪ አባባል መናገር ቻለ በማለት ይገረማሉ፡፡
ሆኖም ይህ በእግዚአብሄር ፊት የጽድቅ ምግባር እንደነበር መጽሐፍ ቅዱስ
መዝግቦ ይነግረናል፡፡ ነቢያቶች በሙሉ የእግዚአብሄርን የጽድቅ ምግባር
የሚሰብኩ ሰዎች መሆን ይገባቸዋል፡፡ ከአጥማቂው ዮሐንስ ሌላ የጽድቅ
ምግባሮችን ያደረገ ሌላ ሰውም መጥቷል፡፡ ያም ኢየሱስ ነበር፡፡
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሰዱቃውያን ፖለቲከኞች ነበሩ፡፡ እነርሱ
እግዚአብሄርን ከማገልገል ይልቅ ይበልጥ ትኩረት የሚያደርጉት በዚህ ዓለም
ፖለቲካ ላይ ነበር፡፡ ፈሪሳውያን ግን ወግ አጥባቂ የሐይማኖት መሪዎች ነበሩ፡፡
የእግዚአብሄርን ቃል እንደተጻፈው እናምናለን እያሉ ኢየሱስን ካዱት፡፡
እግዚአብሄር እነዚህን ሰዎች ባየ ጊዜ ክፉኛ አዘነ፡፡ ሰዎች በእግዚአብሄር
ፊት ክፉዎች ነበሩ ወይስ አልነበሩም? ፈሪሳውያንና ሰዱቃውያን በእግዚአብሄር
ፊት ክፉዎች ነበሩ፡፡
ፈሪሳውያን ኢየሱስ መሲህ መሆኑን አላመኑም፡፡ አጥማቂው ዮሐንስ
የእፉኝት ልጆች ብሎ መጥራቱ ትክክል የሆነው ለዚህ ነው፡፡ አጥማቂው ዮሐንስ
በዚያን ዘመን ከነበሩት የሐይማኖት መሪዎች ጋር አላመቻመችም፡፡
ከፈሪሳውያንና ከሰዱቃውያን ጋረ ከማመቻመች ይልቅ የእፉኝት ልጆች
መሆናቸውን በወቀሳ መልክ በመንገር ሊመልሳቸው ሞከረ፡፡ አጥማቂው ዮሐንስ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


እውነተኛውን ወንጌልና የኢየሱስን የጽድቅ ምግባር አስፋፉ 59

ወደ እግዚአብሄር እየተመለሱ ያሉትን ሰዎች ንስሐ በቂ እንዳልሆነ፣ የንስሐ ፍሬ


ማፍራት እንደሚገባቸውና ከክፉ ነገር መመለስ እንደሚያስፈልጋቸው
አስተማራቸው፡፡ ለምሳሌ በማጭበርበር ያገኙትን ገንዘብ በሙሉ መመለስ
ነበረባቸው፡፡ ያን ጊዜ በእርሱ ለመጠመቅ መምጣትና ወደ እግዚአብሄር መመለስ
ይችላሉ፡፡
የእርሱን አባባሎች ስናደምጥ እርሱ በእግዚአብሄር የተላከ ባርያ እንደነበር
ያለ ምንም ጥርጣሬ ማየት እንችላለን፡፡ አጥማቂው ዮሐንስ የተገለጠበት ጊዜ
ኢየሱስ ክርስቶስ የአደባባይ አገልግሎቱን የጀመረበት ጊዜ ነበር፡፡ የአጥማቂው
ዮሐንስ እወጃ የኢየሱስን ሥራ የሚያግዝ ነበር፡፡ በዚያን ዘመን የእስራኤል ሕዝብ
ለ400 ዓመታት ያህል አገልጋይ አልነበረውም፡፡ ስለዚህ የአጥማቂው ዮሐንስ
መምጣት የእግዚአብሄርን ችሮታና የእግዚአብሄርን ድምጽ ለመስማት ጥሩ ዕድል
ነበር፡፡
አጥማቂው ዮሐንስ ‹‹የእፉኝት ልጆች ንስሐ ግቡ፤ ወደ እግዚአብሄርም
ተመለሱ፤ ከጣዖት አምልኮ ተመለሱ፤ ከእግዚአብሄር ፍርድ ለማምለጥ እንግዳ
አማልክቶችን አውግዛችሁ ወደ እግዚአብሄር ተመለሱ›› በማለት ጮኸ፡፡
የእግዚአብሄር ባርያ በዚህ ሁኔታ እነርሱን መውቀሱና መምከሩ ለእስራኤል
ሕዝብ ታላቅ በረከት ነበር፡፡ መላው የእስራኤል ሕዝብ በአጥማቂው ዮሐንስ
ስብከት ተናወጠ፡፡ ሊቀ ካህናት ሰዱቃውያንና ፈሪሳውያን ንስሐ የገቡበትና ወደ
እግዚአብሄር የተመለሱበትም ተዓምር ተከናወነ፡፡
አጥማቂው ዮሐንስ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ችሎታዎች መሰከረ፡-‹‹እኔስ
ለንስሐ በውሃ አጠምቀችኋለሁ፤ ጫማውን እሸከም ዘንድ የማይገባኝ ከእኔ በኋላ
የሚመጣው ግን ከእኔ ይልቅ ይበረታል፡፡ እርሱ በመንፈስ ቅዱስ በእሳትም
ያጠምቃችኋል፡፡ መንሹም በእጁ ነው፤ አውድማውንም ፈጽሞ ያጠራል፤
ስንዴውንም በጎተራው ይከታል፤ ገለባውን ግን በማይጠፋ እሳት ያቃጥለዋል፡፡››
(ማቴዎስ 3፡11-12) እርሱ ሰዎችን በመውቀስ ወደ እግዚአብሄር የሚመለሱበትን
ሥራ እንደሚሰራ ከእርሱ በኋላ የሚመጣው ግን በመንፈስ ቅዱስና በእሳት
እንደሚያጠምቃቸው መሰከረ፡፡
አጥማቂው ዮሐንስ ኢየሱስን በማመን ዳግመኛ የተወለዱ ሰዎች በሰማይ
ስንዴ ሆነው እንደሚሰበሰቡ ዳግመኛ ያልተወለዱትም እንደ ገለባ በመንሽ
ተበጥረው በማይጠፋ እሳት እንደሚቃጠሉ ተናግሮዋል፡፡
አጥማቂው ዮሐንስ ወደ እግዚአብሄር ስለ መመለስ እንደተናገረና ኢየሱስ
ክርስቶስም ወደዚህ ዓለም በመጣ ጊዜ በአጥማቂው ዮሐንስ እንደተጠመቀ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


60 እውነተኛውን ወንጌልና የኢየሱስን የጽድቅ ምግባር አስፋፉ

ማወቅ አለብን፡፡ በሉቃስ ወንጌል መሰረት ኢየሱስ በተጠመቀ ጊዜ 30 ዓመቱ


ነበር፡፡ (ሉቃስ 3፡23) ኢየሱስ ሰላሳ ዓመት ሲሆነው ለምን መጠመቅ ፈለገ?
‹‹ሰላሳ ዓመት›› የሆነበት ምክንያት አንድ ሰው ሊቀ ካህን ሆኖ ተግባራቶቹን
ለመፈጸም የሰላሳ ዓመት ዕድሜ ያለው መሆን ስለነበረበት ነው፡፡ እግዚአብሄር
የሊቀ ካህናት ልጆች ሐላፊነትን የመሸከም ችሎታ የሚኖራቸው 30 ዓመት
ሲሆናቸው እንደሆነ በብሉይ ኪዳን ውስጥ ተናግሮዋል፡፡ (ዘሁልቁ 4፡35) ልክ
እንደዚሁ ኢየሱስም 30 ዓመት ሲሆነው በአጥማቂው ዮሐንስ ተጠመቀ፡፡
ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ የተጠመቀው የእግዚአብሄርን ጽድቅ ሁሉ
ለመፈጸም ነበር፡፡ ኢየሱስ በዓለም ላይ ያለውን የእያንዳንዱን ሰው ሐጢያቶች
ለመውሰድ በአጥማቂው ዮሐንስ ተጠመቀ፡፡
ነገር ግን ሰዎች ኢየሱስ ለምን በአጥማቂው ዮሐንስ እንደተጠመቀ ግራ
ስለተጋቡ አልገባቸውም፡፡ ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ መጠመቁ በመጽሐፍ
ቅዱስ ውስጥ የተገለጠ ምስጢር ነው፡፡ ብዙ ሰዎች የጥምቀትን ምስጢር
ስላልተረዱ ኢየሱስ ለምን እንደተጠመቀ አልገባቸውም፡፡ ምሳሌ ለመተው ወይም
ትህትናን ለማሳየት እንደሆነ ያስባሉ፡፡
ኢየሱስ ወደዚህ ዓለም መጥቶ የተጠመቀው በዓለም ላይ የሚኖረውን
እያንዳንዱን ሰው ከሐጢያቶቹ ለማዳን እንደሆነ ማወቅ አለብን፡፡ ኢየሱስ
ወደዚህ ዓለም መጥቶ በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅ የዚህን ዓለም ሐጢያቶች
የመውሰድ የጽድቅ ምግባርን መፈጸም ቻለ፡፡ የጽድቁ ምግባር ኢየሱስ
በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅ የዓለምን ሐጢያቶች ለአንዴና ለመጨረሻ
መውሰዱ ነው፡፡ የኢየሱስ ጥምቀት ዓላማው የእግዚአብሄርን ጽድቅ ሁሉና
እርሱን የሚያስደስተውን የአምላክ ፈቃድ ለመፈጸም ነበር፡፡ ጌታችን እኛን
ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ለማዳን ወደዚህ ዓለም መጣ፡፡ የእናንተንና የእኔን
ሐጢያቶች በጥምቀቱ ለአንዴና ለመጨረሻ ለመውሰድና ለእኛም እስከ ሞት
ድረስ ለመድማት ተጠመቀ፡፡ ጌታ የዓለምን ሐጢያቶች ለአንዴና ለመጨረሻ
ወሰደ፡፡
በማቴዎስ 3፡15 ላይ ‹‹ጽድቅን ሁሉ›› ማለት ኢየሱስ በዮሐንስ በመጠመቅና
በመስቀል ላይም ደሙን አፍስሶ በመሞት የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ ወስዶዋል
ማለት በዚያን ወቅት ኢየሱስ የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ፤ ሐጢያቶቻችንን
በሙሉ ወሰደ፡፡ ይህ እንዴት መታደል ነው! እኛስ ምንኛ አመስጋኞች ነን?
ውድ ክርስቲያኖች በዚህ ዓለም ላይ ሐጢያቶችን እንሰራለን ወይስ
አንሰራም? ሐጢያቶችን እንሰራለን፡፡ የምንሰራቸው ሐጢያቶች ጥቂቶች ናቸውን?

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


እውነተኛውን ወንጌልና የኢየሱስን የጽድቅ ምግባር አስፋፉ 61

ወይም አብዝተን ሐጢያት እንሰራለን? በዚህ ዓለም ላይ ብዙ ሐጢያቶችን


እንሰራለን፡፡ የእናንተም ሐጢያቶች በዓለም ሐጢያቶች ሁሉ ውስጥ ተካተዋል፡፡
ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅ የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ ለአንዴና
ለመጨረሻ ወሰደ፡፡ በመስቀል ላይም ለአንዴና ለመጨረሻ ሞተ፡፡ ሐጢያቶችንና
ፍርድንም ጠራርጎ አስወገደ፡፡
ኢየሱስ የእናንተንና የእኔን ሐጢያቶች ለአንዴና ለመጨረሻ ባይወስድ ኖሮ
እናንተና እኔ እንዴት ያለ ሐጢያት መሆን እንችል ነበር? ይህ እውነት ጌታችን
ወደዚህ ዓለም በመጣ ጊዜ በጥምቀቱና በደሙ የፈጸመው ጽድቅ ነው፡፡
የእግዚአብሄር ልጅ ሆኖ ወደዚህ ዓለም በመምጣት የዓለምን ሐጢያቶች የወሰደና
ስለ እኛም ሐጢያት ፍርድን የተቀበለ አዳኝ ነው፡፡

ማስታወስ የሚያስፈልገን ነገር፡፡

በዚህ ዓመት የገናን በዓል ስንቀበል አጥማቂው ዮሐንስና ኢየሱስ ሌላ


ማንም ሊያደርገው የማይችለውን የእግዚአብሄርን ጽድቅ እንደፈጸሙ ማስታወስ
ይገባናል፡፡ የገናን በዓል ስንቀበል ‹‹እንዴት ደስታን ላገኝ እችላለሁ? እንዴት ጥሩ
ትዝታዎችን ማሳለፍ እችላለሁ?›› በማለት ፋንታ ‹‹የገና በዓልን ስንቀበል ጽድቅን
የፈጸመውን ጌታችንን ስናስብ በጽድቅ ሥራ ውስጥ መሳተፍ የምንችለው እንዴት
ነው?›› በማለት ማሰብ ያስፈልገናል፡፡ የአጥማቂውን ዮሐንስንና የኢየሱስን ሥራ
በእርግጠኝነት ማስታወስ እንችላለን፡፡ እኛም ደግሞ በዚህ የገና በዓል ጽድቅን
ሁሉ የፈጸመውን የኢየሱስንና የአጥማቂውን ዮሐንስን ሥራ የሚያስታውሱ ሰዎች
መሆን ይገባናል፡፡ ሕይወታችን የእግዚአብሄርን ጽድቅ ለማስፋፋት ብቻ የተሰጠ
መሆን ይገባዋል፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን የሐጢያት ስርየትን
ከተቀበልን በኋላ ይህንን ወንጌል የሚያስፋፋ ሕይወት መኖር ይገባናል፡፡
ራሳችንን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለሚያስፋፋው ለዚህ የጽድቅ
አገልግሎት ባንሰጥ ምን እንሆናለን? በዚህ የጽድቅ አገልግሎት ውስጥ ስንሳተፍ
እግዚአብሄር በረከቱን እንዲሰጠን እንዴት መጠበቅ እንችላለን? ኢየሱስ የሰውን
ዘር ሐጢያቶች በሙሉ በመውሰድ እንዳዳነን ስለምናውቅ መሳተፍ አለብን፡፡
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በመላው ዓለም ማሰራጨት አስፈላጊ
አይደለምን? በሥጋ በጎ ምግባሮችን ማድረግ እንችላለን? ሐጢያቶችን
ላለማድረግ በመሞከር ልናስወግዳቸው እንችላለን? እኛ ደካሞች የሐጢያት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


62 እውነተኛውን ወንጌልና የኢየሱስን የጽድቅ ምግባር አስፋፉ

ስርየትን ከተቀበልን በኋላ እንዴት የጽድቅ ሕይወትን መኖር እንችላለን? ይህ


ወደዚህ ዓለም በመጣው ሐጢያቶችን ሁሉ ወደ መስቀል በወሰደውና
የሐጢያቶችን ፍርድ ለእኛ ሲል ይወስድ ዘንድ በደማውና በሞተው ኢየሱስ
አማካይነት በዚህ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ስርጭት የሚቻል አይደለምን?
እናንተና እኔ በዚህ ዓለም ላይ የምንሰራው በጎ ሥራ በእርግጥ ምንድነው?
እግዚአብሄር ጥሩ በሆነው ባህሪያችንና በሚታወሱ ምግባሮቻችን ይደሰታልን?
በዚህ ዓለም ላይ ምርጥ የሆነው የጽድቅ ሥራችን የውሃውንና የመንፈሱን
ወንጌል ማሰራጨት ነው፡፡ ልባችንንና ጉልበታችንን ሁሉ ይህንን የውሃና
የመንፈስ ወንጌል ለማሰራጨት ማዋላችን እርሱ ጽድቅ ነው፡፡ ምንም ዓይነት
ማንነት ይኑራችሁ እግዚአብሄር የሚደሰተው የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
በማሰራጨት ሥራ ላይ ስትሳተፉ ብቻ ነው፡፡
ኢየሱስ ሊጠመቅ ባለ ጊዜ ‹‹እንዲህ ጽድቅን ሁሉ መፈጸም ይገባናልና፡፡
ያን ጊዜ ፈቀደለት›› (ማቴዎስ 3፡15) ማለቱ ምን ማለት ነው? እነዚህ ኢየሱስ
ከአጥማቂው ዮሐንስ በተቀበለው ጥምቀት የሰራናቸውን ሐጢያቶች በሙሉ
መውሰዱን የሚነግሩን የምስክርነት ቃሎች ናቸው፡፡ ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ
በተጠመቀ ጊዜ የዓለም ሐጢያቶች በሙሉ ለአንዴና ለመጨረሻ ወደ ኢየሱስ
ተላለፉ፡፡ ኢየሱስ በጥምቀቱ አማካይነት የእናንተና የእኔ የሆኑትን የዓለም
ሐጢያቶች በሙሉ ተቀበለ፡፡ የኢየሱስ ሥጋ የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ
መውሰድ የቻለው በዚህ መንገድ ነው፡፡ እጆቹና እግሮቹ በመስቀል ላይ
ተቸንከረው ፍርድን የተቀበለው በዚህ መንገድ ነው፡፡ ይህ ማለት ግን ሐጢያት
ነፍሱ ውስጥ ነበረ ማለት አይደለም፡፡ ኢየሱስ ወደዚህ ዓለም መጥቶ
የእግዚአብሄርን ጽድቅ እንደተቀበለ በማመን ደህንነታችሁን መቀበል አለባችሁ፡፡
በአጥማቂው ዮሐንስም እንደዚሁ እጆቹን በመጫን ሐጢያቶችን ወደ ኢየሱስ
በማስተላለፍ ረገድ በዚህ ታላቅ አገልግሎት ውስጥ ተሳትፏል፡፡
አጥማቂው ዮሐንስ የእግዚአብሄር አገልጋይ ከሴት ከተወለዱት መካከል
እጅግ ታላቁ ወኪል ሆኖ ሁለት ነገሮችን አድርጓል፡፡
የመጀመሪያው የእያንዳንዱን ሰው ክፋት መጠቆም ነበር፡፡ ሰዎችን
‹‹ከእግዚአብሄር ውጭ ሌሎች አማልክቶችን ማምለክ ሐጢያት ነው›› እያለ
በመውቀስ ወደ እግዚአብሄር እንዲመለሱ ሰበከ፡፡ ሁለተኛው በዚህ ዓለም ላይ
የሚኖረውን የእያንዳንዱን ሰው ሐጢያቶች ለማስተላለፍ ኢየሱስን ማጥመቁ
ነበር፡፡ ይህ ለእናንተና ለእኔ የተሰጠን የእግዚአብሄር ጽድቅ ነው፡፡ ጌታ በዚህ
ዓለም ላይ ሊፈጽመው የመጣለት ዋና ጽድቅ ይህ ነው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


እውነተኛውን ወንጌልና የኢየሱስን የጽድቅ ምግባር አስፋፉ 63

ኢየሱስ የእናንተንና የእኔን ሐጢያቶች ለመውሰድና ለመሸከም ወደዚህ


ዓለም መጣ፡፡ በዚህ ዓለም ላይ ያለውን የእያንዳንዱን ሰው ሐጢያቶች፣
የእናንተን ሐጢያቶች፣ የዘሮቻችሁን ሐጢያቶች፣ የእነርሱን ዘሮች ሐጢያቶች፣
የወላጆቻችሁን ሐጢያቶች፣ የቅድመ አያቶቻችሁን ሐጢያቶች፣ ከአዳም ጀምሮ
ይህች ዓለም እስከምትቆይበት ምንም እንኳን ምድር መቼ መኖርዋን
እንደምታቆም ባናውቅም እስከ መጨረሻው ቀን ድረስ የሚኖረውን የእያንዳንዱን
ሰው ሐጢያቶች ለመውሰድ ተጠምቆዋል፡፡ ኢየሱስ ሐጢያቶቻችንን ሊደመስስና
ከሐጢያቶቻችን ሊያነጻን ተጠመቀ፡፡
‹‹ማጥመቅ›› የሚለው ቃል ‹‹በመንከር ወይም በማጥለም ማንጻት፣ ማጠብ፣
በውሃ ማጥራት፣ ራስን ማጠብ ወይም መታጠብ›› ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ኢየሱስን
የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ ለመውሰድ ተጠመቀ፡፡ ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ
አማካይነት ሐጢያቶችን በመውሰድ ሐጢያቶቻችንን አነጻ፡፡ ልብሶቻችሁን በውሃ
ስታጥቡ ቆሻሻችሁ እንደሚጠራ ሁሉ ኢየሱስም በአጥማቂው ዮሐንስ አማካይነት
ጥምቀትን በመቀበልና በልባችን ውስጥ ያሉትን ሐጢያቶች በሙሉ በመውሰድ
ሐጢያቶቻችንን አነጻ፡፡
ውድ ክርስቲያኖች በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ታምናላችሁን? --አዎ--፡፡
ጌታ የእግዚአብሄርን ጽድቅ ለመፈጸም ወደዚህ ምድር እንደመጣ፣
እንደተጠመቀና በመስቀል ላይ እንደሞተ ታምናላችሁን?
የገናን በዓል ስንቀበል ለእኛ ሲል ጽድቅን የፈጸመውን ጌታችንን ኢየሱስን
ማስታወስ ይገባናል፡፡ እንዲህ ተብሎዋል፡- ‹‹እንግዲህ የምትበሉ ወይም
የምትጠጡ ብትሆኑ ወይም ማናቸውን ነገር ብታደርጉ ሁሉን ለእግዚአብሄር
ክብር አድርጉት፡፡›› (1ኛ ቆሮንቶስ 10፡31) የገናን በዓል ስንቀበል በእርግጥ ጽድቅ
ምን እንደሆነ፣ እንዴት የጽድቅ ሕይወትን መኖር እንደምንችልና አጥብቀን
እንደምናምን ማሰብ ይገባናል፡፡ እናንተና እኔ በዚህ ዓለም ላይ በኢየሱስ ክርስቶስ
ያለንን እምነታችንን ጠብቀን አንድ ቀን ወደ እግዚአብሄር መመለስ ያስፈልገናል፡፡
በዚህ ዓለም ላይ ያለችንን አንዲት ሕይወት የጽድቅ ሥራን በመስራት ልንኖራት
ይገባናል፡፡ ስለ ጽድቅ ማሰብ ይገባናል፡፡ ለእግዚአብሄር ጽድቅ መኖር እንዳለብን
ወይም እንደሌለብን ማሰብ ከመቻላችን በፊት በመጀመሪያ ጽድቅ ራሱ ምን
ማለት እንደሆነ ማሰብ አለብን፡፡
እኔ ይህንን የገና በዓል ስቀበል እግዚአብሄርን በአያሌው አመሰግነዋለሁ፡፡
እናንተም ‹‹የጽድቅን ነገር›› እንድታደርጉ እመኛለሁ፡፡ በእግዚአብሄር ፊት ምን
ዓይነት የጽድቅ ነገር ልታደርጉ ትችላላችሁ? ሥጋችንን በማሳመር አንዳች የጽድቅ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


64 እውነተኛውን ወንጌልና የኢየሱስን የጽድቅ ምግባር አስፋፉ

ነገር ማድረግ እንችላለን? ይህንን አስቡት፡፡ በሥጋ የጽድቅ ነገሮችን ማድረግ


በአንዲት ቅጽበት የሚፈርስ ግምብ በአሸዋ ላይ እንደ መስራት ነው፡፡ በሕይወት
ዘመናችሁ ሁሉ ጥሩ ሰዎች ብትሆኑም እንኳን አንዲት የተሳሳተች እንቅስቃሴ
የምታደርጉ ከሆነ ሰውኛው ጽድቅ ሁሉ ይፈረካከሳል፡፡
እውነተኛ ጽድቅ እግዚአብሄር ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ያስወገደበትን
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በየቀኑ ማሰራጨት ነው፡፡ በዚህ የወንጌል
ስርጭት ውስጥ መሳተፍ ማለት በእግዚአብሄር ሥራ ውስጥ መሳተፍ ማለት
ነው፡፡ እናንተና እኔ የምንኖረው ለዚህ ሥራ ዓላማ ነው፡፡ ለካምፓኒ የምትሰሩ
ወይም የራሳችሁ ሥራ ያላችሁ ብትሆኑም ራሳችሁን ለዚህ የውሃና የመንፈስ
ወንጌል አሳልፋችሁ ብትሰጡ ጽድቅ ይሆንላችኋል፡፡ ይህንን ራሳችሁ ማድረግ
ባትችሉ በጸሎታችሁና በትናንሽ ቁሳቁሶች ብታግዙ ጽድቅ ይሆንላችኋል፡፡ ምንም
ነገር ብታደርጉ፤ ብትበሉ ወይም ብትጠጡ ይህንን ወንጌል ለማሰራጨት መኖር
ጽድቅ ነው፡፡
ውድ ክርስቲያኖች መጽሐፍ ቅዱስን ቁጥር በቁጥር ባንዘልቀውም እናንተ
እነዚህን ቃሎች በጥቅሉ ሰምታችኋል፡፡ እነዚህን ቃሎች እውነት ነው ብላችሁ
እንደምትቀበሉዋቸው አምናለሁ፡፡ ኢየሱስ ወደዚህ ዓለም መጥቶ ጽድቅን ሁሉ
እንደፈጸመ ታምናላችሁን? ጌታ የእናንተንና የእኔን ሐጢያቶች በሙሉ
ያስወገደውን እጅግ ታላቁን ሥራ እንደሰራ ታምናላችሁን? --አዎ--፡፡
ኢየሱስ ሐጢያቶችን በሙሉ መውሰዱ የሚያስደስት ነው፡፡ ‹‹ጽድቅን
ሁሉ›› በመፈጸሙም እጅግ አመስጋኞች ነን፡፡ እርሱ አንዳንድ ሐጢያቶችን ወስዶ
ሌሎች ሐጢያቶችን ቢተው ኖሮ ምንኛ አሳዛኝ በሆነ ነበር? ነገር ግን ምንም
ዓይነት ሐጢያት ስሩ ኢየሱስ ወስዶታል፡፡ ብርቱ እምነት ይኑራችሁ፡፡
እግዚአብሄርን በእምነታችሁ እንደምታስደስቱትና በእምነታችሁም የጽድቅ
ምግባሮችን እንደምታደርጉ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ በእምነታችሁ ሐጢያት
የሌለባችሁ ሰዎች እንደምትሆኑም ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ በእውነተኛው የውሃና
የመንፈስ ወንጌል በማመን መንፈስ ቅዱስን የተቀበላችሁ ሰዎች እንደሆናችሁም
ተስፋ አደርጋለሁ፡፡
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ስለማምን እግዚአብሄርን ደጋግሜ ከልቤ
አመሰግነዋለሁ፡፡ ውድ ክርስቲያኖች በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ታምናላችሁን?
--አዎ--፡፡ የገናን በዓል ስንቀበል ሁላችሁም በእውነተኛው ወንጌል ከልባችሁ
የምታምኑ ሰዎች እንደሆናችሁ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ ሐሌሉያ! 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ሐጢያቶቻችሁን ለመደምሰስ
የመጣው ኢየሱስ
‹‹ ማቴዎስ 3፡13-17 ››
‹‹ያን ጊዜ ኢየሱስ በዮሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ፡፡
ዮሐንስ ግን፡- እኔ በአንተ ልጠመቅ ያስፈልገኛል፤ አንተም ወደ እኔ ትመጣለህን?
ብሎ ይከለክለው ነበር፡፡ ኢየሱስም መልሶ፡- አሁንስ ፍቀድልኝ፤ እንዲህ ጽድቅን
ሁሉ መፈጸም ይገባናልና አለው፡፡ ያን ጊዜ ፈቀደለት፡፡ ኢየሱስም ከተጠመቀ
በኋላ ወዲያው ከውሃ ወጣ፤ እነሆም ሰማያት ተከፈቱ የእግዚአብሄርም መንፈስ
እንደ ርግብ ሲወርድ በእርሱ ላይም ሲመጣ አየ፤ እነሆም ድምጽ ከሰማያት
መጥቶ፡- በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው አለ፡፡››

የዘመኑ ክርስቲያኖች ኢየሱስ አዳኛቸው መሆኑን ቢናገሩም ብዙዎቹ


ኢየሱስ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ያዳነን
ጌታ መሆኑን አያውቁም፡፡ ስለዚህ ኢየሱስ በእርግጥም አዳኛቸው እንደሆነ በዚህ
የውሃና የመንፈስ ወንጌል ልናረጋግጥላቸው ያስፈልጋል፡፡ ሁሉም ሐጢያተኞች
ሆነው ስለተወለዱ ሁሉም ከሐጢያቶቻቸው ይነጹ ዘንድ በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል ማመን አለባቸው፡፡ ጌታን መገናኘት የሚችሉት እንዲህ ሲያምኑ ብቻ
ነው፡፡ የሐጢያቶቻችንን ስርየት የመቀበላችንና ዳግመኛ የመወለዳችን ጉዳይ
ያረፈው ኢየሱስ ክርስቶስን በትክክል በማወቅ ወይም አለማወቅና በማመን
ወይም አለማመን ነው፡፡
ለእኛ ወደ ሐጢያት ስርየት እውነት የመድረሻው እጅግ አስፈላጊው ቁልፍ
ጌታ ማን እንደሆነና ምን እንደሰራ ማወቁና ማመኑ ነው፡፡ ኢየሱስ ደቀ
መዛሙርቱን ‹‹እናንተስ እኔን ማን ትሉኛላችሁ?›› ብሎ በጠየቀ ጊዜ ጴጥሮስ
‹‹አንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሄር ልጅ ነህ›› በማለት መለሰ፡፡ ጴጥሮስ
እውነተኛ እምነቱን በዚህ መንገድ የመሰከረው እዚህ መረዳት ላይ ይደርስ ዘንድ
በእግዚአብሄር አብ ሰለተመራና ስለተስተማረ ነበር፡፡
እኛም የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በትክክል መረዳት አለብን፡፡ እንደ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


66 ሐጢያቶቻችሁን ለመደምሰስ የመጣው ኢየሱስ

ጴጥሮስም ስለ ጌታችን እውነተኛ የእምነት ምስክርነትን መስጠት መቻል


አለብን፡፡ እዚህ ላይ ልናስተውለው የሚገባን ነገር የኢየሱስ ጥምቀትና በመስቀል
ላይ ያፈሰሰው ደሙ ጌታችን ሐጢያቶቻችንን ለመሸከምና ለእነዚህ ሐጢያቶችም
ለመኮነን የከፈለው ትክክለኛ መስዋዕትነት መሆኑን መገንዘብና ማመን
የሚያስፈልገን መሆኑን ነው፡፡ እንዲህ ስናምን ሙሉ በሙሉ ከሐጢያቶቻችን
መዳን እንችላለን፡፡
የእግዚአብሄር ቃል ብሉይና አዲስ ኪዳናት ተብሎ በሁለት ክፍሎች
የተከፈለ ነው፡፡ አዲስ ኪዳን በብሉይ ኪዳን ውስጥ ተስፋ የተሰጡት ትንቢቶች
ፍጻሜ ነው፡፡ ደግሞም ጌታ ለደቀ መዛሙርቱ ተስፋ የሰጠው ሊመጣ ያለው
የአዲሱ ዓለም ትንቢታዊ አዋጅም ነው፡፡ ይህ አዲሱ ዓለም በቅርቡ በኢየሱስ
ክርስቶስ ይፈጸምልናል፡፡ ብሉይ ኪዳንም እንደዚሁ የሰውን ዘር ደህንነት፣
የእግዚአብሄር ልጅ ወደዚህ ዓለም እንደሚመጣ፣ በብሉይ ኪዳን የመስዋዕት
እንስሳ ላይ እጆች እንደሚጫኑና ደሙም እንደሚፈስስ፣ እርሱም በአጥማቂው
ዮሐንስ በመጠመቅ የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ በራሱ ላይ እንደሚወስድ፣
በመስቀል ላይ በመሞትም ደሙን እንደሚያፈስስና በዚህም የዓለምን
ሐጢያተኞች በሙሉ እንደሚያድን የሚናገረውን ትንቢት የመዘገበ እውነተኛ
የእግዚአብሄር ቃል ነው፡፡ ጌታችን በመገናኛው ድንኳን ውስጥ በተገለጠው
የመስዋዕት ስርዓት አማካይነት እርሱ ይህንን ተስፋ የሚፈጽም በእርግጥም
ይህንን የፈጸመ አዳኝ እንደሆነ ገልጦልናል፡፡ በሌላ አነጋገር መላው ብሉይ ኪዳን
በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በአዲስ ኪዳን ሁሉ ውስጥ በትክክል ተፈጽሞዋል፡፡
ኢየሱስ እውነተኛውን የውሃና የመንፈስ ወንጌል ስለሰጠን እርሱን አዳኛችን
አድርገን ስናምነው በብሉይ ኪዳን ውስጥ ትንቢት የተነገረለት አዳኝ በእርግጥም
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መሆኑን በትክክል ተረድተን እናምናለን፡፡
የብሉይ ኪዳኑ የመስዋዕት ስርዓት ሙሉ ወደሆነው የደህንነቱ እውነት
ለመድረስ የመረማመጃ ድንጋዮች ነበር፡፡ ይህም የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
በማወቅና በማመን ያለ ምንም መሳሳት የሐጢያቶቻችንን ስርየት እንድንቀበል
ያስችለናል፡፡ ኢየሱስ ለምን በአጥማቂው ዮሐንስ መጠመቅ እንደነበረበት በዚህ
ጥምቀት የተነሳም በመስቀል ላይ በመሞት እንዴት ደሙን ማፍሰስ እንደነበረበት
እንድናስተውል አስችሎናል፡፡ በትክክል መዳን የምንችለውና የራሱ የእግዚአብሄር
ልጆች የምንሆነው ይህንን የወንጌል እውነት በትክክል ስንረዳ ብቻ ነው፡፡ ኢየሱስ
የሰጠን የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል እውነት የእርሱን የአደባባይ አገልግሎቶች
በትክክል እንድንረዳና እንድናምንባቸው አስችሎናል፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ሐጢያቶቻችሁን ለመደምሰስ የመጣው ኢየሱስ 67

ኢየሱስ ወደዚህ ምድር በመጣ ጊዜ የፈጸማቸው


የውሃና የመንፈስ አገልግሎቶች እነዚህ ናቸው፡፡

የአዲስ ኪዳን ዋናው ቃል ይህ ነው፡፡ ኢየሱስ ወደዚህ ምድር በመምጣት


ከአጥማቂው ዮሐንስ በተቀበለው ጥምቀት የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ በራሱ
ላይ ወስዶ በደሙ የሐጢያትን ደመወዝ በሙሉ ከፈለ፡፡ የነፍሳችሁ ሕይወትና
ሞት ያረፈው ይህንን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በትክክል በመረዳታችሁና
በማመናችሁ ላይ ነው፡፡ 39ኙ የብሉይ ኪዳን መጽሐፎችና 27ቱ የአዲስ ኪዳን
መጽሐፎች በሙሉ ይህንን ወሳኝ የሆነውን የውሃና የመንፈስ ወንጌል እውነት
በዝርዘር ያብራራሉ፡፡
በብሉይ ኪዳን የመገናኛ ድንኳን ውስጥ ለእስራኤል ሕዝብ ሐጢያቶች
የቀረበው የመስዋዕት እንስሳ ሐጢያቶቻቸውን አስወግዶላቸዋል፡፡ ምክንያቱም
እጆቻቸውን በራሱ ላይ ጭነው ደሙንና ሥጋውን ለእግዚአብሄር አቅርበዋልና፡፡
እኛም የሐጢያቶቻችንን ስርየት በትክክል መረዳትና በእርሱም ማመን
የምንችለው ይህንን የብሉይ ኪዳን የመስዋዕት ስርዓትና በአዲስ ኪዳን የሆነውን
የኢየሱስን ጥምቀትና ያፈሰሰውን ደም በሚያነጻጽር መረዳት ላይ ስንደርስ ብቻ
ነው፡፡ በሌላ አነጋገር ለመስዋዕት የቀረበው ጠቦት ወይም ፍየል በእጆቻቸው
መጫን ወይም በሊቀ ካህኑ እጅ መጫን የሐጢያተኞችን ሐጢያቶች እንደተቀበለ
ሁሉ ኢየሱስም የዓለምን ሐጢያቶች ተቀብሎ በመስቀል ላይ ደሙን በማፍሰስ
የሞተው በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቁ ነበር፡፡
የመጽሐፍ ቅዱስን ዝርዝሮች በሙሉ ባናውቅም ከብሉይ ኪዳን የመስዋዕት
ስርዓት ጋር በአዲስ ኪዳን የተነጻጸረውን የኢየሱስን ጥምቀትና የፈሰሰውን ደም
ግልጽና ተጨባጭ በሆነ መንገድ ስንረዳ የሐጢያትን ስርየት በእምነት መቀበል
እንችላለን፡፡ እግዚአብሄር የሰጠውን የሐጢያት ስርየት ለመቀበል በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል ማመን አለብን፡፡
የተጻፈው የእግዚአብሄር ቃል እንደሚናገረው እርሱ ሐጢያቶቻችንን
በሙሉ ማስወገድ የሚችለውን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ጻፈ፡፡ እርሱ
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ለሚያምኑ መዕመናኖች ክህነትን በአደራ
ሰጥቶዋቸዋል፡፡ ይህንን ያደረገው በዚህ ምድር ላይ የሚኖር እያንዳንዱ ሰው
ሐጢያቶችን በእምነት እንዲያነጻ ነው፡፡ በብሉይ ኪዳን ይህ ክህነት ተስፋ
የተሰጠው ለሌዊ ዘሮች ብቻ ነበር፡፡ የእስራኤሎችን ሐጢያቶች የሚያነጹትንና
የእግዚአብሄርን ንጹህ ፍቅር የሚፈጽሙትን የአማላጅነት ምግባሮች የተቀበሉት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


68 ሐጢያቶቻችሁን ለመደምሰስ የመጣው ኢየሱስ

እነዚህ የሌዊ ዘሮች ነበሩ፡፡ ስለዚህ በዚህ የአዲስ ኪዳን ዘመን ይህንን ክህነት
በእግዚአብሄር ፊት በትክክል ለመፈጸም እኛ የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል
አማኞች የብሉይ ኪዳንን የመስዋዕት ስርዓት መረዳትና የኢየሱስን ጥምቀትና
ስቅለቱን ይበልጥ በጥልቀት መረዳት አለብን፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ምድር ላይ ከተወለደ አሁን 2005 ዓመት
ሆኖታል፡፡ ይህ ኢየሱስ አዳኝ ሆኖ ወደዚህ ምድር መጣ፡፡ በአጥማቂው ዮሐንስ
በመጠመቅና ደሙን አፍስሶ በመሰቀል ሐጢያቶቻችንን ለዘላለም አነጻ፡፡ ስለዚህ
ኢየሱስ የተወለደበት ዓመት የዓለም የዘመን ቅደም ተከተል ሰሌዳ ማጣቀሻ
መሆኑ ተገቢ ነው፡፡ ይህም የነገሮች ሁሉ ጅማሬ ኢየሱስ ክርስቶስ መሆኑን
ያመለክታል፡፡ ምክንያቱም በእኛ እሳቤ ኢየሱስ ይህንንን ዩኒቨርስ የፈጠረ
አምላክና በውሃውና በደሙ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ የደመሰሰ አዳኝ ነው፡፡
እርሱ የዩኒቨርስ ታሪክ ማዕከልም ነው፡፡

የዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ሐጢያቶቻችን መተላለፋቸውን


አይነግረንምን?

በዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ላይ እንዲህ ተጽፎዋል፡- ‹‹ያን ጊዜ


ኢየሱስ በዮሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ፡፡ ዮሐንስ ግን፡- እኔ
በአንተ ልጠመቅ ያስፈልገኛል፤ አንተም ወደ እኔ ትመጣለህን? ብሎ ይከለክለው
ነበር፡፡ ኢየሱስም መልሶ፡- አሁንስ ፍቀድልኝ፤ እንዲህ ጽድቅን ሁሉ መፈጸም
ይገባናልና አለው፡፡ ያን ጊዜ ፈቀደለት፡፡ ኢየሱስም ከተጠመቀ በኋላ ወዲያው
ከውሃ ወጣ፤ እነሆም ሰማያት ተከፈቱ የእግዚአብሄርም መንፈስ እንደ ርግብ
ሲወርድ በእርሱ ላይም ሲመጣ አየ፤ እነሆም ድምጽ ከሰማያት መጥቶ፡- በእርሱ
ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው አለ፡፡››
ሁላችንም ወደዚህ ዓለም ከተወለድንበት ቀን ጀምሮ አስራ ሁለት ዓይነት
ሐጢያቶችን ይዘን የተወለድን የአዳም ዘሮች ስለሆንን ሁላችንም ስለ
ሐጢያቶቻችን ከመሞትና በእነርሱ የተነሳም በእግዚአብሄር ፊት ከመኮነን በቀር
ምርጫ አልነበረንም፡፡ (ማርቆስ 7፡21-23) በሐጢያቶቻችን ምክንያት በፍርሃት
ከመሞትና ያለ ተስፋ ከመሞት መሸሽ አልቻልንም፡፡ ሁላችንም አስፈሪ ለሆነው
የሲዖል እሳት የታጨን ነበርን፡፡ ነገር ግን እኛ እኛ በዘላለም ጥፋት ጠርዝ ላይ
ሳለን ኢየሱስ በምድር ላይ ተወለደ፡፡ እርሱ እኛን ሰዎችን ከዓለም ሐጢያቶች

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ሐጢያቶቻችሁን ለመደምሰስ የመጣው ኢየሱስ 69

ሁሉ ለማዳን ሲል የባርያን መልክ ይዞ ተወለደ፡፡ ጌታ ወደዚህ ምድር መጥቶ


የሰው ሥጋ የለበሰው እናንተንና እኔን የመሳሰልን ሰዎችን ከዚህ ዓለም የዘላለም
ሐጢያቶች ለማዳን ነበር፡፡
ጌታችን 30 ዓመት ሲሆነው በዮርዳኖስ ወንዝ በአጥማቂው ዮሐንስ
በመጠመቅ የዓለምን ሐጢያቶች ተሸከመ፡፡ በዚያን ጊዜ አጥማቂው ዮሐንስ ብዙ
እስራኤሎችን ወደ እግዚአብሄር እንዲመለሱ የሚያደርጋቸውን የንስሐ ጥምቀት
እያጠመቀ ነበር፡፡ ነገር ግን አጥማቂው ዮሐንስ ለኢየሱስ የሰጠው ጥምቀት
የእግዚአብሄርን ጽድቅ ሁሉ የሚፈጽምበት ጥምቀት ነበር፡፡ ይህ ጥምቀት የዚህን
ዓለም ሐጢያቶች በሙሉ የእግዚአብሄር በግ ወደሆነው የኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋ
የሚያስተላልፍ ጥምቀት ነበር፡፡
አጥማቂው ዮሐንስ የሰው ዘር ወኪል ነበር፡፡ (ማቴዎስ 11፡11) እርሱ ከሊቀ
ካህን ቤተሰብ የተወለደ በመጽሐፍ ቅዱስም ድጋፍ ያለው ካህን የመጨረሻው
የብሉይ ኪዳን ነቢይ በመሆኑ የብሉይ ኪዳን ዘመን የመጨረሻው ካህን ሆኖ
አገልግሎዋል፡፡ (ሉቃስ 1፡1-21) ስለዚህ ሁላችንም የኢየሱስን አገልግሎት
ለመረዳት ከመሞከራችን በፊት የአጥማቂውን ዮሐንስን አገልግሎት ከኢየሱስ
አገልግሎት ጋር አያይዘን ልንረዳው የምንችለውና የሐጢያትን ስርየት
የእውነተኛውን ስርየት ምሉዕ እውነት በሚገባ የምናስተውለው የአጥማቂውን
ዮሐንስን አገልግሎት በጥልቀት ስናውቀው ነው፡፡
ብሉይና አዲስ ኪዳናት ስለ አጥማቂው ዮሐንስ አገልግሎት ሰፋ ያሉ
ትንቢቶችንና ጥልቅ የሆኑ ማብራሪያዎችን አቅርበዋል፡፡ ማቴዎስ 11፡11 ስለ
አጥማቂው ዮሐንስ የሚከተለውን ጽፎዋል፡- ‹‹እውነት እላችኋለሁ፤ ከሴቶች
ከተወለዱት መካከል ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ አልተነሳም፡፡›› በብሉይ ኪዳን
በሚልክያስ መጽሐፍ ምዕራፍ 3 እና 4 ላይ እንዲህ ይላል፡- ‹‹እነሆ ታላቁና
የሚያስፈራው የእግዚአብሄር ቀን ሳይመጣ ነቢዩን ኤልያስን እልክላችኋለሁ፡፡››
ቁጥር 6 ደግሞ እንዲህ ይላል፡- ‹‹መጥቼም ምድርን በእርግማን እንዳልመታ
እርሱ የአባቶችን ልብ ወደ ልጆች የልጆችንም ልብ ወደ አባቶች ይመልሳል፡፡››
(ሚልክያስ 4:5) መጽሐፍ ቅዱስ በብሉይ ኪዳን የሚልክያስ መጽሐፍ ውስጥ
የተተነበየለት ይህ ኤልያስ የሰውን ዘር ሐጢያቶች፤ የዓለምን ሐጢያቶች
በጥምቀቱ አማካይነት ያስተላለፈው አጥማቂው ዮሐንስ እንጂ ሌላ ማንም
እንዳልሆነ ያስተምረናል፡፡
በአዲስ ኪዳን ውስጥ ኢየሱስ ራሱ አጥማቂው ዮሐንስ ‹‹ከሴቶች
ከተወለዱት ሁሉ እንደሚበልጥ›› እና ‹‹ሊመጣ ያለው ኤልያስ›› (ማቴዎስ 11፡11-

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


70 ሐጢያቶቻችሁን ለመደምሰስ የመጣው ኢየሱስ

14) እንደነበር ተናግሮዋል፡፡ ታዲያ አጥማቂው ዮሐንስ ወደዚህ ዓለም በመጣ


ጊዜ የፈጸመው ሚና ምን ነበር? የሰው ዘር ወኪል እንደመሆኑ ኢየሱስን
በማጥመቅ የዓለምን ሐጢያቶች ያስተላለፈው አጥማቂው ዮሐንስ ነበር፡፡
የሐጢያተኞችን ልብ ወደ እግዚአብሄር የመለሰበትንና እንደዚሁም የዓለምን
ሐጢያቶች ወደ እርሱ ለማስተላለፍ ኢየሱስን ያጠመቀበትን አገልግሎት
የፈጸመው እርሱ ነበር፡፡ አጥማቂው ዮሐንስ በእግዚአብሄር ችሮታ ከሊቀ ካህኑ
አሮን ቤተሰብ የተወለደ ሰው ሆኖ የሊቀ ካህን ተግባራቶችን ለመፈጸም ብቁ
ሆነ፡፡ (ሉቃስ 1፡1-10) ስለዚህ የእያንዳንዱን ሰው ሐጢያቶች በጥምቀቱ
አማካይነት ወደ ኢየሱስ የማስተላለፍ ክህነታዊ ሐላፊነቱን የተወጣው አጥማቂው
ዮሐንስ ነበር፡፡
አጥማቂው ዮሐንስ ወደዚህ ምድር የመጣበት ምክንያት ኢየሱስን
በማጥመቅ የዓለምን ሐጢያቶች ወደ እርሱ ለማስተላለፍ ነበር፡፡ እግዚአብሄርን
የተዉትን ሰዎች የወቀሰውና ኢየሱስ ክርስቶስ የዓለምን ሐጢያቶች በጥምቀቱና
ባፈሰሰው ደሙ የሚደመስስ የእግዚአብሄር ልጅ የመስዋዕቱ በግ እንደነበር
የመሰከረላቸውም አጥማቂው ዮሐንስ ነበር፡፡ ኢየሱስ የዚህን ዓለም ሐጢያቶች
የሚያስወግድ የመስዋዕት ቁርባን ሆኖ ወደ አጥማቂው ዮሐንስ በመምጣትና
በእርሱ በመጠመቅ በዘሌዋውያን መጽሐፍ ውስጥ የተጻፈውን በመስዋዕት
እንስሶች ራስ ላይ እጆችን ስለ መጫን የሚናገረውን ትንቢት ፈጸመ፡፡
(ዘሌዋውያን 1፡3-5)
አጥማቂው ዮሐንስ ኢየሱስን ያጠመቀውና የዚህን ዓለም ሐጢያቶች ወደ
እርሱ ያስተላለፈው በዚህም የእግዚአብሄር አብ ፈቃድ የሆነውን የአምላክ ጽድቅ
የፈጸመው ለዚህ ነው፡፡ ኢየሱስ ከሴቶች ከተወለዱት ሁሉ መካከል በሚበልጠው
ሰው በመጠመቅ በዚህ ዓለም ላይ የእያንዳንዱን ሰው ሐጢያቶች የተቀበለ
የእግዚአብሄር በግ ነበር፡፡ በሌላ አነጋገር ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ
የተጠመቀው የዚህን ዓለም ሐጢያቶች ለአንዴና ለመጨረሻ መቀበል ስለፈለገ
ነበር፡፡
አጥማቂው ዮሐንስ ለእስራኤል ሕዝብ የንስሐ ጥምቀትን እየሰጠ ሳለ
ኢየሱስ ወደ እርሱ መጥቶ ‹‹አጥምቀኝ፤ በአንተ ልጠመቅና የእግዚአብሄርን ጽድቅ
ሁሉ ልፈጽም ይገባኛልና›› (ማቴዎስ 3፡15) አለው፡፡ ኢየሱስ የዚህን ዓለም
ሐጢያቶች በሙሉ ለመሸከም በአጥማቂው ዮሐንስ መጠመቅ ነበረበት፡፡
ምክንያቱም በዚህ ዓለም ላይ የሚኖረውን የእያንዳንዱን ሰው ሐጢያቶች
የወሰደው በጥምቀት አማካይነት ነበርና፡፡ ኢየሱስ ከአጥማቂው ዮሐንስ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ሐጢያቶቻችሁን ለመደምሰስ የመጣው ኢየሱስ 71

በተቀበለው በዚህ ጥምቀት አማካይነት የዚህን ዓለም ሐጢያቶች በሙሉ


በመሸከም፣ በመሰቀል፣ እስከ ሞት ድረስ ደሙን በማፍሰስና በሦስት ቀናት
ውስጥ ከሙታን በመነሳት ዘላለማዊ አዳኝ አምላክ ሆነ፡፡
ስለዚህ ኢየሱስ የተጠመቀው የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ መፈጸም
ስለሚገባው ነበር፡፡ (ማቴዎስ 3፡15) አጥማቂው ዮሐንስም ያጠመቀው በዚህ
የእግዚአብሄር ፈቃድ ነው፡፡ በሌላ አነጋገር ኢየሱስ መንፈሳዊውን እጆች መጫን
ልክ በብሉይ ኪዳን ውስጥ እንዳለው የመስዋዕት እንስሳ ደሙን አፈሰሰ፡፡
በዘሌዋውያን 16 ሁለት ለመስዋዕት የቀረቡ ፍየሎች በሊቀ ካህኑ እጆች መጫን
የሕዝቡን ዓመታዊ ሐጢያቶች እንደተቀበሉ እናያለን፡፡ ልክ እንደዚሁ ኢየሱስም
ከአጥማቂው ዮሐንስ በተቀበለው ጥምቀት አማካይነት የዚህን ዓለም ሐጢያቶች
በሙሉ ለአንዴና ለመጨረሻ ተቀብሎ ክቡር ደሙን በመስቀል ላይ አፈሰሰ፡፡
ስለዚህ ኢየሱስ በጥምቀት ሐጢያቶቻቸውን በራሱ ላይ የተሸከመ የሰው ዘር
አዳኝ ሆነ፡፡
ኢየሱስ የእግዚአብሄር አብ አንድያ ልጅና የእግዚአብሄር መንግሥት
ሰማያዊ ሊቀ ካህን ነው፡፡ ስለዚህ የሰው ዘር ወኪል የሆነው አጥማቂው ዮሐንስ
ምድራዊ ሊቀ ካህን ሆኖ ክህነቱን ይፈጽም ዘንድ የመንግሥተ ሰማይ ሊቀ ካህን
ከሆነው ኢየሱስ ጋር መገናኘትና የእግዚአብሄር አብን ጽድቅ ሁሉ መፈጸም
ነበረበት፡፡ የእግዚአብሄር ንጹህ ፍቅር በኢየሱስ ጥምቀት አማካይነት ታወቀ፡፡
ታዲያ በአጥማቂው ዮሐንስና በኢየሱስ መካከል ታላቁ ማነው? ሰማያዊው
ሊቀ ካህን ኢየሱስ ከአጥማቂው ዮሐንስ እንደሚበልጥ እርግጥ ነው፡፡ ኢየሱስ
ከማንኛውም ሌላ ሰው ይበልጥ የላቀ ነው፡፡ ኢየሱስ ከማነኛውም ሌላ ሰው
ይበልጥ የላቀ ነው፡፡ ምክንያቱም እርሱ ራሱ መላውን ዩኒቨርስ የፈጠረ አምላክ
ነውና፡፡ የሰውን ዘር ከዓለም ሐጢያቶች ለማዳን ወደዚህ ምድር የመጣ
የእግዚአብሄር ልጅም ነው፡፡ ኢየሱስ የሰውን ዘር ከዓለም ሐጢያቶች ለማዳን
ወደዚህ ምድር መጥቶ በአጥማቂው ዮሐንስ ተጠመቀ፡፡ ኢየሱስ እንደ እኛ ተራ
ፍጡር አይደለም፡፡
ኢየሱስ ከአጥማቂው ዮሐንስ በተቀበለው ጥምቀት ውስጥ ለእግዚአብሄር
የተለየ ሥራ ምሳሌ የሚሆን ነገር አለ፡፡ ኢየሱስ ለመጠመቅ ወደ አጥማቂው
ዮሐንስ በመጣ ጊዜ አጥማቂው ዮሐንስ በመጣ ጊዜ አጥማቂው ዮሐንስ ኢየሱስን
‹‹እኔ በአንተ ልጠመቅ ያስፈለገኛል፤ አንተ ወደ እኔ ትመጣለህን?›› አለው፡፡ ከዚህ
ማየት እንደምንችለው አጥማቂው ዮሐንስ በመጀመሪያ ኢየሱስን በማጥመቅ
ሐጢያቶችን ሁሉ ወደ እርሱ ለማስተላለፍ አቅማምቶ ነበር፡፡ በመጨረሻ ግን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


72 ሐጢያቶቻችሁን ለመደምሰስ የመጣው ኢየሱስ

እምቢ ማለት አልቻለም፡፡ ምክንያቱም ኢየሱስ ራሱ በእርሱ ሊጠመቅና በዚህም


የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ ሊሸከም ፈልጎዋልና፡፡ ስለዚህ አጥማቂውን ዮሐንስን
‹‹አሁንስ ፍቀድልኝ እንዲህ ጽድቅን ሁሉ መፈጸም ይገባናል›› (ማቴዎስ 3፡15)
በማለት እንዲያጠምቀው አዘዘው፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስ በአጥማቂው ዮሐንስ ከመጠመቁ በፊት አህዛቦችና
አይሁዶች ሁሉም በልቦቻቸው ውስጥ ሐጢያቶች ነበሩባቸው፡፡ ስለዚህ
ለሐጢያቶቻቸው ከመኮነንና ከመጥፋት ማምለጥ አልቻሉም፡፡ ሰው ሁሉ በዚህ
ዓለም ላይ በእግዚአብሄር ላይ ሐጢያት በመስራቱ ከጥፋት ማምለጥ የማይችል
ተሰባሪ ፍጡር መሆን እናውቃለን፡፡ ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅ
የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ በራሱ ላይ የወሰደው ለዚህ ነው፡፡ ጌታችን ይህንን
ሥራ በአጥማቂው ዮሐንስ በኩል መፈጸም ነበረበት፡፡ ኢየሱስ የእነዚህን ሰዎች
ሐጢያቶች በሙሉ በራሱ ላይ ይወስድ ዘንድ የእግዚአብሄርን ጽድቅ ሁሉ
የሚፈጽመውን ጥምቀት ከአጥማቂው ዮሐንስ መቀበል ነበረበት፡፡
‹‹አሁንስ ፍቀድልኝ እንዲህ ጽድቅን ሁሉ መፈጸም ይገባናልና፡፡›› (ማቴዎስ
3፡15) እዚህ ላይ ‹‹ጽድቅን ሁሉ›› የሚለው በግሪክ ‹‹πᾶσαѵ
δικαιοσύѵηѵ›› (pasan dikaiosunen) ነው፡፡ ‹‹ዲካዮሱን›› የሚለው ይህ
ቃል ‹‹እጅግ ያማረ ሁኔታ›› ወይም ‹‹ጽድቅ›› ወይም ‹‹ትክክለኝነት›› ማለት ነው፡፡
የብሉይ ኪዳን የመስዋዕት ቁርባን የእስራኤላውያኖችን ሐጢያቶች በሙሉ
በመሸከም እንደደመሰሰላቸው ሁሉ በአዲስ ኪዳንም ኢየሱስ ወደዚህ ምድር
መጥቶ በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅ፣ ሐጢያቶቻቸውን በሙሉ በራሱ ላይ
በመሸከም የሰውን ዘር ሐጢያቶች በሙሉ አንጽቷል፡፡ ኢየሱስ ወደዚህ ምድር
የመጣው የእግዚአብሄር በግ ሆኖ ነው፡፡ ለእኛ ሐጢያቶች እንዲህ የመስዋዕት
ቁርባን በመሆን ከዓለም ሐጢያቶች አድኖናል፡፡ አዳኙ ሰው የሆነበትና
በአጥማቂው ዮሐንስ ለመጠመቅ የፈለገበት ምክንያት ያረፈው በእግዚአብሄር
ጽድቅ መፈጸም ላይ ነው፡፡
ኢየሱስ እንዲህ አለ፡- ‹‹አሁንስ ፍቀድልኝ እንዲህ ጽድቅን ሁሉ መፈጸም
ይገባናልና፡፡›› በመንፈሳዊ አነጋገር ይህ ማለት ‹‹በአንተ በመጠመቅ የእያንዳንዱን
ሰው ሐጢያቶች ለአንዴና ለመጨረሻ በራሴ ላይ መውሰድና ሁሉንም ማንጻት
ለእኔ ተገቢ ነው›› ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ሁላችንም በዚህ ኢየሱስ በተቀበለው
በዚህ ጥምቀት ውስጥ የተገለጠውን እውነት የሚያውቅና የሚያምን እምነት
ሊኖረን ይገባል፡፡ ኢየሱስ ከአጥማቂው ዮሐንስ የተቀበለው ጥምቀትና በመስቀል
ላይ ያፈሰሰው ደም ያመጣውን ውጤት ማወቅ አለብን፡፡ ይህንንም በትክክል

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ሐጢያቶቻችሁን ለመደምሰስ የመጣው ኢየሱስ 73

መረዳትና ማመን አለብን፡፡


የፕሪስባይቴርያን ቤተክርሰቲያን የተከለሰ የጥምቀት ትርጉም በመስጠቷ
የእርስዋ አባሎች በአብ፣ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም በውሃ ይረጫሉ እንጂ
ሙሉ በሙሉ በመጥለም አያጠምቁም፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የዚህ ዓይነቱ
ጥምቀት የሚሰጠው እንደ ምድረ በዳ ባሉ የውሃ እጥረት ባለባቸው ስፍራዎች
ነበር፡፡ ለምሳሌ ፊልጶስ ኢትዮጵያዊውን ጃንደረባ ያጠመቀው በዚህ መንገድ
ነው፡፡ ነገር ግን ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ በተጠመቀ ጊዜ ከወገቡ በታች
ጠልቆ በዮርዳኖስ ወንዝ ውስጥ ቆሞ ነበር፡፡ ኢየሱስ ከዮሐንስ የተቀበለው
ጥምቀት አጥማቂው ዮሐንስ ሁለት እጆቹን በኢየሱስ ራስ ላይ ጭኖ በውሃ
ውስጥ አጥልሞ ከውሃው ውስጥ ያወጣበት ጥምቀት ነበር፡፡ ይህ ጥምቀት
በብሉይ ኪዳን ሊቀ ካህኑ ሁለት እጆቹን በመስዋዕቱ ራስ ላይ በመጫን
የእስራኤሎችን ሐጢያቶች ካስተላለፈበት የብሉይ ኪዳን እጆች መጫን ጋር
ተመሳሳይ ነበር፡፡ ኢየሱስ ከአጥማቂው ዮሐንስ የተቀበለው ጥምቀት የዓለምን
ሐጢያቶች በመቀበል ሁሉንም የተሸከመበት ጥምቀት ነበር፡፡
አጥማቂው ዮሐንስ ኢየሱስን ለማጥመቅ እጆቹን በራሱ ላይ የመጫኑ
እውነታ ፍቺ ምንድነው? በብሉይ ኪዳን ‹‹እጆችን የመጫን›› ስርዓት
የሚፈጸመው በሚከተሉት ሁኔታዎች ነበር፡፡ 1) የአንድን ሰው ሐጢያቶች
ለመስዋዕት ወደቀረበው እንስሳ ለማስተላለፍ (ዘሌዋውያን 1፡1-10፤4፡1-25) 2)
የእግዚአብሄርን አገልጋዮች ለመቀደስ (ዘሁልቁ 8፡10፤ 27፡18) 3) ስድብን ወደ
ተሳዳቢው ለመመለስ (ዘሌዋውያን 24፡14)፡፡
ጉዳዩ ምን ይሁን ‹‹እጆችን መጫን›› ‹‹አንድን ነገር የማስተላለፍ›› መንገድ
ነበር፡፡ ለምሳሌ አንድ አገልጋይ መጋቢ ሆኖ ሲቀደስ የበላይ መጋቢዎች
እጆቻቸውን በራሱ ላይ ይጭናሉ፡፡ ይህም እግዚአብሄር የሰጣቸው ሥልጣንና
ስጦታዎች አሁን ለአዲሱ መጋቢም መሰጠታቸውን ያመለክታል፡፡ ይህ ማለት
በእጆች መጫን ለበላይ መጋቢዎች የተፈቀዱላቸው ሥልጣንና ስጦታዎች በሙሉ
አሁን ለአዲሱ መጋቢም ተለግሰዋል ማለት ነው፡፡
ነገር ግን እጅግ ልዩ የሆነው ‹‹እጆችን የመጫን›› ጉዳይ ሐጢያቶችን ወደ
መስዋዕቱ እንስሳ ለማስተላለፍ ይፈጸም የነበረው የመስዋዕት ስርዓት ነበር፡፡
ከዚህ ጋር በተዛመደ መልኩ አጥማቂው ዮሐንስ እጆቹን በኢየሱስ ራስ ላይ
የጫነው የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ ለማስተላለፍ ነበር፡፡ እስከ ዛሬ ድረስ
መጋቢዎች ምዕመናንን ሲያጠምቁ በመደበኛነት እጆቻቸውን በራሶቻቸው ላይ
የሚጭኑት ለዚህ ነው፡፡ ይህ ለምን ይደረጋል? ይህ እነርሱ ኢየሱስ በጥምቀቱ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


74 ሐጢያቶቻችሁን ለመደምሰስ የመጣው ኢየሱስ

አማካይነት የዓለምን ሐጢያቶች መሸከሙንና እነርሱም መጠመቃቸውን


የሚያሳዩበት የእምነታቸው ምልክት ነው፡፡
ኢየሱስ አዳኝ ሆኖ የሰው ዘር ወኪል በሆነው በአጥማቂው ዮሐንስ
በመጠመቅ የዓለምን ሐጢያቶች ወሰደ፡፡ ይህም የብሉይ ኪዳኑ ሊቀ ካህን
እጆቹን በመስዋዕቱ ራስ ላይ በመጫን የእስራኤልን ሕዝብ ሐጢያቶች
ከሚያስተላልፍበት ሒደት ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡ (ዘሌዋውያን 16፡21)
ኢየሱስ የሰው ዘር ወኪል በሆነው በአጥማቂው ዮሐንስ ከተጠመቀ በኋላ
በውሃ ውስጥ ጠልሞ ከዚያም ከውሃው ውስጥ ወጣ፡፡ በመንፈሳዊ አነጋገር ይህ
ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅ የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ በራሱ ላይ
በመውሰዱ እውነታ ቃሉ በመስቀለ ላይ እንደሞተ፣ ዳግመኛም ከሙታን
እንደተነሳና በዚህም ፍጹም የሆነ አዳኝ እንደሆነ ያመለክታል፡፡ ይህም ኢየሱስ
በጥምቀቱ አማካይነት የዚህን ዓለም ሐጢያቶች እንደተቀበለ፣ ሐጢያቶቻችንን
እንደተሸከመና በመስቀል ላይም እስከ ሞት ድረስ ደሙን በማፍሰስ ለሐጢያቶች
ሁሉ እንደተኮነነ ይነግረናል፡፡
በአጭሩ በእጆች መጫን የተደረገው የኢየሱስ ጥምቀት እርሱ የዓለምን
ሐጢያቶች እንደተቀበለ ያመለክታል፡፡ በውሃ ውስጥ መጥለሙ በመስቀል ላይ
መሞቱን ሲያመለክት ከውሃ ውስጥ መውጣቱም ትንሳኤውን ያመለክታል፡፡
በሌላ አነጋገር ኢየሱስ እኛ ራሳችን ልንፈጽማቸው የሚገቡትን የሐጢያትና የሞት
ሕግ መጠይቆች በይፋ በማሟላት የእግዚአብሄርን ጽድቅ ሁሉ ስለ ሁላችን
ፈጸመ፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ የሚለው ለዚህ ነው፡- ‹‹ከሥጋ የተነሣ ስለደከመ
ለሕግ ያልተቻለውን እግዚአብሄር የገዛ ልጁን በሐጢአተኛ ሥጋ ምሳሌ
በሐጢአትም ምክንያት ልኮ አድርጎአልና፡፡ እንደ መንፈስ ፈቃድ እንጂ እንደ ሥጋ
ፈቃድ በማንመላለስ በእኛ የሕግ ትዕዛዝ ይፈጸም ዘንድ ሐጢአትን በሥጋ
ኮነነ፡፡›› (ሮሜ 8፡3-4)
በዚህ ጊዜ ኢየሱስ ከውሃ ውስጥ ሲወጣ እግዚአብሄር አብ የሰማይን በሮች
ከፍቶ ‹‹በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው›› (ማቴዎስ 3፡17) አለ፡፡
እግዚአብሄር የሰውን ዘር ሐጢያቶች በሙሉ በልጁ በኩል ለመደምሰስ ያቀደው
ከፍጥረት በፊት ነበር፡፡ ይህ ሥራም ወደዚህ ምድር መጥቶ በአጥማቂው ዮሐንስ
በመጠመቅ፣ የሰውን ዘር ሐጢያቶች በመውሰድ፣ በመስቀል ላይም እስከ ሞት
ድረስ ደሙን በማፍሰስና በዚህም በእርሱ የሚያምኑትን ከሐጢያት በማዳን
በልጁ ተፈጸመ፡፡ ጌታችን በጥምቀቱና ደሙን በማፍሰሱ የእግዚአብሄርን ፈቃድ
ለአንዴና ለመጨረሻ ፈጸመ፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ሐጢያቶቻችሁን ለመደምሰስ የመጣው ኢየሱስ 75

ስለዚህ ኢየሱስ በጥምቀቱ የሰውን ዘር ሐጢያቶች በሙሉ በራሱ ላይ


በመውሰድ የአብን ፈቃድ በታዘዘ ጊዜ እግዚአብሄር አብ ‹‹ይህንን ያደረገው
በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ነው›› በማለት በልጁ በኢየሱስ ተደሰተ፡፡
ክርስቲያኖች ኢየሱስ ከአጥማቂው ዮሐንስ በተቀበለው ጥምቀትና እንደዚሁም
ለሐጢያቶቻችን ሁሉ ኩነኔ በመስቀል ላይ ያፈሰሰውን ደሙን ማመን ያለባቸው
ለዚህ ነው፡፡ እግዚአብሄር አብ የሰማይን ደጆች ከፍቶ አሁን የተጠመቀው ደስ
የሚሰኝበት ልጁ እንደነበር የተናገረው ለዚህ ነው፡፡

‹‹እነሆ የዓለምን ሐጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሄር በግ!››

እናንተና እኔ ወደ ዮሐንስ 1፡29 ተመልሰን ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ


በመጠመቅ ለአንዴና ለዘላለም የዓለምን ሐጢያቶች መውሰዱን
የሚያረጋግጠውን ማስረጃ መረዳትና ይህንንም በልባችን ማመን አለበብን፡፡
አጥማቂው ዮሐንስ ያጠመቀው ኢየሱስ ከጥምቀቱ በኋላ በነጋታው ወደ እርሱ
ሲመጣ አይቶ፡- ‹‹እነሆ የዓለምን ሐጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሄር በግ!››
ሲል መሰከረ፡፡
በሌላ አነጋገር አጥማቂው ዮሐንስ ‹‹በጥምቀቱ ሐጢያቶቻቸውን
የተቀበለውና ስለ እነርሱም ደሙን ያፈሰሰው የሰው ዘር አዳኝ ሌላ ሳይሆን
ኢየሱስ ነው›› ብሎ መሰከረ፡፡ አጥማቂው ዮሐንስ በነጋታው እንደገና ኢየሱስን
አይቶ፡- ‹‹እነሆ የእግዚአብሄር በግ!›› በማለት መሰከረ፡፡ ኢየሱስ ቀድሞውኑም
በአጥማቂው ዮሐንስ ስለተጠመቀና በዚህም የዓለምን ሐጢያቶች ስለተቀበለ
መሰቀልና ደሙን ማፍሰስ ነበረበት፡፡ አጥማቂው ዮሐንስ፡- ‹‹እነሆ የዓለምን
ሐጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሄር በግ!›› ብሎ የመሰከረው ለዚህ ነው፡፡
‹‹የዓለም ሐጢአት›› የሚለውን ሐረግ ትርጉም መረዳትና የእርሱን
የጥምቀት እውነት ማመን እንደሚኖርብን ወይም እንደማይኖርብን መወሰን
ይገባናል፡፡ የዚህ ዓለም ሐጢያቶች ትክክለኛ መረዳት ምንድነው? ብዙ ሰዎች
በጥቅሉ እዚህ ላይ ‹‹ዓለም›› የሚያመለክተው በወቅታዊ አነጋገር የራሳቸውን
ትንሽዬ ዓለም ብቻ ማለትም ከተወለዱበት ጊዜ ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ
የሚያውቁትን ማንኛውንም ነገር እንደሆነ ያስባሉ፡፡ ነገር ግን የዓለም ሐጢያቶች
ትክክለኛ መረዳት እዚህ ላይ የተጠቀሰውን ‹‹ዓለም›› ከዚህ ዩኒቨርስ ጅማሬ
ጀምሮ እስከ ፍጻሜው ድረስ ያለውን ሁሉን የሚያቅፍ ዘመን የሚያካትት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


76 ሐጢያቶቻችሁን ለመደምሰስ የመጣው ኢየሱስ

አድርገን እንድንመለከተው ይጠይቀናል፡፡


የሆነ ዓይነት ዝንብ ቢበዛ ሊኖር የሚችለው አንድ ቀን ብቻ እንደሆነ
ተነግሮኛል፡፡ እንደ እነዚህ ላሉ ነፍሳቶች ለ12 ሰዓታት መኖር ማለት
የሕይወታቸውን ግማሽ መኖር ማለት ነው፡፡ ጥቂት ቢቆዩ መጨረሻቸው
ይሆናል፡፡ 24 ሰዓት ቢኖሩ ሙሉ ዕድሜያቸውን ኖረዋል ማለት ነው፡፡ ስለዚህ
ለእነርሱ ‹‹ነገ›› የሚለው እሳቤ ትርጉም የለውም፡፡
እኛም የምንኖረው ለ70-80 ዓመታት ብቻ በመሆኑ ‹‹ዘላለማዊ›› ወይም
‹‹ወሰን አልባ›› ስለሚባሉት እሳቤዎች ተጨባጭ የሆነ ግልጽ መረዳት የለንም፡፡
ነገር ግን ሁሉን የሚችለው ጌታ አምላካችን እንዲህ ይለናል፡፡ ዓለም ከዚህ
ዩኒቨርስ ጅማሬ እስከ ፍጻሜው ድረስ ያለው ጊዜ ነው፡፡ በሌላ አነጋገር የጊዜ
እሳቤያችን እግዚአብሄር እዚህ ላይ እየተናገረ ካለው ጊዜያዊ የዓለም እሳቤ የተለየ
መሆኑ እርግጥ ነው፡፡ ጌታችን የሚናገርለት የዓለም ዘመን ከእኛ እሳቤ በጣም
የሰፋ ነው፡፡
እምነታችን በእግዚአብሄር ቃል ላይ መመስረት አለበት፡፡ ያም ማለት
በእግዚአብሄር ቃል ውስጥ በተጻፈው የውሃና የመንፈስ ወንጌል ማመን አለብን፡፡
ስለዚህ አጥማቂው ዮሐንስ ‹‹የዓለምን ሐጢያት የሚያስወግድ የእግዚአብሄር
በግ›› ያለውን ወይም ራሱ ጌታችን ‹‹እንዲህ ጽድቅን ሁሉ መፈጸም ይገባናልና››
ያለውን ስንመለከት ኢየሱስ በጥምቀቱ የሰዎችን ሐጢያቶች በሙሉ ወስዶ
በመስቀል ላይ ተሸክሞዋቸዋል ማለት መሆኑን መረዳት ይገባናል፡፡ ይህንንም
በልባችን ማመን አለብን፡፡
ኢየሱስ የዚህን ዓለም ሐጢያቶች የተሸከመው መቼ ነበር? ኢየሱስ
የዓለምን ሐጢያቶች ለአንዴና ለዘላለም የወሰደው በዮርዳኖስ ወንዝ በአጥማቂው
ዮሐንስ በመጠመቅ ሐጢያቶችን ሁሉ በተቀበለ ጊዜ ነው፡፡ እዚህ ላይ ‹‹እንዲህ››
የሚለው ሐረግ በግሪክ ‹hutos gar› ሲሆን ትርጓሜውም ‹በዚህ መንገድ ብቻ›
‹እጅግ ተገቢ› ወይም ‹ከዚህ ውጪ ሌላ መንገድ የለም› ማለት ነው፡፡ ይህ ቃል
ኢየሱስ ከአጥማቂው በተቀበለው ጥምቀት አማካይነት የሰውን ዘር ሐጢያቶች
ለዘላለም እንደወሰደ ያሳያል፡፡ በሌላ አነጋገር ኢየሱስ የዓለምን ሐጢያቶች
መደምሰስ የቻለው ያለ ምንም ስህተት በአጥማቂው ዮሐንስ በተጠመቀ ጊዜ ብቻ
ነበር፡፡ ስለዚህ የኢየሱስ ጥምቀትና ያፈሰሰው ደሙ የሐጢያቶቻችን ስርየት
መሆኑን ተረድተን እንደዚህ ማመን ይገባናል፡፡
ኢየሱስ የአጥማቂው ዮሐንስ እጆች በራሱ ላይ ተጭነውበት የዓለም
ሐጢያቶች ወደ እርሱ በተላለፉበት በዚህ ዘዴ የዓለምን ሐጢያቶች ለዘላለም

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ሐጢያቶቻችሁን ለመደምሰስ የመጣው ኢየሱስ 77

ወሰደ፡፡ ደሙንም አፈሰሰ፡፡ በዚህም ስርየታችንን በፍጽምና አጠናቀቀ፡፡ የኢየሱስ


ጥምቀት ዓላማው ይህ ነበር፡፡ በብሉይ ኪዳን ውስጥ ለመስዋዕት በቀረበው
እንስሳ ላይ የሚጫነው እጅና የሚፈሰው ደም ለእስራኤሎች ስርየትን የሚያመጣ
ነበር፡፡ ልክ እንደዚሁ እኛም ኢየሱስ በጥምቀቱ አማካይነት የዓለምን ሐጢያቶች
በመቀበል የእያንዳንዱን ሰው ሐጢያቶች እንዳነጻና እኛም የኢየሱስ ክርስቶስን
ሥጋ በማቅረብ ለዘላለም እንደተቀደስን (ዕብራውያን 10፡10) ማመን አለብን፡፡
‹‹ጥምቀት-›› የሚለው ቃል በግሪክ ባፕቲዝማ ሲሆን
ትርጓሜውም ‹‹መጥለም›› ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ‹‹ማጥመቅ›› ቃል በቃል በውሃ
ውስጥ መጥለም ወይም መስመጥ ማለት ነው፡፡ ይበልጥ ግልጽ ለማድረግ ይህ
ማለት 1) በማጥለቅ ወይም በማስመጥ ማንጻት፣ ራስን ማጠብ፣ መታጠብ 2)
መጥለቅለቅ 3) መቀበር እና 4) ማሳለፍ ማለት ነው፡፡
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለምን በትክክል መረዳትና በእርሱም
ማመን እንዳለባችሁ ምክንያቱ ይኸውላችሁ፡፡ በመጀመሪያ ሐጢያቶቻችሁ
በሙሉ ከአጥማቂው ዮሐንስ በተቀበለው ጥምቀት አማካይነት ወደ ኢየሱስ
ተላልፈዋል፡፡ ኢየሱስ በጥምቀቱ አማካይነት የዓለም ሐጢያቶቻችንን በሙሉ
ስለተቀበለ ይህንን የሚያምኑ ሁሉ አሁን ያለ ሐጢያት ናቸው፡፡ ኢየሱስ
በጥምቀቱ ቀድሞውኑም የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ በማንጻቱ ዳግመኛ ምንም
ሐጢያት ሊኖር አይችልም፡፡ ኢየሱስ የዚህን ዓለም ሐጢያቶች የወሰደ
የእግዚአብሄር በግ ነበር፡፡ እነዚህ የዓለም ሐጢያቶች ከልጅነታችሁ እስከ
ጉልምስናችሁ ከዚያም እስከምትሞቱበት ቀን ድረስ እናንተ የሰራችኋቸውንና
የምትሰሩዋቸውን ሐጢያቶች በሙሉ ያካትታሉ፡፡ ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ
በመጠመቅ እነዚህን ሐጢያቶች ተቀብሎ በመስቀል ላይ በመሸከም ጽድቅን ሁሉ
ፈጽሞዋል፡፡
ሁለተኛ የመታጠብ ትርጉም የዓለም ሐጢያት በእርሱ ጥምቀት ወደ
ኢየሱስ በመተላለፋቸው ሁሉም መንጻታቸውን ያመለክታል፡፡ ሦስተኛ የመቀበር
ትርጉም የዓለም ሐጢያቶች ከእኛ ጋር በነበሩ ጊዜ የሐጢያትን ኩነኔ መሸከምና
ወደ ሲዖል እሳት መጣል ነበረብን፡፡ አሁን ግን ሐጢያቶቻችን በእርሱ ጥምቀት
ላይ ባለን እምነት አማካይነት ወደ ኢየሱስ በመተላለፋቸው ኢየሱስ በእኛ ፋንታ
ስለ ሐጢያቶቻችን መሞት ነበረበት፡፡ ኢየሱስ በእኛ ፋንታ የተጠመቀው፣ በይፋ
በምትካችን የተሰቀለውና እስከ ሞት ድረስ የደማው፣ በእኛ ፋንታም የተቀበረውና
ዳግመኛም ከሙታን በመነሳት በእግዚአብሄር አብ ቀኝ በመቀመጥና ሐጢያተኞች
በሙሉ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ወደ ማመን እንዲመጡ በመፍቀድ በዚህ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


78 ሐጢያቶቻችሁን ለመደምሰስ የመጣው ኢየሱስ

የሚያምኑትን ሁሉ በእምነት የሐጢያቶቻቸውን ስርየት እንዲቀበሉ አስቻላቸው፡፡


በኢየሱስ አዳኝነት፣ በጥምቀቱና በመስቀል ላይ ባፈሰሰው ደሙ አምነን
ስንድን በእርግጠኝነት የእግዚአብሄር ልጆች እንሆናለን፡፡ ይህ ለእኛ ማለት
ሐጢያቶቻችን ወደ ኢየሱስ ተላልፈዋል ማለት ነው፡፡ ኢየሱስ በአጥማቂው
ዮሐንስ በመጠመቁና ደሙንም በመስቀል ላይ በማፍሰሱ ሐጢያቶቻችን
ከእንግዲህ ወዲህ አብረውን የሉም፡፡ ከልጅነታችን እስከ ጉልምስናችንና
እስከምንሞትበት ቀን የሰራናቸው ሐጢያቶች በሙሉ ሙሉ በሙሉ ወደ ኢየሱስ
ሥጋ ተላልፈው ቀድሞውኑም ተፈርዶባቸዋል፡፡ ኢየሱስ በእኛ ፋንታ በመስቀል
ላይ ደሙን ያፈሰሰው፣ የሞተው፣ ከሙታን የተነሳውና አዲስ ሕይወትን የሰጠን
ሐጢያቶቻችን በሙሉ ወደ እርሱ ስለተላለፉ ነው፡፡
ይህንን ኢየሱስን አዳኛችሁ አድርጋችሁ ካመናችሁበት ያን ጊዜ ሁላችሁም
ሐጢያት አልባ መሆን ትችላላችሁ፡፡ ከአሁን ጀምሮ የውሃውንና የመንፈሱን
ወንጌል የምታውቁ፣ የምትረዱና በልባችሁ የምታምኑ ሰዎች በሙሉ
ጸድቃችኋል፡፡ ከእንግዲህ ወዲህ ሐጢያተኞች አይደላችሁም፡፡ አሁን ጻድቃን
ናችሁ፡፡ ጻድቃን መሆን የምትችሉት በዚህ የውሃና የመንፈስ ወንጌል በማመን
ነው፡፡ በራሳችን ውጥኖች ደህንነትን ማግኘት አንችልም፡፡ ምክንያቱም
በድካማችን የምንቀጥልና ሐጢያትን የምንሰራ ነንና፡፡ ጌታ ግን ከአጥማቂው
ዮሐንስ በተቀበለው ጥምቀቱና በመስቀል ላይ ባፈሰሰው ደሙ አስቀድሞ
ሐጢያቶቻችንን ሁሉ አንጽቷል፡፡ ስለዚህ ደህንነት ወደ ልባችን የሚመጣው
እውነትን በማወቅ ነው፡፡

በብሉይ ኪዳኑ የመገናኛው ድንኳን የመስዋዕት ስርዓት የተረጋገጠው


የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል፡፡

በመጀመሪያ የብሉይ ኪዳንን የመገናኛ ድንኳን መሰረታዊ የቅርጽ ንድፍ


ላብራራ፡፡ የመገናኛው ድንኳን በራሱ በአንጻራዊ መልኩ ትንሽዬ መዋቅር ነው፡፡
ነገር ግን በአእማዶችና ከጥሩ በፍታ በተሰሩ መጋረጃዎች በታጠረ ውጪያዊ
አደባባይ የተከበበ ነበር፡፡ ወደዚህ አደባባይ የሚያስገባ በር ነበር፡፡ አንድ ሰው
ይህንን በር አልፎ ወደ መገናኛው ድንኳን ሲቀርብ የሚቃጠል መስዋዕት
የሚቀርብበት መሰውያ ቆሞዋል፡፡ ይህንን መሰውያ አልፎም የናሱ የመታጠቢያ
ሰን ይገኛል፡፡ የመገናኛው ድንኳን ራሱ በሁለት ክፍሎች የተከፈለ ሲሆን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ሐጢያቶቻችሁን ለመደምሰስ የመጣው ኢየሱስ 79

እነርሱም ቅድስትና ቅድስተ ቅዱሳን ነበሩ፡፡ የዚህ የእግዚአብሄር ቤት በሮች


(የቅድስቱ በርና የቅድስተ ቅዱሳኑ በር) እንደዚሁም የአደባባዩ በር ሁሉም
ከተፈተለ ሰማያዊ፣ ሐምራዊ፣ ቀይ ግምጃና ከጥሩ በፍታ የተሰሩ ነበሩ፡፡
እግዚአብሄር የመገናኛውን ድንኳን በሮችና መግቢያ ሁሉ በተፈተሉ
በእነዚህ ሰማያዊ፣ ሐምራዊ፣ ቀይ ገምጃና በጥሩ በፍታ እንዲሰሩ ያደረገው
ለምንድነው? ምክንያቱም በእነርሱ አማካይነት እግዚአብሄር ኢየሱስ ወደዚህ
ምድር በመምጣት ከአጥማቂው ዮሐንስ በሚቀበለው ጥምቀት የዓለምን
ሐጢያቶች ለአንዴና ለዘላለም እንዴት እንደሚወስድ፣ እንደሚሰቀልና ደሙን
እንደሚያፈስስ አስቀድሞ ለመተንበይ ነው፡፡ ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ
በመጠመቅና ለዓለም ሐጢያቶች በመሰቀል የራሱን ሥጋ ስለ እኛ የመስዋዕት
ቁርባን አድርጎ አቀረበ፡፡
ኢየሱስን አዳኝ አድርጎ በማመንና ሰማያዊ፣ ሐምራዊና ቀይ ማግ የሆነው
ኢየሱስ በጥምቀቱ የዓለምን ሐጢያቶች እንደወሰደ በሚነግረን ቃሉ በማመን
በአንድ ጊዜ በእምነት ከሐጢያቶቻችን ሁሉ መዳን እንችላለን፡፡ ኢየሱስ እነዚህን
ሰማያዊ፣ ሐምራዊ፣ ቀይ ማግና ጥሩ የተፈተለ በፍታ ለመገናኛው ድንኳን በር
የተጠቀመው እርሱ የነገሥታት ንጉሥ እንደሆነና በጥምቀቱና በመስቀሉ
ከሐጢያታችን እንዳዳነን ሊነግረን ነው፡፡ ለመገናኛው ድንኳን የመግቢያ በር
ጥቅም ላይ የዋሉት ሰማያዊ፣ ሐምራዊ፣ ቀይ ማግና የተፈተለ ጥሩ በፍታ ጌታ
ፈጽሞ እንዳዳነን የሚነግሩን የደህንነት ምሳሌ ናቸው፡፡ (1ኛ ጴጥሮስ 3፡21)
የመገናኛውን ድንኳን አደባባይ በር ከፍተን ብንገባ የሚቃጠለውን
መስዋዕት መሰውያውን አልፎ ያለውን የናሱን የመታጠቢያ ሰን የምናየው ለዚህ
ነው፡፡ የሚቃጠለው መስዋዕት መሰውያ ከደህንነት ሕጉ በፊት ያለውን ‹‹ለሰዎች
አንድ ጊዜ መሞት ከእርሱ በኋላም ፍርድ እንደተመደበባቸው›› የሚለውን
የእግዚአብሄር የፍትህ ሕግ ያሳየናል፡፡ በሌላ አነጋገር እግዚአብሄር እኛ ስለ
ሐጢያቶቻችን እንደምንኮነን አሳይቶናል፡፡ ኢየሱስን በእርግጥ አዳኝ አድርገን
የምናምነው ከሆነ በብሉይ ኪዳን ውስጥ እስራኤሎች ከሐጢያቶቻቸውና
ከሐጢያት ኩነኔ ሁሉ ይድኑ ዘንድ ሐጢያቶቻቸውን ወደ መስዋዕቱ እንስሳ
ማስተላለፍና በመሰውያው ፊት ማረድ እንደነበረባቸው መረዳት ይኖርብናል፡፡
ልክ እንደዚሁ ኢየሱስም በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅ የዓለምን
ሐጢያቶች ለአንዴና ለመጨረሻ ወስዶዋል፡፡ ስለ እኛ የተሰቀለውና ደሙን
ያፈሰሰው ለዚህ ነው፡፡ ጌታችን ወደዚህ ምድር በመምጣት በአጥማቂው ዮሐንስ
ተጠምቆ ሐጢያቶቻችንንና የሐጢያት ኩነኔን ሁሉ ለአንዴና ለመጨረሻ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


80 ሐጢያቶቻችሁን ለመደምሰስ የመጣው ኢየሱስ

ተሸከመ፡፡ በአጭሩ ኢየሱስ እኛን ከሐጢያቶቻችንና ከኩነኔ ለማዳን በጥምቀቱ፣


ደሙን በማፍሰስና ዳግመኛ ከሙታን በመነሳት እውነተኛ አዳኛችን ሆነ፡፡

አሁን የግል ሐጢያቶቻችን የሚገኙት የት ነው?

በሕይወት ስንኖር ሳለን በየቀኑ ስለምንፈጽማቸው የግል ሐጢያቶቻችን


ምን ማድረግ ይገባናል? ወንድሞችና እህቶች ሐጢያቶቻችን በሙሉ ኢየሱስ
በዮርዳኖስ ወንዝ በተጠመቀ ጊዜ ወደ እርሱ እንደተላለፉ የምናስታውስ ከሆነ
ማለትም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ቃል በልባችን የምናምን ከሆነ ያን ጊዜ
ሁልጊዜም ሐጢያት አልባ እንሆናለን፡፡ ለምን? ምክንያቱም ኢየሱስ በየቀኑ
ሐጢያት እንደምንሰራ በማወቅ በአጥማቂው ዮሐንስ ተጠምቆ የዓለምን
ሐጢያቶች በሙሉ በመውሰድ በመስቀል ላይ ተሸከማቸው፡፡ እየሞተ ሳለም
ደሙን አፈሰሰ፡፡ ዳግመኛም ከሙታን በመነሳት ሁሉንም በአንዴ ደመሰሳቸው፡፡
ሆኖም ይህ የደህንነት እውነት የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል እውነት
ውጤታማ የሚሆነው በትክክል ስንረዳውና በሙሉ ልባችን ስናምነው ብቻ
ነው፡፡ ፈጽሞ ሐጢያት አልባ መሆን የምንችለው ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ
በተጠመቀ ጊዜ ሐጢያቶቻችን በሙሉ ወደ እርሱ እንደተላለፉና እንደተወገዱ
በማስታወስና በማመን ብቻ ነው፡ ምክንያቱም በየቀኑ ሐጢያት እንሰራለንና፡፡
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ባለን እምነታችን ከአዳም ሐጢያታችንና ከግል
ሐጢያቶቻችን በሙሉ ነጽተናል፡፡
ውድ ክርስቲያኖች ከሐጢያቶቻችሁ ሁሉ ለመንጻት የምትፈልጉ ከሆናችሁ
ኢየሱስ በተጠመቀ ጊዜ ሐጢያቶቻችን በሙሉ ወደ እርሱ እንደተላለፉ መረዳትና
ማመን አለባችሁ፡፡ ሁልጊዜም በተለይም የምግባር ሐጢያቶችን በምትሰሩበት
ጊዜ ሁሉ የእውነተኛውን ወንጌል ቃል ማሰላሰል ይገባችኋል፡፡ ልባችሁ
ሁልጊዜም ሊነጻ የሚችለው ያን ጊዜ ብቻ ነው፡፡ የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል
ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ በተጠመቀ ጊዜ ሐጢያቶቻችን በሙሉ ወደ እርሱ
እንደተላለፉና ለእነዚህ ሐጢያቶችም በመስቀል ላይ እንደተኮነነ ይነግረናል፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ሐጢያት ስርየት የሚነግረን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
በኩል ነው፡፡
ሁላችንም የእግዚአብሄርን ቃል እውነት እንደሆነ መቁጠርና ማመን
አለብን፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የምታምኑ ከሆነ አንዳች ሐጢያት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ሐጢያቶቻችሁን ለመደምሰስ የመጣው ኢየሱስ 81

ሊኖርባችሁ አይችልም፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስን በተጨባጭ አዳኛችን አድርገን


የምናምን ከሆንን ያን ጊዜ ኢየሱስ ምንም ይሁኑ ከአጥማቂው ዮሐንስ
በተቀበለው ጥምቀት የዚህን ዓለም ሐጢያቶች በሙሉ በአንድ ጊዜ እንደወሰደ
የምናምን የእምነት ሰዎች ነን፡፡ ኢየሱስ ከአጥማቂው ዮሐንስ የተቀበለው ጥምቀት
እያንዳንዱን ሰው ሐጢያት አልባ አድርጎታል፡፡ የሮሜ መጽሐፍ እንዲህ
ይነግረናል፡- ‹‹በአንዱ ሰው አለመታዘዝ ብዙዎች ሐጢአተኞች እንደሆኑ እንዲሁ
ደግሞ በአንዱ መታዘዝ ብዙዎች ጻድቃን ይሆናሉ፡፡›› (ሮሜ 5፡19)
በዚህ ዓለም ላይ ስንኖር በየቀኑ ሐጢያት እንሰራለን፡፡ ሐጢያቶቻችንን
በሙሉ ቀድሞውኑም ወደ ኢየሱስ ተላልፈዋልን? ሐጢያቶቻችን በሙሉ ከረጅም
ጊዜ በፊት ከ2,000 ዓመታት በፊት ቀድሞውኑም ወደ ኢየሱስ ሥጋ
ተላልፈዋል፡፡ ወደፊት በድክመቶቻችን የተነሳ የምንሰራቸው ሐጢያቶችም ወደ
ኢየሱስ ተላልፈዋል፡፡ እርሱ ለእነዚህም ደግሞ ተኮንኖዋልን? አዎ ትክክል ነው፡፡
ታዲያ ይህ ማለት በራሳችን ስሜት ሁሉንም ዓይነት ሐጢያት መስራት
ትክክል ነው ማለት ነውን? ነገሩ እንደዚያ አይደለም፡፡ በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል አምነው ዳግመኛ የተወለዱ ሰዎችም እንኳን ከድክመቶቻቸው የተነሳ
ሐጢያትን በመስራት ለመቀጠል የታሰሩ ናቸው፡፡ ነገር ግን አሁንም የውሃውንና
የመንፈሱን እውነተኛ ወንጌል በማሰብ ሁልጊዜም ልቦቻቸውን ንጹህ አድርገው
ማቆየት ይችላሉ፡፡ ሰዎች በፈቃዳቸው ከሚሰሩት ይበልጥ ከድክመታቸው የተነሳ
የሚሰሩት ሐጢያት ይበልጣል፡፡
ስለዚህ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምኑ ምዕመናኖች ሲደክሙ
በጥምቀቱና በፈሰሰው ደሙ እምነታቸውን በማደስ ይበልጥ እግዚአብሄርን
ማመስገን ይጠበቅባቸዋል፡፡ ምክንያቱም ጌታ ቀድሞውኑም በጥምቀቱና
በመስቀል ላይ ባፈሰሰው ደሙ ሐጢያቶቻቸውን በሙሉ በማንጻት ለእነዚህ
ሐጢያቶች ተኮንኖዋልና፡፡ አሁን እነርሱ ዳግመኛ በሐጢያት የታሰሩ አይደሉም፡፡
ነገር ግን ይህንን እውነት ለሌሎች ለማሰራጨት ፈቃደኞች ናቸው፡፡ እንዲህ
በማድረግ ልባችን ይበልጥ ይደሰታል፡፡
ታዲያ እናንተስ? ኢየሱስ ሐጢያቶቻችሁን በሙሉ ለመደምሰስ ወደዚህ
ዓለም እንደመጣ፣ በአጥማቂው ዮሐንስ እንደተጠመቀ፣ እስከ ሞት ድረስም
ደሙን እንዳፈሰሰና ዳግመኛ ከሙታን እንደተነሳ ታምናላችሁን? አዎ
ሐጢያቶቻችንን ፈጽሞ ለመደምሰስ ለመጣው ኢየሱስ ምስጋናን እናቀርባለን፡፡
እርሱ በእርግጥም ሐጢያቶቻችንን ለአንዴና ለመጨረሻ ፈጽሞ
አስወግዶዋቸዋል፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


82 ሐጢያቶቻችሁን ለመደምሰስ የመጣው ኢየሱስ

በብሉይ ኪዳን የመገናኛው ድንኳን ውስጥ የአደባባዩን በር አልፈን


በመግባት የሚቃጠል መስዋዕት መሰውያውን ስናልፍ ወደ ናሱ የመታጠቢያ ሰን
እንደርሳለን፡፡ ለመገናኛው ድንኳን ሌሎች ዕቃዎች ሁሉ ልኬቶችና ወሰኖች
ያሉዋቸው ሲሆን ለዚህ ናስ የመታጠቢያ ሰን ግን ውሱን የሆኑ ልኬቶች
የሉትም፡፡ በመንፈሳዊ አነጋገር ይህ የሚያመለክተው ኢየሱስ በጥምቀቱና
ባፈሰሰው ደሙ ያለ ምንም የልኬት ወሰን ሐጢያቶቻችንን ሁሉ የመደምሰሱን
እውነት ነው፡፡ ስለዚህ የናሱ የመታጠቢያ ሰን ሐጢያቶቻችንን ሁሉ
የመደምሰሱን እውነታ ነው፡፡ ስለዚህ የናሱ የመታጠቢያ ሰን ሐጢያቶችንን ሁሉ
የማንጻት ያልተገደበ ብቃት አለው፡፡
ይህ የመታጠቢያው ሰን ከናስ መሰራቱ ሐጢያቶች በሙሉ መኮነን
እንዳለባቸው ያመለክታል፡፡ ይህ መታጠቢያ ሰን ካህኑ እጆቹንና እግሮቹን
የሚታጠብበትን ውሃ ይዞዋል፡፡ ይህም ጌታ በጥምቀቱ የዓለምን ሐጢያቶች
ፈጽሞ እንዳነጻ ይነግረናል፡፡ የብሉይ ኪዳን ካህናቶች በሚቃጠለው መስዋዕት
መሰውያ ላይ መስዋዕቶችን ሲያቀርቡ እጆቻቸውን በእነርሱ ላይ ጭነው
የመስዋዕቶቹን እንስሶች ሲያርዱ ከእንስሳው ደም እስከ ሰገራው ድረስ በሁሉም
ዓይነት ሰገራ ይበላሻሉ፡፡ ከዚህ ዓይነቱ ቆሻሻ ራሳቸውን የሚያጸዱት በናሱ
የመታጠቢያ ሰን ውስጥ ባለው ውሃ ነው፡፡ ስለዚህ የናሱ የመታጠቢያ ሰን ቆሻሻ
ሐጢያቶችን የሚያነጻውን የኢየሱስን ጥምቀት ያመለክታል፡፡ በዚህ ዓለም ላይ
የምንሰራቸው የግል ሐጢያቶቻችን በሙሉ ቀድሞውኑም በኢየሱስ ጥምቀት
ተደምስሰዋል፡፡ በናሱ የመታጠቢያ ሰን ውስጥ የተገለጠው ይህ ነው፡፡ እኛ በዚህ
እውነት በማመን ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ይቅርታን አግኝተን ሁልጊዜም ለዘላለም
በንጹህ ሕሊና እንኖራለን፡፡
ኢየሱስ የዚህን ዓለም ሐጢያቶች ለመቀበል በአጥማቂው ዮሐንስ
የተጠመቀው ምን ያህል ጊዜ ነው? እርሱ የተጠመቀው አንድ ጊዜ ብቻ ነው፡፡
ኢየሱስ ከአጥማቂው ዮሐንስ አንድ ጊዜ ብቻ በመጠመቅ የዚህን ዓለም
ሐጢያቶች በሙሉ ፈጽሞ ለዘላለም አነጻቸው፡፡ እርሱ ለምን አንድ ጊዜ ብቻ
ተጠመቀ? ምክንያቱም ኢየሱስ በጥምቀቱ የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ
ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ ድረስ ለአንዴና ለመጨረሻ የመውሰድ ሥልጣን
ያለው የእግዚአብሄር ዘላለማዊ ልጅ ስለሆነ ነው፡፡ ኢየሱስ ‹‹አልፋና ዖሜጋ እኔ
ነኝ›› ስላለ እርሱ ዘላለማዊ አምላክ ነው፡፡ ኢየሱስ የዘላለማዊው ሕያው አምላክ
ልጅ ስለሆነ የዘላለም ደህንነቱን ለአንዴና ለመጨረሻ መፈጸም ችሎዋል፡፡ እርሱ
አንድ ጊዜ ወደዚህ ዓለም መጣ፡፡ በአጥማቂው ዮሐንስ አንድ ጊዜ በመጠመቅም

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ሐጢያቶቻችሁን ለመደምሰስ የመጣው ኢየሱስ 83

የዓለምን ሐጢያቶች በአንድ ጊዜ ተሸከመ፡፡ አንድ ጊዜ ተሰቀለ፡፡ ደሙንም


አፈሰሰ፡፡ በዚህም ሐጢያቶቻችንን በሙሉ በአንድ ጊዜ አነጻቸው፡፡
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል እውነት ማወቅና ኢየሱስን አዳኝ አድርገን
ማመን ይገባናል፡፡ ኢየሱስ የዓለምን ሐጢያቶች ያነጻው አንድ ጊዜ በመጠመቅ
ነው፡፡ ኢየሱስ በተጠመቀ ጊዜ ሐጢያቶቻችሁ ለዘላለም ወደ እርሱ ተላልፈዋል፡፡
ኢየሱስ እንዲህ አንድ ጊዜ በመጠመቅ የዓለምን ሐጢያቶች የደመሰሰውን
የእግዚብሄርን ጽድቅ ሁሉ ፈጸመ፡፡ ሐጢያቶቻችሁ በሙሉ በጥምቀቱ
አማካይነት ወደ ኢየሱስ እንደተላለፉ መረዳት አለባችሁ፡፡ ይህንን ማመን
አለባችሁ፡፡ ይህንን በማመናችሁ የምታጡት ምንም ነገር የለም፡፡ ዘላለማዊውን
የሐጢያቶቻችንን ስርየት መቀበል የምንችለው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ላይ
ባለን እምነታችን ነው፡፡
እናንተ ኢየሱስ በየቀኑ ሐጢያቶቻችሁን ይቅር እንዲል የምትጠይቁ ሰዎች
ከሆናችሁ ገና ዳግመኛ ያልተወለዳችሁ መሆናችሁን ማወቅ ይገባችኋል፡፡
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል እውነትም መረዳት ይኖርባችኋል፡፡ በዚህ ወንጌል
መሰረትም ኢየሱስን እንደገና እንደ አዲስ እውነተኛ አዳኛችሁ አድርጋችሁ ማመን
አለባችሁ፡፡ በመላው ዓለም የሚገኙና የኢየሱስን ጥምቀት በትክክል ያልተረዱ
መጋቢዎችም እንደገና እንደ አዲስ በእርሱ ማመን ይገባቸዋል፡፡ ብዙ መጋቢዎች
ሐጢያቶቻቸውን ያነጻውን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በትክክል
አልተረዱትም፡፡ ታዲያ እነርሱ ራሳቸው ያልተቀበሉትን የሐጢያት ስርየት ሌሎች
እንዲቀበሉ መርዳት የሚችሉት እንዴት ይመስላችኋል? እንዲያው በአጋጣሚ
ልባችሁ ሐጢያተኛ ሆኖ ሳለ በሥጋ ምግባሮችና ገጽታ ብቻ ቅዱሳን እንደሆናችሁ
ብታስመስሉ ግብዝ ሐይማኖተኞችና የጥፋት ልጆች ብቻ ከመሆን
አታመልጡም፡፡ ሰዎች በእናንተ እገዛ የሐጢያት ስርየትን መቀበል አይችሉም፡፡
ነገር ግን ከዓለም የሐሰት ሐይማኖቶች ተለይታችሁ የውሃውንና የመንፈሱን
ወንጌል በሚያውቅና በሚያምን እምነት የደህንነትን እውነት መረዳት ስትችሉ
ነፍሳችሁ ከሐጢያቶቻችሁ ሁለ ነጻ መውጣት ትችላለች፡፡ ከሐጢያቶቻችሁ
በሙሉ መንጻት የምትችሉት የእግዚአብሄር የሕይወት ቃል የሆነውን የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል በትክክል ስትረዱና እርሱንም በትክክል በልባችሁ ስታምኑት
ብቻ ነው፡፡ ነገር ግን እጅግ ብዙ ቁጥር ያላቸው ሰዎች አሁንም ድረስ ኢየሱስ
በአጥማቂው ዮሐንስ በተጠመቀ ጊዜ የዓለም ወደ እርሱ የተላለፉ የመሆናቸውን
እውነታ አያውቁም፡፡ ስለዚህ በመጀመሪያ እናንተ ራሳችሁ በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል በትህትና በማመን ልትቀበሉት ይገባል፡፡ ኢየሱስ እንዲህ ብሎዋል፡-

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


84 ሐጢያቶቻችሁን ለመደምሰስ የመጣው ኢየሱስ

‹‹እንዲህ ጽድቅን ሁሉ መፈጸም ይገባነልና፡፡›› (ማቴዎስ 3፡15) ኢየሱስ ሲጠመቅ


የእግዚአብሄርን ጽድቅ ሁሉ ፈጽሞዋል፡፡ ኢየሱስ በተቀበለው በዚህ ጥምቀት
አማካይነት የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ ወስዶዋል፡፡ በዚህ ጥምቀት ኢየሱስ
የእናንተንም ሐጢያቶች በሙሉ ደግሞ ወስዶዋል፡፡
እናንተ በዚህ ዓለም ላይ የምትኖሩ ሰዎች አይደላችሁምን? በእርግጥም
ናችሁ፡፡ ሐጢያቶቻችሁ በዓለም ሐጢያቶች ውስጥ አልተካተቱምን? በእርግጥም
ተካትተዋል፡፡ አንድ ጊዜ ይህንን ስታውቁ ኢየሱስ በጥምቀቱ ሐጢያቶቻችሁን
በሙሉ የተሸከመ በመሆኑ እውነት አማካይነት መዳን ትችላላችሁ፡፡ ብቸኛው
አዳኛችሁ ራሱ ኢየሱስ ክርስቶስ መሆን ወደ መረዳት የሚመራችሁ የመረማመጃ
ድንጋይ በሐጢያቶቻችሁ ምክንያት ለመኮነን የታጫችሁ ሐጢያተኞች
መሆናችሁን መረዳት ነው፡፡
ወደ ክርስቶስ መጥታችኋልን? ወይስ አሁንም ድረስ ከክርስቶስ ውጭ
ሆናችሁ ቆማችኋል? በትክክል የት እንደቆማችሁ በግልጽ ማወቅ አለባችሁ፡፡
እናንተ በዚህ ዓለም ላይ የምትኖሩ ሰዎች ናችሁ፡፡ ታዲያ ሐጢያቶቻችሁ በሙሉ
ወደ ኢየሱስ ተላልፈዋል ወይስ አልተላለፉም? ተላልፈዋል፡፡ ታዲያ ‹‹አቤቱ
አሁንም ሐጢያተኛ ነኝ›› የሚሉ ክርስቲያኖች ዳግመኛ የተወለዱ ቅዱሳን
እንዳልሆኑ ታምናላችሁን? እነርሱ በኢየሱስ ቢያምኑም ሐጢያቶቻቸው
በጥምቀቱ አማካይነት ወደ ኢየሱስ መተላለፋቸውን ስላልተረዱ የሚደገፉት
በመስቀሉ ላይ በፈሰሰው ደም ብቻ በመሆኑ ጌታ ሐጢያቶቻቸውን ይቅር
እንዲላቸው በመጠየቅ በየቀኑ እየተሰቃዩ፡፡
ነገር ግን ሐዋርያው ጳውሎስ ምን ነግሮናል? እርሱ እንዲህ ሲል ነገረን፡-
‹‹ሁልጊዜ ደስ ይበላችሁ፤ ሳታቋርጡ ጸልዩ፤ በሁሉ አመስግኑ፡፡ ይህ
የእግዚአብሄር ፈቃድ በክርስቶስ ኢየሱስ ወደ እናንተ ነውና፡፡›› (1ኛ ተሰሎንቄ
5፡16-18) ስለዚህ ሐጢያቶቻችንን ይቅር ይለን ዘንድ ጌታን ያለ ማቋረጥ
በመጨቅጨቅ የምናላዝንና የሙጥኝ የምንል ከሆንን በእርሱ እናምናለን ብንልም
እንኳን እያደረግን ያለነው ነገር የእርሱን ጥምቀትና ያፈሰሰውን ደሙን መሳደብ
ብቻ ነው፡፡ የዚህ ዓይነቱ እምነት ኢየሱስን የሚሳደብ ነው፡፡

ሁላችንም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል እናምናለን?

ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ ተጠመቀ፡፡ ያን ጊዜ ሐጢያቶቻችን በሙሉ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ሐጢያቶቻችሁን ለመደምሰስ የመጣው ኢየሱስ 85

ለአንዴና ለመጨረሻ ወደ ኢየሱስ ተላለፉ፡፡ ኢየሱስ በጥምቀቱ አማካይነት


የዓለምን ሐጢያቶች በመቀበል ደሙን አፍስሶ በመስቀል ላይ ሞተ፡፡ በሦስት
ቀናት ውስጥም ከሙታን ተነሳ፡፡ አሁን በእግዚአብሄር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦዋል፡፡
በመጀመሪያ ኢየሱስ ሲመጠቅ የእኛን ሐጢያቶች ጨምሮ የዓለምን
ሐጢያቶች የወሰደ መሆኑን ወይም አለመሆኑን በትክክል መረዳታችን ወሳኝ
ነው፡፡ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በመረዳትና በእርሱም በማመን
ለእግዚአብሄር ማዳን ምላሽ መስጠት አለብን፡፡ ‹‹ይህ ትክክል ነው›› በማለት
እግዚአብሄር ላደረገው ነገር ምላሽ መስጠት አለብን፡፡ ጌታ በጥምቀቱ አማካይነት
ሐጢያቶቻችሁን ባያስወግድ ኖሮ በመስቀል ላይ ያፈሰሰው ደሙ በሙሉ ከንቱ
ይሆን ነበር፡፡ በልባችን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ማመን አለብን፡፡ ጌታ
የዓለም ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ፈጽሞ ደምስሶዋቸዋል፡፡
እምነትና ደህንነት በእናንተ ጥረቶች ላይ ያረፈ አይደለም፡፡ ከሐጢያት
መዳናችሁ ያረፈው ኢየሱስ በሰጣችሁ የውሃና የመንፈስ ወንጌል በሚያምነው
እምነታችሁ ላይ ነው፡፡
አሁን የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ብቸኛው እውነተኛ ወንጌል መሆኑን
ተገንዘባችሁ ይህንን እውነት በልባችሁ ልትቀበሉ ትፈልጋላችሁን? እንግዲያውስ
የሚከተለውን መናዘዝ አለባችሁ፡- ‹‹ጌታ ሆይ እስከዛሬ ድረስ በጥምቀትህ
የዓለምን ሐጢያቶች ለአንዴና ለመጨረሻ እንደወሰድህ አላውቅም ነበር፡፡
የተሳሳተ መረዳትና የተሳሳተ እምነት ነበረኝ፡፡ ነገር ግን አሁን የአንተን ደህንነት
በተሳሳተ መንገድ እንደተረዳሁት እንድገነዘብ ስላደረከኝ አመሰግንሃለሁ፡፡ አሁን
የውሃውንና የመንፈሱን እውነት ወደ መረዳትና ወደ ማወቅ ስለመጣሁ
አምንበታለሁ፡፡ ስለ እርሱም አመሰግንሃለሁ፡፡››
እናንተም ደግሞ ይህ ለሌላ ሰው ሳይሆን ለራሳችሁ የመጣ መሆኑን
በመረዳት የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል መረዳትና በልባችሁ ይገባችኋል፡፡
እምነት ማለት ሁልጊዜም ደህንነትን በልባችሁ ውስጥ ያለ አድርጋችሁ መቀበል
ማለት ነው፡፡ የእግዚአብሄር ልጆች የምትሆኑበት መንገድ ይህንን እውነት ማመን
ነው፡፡ ይህም የሐጢያቶቻችሁን ይቅርታ የሚሰጣችሁ እምነት ነው፡፡ የውሃውና
የመንፈሱ ወንጌል መረዳታችሁ ምንድነው? ምን ያህልስ በትክክል
ታምኑበታላችሁ?
ጌታችን እንዲህ ብሎዋል፡- ‹‹እውነትንም ታውቃላችሁ፤ እውነትም አርነት
ያወጣችኋል፡፡›› (ዮሐንስ 8፡32) የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ልክ
እንደተጻፈው ልናውቅ ይገባናል፡፡ በእግዚአብሄር የሚያምነው እምነት ይህ ነው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


86 ሐጢያቶቻችሁን ለመደምሰስ የመጣው ኢየሱስ

እርሱ በውሃውና በደሙ ከዓለም ሐጢያቶች አድኖናል፡፡ እርሱ በውሃና


በመንፈሱ ከዓለም ሐጢያቶች ስላዳነን ይህንን በእግዚአብሄር ፊት ከልባቸው
የሚያምኑ ሰዎች በእርግጥም ዳግመኛ ይወለዳሉ፡፡

አሁንም ድረስ ባለ ዕዳዎች ናችሁን?

ኢየሱስ በዮሐንስ 3 ላይ ሰው ከውሃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ


እግዚአብሄር መንግሥት መግባትም ሆነ ያንን መንግሥት ማየት እንደማይችል
ተናግሮዋል፡፡ ከውሃና ከመንፈስ መወለድ የሚቻለው በኢየሱስ ጥምቀት
በመስቀል ላይ ባፈሰሰው ደሙና እርሱ የእግዚአብሄር ልጅና አዳኛችን የመሆኑን
እውነት ስናምን ብቻ ነው፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ታምናላችሁን?
እዚህ ላይ አንድ ሰው የግማሽ ሚሊዮን ዶላር ዕዳ አከማቸ ብለን
እንገምት፡፡ ወለዱ ራሱ ሊሸከመው ከሚችለው በላይ በጣም ብዙ ነው፡፡ የዚህ
ዓይነቱ ዕዳ ተራ ሰራተኞች ሊከፍሉት ከሚችሉት በላይ ነው፡፡ ይህ ሰው ዕዳውን
መክፈል አልቻለም፡፡ ስለዚህ ከስሮ ተሰወረ፡፡ ነገር ግን ወደ ሌላ ቦታ ሸሽቶ
ዕዳውን ለመክፈል ጠንክሮ ቢሰራም ዋናውን ዕዳ ይቅርና ይቅርና ወለዱንስ
እንኳን መክፈል ይቻለዋልን? ውሎ አድሮ አበዳሪው ገንዘቡን ለማስመለስ ዋስትና
የገባውን ሰው ያዘው፡፡ ነገር ግን ዋስትና የገባው ሰውም ቢሆን መልሶ
የሚከፍልበት መንገድ አልነበረም፡፡ ስለዚህ አበዳሪው ክፉ ነውና ዕዳውን
እንዲከፍሉ ለማስገደድ ሁሉንም ዓይነት ዛቻዎችን በመዛት ወደ ወላጆቹ ሄደ፡፡
ወላጆቹ ይህንን መቋቋም ባለመቻላቸው ለአበዳሪው ዕዳውን ከፈሉ፡፡ በምላሹም
ከእርሱ ዘንድ ደረሰኝ ይቀበላሉ፡፡
የአበዳሪው ዕዳ ከተከፈለ በኋላ አባት በሥጋና በአእምሮ የተጎዳውን ልጁን
መፈለግ ጀመረ፡፡ ለ10 ዓመታት ያህል በየስፍራው ልጁን ቢፈልግም ሊያገኘው
አልቻለም፡፡ 12 ዓመታት ካለፉ በኋላ አንደ ቀን ልክ የተወሰነ ገንዘብ አጠራቅሞ
ተመለሰ፡፡ መጀመሪያ ወደ አባቱ ሄደና ‹‹400,000 ብር አጠራቅሜያለሁ፡፡ ነገር
ግን አሁንም 100,000 ብር ይጎድለኛል፡፡ ይህንን ገንዘብ ልታበድረኝ ትችላለህ?
ከአንተ ጋር እየኖርሁ መልሼ ልከፍልህ ጠንክሬ እሰራለሁ›› አለው፡፡ ያን ጊዜ
አባት ዓይኖቹ ዕንባ አቅርረው ልጁን በማቀፍ ‹‹እኔ ቀድሜ ዕዳህን ከፍያለሁ!
ዳግመኛ የሚያስጨንቅህ ምንም ነገር የለም! በዚህ ጊዜ ሁሉ ብዙ ተቸግረሃል!››
አለው፡፡ አባት ለልጁ ዕዳው እንደተከፈለ ከነገረው በኋላ ደረሰኙን አሳየው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ሐጢያቶቻችሁን ለመደምሰስ የመጣው ኢየሱስ 87

ልጅ በምስጋና ተጥለቀለቀ፡፡ ነገር ግን በዚያው ጊዜ ደግሞ ‹‹ላለፉት 12


ዓመታት በእርግጥ ሊኖረኝ የማይገባ ቢሆንም ለቅጽበት ያህል ፈጽሞ ሰላም
ሳይኖረኝ ተሰላችቼ ኖርሁ፡፡ ስልቹ ሆኜ ኖርሁ፡፡ አላወቅሁም፤ ችግሬ ሁሉ
በከንቱ ነበር!›› ብሎ በማሰብ በከንቱ እንደተቸገረ ተሰማው፡፡
ውድ ክርስቲያኖች ኢየሱስ ቀድሞውኑም በጥምቀቱና በመስቀሉ
አማካይነት ሐጢያቶቻቸውን በሙሉ አስቀርቶላቸው ሳለ በራሳቸው መንገድ
የሐጢያቶቻቸውን ስርየት ለማግኘት የሚሞክሩ ሰዎች ልክ እንደዚህ ልጅ
አሁንም በሐጢያት ችግር ይሰቃያሉ፡፡
ኢየሱስ በጥምቀቱ ቀድሞውኑም ሐጢያቶቻችንን ደምስሶዋል፡፡
ቀድሞውኑም በጥምቀቱ ሐጢያቶቻችንን ወስዶዋል፡፡ በመስቀል ላይ ደሙን
በማፍሰስም የሐጢያትን ኩነኔ በሙሉ ተሸክሞ አድኖናል፡፡ በእርግጥም ኢየሱስ
ሐጢያቶቻችሁን ሁሉ ወስዶዋል፡፡ ይህንን እመኑ፡፡

‹‹ከዚህ ወዲህ ስለ ሐጢአት ማቅረብ የለም፡፡››

አሁን ወደ ዕብራውያን 10፡1-18 እንመለስ፡- ‹‹ሕጉ ሊመጣ ያለው የበጎ ነገር


እውነተኛ አምሳል ሳይሆን የነገር ጥላ አለውና፡፡ ስለዚህ በየዓመቱ ዘወትር
በሚያቀርቡት በዚያ መስዋዕት የሚቀርቡትን ሊፈጽም ከቶ አይችልም፡፡
እንደዚህማ ባይሆን የሚያመልኩት አንድ ጊዜ ነጽተው ከዚያ በኋላ በሕሊናቸው
ሐጢአትን ስላላወቁ ማቅረብን በተዉ አልነበረምን? ነገር ግን በዚያ መሥዋዕት
በየዓመቱ የሐጢአት መታሰቢያ አለ፡፡ የኮርማዎችና የፍየሎች ደም ሐጢአትን
እንዲያስወግድ የማይቻል ነውና፡፡ ስለዚህ ወደ ዓለም ሲገባ፡-
መሥዋዕትንና መባን አልወደድህም
ሥጋን ግን አዘጋጀህልኝ
በሙሉ በሚቃጠል መሥዋዕትና
ስለ ሐጢአት በሚሰዋ መሥዋዕት
ደስ አላለህም፡፡ በዚያን ጊዜ፡-
እነሆ በመጽሐፍ ጥቅልል
ስለ እኔ እንደተጻፈ፡- አምላኬ
ሆይ ፈቃድህን ላደርግ መጥቻለሁ አልሁ
ይላል፡፡ በዚህ ላይ፡- መሥዋዕትንና መባን፣ በሙሉ የሚቃጠል

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


88 ሐጢያቶቻችሁን ለመደምሰስ የመጣው ኢየሱስ

መሥዋዕትንም፣ ስለ ሐጢአትም የሚሰዋ መሥዋዕትን አልወደድህም፤ በእርሱም


ደስ አላለህም ብሎ እነዚህም እንደ ሕግ የሚቀርቡት ናቸው፡፡ ቀጥሎ፡- እነሆ
አምላኬ ሆይ ፈቃድህን ላደርግ መጥቼአለሁ ብሎአል፡፡ ሁለተኛውንም ሊያቆም
የፊተኛውን ይሽራል፡፡ በዚህም ፈቃድ የኢየሱስ ክርስቶስን ሥጋ አንድ ጊዜ ፈጽሞ
በማቅረብ ተቀድሰናል፡፡ ሊቀ ካህናትም ሁሉ ዕለት ዕለት እያገለገለ ሐጢአትን
ሊያስወግዱ ከቶ የማይችሉትን እነዚያን መሥዋዕቶች ብዙ ጊዜ እያቀረበ
ቆሞአል፡፡ እርሱ ግን ስለ ሐጢአት አንድን መሥዋዕት ለዘላለም አቅርቦ
በእግዚአብሄር ቀኝ ተቀመጠ፤ ጠላቶቹም የእግሩ መረገጫ እስኪደረጉ ድረስ
ወደፊት ይጠብቃል፡፡ አንድ ጊዜ በማቅረብ የሚቀደሱትን የዘላለም ፍጹማን
አድርጎአቸዋልና፡፡ መንፈስ ቅዱስም ደግሞ ስለዚህ ይመሰክርልናል፤ ከዚያ ወራት
በኋላ ከእነርሱ ጋር የምገባው ኪዳን ይህ ነው ይላል ጌታ፤ በልባቸው ሕጌን
አኖራለሁ በልቡናቸውም እጽፈዋለሁ ብሎ ከተናገረ በኋላ ሐጢአታቸውንና
ዓመጻቸውንም ደግሜ አላስብም ይላል፡፡ የእነዚህም ስርየት ባለበት ዘንድ ከዚህ
ወዲህ ስለ ሐጢአት ማቅረብ የለም፡፡››
ይህ ምንባብ ሕጉ ‹‹ሊመጣ ያለው የበጎ ነገር ጥላ ነው›› ይላል፡፡ በብሉይ
ኪዳን እጆችን በመጫን ዓመታዊ ሐጢያቶችን ማስተላለፉ እውነት እንደነበር
ሁሉ ኢየሱስ በመጠመቅ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ለአንዴና ለመጨረሻ
መውሰዱም እውነት ነበር፡፡ ብሉይ ኪዳን የአዲስ ኪዳን ጥላ ነው፡፡ ጥላዎች
ሊኖሩ የሚችሉት እነርሱን የሚያጠሉ ትክክለኛ ነገሮች ሲኖሩ ብቻ ነው፡፡
ልክ እንደዚሁ በብሉይ ኪዳን የመስዋዕት ስርዓት ውስጥ የተገለጠው
የእግዚአብሄር ደህንነት የሚስተዋለው በኢየሱስ ክርስቶስ አገልግሎት አማካይነት
ነው፡፡ በብሉይ ኪዳን በርካታ ጠቦቶች፣ ፍየሎችና ዋኖሶች ታርደው
ለእግዚአብሄር ቀርበዋል፡፡ ነገር ግን የኮርማዎችና የፍየሎች ደም ሐጢያቶችን
ፈጽሞ ማስወገድ አልቻለም፡፡ ዘላለማዊው የሐጢያት ስርየት የሰማይ ሊቀ ካህን
በሆነው ኢየሱስ መፈጸም ነበረበት፡፡ ጌታችን ወደዚህ ዓለም የመጣው፣
የተጠመቀውና ስለ እኛም ደሙን ያፈሰሰው ለዚህ ነው፡፡
የዕብራውያን መጽሐፍ ስለ ኢየሱስ ሲናገር እርሱ የሰማይ ሊቀ ካህን
እንደሆነ ተናግሮዋል፡፡ በብሉይ ኪዳን በእነርሱ ፋንታ ለእግዚአብሄር
መስዋዕቶችን በማቅረብ የእስራኤሎችን ሐጢያቶች ያስተሰረየው ሊቀ ካህኑ
ነበር፡፡ ልክ እንደዚሁ ጌታችንም የሰማይ ሊቀ ካህን ሆኖ መጣ፡፡ ‹‹እነሆ
በመፅሐፍ ጥቅልል ስለ እኔ እንደተጸፈ አምላኬ ሆይ ፈቃድህን ላደርግ
መጥቻለሁ፡፡›› ኢየሱስ የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ ለማድረግ መጣ፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ሐጢያቶቻችሁን ለመደምሰስ የመጣው ኢየሱስ 89

የእግዚአብሄር አብ ፈቃድ ምን ይመስላችኋል? ፈቃዱ ሰዎችን ሁሉ


ከሐጢያቶቻቸው ማዳን ነው፡፡ በእርግጥ በዚህ ምድር ላይ የእግዚአብሄርን
ፈቃድ ማድረግ የቻለ ሰው የለም፡፡ የአብን ፈቃድ ማድረግ የቻለው አንዱ ብቻ
ነበር፡፡ እርሱም ሌላ ሳይሆን ኢየሱስ ነው፡፡ ኢየሱስ ለእግዚአብሄር አብ ፈቃድ
በመታዘዝ የሰውን ዘር ሐጢያቶች በሙሉ ስለተቀበለና ሁሉንም ስለደመሰሰ
አሁን አብ በልጁ የሚያምኑትን ልጆቹ አድርጎ ሊቀበላቸው ይችላል፡፡
የእግዚአብሄር አብ ፈቃድ ይህ ነበር፡፡ በሌላ አነጋገር የእርሱ ፈቃድ
ሐጢያቶቻችንን መደምሰስ ነበር፡፡
ኢየሱስ የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ በመከተል ወደዚህ ዓለም መጥቶ
በጥምቀቱ የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ ወሰደ፤ ደሙንም አፈሰሰ፤ በመስቀል
ላይም ሞተ፡፡ እንዲህ በማድረጉም አዲስ ሕይወትን ሰጠን፡፡ ጌታችን
በዕብራውያን 10፡9 ላይ፡- ‹‹አምላኬ ሆይ ፈቃድህን ላደርግ መጥቼአለሁ›› ያለው
ለዚህ ነው፡፡
ቁጥር 9 እንዲህ በማለት ይቀጥላል፡- ‹‹ሁለተኛውን ሊያቆም የፊተኛውን
ይሽራል፡፡›› የሕጉ መስዋዕታዊ ስርዓት ለሰዎች የዘላለም ደህንነትን መስጠት
አልቻለም፡፡ ስለዚህ እግዚአብሄር በሕጉ ሳይሆን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
ለሚያምኑት የዘላለምን ደህንነት ሰጥቷል፡፡ አንዳንድ የልግስና ሥራዎችን
በመስራት ወይም የንስሐ ጸሎቶችን በማቅረብ ወይም ለቤተክርስቲያኖቻችን ብዙ
መባ በመስጠት ሐጢያቶቻችንን ማንጻት እንችላለንን? ከእነዚህ አንዳቸውም
ሐጢያቶቻችንን ማንጻት አይችሉም፡፡ በራሳችን በጎ ምግባሮች አማካይነት
የሐጢያቶቻችንን ስርየት ማግኘት አንችልም፡፡ ጌታችን ሊጠመቅና ደሙን
ሊያፈስስ ወደዚህ ምድር የመጣው ለዚህ ነው፡፡
ዕብራውያን 10፡10 እንዲህ ይላል፡- ‹‹በዚህም ፈቃድ የኢየሱስ ክርስቶስን
ሥጋ አንድ ጊዜ ፈጽሞ በማቅረብ ተቀድሰናል፡፡›› ኢየሱስ አንድ ጊዜ በመጠመቅ፣
አንድ ጊዜ በመስቀል ላይ በመሞትና አንድ ጊዜ ዳግመኛ ከሙታን በመነሳት
በእርሱ ለሚያምኑት አዳኝ ሆኖላቸዋል፡፡ ውድ ክርስቲያኖች በሕጉ አማካይነት
የሐጢቶቻችሁን ስርየት ማግኘት እንደማትችሉ ማወቃችሁ ወሳኝ ነው፡፡ ነገር
ግን አንድ ጊዜ በውሃውና በኢየሱስ ደም እርሱ ራሱ አምላክ ስለመሆኑ ካመናችሁ
ሁላችሁም ሰማይ መግባት ትችላላችሁ፡፡
ኢየሱስ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ለማስወገድ በመጠመቁና ደሙን
በማፍሰሱ በሥጋው የዘላለም መስዋዕትን አቀረበ፡፡ እርሱ ወደዚህ ምድር
በመምጣት፣ በመጠመቅ፣ በመስቀል ላይ በመሞትና እንደገና ከሙታን በመነሳት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


90 ሐጢያቶቻችሁን ለመደምሰስ የመጣው ኢየሱስ

የዘላለም አዳኝ ሆነ፡፡ ኢየሱስ በተጠመቀ ጊዜ ሐጢያቶቻችሁ ለዘላለም ወደ


እርሱ ተላልፈዋልን? ኢየሱስ በመስቀል ላይ ነፍሱን ሲሰጥ ‹‹ተፈጸመ›› ያለው
ለዚህ ነውን? እግዚአብሄር የሕይወት መንፈስ ሕጉን በልባችን ውስጥ አስቀምጦ
ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ደምስሶዋልን? አሁን በዚህ ወንጌል በማመናችሁ
ጸድቃችኋልን? ወይስ አሁንም ድረስ ሐጢያተኞች ናችሁ?
ሁለችሁም ጻድቃን ናችሁ፡፡ ቃሉን ከመስማታችሁ በፊት ሁላችሁም
ሐጢያተኞች እንደነበራችሁ ግልጽ ነው፡፡ ነገር ግን ቃሉን ከሰማችሁ በኋላ አሁን
ጻድቃን ሆናችኋል፡፡ በዕውቀት የታደሰውንም አዲሱን ሰው ለብሳችኋል፡፡
(ቆላስያስ 3፡10) ታዲያ በኢየሱስ ውስጥ መጠመቅ የምንችለው እንዴት ነው?
በልባችን የኢየሱስን የጽድቅ አገልግሎት በማመን ከእርሱ ጋር አብረን ልንጠመቅ፣
አብረነው ልንሞትና አብረነው ሕያው ልንሆን እንችላለን፡፡ ከልብ የሚያምነው
የእምነት የመጀመሪያው መርህ ይህ ነው፡፡
ውድ ክርስቲያኖች ሁላችንም በእምነት ካልሆነ በቀር ሰማይ መግባት
የሚቻልበት ሌላ መንገድ እንደሌለ እንገንዘብ፡፡ የራሳችንን ጽድቅ ከማሳየት ይልቅ
ይህንን የኢየሱስን ጥምቀትና ደሙን ተረድተን እንመነው፡፡ እንዲህ በማድረግም
ሁላችንም ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ታጥበን ንጹህ እንሁን፡፡
እኔ በእምነቴ በጌታችን አማካይነት በተሰጠን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
ፊት ለእግዚአብሄር ወሰን የሌለውን ምስጋናዬን አቀርባለሁ፡፡ ልባዊ ተስፋዬና
ጸሎቴ እያንዳንዳችሁ በማቴዎስ 3፡13-17 ላይ የተገለጠውን የውሃና የመንፈስ
ወንጌል እውነት ወደ ማወቅና መረዳት ደርሳችሁ ሁላችሁም የእግዚአብሄር
ሕዝብ ትሆኑ ዘንድ በልባችሁ እንድታምኑበት ነው፡፡
የእርሱ ባርኮቶች በሙሉ ከእናንተ ጋር ይሁኑ! 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ምዕራፍ
4

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት
ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
በረከት ማለት እግዚአብሄርን
መፍራትና አምላክን ማገልገል ነው
‹‹ ማቴዎስ 4፡1-11 ››
‹‹ከዚያ ወዲያ ኢየሱስ ከዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ መንፈስ ወደ ምድረ በዳ
ወሰደው፡፡ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ከጦመ በኋላ ተራበ፡፡ ፈታኝም ቀርቦ፡-
የእግዚአብሄር ልጅ ከሆንህ እነዚህ ድንጋዮች እንጀራ እንዲሆኑ በል አለው፡፡
እርሱም መልሶ፡- ሰው ከእግዚአብሄር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ
ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጽፎአል አለው፡፡ ከዚህ በኋላ ዲያብሎስ ወደ ቅድስት
ከተማ ወሰደውና እርሱን በመቅደስ ጫፍ ላይ አቁሞ፡-
መላእክቱን ስለ አንተ ያዝልሃል
እግርህንም በድንጋይ ከቶ
እንዳትሰናከል በእጃቸው ያነሱሃል
ተብሎ ተጽፎአልና የእግዚአብሄር ልጅስ ከሆንህ ወደ ታች ራስህን ወርውር
አለው፡፡ ኢየሱስም፡- ጌታ አምላክህን አትፈታተነው ተብሎ ደግሞ ተጽፎአል
አለው፡፡ ደግሞ ዲያብሎስ እጅግ ረጅም ወደሆነ ተራራ ወሰደው፡፡ የዓለምንም
መንግሥታት ክብራቸውንም ሁሉ አሳይቶ፡- ወድቀህ ብትሰግድልኝ ይህን ሁሉ
እሰጥሃለሁ አለው፡፡ ያን ጊዜ ኢየሱስ፡- ሂድ አንተ ሰይጣን ለጌታህ ለአምላክህ
ስገድ፤ እርሱንም ብቻ አምልክ ተብሎ ተጽፎአልና አለው፡፡ ያን ጊዜ ዲያብሎስ
ተወው፡፡ እነሆም መላዕክት ቀርበው ያገለግሉት ነበር፡፡››

እኛን ከሐጢያቶቻችን ያዳነን የእግዚአብሄር ጽድቅ ኢየሱስ እኛን


ከሐጢያቶቻችን ለአንዴና ለመጨረሻ ለማዳን በአጥማቂው ዮሐንስ መጠመቁና
በመስቀል ላይ መሞቱ እግዚአብሄርም እርሱ አዳኝ መሆኑን መመስከሩ ነው፡፡
እርሱ አዳኝ ነበር፡፡ የዛሬው መጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ኢየሱስ በዮርዳኖስ ወንዝ
ከተጠመቀ በኋላ ስለሆነው ሁነት የሚተርክ ነው፡፡
ኢየሱስ ከተጠመቀ በኋላ በዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ ወደ ምድረ በዳ
ተወሰደ፡፡ ለ40 ቀናትና ለ40 ሌሊቶች ከጦመ በኋላ ስለተራበ ዲያብሎስ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


94 በረከት ማለት እግዚአብሄርን መፍራትና አምላክን ማገልገል ነው

ኢየሱስን በሦስት ፈተናዎች ሊፈትነው ሞከረ፡፡

የመጀመሪያ ፈተና፡፡

የመጀመሪያው የዲያብሎስ ፈተና በቁጥር 3 ላይ ተጽፎዋል፡- ‹‹ፈታኝም


ቀርቦ፡- የእግዚአብሄር ልጅ ከሆንህ እነዚህ ድንጋዮች እንጀራ እንዲሆኑ በል
አለው፡፡››
ኢየሱስ 40 ቀንና ሌሊት ከጦመ በኋላ ምን ያህል ተራበ? የኢየሱስ ሥጋ
በእጅጉ በተራበ ጊዜ ዲያብሎስ በምግብ ፈተነው፡፡ ‹‹የእግዚአብሄር ልጅ ከሆንህስ
እነዚህ ድንጋዮች እንጀራ እንዲሆኑ በል፡፡ ያን ጊዜ ልትበላቸው ትችላለህ! እንጀራ
እንዲሆኑ እዘዝ፤ ያን ጊዜ በሕይወት መኖር ትችላለህ! 40 ቀን ጦመሃል፤ እስከ
ሞት ድረስ የተራብህ መሆን አለብህ፤ መብላት የምትፈልገው ምን ያህል ነው?
እዚህ ምድረ በዳ ምን አለ? የእግዚአብሄር ልጅ ከሆንህ እንጀራ እንዲሆኑ ልታዝና
ልትበላቸው ትችላለህ፤ አትችልምን? ስለዚህ ብላ፤ ብላ፡፡››
ዲያብሎስ ኢየሱስን የፈተነው ኢየሱስ የእግዚአብሄር ልጅ እንደሆነ ስላወቀ
መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ዲያብሎስ ግን በምግብ ፈተነው፡፡ በሌላ አነጋገር በሥጋ
ሕይወቱ እየፈተነው ነበር፡፡ ‹‹በረሃብ ከምትሞት ይልቅ እነዚህን ድንጋዮች
እንጀራ አድርገህ በሕይወት መኖር ይገባሃል፡፡ አሁን በሕይወት መኖር ከፈለግህ
ለሥጋህ የሚሆን እንጀራ ያስፈልግሃል! ያን ጊዜ በሕይወት ትኖራለህ፡፡ ስለዚህ
ያንን አድርግ፡፡›› እርሱ ኢየሱስ በሕይወት የሚኖረው እንጀራ ሲበላ ብቻ
ይመስል በጣም በተራበ ጊዜ ፈተነው፡፡ ነገር ግን ኢየሱስ ‹‹ሰው ከእግዚአብሄር
አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም›› በማለት ይህንን
ተቃወመ፡፡
ውድ ክርስቲያኖች የሰው ሥጋና ነፍስ የሚኖረው በምንድነው? ሰው ለሥጋ
በሚሆን እንጀራ ለዘላለም መኖር ይችላልን? ዲያብሎስ ኢየሱስን ለሥጋ በሚሆን
እንጀራ ፈተነው፡፡ በሕይወት ለመኖር ማመን የሚገባን ምንድነው? ጌታ እንዲህ
አለ፡- ‹‹ሰው ከእግዚአብሄር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ
አይኖርም፡፡›› ይህ እውነት ነው፡፡
ሰው ሲራብ በሕይወት ለመቆየት እንጀራ መብላት እንደሚኖርበት
ያስባል፡፡ ነገር ግን የአንድ ሰው የሥጋና የነፍስ ሕይወት መሰረቱ በእግዚአብሄር
ቃል ማመን ነው፡፡ የእግዚአብሄር ቃል በዓለም ላይ ባይኖር ኖሮ መንፈሳችንና

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በረከት ማለት እግዚአብሄርን መፍራትና አምላክን ማገልገል ነው 95

ሥጋችን ለሞት የታጩ ይሆኑ ነበር፡፡ እግዚአብሄር ሥጋችንና ነፍሳችን


ከእግዚአብሄር አፍ በሚወጣው ቃል በማመን በሕይወት እንደሚኖሩ
ይነግረናል፡፡ ከተጻፈው የእውነት ቃል የተነሳ ነፍሳችን በእምነታችን አማካይነት
በእግዚአብሄር ቃል መኖር ትችላለች፡፡ ለሕይወት ምግብ ከሆነው የእግዚአብሄር
ቃል የተነሳ የእናንተና የእኔ ሥጋዎችና ነፍሶች በምልዓት መኖር ይችላሉ፡፡
እግዚአብሄር ቃሉን ለሰዎች ሰጥቶዋል፡፡ እርሱ በቃሉ አማካይነት
ይመግባል፡፡ ሐጢያቶችን ይቅር ይላል፡፡ ሰዎችም በሕይወት እንዲኖሩ
ይፈቅዳል፡፡ የእግዚአብሄር ቃል በዩኒቨርስ ውስጥ ያለውን ነገር ሁሉ ፈጥሮዋል፡፡
በዚህ ዓለም ላይ ሰዎች የሚያስፈልጋቸውን እያንዳንዱን ነገር ፈቅዶዋል፡፡
የእግዚአብሄር ቃል ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ጠራርጎ የሚያስወግድ ቃል ነው፡፡
የእግዚአብሄር ቃል ወደ ብርሃን የሚመራን የእውነት ቃል ነው፡፡ ስለዚህ
በሕይወት መኖር የሚችሉት በዚህ የሚያምኑ ብቻ ናቸው፡፡ በሕይወት መኖር
የምንችለው በእግዚአብሄር ቃል ብቻ ስናምን መሆኑንም ማወቅ ያስፈልገናል፡፡
ይህ እውነት ነው፡፡ ሰዎች ለሥጋ የሚሆን እንጀራ እየተመገቡ በሕይወት ከመኖር
ይልቅ የተጻፈውን የእግዚአብሄር ቃል በማመን እንደሚኖሩ ማወቅ አለብን፡፡
ጌታችን ስለ እግዚአብሄር ቃል ነግሮናል፡፡
በዚህ ዓለም ላይ ስንኖር በስስታችን ስለምንማረክ አንዳንድ ጊዜ በፈተና
እንወድቃለን፡፡ ሰዎች የተወሰነ መጠን ያለው ገንዘብ ካለን በድሎት እንኖራለን
ብለው ያስባሉ፡፡ ይህ ተገቢ ነው፡፡ ነገር ግን ሰው በእርግጥ በሕይወት
የሚኖርበት ነገር ምንድነው? ሰው በሕይወት የሚኖረው በምንድነው? ሰው
የተጻፈውን የእግዚአብሄር ቃል በማመን በሕይወት መኖር ይችላል፡፡
የእግዚአብሄር ቃል ባይኖር ኖሮ በእግዚአብሄር ማመን ወይም እግዚአብሄርን
ማግኘት ባልተቻለን ነበር፡፡
ሰው በሥጋ እንጀራ ብቻ ሊኖር አይችልም፡፡ በተለይም ጻድቃን መኖር
የሚችሉት ትክክለኛውን የእግዚአብሄር ቃል ትምህርቶች ሲሰሙ ብቻ ነው፡፡
ሰው የተሰራው ከሥጋ ብቻ ሳይሆን ከነፍስና ከመንፈስም ደግሞ ነው፡፡ ስለዚህ
በሕይወት ስንኖር የነፍስን ችግሮች መፍታት የምንችለው እውነተኛውን
የእግዚአበሄር ቃል ስንሰማ ብቻ ነው፡፡ ነፍሳችንና ሥጋችን የእግዚአብሄርን ቃል
በማንበብና በመስማት ይወፍራሉ፡፡ እኛም በድሎት እንኖራለን፡፡ የነፍሳችንን
ሐጢያቶች መንጻት መቀበል የምንችለው እውነተኛውን የሐጢያት ይቅርታ ቃል
ስንሰማ ብቻ ነው፡፡ እውነተኛውን የእግዚአብሄር ቃል የሰማ እያንዳንዱ ሰው
በዚህ በማመን በሥጋና በነፍስ መኖር የሚችለው ለዚህ ነው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


96 በረከት ማለት እግዚአብሄርን መፍራትና አምላክን ማገልገል ነው

ዲያብሎስ ሁልጊዜም እንደዚህ ባሉ ቃሎች ሰውን ሁሉ ይፈትናል፡፡


‹‹የእግዚአብሄር ልጅ ከሆንህ እነዚህ ድንጋዮች እንጀራ እንዲሆኑ እዘዝ፡፡ እነዚህን
ድንጋዮች እንጀራ አድርገህ ብላቸው፡፡ የእግዚአብሄር ልጅ ከሆንህ ይህንን
ማድረግ ይቻል የለ? ተርበሃል አይደል? አድርገው፤ አድርገው፤ እንጀራ ብታገኝ
በሕይወት መኖር ትችላለህ፡፡ አይደለምን? አንድ ሰው በሕይወት የሚኖረው
በቀን ሦስት ጊዜ ምግብ ሲመገብና ለ70 ወይም ለ80 ዓመታት በዓመት 365
ቀናት በቂ ምግብ ሲያከማች ነው፡፡ ሰው የሚመገገበው ምግብ ካለው በሕይወት
ይኖራል እንጂ ይሞታል እንዴ?›› ዲያብሎስ የሚነግረን ይህንን ነው፡፡
ዲያብሎስ ለሰዎች የሚነግራቸው ይህንን ነው፡፡ ብዙ ሰዎችም በዚህ
ተሞኘተው ወድቀዋል፡፡ ‹‹ትክክል ነው፤ ይህንን ባገኝ በሕይወት መኖር
እችላለሁ›› ብለው በማሰብ እዚህ ላይ የሚወድቁ ሰዎች አሉ፡፡ እየተነጋገርን
ያለነው የግድ ስለ ገንዘብ ብቻ ሳይሆን የምንፈልጋቸው ጥቂት ዓለማዊ ቁሳቁሶች
ቢኖሩን በሕይወት መኖር እንችላለን ስለሚለው እሳቤም ነው፡፡ ‹‹ያለ
እግዚአብሄር ቃል በሕይወት መኖር እችላለሁ፤ አልሞትም›› ብለን እናስባለን፡፡
ነገር ግን ይህ ትልቅ የተሳሳተ ስሌት ነው፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ ያለ
እግዚአብሄር ቃል ሥጋችንም ደግሞ ይሞታል፡፡ በእንጀራ፣ በዓለማዊ
የተትረፈረፈ ቁስ ወይም ዓለም በሚደሰትበት የጾታ ግንኙነት አይኖርም፡፡ ኢየሱስ
ዲያብሎስ በፈተነው ጊዜ የተናገረውን ነገር በጥንቃቄ ማድመጥ የሚያስፈልገን
ለዚህ ነው፡፡ ‹‹ሰው ከእግዚአብሄር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ
አይኖርም፡፡›› ዲያብሎስ የሚፈትነን ስንደክም፣ ስንራብና ጠኔ ሲይዘን ነፍሳችንም
ስተታክት ነው፡፡ እርሱ ሰዎችን ‹‹በሕይወት የምትኖረው እንጀራ ሲኖርህ ብቻ
አይደለምን? ይህንን መስክሩ ይላቸዋል፡፡›› ብዙ ሰዎች ያላቸውን ነገር አጢነው፡-
‹‹ኦ! ሕይወቴን የማቆይባቸው በቂ ሐብቶች አሉኝ! የእግዚአብሄርን ቃል
ባልሰማም በሕይወት እኖራለሁ፤ አልሞትም›› ይላሉ፡፡
ነገር ግን ውድ ክርስቲያኖች ዲያብሎስ እንደዚህ ቢፈትነንም እንኳን
የምንኖረው ከእግዚአብሄር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ
አይደለም፡፡ ይህንን በአእምሮዋችን እንደምንይዘው ተስፋ አደርጋለሁ፡፡
የእግዚአብሄር ቃል ከሌለን በሕይወት መኖር እንደማንችል ይህንን በአእምሮዋችን
እንደምንይዝ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡
በሕይወት መኖር የምትችሉት የእግዚአብሄር ቃል በልችሁ ውስጥ ሲኖር
ብቻ ነው፡፡ ውድ ክርስቲያኖች ይህ እንደዚህ ነው? እንደዚህ ነው፡፡ እኛ
የእግዚአብሄር ቃል ስላለ መኖር እንደምንችል አትርሱ፡፡ የሰው ዘር እስከ አሁን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በረከት ማለት እግዚአብሄርን መፍራትና አምላክን ማገልገል ነው 97

ድረስ የኖረው የእግዚአብሄር ቃል ስላለ ነው፡፡ የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል እስከ


ዓለም ዳርቻ ድረስ ሲሰራጭ ጌታ ይመጣል፡፡ እርሱ ሲመጣ ይህንን ዓለም ወደ
ፍጻሜ አምጥቶ አዲስ ዓለም እንደሚጀምር ተናግሮዋል፡፡ እነዚህ ሁሉ በቃሉ
መሰረት ይፈጸማሉ፡፡
ውድ ክርስቲያኖች የእግዚአብሄር ቃል እውነት ነው፡፡ ኢየሱስ ‹‹ሰው
ከእግዚአብሄር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም ተበሎ
ተጽፎዋል›› በማለት የመጀመሪያውን የዲያብሎስ ፈተና አሸነፈ፡፡ ዲያብሎስ
ይህንን ሲሰማ ተገረመ፡፡ ሆኖም ዲያብሎስ እዚህ ላይ የሚያቆም ዓይነት
አልነበረም፡፡

ሁለተኛ ፈተና፡፡

ሁለተኛው ፈተና በቁጥር 5 ላይ ተጠቅሶዋል፡- ‹‹ከዚህ በኋላ ዲያብሎስ


ወደ ቅድስት ከተማ ወሰደውና እርሱን በመቅደስ ጫፍ ላይ አቁሞ፡-
መላእክቱን ስለ አንተ ያዝልሃል
እግርህንም በድንጋይ ከቶ
እንዳትሰናከል በእጃቸው ያነሱሃል
ተብሎ ተጽፎአልና የእግዚአብሄር ልጅስ ከሆንህ ወደ ታች ራስህን ወርውር
አለው፡፡ ኢየሱስም፡- ጌታ አምላክህን አትፈታተነው ተብሎ ደግሞ ተጽፎአል
አለው፡፡››
ዲያብሎስ ኢየሱስን ወደ መቅደስ ጫፍ አውጥቶ ራሱን ወደ ታች
እንዲወረውር በመንገር ፈተነው፡፡ ‹‹መላእክቱን ስለ አንተ ያዝልሃል፤ እግርህንም
በድንጋይ ከቶ እንዳትሰናከል በእጃቸው ያነሱሃል ተብሎ ተጽፎአልና›› በማለት
የእግዚአብሄርን ቃል በእርሱ ላይ አዞረበት፡፡ ቀደም ብሎ በተጻፈው ቃል
ስላመንህ ፈተናዬን አሻፈረኝ አልህ፤ አላልህምን? ስለዚህ እንደተጻፈው ልታደርግ
ይገባሃል፡፡ እነዚህን ቃሎች ታምናለህ አይደል? ራስህን ወደታች ወርውር፤
በተጻፈው ቃል መሰረት እግዚአብሄር በእጆቻቸው ይደግፉህ ዘንድ መላእክቶችን
ይሰጥሃል፡፡ ራስህን ወደ ታች ስትወረውርም እግርህ በድንጋይ እንዳይሰናከል
ይሸከሙሃል፡፡ አሁኑኑ ሞከረው፡፡›› ያን ጊዜ ኢየሱስ እንዲህ አለ፡- ‹‹ጌታ
አምላክህን አትፈታተነው ተብሎ ተጽፎአልና፡፡››
ውድ ክርስቲያኖች አንዳንድ ጊዜ ዲያብሎስ የተጻፈውን የእግዚአብሄር ቃል

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


98 በረከት ማለት እግዚአብሄርን መፍራትና አምላክን ማገልገል ነው

በመጠቀም ሰዎችን ይፈትናል፡፡ ኢየሱስ ግን ጌታ አምላካችንን እንዳንፈትነው


ተናግሮዋል፡፡ ዲያብሎስ ኢየሱስን ‹‹በእርግጥ አትሞትም፤ ለምን? ምክንያቱም
አንተ የእግዚአብሄር ልጅ ነህና›› አለው፡፡ ይህ እውነት ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ
የእግዚአብሄር ልጅ ነው፡፡ ስለዚህ አይሞትም ነበር፡፡ ኢየሱስ ከእኛ ከሰዎች
የተለየ ነው፡፡ ዲያብሎስ ግን ፈተነው፡፡ የተጻፈው የእግዚአብሄር ቃል ግን
እግዚአብሄርን ‹‹አትፈታተነው›› ይላል፡፡ በሌላ አነጋገር እግዚአብሄርን
ከመፈታተን ይልቅ የተጻፈውን ቃልና እግዚአብሄርን በማመን መኖር ይገባናል፡፡
ብዙውን ጊዜ ሰዎች ኢየሱስን ይፈታተኑታል፡፡ ሰዎች እግዚአብሄርን
‹‹ይህንን አደረግሁ፤ ታዲያ እግዚአብሄር በዚህ መንገድ የሚያስተናግደኝ
ለምንድነው?›› በማለት እግዚአብሄርን ይፈታተኑታል፡፡ ነገር ግን በእግዚአብሄር
አምነን ከሆነ እርሱን መፈታተን አስፈላጊ አይደለም፡፡ እኛ እርሱን
የምንፈታተንባቸው ብቃቶች የሉንም፡፡ ልነንፈታተነውም አይገባንም፡፡
እግዚአብሄር በእኛ የሚፈተን አምላክ አይደለም፡፡ እኛ የምንፈተነው በስስታችን
ስለምንሳብ ነው፡፡ የምንፈተነው እግዚአብሄር ስለፈተነን አይደለም፡፡
ሰው አብርሃምን ምሳሌ በማድረግ በእግዚአብሄር ላይ ተቃውሞ ሊያስነሳ
ይችለል፡፡ ‹‹እግዚአብሄር አብርሃም ልጁን ይስሐቅን መስዋዕት አድርጎ
እንዲያቀርብ የጠየቀው ለምንድነው? እግዚብሄር አብርሃም አምኖ እንደሆነ
ወይም እንዳልሆነ ለማየት የፈተነው አይደለምን?›› ነገሩ እንደዚያ አይደለም፡፡
እግዚአብሄር አብርሃምን መፈተኑ አልነበረም፡፡ እግዚአብሄር አብርሃም በእርግጥ
ምን ያህል በትክክል የእግዚአብሄርን ቃል በልቡ የሚያምን እምነት እንደነበረውና
እንዴት በእምነቱ የእምነት አባት እንደሆነ ሊያሳየን የፈቀደበት ሒደት ነው፡፡
ውድ ክርስቲያኖች በእግዚአብሄር ቃል ማመን አለብን፡፡ እግዚአብሄር
ባታየንም የተጻፈውን የእግዚአብሄር ቃል እግዚአብሄር የተናገረው የእግዚአብሄር
ቃል መሆኑን ማመን አለብን፡፡ የእግዚአብሄርን ቃል በማመን የእግዚአብሄር ቃል
በምልዓቱ እንደሚፈጸም እናያለን፡፡ ስለዚህ ማመን አለብን፡፡ የእግዚአብሄር ቃል
እንደዚህ ከሆነ እንደተጻፈው ልናምነው ይገባናል፡፡ ሁኔታዎችና አጋጣሚዎች
ምንም ያህል ቢናወጡና ቢለዋወጡም በቃሉ ላይ ያለንን እምነት በሚመለከት
መናወጥ አይገባንም፡፡
የእግዚአብሄር ቃል እንዲህ ከሆነ እውነቱ ያ ነው፡፡ የእግዚአብሄር ቃል
እንደሚለው ካልተፈጸመም ችግሩ ያለው በእኛ ዘንድ ነው፡፡ እምነታችን
የሚናወጠው እምነት ስለሌለን ወይም እምነታችን ጠንካራ ስላልሆነ ነው፡፡
አንዳንድ ጊዜ እምነት ያለን ይመስለናል፡፡ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ እምነት ያለን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በረከት ማለት እግዚአብሄርን መፍራትና አምላክን ማገልገል ነው 99

አይመስለንም፡፡ በአጭሩ ቃሉ እንደሚናገረው የማንፈጽመው በእግዚአብሄር ቃል


ላይ ችግር ስላለ ሳይሆን እምነታችን ችግር ስላለው ነው፡፡
እግዚአብሄር የአምላክን ቃል ከልባቸው ለሚያምኑ ሰዎች ተዓምራትን
ያደርግላቸዋል፡፡ ነገር ግን ያልጸና እምነት ያላቸው ሰዎች አንዳች ሊያገኙ
እንዳይመስላቸው እግዚአብሄር ተናግሮዋል፡፡ (ያዕቆብ 1፡7-8) እምነታችን ምንም
ያህል ትነሽ ብትሆንም አስፈላጊው ነገር ማመናችን ወይም አለማመናችን ነው፡፡
እኛ ማመን አለብን፡፡ እግዚአብሄርንም መፈተን የለብንም፡፡ በአግዚአብሄር ቃል
ብናምን የሐጢያት ስርየትን እናገኛለን፡፡ ይህም ቃሉ እንደሚለው በእኛ
ይፈጸማል፡፡ ውድ ክርስቲያኖች ታምናላችሁን? --አዎ--፡፡
ለእናንተና ለእኔ አስፈላጊው ነገር በእግዚአብሄር ቃል የሚያምነው እምነት
ነው፡፡ እግዚአብሄር የሚያየው የሰውን ልብ እንጂ ውጫዊ ገጽታ አይደለም፡፡
እግዚአብሄር የሚያየው ማመኑን፣ በእምነት መሰረት መንቀሳቀሱንና በእምነት
መኖሩን ነው፡፡ ይህ ማለት ግን አሁኑኑ ጠንካራ የሆነውን እምነታችሁን
ለእግዚአብሄር ማሳየት ይኖርባችኋል ማለት አይደለም፡፡ እምነታችሁ እንደ
ሰናፍጭ ቅንጣት ትንሽ ብትሆንም እንኳን ‹‹አምናለሁ እምነት ይጎድለኛል፤ ነገር
ግን አምናለሁ፡፡ ይህንን የማደርገው ስለማምን ነው፡፡ በአንተ ስለማምን
መልስህን እጠብቃለሁ፡፡ የተስፋ ቃልህን ስለማምን እከተልሃለሁ›› በማለት
በቃሉ ላይ ያላችሁን እምነት መመስከር ይኖርባችኋል፡፡ እግዚአብሄር እንዲህ
ያለውን የተረጋጋና ጽኑ እምነት በልባችን ውስጥ ያያል፡፡ ዲያብሎስ እናንተንና
እኔን ሲፈትነን በተጻፈው ቃል በማመን እናባርረዋለን፡፡

ሦስተኛ ፈተና፡፡

ሦስተኛው ቁጥር እንዲህ ይነግረናል፡- ‹‹ደግሞ ዲያብሎስ እጅግ ረጅም


ወደሆነ ተራራ ወሰደው፡፡ የዓለምንም መንግሥታት ክብራቸውንም ሁሉ
አሳይቶ፡- ወድቀህ ብትሰግድልኝ ይህን ሁሉ እሰጥሃለሁ አለው፡፡ ያን ጊዜ
ኢየሱስ፡- ሂድ አንተ ሰይጣን ለጌታህ ለአምላክህ ስገድ፤ እርሱንም ብቻ አምልክ
ተብሎ ተጽፎአልና አለው፡፡››
ለጌታህ ለአምላክህ ስገድ፤ እርሱንም ብቻ አምልክ ተብሎ ተጽፎአልና፡፡››
እኛ የእግዚአብሄር ሰዎች ማድረግ የሚኖርብን ለእግዚአብሄር መስገድና ለእርሱ
ብቻ መስገድ ነው፡፡ በእግዚአብሄርና በእኛ መካከል የሚያስፈልገው ምንድነው?

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


100 በረከት ማለት እግዚአብሄርን መፍራትና አምላክን ማገልገል ነው

በእግዚአብሄር ፊት መኖር የሚገባንስ እንዴት ነው?


እግዚአብሄርን መፍራት፣ ለእርሱ መስገድ፣ እርሱን ማመንና ፈቃዱ ከሆነም
መከተል አለብን፡፡ እግዚአብሄር የቃሉ አምላክ ስለሆነና ቃል ሆኖም ስለሚኖር
እርሱን ስናምን ቃሉን እናምናለን፡፡ እርሱንም እናመልካለን፡፡ በዚሀ እምነትም
እንከተለዋለን፡፡ በእርሱ ፊት መኖር ያለብን እንዲህ ነው፡፡ ‹‹ለጌታህ ለአምላክህ
ስገድ፤ እርሱንም ብቻ አምልክ፡፡›› እናንተና እኔ ሰዎችም በሙሉ በእግዚአብሄር
ፊት ማድረግ ያለባቸው ተግባር ይህ ነው፡፡ በሕይወታችን ውስጥ እግዚአብሄርን
ከማወቅ፣ በታላቁ አምላክ ከማመን፣ ፈጣሪ አምላክን ከመታዘዝ፣ ለእርሱ
ከመስገድ፣ እርሱን ከማመን፣ ከመከተልና ከማምለክ በቀር ሌላ ብዙ ልናደርገው
የሚያስፈልገን ነገር የለም፡፡ ክቡር ተግባራችን ይህ ነው፡፡ ይህም እንደዚሁ ነው፡፡
ዲያብሎስ ኢየሱስን ወደ ረጅም ተራራ ወስዶ የዓለምን መንግሥታቶችና
ክብራቸውን አሳየው፡፡ በዓለም ላይ እጅግ ትልቁ ተራራ ምንድነው? የኤቨረስት
ተራራ ነው፡፡ ተራራው 8,848 ሜትር ከፍታ አለው፡፡ ይህንን ማስታወስ በጣም
ቀላል ነው አይደል? ውድ ክርስቲያኖች ምናልባት ዲያብሎስ ዓለምን ያሳየው
በኤቨረስት ተራራ ላይ አቁሞት ይሆናል፡፡ ዲያብሎስ ኢየሱስን እጅግ ረጅም
ተራራ ጫፍ ላይ አውጥቶ ዓለምን አብረው ካዩ በኋላ ኢየሱስ ወድቆ
ቢሰግድለትና ቢታዘዘው ዓለምን ሁሉ እንደሚሰጠው ነገረው፡፡
ኢየሱስ ግን ምን አለ? ኢየሱስ እንዲህ አለ፡- ‹‹አንተ ሰይጣን ሂድ፡፡ ለጌታህ
ለአምላክህ ብቻ ስገድ፡፡ እርሱንም ብቻ አምልክ ተብሎ ተጽፎአልና፡፡ መስገድና
ማምለክ የሚያስፈልገኝ ለአንተ ሳይሆን ለእግዚአብሄር አብ ነው፡፡ ለዚህ ዓለም
ክብር አልሰግድም፡፡ አላመልከውምም፡፡›› ኢየሱስ የተናገረው ይህንን ነው፡፡
ለእግዚአብሄር መስገድና ማምለክ ደስታችን፣ እርካታችንና ሙላታችን
ነው፡፡ ለእግዚአብሄር መስገድና እርሱን ማምለክ የሰው ሁለንተና ነው፡፡ ማድረግ
የሚኖርብን ይህንን ነው፡፡ ሌላ ምንም የሚደረግ ነገር የለም፡፡ ከዚህ የሚበልጥ
ዋጋ ያለውና የከበረ ምንም ነገር የለም፡፡ ለእግዚአብሄር መስገድ እያንዳንዱን
የእግዚአብሄር ቃል መቀበል ነው፡፡ የእርሱ ፍጥረት አድርጎ ለሰራን አምላክ
ከመስገድ የሚበልጥ ምን የተሻለ ነገር አለ? ከዚህ የበለጠ ምን የተሻለ ሕይወት
ሊኖር ይችላል? እኛ በትህትና ለእግዚአብሄር እንሰግዳለን፡፡ ስለ በረከቶቹ ሁሉ፤
በእርሱ ስላለው ነገር ሁሉ እግዚአብሄርን እናመሰግነዋለን፡፡
ለእኛ በረከት ማለት ለእግዚአብሄር መስገድ የምንችል መሆናችን ነው፡፡
በፊቱ ስንጎነበስ፣ ስንታዘዘው፣ በእርሱ ስናምንና የውሃውንና የመንፈሱን ወንገል
ስናሰራጭ እግዚአብሄር በሰማያዊ በረከቶች ይቀባናል፡፡ ሁሉን የሚሰጠን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በረከት ማለት እግዚአብሄርን መፍራትና አምላክን ማገልገል ነው 101

እግዚአብሄር ስለሆነ እርሱ የእኛ ሁለንተና ነው፡፡ እርሱን ሁለንተናችን ስለሆነ፣


ዳግመኛ ለተወለዱት ሁሉን ነገር ስለሆነ ለእግዚአብሄር መስገድ በረከት እንደሆነ
ታውቃላችሁ ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡
አሁንም እንኳን እግዚአብሄር ሕያው ስለሆነ ደስተኞች ነን፡፡ ባርኮቶቹን
የተቀበልን በሕይወት እየኖርን ነው፡፡ አምላክ ስላለ፣ እኛም እግዚአብሄርን
የሚፈራ ልብ ስላለን በባርኮቱ ልናከብረው እንችላለን፡፡
ዲያብሎስ የዓለምን መንግሥታቶች በሙሉ አሳይቶ ብንስግድለት ሁሉን
እንደሚሰጠን ተናግሮዋል፡፡ በዚህ ዓለም ላይ የማናውቃቸው ብዙ ታላላቅ ነገሮች
አሉ፡፡ ለቅጽበት ያህልም በእነርሱ ልንማረክ እንችላለን፡፡ ነገር ግን የዓይን አዋጅ
የሆኑ ብዙ ነገሮች ቢኖሩም ለዲያብሎስ አንሰግድም፡፡
ዲያብሎስ በዓለማዊ ቁሳቁስ ቢፈትነንና እርሱን አምላክ አድርገን
ብናመልከውም በዓለም ላይ ያለውን ነገር ሁሉ እንደሚሰጠን ቢነግረን ‹‹ሂድ
አንተ ሰይጣን ለጌታህ ለአምላክህ ስገድ፤ እርሱንም ብቻ አምልክ ተብሎ
ተጽፎአልና›› በማለት በተጻፈው የእግዚአብሄር ቃል ልናባርረው ይገባናል፡፡
በተጨባጭ ሲታይ ዲያብሎስ ብዙ ነገሮችን ሊሰጠን አይችልም፡፡ ዲያብሎስ
አምላክ የሆነ ይመስል በኢየሱስ ላይ በመቀለድ ‹‹በፊቴ ብትሰግድልኝ ይህንን
ሁሉ እሰጥሃለሁ›› አለው፡፡ በትክክል ሲታይ ግን የሁሉ ነገር ባለቤት ማነው?
ኢየሱስ ነው፡፡
ውድ ክርስቲያኖች በዩኒቨርስ ውስጥ ያለው ሁሉ ነገር የማነው? የእናንተ
የጻድቃኖች ነው፡፡ በዩኒቨርስ ውስጥ ያለው እያንዳንዱ ነገር የማነው?
የእግዚአብሄር ልጆች ነው፡፡ እግዚአብሄር የሰማይ ወራሾች ብሎ የጠራን ለዚህ
ነው፡፡ እርሱ ዳግመኛ የተወለዱትን የሰማይ ወራሾች ብሎ ይጠራቸዋል፡፡ ይህ
ዩኒቨርስ ወራሽ አለው፡፡ ወራሹ ማነው? ጻድቃን ናቸው፡፡
ዲያብሎስ ግን እንዲህ ይላል፡- ‹‹በፊቴ ስገዱልኝ፤ በእግዚአብሄር ባታምኑ
በእኔ እመኑ፤ ተከተሉኝም፡፡ በዓለም ላይ ያለውን ነገር ሁሉ እሰጣችኋለሁ፡፡››
ዲያብሎስ ብዙውን ጊዜ የሚጠቀምበት ዘዴ ይህ ነው፡፡ ዲያብሎስ በአንድ ወቅት
በዚህ መንገድ አደናቅፎኛል፡፡ ይህ በኢየሱስ ከማመኔ በፊት በእኔ ላይ
የተጠቀመው ዘዴ ነው፡፡ በነገራችን ላይ ዲያብሎስ በሦስተኛው ዙር ተዘርሮ
ወጥቷል፡፡
ውድ ክርስቲያኖች በእግዚአብሄር ፊት መኖር የሚገባን እንዴት ነው?
ለእግዚአብሄር የሚሰግድ ሕይወትን መኖር ያስፈልገናል፡፡ በሕይወት ዘመናችን
ሁሌም እርሱን ብቻ ማምለክ ይኖርብናል፡፡ እግዚአብሄር ሐጢያቶቻችንን ሁሉ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


102 በረከት ማለት እግዚአብሄርን መፍራትና አምላክን ማገልገል ነው

በውሃና በደም ይቅር ብሎ አጽናንቶናል፡፡ ልጆቹም አድርጎናል፡፡ ለእግዚአብሄር


የምንሰግድበትንና አምላክን የምናመልክበትንም በረከት ሰጥቶናል፡፡ የደህንነትን
በረከት ለሰጠን አምላክ ምስጋናን ማቅረብ፣ በእምነት ለእርሱ መስገድና
በሕይወት ዘመናችን ሁሉ እርሱን ማምለክና ማገልገል ይገባናል፡፡
ሐጢያቶቻችንን ያነጻውን የእግዚአብሄር ቃል በጥንቃቄ አጢኑት፡፡ ጌታ
በጥምቀቱ አማካይነት ሐጢያቶቻችንን በሙሉ በመውሰድ፣ በመስቀል ላይ
በመሰቀልና ስለ እኛም የሐጢያቶችን ፍርድ በመቀበል አንጽቶናል፡፡ ጌታ እኛን
በውሃውና በደሙ በማጠብና በማንጻት የእግዚአብሄር ሕዝቦች አድርጎን
ለእግዚአብሄር መስገድና አምላክን ማምለክ የምንችልበትን በረከት ሰጥቶናል፡፡
በእናንተና በእኔ ላይ እየገፋ የመጣው ፈተና ምን ዓይነት ነው? እነዚህን
ፈተናዎች የምታባርሩትስ እንዴት ነው? በዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ላይ
ኢየሱስ ለገጠሙት ሦስት ፈተናዎች ትክክለኛውን መልስ ሰጥቶናል፡፡ እርሱ
የዲያብሎስን ፈተናዎች የተቋቋመው በእግዚአብሄር ቃል ላይ ባለው እምነቱ
ነበር፡፡ ይህንን መልስ ከተረዳንና ሕይወታችንን ከኖርን፣ በዚህም ካመንን እኛም
ደግሞ እነዚህን ፈተናዎች መቋቋም እንችላለን፡፡ ለእግዚአብሄር መስገድ በረከት
ቢሆንም በሚገባ አላወቅነውም፡፡
ውድ ክርስቲያኖች እርሱን ያለ ገደብ ከማገልገል ይልቅ መገልገል የተሻለ
ነው ብላችሁ ታስባላችሁን? ነገር ግን እናንተና እኔ እግዚአብሄርን ማገልገላችን
ጥሩ ነገር ነው፡፡ ውድ ክርስቲያኖች ለእግዚአብሄር መስገድ ታላቅ በረከት ነው፡፡
በጣም ከፍ ያለ ሥልጣን ላለው ሰው መስገድ ትልቅ በረከት ነው፡፡ እንደዚያ ነው
ወይስ አይደለም? እንደዚያ ነው፡፡ በዚህ ዓለም ላይ አንድን ሰው ማገልገል
ይኖርብናል፡፡ ማንንም ሳናገለግል መኖር አንችልም፡፡ በእርግጥ ሰዎችን እንጂ
ዲያብሎስን አናገለግልም፡፡ በማናቸውም ሁኔታ ውስጥ የማን አገልጋይ
እንደምንሆን መወሰን ይኖርብናል፡፡ ውድ ክርስቲያኖች በዚህ ሁኔታ ውስጥ
እግዚአብሄርን ማገልገላችን ትልቅ በረከት አይደለምን? ሆኖም ይህንን ሳናውቅ
በመኖራችን ኢየሱስ ሦስተኛውን ፈተና ተቀብሎ ትክክለኛውን መልስ ነገረን፡፡
‹‹ለጌታህ ለአምላክህ ስገድ፤ እርሱንም ብቻ አምልክ፡፡››
ውድ ክርስቲያኖች በእግዚአብሄር ቃል ማመን አለብን፡፡ የእግዚአብሄርን
ቃል ስንሰማ ‹‹ኦ! ኢየሱስ ትክክለኛ መልሶችን ሰጥቶናል፡፡ ለእግዚአብሄር ስሰግድ
በዚህ መንገድ መኖር ትከክል ነው፡፡ የእግዚአብሄር ቃል ከሆነ መስገድ ጽድቅ
ነው፡፡ አንዳንድ ጊዜ የማልረባ፣ ገልቱ፣ ሰነፍና ጅል ብሆንም ትልቅ በረከት
የተቀበልሁ ሰው ነኝ ‹ይህ የእኔ ሕይወት ነው› ማለት በማንም ሳልገድብ በልቤ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በረከት ማለት እግዚአብሄርን መፍራትና አምላክን ማገልገል ነው 103

ፈቃድ መኖር እንደሚገባኝ ባስብም ነገሩ ግን እንደዚያ አልነበረም፡፡ አሁን በዚያ


መንገድ መኖር እንግዳ ነገር እንደሆነ አውቄያለሁ፡፡ ጌታን አለቃዬ አድርጌ
መቀበሌና የእግዚአብሄር አገልጋይ ሆኜ መኖሬ ጽድቅ ነው›› እንላለን፡፡
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል እውነት መረዳትና ተባርኮ በመኖር የሚያምን
እምነት ሊኖረን ይገባል፡፡ አንዳንድ ጊዜ ራሳችንን ስንመለከት ገልቱዎች
ብንመስልም እናንተና እኔ ለእግዚአብሄር መስገድና አምላክን ማገልገል መቻላችን
እውነት ነው፡፡ ይህ ለእናንተ ትልቅ ዕድልና ጻድቅ የሕይወት መንገድ እንደሆነ
ማወቅ አለባችሁ፡፡
አሁን እግዚአብሄርን እያገለገልሁ ባይሆን ኖሮ ምን እንደማገለግል
አላውቅም ነበር፡፡ በእርግጥም የሥጋ ተድላዎችን የሚሰጡኝን የዚህን ምድር
አማልክቶች አገልግል ነበር፡፡ በየቀኑ እጠጣና እየበላ ነበር፡፡ እንዴት እንደምኖር
በመጨነቅም የዚህን አገር አማልክቶች አመልክ ነበር፡፡ ሁሉም ዓይነት መጠጥ
አምላኬ ሊሆን ይችል ነበር፡፡ እነዚህን የሙጥኝ ብዬ በመያዝ እኖር ነበር፡፡
ውድ ክርስቲያኖች ኢየሱስ ዳግመኛ እንድንወለድ አድርጎን ምን ዓይነት
ሕይወት መኖር እንዳለብንና ትክክለኛው እውነተኛ እምነትም ምንም ዓይነት
እምነት እንደሆነ ነግሮናል፡፡ ጎዶሎዎችና ደካሞች ብንሆንም ከዚህ በፊት
እንደነበርነው አይደለንም፡፡ መዳን የምንችልበትን እግዚአብሄርን
የምናውቅበትንና ለእግዚአብሄር የምንሰግድበትን በረከት የሰጠንን ጌታ
እንደምታመሰግኑት ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ እናንተ ጌታን የሚያመሰግን ልብ አላችሁ
አይደል? አዎ በአያሌው አመስጋኞች መሆናችን በእርግጥም በረከት ነው፡፡
ኢየሱስ ሦስቱንም ፈተናዎች በሙሉ በመቋቋም ይህንን እምነት ሰጥቶናል፡፡
ሰው በእግዚአብሄር ቃል እንደሚኖር ማመን፣ እግዚአብሄርን ልንፈታተነው
እንደማይገባን ማመን፣ በሕይወታችንም ለእግዚአብሄር መስገድና ጌታን ማምለክ
ጽድቅ እንደሆነ ማመን፡፡ እግዚአብሄር ትልቅ በረከት የሆነውን እምነት ሰጥቶናል፡፡
እምነት ሊኖረን ይገባል፡፡ በሕይወታችንም ለእግዚአብሄር እየሰገድንና አምላክን
እያመለክን መኖር ይገባናል፡፡
መኖር ያለብን እንደዚህ ነው፡፡ ውድ ክርስቲያኖች ታምናላችሁን? -አዎ-፡፡
ይህ ጽድቅ መሆኑን ታምናላችሁን? -አዎ-፡፡ ይህ ጻድቅ የሕይወት መንገድ
መሆኑን በልባችን ማመን አለብን፡፡
እኛ ጻድቃኖች ጉድለት ያለብን ብንሆንም ለእግዚአብሄር መስገድ
መቻላችን እንዴት ያለ ባርኮት ነው? የቃሉ አምላክ ያለን ሰዎች የመሆናችን ይህ
ባርኮት ምንኛ ታላቅ ባርኮት ነው? ለእግዚአብሄር ምስጋናን እናቀርባለን፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


104 በረከት ማለት እግዚአብሄርን መፍራትና አምላክን ማገልገል ነው

እግዚአብሄር ይህንን የጽድቅ እምነት ለሁላችንም ሰጥቶናል፡፡ እግዚአብሄር


ይህንን እምነት በዓለም ላይ ለሚኖር ለእያንዳንዱ ሰው እንደሚሰጥ ተስፋ
እናደርጋለን፡፡ የእናንተና የእኔ ነፍስ በእግዚአብሄር ቃል በማመን ሁልጊዜም
ከእግዚአብሄር ዘንድ በረከትን እንድትቀበል ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ምዕራፍ
5

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት
ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
የተራራው ስብከት
‹‹ ማቴዎስ 5፡1-16 ››
‹‹ሕዝቡንም አይቶ ወደ ተራራው ወጣ፡፡ በተቀመጠም ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ
ወደ እርሱ ቀረቡ፡፡ አፉንም ከፍቶ አስተማራቸው፤ እንዲህም አለ፡-
በመንፈስ ድሆች የሆኑ ብጹዓን ናቸው
መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና፤
የሚያዝኑ ብጹዓን ናቸው
መጽናናትን ያገኛሉና፡፡
የዋሆች ብጹዓን ናቸው
ምድርን ይወርሳሉና፡፡
ጽድቅን የሚራቡና የሚጠሙ ብጹዓን ናቸው
ይጠግባሉና፡፡
የሚምሩ ብጹዓን ናቸው ይማራሉና፤
ልበ ንጹሆች ብጹዓን ናቸው
እግዚአብሄርን ያዩታልና፡፡
የሚያስተራርቁ ብጹዓን ናቸው
የእግዚአብሄር ልጆች ይባላሉና፡፡
ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ ብጹዓን ናቸው
መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና፡፡
ሲነቅፉአችሁና ሲያሳድዱአችሁ በእኔም ምክንያት ክፉውን ሁሉ በውሸት
ሲናገሩባቸው ብጹዓን ናችሁ፡፡ ዋጋችሁ በሰማያት ታላቅ ነውና ደስ ይበላችሁ፤
ሐሴትም አደረጉ፤ ከእናንተ በፊት የነበሩትን ነቢያትን እንዲሁ አሳድደዋቸዋልና፡፡
እናንተ የምድር ጨው ናችሁ፤ ጨው አልጫ ቢሆን ግን በምን ይጣፍጣል? ወደ
ውጭ ተጥሎ በሰው ከመረገጥ በቀር ወደፊት ለምንም አይጠቅምም፡፡ እናንተ
የዓለም ብርሃን ናችሁ፡፡ በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሰወር አይቻላትም፡፡
መብራትንም አብርተው ከዕንቅብ በታች አይደለም እንጂ በመቅረዙ ላይ
ያኖሩታል በቤት ላሉት ሁሉም ያበራል፡፡ መልካሙን ሥራችሁን አይተው
በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት
ይብራ፡፡››

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


108 የተራራው ስብከት

በማቴዎስ ምዕራፍ 5 ቁጥር 1-7 ላይ ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱና ለእኛ


ሲናገር እናነባለን፡፡ ክርስቲያኖች ይህንን ስብከት ‹የተራራው ስብከት› ብለው
ጠርተውታል፡፡ ምክንያቱም ኢየሱስ እነዚህን ነገሮች የተናገረው በተራራ ላይ
ነበርና፡፡

በመንፈስ ድሆች ለሆኑ የተሰጠ ብጽዕና፡፡

በመጀመሪያ ማቴዎስ ምዕራፍ 5 ቁጥር 3ን ስናነብ ኢየሱስ እንዲህ ይላል፡-


‹‹በመንፈስ ድሆች የሆኑ ብጹዓን ናቸው መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና፡፡››
ጌታ ‹‹በመንፈስ ድሆች የሆኑ›› ሲል ሰማይን የሰጠው በመንፈስ ድሆች ለሆኑት
ብቻ ነው ማለቱ ነው፡፡
‹‹በመንፈስ ድሆች የሆኑ ብጹዓን ናቸው›› የሚለው ትምህርቱ እውነት
ነው፡፡ ኢየሱስ የተናገረላቸው የመንፈስ ድሆች በዚህ ዓለም እርካታ የላቸውም፡፡
ስለዚህ ጌታ የሰጠውን ደህንነት ተቀብለዋል፡፡ መንፈሳችሁ በዓለማዊ ቁሳቁሶች
የሚረካ ከሆነ እርሱ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት የሰጠውን
የሐጢያት ስርየት በልባችሁ መቀበል አይቻላችሁም፡፡ በመንፈስ ድሆች
ከሆናችሁ መንግሥተ ሰማይ የእናንተ ትሆናለች ያለው ለዚህ ነው፡፡ እግዚአብሄር
ለእናንተ በመንፈስ ድሆች ለሆናችሁ የሐጢያት ይቅርታንና መንግሥተ ሰማይን
ይሰጣችኋል፡፡

በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት ለሚያለቅሱ የተሰጠ


ብጽዕና፡፡

በማቴዎስ 5፡4 ላይ ያለው የኢየሱስ ሁለተኛው ትምህርት እንዲህ ይላል፡-


‹‹የሚያለቅሱ ብጹዓን ናቸው፡፡ መጽናናትን ያገኛሉና፡፡›› እርሱ ይህንን ትምህርት
የሰጠው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምኑ በእግዚአብሄር ፊት በሰሩዋቸው
ሐጢያቶች ምክንያት ሲሰቃዩ በማየቱ ጌታ በሐጢያቶቻቸው ምክንያት
በእግዚአብሄር ስለሚያዝኑ ነው፡፡ እግዚአብሄርን የሚያውቅና እርሱ ሕያው
እንደሆነ የሚያምን ሰው ለሐጢያቶቻቸው ያለቅሳሉ፡፡ እግዚአብሄር በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት ደህንነትን በመስጠት ያጽናናቸዋል፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የተራራው ስብከት 109

በእርግጥ በኢየሱስ ብናምንም ብዙውን ጊዜ በእግዚአብሄር ፊት ስህተቶችን


እንፈጽማለን፡፡ ሐጢያቶችንም እንሰራለን፡፡ ነገር ግን በፈጸሙዋቸው ሐጢያቶች
ምክንያት ልባቸው ለተጎዳ ሰዎች አግዚአብሄርን ቢያውቁም በእግዚአብሄር ፈቃድ
አልኖሩም፡፡ አሁንም ድረስ ሐጢያቶችን ይሰራሉና፡፡
በእርግጥ በኢየሱስ ብናምንም ብዙውን ጊዜ በእግዚአብሄር ፊት ስህተቶችን
እንፈጽማለን፡፡ ሐጢያቶችንም እንሰራለን፡፡ ነገር ግን በፈጸሙዋቸው ሐጢያቶች
ምክንያት ልባቸው ለተጎዳ ሰዎች የእግዚአብሄር መጽናናት አለ፡፡ ምክንያቱም
እግዚአብሄርን ቢያውቁም በእግዚአብሄር አልኖሩም፡፡ አሁንም ድረስ
ሐጢያቶችን ይሰራሉና፡፡
በእግዚአብሄር ፊት በብዙ መንገዶች ጎዶሎዎች ነን፡፡ በእርግጥ አንዳንዶች
በደሎቻቸውና መተላለፎቻቸው ላይሰሙላቸው ይችላሉ፡፡ ምክንያቱም
እግዚአብሄር በሰጠው ደመ ነፍስ መንቀሳቀስ መጥፎ ሊሆን አይችልም የሚል
ውሳኔ ላይ ደርሰዋልና፡፡ ሆኖም ስንወድቅ በእግዚአብሄር ፈቃድ ሳንኖር ስንቀር
የሚያለቅስ ልብ ከሌለን መጽናናትን አናገኝም፡፡ እናንተና እኔ ስለ ክፉ
ምግባሮቻችን በእግዚአብሄር ፊት ስናለቅስና እርስ በርሳችንም ስለ ሐጢያቶቻችን
ስናለቅስ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምን ልብ ሊኖረን ያስፈለጋል፡፡
ልባችን እግዚአብሄር በሰጠን የደህንነት መጽናናት ብቸኛው መንገድ ይህ ነው፡፡

የዋሆች የሚቀበሉት ብጽዕና፡፡

መጽሐፍ ቅዱስ በማቴዎስ 5፡5 ላይ ‹‹የዋሆች ብጹዓን ናቸው ምድርን


ይወርሳሉና›› ይላልና፡፡ ልባችን በእግዚአብሄር ፊት የዋህ የሚሆንበት ምክንያት
አለ፡፡ ልባችን በእግዚአብሄር ፊት የዋህ ሲሆን እርሱ ለልባችን የሚናገራቸውን
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል የደህንነት ቃሎች መቀበል አንችልም፡፡ የዋህ
ያልሆነ ልብ ችግር ያለበት ለዚህ ነው፡፡ የልባችን አዝማሚያ በእግዚአብሄር ፊት
አስፈላጊ የሆነው ለዚህ ነው፡ ግብዞች ሰዎችን ለጊዜው ሊያሞኙ ይችላሉ፡፡ ነገር
ግን የእግዚአብሄርን ቃል በየዋህ ልብ እስካልተቀበሉ ድረስ ከእግዚአብሄር ጋር
ዘላለማዊ ሕብረት ሊኖራቸው አይችልም፡፡
‹የእግዚአብሄር ቃሎች በሙሉ ተዓማኒት ያላቸው መሆናቸውን› በልባችን
መቀበል አለብን፡፡ እግዚአብሄር በተጻፈው የአምላክ ቃል በኩል ተናግሮናል፡፡
እግዚአብሄር በቃሉ አማካይነት እንዲህ ይለናል፡- ‹‹በቅድመ አያቶቻችሁ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


110 የተራራው ስብከት

ምክንያት በሐጢያቶች የተሞላችሁ ናችሁ፡፡›› ስለዚህ ሁላችንም የእግዚአብሄርን


ቃሎች የሚቀበል ልብ ሊኖረን ይገባናል፡፡ እውነት የሆነው እግዚአብሄር
የተናገራቸው ማናቸውም ቃሎች በሙሉ (ማስታወሻ፡-‹‹ተዓማኒ እውነት››
የሚለው የተለመደ የአሜሪካውያን መግለጫ አይደለም) እውነት ናቸው፡፡
የእግዚአብሄርን ቃሎች በሙሉ በየዋህነት በልባቸው የሚቀበሉ ሰዎች መንግሥተ
ሰማይን የሚወርስ እምነት ሊኖራቸው ይችላል፡፡
በእግዚአብሄር ፊት የዋህ ልብ ያላቸው ሰዎች እግዚአብሄር የነገረንን ቃሎች
እንዳሉ በጽናት ያምኑዋቸዋል፡፡ ስለዚህ እግዚአብሄር ስለ ውሃውና መንፈሱ
ወንጌል ይነግራቸዋል፡፡ በልባቸው የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለተቀበሉ
ሰዎችም የሺህ ዓመቱን መንግስት ርስት አድርጎ ይሰጣቸዋል፡፡ ይህ እምነት አዲስ
ምድርን እንድንወርስ የሚያስችለን እምነት ነው፡፡

የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለማገልገል ለሚፈልጉ የተሰጠ


ብጽዕና፡፡

ቁጥር 6 እንዲህ ይላል፡- ‹‹ጽድቅን የሚራቡና የሚጠሙ ብጹዓን ናቸው


ይጠግባሉና፡፡›› እነዚህ ቃሎች የእግዚአብሄርን ሥራ የሚጠሙ ሰዎች
የእግዚአብሄርን ጽድቅ ይጠግባሉ ማለት ናቸው፡፡ ጻድቃን እግዚአብሄርን
ለማገልገል ይራባሉ፡፡ ስለዚህ የመንፈሳቸውን መብል ይበሉ ዘንድ የጽድቅ ሥራን
ይሰራሉ፡፡ ምክንያቱም የእግዚአብሄር ቃሎች በሙሉ ለሰው ነፍስ ሕይወትን
የሚሰጡ መብል ናቸውና፡፡ (ኢሳይያስ 55፡1) የእግዚአብሄር ሥራም ለጻድቃን
መንፈሳዊ ማዕድ ነው፡፡ ይህ እውነት ዳግመኛ ላልተወለዱ ሰዎች ድብቅ ምስጢር
ነው፡፡ ጻድቃን ከቤተክርስቲያን ጋር በመተባበር ሆዳቸውን በጽድቅ ምግባሮች
ይሞላሉ፡፡
እኛ የሐጢያቶችን ስርየት በማግኘት ጻድቃን የሆንን ሰዎች ወይ
የእግዚአብሄርን ሥራ እንራባለን አለበለዚያም በሥጋ ፍላጎቶች እንራባለን፡፡
እግዚአብሄር የአምላክን የጽድቅ ሥራ የመስራት ፍላጎት ላለው ሰው ሁሉ
ሁልጊዜም በቤተክርስቲያኑ አማካይነት የጽድቅን ሥራ በሙላት እንዲሰራ
ያስችለዋል፡፡ እግዚአብሄር የእርሱን ሥራ መስራት እንችል ዘንድ መንፈሳዊ
እምነትን ሰጥቶናል፡፡ የጽድቅ ሥራን ስንሰራም ያጠግበናል፡፡ ለእግዚአብሄር
የጽድቅ ሥራዎችን መስራት የሚፈልጉ ሰዎች የመንፈስን ሙላት እንደሚያገኙ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የተራራው ስብከት 111

ከተሞክሮ ይማራሉ፡፤
የእግዚአብሄርን የጽድቅ ሥራ ተርባችኋልን? እንደዚያ ከሆነ የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል በማሰራጨትና የእግዚአብሄርን ሥራ በመስራት
የመንፈሳችሁን ሙላት ትቀበላላችሁ፡፡ ውጫዊው ማንነታችሁ ሥጋዊ ፍላጎቶችን
የመከተል ልብ ቢኖረውም በውስጣችሁ ያለው መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሄርን
የጽድቅ ሥራ ይራባል፡፡ ሁልጊዜም የጽድቅን ሥራ መስራት ይሻል፡፡
ጌታችን በማቴዎስ ምዕራፍ 4 ላይ እንዲህ ብሎዋል፡- ‹‹ሰው ከእግዚአብሄር
አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም፡፡›› ኢየሱስ 40 ቀን
ከጦመ በኋላ ዲያብሎስ ወደ ኢየሱስ ቀርቦ ‹‹የእግዚአብሄር ልጅ ከሆንህስ እነዚህ
ድንጋዮች እንጀራ እንዲሆኑ በል›› አለው፡፡ ዲያብሎስ ኢየሱስንና ማንኛውንም
ሌላ ሰው ሁሉ ‹‹ለሥጋ የሚሆን እንጀራ ሕይወትን ይሰጣል›› በማለት
ይፈትናል፡፡ ነገር ግን እንደዚያ አይደለም፡፡ ‹‹ሰው ከእግዚአብሄር አፍ በሚወጣ
ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም፡፡›› ሰው ለሥጋ በሚሆን እንጀራ ብቻ
አይኖርም፡፡ ምክንያቱም ሰዎች መንፈስ አላቸውና፡፡ ስለዚህ ሰዎች ለሥጋ
የሚሆን እንጀራ መብላት ያስፈልጋቸዋል፡፡ ነገር ግን ደግሞ ከእግዚአብሄር አፍ
የሚወጣውንና የመንፈስ ምግብ የሆነውን የእግዚአብሄር ቃልም መመገብ
ያስፈልጋቸዋል፡፡ ሥጋችንና መንፈሳችን በሕይወት ሊኖሩ የሚችሉበት ብቸኛው
መንገድ ይህ ነው፡፡
በመሰረቱ ይህ እውነት እግዚአብሄር የተናገረው የአምላክ ቃል መንፈሳችን
በሕይወት ይኖር ዘንድ እንደሚያደርገው ይነግረናል፡፡ እኛ ጻድቃኖች ለሥጋችን
የሚሆነውን እንጀራ በመመገብ ብቻ በሕይወት መኖር አንችልም፡፡ ነገር ግን
ከእግዚአብሄር የሚወጣውን የእግዚአብሄር ቃል በመስማትና በማመን በሕይወት
መኖር መቻል አለብን፡፡ ዳግመኛ የተወለደ ሰው ምንም ያህል ብዙ እንጀራ
ቢመገብ መራቡና መጠማቱ አይቀርም፡፡ ምክንያቱም መንፈስ ቅዱስ በጻድቃን
ልብ ውስጥ ስለሚኖር የጽድቅ ምግባሮችን በማድረግ ልንኖር ይገባናል፡፡ ያም
ማለት ጻድቃን በሕይወት መኖር የሚችሉት ከእግዚአብሄር አፍ የሚወጣውን
ቃል ሁሉ በመስማትና በማመን ነው፡፡ ይህም እኛ በሕይወት መኖር የምንችለው
የእግዚአብሄርን ቃል ሁሉ በማመንና ጌታንም በእምነት በመከተል እንደሆነ
ያሳየናል፡፡
ዳግመኛ የተወለዱ ሰዎች መንፈስ የእግዚአብሄርን ጽድቅ ይራባል፡፡ ሰዎች
በሕይወት የሚኖሩት ከእግዚአብሄር የሚወጣውን ቃል ሁሉ በመስማትና
በማመን እንጂ ለሥጋ በሚሆን እንጀራ አይኖሩም፡፡ የጻድቃን መንፈስ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


112 የተራራው ስብከት

የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በማሰራጨት በመንፈሳዊ መጥገብ ይደሰታል፡፡


የጻድቃን መንፈስና ሥጋ ሌሎችን ከሐጢያቶች የሚያድን የጽድቅ ሥራ በመስራት
በሕይወት ይኖራል፡፡
ዳግመኛ በተወለዱ ቅዱሳን ልብ ውስጥ የጽደቅ ሥራዎችን የመስራት
ፍላጎት አለ፡፡ እኛ ጻድቃኖች የዚህ ዓለም በሆነው ነገር ብቻ ፈጽሞ መኖር
አንችልም፡፡ እኛ በሥጋ ብቻ ፈጽሞ መኖር አንችልም፡፡ ደካማ እምነት ያላቸው
ጻድቃኖች እንዲህ ያስባሉ፡- ‹‹የሐጢያቶችን ስርየት ስለተቀበልሁ አሁን
የምግብን፣ የልብስንና የመጠለያን ችግር ለመፍታት ብቻ እኖራለሁ፡፡›› እንዲህ
የሚያስብ ጻድቅ ሰው መጨረሻው የራሱን ፍላጎቶች መከተልና ውሎ አድሮም
ሕይወቱን ማጣት ይሆናል፡፡
ሆኖም ጻድቅ ሰው የሥጋ ፍላጎቶቹን በመከተል ብቻ በሕይወት መኖር
አይችልም፡፡ ጻድቅ ሰው የሥጋ ፍላጎቶቹን ቢከተል እንኳን የሥጋ ፍላጎቱን
ሊፈጽም አይችልም፡፡ እርሱ የሥጋን ፍላጎቶች ብቻ የሚከተል ከሆነ የጻድቅ ሰው
ልብ ባዶ ይሆናል፡፡ በሌላ በኩል እኛ ዳግመኛ የተወለድን ሰዎች የጽድቅን
ምግባሮች የምንራብና የምንጠማ ሰዎች ነን፡፡ ስለዚህ ሁልጊዜም የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል በማሰራጨት እንደሰታለን፡፡ ጻድቅ ሰው የእግዚአብሄርን ቃል
በማመንና የጽድቅ ሥራዎችን በመስራት የመንፈስንና የሥጋን ደህንነት
ይለማመዳል፡፡
ብዙውን ጊዜ አዳዲስ ምዕመናኖች ይህንን የእምነት እውነት አይረዱም፡፡
ስለዚህ በእምነታቸው ደካማ የሆኑ ሰዎች ብዙውን ጊዜ ሥጋዊ ፍላጎቶችን
ይከተላሉ፡፡ የሥጋን ፍላጎቶች የሚከተሉ ጻድቃን ሰዎች በሥጋ ነገሮች
በዲያብሎስ ይፈተናሉ፡፡ ጻድቅ ሰው ለዚህ ፈተና ከተሸነፈ በእርግጥም ይሞታል፡፡
ጌታ ጽድቅን የሚራቡና የሚጠሙ ሰዎች ብጹዓን ናቸው ያለው ለዚህ
ነው፡፡ አሁን እናንተና እኔ የእግዚአብሄርን ጽድቅ የምንፈጽም ሰዎች ሆነናል፡፡
ስለዚህ የመንፈሳችን እውነተኛ መብል የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ስናሰራጭ
ለእናንተና ለእኔ የመንፈስ መብላችን ይሆናል፡፡
ጌታችን በዚህ ምድር ላይ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር አብሮ ሳለ ለሥጋው
የሚሆን ምግብ የፈለገበት ጊዜ ነበር፡፡ በአንድ ወቅት የሰማርያ ከተማ በሆነችው
በሲካር ሳሉ የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት ምግብ ፍለጋ ርቀው ሄዱ፡፡ ደቀ
መዛሙርት ምግቡን ይዘው ከመጡ በኋላ ‹‹ጌታ ሆይ ይህንን ብላ›› ባሉት ጊዜ
ጌታ ‹‹እኔ እናንተ የማታውቁት መብል አለኝ›› አላቸው፡፡ እርሱ የጠቀሰው ያ
ምግብ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል የማሰራጨት ሥራ ነበር፡፡ ኢየሱስ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የተራራው ስብከት 113

በውሃው ጉድጓድ አጠገብ ለነበረችው ሴት እርሱ መሲህ መሆን በነገራት ጊዜ


ይህንን ማለቱ ነበር፡፡
ኢየሱስ የአብን ፈቃድ በመፈጸም ለመንፈሱ የሚሆን መብል እንዳዘጋጀ
ማወቅ አለብን፡፡ ደቀ መዛሙርት ገናም በመንፈስ ያልጠኑ ስለነበሩ ይህን እውነት
ባለማወቃቸው ኢየሱስ ይህንን ነገራቸው፡፡ እነዚህ ለእናንተ፣ ለእኔና ለሌሎች
ዳግመኛ የተወለዱ ክርስቲያኖች የሚሆኑ ቃሎች ነበሩ፡፡
ስለዚህ የጻድቃን መንፈስ በሕይወት ይኖር ዘንድ መንገዱ የእግዚአብሄርን
ጽድቅ መከተል፣ ማመን፣ መፈጸምና በየቀኑ መጥገብ ነው፡፡ ጻድቃን
የእግዚአብሄርን ጽድቅ በማመንና በመፈጸም ጠግበዋል፡፡ የእግዚአብሄርን ጽድቅ
ስንፈጽም እንጠግባለን፡፡ እግዚአብሄርንም ስናመሰግን በሕይወት እንኖራለን፡፡
የእግዚአብሄርን ጽድቅ ለሚራቡና ለሚጠሙ ሰዎች የተዘጋጀ በረከት አለ፡፡
የእግዚአብሄርን ጽድቅ ተርባችሁ ተጠምታችኋልን? --አዎ-- እኔም
የእግዚአብሄርን ጽድቅ ተጠምቻለሁ፡፡ ስለዚህ በዚህ ዘመን ይህንን የእግዚአብሄር
ሥራ ከሰራሁ በኋላ ለጽድቁ የሚሆን ሌላ ሥራ እሰራለሁ፡፡ የእግዚአብሄርን ሥራ
እሰራለሁ፡፡ የእግዚአብሄርን ሥራ እሰራለሁ፡፡ ጽድቅንም በመሻትና በመፈጸም
እቀጥላለሁ፡፡
አንድ ቀን ‹ዎርልድ ትራቭል› የሚል የቴሌቪዥን ፕሮግራም ተመለከትሁ፡፡
በዚህ ፕሮግራም በተለያዩ የዓለም ክፍሎች ሁሉ የተጓዙ ሰዎች በዓለም ላይ
በተለያዩ አገሮች ዞረው ያነሱዋቸውን ፊልሞች ያሰዩ ነበር፡፡ ፕሮግራሙን
ስመለከት ‹‹ለዚያች አገር የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ማሰራጨት ይገባኛል››
ብዬ አሰብሁ፡፡ ፕሮግራሙን የተመለከቱ ብዙ ሰዎች እንኳን በአዲሱ ባህል ያን
ያህል ሲደሰቱ ፕሮግራሙን ስመለከት እኔ ጻድቁ ሰው በዚያች አገር የሚኖሩ
ሰዎች የውሃና የመንፈስ ወንጌል እንደሚያስፈልጋቸው ተረዳሁ፡፡ ጻድቃን
የሚያዩት ነገር ምንም ይሁን ጽድቅን ስለሚራቡና ስለሚጠሙ አተያያቸው ለየት
ያለ ነው፡፡ እኛ ጻድቃኖች የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በዓለም ላይ
የእግዚአብሄርን ጽድቅ ለማያውቁ ሰዎች የማሰራጨቱ አስፈላጊነት ይታወቀናል፡፡
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለእነርሱ ብናሰራጭ ምን ይከሰታል?
ከሐጢያቶቻቸው ይድናሉ አይደል? በትክክል! የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
በዚያች አገር ለሚኖሩ ሰዎች ማሰራጨት ከፈልግን በመጀመሪያ ልናደርገው
የሚገባን ነገር አለ፡፡ ያም የዚያችን አገር ቋንቋና ባህል የሚያውቅ ሰው ማግኘት
ነው፡፡ በመጀመሪያ በተለያዩ ቋንቋዎች የሚተረጉሙ ተርጓሚዎችን ለማግኘት
የምንሞክረው ለለዚህ ነው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


114 የተራራው ስብከት

እግዚአብሄር የጽድቅ ሥራዎችን ለመስራት ሲሉ ጽድቅን የሚራቡና


የሚጠሙ ሰዎችን ሁልጊዜም ያግዛል፡፡ መተርጎም የሚችሉ ሰዎችን ለማግኘት
ስንሞክር እነርሱን ማግኘት የምንችለው በኢንተርኔት ማስታወቂያ ስንለቅና
ማስታወቂያዎችን ስናወጣ እንደሆነ ተገንዝበናል፡፡ በመጨረሻም አንዳንድ
ምላሾችን አገኘን፡፡ ብዙ ፍላጎት ያላቸው ሰዎችም አመለከቱ፡፡ እኛም በእያንዳንዱ
ቋንቋ ብቃት ያላቸውን ተርጓሚዎች ከመረጥን በኋላ የትርጉሙን ሥራ ለእነርሱ
በአደራ ሰጠናቸው፡፡
እኛ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በዓለም ለሚኖሩ ሰዎች የማሰራጨት
ሥራ የምንሰራ ጻድቃን ሰዎች ነን፡፡ ጻድቃን ጽድቅን በዓለም ላይ ላለ
ለእያንዳንዱ የጠፋ ነፍስ ማሰራጨት ይፈልጋሉ፡፡ እኛ ዳግመኛ የተወለድን ሰዎች
የጽድቅን ወንጌል በዓለም ላይ ለሚኖር ለእያንዳንዱ ሰው ማሰራጨት
ስለምንፈልግ እንራባለን፡፡
የእግዚአብሄር ጽድቅ ለጻድቃኖች ነፍስ እውነተኛ የሕይወት መብል ስለሆነ
ጽድቅን የሚራቡና የሚጠሙ ሰዎች ይጠግባሉ፡፡ ጻድቃን የእግዚአብሄርን ጽድቅ
በዚህ ዓለም ላይ ሳይተገብሩ መኖር አይችሉም፡፡ መንፈሳዊ መብል ከሌላቸው
መጨረሻቸው በመንፈስ ጠኔ መሞት ነው፡፡ በመንፈሳዊ አነጋገር ጻድቃን ፍሬ
እንደሚያፈሩ መልካም ዛፎች ናቸው፡፡ እኛ ሰዎች ለሥጋችን የሚሆን ምግብ
ባንመገብ እንደምንራብ ሁሉ የሐጢያቶችን ስርየት የተቀበሉ ጻድቃንም ጽድቅን
የማይፈጽሙ ከሆኑ ከመንፈስ ጠኔ የተነሳ በሕይወት መኖር አይችሉም፡፡ ጓዴ
ክርስቲያኖች ጽድቅን የማይፈጽም ወይም ከቤተክርስቲያናችሁ ጋር የማይስማማ
ሕይወትን ለመኖር ሞክሩ፡፡ ያን ጊዜ መንፈሳችሁ በእግዚአብሄር ጽድቅ ጠኔ
እንደተመታ በግልጽ ይታወቃችኋል፡፡ የጻድቃን ሰዎች ልብ ጽድቅን ስለሚራብና
የእግዚአብሄርን ሥራ ለመስራት ስለሚሻ የመንፈስን መብል መብላት ይፈልጋል፡፡
በእምነታቸው ያልበሰሉ ሰዎች የመንፈስን መብል በመብላት መቀጠል
ያስፈልጋቸዋል፡፡ ነገር ግን እምነታቸው የተወሰነ መጠን ያለው መንፈሳዊ መብል
ከተመገበና ጽድቅን ከፈጸመ በኋላ በተወሰነ ደረጃ ካደገ የደህንነትን ደስታ
ይደሰታሉ፡፡ የእምነት ጽድቅን የተከተሉት ለዚህ ነው፡፡ እኔ ብዙውን ጊዜ
ለጓደኞቼ ‹‹ከዚህ በኋላ ዕረፍት እንውሰድ›› እላቸዋለሁ፡፡ ሆኖም ያንን ማድረግ
አስቸጋሪ ነው፡፡ እናንተና እኔ የእግዚአብሄርን ሥራ ባንሰራ የሚገጥመንን
የመንፈስ ሞት እንዴት ልንቋቋመው እንችላለን! የመንፈስን ሥራ ማከናወን
ይኖርብናል፡፡
የምወዳችሁ ክርስቲያኖች ሥጋችሁ ሲራብ አትበሉምን? እስከ ሞት ድረስ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የተራራው ስብከት 115

እንደተራባችሁ ሲሰማችሁ መብላት ይኖርባችኋል፡፡ ስለዚህ የእግዚአብሄርን


ጽድቅ የሚራብና የሚጠማ ማንም ሰው የእግዚአብሄርን ሥራ መስራት አለበት፡፡
እንዲህ ዓይነት ሰዎች የተባረኩ ሰዎች ናቸው፡፡ ጌታችን ሁልጊዜም እነዚህን
ቃሎች ለጻደቃን ይነግራቸዋል፡፡ እኛ ጻድቃኖች የእግዚአብሄርን ሥራ ስንሰራ
በመንፈስ እንጠግባለን፡፡ ውድ ክርስቲያኖች መጥገብ ከፈለጋችሁ በእግዚአብሄር
ሥራ ውስጥ ትጉሃን ሁኑ!
ሆኖም የእግዚአብሄርን ሥራ ብቻችሁን መስራት አትችሉም፡፡ ስለዚህ
የእግዚአብሄርን ሥራ እርስ በርሳችን ተባብረን ልንሰራ ይገባናል፡፡
የእግዚአብሄርን ቃል መስማት ጽድቅ ነው፡፡ የእግዚአብሄርን ቃል ማንበብና
ከእግዚአብሄር ዘንድ ዕርዳታን ለመጠየቅ መጸለይም ለእግዚአብሄር ጽድቅ ነው፡፡
በእያንዳንዱ የሥልጣን ቦታ ላይ በታማኝነት መስራትም ለእግዚአብሄር ጽድቅ
የሚሰራ ሥራ ነው፡፡ ጌታ ‹‹ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሄርን መንግሥት
ጽድቁንም ፈልጉ፤ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል›› ብሎዋል፡፡ እግዚአብሄር
አስቀድመን ጽድቅን እንድንፈልግ ነግሮናል፡፡ ያ ማለት በመጀመሪያ ስለ
እግዚአብሄር በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ ስለ ጉዳዮች እናስባለን ማለት ነው፡፡
በእግዚአብሄር ፊት እንደዚህ ከሆንን ከእግዚአብሄር ዘንድ የሥጋና መንፈስ
እውነት ይህ ነው፡፡ ክርስቲያኖችና የእግዚአብሄር አገልጋዮች ፈጽሞ ሊረሱት
የማይገባው እውነት ይህ ነው፡፡

የሚምሩ ሰዎች የሚቀበሉት ብጽዕና፡፡

ማቴዎስ 5፡7 እንዲህ ይላል፡- ‹‹የሚምሩ ብጹዓን ናቸው ይማራሉና፡፡››


በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ለሌሎች ምህረትን ማድረግ ማለት ለሐጢያተኞች
መራራት ማለት ነው፡፡ ሐጢያተኛ የሆኑ ሰዎችን ስናይ ‹‹እንዴት ያሳዝናል!››
ብለን እናስባለን፡፡ እኛ ጻድቃኖች ዳግመኛ ያልተወለዱ ነፍሳቶችን ስናይ
ያሳዝኑናል፡፡ እነዚህ የአገራችን ሰዎች ብቻ አይደሉም፡፡ በዓለም ላይ ባሉ ብዙ
ሌሎች አገሮች ውስጥ የሚኖሩ ሰዎችንም ስናይ ነገሩ ተመሳሳይ ነው፡፡
ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ቻይና ባደረግሁት የሚሽን ጉዞ ከጓደኛዬ ጋር ዕረፍት
ለማድረግ በቤጂንግ በሚገኝ አንድ የቡና መጠጫ መደብር ገባሁ፡፡ አጠገባችን ዳቦና
ሁለት ኩባያ ቡና ያዘዙ ሁለት ምዕራባውያን መንገደኞች አገኘሁ፡፡ ለአገሪቱ
ስለሚሆኑት የሚሽን ዕቅዶች በጥብቅ ስንነጋገር እነርሱም እርስ በርሳቸው ለሁለት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


116 የተራራው ስብከት

ሰዓታት ያህል ይነጋገሩ ነበር፡፡ አንዱ ሲናገር ሌላው ያዳምጥና ‹አዎ› ይላል፡፡ ሌላው
ሲናገር የመጀመሪያው ሰው ‹አዎ› ይላል፡፡ እርስ በርሳቸው በመነጋገርና
በመደማመጥ ይደሰቱ ነበር፡፡ የውይይታቸው ይዘት ምንም ነገር ይሁን ለውይይት
ያላቸው ረሃብ በጣም ከልብ የመነጨ ይመስል ነበር፡፡
እኔ የዚህ ዓይነት ሰዎች ስመለከት ርህራሄ ይሰማኛል፡፡ እነርሱ ስለማይረቡ
የሥጋ ጉዳዮች ሲወያዩ ከልባቸው ነበር፡፡ ነገር ግን የውሃውንና የመንፈሱን
ወንጌል ከእኛ መስማት ያስፈልጋቸዋል፡፡ ሊወያዩበት የሚገባቸው በጣም ወሳኙ
ርዕስም ይህ ነው፡፡ የዚህ ዓይነት ሰዎች ስመለከት ሐዘኔታ ይሰማኛል፡፡
ቢኩራሩም የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ስለማያውቁ ያሳዝናሉ፡፡
በእኛ የጻድቃኖች ልብ ውስጥ ለጠፉት ነፍሳቶች መብል ይሆኑ ዘንድ
መጽሐፎችን የማተምና ለእያንዳንዱ ግለሰብ የማሰራጨት ፍላጎት አለን፡፡
አገራችን ከሰለጠኑት ምዕራባውያን አገሮች ጋር ስትነጻጸር ብዙ ሐብትና ብሄራዊ
ጉልበት ባይኖራትም እኛ ጻድቃኖች በዚህ ዓለም ላይ ለሚኖር ለእያንዳንዱ ነፍስ
ሐዘኔታ አለን፡፡ ብዙ ሐብት ባላቸው አገሮች የሚኖሩ ሰዎች እንኳን በጻድቃን
ዓይን ሲታዩ የሚያሳዝኑ ናቸው፡፡
‹‹የሚምሩ ብጹዓን ናቸው፤ ይማራሉና፡፡›› ይህ ማለት ለሌሎች የሚራሩ
ሰዎች ምህረትን ይቀበላሉ ማለት ነው፡፡ ልንምራቸው የሚገቡን ሰዎች እንደምን
ብዙ ናቸው! ይህ በመላው ዓለም እውነት ነው፡፡

የሐጢያት ይቅርታ ላገኙ ሰዎች የተሰጠ ብጽዕና፡፡

ጌታ በማቴዎስ 5፡8 ላይ እንዲህ ብሎዋል፡- ‹‹ልበ ንጹሆች ብጹዓን ናቸው፡፡››


ልበ ንጹሆች እግዚአብሄርን ያዩታል ብሎዋል፡፡ ውድ ክርስቲያኖች በመሰረቱ ልበ
ንጹሆች በእግዚአብሄር ቃልና በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን የሐጢያት
ስርየትን የተቀበሉ ሰዎች ናቸው፡፡ የሥጋ ምኞቶቻቸውን ሳይሆን የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል የሚከተሉ ሰዎች ልበ ንጹሆች ናቸው፡፡
ትናትና በቴሌቪዥን አንድ ታሪካዊ ድራማ ተመለከትሁ፡፡ በድራማው ውስጥ
ከንጉሡ ባለሟሎች አንዱ በመጨረሻ በንጉሡ ላይ ያምጸና ቤተ መንግሥቱን
ያጠቃል፡፡ በዙፋኑ ላይ የተቀመጠው ሰው በዓመጹ ይደናገጣል፡፡ በመጨረሻ
የንጉሡ ባለሟል የእርሱ አገልጋዮች ከሆኑት ጋር በመተባበር የአገር ክህደትን
ያሴራሉ፡፡ በመጀመሪያ ባለሟሉ ዙፋኑን የመውሰዱን ጉዳይ ይቃወማል፡፡ ‹‹ፈጽሞ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የተራራው ስብከት 117

ያንን አላደርግም፤ ባለሟል ሆኜ ንጉሡን መክዳት ከምከተላቸው መርሆዎች ጋር


የሚቃረን ነው፡፡›› ነገሩ መርሆዎችን የሚያወቅና ጻድቅም እንደሆነ ወደ ማስመሰል
የተቃረበ ነበር፡፡ ነገር ግን ይህ ሰው ፈሪ ነበር፡፡ ዙፋኑን ለመረከብ አጋጣሚን
ሲጠብቅ ነበር፡፡ በመጨረሻ ይህ ከእርሱ ፈቃድ ውጭ ስለመሆኑ በማስመሰል
ንጉሡን ለመገልበጥ የተባባሪዎቹን ፍላጎት ተቀበለ፡፡ በሚስቱ አሳማኝነትም ይህንኑ
አደረገ፡፡ በዚህ ዓለም ላይ አብዮት የሚያስነሱ ሁሉ እንደዚሁ ናቸው፡፡ ስለዚህ
አንድ ሰው እንዳለው ፖለቲካ የእያንዳንዱን ሰው የግል ፍላጎቶች የሕዝብ ፍላጎቶች
የማድረግ ሒደት መሆኑ ትክክል ነው፡፡
ውድ ክርስቲያኖች ጌታችን የእኛን ድጋፍ ሊያጣ ይችላልን? አይችልም፡፡
ጌታ ከሁሉ በላይ የሆነ የነገሥታት ንጉሥና ለእኛም መልካም ንጉሥ ነው፡፡
የነገሥታት ንጉስ ራሱን ዝቅ አድርጎ ሕዝቡን ከሐጢያቶቻቸው አድኖዋቸዋል፡፡
የሕዝቡን ሐጢያቶች በሙሉ አስወግዶ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
አድኖዋቸዋል፡፡ ታዲያ የእርሱ ሕዝብ በታማኝነት ይከተለዋል ወይስ
አይከተለውም? እነርሱ በፈቃዳቸው ንጉሣቸውን ይከተሉታል፡፡
የነገሥታት ንጉሥ የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ የጻድቃን ንጉሥ ነው፡፡
የዩኒቨርስ ንጉሥ የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ ለእኛ አምላክ ነው፡፡ በማቴዎስ
ምዕራፍ 1 እስከ 7 ድረስ ያለውን ዘገባ ስንመለከት ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ
ኮንፊሺስ፣ ሶቅራጥስ፣ ፕሌቶ ወይም ቡድሃ ፍጡር የነበረ ሰው እንዳልሆነ በግልጽ
ማየት እንችላለን፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሁላችንም ሉዓላዊ አምላክና አዳኛችን
ነው፡፡ እርሱ በሰማይና በምድር የነገሥታት ንጉሥ ነው፡፡
ጌታችን እንዲህ ብሎዋል፡- ‹‹በመንፈስ ድሆች የሖኑ ብጹዐወን ናቸው፤
መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና፡፡›› እነዚህን ነገሮች መናገር የሚችል ማነው?
ማንም ያንን ማድረግ አይችልም፡፡ ንጉሣችን አዳኛችን የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ
ብቻ ነው፡፡ ዛሬ የኢየሱስን አምላክነት የሚክዱ ብዙ የቃለ እግዚአብሄር
ሊቃውንቶች አሉ፡፡ ነገር ግን ኢየሱስ፣ የኢየሱስ አባትና መንፈስ ቅዱስ
ሰማያትንና ምድርን የፈጠረ አምላክ መሆናቸው እውነት ነው፡፡ (ዘፍረት 1፡1) ጌታ
ለደቀ መዛሙርቱ ‹‹ልበ ንጹሆች ብጹዓን ናቸው እግዚአብሄርን ያዩታልና››
አላቸው፡፡
የሐጢያትን ስርየት ከተቀበላችሁት ከእናንተ መካከል የኢየሱስን አምላክነት
የሚክድ ሰው አለ? ኢየሱስ ክርስቶስ የሥላሴ አምላክ አካልና የነገሥታት ንጉሥ
መሆኑን ለአፍታ ልንክድ አንችልም፡፡ ጌታ ወደዚህ ምድር መጥቶ በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል ከሐጢያቶቻችንና ከሐጢያቶች ፍርድ አድኖናል፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


118 የተራራው ስብከት

ከእውነተኛው ወንጌል ጋር አብረን ኢየሱስ ክርስቶስን አዳኛችን አድርገን ብናምን


እግዚአብሄር አብ ለአንዴና ለመጨረሻ ከሐጢያቶቻችን ሁሉ እንድንድን
ይፈቅድልናል፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ሐይል እናምናለን፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ ባይሆን ኖሮ የሰው ዘር ከሐጢያት ነጻ መውጣት
አይችልም ነበር፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ለእኛ ፍጹም አምላክ ባይሆን ኖሮ ሥራው
ሁሉ ፍጹም አይሆንም ነበር፡፡ ነገሩ ይህ ቢሆን ኖሮ እርሱን አዳኛችን አድርገን
በማመን ከሐጢያቶቻችን መዳን አንችልም ነበር፡፡ እኛ ከሐጢያቶቻችን ሁሉ
ደህንነትን ያገኘነው የእግዚአብሄር ልጅ አዳኝ ሆኖ ወደዚህ ዓለም በመምጣት
ከዓለም ሐጢያቶች በሙሉ ስላዳነን ነው፡፡

የሚያስተራርቁ ሰዎች የሚቀበሉት ብጽዕና፡፡

ጌታ በማቴዎስ 5፡9 ላይ እንዲህ ብሎዋል፡- ‹‹የሚያሰረተራርቁ ብጹዓን


ናቸው፤ የእግዚአብሄር ልጆች ይባላሉና፡፡›› ጌታ ዳግመኛ የተወለድነውን
ክርስቲያኖች መንፈሳዊ ካህናት ብሎ ጠርቶናል፡ በመንፈሳዊ አነጋገር በዚህ ዓለም
ሕዝብ መካከል በመቆም በክርስቶስ በኩል ከእግዚአብሄር ጋር የምናስታርቃቸው
ካህናት ነን፡፡ በእግዚአብሄር ፊት ካህናት የሆኑ ሰዎች በእግዚአብሄርና በሰዎች
መካከል ዕርቅን ለማምጣት በርትተው ይሰራሉ፡፡ የውሃውንና የመንፈሱን
ወንጌልና የሐጢያቶችን ስርየት እውነት በዚህ ዓለም ላይ ለሚኖሩ ሰዎች
ብናሰራጭ በእነርሱና በእግዚአብሄር መካከል የዕርቅ ሥራን እንሰራለን፡፡ ጻድቃን
የእግዚአብሄር ፈቃድ የሆነውን የአምላክ ደህንነት ለሰዎች ያጋራሉ፡፡
ይህንን እውነት ያሰራጫሉ፡፡ ‹‹ሰዎች በእግዚአብሄር ፊት ሐጢያት
ሰርተዋል፡፡ ስለዚህ በሐጢያቶቻቸው ምክንያት ወደ ጥፋት እየነጎዱ ነው፡፡ ወደ
ሲዖል ይወርዳሉ፡፡ በመሆኑም በውሃውና በመንፈስ ወንጌል በማመን
የእግዚአብሄርን ፍቅርና ድህንነት ተቀበሉ፡፡ ያን ጊዜ ከሐጢያቶቻችሁ ሁሉ
ትድናላችሁ፡፡›› እኛ የደህንነትን ወንጌል ከልባችን እንወደዋለን፤
እናሰራጨውማለን፡፡ ሰዎችን ነጻ እናወጣለን፡፡ የእግዚአብሄርን ሕግና የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል በማሰራጨት በእነርሱና በእግዚአብሄር መካከል ዕርቅን
እናደርጋለን፡፡
የሚሽን ትምህርት ቤት ተማሪዎቻችን ወጥተው ሰዎችን እየደረሱ ነው፡፡
ሰዎችን መድረስ ከፈለግን በምንወጣበት ጊዜ መንፈሳዊውን የቃል ሰይፍ መሳል

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የተራራው ስብከት 119

አለብን፡፡ እኛ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ተረድተን አምነንበታል፡፡ እኛ


የምናምነውን ይህንን ወንጌል ለጠፉት ነፍሳቶች እናጸናላቸዋለን፡፡ ስለዚህ
በመጀመሪያ ስለ ውሃውና መንፈሱ ወንጌል የተመዘገቡባቸውን ምንባቦች ምልክት
ልናደርግባቸው ይገባናል፡፡ ከዚያ በኋላ ሰዎችን ለመድረስ መውጣት እንችላለን፡፡
በሐጢያት የታሰሩትን ነፍሳቶች ማግኘትና በትክክል ማስተማር የምንችለው ያን
ጊዜ ብቻ ነው፡፡ በእያንዳንዱ ነገር ውስጥ ነገርን በእምነት በማድረግና ከእምነት
ውጭ በማድረግ መካከል ልዩነት አለ፡፡ እነዚህ የመጽሐፍ ቅዱስ ቃሎች
ለጻድቃኖች መንፈሳዊ የጦር መሳርያዎች ናቸው፡፡ የእግዚአብሄር ቃል
ለእያንዳንዱ ሰው ብርቱ መሳርያ ነው፡፡
ጌታ የሚያስተራርቁ ብጹዓን እንደሆኑ ተናግሮዋል፡፡ ይህ ማለት ይህንን
የውሃና የመንፈስ ወንጌል የሚያሰራጩ ሰዎች ይባረካሉ ማለት ነው፡፡ እርሱ
እነዚህ ሰዎች የእግዚአብሄር ልጆች ተብለው እንደሚጠሩ ተናግሮዋል፡፡
በእርግጥም የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ማሰራጨት የሚችሉት የእግዚአብሄር
ልጆች ብቻ ናቸው፡፡ ወንጌልን የሚሰሙ ሰዎችም ከእግዚአብሄር ጋር ሰላምን
ይፈጥራሉ፡፡ ጻድቃን የውሃውንና መንፈሱን ወንጌል በመስበክ ታማኞች ናቸው፡፡
ስለዚህ በሥጋና በመንፈስ ከእግዚአብሄር ዘንድ የተትረፈረፉ ባርኮቶችን
ይቀበላሉ፡፡

ለጽድቅ የሚሰደዱ ሰዎች የሚቀበሉት ብጽዕና፡፡

በማቴዎስ 5፡10 ላይ እንዲህ ይላል፡- ‹‹ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ ብጹዓን


ናቸው፤ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና፡፡›› በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
የሚያምኑና ይህንን ሥራ የሚሰሩ ሰዎች መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናት፡፡ ስለ
ጽድቅ የሚሰደዱ ሰዎች ብጹዓን ናቸው፡፡
ውድ ክርስቲያኖች ስለ ጽድቅ ተሰዳችሁ ታውቃላችሁን? በሐጢያተኞች
አማካይነት ስለ ጽድቅ፣ ስለ ውሃውና መንፈሱ ወንጌል፣ ከእግዚአብሄር
ቤተክርስቲያንና ከእግዚአብሄር መንግሥት ጋር ስለ መተባበራችሁና
የእግዚአብሄርን ሥራ ስለ መስራታችሁ ተሰዳችሁ ታውቃላችሁን? በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል በማመናችሁ ምክንያት ሰዎች ችላ ብለዋችሁ ያውቃሉን? ስለ
እግዚአብሄር ጽድቅ መሰደድ ማለት ይህ ነው፡፡ ጻድቃን ስለ እግዚአብሄር ጽድቅ
ሲሉ በወለዱዋቸው ቤተሰቦቻቸውም ይሰደዳሉ፡፡ ይህ ለእነዚህ ሰዎች

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


120 የተራራው ስብከት

ከእግዚአብሄር የተላከ በረከት ነው፡፡


ጻድቃን ስለ እግዚአብሄር ቃል በመሰደዳቸው ማፈር አይገባቸውም፡፡ ይህ
እግዚአብሄር የላከው በረከት ነው፡፡ ጻድቃን ለእግዚአብሄር ጽድቅ ከኖሩ
በሐጢያተኞች ይሰደዳሉ፡፡ ጻድቃን በጓደኞቻቸው እንኳን ይሰደዳሉ፡፡
ከእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ጋር ለመቆራኘት ከሞከራችሁ በእርግጥም
ትሰደዳላችሁ፡፡ ጻድቃን መሰደዳቸው የእግዚአብሄር ፈቃድ ነው፡፡ (2ኛ
ጢሞቴዎስ 3፡12) ‹‹በግብር ይውጣ እምነት ላይ የተመሰረተ ሕይወት
ከሚኖራችሁ ይልቅ በእርግጥ በእያንዳንዱ አገልግሎት ላይ ትገኛላችሁን? ባተሌ
አይደላችሁምን? ረጋ በሉ፤ በዓመት አንድ ጊዜ በእሁድ አገልግሎት ላይ ባትገኙ
ችግሩ ምንድነው? በእርግጥ በእምነት መኖር አለባችሁን? በእርግጥ ያንን ማድረግ
ይኖርባችኋልን?›› በማለት ጻድቃንን በቃላት ያሰድዱዋቸዋል፡፡
ይህንን ያደርጋሉ ወይስ አያደርጉም? ያደርጋሉ፡፡ ‹‹በእርግጥ ይህንን
በማድረግ ጥብቅ የሆነውን ወዳጅነታችንን ታፈርሳለህን? በኢየሱስ ላይ ያለህ
እምነት የተሳሳተ ይመስላል፡፡›› ሰዎች የሚሉት ይህንን ነው፡፡ በዓለም ላይ
የሚኖሩ ሰዎች ሰላም ነው ሲሉ ሰላም ከእነርሱ ጋር መተባበር ነው ብለው
ያስባሉ፡፡ እውነተኛ ሰላም ግን ለእግዚአብሄር መንግሥት፣ ለእግዚአብሄር
ወንጌል፣ ለነፍሳቶች ደህንነት መሰደድ ማለት ነው፡፡ ለእግዚአብሄር የጽድቅ
ወንጌል መሰደድ ማለት ይህ ነው፡፡
ለራሳችሁ፣ ለኩራታችሁ፣ ለዝናችሁ፣ ኪሳራችሁን ለማስወገድ
የምታደርጉት ሰላም ለጽድቅ መሰደድ አይደለም፡፡ እነዚህ ለጽድቅ የሚደረጉ
ስደቶች አይደሉም፡፡ እነዚህ ስደቶች እናንተ በራሳችሁ ላይ ያመጣችኋቸው
ስደቶች ናቸው፡፡ ጌታችን የተናገረው ስለ ጽድቅ ምግባሮች፣ ስለ ነፍሳቶች
ደህንነትና ስለ እግዚአብሄር መንግሥት መሰደድን ነው፡፡
አንድ ሰው ሲነቅፋችሁና ሲያሳድዳችሁ ስለ እግዚአብሄር ጽድቅም ክፉውን
ሁሉ በውሸት ሲናገርባችሁ በአእምሮዋችሁ ‹‹ስላልተረዳኝ ቢያሰድደኝም ያንን
ሰው ከሐጢያቶቹ ለማዳን ይህንን ማድረግ አለብኝ›› ብላችሁ መወሰን
ትችላላችሁ፡፡ መንግሥተ ሰማያት እንደ እናንተ ላሉት ናት፡፡
ዛሬ እውነተኛውን ወንጌል የሰሙ ብዙዎች ስለ ጽድቅ መሰደድ
አይፈልጉም፡፡ ስለዚህ በክርስቶስ እውነተኛ እምነት እንዲኖራቸው ይፈራሉ፡፡
አንዳንድ ሰዎች የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ያውቃሉ፤ ነገር ግን ለሌሎች
አያጋሩትም፡፡ አንዳንዶችም ስደትን ለመሸሽ ሲሉ ከእግዚአብሄር ጋር ከመወገን
ይልቅ ከሐጢያተኞች ጋር ይወግናሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች ባርኮቶችን አያገኙም፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የተራራው ስብከት 121

የሐጢያትን ስርየት ቢያገኙም ለዚህ የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ሲሉ ስደትን


ካልቀመሱ በጌታ ፊት እስከሚቆሙበት ቀን ድረስ እምነታቸውን ከመጠበቅ
ይልቅ መጨረሻቸው እውነተኛውን ወንጌል መካድ ይሆናል፡፡ ሰው ሊደክም
ይችላል፤ ነገር ግን እውነተኛውን ወንጌል ከልቡ ክዶ ወንጌልን ለመቃወም
ከዓለም ሰዎች ጋር ከተጨባበጠ እርሱ ብሩክ አይደለም፡፡
ዓሳ አጥማጆች መልካሙን ዓሳ በዕቃዎቻቸው እንደሚሰበስቡና ክፉውን
እንደሚጥሉት ሁሉ እግዚአብሄርም ክፉዎችን ከጻድቃን መካከል ይለያል፡፡
(ማቴዎስ 13፡47-49) ይህ በማቴዎስ መጽሐፍ ላይ ስለ መንግሥተ ሰማይ
በተሰጡት ምሳሌዎች ውስጥ የሚገኝ ነው፡፡ ነገር ግን እንደ እውነቱ ከሆነ መንፈስ
ቅዱስ ያለው ማንኛውም ሰው ስለ ጽድቅ ከመሰደድ ማምለጥ አይችልም፡፡ ሰው
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ካመነና የሐጢያት ስርየትን ከተቀበለ በኋላ ለጽድቅ
ከመኖር በቀር የሚያደርገው ሌላ ነገር ሊኖር አይችልም፡፡ አንድ ሰው በልቡ
ውስጥ ባለው መንፈስ ቅዱስ በትክክል ከተመራ ፈጽሞ ከራሱ ፍላጎት ጋር
ሊማከር አይቻለውም፡፡ ጻድቅ ሰው ስለ ጽድቅ ይሰደዳል፡፡
ጻድቅ ሰው ችግር የሚገጥመው መሆኑ በራሱ መጥፎ ነውን? ያ ሊሆን
አይችልም፡፡ አንዳንድ ጊዜ ወንጌልን ስናሰራጭ ችግር ይገጥመናል፡፡ ነገር ግን
አስቸጋሪ ያልሆነ ነገር አለን? ሁላችሁም ለእግዚአብሄር ጽድቅ የምትሰደዱ ሰዎች
እንደምትሆኑ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ እኔ ራሴ አስቀድሜ እንደዚያ ዓይነት ሰው
መሆን እፈልጋለሁ፡፡ ጻድቅ ሰው እንደ መሆናችሁ ሰክራችሁ በመንዳት
ተይዛችሁ፣ ከመጋዘን ውስጥ ስትሰርቁ ተይዛችሁ ወይም በማጭበርበር ተይዛችሁ
በመታሰር ዓይነት ብዙ ብልሹ ባህሪዎቻቸው ምክንያት አላስፈላጊ በሆነ ሁኔታ
እንደማትሰደዱ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ እግዚአብሄር በዚህ አይደሰትም፡፡
ኢየሱስ በማቴዎስ 5፡11-12 ላይ እንዲህ ብሎዋል፡- ‹‹ሲነቅፉአችሁና
ሲያሳድዱአችሁ በእኔም ምክንያት ክፉውን ሁሉ በውሸት ሲናገሩባቸው ብጹዓን
ናችሁ፡፡ ዋጋችሁ በሰማያት ታላቅ ነውና ደስ ይበላችሁ፤ ሐሴትም አደረጉ፤
ከእናንተ በፊት የነበሩትን ነቢያትን እንዲሁ አሳድደዋቸዋልና፡፡›› እርሱ ስንነቀፍና
ስንሰደድ፣ በእርሱም ምክንያት ክፉው ሁሉ በውሸት ሲነገርብን እንደምንባረክ
ተናግሮዋል፡፡
በዓለም ላይ የሚኖሩ ሰዎች ብዙውን ጊዜ የእግዚአብሄርን ልጆችና
የእግዚአብሄርን ቤተክርስቲያኖች ያሳድዳሉ፡፡ ያ ምን ማለት ነው? ያ ማለት እኛ
ጻድቃኖች የተባረክን ነን ማለት ነው፡፡ የእግዚአብሄርን ጽድቅ በማመናችንና
በመከተላችን በዓለም ላይ በሚኖሩ ሰዎች ስንነቀፍ በእግዚአብሄር እንባረካለን፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


122 የተራራው ስብከት

ነገር ግን አንዳንዶች በቃሉ ላይ እምነት ስለሌላቸው ስለ እግዚአብሄር


የሚመጣባቸውን ስደት ለመሸሽ ይሞክራሉ፡፡
የእምነት ፋናዎቻችን የሆኑት የብሉይ ኪዳን ነቢያቶችና አገልጋዮች ከእኛ
ይልቅ ስለ እግዚአብሄር በብዙ ተሰደዋል፡፡

እኛ የዓለም ጨውና ብርሃን ነን፡፡

ኢየሱስ እንዲህ አለ፡- ‹‹እናንተ የምድር ጨው ናችሁ፤ ጨው አልጫ ቢሆን


ግን በምን ይጣፍጣል? ወደ ውጭ ተጥሎ በሰው ከመረገጥ በቀር ወደፊት
ለምንም አይጠቅምም፡፡›› እኛ ጻድቃኖች የምድር ጨው ነን፡፡ ጻድቃን የምድር
ጨው ናቸው ማለት በዚህ ምድር ላይ ተፈላጊ ሰዎች ናቸው ማለት ነው፡፡
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምኑ ሰዎች በዚህ ዓለም ላይ ተፈላጊ ሰዎች
ናቸው፡፡
ነገር ግን ጨው ጣዕሙን ቢያጣስ? ጨው ጣዕሙን አጣ ማለት ምን
ማለት ነው? ያ ማለት ጨው ሆኖ ሊያገለግል አይችልም ማለት ነው፡፡ ጻድቅ
ሰው ለውሃውና ለመንፈሱ ወንጌል ከመኖር ይልቅ እውነትን አሽቀንጥሮ ጥሎ
በዚህ ዓለም መንገድ የሚሄድ ከሆነ ሐይሉን ያጣል፡፡
በማቴዎስ 5፡14-15 ላይ እንዲህ ይላል፡- ‹‹እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ፡፡
በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሰወር አይቻላትም፡፡ መብራትንም አብርተው
ከዕንቅብ በታች አይደለም እንጂ በመቅረዙ ላይ ያኖሩታል በቤት ላሉት ሁሉም
ያበራል፡፡››
ጻድቃን የደህንነት ብርሃን ናቸው፡፡ ዓለም የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
ከጻድቃኖች ይሰማል፡፡ በሌላ አነጋገር ሐጢያተኞች የሐጢያታቸውን ደህንነት ከእኛ
ከጻድቃን ያገኛል፡፡
በማቴዎስ 5፡16 ላይ እንዲህ ይላል፡- ‹‹መልካሙን ሥራችሁን አይተው
በሰመያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት
ይብራ፡፡›› የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በማመንና በእምነትም ስምንቱን
ብጽዕናዎች (በረከቶች) በመቀበል እግዚአብሄርን እያከብርን እንኖራለን፡፡ እኛ በጌታ
በሚያምነው እምነት ይህንን የእምነት ሕይወት ሁልጊዜም በመኖር መቀጠል
ይገባናል፡፡ መለኮታዊ በረከቶችን የሰጠንን አምላክ እናመሰግነዋለን፡፡ ይህ እውነት
ሁሉ ጌታ የተናገረው የተራራው ስብከት ነው፡፡ 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ምዕራፍ
6

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት
ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
ጌታ ስለ ጸሎት
ያስተማረው ትምህርት (1)
‹‹ ማቴዎስ 6፡1-15 ››
‹‹ለሰዎች ትታዩ ዘንድ ምጽዋታችሁን በፊታቸው እንዳታደርጉ ተጠንቀቁ፤
ያለዚያ በሰማያት ባለው አባታችሁ ዘንድ ዋጋ የላችሁም፡፡ እንግዲህ ምጽዋት
ስታደርግ ግብዞች በሰው ዘንድ ሊከበሩ በምኩራብ በመንገድም እንደሚያደርጉ
በፊትህ መለከት አታስነፋ፤ እውነት እላችኋለሁ ዋጋቸውን ተቀብለዋል፡፡ አንተ
ግን ምጽዋት ስታደርግ ምጽዋትህ በስውር እንዲሆን ቀኝህ የምትሠራውን ግራህ
አትወቅ፤ በስውር የሚያይ አባትህም በግልጥ ይከፍልሃል፡፡ ስትጸልዩም እንደ
ግብዞች አትሁኑ፤ ለሰው ይታዩ ዘንድ በምኩራብና በመንገድ ማዕዘን ቆመው
መጸለይ ይወዳሉና፤ እውነት እላችኋለሁ ዋጋቸውን ተቀብለዋል፡፡ አንተ ግን
ስትጸልይ ወደ እልፍኝህ ግባ፤ መዝጊያህንም ዘግተህ በስውር ላለው አባትህ
ጸልይ፤ በስውር የሚያይ አባትህም በግልጥ ይከፍልሃል፡፡ አሕዛብም
በመናገራቸው ብዛት እንዲሰሙ ይመስላቸዋልና ስትጸልዩ እንደ እነርሱ በከንቱ
አትድገሙ፡፡ ስለዚህ አትምሰሉአቸው፤ ሳትለምኑት አባታችሁ የሚያስፈልጋችሁን
ያውቃልና፡፡ እንግዲህ እናንተስ እንዲህ ጸልዩ፡፡ በሰማያት የምትኖር አባታችን
ሆይ፤ ስምህ ይቀደስ፤ መንግሥትህ ትምጣ፤ ፈቃድህ በሰማያት እንደሆነች
እንዲሁ በምድር ትሁን፤ የዕለት እንጀራችንን ዛሬ ስጠን፤ እኛም ደግሞ የበደሉንን
ይቅር እንደምንል በደላችንን ይቅር በለን፡፡ ከክፉም አድነን እንጂ ወደ ፈተና
አታግባን፤ መንግሥት ያንተ ናትና ሐይልም ክብርም ለዘለዓለሙ አሜን፡፡ ለሰዎች
ሐጢአታቸውን ይቅር ብትሉ የሰማዩ አባታችሁ እናንተን ደግሞ ይቅር
ይላችኋልና፤ ለሰዎች ግን ሐጢአታቸውን ይቅር ባትሉ አባታችሁም
ሐጢአታችሁን ይቅር አይላችሁም፡፡››

በቤተክርስቲያናችን ጂን ዉ ኪም የሚባል ልጅ አለ፡፡ እንግዳ በሆነ በሽታ


ወደ ሞት ተቃርቦ ነበር፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲታከም ሐኪሞቹ እንኳን ምክንያቱን
አላወቁትም፡፡ ስለዚህ እንዴት እንደሚያድኑት ግራ ተጋቡ፡፡ እኛ ማድረግ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


126 ጌታ ስለ ጸሎት ያስተማረው ትምህርት (1)

የቻልነው ነገር ቢኖር እግዚአብሄር ይፈውሰው ዘንድ ለልጁ መጸለይ ብቻ ነበር፡፡


በዚህ ጊዜ ጌታ ልጁ የተሻለ ሐኪም እንዲያገኝ አደረገ፡፡ አሁን በጣም በተሻለ
ሁኔታ ላይ ይገኛል፡፡ በመንገዳችን ላይ አስቸጋሪ ወቅቶች ሲመጡ ማድረግ
የሚገባንን ሁሉ ማድረግ አለብን፡፡ ነገር ግን በመጀመሪያ መጸለይን ማስታወስ
ይገባናል፡፡
ጌታ በማቴዎስ 6፡1 ላይ እንዲህ ብሎዋል፡- ‹‹ለሰዎች ትታዩ ዘንድ
ምጽዋታችሁን በፊታቸው እንዳታደርጉ ተጠንቀቁ፤ ያለዚያ በሰማያት ባለው
አባታችሁ ዘንድ ዋጋ የላችሁም፡፡›› ይህ ማለት በሐይማኖት ሕይወታችን
ጽድቃችንን ለሌሎች ሰዎች ማሳየት አይገባንም ማለት ነው፡፡ እነዚህ ቃሎች
ዳግመኛ ለተወለዱትና ገና ዳግመኛ ላልተወለዱት የተነገሩ ቃሎች ናቸው፡፡ ነገር
ግን እኛ ጻድቃኖች ‹‹ለሰዎች ትታዩ ዘንድ ምጽዋታችሁን በፊታቸው እንዳታደርጉ
ተጠንቀቁ፤›› የሚለውን ይህንን አባባል በአእምሮዋችን መያዝ ይገባናል፡፡ ለሌሎች
ለማሳየት ስንል የጽድቅ ምግባሮችን የምናደርግ ከሆንን በሰማይ ያለው አባታችን
በኋላ ዋጋ እንደማይሰጠን ጌታ ነግሮናል፡፡
በዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ላይ አንድ የተለመደ ርዕሰ ጉዳይ
ማግኘት እንችላለን፡፡ ያም ምንም ነገር ብናደርግ ጽድቃችንን ለማሳየት ስንል
በሌሎች ፊት ማድረግ የማይገባን መሆኑ ነው፡፡ ጌታ በአርሱ ማመንና ቃሉንም
በልባችን ማመን እንደሚገባን፤ በስውር በሚያየን አምላክ ፊትም ከሙሉ ልባችን
የጽድቅ ሥራ እንድንሰራ ነግሮናል፡፡ ይህ ማለት አንድን መልካም ነገር ለታይታ
ሳይሆን ከልባችን ማድረግን አለብን ማለት ነው፡፡ እግዚአብሄር አብ ዋጋ
የሚሰጠን ያን ጊዜ ብቻ ነው፡፡ እግዚአብሄር በሚከፍልበት ጊዜም ዋጋችንን
እንቀበላለን፡፡ በሌላ አነጋገር የእምነትን ሕይወት የምንኖረው ለታይታ ብቻ ከሆነ
እግዚአብሄር ማረጋገጫ አይሰጠንም፡፡ ሰው ምንም ያህል መልካም ነገር
ለማድረግ በርትቶ ቢሞክርም ለታይታ የተደረገ ከሆነ ተቀባይነት አያገኝም፡፡
ታዲያ ሌሎች ሰዎች ይህን ቢያውቁ የምናደርገው ነገር ሁሉ ግብዝነት
ነውን? እንደዚያ አይደለም፡፡ ሌሎች ሰዎች ቢያውቁት ወይም ባያውቁት አንድ
ሰው በእምነቱ ምክንያት ጽድቅን ቢያደርግ ያደረገው በእምኑ ለታይታ
አይደለም፡፡ በእምነት በሚያምን ልብ ያልተደረገ ነገር ሁሉ ግብዝነት ነው፡፡
ሌሎች ሰዎች መልካም ምግባሮቻችንን ማየታቸው ወይም አለማየታቸው ለውጥ
አያመጣም፡፡ በአጭሩ የእግዚአብሄርን ቃል በፊቱ በእምነት መፈጸም ሁልጊዜም
በእግዚአብሄር የተደገፈ ነው፡፡ ነገር ግን ከእግዚአብሄር ይልቅ የሌሎችን ይሁንታ
ለማግኘት የምናደርገው ማንኛውም ነገር ታይታ ነው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ጌታ ስለ ጸሎት ያስተማረው ትምህርት (1) 127

እግዚአብሄር ግብዝ ለሆነ እምነት ዋጋ አይሰጥም፡፡ ስለዚህ በሐይማኖት


ሕይወታችን ውስጥ ይህንን እምነት ማስወገድ ይኖርብናል፡፡ የልግስና ምግባር
ስናደርግ ወይም ስንጸልይ ይህንን ትምህርት ማሰብ ይኖርብናል፡፡

እርሱ እንድንጸልይ የሚፈልገው እንዲህ ነው፡፡

በማቴዎስ 6፡5-6 ላይ እንዲህ ይላል፡- ‹‹ስትጸልዩም እንደ ግብዞች


አትሁኑ፤ ለሰው ይታዩ ዘንድ በምኩራብና በመንገድ ማዕዘን ቆመው መጸለይ
ይወዳሉና፤ እውነት እላችኋለሁ ዋጋቸውን ተቀብለዋል፡፡ አንተ ግን ስትጸልይ ወደ
እልፍኝህ ግባ፤ መዝጊያህንም ዘግተህ በስውር ላለው አባትህ ጸልይ፤ በስውር
የሚያይ አባትህም በግልጥ ይከፍልሃል፡፡››
ስንጸልይ በእርግጥ የምንፈልገው ምንድነው? ልክ እንደ ሕጻን
በእግዚአብሄር ፊት በሚቀርብ ልብ ልንጸልይ ይገባናል፡፡ ‹‹ጌታ ሆይ ይህ
የለኝምና ይህን ስጠኝ፡፡›› የሕጻን ልጅ ልብ ይዞ መጸለይ ልክ እንደዚህ መጸለይ
ነው፡፡ ቀለል ያለ እምነት ካለን ይህ የሚቻል ነው፡፡ ስለዚህ ስንጸልይ ወይም
የጽድቅ ምግባሮችን ስናደርግ በልባችን ውስጥ እምነት ስላለን እነዚህን ነገሮች
ሁሉ ማድረግ አለብን፡፡
ጌታ እንዲህም ደግሞ ብሎዋል፡- ‹‹አንተ ግን ስትጸልይ ወደ እልፍኝህ ግባ፤
መዝጊያህንም ዘግተህ በስውር ላለው አባትህ ጸልይ፤ በስውር የሚያይ አባትህም
በግልጥ ይከፍልሃል፡፡›› (ማቴዎስ 6፡6) ወደ እግዚአብሄር ስንጸለይ በስውር
ወዳለው አምላክ ጸሎቶቻችንን እንድናቀርብ ወደ ልባችን ስውር ስፍራ መግባት
አለብን፡፡ እግዚአብሄርን ብቻ ስንመለከትና በፊቱም ሆነን እርሱን ስንጠይቅ
እግዚአብሄር አብ ጸሎቶቻችንን ሰምቶ ዋጋችንን ይሰጠናል፡፡ በሌላ አነጋገር ወደ
እግዚአብሄር ስንጸልይ የምንጸልየው በስውር ስፍራ ወዳለው እግዚአብሄር ስለሆነ
ለሌሎች መታየት አያስፈልገንም፡፡ ይህ ማለት ግን መጸለይ የምንችለው በስውር
ብቻ ነው ማለት አይደለም፡፡ በሰዎች ለመታየት ስንል አንጸልይም፡፡ እግዚአብሄር
በልባችን ውስጥ እንዲኖር በትክክል ስለምንፈልግ እግዚአብሄርን በሚለምን ልብ
እንጸልያለን፡፡
ከላይ ከተጠቀሰው የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ምን ትማራላችሁ? ጌታ
ታይታን እንደሚጠላ ተምረናል፡፡ እግዚአብሄር ታይታን የማይወድደው
ለምንድነው?

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


128 ጌታ ስለ ጸሎት ያስተማረው ትምህርት (1)

ሰዎች ተሰብስበው ሦስት ጊዜ ‹‹ጌታ›› እያሉ በከፍተኛ ድምጽ በመጮህ


ከምስባኩ ጋር ይጋጫሉ፡፡ ብዙዎቹም፡- ‹‹ጌታ ሆይ ይቅር በበለኝ፤ በድያለሁ››
እያሉ በሰቆቃ ንስሐ ይገባሉ፡፡ ሰዎች እንደዚህ ያለቅሳሉ፡፡ ነገር ግን
ከቤተክርስቲያን እንደወጡ ወዲያውኑ ይስቃሉ፡፡ አንድ ጊዜ ያለቅሳሉ፤ በቀጣዩ
ጊዜ ደግሞ እያጨበጨቡ ይስቃሉ፤ ይቀላለዳሉ፡፡ በዚህ አምልኮ ውስጥ ያለ
እያንዳንዱ ሰው አእምሮው ከቁጥጥር ውጪ በመሆኑ ጤነኛ የሆነ ሰው እንኳን
‹‹አብጃለሁ እንዴ? አንድ ጊዜ የሚያለቅሱ በቀጣዩ ጊዜ ደግሞ የሚስቁ ሰዎችን
ስመለከት የማብድ መስሎ ይሰማኛል›› የሚል ስሜት ይኖረዋል፡፡ ትክክለኛ
አእምሮና ስሜት ያላቸው ሰዎች እንደዚህ ወዳሉ ቤተክርስቲያኖች የማይሄዱት
ለዚህ ነው፡፡ እግዚአብሄር እንደዚህ ያሉ ሰዎችንም አብዝቶ ይጠላል፡፡ ፊቱንም
ከእነርሱ ይመልሳል፡፡ ግብዞችም ብሎ ይጠራቸዋል፡፡
ታዲያ ሲጸልዩ የሚያለቅሱና የሚጮሁ ወደ ቤታቸው ሲመለሱ
እንደተመለሱ ወዲያውኑ ስለ ጌታ ዴንታ እንዳኖራቸው የሚፈልጉ ሰዎች እነማን
ናቸው? እነዚህ ሰዎች ብዙዎቹ በአጋንንት የተያዙ ናቸው፡፡ በጉባኤዎቻቸውም
መሪዎቻቸውም እንኳን በአጋንንት የተያዙ ናቸው፡፡ ሰዎች በማይገባቸው ልሳንም
ይናገራሉ፡፡ አንዳንድ ጊዜም ከፍተኛ ድምጽ የሚያወጣ የድምጽ ማጉያ
በመጠቀም ‹‹እሳት ተቀበሉ1 እሳት - እሳት - እሳት!›› እያሉ ተከታዮቻቸውን
ከፍተኛ ስሜት ውስጥ ይከቱዋቸዋል፡፡ አንድ ጊዜ በዕንባና በልቅሶ እንዲጸልዩ
ሌላ ጊዜ ደግሞ ቅጥ ባጣ ዕብደት ጌታን እንዲያመሰግኑ በመፍቀድ ሰዎችን ግራ
ያጋባሉ፡፡
እንደዚህ ዓይነት ባህሪዎች ከጌታ ፈቃድ ጋር ምንም ግንኙነት የሌላቸው
እይታዎች ናቸው፡፡ የእግዚአብሄርን ቃል ስናነብ እግዚአብሄር ታይታን
እንደማይወድ ማየት እንችላለን፡፡ እግዚአብሄር የሚደሰተው ከሙሉ ልባችን
ለእግዚአብሄር ልባችንን በመስጠት በእምነት ስንጸልይ ብቻ ነው፡፡ እግዚአብሄር
በምን ዓይነት እምነት እንደምንጸልይ ቀድሞውኑም ያውቃል፡፡ በፊቱም እውነተኛ
ጸሎቶቻችንን ለመስማት ይሻል፡፡
በጌታችን ፊት የጸሎት ዝንባሌያችንን መለወጥ አለብን፡፡ ‹‹ጌታ ሆይ ይህ
የለኝም፤ እባክህ ስጠኝ›› ብለን ስንጠይቅ ማድረግ የሚኖርብን ነገር እውነተኞችና
የዋሆች መሆን ነው፡፡ በምንጸልይበት ጊዜ ብዙ ያሸበረቁ ሐረጎችን የምንጠቀመው
እምነታችን ያን ያህል ጠንካራ ስላልሆነ ነው፡፡ ስለ እግዚአብሄር ቃል
መስማታችንን ብንቀጥል በእግዚአብሄር የሚታመነው እምነታችን ያድጋል፡፡
የእግዚአብሄርን ቃል አጥብቀን ይዘን ስንጸልይ በእግዚአብሄር በማመን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ጌታ ስለ ጸሎት ያስተማረው ትምህርት (1) 129

እናድጋለን፡፡ በእምነት ላቀርብናቸው ጸሎቶቻችንም ምላሾችን ስናገኝ ይበልጥ


እግዚብሄርን እናመሰግናለን፡፡ ስለ እግዚአብሄር ብዙ በተማርን ቁጥር ወደ በኋላ
የእምነት ሰው ወደ መሆን እናድጋለን፡፡ ስለዚህ ይበልጥ ወደ እግዚአብሄር
እንጸልያለን፡፡ በምንጸልይበት ጊዜ ሁሉ ወደ እግዚአብሄር ብቻ የሚጸልይ ሰው
እንሆናለን፡፡ አንዳንድ ጊዜ በተወሰኑ ጉዳዮች ላይ በመስማማት ወደ እግዚአብሄር
እንጸልያለን፡፡ ጮክ ብለን የምንጸልይባቸው ወቅቶች እንዳሉ እውነት ነው፡፡ ነገር
ግን ይህ በማናቸውም ሁኔታ ሌሎች ሰዎች እንዲሰሙን ለማድረግ ፈልገን ሳይሆን
እግዚአብሄር ጸሎቶቻችንን እንዲሰማ ስለምንፈልግ ነው፡፡ እውነተኛ ጸሎቶች ልክ
እንደ እነዚህ ውስብስብ ካልሆነ እምነት የሚፈልቁ ናቸው፡፡ ‹‹አቤቱ እከሌ በዚህ
ዓይነት ሁኔታ ውስጥ ስላለ ዕርዳው፡፡ እከሌን ፈውሰው፤ ለእከሌ ጤናን ስጠው፤
እከሌ በዚህ ዓይነት ሁኔታ ውስጥ ስላለ ባርከው፡፡››
ዳግመኛ ከመወለዴ በፊት ንዲህ በሚሉ ብዙ ያሸበረቁ ሐረጎች መጸለይ
አዘወትር ነበር፡፡ ‹‹ቅዱስ የሆንህ መሐሪና በበረከት የተሞላህ አባታችን ሆይ
ስለሰጠኸን ፍቅርና ምህረት ተመስገን…›› በምንጸልይበት ጊዜ ሁሉ ውብ
ቃላቶችን ማሰለፍ አዘወትር ነበር፡፡ እነዚህ ጸሎቶች በእርግጥ በስውር ስፍራ
ላለው ጌታ የሚቀርቡ ጸሎቶች ናቸውን? በእርግጥ ሁልጊዜ እንደዚህ የምንጸልይ
ከሆነ ጌታ ያዳምጣልን? በእርግጥ እንደዚያ ብዙ የምንጸልይባቸው ነገሮች አሉን?
አይመስለኝም፡፡ ጌታ ‹‹አህዛቦች ወይም ፈሪሳውያን እንደሚደግሙት አትድገሙ፤
እኔ ልሰማችሁ የምችለው ብዙ ቃላቶችን ስለተናገራችሁ ይመስላችኋልን? ያ
እውነት አይደለም›› ብሎዋል፡፡ እርሱ እንዲህም ብሎዋል፡- ‹‹ስለዚህ
አትምሰሉአቸው፤ ሳትለምኑት አባታችሁ የሚያስፈልጋችሁን ያውቃልና፡፡››
(ማቴዎስ 6፡8) ጌታ እንዴት መጸለይ እንደሚገባን ምሳሌ ሲሰጠን ያስተማረን
ጸሎት ይህ ነው፡፡

በጌታ ጸሎት ውስጥ በመጀመሪያ የሐጢያቶችን ይቅርታ እናገኝ ዘንድ


እንድንጸልይ ተነግሮናል፡፡

ጌታ በማቴዎስ 6፡9 ላይ ለናሙና ባቀረበው ጸሎቱ እንዴት እንደምንጸልይ


አስተምሮናል፡፡ የጌታ ጸሎት ማለት ይህ ነው፡፡ እርሱ እንዲህ ብሎዋል፡-
‹‹እንግዲህ እናንተስ እንዲህ ጸልዩ፡፡›› የመጀመሪያው ‹‹በሰማያት የምትኖር
አባታችን ሆይ ስምህ ይቀደስ›› የሚለው ነው፡፡ ይህ ማለት የጌታ ስም እንዲቀደስ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


130 ጌታ ስለ ጸሎት ያስተማረው ትምህርት (1)

መጸለይ አለብን ማለት ነው፡፡ እዚህ ላይ ገና የሐጢያቶችን ስርየት ያልተቀበሉ


ሰዎች በመጀመሪያ የሐጢያቶቻቸውን ስርየት እንዲቀበሉ መጸለይ አለባቸው፡፡
ምክንያቱም የጌታን ስም የሚያከብረው ዋነኛ ጸሎት ይህ ነውና፡፡ ስለዚህ አንድ
ሐጢያተኛ በመጀመሪያ እንዲህ ብሎ መጸለይ አለበት፡- ‹‹አቤቱ እባከህ
ሐጢያቶቼን አንጻልኝ፤ የእግዚአብሄርም ልጅ አድርገኝ፡፡›› በመጀመሪያ እንደዚህ
መጸለይ ይገባቸዋል፡፡ ደግሞም ‹‹የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በመስማት
ዳግመኛ እንድወለድ እርዳኝ፡፡ በቃሎችህ ሁሉ እንዳምን እርዳኝ፡፡ እያንዳንዱን
የእግዚአብሄር ቃል እንዳስተውልም እርዳኝ›› ብለው ሊጸልዩ የሚገባቸው ይህንን
ነው፡፡
ሆኖም ‹‹በሰማይ የምትኖር አባታችን ሆይ ስምህ ይቀደስ›› ከሚለው የጌታ
ጸሎት የመጀመሪያው መስመር ጋር የሚጣጣም ትክክለኛ ሕይወት መኖር
የምንችለው የሐጢያቶችን ስርየት የተቀበልን እኛ ጻድቃኖች ብቻ ነን፡፡ በእርግጥ
የእግዚአብሄርን ስም ከማጠልሸት ለመራቅና የተቀደሰ ሕይወት ለመኖር ከፈለግን
ግዚአብሄር እንዲረዳን እንዲህ ብለን መጠየቅ አለብን፡፡ ‹‹የእንቅፋት ድንጋይና
የስምህ ስድብ እንድሆን እፍቀድ፤ በዕድሜዬ ሁሉ በእምነት የተቀደሰ ሕይወት
እንድኖር እርዳኝ፡፡ ለእግዚአብሄር ጽድቅ የሚሆን የተቀደሰ ሕይወት እንድኖር
እርዳኝ፡፡›› የአምላክን ስም ለማክበር ረድኤትን ስንጠይቅ ‹‹በእያንዳንዲቷ ቅጽበት
እንዲይዘን›› ወደ እግዚአብሄር መጸለይ አለብን፡፡
ስሙ ይቀደስ ዘንድ እርሱ ለእኛ ለጻድቃኖች የተቀደሰ ሕይወት
የምንኖርበትን የመጀመሪያውን የጸሎት ርዕስ ሰጥቶናል፡፡ ሐጢያተኞች
እግዚአብሄርን አባታቸው አድርገው መጥራት ስለማይችሉ በመጀመሪያ
የሐጢያቶቻቸውን ስርየት ለማግኘት መጸለይ አለባቸው፡፡ ‹‹እባክህ ሐጢያቶቼን
አስወግድ፤ የሰጠኸኝን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ላስተውል፡፡ የስርየትህን
እውነት በማወቅና በማመን የሐጢያት ስርየትን ልቀበል፡፡›› በጌታ የመጀመሪያ
የጸሎት መስመር ላይ የተጠቀሰውን የእግዚአብሄር ስም ለማክበር እያንዳንዱ
ሐጢያተኛ አስቀድሞ የሐጢያት ስርየትን ያገኝ ዘንድ እግዚአብሄር እንዲረዳው
መጸለይ አለበት፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ጌታ ስለ ጸሎት ያስተማረው ትምህርት (1) 131

በምድር ላይ ላለው የእግዚአብሄር መንግሥት የሚኖር የጸሎት


ሕይወት ልንኖር ይገባናል፡፡

የጸሎቱ ሁለተኛው ክፍል ምንድነው? ‹‹መንግሥትህ ትምጣ፤ ፈቃድህ


በሰማ እንደሆነች እንዲሁ በምድር ትሁን›› የሚለው ነው፡፡ የእግዚአብሄር
መንግሥት በምድር ላይ እንድትመሰረት መጸለይ አለብን፡፡ እግዚአብሄር
አባታቸን ጌታችንን ልኮ በጌታ ጥምቀትና በመስቀሉ ደም ሐጢያቶቻችንን በሙሉ
ለአንዴና ለመጨረሻ ደምስሶታል፡፡ ስለዚህ በልባችን ውስጥ መንፈስ ቅዱስ አለ፡፡
በመንፈሳዊ መልኩም የእግዚአብሄር መንግስት በልባችን ውስጥ ነው፡፡
ነገር ግን አሁንም ድረስ በልባቸው ውስጥ የሐጢያቶቻቸውን ስርየት
ያልተቀበሉና ከሐጢያት ጋር የሚታገሉ ብዙ ሰዎች አሉ፡፤ የእግዚአብሄር
መንግሥት ገና በልባቸው ውስጥ ስላልሆነች በመጀመሪያ የሐጢያቶቻቸውን
ይቅርታ እንዲያገኙ መጸለይ አለባቸው፡፡ ጌታችን ከ2,000 ዓመታት በፊት
በአጥማቂው ዮሐንስ ሲጠመቅና ሲሰቀል የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ
ደምስሶዋል፡፡ ሆኖም ይህንን ባለማወቃቸውና ባለማመናቸው አሁንም ድረስ
ሐጢያቶች ያለባቸው ብዙ ሰዎች አሉ፡፡ ስለዚህ እነርሱም ደግሞ በሚገባ
የሐጢያቶቻቸውን ስርየት ያገኙ ዘንድ ልንጸልይ ይገባናል፡፡
የእያንዳንዱ ሰው ብቸኛ ባለቤት እግዚአብሄር ነው፡፡ ነገር ግን እውነታው
በዚህ ዓለም ላይ የሚኖሩ ብዙ ሰዎች እግዚአብሄርን ከማገልገል ይልቅ
ለዲያብሎስ የተሰጡና የእርሱ አገልጋዮች መሆናቸው ነው፡፡ ጌታ ይህንን ውርደት
እንደሚጠላ የታወቀ ነው፡፡ እርሱ የፈጠራቸው ፍጥረቶቹ ሁሉ በእርሱ ቃሎች
አምነው ዳግመኛ በመወለድ የእርሱ ሕዝብ እንዲሆኑ በጉጉት ይጠብቃል፡፡
ስለዚህ የዓለም ፍጻሜና የሺህው ዓመት መንግሥቱ ከመምጣቱ በፊት
የእግዚአብሄር መንግሥት ወደ እያንዳንዱ ሰው ልብ እንድትመጣ መጸለይ
ይገባናል፡፡ እግዚአብሄር እያንዳንዱ ሰው የሐጢያት ስርየትን እንዲቀበልና መላው
ዩኒቨርስም እግዚአብሄር የሚነግስበት መንግሥት እንዲሆን ይህ ሁሉም
እንዲደረግ እንድንጸልይ ይሻል፡፡ ስለዚህ እግዚአብሄር ዳግመኛ የተወለድነውን
ሰዎች ለመንግሥቱ መስፋፋት እንድንጸልይ አዞናል፡፡ በሌላ አነጋገር እኛ
ጻድቃኖች ለእግዚአብሄር መንግሥት መስፋት መጸለይ ይገባናል፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


132 ጌታ ስለ ጸሎት ያስተማረው ትምህርት (1)

የሕይወትን መብል ለማግኘት የእምነትን ሕይወት መኖር አለብን፡፡

በጌታ ጸሎት ውስጥ ሦስተኛ የሆነው የጸሎት ርዕስ ከማቴዎስ 6፡11


እናንብብ፡- ‹‹የዕለት እንጀራችንን ዛሬ ስጠን፡፡›› ለምንበላው የዕለት እንጀራችን
መጸለይ ይገባናል፡፡ ይህ ማለት ግን ጌታ የዘላለምን ሕይወት እንጀራ እንዲሰጠን
መጠየቅ ይገባናል ማለትም ነው፡፡ ለሥጋችንና ለመንፈሳችን የሚሆን መብል
መብላት አለብን፡ ስለዚህ ‹‹ሥጋችንና ለመንፈሳችን የሚሆነውን መብል እንበላ
ዘንድ ስጠን›› ብለን መጸለይ ይገባናል፡፡ የምንጠይቀው ለዓመት ወይም ለወር
የሚበቃ ሳይሆን በየቀኑ ለሥጋችንና ለመንፈሳችን የሚያስፈልገውን ነው፡፡
ውድ ክርስቲያኖች በየዕለቱ ለመንፈሳዊ እንጀራችን መጸለይ ያስፈልገናል፡፡
ለሥጋና ለመንፈስ የሚያስፈልገውን መብላችንን ለማግኘት ወደ እግዚአብሄር
መጸለይ ስህተት አይደለም፡፡ እኛ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የምናምን ሰዎች
ስለሆንንና እግዚአብሄር አብን የምንፈልገውን ሁሉ ለመጠየቅ መብት ስላገኘን
በሦስተኛው የጸሎት ርዕስ መሰረትም መጸለይ ይገባናል፡፡ በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል የሚያምኑ ሰዎች በትክክል ለእግዚአብሄር ጽድቅ የሚሰሩ ሰዎች ናቸው፡፡
ስለዚህ እግዚአብሄር ለውሃውና ለመንፈሱ ወንጌል የሚያስፈልገውን ቁሳቁስ
በማበርከት እንዲያግዝና ሥራው ያድግ ዘንድ እንዲባርከው መጸለይ ይገባናል፡፡
ጻድቃን ለእግዚአብሄር ጽድቅ መኖራቸውና የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
በትክክል ለማሰራጨት በሕይወት መኖራቸው ተገቢ ነው፡፡ የጌታን ጸሎት
የምንጸልየው በዕድሜያችን አንድ ጊዜ ብቻ አይደለም፡፡ ነገር ግን እነዚህን የጸሎት
ርዕሶች በየቀኑ ልንጸልያቸው ይገባል፡፡
ውድ ክርስቲያኖች ለመንፈሳዊ እንጀራችን መጸለይ ያስፈልገናል፡፡
እግዚአብሄር የዕለት ምግባችንን እንዲሰጠን ከጸለይን እግዚአብሄር መልሱን
ይሰጠናል፡፡ ከልባችን ስንጸልይ በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ የሥጋና
የመንፈስ ምግብ አበላችንን እናገኛለን፡፡ እርሱ የእግዚአብሄር አገልጋዮች የእርሱ
ሕዝቦችና ክርስቲያኖች ሁሉ በእርሱ ቤተክርስቲያን ውስጥ ተሰብስበው
የወንጌልን ሥራ በመስራት ወይም ጌታን በማመስገንና በማገልገል እርስ በርሳቸው
ተስማምተው እንዲኖሩ ይህንን መብል አትረፍርፎ ይሰጠናል፡፡ የአገልጋዮቹን
ስብከቶች የቅዱሳንን ምስክርነቶች ስንሰማና መጽሐፍ ቅዱስን ስናሰላስል እንኳ
በየቀኑ መንፈሳዊ መብልን ይሰጠናል፡፡
እኛ ጻድቃኖች የእግዚአብሄርን ቃል ከማንበብ ይልቅ ብዙውን ጊዜ በየቀኑ
ተጨማሪ ምግብ ማግኘት እንችላለን፡፡ በልባችን ውስጥ ያለው መንፈስ ቅዱስ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ጌታ ስለ ጸሎት ያስተማረው ትምህርት (1) 133

ሁልጊዜም እግዚአብሄር አብን በሚያስደስተው መንፈሳዊ ሥራችን ይደሰታል፡፡


በልባችን ውስጥ ያለውን መንፈስ ቅዱስ የሚያስደስተው የዕለት እንጀራችን
ነው፡፡ በየቀኑ ‹‹ምግባችንን ስጠን›› ብለን እየጸለይን ምንም ነገር የማናደርግ
ከሆንን ይህ እውነተኛ ጸሎት አይደለም፡፡ ወደ እግዚአብሄር ከጸለያችሁ
እግዚአብሄር በእኛ አማካይነት ይሰራ ዘንድ እንዴት ጸሎቱን እንደሚሰማ
መጠበቅና የተቻላችሁን ማድረግ ይጠበቅባችኋል፡፡ ለውሃውና ለመንፈሱ ወንጌል
ሳንሰራ ዝም ብለን ተቀምጠን እግዚአብሄር መንፈሳዊ ምግብን እንዲሰጠን
የምንጠብቅ ከሆንን በእግዚአብሄር ላይ እያላገጥን ነው፡፡
ብዙውን ጊዜ ለአምልኮ አገልግሎቶች በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ወስጥ
እንሰበሰባለን፡፡ እኛ የምንበላው መብል በትክክል ይህ ነው፡፡ በቤተክርስቲያን
ውስጥ ቃሉን መስማት ብቻ አይደለም፡፡ የጌታን ሥራ እንደ ፈቃዱ መስራት
መንፈሳዊ መብላችን ነው፡፡ ጻድቅ ሰው የሐጢያትን ስርየት ከተቀበለ በኋላ
የእግዚአብሄርን ሥራ የማይሰራ ከሆነ እምነቱ ፈጥኖ ወይም ዘግይቶ ይሞታል፡፡
የእርሱም መጨረሻ ከእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን መሸሽ ይሆናል፡፡ አንዳንድ
ሰዎች እንዲያውም በእግዚአብሄር ፍጹም የደህንነት እውነት የሚያምነውን
እምነታቸውን ያጣሉ፡፡ ስለዚህ የዕለት ምግባችንን ለማግኘት የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል የማሰራጨቱን የጽድቅ ሥራ መስራት አለብን፡፡

በእምነት የጸደቁ ሰዎች እርስ በርሳቸው ይቅር


መባባል ይኖርባቸዋል፡፡

በማቴዎስ 6፡12 እንዲህ ተጽፎዋል፡- ‹‹እኛም የበደሉንን ይቕር እንደምንል


በደላችንን ይቅር በለን፡፡›› ይህ የጌታ ጸሎት አራተኛው ርዕስ ነው፡፡ ይህ
አራተኛው የጸሎት ርዕስ እኛ በየቀኑ ንስሐ መግባትና በየቀኑ ይቅርታን መቀበል
እንዳለብን የሚናገር ነው ብለን በተሳሳተ መንገድ ልንረዳው እንችላለን፡፡ ነገር ግን
ይህ አራተኛው ርዕሰ ጉዳይ በሁኔታ ላይ የተመሰረተ ነው፡፡ በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል በማመን በአንድ ጊዜ ከእግዚአብሄር ዘንድ የሐጢያትን ስርየትን
ስለተቀበልን የበደሉንን ሰዎች ይቅር በማለት ለእግዚአብሄር ጽድቅ መኖር
አለብን፡፡ ጌታ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ በውሃና በደም ሐጢያቶቻችንን በሙሉ
ይቅር እንዳለን እኛም የበደሉንን ሰዎች ይቅር ማለት አለብን፡፡ እነዚህ
የእግዚአብሄር ቃሎች የሚነግሩን እግዚአብሄር ሐጢያቶቻችንን በሙሉ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


134 ጌታ ስለ ጸሎት ያስተማረው ትምህርት (1)

ስለተወልን እኛም የሌሎችን በደል መተው እንዳለብን ነው፡፡


ዕድሜያችንን በሙሉ ብንለፋ ልንከፍለው የማንችለው የ5 መቶ ቢሊዮን
ብር ዕዳ እንዳለብን እናስብ፡፡ የእያንዳንዳችንም የሐጢያት ደመወዝ ያን ያህል
መጠን ያለው ይሆናል፡፡ እግዚአብሄር ግን ራርቶልን የሐጢያቶቻችንን ዕዳ ያለ
ምንም ቅድመ ሁኔታ ሰረዘልን፡፡ እግዚአብሄር አብ ‹‹እንደተከፈለ እቆጥረዋለሁ››
ከማለት ይልቅ ልጁን ላከ፡፡ እንዲጠመቅ፣ የዓለምንም ሐጢያቶች እንዲወስድና
እንዲሰቀል አደረገው፡፡ ስለዚህ ኢየሱስ በጥምቀቱና በመስቀሉ ደም
የሐጢያቶቻችንን ዋጋ ከፍሎ አዳነን፡፡ በእርሱ የሐጢያቶች ስርየት በማመናችንም
ጌታችን ዕዳችንን የሰረዘው እንዲህ ነው፡፡ የሐጢያት ስርየትን የተቀበልነው
ሐጢያቶቻችንን ለማስወገድ ባደረግነው አንዳች ነገር ሳይሆን እውነቱን በማመን
ብቻ ነው፡፡ ባለን እምነት የደህንነትን ስጦታና የሐጢያቶቻችንን መንጻት
ከእግዚአብሄር ተቀብለናል፡፡ ኢየሱስ እኛ በዕድሜያችን ሁሉ መልሰን መክፈል
የማንችለውን የ5 መቶ ቢሊዮን ብር ዕዳ በጥምቀቱና በመስቀል ላይ ባፈሰሰው
ደሙ ስለከፈለ ሐጢያቶቻችን ምንም ሳናደርግ ተሰርዘዋል፡፡ ይህ የሆነው ግን
በእርሱ ጸጋ ብቻ ነው፡፡
እኛም ሌሎች በእኛ ላይ የፈጸሙዋቸውን ጥቃቅን በደሎች መሰረዝ
አለብን፡፡ እርስ በርሳችን በይቅርታ መሰረት ላይ መኖር አለብን፡፡ ከሌሎች
ሐጢያተኞችና ጻድቃኖች ጋር ስንኖር ሌሎች የበደሉንን በደል እርስ በርሳችን
ይቅር መባባል ያስፈልገናል፡፡ በጌታ ወንጌል መሰረት እርስ በርሳችን ይቅር
መባባል ያስፈልገናል፡፡
እኛ ስለ ሐጢያቶቻችን የእግዚአብሄር ዕዳ አለብን፡፡ ጌታ ግን ወደዚህ
ምድር መጥቶ ከአጥማቂው ዮሐንስ በተቀበለው ጥምቀትና ደም ሐጢያቶቻችንን
በሙሉ ይቅር አለ፡፡ ጌታ ሐጢያቶቻችንንና ረዳተ ቢስነታችንን አይቶ ሁሉን
ጠራርጎ አስወገዳቸው፡፡ ጌታ ሕይወታችንን ለእርሱ አሳልፈን ብንሰጥም ጻድቃን
መሆን እንደማንችል ስላወቀ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል እውነት
ሐጢያቶቻችንን ለአንዴና ለዘላለም አነጻቸው፡፡ እግዚአብሄር አብ አንድያ ልጁን
ልኮ በጥምቀቱ የዓለምን ሐጢያቶች እንዲወስድ፣ እንዲሰቀል፣ እንዲነሳና
ከሐጢያቶቻችን ሁሉም ፈጽሞ እንዲያድነን አደረገ፡፡ ስለዚህ ኢየሱስ ከዘላለም
ሐጢያት ያዳነን የዘላለም መድህናችን ሆነ፡፡
እኛ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን ሕያው የሆነውን ጌታን
ተገናኝተናል፡፡ የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ደህንነታችሁ እንደሆነ በልባችሁ
ታምናላችሁን? --አዎ--፡፡ ኢየሱስ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ሐጢያቶቻችንን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ጌታ ስለ ጸሎት ያስተማረው ትምህርት (1) 135

በሙሉ ይቅር እንዳለ በማመን የሐጢያቶቻችንን ስርየት ተቀብላችኋልን? --አዎ--፡፡


ስለዚህ አስገራሚ በሆነ ጸጋ ከዓለም ሐጢያቶች ይቅርታን ስላገኘን ሌሎች
የበደሉንን በደል ይቅር ማለት ያስፈልገናል፡፡ የጌታ ጸሎት አራተኛው ርዕሰ ጉዳይ
እርስ በርስ ይቅር መባባል ነው፡፡ ጌታ ያዘዘንን ይህንን ጸሎት ተግባራዊ ማድረግ
የመንፈሳዊ ሕይወታችን ትክክለኛ መንገድ ነው፡፡
እዚህ በአራተኛው የጌታ ጸሎት ክፍል ውስጥ ግልጽ ሊሆንልን
የሚያስፈልገው የሐጢያቶቻችንን ስርየት የምናገኘው የንስሐ ጸሎቶችን በመጸለይ
አለመሆኑ ነው፡፡ አንዳንዶች ‹‹እኛም የበደሉንን ይቅር እንደምንል በደላችንን
ይቅር በለን›› የሚለውን ይህንን ምንባብ ተመልክተው ‹‹ይህንን ተመልከቱ፤
የሐጢያቶችን ስርየት የምታገኙት የንስሐ ጸሎቶችን ስትጸልዩ ነው›› ይላሉ፡፡ ነገሩ
ግን እንደዚህ አይደለም፡፡ እንዲህ ያለ ዕብለት የመነጭው የውሃውንና የመንፈሱን
ወንጌል በተሳሳተ መንገድ በመረዳታቸው ነው፡፡
ይህ መስመር በትክክል የሚናገረው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
የሐጢያቶችን ስርየት የተቀበሉ እርስ በርሳቸው ይቅር መባባልና አንዳቸው
የሌላቸውን ድክመቶች መሸፈን እንደሚገባቸው ነው፡፡ የሰው ሐጢያቶች
በአንደበት በመናገር ብቻ ይቅር ሊባሉ አይችሉም፡፡ ነገር ግን ትክክለኛ ስርየት
ያስፈልጋቸዋል፡፡ ነውር የሌለበት ትክክለኛ እንስሳ በእጆች መጫን አማካይነት
ሐጢያቶች ተላልፈውበት የሐጢያቶችን ደመወዝ የሚከፍል ይፋ የሆነ ሞት
መሞት አለበት፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ በመውሰድ የጋራ
ለሆነው ይቅርታ መሰረቶችን ሁሉ ጥሎዋል፡፡ ስለዚህ በሕይወት ስንኖር
የሐጢያቶችን ስርየት በሚሰጠን እምነታችን አማካይነት አንዳችን የሌላችንን
ስህተቶች መሰረዝ አለብን፡፡

እግዚአብሄር በሁሉም መንገድ እንዲጠብቀን መጸለይ አለብን፡፡

ማቴዎስ 6፡13 እንዲህ ይላል፡- ‹‹ወደ ፈተናም አታግባን ከክፉ አድነን


እንጂ፡፡›› ፈተና ማለት ወደ ችግሮች መሮጥ ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ‹‹ወደ ፈተና
አታግባን›› ማለት ግራ ወደ መጋባትና ወደ ችግር እንዳንገባ ይጠብቀን ዘንድ
መጸለይ ማለት ነው፡፡ በእግዚአብሄር አብ ፊት ስንጸልይ እንዲህ ብለን መጸለይ
ይኖርብናል፡- ‹‹እግዚአብሄር አብ ወደ ችግሮች እንድገባ አትፍቀድ፡፡ በእያንዳንዱ
አደገኛ ሁኔታ ውስጥ ጠብቀኝ፡፡ እግዚአብሄር ሆይ እባክህ ባርከኝ፤ ከመሳሳት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


136 ጌታ ስለ ጸሎት ያስተማረው ትምህርት (1)

ጠብቀኝ፡፡ ምክንያቱም በጣም ብዙ ዓለማዊ ቁሳቁስ ስላለኝ ወይም በቂ ቁሳቁስ


ስለሌለኝ ከክፉዎች ጠብቀኝ፡፡ በፈተናዎች ውስጥ እንድወድቅ አትፍቀድ፡፡››
ብዙውን ጊዜ ወደ ፈተና አታግባን ብለን ልንጸልይ ይገባናል፡፡
በየቀኑ ከመጀመሪያው ጸሎት ጀምሮ እስከ ስድስተኛው ጸሎት ድረስ
ያሉትን በጥንቃቄ ልንጸልይ ይገባል፡፡ ሰው ፈተና ውስጥ ሲወድቅ አእምሮው
ይጨነቃል፡፡ መጨረሻውም መሞት ይሆናል፡፡ ስለዚህ ችግሮች ውስጥ እንዳንገባ
በየቀኑ ወደ እግዚአብሄር መጸለይ ይገባናል፡፡
በተጨማሪም በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ ከሚገኙ ወንድሞችና
እህቶች ጋር የእምነትና የእውነት ሕብረትን በማድረግ በልቦቻችን ውስጥ ካሉት
ችግሮቻችንም መውጣት አለብን፡፡ የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ዳግመኛ
የተወለዱ ክርስቲያኖች ሕብረት የሚያደርጉባት ትልቅ ስፍራ ነች፡፡ ገና ዳግመኛ
ባልተወለዱ ሰዎች መካከል እውነተኛና ከልብ የሆነ ሕብረት ማድረግ
አይቻልም፡፡ ሆኖም በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ እናንተ በፈለጋችሁት
መጠን ሕብረት የሚያደርጉ ብዙ ሰዎች አሉ፡፡
ከአንድ ሰው ጋር ሕብረት እንዲኖራችሁ ስትሞክሩ በመንፈሳዊ ደረጃ
ከእናንተ ጥቂት ከፍ ከሚል ሰው ጋር ብታደርጉ የተሻለ ነው፡፡ ይህ የሚሆነበት
ምክንያት እንደዚህ ያሉ ሰዎች ተጨባጭና ተገቢ የሆኑትን መንፈሳዊ ዕውቀትና
ተሞክሮዎች በዝርዝር ማጋራት ስለለሚችሉ ነው፡፡ ይህ ለእኛ መልካም ነው፡፡
ምክንያቱም ከእኛ ጋር በመነጋገር መንፈሳዊውን የእምነት ምግብ እንድንመገብ
ቀለል ያደርጉልናልና፡፡ ከእኛ ሁኔታ ጋር በብዙ በተዛመደ መልኩም ከእኛ ጋር
ሊጣጣሙ ይችላሉ፡፡ ላደጉ ሰዎች የሚሆን ብዙ የእምነት ምግብ አለ፡፡ ነገር ግን
በእምነት ከእኛ ብዙ ከመጠቀ ሰው ጋር ሕብረት የሚኖረን ከሆነ
አይጠቅመንም፡፡ ምክንያቱም መፍጨት የሚያቅተን በጣም ብዙ መንፈሳዊ
ምግብ ሊመግቡን ይችላሉና፡፡
ይህንን ለመጀመሪያ ጊዜ ብስክሌት መንዳት ስንማር ከነበረበት ሁኔታ ጋር
ልናነጻጽረው እንችላለን፡፡ ገና ብስክሌት በመማር ላይ ላለ ትንሽ ልጅ ምርጡ
አስተማሪ ከወላጆቻቸው ይልቅ ብስክሌት በመንዳት የተካኑት ወንድሞቹ ወይም
እህቶቹ ናቸው፡፡ አንድ ትንሽ ልጅ መረዳት በሚችልበት ደረጃ ማብራራት
የሚችለው ሰው በተመሳሳይ ነገር ውስጥ ያለፈ ሰው ነው፡፡ አባት ትንሹን ልጁን
እንዴት ብስክሌት እንደሚነዳ ሊያስተምረው ቢፈልግ በራሱ ደረጃ የሚመጥን
ትልቅ ብስክሌት ሊያመጣና ለመማር የሚፍጨረጨረውን ትንሽ ልጅ
ሊያስቀይመው ይችላል፡፡ ትንሹ ልጅ ፈጥኖ መማር የሚችለው እህቶቹ ወይም

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ጌታ ስለ ጸሎት ያስተማረው ትምህርት (1) 137

ወንድሞቹ ትንሽ ብስክሌት ሲነዱ በመመልከትና ‹‹እኔም ያንን ማድረግ


እችላለሁ›› በሚል አሳብ በመደፋፈር ነው፡፡ የእርሱ ታላላቆች ለትንሹ ልጅ
ተጨባጭ መመሪያዎችን በመስጠት ሊያግዙት ይችላሉ፡፡ የአባትየው ትልቁ
ብስክሌት ብስክሌቱ ላይ ከመፈናጠጣቸው በፊት እንኳን ከአባቱ ጋር መንዳትን
የሚማረውን ልጅ ግራ ሊያጋባው ይችላል፡፡
ይህ ከእምነት ሕብረታችን ጋርም ተመሳሳይነት አለው፡፡ በእኔ ደረጃ እጅግ
ተጨባጭና ትክክለኛ በሆነ መንገድ ደረጃ በደረጃ በእምነት እንዳድግ ሊረዳኝ
የሚችለው ተመሳሳይ በሆነ ጎዳና የተጓዘ ሰው ነው፡፡ ሕብረት ከእኔ ቀደም ብሎ
ወዲያውኑ ተመሳሳይ በሆነ ነገር ውስጥ ካለፈ ሰው ጋር ሲሆን በጣም ጠቃሚ
ነው፡፡
ሁልጊዜም ‹‹ወደ ፈተና አታግባን፤ ጠብቀን፡፡›› ‹‹ከክፉ አድነን›› በማለት
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን መጸለይ ይገባናል፡፡ በክፉው እጅ ላይ
ስንወድቅ እጅግ ትልቁ አደጋ በአደጋ ላይ እንዳለን አለማወቃችን ነው፡፡ ያ ምን
ያህል አደገኛ ነው? ስለዚህ በክፉው እጅ ላይ እንዳንወድቅና እግዚአብሄርም
ከክፉው እንዲያድነን መጸለይ ይገባናል፡፡ በፈተና ውስጥ እንዳላችሁ የሚሰማችሁ
ከሆነ በተቻላችሁ ፍጥነት በእምነታችሁ ውጡ፡፡
ማቴዎስ 6፡14-15 እንዲህ ይላል፡- ‹‹ለሰዎች ሐጢአታቸውን ይቅር ብትሉ
የሰማዩ አባታችሁ እናንተን ደግሞ ይቅር ይላችኋልና፡፡ ለሰዎች ግን
ሐጢአታቸውን ይቅር ባትሉ አባታችሁም ሐጢአታችሁን ይቅር አይላችሁም፡፡››
እርስ በርስ ይቅር መባባል አለብን፡፡ በእርግጥ ዳግመኛ የተወለዱ ሰዎች
ይቅር በማለት አይታሙም፡፡ ሆኖም በእኛው በጻድቃኖች መካከልም እጅግ
አስቸጋሪው ነገር አንድን ሰው ይቅር ማለት ነው፡፡ ምናልባትም ጌታችን እዚህ ላይ
አበክሮ የተናገረው ለዚህ ሳይሆን አይቀርም፡፡ የሌሎችን ስህተቶች፣ ውድቀቶችና
ድክመቶች ስታዩ በቀላሉ ይቅር ትላላችሁ ወይስ አትሉም?
አንዳንድ ነገሮች ሊቀየሩ ስለማይችሉ ልባችን ይጎዳ ይሆናል፡፡ ነገር ግን
በቀላሉ ይቅር እንላለን፡፡ ሌሎቹ ሰዎች ባደረጉት ነገር ከልባቸው ተጸጽተው
ልባቸውን ከመለሱ ይቅር ልንለው የማንችለው ምንም ነገር የለም፡፡ ተመልሰው
ባህርያቸውን ከለወጡ መቀበል የማንችለው ምንም ነገር የለም፡፡
ሆኖም ይህንን ማድረግ የማይችሉ ብዙዎች አሉ፡፡ በክፉው ፈተና ውስጥ
የወደቁ ሰዎች ሌሎችን ይቅር ከማለት ይልቅ ወደ ፈተና ይመሩዋቸዋል፡፡ ስለዚህ
ያለንበትን ችግርና ሁኔታ እንደ ዕዳ በመመልከት ሌሎችን ወደ ፈተና መምራት
አይገባንም፡፡ አጋር ምዕመናኖችን ግራ እንዲጋቡና በእግዚአብሄር ላይ እንዲነሱ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


138 ጌታ ስለ ጸሎት ያስተማረው ትምህርት (1)

የሚያደርጉ ሰዎች መጨረሻቸው በእርግጥም ጥፋት ነው፡፡


እምነታችንን ለማሳየት ስንል የሐይማኖትን ሕይወት መኖር የለብንም፡፡
ረጅሙን ታሪክ ለማሳጠር ትክክልም ይሁን ስህተት ማድረግ የሚገባን ነገር ቢኖር
ነገሩን በእግዚአብሄር ፊት ማጤን ነው፡፡ ያንን ስናደርግ ስህተት እንደሰራን
ከልባችን ከተረዳን ማድረግ ያለብን ‹‹ስህተት ነበር›› በማለት ስህተቱን መቀበልና
ማመን ነው፡፡ የይቅርታ ወይም ስህተቶችን የማመን ቃሎችን ከሰማን ከልባችን
ውስጥ ቁጣን ማስወገድና ይቅር ማለት አለብን፡፡ ኢየሱስ እንዲህ ብሎዋል፡-
‹‹ነገር ግን ቃላችሁ አዎን አዎን ወይም አይደለም አይደለም ይሁን፡፡ ከእነዚህም
ወጣ ከክፉው ነው፡፡›› (ማቴዎስ 5፡37) ማብራሪያ ወይም ማማኻኛ
አያስፈልገንም፡፡ ማድረግ ያለብን ብቸኛው ነገር በእግዚአብሄር ፊት ጽድቅን
ማሰብና አንዳች ስህተት ከተሰራም ስህተቶቻችንን ማመን ነው፡፡ 
አንድ ወንድም ተሳስቶ ከሆነ ሙሉውን ታሪክ ከሰማን በኋላ እኛ ማድረግ
የሚያስፈልገን ‹‹ስህተት›› መሆኑን መንገርና እንዲያምን ማድረግ ነው፡፡ እርሱም
ማድረግ ያለበት ነገር ቢኖር እነዚህን ነገሮች በእግዚአብሄር ፊት ማሰብ፣ እነዚህን
ስህተቶች በጥምቀቱና በመስቀል ላይ ደሙ የደመሰሰውን ጌታን መመልከትና
እንደገና በእምነት መቆም ነው፡፡ ምንም ዓይነት ስህተት እንስራ በእግዚአብሄር
ጽድቅ ላይ በእምነት መቆም፣ ሐጢያቶቻችንን ያስወገደውን አምላክ ማመስገንና
ወደፊት የተሻለውን ለማድረግም በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት የእግዚአብሄርን
ምሪት መሻት ነው፡፡

የጌታ ጸሎት ማጠቃለያ፡፡

‹‹በሰማይ የምትኖር አባታችን ሆይ ስምህ ይቀደስ›› በሚለው


የመጀመሪያው የጸሎት ርዕሰ ጉዳይ መሰረት መጸለይ አለብን፡፡ ገና ዳግመኛ
ላልተወለደ ሐጢያተኛ ‹‹ስምህ ይቀደስ›› የሚለው የጸሎቱ የመጀመሪያ ክፍል
‹‹የእግዚአብሄርን ስም ማክበር እችል ዘንድ የሐጢያትን ስርየት እንድቀበል
እርዳኝ›› ብሎ መጸለይ ማለት ነው፡፡ ዳግመኛ ያልተወለዱ ግን እግዘአብሄርን
ያከብሩ ዘንድ በመጀመሪያ የሐጢያትን ስርየት ለማግኘት መጸለይ አለባቸው፡፡
ስለዚህ ጻድቃን ‹‹እባክህ የተቀደሰ ሕይወት እንድኖር ፍቀድልኝ፤ እባክህ
ስምህን እንዳረክሰው አትፍቀድ›› ብለው ሊጸልዩ ይገባቸዋል፡፡ ጻድቅ ሆነው
አብረውን ይሰሩ ዘንድ ወደ ሐጢያተኞች ሄዶ እምነታቸውን መደገፍ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ጌታ ስለ ጸሎት ያስተማረው ትምህርት (1) 139

የእግዚአብሄርን ስም የሚያረክስ አሳፋሪ ባህርይ ነው፡፡ ያንን ማድረግ የለብንም፡፡


እግዚአብሄርን የሚቃወሙትን ልንዋጋቸው ይገባናል፡፡ ከእነርሱ ጋር ሰላምን
መፍጠርና ሕብረትን መሻት እግዚአብሄርን የሚቃወም ትልቅ ሐጢያት ነው፡፡
ስለዚህ እምነት ካላቸው ጋር በእምነት ተባብሮ ለወንጌል መስራት ጽድቅ ነው፡፡
ልባችንን ከሐጢያተኞች ጋር ማቀናጀት፣ በክፉ ላይ መውደቅና ጌታን ማሰደብ
ነው፡፡
ጠቃሚ መረጃ ለማነፍነፍ ወደ አገራችን ከገባ ሰላይ ጋር ብንተባበር ምን
ይገጥመናል? ይህ ከሰላዩ የበለጠ ክፉና የራሱን አገር የሚሸጥ ከሃዲ ያደርገናል፡፡
ይህ የማን ወገን መሆን እንደሚገባው የማያውቅና የገዛ አገሩን ለመሸጥ ከጠላት
ጋር የሚተባበር ከሐዲ የሚያደርገው ነገር ነው፡፡ ደግሞም በሞት የሚያስቀጣ
ትልቅ ሐጢያት ነው፡፡
የጌታ ጸሎት ሁለተኛው መስመር ‹‹መንግሥትህ ትምጣ፤ ፈቃድህ በሰማይ
እንደሆነች እንዲሁ በምድር ትሁን›› የሚለው ነው፡፡ ይህ ጻድቃኖች ገና
የሐጢያት ስርየትን ላልተቀበሉ ነፍሳቶች የሚጸልዩት ጸሎት ነው፡፡ የእግዚአብሄር
ፈቃድ በምድር ላይ እንዲሆን የሚጸለይ ጸሎት ነው፡፡
ታዲያ የእግዚአብሄር ፈቃድ ምንድነው? እያንዳንዱ ሰው የሐጢያትን
ስርየት እንዲቀበል ነው፡፡ እግዚአብሄር ለዚህ እንዲያግዘን መጠየቅ አለብን፡፡
ለሰራተኞችና ለዓለማዊ ቁሳቁሶችም መጸለይ አለብን፡፡ ከዚያም የእርሱን ሥራ
ለመስራት ሁለንተናችንን መስጠት ያስፈልገናል፡፡ የእግዚአብሄር ፈቃድ በምድር
ላይ ይሆን ዘንድ ሁለንተናችንን፣ ጊዜያችንንና ጥረታችንን እንደዚሁም የእኛ
የሆነውን ሁሉ መስጠት አለብን፡፡ ሰውን ሁሉ ወደ ሐጢያት ስርየት ለሚመራው
ሥራ መኖር አለብን፡፡ ለዚህም በየቀኑ መጸለይና ልባችንንና ሰውነታችንን
በተጨባጭ በመስጠት የእግዚአብሄር ፈቃድ በምድር ላይ እንዲፈጸም ጥረቶችን
ማድረግ አለብን፡፡
አንዳንድ ሰዎች የሐጢያት ስርየትን ከተቀበሉ በኋላ ለእግዚአብሄር
መንግሥት እንድጸልይ ያስተማረንን ምክር ችላ ይሉታል፡፡ የሐጢያት ስርየትን
የተቀበለ ሰው ለወንጌል መስፋፋት የማይጸልይ ወይም ለዚህ ዓላማ
ከእግዚአብሄር ቤተከርስቲያን ጋር የማይተባበር ከሆነ በክፉ ሰው ቦታ ላይ
የተቀመጠ ነው፡፡ እንደዚህ ዓይነት ሰው ከእግዚአብሄር ዘንድ የሥጋና የነፍስ
ባርኮቶችን መጠበቅ አይገባውም፡፡ ስለዚህ በተጨባጭ ለእግዚአብሄር ጽድቅ
የማይኖሩና የማይጸልዩ ጻድቃን ሰዎች ከእግዚአብሄር ፈቃድ ውጭ እየኖሩ ነው፡፡
ከእግዚአብሄር ፈቃድ ጋርም እየተባበሩ አይደሉም፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


140 ጌታ ስለ ጸሎት ያስተማረው ትምህርት (1)

በየቀኑ ስለ ዕለት እንጀራችን መጸለይ ይገባናል፡፡ ይህም ሦስተኛው የጸሎት


ርዕሰ ጉዳይ ነው፡፡ ‹‹እንዳንራብ መብልን ስጠን፤ የሥጋና የመንፈስ ምግብ
ስጠን፡፡ የእግዚአብሄርን ሥራ መስራት እንችል ዘንድ ሥራችንን ባርክልን፡፡››
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል እናገለግል ዘንድ ስለ ችሮታዎቹ መጸለይ
ይገባናል፡፡ ይህ ሦስተኛው የጸሎት ክፍል ነው፡፡
አራተኛው የጸሎት ክፍል ጌታ በውሃና በደም ሐጢያቶቻችንን ሁሉ ይቅር
እንዳለን የበደሉንን ሌሎችም ይቅር ማለት ይገባናል፡፡ የሐጢያቶችን ስርየት
በተቀበሉት ቤተሰቦቻችን ውስጥ ባሉት ወንድሞችና እህቶች፣ በወንድና በሴት
የእግዚአብሄር አገልጋዮች መካከል ጌታ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ እንደደመሰሰ
አንዳችን የሌላችንን በደሎች ይቅር ማለት አለብን፡፡ አንድ ሰው ‹‹ይህ ስህተት
ነው›› ቢል ሌላው ሰው ‹‹አሃ! አዎ ተሳስቻለሁ›› ብሎ ማመን ይገባዋል፡፡ ያን ጊዜ
እርስ በርሳችን ከልባችን ይቅር መባባል ይገባናል፡፡ እኔ ከእንግዲህ ወዲህ ስለዚህ
ነገር ባላወራም ሁላችሁም በቀላሉ ይቅር እንደምትሉ አምናለሁ፡፡ እስከ አሁን
ድረስ በታማኝነት የኖርነው ለዚህ ነው፤ አይደለምን?
ወደ ፈተና እንዳንገባ፣ ችግሮች ውስጥ እንዳንወድቅና ጌታም በሰላም
እንዲጠብቀን መጸለይ ይገባናል፡፡ ስድስተኛው የጸሎት ክፍል ‹‹ከክፉ ጠብቀን››
የሚል ነው፡፡ እኛ ዳግመኛ የተወለድን ሰዎች በክፉዎች እጅ ላይ እንዳንወድቅ
ወይም በእነርሱ እንዳንማረክና በክፉዎች እጅ ላይ ስንወድቅም እግዚአብሄር
እንዲያድነን መጸለይ አለብን፡፡
ከዚያም ጌታ ‹‹እርስ በርሳችን በደሎቻችንን ይቅር እንድንባባል›› ነግሮናል፡፡
ይህ ማለት ጻድቃን እርስ በርሳቸው ይቅር መባባል አለባቸው ማለት ነው፡፡
እኛ ጻድቃኖች ጌታ እንድንጸልይ ባስተማረን መንገድ ሁልጊዜም መጸለይና
በእርሱም ማመን አለብን፡፡ በየቀኑ እነዚህን ርዕሰ ጉዳዮች መጸለይ ይገባናል፡፡
በተጨማሪም በየቀኑ በዚያ መንገድ መኖር አለብን፡፡ እርስ በርሳችን ይቅር
ለመባባል፣ ወደ ፈተና ወይም ወደ ክፉ እንዳንወድቅ፣ ለዕለት እንጀራችንና
የእግዚአብሄር መንግሥትም በምድር ላይ እንድትመጣ መጸለይ ይገባናል፡፡ ያም
ብቻ አይደለም፤ እንዲህ ያለውን ሕይወት በእምነት ልንኖር መፍጨርጨር
ይገባናል፡፡ እግዚአብሄርን ለማክበርም በጎደልንባቸው አካባቢዎች የጸሎት
ሕይወትን መኖር አለብን፡፡ በየቀኑ ጌታ ያስተማረንን ጸሎት የሚጸልይ ሰው
‹‹የእምነት ሰው›› ነው፡፡
ውድ ክርስቲያኖች የዛሬውን የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ገና ዳግመኛ
ላልተወለዱ ሰዎች ብናቀርብላቸው በተለየ መንገድ ይተረጉሙታል፡፡ ነገር ግን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ጌታ ስለ ጸሎት ያስተማረው ትምህርት (1) 141

እኛ ዳግመኛ የተወለደን ሰዎች ምንባቡን ወስደን ስንመረምረውና ስንተረጉመው


እነርሱም ደግሞ እስከ አሁን ድረስ የተናገርሁት ነገር ስህተት ሳይሆን ትክክል ነው
ብለው ይቀበላሉ ብዬ አምናለሁ፡፡ ያንን ታምናላችሁን? --አዎ--፡፡
እርሱ ዳግመኛ ለተወለዱት ሰዎች የተናገረው የመጀመሪያው የጸሎት ርዕሰ
ጉዳይ ‹‹ስምህ ይቀደስ›› የሚለው ነው፡፡ ሆኖም በቀን ተቀን ሕይወታችን
የእግዚአብሄርን ስም ከሚያከብር ይልቅ ምናልባት የእግዚአብሄርን ስም
የሚያሰድቡ ነገሮች አያደረግን ይሆን? እናንተና እኔ ሁልጊዜም 100% ጥረት
ማድረግ የምንችል ሰዎች ነን? ጌታን ማክበር ባንችል እንኳን ቢያንስ የጌታን ስም
ማጠልሸት የለብንም፡፡ ይህ ማለት የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ለማድረግ
እየሞከረች ላለው ነገር የዕንቅፋት ድንጋይ ከመሆን ይልቅ የእግዚአብሄር ስም
ይቀደስ ዘንድ የእርሱን ቤተክርስቲያንና አገልግሎቶችዋን ማክበር፣ መውደድ፣
ከእርስዋ ጋር መተባበርና መቀናጀት ይገባናል፡፡
ውድ ክርስቲያኖች ለወንድሞችና ለእህቶች፣ ለወንድና ሴት አገልጋዮች፣
ለእግዚአብሄር መንግሥት መስፋት፣ የእግዚአብሄርን ስም ለማያረክስ ሕይወትና
ለዕለት እንጀራችን ከልብ መጸለይ ይገባናል፡፡ ጌታ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ
እንዳስወገደልን እኛም የበደሉንን ሁሉ ከልባችን ይቅር ማለት ይገባናል፡፡ ችግር
ውስጥ እንዳንገባም መጸለይ ይገባናል፡፡
ልባችን ፈተና ውስጥ እንዳይወድቅ እንጸልይ፡፡ ቃሉን ካልሰማን ልባችን
ፈተና ውስጥ ይገባል፡፡ ችግር ውስጥም ይዘፈቃል፡፡ መንፈሳዊ ምግብ የሆነውን
የእግዚአብሄርን ቃል ካልሰማን ልባችን ይታመማል፡፡ ይህ በሚሆንበት ጊዜ ፈተና
ማለትም ችግር ውስጥ እንወድቃለን፡፡ ሥጋዊ አስተሳሰቦቻችን ይገኑና መንፈሳዊ
አስተሳሰቦችን ይቆጣጠራሉ፡፡ ይህ በሚሆንበት ጊዜ እኛ ጻድቅ የሆንን ሰዎች
የሥጋን ፍላጎቶች በ100% ውጤት ልንከተል ስለማንችል ልባችን ችግር ውስጥ
ይወድቃል፡፡ ምክንያቱም በሥጋና በመንፈስ መካከል እንዋዥቃለንና፡፡ ስለዚህ
በዚህ ዓይነት ሁኔታ ውስጥ እንዳንወድቅ መጠንቀቅ አለብን፡፡
ለመንፈሳዊ ጤንነት ዝግጁ ለመሆን ወደ እግዚአብሄር ቤተክርስቲያን
መጥተን ቃሉን መስማት አለብን፡፡ በአገልግሎቱ ወቅት ቃሉን የሚሰብከው
ማንም ይሁን ቃሉ በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ ላለ ደካማ ሰው
ይሰበካል፡፡ ከሥጋዊ አስተሳሰቦችና ስህተቶች አተላ መላቀቅ የምንችለው ቃሉን
በመስማት ብቻ ነው፡፡ የሚፈስስ ውሃ እስከፈሰሰ ድረስ አተላዎችንና ቆሻሻዎችን
ስለሚያጠራ እንደማይከረፋ ሁሉ የእግዚአብሄርም ቃል በልባችን ውስጥ
የሕይወት ውሃ ሆኖ እስከፈሰሰ ድረስ በልባችን ውስጥ ያሉትን አተላዎች

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


142 ጌታ ስለ ጸሎት ያስተማረው ትምህርት (1)

ማስወገድ ይችላል፡፡ ሥጋዊ አስተሳሰቦቻችን ሲወገዱ አዳዲስ መንፈሳዊ


አስተሳሰቦች ብቅ ይሉና አእምሮዋችን በሰላም ተጠብቆ እንዲቆይ ባዶ የሆነውን
ስፍራ ይይዛሉ፡፡
ስለዚህ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ከተጻፉት የጸሎት ርዕሰ ጉዳዮች ችላ
ያልናቸው ይኖሩ እንደሆነ ወይም እንዳልሆነ በተቻለ መጠን አዘውትረን
መመርመር ይገባናል፡፡ ችላ ያልነው አንዳች ነገር ካለ ከአሁን ጀምሮ ልናቆመው
ይገባናል፡፡ በዚህ አቅጣጫ መጸለይ መጀመርና እነዚህን አቅጣጫዎች ይበልጥ
መጠንቀቅ ይገባናል፡፡ ጌታ ስንጸልይ ለታይታ እንዳንጸልይ የተናገረውና ጥቂት
በሆኑ የተለያዩ ክፍሎች እንዴት እንደምንጸልይ ያስተማረን ለዚህ ነው፡፡
በጌታ ጸሎት ውስጥ ሁሉም ነገር ተጠቃሎዋል፡፡ ይህም እንዴት የጸሎትን
ሕይወት እንደምንኖር ያሳያል፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ የጸሎቱ የመጀመሪያው ክፍል
ቀድሞውኑም ተመልሶልናል፡፡ በጸሎቱ የመጀመሪያ ክፍል ውስጥ ያለው
የሐጢያት ስርየት ተፈጽሞዋል፡፡ አሁን ግን የተቀደሰ ሕይወት መኖር እንችል
ዘንድ ልንጸልይ ይገባናል፡፡ ስለዚህ የእግዚአብሄርን ክብር የሚያደናቅፉ ሰዎች
እንዳንሆን፣ ጌታ በሰላም እንዲጠብቀንና እንዲባርከን በየቀኑ መጸለይ ይገባናል፡፡
መመገብ ያለበት ሥጋችን ብቻ ሳይሆን መንፈሳችንም ደግሞ ነው፡፡
የሐጢያቶቻቸውን ስርየት የተቀበሉ ጻድቃኖች መንፈሳዊ ምግባችን ቃሉን
መስማት መጸለይ ሊሆን ይችላል፡፡ በተጨባጭ ግን ለእነርሱ እውነተኛው
መንፈሳዊ ምግብ ወንጌልን ማስፋፋት ነው፡፡ ቃሉን መስማትና በልባችን ጽላት
ላይ መጻፍን ማቆም ጠንካራ ጤናን ሊያስገኝ አይችልም፡፡ ለልባችን ትክክለኛ
ጤናን የሚሰጠው ከፍተኛ ጥራት ያለው የምግብ ዘር በድርጊት የሚገለጥ እምነት
ነው፡፡ ቃሉን ከልባችን አምነን በዚያ እምነት መሰረት ስንተገብረው በትክክል
እምነታችን ይሆናል፡፡ አስፈላጊ የሆኑ ከፍተኛ ጥራት ያላቸው የምግብ ዘሮች
በሰውነታችን ውስጥ እንዲሰራጩና እኛም የእምነት ሰዎች ሆነን ማደግ
እንድንችል በዚህ መንገድ በመንፈሳዊ ሁኔታችን ምሉዓን እንሆናለን፡፡
ክፉው ረብሻዎችን ከፈጠረ መተባበርና ክፉውን ነገር እንዲያፈገፍግ
ማድረግ አለብን፡፡ ከመካከላችን አንዱ በክፉው እጆች ውስጥ ከወደቀ እርሱን
ለመርዳት መተባበር አለብን፡፡ ‹‹እግዚአብሄር ሆይ እባክህ ከክፉው የሚመጣውን
ይህንን መንፈሳዊ ማዕበል አቁመው፡፡ እባክህ እያንዳንዳችንን እርዳን›› ብለን
በመጸለይ መተባበርና ራሳችንን መከላከል ይገባናል፡፡
ችላ ስላልናቸው የጸሎት ርዕሰ ጉዳዮች ማሰብ አለብን፡፡ ችላ ያልነው ነገር
ካለም ከዚያ ተመልሰን የጽድቅ ሕይወትን መኖር አለብን፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ጌታ ስለ ጸሎት ያስተማረው ትምህርት (1) 143

ጌታ መጨረሻው እየተቃረበ ሲመጣ እርስ በርሳችን እንድንያያዝ፣ እርስ


በርሳችን እንድንዋደድ፣ እርስ በርሳችን እንድንተናነጽና እንድንመካከር
መክሮናል፡፡ እኛ ዳግመኛ የተወለድን ጻድቃኖች ልባችንን በእምነት መሙላት፣
እርስ በርሳችን መደጋገፍና ለጋስና አፍቃሪ ልብን መለገስ ይገባናል፡፡ አንድ ሰው
ችግር ውስጥ ሲወድቅ ሁኔታውን ከመጠቀም ይልቅ ራሳችንን በእርሱ ሁኔታ
ውስጥ አስቀምጠን ችግሩ የራሳችን ችግር እንደሆነ ማሰብና ‹‹ሁኔታው የእኔ
ቢሆን ኖሮ ምን ይመስል ነበር? ምንስ አደርግ ነበር?›› በሚል እሳቤ መረዳዳት
ይኖርብናል፡፡ ሌላው ሰው እኛ እንደምናደርገው ባለማድረጉና የጽድቅ ሕይወትን
ባለመኖሩ መታገሱ አስቸጋሪ ቢሆንም ሊመለስ እንደሚችል ተስፋ በማድረግ
ልንጸልይና ልንቀበለው ይገባናል፡፡
እኛ ብዙ ጉድለቶች ያሉብን ሰዎች ስለሆንን ብዙውን ጊዜ በቃላት ሊገለጡ
የማይችሉ አሳፋሪ ስህተቶችን እንሰራለን፡፡ ያን ጊዜም ቢሆን እግዚአብሄር
በመጨረሻው ፍርድ ላይ ዳኛ በመሆኑ እነዚህን ሐጢያቶች ያስወገደውን ቃል
በእግዚአብሄር ላይ ባለን እምነት አጥብቀን ብንመለስ ያን ያህል የሚጋነን ጉዳይ
አይሆንም፡፡ ምክንያቱም እግዚአብሄር ይህ ምንም አይደለም ካለ ምንም
አይደለም ማለት ነው፡፡ ሁላችንም ቅቡልነትን ባገኘንበት በጌታ ልብ በሚያምነው
እምነት ውስጥ እርስ በርስ መቀባበል ይገባናል፡፡
ነገሩ ምንም ይሁን በእግዚአብሄር ላይ ባተኮረ መስፈርት፣ በእግዚአብሄር
ዙሪያ ባተኮረ ጸሎት፣ በእግዚአብሄር ዙሪያ ባተኮረ ሕይወት የመጨረሻውን
ውሳኔ መወሰንና በጌታ ጸሎት መሰረት መኖር አለብን፡፡ የጌታን ጸሎት ብቻ
ተረድተው እምነታቸው ደካማ የሆኑ ሰዎችን ልንመስላቸው አይገባንም፡፡ ነገር
ግን ትክክለኛ አእምሮ ይዘው ጠንካራ እምነት ያላቸውና በጸሎትም የእምነትን
ድርጊት የሚተገብሩ ሰዎች መሆን አለብን፡፡ ሁላችንም በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል በማመን በጌታ ጸሎት መሰረት የምንኖረው ያን ጊዜ ነው፡፡
እንደ ጌታ ፈቃድ እንድንኖር ለረዳን አምላክ በቂ ምስጋናን መስጠት
ያቅተኛል፡፡ 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


ጌታ ስለ ጸሎት ያስተማረው
ትምህርት (2)
‹‹ ማቴዎስ 6፡5-15 ››
‹‹ስትጸልዩም እንደ ግብዞች አትሁኑ፤ ለሰው ይታዩ ዘንድ በምኩራብና
በመንገድ ማዕዘን ቆመው መጸለይ ይወዳሉና፤ እውነት እላችኋለሁ ዋጋቸውን
ተቀብለዋል፡፡ አንተ ግን ስትጸልይ ወደ እልፍኝህ ግባ፤ መዝጊያህንም ዘግተህ
በስውር ላለው አባትህ ጸልይ፤ በስውር የሚያይ አባትህም በግልጥ ይከፍልሃል፡፡
አሕዛብም በመናገራቸው ብዛት እንዲሰሙ ይመስላቸዋልና ስትጸልዩ እንደ እነርሱ
በከንቱ አትድገሙ፡፡ ስለዚህ አትምሰሉአቸው፤ ሳትለምኑት አባታችሁ
የሚያስፈልጋችሁን ያውቃልና፡፡ እንግዲህ እናንተስ እንዲህ ጸልዩ፡፡ በሰማያት
የምትኖር አባታችን ሆይ፤ ስምህ ይቀደስ፤ መንግሥትህ ትምጣ፤ ፈቃድህ
በሰማያት እንደሆነች እንዲሁ በምድር ትሁን፤ የዕለት እንጀራችንን ዛሬ ስጠን፤
እኛም ደግሞ የበደሉንን ይቅር እንደምንል በደላችንን ይቅር በለን፡፡ ከክፉም
አድነን እንጂ ወደ ፈተና አታግባን፤ መንግሥት ያንተ ናትና ሐይልም ክብርም
ለዘለዓለሙ አሜን፡፡ ለሰዎች ሐጢአታቸውን ይቅር ብትሉ የሰማዩ አባታችሁ
እናንተን ደግሞ ይቅር ይላችኋልና፤ ለሰዎች ግን ሐጢአታቸውን ይቅር ባትሉ
አባታችሁም ሐጢአታችሁን ይቅር አይላችሁም፡፡››

ሁላችሁም የጸሎት ሰዎች እንደሆናችሁ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡


ከእግዚአብሄርም ዘንድ ምላሽን በማግኘት የእምነት ሰዎች እንደምትሆኑ ተስፋ
አደርጋለሁ፡፡ ጴጥሮስ እንዳለው፡- ‹‹ብርና ወርቅ የለኝም፤ ይህን ያለኝን ግን
እሰጥሃለሁ፡፡ በናዝሬቱ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተነሳና ተመላለስ፡፡›› (የሐዋርያት
ሥራ 3፡6) ብርቱ እምነት ያላችሁና ብዙ ሰዎችን የምትረዱ ሰዎች እንደምትሆኑ
ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ ለምትፈልጉት ነገር ጸልያችሁ እንደምትቀበሉም ተስፋ
አደርጋለሁ፡፡
ሰዎች ሁልጊዜም ደካሞች ናቸው፡፡ ስለዚህ ያለ ማቋረጥ መጸለይ
ያስፈልገናል፡፡ ‹‹ሁልጊዜ ደስ ይበላችሁ፤ ሳታቋርጡ ጸልዩ፤ በሁሉ አመስግኑ››

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ጌታ ስለ ጸሎት ያስተማረው ትምህርት (2) 145

ያለው ለዚህ ነው፡፡ በእግዚአብሄር ላይ ባላችሁ እምነት የምትጸልዩትን ጸሎት


መማር አለባችሁ፡፡ በአንድ የጸሎት ርዕስ ጉዳይ ላይ አብራችሁ በምትጸልዩበት
ጊዜ ጮክ ብላችሁ የመጸለይን ልማድ ካላዳበራችሁ በኋላ ለራሳችሁ መጸለይ
ስትፈልጉ በድፍረት መጸለይ አትችሉም፡፡
ጸሎት የሕይወት እስትንፋስና ባዶ ቼክ ነው፡፡ ይህ ማለት እግዚአብሄርን
ምንም ነገር ብትጠይቁት ይሰጣችኋል ማለት ነው፡፡ እግዚአብሄር የጻድቃን
አምላክ ስለሆነ ስንጸልይ ይሰማናል፡፡ መልስም ይሰጠናል፡፡

በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ባለን እምነት እግዚአብሄርን እንዲረዳን


ልንጠይቀው ይገባናል፡፡

ማቴዎስ 7፡7-12 እንዲህ ይላል፡- ‹‹ለምኑ ይሰጣችሁማል፤ ፈልጉ


ታገኙማላችሁ፤ መዝጊያን አንኳኩ ይከፈትላችሁማል፡፡ የሚለምነው ሁሉ
ይቀበላልና፤ የሚፈልገውም ሁሉ ያገኛል፡፡ መዝጊያንም ለሚያንኳኳ
ይከፈትለታል፡፡ ወይስ ከእናንተ ልጁ እንጀራ ቢለምነው ድንጋይን የሚሰጠው
ከእናንተ ማን ሰው ነው? ዓሣስ ቢለምነው እባብን ይሰጠዋልን? እንኪያስ እናንተ
ክፉዎች ስትሆኑ ለልጆቻችሁ መልካም ስጦታ መስጠትን ካወቃችሁ በሰማያት
ያለው አባታችሁ ለሚለምኑት እንዴት አብልጦ መልካም ነገርን ይሰጣቸው?
እንግዲህ ሰዎች ሊያደርጉላችሁ የምትወዱትን ሁሉ እናንተ ደግሞ እንዲሁ
አድርጉላቸው፡፡ ሕግም ነቢያትም ይህ ነውና፡፡››
ይህ ምንባብ በእውነት በእምነት ስንጠይቅ እግዚአብሄር አብ የጠየቀንውን
እንደሚሰጠን ይናገራል፡፡ ጌታ እንዴት እንደምንጸልይ አስተምሮናል፡፡ አብም
የሚያስፈልገንን ሁሉ ያውቃል፡፡ ነገር ግን አሁንም ቢሆን ወደ እግዚአብሄር
መጸለይ ይገባናል፡፡ እግዚአብሄር የሚሰማንና መልስ የሚሰጠን ያን ጊዜ ብቻ
ነው፡፡ የእግዚአብሄርን ጸጋ በወንጌሉ አማካይነት መማር ቢያስፈልገንም
ከእግዚአብሄር ጋር ሕብረት የማድረግ ሕይወትንም መማር አለብን፡፡ እኛ
ጻድቃኖች ወደ አብ ብንጸልይ ጸሎታችንን እንደሚመልስልንም በእምነታችን
አማካይነት መማር ያስፈልገናል፡፡
እግዚአብሄር አብ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ለሚያምኑ ሰዎች አባት
ሆኖ ሳለ የሚፈልጉትን ለሚጠይቁት ልጆቹ መልካም ነገሮች የማይሰጠው
ለምንድነው? እግዚአብሄር አባታችን መሆኑንና በምንጸልይበት ጊዜም መልካም

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


146 ጌታ ስለ ጸሎት ያስተማረው ትምህርት (2)

ነገሮችን እንደሚሰጠን ማመን አለብን፡፡ በዚህ በሚያምን እምነት መጸለይ


ይገባናል፡፡ ከልባቸው በእምነት ወደ እግዚአብሄር መጸለይን የሚያውቁ ሰዎች
ለወንድሞቻቸውና ለእህቶቻቸው እንደዚሁም ለሌሎች ነፍሳቶች መዳን መጸለይ
ይችላሉ፡፡ አንድን ሰው የእምነት ሰው የሚያደርገው በእግዚአብሄር ጽድቅ ውስጥ
ሆኖ ለመጸለይ መሞከሩ ነው፡፡ በእውነተኛው የአዳኙ ደህንነት የሚያምኑ ሰዎች
እምነት ከልብ የሆኑ ጸሎቶች ያላቸውን እየተለማመዱ ቀስ በቀስ ያድጋል፡፡
ስለዚህ በእምነት አማካይነት ስለ ጸሎቶች መማር አለብን፡፡
እኛ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት ከሐጢያቶቻችን ለአንዴና
ለዘላለም የዳንን ብንሆንም ልክ ያለ ማቋረጥ እንደምንተነፍሰው ሁሉ ‹‹ያለ
ማቋረጥ›› ወደ እግዚአብሄር መጸለይ ይገባናል፡፡ ጌታ እንዲረዳን ሁልጊዜ
የምንጸልይ ከሆንን እርሱ ይሰማናል፡፡ በእምነት አማካይነት ከእግዚአብሄር ጋር
ግንኙነትን በማዳበር፣ ሁልጊዜም እንዲረዳን በመጠየቅና የእርሱን እርዳታ
በመቀበል መኖር አለብን፡፡
የጸሎት ሰዎች እንደምትሆኑ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ እኔም ደግሞ በእምነት
አማካይነት የሚጸልይ ሰው እንደምሆን ተስፋ አለኝ፡፡ እናንተና እኔ በእምነት
ጸልየው መልሶቻቸውን የሚቀበሉ ሰዎች እንደምንሆንም ተስፋ አደርጋለሁ፡፡
እናንተና እኔ በእምነት፣ በብልጥግና፣ በጤናና በእግዚአብሄር ጽድቅ ባለጠጋ ሆነን
እነዚህን ነገሮች ለሌሎች ለማጋራት እንችል ዘንድ እግዚአብሄርን ብዙ ነገሮች
እንደምንጠይቀው ተስፋ አለኝ፡፡ እግዚአብሄር እነዚህን በረከቶች እንደሚሰጠንና
እውነተኛ የጸሎት ሰዎች ስንሆንም ብሩካኖች እንደምንሆን ተስፋ አለኝ፡፡

የእግዚአብሄር አብን ቅዱስ ስም የሚያከብር እምነት እንዲኖረን


ልንጠይቅ ይገባናል፡፡

በዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ውስጥ ጌታ ስለ ምን እንደምንጸልይና


መጀመሪያም እንዴት እንደምንጸልይ አስተምሮናል፡፡ እርሱ እንዲህ ብሎዋል፡-
‹‹እንግዲህ እናንተስ እንዲህ ጸልዩ፡፡ በሰማያት የምትኖር አባታችን ሆይ ስምህ
ይቀደስ፡፡›› (ማቴዎስ 6፡9) ጌታ በመጀመሪያ ይህንን ክፍል እንድንጸልይ
ነግሮናል፡- ‹‹በሰማያት የምትኖር አባታችን ሆይ ስምህ ይቀደስ፡፡›› በመጀመሪያ
የእግዚአብሄር አብ ስም እንዲቀደስ መጸለይ አለብን፡፡
ያንን ለማድረግ ምን ዓይነት እምነት ሊኖረን ያስፈልገናል? በእርግጥም

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ጌታ ስለ ጸሎት ያስተማረው ትምህርት (2) 147

የሐጢያት ስርየትን በሚሰጠን የደህንነት ወንጌል የሚያምን እምነት ሊኖረን


ይገባናል፡፡ እንደዚያ ዓይነት እምነት ይኖረን ዘንድ ጌታ ለኒቆዲሞስ የነገረውን
የውሃና የመንፈስ ወንጌል መረዳትና ማመን አለብን፡፡ (ዮሐንስ 3፡1-17)
ስለዚህ በሰማይ ያለውን የእግዚአብሄር አብን ስም ለመቀደስ በመጀመሪያ
በእግዚአብሄር ፊት የሐጢያት ስርየትን ያገኘን ሰዎች መሆን ይገባናል፡፡ ይህ
ማለት እኛ እግዚአብሄር አብና ኢየሱስ ክርስቶስ እናንተንና እኔን የፈጠሩ አምላክ
መሆናቸውን፣ እርሱም እናንተንና እኔን ከሐጢያቶቻችን ለማዳን ከአጥማቂው
ዮሐንስ መጠመቁን፣ የተሰቀለ አዳኝ መሆኑንም የምናምን ሰዎች መሆን አለብን
ማለት ነው፡፡ የኢየሱስ ክርስቶስን አባት አባታችን ብሎ መጥራት የሚችለው
እምነት በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምን እምነት ነው፡፡ እግዚአብሄርን
‹‹በሰማይ ያለህ አባታችን›› ብለን የምንጠራበት ብቸኛው ሕጋዊ መንገድ ይህ
ነው፡፡ እግዚአብሄር የእናንተና የእኔ አዳኝና አባት በመሆኑ ወደ እግዚአብሄር
የምንጸልይበትን ብቃት መቀበል የሚያስችለን ብቸኛው እምነት ይህ ነው፡፡
የሐጢያቶችን ስርየት ያገኙ ሰዎች ይህ እምነት ስላላቸው ‹‹በሰማያት የምትኖር
አባታችን ሆይ ስምህ ይቀደስ›› ብለው መጸለይ ይችላሉ፡፡ ስለዚህ ጌታ ለዚህ
እምነት እጅግ ተስማሚው ጸሎት ምን እንደሆነ አስተማረን፡፡
‹‹ስምህ ይቀደስ›› ማለት የእርሱን ስም ማርከስ የለብንም ማለት ነው፡፡
እንደዚያ ከሆነ የአብን ስም የሚያረክሰው ምንድነው? እዚህ ላይ ‹‹ስምህ ይቀደስ››
ማለት እግዚአብሄርን ለማክበርና የእግዚአብሄርንም ስም የማያረክስ ሕይወት
ለመኖር ምን ዓይነት እምነት ሊኖረን ይገባል ማለት ነው፡፡ ይህ ማለት ያንን
ለማድረግ እግዚአብሄር በሰጠን የሐጢያቶች ሁሉ ደህንነት ማመን አለብን ማለት
ነው፡፡ ‹‹ጌታ የደህንነትን ጽድቅ በመስጠትና በእግዚአብሄር ጽድቅ እንድናምን
በማድረግ ከዓለም ሐጢያቶች ሁሉ አድኖናል፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌልም
ሐጢት አልባ አድርጎናል፤ ስለዚህ የእግዚአብሄር ሕዝብ ነን፡፡›› በምንጸልይበት
ጊዜ በዚህ እምነት በእግዚአብሄር አብ ፊት መቅረብ አለብን፡፡
ሁላችንም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምን እምነት ሊኖረን
ይገባል፡፡ ጌታ በተናገረው የውሃና የመንፈስ ወንጌል ላይ ያለንን ብርቱ እምነት
በጽናት መጠበቅ አለብን፡፡ ስለዚህ ጌታ የሐጢያት ስርየትን እንድንቀበል
የሚያስችለን የተቀደሰ እምነት ይኖረን ዘንድ መጸለይ እንደሚገባን ተናግሮዋል፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


148 ጌታ ስለ ጸሎት ያስተማረው ትምህርት (2)

የእግዚአብሄር መንግሥት ፈጥኖ በምድር ላይ እንዲመሰረት በዓለም


ላይ የሚኖር እያንዳንዱ ሰው የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
እንደሚቀበል ማመን አለብን፡፡

ሁለተኛ እርሱ እንዲህ ብሎዋል፡- ‹‹መንግሥትህ ትምጣ፤ ፈቃድህ በሰማይ


እንደሆነች እንዲሁ በምድር ትሁን፡፡›› ይህ ማለት የእግዚአብሄር መንግሥት
ትመጣ ዘንድ ሰዎች ሁሉ የእግዚአብሄር ሕዝብ መሆን አለባቸው ማለት ነው፡፡
በእርግጥም ከፍጥረት በፊት እንኳን እግዚአብሄር በክርስቶስ በኩል በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል የእግዚአብሄር ሕዝብ እንድንሆን አቅዶዋል፡፡ ሰውንም በዚያ
ችሮታ በመፍጠር ሐጢያተኞች የሆነውን ከሐጢያቶቻችን ሁሉ አድኖናል፡፡
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ለምናምነውም ፍጹም የሆነውን ደህንነቱን
ሰጥቶናል፡፡ ስለዚህ እኛ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በማመን የእግዚአብሄር
ሕዝብ የሆንን ሰዎች የእግዚአብሄር መንግሥት ፈጥና ትመጣ ዘንድ የሚጸልይና
ጠንክሮ የሚሰራ ሕይወትን ልንኖር ይገባናል፡፡
የሐጢያት ስርየትን የሚቀበሉ ሰዎች ቁጥር እንዲጨምር ይህንን ማድረግ
አለብን፡፡ ጌታ በቅርብ እንደሚመጣና እርሱ ለሰጠው ታላቁ ተልዕኮ ታማኝ
ለሆንነውም ባርኮቶችንና ሽልማቶችን እንደሚሰጠን እርግጠኞች ነን፡፡
እግዚአብሄር አስቀድሞ በኢየሱስ ክርስቶስ የወሰናቸውን ዕቅዶች ሁሉ ይፈጽም
ዘንድ የእግዚአብሄር መንግሥት ፈጥና እንድትመሰረት መጸለይ ይገባናል፡፡
በእምነት መኖር አለብን፡፡ ሰዎችም የሐጢያቶቻቸውን ስርየት እንዲቀበሉና
የእግዚአብሄርም መንግሥት እንድትስፋፋ ልንጸልይ ይገባናል፡፡ የማያምኑ ሰዎች
እንዲያምኑና እግዚአብሄርንም ለማክበር ወደ እርሱ እንዲመለሱ ይህንን የውሃና
የመንፈስ ወንጌል በዓለም ላይ በሚገኝ በእያንዳንዱ አገር ለማሰራጨት ጠንክረን
መስራት አለብን፡፡ የማያምኑ ሰዎች የእርሱን ፍጹም የሆነ ደህንነት ያገኙ ዘንድ
ፈጽመው ንስሐ እንዲገቡ ልናደርጋቸው ይገባናል፡፡ ‹‹መንግሥትህ ትምጣ፤
ፈቃድህ በሰማይ እንደሆነች እንዲሁ በምድር ትሁን›› የሚለው ምንባብ ፍቺው
ይህ ነው፡፡
ሰለዚህ በጌታ ጸሎት መሰረት መጸለይና ጠንክረን መስራት ይገባናል፡፡
የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ፈጥኖ እንዲሰራጭ በርን እንዲከፍት መጸለይ
ይገባናል፡፡ ለዚህ ሚሽንም ልንጸልይ ይገባናል፡፡ ‹‹ሥራውን እንሰራ ዘንድ እባክህ
በሰላም ጠብቀን፤ ባርከንም፡፡›› በእርግጥም የሐጢያቶች ስርየት በልባችን ውስጥ
እንደተፈጸመ ሁሉ የውሃውና የመንፈሱም ወንጌል ወንጌልን ባልሰሙት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ጌታ ስለ ጸሎት ያስተማረው ትምህርት (2) 149

በብዙዎቹ ልብ ውስጥ ይፈጸም ዘንድ የጸሎት ሕይወትን መኖር አለብን፡፡


ስንጸልይ ሳለንም ውብ የሆነውን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በመላው ዓለም
ማሰራጨትና እግዚአብሄርንም በእውነተኛ እምነት እናከብር ዘንድ እግዚአብሄር
እምነትን በእግዚአብሄር ላሉ ወንድሞችና እህቶች ሁሉ እንዲሰጣቸው ሆነን
መኖር አለብን፡፡

ለዕለት ምግባችን መጸለይ ይገባናል፡፡

ሦስተኛ ጌታ ለዕለት ምግባችን እንድንጸልይ ነግሮናል፡፡ ‹‹የዕለት


እንጀራችንን ዛሬ ስጠን፡፡›› በሕይወት ልንኖር የምንችለው መንፈሳዊ ምግባችንን
ስንመገብ ብቻ ነው፡፡ ስለዚህ እግዚአብሄር ስለ መንፈሳዊ ምግብ እንድንጸልይ
ነገረን፡፡ በየቀኑ የዕለት እንጀራችንን መጠየቅ እንደሚገባን ነግሮናል፡፡ ለዕለት
ምግባችን መጸለይ አለብን፡፡ ‹‹አቤቱ መንፈሳዊ ምግብን ተመግበን በሕይወት
እንድንኖር እርዳን፡፡››
እግዚአብሄር ለዕለት እንጀራችን እንድንጸልይ ነግሮናል፡፡ ስለዚህ እንዲህ
ብለን ልንጸልይ ይገባናል፡- ‹‹እግዚአብሄር አባት ለሥጋና ለመንፈስ የሚሆን
አንዳች ነገር እንዳናጣ ከሌሎች ከመበደር ይልቅም ያለንን ከሌሎች ጋር ለመካፈል
ይባርከን ዘንድ እባክህ በዓለማዊ ብልጥግና ሙላን፡፡ መንፈሳዊ ምግብን
ለመመገብ፣ በእያንዳንዱ ጉባኤ ላይ ለመገኘትና ከሌሎች ዳግመኛ የተወለዱ
ሰዎች ጋር ሕብረትን ለመጋራት የሚሞክር የእምነት ሰው ልሁን፡፡››
ውድ ክርስቲያኖች መንፈሳዊ ምግብ ሳንመገብ አንድ ቀን በሕይወት
መቆየት እንችላለን? ጌታችን እንዲህ ብሎዋል፡- ‹‹እናንተ የማታውቁት የምበላው
መብል ለእኔ አለኝ፡፡›› (ዮሐንስ 4፡32) እኛ ዳግመኛ የተወለድን ሰዎች
የምንበላው መብል የእግዚአብሄርን ሥራ መስራት ነው፡፡ የእግዚአብሄርን ሥራ
ስንሰራ በልባችን ውስጥ መብል ይሆናል፡፡ በልባችን ውስጥ ያለው መንፈስ
ቅዱስም ይደሰታል፡፡ የሐጢያትን ስርየት ብትቀበሉም ስትናደዱ የእግዚአብሄርን
ሥራ ለመስራት ሞክሩ፡፡ እግዚአብሄርን ስታገለግሉ ሥጋችሁ ይደክም ይሆናል፡፡
በውስጣችሁ ያለው መንፈስ ቅዱስ ግን ይደሰታል፡፡ መንፈስ ቅዱስ ስለተደሰተ
ልባችን ይደሰታል፡፡ መንፈሳዊ መብል ይህ ነው፡፡
ከወንድሞቻችንና ከእህቶቻችን ጋር ተገናኝተን ሕብረት ስናደርግም
መንፈሳዊ መብላችንን መብላት እንችላለን፡፡ ምክንያቱም ሕብረት ስናደርግ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


150 ጌታ ስለ ጸሎት ያስተማረው ትምህርት (2)

የመንፈስ ቅዱስ አሳብና ፈቃድ በወንድሞቻችንና በእህቶቻችን አማካይነት እርስ


በርሳችን ያስተሳስረናል፡፡ ነገር ግን ይህ ማለት ኑሮዋችንን ከዓለም መነጠል
አለብን ማለት ማለት አይደለም፡፡ ይህ ማለት በዚህ ዓለም ላይ እንኖራለን፤ ነገር
ግን በተቻለ መጠን አዘውትረን ሌሎች ጻድቃን ሰዎችን መገናኘት አለብን ማለት
ነው፡፡
የዕለት መብላችንን ለመብላት መጸለይና መፅሐፍ ቅዱስን ማንበብም ደግሞ
አለብን፡፡ በየቀኑ መንፈሳዊ ምግብን በመመገብ ሁልጊዜም በጎ ነገር የሚያደርግ
ማነው? እኛ ግን ወደ ቤተክርስቲያን በመምጣት መንፈሳዊ መብልን ልንበላና
መንፈሳዊ ጉልበታችንን ልንጠብቅ እንችላለን፡፡ እያንዳንዱን የእግዚአብሄር
ቤተክርስቲያን የአምልኮ አገልግሎትና ጉባኤ መካፈል የሚገባን ለዚህ ነው፡፡
አብሮ መሰብሰብ ጥሩ ነው፡፡ ደግሞም መንፈሳዊ መብል መብላት ትልቅ በረከት
ነው፡፡ ይህም መንፈሳዊ ሥራን መስራት ነው፡፡ መዝሙረ ዳዊት 133፡1 እንዲህ
ይላል፡- ‹‹ወንድሞች በሕብረት ቢቀመጡ እነሆ መልካም ነው፤ እነሆም ያማረ
ነው፡፡›› በቤተክርስቲያን ውስጥ የሚደረጉ ስብሰባዎችና አገልግሎቶች በሙሉ
ምንም ፋይዳ የሌላቸው በዘፈቀደ የታቀዱ ሳይሆኑ ብቻችንን ልንመገበው
የሚያዳግተንን የዕለት መብል አብረን እንበላ ዘንድ በብልሃት የተቀናበሩ ናቸው፡፡
ስለዚህ ወደዚህ ጉባኤ በመምጣት ብዙ መብል መብላት እንችላለን፡፡
ውድ ክርስቲያኖች እርሱ ስለ መብል ዕጥረት ከማጉረምረም ይልቅ ለዕለት
ምግባችን ወደ እግዚአብሄር እንድንጸልይ ስለተናገረ ‹‹አቤቱ የዕለት ምግብ
ስጠኝ፤ በዓለማዊ ቁሳዊ ነገሮች እንዳልጎድል ብዙ ቁሳዊ ነገሮችን የማገኝባቸውን
በረከቶች ስጠኝ፡፡ መንፈሳዊ ምግብና እምነት ስጠኝ፡፡ የእግዚአብሄርን ሥራ
በእምነት መስራት እንድችልም ባርከኝ፡፡ የሥጋና የመንፈስ በረከቶችንም ስጠኝ››
ብለን ስንጸልይ መብልን ልናገኝ የምንችለው እርዳታን ስንጠይቅ በቻ ነው፡፡
የሥጋና የመንፈስ ምግብን እናገኝ ዘንድ መጠየቅ አለብን፡፡ የእግዚአብሄርን
ሥራ መስራትና በእርሱም መደሰት አለብን፡፡ መጸለይ፣ መሻት፣ ማንኳኳትና
እነዚህን መጠየቅ ይገባናል፡፡ በትጋት መጠየቅ አለብን፡፡ ምክንያቱም ‹‹ለምኑ
ይሰጣችኋል፤ ፈልጉ ታገኙማላቸሁ፤ አንኳኩ ይከፈትላችሁማል›› (ማቴዎስ 7፡7)
በማለት ቃል ገብቶልናልና፡፡ ከልባችን እንጠይቃለን፡፤ በአንደበታችን
እናጸድቃለን፡፡ ለመሻት፣ ለመጠየቅና ለመቀበልም እንጥራለን፡፡ ወደ ላይ
ብንመለከት፣ ብንጸልይና እግዚአብሄር እንዴትና በምን በኩል እንደሚሰጠን
ብንሻ እንቀበላለን፡፡ በየቀኑ የምንኖረው እንደዚህ ነው፡፡ ስለዚህ እግዚአብሄር
እነዚህን ነገሮች ለማግኘት እንድንጸልይ ነገረን፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ጌታ ስለ ጸሎት ያስተማረው ትምህርት (2) 151

የእግዚአብሄር አብ ልጆች በመሆናችን እርስ በርሳችን


ይቅር መባባል አለብን፡፡

የጸሎቱ አራተኛው ክፍል፡- ‹‹እኛም ደግሞ የበደሉንን ይቅር እንደምንል


በደላችንን ይቅር በለን፤ ከክፉም አድነን እንጂ ወደ ፈተና አታግባን›› የሚለው
ነው፡፡ ይህ ማለት እግዚአብሄር ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ይቅር ስላለን እኛ
ዳግመኛ የተወለድን ሰዎችም እርስ በርስ ይቅር እንዳንባባል ምንም ነገር ማድረግ
የለብንም ማለት ነው፡፡ በልባችን ውስጥ ሌሎችን ይቅር የማይል አንዳች ክፉ
ሥጋዊ አሳብ ካለ ‹‹አምላኬ በሰላም ጠብቀኝ፤ በክፉ ላይ እንዳልወድቅም
ከክፉው አድነኝ፡፡ ይቅር የሚል ልብና እምነትም ስጠኝ›› ብላችሁ ልትጸልዩ
ይገባችኋል፡፡ ይህ ማለት የእግዚአብሄርን ፈቃድ ለመከተል ጉልበት በማይኖረን
ጊዜ እግዚአብሄር እንዲረዳን መጠየቅና ከእግዚአብሄር በምናገኘው እርዳታ
መኖር ይገባናል ማለት ነው፡፡
በተጨማሪም የእምነት ሕይወቱ ከመጀመሪያ ጀምሮ ፍጹም የሆነ ሰው
የለም፡፡ ራሳችሁን ስትመለከቱ የራሳችሁን ብዙ ጉድለቶች ታያላችሁን? --አዎ--፡፡
ከጽድቅ ምግባሮች ይልቅ ብዙ የተሳሳቱ ምግባሮች አሉን? --አዎ--፡፡ ውድ
ክርስቲያኖች ተስፋ አትቁረጡ፡፡ ስህተቶችን የምንሰራ ከሆንን ጉድለቶች ካሉብንና
ከተጸጸትን ነገር ግን ይህንን ለማስተካከል ጉልበት ከሌለን ምን እናደርጋለን?
እንደገና እግዚአብሄርን እንጠራዋለን፡፡
‹‹እግዚአብሄር አባት የሚባርክ ሰው፣ የእምነት ሰው፣ የደስታ ሰው
አድርገኝ፤ እምነትን ስጠኝ፡፡›› እግዚአብሄር ይረዳን ዘንድ እንዲህ መጠየቅ
አይገባንምን? ይህ እውነት አይደለምን? ማድረግ ያለብን ይህንን ነው፡፡
እግዚአብሄር እንዲረዳን ስንጠይቀው ይረዳናል ወይስ አይረዳንም? --ይረዳናል--
፡፡ ሲረዳን የእምነት ሰዎች እንሆናለን ወይስ አንሆንም? --እንሆናለን--፡፡ ስለዚህ
እናንተ ያለፈውን በተስፋ መቁረጥ መለስ ብሎ የሚመለከት፣ በአሁኑ የሚጸጸትና
በወደፊቱ ተስፋ የሚቆርጥ ሕዝብ ከመሆን ፋንታ በእምነት የሚኖር የእምነት
ሕዝብ እንደምትሆኑ ተስፋ አለኝ፡፡ ያለፈው አልፎዋል፤ አሁን ያለው አለ፡፤
መዝሙሩ ‹‹ስለ ወደፊቱ አትጠይቅ›› እንደሚል ያለፈው ያን ያህል አስፈላጊ
አይደለም፡፡
እግዚአብሄር ብርቱ ነው፡፡ ስለዚህ ብዙ የሚጠይቁትን ሰዎች ይወዳል፡፡
እግዚአብሄርን ስለምንፈልገው ነገር ስንጠይቀው ይደሰታል፡፡ ‹‹እኔ ብርቱ
እንደሆንሁ ታውቃላችሁ፡፡ አባታችሁ ባለጠጋ እንደሆነ ታውቃላችሁ፡፡ ይህ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


152 ጌታ ስለ ጸሎት ያስተማረው ትምህርት (2)

የሚያስመሰግን ነው›› ብሎ ያስባል፡፡ ‹‹ራሴ አደርገዋለሁ›› ማለት የእግዚአብሄርን


ክብር ስለሚያሳንሰው ከዚህ ይልቅ በጎ ነገሮችን ልንጠይቅ ይገባናል፡፡ እኛን
ያዳነን እግዚአብሄር ነገሮችን እንዲሰጠን ስንጠይቀው በእኛ ይደሰታል፡፡
እንዲሰጣችሁ ጠይቁት፡፡ በየቀኑ ‹‹የዕለት ምግባችንን ስጠን›› እያልን ልንጠይቀው
ይገባናል፡፡ አንደበታችንን በምንከፍትበት ጊዜ ሁሉም በረከትን እንዲሰጠን
ልንጠይቀው ይገባናል፡፡ ሥጋዊ አባታችን ቢሆን ኖሮ በየቀኑ ስለምንጠይቀው
በጥፊ ያጠናግረናል፡፡ መንፈሳዊ አባታችን ግን እንደዚያ አይደለም፡፡ ይልቁንም
እርሱ በየቀኑ ለውሃውና ለመንፈሱ ወንጌል ሥራ የሚያስፈልገንን እንዲሰጠን
ስንጠይቀው ይደሰታል፡፡
የሥጋ አባታችሁ ትናትና ሰጥቶዋችሁ ከሆነና ዛሬም ያንኑ ነገር
እንዲሰጣችሁ የምትጠይቁት ከሆነ በእርግጥም ይቆጣል፡፡ ስለዚህ ሥጋዊው ልጅ
ስለሚፈራ ሊጠይቅ አይችልም፡፡ የአባታችንንና የእናታችንን ስሜት መርምረን
‹‹ኦ! ዛሬ እንዲሰጠኝ ብጠይቅ ጥፊ ይከተለኛል›› ብለን እናስባለን፡፡ ወደ አባታችን
የምንሄደው ጥሩ ስሜት ላይ ሲሆን ብቻ ነው፡፡ ያን ጊዜ ማንኛውንም ነገር
ከእርሱ እንቀበላለን፡፡ ነገር ግን መንፈሳዊ አባታችን እንደዚያ አይደለም፡፡
ዓይኖቻችንን እንደገለጥን ወዲያውኑ ‹‹ስጠኝ፡፡›› በእንቅልፍ ላይ ሆነንም ‹‹ስጠኝ››
ብለን ብንጠይቅ እግዚአብሄር ተደስቶ ‹‹አዎ እሰጥሃለሁ፤ እሰጥሃለሁ፤ ነገር ግን
በዘፈቀደ ልትጠቀምበት አትችልም፡፡ በትክክል ተጠቀምበት እሺ?›› በማለት
በአንድ ጊዜ ይሰጠናል፡፡ ይህ ተጨባጭ ነው፡፡
እናንተንና እኔን ያዳነን እግዚአብሄር አብ ብዙ የሚጠይቁትን አብዝቶ
ይወዳል፡፡ እምነት ከሌላችሁ ‹‹እምነትን ስጠኝ፤ ስጠኝ፤ ስጠኝ›› ብላችሁ
ጠይቁት፡፡ ያን ጊዜ እግዚአብሄር እምነትን እንደሰጣችሁ ወዲያውኑ
ታውቃላችሁ፡፡ ‹‹ኦ! እምነት አለኝ፤ ማመን እችላለሁ፤ እምነቴን ተጠቅሜያለሁ፤
እምነት አለኝ!›› የሚል ስሜት ሊሰማችሁ ይችላል፡፡ በራሳችሁ እሳቤ ታስራችሁ
እግዚአብሄርን ከመጠየቅ አታመንቱ፡፡ ለእግዚአብሄር በአደራ እንደሰጣችሁት
ያህል ማንኛውንም ነገር በድፍረት ጠይቁት፡፡ ጌታ ይህንን ይወዳል፡፡
ውድ ክርስቲያኖች ከዚህ በፊት በዚያ ያልነበረ እምነት እንዴት ወደ መኖር
እንደሚመጣ ታውቃላችሁን? የሚመጣው ‹‹እምነትን ስጠኝ፤ ስጠኝ፤ ስጠኝ››
ብላችሁ ስትጠይቁ ነው፡፡ ስለዚህ እግዚአብሄር ሰጣችሁ፡፡ እምነትን የተቀበልነው
እግዚአብሄር ስለሰጠን ነው፡፡ እምነትን ለማግኘት ሌላ መንገድ የለም፡፡ ይህ
የሆነው እግዚአብሄር ስላዳነንና ለእናንተና ለእኔ አባት ስለሆነ ነው፡፡ ‹‹ጌታ ሆይ
ስጠን፤ ስጠን›› ብለን ከመጠየቅ የበለጠ ያደረግነው ምንም ነገር የለም፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ጌታ ስለ ጸሎት ያስተማረው ትምህርት (2) 153

ትንንሽ ልጆችን ስለ ጸሎት ስናስተምራቸው ልጆቹ ‹‹ኢየሱስ ሆይ ኪኪሶችን


ስጠኝ፤ በኢየሱስ ስም ጸለይሁ አሜን›› ብለው ይጸልያሉ፡፡ ከዚያም
ዓይኖቻቸውን ይገልጣሉ፡፡ ዓይኖቻቸውን ሲገልጡ ኩኪሶቹ ከሌሉ ‹‹ኩኪሶች
የሉም›› ብለው ማልቀስ ይጀምራሉ፡፡ እንዲህ ሲሆን ‹‹እናንተ ረባሾች እርሱ
አምላክ ቢሆንም ከጸለያችሁ በኋላ ወዲያውኑ ዓይኖቻችሁን ገልጣችሁ ሳለ
እንዴት ኩኪሶችን ሊያቀርብ ይችላል? አሁን እግዚአብሄር እያደመጠ ነው፡፡
‹ጥሩ› ነው ብሎዋል፡፡ በልቡ ይህንን እሰጠዋለሁ ብሎ እያሰበ ነው፡፡
መላዕክቶችም ኩኪሶቹን እንዲያመጡ ያዛቸዋል›› በማለት አብራራለሁ፡፡
በምንጸልይበት ጊዜ እግዚአብሄር ወዲያውኑ ባይሰጠንም በትክክለኛው
ቦታ ለትክክለኛው ሰው እንደሚሰጥ እናውቃለን፡፡ እርሱ እንደሚሰጥ መመስከር
እንችላለን፡፡ ብዙ እንዲሰጠን ሁልጊዜም መጸለይ የሚገባን ለዚህ ነው፡፡
ብዙ ፍላጎቶች የሉዋችሁምን? የሚያስፈልገን ማንኛውም ነገር ቢኖረን
ለሥጋ ወይም ለመንፈስ የሚሆን ነገር ከጎደለን እነዚያን ለማግኘት መጸለይ
ይገባናል፡፡ ‹‹እምነትን ስጠን፡፡ በረከቶችን ስጠን፡፡ የመንፈስ ቅዱስ ሙላትን
ስጠን፡፡ የመንፈስ ቅዱስ ሙላት እንዳለ ሰምቻለሁ፡፡ ያንን ስጠን፡፡ ለጽድቅ
እንድንኖር እርዳን፤ ስጠን፡፡›› እንዲህ ብለን የምንጸልይ ከሆነ አንድ ያልበሰለ ልጅ
የሚጸልየው ጸሎት ቢሆንም እንኳን አባት ልጅ ምን እንደሚያስፈልገው
ስለሚያውቅ ልጁ የሚያስፈልገውን በትክክለኛው ቦታ በትክክለኛው ሰው
ይሰጠዋል፡፡
ጸሎት አስቸጋሪ ያልሆነው ለዚህ ነው፡፡ ‹‹ስጠኝ›› ማለት ብቻ ጸሎት ነው፡፡
እንደዚህ ታስባላችሁን? ‹‹እኔ አድጌያለሁ፤ አንድን ነገር ደጋግሜ እንዳልናገር
ተናግሮዋል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስም ወደ እልፍኜ ገብቼ መጸለይ እንደሚገባኝ
ይናገራል፡፡ ነገር ግን ወደ እልፍኜ ከገባሁ እንቅልፋም እሆናለሁ እንጂ መጸለይ
አልችልም፡፡›› ሁልጊዜም በልባችን ‹‹ስጠን፤ ስጠን›› እያልን መጸለይና ዕርዳታን
መጠየቅ ጸሎት ነው፡፡
መጸለይ ከጀመርሁበት ጊዜ ጀምሮ እግዚአብሄር ባማሩ ሐረጎች ያሸበረቁ
ጸሎቶችን እንደማይወድ ተረድቻለሁ፡፡ ‹‹ቅዱሱ፣ ለጋሱ፣ ባለጠጋውና ሁሉን ቻይ
የሆንህ እግዚአብሄር አብ…›› የሚል ጋጋታ ስንፈጥር እግዚአብሄር ‹‹ዋናው ዓላማ
ምንድነው?›› በማለት ይቁነጠነጣል፡፡ ምንም ያህል የተዋጣለት የንግግር ጥበብ
ብንናጋጋ ዓላማውን ካልነገርነው ነገሩ ከንቱ ነው፡፡ የምንፈልገውን ነገር ለማግኘት
ስንሟሟት ዋናው ጉዳይ ወዲያውኑ ብቅ ይላል፡፡ ‹‹ይህንን ስጠኝ›› ብለን
ስንጠይቅ አንዲት አጭር አረፍተ ነገር ትሻላለች፡፡ ጸሎታችን ጥሩ መስሎ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


154 ጌታ ስለ ጸሎት ያስተማረው ትምህርት (2)

እንዲታይ አላስፈላጊ በሆነ መንገድ ስናስረዝመው ስለምን እንደምንጸልይ


እንረሳለን፡፡ ‹‹ስለምን እየጸለይሁ ነበር? ኦ! ያናድዳል፡፡ አላውቅም፡፡›› ያን ጊዜ
እንግዳ ስለሆነ ነገር እንጸልያለን፡፡ መጨረሻችንም ለአንድ ሌላ ሰው መጸለይ
ይሆናል፡፡ ለራሳችን የሚያስፈልጉንን ጸሎቶች አንጸልይም፡፡ አንዳንድ ጊዜ ያንን
አታደርጉምን?
ለመጀመሪያ ጊዜ የሚሽን ትምህርት ቤት ስንከፍት ትምህርት ከጨረስን
በኋላ ክብ ሆነን ተቀምጠን መጸለይ እናዘወትር ነበር፡፡ አንዳንድ ጊዜ በጋራ
እንጸልያለን፡፡ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ በየተራ እንጸለያለን፡፡ ብዙውን ጊዜ ከሁለት
ሰዓት በላይ ረጅም ጸሎት ስለምንጸልይ ጀርባችን ተጎድቷል፡፡ ሆኖም በትጋት
ጸለይን፡፡ መሪውም የጸሎት ርዕሶችን መስጠቱን ቀጠለ፡፡ ሁላችንም በጸሎት
ተጠመድን፡፡ አንዳንድ ወንድሞችና እህቶችም እንዲህ ባለው ረጅም የጸሎት
ጉባኤ የተነሳ ጀርባዎቻቸው በመታመማቸው አጉረመረሙ፡፡
በአንድ ወቅት አንድ የቤተክርስቲያን መሪ በማለዳ የአምልኮ አገልግሎት
ጊዜ ከዘፍጥረት እስከ ራዕይ ድረስ የተወጣጡ ምንባቦችን በመጠቀም ለሦስት
ሰዓታት ያህል የጸለየበት ታሪክ ተነግሮኛል፡፡ ጸሎቱ ፈጽሞ ማብቂያ ስላልነበረው
በቤተክርስቲያን ውስጥ ያለው ሰው ሁሉ ወደ ቤቱ ሄዶ ቁርሱን በልቶ ሲመለስ
እንኳን እርሱ ገናም እየጸለየ ነበር፡፡ በጥቅሉ እንደዚህ ዓይነት ሰዎች በቤታቸው
ወይም በሌላ በማንኛውም ስፍራ ብዙ አይጸልዩም፡፡ በአገልግሎቶች ወቅት
ለረጅም ጊዜ የሚጸልዩት የመጸለይ ጉድለታቸውን ለማካካስ ነው፡፡ ነገር ግን እኛ
መጸለይ የሚገባን እንደዚያ አይደለም፡፡ አጭር ጸሎት ጥሩ ጸሎት ነው፡፡ የላስቲክ
ጎማን እንደምንለጥጥ ጸሎትን የምንለጥጥ ከሆነ በትክክል ስለምን እንደምንጸልይ
እንረሳለን፡፡
አንዳንድ ጊዜ ጥቂት በሆኑ የጸሎት ርዕሰ ጉዳዮች ላይ በሕብረት
እንጸልያለን፡፡ እውነቱን ለመናገር የጸሎት መሪው በአንድ ጊዜ ብዙ የጸሎት
ርዕሶችን የሚናገር ከሆነ አንዳንድ ጊዜ ቀደም ያሉትን የጸሎት ርዕሶች ማስታወስ
አልችልም፡፡ የማስታውሳቸው የኋለኞቹን ርዕሶች ብቻ ነው፡፡ ይህ በሚሆንበት
ጊዜ በመጀመሪያ ላይ ኋላ ላይ በቀረቡት የጸሎት ርዕሶች እጀምራለሁ፡፡
‹‹እግዚአብሄር ሆይ ይህንን ስጠኝ፤ ያንን ስጠኝ፡፡›› እንዲህ በማለት ስጸልይ
አንዳንድ ጊዜ ቀደም ያሉትን የጸሎት ርዕሰችም አስታውሳለሁ፡፡
‹‹እግዚአብሄር አባት ሆይ የዕለት እንጀራችንን ስጠን፡፡ ዛሬ የሚያስፈልገንን
ዓለማዊ ቁሳዊ ነገሮች ስጠን፡፡ ጤናን ስጠን፡፡ የእግዚአብሄርን ሥራ እንድንሰራ
ጉልበት ስጠን፡፡ በረከቶችን ስጠን፡፡ ጽድቅን በእምነት እንድናከናውን እርዳን፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ጌታ ስለ ጸሎት ያስተማረው ትምህርት (2) 155

ሕይወታችንን በከንቱ እንዳናባክን እርዳን፡፡›› ዋናውን ርዕሰ ጉዳይ በማስቀመጥ


በዚህ መንገድ እንጸልያለን፡፡
በእምነት መጸለይ አዳጋች አይደለም፡፡ ከዳንን እግዚአብሄር አባታችን
ነው፡፡ አባትን ‹‹አባት›› ብሎ በመጥራት ማፈር እንግዳ ነገር ነው፡፡ ‹‹ኢየሱስ አባት
ነውን? የኢየሱስ አባት አባት ነውን? መንፈስ ቅዱስ አምላክ ከሆነ እንግዲያውስ
መንፈስ ቅዱስ አባት አይደለምን?›› ነገሩን እንዲህ ካሰባችሁት ራሳችሁን
ያሳምማችኋል፡፡ ውድ ክርስቲያኖች ሥላሴ አምላክ አዳኛችንና አባታችን ነው፡፡
ለ20 ዓመታት በኢየሱስ ካመኑ በኋላ አሁንም ድረስ ይህንን መረዳት
አይችሉም፡፡ ስለዚህ አሁንም ድረስ እግዚአብሄር አባት ስለ መሆኑ ወይም
ኢየሱስ አባት ስለ መሆኑ ወይም መንፈስ ቅዱስ አባት ስለ መሆኑ ግራ
ተጋብተዋል፡፡ ሁሉም ተመሳሳይ ነገር ማለት ናቸው፡፡
የሆዋ አምላክ ማለት ‹‹የሚኖር አምላክ›› ማለት ነው፡፡ እግዚአብሄር ፍጡር
አይደለም፡፡ ኢየሱስ አዳኛችን ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስም እግዚአብሄር መንፈስ
ቅዱስ ነው፡፡ ስለዚህ ሁሉም በመለኮትነታቸው አንድ አምላክ ናቸው፡፡ ነገሩን
ማወሳሰብ አያስፈልግም፡፡ ‹‹እግዚአብሄር እንዲህ ስለተናገረ ስለዚህ ትክክል ነው››
ብላችሁ እመኑ፡፡ በእርግጥ ዳግመኛ ተወልደንና የሐጢያት ስርየትን ተቀብለን
ከሆነ ሁሉ ነገር ተፈቅዶልናል፡፡ ይህንን በማወቃችሁ ሁላችሁም ለዕለት
ምግባችሁ የምትጸልዩ የእግዚአብሄር ቅዱሳኖችና ወንድና ሴት የእግዚአብሄር
ባሮች ትሆናላችሁ፡፡
እንደገና ዋናውን ርዕሰ ጉዳዮቻችንን አጥብቀን እንያዝ፡፡ ስለ እርሱ
ትምህርት እየተነጋገርን ነበር፡፡ ‹‹እኛም የበደሉንን ይቅር እንደምንል በደላችንን
ይቅር በለን፡፡›› ሌሎች የሚበድሉን በደል አለ፡፡ እኛም ሌሎችን የምንበድለው
በደል አለን፡፡ ነገር ግን እግዚአብሄር የእኛን ሐጢያቶችና የሌሎችን ሐጢያቶች
በሙሉ አስወግዶዋል ወይስ አላስወገደም? --ሁሉንም አስወግዶዋል--፡፡ እርሱ
ሁሉንም ከደመሰሰ እኛን የበደሉንን ሰዎች ከልባችን ይቅር ልንላቸው
አይገባንምን? --ይቅር ልንላቸው ይገባናል--፡፡ የጸሎታችን መሰረቱ ‹‹እኛን
የበደሉንን ይቅር እንደምንል በደላችንን ይቅር በለን›› የሚለው ነው፡፡
እግዚአብሄር ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ይቅር ብሎን ሳለ እርስ በርሳችን ይቅር
መባባል ካልቻልን የእግዚአብሄር ልጆች እንደ መሆናችን ተገቢ አይደለም፡፡
ይህንን የተናገረው ለዚህ ነው፡፡
ስለዚህ በተሳሳተ መንገድ ላይ የምንፈረጥጥ፣ ክፉ አሳብም በርትቶብን ወደ
ክፋት ገብተን ሌሎችን ለመቅጣትና ሌሎችን ለማሸነፍ የምንሞክር፣ በሰውም ላይ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


156 ጌታ ስለ ጸሎት ያስተማረው ትምህርት (2)

ቂም የምንይዝ ከሆንን ‹‹ክፉ ነገር ውስጥ እንድንወድቅ አትፍቀድልኝ፤ ወደ ፈተና


እንድገባ አትፍቀድልኝ፤ ለወንጌል ጥቅም ከመሆን ፋንታ የዕንቅፋት ድንጋይ
በሆነው ሥጋዊ ንዴት የተነሳ ችግር ውስጥ እንድወድቅ አትፍቀድልኝ፡፡
ቤተክርስቲያን፣ ሌሎች ክርስቲያኖችና እኔ ራሴ በዚያ ውስጥ እንዳልጎዳ፣ ወደ
ፈተና እንድገባና ችግር ውስጥ እንድወድቅ አትፍቀድ፡፡ ክፉ ነገር ውስጥ
ከመውደቅ ጠብቀኝ፡፡ ልቤን እንድጠብቅ እርዳኝ፡፡ ጉልበትን ስጠኝ፡፡
የእግዚአብሄርን የጽድቅ ሥራዎች መስራት የሚችል ጉልበት ስጠኝ›› በማለት
መጸለይ ይገባናል፡፡
እርሱ ይቅር እንድንል፣ እንድንወድ፣ እንድንነግስና ለሌሎች እንድንጸልይ
ነግሮናል፡፡ ‹‹አቤቱ ከሐጢያቶቹ ሁሉ ይድን ዘንድ እምነትን ስጠው፡፡ ባህሪው
ጥሩ ነው፤ ነገር ግን እባክህ አድነው›› እያልን ለሰው ሁሉ መጸለይ ይገባናል፡፡
እንዲህ ልንጸልይ ይገባናል፡፡ በዓለም ላይ ለሚኖር ለእያንዳንዱ ሰው መጸለይ
እንችላለን ወይስ አንችልም? --እንችላለን--፡፡ ውብ በሆነው የውሃውና የመንፈሱ
ወንጌል ውስጥ ሁሉንም ከልባችን ይቅር ልንልና ልንወድድ እንችላለን፡፡
ጻድቃን ክፉ ነገር ውስጥ መውደቅ እንደሌለባቸው እውነት ነው፡፡ ጽድቅ
ላይ መውደቅ ጥሩ ነው፡፡ ክፉ ነገር ውስጥ መውደቅ ግን ጥሩ ነውን? ሰክረን
ሰዎችን መረበሽና መማታት ይገባናልን? አይገባንም፡፡ እንደዚያ ካላችሁ
ለእግዚአብሄር ሥራ ተጠቀሙበት፡፡ ያንን ጉልበት ለጠብ ከምንጠቀምበት ይልቅ
የእግዚአብሄርን ሥራ በትጋት ለመስራት ልንጠቀምበት ይገባናል፡፡ እግዚአብሄር
ወደ ክፉ ነገር እንዳንወድቅ እነዚህን ነገሮች እንድንጸልይ የነገረን ለዚህ ነው፡፡
ክፉ ነገር ውስጥ መውደቅ የለብንም፡፡
በዚህ ዓለም ላይ ብዙ ቁጡ ሰዎች አሉ፡፡ ከእነዚህ ሰዎች ጋር ስንገናኝ እኛን
የሚጠቅሙን ሰዎች ካልመሰሉን ከእነዚህ ሰዎች መራቅና መሸሽ ጠቢብነት ነው፡፡
ጌታ ይህንን ቁጥር በጌታ ጸሎት መጨረሻ ላይ ለምን አካተተው? ‹‹ለሰዎች
ሐጢአታቸውን ይቅር ብትሉ የሰማዩ አባታችሁ እናንተን ደግሞ ይቅር
ይላችኋልና፡፡ ለሰዎች ግን ሐጢአታቸውን ይቅር ባትሉ አባታችሁም
ሐጢአታችሁን ይቅር አይላችሁም፡፡›› ይህ ማለት ጻድቅ ሰው በእምነት ጻድቅ
ሰው ሆኖ መኖር አለበት ማለት ነው፡፡ በእግዚአብሄር ፊት የሐጢያቶቻችንን
ስርየት ሁሉ ከተቀበልን ወንድሞቻችንንና እህቶቻንን ሁሉ እንደዚሁም ገና
ዳግመኛ ያልተወለዱትንም ሰዎች ሁሉ ይቅር ማለት ይገባናል፡፡ ይቅር ባይ ልብ
ከሌለን ‹‹እግዚአብሄር አባት ይቅር ባይ ልብ ስጠኝ›› በማለት እርዳታ መጠየቅ
ይገባናል፡፡ እግዚአብሄር እንዲህ እንኖር ዘንድ ሊያዝዘን ይህንን ትምህርት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ጌታ ስለ ጸሎት ያስተማረው ትምህርት (2) 157

መጨረሻ ላይ አካተተው፡፡
ጸሎት አዳጋች ነው ወይስ አይደለም? አዳጋች አይደለም፡፡ የጸሎት መሰረት
እምነት እግዚአብሄር አምላኬ፣ አዳኜና አባቴ ነው የሚል እምነት ነው፡፡ እርሱ
ፈጠረን፡፡ ከሐጢያቶቻችንም ሁሉ አዳነን፡፡ እንደዚያ ከሆነ እኛ ዳግመኛ
የተወለድን ሰዎች የእርሱ ሕዝብ የእርሱ ቤተሰብ ስለሆንን አባት ብለን
ብንጠራው እንግዳ ነገር አይደለም፡፡ በተጨማሪም እኛ የእርሱ ሕዝብ
በመሆናችን እርሱን ማመስገናችን ጽደቅ ነው፡፡
ወደ ክፋትና ፈተና እንዳንገባና በተሳሳተ መንገድ ላይ ቁልቁል እንዳንሮጥ
መጸለይ ይገባናል፡፡ ኢየሱስ መጀመሪያ ምን እንደምንጸልይ አስተምሮናል፡፡
‹‹አስቀድማችሁ የእግዚአብሄርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፤ ይህም ሁሉ
ይጨመርላችኋል፡፡›› የሚያስፈልጋችሁ አንዳች ነገር አለን? እንግዲያውስ
አስቀድማችሁ ለእግዚአብሄር መንግሥት ጸልዩ፤ ኑሩም፡፡ አባታችሁ ሁሉን
ይሰጣችኋል፡፡ የእግዚአብሄር ተስፋ ይህ ነው፡፡
ስለዚህ ይህንን ማመን ይገባናል፡፡ ጉድለቶች ቢኖሩብንም እንኳን
አስቀድመን በእግዚአብሄር ፈቃድ ለመኖር በመሞከርና የእግዚአብሄርን እርዳታ
በመጠየቅ አስቀድመን የእግዚአብሄርን ሥራ መሻት አለብን፡፡ ሁልጊዜም በመንፈስ
የማደግና ጉድለቶች ቢኖሩብንም እንኳን የእርሱን ጸጋና እርዳታ በመጠየቅ
ለእግዚአብሄር ሥራዎች ታማኝ መሆን ይኖርብናል፡፡ ገባችሁ? --አዎ--፡፡
ታምናላችሁን? --አዎ--፡፡
ሁላችንም አብረን ስንጸልይ በጥንቃቄ ድምጻችንን ከፍ አድርገን ልንጸልይ
ይገባናል፡፡ ያንን ስታደርጉ አሳቦቻችሁ ስለሚቀናጁ ‹‹እንደዚህ ጸለይሁ፤ እንዲህም
አምናለሁ›› በማለት እምነታችሁ ይዳብራል፡፡ እግዚአብሄር መልስ ሲሰጥም
‹‹ከእግዚአብሄር ዘንድ መልስ የመጣው እንደዚህ ስለጸለይሁ ነው›› በማለት
ስለምናውቅ እምነታችን ያድጋል፡፡ በአንደበታችን ጥርት አድርገን መጸለይ ጥሩ
የሚሆነው ለዚህ ነው፡፡
በተጨማሪም በምንጸልይበት ጊዜ ተመሳሳይ በሆኑ ነገሮች ላይ ደጋግመን
መጸለይ ይቻላል፡፡ ነገር ግን እንደ ስርዓተ ደንብ አድርገን ልንጸልይ አይገባንም፡፡
አንዳንድ የሚያስቆጡ ነገሮች ሊወጡ ይችላሉ፡፤ ያ በሚሆንበት ጊዜ በቃላት
ልናርመው ይገባል፡፡ እግዚአብሄር በልባችን ማዕከል ውስጥ ያለውን ያያል፤
ያውቃል፡፡ በዚያ ውስጥም ይሰራል፡፡ ነገር ግን በአንደበታችን በትክክል
መመስከርም እንደዚሁ አስፈላጊ ነው፡፡ ‹‹ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃልና በአፉም
መስክሮ ይድናልናል፡፡››

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


158 ጌታ ስለ ጸሎት ያስተማረው ትምህርት (2)

ጌታም እንዲህ ብሎዋል፡- ‹‹እንግዲህ ሰዎች ሊያደርጉላችሁ የምትወዱን


ሁሉ እናንተ ደግሞ እንዲሁ አድርጉላቸው፡፡ ሕግም ነቢያትም ይህ ነውና፡፡››
(ማቴዎስ 7፡12) በእርግጥ አንድን ነገር የምንፈልግ ከሆንን፣ በጽድቅ መኖር
የምንፈልግ ከሆንን፣ በሥጋና በመንፈስ የተትረፈረፈ ሕይወት መኖር የምንፈልግ
ከሆንን አዘውትረን ብዙ ነገሮችን መጠየቅ ይገባናል፡፡
እንዲህ ባለ እምነት እንኑር፡፡ እንዲህ ባለ እምነት እየኖርን ጌታ ተመልሶ
ሲመጣ እንቀበለው፡፡ እምነቴ ይህ ነው፡፡ በእግዚአብሄርም ፊት ጸሎቴ ይህ
ነው፡፡ ይህ እንደሚሆንም አምናለሁ፡፡
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በጽሁፍ አገልግሎቶች አማካይነት በመላው
ዓለም ለማሰራጨት ራሳችንን ቀድሰን ስንሰጥ ከፍተኛ የሆነ የገንዘብ መጠን
ያስፈልገናል፡፡ ለሕትመቱ የሚሆነውን መዋዕለ ንዋይ በሚመለከት እግዚአብሄር
እንደሚያዘጋጅልን አምናለሁ፡፡ እስከ አሁን ድረስ እግዚአብሄር የሚያስፈልገንን
ሁሉ አቅርቦልናል፡፡ በእርግጠኝነትም በበቂ ሁኔታ ይደግፈናል፡፡ የእርሱን
ሥራዎች በሚገባ መስራት ችለናል፡፡ በክርስቲያን ጽሁፎቻችን አማካይነትም
ዳግመኛ በተወለዱት መካከል ብዙ ቁጥር ያላቸው አጋር ሰራተኞች ተነስተዋል፡፡
ነገር ግን ዲያብሎስ ይህንን በማወቁ አገልግሎቶቻችንን ለማደናቀፍ ሞክሮዋል፡፡
ዲያብሎስ ይህንን ሥራ ሊቀለብስና ብዙ ችግሮችን በእኛ ላይ ሊፈጥር ይችል
ይሆናል ብዬ እፈራለሁ፡፡ ስለዚህ እግዚአብሄር እንዲረዳንና ጥበቃውን
እንዲያደርግልን ከመጸለይ በቀር ልናደርገው የምንችለው ነገር የለም፡፡
እኛ መጽሐፎችን ስናትም በአብዛኛው የምንሰራው ዳግመኛ ከተወለዱ
ሰዎች ጋር ነው፡፡ አንዳንድ ጊዜ ዳግመኛ ካልተወለዱ ሰዎች ጋር ከመስራት
አንሸሽም፡፡ የመጀመሪያውን የፈረንሳይኛ መጽሐፍ ዕትም በምናርምበት ጊዜ
ከፍተኛ ጥረት አድርገናል፡፡ ነገር ግን በሽፋኑ ላይ ከኦሪጅናሉ መጽሐፍ ፈጽሞ
ያፈነገጠ ስህተት አገኘን፡፡ የፈረንሳይኛ ተርጓሚው በራሱ መንገድ የተቻለውን
አድርጎ ሊሆን እንደሚችል የታወቀ ነው፡፡ ነገር ግን ጥረቱን ሁሉ መና የሚያስቀር
አደገኛ ስህተት ሰራ፡፡ ስለዚህ ከአሁን ወዲያ እንዲህ ያለውን ክስረት ለመከላከል
ወደ እግዚአብሄር መጸለይ ይገባናል፡፡
በአሁኑ ጊዜ ተከታታይ ከሆኑት የወንጌል መጽሐፎቻችን ውስጥ
የእንግሊዝኛ ትርጉሞችና የስፓኒሽ ትርጉሞች በጣም ተቀባይነት አግኝተዋል፡፡
ሌላው ቀጣዩ ተቀባይነት ያገኘው ትርጉም ፈረንሳይኛው ነው፡፡ ይህ ምን ማለት
ነው? እግዚአብሄር በአያሌው በሚሰራባቸው አካባቢዎች ዲያብሎስም
ሥራዎቻችንን ለመቀልበስ በርትቶ ይሰራል፡፡ እግዚአብሄር ከክፉዎች

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ጌታ ስለ ጸሎት ያስተማረው ትምህርት (2) 159

አንዲጠብቀን፣ ከእኛ ጋር አብረው የሚሰሩትንም እንዲቆጣጠራቸውና


እንዲነግስባቸው ሁሉም ነገር በደህና እንዲሄድ መጸለይ የሚገባን ለዚህ ነው፡፡
እግዚአብሄር ራሳቸውን ለዚህ ክቡር ሚሽን አሳልፈው የሰጡትን ወንድሞችና
እህቶች፣ ወንድና ሴት ባርያዎች በሙሉ እንዲረዳና እንዲጠብቃቸውም መጸለይ
ይገባናል፡፡ የምንጸልየው ለዚህ ነው፡፡
ለራሳችሁም ደግሞ ልትጸልዩ ይገባል፡፡ የታመነ ሕይወትን ስትኖሩ
እግዚአብሄር ይከብራል! ሌሎች በእናንተ በኩል ይድኑ ዘንድም ጻድቅ የሆነ
የእምነት ሕይወት መኖር ያስፈልጋችኋል፡፡ በሥጋችሁና በመንፈሳችሁ
የምትባረኩበት ብቸኛው መንገድ ይህ ነው፡፡ የምንጸልየውም ለዚህ ነው፡፡
የጸሎትን አስፈላጊነት ማወቅና በእምነትም እየጸለይን መኖር አለብን፡፡
ሁልጊዜም በእግዚአብሄር በሚያምን እምነት በጸሎት እየጠየቅን በሕይወት
እንኑር፡፡ ለወንጌል በምንሰራባቸው አካባቢዎች እግዚአብሄር ወንድና ሴት
አገልጋዮችንና የእግዚአብሄርን ሕዝብ ሁሉ እንዲባርክና ይህ የውሃና የመንፈስ
ወንጌል ስርጭትም በሐይል ይከናወን ዘንድ ሁሉን ነገር በማሟላት እንዲባርክ
እየጸለይን እንኑር፡፡ 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


ልቦቻችሁን በጌታ ላይ
አድርጋችሁ ኑሩ
‹‹ ማቴዎስ 6፡21-23 ››
‹‹መዝገብህ ባለበት ልብህ ደግሞ በዚያ ይሆናልና፤ የሰውነት መብራት
ዓይን ናት፡፡ ዓይንህ እንግዲህ ጤናማ ብትሆን ሰውነትህ ሁሉ ብሩህ ይሆናል፡፡
ዓይንህ ግን ታማሚ ብትሆን ሰውነትህ ሁሉ የጨለመ ይሆናል፡፡ እንግዲህ
በአንተ ያለው ብርሃን ጨለማ ከሆነ ጨለማውስ እንዴት ይበረታ!››

የዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ‹‹የሰውነት መብራት ዓይን ናት፡፡


ዓይንህ እንግዲህ ጤናማ ብትሆን ሰውነትህ ሁሉ ብሩህ ይሆናል›› ይላል፡፡
ልቦቻችን ልክ ዝናብ እንደማያጣው የበጋ አየር ጠባይ ተለዋዋጭ ናቸው፡፡ የሰው
አእምሮም ደግሞ እንደዚያው ነው፡፡ ነገር ግን ጌታ እንዲህ አለ፡- ‹‹የሰውነት
መብራት ዓይን ናት፡፡›› ጌታ እንደዚህ ሲል ዓይናችን ጤነኛ ከሆነ ሰውነታችን
በሙሉ ብሩህ ስለሚሆን በሚመጣውና በሚሄደው አሳባችን ላይ ትኩረት
ማድረግ ይገባናል ማለቱ ነው፡፡
ዓይን የሰውነት መብራት ስለሆነ አይን ጤነኛ ከሆነ ሰውነት በሙሉ ብሩህ
ይሆናል፡፡ ዓይን ታማሚ ከሆነ ግን ሰውነት በሙሉ ጨለማ ይሆናል፡፡ ልባችን
ሲዳምን የምናየው ነገር ሁሉ ጨለማ ነው፡፡ ነገር ግን እንደገና የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል ብናሰላስል ልባችን ይበራል፡፡ ጌታ ስለ ሰው ዓይን ሲናገር
የእምነት ልባችንን ጠቅሶዋል፡፡
ልቦቻችን ጽኑ አይደሉም፡፡ የእናንተና የእኔ ልቦች ይዋልላሉ፡፡ አንዳንድ
ጊዜ ልቦቻችን ያመነታሉ፡፡ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ስናሰላስል ልባችን
ጌታን ይወዳል፡፡ ነገር ግን ከዚያ በኋላ ወዲያውኑ ከሥጋዊ አስተሳሰቦቻችን የተነሳ
ዓለምን ወደ መውደድ እናዘነብላለን፡፡ እየተነጋገርን ያለነው ልቦቻችን ማሰብ
ስለሚገባቸው ነገር ነው፡፡
ዓይን የሰውነት መብራት ነው፡፡ ስለዚህ ስለ ጌታ ማሰብና ለውሃና
ለመንፈሱ ወንጌል መስፋፋትም ልቦቻችንን ማፍሰስ ይገባናል፡፡ ጌታችን ምን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


161 ልቦቻችሁን በጌታ ላይ አድርጋችሁ ኑሩ

ያህል ፈጽሞ ሐጢያቶቻችንን እንዳነጻ ስናስብ ልቦቻችን እንዴት እንደነጹ


እንገነዘባለን፡፡ ጌታችን በብሉይ ኪዳን ውስጥ ‹‹ሐጢአታችሁ እንደ አለላ ብትሆን
እንደ አመዳይ ትነጻለች፡፡ እንደ ደምም ብትቀላ እንደ ባዘቶ ትጠራለች››
(ኢሳይያስ 1፡18) ብሎ እንደተነገረው ጌታ በአዲስ ኪዳን ከአጥማቂው ዮሐንስ
በተቀበለው ጥምቀቱና በስቅለቱ አማካይነት የዓለምን ሐጢያቶች በመውሰድ
ሐጢያቶቻችንን ፈጽሞ አስወግዶዋቸዋል፡፡
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ላይ ማተኮር አለብን፡፡ ልባችን አልፎ አልፎ
በጌታና በዓለም መካከል ቢዋልልም አእምሮዋችን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
መስፋፋት ላይ እንዲያተኩር ማድረግ አለብን፡፡ ጌታ የእናንተንና የእኔን
ሐጢያቶች በማስወገዱ እናመሰግነዋለን፡፡ ጌታ ልቦቻችንን እንደ ጭጋግ
(ኢሳይያስ 44፡22) የሸፈኑትን ሐጢያቶቻችንን በሙሉ እንደደመሰሰ
በአእምሮዋችን መያዝ አለብን፡፡ በዚህ መንገድ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ
እንደደመሰሰ በአእምሮዋችን መያዝ አለብን፡፡ እንደዚህ ሐጢያቶቻችንን
ያስወገደውን ጌታን ስናስብ ልቦቻችን ይበራሉ፡፡
‹‹የሰውነት መብራት ዓይን ናት፡፡›› ልቦቻችንና ነፍሶቻችን ብሩህ ሊሆኑ
የሚችሉበት ከጌታ ውጭ ሌላ መንገድ ስለሌለ ስለ ጌታ በምናስብበት ጊዜ
ልቦቻችን በእግዚአብሄር ፊት በመንፈሳዊ መልኩ ብሩህ የሆኑ ልቦች ይሆናሉ፡፡
ልቦቻችንን በመንፈሳዊውና በሥጋዊው መካከል ይዋልላሉ፡፡ ነገር ግን ልባችንን
ሐጢያቶቻችንን ባስወገደው በጌታ ላይ ስናኖርና ጌታ የእያንዳንዱን ሰው
ሐጢያቶች ሸክም በመውሰድ ሁሉንም ለአንዴና ለዘላለም እንደደመሰሳቸው
ስለሚነግረን ወንጌል ስናስብ ጌታን ከማመስገንና እርሱን ይበልጥ ከመውደድ
በቀር የምናደርገው ነገር የለም፡፡
ስለዚህ ይህንን የውሃና የመንፈስ ወንጌል ይበልጥ ለሌሎች ለማሰራጨት
እንመኛለን፡፡ ልባችንን ሐጢያቶቻችንን ባስወገደው በጌታና በጽድቅ ምግባሮቹ
ላይ ስንኖር ልቦቻችን ብሩህ ስለሚሆኑ ከዚህ የተነሳ ብዙ ነፍሳቶች ደህንነትን
ያገኛሉ፡፡ ስለ ጌታ ስናስብና በእምነት ስናመሰግነው ልቦቻችን በመንፈስ ቅዱስ
ይረሰርሳሉ፡፡ በመንፈሳዊ መልኩ በብርሃን ውስጥ ባለው የተትረፈረፈ የደህንነት
በረከት ይረጥባሉ፡፡ ያን ጊዜ ልቦቻችን በእግዚአብሄር ዓይን ፊት ጻድቅ፣
መልካምና ውብ ይሆናሉ፡፡ የጽድቅ ሥራዎችን ለመስራትም ትልቅ ጥማት
ይኖራቸዋል፡፡
ልቦቻችንን በጨለማ ውስጥ ወይም በብርሃን ውስጥ ልንተዋቸው
እንችላለን፡፡ ልባችንን ጌታ ሐጢያቶቻችንን ባስወገደበት ስፍራ ማኖር

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


ልቦቻችሁን በጌታ ላይ አድርጋችሁ ኑሩ 162

የሚያስፈልገን መሆኑ ስህተት እንደሌለበት የተረጋገጠ ነው፡፡ በተጨማሪም


ጌታችን ሐጢያቶቻችንን ባስወገደበት ስፍራ ማኖር የሚያስፈልገን መሆን ስህተት
እንደሌለበት የተረጋገጠ ነው፡፡ በተጨማሪም ጌታችን ሐጢያቶቻችንን ያስወገደ
ብቻ ሳይሆን ልጆቹም ያደረገን በመሆኑ ልቦቻችንን በሰማያዊው መንግሥቱ ላይ
ማነጣጠር አለብን፡፡
በሐጢያቶቻችንን ምክንያት ልንሞትና የዲያብሎስ ልጆች ልንሆን
የምንችለውን እኛን ኢየሱስ ክርስቶስን በመላክ እንዲጠመቅ፣ የዓለምን
ሐጢያቶች ወደ መስቀል እንዲወስድና ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ለአንዴና
ለመጨረሻ በማስወገድ እስከ ሞት ድረስ ደሙን እንዲያፈስስ በማድረግ እኛን
ስላዳነባቸው በረከቶቹ እግዚአብሄርን በእምነታችን ልናመሰግነው ይገባናል፡፡
ልባችንን ያኖርንበት ስፍራ በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ ነገሩ ልቦቻችን እግዚአብሄር
የሰጠንን የደህንነት ባርኮቶች የሙጥኝ ብለው ይዘዋል ወይስ ከዓለምና ከሥጋ
የመጡትን ሥጋዊ አስተሳሰቦች የሙጥኝ ብለው ይዘዋል የሚለው ነው፡፡
ልቦቻችንን ባኖርባቸው ስፍራዎች ላይ በመመስረት ውጤቶቹ በአያሌው
ይለያያሉ፡፡ በዚህ መንገድ ወይም በዚያ መንገድ ልንወሰን እንችላለን፡፡
የሚወላወሉ ልቦች ቢኖሩንም ልቦቻችንን እግዚአብሄር በሰጠን ደህንነት ላይ
ማኖር እንደሚገባን ልነግራችሁ እሻለሁ፡፡ ልቦቻችንን እግዚአብሄር መንግሥተ
ሰማይንና የአምላክን በረከቶች የሰጠን በመሆኑ እውነታ ላይ ማኖር አለብን፡፡
እግዚአብሄር ልክ እንደ ጭጋግ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ በደመሰሰበትና
እንደ አመዳይ ባነጻበት አካባቢ ልቦቻችንን ቀድሰን ስንሰጥና ወደ እግዚአብሄር
ስንጸልይ ጸሎቶቻችንን ሰምቶ መልስ ይሰጠናል፡፡ እግዚአብሄር የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል በማስፋፋት ሥራችን እንደሚደሰት በማመን ልቦቻችንን
ለእግዚአብሄርና ለመንፈሳዊ ሥራ አሳልፈን መስጠት አለብን፡፡ ያን ጊዜ ልቦቻችን
ምን ያህል ብሩህ ሊሆኑ እንደሚችሉና የእግዚአብሄርም ሥራ እንዴት
እንደሚያድግ እንመለከታለን፡፡ ለአስደሳቹና ለተባረከው የእግዚአብሄር ሥራ
መጠቀሚያ በመሆናችን እርሱ የባረካቸው ሰዎች እንሆናለን፡፡
ውድ ወንድሞችና እህቶች ልቦቻችንን ለውሃውና ለመንፈሱ ወንጌል
መስፋፋት አሳልፈን ስንሰጥ ልቦቻችን ይደሰታሉ፡፤ በዚህ ዓለም ላይ ስንኖር
አንዳንድ ጊዜ ተስፋ እንቆርጣለን፡፡ አንዳንድ ጊዜም በሥጋዊ ፍትወቶቻችን
እንወድቃለን፡፡ ከቶውኑም የማይወድቅ ጻድቅ ሰው የለም፡፡ ነገር ግን እንደዚህ
ዓይነት ሰዎች ብንሆንም አስፈላጊው ነገር የልባችንን ፍላጎት ያኖርንበት ስፍራ
ነው፡፡ እያንዳንዳችን የልባችንን ትኩረት ያደረግነው የት ላይ ነው? እንዲያው

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


163 ልቦቻችሁን በጌታ ላይ አድርጋችሁ ኑሩ

በአጋጣሚ በጨለማ ያደረጋችሁት ነገር ካለ ወደ ብርሃን እንደምታወጡት ተስፋ


አደርጋለሁ፡፡
እኛ ወንጌልን ለቀረው ዓለም ለማሰራጨት እየሞከርን ነው፡፡ እንዴት
ልናሰራጨው ይገባናል? እስራኤሎች መጀመሪያ ላይ ወደ ከንዓን ምድር በገቡ
ጊዜ የማይበገረው የኢያሪኮ ግምብ የገጠማቸው ዓይነት ስጋት ይሰማኛል፡፡
ለእስራኤሎች የመጀመሪያው መሰናክል የኢያሪኮ ግምብ ነበር፡፡ የኢያሪኮ ግምብ
በጣም ጠንካራና አስተማማኝ ነበር፡፡ በጦርና በሰይፍ የሚወድቅ አልነበረም፡፡
በጣም ትላልቅ በሆኑ ዓለቶች የተገነባ በመሆኑ በቀላሉ ሊወድቅ የሚችል
አልነበረም፡፡ የኢያሪኮ ሰዎችም በግምቡ ጫፍ ላይ ነበሩ፡፡ ስለዚህ እስራኤሎች
ግምቡን ለማፍረስ ጥረቶችን ሁሉ ቢያደርጉም እነርሱ እስራኤሎችን ከላይ ሆነው
እያዩ ያፌዙባቸው ነበር፡፡ በትላልቅ የዛፍ ጉማጆች ላይ መንኩራኩሮችን በማኖር
ወታደሮቹ የከተማይቱን በር ለመግፋት፣ ለመስበርና ለመፈረካከስ ሞክረዋል፡፡
ነገር ግን ግምቡ በጣም አስተማማኝ ስለነበር የሚቻል አልሆነም፡፡ ሆኖም
እስራኤሎች በእግዚአብሄር ተማምነው የተስፋ ቃሉን በሚገባ ሲታዘዙ ከተማይቱ
ወደቀች፡፡
እኛም የዚያ ዓይነት እምነት ያስፈልገናል፡፡ በእኛም ዘመን ልባችንን
በእግዚአብሄር ላይ ካላኖርን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል የማስፋፋት
ተልዕኮዋችንን መፈጸም አንችልም፡፡ ነገር ግን ልቦቻችንን በእግዚአብሄር ላይ
ካኖርን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለቀረው ዓለም ማሰራጨት እንደሚቻል
አውቃለሁ፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምን እምነት ከሌለን ወንጌልን
ማሰራጨት አንችልም፡፡ ከዚህ የተነሳም ይህ ዓለም ወደ ጥፋት ይነጉዳል፡፡
እስከ አሁን ድረስ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለቀረው ዓለም
ስናሰራጭ ብዙ ችግሮች ነበሩ፡፡ ስለ ውሃውና መንፈሱ ወንጌል የሚናገሩትን
የሚሽን መጽሐፎቻችንን በብዙ የተለያዩ ቋንቋዎች ለማተምና በዓለም ላይ
ለሚኖር ለእያንዳንዱ ሰው ለመላክ ወሰንን፡፡ ስለዚህ የወንጌል መጽሐፎች በብዙ
የተለያዩ የዓለም ቋንቋዎች ተተረጎሙ፡፡ እነዚህን መጽሐፎች በማተምና
በማሰራጨትም እውነተኛውን ወንጌል ለመላው ዓለም ማሰራጨት ቻልን፡፡
የውሃውንና የመንፈሱ ወንጌል ለቀረው ዓለም ለማሰራጨት ስናስብና
ልቦቻችንንም ለዚህ አሳልፈን ስንሰጥ ልቦቻችን ይደሰታሉ፡፡ በእግዚአብሄርም
ፊት ለወንጌል ሥራ ተስማሚ ይሆናሉ፡፡ በሌላ በኩል ልቦቻችንን ለወንጌል
ስርጭት ሳይሆን ለዓለማዊ ነገሮች አሳልፈን ከሰጠን ልቦቻችን ከልክ በላይ
ይረክሳሉ፡፡ ልቦቻችን የስጋና የመንፈስ በሆኑት ነገሮች መካከል ቢዋልሉም

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


ልቦቻችሁን በጌታ ላይ አድርጋችሁ ኑሩ 164

ልቦቻችንን በውሃውና በመንፈሱ ወንገል ላይ ማጽናት አስፈላጊ ነው፡፡ እንዲህ


ተብሎ ተጽፎዋልና፡- ‹‹መዝገብህ ባለበት ልብህ ደግሞ በዚያ ይሆናልና፡፡››
ልቦቻችንን ባኖርንበት ነገር ላይ ተመስርተን በእግዚአብሄር ፊት የብርሃን ሰዎች
ልንሆን ወይም የማይረቡ ሰዎች ልንሆን እንችላለን፡፡ እንደ አብርሃምም ብሩካኖች
ልንሆን እንችላለን፡፡ ሕይወትን የሚሰጠውን ወንጌል ከሰው ሁሉ ጋር የምንጋራ
የእግዚአብሄር ሰዎችም መሆን እንችላለን፡፡
ልቦቻችንን በእግዚአብሄር ላይ እናኑር፡፡ በዚህ ዓለም ላይ ብንኖርም
ልቦቻችንን በእግዚአብሄር ላይ ማጽናት አለብን፡፡ ልቦቻችን ቢዋልሉም
ልቦቻችሁን በዓለም ላይ ከማኖር ይልቅ ጌታ በለገሳችሁ የውሃና የመንፈስ
ወንጌልና ባርኮቶች ላይ እንደምታኖሩ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ እግዚአብሄር በዚህ
ወንጌል አማካይነት ምን ያህል የደህንነት በረከቶችን ሰጥቶናል? ስለዚህ ነገር
ስናስብ ልቦቻችንን ለእግዚአብሄር አሳልፈን ከመስጠት በቀር የምናደርገው ነገር
ሊኖር አይችልም፡፡ ልቦቻችንን ለእግዚአብሄር መስጠት ተገቢ ነው፡፡ ጌታን
ማመስገንና ጌታን ማክበር ተገቢ ነው፡፡ ልቦቻችንን ለወንጌል መስጠትም
እንደዚሁ ተገቢ ነው፡፡ ሐጢያቶቻችንን ሁሉ ላስወገደው ታላቅ ደህንነት
ልባችንን መስጠት ተገቢ ነው፡፡ የዕርሱ ልጆች ስላደረገንም እግዚአብሄርን
እናመሰግነዋለን፡፡ ጌታ ሰማይን ሰጥቶናል፡፡ ልቦቻችንን ለጌታ መስጠት ትክክል
ነው፡፡
ልቦቻችሁን በጌታ ላይ እንደምታጸኑ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ የእናንተ ልቦችና
የእኔ ልብ አንዳንድ ጊዜ ስሜታዊ ሊሆኑና ሊዋልሉ ይችላሉ፡፡ ነገር ግን
ሁልጊዜም ልቦቻችንን ወደ እግዚአብሄር መመለስና ለጌታ ሥራ መኖር
ይገባናል፡፡ በመንገድ ላይ ስንጓዝ አንድ ያማረ ነገር ብናይ ዓይኖቻችንና ልቦቻችን
ለጊዜው ይከተሉታል፡፡ ነገር ግን ልባችንን ወዲያውኑ መልሰን ለጌታ ልንሰጠው
ይገባናል፡፡
በማቴዎስ ምዕራፍ 6 ላይ ጌታ በግልጽ ስለ ቁሳዊ ነገሮች ተናግሮዋል፡-
‹‹መዝገብህ ባለበት ልብህ ደግሞ በዚያ ይሆናልና፡፡›› በልቦቻችን ውስጥ ያለው
መዝገብ ምንድነው? የእናንተና የእኔ መዝገብ ምንድነው? ጌታ ነውን? ከጌታ
ያገኘናቸው በረከቶች ናቸውን? ወይስ ይህ ዓለም ነው? የትኛው ነው?
መዝገቡ ጌታ ነው፡፡ መዝገቡ ማንኛውም ዓይነት ቁሳዊ ነገር ነው ብላችሁ
ካመናችሁ እባካችሁ አእምሮዋቸሁን ለውጡ፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ ቁሳዊ ነገሮች
ከጌታ ይበልጥ የከበሩ አይደሉም፡፡ ምክንያቱም የቁሳዊ ነገሮች ሁሉ ባለቤት ጌታ
ነውና፡፡ ነገር ግን ያለ ቁሳዊ ነገሮች መኖር እንችላለን? አንችልም፡፡ በሌላ በኩል

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


165 ልቦቻችሁን በጌታ ላይ አድርጋችሁ ኑሩ

ቁሳዊ ነገሮችስ ከጌታ የመጡ አይደሉምን? ከጌታ የመጡ ናቸው፡፡ እርሱ እንዲህ
ብሎዋል፡- ‹‹መዝገብ ባለበት ልብህ ደግሞ በዚያ ይሆናልና፡፡›› ስለዚህ
ልቦቻችሁን በእግዚአብሄር ላይ ካኖራችሁ ሁሉም ነገር ወደ እናንተ ይመጣል፡፡
ሁሉም ነገር በጽድቅ መንገድ ይቀርብላችኋል፡፡
ሆኖም አንዳንድ ሐሳዊ ሰባኪዎች ይህንን ቁጥር ‹‹ብዙ መባዎችን ብትሰጡ
ትልቅ እምነት አላችሁ ማለት ነው›› ‹‹መዝገቦቻችሁን በሰማይ እንጂ በምድር ላይ
አታኑሩ፡፡ በሌላ አነጋገር ብዙ አስራትና ስጦታዎችን ለቤተክርስቲያን ስጡ›› እያሉ
ያስተምራሉ፡፡ በስጦታ ፖስታው ላይም ‹‹መዝገብህ ባለበት ልብህ ደግሞ በዚያ
ይሆናልና›› የሚለውን በመጻፍ ከውስጥ ይከቱታል፡፡
ይህ የሐሰት ትምህርት ነው፡፡ የዓለማዊ ቤተክርስቲያኖች ዓላማ በዚህ
ዓለም ላይ ለመበልጠግ ስለሆነ የሚጨነቁት ገንዘብን ለማከማቸት ነው፡፡ ለጽድቅ
ቢጠቀሙበት በማን ዕድላቸው! ነገር ግን የሚጠቀሙበት የስስታምነት
ፍላጎታቸውን ለመሙላት ነው፡፡ ገንዘብን በማከማቸት በጣም የተካኑ ስለሆኑ
ከክርስቲያኖች ገንዘብ ለመጠየቅ የዚህ ዓይነት የመጽሐፍ ቅዱስ ቁጥሮችን
ይጠቅሳሉ፡፡ በስሞቻቸው የቆጠቡትን ገንዘበቸውን ሁሉ ወደ ቤተክርስቲያን
እንዲያመጡ ያደርጉዋቸዋል፡፡
አንዳንድ ሰባኪዎች ከቤተክርስቲያን አባሎች ገንዘብ በመውሰድ አዳዲስ
ቤተክርስቲያኖችን ለመገንባት ግፊት ያደርጋሉ፡፡ ይህ ጽድቅ ነውን? ‹‹መዝገብህ
ባለበት ልብህ ደግሞ በዚያ ይሆናልና፡፡›› እነርሱ የሚያስቡት ስለ ቤተክርስቲያን
ግንባታ ብቻ ስለሆነ መዝገባቸው ያ ነው፡፡ የቤተክርስቲያን አባሎች
$15,000,000 ስለፈጀው የቤተክርስቲያን ሕንጻ በመኩራራት እንደዚህ ባለ
ቤተክርስቲያን ውስጥ መገኘት በጣም የሚያስከብርና የሚያኮራ ነገር እንደሆነ
ያህል ጉራቸውን ይነዛሉ፡፡ አስተሳሰቦቻቸውን ጠልቀን ብንመለከት ምናልባትም
ባዶ ነው፡፡ በእርግጥም ልባቸው ባዶ ነው፡፡ ልቦቻቸውን ያኖሩት $15,000,000
በፈጀው የቤተክርስቲያን ሕንጻ ላይ ስለሆነ ኢየሱስ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
ሐጢያቶቻችንን በሙሉ እንደ ጭጋግ የደመሰሰ መሆኑን ማየት አይችሉም፡፡
እግዚአብሄር ልጆቹ እንዳደረጋቸውና መንግሥተ ሰማይን እንደሰጠን ማየት
የማይችሉ ብዙ የሚያሳዝኑ ሰዎች አሉ፡፡
በተቃራኒው ለእኛ ዳግመኛ ለተወለድነው መዝገባችን ጌታችን ነው፡፡
ጌታችን የለገሰን የምህረት በረከቶች ሁሉ --የእርሱ ደህንነት፣ የእግዚአብሄር
ልጆች ያደረገን መሆኑ፣ መንግሥተ ሰማይን የሰጠን መሆኑ፣ ሐጢያቶቻችንን
ማስወገዱና ጻድቃን ያደረገን መሆኑ-- መዝገቦቻችን ናቸው፡፡ ከእነዚህ የበለጠ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


ልቦቻችሁን በጌታ ላይ አድርጋችሁ ኑሩ 166

ዋጋ ያለው ምንም ነገር የለም፡፡ ዝማሬው ‹‹♫ከወርቅ ወይም ከብር ይልቅ


♪ኢየሱስ ይሻለኛል›› እንደሚል ጌታ ኢየሱስን የራስ ከማድረግ የሚበልጥ ዋጋ
ያለው ክብር በዚህ ዓለም ላይ የለም፡፡ ጌታ ከሰጠን ደህንነት የሚበልጥ ዋጋ
ያለው ምንም ነገር የለም፡፡
ስለዚህ እናንተና እኔ የውሃወንና የመንፈሱን ወንጌል ለሰዎች ልቦች
ማሰራጨት አለብን፡፡ የሚዋልሉትን ልቦቻችንን ወስደን ለጌታ ሥራ ልንሰጣቸው
ይገባናል፡፡ ልቦቻችንን ለጌታ ከሰጠን የማይጠቅም ሥራ አንሰራም፡፡ ነገር ግን
ወደ ጌታ መንግሥት ለመግባት እንችላለን፡፡ አንዳንድ ጊዜ የማይረቡ ነገሮችን
እናደርጋለን፡፡ ነገር ግን ብዙ ጠቃሚ ሥራ ብንሰራ በእግዚአብሄር
እንመሰገናለን፡፡ በሰዎችም እንከበራለን፡፡
ማቴዎስ ምዕራፍ 6 በዚህ ርዕሰ ጉዳይ ላይ በጥልቀት ይናገራል፡- ‹‹ነገር ግን
አስቀድማችሁ የእግዚአብሄርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፤ ይህም ሁሉ
ይጨመርላችኋል፡፡ ነገ ለራሱ ይጨነቃልና ስለ ነገ አትጨነቁ፡፡ ለቀኑ ክፋቱ
ይበቃዋል፡፡›› እናንተና እኔ ልቦቻችንን በእርሱና በሥራው ላይ ልናኖር ይገባናል፡፡
አስቀድመን የእርሱን መንግሥትና ጽድቁን ልንፈልግ ይገባናል፡፡ እግዚአብሄር
እንዴት አዳነን? እርሱ በውሃ፣ በደምና በመንፈስ ቅዱስ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ
እንደ አመዳይ አነጻ፡፡ ፍጹም አዳኛችን የሆነውን አምላክና ጌታ ማመስገን
አለብን፡፡ አስቀድመንም መንግሥቱን በልቦቻችን ውስጥ መሻት አለብን፡፡
የሚያምኑ እንዲያምኑበት የማያምኑበትም ደግሞ እንዳያምኑበት የውሃውና
የመንፈሱ ወንጌል በመላው ዓለም መሰራጨት ያለበት መሆኑ የእግዚአብሄር
ፈቃድ ነው፡፡ የእግዚአብሄርን ፈቃድ ለመፈጸም እያንዳንዱ ሰው ወንጌልን
የሚሰማበት እኩል ዕድል ልንሰጠው ይገባናል፡፡ ይህንን ሥራ መስራት አለብን፡፡
በነገራችን ላይ ለእናንተና ለእኔ እውነተኛው መዝገብ ጌታ ነው፡፡ እኛ ብዙ
ጉድለቶች ያሉብን ሰዎች ብንሆንም ልባችንን በጌታ ላይ እናጽና፡፡ ልቦቻችንን
በጌታ ላይ በማኖር በተቻለ መጠን አዘውትረን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
እናሰራጭ፡፡
ሐሌሉያ! ልቦቻችንን በጌታ ላይ እንድናኖር ስለረዳን እግዚአብሄርን
እናመሰግናለን፡፡ 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ስለ ሕይወታችሁ አትጨነቁ፤
ነገር ግን በእግዚአብሄር
ብቻ እመኑ
‹‹ ማቴዎስ 6፡25-34 ››
‹‹ስለዚህ እላችኋለሁ፤ ስለ ነፍሳችሁ በምትበሉትና በምትጠጡት ወይም
ስለ ሰውነታችሁ በምትለብሱት አትጨነቁ፡፡ ነፍስ ከመብል ሰውነትም ከልብ
አይበልጥምን? ወደ ሰማይ ወፎች ተመልከቱ፤ አይዘሩም አያጭዱምም፤ በጎተራም
አይከቱም፡፡ የሰማይ አባታችሁም ይመግባቸዋል፡፡ እናንተ ከእነርሱ እጅግ
አትበልጡምን? ከእናንተ ተጨንቆ በቁመቱ ላይ አንድ ክንድ መጨመር የሚችል
ማን ነው? ስለ ልብስስ ስለምን ትጨነቃላችሁ? የሜዳ አበቦች እንዴት
እንዲያድጉ ልብ አድርጋችሁ ተመልከቱ፡፡ አይደክሙም አይፈትሉምም፡፡ ነገር
ግን እላችኋለሁ፤ ሰለሞንስ እንኳን በክብሩ ሁሉ ከእነዚህ እንደ አንዱ
አልለበሰም፡፡ እግዚአብሄር ግን ዛሬ ያለውን ነገም ወደ እቶን እሳት የሚጣለውን
የሜዳ ሣርን እንዲህ የሚያለብሰው ከሆነ እናንተ እምነት የጎደላችሁ እናንተንማ
ይልቁን እንዴት? እንግዲህ ምን እንበላለን? ምንስ እንጠጣለን? ምንስ
እንለብሳለን? ብላችሁ አትጨነቁ፡፡ ይህንስ ሁሉ አሕዛብ ይፈልጋሉ፡፡ ይህ ሁሉ
እንዲያስፈልጋችሁ የሰማዩ አባታችሁ ያውቃልና፡፡ ነገር ግን አስቀድማችሁ
የእግዚአብሄርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፤ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል፡፡ ነገ
ለራሱ ይጨነቃልና ለነገ አትጨነቁ፤ ለቀኑ ክፋቱ ይበቃዋል፡፡››

እኛ ዳግመኛ የተወለድን ሰዎችም እንደዚሁ የሐጢያት ስርየትን ከተቀበልን


በኋላም እንኳን ስለ ወደፊቱ ለመጨነቅ እናዘነብላለን፡፡ እነዚህ ከአሁን በኋላ
የምኖረው እንዴት ነው? ለመብላት ምን ማድረግ አለብኝ? ለመልበስ ምን
ማድረግ ይገባኛል? እንዴትስ ልኖር ይገባኛል? የሚሉ ጭንቀቶች ናቸው፡፡ በዚህ
መንገድ በልቦቻችን ውስጥ ስለ ወደፊቱ የሚጨነቁ ልቦች አሉን፡፡ ዳግመኛ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


ስለ ሕይወታችሁ አትጨነቁ፤ ነገር ግን በእግዚአብሄር ብቻ እመኑ 168

በተወለዱት መካከል ገና ያበሰሉት እግዚአብሄር እንደሚረዳቸው ስለማይረዱና


መንገዳቸውንም የሚመራቸው እግዚአብሄር መሆኑን ስላልተለማመዱ ለቀሪው
የሕይወት ዘመናቸው ለመጨነቅ የተጋለጡ ናቸው፡፡ በእርግጥ ሰዎች ስለሆንን
መጨነቃችን ተፈጥሮአዊ ነው፡፡
ወደዚህ ዓለም የተወለደ እያንዳንዱ ሰው ለራሱ ጠንክሮ ይሰራል፡፡ እነርሱ
እግዚአብሄርን በማመን ስላልኖሩ በራሳቸው ጥረቶችና ብርታት በመደገፍ የመኖር
ልማድ ስላላቸው ዳግመኛ ከተወለዱም በኋላ እንኳን የሚጨነቁበት
የመጀመሪያው ነገር ምን መብላት እንደሚገባቸው፣ ምን መጠጣት
እንደሚገባቸውና እንዴት መኖር እንደሚገባቸው ነው፡፡ ነገር ግን ጌታ ዳግመኛ
የተወለዱት አስቀድመው ምን ማሰብ እንደሚገባቸው ነግሮናል፡፡ ‹‹ነገር ግን
አስቀድማችሁ የእግዚአብሄርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፤ ይህም ሁሉ
ይጨመርላችኋል፡፡›› እርሱ እንዲህ ብሎዋል፡፡ ‹‹የእግዚአብሄርን መንግሥት
የእግዚአብሄርን ጽድቅ ፈልጉ፡፡ መጀመሪያ ከቤተክርስቲያን ጋር ተባበሩ፡፡
የእግዚአብሄርን ሥራ የሚሰራውን ሥራ፣ መንግሥቱንና ሰዎችን ማዳን ፈልጉ፤
ጸልዩ! ያን ጊዜ በሥጋ አካባቢ ያሉትን እንደ መብላት፣ እንደ መጠጣትና
በሕይወት እንደ መኖር ያሉ ፍላጎቶቻችሁን ሁሉ አሟላለሁ፡፡››
እኔም ደግሞ ከሐጢያቶቼ እንደዳንሁ ወዲያውኑ ስለ ወደፊት ሕይወቴ
አስቤያለሁ፡፡ ‹‹እንዴት ነው የምኖረው? ምን እበላለሁ? ምን እለብሳለሁ? ኑሮን
ለመግፋትስ ምን እሰራለሁ?›› ስለ እነዚህ ነገሮች ተጨንቄያለሁ፡፡ ላደርጋቸው
የነበሩ የተወሰኑ ነገሮች ከሌሉ በዚያን ጊዜ ምን እንደማደርግ አላውቅም ነበር፡፡
የሐጢያቶቻቸውን ስርየት ከማግኘታቸው በፊት የተወሰነ ገንዘብ የቆጠቡ ሰዎች
ብዙም ግራ አይጋቡ ይሆናል፡፡ ነገር ግን የሐጢያት ስርየትን ከማግኘቱ በፊት
እንደ እኔ በትምህርት ላይ ብቻ የነበረ ሰው ይበልጥ ግራ ይጋባል፡፡ በዚህ ዓለም
ላይ እንዴት እንደምኖር ከመጨነቅ በቀር ላደርገው የቻልሁት ነገር አልነበረም፡፡
በቤተክርስቲያኖቻችን ውስጥ በተጨባጩ ዓለም ተማሪዎች ወይም
ጀማሪዎች የሆኑ ወጣት ወንድሞችና እህቶች በዚህ ዓለም ላይ እንዴት መኖር
እንደሚችሉ በማሰብ ተስፋ ሊቆርጡ ይችላሉ፡፡ ለመብላት ምን መስራት አለብን?
ምንስ መልበስ አለብን? እንዲህ ያሉ ብዙ ጭንቀቶች አሉ፡፡
ነገር ግን ጌታ ለሁላችንም እንዲህ ብሎናል፡- ‹‹ስለ እነዚህ ነገሮች
አትጨነቁ፡፡ ዳግመኛ ያልተወለዱ ሰዎችም የሚጨነቁት ስለ እነዚህ ነገሮች
ነው፡፡›› ያን ጊዜ ልባችን በአእምሮዋችን ተመርቶ እንዲህ ይላል፡- ‹‹ጌታችን ስለ
ሁኔታችን ፍንጭ የለውም፡፡ ይህ የተጨባጭነት ችግር ነው፡፡ ታዲያ ስለዚህ ነገር

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


169 ስለ ሕይወታችሁ አትጨነቁ፤ ነገር ግን በእግዚአብሄር ብቻ እመኑ

እንዴት ላንጨነቅ እንችላለን? ጌታ ግን አጥብቆ እንዲህ ብሎናል፡- ‹‹አሕዛቦች


የሚጨነቁት ለዚህ ነው፡፡ እንዴት ልንኖር እንችላለን? ብላችሁ አትጨነቁ፡፡
አስቀድማችሁ ስለ እግዚአብሄር ጽድቅ አስቡ፡፡ የእርሱን ጽድቅ እየፈጸማችሁም
ሕይወታችሁን ኑሩ፡፡›› ጌታ እንዲህ ብሎዋል፡- ‹‹ወደ ሰማይ ወፎች ተመልከቱ፤
አይዘሩም አያጭዱምም፤ በጎተራም አይከቱም፡፡ የሰማይ አባታችሁም
ይመግባቸዋል፡፡ እናንተ ከእነርሱ እጅግ አትበልጡምን?››
በእርግጥ ጌታ የተናገረውን ካመንን እርሱን ልንከራከርበት የምንችልበት
ምንም ነገር የለም፡፡ ስለ ሕይወታችን እንጨነቃለን፡፡ ጌታ ግን ግልጽ በሆነ
አነጋገር ‹‹ስለ ቁሳዊ ነገሮች አትጨነቁ፤ ያንን አህዛቦችም ይጠይቃሉ፡፡ ዳግመኛ
ያልተወለዱ ሰዎችም የሚጠይቁት ያንን ነው፡፡ የሜዳ አበቦች እንዴት
እንደሚያድጉ ተመልከቱ፡፡ አይደክሙም አይፈትሉምም፡፡ እግዚአብሄር ዛሬ
ያለውን ነገም ወደ እቶን የሚጣለውን የሜዳን ሣር እንዲህ የሚያለብሰው ከሆነ
እናንተ እምነት የጎደላችሁ እናንተንማ ይልቁን እንዴት? በማለት ይወቅሰናል፡፡
ውድ ክርስቲያኖች በሜዳ ያሉ አበቦች የሚያድጉት እንዴት ነው?
ወዲያውኑ ማጎንቆል ጀምረው በማደግ ያብባሉን? ይህ የሚሆነው እግዚአብሄር
ስለሚዘራቸው፣ የሚያስፈልጋቸውን የጸሐይ ብርሃን ስለሚሰጣቸው፣ ዝናብ
ስለሚለግሳቸውና እንዲያብቡ ስለሚያደርጋቸው ነው፡፡ እግዚአብሄር የሜዳን
ሣር እንዲህ የሚንከባከበው ከሆነ ጻድቅ የሆናችሁትን እናንተንማ እንዴት
አብልጦ እንደሚንከባከባችሁ ጌታ ተናግሮዋል፡፡
ውድ ክርስቲያኖች በእኛ ጭንቀቶችና ከእግዚአብሄር የእውነት ቃል
በሚመጣው መጽናናት መካከል ብዙ ልዩነት አለ፡፡ እኛ ስለ ወደፊት ሕይወታችን
ብዙ እንጨነቃለን፡፡ ነገር ግን ‹‹የሜዳ አበቦችን ተመልከቱ›› በማለት ዝም
እንድንል ስላደረገን ብዙ የምናገረው ነገር የለም፡፡ እግዚአብሄር አበቦቹን
ለማሳመር የጸሐይ ብርሃንና ዝናብን ሰጥቶዋል፡፡ ታዲያ የእርሱ ልጆች የሆንነውን
እኛን አይንከባከበንምን? በእግዚአብሄር የሚታመን እምነት ይኑራችሁ፡፡ ያን ጊዜ
ከእግዚአብሄር ጋር መግባባት ትችላላችሁ፡፡
ከእግዚአብሄር ጋር ለመግባባት ምን እናድርግ በእግዚአብሄር ቃል ከማመን
በስተቀር ሌላ መንገድ የለም፡፡ ቃሉን እንዳለ ስናምን ከእርሱ ጋር በእምነት
መግባባት እንችላለን፡፡ እግዚአብሄር እንደዚህ ካለ ‹‹እግዚአብሄር
እንደሚያስብልኝ፣ እንደሚመግበኝ፣ በሕይወት እንድኖር እንደሚረዳኝ›› በቃሉ
መሰረት በእርሱ ስናምን ከእግዚአብሄር ጋር መዛመድና አንድ መሆን እንችላለን፡፡
በእምነታችን መሰረትም መልስ እናገኛለን፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


ስለ ሕይወታችሁ አትጨነቁ፤ ነገር ግን በእግዚአብሄር ብቻ እመኑ 170

የሜዳ አበቦችን ተመልከቱ፡፡

‹‹እግዚአብሄር የሜዳ አበቦችን አብቅሎዋል፡፡ እኔም ከእግዚአብሄር ሕዝብ


አንዱ ነኝ፡፡ የእግዚአብሄር ልጅ ነኝ፡፡ እግዚአብሄርም አባቴና እረኛዬ ስለሆነ
እንደሚመግበኝና እንደሚያለብሰኝ አምናለሁ›› በማለት እንዲህ የሚመስክር
እምነት አላችሁን? ጭንቀቶችን ለማስወገድ ብቸኛው መንገድ ማመን ነው፡፡
‹‹አምላኬ በአንተ አምናለሁ!›› በእግዚአብሄር ፊት ከእነዚህ የሚበልጡ ሌሎች
ቃሎች የሉም፡፡ መናገር የምንችላቸው ሌሎች ቃሎች የሉም፡፡
ውድ ክርስቲያኖች ጌታ አንድ ነገር ሲናገር ያንን በመቃወም ሌላ ነገር
መናገር እንችላለን? በዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ላይ እግዚአብሄር
አስቀድመን የእግዚአብሄርን መንግሥትና ጽድቁን በምንፈልግበት ጊዜ
የሚያስፈልገንን ሁሉ እንደሚሰጠን ቃል ገብቶልናል፡፡ ይህንን ምንባብ በእምነት
ለራሳችን ስንወስድ ሌላ ነገር ልንናገር አንችልም፡፡ እምነት የሌለን መሆናችንን
ከመናገር በቀር ሌላ አንዳች ማማኻኛ ልንቀርብ አንችልም፡፡ ‹‹እኔ የሜዳ አበቦችን
አበቅላለሁ፤ እንደዚያ ከሆነ እናንተንስ አልንከባከባችሁምን? በየዓመቱ የሚበቅል
ተክል አበቅላለሁ፡፡ ልጆቼንስ መንከባከብ አልችልምን?›› አሁን በእርሱ እመኑ፡፡
ይህንን ካመንን እንደዚህ ብለን አናስብም፡- ‹‹ዝናብ እግዚአብሄር ከሰማይ
የሚያወርደው ነገር ነው፡፡ የጸሐይ ብርሃንም እርሱ የሚሰጠው ነገር ነው፡፡
ስለዚህ ሣሩ ይበቅላል፡፡ እኛ ግን በዝናብና በጸሐይ ብርሃን ብቻ መኖር
አንችልም፡፡ አቤቱ ለመኖር ምን ያህል ጠንክረን እንደምንሰራ አታውቅምን?››
በእርግጥ እግዚአብሄር የማያውቀው ነገር የለም፡፡ ጌታ ሁላችንንም
እንደሚያውቀን ከተናገረ እግዚአብሄር በዚህ ዓለም ላይ መኖር የምንችልባቸውን
ችሎታ፣ ጥበብና በረከቶች እንደሚሰጠን ማመን አለብን፡፡ አምላክ በትክክለኛው
ጊዜ ሁሉን ነገር እንደሚሰጠን ሊነግረን ጌታ አበባን እንደ መከራከሪያ ከተጠቀመ
እግዚአብሄር የእርሱ ልጆች ለሆንነው ሁሉን ነገር በትክክለኛው ጊዜ
እንደሚያቀርብ ማመን እንችላለን፡፡
ጌታ እምነታችንን ለመግለጥ ‹‹ወደ ሰማይ ወፎች ተመልከቱ፤ አይዘሩም
አያጭዱምም፤ በጎተራም አይከቱም፡፡ የሰማይ አባታችሁም ይመግባቸዋል፡፡
እናንተ ከእነርሱ እጅግ አትበልጡምን?›› (ማቴዎስ 6፡26) በማለት ሌላ ምሳሌ
ሰጥቶናል፡፡
ነገር ግን አንዳንድ የማያምኑ ሰዎች ‹‹ተመልከቱ! በአየር ላይ የሚበረውን
ወፍ ተመልከቱ! እንዴት ትጉህ ነው! እኛም በአየር ላይ እንደሚበሩት እንደ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


171 ስለ ሕይወታችሁ አትጨነቁ፤ ነገር ግን በእግዚአብሄር ብቻ እመኑ

እነዚህ ወፎች በዚህ ዓለም ላይ ጠንክረን ብንሰራ ተመችቶን እንኖራለን›› በማለት


ይህንን ጥቅስ በማይመስል መልኩ ይተረጉሙታል፡፡ እንደዚህ ዓይነት
መከራከሪያዎችን ያቀርባሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች እምነት ስለሌላቸው ‹‹አሃ! አንድ ሰው
ጠንክሮ ከሰራ በቂ ምግብ ስለሚኖረው በምቾት ይኖራል›› የሚል የዚህ ዓይነት
መከራከሪያዎችን ያቀርባሉ፡፡
እንደዚህ ዓይነት መከራከሪያዎች ጌታ ከነገረን የእምነት መከራከሪያ የተለዩ
ናቸው፡፡ ጠንክረን ብንሰራ ስለ ምግብ አንጨነቅም ማለት የማይችል ማነው?
ነገር ግን ሰው ሁሉ ጠንከሮ በመስራቱ ብቻ ባለጠጋ ይሆናልን? ይህ ሁሉንም
ሰው የሚመለከት አይደለም፡፡ በሥራ ቦታቸው ለወራት ወይም ለዓመታት የሰሩ
ነገር ግን ገናም ያልበለጠጉ ብዙ ሰዎች አሉ፡፡
‹‹ወደ ሰማይ ወፎች ተመልከቱ፤ አይዘሩም አያጭዱምም፤ በጎተራም
አይከቱም፡፡ የሰማይ አባታችሁም ይመግባቸዋል፡፡ እናንተ ከእነርሱ እጅግ
አትበልጡምን?›› ጌታ ይህንን ቃል ሲናገር ጠንክረን ስንሰራ ምግብ ማግኘት
እንችላለን ለማለት ፈልጎ አይደለም፡፡ ያዳነን እግዚአብሄር አባታችን በዚህ ዓለም
ላይ ሕይወታችንን ለማኖር ለመብል፣ ለመጠጥና ለልብስ የሚያስፈልገውን
እንደሚሰጠን ጌታ ተናግሮዋል፡፡ ይህ ማለት እግዚአብሄር እኛን ጻድቃኖችን
ይመግበናል ያለብሰንማል ማለት ነው፡፡ ይህ ማለት ወንጌልን ለማሰራጨት
የሚኖረውን ማንኛውንም ጻድቅ ሰው ይንከባከባል ማለት ነው፡፡ የዚህ ቁጥር
ዋናው ነጥብ ይህ ነው፡፡ ‹‹ልጆቼ ሆናችሁ አስርባችኋለሁን? አራቁታችኋለሁን?›
ልጆቼ ሆናችሁ በዚህ ዓለም ላይ ስትኖሩ፣ የራሳችሁ ሕይወት ሳላችሁ፣ በዚህ
ዓለም ላይ የምትሰሩዋቸው ሥራዎች ሲኖሩዋችሁ አልንከባከባችሁምን?››
እኔም ዳግመኛ ከመወለዴ በፊት ይህንን ምንባብ ሳነብ የማይሆን ዓይነት
ስሜት ይሰማኝ ነበር፡፡ ጌታን ለመጀመሪያ ጊዜ ሳገኝ ምን እንደማደርግ አላውቅም
ነበር፡፡ ስለዚህ በመጀመሪያ ኑሮዬን ለመኖር ሥራ ሊኖረኝ እንደሚገባ አሰብሁ፡፡
እንደ እውነቱ ከሆነ በአእምሮዬ ውስጥ ሌሎች ዕቅዶች አልነበሩኝም፡፡ ጌታን
ለመጀመሪያ ጊዜ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት ሳገኘው በእርግጥም
ግራ ተጋብቼ ነበር፡፡ እንዴት እንደምኖር፣ ምን እንደምበላና ምን እንደምለብስ
በጭንቀቶች ተወጥሬ ስለነበር ደህንነትን ከተቀበልሁ በኋላ ወንጌልን
የማሰራጨው እንዴት ነው? የሚለው ጭንቀት አላሳሰበኝም፡፡ ጌታ ግን
‹‹አህዛቦችም የሚፈልጉት ይህንን ነው›› አለ፡፡ ሆኖም ‹‹ያ የአንተ ስነ አመክንዮ
ነው፡፡ የእኔ ስነ አመክንዮ አሁን ያንን አይከተልም›› በማለት አዘውትሬ በቃሉ ላይ
ሳምጽ ነበር፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


ስለ ሕይወታችሁ አትጨነቁ፤ ነገር ግን በእግዚአብሄር ብቻ እመኑ 172

ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ወደፊት እንዴት እንደምኖር ስመለከት ጨለማ ነበር፡፡


ሁኔታዬን ስመለከት በጣም የከፋ ነበር፡፡ ምን እንደማደርግ አላውቅም ነበር፡፡
በዚያን ወቅት ምንም የማውቀው ነገር አልነበረም፡፡ ነገር ግን እርግጠኛ
የሆንሁበት አንድ ነገር እግዚብሄር አባቴ መሆኑንና ጌታም ሐጢያቶቼን በሙሉ
መደምሰሱን ነበር፡፡ ያን ጊዜ ጌታ እንዲህ አለ፡- ‹‹የሰናፍጭ ቅንጣት የምታህል
እምነት ቢኖራችሁ ይህንን ተራራ ተነቅለህ ሂድ ብትሉት ይሆንላችኋል፡፡›› ይህ
ማለት ጌታ በእምነት መኖር ያስቻለኝን የወንጌል እውነት ሰጥቶኛል ማለት ነው፡፡
እንዲህም ደግሞ ብሎኛል፡- ‹‹አስቀድማችሁ የእግዚአብሄርን መንግሥት
ጽድቁንም ፈልጉ፤ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል፡፡››
‹‹አሃ! መኖር የምችልበት መንገድ ይህ ነው!›› ራሴን ለእግዚአብሄር አሳልፌ
ለመስጠት አእምሮዬን አዘጋጀሁ፡፡ ይህንን ቃል የሙጥኝ ብዬ ይዤ
ስለሚያስፈልገኝ ነገር ሁሉ ጸለይሁ፡፡ ‹‹እግዚአብሄር አባት ምንም ገንዘብ
የለኝም፡፡ አምላኬ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ማስፋፋት እፈልጋለሁ፡፡ ነገር
ግን ምንም ገንዘብ የለኝም፡፡ ገንዘብ ስጠኝ፡፡ ቁሳዊ ነገሮችን ስጠኝ፡፡ ቤት
የለኝም፤ የቤተክርስቲያን ሕንጻ ስጠኝ፡፡ ነፍሳቶችን ስጠኝ፡፡ የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል ለማሰራጨት መጽሐፎችን ለማዘጋጀት እየተፍጨረጨርሁ
ነው፡፡ ማተሚያ ግን የለኝም፤ ማተሚያ ስጠኝ›› ብዬ ጸለይሁ፡፡
አሁን ትንሽዋ እምነቴ ስላደገች የእግዚአብሄርን ሥራ ለመስራት ትልቅ ነገር
ጠየቅሁ፡፡ እግዚአብሄር ለእያንዳንዱ ነገር -- ትልቅ ይሁን ትንሽ መልስ
እንደሚሰጥ አረጋገጥሁ፡፡ ይህም ቀስ በቀስ የእምነት ሰው ሆኜ እንዳድግ
አደረገኝ፡፡ ይህ ማለት የእምነት ሰዎች የምንሆነው ሳናውቀው ነው ማለት ነው፡፡
አንድ ነገር ሲከሰት ‹‹ከጸለይን እግዚአብሄር ይሰጣል! ወንድሞችና እህቶች
ሊጨነቁበት የሚያስፈልግ ምን ነገር የለም! እግዚአብሄር ይረዳል! እግዚአብሄር
ወንድሞችንና እህቶችን ይረዳል! ወንድሞችና እህቶች ችግር ሲያጋጥማቸውና
ሲጨነቁ ከጸለይን እግዚአብሄር ይሰጠናል!›› ብዬ አሰብሁ፡፡ በእምነት
እስከጸለይን ድረስ እምነታችን ቀስ በቀስ ያድጋል፡፡ ጌታ እንዲህ ያለው ለዚህ
ነው፡- ‹‹በነገር ሁሉ በጸሎትና በምልጃ ከምስጋና ጋር በእግዚአብሄር ዘንድ
ልመናችሁን አስታውቁ እንጂ በአንዳች አትጨነቁ፡፡ አእምሮንም ሁሉ የሚያልፍ
የእግዚአብሄር ሰላም ልባችሁንና አሳባችሁን በክርስቶስ ኢየሱስ ይጠብቃል፡፡››
(ፊልጵስዩስ 4፡6-7) አምላካችን ከምንጠይቀው ወይም ከምናስበው ሁሉ ይልቅ
እጅግ አብልጦ ሊያደርግ ይችላል፡፡ (ኤፌሶን 3፡20)
እኛ ይህንን ስለምናምን ጌታን በድፍረት እንጠይቀዋለን፡፡ አንድን ነገር

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


173 ስለ ሕይወታችሁ አትጨነቁ፤ ነገር ግን በእግዚአብሄር ብቻ እመኑ

በራሳችን ስሜት ከመጀመር ይልቅ፣ እያንዳንዱን ሰውኛ ዘዴ ለመጠቀም


ከመሞከር ይልቅ ‹‹አምላካችን! ይህንን ስጠን፤ በእርግጥ እንፈልገዋለን›› ብለን
እንጸልያለን፡፡ በዓይኖቻችን አንዳች አዎንታዊ ምልክት ማየት ባንችልም እንኳን
እግዚአብሄርን እንዲሰጠን እንጠይቀዋለን፡፡ ለምን? ጸሎት ነገሮችን እንዲሆኑ
ያደርጋቸዋልና፡፡ ስለዚህ ጸሎት እኛ ከምንሞክራቸው የራሳችን መንገዶች የተሻለ
ነው፡፡ እኔ ዳግመኛ ስወለድ ኑሮዬን ለመግፋት የማሰሮ ሽያጭ ሥራ ለመስራት
ዕቅድ ነበረኝ፡፡ ነገር ግን እምነቴ ሲያድግ በራሴ መንገድ አንዳች ነገር ለማድረግ
ከመሞከር ይልቅ ጸለይሁ፡፡
በእግዚአብሄር ላይ እምነት ካለን የእርሱን እርዳታ ለማግኘት በመጀመሪያ
ወደ እርሱ እንጸልያለን፡፡ መልሶች ባይኖሩም እንኳን በትጋት እንጸልያለን፡፡
‹‹እግዚአብሄር ሆይ ይህንን አድርግልን፤ ያንን አድርግልን፡፡›› ለረጅም ጊዜ ያለ
ማቋረጥ ስንጸልይ እግዚአብሄር መልሶችን ሲሰጥ እናያለን፡፡ ከዚያም መልስ
እናገኛለን፡፡ እንደገናም ሌላ የጸሎት ርዕስ ይዘን እንጸልያለን፡፡ በዚህም
ከእግዚአብሄር ዘንድ መልሶችን የመቀበል ተሞክሮ እናዳብራለን፡፡ ስለዚህም
የእምነት ሰዎች እንሆናለን፡፡ በእግዚአብሄር የሚያምን ብርቱ እምነት ይኖረናል፡፡
ጌታ እንደሚመግበን፣ እንደሚያለብሰንና በሕይወት እንደሚያኖረን አጥብቀን ወደ
ማመን እንደርሳለን፡፡ ለእግዚአብሄር ጽድቅ ስንኖር በእግዚአብሄር ላይ ያለንን
እምነታችንን እናዳብራለን፡፡
ስለዚህ ለእግዚአብሄር ጽድቅ ስንሰራ ከአሁን በኋላ ምን እንደምንበላ፣ ምን
እንደምንጠጣና ምን እንደምንለብስ ብዙ አያስጨንቀንም፡፡ አንድ ነገር
ሲያስፈልገን እንጸልያለን፡፡ ‹‹እግዚአብሄር ሆይ እንደገና ስጠን፡፡ ለወንድሞቻችንና
ለእህቶቻችን ቁሳቁሶችን ስጣቸው፡፡ ጤናን ስጠን፤ ይህንን ስጠን፤ ያንን ሰጠን››
እያልን እንጸልያለን፡፡ ይህ ማለት ተቀምጠን መጸለይ እንጂ ለራሳችን የሚሆን
ነገር ማድረግ የለብንም ማለት አይደለም፡፡ በመጀመሪያ መጸለይና
የእግዚአብሄርን ጽድቅ መፈለግ ይኖርብናል፡፡ ያን ጊዜ እግዚአብሄር ለመብላት፣
ለመጠጣትና ለሕይወት የሚያስፈልጉ ሌሎች የተለያዩ ነገሮችን እንደዚሁም
እያንዳንዱን ነገር ሁሉ ይሰጠናል፡፡ እርሱ ሁሉን እንደሚሰጥ እንደምታምኑ ተስፋ
አደርጋለሁ፡፡
እንደ እውነቱ ከሆነ እስከ አሁን ድረስ በሕይወት መኖርና ሥራውን
በሚገባ መስራት የቻልነው እግዚአብሄር ሁሉን ነገር ስላዘጋጀልን ነው፡፡ ስለዚህ
ወደፊትም ደግሞ እግዚአብሄር ለእኛ ለጻድቃኖች ለሕይወታችን የሚያስፈልጉትን
ልብስ፣ ምግብና መጠጥ እንደሚሰጠን የተረጋገጠ ነው፡፡ እነዚህን ብቻ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


ስለ ሕይወታችሁ አትጨነቁ፤ ነገር ግን በእግዚአብሄር ብቻ እመኑ 174

አይደለም፤ ለእግዚአብሄር መንግሥት የምንጠይቀውን ሌላውን ነገር ሁሉ


እግዚአብሄር አትረፍርፎ ይሰጠናል፡፡
ወንድሞችና እህቶች በእግዚአብሄር ውስጥ መኖር በረከት የሆነው ለዚህ
ነው፡፡ የምንኖረው በእግዚአብሄር ላይ ባለን እምነት እንጂ ባለን ነገር አይደለም፡፡
ጻድቃን በሥጋና በመንፈስ በልጥገው መኖር የሚችሉት ለዚህ ነው፡፡ በእርግጥ
በእግዚአብሄር በሚያምን እምነት ብንኖር በሥጋና በመንፈስ ተመችቶን
እንኖራለን፡፡
እግዚአብሄር እንዲህ ነግሮናል፡- ‹‹አስቀድማችሁ የእግዚአብሄርን
መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፤ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል፡፡›› ይህ ማለት
ለእግዚአብሄር መንግሥት፣ ለጽድቁ፣ ለወንጌልና ለሌሎች ነፍሳቶች መዳን ከእርሱ
ቤተክርስቲያን ጋር ተባብረን እንኖራለን ማለት ነው፡፡ ጌታ ለውሃውና ለመንፈሱ
ወንጌል እንድንኖር ነግሮናል፡፡ ይህ ማለት ለእግዚአብሄር ጽድቅ ከኖርን
እግዚአብሄር ሁሉን ይሰጠናል ማለት ነው፡፡ እግዚአብሄር ለእናንተና ለእኔ የሰጠን
አስተማማኝ ተስፋ ነው፡፡ እግዚአብሄር ከእኛ ዳግመኛ ከተወለድነው ጋር
የተጋባው ቃል ኪዳን ይህ ነው፡፡ ልቦቻችንን ሰጥተን ለእግዚአብሄር ወንጌል
ብንኖር እግዚአብሄር የምንበላውን፣ የምንጠጣውንና የምንለብሰውን በመስጠት
በእርግጠኝነት ለሕይወታችን ዋስትናን ይሰጣል፡፡ እግዚአብሄር ቢያንስ በሥጋና
በመንፈስ ብልጥግና ውስጥ እንድንኖር ዋስትና ይሰጠናል፡፡
ውድ ክርስቲያኖች ለእግዚአብሄር ኑሩ፡፡ ስለ ሕይወታችሁ
ተጨንቃችኋልን? ለእግዚአብሄር ወንጌል ኑሩ፡፡ ለውሃውና ለመንፈሱ ወንጌል
ኑሩ፡፡ አእምሮዋችሁን በእግዚአብሄር ሥራ ላይ አድርጉ፡፡ ያንን ካደረጋችሁ
የወደፊት ሕይወታችሁ ዋስትና ተሰጥቶታል፡፡ ሰዎች እንደ መሆናችን ብዙ
የምንጨነቀው መቼ ነው? ምንም ያህል ትንሽ ቢሆኑም የሚያኖሩን ነገሮች እያለቁ
ሲሄዱ በጣም እንጨነቃለን፡፡ ይልቁንስ ሁሉም አልቆ ባዶ እጃችንን ብንቀር
እንረጋጋለን፡፡ የምንቆጥበው ምንም ነገር ስለሌለንና ያስቀመጥነው ምንም ነገር
ስለሌለን እንደገና ጌታን በማመን መሞከሩ በጣም ይቀለናል፡፡ ነገር ግን ሙሉ
በሙሉ ባዶ እጃችንን ሳንሆን ገናም በቀረችን ጥቂት ነገር ለመኖር ስንሞክር
ይበልጥ እንቅበጠበጣለን፡፡ የቀረችንን እንኳን ልናጣት እንደምንችል ስንፈራ ምን
ያህል ጭንቀታሞች እንሆናለን?
ውድ ክርስቲያኖች የቀረን አንዳች ነገር ይኑረንም አይኑረንም ለጌታና
ለወንጌል እንኑር፡፡ በጌታም እንመን፡፡ ያን ጊዜ ጌታ ባለን ላይ ሳይሆን አትረፍረፎ
ይሞላናል፡፡ ይህም ለወንጌል ስንኖር ጌታ አትረፍርፎ ስለሚሞላንና ያለንን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


175 ስለ ሕይወታችሁ አትጨነቁ፤ ነገር ግን በእግዚአብሄር ብቻ እመኑ

አብቃቅተን ስንኖርም ስለሚረዳን ነው፡፡


እንደዚያ ነው፡፡ የዛሬውን የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ በአእምሮዋችሁ
ያዙት፡- ‹‹አስቀድማችሁ የእግዚአብሄርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፤ ይህም
ሁሉ ይጨመርላችኋል፡፡›› ለእግዚአብሄር የምንኖር ከሆንን እግዚአብሄር
የምንፈልገውን ሁሉ ይሰጠናል፡፡
ልብስ የሚሰፋ አንድ ወንድም ነበር፡፡ ሰው ልብስ ሰፊ ሆኖ ብዙ ገንዘብ
ሊያገኝ አይችልም፡፡ አንድ ሙሉ ልብስ ለመስፋት ብዙ ሌሊቶችን ማሳለፍ
እንደነበረበት ነገረኝ፡፡ ስለዚህ ለቤተክርስቲያን ብዙ ሥራ በመስራቱ ገንዘቡ ሁሉ
አለቀበት፡፡ ያን ጊዜ ወደ እግዚአብሄር መጸለይ ጀመረ፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ሰዎች
ከሙሉ ልብሶች ይልቅ ብዙ የሥልጠና ልብሶችን አዘዙ፡፡ አንዳንድ ካምፓኒዎች
በብዙ መቶዎች ወይም በብዙ ሺህዎች ብዛት ያላቸው የሥልጠና ልብሶችን ማዘዝ
በመጀመራቸው ሥራውን ሲጀምር ብዙ ገንዘብ ማግኘት ጀመረ፡፡ ስለዚህ
አሁንም ድረስ ጌታን እያገለገለ መኖር ቻለ፡፡
እርሱ ሙሉ ልብሶችን ወይም የስልጠና ልብሶችን ቢሰፋም መኖር መኖር
ነው፡፡ ነገር ግን በተቸገሩ ጊዜ ወደ እግዚአብሄር በመጸለያቸው ጌታን ማገልገል
የቻሉ ብዙ ወንድሞች አሉ፡፡ ለጌታ የኖረ ማንኛውም ሰው ያ ልምድ አለው፡፡ እኛ
ጻድቃኖች ባለን ነገር ብቻ አንኖርም፡፡ ጌታ በሰጠው ነገር ጌታን እናገለግላለን፡፡
ምክንያቱም ጌታ አሟልቶልናልና፡፡ በእጃችን ላይ ባለነው ነገር ብቻ ብንኖር
ወዲያው ባዶዋችንን እንቀራለን፡፡
በብሉይ ኪደን ውስጥ ሰራፕታ በምትባል ስፍራ አንዲት መበለት ነበረች፡፡
በዚያን ዘመን እግዚአብሄር ዘንድ ዓመታቶችን የፈጀ ከባድ ድርቅ ተከስቶ ነበር፡፡
ሁሉም ነገር አልቆባት በማሰሮ ውስጥ ጥቂት እፍኝ ዱቄት ብቻ ተርፎዋት ነበር፡፡
ዱቄቱን በውሃ ስታቦካ የተገኘው ሊጥ የሁለት ወይም የሦስት ሰዎችን ረሃብ
የሚያስታግስ ብቻ ነበር፡፡ ዳቦ ለመጋገርም ሊጡን በመዳመጫ ዳጠችው፡፡
አይሁዶች የሚመገቡት ዳቦ ነበር፡፡ ሊጡን ይደፈጥጡታል፡፡ እሳቱ ነዶ ሲያልቅና
ፍሙ ብቻ ሲቀር ሊጡን እዚያ ላይ ያኖሩታል፡፡
ሴቲቱ እርስዋና ልጁዋ ለመጨረሻ ጊዜ የሚበሉትን እንደ ፓን ኬክ ያለ ዳቦ
ለመጋገር ስትዘጋጅ ከዚህ በኋላ እንደሚራቡ እያሰበች ነበር፡፡ ያን ጊዜ
የእግዚአብሄር ባርያ የሆነው ኤልያስ ተገለጠ፡፡
‹‹አንቺ ሴት አንዳች የሚበላ ነገር አለሽን?››
‹‹አዎ ይህን ያህል ዱቄት አለኝ፡፡››
‹‹እንግዲያውስ ያነን ጋግረሽ እንድበላው አቅርቢልኝ፡፡››

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


ስለ ሕይወታችሁ አትጨነቁ፤ ነገር ግን በእግዚአብሄር ብቻ እመኑ 176

ውድ ክርስቲያኖች የእግዚአብሄር ባርያ ያንን እንድታመጣለት ስለነገራት


አመጣችለት፡፡ ይህንን የመጨረሻ ምግብ ከልጅዋ ጋር እንደመትመገበው አስባ
ነበር፡፡ ያላትም ይህ ብቻ ነበር፡፡ የእግዚአብሄር ባርያ እንዲበላው ሰጠችው፡፡
መበለቲቱ ያላትን የመጨረሻውን ነገር ለእግዚአብሄር ባርያ ሰጠችው፡፡ ለእርስዋ
ተስፋ ያለ አይመስልም ነበር፡፡ ነገር ግን በወቅቱ አንድ የማይታመን ነገር ሆነ፡፡
የእግዚአብሄር ባርያ ከበላ በኋላ ጸለየ፡፡ ያን ጊዜ በማሰሮው ውስጥ ያለው ዱቄት
አላለቀም፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ይህንን መዝግቦዋል፡፡
ውድ ክርስቲያኖች መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል፡- ‹‹አስቀድማችሁ
የእግዚአብሄርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፤ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል፡፡››
ዳግመኛ ያልተወለዱ ሰዎች በዚህ ጥቅስ ከሌሎች ገንዘብን ያጭበረብራሉ፡፡ ይህ
በቀን ተቀን ሕይወት ውስጥ ብዙውን ጊዜ ይከሰታል፡፡ በተጨባጭ ግን
ነፍሳቶችን በእምነት እንዲኖሩና የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል እንዲያገለግሉ
መምራት የእግዚአብሄር ቃል እንጂ ማታለያ አይደለም፡፡ በትክክል ለጌታ
የምንኖር ከሆንን ጌታ በትክክል ለእኛ ያዘጋጅልናል፡፡ ይህንን እመኑት፤ ልታምኑት
ይገባችኋል፡፡
ውድ ክርስቲያኖች ከእኔ በኋላ ደግማችሁ በሉት፡፡ ‹‹ጌታ ሆይ በአንተ
አምናለሁ!›› ማለት ትችላላችሁ፡፡ እስከ አሁን ድረስ የኖራችሁት በራሳችሁ
ጉልበት ነውን? እንግዲያውስ ይበልጥ በእምነት እግዚአብሄርን የሙጥኝ ብላችሁ
ያዙት፡፡ አንድን ነገር እስከ መጨረሻው ድረስ የሙጥኝ ብላችሁ ብትይዙትም
ማለቁ አይቀርም፡፡ በጉልበታችሁ ልታቆሙት አትችሉም፡፡ ጌታ በእምነት
እንድንኖር የነገረን ለዚህ፡፡
ብዙም ኖረን ወይም አልኖረን ለጌታ በተሰጠ ልብ መኖርና ጌታን ማገልገል
ይኖርብናል፡፡ ያን ጊዜ ጌታ በእርግጥም የምትፈልጉትን ሁሉ ይሰጣችኋል፡፡ ጌታን
የምናገለግል ከሆነን ለእኛ የመስጠት ሐላፊነት አለበት፡፡ አትረፍርፎ ይሰጠናል፡፡
ምክንያቱም ሁልጊዜ በእኛ ይገለገላልና፡፡ እርሱ ሁሉን ቻይ አምላክ ስለሆነ ሌላ
አንዳች ነገር ባይኖርም ኪዳኑን ለመጠበቅ ሲል እንኳን በእርግጠኝነት
ይሞላናል፡፡
ሕይወታችን የተመሰረተው በእምነታችን ላይ እንጂ በፈቃዳችን ላይ
አይደለም፡፡ እኛ የእግዚአብሄር አገልጋዮች እንደዚሁም ወንድሞችና እህቶች ሁሉ
ለጌታ በኖሩ ጊዜ እግዚአብሄር ያደረገላቸውን በሚለማመድ እምነት ሊኖሩ
ይገባቸዋል፡፡ ለራሳችን የምንኖር ከሆንን እምነታችን ሊያድግ አይችልም፡፡ ለጌታ
ስንኖር በጌታ ላይ ያለን እምነት ቀስ በቀስ ማደግ ይችላል፡፡ ውድ ክርስቲያኖች

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


177 ስለ ሕይወታችሁ አትጨነቁ፤ ነገር ግን በእግዚአብሄር ብቻ እመኑ

የእግዚአብሄር በረከቶች በእምነት ለሚኖሩ ሰዎች ልክ እንደ ጉርሻ እንደሆነ


ታውቃላችሁን? ጉርሻ ከተለመደው ወይም ከሚጠበቀው በተጨማሪ የሚሰጥ
ነገር ነው፡፡
እግዚአብሄር ከደህንነቱ ባሻገር ብዙ ጉርሻዎችን ሰጥቶዋል፡፡ በሕይወት
የምንኖረው እግዚአብሄር ብዙ በረከቶችን እንደ ጉርሻ ስለሰጠን ነው፡፡ የሚገባንን
ብቻ እንጂ አንዳች ጉርሻ ባይሰጠን ኖሮ በሕይወት መኖር አንችልም፡፡
የሰራንበትን ብቻ የምንቀበል ከሆነ ሰነፎች ሁሉ አይሞቱም ነበርን? እግዚአብሄር
ብዙ ነገሮችን ጉርሻ አድርጎ ሰጥቶዋል፡፡ ያም የበረከቶቹ ድርሻ ነው፡፡ እኛም ጸጋን
ከሰጠን ከእግዚአብሄር ጋር አብረን እንኖራለን፡፡ ስለዚህ ባዳነን በእግዚአብሄር
በሚያምነው እምነት እንኖራለን፡፡
ውድ ክርስቲያኖች በእግዚአብሄር ካመንን እግዚአብሄር በውስጣችን
ይሰራል፡፡ በእግዚአብሄር እመኑ፡፡ አስቸጋሪ ቢሆንም በእግዚአብሄር እመኑ፡፡
እግዚአብሄር በእርሱ ብናምን እንደሚሰማን ተስፋ ሰጥቶናል፡- ‹‹አስቀድማችሁ
የእግዚአብሄርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፤ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል፡፡››
በሕይወት ስትኖሩ እግዚአብሄር ‹‹ይህንን ሁሉ›› እንዴት እንደሚሰጣችሁ
ተለማመዱ፤ ማለቴ እግዚአብሄር እንዴት እንደሚያሟላ እንዴት እንደሚሰጣችሁ
ልትለማመዱ ይገባችኋል፡፡ በእምነት ካልኖራችሁ በምህረቱ በኩል የሚመጡትን
የእግዚአብሄር ሙላት፣ ችሮታና በረከቶች እንዴት መለማመድ ትችላላችሁ?
ውድ ክርስቲያኖች በእምነት ኑሩ፡፡ ‹‹እግዚአብሄር ሆይ በአንተ አምናለሁ!
እንደምታለብሰኝ፣ እንደምትመግበኝ፣ ራቁቴን እንደማልኖር፣ እንዳላፍርም
እንደምታለብሰኝና በሕይወት እንድኖር እንደምታደርገኝ አምናለሁ፡፡
እንደምትመግበኝ አምናለሁ፡፡ ሕይወቴን እንድኖር እንደምትፈቅድልኝም
አምናለሁ፡፡››
እንደዚህ እመኑ፤ ካመናችሁ እግዚአብሄር ይሰጣችኋል፡፡ አምላካችን ያንን
ማድረግ የማይችል አምላክ ነውን? እርሱ መመገብ የማይችል አምላክ ነውን?
እግዚአብሄር ይህንን ሁሉ ለማድረግ ብርቱ የሖነ አምላክ ነው፡፡ ስለዚህ
የራሳችንን መለኪያዎች አስወግደን ሁሉን በሚችለው አምላክ ማመንና መታመን
አለብን፡፡ ቃሉን እመኑ፤ ታመኑ! እምነት በቃሉ መታመን ነው፡፡ ውድ
ክርስቲያኖች አስተዋላችሁን?

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


ስለ ሕይወታችሁ አትጨነቁ፤ ነገር ግን በእግዚአብሄር ብቻ እመኑ 178

አሁንም ድረስ ስለ ወደፊት ሕይወታችሁ ትጨነቃላችሁን?

አሁንም ድረስ ስለ ወደፊቱ ሕይወታችሁ ትጨነቃላችሁን? እኔም በኮሌጅ


ሳለሁ በተለይም ልመረቅ አካባቢ ብዙ ጭንቀቶች ነበሩብኝ፡፡ ገና አዲስ ገቢ
ሳለሁ ወደ ትምህርት ቤት የምሄደው ልክ እንደ ጎሽ እንስሳ ነበር፡፡ ምንም
የሚያስጨንቀኝ ነገር አልነበረም፡፡ ‹‹ሄይ ፓን ኬክ እንብላ፡፡›› ግድ አልነበረኝም፡፡
ነገር ግን በመጨረሻው ዓመት በሁለተኛው መንፈቀ ትምህርት መጨነቅ
ጀመርሁ፡፡ ‹‹በቅርቡ እመረቃለሁ፡፡ ኦ! ያን ጊዜ ምን አደርጋለሁ? ኦ…በእርግጥም
ተቸግሬያለሁ፡፡›› ስለዚህ ነገር ሳስብ በእርግጥም ትልቅ ችግር ነበር፡፤ የምግብ
ፍላጎቴ እንኳን ጠፍቶ ነበር፡፡
እንደ እውነቱ ከሆነ ከዳኑ በኋላ እንኳን ‹‹እንዴት እኖራለሁ?›› ‹‹እንዴት
እበላለሁ?›› ብለው የሚጨነቁት ተማሪዎች ብቻ ሳይሆኑ ሁሉም ሰው ሁሉ
ነው፡፡ ነገር ግን ይህ ዳግመኛ ለሚወለዱ ሰዎች አዲስ ጅማሬ ነው፡፡ ዳግመኛ
ከተወለድን ባለፈው ጊዜ ያደረግነውን፣ የነበረን የሥራ ዓይነትና የኖርነው ኑሮ
ዳግመኛ ከቁም ነገር የሚቆጠር አይደለም፡፡ ባለፈው ጊዜ ምንም ሆናችሁ
ብትኖሩም አሁን ዳግም ስለተወለዳችሁ አዲስ ጅማሬ መጀመር አለባችሁ፡፡ እኛ
አዲስ ዓመት እያመጣን ነው፡፡ አዲስ ዘመን!
በዘጸዓት 12 ላይ እንዲህ ተብሎዋል፡- ‹‹ይህ ወር የወሮች ሁሉ መጀመሪያ
ይሁናችሁ፤ የዓመቱም መጀመሪያ ወር ይሁናችሁ፡፡›› (ዘጸዓት 12፡2) እግዚአብሄር
ለእስራኤሎች ከባርነታቸው ሸሽተው ከግብጽ የወጡበትን ዘጸዓታቸውን
የሚያስታውሱበት አዲስ የዘመን መቁጠሪያ ሰጣቸው፡፡ ዘጸዓት የእስራኤላውያን
ታሪክ አዲስ ጅማሬ ነበር፡፡ እነርሱ የሞት ባህር የሆነውን ቀይ ባህር ተሻግረው
ወደ ተስፋይቱ ምድር የሚያደርጉትን የመጀመሪያውን እርምጃቸውን ጀመሩ፡፡
እነርሱ ከእንግዲህ ወዲህ የፈርዖን ሕዝብ አልነበሩም፡፡ በምትኩ የእግዚአብሄር
ሕዝብ ሆነዋል፡፡
ስለዚህ ዳግመኛ ከተወለድንበት ቅጽበት ጀምሮ እኛ አዲስ ፍጥረቶች ነን፡፡
ፈጽሞ የተለየ አዲስ ሕይወት መጀመር የሚገባን ለዚህ ነው፡፡ እንዲህ ተብሎ
ተጽፎዋልና፡- ‹‹እንግዲህ ክርስቶስ በአብ ክብር ከሙታን እንደተነሳ እኛም በአዲስ
ሕይወት እንድንመላለስ ከሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ በጥምቀት ከእርሱ ጋር
ተቀበርን፡፡›› (ሮሜ 6፡4)
‹‹ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር
አልፎአል፤ እነሆ ሁሉ አዲስ ሆንዋል›› (2ኛ ቆሮንቶስ 5፡17) ዳግመኛ ለተወለዱ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


179 ስለ ሕይወታችሁ አትጨነቁ፤ ነገር ግን በእግዚአብሄር ብቻ እመኑ

ሁሉ አዲስ ሆንዋል፡፡ አዳዲስ ነገሮችን እናጠናለን፡፡ አዳዲስ ነገሮችን ይዘን ወደ


ሥራ እንሰማራለን፡፡ ጌታን በአዳዲስ ነገሮች እናገለግላለን፡፡ በአዳዲስ ነገሮችም
እንኖራለን፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ በአዳዲስ ነገሮች እንኑር፡፡ በአንድ መልኩ ዳግመኛ
የተወለዱ ሰዎች ሕይወት በአጭሩ ያለፈው ሕይወታቸው ቅጥያ ይመስል
ይሆናል፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ ግን እግዚአብሄር ሲያየን ፈጽሞ የተለየ የሕይወት
መንገድና የአዲስ ሕይወት ጅማሬ ነው፡፡ ሁሉም አዲስ ነው፡፡
አንድ ጊዜ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አምነን ከሐጢያቶቻችን ሁሉ
ስለዳነን አዲስ ፍጥረቶች ነን፡፡ አሁን እናንተና እኔ አዲስ ፍጥረቶች ነን፡፡ አሁን
አሮጌው አልፎዋል፡፡ ድክመቶቻችሁ፣ ፍርሃታችሁና በሰው መንገዶች ላይ ብቻ
መደገፍ የሚያዘወትረው አሮጌው የሕይወት መንገዳችሁ በሙሉ አልፎዋል፡፡
አሁን እናንተ አዲስ ፍጥረት ሆናችኋል፡፡ አሁን የምንኖረው በእምነት ነው፡፡
ውድ ክርስቲያኖች! በዚህ ቁጥር ላይ እንደተጻፈው በእምነት እንኖራለን፡፡
‹‹ጻድቅ በእምነት ይኖራል፡፡›› መጀመሪያም በእምነት ነው፡፡ ሁለተኛም በእምነት
ነው! ሦሰተኛና አራተኛም እንደዚሁ በእምነት ነው፡፡ ስንወድቅ በእምነት
እንኖራለን፡፡ ስንደክም በእምነት እንኖራለን፡፡ በምንም ዓይነት ሁኔታ ውስጥ
ብንሆን በእምነት እንኖራለን፡፡ እምነት ማለት ይህ ነው፡፡ እምነት በሕይወት
እንድንኖር አድርጎናል! ትክክለኛው መልስ ይህ ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ በዛሬው
ቃለ ምንባብ ላይ ‹‹እንግዲህ ምን እንበላለን? ምንስ እንጠጣለን? ምንስ
እንለብሳለን? ብላችሁ አትጨነቁ፡፡ ለቀኑ ክፋቱ ይበቃዋል›› በማለት ይህንን
ምንባብ የነገረን ለዚህ ነው፡፡ ይህ ማለት ስለ ወደፊቱ አትጨነቁ ማለት
አይደለም፡፡ ለምን ምክንያቱም ጉዳዩ የጌታ ነውና፡፡ ጌታ ወደፊት ስለሚመጡት
ነገሮች እንዳንጨነቅ የነገረን ለዚህ ነው፡፡ ስለ ወደፊቱ ስለተጨነቅን ምን
የሚከናወን ነገር ይኖራል?
ጌታ ‹‹ነገ ለራሱ ይጨነቃልና ለነገ አትጨነቁ፤ ለቀኑ ክፋቱ ይበቃዋል›› ብሎ
ነግሮናል፡፡ ዛሬም ይሁን ነገ በእምነት ልንኖር ይገባናል፡፡ የወደፊቱን
በእግዚአብሄር ፊት ባለን እምነት እንገዳደረዋለን፡፡ እግዚአብሄርን ‹‹አምላክ ሆይ!
ይህንን አድርግልኝ፤ ያንን አድርግልኝ›› በማለት በእምነት እንጠይቀዋለን፡፡ ጸሎት
ሰው በእግዚአብሄርን በሚያምንበት እምነት መገዳደርና እርሱ ለእኛ
እንደሚያደርግልን ማመን ነው፡፡ እኛ ማድረግ የምንችለው ይህንን ብቻ ነው፡፡
ወደፊት ስለምናደርገው ነገር ያለን የራሳችን ፈቃድና ስለት እርባነ ቢስ ነው፡፡
ለወደፊት ሕይወታችን ወይም ለራሳችን የምንሰጠው ምንም ዋስትና የለንም፡፡
ምንም እርግጠኛ የሆነ ነገር የለም፡፡ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሄር የዛሬውን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


ስለ ሕይወታችሁ አትጨነቁ፤ ነገር ግን በእግዚአብሄር ብቻ እመኑ 180

የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርቶች የሰጠን ስለምንበላው፣ ስለምንጠጣውና


ስለምንለብሰው እንዳንጨነቅ ነው፡፡
ውድ ክርስቲያኖች እንዴት እንደምንኖር ሥጋችንም እንዴት እንደሚሆን
መጨነቅ አይገባንም፡፡ አንጨነቅ፡፡ ‹‹ከእናንተ ተጨንቆ በቁመቱ ላይ አንድ ክንድ
መጨመር የሚችል ማን ነው?›› እኔ ቁመቴ ይህን ያህል ነው፡፡ ነገር ግን
በመጨነቄ አንድ ሳንቲ ሜትር እንኳን ማደግ እችላለሁን? ‹‹መሆን የምፈልገው
ይህንን ነው!›› በማለቱ ሌሊቱን ሁሉ ስለዚህ ነገር ብጨነቅ ይሆናልን?
ስለተጨነቅን የሚሆን ምንም ነገር የለም፡፡ ዳቦ እናገኛለን ወይም አንዳች ገንዘብ
እናገኛለን?
ስለ ምንም ነገር መጨነቅ አይገባንም፡፡ ነገር ግን በነገር ሁሉ በጸሎትና
በምልጃ ልመናችንን ለእግዚአብሄር ማቅረብ ይገባናል፡፡ በትጋት ጸልዩ፡፡
በእግዚአብሄር አምናችም ጠይቁ፡፡ ማድረግ ያለብን ይህንን ነው፡፡ ማድረግ
ያለብን ማመንና መጸለይ ነው፡፡ ከተጨነቅን የእግዚአብሄርን እርዳታ እንጠይቅ፡፡
በእግዚአብሄር እመኑ፡፡ አጋር ክርስቲያኖች በእግዚአብሄር በማመን
ሕይወታችሁን ኑሩ፡፡ ገባችሁ? --አዎ--፡፡ ካመንን በሕይወት እንኖራለን፤
ካላመንን እንሞታለን፡፡
ውድ ክርስቲያኖች በእግዚአብሄር ካላመናችሁ ትሞታላችሁ፡፡ ባሉዋቸው
ሐብቶች ሁሉ ላይ ከተደገፋችሁ እነርሱም ያልቃሉ፡፡ የአተር ልባስ ሲከፈት
አተሮቹ እንደሚበተኑ ሁሉ ሁሉም ይበተናል፡፡ አንድ የአተር ልባስ ስንት አተሮች
ይይዛዛል? አንድ መቶ አተሮች ይይዛል? አይደለም፡፡ የሚይዘው አራት ወይም
አምስት አተሮች ነው፡፡ ውድ ክርስቲያኖች ስለዚህ ነገር እናስብ፡፡ ባላችሁ
ሥልጣን፣ ችሎታ፣ ጤንነትና ሐብት ብቻ ሙሉውን ሕይወታችሁን መኖር
ትችላላችሁን? ለልጆቻችሁ፣ ለወላጆቻችሁ ያሉባችሁን ሰብዓዊ ግዴታዎች
በሙሉ ማድረግ ትችሉ እንደሆነ ወይም እንዳልሆነ ማስላት አለባችሁ ማለቴ
ነው፡፡ ውድ ክርስቲያኖች ማስላት ትችላላችሁን? ምንም ያህል ሐብት ቢኖር
ሕይወታችንን የምንኖረው በዚያ ብቻ ከሆነ መኖር አንችልም፡፡ ታዲያ
የሚያስፈልገን ምንድነው? በእግዚአብሄርና በቃሉ የሚያምን እምነት
ያስፈልገናል፡፡
በጩኸት ልነግራችሁ የምፈልገው አንድ ነገር አለ፡፡ ያም በእግዚአብሄር
ብቻ እንድታምኑ ነው፡፡ እግዚአብሄርን በዓይኖቻችሁ ልታዩት ባትችሉና በእርሱ
ማመንም በጣም መሰረተ ቢስ ቢመስላችሁ እንኳን በእርሱ ልታምኑ
ይገባችኋል፡፡ በእርሱ ብቻ እመኑ በቃ፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


181 ስለ ሕይወታችሁ አትጨነቁ፤ ነገር ግን በእግዚአብሄር ብቻ እመኑ

መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል፡- ‹‹እምነትም ተስፋ ሰለምናደርገው ነገር


የሚያስረግጥ የማናየነውንም ነገር የሚያስረዳ ነው፡፡ ለሽማግሌዎች
የተመሰከረላቸው በዚህ ነውና፡፡›› (ዕብራውያን 11፡1-2) በዓይን የሚታይ ማስረጃ
ባይኖር በእጅ የሚጨበጥ አመርቂ ነገር ባይኖር ማንኛውንም ነገር በእምነት
እግዚአብሄርን መጠየቅ አለብን፡፡ ‹‹እግዚአብሄር ሆይ ስጠኝ፡፡ አምናለሁ!
የምፈልገውን ሁሉ--በሕይወቴ ችግሮች የሆኑብኝን ምግብ፣ ልብስ፣ መጠለያ
ስጠኝ፡፡›› በእርሱ አምናችሁ የእርሱን እርዳታ ለማግኘት ከጸለያችሁ እርሱን
መልሶችን ይሰጣችኋል፡፡ ነገር ግን ካላመናችሁና በራሳችሁ ጉልበት በስሌቶቻችሁ
ላይ በመደገፍ የምትኖሩ ከሆናችሁ ትሞታላችሁ፡፡ ያላችሁን ጥቂት ነገር እንኳን
አጥታችሁ እውነተኛ ለማኝ ትሆናላችሁ፡፡
‹‹ጻድቅ በእምነት ይኖራል›› የሚለው ጥቅስ ጻድቅ ሰው በሕይወት መኖር
የሚችልበት ብቸኛው መንገድ በእምነት ነው ማለት ነው፡፡ ‹‹ጻድቅ በእምነት
ይኖራል፡፡›› (ሮሜ 1፡17፤ዕብራውያን 10፡38) ውድ ክርስቲያኖች ታምናላችሁን?
እምነት የሌሎችን አንዳች ነገር አይፈልግም፡፡ እምነታችሁን ለሌላ ሰው ለመስጠት
ብላችሁ አታሳድጉትም፡፡ እምነቱ የራሳችሁ ነው፡፡
በሕይወት መኖር የምንችለው በእግዚብሄርና በእግዚአብሄር ቃል በማመን
ብቻ ነው፡፡ ይህ የሚሰራው በእግዚአብሄርና በቃሉ ላይ ባለን እምነታችን
መሰረት ነው፡፡ በእግዚአብሄር ቃል ማመን፣ እግዚአብሄርን በማመን መጸለይና
ስለ አንዳች ነገር በመጨነቅ ፋንታም የእርሱን ፈቃድ ተከትለን መኖር ይበልጥ
አስፈላጊ ነው፡፡ 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


ለቀኑ ችግሩ ይበቃዋል
‹‹ ማቴዎስ 6፡34 ››
‹‹ነገ ለራሱ ይጨነቃልና ለነገ አትጨነቁ፡፡ ለቀኑ [ችግሩ] ይበቃዋል፡፡››
(ከእንግሊዝኛው መጽሐፍ ቅዱስ የተተረጎመ፡፡)

ጌታ እንዲህ አለ፡- ‹‹ነገ ለራሱ ይጨነቃልና ለነገ አትጨነቁ፡፡ ለቀኑ [ችግሩ]


ይበቃዋል፡፡›› የእምነት ሕይወትን ለሚኖሩ ጻድቃኖች እጅግ ትልቁ ጠላት
ጭንቀት ነው፡፡ እንዲውም ለዛሬ መጨነቅ ሳይሆን ለወደፊቱ መጨነቅ ነው፡፡
ለእኛ ለጻድቃኖች ስለ ወደፊቱ መጨነቅ ከጉድለቶቻችንና ከድክመቶቻችን
የሚመነጭ ነው፡፡ ስለዚህ ‹‹አሁን እኔ ማለት እንዲህ ነኝ፤ ታዲያ እንዴት ስለ
ወደፊቱ ላልጨነቅ እችላለሁ?››
ራሳችንን ስንመለከት መጨነቃችን የተለመደ ነው፡፡ ነገር ግን የዛሬዎቹን
ጉድለቶቻችንን አይተን አንዳች የተሻለ ዕጣ ፈንታ ሊኖረን የሚችል
የማይመስለንን ራሳችንን ስንመለከት ስለዚሁ ነገር ከመጨነቅ በቀር ልናደርገው
የምንችለው ነገር የለም፡፡ ይህም በእምነት ሕይወታችን ተስፋ እንድንቆርጥ
ሊያደርገን ይችላል፡፡ ለዚህም ምክንያቱ ራሳችንን በሚገባ እናውቃለን ብለን
ስለምናስብና የወደፊቱ የተሻለ ይሆናል ለማለትም ዋስትና ስለሌለ ተስፋ በሌለ
ጊዜ ጭንቀት ውስጥ ስለምንወድቅ ነው፡፡ እነዚህ ጭንቀቶችም እምነታችንን
ክፉኛ ያደርቁታል፡፡ ‹‹እምነቴን ልተወውን?›› በሚሉት ገዳይ ጭንቀቶች ላይ
እንድንወድቅ ያደርጉናል፡፡
ጌታችን ግን እንዲህ ብሎዋል፡- ‹‹ነገ ለራሱ ይጨነቃልና ለነገ አትጨነቁ፡፡
ለቀኑ [ችግሩ] ይበቃዋል፡፡›› አሁን የሚጎድለን አንዳች ነገር ካለ በየቀኑ
የሚጎድለንን በየቀኑ እንጋፈጠዋለን፡፡ ነገ ስለ ራሱ ነገሮች ይጨነቃል፡፡ ለቀኑም
ችግሩ ይበቃዋል፡፡
የራሳችንን ጉድለቶችና ድክመቶች በመመልከት ጭንቀት ውስጥ ስንወድቅ
ምን ይከሰታል? ትንሽ እርሾ ዳቦውን በሙሉ እንደምታፋፋው ሁሉ የእኛ
የሰዎችና የጻድቃንም እንኳን ልቦቻችን በጭንቀት ጥላ ይሸፈናሉ፡፡
ድካም የሌለበት ሰው የለም፡፡ ሁሉም አለበት፡፡ ራሳችንን 100%

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ለቀኑ ችግሩ ይበቃዋል 183

ብንመለከት ሰው አሁን ስላለበት ሁኔታውና ስለ ወደፊቱ የሚያስበው ከ100%


10% ነው ብለን እናስብ፡፡ ከ100% 10%ቱ ችግር ውስጥ ያለ ነው፡፡ ቀሪው 90%
ግን ደህና ነው፡፡ ሆኖም ከዚህ 10% የተነሳ ልንጨነቅባቸው የሚያስፈልጉን
ነገሮች ብቻ ያሉብን መስሎ ይታየናል፡፡ ይህ 10% ጎዶሎዎች ደካሞች፣ ሁልጊዜም
ስህተቶችን የምንሰራ፣ አንዳች ነገር ማድረግ የማንችልና የወደፊቱም ቢሆን
በትክክል ምንም የተሻለ እንዳልሆነ በማሰብ 90% ይቆጣጠረዋል፡፡ ከዚህ የተነሳ
ይህ ምንም ነገር ማድረግ የማንችል ማለትም ደካማ ሰዎች ያደርገናል፡፡
ነገር ግን ጌታችን በተጨባጭ እንዲህ ብሎዋል፡- ‹‹ነገ ለራሱ ይጨነቃልና
ለነገ አትጨነቁ፡፡ ለቀኑ [ችግሩ] ይበቃዋል፡፡›› ጌታ እዚህ እንዲህ ማለቱ ነው፡፡
‹‹የሚጎድላችሁ አንዳች ነገር አለ? ከጎደላችሁ ነገር የተነሳ ዛሬ ብትቸገሩ ያ በቂ
ችግር ነው፡፡ ወደፊት ስለሚጎድለው ነገር መጨነቅ አይኖርባችሁም፡፡
የወደፊቶቹን ችግሮች ወደ አሁኑ አምጥታችሁ በተስፋ አትቸገሩ፡፡›› ጌታ ነገ ስለ
ራሱ እንደሚጨነቅ ነግሮናል፡፡
በዚህ ትምህርት ውስጥ ያለው ምንድነው? ሕይወታችንን 100% አድርገን
ስናየው ከ100% የሚያስጨንቀን 10% ቢኖር በቀኑ ውስጥ መጨነቅ
የሚያስፈልገን በዚያ መጠን ብቻ ነው፡፡ ይህ ማለት ደካማ የሆንበት ወይም
የጎደልንበት አንዳች ነገር የለም ማለት አይደለም፡፡ ሁላችንም ያ አለብን፡፡ ነገር
ግን ድክመቱ ከተገለጠ መጨነቅ የሚያስፈልገን ድክመቱ ለቀኑ በተገለጠባቸው
አካበቢዎች ብቻ ነው፡፡ የወደፊት ጭንቀቶችን ወደ ዛሬው አምጥተን አሁን
በተስፋ የምንጨነቅበት ምንም ምክንያት የለም፡፡ ጌታችን እኛ አንዳች ነገር
ማድረግ የማንችል ስንኩል ሰዎች እንደሆንን በማሰብና ከእንግዲህ ወዲህ
የእምነት ሕይወትን መኖር እንደማንችል ተስፋ ስለቆረጥን ራሳችንን በመጣል
በራሳችን መበሳጨት እንደማያስፈልገን እየነገረን ነው፡፡
እናንተና እኔ ጻድቃን ሰዎች ነን፡፡ ነገር ግን በነገር ሁሉ ፍጹማን
አይደለንም፡፡ ሁሉም ሰው እንከኖችና ድካሞች አለበት፡፡ ይህ በመጀመሪያ
ሲገጥመን ገና ዳግመኛ የተወለድን ከሆንን ችግር የለውም፡፡ ለምን? ምክንያቱም
ገና ተስፋ ስላለን ደህና ነው፡፡ ነገር ግን የእምነት ሕይወታችንን በመኖር ስንቀጥል
ከዚያ ወዲያ ደህና አይሆንም፡፡ የእምነትን ሕይወት ስለምንኖር ሥጋችን
አይለወጥም፡፡ ጳውሎስም እንኳን ጉድለቶች የሉብኝም ብሎ መናገር አልቻለም፡፡
በፋንታው ጳውሎስ እንዲህ አለ፡- ‹‹እኔ ምንኛ ጎስቋላ ሰው ነኝ! ለዚህ ሞት
ከተሰጠ ሥጋ ማን ያድነኛል?›› (ሮሜ 7፡24) እርሱም ጭንቀቶችና ድካሞች
እንደነበሩበት ማወቅ እንችላለን፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


184 ለቀኑ ችግሩ ይበቃዋል

ስለዚህ የሚያስጨንቀን ነገር ሲኖር ወደፊት የሚሆነውን አምጥተን


በጭንቀት ሸክም መሞት የለብንም፡፡ በአንዳንድ ችግሮች ወይም በድክመቶቻችን
ስንጨነቅ ከጉድለታችን የተነሳ የእምነት ሕይወታችንን መተው ወይም መሞት
እንደሚሻል ያሳየናል፡፡ ጌታችን የሰጠን የማደፋፈሪያ ቃል ይህ ነው፡፡ ‹‹ነገ ለራሱ
ይጨነቃልና ለነገ አትጨነቁ፡፡ ለቀኑ [ችግሩ] ይበቃዋል፡፡›› በዚህ ትምህርት
በማመን ደፋሮች መሆን እንችላለን፡፡
እኛ ጻድቃኖች ለእግዚአብሄርና ለጽድቁ መኖር ይገባናል፡፡ እኛ ጻድቃኖች
የራሳችሁን የሆኑ አሉታዊ ጎኖች ቢኖሩንም ከእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ጋር
በምንተባበርበት ጊዜ ሕይወታችን ውብ ይሆናል፡፡ እኛ የእግዚአብሄር አገልጋዮች
ብዙ ጉድለቶች ጭንቀቶችና ድካሞች አሉብን፡፡ ነገር ግን በዚያ ምክንያት በእነርሱ
ተጨንቀን ወደፊት መጓዝ አይኖርብንምን? እንደዚያ አይደለም፡፡ ስለ እነርሱ
መጨነቅ አቁመን ቃሉን በማመን ወደፊት እንዘልቃለን፡፡
ድክመቶቻችንን ለመደበቅ ምንም ያህል ጠንክረን ብንሞክርም ራሳችንን
መለወጥ እንደማንችል እናውቃለን፡፡ ከዚሀ የተነሳም የእምነት ሕይወታችን
ልንተወው እንችላለን፡፡ ጌታችን ‹‹ለምን ትጨነቃላችሁ? ነገ እንደገና
ስለሚከሰቱት ነገሮች አስቀድማችሁ አትጨነቁ፡፡ በዚያ ምክንያትም አትቸገሩ፡፡
ለዚያ ቀን መቸገሩ በቂ ነው›› ያለን ለዚህ ነው፡፡ ዛሬ ምንም ተስፋ እንደሌለን
በማሰብ በዚያ ምክንያት መሞት የለብንም፡፡ ወይም የጭንቀቶችን ከባድ ሸክም
በመሸከም የእምነት ሕይወታችንን መተው ወይም ማዘንና ብርታታችንን ማጣት
ወይም መሞት የለብንም፡፡
እናንተና እኔ የሥጋ ድካሞች አሉብን፡፡ ለቀኑ የአንድ ዕለት ችግር በቂ
ነው፡፡ የወደፊት ችግርን በአንድ ጊዜ መሸከምና መሞት አስፈላጊ አይደለም፡፡
ፍጹማኖችን ስንመለከት አንዳንድ ጊዜ በወደፊቱ ተስፋ አድርገው ያልተጓዙበትን
መንገድ ይተዉታል፡፡ ራሳቸውን ተመልክተው እንደዚህ ይቆጥራሉ፡- ‹‹እኔ
እንደዚህ ዓይነት ሰው ነኝ፤ በእርግጥም ለጌታ ሥራና ለጌታ መንግሥት የበቃሁ
አይደለሁም፤ የእምነትን ሕይወት መኖር በተፈጥሮዬ ውስጥ የለም፡፡›› ይህ 10%
ጭንቀት ተስፋ እንዲቆርጡ ሊያደርጋቸው ይችላል፡፡ ውሎ አድሮም ‹‹እነዚህ
ለዚህ የበቃሁ ስላልሆንሁ የእምነትን ሕይወቴን ልተወው ነው›› በማለት የእምነት
ሕይወታችንን ይተዉታል፡፡
ስለዚህ ይህ የዲያብሎስ ዕቅድ እንደሆነ ልታውቁ ይገባችኋል፡፡ ጌታ በዚህ
ጭንቀት ውስጥ እንዳንወድቅ እንዲህ ብሎናል፡- ‹‹ነገ ለራሱ ይጨነቃልና ለነገ
አትጨነቁ፡፡ ለቀኑ [ችግሩ] ይበቃዋል፡፡›› እኛ በሥጋችን ፍጹም ባንሆንም

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ለቀኑ ችግሩ ይበቃዋል 185

ኢየሱስ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ስለደመሰሰልን ማድረግ የሚኖርብን በየቅጽበቱ


አሁን የሚገጥሙንን ችግሮች መቋቋም ብቻ ነው፡፡ በእርግጥ የምንቸገርበት ነገር
ካለ ለዚያ ቀን መቸገር በቂ ነው፡፡ አንዳንድ ጊዜ 10% ጭንቀት የእምነት
ሕይወታችንን ቀሪውን 90% በሙሉ ስለሚሸፍን ተስፋ መቁረጣችን እርግጥ
ነው፡፡ ነገር ግን እምነታችንን በሙሉ ከማቃጠላቸው በፊት ትናንሾቹን የጭንቀት
እሳቶች ማጥፋት አለብን፡፡ ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ በተጠመቀ ጊዜ
ድክመቶቻችንንና ጉድለቶቻችንን በሙሉ ከሐጢያቶቻችን ጋር አብሮ እንደወሰደ
ደግመን ማረጋገጥ ይኖርብናል፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ በማቴዎስ 6፡34 ላይ የተናገረውን በጥንቃቄ ማድመጥ
አለብን፡፡ ስለ ራሱ በጥልቀት የሚያስብ ጻድቅ የሆነ ሰው የጌታን ትምህርት
በጥንቃቄ ማድመጥ አለበት፡፡ ኢየሱስ ስለ ነገ የነገረንን በጥኝቃቄ መመልከት
አለብን፡፡ እርሱን ለነገ መመልከት፣ ስለዚያ መጨነቅ፣ የእርሱን የእምነት ሕይወት
መተው የሚባል እንዲህ ያለ ነገር መኖር የለበትም፡፡ ዛሬ ቢጎድለን ዛሬ ትንሽ
እንቸገራለን፡፡ ነገ የሚጎድል አንዳች ነገር ካለ ነገም ትንሽ እንቸገራለን፡፡ ‹‹ኦ
አይሆንም፡፡ ኢየሱስን መከተል አይቻለኝም›› እንደሚልና ራሱን እንደ ይሁዳ
እንደሚገድል ፍጹም ሰው መሆንና ሞኝ ክርስቲያኖች ወይም የእግዚአብሄር
ሰራተኞች መሆን የለብንም፡፡ ምን እያልሁ እንደሆነ ተረዳችሁን?
እንደ እውነቱ ከሆነ ስለ ወደፊቱና ስለ ነገ የምንጨነቅባቸው አካባቢዎች
አሉን? በእርግጥም አሉ፡፡ እጅግ ትልቁ ራሳችንን መመልከትና ስለ እርሱ መጨነቅ
ነው፡፡ እኛ ሰዎችና በተለይም በእነርሱ መካከል ያለን ጻድቃኖች ስለሆንን ብዙ
እንጨነቃለን፡፡ ስለ ነገ ስንጨነቅ መንፈሳዊ ሞት እንሞታለን፡፡ አሁኑኑ
እንሞታለን፡፡ ነገን ሳንኖር ዛሬን መሞት በእርግጥም ሞኝነት ነው፡፡
እምነታችንን የሚያሰናክሉት የዓለም ጭንቀቶች ናቸው፡፡ ስለ ነገ መጨነቅ
ነው፡፡ ይህ በልቦቻችን ውስጥ ደብቀን ለማንም የማንናገረው ጭንቀት ነው፡፡ ስለ
ዛሬው ድክመቶችና ጉድለቶች መጨነቅና ነገም ይህንኑ መድገም ያደክመናል፡፡
‹‹ስለዚህ ነገር ለማንም አልናገርም›› በማለት ሸክሙን ብቻችንን ተሸክመን
ብቻችን እንሞታለን እንዴ? ያ የእግዚአብሄር ፈቃድ አይደለም፡፡
ወደ እግዚአብሄር መንግሥት በሚጓዘው የመናኝ ጉዞ መጽሐፍ ውስጥ
እንዳለው እኛም መናኞች ነን፡፡ ጴጥሮስም እንደዚሁ ቅዱሳኖችን ‹‹እንግዶችና
መጻተኞች›› (1ኛ ጴጥሮስ 2፡11) ብሎ ጠርቶዋቸዋል፡፡ እኛ ነፋስ እንደሚያልፍ
በዚህ ዓለም ላይ የምንኖር ወደ እግዚአብሄር መንግሥት የምንጓዝ መጻተኞችና
ተጓዦች ነን፡፡ አንድ ተጓዥ በየቅጽበቱና በየቀኑ ችግር ይገጥመዋል፡፡ ‹‹የት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


186 ለቀኑ ችግሩ ይበቃዋል

እተኛለሁ፤ የት አርፋለሁ›› ብለን የምንጨነቅ ከሆንን ተጓዥ መንገደኞች መሆን


አንችልም፡፡ ችግራችንን ቀደም ብለን ጎትተን አምጥተን በአንድ ጊዜ በሁሉ
ተቸግረን መሞት ጠቢብነት አይደለም፡፡ በልባችን ‹‹ነገ ለራሱ ይጨነቃልና ለነገ
አትጨነቁ፡፡ ለቀኑ [ችግሩ] ይበቃዋል፡፡›› ብለን መጮህ አለብን፡፡
‹‹ይህ እውነት ነው፡፡ የጌታችን ትምህርት እውነት ነው፡፡ ትክክልም ነው፡፡
ጌታችን ችግር ሲመጣ በየቀኑ ልጋፈጠው እንደሚገባኝና የወደፊቱን ችግር
አምጥቶ አሁን መቸገር ጠቢብነት እንዳይደለ አስተምሮኛል፡፡ በእርግጥም ጌታ
እንዳስተማረው በየቀኑ ችግሮቼን እጋፈጣለሁ፡፡ እግዚአብሄር ምንም ዓይነት
ችግር እንዲመጣብኝ ከፈቀደ በፈቀደበት ቀን ችግሩን እጋፈጣለሁ›› በማለት
በእምነት ልንመሰክር ይገባናል፡፡
ነገ ምን እንደሚሆን አናውቅም፡፡ ምንም ያህል ትልቅ ጉድለት ቢከሰትም
ምን ያህል አስቸጋሪ እንደሚሆን አይታወቅም፡፡ ጭንቀት በየቀኑ ይከሰት
ይሆናል፡፡ ነገር ግን ከዚህ ጭንቀት የተነሳ የጌታን ፈቃድ እንደማታደናቅፉ ተስፋ
አለኝ፡፡ እኛ ጻድቃኖች ቢያንስ 90% በጌታ ፈቃድ እንኖራለን፡፡ በድክመቶቻችን
ውስጥ የተቀበረው የእኛ የሆነው 10% ብቻ ነው፡፡ ሰው ሁሉ በ10% ድካሙ
ውስጥ ተቀብሮዋል፡፡ ስለዚህ በዚያ ምክንያት መሞት አይገባንም፡፡ በዚያ
ምክንያት ራሳችንን መግደል አይኖርብንም፡፡ እንዲህ ተብሎ ተጽፎዋል፡- ‹‹ነገ
ለራሱ ይጨነቃልና ለነገ አትጨነቁ፡፡ ለቀኑ [ችግሩ] ይበቃዋል፡፡›› የቀኑን ችግር
ብቻ መቸገር በቂ እንደሆነ እርግጠኞች ናችሁን? አዎ እርግጠኞች ነን፡፡
ውድ ክርስቲያኖች ተቸግራችኋልን? ጭንቀት አለባችሁን? -አዎ-፡፡ ዛሬ
ተቸግረን ከሆነ ለዛሬ ብቻ መቸገር አለብን፡፡ ከዚያ ያበቃል፡፡ ነገ አዲስ ቀን
ነው፡፡ ይህንን ለቅዱሳን ሁሉና ለወንድና ሴት አገልጋዮች እላለሁ፤ ጌታ እንዲህ
ነግሮናል፡፡ ‹‹ነገ ለራሱ ይጨነቃልና ለነገ አትጨነቁ፡፡ ለቀኑ [ችግሩ]
ይበቃዋል፡፡›› ይህ እንዴት ያለ ትልቅ እውነት ነው? ይህ ምክር በጣም ክቡር
ነው!
ጌታችን ይህንን ባይናገር ኖሮ አሁን ባሉን ድክመቶቻችን ታስረን እንቀር
ነበር፡፡ ‹‹ወደፊትም ያንኑ ነገር ማድረግ አለብኝ›› በማለት የወደፊት
ድክመቶቻችንን በመጠበቅ ባጥለቀለቁን ጭንቀቶች የተነሳ እንሞት ነበር፡፡
የአስቆሮቱ ይሁዳ የነበረው ጥርጣሬም ይኸው ነበር፡፡ ይሁዳ ኢየሱስ
በተፈረደበት ጊዜ ተጸጸተ፡፡ ከዚያም ሰላሳውን ብር በቤተ መቅደስ ውስጥ በትኖ
‹‹እንደዚህ መሞት ያለብኝ ሰው ነኝ›› በማለት ሄዶ ራሱን ሰቀለ፡፡ በዚህ የታመነ
መስሎት ይሆን? አይደለም፡፡ ያ የጌታችን ፈቃድ አይደለም፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ለቀኑ ችግሩ ይበቃዋል 187

ላደረጋችሁት ነገር ሐላፊነትን ለመውሰድ ራሳችሁን መግደል በጌታ ፊት


መታዘዝን ለማቅረብ ብቸኛው መንገድ አይደለም፡፡ ‹‹ለቀኑ ችግሩ ይበቃዋል፡፡››
ሕይወታችን አስቸጋሪና እንከን ያለበት ነው፡፡ ሕይወታችን እንደዚህ ነው፡፡
ፍጹማን ባለመሆናችን መቸገር ካለብን እንከናችን ለተገለጠበት ቅጽበት ብቻ
መቸገር ይኖርብናል፡፡ ቀድመው ችግር ውስጥ በመግባት እንደሚሞቱ ወይም
የወደፊቱን በመፍራት ዛሬ እምነታቸውን እንደሚተዉ ሰዎች እንደማትሆኑ ተስፋ
አደርጋለሁ፡፡
የራሳችን ጌቶች መሆን የለብንም፡፡ የሁላችንም ብቸኛው ጌታ ኢየሱስ
ነው፡፡ የእምነትን ሕይወት አብዝተን በኖርን መጠን ብቁ አለመሆናችን ይበልጥ
የሚታወቀን መሆኑ ትክክል ነው፡፡ ነገር ግን ነገ ስለሚገጥመን ነገር መጨነቅ
የለብንም፡፡ ነገ ነገ ነው፡፡ አሁን ደግሞ አሁን ነው፡፡
ላካፍላችሁ የምችለው ነገር ይህንን ብቻ ነው፡፡ አንድ ነገር ገብቶዋችሁ
ከሆነ ስብከቴ የተሳካ እንደሆነ አምናለሁ፡፡ አንዱን ትምህርት ሁልጊዜም
በስብከት ውስጥ የምደጋግመው ለዚህ ነው፡፡
እኛ ስለ ነገ በመጨነቅ የምንሞት ሰዎች መሆናችን እውነት ነው፡፡ እናንተና
እኔ በሥጋዊ አስተሳሰቦቻችን ውስጥ ብቻ ከሆንን እንደዚህ ዓይነት ሰዎች ነን፡፡
ነገር ግን እንደዚያ የሆነው ጌታችን በውሃውና በመንፈሱ ስላዳነን ነው፡፡ እንዲህ
በማለትም መክሮናል፡- ‹‹ነገ ለራሱ ይጨነቃልና ለነገ አትጨነቁ፡፡ ለቀኑ [ችግሩ]
ይበቃዋል፡፡›› ጌታችን ከጭንቀቶቻችንና ከጉድለቶቻችን አድኖናል፡፡ እናንተንና
እኔን አድኖናል፡፡ ውድ ክርስቲያኖች ይህ ትክክል አይደለምን? --አዎ--፡፡
የእምነት ሕይወታቸውን የተዉ ሰዎች ወደፊት ምን ሊሆን እንደሚችል
አርቀው በመመልከት አስቀድመው ይጨነቃሉ፡፡ የእምነት ሕይወታቸውንም
ይተዋሉ፡፡ እንደ እነዚህ ዓይነት ሰዎች መብዛታቸው አይቀርም፡፡ ጌታችን ይህንን
የተናገረው ለዚህ ነው፡፡ ‹‹ነገ ለራሱ ይጨነቃልና ለነገ አትጨነቁ፡፡ ለቀኑ [ችግሩ]
ይበቃዋል፡፡›› ለዚህ ቀን መቸገር በሚያስፈልገን ነገር ለዛሬ ብቻ መቸገር አለብን፡፡
ያን ያህል ችግር የሌለበት ሰው የለም፡፡ ጌታ አምላክ እኛን ጻድቃኖችን ችግራችንን
ሁሉ በእምነት እንድናሸንፍ አድርጎናል፡፡ ችግሩ የመጣው ከራሳችን ጊድለቶች
ይሁን ወይም ጌታ ከፈቀደው ስደት የተነሳ ለዚያ ቀን ችግሮቻችንን መቸገር
ይኖርብናል፡፡ ስለ እነርሱ አስቀድመን የምንጨነቅበት ምንም ምክንያት የለም፡፡
እምነት ይህ ነው፡፡ ጌታችን ድክመቶቻችንን ሁሉ ወስዶዋል፡፡ ጌታችን እኛን
ያዳነን ከሐጢያቶቸችን ሁሉ ብቻ ሳይሆን ከጭንቀቶቻችንም ነው፡፡ ይህንን
ስናምንና ጌታን ስንከተል ፈጽሞ ጭንቀቶች፣ አሳቦች፣ ፍርሃት ወይም ሐዘን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


188 ለቀኑ ችግሩ ይበቃዋል

እንደሌለ ይሰማናል፡፡
ዛሬ ይህ ትምህርት ባይኖረን ኖሮ ‹‹ኦ! አሁን ተስፋ ቆርጫለሁ፡፡ ኦ አሁን
እሞታለሁ!›› እንደምንል የታወቀ ነው፡፡ የጌታ ምጽዓት ሲቃረብ እንዲህ ያሉ ብዙ
ሰዎችን እንደምናይ እርግጠኛ ነኝ፡፡ ለዚህም ምክንያቱ የዚህ ዘመን ተስፋ ሰውን
ሁሉ ለጉድለቶች እንዲጋለጥ እያደረገው መሆኑ ነው፡፡ አለም እየተበጠበጠና
ለመኖርም አስቸጋሪ እየሆነ ስለመጣ ጭንቀቶቻችን ይጨመራሉ፡፡ ነገር ግን
የወደፊቱን ጭንቀት አስቀድማችሁ ዛሬ መጨነቅና ዛሬ መሞት የለባችሁም፡፡ ስለ
ነገዎቹ ችግሮች ነገ እንደሚጨነቁ ሰዎች እንደምትሆኑ ተስፋ አደርጋለሁ፡፤ ለቀኑ
ችግሩ የሚበቃው መሆኑን የምታምኑ ሰዎች እንደምትሆኑም ተስፋ አለኝ፡፡
ችግሮችና ጭንቀቶች ለዘላለም አይቆዩም፡፡ የሐጢያት ይቅርታን ለተቀበልን
ሰዎች ለዘላለም የሚዘልቁት ጌታ፣ ደህንነትና መንግሥተ ሰማይ ናቸው፡፡
ጭንቀቶች ጊዜያዊ ስለሆኑ አይዘልቁም፡፡ ቀኑ ብራ ወይም ደመናማ ወይም
ዝናባማ ወይም ጸሐያማ ሊሆን እንደሚችል ሁሉ እኛም ሁልጊዜ ዓለማዊ ወይም
ሁልጊዜ መንፈሳዊ አንሆንም፡፡ ደካሞች ብንሆንም እኛ ጻድቃኖች ሁልጊዜም
ዓመጸኞች አይደለንም፡፡ ደካሞች ብንሆንም የጌታን ፈቃድ የምንከተል ነን፡፡
ኢየሱስ አስቀድሞ ጉድለቶቻችንን ሁሉ ወስዶዋል፡፡ ስለዚህ በጌታ ትምህርት ላይ
በእምነት እንደምትኖሩ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ ጭንቀቶች ውስጥ እንዳንወድቅ
እንዲህ ያለውን ትምህርት ስለሰጠን ጌታን እናመሰግነዋለን፡፡ ይህ ትምህርት ለእኛ
በመጨረሻዎቹ ቀኖች ውስጥ ለምንኖር እንዴት ታላቅ ነው! በእርግጥም
አመስጋኞች ነን፡፡
በየቀኑ ችግሮች ይገጥሙናል፡፡ ነገር ግን የአንድ ቀን ችግር ለዚያ ቀን በቂ
ነው፡፡ እርሱ የወንጌልን ሥራ ለመስራት እንቅፋት የሚሆኑብንን ችግሮችና
መከራዎች ሁሉ ለማሸነፍ በየቀኑ አዲስ ጉልበት እንደሚሰጠን በማመን በየቀኑ
ለተባረከው የእግዚአብሄር ሥራ መኖር አለብን፡፡
ሐሌሉያ! 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ምዕራፍ
7

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት
ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
በወንጌል ሐይል በማመን
በጠባቡ ደጅ መግባት አለብን
‹‹ማቴዎስ 7፡13-14››
‹‹በጠበበው ደጅ ግቡ፤ ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጅ ሰፊ መንገዱም ትልቅ
ነውና፡፡ ወደ እርሱም የሚገቡ ብዙዎች ናቸው፡፡ ወደ ሕይወት የሚወስደው ደጅ
የጠበበ መንገዱም የቀጠነ ነውና፤ የሚያገኙትም ጥቂቶች ናቸው፡፡››

በዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ውስጥ ጌታችን ‹‹በጠበበው ደጅ


እንድንገባ›› አዞናል፡፡ እንግዲያውስ እንድንገባበት የነገረን ይህ ጠባብ ደጅ
ምንድነው? ሰፊው ደጅ ሲልስ ምን ማለቱ ነበር? አሁን ሁላችንም በጠባቡና
በአስቸጋሪው መንገድ ላይ መጓዝ አለብን፡፡ እንደዚያ ለማድረግ በውሃውና
በመንፈሱ ቃል ይበልጥ በግለት ማመን አለብን፡፡ መጓዝ ያለብንም በእግዚአብሄር
ቃል ላይ ባለን እምነት ብቻ ነው፡፡ ጠባቡን መንገድ ትተን ቀላልና ሰፊ ወደሆነው
መንገድ እንደምንመለስ የታወቀ ነው፡፡ ነገር ግን ይህንን ማድረግ የለብንም፡፡
ምክንያቱም ጌታ በጠባቡና በአስቸጋሪ መንገድ ላይ እንድንጓዝ ነግሮናልና፡፡
በዚህ ዓለም ላይ በአስቸጋሪው መንገድ በኩል ወደ ጠባቡ ደጅ መግባት
የማይወዱ ብዙ ሰዎች አሉ፡፡ መንገዱ በጣም ጠባብ፣ አስቸጋሪና አደገኛ
ስለሚመስላቸው የሚያገኙትም ጥቂቶች ብቻ ስለሆኑ እዚያ ላይ ለመሳፈር
ያመነታሉ፡፡ በዚህ መንገድ ላይ የሚጓዝ ማንኛውም ሰው ሞኝ መሆን አለበት
ብለውም ያስባሉ፡፡ ነገር ግን የዚህ ዓይነቱ እምነት የጠቢብ ምዕመን እምነት
አይደለም፡፡
ወደ ሕይወት የሚመራው ጥበብ የሚገኘው በጠባቡ መንገድ ላይ ነው፡፡
ወደ ሕይወት በሚወስደው በዚህ መንገድ ላይ ያሉ ሰዎች ጠቢብ መሆናቸው
ግልጽ ነው፡፡ ስለዚህ እነዚህ ሰዎች ጥቂቶች ቢሆኑም እንኳን በዚህ መንገድ ላይ
ለመጓዝ አያመነቱም፡፡ በዚህ ዓለም ላይ ጠባቡን መንገድ የማይወዱ ብዙ ሰዎች
መኖራቸው እውነት ቢሆንም ይህ ግን ሁሉንም የሚመለከት አይደለም፡፡
ቁጥራቸው በጣም ትንሽ ቢሆንም ጠባቡን መንገድ የሚሹና በእርሱም ላይ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


192 በወንጌል ሐይል በማመን በጠባቡ ደጅ መግባት አለብን

ለመጓዝ የሚደሰቱ ሰዎች መኖራቸው እርግጥ ነው፡፡ እያንዳንዱ ሰው


ከሐጢያቶቹ ይድን ዘንድ ፈጽሞ በጠባቡ ደጅ መግባት አለበት፡፡

ጠባቡ መንገድ የእውነት መንገድ፣ ወደ ዘላለም


ሕይወት የሚያደርስ መንገድ ነው፡፡

በዚህ ዓለም ላይ የሚኖሩ በርካታ ሰዎች በኢየሱስ እናምናለን ይላሉ፡፡


ከእነርሱ ብዙዎቹ ግን ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅ የዓለምን
ሐጢያቶች በሙሉ መውሰዱን ባለማወቃቸውና ባለማመናቸው በእርግጥም
በሰፊው መንገድ ላይ እየተጓዙ ነው፡፡ በጠባቡ መንገድ ላይ የሚጓዙ ሰዎች ወደ
ዘላለም ሕይወት በሚወስደው ትክክለኛ መንገድ ላይ እንደሆኑ ያውቃሉ፡፡
ምክንያቱም የኢየሱስ ጥምቀት ሐጢያቶቻቸውን በሙሉ ለአንዴና ለዘላለም
የወሰደ በመሆኑ እውነት ያምናሉና፡፡
ነገር ግን በዚህ ዓለም ላይ ባሉ ክርስቲያኖች መካከል ይህንን የጠባቡን
ደጅና የአስቸጋሪውን መንገድ ምስጢር የሚውቅ ማነው? የዚህ ዘመን
ወንጌላውያን ተብዬዎች እንኳን ኢየሱስ ከአጥማቂው ዮሐንስ በተቀበለው
ጥምቀት አማካይነት የተቀበላቸውን የዓለም ሐጢያቶች እንደወሰደ አያውቁም፡፡
የኢየሱስ ጥምቀት አቢይ ፋይዳ አስገራሚውን የደህንነት እውነት ማለትም
ኢየሱስ የዚህን ዓለም ሐጢያቶች መውሰዱንና ስለ እኛ መሰቀሉን የያዘ መሆኑ
ነው፡፡
ሆኖም ከብዙ የዓለም ሐይማኖቶች አንዱን ብቻ የተለማመዱ ይመስል
በኢየሱስ እናምናለን የሚሉ የስም ክርስቲያኖች ኢየሱስ ሐጢያቶቻቸውን ሁሉ
ይቅር ያለው በመስቀል ላይ ብቻ እንደነበር ያስባሉ፡፡ እነዚህ ክርስቲያኖች
በልቦቻቸው ውስጥ ሐጢያቶች እንዳሉ ያውቃሉ፡፡ ወንጌላውያን ነን በሚሉት
መካከልም ብዙዎቹ ሰው ኢየሱስን አዳኙ አድርጎ በማመን ብቻ ሐሐጢያት አልባ
መሆን እንደሚችል ይናገራሉ፡፡ እንዲያውም ‹‹እኛ ማድረግ ያለብን ኢየሱስን
የግል አዳኛችን አድርገን ማመን ብቻ ነው፡፡ ታዲያ ይህንን የውሃና የመንፈስ
ወንጌል ማወቅና ማመን የሚያስፈልገን ለምንድነው?›› በማለት ያላግጡብናል፡፡
ራሳቸውን ሐጢያት አልባ እንደሆኑ አድርገው ማመን ትክክል ነው በማለት ግትር
ስለሚሉ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ለማመን እምቢተኞች ናቸው፡፡ ነገር ግን
በትክክል ከአብዛኞቹ ዓለማዊ ክርስትና ተከታዮች ጋር አብረው ተውጠው

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በወንጌል ሐይል በማመን በጠባቡ ደጅ መግባት አለብን 193

በሰፊው መንገድ ላይ እየተጓዙ ነው፡፡


ጌታ ስለ ውሃውና ስለ መንፈሱ ወንጌል ከተናገረን ይህንን የደህንነት
ወንጌል እንዳለ በማመን የሐጢያት ስርየትን ሐይል በመቀበል ልንደሰት
ይገባናል፡፡ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በማመንና በማሰራጨት በእርግጥም
በጠባቡና በአስቸጋሪው መንገድ ላይ እየተጓዝን ነው፡፡ በጠባቡ መንገድ ላይ
የሚጓዙ ሰዎች በሰፊው መንገድ ላይ የሚጓዙትን ሰዎች ወደ እግዚአብሄር ቃል
ተመልሰው ቃሉን እንዲከተሉ መምከር አለባቸው፡፡ የውሃውንና የመንፈሱን
ወንጌል የሚያምኑ ምዕመናኖች ያሉባቸው ሁኔታዎች ምንም ይሁኑ ጌታ ራሱ
በጠባቡ መንገድ ላይ እንዲጓዙ ከነገራቸው በዚህ ጠባብ መንገድ ላይ በእምነት
መጓዝ አለባቸው፡፡
ነገር ግን እጅግ ብዙ ክርስቲያኖች በሰፊው መንገድ ላይ ለመጓዝ ከዚህ
ዓለም ሰዎች ጋር በጣም ብዙ ስምምነቶችን ስላደረጉ የሐጢያቶችን ስርየት
በልቦቻቸው ውስጥ መቀበል የሚችሉት እንዴት ነው? ከዓለም ሰዎች ጋር
በመስማማት ሕይወታቸውን የሚኖሩ እነዚህ ክርስቲያኖች አሁንም ድረስ
ሐጢያቶቻቸው በልቦቻቸው ውስጥ ተቀምጠዋል፡፡ ኢየሱስን አዳኛቸው እንደሆነ
አድርገው ቢያምኑም በመጨረሻ ወደ ጥፋታቸው ለመድረስ በሰፊው መንገድ ላይ
ብቻ እየተጓዙ ነው፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ እንዲህ ብሎዋል፡-- ‹‹ወይስ ከክርስቶስ ኢየሱስ ጋር
አንድ እንሆን ዘንድ የተጠመቅን ሁላችን ከሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ
እንደተጠመቅን አታውቁምን?›› (ሮሜ 6፡3) እንዲህም ደግሞ ብሎዋል፡-
‹‹የክርስቶስ መንፈስ የሌለው ከሆነ ግን ይኸው የዕርሱ ወገን አይደለም፡፡›› (ሮሜ
8፡9) ኢየሱስን አዳኝ አድርጎ የማመን ውጤቶች ከሐጢያት መዳን፣ ሐጢያት
አልባ መሆንና የመንፈስ ቅዱስ በልብ ውስጥ መኖር ናቸው፡፡
መንፈስ ቅዱስ በዓይኖቻችን ሊታይ ባይችልም ኢየሱስ በሰጠው የውሃውና
የመንፈሱ ወንጌል በሚያምኑ ሰዎች ላይ የሚወርድ የእውነት መንፈስ ነው፡፡
የመንፈስ ቅዱስ ሚና ‹‹ጌታ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት ፈጽሞ
ከሐጢያቶቻችሁ ሁሉ አድኖዋችኋል፤ ስለዚህ አሁን እናንተ ሐጢያት አልባ
ናችሁ›› ብሎ በማስረገጥ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ለሚያምኑ ለእነዚህ
ምዕመናኖች መመስከር ነው፡፡
እርሱ በወሃውና በመንፈሱ ወንጌል በሚያምኑ ምዕመናኖች ልቦች ውስጥ
የእውነት ቃል ምስክር የሆነ መንፈስ በመሆኑ በልቦቻቸው ውስጥ ምንም ዓይነት
ሐጢያት ሊኖር አይችልም፡፡ እርሱ ዳግመኛ በተወለዱ ሰዎች ልቦች ውስጥ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


194 በወንጌል ሐይል በማመን በጠባቡ ደጅ መግባት አለብን

ያድራል፡፡ አእምሮዋቸውም ተጨባጭ የደህንነት ምስክርነቶች እንዲኖረው


ይፈቅዳል፡፡ በሌላ አነጋገር መንፈስ ቅዱስ የዓለም ሐጢያቶች በሙሉ ኢየሱስ
በአጥማቂው ዮሐንስ በተጠመቀ ጊዜ ወደ ሰውነቱ እንደተላለፈ ይመሰክራል፡፡
መንፈስ ቅዱስ በጠባቡ መንገድ ላይ ለሚጓዙት እምነትን በመስጠት፣
በመምራትና በእውነት ቃል ሁሉን ነገር በማስተማር እንደዚሁም አጽንቶ በመያዝ
ሐይልን ያስታጥቃቸዋል፡፡ መንፈስ ቅዱስ ከሐጢያቶቻችን ያነጻንን የውሃና
የመንፈስ የወንጌል ቃል በማስታወስ ነፍሳችንን፣ አእምሮዋችንና አካላችንን
ያበረታል፡፡ በአጭሩ ኢየሱስ ስለ እኛ እንደተጠመቀና ለእኛም በመስቀል ላይ
እንደሞተ ይመሰክራል፡፡

የእውነትን ወንጌል የሚያምኑና የሚከተሉ በጠባቡ


መንገድ ላይ የሚጓዙ ሰዎች ናቸው፡፡

በጠባቡ መንገድ ላይ የሚጓዙ ሰዎች በሐጢያቶቻቸው ጥፋት ላይ


የወደቁትን የሚያድኑ መንፈሳዊ ካህናት ናቸው፡፡ እነርሱ የውሃውንና የመንፈሱን
የወንጌል ቃል የሚያምኑ ምዕመናኖች ናቸው፡፡ ጌታም በጠባቡና በአስቸጋሪው
መንገድ ላይ በሚጓዙት በእነዚህ ሰዎች ይደሰታል፡፡ ይህ የጻድቃን መንገድ ምንም
ያህል አስቸጋሪ ቢሆንም ሌሎችን ከሐጢያቶቻቸው የሚያድን መንገድ ስለሆነ
ሁላችንም በዚህ መንገድ ላይ መጓዝ አለብን፡፡ ገና የሐጢያቶቻቸውን ስርየት
ያላገኙትን ሰዎች ከሐጢያቶቻቸው ሁሉ ለማዳን ቀንና ሌሊት ወንጌልን ማገልገል
አለብን፡፡ በሌላ አነጋገር አሁንም ድረስ በሰፊው መንገድ ላይ እየተጓዙ ያሉ ሰዎች
ወደ ጠበበው ደጅ ይገቡ ዘንድ ልንመራቸው ይገባናል፡፡ በሰፊው መንገድ ላይ
የሚጓዙት እነዚህ ሰዎች ይህ መንገድ ምቹ ቢሆንላቸውም መንገዱን በመከተል
የሚቀጥሉ ከሆነ በመጨረሻ ፍጻሜያቸው የጥፋት መንገድ መሆኑን ማስታወስ
ይኖርባቸዋል፡፡
እዚህ ላይ በሰፊው መንገድ ላይ የሚጓዙት የሚያመለክቱት ከዓለም ሰዎች
ጋር ተስማምተው ወደ ጥፋት በሚወስዳቸው መንገድ ላይ የሚጓዙትን ግብዝ
ክርስቲያኖች ነው፡፡ እነርሱ በኢየሱስ ቢያምኑም አሁንም ድረስ ሐጢያት
ያለባቸው መሆናቸው ትክክል ነው የሚሉ የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል እውነት
ተቃዋሚዎች ናቸው፡፡
ጌታችን በሰፊው መንገድ ላይ ስለሚጓዙት ስለ እነዚህ ሰዎች ምን ብሎዋል?

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በወንጌል ሐይል በማመን በጠባቡ ደጅ መግባት አለብን 195

እንዲህ ብሎዋል፡- ‹‹ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጅ ሰፊ መንገዱም ትልቅ ነውና፤


ወደ እርሱም የሚገቡ ብዙዎች ናቸው፡፡›› በሌላ አነጋገር የውሃውንና የመንፈሱን
ወንጌል ባለማወቃቸው በኢየሱስ እናምናለን ቢሉም እንኳን ሐጢያቶቻቸው
አብረዋቸው ያሉ ብዙ ክርስቲያኖች አሉ፡፡ ነገር ግን ሰዎችን የሚስበው ይህ
የሐሰት እምነታቸው ነው፡፡ ሰዎችም የሚከተሉት የእነርሱን ሰፊ የጥፋት መንገድ
ነው፡፡
እነርሱ ክርስቲያኖች ማድረግ ያለባቸው መልካም መሆን ብቻ ነው ብለው
ያስተምራሉ፡፡ ይህ ግን ከእውነት ያፈነገጠ ትልቅ እንከን ያለበት የትምህርት
ዓይነት ነው፡፡ ይህም ሆኖ የዚህ ዓለም ሰዎች በውሃውና በመንፈሱ የወንጌል ቃል
የማያምኑ ሰዎችን እምነት ይበልጥ የሚመስጥ ሆኖ አግኝተውታል፡፡ እነዚህ የስም
ክርስቲያኖች ቤተክርስቲያን እየሄዱም የሐጢያቶቻቸውን ስርየት ባይቀበሉም
በጥሩ ሥነ ምግባር ብቻ ከኖሩ አሁንም የዓለም ሰዎችን ድጋፍ ያገኛሉ፡፡
እግዚአብሄር ግን የዚህ ዓይነቱን እምነት ትክክለኛ እምነት ነው ብሎ
አይደግፈውም፡፡
ስለዚህ ጠባቡን መንገድ የመረጥን ሰዎች የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
በምትሰብክና ቃሉንና ፈቃዱንም በምትከተል ቤተክርስቲያን ውስጥ
ሕይወታችንን እንኖራለን፡፡ እኛ የውሃውንና የመንፈሱን የወንጌል ቃል ሰምተን
አምነናል፡፡ በዚህም ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ድነን ለአንዴና ለዘላለም ሐጢያት
አልባዎች ሆነናል፡፡ ከሐጢያቶቻችን ከዳንን በኋላም ሌሎች ነፍሳቶችን ወደ
ሕይወት መንገድ የምንመራ የእግዚአብሄር ሰራተኞች ሆነናል፡፡ ስለዚህ በጠባቡና
በአስቸጋሪው መንገድ የምንጓዝ ሰዎች ሆነናል፡፡
ሆኖም አብዛኞቹ ክርስቲያኖች ከሐጢያቶቻቸው ይነጹ ዘንድ በኢየሱስ
አያምኑም፡፡ ጻድቅ ለመሆንም አይፈልጉም፡፡ እንደዚህ ዓይነት እምነት በስፋት
መሰራጨቱና ደጋፊዎቹም በሰፊውና በዓለማዊው መንገድ እየተጓዙ ሲኩራሩ
ማየት በጣም ይረብሻል፡፡ እነርሱ ራሳቸውን ጠቢባን አድርገው በመቁጠር
ሁልጊዜም ጥሩንባቸውን ይነፋሉ፡፤ በሰፊው መንገድ ላይ መጓዝ ስህተት መሆኑን
እንኳን አይገነዘቡም፡፡ ነገር ግን በጠባቡ መንገድ ላይ የሚጓዙትን ዳግመኛ
የተወለዱ ሰዎች ሞኞች እንደሆኑ አድርገው በጠማምነት ማውገዛቸውን
ቀጥለዋል፡፡
የክርስቲያን መሪዎች እንኳን በእርግጥ ሳያውቁት በሰፊው መንገድ ላይ
እየተጓዙ የመሆኑን እውነታ ችላ ብለውታል፡፡ ለእነርሱ እጅግ ጠቃሚ ከሆኑት
ጉዳዮች አንዱ በሌሎች መታወቅና ዓለማዊ ክብርን ማግኘት ነው፡፡ አሳዛኙ ነገር

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


196 በወንጌል ሐይል በማመን በጠባቡ ደጅ መግባት አለብን

ደግሞ ልክ ተውኔት በመስራት የተካነ ፖለቲከኛ ብዙ ድምጽ ሰጭዎችን


እንደሚስብ ሁሉ እምነታቸውም ብዙ ሰዎች መሳቡና መጎተቱ ነው፡፡ ሰዎች ምን
እንደሚወዱና ምን ሊኖራቸው እንደሚፈልጉ በሚገባ ያውቃሉ፡፡ የሚናገሩት
እግዚአብሄርን የሚያስደስተውን ሳይሆን ሰዎችን የሚያስደስተውን ነው፡፡ እነርሱ
ሐሰተኛ አስተማሪዎችና የሰይጣን አገልጋዮች ናቸው፡፡ እውነተኛ የእግዚአብሄር
አገልጋዮች እነዚህ ሐሰተኛ አስተማሪዎች የሚያደርጉትን በጭራሽ አያደርጉም፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ እንዲህ ብሎዋል፡- ‹‹ሰውን ወይስ እግዚአብሄርን አሁን እሺ
አሰኛለሁን? ወይስ ሰውን ደስ ላሰኝ እፈልጋለሁን? አሁን ሰውን ደስ ባሰኝ
የክርስቶስ ባር ባልሆንሁም፡፡›› (ገላትያ 1፡10)
ስለዚህ የዓለምን እምነት ጥለን ጌታችንን ወደሚያስደስተው ወደዚህ ጠባብ
መንገድ የሚመራንን የውሃና የመንፈስ ወንጌል ለመከተል የላቀ ምክንያት አለን፡፡
ይህንን ለማድረግ የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል በጠባቡ መንገድ ላይ የሚያቆመን
እውነት መሆኑን ማመንና ይህንኑ መከተል አለብን፡፡ እምነታችንን በተጻፈው
የእውነት ቃል ላይ ለማኖር ሁላችንም ይህንን መንገድ መከተል አለብን፡፡ ጌታችን
ለምን በጠባቡ ደጅ እንድንገባ እንደነገረን መረዳት አለብን፡፡ የውሃውንና የመንፈሱን
ወንጌል መከተልና ማገልገልም ይገባናል፡፡
ዳግመኛ የተወለድን ሰዎች ቀድሞውንም በጠበበው ደጅ ገብተናል፡፡
ምክንያቱም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አምነናልና፡፡ ከውሃውና ከመንፈሱ
ወንጌል ጋርም በጋራ በጠባቡ መንገድ ላይ እየተጓዝን ነው፡፡
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምኑ ጻድቃን በሰፊው መንገድ ላይ
አይጓዙም፡፡ እንዲህ ተብሎ ተጽፎዋልና፡- ‹‹ዓለምን ወይም በዓለም ያሉትን
አትውደዱ፤ በዓለም ያለው ሁሉ እርሱም የሥጋ ምኞትና የዓይን አምሮት ስለ
ገንዘብም መመካት ከዓለም ስለሆነ እንጂ ከአባት ስላልሆነ ማንም ዓለምን ቢወድ
የአባት ፍቅር በእርሱ ውስጥ የለም፡፡ ዓለሙም ምኞቱም ያልፋሉ፤ የእግዚአብሄርን
ደፈቃድ የሚያደርግ ግን ለዘላለም ይኖራል፡፡›› (1ኛ ዮሐንስ 2፡15-17)
በጠባቡ መንገድ ላይ ላስቀመጠን ጌታችን ምስጋናዬን ሁሉ
አቀርባለሁ፡፡ 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በመጨረሻው ቀን
ጌታ ቢተወን ምን እናደርጋለን?
‹‹ ማቴዎስ 7፡21-23 ››
‹‹በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ
የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም፡፡ በዚያ ቀን ብዙዎች፡- ጌታ
ሆይ ጌታ ሆይ በስምህ ትንቢት አልተናገርንምን? በስምህስ አጋንንትን
አላወጣንምን? በስምህስ ብዙ ተዓምራትን አላደረግንምን? ይሉኛል፡፡ የዚያን
ጊዜም፡- ከቶ አላወቅኋችሁም፤ እናንተ ዓመጸኞች ከእኔ ራቁ ብዬ
እመሰክርባቸዋለሁ፡፡››

በዚህ ዓለም የተወለደ እያንዳንዱ ሰው ቢያንስ አንድ ጊዜ ፍቅር


ይይዘዋል፡፡ ወንድና ሴት በትዳር አንድ የሚሆኑት በዚህ መንገድ ነው፡፡ ነገር ግን
በብዙ ሰዎች ብድር የማይመልስ ፍቅር ተብሎ የሚጠራ የፍቅር ገጽታ አለ፡፡
በሌላ አነጋገር ሌላው እንዴት እንደሚሰማውና አሳቡ ምን እንደሆነ ብዙም
የማይጨነቅ የአንድ ወገን ፍቅር አለ፡፡ ከእንደዚህ ዓይነት ፍቅሮች ውስጥ ሙሉ
ፍሬዎችን የሚያፈሩት ጥቂቶች ናቸው፡፡ በአብዛኛው ይህ ዓይነቱ ፍቅር
ማብቂያው አንዱን ሰው ብቻ በሚጠቅም የአንድ ወገን ፍቅር ላይ ነው፡፡
እንደዚህ ባሉ ሁኔታዎች ውስጥ ፍቅር በጥቅሉ በጊዜ ሒደት ውስጥ ተረስቶ
የረጅም ጊዜ ልብ የሚያሳምም የሩቅ ትዝታ ብቻ ሆኖ ይቀራል፡፡ ደግሞም ብድር
ከማይመልስ ፍቅር በጣም የሚከፋ የአድቢዎች ፍቅር አለ፡፡ እነዚህ ሰዎች
በተደጋጋሚ ተቀባይነት ባያገኙም የፍቅራቸው ባለቤት በሆነው ሰው የተያዙ
ናቸው፡፡ ነገሩ ከተለጠጠ እንዲህ ያለ አስጨናቂ ፍቅር ሰው የሚወደውን ሌላውን
ሰው ወደ መግደል ይመራል፡፡
እነዚህ በፍቅር ያበዱ ሰዎች ብዙውን ጊዜ ሌላውም ሰው ልክ እንደ እነርሱ
በትክክል እንደሚወዳቸው ያስባሉ፤ ያምናሉም፡፡ ነገሩ ግን በጭራሽ እንዲህ
እንዲህ አይደለም፡፡ እነርሱ በሆነ ዓይነት የአእምሮ በሽታ የተለከፉ ናቸው፡፡
የጭብጨባ ድምጽ ሊፈጠር የሚችለው ሁለት እጆች ሲሳተፉ ብቻ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


198 በመጨረሻው ቀን ጌታ ቢተወን ምን እናደርጋለን?

እንደሆነ ሁሉ በፍቅር ውስጥም የእርስ በርስ ፈቃድ በጣም አስፈላጊ ነው፡፡


አንድን ሰው ለብቻ ከልብ መውደድ ትክክለኛ ፍቅር ሊሆን አይችልም፡፡ በሰዎች
መካከል ያለው ብድር የማይመልስ ፍቅር እንኳን እንደዚህ ትርጉም የለሽ ከሆነ
ሐጢያተኛ እግዚአብሄርን በማን አለብኝነትና በድፍረት ለመውደድ መሞከሩ
ምንኛ ትርጉም አልባ ይሆናል?
እግዚአብሄር ሁሉንም እኩል እንደሚወድ ነግሮናል፡፡ ፍቅሩን በትክክል
የሚረዱትንና በእምነት በምስጋና የሚቀበሉትን ይባርካቸዋል፤ ይወዳቸውማል፡፡
ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታም ከሐጢያት ያድናቸዋል፡፡ ነገር ግን ይህንን ማድረግ
የተሳናቸውን ይቆጣቸዋል፤ ይወቅሳቸውማል፡፡ ለዚህም ምክንያቱ እነዚህኛዎቹ
ለእግዚአብሄር ያላቸው ፍቅር እንከን ያለበት ነውና፡፡ እግዚአብሄር በማቴዎስ ላይ
እነዚህን ሰዎች እንደማያውቃቸው ተናግሮዋል፡፡
ሰዎች ‹‹ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ በስምህ ትንቢት አልተናገርንምን? በስምህስ
አጋንንትን አላወጣንምን? በስምህስ ብዙ ተዓምራትን አላደረግንምን?›› ሲሉት
‹‹ከቶ አላወቅኋችሁም፤ እናንተ ዓመጸኞች ከእኔ ራቁ›› (ማቴዎስ 7፡23) ብሎ
መሰከረባቸው፡፡
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የማያምኑ ሰዎች ሐጢያቶቻቸው ሁሉ
አብረዋቸው እያሉ በእግዚአብሄር ፊት ቢቀርቡ ምን እንደሚፈጠር ለቅጽበት
እናስብ፡፡ ልክ ለሌላ ሰው እንደሚናገሩት ለእግዚአብሄር ይነግሩታል፡፡ እንዲህ
ባለ ሰውና በጌታ በኢየሱስ መካከል የሚደረገውን ቀጣዩን ንግግር ማሰብ
እንችላለን፡፡
‹‹ጌታ ሆይ እንደምነህ? በምድር ላይ ስኖር በነበረ ጊዜ ሁሉ ውብ
እንደምትሆን አስብ ነበር፡፡ በመጨረሻ በዚህ ሁኔታ ከአንተ ጋር በመገናኘቴ
ትልቅ ክብር ይሰማኛል፡፡ ጌታ ሆይ ተመስገን፡፡ ልክ እንደዚህ አድነኸኛል፡፡ ከእኔ
ጋር ጥቂት ሐጢያቶች አብረውኝ ያሉ ቢሆንም በአንተ ስለማምን እንደዳንሁ
እርግጠኛ ነኝ፡፡ አሁን እዚያ አካባቢ ለእኔ ወዳዘጋጀኸው ውብ ስፍራ እሄዳለሁ፡፡
ደህና ሁን፤ በኋላ እንደገና እንገናኛለን፡፡›› ይህ ሰው ከጌታ ፊት ለመሄድ ሲሞክር
ጌታ ሊነግረው የሚሻው ጥቂት ቃላት ስላለው እንዲመለስ ይጠራዋል፡፡
‹‹ግን ቆይ እስቲ! ሐጢያት ያለባቸው ሰዎች ወደዚያ ስፍራ መሄድ
አይችሉም!››
‹‹አሁንም ድረስ ከእኔ ጋር አብረው ያሉ ሐጢያቶች እንዳሉ እውነት ነው፡፡
ነገር ግን አሁንም ቢሆን ወደዚያ መሄድ እንደምችል አስባለሁ፤ ምክንያቱም
ኢየሱስን አዳኜ አድርጌ አምኛለሁና፡፡››

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በመጨረሻው ቀን ጌታ ቢተወን ምን እናደርጋለን? 199

‹‹አይደለም፤ ነገሩ እንደዚህ አይሰራም! አሁንም ሐጢያቶችህ አብረውህ


አሉ አይደል?››
‹‹አዎ አሁንም ድረስ ሐጢያቶች አሉብኝ፡፡››
‹‹ታዲያ እኔ ሐጢያት ለሌለባቸው ሰዎች ብቻ ወዳዘጋጀሁት ወደዚያ ስፍራ
ለመሄድ እንዴት ልትደፍር ትችላለህ? ኑ! ይህ ሰው ለዘላለም ወደሚሰቃይበት
ፈጽሞ ወደማይጠፋው እሳት ጣሉት! እነርሱ ይህንን ከማድረጋቸው በፊት
አስቀድመህ ሐጢያቶችህን መናዘዝ ይገባሃል፡፡››
ያን ጊዜ ሰውየው አፉን ከፍቶ ከዚህ በፊት የሰራቸውን ሐጢያቶች በሙሉ
ያለ አንዳች ማመንታት ‹‹ባለፈው ዓለም ላይ ስኖር እነዚህንና እነዚህን ሐጢያቶች
ሰርቻለሁ…›› በማለት ይናዘዛል፡፡
ከዚያም ጌታ እንዲህ አለው፡- ‹‹እሺ ያ በቂ ነው፡፡ አንተ ወደ ሲዖል
ለመወረድ ከብቁም በላይ ነህ፡፡ ሐጢያቶች ስላሉብህ ለእንዳንተ ዓይነቱ ሰው
ግሩምና ሞቃት ወደሆነው ሲዖል ሂድ፡፡››
‹‹ምን? በዓለም ሳለሁ ግን በአንተ አምኛለሁ! በስምህ ትንቢት
ተናግሬያለሁ! ለብዙ ሰዎች መስክሬአለሁ! አንተን ለማገልገል ቤቴን ሸጫለሁ፡፡
ቤተሰብ አልባዎችን በብዙ ረድቻለሁ፡፡ በየማለዳው በሚደረገው የጸሎት ጉባኤ
ላይም በትጋት ተሳትፌያለሁ፡ ብዙ የታመሙ ሰዎችን ፈውሻለሁ፡፡ ለአንተ
ጾሜያለሁ፡፡ ለአንተ ብዙ ነገር መስዋዕት አድርጌያለሁ!›› አሁን ይህ ሁሉ በጣም
ተገቢ እንዳልሆነ በማሰብ ጥርሱን ክፉኛ በማፋጨቱ ጥርሱ ተሰብሮ የሚወድቅ
ይመስል ነበር፡፡ በሲዖል የጥርስ ሕክምና እያደገ መሆኑ ሊታሰበን ይችላል! ነገር
ግን ከምር እንነጋገር ከተባለ ሐጢያተኞች በሙሉ በኢየሱስ ቢያምኑ ወይም
ባያምኑ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ውስጥ ሆነው በኢየሱስ ካላመኑ ሁሉም
ወደዚህ የዘላለም እሳት ስፍራ ለመጣል የታጩ ናቸው፡፡
በኤርምያስ 17፡1 ላይ እግዚአብሄር እንዲህ ብሎዋል፡- ‹‹የይሁዳ ሐጢአት
በብረት ብርዕና በተሾለ ዕብነ አልማዝ ተጽፎአል፡፡ በልባቸው ጽላትና
በመሠውያቸው ቀንዶች ተቀርጾአል፡፡›› እዚህ ላይ ይሁዳ የሚያመለክተው
በእስራኤሎች መካከል የነበረውን ንጉሣዊ ነገድ ነበር፡፡ እግዚአብሄር ይህንን ቃል
የተጠቀመው የእስራኤልን ሕዝብ ሁሉ ለማመልከት ነው፡፡ በተጨማሪም
መጽሐፍ ቅዱስ ወኪል መርህ የሚለውን ስለሚጠቀም ሰዎችንም ሁሉ
ይመለከታል፡፡ ለምሳሌ አዳም የሰው ዘር ወኪል ተብሎ ተጠርቷል፡፡ (ሮሜ 5፡18)
አልማዞች ክርስታላይን መልክ ያላቸው የካርቦን ቁራጭ ናቸው፡፡ በዓለም
ላይ የሚታወቁ እጅግ ጠንካራ የተፈጥሮ ቁስ ናቸው፡፡ ስለዚህ እዚህ ላይ የሕዝቡ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


200 በመጨረሻው ቀን ጌታ ቢተወን ምን እናደርጋለን?

ሐጢያቶች በተሾለ ዕብነ አልማዝ በልቦቻቸው ጽላቶች ላይ ተጽፈዋል ሲል


በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አምነው ከሐጢያቶቻቸው ሁሉ እስካልነጹ ይህ
ሊፋቅ አይችልም ማለት ነው፡፡
ስለዚህ ገና የሐጢያቶቻቸውን ስርየት ያልተቀበሉ ሐጢያተኞች
ሐጢያቶቻቸው በሙሉ በልቦቻቸው ጽላቶች ላይ ተጽፈዋል፡፡ በስነ አመክንዮ
ላይ በተመሰረተ የቃለ እግዚአብሄር ዕውቀት ምንም ያህል የተካኑ ቢሆኑ፣
በካልቪናውያን የሥነ መለኮት ዕውቀት ምንም ያህል ቢጠበቡ፣ ፕሮፌሰሮች
ሆነው በሴሚናሪዎች ውስጥ የሥነ መለኮት ትምህርት ቢያስተምሩ ወይም
በቤተክርስቲያኖች ውስጥ ከፍተኛ የሥልጣን ቦታዎችን ቢይዙ በልቦቻቸው
ጽላቶች ላይ የተጻፉት ሐጢያቶች ከውሃውና ከመንፈሱ ወንጌል ውጭ አንዳች
ነገር በማመን ሊደመሰሱ አይችሉም፡፡ እነዚህ ሰዎች ወደ እግዚአብሄር ሲጸልዩ
ሐጢያተኞች መሆናቸውን ሲናዘዙ የምናየው ለዚህ ነው፡፡ የልቦቻቸው ጽላቶች
በሐጢያቶቻቸው ተሞልተዋልና፡፡
ሐጢያተኞች ቢፈልጉም እንኳን በእውነት ከእግዚአብሄር ጋር ሕብረት
ሊኖራቸው ስለማይችል ራሳቸውን አዘውትረው በተራራ ላይ ለሚደረጉ ጸሎቶች
አሳልፈው ይሰጣሉ፤ ይጾማሉ፤ በልሳን ይናገራሉ፡፡ ጌታን ረቂቅ ተብለው በሚጠሩ
ልምምዶች ለመገናኘት ሲሉም ራዕዮችን ያያሉ፡፡ ነገር ግን በመጨረሻ እነዚህ ሁሉ
ከንቱዎች ናቸው፡፡ ያደረጉት ነገር ሁሉ የራሳቸውን ልቦች ባሳተ የተታለለ
የእምነት ሕይወት ውስጥ መኖር ነው፡፡
ከኤርምያስ የተወሰደው የላይኛው ምንባብ የይሁዳ ሐጢያት
‹‹በመሰውያቸው ቀንዶች›› ላይ እንደተቀረጸም ይናገራል፡፡ የመሰውያው ቀንዶች
እዚህ ላይ የሚያመለክቱት የምግባር መጽሐፎችን ነው፡፡ በእግዚአብሄር
መንግሥት ውስጥ ሁለት መጽሐፎች አሉ፡፡ እነርሱም የሕይወት መጽሐፍና
የምግባሮች መጽሐፍ ናቸው፡፡ (ዮሐንስ ራዕይ 20፡12) እግዚአብሄር በምግባር
መጽሐፎች ውስጥ የሐጢያተኞችን ሁሉ እያንዳንዱን ሐጢያት በዝርዝር
ጽፎዋል፡፡
ስለዚህ እነዚህ ሐጢያተኞች በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የማያምኑ ከሆኑ
በዚህ ዓለም ላይ ሳሉ በጭራሽ ከሐጢያተኛ ማንነታቸው አያመልጡም፡፡ ማንም
ይሁኑ በልቦቻቸው ጽላቶች ላይ የተጻፉትን ሐጢያቶች በሙሉ መደምሰስ የሚሹ
ሁሉ ኢየሱስ ከዮሐንስ በተቀበለው ጥምቀትና በመስቀል ላይ ባፈሰሰው ደሙ
ሐጢያቶቻቸውን ሁሉ በመውሰድ እጅግ ተገቢና ገጣሚ በሆነ መንገድ
እንዳዳናቸው በሚናገረው የውሃና የመንፈስ ወንጌል ማመን አለባቸው፡፡ ያን ጊዜ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በመጨረሻው ቀን ጌታ ቢተወን ምን እናደርጋለን? 201

ስሞቻቸው በሕይወት መጽሐፍ ውስጥ ሊጻፉ ይችላሉ፡፡ እነርሱ የእግዚአብሄር


ሕዝብ መሆን የሚችሉት ያን ጊዜ ብቻ ነው፡፡

አሁን ስሞቻችሁ በሕይወት መጽሐፍ ውስጥ ተጽፈዋልን?

ሁሉም ሰው አንድ ጊዜ በእግዚአብሄር የፍርድ ዙፋን ፊት ለመቆም


ታጭቷል፡፡ እዚህ ላይ አንድ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምን አማኝ
በዚያን ቀን በእግዚአብሄር ፊት እንደሚቆም እናስብ፡፡ እግዚአብሄር መላዕክቶቹን
‹‹ስሙ በሕይወት መጽሐፍ ውስጥ ይገኝ እንደሆነ ተመልከቱ›› ብሎ ያዛቸዋል፡፡
ስለዚህ መላዕክቶቹ ይመረምራሉ፡፡ በእርግጥም ስሙ እዚያ ውስጥ ተጽፎዋል፡፡
ያን ጊዜ ጌታ እንዲህ ይለዋል፡- ‹‹ውድ ልጄ በምድር ላይ በነበርህ ጊዜ እኔ
በነጻ የሰጠሁህን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል እውነት በማመን ሐጢያቶችህን
ሁሉ አንጽተሃል፡፡ ከዚያም ለእኔ ጠንክረህ ለፍተሃል፡፡ እንዲሁም ብዙ ዕንባዎችን
ስለ እኔ አፍስሰሃል፡፡ ከእንግዲህ ወዲህ ምንም ዓይነት ዕንባዎች ከዓይኖችህ
እንዳይፈሱ አረጋግጣለሁ፡፡ ከእንግዲህ ወዲህ እንዲህ ያሉ መከራዎች
አይኖሩም፡፡ ሰይጣንም ዳግመኛ አያስጨንቅህም፡፡ ልጄ ሆይ ጥሩ አድርገሃል፡፡››
ከዚያም ጌታ መላዕክቶቹን አክሊል እንዲጭኑለት ያዛቸዋል፡፡
‹‹ጌታ ሆይ አመሰግንሃለሁ፤ ይህ ለእኔ ክብር ነው!››
‹‹አክሊል አምጥታችሁ በራሱ ላይ ጫኑለት!››
‹‹ጌታ ሆይ እኔ ፈጽሞ አመስጋኝ ነኝ፡፡ እኔን ከሐጢያቶቼ ማዳን ብቻውን
እኔን ወሰን የሌለው የአንተ ባለ ዕዳ አደርጎኛል፡፡ አሁን እኔ ለሰራሁልህ ትንሽዬ
ሥራ አክሊል ልትጭንልኝ ነውን? ጌታ ሆይ አመሰግንሃለሁ፡፡ እኔን ማዳንህ በቂ
ነው፡፡ በዚያ ለዘላለም እኖር ዘንድ ወደ መንግሥትህ መግባት መቻሌ ለእኔ በቂ
ሽልማት ነው፡፡ እንግዲያውስ አሁን ሰማይ መግባት እችላለሁን?››
‹‹በእርግጥ! መልአክ አምጡለት! ሚሊዮንኛውን የእግዚአብሄር ልጅ
በጀርባው ይሸከመው፡፡››
የተመደበው መልአክም ቀርቦ እንዲህ ይለዋል፡- ‹‹ጌታዬ ይኸው አለሁ!
እባክህ ጀርባዬ ላይ ውጣ፡፡››
‹‹በጣም ይመቻል፡፤ ውብ ወደሆነ ስፍራ ልሂድ፡፡››
መልአኩ ይበር ዘንድ ክንፎቹን በጥንቃቄ ማዞር ይጀምራል፡፡
‹‹ጌታዬ ለጉብኝት መሄድ ይወዳሉን?››

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


202 በመጨረሻው ቀን ጌታ ቢተወን ምን እናደርጋለን?

‹‹ዋው! ይህ በጣም ድንቅ ነው! ይህ ሰማ ምን ያህል ሰፊ ነው?››


‹‹እኔ ለቢሊዮን ዓመታቶች በዚህ ዙሪያ ስበር ነበር፡፡ ነገር ግን አሁንም
ድረስ የሰማዩን መጨረሻ አላየሁትም፡፡››
‹‹እውነት? አሁን ልታወርደኝ ትችላለህ፤ ከብጄሃለሁ፡፡››
‹‹ጌታዬ እኛ እዚህ ሰማይ ላይ ፈጽሞ ጉልበት አያንሰንም፡፡››
‹‹እንደዚያ ነው? አመሰግናለሁ፤ በሰማይ መሬት ላይ የመጀመሪያውን
እርምጃ ልራመድ፡፡ ከእኔ ቀደም ብለው የመጡት ጻድቃኖች በሙሉ የት አሉ?››
‹‹እዚያ ናቸው፡፡››
‹‹እነርሱን ለማግኘት ወደዚያ እንሂድ፡፡››
በዚህም አማኙ ከእርሱ በፊት የነበሩትን ጻድቃኖች በሙሉ አግኝቶ እንደ
ልቡ ፍላጎት ሁሉ ከእነርሱ ጋር የዘላለም ሕብረት ያደርጋል፡፡ እነዚህ ነገሮች
በሙሉ ምናብ ይመስሉ ይሆናል፡፡ ነገር ግን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
የሚያምኑ ሁሉ በትክክል የሚገጥማቸው ይህ ነው፡፡ በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል በማመን የዳኑ ሰዎች እንደምን የተባረኩ ናቸው!
ነገር ግን በዛሬው ክርስትና ውስጥ እግዚአብሄር በነጻ የሰጠውን
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለመቀበል በጣም ግትር የሆኑ በጣም ብዙ
መንፈሳዊ ገልቱዎች አሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች በኢየሱስ ቢያምኑም ያመኑት በተሳሳተ
መንገድ ነው፡፡ ምክንያቱም የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል አያውቁምና፡፡
እውነተኛው ወንጌል በግልጽ ተነግሮዋቸው ሳለ የተሳሳተውን እምነታቸውን ምን
ያህል በአልሞት ባይ ተጋዳይነት የሙጥኝ ብለው እንደያዙ ማየት አስጎምጂ ነው፡፡
ሰዎች ከልባቸው ሐጢያቶች መዳን የሚፈልጉ ከሆኑ ኢየሱስ በአጥማቂው
ዮሐንስ በመጠመቅ የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ መቀበሉንና (ማቴዎስ 3፡13-17)
በእኛ ፋንታም ደሙን በመስቀል ላይ በማፍሰስ የሐጢያቶቻችንን ቅጣት በይፋ
መሸከሙን በሚነግረን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል እውነት ከልባቸው ማመን
አለባቸው፡፡ በማንኛውም ነገር በማመን ሰማይ ለመግባት መሞከር አንችልም፡፡
ወደ ሐጢያትና ደህንነት ጉዳይ ስንመጣ እግዚአብሄር ጻድቅ ስለሆነ ሁልጊዜም
ማንኛውንም ነገር እንደሚታገሰው ጎረቤታችሁ ጥሩ ልብ ያለው ብቻ አይደለም፡፡
አንድ አስቂኝ ታሪክ ልንገራችሁ፡፡ አንድ ሰው ሰማይ ገባ፡፡ በአንድ ጥግ ላይ
ብዙ ጆሮዎችና ከንፈሮች ተከማችተው ተመለከተ፡፡ ይህ ሰው መልአኩን የዚህን
ምክንያት ጠየቀው፡፡ መልአኩም እነዚህ እዚህ ሰማይ የተገኙት የዳኑት ከንፈሮችና
ጆሮዎች ብቻ ስለሆኑ እንደሆነ አብራራለት፡፡ በጌታ ስናምን በውሃውና
በመንፈሱም ወንጌል ከልባችን ማመናችን ፈጽሞ አስፈላጊ ነው፡፡ ስለዚህ በዚህ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በመጨረሻው ቀን ጌታ ቢተወን ምን እናደርጋለን? 203

እምነት ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ለአንዴና ለመጨረሻ እንድናለን፡፡


በኢየሱስ ቢያምኑም እንኳን አሁንም ድረስ በጌታ ፊት ሐጢያቶቻቸውን
ይዘው የተቀመጡ ብዙ ክርስቲያኖች ሐጢያቶቻቸው አብረዋቸው ያሉ ሆነው ሳለ
ሰማይ የመግባት ችግር እንደሌለባቸው ያስባሉ፡፡ ጌታችን ግን ‹‹አሁንም ድረስ
ሐጢያቶቻችሁ አብረዋችሁ እያሉ ሐጢያት አልባ ናችሁ ብዬ ላስብ አልችልም፡፡
እኔ ቀድሞውኑም በዚህ ዓለም ላይ ሳላችሁ ሐጢያቶቻችሁን ሁሉ በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል አስወግጃለሁ፡፡ እናንተ ግን ይህንን ወንጌል በልባችሁ ለማመን
አሻፈረኝ ብላችኋል፡፡ ምን ማለቴ እንደሆነ ይታያችኋልን? ኑ! ፍቅሬን የናቁትን
እነዚህን ሰዎች ወደ ዘላለም እሳት ጣሉዋቸው!››
በኢየሱስ እያመናችሁ በልቦቻችሁ ውስጥ ሐጢያት ካለ ገና በዚህ ምድር
ላይ እያላችሁ የወሃውንና የመንፈሱን ወንጌል አድምጡ፡፡ በእርሱም እመኑ፡፡
እግዚአብሄር ከተትረፈረፈው ጸጋው የተነሳ እንዲህ በነጻ የሰጣችሁን
የሐጢያቶቻችሁን ስርየት ተቀበሉ፡፡ ይህንን የማያደርጉ ነፍሳቶች በሙሉ በቀጣዩ
ዓለም ወደ ዘላለም የሲዖል እሳት እንደሚጣሉ መረዳት አለባችሁ፡፡
በልቦቻቸው ውስጥ ሐጢያት እያለባቸው ሐጢያት አልባ ነን የሚሉ ሰዎች
በእግዚአብሄር ላይ ከማላገጥና እርሱን ለማታለል ከመሞከር ያለፈ አንድም ነገር
እየሰሩ አይደለም፡፡ እግዚአብሄር በዚህ ዓለም ላይ የሚፈርድበት ጊዜ ሲመጣ
በሐጢያተኛና በሐጢያት አልባ ሰው መካከል ትልቅ ልዩነት እንዳለ ይገነዘባሉ፡፡
በዚህ ቀን ሁሉም ጌታ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል እንዲያምኑና የሐጢያትን
ስርየት እንዲቀበሉ ለምን ከልቡ እንደለመናቸው ይገነዘባሉ፡፡ ያን ጊዜ ሁሉም
በዚህ ባለማመናቸው ተጸጽተው ያለቅሳሉ፡፡
እያንዳንዱ ክርስቲያን ኢየሱስን በእኩል ደረጃ አዳኙ አድርጎ ያምን
ይሆናል፡፡ ነገር ግን የሐጢያትን ስርየት በተቀበሉ ሰዎችና ባልተቀበሉ ሰዎች
መካከል ትልቅ የእምነት ልዩነት አለ፡፡ የመጀመሪያዎቹ ሰማይ ሲገቡ የኋለኛዎቹ
ግን ወደ ሲዖል ይጣላሉ፡፡ የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ቃል የሐጢያቶቻችሁን
ስርየት የምታገኙበት እውነት መሆኑን አሁን ካልተረዳችሁ በኋላ በመጨረሻው
ቀን በእርግጥም በጣም ይረፍድባችኋል፡፡
ኢየሱስን አዳኝ አድርጋችሁ እያመናችሁት በልቦቻችሁ ውስጥ ሐጢያት
አለን? እንደዚያ ከሆነ እናንተም ደግሞ ሐጢያተኞች ናችሁ፡፡ ኢየሱስ ሐጢያት
አለብን የሚሉትን ሰዎች የሚኮንን አዳኝ ነው፡፡ ታዲያ ይህ ማለት እንዲያው
በዕውር ድንብር ሐጢያት የለብንም ብለን ግትር ብንል ትክክል ነው ማለት
ነውን? ነገሩ እንዲህ አይደለም፡፡ ሐጢያት አልባ መሆን የምንችለው ከልባችን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


204 በመጨረሻው ቀን ጌታ ቢተወን ምን እናደርጋለን?

የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በትክክል ስናምንና ከሐጢያቶቻችንም ለአንዴና


ለዘላለም ስንነጻ ብቻ ነው፡፡ ሰማይ ሐጢያቶችን በሙሉ ፈጽሞ በደመሰሰው
የውሃና የመንፈስ ወንጌል የሚያምኑ ሰዎች ብቻ የሚገቡበት ስፍራ ነው፡፡
አሁኑኑ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ከሐጢያቶቻችሁ የሚያድናችሁን
እምነት አዘጋጁ፡፡ ይህንን ለበኋላ የምታቆዩት ከሆነ በጣም ይረፍዳል፡፡ በጣም
ከመርፈዱ በፊት አሁኑኑ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አምናችሁ ተዘጋጁ!
የሐጢያት ስርየት እውነት የሆነውን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በልቦቻችሁ
ውስጥ ካልተቀበላችሁ ወደ ሲዖል ትጋዛላችሁ፡፡ ሐጢያተኞች ሁሉ በሲዖል
ውስጥ ይታሰራሉ፡፡ ጻድቃን ግን ሰማይ ላይ ይኖራሉ፡፡
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በማመን የሐጢያትን ስርየት መቀበል
ይህንን ያህል የከበረ መሆኑን ማን ያውቅ ነበር? በዚህ ዓለም ላይ የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል የሰሙና በእርሱም ያመኑ ሰዎች በእርግጥም የታደሉ ሰዎች
ናቸው፡፡
እኔ በዚህ ወንጌል ጌታን አመሰግናለሁ፡፡ እኛን ሐጢያተኞች የነበርነውን
ለአንዴና ለዘላለም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት ከዓለም ሐጢያቶች
ሁሉ ስላዳነንም ጌታን ደግሜ አመሰግነዋለሁ፡፡ እናንተም ደግሞ አሁኑኑ
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ሐይል ማመን አለባችሁ! ያን ጊዜ ሁሉም ለዘላለም
የእግዚአብሄር ልጆች ይሆናሉ፡፡ ሐሌሉያ! 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ
መፈጸም የሚችለው እምነት
‹‹ ማቴዎስ 7፡20-27 ››
‹‹ስለዚህ ከፍሬያቸው ታውቁዋቸዋላችሁ፡፡ በሰማያት ያለውን የአባቴን
ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት
የሚገባ አይደለም፡፡ በዚያ ቀን ብዙዎች፡- ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ በስምህ ትንቢት
አልተናገርንምን? በስምህስ አጋንንትን አላወጣንምን? በስምህስ ብዙ ተዓምራትን
አላደረግንምን? ይሉኛል፡፡ የዚያን ጊዜም፡- ከቶ አላወቅኋችሁም፤ እናንተ
ዓመጸኞች ከእኔ ራቁ ብዬ እመሰክርባቸዋለሁ፡፡ ስለዚህ ይህን ቃሌን ሰምቶ
የሚያደርገው ሁሉ ቤቱን በዓለት የሰራ ልባም ሰውን ይመስላል፡፡ ዝናብም
ወረደ፤ ጎርፍም መጣ፤ ነፋስም ነፈሰ፤ ያንም ቤት ገፋው፤ በዓለት ላይም
ስለተመሰረተ አልወደቀም፡፡ ይህንም ቃሌን ሰምቶ የማያደርገው ሰው ሁሉ ቤቱን
በአሸዋ ላይ የሰራ ሰውን ይመስላል፡፡ ዝናብም ወረደ፤ ጎርፍም መጣ፤ ነፋስም
ነፈሰ፤ ያንም ቤት መታው ወደቀም፡፡ አወዳደቁም ታላቅ ሆነ፡፡››

ጌታችን ለደቀ መዛሙርቱ ‹‹ከፍሬያቸው ታውቁዋቸዋላችሁ›› በማለት


ነገራቸው፡፡ ለኢየሱስ ደቀ መዛሙርት እዚህ ላ ተጠቀሱት ፍሬዎች
የእምነታቸውን የመጨረሻ እርጋታ የሚያመለክት ነው፡፡ በቀላል አነጋገር
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን ከሐጢያት መዳን እግዚአብሄር
የሚደግፈው ፍሬ ነው፡፡ ጥያቄው እነዚህ ፍሬዎች አሉን ወይስ የሉንም የሚለው
ነው፡፡ በእግዚአብሄር ፊት ሐሰተኞች ሳንሆን እውነተኛ ቅዱሳኖች የምንሆንበት
መንገድ የሚገኘው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በሚያምነው እምነት ውስጥ
ነው፡፡ በሌላ አነጋገር በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ስናምን ሐሰተኛ ነቢያቶች
ከመሆን ይልቅ እውነተኛ የእግዚአብሄር ሕዝብ እንሆናለን፡፡ እምነታችን
ገለባዎችን ሳይሆን እውነተኛ ፍሬዎችን ያፈራ ዘንድ ልቦቻችን በውሃውና
በመንፈሱ የወንጌል ቃል ማመን አለባቸው፡፡
ጌታችን እንዲህ ብሎዋል፡- ‹‹መልካም ዛፍ ሁሉ መልካም ፍሬ ያደርጋል፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


206 የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ መፈጸም የሚችለው እምነት

ክፉም ዛፍ ክፉ ፍሬ ያደርጋል፡፡›› ስለዚህ እነርሱን በፍሬዎቻቸው ልናውቃቸው


እንችላለን፡፡

የጌታን ስም ብቻ በመጥራት ከሐጢያቶቻችን ሁሉ መዳንና


የእግዚአብሄር ልጆች መሆን እንችላለን?

ዛሬ የእግዚአብሄርን ፈቃድ ማድረግ ስለሚችል የእምነት ዓይነት


ላካፍላችሁ እፈልጋለሁ፡፡ ኢየሱስ ራሱ በማቴዎስ 7፡21 ላይ እንዲህ ብሎዋል፡-
‹‹የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ
ሰማያት የሚገባ አይደለም፡፡›› በጌታ ፈቃድ መንግሥተ ሰማይ የሚገቡ ሰዎች
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምኑ ናቸው፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
ከማመን የሚወለደው ፍሬ የሐጢያቶች ሁሉ ይቅርታና ጻድቅ መሆን ነው፡፡
ስለዚህ ሰማይ መግባት የሚችሉት የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ የሚያደርጉ ብቻ
ናቸው፡፡ ጌታችን ‹‹የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ የሚለኝ
ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም›› ያለበትን ምክንያት ማወቅ አለብን፡፡
ኢየሱስ በዚህ ምንባብ ላይ እንዲህ ብሎዋል፡- ‹‹ከሰጠኝም ሁሉ አንድን
ስንኳ እንዳላጠፋ በመጨረሻው ቀን እንዳስነሳው እንጂ የላከኝ የአብ ፈቃድ ይህ
ነው፡፡ ልጅንም አይቶ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወትን እንዲያገኝ
የአባቴ ፈቃድ ይህ ነውና፡፡ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሳዋለሁ፡፡›› (ዮሐንስ
6፡39-40) እግዚአብሄር በእርግጥም እኛን ሐጢያተኞችን ሁሉ ከሐጢያቶቻችን
ሊያድነን ይፈልጋል፡፡
ታዲያ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ማመን የሆነውን የእግዚአብሄር አብ
ፈቃድ የሚታዘዝ ማነው? በመጀመሪያ እነርሱ እግዚአብሄር አብ አንድያ ልጁን
ኢየሱስ ክርስቶስን እንደላከ፣ አብ ኢየሱስ የዓለምን ሐጢያቶች በመስቀል ላይ
እንዲሸከም እጆቹና እግሮቹ እንዲቸነከሩና እስከ ሞት ድረስም ደሙን
እንዲያፈስስ በማድረግ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ እንዳነጻና የሐጢያት ኩነኔያችንን
ሁሉ እንደተሸከመ የሚያምኑ ሰዎች ናቸው፡፡
በዚህ የደህንነት እውነት ማመን በሰማይ ባለው የአብ ፈቃድ መሰረት
የሚያምን እምነት ነው፡፡ የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ የሚያደርጉና በዚያው
መሰረት የሚያምኑ ሰዎች በሙሉ ሰማይ ይገባሉ፡፡ ምክንያቱም የእግዚአብሄር ዋና
ፈቃድ በሆነው የውሃና የመንፈስ ወንጌል አምነዋልና፡፡ የእግዚአብሄር አብ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ መፈጸም የሚችለው እምነት 207

የመጨረሻው ችሮታ ይህ ነው፡፡ ሁላችንም ይህንን በግልጽ መረዳት አለብን፡፡


ሁላችንም በደህንነት ወንጌል የሚያምኑ ቅዱሳኖች መሆን አለብን፡፡ የእግዚአብሄር
ልጆች መሆን የምንችለው ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ይቅርታን የምናገኘውና ውሎ
አድሮም ሰማይ የምንገባው የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በማመን ብቻ ነው፡፡
ጌታችን ለሁላችንም ‹‹ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ የሚለኝ ሁሉ መንግስተ ሰማያት
የሚገባ አይደለም›› ሲል ምን ማለቱ ነበር? የዚህ ምንባብ ፍቺ እግዚአብሄር አብ
ባስቀመጠው የሐጢያት ስርየት ማለትም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ከሙሉ
ልብ የሚያምን እምነት የሌላቸው ሰዎች ሰማይ ለመግባት ቢሞክሩም ፈጽሞ
ሰማይ ሊገቡ አይችሉም የሚል ነው፡፡ በሌላ አነጋገር ጌታችን እዚህ ላይ
እያስተማረን ያለው ሰዎች በዕውር ድንብር ‹‹ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ›› በማለት ስሙን
ስለጠሩት ብቻ ሰማይ መግባት የሚችሉበት እምነት አላቸው ማለት እንዳልሆነ
ነው፡፡ ወደ አብ መንግሥት መግባት የሚችሉት በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
አምነው ከሐጢያቶቻቸው ሁሉ የዳኑ ማለትም የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ
የሚያደርጉ ሰዎች ብቻ ናቸው፡፡
ብዙ ክርስቲያኖች ኢየሱስን አዳኛቸው አድርገው ቢያምኑም በመጨረሻ
ሰማይ የማይገቡት ፍጹም የሆነውን የሐጢያት ስርየት ሊሰጣቸው በሚችለው
የውሃና የመንፈስ ወንጌል ቃል የሚያምነው ይህ እምነት ስለሌላቸው ነው፡፡
ጌታችን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ቃል ለእኛ በመስጠት፣ በእርሱም
እንድናምን በማድረግና ይህንን ወንጌል ሙሉ በሙሉ በልቦቻችን ውስጥ
እንድናውቀው በማድረግ አሁን በእምነት ሰማይ እንድንገባ አስችሎናል፡፡
በእርግጥ ሁላችንም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ቃል የሚያምን ይህ እምነት
ቢኖረን ማናችንም የሐጢያት ስርየትን የማናገኝበት ምከንያትም ሆነ፡፡ ሰማይ
መግባት የማንችልበት ምክንያት አይኖርም፡፡
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ላይ እምነት ካለን ይህ ማለት ሁላችንም
የሐጢያቶቻችንን ስርየት እንድንቀበልና እንድንጸድቅ፣ የእግዚአብሄር ልጆች
መሆን የሚያስችለን፣ ሰማይ የሚያስገባንና በእርሱ የሚያኖረን እምነት ይኖረናል
ማለት ነው፡፡ በአጭሩ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምን ይህ እምነት
ያላቸው ሰዎች ከሐጢያቶቻቸው ሁሉ ስርየትን ስላገኙ ሁሉም ሰማይ መግባት
ይችላሉ፡፡ ይህ እምነት የሌላቸው ብዙ ክርስቲያኖች ግን ኢየሱስ አዳኛቸው
አድርገው ቢያምኑም እንኳን በመጨረሻ ሰማይ ሊገቡ አይችሉም፡፡ ምክንያቱም
በዚህ የውሃና የመንፈስ ወንጌል ባለ ማመናቸው ሐጢያተኞች ሆነው ቀርተዋል፡፡
ጌታችን ሰማይ ለመግባት የአብን ፈቃድ ማድረግ እንዳለብን ተናግሮዋል፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


208 የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ መፈጸም የሚችለው እምነት

በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምን ይህ እምነት ሲኖራችሁ የአብን ፈቃድ


ማድረግ ይቻላችኋል፡፡ እስክንሞት ደረስ በደመ ነፍስ ሐጢያቶችን ከመስራት
መቆጠብ ባንችልም በዚህ የውሃና የመንፈስ ወንጌል ቃል ስናምንና ስናውቀው
በእግዚአብሄር ፊት ከሐጢያቶቻችን ሁሉ መንጻት እንችላለን፡፡
የእግዚአብሄርን ፈቃድ ማድረግ ማለት የእርሱን በጎ ሥራዎች መስራት
ማለትም የውሃውንና የመንፈሱ ወንጌል በማሰራጨት ነፍሳቶችን ማዳን ነው፡፡
ስለዚህ የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ መከተል የምንፈልግ ከሆንን በመጀመሪያ
ፍጹም በሆነው የእርሱ እውነት በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ማመን
ይኖርብናል፡፡ ያንን እስካላደረግን ድረስ ትክክል የሆነውን ነገር ማድረግ
አንችልም፡፡ ምክንያቱም ሐጢያቶቻችንን በሙሉ አሁንም ድረስ በልቦቻችን
ውስጥ አብረውን አሉና፡፡ በሌላ አነጋገር የእግዚአብሄርን መልካም ሥራዎች
ለመስራት በመጀመሪያ ዳግመኛ መወለድ ይኖርብናል፡፡ (ኤፌሶን 2፡10)
እኛ በምናስፋፋው የውሃና የመንፈስ ወንጌል ቃል የሚያምን ሁሉ
የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ የማድረግ አቅም አለው፡፡ ስለዚህ በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል የሚያምኑና ይህንን ወንጌል የሚያውቁ ሰዎች ይህንን የውሃና
የመንፈስ ወንጌል በሙሉ አመኔታ ለሐጢያተኞች ሁሉ የሚያሰራጩ ሰዎች
ናቸው፡፡ ይህንን የእውነት ወንጌል በመስበካቸው ቢሰደዱና ችግሮች
ቢገጥሙዋቸውም በመጨረሻ ሁሉም የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ የሚያደርጉ
ሰዎች ይሆናሉ፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምነው ይህ እምነት ሲኖረን
የእግዚአብሄርን ፈቃድ በተሳካ መንገድ የሚያደርጉ ሰዎች እንሆናለን፡፡
በሌላ በኩል እግዚአብሄር በሰጠው የውሃና የመንፈስ ወንጌል ባናምን
የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ ማድረግ አንችልም፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
ካላመንንና ከሐጢያቶቻችን ካላዳነን በሰማይ ባለው የእግዚአብሄር አብ ፈቃድ
መሰረት መኖር ብንፈልግም በሐጢያት ባርነት ውስጥ መኖራችንን ከመቀጠል
ማምለጥ አንችልም፡፡ ነገር ግን እኛ ከሙሉ ልባችን በእግዚአብሄር ወንጌል
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ስለምናምን ሁላችንም እግዚአብሄርን በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት በማገልገል የአብን ፈቃድ የምናደርግ ሰዎች
ሆነናል፡፡
ወንድሞችና እህቶች ትክክለኛው የእግዚአብሄር ፈቃድ ዕውቀት ያገኘነው
መቼ ነበር? የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ቃል ከእግዚአብሄር ቃል ውስጥ
መረዳትና ማመን በቻልንበት ጊዜ ነበር፡፡ በእግዚአብሄር ቃል የማናምን ከሆንን
በዚህ ዓለም ላይ የእግዚአብሄርን ፈቃድ ማወቅም ሆነ ፈቃዱን ማድረግ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ መፈጸም የሚችለው እምነት 209

አንችልም፡፡ ባልንጀራዎቻችንን ለመውደድ የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ ለማድረግ


በገባነው ቃል መሰረት የተራቡትን ብናበላ፣ የታመሙትን ብናስታምምና ወላጅ
አልባዎችንም ብንንከባከብም ይህ በእርግጥም የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ
ከማድረግ በጣም የተለየ ነው፡፡ የእግዚአብሄርን ፈቃድ በማድረግ ውስጥ
መልካም የሆኑ የሥጋ ምግባሮቻችን ጌታችን በሰጠን የውሃና የመንፈስ ወንጌል
የሚያምነውን እምነት መተካት አይችሉም፡፡
በዚህ ዓለም ላይ ያለ በጎ ምግባር ሐጢያተኞችን የሚያድነውን የአብ
ፈቃድ የሆነውን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምን እምነት መቼም ቢሆን
መተካት አይችልም፡፡ በውሃወና በመንፈሱ ወንጌል በማመንና ይህንንም ወንጌል
በመላው ዓለም በማሰራጨት የአብን ፈቃድ ማድረግ መቻላችን በሥጋችን
በምናደርጋቸው በማናቸውም በጎ ምግባሮች ሊተካ አይችልም፡፡ ይህንን አስገራሚ
እውነት ለአንዴና ለመጨረሻ በመረዳት ዳግመኛ እምነታችን ስለ አብ ፈቃድ
ፈጽሞ ግራ እንዲጋባ መፍቀድ የለብንም፡፡
ሆኖም በዚህ ዓለም ላይ በሥጋቸው በጎ ምግባሮችን በማድረግ የአብን
ፈቃድ ለመተካት የሚሞክሩ በጣም ብዙ ሰዎች አሉ፡፡ እኛ የአብን ፈቃድ
የምናደርግና የውሃውንና የመንፈሱንም ወንጌል በመላው ዓለም ላይ ማገልገል
የምንችል ሰዎች የሆንነው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ቃል በማመን
የሐጢያቶቻችንን ስርየት ስለተቀበልን ነው፡፡
ወደ መንፈሳዊው የእምነት ሕይወታችን ስንመጣ የውሃውንና የመንፈሱን
ወንጌል ቃል በማመን የአብን ፈቃድ ማድረጋችን ትክክል እንደሆነ ማመን
አለብን፡፡ ያንን ለማድረግ በመጀመሪያ እውነተኛውን ወንጌል ማወቅ አለብን፡፡
አንድ ሐጢያተኛ የእግዚአብሄር ፈቃድ ምን እንደሆነ እንኳን ሳያውቅ
የእግዚአብሄርን ፈቃድ እንዴት ማድረግ ይቻለዋል? እንደ እግዚአብሄር አብ
ፈቃድ እንኖር ዘንድ የሚፈቅድልን እምነት ምን ዓይነት እምነት እንደሆነ ካላወቅን
በሰማይ ያለውን የአብ ፈቃድ ለማድረግ የሚያስችል ጉልበት ፈጽሞ አይኖረንም፡፡
ስለዚህ በመጀመሪያ የእግዚአብሄርን ፈቃድ በያዘው በዚህ ወንጌል በማመን
የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ ወደምናደርግበት አቅም ላይ መድረስ አለብን፡፡
በአጭሩ በመንፈሱ ወንጌል የሚያምን እምነት ከሌለን ውሎ አድሮ እግዚአብሄር
ይተወናል፡፡ ምክንያቱም ይህ ዓይነቱ እምነታችን ከእርሱ ፈቃድ ጋር ምንም
የሚያገናኘው ነገር የለምና፡፡ በእርግጥ በእግዚአብሄር ቃል እናምን እንደሆነ
ወይም እንዳልሆነ በእርግጥ በልቦቻችን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል እናምን
እንደሆነ ራሳችንን መፈተሽ የሚገባን ለዚህ ነው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


210 የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ መፈጸም የሚችለው እምነት

እንደ እግዚአብሄር ፈቃድ የማይኖሩ ሰዎች መጨረሻቸው የእርሱን


ቤተክርስቲያን ትተው መውጣት ነው፡፡ ምክንያቱም ከሌላው ሁሉ በላይ እዚህ
ግባ የማይባለውን የስጋቸውን ፍትወት ማሸነፍ አይችሉምና፡፡ ወይም
መጨረሻቸው ራሳቸውን በበግ ለምድ ሸፍነው በማቅረብ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም
የራሳቸውን ፈቃድ የሚሹ ሐሰተኛ ነቢያቶች መሆን ይሆናል፡፡ ነገር ግን
የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል በሰማይ ያለው የእግዚአብሄር ፈቃድ ስለሆነ በዚህ
የእውነት ወንጌል የሚያምኑ ሰዎች ኑሮዋቸውን ሲኖሩ የአብን ፈቃድ በመንፈስ
ቅዱስ ሐይል የሚከተሉበትን ጉልበት ማግኘት ይችላሉ፡፡
እግዚአብሄር ለእኛ ያለውን በጎ ፈቃድ ለማወቅና እርሱንም ለመከተል
ከልባችን ከፈለግን በመጀመሪያ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ማመን አለብን፡፡
በእርግጥ የእግዚአብሄር ቃል እውነት ነው ብለን ካመንን መጽሐፍ ቅዱስ አሳማኝ
ባይመስል እንኳን በእግዚአብሄር ውስጥ ለተገለጠው የውሃና የመንፈስ ወንጌል
መገዛት አለብን፡፡ ሁላችንም በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በተገለጠው የእግዚአብሄር
ፈቃድ ብናምን ሁላችንም የእርሱን ፈቃድ በማድረግ እርሱን ልናስደስተው
እንችላለን፡፡ የእነዚህ ሰዎች እምነት ለዘላለም ጸንቶ የሚቆም ነውና፡፡ የጥድ ዛፎች
ቀጥ ብለው ወደ ሰማይ እንደሚያድጉ ሁሉ በእግዚአብሄር ቃል የሚያምኑ
ሰዎችም የእግዚአብሄርን ፈቃድ ለመከተል የማይበገር ሐይል አላቸው፡፡
እምነታችሁ የእግዚአብሄር ቃል በሆነው የውሃና የመንፈስ ወንጌል ላይ
የተመሰረተ ከሆነና በዚህም የሐጢያቶቻችሁን ስርየት ከተቀበላችሁ ይህ በሐይል
የተሞላ እምነት ሁልጊዜም የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ እንድታደርጉ ጉልበትን
ይሰጣችኋል፡፡ ሌሎች ሲያዩዋችሁ ያፈጠጡ ድክመቶች ቢኖሩባችሁም በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል የሚያምን ይህ እምነት ካላችሁ አብርሃም የነበረው ዓይነት
ተዓማኒ የሆነ እምነት ሊኖራችሁ ይችላል፡፡ ሁላችንም በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል በማመን የሐጢያቶቻችንን ስርየት ሁሉ የሚሰጠንና ሰማይ መግባት
የሚያስችለን ይህ እምነት እንዲኖረን ማድረግ አለብን፡፡ ሕይወታችንን
የምንኖረው የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ በመታዘዝና በማድረግ ነው፡፡ ከዚያም
በመጨረሻ ሁላችንም ወደ መንግሥቱ እንገባለን፡፡
ስለዚህ እናንተና እኔ ሁልጊዜም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ላይ ያለንን
እምነት አጥብቀን መያዝ ይገባናል፡፡ ሁኔታዎቻችንን የሙጥኝ ብለን ከመያዝ
ይልቅ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ቃል ላይ ያለንን እምነታችንን መጠበቅ
አለብን፡፡ እርሱ እስከሚመለስበት ቀን ድረስም ወንጌልን በታማኝነት
ማሰራጨትና ጌታን መጠበቅ አለብን፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ መፈጸም የሚችለው እምነት 211

የሐጢያት ስርየትን በእምነት የተቀበሉ ጻድቃኖችም እንደዚሁ ሁልጊዜ


ከፍታዎችና ዝቅታዎች ይገጥሙዋቸዋል፡፡ በተፈጥሮ ውስጥ አራት የተለያዩ
የጸደይ፣ የበጋ፣ የበልግና የክረምት ወቅቶች እንዳሉ ሁሉ ጻድቃኖችም እንደዚሁ
በተለያዩ ጊዜያቶች የተለያዩ ሁኔታዎች ይገጥሙዋቸዋል፡፡ አንዳንድ ጊዜ ሞቃትና
የሚያነቃቃ ነው፡፡ ሌላ ጊዜ ደግሞ ስልቹነትና ስቃይ ነው፡፡ በሌላ አጋጣሚ
ደግሞ ሰላማዊ ሁኔታ ይገጥማቸዋል፡፡
ሆኖም እምነታችን በማንኛውም ጊዜ ከሚከሰቱ ሁኔታዎቻችን ጋር
ይለያያሉ፡፡ ሁኔታዎቻችን ልክ እንደዚህ ብዙ ቢለዋወጡም በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል ላይ ያለን እምነት በማናቸውም ሁኔታዎች ውስጥ ከቶውኑም ሳይለወጥ
ሁልጊዜም ከሁሉም እርግማኖች ይከላከልልናል፤ ይጠብቀንማል፡፡ በእግዚአብሄር
ቃል የምናምን ከሆንን በዚህ እምነት ምክንያት ከቶውኑም ቢሆን መንፈሳዊ
ድርቀት ውስጥ አንገባም ወይም በክረምታችን ውስጥ እስከ ሞት ደረስ
አንቀዘቅዝም፡፡ በበጋም ከሙቀት የተነሳ አንሞትም፤ በበልግም ባዶነት ውስጥ
አንወድቅም፡፡ በጸደይ ወቅትም ወደ ዓለም አንሳብም፡፡ በመንፈሳዊ ሕይወታችን
ውስጥ ምንም ያህል ከፍታዎችና ዝቅታዎች ቢገጥሙንም ሁልጊዜም
የእግዚአብሄርን ፈቃድ ለዘላለም እናደርጋለን፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
የሚያምን እምነት ካለን ችግሮቻችንን ሁሉ ማሸነፍ እንችላለን፡፡ በዚህ እምነትም
በእግዚአብሄር አብ ፊት ፈቃዱን እያደረግን እጅግ ያማረ ሕይወትን መኖር
እንችላለን፡፡
የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ሁላችንንም በእግዚአብሄር ፈቃድ መሰረት
የሚኖሩ ሰዎች አድርጎ ሊለውጠን ብቃት አለው፡፡ እናንተና እኔ ሁልጊዜም
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ላይ ያለንን እምነት መጠበቅ የሚገባን ለዚህ ነው፡፡
እንዲህ በማድረግ የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ በመታዘዝ መኖር እንችላለን፡፡
አሁን በእግዚአብሄር ቃል እየኖራችሁ ነውን? ወይስ በሁኔታዎቻችሁ ታስራችሁ
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ቃል በማመን መኖር አልቻላችሁም? የኋለኛው
ከሆነ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ሐይል በትክክል ታምኑ እንደሆነ ወይም
እንዳልሆነ ራሳችሁን ጠይቁ፡፡ በተጻፈው የእግዚአብሄር ቃል ውስጥ በሚገኘው
የውሃና የመንፈስ ወንጌል ማመን አለብን፡፡ ይህ ወንጌል በሰጠን ሐይልም መኖር
አለብን፡፡ ተጨባጭ በሆነው የውሃና የመንፈስ ወንጌል አማካይነትም
የእግዚአብሄርን ሐይል በመቀበል ሕይወታችንን ፍሬያማ በሆነ ደስታ መኖር
እንደሚገባን ግልጽ ነው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


212 የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ መፈጸም የሚችለው እምነት

ብርቱ በሆነው የእግዚአብሄር ቃል ማመን አለብን፡፡

ታደርጉት ዘንድ ፈጽሜ ልጠይቃችሁ የምፈልገው አንድ ነገር በእምነታችሁ


የተጻፈውን የእግዚአብሄር ቃል እያንዳንዱን ምንባብ አጥብቃችሁ ትይዙ ዘንድ
ነው፡፡ የእግዚአብሄር ቃል የሆነውን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል እንድታምኑ
አጥብቄ እመኝላችኋለሁ፡፡ እንደዚያ ካላደረጋችሁ ከምትሰሩዋቸው ሐጢያቶች
የተነሳ እምነታችሁ በማንኛውም ጊዜ ሊወድቅ ይችላል፡፡ ለእነዚህ ሐጢያቶች
የተነሳም እናንተ ራሳችሁ ለጥፋት ትታጫላችሁ፡፡ ሁላችንም የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል ቃል አጥብቀን መያዝ አለብን፡፡ እንደዚህ ካላደረግን ለአንድም
ቀን እንኳን ቀጥ ብለን መቆም አንችልም፡፡ መቆም አለመቻል ብቻ ሳይሆን በሞት
ሸለቆ ውስጥ ለመኖር የታጨን ልንሆን እንችላለን፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ አዘውትሮ ‹‹የእምነት ሥራ፣ የፍቅር ልፋትና የተስፋ
ትዕግስት›› (1ኛ ተሰሎንቄ 1፡3) ዳግመኛ ለተወለዱ ቅዱሳን አስፈላጊ ጸጋዎች
መሆናቸውን አውስቷል፡፡ እኛ ሰማይ የምንገባበት ተስፋና ከእግዚአብሄር
የተቀበልነው ፍቅር ቢኖረንም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምን እምነት
እስከሌለን ድረስ ምንም አይደለንም፡፡ እንደዚህ ዓይነት ክቡር ሕይወት
እንድንኖር ሐይልን የሚያስታጥቀን ይህ የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ብቻ
ነውና፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ካላመናችሁ የተባረከው የመጽሐፍ ቅዱስ
የትንቢት ቃል ሁሉ የሌላ ሰው እንጂ የእናንተ አይሆንም፡፡
ወደፊት ሰማይ እንደምትገቡ ታምኑ ይሆናል፡፡ ነገር ግን ልቦቻችሁ
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል እስካላመኑና ይህንን አሁኑኑ አጥብቃችሁ
እስካልያዛችሁ ድረስ ሕይወታችሁ አብቅቶለት ሊሆን ይችላል፡፡ በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል ቃል የሚያምን እውነተኛ እምነት ከሌለን በሕይወት መኖር
መቀጠል አንችልም፡፡ የእግዚአብሄር ቃል ካልቀረበልን፣ ያንንም ቃል አሁኑኑ
ካልተመገብን ነፍሳችን እስከ ሞት ድረስ ትራባለች፡፡
እውነተኛ እምነት የተመሰረተው ምን ላይ ነው? እውነተኛ እምነት
በተጻፈው የእግዚአብሄር ቃል ላይ መመስረት አለበት፡፡
እኔ ገና ዳግመኛ ሳልወለድ በፊት ያለኝን ሐብት በሙሉ ለእግዚአብሄር
ብሰጥ እውነተኛ እምነት ይኖረኝ ነበር ብዬ ማሰብ አዘወትር ነበር፡፡ ነገር ግን
የነበረኝን ሁሉ ብሰጥና ሁሉንም ለእግዚአብሄር ከሰጠሁ በኋላ ምንም ነገር
ባይተርፈኝ በዚህ ቀዝቃዛና ራስ ወዳድ ዓለም ውስጥ ለመኖር ስፍጨረጨር
ችግር ይገጥመኛል ብዬ ተጨነቅሁ፡፡ በነገራችን ላይ ያለኝን ሁሉ መስጠት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ መፈጸም የሚችለው እምነት 213

ባልችልም የድህነት ሕይወት ለእኔ ሁልጊዜም የክርስቲያን እምነት ተምሳሌት


ነበር፡፡
ዳግመኛ ከመወለዴ በፊት ሁልጊዜም በራሴ ስሜት መሞላት በራሱ እምነት
ነው ብዬ አስብ ነበር፡፡ ስለዚህ የፍቅርና የአምልኮ ስሜቴን ከፍ ለማድረግ
የቤተክርስቲያን ጉባኤዎች ላይ መገኘት፣ መጾምና የተቸገሩትን መርዳት ወ.ዘ.ተ
የመሳሰሉትን ነገሮች ማድረግ አዘወትር ነበር፡፡ ነገር ግን የዚህ ዓይነቱ በሕግ ላይ
የተመሰረተ እምነት ብዙ ስላደከመኝ ዳግመኛ በእምነት መኖር አልቻልሁም፡፡
በራሴ ስሜቶች እስካልተሞላሁ ድረስ አንድ ነገር የጎደለ ይመስል ልቤ ባዶ የሆነ
ይመስለኝ ስለነበር ይህ የእምነት ጉድለት ምልክት ነበር ብዬ አስብ ነበር፡፡
ታዲያ ከዚህ ቀደም ከነበረኝ ከዚህ ባዶ እምነት ፈጽሞ የተለየውን
እውነተኛ እምነቴን እንዴት አገኘሁት? ያገኘሁት በተጻፈው የውሃውና የመንፈሱ
ወንጌል ቃል ውስጥ ነው፡፡ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል የያዘው የእውነት ቃል
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስለተጻፈ ይህንን የእግዚአብሄር ቃል በማመን
ከሐጢያቶቼ ሁሉ ይቅርታን ማግኘት ችያለሁ፡፡ በዚህ እምነትም ለሰው ሁሉ
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ታላቅነት መናገር ችያለሁ፡፡ በሌላ አነጋገር
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ ማድረግና
በፊቱም በድፍረት መቆም ችያለሁ፡፡ የእግዚአብሄር ቃል እስከ ዛሬ ድረስ በዚህ
መንገድ ደግፎ ስላቆመኝ በኢየሱስ ክርስቶስ በመኖር ቀጥያለሁ፡፡ በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል የሚያምን ይህ እምነት ባይኖረኝ ኖሮ ነፍሱ አሁንም ድረስ
ለሲዖል የታጨች ትሆን ነበር፡፡
ውድ ክርስቲያኖች በልቦቻችሁ ውስጥ የእግዚአብሄር ቃል ከሌለ
የምታምኑት በምንድነው? ይህ ማለት እናንተ በእርግጥ የምታምኑት
በስሜቶቻችሁ ነው ማለት ነው፡፡ የሥጋ ዓይኖቻችን እናምነዋለን የምትሉትን
አምላካችንን አያዩም፡፡ ታዲያ በእግዚአብሄር የምታምኑት በምን ላይ
ተመስርታችሁ ይሆን?
ጸሎቶቻችሁ ምላሽ ቢያገኙ ወይም ባያገኙ እምነታችሁን በጸሎት
ልምምዶቻችሁ ላይ ከማሳረፍ በቀር ሌላ ምርጫ የላችሁም፡፡ ነገር ግን
እግዚአብሄር በጸሎቶቻችሁ ባይረካና መልስ ባይሰጣችሁስ? እግዚአብሄር
እንዳንስት ሲል አንዳንድ ጊዜ የምንጠይቀውን አይመልስልንም፡፡ ታዲያ እንዴት
በእርሱ ልታምኑ ቻላችሁ? እንዴት በእግዚአብሄር ልታምኑና በእምነት
ልትከተሉት ቻላችሁ?
መሰረታችንን በመሰጠታችን ወይም በስሜታችን ላይ ከጣልን በመጨረሻ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


214 የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ መፈጸም የሚችለው እምነት

መቆየት በማያስችሉን የመሰጠት ምግባሮቻችን ላይ እንወድቃለን፡፡ ከዚህ


የተነሳም አለማመን ውስጥ እንወድቅና በእግዚአብሄር ላይ ያለንን እምነት
እንጥለዋለን፡፡ እግዚአብሄር የተጻፈውን ቃሉን የሰጠን ለዚህ ነው፡፡ እርሱ ይህንን
የተጻፈውን ቃል ለእኛ በመስጠት ይህንን የእግዚአብሄር ቃል አጥብቀን በመያዝ
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል እንድንገናኘው አስችሎናል፡፡ በተስፋ ቃሉ በማመን
ተስፋ እንዲኖረንና እስከ መጨረሻው ድረስም የእግዚአብሄርን ፈቃድ
እንድናደርግ አስችሎናል፡፡
የእግዚአብሄርን ቃል አጥብቀን መያዝና በእርሱም ማመን አለብን፡፡
በእርግጥ በቃሉ የሚያምኑና እንደ ሰናፍጭ ቅንጣት የሆነችው እምነት
የሚኖራቸው ሰዎች መሆን የምንችለው ያን ጊዜ ብቻ ነው፡፡ ጌታችን የሰናፍጭ
ቅንጣት የምታህል እምነት ብትኖረን ተራራውን ወደ ባህር መወርወር
እንደምንችል እንደተናገረ ሁሉ ሁላችንም መላውን ዓለም ለክርስቶስ መማረክ
የምንችል የእምነት ሰዎች መሆን እንችላለን፡፡ ስለዚህ እናንተና እኔ
የእግዚአብሄርን ቃል በጽናት አጥብቀን መያዝ አለብን፡፡ ሁላችንም ቃሉን
በትክክል እንደተጻፈው ማመን አለብን፡፡ ያን ጊዜ የአብን ፈቃድ የምናደርግ ሰዎች
እንሆናለን፡፡ ከዚህ የተነሳም ሁላችንም ሰማይ እንገባለን፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስ የመንፈስ ፍሬዎችን እንድናፈራ መክሮናል፡፡ ፍሬዎችን
ማፍራት የሚችለው ሕያውና ጤናማ ዛፍ ብቻ እንደሆነ ሁሉ የእውነተኛውን
እምነት ፍሬዎች ማፍራት የሚችሉትም በእግዚአብሄር ቃል በማመን የዘላለም
ሕይወት ያገኙና ከእግዚአብሄር ጋር ትክክለኛ ግንኙነት ያላቸው ብቻ ናቸው፡፡
ሕይወታቸውን በእግዚአብሄር ላይ ባላቸው እምነታቸው መኖር የሚችሉት
በእግዚአብሄር ቃል የሚያምኑ ብቻ ናቸው፡፡ የእርሱን ሥራ መስራት
የሚችሉትም እነርሱ ናቸው፡፡ ድክመቶች ቢኖርባቸውም በእርሱ ወንጌል በማመን
እግዚአብሄርን መከተል የሚችሉት እነርሱ ናቸው፡፡
በእግዚአብሄር ቃል የሚያምን ይህ እምነት ከሌለን የእርሱን ፈቃድ
መከተል አንችልም፡፡ ሁኔዎቻችን ምንም ይሁኑ የእግዚአብሄርን ቃል አጥብቀን
ከያዝን ይህንን ሁሉ ማድረግ ይቻለናል፡፡ ትልቅ እምነት ከሌላችሁ ለአስራ ሁለት
ዓመት ደም ሲፈሳት የነበረችው ሴት የኢየሱስን ቀሚስ እንደያዘች ሁሉ እናንተም
የእግዚአብሄርን ቃል ጫፍ እንኴን አጥብቃችሁ ያዙ፡፡ አንድ ሰው ቃሉን አጥብቃ
የምትይዝ የሰናፍጭ ቅንጣት የምታህል እምነት ቢኖረው እርሱ የእምነት ሰው
ነው፡፡ በዚህም በትክክል የአብን ፈቃድ ያደርጋል፡፡ ሁላችንም በእግዚአብሄር
ቃል የሚያምኑ የእምነት ሰዎች እንጂ እምነት የለሾች መሆን የለብንም፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ መፈጸም የሚችለው እምነት 215

ለእኛ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ሐይል ማመን በጣም አስፈላጊ


ነው፡፡

በተጨባጭ በእግዚአብሄር የሚያምኑና በእምነት ዓለት ላይ በጽናት


የተተከሉ እነማን ናቸው? እነርሱ በዚህ በተጻፈው የእግዚአብሄር ቃል የሚያምኑ
ሰዎች ናቸው፡፡ ይህንን ማድረግ የማይችሉትስ እነማን ናቸው? እነርሱ በዚህ
በተጻፈው ቃል የማያምኑና በምትኩ ዲያብሎስን የሚያዳምጡ ናቸው፡፡ ከዚህ
የተነሳ እነዚህ ሰዎች የራሱ የዲያብሎስ አገልጋዮች ሆነው ተይዘዋል፡፡
ኢየሱስ በቃሉ የሚያምኑ ምዕመናኖችን በመጠቆም እንዲህ ብሎዋል፡-
‹‹ስለዚህ ይህን ቃሌን ሰምቶ የሚያደርገው ሁሉ ቤቱን በዓለት የሰራ ልባም ሰውን
ይመስላል፡፡ ዝናብም ወረደ፤ ጎርፍም መጣ፤ ነፋስም ነፈሰ፤ ያንም ቤት ገፋው፤
በዓለት ላይም ስለተመሰረተ አልወደቀም፡፡››
በጥንት ዘመን ሰዎች ቤት ሲሰሩ በቤቱ በአራቱም ማዕዘኖች ላይ የማዕዘን
ድንጋዮች የሚሆኑ ትላልቅ ዓለቶችን ያኖራሉ፡፡ እነዚህ ዓለቶች በመሬት ውስጥ
በግማሽ ይቀብሩና ቀሪው ግማሽ ከመሬቱ በላይ ይውላል፡፡ በእነዚህ ዓለቶች
ላይም አንድ ላይ በሚያስተሳስሩዋቸው መሰቀልያ ርብራቦች የተያያዙ ትላልቅ
የዛፍ እንጨቶች አእማዶች ሆነው ይተከላሉ፡፡ ቤቱ ጸንቶ ሊገነባ የሚችለው
በዚህ መሰረታዊ መዋቅር ላይ ነበር፡፡
ታዲያ ጠንካራ እምነት ምንድነው? እዚህ ላይ ዓለቱ የሚያመለክተው ሰው
በእግዚአብሄር ቃል ላይ ያለውን እምነት ነው፡፡ ኢየሱስ የእግዚአብሄርን ቃል
ሰምቶ የሚያደርግ ሰው ቤቱን በዓለት ላይ የመሰረተን ጠቢብ ሰው እንደሚመስል
ተናግሮዋል፡፡ ምክንያቱም እምነቱን ዓለት በሚመስለው የእግዚአብሄር ቃል ላይ
መስርቷልና፡፡ እውነተኛ እምነት የእግዚአብሄር ቃል በሆነው የውሃና የመንፈስ
ወንጌል ማመን ነው፡፡
የእምነታችንን መሰረት በልምምዶቻችን ላይ ለማኖር እናዘነብላለን፡፡
ለምሳሌ አብዛኞቹ ክርስቲያኖች አንድ ሰው በራዕዮች ስላየው ወይም በጸሎቶቹ
ወቅት ስለሰማው ነገር በሚሰጣቸው ምስክርነቶች ይነቃቃሉ፡፡ አንዳች ረቂቅ የሆነ
ነገር ለመለማመድም ይጓጓሉ፡፡ በዛሬው ክርስትና ውስጥ የክርስቲያን ረቂቅ
መንፈሳዊነት የገነነው ለዚህ ነው፡፡ እናንተ ግን እንዲህ ባለ ረቂቅ መንፈሳዊነት
ላይ የተመሰረተ እምነት የሚቆየው እስከ ቀጣዩ ልምምድ ድረስ ብቻ እንደሆነና
ዓይኖቻችን የሚያዩትም የሚታመን እንዳልሆነ ማወቅ ይገባችኋል፡፡ ለምን?
ምክንያቱም እነዚህ ነገሮች ዘላለማዊ ስላልሆኑ በመጨረሻ ሊጠፉ የሚቆዩት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


216 የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ መፈጸም የሚችለው እምነት

ለአጭር ጊዜ ብቻ ሰለሆነ ነው፡፡ ፍጹም ባልሆነ ነገር ማመንም እውነተኛ


እምነትን አይፈጥርም፡፡
በእግዚአብሄር ማመን ፍጹምና ለዘላለም በማይለወጠው የእውነት ቃል
ማመን ማለት ነው፡፡ በዚህ የእግዚአብሄር ቃል ማመንም እውነተኛ መንፈሳዊ
እምነት ነው፡፡ የእግዚአብሄር ወንጌል በሆነው የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ቃል
በማመን የዳኑና በዚህም የአብን ፈቃድ የሚያደርጉ እውነተኛ እምነት ያላቸው
ሰዎች ናቸው፡፡ እግዚአብሄርን በትክክል ማወቅና ማመን የምንችለው በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል ስናምን ብቻ ነው፡፡
ጌታችን የሰጠን የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ፈጽሞ አይለወጥም፡፡ በዚህ
በእውነተኛው ወንጌል የሚያምን እምነት ማለት ሌላ ነገር ሳይሆን ጌታችን
የተናገረውን ማመን ማለት ነው፡፡ እግዚአብሄር የሚደግፈው እምነት ይህንን
ነው፡፡ በዚህ ቃል ስናምን ስሜቶቻችን፣ ሁኔታዎች ወይም ሌላ አንዳች ነገር
ሊያናውጡን ቢሞክሩም ይህንን ቃል አጥብቆ የያዘው እምነታችን ፈጽሞ
አይናወጥም፡፡ ምክንያቱም የእምነታችን መሰረት ፈጽሞ አይናወጥምና፡፡ እናንተና
እኔ በእግዚአብሄር ቃል ማመን ያለብን ለዚህ ነው፡፡ ወንድሞችና እህቶች
በእርግጥ በእግዚአብሄር ቃል ታምናላችሁን? በእርግጥ የእግዚአብሄርን ቃል
አጥብቃችሁ መያዝ ትፈልጋላችሁን? በእርግጥም እናንተ በቀሪው ሕይወታችሁ
የእግዚአብሄርን ቃል አጥብቃችሁ ትይዙ ዘንድ ልባዊ ጸሎቴ ነው፡፡
የእግዚአብሄርን ፈቃድ ያደረጉ ሰዎች ሁሉ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
አምነዋል፡፡ ሁላችንም የምናውቃቸው እንደ ሐዋርያቱ ጳውሎስ፣ ዮሐንስና
ጴጥሮስ ያሉ የእምነት ሰዎች ብዙውን ጊዜ የብሉይ ኪዳንን ቃል ለበርካታ ጊዜ
ጠቅሰዋል፡፡ እነርሱ በብሉይ ኪዳን የተጠቀሰውን አዳኝ በጽናት አምነው የጠበቁ
የእምነት ሰዎች ነበሩ፡፡ በዘመናቸው አዲስ ኪዳን አልነበረም፡፡ ነገር ግን በተጻፈው
የብሉይ ኪዳን ቃልና በውሃና በደም በመጣው ኢየሱስ ክርስቶስ (1ኛ ዮሐንስ
5፡6) በማመናቸው መንፈስ ቅዱስ በውስጣቸው አድሮ በሕይወታቸው ላይ
ሰራ፡፡ ኢየሱስን ከተገናኙባት ቀን ጀምሮም ጌታን መከተል ቻሉ፡፡
እኛም በማይለወጠው የተጻፈ የእግዚአብሄር ቃል በእርግጠኝነት ማመን
አለብን፡፡ እንዲህ በማድረግ ሁላችንም በእግዚአብሄር ፊት ፈጽሞ የማይናወጡ
ሰዎች መሆን አለብን፡፡ እንዲህ በማድረግም የእግዚአብሄርን ፈቃድ መከተል፣
እርሱን የሚያስደስተውን የሕይወት ዓይነት መኖርና መንፈሳዊ ፍሬዎችን
የሚያፈሩ ሰዎች መሆን አለብን፡፡ በእግዚአብሄር ቃል የሚያምኑ ሰዎች ጎርፉ
ቢጎርፍ ነፋሱም ቢነፍስ አይጨነቁም፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ መፈጸም የሚችለው እምነት 217

ነገር ግን የውሃና የመንፈስ ወንጌል በሆነው በዚህ የእግዚአብሄር ቃል


የማያምኑ ሰዎች ጎርፉ ሲጎርፍና ነፋሱ ሲነፍስ ይወድቃሉ፡፡ አወዳደቃቸውም
ታላቅ ይሆናል፡፡ ይህ የሚሆንበት ምክንያት በእግዚአብሄር ላይ ያላቸው እምነት
በራሳቸው አስተሳሰቦች ላይ የተመሰረተ ስለሆነ ነው፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ
አሸዋ ወይም አፈር የሚያመለክተው ሰው ሰራሽ አስተሳሰቦችን ነው፡፡ ለምሳሌ
ያህል ዘፍጥረት ጥንታውያኑ ሰዎች የባቤልን ግምብ በገነቡ ጊዜ ጡቦችንና ሬንጅን
እንደተጠቀሙ ይነግረናል፡፡ ጡቦቹ ከምን የተሰሩ ናቸው? ከምድር አሸዋና አፈር
የተሰሩ ናቸው፡፡ የእግዚአብሄር ቃል እዚህ ላይ የሚነግረን እነርሱ ግምቡን
የገነቡት በራሳቸው ሰው ሰራሽ አስተሳሰቦች መሆኑን ነው፡፡
በዛሬውም ዓለም እንደዚሁ ሰዎች በንጹህ ቅንነት እግዚአብሄር የሰጠውን
ቃል በማመን የእምነት ቤቶቻቸውን ለመኖርያነት መስራት ሲገባቸው
እግዚአብሄርን ለመገዳደር ሲሉ የእምነት ቤቶቻቸውን አሸዋንና ሲሚንቶን
በመደባለቅ በእነዚህ ጡቦች የሚሰሩ ሰዎች አሉ፡፡ በረከሱ ሰው ሰራሽ
አስተሳሰቦች ማመንና በራሱ በሰው ዘር ጥበብ፣ በችሎታዎቻቸውና
በሥልጣናቸው ማመን ቤትን በአሸዋ ላይ መስራት ነው፡፡ ነገር ግን የእግዚአብሄር
ቃል በሆነው የውሃና የመንፈስ ወንጌል ቃል ማመን ልክ እንደ ዓለት የጠነከረ
እምነት ነው፡፡
እምነታችን እንደ ዓለት ጠንካራ እንዲሆን በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ
በተጻፈው በእያንዳንዱ ምንባብ ወደሚያምን የእምነት ዓይነት መመለስ አለብን፡፡
ያንን ስናደርግ እምነታችን ይጠነክራል፡፡ ይህንን የማናደርግና በፈንታው በራሳችን
አስተሳሰቦችና በራሳችን ሁኔታዎች የምናምን ከሆነ ግን ኢየሱስ ራሱ እንደነገረን
እንወድቃለን፡፡ አወዳደቃችንም ታላቅ ይሆናል፡፡ በሌላ አነጋገር በራሳችን
አስተሳሰቦች ማመን ማለት እምነታችን ፈጥኖ ወይም ዘግይቶ ይወድቃል ማለት
ብቻ ነው፡፡ እናንተስ ታዲያ? በእርግጥ በተጻፈው የእግዚአብሄር ቃል
ታምናላችሁን? አዎ ካላችሁ ሁላችሁም ልክ እንደ አብርሃም የእምነት ሰዎች
ናችሁ፡፡
እግዚአብሄር አብርሃምን ከቤተሰቡና ከአባቱ ቤት ተለይቶ አገሩን ትቶ
እርሱ ወደሚያሳየው ምድር እንዲሄድ አዘዘው፡፡ ያን ጊዜ እግዚአብሄር
በአብርሃም ፊት የተገለጠው በመንፈሰ-አካል ነበርን? አይደለም፡፡ እግዚአብሄር
አብርሃምን ያናገረው በቃሉ አማካይነት ነበር፡፡ አብርሃምም በበኩሉ እግዚአብሄር
የነገረውን በመያዝ እግዚአብሄር ወደ መራው ስፍራ ሄደ፡፡ በእግዚአብሄር ቃል
ባይሆን ኖሮ አብርሃም ለሁልጊዜውም በጠፋ ነበር፡፡ ስለዚህ ሁልጊዜ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


218 የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ መፈጸም የሚችለው እምነት

መሰውያዎችን በመስራት ለእግዚአብሄር የሚቃጠሉ መስዋዕቶችን እያቀረበ በዚያ


ይጸልይ ነበር፡፡
አብርሃም መሰውያ ሰርቶ የእምነት ቁርባኑን ለእግዚአብሄር ባቀረበባቸው
በእነዚያ አጋጣሚዎች በአንዱ እግዚአብሄር ዳግመኛ በፊቱ ተገለጠለት፡፡ እንደ
በፊቱ በዚህ ጊዜም መንፈሰ-አካል ሆኖ አልተገለጠለትም፡፡ እግዚአብሄር
በሐምሌት ፊት እንደተገለጠው መንፈሰ-አካል በእርግጥ በፊታችን ቢገለጥ ኖሮ
እግዚአብሄርን ማመን ምንኛ ቀላል በሆነ? ያን ጊዜ ማንኛውም ሰው
እግዚአብሄርን በቀላሉ ማወቅና ማመን ይችል ነበር፡፡ ሆኖም እግዚአብሄርን ያለ
ጥርጥር ማመን አዳጋች ሆኖ የምናገኘው በሙሉ አምሳሉ ስለማይገለጥና እርሱን
መስማት የምንችለውም ለልባችን በሚናገረው በቃሉ በኩል ብቻ በመሆኑ ነው፡፡
አብርሃም ግን እግዚአብሄር የነገረውን መስማት ቻለ፡፡ ዛሬም እንደዚያን ጊዜው
እግዚአብሄር በፊታችን በአምሳሉ አይገለጥም፡፡ ነገር ግን በተጻፈው ቃሉ
አማካይነት በእኩል ደረጃ ራሱን ለእኛ ይገልጣል፡፡ እግዚአብሄር በቃሉ
አማካይነት ለአብርሃም እንደተናገረ ለእኛም ደግሞ በተጻፈው ቃሉ አማካይነት
ይናገረናል፡፡
ለእኛ በእግዚአብሄር ቃል ማመን ማለት ሌላ ነገር ሳይሆን እምነት ማለት
ነው፡፡ ሰው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ላይ እምነት ካለው ታላቅ የእምነት
ሰው ነው፡፡ በእግዚአብሄር ቃል የማምን እኔ ራሴ ታላቅ የእምነት ሰው ነኝ፡፡
እናንተና እኔ ሁላችንም መላውን ዓለም መለወጥ የምንችል የእምነት ሰዎች ነን፡፡
አብርሃም በእግዚአብሄር እንደተባረከ እናንተና እኔም እርሱ ያገኛቸውን እነዚያኑ
በረከቶች መቀበል እንችላለን፡፡
ነገር ግን በእግዚአብሄር ቃል ካላመንን እምነታችን እንደ ሎጥ ዓይነት
እምነት ነው፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን ከሐጢያቶቻቸው የዳኑ
ሰዎች ያሉባቸው ሁኔታዎች የሚሉዋቸውን ነገር የሚከተሉ ከሆኑ የእምነት ሰዎች
አይደሉም፡፡ አብርሃም የእግዚአብሄርን ቃል በትጋት ሲከተል ሎጥ ግን ያለበት
ሁኔታዎች እንዲያደርግ ያዘዙትን ተከተለ፡፡
ሎጥ ከአጎቱ ከአብርሃም ጋር ሲኖር በነበረ ጊዜ ባለጠጋ ሆኖ ነበር፡፡ ነገር
ግን ቀስ በቀስ ከአጎቱ ጋር በመኖር ቢቀጥል በጣም ብዙ ከብቶችን እንደሚያጣ
አሰበ፡፡ ከዚህም በላይ አጎቱ ከዚህ በፊት ለሎጥ ትልቅ አጋዥ የነበረ ቢሆንም
አሁን የአብርሃም እገዛ ለእርሱ ሸክም ብቻ መሰለው፡፡ ስለዚህ ሎጥ ከአጎቱ
ለመለየት ምክንያት ፈለገ፡፡ ተስፋ እንዳደረገውም አንድ ቀን ይህ ምክንያት
ተፈጠረ፡፡ በአብርሃም ከብት እረኞችና በሎጥ ከብት እረኞች መካከል

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ መፈጸም የሚችለው እምነት 219

አለመስማማት ተከሰተ፡፡ ሐብቶቻቸው እጅግ ብዙ ስለነበሩ አብረው መኖር


አልቻሉም፡፡
ስለዚህ አብርሃም እንዲህ ሲል አሰበ፡- ‹‹አሁን ሎጥ በራሱ ሁኔታዎች
እንደሚያምን እያየሁ ነው፡፡ የከለዳውያንን ዑር ትቶ ሲወጣ በእኔ ላይ ተደግፎ
ነበር፡፡ እኔ የማምነውን አምላክ በማመንም እኔን ተከትሎኝ ነበር፡፡ አሁን ግን
ባለጠጋ በመሆኑ በራሱ መንገድ ማድረግ የሚፈልገውን ማንኛውንም ነገር
ማድረግ ፈልጎዋል፡፡›› ከዚያም አብርሃም ሎጥን እንዲህ አለው፡- ‹‹ከፈለግህ ከእኔ
የመለየት ነጻነት አለህ፡፡ አንተ ቀኙን ብትወስድ እኔ ወደ ግራው እሄዳለሁ፤ ወይም
አንተ ወደ ግራው ብትሄድ እኔ ወደ ቀኙ እሄዳለሁ፡፡ የምትሻውን ማንኛውንም
ነገር ወስን፡፡ እዚህ ወይስ እዚያ?››
ሎጥ የመረጠው ስፍራ ውሎ አድሮ የእሳት ኩነኔ የሚገጥመውንና
የሚጠፋውን የሰዶምና የገሞራ ምድር ነበር፡፡ ነገር ግን ይህ ጥፋት ከመምጣቱ
በፊት ያ ምድር ልክ እንደ ኤድን ገነት እጅግ ለም ምድር ነበር፡፡ ይህ ስፍራ
ከብቶችን ለማገድ አመቺ ስፍራ ነበር፡፡ ያን ጊዜ አብርሃም ሎጥን እንዲህ አለው፡-
‹‹አንተ ያንን ስፍራ ስለመረጥህ እኔ ተቃራኒውን እመርጣለሁ፡፡›› ስለዚህ አብርሃም
ሎጥ የመረጠውን ተቃራኒ መረጠ፡፡ ለም ወደሆነው የዮርዳኖስ ሜዳ ከመሄድ
ይልቅ ወደ ተራራማ ስፍራዎች ሄደ፡፡ ለምን? ምክንያቱም አብርሃም የሎጥ ልብ
ትክክል እንዳልነበረ አውቆዋልና፡፡
ያን ጊዜ እግዚአብሄር ለአብርሃም ተገልጦ እንዲህ አለው፡- ‹‹ዓይንህን
አንሳና አንተ ካለህበት ስፍራ ወደ ሰሜንና ወደ ደቡብ ወደ ምሥራቅና ወደ
ምዕራብም እይ፡፡ የምታያትን ምድር ሁሉ ለአንተና ለዘርህ ለዘላለም
እሰጣለሁና፡፡›› (ዘፍጥረት 13፡14-15) እግዚአብሄር ቃል በገባው መሰረት
የተስፋይቱን ምድር በመስጠት በእርግጥም አብርሃምን ባረከው፡፡
የዕብራውያን ሕዝብ አባት የሆነው አብርሃም የከለዳውያንን ዑር ትቶ ወደ
ከንዓን ምድር የተጓዘ የሚቅበዘበዝ ዘላን ነበር፡፡ ‹‹ዕብራዊ›› የሚለው ቃል
‹‹ኤፍራጥስን የተሻገረ ሰው›› ማለት ነው፡፡ በከንዓን ምድር እንግዳ ሆኖ
የተገለለውና የተጠቃው ይህ አብርሃም የእምነት ሰው መሆን የቻለው
በእግዚአብሄር ስላመነ ነበር፡፡
እናንተና እኔም በተጻፈው ቃል ስለምናምን የእምነት ሰዎች ነን፡፡ በጋ
ስለሆነ ይህ የተጻፈው ቀልጦ ይለወጣልን? ክረምት ስለሆነ ረግቶ ይፈረካሳልን?
ሰማያትና ምድር ይለዋወጡ ይሆናል፡፡ ይህ ቃል ግን ከቶውኑም አይለወጥም፡፡
ሁሉ እስኪፈጸም ድረስ የቃሉ አንዲት ነጥብ ወይም ፊደል መቼም ቢሆን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


220 የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ መፈጸም የሚችለው እምነት

አትከስምም፡፡
ማቴዎስ 7፡22 እንዲህ ይላል፡- ‹‹በዚያን ቀን ብዙዎች፡- ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ
በስምህ ትንቢት አልተናገርንምን? በስምህስ አጋንንትን አላወጣንምን? በስምህስ
ብዙ ተዓምራትን አላደረግንምን? ይሉኛል፡፡›› እግዚአብሄር በጻፈው ቃል
የማያምኑ ብዙዎቹ እምነት የለሽ ሰዎች የሚሉት ይህንን ነው፡፡ ይህንን
የተጻፈውን የእግዚአብሄር ቃል ሳያምኑ የሚኖሩ ክርስቲያኖች ምን ያህል ናቸው?
በዚያ ቀን ከእነርሱ ብዙዎቹ ‹‹ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ›› ይላሉ፡፡ ነገር ግን በተጨባጭ
በእግዚአብሄር አላመኑም፡፡ ያመኑት ልክ እንደ ሎጥ በራሳቸው ሁኔታዎች ነው፡፡
ብዙ ክርስቲያኖች በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ቃል እንደማያምኑ የታወቀ
ነው፡፡ የሚያምኑት ከንቱ በሆኑት አስተሳሰቦቻቸው ነው፡፡ ከእነርሱ ብዙዎቹ
የሚያምኑት በራሳቸው አስተሳሰቦች፣ በሐሰት ምልክቶችና በአጋንንቶች ሐይል
ነው፡፡ በዚህ ዓለም ላይ በእግዚአብሄር ቃል ላይ ተመስርተው ሳይሆን በሐሰተኛ
ትምህርቶችና በአጋንንቶች ሐይል ላይ ተመስርተው የሚያምኑ ብዙ ‹‹ዕውር
ክርስቲያን›› ተብዬዎች አሉ፡፡ ዳግመኛ ባልተወለዱት መካከል በአጋንንቶች
የተያዙ በርካታ ሰዎች አሉ፡፡ በተቀበሉት በዚህ አጋንንታዊ ሐይል ላይ
ተመስርተው በኢየሱስ እናምናለን ይላሉ፡፡ ይህ ለእናንተ የማይመስል መስሎ
ይታያችኋልን? የዛሬው ዋናው ምንባብ በትክክል የሚለው ይህንን አይደለምን?
በእርግጥም ከላይ በማቴዎስ 7፡22 ላይ የተጠቀሰው ምንባብ የሚለው ይህንኑ
ነው፡፡ ‹‹በስምህ ትንቢት አልተናገርንምን? በስምህስ አጋንንትን አላወጣንምን?
በስምህስ ብዙ ተዓምራትን አላደረግንምን?››
አጋንንት የያዛቸው ሰዎች አጋንንቶችን በመለየትና እነርሱን በማስወጣት
የተካኑ ናቸው፡፡ ትንቢት በመናገርም የተካኑ ናቸው፡፡ አንዳንድ ጠንቋዮች
አንዳንድ ጊዜ የወደፊቱን የመተንበይ ብልህ ችሎታ ያላቸው አይመስሉምን? በጌታ
ስም ትንቢት የሚናገሩ፣ በስሙ አጋንንቶችን የሚያወጡና በስሙ ብዙ ድንቆችን
የሚያደርጉ ሰዎች አጋንንት ከያዙዋቸው ከእነዚህ ጠንቋዮች አይለዩም፡፡ እነዚህ
ሰዎች በአጋንንት ተይዘው ለመረዳት የሚያዳግቱ፣ የማይጣጣሙና ፈጽመው ግራ
የሚያጋቡ አይረቤ ነገሮችን የሚናገሩባቸው ብዙ ስፍራዎች አሉ፡፡
‹‹ቫይንያርድ ፌሎውሺፕ›› ተብሎ ስለሚጠራ የመናፍቅ ቡድን ሰምታችሁ
ይሆናል፡፡ እነርሱ ‹‹መንፈስ ቅዱስ›› ሲወርድባቸው ከቁጥጥር ውጭ በሆነ ሳቅ
እንደሚጠለቀለቁ፣ እንደ በግ፣ ፈረሶች ወይም እንደሚያገሱ አንበሶች የእንስሶችን
ድምጽ እንደሚያወጡና ሚዛናቸውን ስተው እንደ ወፈፌ በመሳቅ ‹‹መንፈሳዊ
ስካር›› ብለው የሚጠሩትን እንደሚለማመዱ አበክረው ይናገራሉ፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ መፈጸም የሚችለው እምነት 221

ወደ እነርሱ ጉባኤ የሚሄድ ሰው ሁሉ በአጋንንት የተያዘ መሆን አለበት


ወይም በዚያ ቡድን ውስጥ እስከ መጨረሻው አይቆይም፡፡ ዳግመኛ ያልተወለዱ
ሰዎች በአጋንንቶች እስካልተያዙ ድረስ በኢየሱስ የማመንን ደስታ አይረዱም፡፡
በሌላ አነጋገር ሐይማኖታዊው ኑሮዋቸው በአጋንንት እስካልተያዙ ድረስ ደስታን
አይሰጣቸውም፡፡
ዳግመኛ ከመወለዳችሁ በፊት አንዳንዶቻችሁ ያን ጊዜ ክርስቲያን
ሐጢያተኞች ሆናችሁ በልሳን ተናግራችሁ አታውቁምን? እነዚህ ግራ የተጋቡ
ክርስቲያኖች በልሳን እስካልተናገሩ ድረስ አንድ የሆነ ደስታ የጠፋባቸው ይመስል
አይደሰቱም፡፡ ስለዚህ ሁሉንም ዓይነት ስሜት የማይሰጡ፣ ፈጽመው ግራ
የሚያጋቡና ትርጉም የለሽ ቃሎችን እየደጋገሙ ይናገራሉ፡፡ በልሳን መናገር
ማለትም ይህ ነው ብለው በመገመት ያምናሉ፡፡
ነገር ግን ይህ ክፉ መናፍስቶች ወደ ውስጣቸው ገብተው ፈጽሞ ስሜት
የማይሰጡ፣ ሊስተዋሉ የማይችሉ ቃሎችን በመናገር እንዲቀጥሉ እያደረጉዋቸው
መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡ በሌላ አነጋገር የአጋንንቶችን ሐይል ስለጠጡ ጥሩ
ስሜት ይሰማቸዋል፡፡ ሰውነቶቻቸው በአንድ በማይታወቅ ሐይል ከፈቃዳቸው
ውጭ ሊንሳፈፉ እንደሚችሉ፣ በጉልበቶቻቸው ሲዘሉም ጉልበቶቻቸው ቢያንስ
በ10 ኢንች ከወለሉ በላይ እንደሚንሳፈፉ የሚናገሩ፣ እጅግ ሩቅ በሆኑ ተራራዎች
ላይ ወጥተው በጸሎት ሲጠመዱ እንደማይፈሩ የሚናገሩ፣ ከእነርሱ መለኮታዊ
ሐይል እንደሚፈነጥቅ የሚናገሩ፣ አንድን ሰው ማንኛውንም ሰው ይዘው
እጆቻቸውን በእርሱ ላይ በመጫን መጸለይ እንደሚፈልጉ የሚናገሩ ሰዎች በሙሉ
አጋንንት የያዛቸው ሰዎች ናቸው፡፡ እነዚህ ሰዎች አጋንንት የያዛቸውን ሌሎች
ሰዎች ሲያዩ ‹‹አንተ ሰይጣን ከእኔ ራቅ! በኢየሱስ ስም ውጣ!›› ይላሉ፡፡ ይህንን
የሚሉት አጋንንቶች የሚወጡት እንደዚህ ነው ብለው ስለሚያስቡ ነው፡፡
በተጨባጭ ግን ማንኛውም አጋንንት የሚወጣበት ምክንያት እርሱን
ከሚያስወጣውና አጋንንት ከያዘው ሰው ይልቅ ደካማ በመሆኑ ነው፡
ስለዚህ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ቃል የማያምኑ ሰዎች ዓመጻን
የሚያደርጉ ሰዎች ናቸው፡፡ የእግዚአብሄርን ቃል አጥብቆ መያዝ ያለበት ለዚህ
ነው፡፡ የእግዚአብሄርን ቃል በየቀኑ አጥብቀን መያዝ አለብን፡፡ ጌታችን
እስከሚመለስበት ቀን ድረስ አጥብቀን ልንይዘው ይገባናል፡፡ ደህንነትን
ያመጣልንን ቃል በማናቸውም ጊዜ ሁልጊዜም አጥብቀን ልንይዘው ይገባናል፡፡
ይህ ቃል ከዚህ በፊት የነበረው ዓይነት ያው ሐይል አለው፡፡ ምክንያቱም ሕያውና
ብርቱ የእግዚአበሄር ቃል ነውና፡፡ በዚህ ቃል ውስጥ ያሉት ሐይል፣ እውነት፣

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


222 የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ መፈጸም የሚችለው እምነት

ጉልበት፣ ፍቅርና ደህንነት ሁልጊዜም እዚያው ናቸው፡፡


ስለዚህ ይህ ቃል ልቦቻችንን ይለውጣል፡፡ ጉልበትን ይሰጠናል፡፡
በእምነትም አጽንቶ ይይዘናል፡፡ ስለዚህ እውነተኛ እምነት የሚኖረን በቃሉ
በማመንና እርሱን አጥብቀን በመያዝ ነው፡፡ ጌታችን እንዳለው ተራሮችንም
እንኳን ማንቀሳቀስ የምንችለውና የጌታችንን ፈቃድ የምናደርገው፣ እስከ መጨረሻ
ድረስም እርሱን የምንከተለው ይህንን እምነት በመያዝ ነው፡፡ የዚህ ሁሉ
ውጤትም የእግዚአብሄር ጽድቅ አገልጋዮች የመንግሥቱ ሰራተኞች መሆን ነው፡፡
ይህ እንደዚህ ከሆነ ሁላችንም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት
የፈለቀውን የእግዚአብሄር ቃል የሚያምን ይህ እምነት ሊኖረን ፈጽሞ አስፈላጊ
ነው፡፡ የእግዚአብሄርን ቃል ብታምኑና አጥብቃችሁ ብትይዙት ሁላችሁም የእርሱ
ሕዝብ ትሆናላችሁ፡፡ በእርግጥ በእግዚአብሄር ቃል ካመናችሁ የውሃውና
የመንፈሱ ወንጌል ቃል እንዴት በስፋት በመላው መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ
እንደሚገኝ ልታውቁ ይገባችኋል፡፡
ነገር ግን ቀድሞውኑም በዚህ ወንጌል በማመን የሐጢያቶቻችሁን ስርየት
ብትቀበሉም እንኳን የተጻፈውን የእግዚአብሄር ቃል አጥብቃችሁ በመያዝ
ቀጥሉ፡፡ ይህንን ማድረግ ካቃታችሁ እምነታችሁ በማንኛውም ጊዜ ይስታል፡፡
የእግዚአብሄርን ቃል አጥብቀን እስካልያዝን ድረስ እንከን ያለባቸውን
አስተሳሰቦቻችንን የሙጥኝ ብለን እንይዛቸዋለን፡፡ ሁልጊዜም በእግዚአብሄር ፊት
ትክክለኛ ሆነን መቆም ያዳግተኛል፡፡ ነገር ግን በቤተክርስቲያኑ በኩል
የእግዚአብሄርን ቃል በመስማትና በማንበብ ሁልጊዜም አዳዲስ ጉልበት ማግኘት
የቃሉን ሐይልም ሁልጊዜ መቀበልና ጌታንም ሁልጊዜ በእምነት ልንከተለው
እንችላለን፡፡
ሁላችሁም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ሐይል በማመን የእግዚአብሄር
አብን ፈቃድ ማድረግ እንደምትችሉ አሁኑኑ እመኑ! 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ሰማይ መግባት የምንችለው
የአብን ፈቃድ ስናውቅና
ስናምንበት ብቻ ነው
‹‹ ማቴዎስ 7፡21-27 ››
‹‹በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ
የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም፡፡ በዚያ ቀን ብዙዎች፡- ጌታ
ሆይ ጌታ ሆይ በስምህ ትንቢት አልተናገርንምን? በስምህስ አጋንንትን
አላወጣንምን? በስምህስ ብዙ ተዓምራትን አላደረግንምን? ይሉኛል፡፡ የዚያን
ጊዜም፡- ከቶ አላወቅኋችሁም፤ እናንተ ዓመጸኞች ከእኔ ራቁ ብዬ
እመሰክርባቸዋለሁ፡፡ ስለዚህ ይህን ቃሌን ሰምቶ የሚያደርገው ሁሉ ቤቱን
በዓለት የሰራ ልባም ሰውን ይመስላል፡፡ ዝናብም ወረደ፤ ጎርፍም መጣ፤ ነፋስም
ነፈሰ፤ ያንም ቤት ገፋው፤ በዓለት ላይም ስለተመሰረተ አልወደቀም፡፡ ይህንም
ቃሌን ሰምቶ የማያደርገው ሰው ሁሉ ቤቱን በአሸዋ ላይ የሰራ ሰውን ይመስላል፡፡
ዝናብም ወረደ፤ ጎርፍም መጣ፤ ነፋስም ነፈሰ፤ ያንም ቤት መታው ወደቀም፡፡
አወዳደቁም ታላቅ ሆነ፡፡››

ከላይ በተጠቀሰው የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ውስጥ ጌታችን እንዲህ


ብሎዋል፡- ‹‹በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ ጌታ ሆይ ጌታ
ሆይ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም፡፡›› ጌታ እዚህ ላይ
ሰማይ መግባት የሚችሉት የአብን ፈቃድ የሚያደርጉ እንጂ በእርሱ አምናለሁ
የሚሉ ማናቸውም እርሱ ወዳለበት ሰማይ መግባት እንደማይችሉ ተናግሮዋል፡፡
በመጨረሻው የፍርድ ቀን በኢየሱስ ያመኑ ብዙዎች ‹‹ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ በስምህ
ትንቢትን አልተናገርንምን? በስምህ አጋንንቶችን አላወጣንምን? በስምህ ብዙ
ተዓምራቶችን አላደረግንምን?›› በማለት ተቃውሞዋቸውን ሲያሰሙ ጌታችን ‹‹ከቶ
አላወቅኋቸውም፤ እናንተ ዓመጸኞች ከእኔ ራቁ›› ይላቸዋል፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


224 ሰማይ መግባት የምንችለው የአብን ፈቃድ ስናውቅና ስናምንበት ብቻ ነው

ጌታችን ለሁላችንም እንዲህ ብሎናል፡- ‹‹ስለዚህ ይህን ቃሌን ሰምቶ


የሚያደርገው ሁሉ ቤቱን በዓለት የሰራ ልባም ሰውን ይመስላል፡፡ ዝናብም
ወረደ፤ ጎርፍም መጣ፤ ነፋስም ነፈሰ፤ ያንም ቤት ገፋው፤ በዓለት ላይም
ስለተመሰረተ አልወደቀም፡፡ ይህንም ቃሌን ሰምቶ የማያደርገው ሰው ሁሉ ቤቱን
በአሸዋ ላይ የሰራ ሰውን ይመስላል፡፡ ዝናብም ወረደ፤ ጎርፍም መጣ፤ ነፋስም
ነፈሰ፤ ያንም ቤት መታው ወደቀም፡፡ አወዳደቁም ታላቅ ሆነ፡፡›› (ማቴዎስ 7፡24-
27) ስለዚህ ኢየሱስ እዚህ ላይ የጌታችንን ቃል ሰምተው የሚያምኑበትና
የሚታዘዙት ሰዎች የእምነት ቤታቸውን በዓለት ላይ የሰሩ ልባም ሰዎችን
እንደሚመስሉ ይህንን የማያደርጉ ሰዎች ግን እምነታቸው ሲፈርስ የሚያዩ ሰዎች
እንደሚሆኑ ነግሮናል፡፡
ጌታችን እዚህ ላይ እያለ ያለው ቃሉን በጆሮዋቸው የሚያደምጡና
በልቦቻቸውም የሚያምኑት ብሩካን መሆናቸውን ነው፡፡ በሌላ በኩል ሰው
የጌታን ቃል ሰምቶ በልቡ የማያምንበት ከሆነ የእምነት ሕይወቱ በሙሉ ከንቱ
ነው፡፡
የጌታችንን ቃል ሰምተው ኑሮዋቸውን በእምነት የሚኖሩ ሰዎች ቤቱን
በዓለት ላይ የሰራውን ሰው ይመስላሉ፡፡ ይህንን የእግዚአብሄር ቃል በማመን
ከሐጢያቶቻችሁ ሁሉ ድናችኋልን? በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን
ለአንዴና ለዘላለም ከሐጢያቶቻቸው ሁሉ የነጹ ሰዎች በእግዚአብሄር ቃል ላይ
በተተከለው በዚህ እምነት የአብን ፈቃድ በማድረግ ኑሮዋቸውን ይኖራሉ፡፡
እነዚህ ሰዎች የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በመላው ዓለም ለሚኖር
ለእያንዳንዱ ሰው ከማሰራጨታቸውም በላይ የእምነት ወንድሞቻቸውንና
እህቶቻቸውንም ይወዳሉ፡፡ በሌላ አነጋገር እነርሱ በዚህ የውሃና የመንፈስ ወንጌል
ስለሚያምኑ እውነተኛ እምነታቸውን በምግባሮቻቸው ማሳየት ይሻሉ፡፡
ጌታችን ለሁላችንም እንዲህ ብሎናል፡- ‹‹ቃሉን የሚያምኑና የሚተገብሩ
ሰዎች ሁኑ፡፡›› በዚህ ዓለም ላይ በኢየሱስ እናምናለን የሚሉ ብዙ ክርስቲያኖች
ቢኖሩም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ቃል ከልባቸው በማመን
ከሐጢያቶቻቸው ሁሉ በትክክል እንደ አመዳይ የነጹና ጻድቃን የሆኑ ከእነርሱ
ጥቂቶቹ ናቸው፡፡ ሆኖም የውሃውንና የመንፈሱን እምነታቸውን በመጠበቅ
እምነታቸውን የሚተገብሩ ሰዎችም ደግሞ አሉ፡፡ የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል
እውነተኛ ወንጌል መሆኑን እየተረዱ ያሉ ሰዎችም ብዙዎች ናቸው፡፡
ሰው ግን በዚህ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ከልቡ የሚያምን ከሆነ
ለሌሎች ይሰብከዋል፡፡ ይህንን ወንጌል የማያሰራጩ ሰዎች እምነታቸው ሲፈርስ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ሰማይ መግባት የምንችለው የአብን ፈቃድ ስናውቅና ስናምንበት ብቻ ነው 225

ያያሉ፡፡ በአንደበታቸው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል እንደሚያምኑ የሚናገሩ


እንደ እውነቱ ከሆነ ግን ከልባቸው የማያምኑበትና እምነታቸውንም
በድርጊቶቻቸው የማያሳዩ ጥቂት ሰዎች አሉ፡፡
እነዚህ ሰዎች የሐሰት ወንጌላቶችም እውነት ናቸው ብለው ይሰብካሉ፡፡
እንደዚህ የሚሰብኩት በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በትክክል የሚያምን እምነት
ስለሌላቸው ነው፡፡ እኛ ግን ከውሃውና ከመንፈሱ ወንጌል ውጭ አንዳች ሌላ
ወንጌል አንሰብክም፡፡ ምክንያቱም እውነተኛው ወንጌል ይህ ወንጌል ብቻ ነውና፡፡

በውሃውና በመንፈሱ ሐይል ማመን አለብን፡፡

ጌታችን እንዲህ ብሎዋል፡- ‹‹በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ


እንጂ ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም፡፡››
በሌላ አነጋገር የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል እውነተኛ ወንጌል መሆኑን
በእርግጠኝነት የሚያምኑ ሰዎች ለሌሎች ይመሰክሩታል፡፡ ስለዚህ የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል ለሌሎች የማያሰራጩ ሰዎች ጻድቅ ምግባሮች የሉዋቸውም፡፡
የእግዚአብሄር አብን ፈቃድም አያደርጉም፡፡ ስለዚህ በጌታችን ተቀባይነት
የላቸውም፡፡ በመጨረሻም እምነታቸው ይፍረከረካል፡፡ የእነዚህ ሰዎች ሐጢያቶች
በልቦቻቸው ውስጥ ስለሚቀር በኢየሱስ እናምናለን ቢሉም ሁሉም ሐጢያተኞች
ሆነው ይቀራሉ፡፡ የእምነት ሕይወታቸውን ምንም ያህል በግለት ቢመሩትም
ሁሉም ሐጢያተኞች ናቸው፡፡ በእርግጠኝነት በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
ስለሚያምኑ እውነተኛዎቹን የእምነት ምግባሮቻቸውን አያሳዩም፡፡ ስለዚህ
በመጨረሻው ቀን ጌታ እንዳይተዋቸው መሸሽ አይችሉም፡፡
የሐጢያቶቻቸውን ስርየት ላገኙ ጻድቃኖች ራስ ምታት የሚሆንባቸው
ምንድነው? በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል እናምናለን ቢሉም ይህ ወንጌል ብቻ
እውነት እንደሆነ በእርግጠኝነት የማያምኑና የማያሰራጩ አንዳንድ ሰዎችን ሲያዩ
ልባቸው ይጎዳል፡፡ ለምን? ምክንያቱም ይህ እንደሚሉት ወንጌልን ከሙሉ
ልባቸው ያምኑ እንደሆነ ወይም እንዳልሆነ ከበድ ያለ ጥያቄ ያስነሳልና፡፡
ሁላችንም የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል እንዳለ ማወቅና ማመን አለብን፡፡
ይህም ጌታችን እዚህ ላይ የተናገረውን ደግመን እንድናስታውስ ይረዳናል፡፡
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የማያምኑ ማለትም የአባቱን ፈቃድ የማያደርጉ
ሰዎች ከቶውኑም ሰማይ መግባት አይችሉም፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


226 ሰማይ መግባት የምንችለው የአብን ፈቃድ ስናውቅና ስናምንበት ብቻ ነው

ጌታችን ኢየሱስን አዳኝ አድርገው እንደሚያምኑ ለሚናገሩ ነገር ግን


በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ለማያምኑና ይህንን ለማይሰብኩ ሰዎች ‹‹እናንተ
ዓመጸኞች ከእኔ ራቁ›› ብሎ የሚያውጀው ለዚህ ነው፡፡ እነርሱ በእርግጠኝነት
የውሃውና የመንፈሱ መላው ወንጌል ተጨባጭ የእውነት ወንጌል እንደሆነ
ቢያምኑ ኖሮ በእውነቱ መሰረት በትክክል ይሰብኩት ነበር፡፡ እነርሱ ይህንን
የማያምኑትም ሆነ የማይሰብኩት የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል የእግዚአብሄር
ዘላለማዊ ፍቅር መሆኑን ስለማያምኑ ነው፡፡
እነርሱ በጌታ የደህንነት ቃል በእርሱ የደህንነት ሕግ መሰረት በእርግጠኝነት
በኢየሱስ ስለማያምኑ በአብ ፍቅር መሰረት እንደኖሩ የሚያሳይ ምግባር
የላቸውም፡፡ ‹‹በጌታ ስም ትንቢት አልተናገርንምን? በስሙ አጋንንቶችን
አላወጣንምን? በስሙ ብዙ ተዓምራቶችን አላደረግንምን?›› ይሉ ይሆናል፡፡
በመጨረሻ ግን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ባለማመናቸው የፈጸሙት ሐሰተኛ
ተዓምራቶችን ብቻ ነው፡፡
ጌታችን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በማመን ፋንታ ዓመጽን
የሚያደርጉትን እነዚህን ሰዎች ‹‹ለእኔ ምን አደረጋችሁልኝ? ተዓምራቶችንና
ምልክቶችን አድርጋችኋልን? እኔ በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅ የዓለምን
ሐጢያቶች እንደተሸከምሁ፣ ለእናንተም በመስቀል ላይ ደሜን እንዳፈሰስሁና
የዓለምንም ሐጢያቶች በሙሉ የሚደመስሰው ደህንነትም ይህ እንደሆነ
በእርግጠኝነት አምናችኋልን? ይህንንስ ለሌሎች አሰራጭታችኋልን? ከእነዚህ
አንዱንም አላደረጋችሁም፡፡ ነገር ግን ስሜን በመጥራት ዓመጻን ያደረጋችሁት
ስንት ጊዜ ነው? በስሜ አሰዳቢ የሐሰት ተዓምራቶችን እንዳደረጋችሁ በሚገባ
አውቃለሁ፡፡ ስለዚህ ከእኔ ራቁ!››

በዋሾዎች መታለል የለብንም፡፡

በመላው ዓለም በኢየሱስ ስም ተዓምራቶችንና ምልክቶችን የሚያደርጉ


ብዙዎች አሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች በሚመሩዋቸው ቤተክርስቲያኖች ውስጥ የአምልኮ
አገልግሎቶቻቸው ዋናው ዓላማ ተዓምራቶችን ማድረግ ብቻ ነው፡፡ የውሃውና
የመንፈሱ ወንጌል በስፋት ሊሰብክላቸው ሲገባና ጉባኤውም ማድረግ ያለበት
ለዚህ በእምነት ምላሽ መስጠት ብቻ ሆኖ ሳለ በዚህ ሰዓት ምልክቶችን አብዝተው
የሚሹት ለምንድነው? እዚህ ላይ ልንገነዘበው የሚገባን ነገር ቢኖር ብዙ የሐሰት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ሰማይ መግባት የምንችለው የአብን ፈቃድ ስናውቅና ስናምንበት ብቻ ነው 227

ተዓምራቶችን የሚያደርጉት አጋንንት የያዛቸው ሰዎች መሆናቸውን ነው፡፡ በሌላ


አነጋገር በርኩሳን መናፍስቶች የተያዙ ሰዎች ተዓምራቶችን እናደርጋለን እያሉ
በማስመሰል ተከታዮቻቸውን እያታለሉ ስሜቶቻቸውን ይሰርቃሉ፡፡ ከእነርሱም
ደግሞ ብዙ ቁሳዊ ስጦታዎችን ይዘርፋሉ፡፡ እነዚህ በግልጽ የሰይጣንን ሥራ
የሚሰሩ አገልጋዮች ናቸው፡፡ እነዚህ ሁሉ ተዓምራቶች ከምናባዊ ተውኔት የዘለሉ
አይደሉም፡፡ ኢየሱስ እነዚህ ሰዎች ‹‹በስምህ አጋንንቶችን አላወጣንምን?›› ሲሉት
ከቶውኑም እንዳላወቃቸው የነገራቸው ለዚህ ነው፡፡ በዚህ በመጨረሻው ዘመን
ጌታ ያለ ምንም አድልዎ ሐጢያት ያለባቸውን ሰዎች በሙሉ ያስወግዳቸዋል፡፡
አጋንንቶች ዳግመኛ በተወለዱ ሰዎች ዓይን አይታዩም፡፡ ዳግመኛ
ያልተወለዱ ሰዎች ግን አጋንንቶችን መስማትና ምስሎቻቸውንም ማየት ይችላሉ፡፡
ምክንያቱም በልቦቻቸው ውስጥ ሐጢያቶች አሉ፡፡ በእነዚህ ሐጢያተኛ ሰዎች
ልቦች ውስጥ ክፉ መናፍስቶች መግባትና በውስጣቸውም በነጻነት መስራት
ይችላሉ፡፡ ስለዚህ አጋንንት የያዘው ሰው በቀላሉ ከአጋንንቶች ጋር መገናኘት
ይችላል፡፡ አጋንንቶች የሚሰሩትና ክፉ ፍሬዎቻቸውን የሚያፈሩት
ሐጢያቶቻቸው አሁንም ደረስ አብረዋቸው ባሉ ሰዎች ውስጥ ነው፡፡
ሰዎች በእርግጠኝነት ማድረግ የሚገባቸው ነገር ቢኖር የሐሰት
ተዓምራቶችን በመሻት ፋንታ ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቁ
ሐጢያቶቻቸውን በሙሉ እንደወሰደና የሐጢያቶቻቸውንም ኩነኔ የራሱን ደም
በማፍሰስ እንደተሸከመ ማመን ነው፡፡ እኛ በአጋንንቶች ሥራዎች ውስጥ
ከመሳተፍ ርቀን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን ጉልበታችንን ሁሉ ይህንን
ወንጌል ለማሰራጨት መስጠት አለብን፡፡ ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ
በመጠመቅ የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ በራሱ ላይ ስለወሰደና የሐጢያትን
ኩነኔም ሁሉ በመስቀል ላይ ስለተሸከመ ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ድነን በእምነት
ሐጢያት አልባ ሆነናል፡፡ ጌታችን ሐጢያቶቻችንን በሙሉ በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል ስላነጻ በዚህ የሚያምኑ ሰዎች በሙሉ ነጽተዋል፡፡ ስለዚህ ክፉ
መናፍስቶች ከቶውኑም በልቦቻቸው ውስጥ ሊኖሩ አይችሉም፡፡ በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል ስላነጻ በዚህ የሚያምኑ ሰዎች በሙሉ ነጽተዋል፡፡ ስለዚህ ክፉ
መናፍስቶች ከቶውኑም በልቦቻቸው ውስጥ ሊኖሩ አይችሉም፡፡ በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል ለሚያምኑ ምዕመናኖች ፈጽሞ የሰይጣን ሥራ የሚባል ነገር
የለም፡፡
ጌታችን ‹‹መንግሥተ ሰማይ የሚገባው በሰማይ ያለውን የአባቴን ፈቃድ
የሚያደርግ ነው›› ያለው ለዚህ ነው፡፡ እዚህ ላይ ልናጤነው የሚገባን ነገር ቢኖር

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


228 ሰማይ መግባት የምንችለው የአብን ፈቃድ ስናውቅና ስናምንበት ብቻ ነው

የእግዚአብሄር ፈቃድ በትክክል ምን እንደሆነ ነው፡፡ የአብ ፈቃድ እኛ


የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በማመን እንድንድን ነው፡፡ አዳኛችን ኢየሱስ
ክርስቶስ በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅና በመስቀል ላይም እስከ ሞት ድረስ
በመሞት ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ደምስሶዋል፡፡ ይህ እምነት እንደ አብ ፈቃድ
የሚያምን ትክክለኛ እምነት ነው፡፡ በሌላ አነጋገር እግዚአብሄር አባታችን ልጁን
በመላክ እንዲጠመቅ አድርጎ የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ እንዲቀበልና ደሙንም
በመስቀል ላይ እንዲያፈስስ በማድረግ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ አንጽቷል፡፡
በዚህ እውነት ስናምን ከሐጢያቶቻችን ሁሉ መንጻትና በደስታ ለዘላለም
እንኖር ዘንድም ወደ እግዚአብሄር ዘላለማዊ መንግሥት መግባት እንችላለን፡፡ ጌታ
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ከሐጢያቶቻችን አድኖናል፡፡ ለእኛ በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት ኢየሱስ አዳኛችን አድርገን ማመን ማለት እንደ
እግዚአብሄር አብ ፈቃድ ማመንና ፈቃዱን ማድረግ ማለት እንጂ ሌላ አይደለም፡፡
ሆኖም እንደዚህ ማመን ተስኖዋቸው ኢየሱስን አዳኛቸው አድርገው
ቢያምኑም እንኳን ከሐጢያቶቻቸው ማምለጥ የማይችሉ በዚህም በመጨረሻ
ተጥለው የሚጠፉ ብዙ ሰዎች አሉ፡፡ በሌላ አነጋገር እነርሱ ተረስተዋል፡፡
ምክንያቱም የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል እስከ መጨረሻው ድረስ ተጨባጭ
እውነት መሆኑን አያምኑምና፡፡ በዚህ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ስለማያምኑና
የአብንም ፈቃድ በእምነት ማድረግ ስለማይችሉ የመጨረሻው ቀን ሲመታ
በራሳቸው አስተሳሰቦች የፈጠሩት እምነታቸው ተፈረካክሶ ይወድቃል፡፡ ሰዎች
በመጨረሻው ዘመን በጌታ ዘንድ ተቀባይነትን የሚያጡት በእግዚአብሄር የውሃና
የመንፈስ ወንጌል ቃል ስለማያምኑ ነው፡፡ ይህ ለእናንተም ደግሞ እውነት ነው፡፡
አሁን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ከጣላችሁ እግዚአብሄርም በኋላ እናንተኑ
ራሳችሁን ይጥላችኋል፡፡
ጌታችን ኢየሱስ በዘመኑ መጨረሻ መላዕክቶች መጥተው ክፉዎችን
ከጻድቃኖች መካከል እንደሚለዩዋቸውና ወደ እቶን እሳት እንደሚጥሉዋቸው
ተናግሮዋል፡፡ (ማቴዎስ 13፡49-50) ወንድሞችና እህቶች ከጻድቃን መካከል
ክፉዎች እነማን ናቸው? ጌታችን እኛን ከሐጢያቶቻችን ያዳነን በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል እንደሆነ በግልጽና በተብራራ መንገድ ነግሮናል፡፡ ይህም ሆኖ
ሳለ በዚህ ወንጌል አሁንም ድረስ የማያምኑ ከዓለም ጋር የሚስማሙ ብቻ ሳይሆን
የዓለምን አቋም የተጋሩ ሰዎች አሉ፡፡ ክፉዎች እንደ እነዚህ ያሉ ሰዎች ናቸው፡፡
ወንድሞችና እህቶች ሁለት እውነተኛ ወንጌሎች የሉም፡፡ ኢየሱስም ሁለት
አይደለም ያለው አንድ ኢየሱስ ብቻ ነው፡፡ ኢየሱስ ሐጢያቶቻችንን ባስወገደበት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ሰማይ መግባት የምንችለው የአብን ፈቃድ ስናውቅና ስናምንበት ብቻ ነው 229

ወንጌል፣ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን ብቻ ካልሆነ በቀር ሰማይ


የምንገባበት ሌላ መንገድ የለም፡፡ ይህ የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል
ሐጢያቶቻችሁን በሙሉ ደምስሶዋል፡፡
በዚህ እውነት ብታምኑ በእግዚአብሄር አብ ፈቃድ መሰረት የምትኖሩበት
መንገድ ይከፍትላችኋል፡፡ የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል በእርግጥም የእግዚአብሄር
አብ ፈቃድ በተጨባጭ ምን እንደሆነ እንድትገነዘቡ ይፈቅድላችኋል፡፡ 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


ገንዘባችሁን ብቻ ከሚሹ
ሐሰተኛ ነቢያቶች ተጠንቀቁ
‹‹ ማቴዎስ 7፡13-27 ››
‹‹በጠበበው ደጅ ግቡ፤ ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጅ ሰፊ መንገዱም ትልቅ
ነውና፡፡ ወደ እርሱም የሚገቡ ብዙዎች ናቸው፡፡ ወደ ሕይወት የሚወስደው ደጅ
የጠበበ መንገዱም የቀጠነ ነውና፤ የሚያገኙትም ጥቂቶች ናቸው፡፡ የበግ ለምድ
ለብሰው ከሚመጡባችሁ በውስጣቸው ግን ነጣቂዎች ተኩላዎች ከሆኑ
ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ፡፡ ከፍሬያቸው ታውቁዋቸዋላችሁ፡፡ ከእሾህ ወይን
ከኩርንችትስ በለስ ይለቀማልን? እንዲሁ መልካም ዛፍ ሁሉ መልካም ፍሬ
ያደርጋል፡፡ ክፉም ዛፍ ክፉ ፍሬ ያደርጋል፡፡ መልካም ዛፍ ክፉ ፍሬ ማፍራት
ወይም ክፉ ዛፍ መልካም ፍሬ ማፍራት አይቻለውም፡፡ መልካም ፍሬ የማያደርግ
ዛፍ ሁሉ ይቆረጣል፤ ወደ እሳትም ይጣላል፡፡ ስለዚህም ከፍሬያቸው
ታውቁዋቸዋላችሁ፡፡ በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ ጌታ
ሆይ ጌታ ሆይ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም፡፡ በዚያ ቀን
ብዙዎች፡- ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ በስምህ ትንቢት አልተናገርንምን? በስምህስ
አጋንንትን አላወጣንምን? በስምህስ ብዙ ተዓምራትን አላደረግንምን? ይሉኛል፡፡
የዚያን ጊዜም፡- ከቶ አላወቅኋችሁም፤ እናንተ ዓመጸኞች ከእኔ ራቁ ብዬ
እመሰክርባቸዋለሁ፡፡ ስለዚህ ይህን ቃሌን ሰምቶ የሚያደርገው ሁሉ ቤቱን
በዓለት የሰራ ልባም ሰውን ይመስላል፡፡ ዝናብም ወረደ፤ ጎርፍም መጣ፤ ነፋስም
ነፈሰ፤ ያንም ቤት ገፋው፤ በዓለት ላይም ስለተመሰረተ አልወደቀም፡፡ ይህንም
ቃሌን ሰምቶ የማያደርገው ሰው ሁሉ ቤቱን በአሸዋ ላይ የሰራ ሰውን ይመስላል፡፡
ዝናብም ወረደ፤ ጎርፍም መጣ፤ ነፋስም ነፈሰ፤ ያንም ቤት መታው ወደቀም፡፡
አወዳደቁም ታላቅ ሆነ፡፡››

ጌታችን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በሚያምነው እምነት እውነተኛ


ነቢያቶችን ከሐሰተኞቹ፤ የእርሱን እውነተኛ ቤተክርስቲያንም ከሐሰተኛ
ቤተከርስቲያኖች የምንለይበትን ችሎታ ሰጥቶናል፡፡ ኢየሱስ በማቴዎስ 7፡15-20

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ገንዘባችሁን ብቻ ከሚሹ ሐሰተኛ ነቢያቶች ተጠንቀቁ 231

ላይ እንዲህ ብሎዋል፡- ‹‹የበግ ለምድ ለብሰው ከሚመጡባችሁ በውስጣቸው ግን


ነጣቂዎች ተኩላዎች ከሆኑ ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ፡፡ ከፍሬያቸው
ታውቁዋቸዋላችሁ፡፡ ከእሾህ ወይን ከኩርንችትስ በለስ ይለቀማልን? እንዲሁ
መልካም ዛፍ ሁሉ መልካም ፍሬ ያደርጋል፡፡ ክፉም ዛፍ ክፉ ፍሬ ያደርጋል፡፡
መልካም ዛፍ ክፉ ፍሬ ማፍራት ወይም ክፉ ዛፍ መልካም ፍሬ ማፍራት
አይቻለውም፡፡ መልካም ፍሬ የማያደርግ ዛፍ ሁሉ ይቆረጣል፤ ወደ እሳትም
ይጣላል፡፡››
ጌታችን ከሐሰተኛ ነቢያቶች እንድንጠነቀቅ ነግሮናል፡፡ እርሱ
እንዳስጠነቀቀንም በእርግጥም ሐሰተኛ ነቢያቶች መጠርጠር ይገባናል፡፡ አንድ
መጋቢ የእግዚአብሄር ቃል የሆነውን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ቃል
ለጉባኤው መስበክ ከተሳነው ተገቢውን አገልግሎቱን እየፈጸመ አይደለም፡፡
እንዲህ ያለ መጋቢ የጉባኤውን የሐጢያት ችግር የእግዚአብሄር ቃል በሆነው
የውሃውና የመንፈስ ወንጌል መፍታት ሳይችል እንዴት ራሱን መጋቢ ብሎ ሊጠራ
ይችላል?
እንደዚህ ያሉ ዋሾዎች የሚደሰቱት በውጫዊው ማንነታቸው በሚሰብኩበት
ጊዜ በግብዝነት ኮስተር ያሉና ቅዱስ መሆናቸውን በማስመሰል ነው፡፡ በመጨረሻ
ግን ለጉባኤያቸው የሚሰብኩት ሁሉ በዓለም ሥነ ምግባሮችና ደንቦች እንዲኖሩ
የሚያደርግ ነው፡፡ ጥሩ ምግባሮችና ሥነ ምግባሮች ችላ መባል እንደሌለባቸው
የታወቀ ነው፡፡ ነገር ግን መጋቢዎች ማድረግ ያለባቸው ነገር ቢኖር ዘላለማዊ
ሕይወት ላይ ብቻ ትኩረት ማድረግ ሳይሆን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
መስበክ ነው፡፡ ምክንያቱም ሰዎች በየቀኑ ሐጢያት ስለሚሰሩ በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል በማመን ከሐጢያቶቻቸው ሁሉ መዳን አለባቸውና፡፡
እዚህ ላይ ‹‹ሐሰተኛ ነቢያቶች›› የተባሉት እውነትን የሚቃወሙ ሁሉ
ናቸው፡፡ ራሳቸው መጋቢዎችም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን
የሐጢያቶቻቸውን ስርየት ማግኘት ያስፈልጋቸዋል፡፡ የውሃውንና የመንፈሱን
ወንጌል ሳያውቅና ዳግመኛ ሳይወለድ መጋቢ ወይም ሰባኪ ሆኖ የሚያገለግል
ማንም ቢኖር አሳዛኝ ሐሰተኛ ነቢይ ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ እነዚህን ሰዎች
‹‹ሐሰተኛ ነቢያት›› ብሎ ይጠራቸዋል፡፡
ጌታችን እንዲህ ብሎናል፡- ‹‹ከሐሰተኛ ነቢያት ተጠበቁ፡፡›› በእርግጥም
ከእነዚህ ሰዎች ልንጠበቅ ይገባናል፡፡ ሁላችሁም በዚህ ዓለም ላይ ከሚኖሩና
የሐጢያቶቻችሁን ችግር መፍታት ከማይችሉ ከእነዚህ ዋሾዎች መጠበቅ
አለባችሁ፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


232 ገንዘባችሁን ብቻ ከሚሹ ሐሰተኛ ነቢያቶች ተጠንቀቁ

መጽሐፍ ቅዱስ በቲቶ 3፡10-11 ላይ እንዲህ ይላል፡- ‹‹መለያየትን የሚያነሳ


ሰው ጠማማ እንዲሆን በራሱም ላይ ፈርዶ ሐጢአትን እንዲያደርግ አውቀህ
አንድ ጊዜ ሁለት ጊዜም ከገሰጽኸው በኋላ እንዲህ ከሚመስል ሰው ራቅ፡፡›› ይህ
ምንባብ የሚያመለክተው በኢየሱስ እናምናለን ቢሉም ሐጢያቶቻቸው አሁንም
ድረስ አብረዋቸው ያሉትን ሰዎች ነው፡፡ እምነታቸው በኢየሱስ ቢያምኑም
ሐጢያተኛ ሆኖ መቆየት ትክክል እንደሆነ ይነግራቸዋል፡፡ ስለዚህ በእግዚአብሄር
ላይ የከፋ ሐጢያትን እየፈጸሙ ነው፡፡ ኢየሱስ አዳኛችን ነው እያሉ እንዴት
አሁንም ድረስ ሐጢያተኞች ሊሆኑ ይችላሉ? ይህንን እምነታቸውን በማመን
እያደረጉ ያሉት ነገር ሁሉ በራሳቸው መንገድ በእግዚአብሄር ላይ ሐጢያትን
መስራት ነው፡፡
በጌታ ፊት ሐጢያቶቻቸው አብረው እንዳሉ መናገራቸው የሚያሳየው ነገር
ቢኖር አሁንም ድረስ በሐጢያቶቻቸው የሚኮነኑ የመሆኑ የተሳሳተ እምነታቸውን
ነው፡፡ ሆኖም ራሳቸውን በጌታ ፊት ሐጢያተኞች አድርጎ መቁጠር ትክክለኛው
የማመን መንገድ እንደሆነ ያስባሉ፡፡ ነገር ግን እነዚህ ምዕመናኖች በእግዚአብሄር
ፊት እውነተኛ ቅዱሳኖች ሳይሆኑ ዋሾዎች ናቸው፡፡ ኢየሱስ ከእነዚህ ሐሰተኛ
ነቢያቶችና ከተከታዮቻቸው እንድንጠብቅ ነግሮናል፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ ያስጠነቀቅንን ማንኛውንም ነገር ሁልጊዜም በአእምሮዋችን
መያዝ፣ ከሐሰተኛ ነቢያቶች፣ ከሐሰተኛ መጋቢዎችና ከሐሰተኛ ሰባኪዎች ሁሉ
መራቅ አለብን፡፡

ኢየሱስ ሐሰተኛ ነቢያቶችን በፍሬያቸው ልንለያቸው እንደምንችል


ተናግሮዋል፡፡

ጌታችን ሐሰተኛ ነቢያቶችን በማስመልከት እንዲህ ብሎዋል፡- ‹‹በፍሬያቸው


ታውቁዋቸዋላችሁ፡፡›› ሐሰተኛ ነቢያቶችን መለየት የምንችለው በፍሬያቸው
ነው፡፡ ሐሰተኛ ነቢያቶችን የሚለዩት ፍሬዎች ምን ዓይነት ናቸው? ጌታችን መልሶ
እንዲህ ሲል ጠይቋል፡- ‹‹ከእሾህ ወይን ይለቀማልን?›› እሾሆች መልካም ፍሬዎችን
ማፍራት እንደማይችሉ ሁሉ የሐጢያቶቻቸውን ስርየት ያላገኙና አሁንም ድረስ
ሐጢያተኛ ሆነው ያሉ መጋቢዎችም ሰዎችን ዳግመኛ እንዲወለዱ መምራት
አይችሉም፡፡ እነርሱ የሚያፈሩት ሐጢያተኛ የሆኑ ክርስቲያኖችን ብቻ ነው፡፡
ዳግመኛ የተወለዱ ሰራተኞች ግን ሐጢያት አልባ ቅዱሳኖችን ያፈራሉ፤

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ገንዘባችሁን ብቻ ከሚሹ ሐሰተኛ ነቢያቶች ተጠንቀቁ 233

ይንከባከቡዋቸዋል፡፡ አንድ መጋቢ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት


ሐጢያተኞችን ወደ ሐጢያት አልባነት መመለስ የማይችል ከሆነ እርሱ በግልጽ
ሐሰተኛ ነቢይ ነው፡፡
ጌታ ዛፍ በፍሬው እንደሚታወቅ ስለተናገረ የእምነት ፍሬዎቹ የሐጢያት
ስርየትን ከተቀበሉ ጻድቃኖች ሁሉ ከተወገዱ ዋሾዎችና ሐሰተኛ ነቢያቶች
መሆናቸውን እናውቃለን፡፡ ሐሰተኛ መጋቢዎች የበግ ለምድ ለብሰው በሚያምሩ
ቃሎቻቸው ተከታዮቻቸውን በማሳት ወደተሳሳተ መንገድ ይመሩዋቸዋል፡፡
ብዙዎች በእነዚህ ሐሰተኛ ነቢያቶች ተታልለዋል፡፡ ምክንያቱም በውጫዊ
ገጽታቸው በጣም ቅዱስ መስለው ይታያሉና፡፡ ስለዚህ መጽሐፍ ቅዱስ
‹‹እንደነዚህ ያሉ ሰዎች የክርስቶስን ሐዋርያት እንዲመስሉ ራሳቸውን እየለወጡ
ውሸተኞች ሐዋርያትና ተንኮለኞች ሰራተኞች ናቸውና፡፡ ይህም ድንቅ አይደለም፤
ሰይጣን ራሱ የብርሃንን መልአክ እንዲመስል ራሱን ይለውጣልና›› (2ኛ ቆሮንቶስ
11፡13-14) በማለት በእነዚህ ውሸታሞች እንዳንታለል አስጠንቅቆናል፡፡
ሐሰተኛ ነቢያት ሆነው ለተጠሩበት ጥሪ ታማኝ በመሆን ጉባኤዎቻቸውን
በቅንነት እንዲኖሩ፣ ሐጢያት እንዳይሰሩና ለሌሎች ደግ እንዲሆኑ ብቻ
ያስተምሩዋቸዋል፡፡ በውስጣቸው ግን የጉባኤዎቻቸውን ገንዘብ የሚበዘብዙ
ነጣቂ ተኩላዎች ናቸው፡፡ ስብከቶቻቸውም በተለያዩ መልኩ ድምዳሜው ያው
ነው፡፡ ጉባኤያቸውን በጽድቅ እንዲኖር ለእግዚአብሄር ማቅረብ ያለበት ነገር
ቢኖርም ገንዘብ ብቻ እንደሆነ ይነግሩታል፡፡ ለጉባኤያቸው ብዙ የተለያዩ
ስብከቶችን ይሰብኩ ይሆናል፡፡ በመጨረሻ ግን ስብከቶቻቸው በሙሉ
የሚያጠነጥኑት ተከታዮቻቸው ለእግዚአብሄር ብዙ ገንዘብ እንዲያመጡ በመንገር
ነው፡፡ እነርሱ እነዚህን ስብከቶች የሚሰብኩበት ምክንያት ግልጽ ነው፡፡ እነርሱ
ራሳቸው ብዙ እንዲከፈላቸው ይፈልጋሉ፡፡ ስለ ጉባኤዎቻቸው ደህንነት
አይጨነቁም፡፡ በመጨረሻው ዘመን እነርሱን ጨምሮ ክርስቲያን የሆኑ
ሐጢያተኞቻቸው ምን እንደሚገጥማቸው አይጨነቁም፡፡ ምንም ያህል
እውነተኛውን የውሃና የመንፈስ ወንጌል ከልባችን ልናቋድሳቸው ብንሞክርም
ሊያዳምጡን አይፈልጉም፡፡ እነዚህ መጋቢዎች ያለ አንዳች ማመንታት ሁልጊዜም
ሐሰተኛ ነቢያቶች ናቸው፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ ሐሰተኛ ነቢያቶችን በፍሬያቸው እንደምናውቃቸው
ይነግረናል፡፡ እነርሱን የእግዚአብሄር ቃል የሆነውን የውሃውንና የመንፈሱ ወንጌል
ይሰብኩ እንደሆነ ወይም እንዳልሆነ በማየትና ከእነርሱ ተከታዮች መካከል
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ወደ ማመን መጥቶ በእነርሱ በኩል የሐጢያት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


234 ገንዘባችሁን ብቻ ከሚሹ ሐሰተኛ ነቢያቶች ተጠንቀቁ

ስርየትን ተቀብሎ እንደሆነ ወይም እንዳልሆነ በመመርመር መለየት እንችላለን፡፡


በእርግጥ የእግዚአብሄርን ቃል በግልጽ ይሰብካሉ፡፡ ነገር ግን ከስብከታቸው
የሚወጣ የደህንነት ሥራ የለም፡፡ እኛ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ቃል
በማመን እነርሱ በእምነታቸው እውነተኛ ነቢያቶች ወይም ሐሰተኛ ነቢያቶች
መሆናቸውን ማወቅ ብቻ ሳይሆን በእነዚህ ውሸታሞችም ልንታለል አንችልም፡፡
የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ሐሰተኛ ነቢያቶችን የምንለይበት ባሮ ሜትር ነው፡፡
ስለዚህ እኛ ከውሃውና ከመንፈሱ ወንጌል የተወለድን (ዮሐንስ 3፡1-10) ሰዎች ክፉ
ዛፎችን ከመልካም ዛፎች መለየት የምንችል የራሱ የእግዚአብሄር ሕዝብና
አገልጋዮቹ ነን፡፡
አሁን ደግሞ የሐሰተኛ ነቢያቶችን ባህርይ በጥልቀት እንመርምር፡፡ የአንድ
ሐሰተኛ ነቢይ የመጀመሪያው ባህርይ እያንዳንዳቸው በእግዚአብሄር ፊት
ሐጢያት የሚሰሩ መሆናቸው ነው፡፡ ስለዚህ አንድ አገልጋይ በእግዚአብሄር ፊት
ሐጢያተኛ ከሆነ ሐሰተኛ ነቢይ ነው፡፡ ይህ ሰው በየቀኑ ለጉባኤው የሚነግረው
ገንዘብ ይዘው እንዲመጡ መሆኑ አያጠራጥርም፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
ላይም ፈጽሞ ፍላጎት የለውም፡፡ በእርሱም አያምንም፡፡ ይህ መጋቢ ሐሰተኛ
ነቢይ ነው፡፡ እነዚህ ነቢያቶች ጉባኤዎቻቸውን የሚያዩት የሐብታቸው ምንጭ
አድርገው ነው፡፡ ተከታዮቻቸው ዳግመኛ ቢወለዱ ወይም ባይወለዱ ግድ
አይሰጣቸወም፡፡ የእነርሱ ፍላጎት ገንዘብ ብቻ ነው፡፡
ከዚህ በፊት እንዲህ ዓይነት ስብከት ሰምታችሁ እንደሆነ እርግጠኛ
አይደለሁም፡፡ ነገር ግን ሐሰተኛ ነቢያቶች የሚሰብኩት እያንዳንዱ ስብከት
በአንድ ወይም በሌላ መንገድ ከገንዘብ ጋር የሚገናኝ ነገር አለው፡፡ ስብከቶቻቸው
ይህንን ይመስላሉ፡- ‹‹ወንድሞችና እህቶች በእግዚአብሄር ቃል መሰረት መኖር
ይገባናል፡፡ እግዚአብሄር በዘዳግም 28 ላይ ወላጆቻችሁን ብታከብሩና ሕጉን
ብትጠብቁ እንዲህና እንዲያ ያሉ በረከቶችን እሰጣችኋለሁ ብሎዋል፡፡›› ነገር ግን
ስብከቶቻቸውን እንዲህ ቢጀምሩትም በመጨረሻ የእግዚአብሄር በረከቶች
በምናቀርበው የገንዘብ መጠን ላይ የተመሰረቱ ናቸው ማለታቸው አይቀረም፡፡
ነገር ግን ሰማያዊዎቹንና ምድራዊዎቹን ከእግዚአብሄር ዘንድ የምንቀበልበት
መንገድ ይህ አይደለም፡፡ በተቃራኒው በረከቶች ሁሉ የሚመጡት የእግዚአብሄር
ቃል የሆነውን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ቃል ከሚያምነው ወንጌል ነው፡፡
እግዚአብሄር የደህንነት በረከቶቹን እንደዚሁም የምድርን በረከቶች ሁሉ
የሚሰጠው ይህንን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ቃል ለሚሰሙና ለሚያምኑ
ሰዎች ብቻ ነው፡፡ የሐሰተኛው ነቢይ ስብከት ግን ሁልጊዜም የሚሽከረከረው

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ገንዘባችሁን ብቻ ከሚሹ ሐሰተኛ ነቢያቶች ተጠንቀቁ 235

በገንዘብ ዙሪያ ነው፡፡ ስለ ሕግ ይናገሩ ይሆናል፤ ነገር ግን ‹‹ጌታን በሚገባ


አገልግሉ፤ ለቤተክርስቲያናችሁ ስጦታዎችን ስጡ፤ መጋቢያችሁንም አክብሩ›› ሲሉ
በተጨባጭ የሚናገሩት ‹‹ብዙ ገንዘብ አምጡ፤ ለእግዚአብሄር ረብጣ ገንዘብ
ስትሰጡ በብዙ ትባረካላችሁ፡፡ እምነታችሁም በፍጥነት ያድጋል›› እያሉ ነው፡፡
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምኑና መልዕክቱን የተረዱ ሰዎች ግን በእነዚህ
ውሸታሞች አይታለሉም፡፡

ከሐሰተኛ ነቢያቶች ማታለያ ማምለጥ አለብን፡፡

ኢየሱስ እንዲህ ብሎዋል፡- ‹‹የበግ ለምድ ለብሰው ከሚመጡባችሁ


በውስጣቸው ግን ነጣቂዎች ተኩላዎች ከሆኑ ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠበቁ፡፡››
ሐሰተኛ ነቢያቶች ልክ እንደ ተኩላዎች ናቸው፡፡ በመንጋው ፊት የበግ ለምድ
ለብሰው ይቆማሉ፡፡ ልቦቻቸው ግን የተኩላ ናቸው፡፡ በገንዘብ ፍቅር የተነደፉ
ስለሆኑ መንጋውን ለመብላት የተሳሉ ጥርሶቻቸውን ይገልጣሉ፡፡ በመጽሐፍ
ቅዱስ መሰረት ሐሰተኛ ነቢያቶች በሙሉ ከተኩላዎች የተለዩ አይደሉም፡፡ እነርሱ
የአዲስ ሕይወትን ወንጌል ለመንጎቻቸው ከማሰራጨት ርቀው ተከታዮቻቸው
ከውሃውና ከመንፈሱ ወንጌል ውጭ አንዳች ሌላ ነገር እንዲያምኑ ይነዱዋቸዋል፡፡
እንዲህ በማድረግም በልቦቻቸው ውስጥ ባሉት ሐጢያቶቻቸው ተሸፍነው
እየሞቱ ያሉትን ሕዝቦቻቸውን ይበዘብዛሉ፡፡ እነዚህን ነገሮች የሚያደርጉት
ሐሰተኛ ነቢያቶች እንጂ ሌሎች አይደሉም፡፡
ሐሰተኛ ነቢያት ለምን የማይጠቅሙ እንደሆኑ የሚረዱ ሰዎች ብዙ
አይደሉም፡፡ ነገር ግን የዚህ ዓለም ሐሰተኛ ነቢያቶች በማታለል በጣም የተካኑ
ስለሆኑና ሰዎችም በእነዚህ ሐሰተኛ ነቢያቶች በቀላሉ ለመታለል የሚያዘነብሉ
ስለሆኑ ብዙ ሰዎች የተሳሳተ እምነትን እንዲቀበሉ በጣፈጠው አንደበታቸው
ያማልሉዋቸዋል፡፡ በዚህ ዘመን ብቃት ያላቸውን ቅዱሳኖች የከበቡ ብዙ
ውሸታሞች ስላሉ በብዙ ሰዎች አእምሮ ውስጥ ግራ መጋባት ተፈጥሮዋል፡፡
እውነቱ ግን ውሸታሞች በሰው ላይ የሚያሳድሩት መጥፎ ተጽዕኖ መሆኑ ነው፡፡
የዚህ ዓለም ነገሮችም እንኳን ማስመሰያዎች አሉዋቸው፡፡ ለምሳሌ አንዳንድ
የሥጋ መሸጫ ሱቆች በመስኮቶቸቸው ላይ ለዕይታ የሚሆኑ የፕላስቲክ ሥጋዎችን
ያንጠለጥላሉ፡፡ በመጀመሪያ ስታዩት በጣም ትኩስና ግሩም መስሎ ስለሚታይ
የምግብ ፍላጎታችሁን ይቀሰቅሳል፡፡ ነገር ግን ቀረብ ብላችሁ በደንብ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


236 ገንዘባችሁን ብቻ ከሚሹ ሐሰተኛ ነቢያቶች ተጠንቀቁ

ስትመለከቱት እውነተኛ ሥጋ ሳይሆን ማስመሰያ ብቻ እንደሆነ መረዳት


ትችላላችሁ፡፡ ያን ጊዜ እንደተታለላችሁ ይሰማችኋል፡፡ በዳቦም እንደዚሁ ነው፡፡
በዱቄት የሚጋገር እውነተኛ ዳቦ ያለውን ያህል ከፕላስቲክ የተሰራ ማስመሰያ
ዳቦም ደግሞ አለ፡፡ እናንተ ይህንን ለማስመሰያ የቀረበ ዳቦ መብላት
ትችላላችሁን? አትበሉትም፡፡ ሊበላ የሚችል አይደለም፡፡ ምክንያቱም እውነተኛ
ዳቦ ይመስል ዘንድ ከፕላስቲክ የተሰራ ነውና፡፡ ነገር ግን ምንም ያህል ጥሩ መስሎ
ቢታይ ፕላስቲክ መብላት ከፍተኛ የጤና ችግሮችን ወይም ሞትን ሊያመጣ
ይችላል፡፡ ይህ የውሸት ዳቦ ሐሰተኛ ነቢያቶች ከሚሰብኩት ነገር ሁሉ ጋር
በትክክል ይመሳሰላል፡፡
ወንድሞችና እህቶች የቤተክርስቲያኖቻችሁ መሪዎች ምንም ያህል
ቢያሳሱዋችሁ፣ ምንም ያህል ቢወዱዋችሁና ምንም ያህል በግሩም ሁኔታ
ቢንከባከቡዋችሁ ከውሃውና ከመንፈሱ እንድትወለዱ የሚያስችላችሁን የሐጢያት
ስርየት ወንጌል ቃል ሊሰብኩላችሁ ከተሳናቸው እነርሱ ሐሰተኛ ነቢያት ናቸው፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ ከእነዚህ ሰዎች እንድንጠበቅ በግልጽ ነግሮናል፡፡
ጌታችን ሐሰተኛ ነቢያቶችን ነጣቂ ተኩላዎች ብሎዋቸዋል፡፡ አሁንም ድረስ
በእነርሱ ሞግዚትነት ሥር ናችሁን? እነዚህ ሰዎች የሚበዘብዙት ገንዘባችሁን ብቻ
አይደለም፡፡ በጣም አሳሳቢው ነገር ነፍሳችሁንም እየዘረፉ መሆናቸው ነው፡፡
ሐሰተኛ ነቢያቶች ማድረግ የሚፈልጉት ነገር ቢኖር በተቻለ መጠን ብዙ ገንዘብ
ከእናንተ መውሰድ፣ ትላልቅና የተሻለ የቤተክርቲያን ሕንጻ መገንባትን ነው፡፡
ነፍሳችሁ ወደ ሲዖል ቢንደረደር ምንም ግድ የላቸውም፡፡ ታዲያ አሁን ምን
ማድረግ አለባችሁ? ዛፍን የምታውቁት በፍሬዎቹ ነው፡፡ አንደበቱን በከፈተ ቁጥር
ስለ ገንዘብ የሚያወራና ቃሎቹም በንዘብ ስስት ላይ የሚሽከረከር ማንኛውም
ሰው ሙያተኛና ሐሰተኛ ነቢይ ነው፡፡
ስለዚህ ሐሰተኛ ነቢያቶችን በፍሬዎቻቸው ልናውቃቸው እንችላለን፡፡
ታዲያ የእነዚህ ነቢያቶች ፍሬዎች ምንድን ናቸው? የሰዎችን ነፍስ
የሚያጭበረብሩ የማታለያ ፍሬዎች ናቸው፡፡ ሐሰተኛ ነቢያቶች ገንዘብ
እስከሰጣችኋቸው ድረስ ሐጢያት አልባ እንደሆናችሁና ሁሉ ነገር ጥሩ እንደሆነ
ሊነግሩዋችሁ ፈቃደኞች ናቸው፡፡ የንስሐ ጸሎቶቻችሁን እስከጸለያችሁ፣ እስከ
ተቀደሳችሁና ለቤተክርስቲያን ብዙ ገንዘብ እስከሰጣችሁ ድረስ ሁሉ ጥሩ ነው
ይላሉ፡፡ እነዚህ ሁሉ የሐሰተኛ ነቢያቶች ፍሬዎች ናቸው፡፡
ታዲያ መጥፎ የሆኑት ፍሬዎቻቸው የሚገለጡት እንዴት ነው?
የጉባኤዎቻቸውን ቁጥር ያለ ማቋረጥ ለመጨመር ሲሞክሩና

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ገንዘባችሁን ብቻ ከሚሹ ሐሰተኛ ነቢያቶች ተጠንቀቁ 237

ቤተክርስቲያኖቻቸውንም ልክ የንግድ ሥራን እንደሚያንቀሳቅሱ ሲያንቀሳቅሱ


የክፉ አገልግሎቶቻቸው ፍሬዎች ይገለጣሉ፡፡ ብዙ ሰዎችን ወደ
ቤተክርስቲያኖቻቸው ለማምጣት የሚጠቀሙዋቸው ዕቅዶች ምንድን ናቸው?
ከሚጠቀሙባቸው እጅግ መሰሪ ዕቅዶች አንዱ ተከታዮቻቸው ወደ
ቤተክርስቲያኖቻቸው ተጨማሪ ሰዎችን እንዲያመጡላቸው ማበረታቻ ይሆን
ዘንድ ዓለማዊ ሽልማቶችንና ዋጋዎችን መስጠት ነው፡፡ ለምሳሌ አንድ ሰው
በአንድ ዓመት ውስጥ 20 ሰዎችን ወደ ቤተክርስቲያን የሚያመጣ ከሆነ አንድ
ትልቅ ማቀዝቀዣ ሽልማት ይሰጡታል፡፡ 30 አዳዲስ አባሎችን ለሚያመጣ ሰው
ደግሞ ከፍተኛ ጥራት ያለው የአየር ማቀዝቀዣ፣ 50 አዳዲስ አባሎችን
ለሚያመጣ ሰው ደግሞ ቅልብጭ ያለች መኪና፣ በአንድ ዓመት ውስጥም 200
አዳዲስ አባሎችን ለሚያመጣ ሰው ደግሞ የቤተሰብ ሴዳን መኪና ይሸልማሉ፡፡
ሐሰተኛ ነቢያቶች በዚህ መንገድ ሽልማቶችን በማቅረብ ወደ በረቶቻቸው ብዙ
አባሎችን እንዲያመጡ ተከታዮቻቸውን ያስገድዳሉ፡፡ ይህ ፈጽሞ የማይታመን
ነው ብላችሁ ታስቡ ይሆናል፡፡ እዚህ ላይ ይህንን ታሪክ የፈጠርሁት ግን እኔ
አይደለሁም፡፡ ይህ በዓለም ዙሪያ በአንዳንድ የክርስቲያን ማህበረሰብ
ቤተክርስቲያኖች ውስጥ በትክክል እየሆነ ያለ ነገር ነው፡፡
ይህ ምንኛ ክፉ ነገር ነው? የእግዚአብሄር ቤክርስቲያን የገበያ አዳራሽ
ወይም ባንክ ሆና ቀረች ማለት ነውን? ሐሰተኛ ነቢያቶች በዚህ መንገድ ሰዎችን
የቤተክርስቲያን አባል ካደረጉዋቸው በኋላ ምን ያደርጓቸዋል? የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል ቢሰብኩና ተከታዮቻቸውም የሐጢያት ስርየትን እንዲያገኙ
አግዘዋቸው ቢሆን ኖሮ እግዚአብሄር ድጋፉን ይሰጣቸው ነበር፡፡ ነገር ግን
የእነርሱ ፍላጎት ገንዘብ ብቻ እንደሆነ በግልጽ ማየት እንችላለን፡፡
አሁን ሐሰተኛ ነቢያቶች ነፍሳቶችን ወደ ቤተክርስቲያኖቻቸው ስላመጡ
የሚሰብኩላቸው እንዴት ነው? ‹‹ኢየሱስ ይወዳችኋል፡፡ በነገራችን ላይ
ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ቤተክርስቲያን ለመጣችሁ እህቶች ለእያንዳንዳችሁ
መካከለኛ የሆነ ውድ ዣንጥላ፤ ለወንዶች ደግሞ ከሴት ጓደኞቻችሁ ጋር
አብራችሁ ልትጠቀሙበት እንድትችሉ በጣም ትልቅ ዣንጥላ እንሰጣችኋለን፡፡››
እነዚህ አዳዲስ አባሎች ወደ ቤተክርስቲያኖቻቸው የመጡት እነዚህን ሽልማቶች
ለመቀበል መሆኑን ስለሚያውቁ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ሳያውቁ ውሎ
አድሮ ዲያቆናትና ሽማግሌዎች ይሆናሉ፡፡ እስኪሞቱ ድረስም የቤተክርስቲያን
የምጽዋት ሳጥኖችን በሁሉም ዓይነት የአስራትና የምስጋና ስጦታዎች በዚህና
በዚያ መባዎች ይሞላሉ፡፡ ይህም ወጣ ያለ ትርፍ የሚያስገኝ ውጥን ይሆናል፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


238 ገንዘባችሁን ብቻ ከሚሹ ሐሰተኛ ነቢያቶች ተጠንቀቁ

ለእነዚህ ሐሰተኛ ነቢያቶች የዛሬዋ ትንሽ ኢንቨስትመንት ነገ ወደ ትልቅ


ትርፍነት ትለወጣለች፡፡ ሐሰተኛ ነቢያቶች እነዚህን ጉባኤዎች በሽልማት እያጀቡ
የሚያካሂዱት ለዚህ ነው፡፡ የሚከስሩበት ቢሆን ኖሮ ይህንን የሚያደርጉበት
መንገድ አይኖርም ነበር፡፡ ከ500 አዳዲስ አባሎች ውስጥ 10% የሚሆኑት እንኳን
ቢጸኑ አሁንም አዋጭ ነው፡፡ እነዚህ 50 አባሎች እስከ ዕለተ ሞታቸው ድረስ
የቤተክርስቲያኒቱን የመባ ሳጥኖች ይሞላሉ፡፡ የሐሰተኛ ነቢያቶች ፍሬዎች እነዚህ
ናቸው፡፡
በኮርያ እንዲህ ያለው የክርስትና ንግድ ከጥቂት ጊዜ በፊት በጣም
ተስፋፍቶ ስለነበር ይህንን አስመልክቶ በቀልድ መልክ የተዘመረ መዝሙር ነበር፡፡
‹‹ወደ ቤተክርስቲያናቸው እንድንመጣ ነገሩን፡፡ በኢየሱስ እንድናምን ነገሩን፡፡
ከዚያም ገንዘብ፣ ገንዘብና ገንዘብ ጠየቁን፡፡›› ሐሰተኛ ነቢያቶች ሁልጊዜም
የሚናገሩት ስለ ገንዘብና ስለ ብዙ ገንዘብ ብቻ ነው፡፡ ከእነርሱ አንዱ ‹‹አንድ
የተቀደሰ መቅደስ እንስራና ለአምላካችን እንቀድሰው፡፡ ወንድሞችና እህቶች
እግዚአብሄር እዚሁ ሊባርከን ይፈልጋል፡፡ እግዚአብሄር በሐጌ መጽሐፍ ውስጥ
ነቢዩን ሐጌን መቅደሱን እንዲሰራለት ነገረው፡፡ እግዚአብሄር ጥረቶቻቸውን ለዚህ
ውጥን የማያስተባብሩ ሁሉ እንደሚረገሙም ተናገረ፡፡ ምንባቡ መቅደሱን
ለመስራት ብዙ ለሰጡ ሰዎች እግዚአብሄር ታላላቅ በረከቶችን እንደሰጣቸው
ይናገራል፡፡ ይህንን በሐጌ መጽሐፍ ውስጥ ያለውን ምንባብ ትኩረት ልታደርጉበት
ይገባችኋል!›› ስለዚህ ከሐጌ የተወሰደውን ምንባብ በአንድ ባነር ላይ ይጽፍና ከፍ
አድርጎ ይሰቅለዋል፡፡ ስሜቶችን የሚያነቃቃ ሰባኪም ያመጣል፡፡ የስጦታ
ሳህኖችንም ያዞራል፤ ዲያቆናትም ለ300 ካሬ ጫማ መሬት ለእያንዳንዱ፣
ሽማግሌዎችንም ለ1,500 ካሬ ጫማ፣ ተራ ምዕመናኖችም ለ5,000 ጡቦች
መክፈል እንደሚገባቸው ይነገራቸዋል፡፡ የግንባታ ኮሚቴ ካቋቋመ በኋላም ነገ
የሚባል ቀን የሌለ ይመስል ከጉባኤው ገንዘብ መሰብሰብ ይጀምራል፡፡
ወንድሞችና እህቶች በእግዚአብሄር ፊት አንድ ትልቅ የቤተክርስቲያን ሕንጻ
በእርግጥ የሚያስፈልግ ከሆነ መገንባት አለበት፡፡ ይህ በራሱ ስህተት ነው ማለቴ
አይደለም፡፡ ነገር ግን ይህ በእርግጥም አስፈላጊ ካልሆነ፣ አሁን ያለው
የቤተክርስቲያን ሕንጻ ጉባኤውን በሙሉ ለመያዝ ትልቅ ከሆነ ከዚህ የሚተልቅ
ሕንጻ መገንባት አለበት? ሐሰተኛ ነቢያቶች የገንዘብ ጥማት ስላለባቸው
ከጉባኤዎቻቸው ብዙ ገንዘብ ጨምቀው ለመውሰድ እያንዳንዱን ማማኻኛ
ይጠቀማሉ፡፡ ለዚህ አላስፈላጊና ተቀባይነት ለሌለው የቤተክርስቲያን ማስፋፊያ
ግፊት ማድረግም ማማኻኛ ከማቅረብ የዘለለ አይደለም፡፡ ጌታን በሚገባ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ገንዘባችሁን ብቻ ከሚሹ ሐሰተኛ ነቢያቶች ተጠንቀቁ 239

ለማገልገል ብዙ ገንዘብ መስጠት እንደሚገባን ይናገራሉ፡፡ ሰው እነርሱ ያሉትን


በእርግጥም የሚፈጽምላቸው ከሆነ የሰውየው እምነት ትልቅ ነው ለማለት ጊዜ
አይፈጅባቸውም፡፡ ከእነርሱ አንዳንዶቹ እንዲያውም ሁሉን ነገር፤ የትኛው ዲያቆን
ምን ያህል ስጦታና ምን ያህል አስራት እንደሰጠ የሚያሳይ ሁሉን ነገር መዝግቦ
የያዘ ስዕላዊ ቻርትም ሰርተዋል፡፡ ገንዘብ የሌላቸው ሰዎች ወደ
ቤተክርስቲያኖቻቸው እንዳይመጡ ነገሩን አዳጋች አድርገውታል፡፡ የሐሰተኛ
ነቢያቶች ዋናው እምነት ይህ ነው፡፡ ፍሬዎቻቸውም እነዚሁ ናቸው፡፡

የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ ማድረግ አለብን፡፡

እኛ የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ ማድረግ እንሻለን፡፡ እኛ በአብ ፈቃድ


መሰረት እያንዳንዱን መልካም ሥራ ሁሉ ማድረግ እንጂ በግትርነት የገዛ
ራሳችንን ፈቃድ ማድረግ የለብንም፡፡ የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ የሚያደርግ
ማነው? ይህንን ማድረግ የሚችሉት የእርሱ ልጆች ብቻ ናቸው፡፡ የሌላውን አባት
ፈቃድ መከተል የሚችሉት በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምኑ ምዕመናን
ብቻ ናቸው፡፡ እኛ እንዲህ በማመን የሐጢያት ስርየትን ስለተቀበልንና የእርሱ
ልጆች ስለሆንን የእግዚአብሄርን ፈቃድ እየተከተልን ነው፡፡ ለእኛ የእግዚአብሄርን
ፈቃድ ማድረግ ማለት በውሃውና መንፈሱ ወንጌል በማመን የሐጢያት ስርየትን
መቀበልና ሰዎች ሁሉ ከሐጢያቶቻቸው በሙሉ እንዲድኑ መፍቀድ ማለት ነው፡፡
‹‹በሰማይ ያለውን የአብ ፈቃድ ማድረግ›› ማለት ይህ ነው፡፡
ሆኖም በዛሬው የክርስቲያን ማህበረሰብ ውስጥ በጣም ብዙ ሐሰተኛ
ነቢያቶች አሉ፡፡ የእግዚአብሄርን ፈቃድ በማድረግ ፋንታ ዓመጽን ያደርጋሉ፡፡
እግዚአብሄር በመጨረሻው ቀን እነዚህን ውሸታሞች በሙሉ እንደማይቀበላቸው
የታወቀ ነው፡፡ ያን ጊዜ እነዚህ ሐሰተኛ ነቢያቶች ተቀባይነት ሲያጡ ‹‹ነገር ግን
ጌታ ሆይ ያለ ድካም ለአንተ ለፍተን ሳለን የማትቀበለን ለምንድነው? ለአንተ ብዙ
ትንቢት አልተናገርንምን? በስምህ አጋንንቶችን አስወጥተናል፡፡ በሽተኞችን
ፈውሰናል፡፡ እጅግ ትልቁን ቤተክርሰቲያንም ገንብተን ለአንተ ቀድሰን ሰጥተናል!
ከቤተክርስቲያናችም በሺህዎች የሚቆጠሩ የወንጌል አገልጋዮች ልከናል፡፡
በመላው ዓለም ዙሪያም በሺህዎች የሚቆጠሩ ቤተክርስቲያኖችን ተክለናል!
ታዲያ እነዚህን ነገሮች ሁሉ ለአንተ አድርጌ እንዴት አላውቅህም ልትለኝ
ትችላለህ? እዚህ ላይ አንድ የተፈጠረ ስህተት የለምን? ይህ በጣም ተገቢ ያልሆነ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


240 ገንዘባችሁን ብቻ ከሚሹ ሐሰተኛ ነቢያቶች ተጠንቀቁ

ነገር አይደለምን? በእኔ ላይ አሳሳቢ ስህተት እየሰራህብኝ አይደለምን?


በአልዛይመር (የመርሳት) በሽታ እየተሰቃየህ ነውን?›› በማለት ይነጫነጫሉ፡፡
እግዚአብሄርን ‹‹ትንቢት አልተናገርንምን? አጋንንቶችን አላወጣንምን? ብዙ
ተዓምራቶችን አላደረግንምን?›› ሲሉ ራሳቸውን የእግዚአብሄር ታማኝ ሰራተኞች
አድርገው ያስተዋውቃሉ፤ እግዚአብሄርንም ይቃወማሉ፡፡
ጌታችን ግን እንዲህ ይላቸዋል፡- ‹‹እናንተ ዓመጸኞች እኔን እንድታገለግሉኝ
ማን ነገራችሁ? ስሜን እንድታሰራጩ ማን ነገራችሁ? ቃሉን እንድታስተምሩ ማን
ነገራችሁ? ቤተክርስቲያኖችን እንድትገነቡ ነግሬያችኋለሁ? አጋንንቶችን
እንድታውጡ ነግሬአችኋለሁ? እናንተ ዓመጸኞች ስሜን በመዝረፍ እንድትሰሩ
ማን ነገራችሁ? እንድትለፉ ማን ነገራችሁ? ራሳችሁን አሳልፋችሁ እንድትሰጡ
ማን ነገራችሁ? እናንተ ክፉ አድራጊዎች ከእኔ ራቁ፡፡ እኔ ከእናንተ ጋር
የሚያገናኘኝ ምንም ነገር የለኝም! እነዚህን ነገሮች ሁሉ ባታደርጉ ኖሮ እውነተኛ
አገልጋዮቼ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለማሰራጨት ይቀላቸው ነበር፡፡
እናንተ ያደረጋችሁት ነገር ቢኖር የእነርሱን ጥረቶች ማደናቀፍ ብቻ ነበር፡፡
የዲያብሎስ አገልጋዮች ሆናችሁ የሰይጣንን ሥራዎች በመስራት ፈጽማችሁ
እናንተ የሰይጣን አገልጋዮች አሁን ከዲያብሎስ ጋር አብራችሁ ወደ ዘላለም
የሲዖል እሳት ውረዱ! መላዕክቶች አድምጡ! እነዚህ የሰይጣን አገልጋዮች ጨለማ
ውስጥ ይጣሉ!››
እዚህ ላይ ልንገነዘበው የሚገባን ነገር ቢኖር ጌታ እነዚህን ሐሰተኛ
ነቢያቶችና ዳግመኛ ያልተወለዱ ሰዎች ሁሉ የሚተዋቸው መሆኑን ነው፡፡
ፍጻሜያቸው ወደ ዘላለም የሲዖል እሳት መወርወር ነው፡፡ በዛሬዎቹ የሐይማኖት
ሰዎች መካከል ወደዚህ ስፍራ የሚወረወሩ ብዙዎች አሉ፡፡
‹‹በእርግጠኝነት የምናውቀው በተጨባጭ ሲዖል ውስጥ ስንገኝ ብቻ ነው!
ነገር ግን ሲዖል ቀድሞውኑም እንደሞላ ሰምቻለሁ፡፡ ለእኔ የሚሆን ቦታ ይኖራል?
በሲዖል ውስጥ ባዶ ቦታ ስለሌለ ምናልባት እግዚአብሄር በምትኩ ሰማይ
ይወስደኛል!›› እንደዚህ ዓይነት የዕብሪት፣ አይረቤና ከንቱ ነገሮች የሚናገሩ ብዙ
ሰዎች አሉ፡፡ መጨነቅ አያስፈልጋችሁም፡፡ ለሲዖል የታጩ እጅግ በርካታ ሰዎች
ቢኖሩም ሲዖል ራሱ ሁሉንም ለማስተናገድ በጣም ሰፊ ነውና፡፡ ያም ሆኖ ገና ቀሪ
ቦታ አለው፡፡
የሰማይን ከዋክብቶች ተመልከቱ፡፡ አሁን የምናያቸው አንዳንድ ከዋክብቶች
በእርግጥም ከቢሊዮን ዓመታቶች በፊት የነበሩና ቀድመው የጠፉ ሊሆኑ
ይችላሉ፡፡ ይህ ጋላክሲ በእርግጥ ምን ያህል ትልቅ እንደሆነ ታውቃላችሁን?

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ገንዘባችሁን ብቻ ከሚሹ ሐሰተኛ ነቢያቶች ተጠንቀቁ 241

በምሽት ሰማይ ላይ ብዙ ከዋክብቶችን የያዘውን ጋላክሲ ስንመለከት ብዙዎቹ


ከዋክብቶች ብርሃናቸውን ወደ እኛ ለማድረስና እኛም እነርሱን በዓኖቻችን
ለማየት በቢሊዮን የሚቆጠሩ የብርሃን ዓመታቶች ወስደውባቸዋል፡፡ በዚያ ምን
ያህል ከዋክብቶች አሉ? ነገሩ እንዲህ ከሆነ በሲዖል እናንተን ለመቀበል በቂ ስፍራ
አይኖርምን?
እግዚአብሄር ዘላለማዊ ነው፡፡ ሁሉን ቻይ መለኮታዊነቱም ማለቂያ በሌለው
ዩኒቨርስ ውስጥ ይኖራል፡፡ ጌታችን ሁሉን አዋቂ፣ ሁሉን ቻይና በሁሉ ቦታ
የሚገኝ ነው፡፡ በዩኒቨርስ ውስጥ እርሱ የሌለበት ስፍራ የለም፡፡ እርሱ ሊያደርገው
የማይችለውም ምንም ነገር የለም፡፡ አምላካችን ሐጢያተኞችንና ሐሰተኛ
ነቢያቶችን በሙሉ ሲዖል የሚያስቀምጥበት በቂ ስፍራ ማግኘት ባለመቻሉ
ሐጢተኞች ሰማይ ይገቡ ዘንድ ለመፍቀድ ይገደዳል ብላችሁ ታስባላችሁን? ሰው
ሰማይን ወይም ድንቅ የሆነው የተፈጥሮ ክስተት ሲመለከት ሁለት ጊዜ ብቻ ስለ
እግዚአብሄር ቢያስብ ‹‹ኦ አምላኬ ከማመን በቀር ሌላ አንዳች የሚደረግ ነገር
የለም›› በማለት አለማመኑን ያቆም ነበር፡፡ እግዚአብሄር በቃሉ እንዲህ ብሎዋል፡-
‹‹የማይታየው ባህርይ እርሱም የዘላለም ሐይሉ ደግሞም አምላክነቱ ከዓለም
ፍጥረት ጀምሮ ከተሰሩት ታውቆ ግልጥ ሆኖ ይታያልና፡፡ ስለዚህ የሚያመካኙት
አጡ፡፡›› (ሮሜ 1፡20)
ሐሰተኛ ነቢያቶችን ማወቅ ይገባናል፡፡ የተታለሉት ሰዎችም በምን ውሸቶች
እንደተታለሉ ማወቅ አለብን፡፡ እነርሱን በዕውር ድንብር የምንከተላቸው ከሆነ
መጨረሻችን ሲዖል ይሆናል፡፡ ጌታችን እንዲህ ብሎዋል፡- ‹‹ይህን ቃሌን ሰምቶ
የሚያደርገው ሁሉ ቤቱን በዓለት ላይ የሰራ ልባም ሰውን ይመስላል፡፡›› ኢየሱስ
የእግዚአብሄርን ቃል ሰምቶ የሚያደርገው ሁሉ ቤቱን በዓለት ላይ የሰራ ሰውን
እንደሚመስል ስለተናገረ ዳግመኛ ከተወለዱት በቀር የእግዚአብሄርን ቃል ሰምቶ
የሚያደርግ ማንም የለም፡፡ የአብን ፈቃድ ማድረግ የሚችሉት በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል በማመን ከሐጢያቶቻቸው የነጹ ሰዎች ብቻ ናቸው፡፡
በመንግሥተ ሰማይ የእምነትን ቤት የሚሰሩት ዳግመኛ የተወለዱ ብቻ
ናቸው፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ቃል በማመንና በቃሉ ላይም ጸንተን
በመቆም ሁላችንም በዚህ እምነት የእምነት ቤታችንን እየሰራን ነው፡፡ በእምነት
የተሰራ እንዲህ ያለ ቤት ፈጽሞ አይወድቅም፡፡ በኋላም ጎርፍ ይህንን ዓለም
ሲያጥለቀልቅ፣ አውሎ ነፋሶች ሲበረቱና እኛም በውሃ ማዕበሎች ስንመታ
ቤቶቻችንን በዓለት ላይ ስለሰራንና ይህ ዓለትም ከሁሉም ማዕበሎች
ስለሚጠብቀን እነዚህ ቤቶች ፈጽሞ አይወድቁም፡፡ በአንጻሩ ዳግመኛ ሳይወለዱ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


242 ገንዘባችሁን ብቻ ከሚሹ ሐሰተኛ ነቢያቶች ተጠንቀቁ

በኢየሱስ የሚያምኑ ሰዎች ቤቶቻቸውን በአሸዋ ላይ ስለሰሩዋቸው ጎርፍ ሲመጣና


የውሃ ሙላት ሲፈጠር መሰረታቸው ተጠራርጎ ይወስድና ቤቶቻቸው
በአስደንጋጭ ሁኔታ ይፈርሳሉ፡፡
ወንድሞችና እህቶች ሁላችሁም የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ቃል
ከማያውቁ፣ ዳግመኛ ካልተወለዱና ሰዎችን ሰፊ ወደሆነው የጥፋት መንገድ
ከሚመሩ ሐሰተኛ ነቢያቶች መጠበቅ አለብን፡፡

መልካም ዛፍ መልካም ፍሬዎችን ያፈራል፡፡

ትክክለኛ የሆነ መልካም ዛፍ መልካም ፍሬዎችን ያፈራል፡፡ ዛፉ ራሱ


መልካም ስለሆነ መልካም ፍሬዎችን ያፈራል፡፡ ዳግመኛ የተወለዱ ሰዎች ምንም
ያህል ብቃት የሌላቸው ቢሆኑም በወንዝ ዳር እንደተተከሉ ዛፎች ሁልጊዜም
ወቅቱን ጠብቀው መልካም ፍሬዎችን የሚያፈሩ ናቸው፡፡ ገበሬ ማዳበሪያና ውሃ
በማጠጣት የሚንከባከበው መልካም ዛፍ ያለ ምንም ችግር መልካም ፍሬዎችን
ያፈራል፡፡ ይህ ብርቅ አይደለም፤ ምክንያቱም ጻድቃን መልካም ፍሬዎችን
ማፍራት ይሻሉና፡፡ እነርሱ የእርሱን የጽድቅ ፍሬዎች የሚያፈሩት የእግዚአብሄርን
ቃል ስለሚሰሙና በእርሱም ስለሚያምኑ ነው፡፡ መልካም ፍሬዎች የሚፈልቁት
ከጻድቃኖች ብቻ ነው፡፡ እያንዳንዱ መልካም ዛፍ መልካም ፍሬዎችን ያፈራል፡፡
እናንተስ ታዲያ? በመንፈሳዊ ሁኔታችሁ መልካም ዛፎች ናችሁን?
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን የሐጢያት ስርየትን ያገኙ የእግዚአብሄር
ሕዝቦች ሆናችኋልን? በእግዚአብሄር ፊት እውነተኛዎቹ ቅዱሳኖች ጻድቃኖች ብቻ
ናቸው፡፡ የእግዚአብሄር አገልጋዮች መሆን የሚችሉት በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል የሚያምኑ ብቻ ናቸው፡፡
ኢየሱስ ዛፍ በመንፈሳዊ ፍሬዎች እንደሚታወቅ በመናገሩ ስለ ገንዘብ ብቻ
የሚያወሩ ሰዎች ሁሉ ሐሰተኛ ነቢያቶች ናቸው፡፡ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
የሚሰብኩና የጽድቅን ፍሬዎች የሚያፈሩ ሰዎች ግን እውነተኛ ነቢያቶች ናቸው፡፡
መጋቢዎች በጉባኤያቸው ውስጥ ያሉት ብዙዎቹ ከሥራ ተባርረው ምኑን ከምን
እንደሚያደርጉት ግራ በተጋቡበት ሁኔታ ገንዘብ ላይ ብቻ ሲያተኩሩና
ቤተክርስቲያኖቻቸውን ለመገንባት ሁሉንም ዓይነት ግርግር ሲፈጥሩ እንዴት
መልካም ዛፎች ናቸው ብለን ልንገልጣቸው እንችላለን? አሳፋሪ የሆኑትንና
አስፈላጊ ያልሆኑትን ትልልቅ ቤተክርስቲያኖች ሲያጠናቅቁ በእርግጥ ይደሰታልን?

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ገንዘባችሁን ብቻ ከሚሹ ሐሰተኛ ነቢያቶች ተጠንቀቁ 243

ግዙፍ የሆኑትን ቤተክርስቲያኖች በሚሞሉት ዕውር ክርስቲያኖች ይደሰታልን?


ወንድሞችና እህቶች ከሰዎች ሁሉ ቢያንስ እናንተ በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል ማመንና ይህንንም ለሰው ሁሉ ማዳረስ አለባችሁ፡፡ ለሁላችንም ቢሆን
በዚህ ምድር ላይ የምንኖረው ሕይወት ጊዜያዊ ብቻ ነው፡፡ ብዙም ሳይቆይ
ሁላችንም ራሳችንን በእግዚአብሄር ፊት ቆመን እናገኘዋለን፡፡ ሌሎች
የሐጢያቶቻቸውን ስርየት ያገኙ ዘንድ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
ለማሰራጨት የተሰጠ ሕይወት በእግዚአብሄር ፊት የሚኖር ትክክለኛ ሕይወት
ነው፡፡ ሌሎችም የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በጆሮዎቻቸው በመስማት፣
በጭንቅላታቸው በመረዳትና በልቦቻቸው በማመን ወደ እግዚአብሄር ጽድቅ
ይደርሱና በአንደበታቸው በመመስከርም ከሐጢያቶቻቸው ይድኑ ዘንድ
የሚመሩዋቸው ሰዎች መልካም ፍሬዎችን የሚያፈሩ ዛፎች ናቸው፡፡
በዚህ ዘመንና ጊዜ ሁላችንም የእግዚአብሄር ቃል የሆነውን የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል በዚህ ዓለም ላይ ለሚኖር ለእንዳንዱ ሰው ማሰራጨት
አለብን፡፡ ሐሰተኛ ነቢያቶች በእርግጥ እነማን እንደሆኑ ለሌሎች ማስተማር
አለብን፡፡ በቅርቡ የወንጌል ጋዜጦቻችንን ስናሰራጭ ነበር፡፡ ብዙውን ጊዜ
ከአካባቢዎቻችን ሐሰተኛ ነቢያቶች ማን እንደሆኑ እንድናስተምራቸው የሚጠይቁ
የስልክ ጥሪዎች ይደርሱናል፡፡
ለእኛ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ማሰራጨት እነርሱን ከውሸታም
በዝባዦች አድኖ ለእግዚአብሄር መስጠት ነው፡፡ ውሸታሞቹ እነማን እንደሆኑና
ትክክለኛውም እምነት ምን እንደሆነ ለሰው ሁሉ ማስተማር አለብን፡፡ የሚያምኑ
ሁሉ ከሐጢያቶቻቸው ይድኑ ዘንድም እውነተኛውን የውሃና የመንፈስ ወንጌል
ልንሰብክላቸው ይገባናል፡፡
እኛ መረዳት የሚገባን ነገር ቢኖር ጠባቡ መንገድ አስቸጋሪው መንገድ ወደ
ሕይወት የሚመራን መንገድ መሆኑን ነው፡፡ ነገር ግን ጠባቡን የሕይወት በር
የሚያንኳኩና የሚሹት ሰዎች ብዙ አይደሉም፡፡ ያም ቢሆን የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል እውነት ለሰው ሁሉ ማሰራጨታችንን መቀጠል አለብን፡፡ ወደ
ጥፋታቸው እየነጎዱ ያሉትንም አሁን በሐሰተኛ ነቢያቶች እየተታለሉ
ስለመሆናቸው ልናነቃቸው ይገባናል፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የምናምን
እናንተና እኔ ማድረግ ያለብን ይህንን ነው፡፡ ጌታችን እንዲህ ብሎዋል፡- ‹‹እኔ
የዓለም ብርሃን ነኝ፤ የሚከተለኝ የሕይወት ብርሃን ይሆንለታል እንጂ በጨለማ
አይመላለስም፡፡›› (ዮሐንስ 8፡12) ጌታችን እኛ ጻድቃኖችም እንደዚሁ የዓለም
ብርሃን እንደሆንን ተናግሮዋል፡፡ እርሱ እንዲህም ብሎዋል፡- ‹‹መብራትንም

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


244 ገንዘባችሁን ብቻ ከሚሹ ሐሰተኛ ነቢያቶች ተጠንቀቁ

አብርቶ በዕቃ የሚከድነው ወይም ከአልጋ በታች የሚያኖረው የለም፡፡ የሚገቡት


ሰዎች ብርሃኑን እንዲያዩ በመቅረዝ ላይ ያኖረዋል እንጂ፡፡›› (ሉቃስ 8፡16) ሁሉም
ይህንን ብርሃን አይተው ወደ ብርሃኑ እንዲመጡና ይህ ብርሃን እንዲኖራቸው እኛ
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል የሚያውቀውንና የሚያምነውን የእምነት ብርሃን
ማብራት አለብን፡፡
በማጠቃለያው ለሁላችሁም የሰጠሁትን ቁልፍ ምክር እንደገና ላንሳው፡፡
በዚህ በመጨረሻው ዘመን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል የማሰራጨት
ሐላፊነታችንን መፈጸም አለብን፡፡ ሁኔታዎቻችን ምንም ያህል አስቸጋሪ ቢሆኑም
የእግዚአብሄር አብን ፈቃድ ያለ ማቋረጥ ማድረግ አለብን፡፡ ይህ ዓለም በጨለመ
ቁጥር እኛም ይህንን ወንጌል ይበልጥ ማሰራጨት አለብን፡፡ ምክንያቱም ከዓለም
ሐጢያቶችና ከሐሰተኛ ነቢያቶች መዳን ያለባቸው ብዙ ሰዎች የሚገኙት በእነዚህ
የመጨረሻ ጊዜያቶች ነውና፡፡ ስለዚህ ሁላችንም የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
ዘር በላቀ ቁርጠኝነትና መሰጠት በመዝራት እንቀጥል፡፡ 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ምዕራፍ
8

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት
ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
የመንፈሳውያን
ለምጻሞች ፈውስ
‹‹ ማቴዎስ 8፡1-4 ››
‹‹ከተራራም በወረደ ጊዜ ብዙ ሕዝብ ተከተሉት፡፡ እነሆም ለምጻም ቀርቦ፡-
ጌታ ሆይ ብትወድስ ልታነጻኝ ትችላለህ? እያለ ሰገደለት፡፡ እጁንም ዘርግቶ
ዳሰሰውና፡- እወዳለሁ ንጻ አለው፡፡ ወዲያውም ከለምጹ ነጻ፡፡ ኢየሱስም፡-
ለማንም እንዳትናገር ተጠንቀቅ፤ ነገር ግን ሄደህ ራስህን ለካህን አሳይ፤ ለእነርሱም
ምስክር እንዲሆን ሙሴ ያዘዘውን መባ አቅርብ አለው፡፡››

አንድ ለምጻም መጀመሪያ በቫይረሱ ከተበከለበት ጊዜ አንስቶ እስከ ሦስት


ዓመት ድረስ አንዳችም ተጨባጭ የለምጽ ምልክቶች እንደማይታዩበት
ይናገራሉ፡፡ ከአራተኛው ዓመት ጀምሮ ግን አንዳንድ የሚታዩ ምልክቶች ቀስ
በቀስ ይታያሉ፡፡ ለምጻሙ ብክለቱን ከሌሎች መደበቅ የማይችሉበት ደረጃ ላይ
ለመድረስም ተጨማሪ ሦስት ዓመታቶችም ይወስዳል፡፡ ያን ጊዜ የለምጹ
ምልክቶች ሙሉ በሙሉ ይታያሉ፡፡ የለምጹ ተፈጥሮ ይህ ነው፡፡
የዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ኢየሱስ ለምጻሙን እንደፈወሰ
ያብራራል፡፡ በዚህ ምንባብ ላይ የተገለጠው ሁነት በትክክል የሆነ ነው፡፡
እግዚአብሄርም በዚህ አማካይነት የሐጢያቶቻችንን ችግር ፈጽሞ የፈታው
የመሆኑንም እውነት እየነገረን ነው፡፡
በዛሬው ምንባብ ላይ የተገለጠው ለምጻም ራሱን ሳይደብቅ ኢየሱስ
እንዲፈውሰው ፈልጎ ሊጠይቀው በፊቱ ቀረበ፡፡ ምክንያቱም ከሕመሙ ለመዳን
ከልቡ ናፍቆ ነበርና፡፡ ይህ ለምጻም ኢየሱስ ማናቸውንም በሽታዎች መፈወስ
እንደሚችልና እርሱንም ከሕመሙ ሊፈውሰውና ሊያነጻው የሚችል ሌላ ሰው
ሳይሆን ኢየሱስ መሆኑን አምኖ ነበር፡፡ ኢየሱስም የዚህን ለምጻም እምነት
ተመልክቶ የሚሻውን አደረገለት፡፡ በኋላ ላይ ለመቶ አለቃውም ያደረገው ይህንኑ
ነር፡፡ እዚህ ላይ ኢየሱስ በእርግጥም ሊፈውሰው የፈለገው ሥጋዊ ሕማምን
ሳይሆን የሐጢያት በሽታን እንደነበር ማስታወስ ይኖርብናል፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


248 የመንፈሳውያን ለምጻሞች ፈውስ

እዚህ ላይ ለምጽ የሚያመለክተው ይህንን በሽታ የሚመስሉ ሐጢያቶች


በልቦቻችንና በሰውነታችን ውስጥ ያሉ መሆናቸውን ነው፡፡ ከእናታችን ማህጸን
ከተወለድንበት ቅጽበት ጀምሮ ሁላችንም 12 የሐጢያት በሽታዎችን ይዘን
ተወልደናል፡፡ ገና ጨቅላዎች በነበርንበት ጊዜ እንደዚህ ዓይነት ክፉ ሐጢያተኞች
መሆናችንን አናውቅም ነበር፡፡ ነገር ግን የተወሰነ ዕድሜ ላይ ስንደርስ እውነተኛ
ማንነታችንን ተረዳን፡፡ ይህንንም ከእግዚአብሄር መደበቅ አልቻልንም፡፡ ከዚያም
በእምነት በኢየሱስ ፊት ቀርበን ‹‹ብትወድስ ከሐጢያቶቼ ሁሉ ልታነጻኝ
ትችላለህ?›› አልነው፡፡ እናንተና እኔ የሐጢያቶቻችንን ስርየት የተቀበልነው በዚህ
መንገድ ነው፡፡ ኢየሱስ ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ሊፈውሰን የሚችል እንደሆነ
የሚያምን እንዲህ ዓይነት እምነት ሲኖረን ማናቸውንም ሐፍረት መቋቋም
እንችላለን፡፡
ኢየሱስ ይህንን ለምጻም የፈወሰው በአንድ ጊዜ ነበር ወይስ እርሱን
ለመፈወስ ብዙ ጊዜ ወስዶበታል? መጽሐፍ ቅዱስ ኢየሱስ እርሱን የፈወሰው
በአንድ ጊዜ እንደሆነ ይናገራል፡፡ ስለዚህ ኢየሱስ እናንተን ከሐጢያቶቻችሁ
የፈወሳችሁ ብዛት ባላቸው የደረጃ በደረጃ ፈውስ አይደለም፡፡ ነገር ግን
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ቃል አማካይነት ለአንዴና ለዘላለም
ፈውሶዋችኋል፡፡
በደም መፍሰስ ትሰቃይ የነበረች ሴት የኢየሱስን ልብስ በእምነት ስትነካ
ተፈውሳ በአንድ ጊዜ የደምዋ ምንጭ ደረቀ፡፡ (ማርቆስ 5፡23-34) የሶርያ ንጉሥ
የጭፍራ አለቃ የነበረው ንዕማንም የእግዚአብሄርን ቃል በእምነት በመታዘዙ
በአንድ ጊዜ ከለምጹ ተፈወሰ፡፡ (2ኛ ነገሥት 5፡1-14) በዛሬው ምንባብ ላይ
የተጠቀሰውም ለምጻም እንደዚሁ የኢየሱስ እጅ እንደዳሰሰው ወዲያውኑ
ተፈወሰ፡፡ እኛም በእግዚአብሄር ቃል ላይ እምነት ቢኖረን ሁላችንም የሰውን ዘር
ሐጢያቶች በሙሉ እንዲወገዱ ያደረገውን የደህንነት ሐይል ወደ ማወቅና ወደ
ማመን መምጣት እንችላለን፡፡ በዚህ እምነትም ሁላችንም ዘላለማዊውን
የሐጢያቶቻችንን ስርየት ለአንዴና ለዘላለም መቀበል እንችላለን፡፡ የእያንዳንዱ
ሰው የሐጢያት በሽታ የሚፈወሰው በቃሉ ላይ ባለው እምነት በአንድ ጊዜ እንጂ
በጭራሽ ደረጃ በደረጃ አይደለም፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የመንፈሳውያን ለምጻሞች ፈውስ 249

በሐይማኖቶች እምነትና በእውነተኛው ወንጌል በሚያምኑ ሰዎች


እምነት መካከል ያለው ልዩነት፡፡

በሐይማኖተኞችና እውነተኛ እምነት ባላቸው ሰዎች መካከል ያለው ልዩነት


ይህ ነው፡፡ ሐይማኖተኞች እውነትን ችላ በማለታቸው በየቀኑ በሐጢያት ውስጥ
ቢኖሩም የዕለት የንስሐ ጸሎቶቻቸውን በማድረግ ከሐጢያቶቻቸው ስርየትን
ማግኘት እንደሚችሉ በተሳሳተ መንገድ ያስባሉ፡፡ በአንጻሩ ግን በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል የሚያምኑ ምዕመናኖች አሁን ከሐጢያቶቻቸው ሁሉ ለአንዴና
ለዘላለም ስርየትን አግኝተው የእርሱ ልጆች በመሆን በእግዚአብሄር ባርኮቶች
ውስጥ ይኖራሉ፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ ሰው ሁሉ ከሐጢያቶቹ በሙሉ መዳን የሚችለው የእርሱን
ቃል በማመን ብቻ እንደሆነ በግልጽ ይናገራል፡፡ የሐጢያት ችግሮቻችንን
በራሳችን ብርታት፣ በራሳችን ሥራዎችና በራሳችን ሰናይ ምግባሮች መፍታት
ብንችል ኖሮ ኢየሱስ ወደዚህ ምድር መምጣት አያስፈልገውም ነበር፡፡
የሐጢያትን ችግር በእነዚህ ጥረቶች አማካይነት መፍታት ችለን ቢሆን ኖሮ
ኢየሱስን በዕድሜ ዘመናችን ከቶውኑም ልንገናኘው ባልቻልንም ነበር፡፡
ማንም ሰው ምንም ያህል ነገር ቢያደርግ ጠንክሮ ቢሞክር የሐጢያቶቹን
ችግር በራሱ መፍታት አይችልም፡፡ የመፍትሄው ቁልፍ የሚገኘው የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል በማመን ውስጥ ነው፡፡ ሰዎች ምንም ያህል ጠንክረው
ቢሞክሩ ሐጢያት መስራትን ማቆም የማይችሉ ፍጥረታቶች ስለሆኑ በምትኩ
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ማመን አለባቸው፡፡ ሰው የንስሐ ጸሎቶች ፈጽሞ
ሐጢያቶቹን ሊያስወግዱለት እንደማይችሉና በራሱም የሐጢያቶቹን ችግር
መፍታት እንደማይችል ሲረዳ በእግዚአብሄር ፊት ቀርቦ የከፋ ሐጢያተኛ
መሆኑን ለእርሱ ከተናዘዘና በውሃውና በመንፈስ ወንጌል ካመነ ሊነጻ የማይችል
ምንም ዓይነት ሐጢያት የለም፡፡ ሐጢያተኞች ወደ ኢየሱስ ቀርበው የእርሱን
ምህረት ከጠየቁ ኢየሱስ ለምጻሙን በአንድ ጊዜ እንደፈወሰው በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት በእርግጠኝነት ሐጢያቶቻቸውን ለአንዴና
ለዘላለም ያስወግድላቸዋል፡፡
ጌታ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በመስጠት ሐጢያቶቻችንን በሙሉ
የሚተውልን እውነተኛው ማንነታችን በእግዚአብሄር ፊት ሲገለጥና የኢየሱስን
ደህንነት ስንሻ ነው፡፡ ከሐጢያቶቻቸው ሁሉ የሚድኑትና የእርሱ ልጆች
የሚሆኑት ‹‹ጌታ ሆይ ማረኝ፤ በሐጢያቶቼ ምክንያት ወደ ሲዖል ልወርድ ነው››

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


250 የመንፈሳውያን ለምጻሞች ፈውስ

በማለት የእግዚአብሄርን ምህረት የሚለምኑ ሰዎች ናቸው፡፡ ሐጢያተኞች በሙሉ


መሰረታዊ ማንነታቸው ሐጢያተኞች መሆናቸውን አምነው የጌታን ምህረት
ከጠየቁ ቀድሞውኑም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የተፈጸመውን ዘላለማዊውን
የሐጢያት ስርየት ይለግሳቸዋል፡፡
ሮሜ 3፡10 እንዲህ ይላል፡- ‹‹ጻድቅ የለም አንድም ስንኳ፡፡›› በዚህ ምንባብ
ውስጥ ሐዋርያው ጳውሎስ የጠቆመው ገና የሐጢያቶቻቸውን ስርየት
ያልተቀበሉትን ሰዎች ነው፡፡ ኢየሱስ ወደዚህ ምድር የመጣው ሐጢያተኞችን
ፈጽሞ ሐጢያት አልባ ለማድረግና ወደ እግዚአብሄር ልጅነት ለመለወጥ ነው፡፡
ነገር ግን አብዛኞቹ ከርስቲያኖች አሁንም ድረስ ገሚስ ሐጢያተኞች ሆነው
መገኘታቸው ያሳዝናል፡፡ በዚህ ዓለም ላይ ገሚስ የሐጢያት ስርየት ወይም ገሚስ
ጻድቃኖች ሊኖሩ ቢችሉም በእግዚአብሄር መንግሥት ውስጥ ገሚስ ጻድቃኖችም
ሆኑ ገሚስ ሐጢያተኞች አይገኙም፡፡ ገሚስ ሐጢያተኞች የሚባሉት እነማን
ናቸው? እነርሱ በየቀኑ የንስሐ ጸሎቶቻቸውን በመጸለይ የሐጢያት ስርየትን
ለማግኘት የሚሞክሩ ሰዎች ናቸው፡፡ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ የሚደመስሱት
እንዲህ ዓይነት የንስሐ ጸሎቶችን በማቅረብ ሳይሆን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
ቃል በማመን ነው፡፡
የሰውን ዘር በውሃውና በመንፈሱ የወንጌል እውነት ከሐጢያት
በሽታዎቻቸው ፈጽሞ የፈወሳቸው ኢየሱስ ነው፡፡ ኢየሱስ ስለ ሐጢያት በተናገረ
ጊዜ በአዳም ሐጢያትና በግለሰብ ሐጢያቶች መካከል ልዩነትን አላደረገም፡፡
ኢየሱስ የአዳም ሐጢያታቸውን ቢወስድላቸውም በግላቸው ከሚሰሩዋቸው
ሐጢያቶች ይቅር መባል ያለባቸው በንስሐ ነው ብለው የሚያምኑትን ሰዎች
እምነት አልደገፈም፡፡ እንደዚህ የሚያምኑ ሰዎች የእግዚአብሄርን ልብ እየጎዱት
በመሆኑ ይጠፋሉ፡፡ ምክንያቱም ቀሪ ዕድሜያቸውን ሐጢያተኞች ሆነው
ይኖራሉና፡፡
እግዚአብሄር እንዲህ ያለውን ገሚስ እምነት አይቀበልም፡፡ ሰው በኢየሱስ
የማያምን ከሆነ 100% አያምንም፡፡ በሌላ አነጋገር 50% የሚባል እምነት የለም፡፡
‹‹የመንጻት ትምህርት›› ተብሎ የሚጠራው ምንድነው? ‹‹በእምነት ጻድቅ ተብሎ
የመቆጠር እምነት›› ነው፡፡ ማለትም ክርስቲያኖች አሁንም ድረስ ሐጢያቶቻቸው
አብረዋቸው ቢኖሩም በኢየሱስ ባላቸው እምነት ጻድቃን ተብለው ሊጠሩ
ይችላሉ ብለው ያምናሉ፡፡ ይህ እንዴት ያለ ከንቱ ነገር ነው! ጌታችን አንድ ጊዜ
ሐጢያቶቻችንን ከእኛ ባስወገደውና ፈጽሞ በደመሰሳቸው ጊዜ የእያንዳንዱ ሰው
ሐጢያቶች በሙሉ ቀድሞውኑም ተወግደዋል፡፡ ስለዚህ ሐጢያቶቻችንን አጥቦ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የመንፈሳውያን ለምጻሞች ፈውስ 251

ያነጻው ኢየሱስ የተቀበለው ጥምቀት ነው፡፡ (1ኛ ጴጥሮስ 3፡21)


በጥቅል አነጋገር አብዛኞቹ የዛሬዎቹ ክርስቲያን መሪዎች ኢየሱስ የአዳምን
ሐጢያት ወስዶዋል፤ እኛ ግን በተናጥል የንስሐ ጸሎቶቻችንን በማቅረብ
ከሐጢያታችን መንጻት ይገባናል ይላሉ፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ግን ‹‹በሐጢያት›› እና
‹‹በሐጢያቶች›› ማለትም በአዳምና በግለሰብ ሐጢያቶች መካከል ልዩነት
አላደረገም፡፡ በኢየሱስ ፊት ሐጢያቶች በሙሉ ትልቅ ወይም ትንሽ፣ የአዳም
ይሁን የግል በእኩል ደረጃ ‹‹የዓለም ሐጢያቶች›› (ዮሐንስ 1፡29) ተብለው
ተገልጠዋል፡፡ ቆሻሻ ውሃ፣ የቧንቧ ውሃና የጅረት ውሃ ሁሉም ያው ውሃ
እንደሆኑ ሁሉ ሐጢያቶች በሙሉም ያው የዓለም ሐጢያቶች ናቸው፡፡ በመጽሐፍ
ቅዱስ ውስጥ ‹‹ዕውሮችን የሚመሩ ዕውሮች ናቸው፤ ዕውርም ዕውርን ቢመራው
ሁለቱም ወደ ጉድጓድ ይወድቃሉ፡፡›› (ማቴዎስ 15፡14) ራሳቸው መሪዎቻቸው
ዳግመኛ ስላልተወለዱ የሐጢያትን ችግር እንዴት እንደሚፈቱ አያውቁም፡፡
የንስሐ ጸሎቶቻቸውን ባቀረቡ ቁጥር እግዚአብሄር ሐጢያቶቻቸውን ይቅር
እንደሚላቸው በመንገር እንዲህ ባሉ መሰረተ ቢስ ትምህርቶች የሚያምኑት ለዚህ
ነው፡፡

ሁሉም ሰው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ሐይል ማመን አለበት፡፡

እንግዲያውስ የሐጢያትን ስርየት ለማግኘት እውነተኛው ንስሐ ምንድነው?


በእንከን ከተሞላው ዕውቀታቸውና ከተሳሳቱት እምነቶቻቸው ተመልሰው ትክክል
በሆነው ነገር ማመን ነው፡፡ የሰው ዘር ሐጢያቶች ጌታን ሁልጊዜም ይቅር
እንዲላቸው በመጠየቅ ይቅር ሊባሉ አይችሉም፡፡
ጌታ እንዲህ ብሎዋል፡- ‹‹ከመስዋዕት ይልቅ ምህረትን ከሚቃጠል
መስዋዕት ይልቅ እግዚአብሄርን ማወቅ እወድዳለሁና፡፡›› (ሆሴዕ 6፡6) ኢየሱስ
ወደዚህ ምድር የመጣው በሐጢያቶቻቸው ምክንያት ለሲዖል ለታጩ ነፍሳቶች
ሁሉ ስለራራ ነው፡፡ የእግዚአብሄር ፈቃድ በኢየሱስ ክርስቶስ አማካይነት
ሐጢያተኞችን ሐጢያት አልባ ማድረግ፣ እነርሱን መቀደስና የመንግሥቱ ተካፋይ
እንዲሆኑ ማድረግ ነበር፡፡ ጌታችን ወደዚህ ምድር የመጣውና በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት የአብን ፈቃድ የፈጸመው ለዚህ ነበር፡፡
ሮሜ 6፡23 እንዲህ ይላል፡- ‹‹የሐጢአት ደመወዝ ሞት ነውና፤
የእግዚአብሄር የጸጋ ስጦታ ግን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ የዘላለም ሕይወት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


252 የመንፈሳውያን ለምጻሞች ፈውስ

ነው፡፡›› አምላካችን የፍቅር አምላክ ቢሆንም ሐጢያት ያለባቸውን ሁሉ ወደ


ሲዖል ይልካቸዋል፡፡ የእርሱ ፍቅር በውሃወና በመንፈሱ ወንጌል ከሚያምኑ
ምዕመናኖች ጋር አብሮ ለዘላለም በመንግሥቱ ውስጥ ይኖሩ ዘንድ የሐጢያት
ስርየትን መስጠት ነው፡፡ በሌላ አነጋገር እግዚአብሄር ሐጢያት አልባ አድርጎ
የለወጠንን የሐጢያት ስርየት ሰጥቶናል፡፡
በዚህ ዘመን በራሳቸው አስተሳሰቦች ላይ ተመስርተው በፈለጉት
በማንኛውም መንገድ በኢየሱስ የሚያምኑ በጣም ብዙ ክርስቲያኖች አሉ፡፡ አንድ
ሰው አስራትን በታማኝነት በመክፈል፣ ለቤተክርስቲያኑም ብዙ ገንዘብ በመለገስ፣
በየጊዜውም በጠዋት የጸሎት ስብሰባዎች ላይ በመገኘትና ወ.ዘ.ተ ዕድሜውን
በሙሉ ለሐይማኖትና ለበጎ ምግባር ተሰጥቶ ከኖረ በኋላ አሁን በእግዚአብሄር
ፊት ሊቆም ነው እንበል፡፡ እርሱ ለጌታ በኩራት እንዲህ ይላል፡- ‹‹ጌታ ሆይ
መጣሁ፤ ይህ ብዙ ሐጢያቶችን የሰራ ሐጢያተኛ አሁን በፊትህ ቆሞዋል!›› ያን
ጊዜ ጌታ ምን ይለዋል?
በማቴዎስ 7 ላይ ኢየሱስ እንዲህ ብሎዋል፡- ‹‹በሰማያት ያለውን የአባቴን
ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት
የሚገባ አይደለም፡፡ በዚያ ቀን ብዙዎች፡- ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ በስምህ ትንቢት
አልተናገርንምን? በስምህስ አጋንንትን አላወጣንምን? በስምህስ ብዙ ተዓምራትን
አላደረግንምን? ይሉኛል፡፡ የዚያን ጊዜም፡- ከቶ አላወቅኋችሁም፤ እናንተ
ዓመጸኞች ከእኔ ራቁ ብዬ እመሰክርባቸዋለሁ፡፡›› ጌታችን የሚናገረው ይህንን
ነው፡፡ ጌታችን የሐጢያተኞች አባትም ሆነ ጌታ አይደለም፡፡ ነገር ግን እርሱ
ዳግመኛ የተወለዱና የሐጢያቶቻቸውን ስርየት ያገኙ ጻድቃኖች አባት ነው፡፡ ይህ
ሰው ጌታን ‹‹ጌታ ሆይ አታውቀኝምን? እኔ ስምህን ለመመስከር ዕድሜዬን በሙሉ
ለአንተ ሰጥቻለሁ›› ቢለውም እግዚአብሄር ‹‹ሐጢያት ያለብህ አንተ እንዴት የኔ
ልጅ ነኝ ብለህ ለማስመሰል ትደፍራለህ? አንተን የሚጠብቅህ ነገር ቢኖር ሲዖል
ነው፤ አንተ ዓመጸኛ!›› ይለዋል፡፡
ስለዚህ ሐጢያተኞች ሁሉ መጀመሪያ ላይ ማድረግ የሚገባቸው ነገር ቢኖር
አሁኑኑ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ማመንና በእምነት የሐጢያቶቻቸውን
ስርየት መቀበል ነው፡፡ ይህ እጅግ ውብና ክቡር እምነት ነው፡፡ ሐሰተኛ
የክርስቲያን መሪዎች የሐጢያቶቻቸውን ስርየት ያልተቀበሉ ሁሉንም ዓይነት
ሐጢያተኞች ወደ ቤተክርስቲያቻቸው ይሰበስቡ ይሆናል፡፡ ነገር ግን ቅዱሳን ብሎ
በትክክል የሚጠራቸው ሰው ይኖራልን? ‹‹ሐጢያተኛ›› የሆነ ቅዱስ እንዴት ሊኖር
ይችላል? ሐጢያት ያለበት ማንም ሰው ሐጢያተኛ እንጂ ቅዱስ አይደለም፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የመንፈሳውያን ለምጻሞች ፈውስ 253

አንድ ሰው ሐጢያት የሌለበት ቅዱስ ተብሎ ሊጠራ የሚችለው በውሃውና


በመንፈሱ ወንጌል በማመን የሐጢያት ስርየትን ሲቀበል ብቻ ነው፡፡
በሆሴዕ 4፡6 ላይ እንዲህ ተጽፎዋል፡- ‹‹ሕዝቤ ዕውቀት ከማጣቱ የተነሳ
ጠፍቷል፡፡ አንተም ዕውቀትን ጠልተሃልና እኔ ካህን እንዳትሆነኝ እጠላሃለሁ፡፡
የአምላክህንም ሕግ ረስተሃልና እኔ ደግሞ ልጆችህን እረሳለሁ፡፡››
የዕውቀት ሁሉ መጀመሪያ እግዚአብሄርን ማወቅ ነው፡፡ ሆኖም በርካታ
ሰዎች እንከን ያለበትንና የተሳሳተውን ዕውቀታቸውን መጣል ስላልቻሉ ግብዞች
ሆነው እየኖሩ ነው፡፡ ጌታችን የመጨረሻው ቀን ሲመጣ ‹‹አላወቅኋችሁም››
የሚላቸው ለዚህ ነው፡፡
ሐጢያተኛ ሐጢያት አልባ የሚሆንበት ብቸኛው መንገድ የሐጢያት
ስርየትን በሚሰጠው ቃል በማመን ነው፡፡ በጌታ መለኮታዊነት እንደዚሁም
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ቃል እምነት ሊኖረን ይገባል፡፡ ብዙ ሰዎች ግን
የኢየሱስን ጥምቀትና የመስቀሉን ወንጌል ሐይል ችላ ብለው ቀስ በቀስ
ከሐጢያቶቻቸው እንደሚነጹ በሚናገረው የሐሰት እምነታቸው ላይ
የተመሰረተውን ምናባዊ የደረጃ በደረጃ ቅድስናን በከንቱ በመከተል
ሕይወታቸውን እያባከኑ ነው፡፡
ቡዲስቶች ሰው የጥሩ ስነ ምግባርና የምህረት ሰው ለመሆን መጣር አለበት
ብለው ትኩረት እንደሚያደርጉት ክርስትና ሰው በራሱ ጥረትና ሥነ ምግባር
ደህንነት የሚያገኝበት ሐይማኖት አይደለም፡፡ ነገር ግን ሰው ምንም ያህል ሰናይ
ለመሆን ጠንክሮ ቢለፋም ፈጽሞ ሐጢያት አልባ መሆን አይቻለውም፡፡ እውነተኛ
የክርስቲያን እምነት በጸጋው ደህንነት ያለ ምንም የሰው ጥረት ከላይ በሚፈስሰው
የውሃና የመንፈስ ወንጌል የሚያምን እምነት ማለት ነው፡፡ ለምጻሙ በጌታችን
ፍቅርና በእውነቱ ሐይል ወዲያውኑ ከበሽታው እንደተፈወሰ ሁሉ እኛም
እንደዚሁ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ሐይል እንዳመንንና ጌታችን ለእኛ
ያለውን ፍቅር እንደተረዳን ወዲያውኑ በልቦቻችን ውስጥ ካሉት ሐጢያቶቻችን
እንድናለን፡፡

በብሉይ ኪዳን እግዚአብሄር ማዳኑን በሙሴ በኩል አሳይቷል፡፡

ጌታ ለምጻሙን ከፈወሰው በኋላ እንዲህ አለው፡- ‹‹ለማንም እንዳትናገር


ተጠንቀቅ፤ ነገር ግን ሄደህ ራስህን ለካህን አሳይ፤ ለእነርሱም ምስክር እንዲሆን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


254 የመንፈሳውያን ለምጻሞች ፈውስ

ሙሴ ያዘዘውን መባ አቅርብ፡፡›› እዚህ ላይ ሙሴ ያዘዘው መባ የሚያመለክተው


የመስዋዕት እንስሳ የሆነውን ጠቦት ነው፡፡
‹‹እግዚአብሄርም ከመገናኛው ድንኳን ውስጥ ሙሴን ጠርቶ እንዲህ ሲል
ተናገረው፡- ለእስራኤል ልጆች እንዲህ ብለህ ንገራቸው፤ ከእናንተ ማናቸውም
ሰው ለእግዚአብሄር መባ ሲያቀርብ መባችሁን ከእንስሳ ወገን ከላሞች ወይም
ከበጎች ታቀርባላችሁ፡፡ መባውም የሚቃጠል መስዋዕት ከላሞች መንጋ ቢሆን
ነውር የሌለበትን ተባቱን ያቀርባል፡፡ በእግዚአብሄር ፊት እንዲሠምር በመገናኛው
ድንኳን ደጃፍ ፊት ያቀርበዋል፡፡ እጁንም በሚቃጠለው መሰዋዕት ራስ ላይ
ይጭናል፡፡ ያሰሰርይለትም ዘንድ የሰመረ ይሆንለታል፡፡›› (ዘሌዋውያን 1፡1-4)
ሙሴ ያዘዘውን መባ በሚመለከት ከላይ ያለው ቁጥር እንዲህ ይላል፡-
‹‹መባችሁን ከእንስሳ ወገን ካሞች ወይም ከበጎች ታቀርባላችሁ፡፡›› እግዚአብሄር
ሕጉን በመስጠት የሰው ዘር ሐጢያተኛ መሆኑን እንዲያውቅ አስቻለው፡፡ ከዚያም
በመገናኛው ድንኳን የመስዋዕት ስርዓት አማካይነት ለእስራኤል ሕዝብ
ሐጢያቶቻቸውን ወደ እነዚህ የመስዋዕት ቁርባኖች ላይ በማስተላለፍ ይቅርታን
የሚያገኙበትን ስርዓት ሰጣቸው፡፡ እግዚአብሄር አብዝቶ ስለወደደንና
ከሐጢያቶቻችን ሊያድነን ስለፈለገ በእኛ ፋንታ በሚሞቱ የጠቦቶችና የላሞች
መባዎች የመስዋዕት ስርዓትን አቋቋመ፡፡
በመስዋዕት ስርዓቱ ውስጥ ‹የእጆች መጫን› በጣም አስፈላጊ ነበር፡፡ ይህ
ማለት ‹‹ማሻገር›› ወይም ‹‹ማስተላለፍ›› ማለት ነው፡፡ ስለዚህ በብሉይ ኪዳን
ዘመን ያለ አንድ ሐጢያተኛ ለመስዋዕት በሚቀርበው ጠቦት ራስ ላይ እጆቹን
ሲጭን በልቡ ውስጥ ያሉት ሐጢያቶች በሙሉ ወደ እንስሳው ይተላለፋሉ፡፡
(ዘሌዋውያን 16፡21) ከዚያ በኋላ ጠቦቱን ያርደውና ደሙን ያፈስሰዋል፡፡ ያን ጊዜ
ካህኑ ከደሙ የተወሰነውን በጣቱ ይነክርና በሚቃጠለው መስዋዕት መሰውያ
ቀንዶች ላይ ያኖረዋል፡፡ የቀረውን ደም በሙሉ ከመሰውያው በታች ያፈስሰዋል፡፡
ካህኑም ለእግዚአብሄር ጣፋጭ ሽታ ይሆን ዘንድ እንስሳውን በመሰውያው ላይ
ያቃጥለው ነበር፡፡ እስራኤሎች በብሉይ ኪዳን ዘመን የሐጢያቶቻቸውን ስርየት
ያገኙት በዚህ መንገድ ነበር፡፡ (ዘሌዋውያን 4፡27-31)
በቀንዶቹ ላይ የተቀባውና ከመሰውያው በታች የፈሰሰው ደም ለሐጢያት
የተከፈለ የሕይወት ደመወዝ ነበር፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ የሥጋ ሕይወት ያለው በደም
ውስጥ እንደሆነና ለነፍስ ማስተሰርያ የሚሆነውም ደም እንደሆነ ይናገራል፡፡
(ዘሌዋውያን 17፡11) የሚቃጠለው መስዋዕት መሰውያ ቀንዶች የፍርዱን
መጽሐፎች ያመላክታሉ፡፡ (ዮሐንስ ራዕይ 20፡12) እያንዳንዱ መተላለፍ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የመንፈሳውያን ለምጻሞች ፈውስ 255

በመጽሐፎች ላይ መጻፍ ይኖርበታል፡፡ ሐጢያተኞችም እንደ ሥራቸው መጠን


በመጽሐፍቱ ላይ በተጻፉት ነገሮች መሰረት ይፈረድባቸዋል፡፡ በዚህ ዓለም ላይ
ስንኖር ሳለ ፍጹም የሆነውን የሐጢያቶቻችንን ስርየት መቀበል ያለብን ለዚህ
ነው፡፡
በአዲስ ኪዳን ዘመን የሐጢያቶቻችንን ስርየት ያገኘነው በምን ዓይነት
እምነት ነው? ከሐጢያቶቻችን ለመዳናችን ማስረጃ ማግኘት የምንችለው ከየት
ነው? ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ለመዳናችን ማስረጃውን ማግኘት የምንችለው
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ላይ ባለን እምነታችን ውስጥ ነው፡፡ የደህንነታችንን
ማረጋገጫ ማግኘት የምንችለው በራዕዮች፣ ልቅ በሆኑ የደስታ ስሜቶች ወይም
በልሳን በመናገር አይደለም፡፡ ምን ያህል ሐጢያተኞች እንደሆንን ማወቅና
ከሐጢያቶቻችንም እንዴት እንደዳንን መመስከር የምንችለው በእግዚአብሄር ቃል
ብቻ ነው፡፡ ይህ የምስክርነት ቃል የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ቃል ነው፡፡
‹‹በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ
እግዚአብሄር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና፡፡››
(ዮሐንስ 3፡16) እግዚአብሄር አብ እኛን ከዓለም ሐጢያቶች ሁሉ ለማዳን አንድ
ልጁን ኢየሱስን ሰጠ፡፡ እርሱ ከሐጢያቶቻችን ያዳነን እንዴት ነበር? ኢየሱስ
ወደዚህ ምድር በመምጣት በብሉይ ኪዳን እንደነበሩት የመስዋዕት በጎችና
ፍየሎች የእኛ የመስዋዕት ቁርባን በመሆን፣ በጥምቀቱ አማካይነትም
የሐጢያተኞችን ሐጢያቶች በተጨባጭ በሰውነቱ በመቀበልና በዚህም የዓለም
ሐጢያቶች በሙሉ በመደምሰስ የእግዚአብሄርን ጽድቅ ሁሉ ፈጸመ፡፡ ይህ
እውነት በየቀኑ በሚቀርቡት የብሉይ ኪዳን ቁርባኖች በኩል ተገልጦዋል፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ ምድር በመጣ ጊዜ በየቀኑ የምንሰራውን የሰው ዘር
ሐጢያቶች በሙሉ እንዴት እንደተቀበለ መገንዘብ አለብን፡፡ ከዓለም ሐጢያቶች
በሙሉ ነጻ መውጣት የምንችለው ያን ጊዜ ብቻ ነው፡፡

በብሉይ ኪዳን ለስርየት ቀን የሚቀርበው መባ፡፡

አሁን ወደ ዘሌዋውያን 16፡29-34 እንመለስ፡- ‹‹ይህ የዘላለም ሥርዓት


ይሁንላችሁ፤ በዚህ ቀን ትነጹ ዘንድ ማስተሰርያ ይሆንላችኋልና፡፡ በሰባተኛው
ወር ከወሩም በአስረኛው ቀን ራሳችሁን አስጨንቋት፡፡ የአገር ልጅም በእናንተም
መካከል የተቀመጠ እንግዳ ሥራን ሁሉ አትሥሩበት፡፡ በእግዚአብሄርም ፊት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


256 የመንፈሳውያን ለምጻሞች ፈውስ

ከሐጢአቶቻችሁ ሁሉ ትነጻላችሁ፡፡ ታላቅ ሰንበት ይሆንላችኋል፡፡ ራሳችሁንም


ታዋርዳላችሁ፡፡ የዘላለም ሥርዓት ነው፡፡ የሚቀባውም በአባቱም ፋንታ ካህን
ሊሆን የሚካነው ካህን ያስተሰርይ፡፡ የተቀደሰውንም የበፍታ ልብስ ይልበስ፡፡
ለቅድስተ ቅዱሳንም ያስተሰርይ፡፡ ለመገናኛውም ድንኳን ለመሠውያውም
ያሰተሰርይ፡፡ ለካህናቱም ለጉባኤውም ሕዝብ ሁሉ ያሰተሰርይ፡፡ ይህም አንድ ጊዜ
በዓመት ለእስራኤል ልጆች ስለ ሐጢአታቸው ሁሉ ያስተሰርይ ዘንድ ዘላለም
ሥርዓት ይሁንላችሁ፡፡››
ይህ ምንባብ በየቀኑ መስዋዕቶችን ማቅረብ ለማይችሉት ሰዎች ሲባል ሊቀ
ካህኑ በዓመት አንድ ጊዜ ለመላው የእስራኤል ሕዝብ የመስዋዕት ቁርባኖችን
ማቅረብ የሚችልበትንና እግዚአብሄር ለእስራኤሎች የፈቀደውን የስርየት ቀን
ቁርባን ያብራራል፡፡ እግዚአብሄር በዚህ ዓመታዊ መስዋዕት አማካይነት
ለእስራኤል ሕዝብ ዓመታዊ የሐጢያቶቻቸውን ስርየት በረከት ለግሶዋቸዋል፡፡
ዘሌዋውያን 16፡6-10 እንዲህ ይላል፡- ‹‹አሮንም ለእርሱ ያለውን የሐቲአቱን
መስዋዕት ወይፈን ያቀርባል፡፡ ለራሱም ለቤተሰቡም ያስተሰርያል፡፡ ሁለቱንም
አውራ ፍየሎች ወስዶ በመገናኛው ድንኳን ደጃፍ አጠገብ በእግዚአብሄር ፊት
ያቆማቸዋል፡፡ አሮንም በሁለቱ ፍየሎች ላይ ዕጣ ይጥልባቸዋል፡፡ አንዱን ዕጣ
ለእግዚአብሄር ሌላውንም ዕጣ ለሚለቀቅ፡፡ አሮንም የእግዚአብሄር ዕጣ የሆነበትን
ፍየል ያስተሰርይበት ዘንድ ለመለቀቅም ወደ ምድረ በዳ ይሰደደው ዘንድ
በሕይወት በእግዚአብሄር ፊት ያቆመዋል፡፡››
በሌላ አነጋገር እግዚአብሄር እስራኤሎች በየቀኑ የሚሰሩዋቸውን
ሐጢያቶች ብቻ ሳይሆን ዓመቱን ሙሉ የሰሩዋቸውን ሐጢያቶች በሙሉ
ለአንዴና ለመጨረሻ ወደ መስዋዕቱ እንስሳ በማስተላለፍ በእምነታቸው
አማካይነት የሐጢያቶቻቸውን ስርየት እንዲቀበሉ የፈቀደላቸውን የመስዋዕት
ስርዓት ሰጣቸው፡፡ እዚህ ላይ አሮን የሙሴ ወንድም ነበር፡፡ ሊቀ ካህንም ደግሞ
ነበር፡፡ አሮን ከሁለቱ ፍየሎች አንዱን ወደ አደባባዩ አምጥቶ እጆቹን በራሱ ላይ
በመጫን የእስራኤልን ሕዝብ ሐጢያቶች በሙሉ አስተላለፈበት፡፡ ሊቀ ካህኑ
በዚህ መንገድ የእስራኤሎችን ሐጢያቶች በአንድ ጊዜ ለመስዋዕት ወደቀረበው
ፍየል ካስተላለፈ በኋላ ፍየሉን ያርደውና ደሙን ከመጋረጃው በስተ ጀርባ
ማለትም ወደ ቅድስተ ቅዱሳን በመውሰድ በስርየት መክደኛው ላይና ወደ
ምሥራቅ ሰባት ጊዜ ይረጨዋል፡፡ ሊቀ ካህኑም ቢሆን እጆቹን በመስዋዕቱ ራስ
ላይ ጭኖ ስርየትን እስካላገኘና ደሙን ይዞ እስካልመጣ ድረስ ወደ መጋረጃው
ውስጥ ሊገባ አይችልም፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የመንፈሳውያን ለምጻሞች ፈውስ 257

የመገናኛው ድንኳን በቅድስትና በቅድስተ ቅዱሳን ተከፋፍሎዋል፡፡ ሊቀ


ካህኑ የእግዚአብሄር የምስክር ታቦት ወዳለበት ስፍራ መግባት የሚችለው
የእጆችን መጫን የተቀበለውን የመስዋዕት ደም ሲይዝ ብቻ ነበር፡፡ እግዚአብሄር
አሮንን ወደ ቅድሰተ ቅዱሳን እንዲገባ የሚፈቅድለት ይህንን የመስዋዕት ደም
ሲያይ ብቻ ነበር፡፡ ስለዚህ በእጆች መጫን የእስራኤልን ሕዝብ ሐጢያቶች
የተቀበለውን የመስዋዕት ፍየል በማረድ ደሙን ወደ ቅድስተ ቅዱሳን በመውሰድ
በምስክሩ ታቦት ላይ ሰባት ጊዜ ይረጨዋል፡፡ በሊቀ ካህኑ የቀሚስ ዘርፍ ላይ
የወርቅ ሻኩራዎች ስለተንጠለጠሉ እርሱ ደሙን ሲረጭ ያቃጭላሉ፡፡
የእስራኤልም ሕዝብ ይህንን የደውሎቹን ቃጭል ሲሰሙ ሐጢያቶቻቸውን
የተቀበለው የመስዋዕቱ ደም እንስሳ በእርግጥም እየተረጨ መሆኑን ያረጋግጣሉ፡፡
ይህም በምዕመናኑ ልቦች ውስጥ የሐጢያትን ስርየት የሚያጸና ነው፡፡
‹‹መቅደሱንም፣ የመገናኛውንም ድንኳን፣ መሠውያውንም ማስተሰረይ
ከፈጸመ በኋላ ሕያውን ፍየል ያቀርባል፡፡ አሮንም ሁለቱን እጆቹን በሕያው ፍየል
ራስ ላይ ይጭናል፡፡ በላዩም የእስራኤልን ልጆች በደል ሁሉ፣ መተላለፋቸውንም
ሁሉ፣ ሐጢአታቸውንም ሁሉ ይናዘዛል፡፡ በፍየሉም ራሱ ላይ ያሸክመዋል፡፡
በተዘጋጀው ሰውም እጅ ወደ ምድረ በዳ ይሰድደዋል፡፡ ፍየሉም ሐጢአታቸውን
ሁሉ ወደ በረሃ ይሸከማል፡፡ ፍየሉንም በምድረ በዳ ውስጥ ይለቅቀዋል፡፡››
(ዘሌዋውያን 16፡20-22)
‹‹ለያህዌህ›› የሆነው አንዱ ፍየል ስርየት የተደረገበት የሐጢያት መስዋዕት
ነበር፡፡ ነገር ግን የእሰራኤሎች ሐጢያቶች በተጨባጭ ከእነርሱ መወገድ
ነበረባቸው፡፡ ስለዚህ ሊቀ ካህኑ እጆቹን በሌላው ፍየል ራስ ላይ በመጫንና
የዓመቱን ሐጢያቶቻቸውን በመናዘዝ ‹‹የሚለቀቀው አዛዜል›› ወደ ምድረ በዳ
እንዲሰደድ ይፈቅዳል፡፡ (ዘሌዋውያን 16፡8-10ን በአሜሪካን ስታንዳርድ ቨርዥን
ተመልከቱት፡፡) እዚህ ላይ የሚለቀቀው ፍየል ‹አዛዜሉ› በዕብራይስጥ ሙሉ
በሙሉ ከሐጢያት ለመለየት ‹መላቀቅ› ማለት ነው፡፡
ሊቀ ካህኑ ከሁለቱ ፍየሎች አንዱን የሚለቀቅ ፍየል አድርጎ በመውሰድ
እጆቹን በራሱ ላይ ጭኖ ሁሉም ከመገናኛው ድንኳን አደባባይ ደጃፍ ላይ ቆመው
እያዩት የእስራኤልን ሕዝብ ሐጢያቶች በሙሉ በእርሱ ላይ በመናዘዝ
ሐጢያቶቻቸውን በሙሉ ወደ እርሱ ያስተላልፋል፡፡ ከዚያም ፍየሉ ይሞት ዘንድ
በተዘጋጀው ሰው እጅ ወደ ምድረ በዳ ይለቀቃል፡፡ በሌላ አነጋገር ይህ የመስዋዕት
ፍየል በሊቀ ካህኑ እጆችን መጫን የተቀበለውን የእስራኤሎች ሐጢያቶች በሙሉ
ተሸክሞ በእርግጠኝነት በምድረ በዳ መሞት ነበረበት፡፡ እግዚአብሄር

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


258 የመንፈሳውያን ለምጻሞች ፈውስ

የሚለቀቀውን ፍየል ወደ ምድረ በዳ በመስደድ የእስራኤልን ሕዝብ በሙሉ


ከሐጢያቶቻቸው ነጻ አውጥቶዋቸዋል፡፡ እግዚአብር ሙሴ እንዲያቀርብ ያዘዘው
መስዋዕት ይህ ነበር፡፡ እግዚአብሄር የእስራኤል ሕዝብ የሐጢያቶቻቸውን ስርየት
እንዲቀበሉ ያስቻላቸው በእጆች መጫንና በደም መፍሰስ ነበር፡፡
የብሉይ ኪዳን የመስዋዕት ስርዓት እግዚአብሄር ኢየሱስን እንደሚልክ
ኢየሱስም የእርሱ በግ ሆኖ በጥምቀቱ በዚህ ምድር ላይ የሚኖረውን
የእያንዳንዱን ሐጢያተኛ ሐጢያቶች በሙሉ እንደሚቀበልና እንደሚሸከም
በዚህም የሰውን ዘር የየቀንና የዕድሜ ዘመን ሐጢያቶች በሙሉ እንደሚያነጻ
ያስተማረ እውነት ነበር፡፡ የብሉይ ኪዳን ሕዝብ በሙሉ የሐጢያት ስርየትን
ያገኙት በመገናኛው ድንኳን የመስዋዕት ስርዓት አማካይነት እንደሆነ አምነዋል፡፡
የአዲስ ኪዳን ሕዝብም አውቀውም ሆነ ሳያውቁ የሰሩዋቸው ብዙ ሐጢያቶች
ስላሉ የእነዚህን ሐጢያቶች ችግር እንዴት መፍታት እንደሚችሉና ከእነዚህ
ሐጢያቶችም ሁሉ እንዴት እንደሚላቀቁ ማወቅ ያስፈልጋቸዋል፡፡

የአዲስ ኪዳን ትልቁ የስርየት መስዋዕት፡፡

የመጽሐፍ ቅዱስ ብሉይና አዲስ ኪዳናት እርስ በርሳቸው ይጣጣማሉ፡፡


(ኢሳይያስ 34፡16) ከብሉይ ኪዳኑ የስርየት ቀን ቁርባን ጋር የሚስማማው የአዲስ
ኪዳን ክፍል የትኛው ነው? ኢየሱስ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ለመደምሰስ
በትክክል ያደረገው የመጀመሪያው ነገር ምን እንደሆነ እንመርምር፡፡
‹‹ያን ጊዜ ኢየሱስ በዮሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ፡፡ ዮሐንስ
ግን፡- እኔ በአንተ ልጠመቅ ያስፈልገኛል አንተም ወደ እኔ ትመጣለህን? ብሎ
ይከለክለው ነበር፡፡ ኢየሱስም መልሶ፡- አሁንስ ፍቀድልኝ እንዲህ ጽድቅን ሁሉ
መፈጸም ይገባናልና አለው፡፡ ያን ጊዜ ፈቀደለት፡፡ ኢየሱስም ከተጠመቀ በኋላ
ወዲያው ከውሃ ወጣ፡፡ እነሆም ሰማያት ተከፈቱ፤ የእግዚአብሄርም መንፈስ እንደ
ርግብ ሲወርድ በእርሱም ላይ ሲመጣ አየ፡፡ እነሆም ድምጽ ከሰማያት መጥቶ፡-
በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው አለ፡፡›› (ማቴዎስ 3፡13-17)
እግዚአብሄር ኢየሱስን ‹‹ሕዝቡን ከሐጢአቶቻቸው የሚያድን›› (ማቴዎስ
1፡21) ሰው አድርጎ ላከው፡፡ በሌላ አነጋገር ዩኒቨርስን የፈጠረው አምላክ
የመስዋዕት በግ ሆኖ የሰውን ሥጋ በመልበስ በድንግል ማርያም በኩል ወደዚህ
ምድር መጣ፡፡ የኢየሱስ አገልግሎት በጥምቀቱ ጀመረ፡፡ ከላይ ያለው ምንባብ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የመንፈሳውያን ለምጻሞች ፈውስ 259

‹‹ያን ጊዜ›› ሲል ኢየሱስ 30 የሞላበትን ዓመት ማመልከቱ ነው፡፡ ይህ ኢየሱስ


በአጥማቂው ዮሐንስ የተጠመቀበት ዓመት ነበር፡፡
አጥማቂው ዮሐንስ ማን ነበር? ‹‹እውነት እላችኋለሁ፤ ከሴቶች ከተወለዱት
መካከል ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ አልተነሳም፡፡ በመንግሥተ ሰማያት ግን
ከሁሉ የሚያንሰው ይበልጠዋል፡፡ ከመጥምቁም ከዮሐንስ ዘመን ጀምሮ እስከ ዛሬ
ድረስ መንግሥተ ሰማያት ትገፋለች፤ ግፈኞችም ይናጠቋታል፡፡ ነቢያት ሁሉና
ሕጉ እስከ ዮሐንስ ድረስ ትንቢት ተናገሩ፡፡›› (ማቴዎስ 11፡11-13)
ከላይ ያለው ምንባብ እንደሚነግረን ኢየሱስ ‹‹ከሴቶች ከተወለዱት መካከል
ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ አልተነሳም›› ብሎ ተናግሮዋል፡፡ በዚህ ምድር ላይ
ከነቢያቶች ሁሉ ከኢሳይያስ፣ ከሕዝቅኤል፣ ከኤልያስና ከሙሴም ሳይቀር
የሚበልጠው ሰው ሌላ ሳይሆን የሰው ዘር ሁሉ ወኪል የሆነው አጥማቂው
ዮሐንስ ነው፡፡
በብሉይ ኪዳን ሊቀ ክህነቱ 30 ዓመት በሆነውና ከአሮን የወንድ ዘሮች
አንዱ በሆነው ሰው ይተካ ነበር፡፡ የአሮን ዘር የሆነው ሊቀ ካህን እጆቹን
ለመስዋዕት በቀረበው ፍየል ራስ ላይ በመጫን የእስራኤሎችን ሐጢያቶች በሙሉ
ወደ እንስሳው እንዳስተላለፈ ሁሉ ልክ እንደዚሁ እግዚአብሄር በዚህ ምድር ላይ
የሚኖረውን የእያንዳንዱን የሰው ዘር ሐጢያቶች በሙሉ ይደመስስ ዘንድ
ሐጢያቶቻቸውን ወደ ኢየሱስ እንዲያስተላልፍ አጥማቂው ዮሐንስ ተብሎ
የሚጠራውን የሰው ዘር ወኪል አስነሳ፡፡ በሌላ አነጋገር እግዚአብሄር አጥማቂውን
ዮሐንስን የመጨረሻ ነቢይ አድርጎ ወደዚህ ምድር ላከው፡፡ የመጨረሻው ሊቀ
ካህን ሌላ ሳይሆን የአሮን ዘር የሆነው አጥማቂው ዮሐንስ ነበር፡፡
‹‹በይሁዳ ንጉሥ በሔሮድስ ዘመን ከአብያ ክፍል የሆነ ዘካርያስ የሚባል
አንድ ካህን ነበረ፡፡ ሚስቱም ከአሮን ልጆች ነበረች፡፡ ስምዋም ኤልሳቤጥ ነበረ፤
ሁለቱም በጌታ ትዕዛዝና ሕግጋት ሁሉ ያለ ነቀፋ እየሄዱ በእግዚአብሄር ፊት
ጻድቃን ነበሩ፡፡…እርሱም የተዘጋጁትን ሕዝብ ለጌታ እንዲያሰናዳ የአባቶችን ልብ
ወደ ልጆች የማይታዘዙትንም ወደ ጻድቃን ጥበብ ይመልስ ዘንድ በኤልያስ
መንፈስና ሐይል በፊቱ ይሄዳል፡፡›› (ሉቃስ 1፡5-17)
እግዚአብሄር በብሉይ ኪዳን ውስጥ በስርየት ቀን የእስራኤልን ሕዝብ
ሐጢያቶች በሙሉ ያስተላለፈው የአሮን ልጆች በሆኑ ሊቀ ካህናት በኩል ብቻ
ነበር፡፡ ከላይ የተጠቀሰው ምንባብ እግዚአብሄር ቃል በገባው መሰረት በዚህ
ዓለም ላይ የሚኖረውን የእያንዳንዱን ሰው ሐጢያቶች በሙሉ ለማስተላለፍ
የይሁዳ ንጉሥ በነበረው በሔሮድስ ዘመን የአሮንን ዘር እንደመረጠ ያሳየናል፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


260 የመንፈሳውያን ለምጻሞች ፈውስ

ኢየሱስ ከመምጣቱ ከስድስት ወራት በፊት ብዙዎችን ወደ ጻድቃን ጥበብ


ለመመለስና ሕዝቡንም ለጌታ ለማሰናዳት አጥማቂውን ዮሐንስን ወደዚህ ዓለም
የላከው ለዚህ ነው፡፡ (ሉቃስ 1፡17) በሌላ አነጋገር አጥማቂው ዮሐንስ ከሴቶች
ከተወለዱት ሁሉ እጅግ የሚበልጥ ነበር፡፡
ስለዚህ እግዚአብሄር አጥማቂውን ዮሐንስን የሰው ዘር ወኪል አድርጎ
አስነሳው፡፡ የሰውን ዘር ሐጢያቶችም በእርሱ አማካይነት ወደ ኢየሱስ አሻገረ፡፡
አጥማቂው ዮሐንስ ከኢየሱስ በፊት የመጣው ለምስክርነትም ነበር፡፡ አጥማቂው
ዮሐንስ እንዴት እንደመሰከረም ከቃሉ መረዳት ያስፈልገናል፡፡ የእስራኤል ሕዝብ
ሐጢያቶቻቸው በሙሉ በእርግጥም የተላለፉ የመሆናቸውን ማስረጃ ማየት
የቻሉት አሮን ሐጢያቶቻቸውን ስላስተላለፈ ነበር፡፡ ልክ እንደዚሁ አጥማቂው
ዮሐንስ የሰውን ዘር ሐጢያቶች በሙሉ ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ የማስተላለፉ
እውነታ ሐጢያቶቻችን እንዴት እንደተደመሰሱ የሚያሳይ ዋና ማስረጃ ነው፡፡
ቀደም ተብሎ እንደተወሳውና በማቴዎስ 3፡13-17 ላይ እንደታየው ኢየሱስ
በአጥማቂው ዮሐንስ ተጠመቀ፡፡ ይህ ጥምቀት ለእያንዳንዱ ክርስቲያን በጣም
አስፈላጊ ነው፡፡ ክርስቲያኖች በጥቅሉ በውሃ ተጠምቀዋል፡፡ ሆኖም ብዙውን ጊዜ
የሚጠመቁት ፍቺውን ሳይገነዘቡ ነው፡፡ ስለዚህ ጥምቀት አስርቱን ትዕዛዛት
ለመጠበቅ፣ በየእሁዱ በሚደረጉ የቤተክርስቲያን አገልግሎቶች ላይ በታማኝነት
ለመሳተፍና ጌታን የግል አዳኝ አድርጎ ለማወቅ ቃል ለገባ ሁሉ ይሰጣል፡፡ በዚህ
ዓለም ላይ በክርስቲያኖችም መካከል እንኳን ሲጠመቅ የጥምቀትን ትርጉም
በትክክል ያወቀ ሰው ማግኘት በጣም አዳጋች ነው፡፡
ኢየሱስ ወደዚህ ምድር መጥቶ በአጥማቂው ዮሐንስ ተጠመቀ፡፡ እዚህ ላይ
መገንዘብ የሚያስፈልገን ነገር ቢኖር ኢየሱስ ለምን እንደተጠመቀ ነው፡፡ በኢየሱስ
አምናለሁ የሚል እያንዳንዱ ክርስቲያን ‹‹ኢየሱስ ሐጢያት አልባ ሆኖ ሳለ ለምን
መጠመቅ አስፈለገው?›› ብሎ መጠየቅ አለበት፡፡ ነገር ግን የሐጢያቶቻቸውን
ስርየት ያልተቀበሉ ሰዎች ምንም ያህለ ኢየሱስን በግለት ቢያምኑትም ስለዚህ
ጥያቄ የሚያውቁት ምንም ነገር የለም፡፡ ለዚህ ጥያቄ ትክክለኛውን መልስ
መስጠት የሚችሉት የሐጢያቶቻቸውን ስርየት የተቀበሉ ብቻ ናቸው፡፡
ኢየሱስ ሰማያዊ ሊቀ ካህን ሲሆን አጥማቂው ዮሐንስ ግን የሰው ዘር ወኪል
ምድራዊ ሊቀ ካህን ነው፡፡ አጥማቂው ዮሐንስ የሰውን ዘር ሐጢያቶች በሙሉ
ወደ በጉ ኢየሱስ የማስተላለፍ ሥልጣን ነበረው፡፡ የእግዚአብሄር መንግሥት ሊቀ
ካህን የሆነው ኢየሱስም የእንስሳን ደም መባ አድርጎ በማቅረብ ሳይሆን የገዛ
ሥጋውን መስዋዕት በማድረግ ማለትም የሰውን ዘር ሐጢያቶች በሙሉ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የመንፈሳውያን ለምጻሞች ፈውስ 261

የመደምሰስ ሚና ተሰጥቶት ነበር፡፡ የመንግሥተ ሰማይ ሊቀ ካህን ኢየሱስ ነው፡፡


(ዕብራውያን 5፡10፤ 6፡20፤ 10፡9-14)
ኢየሱስ በማቴዎስ 3፡15 ላይ እንዲህ ብሎዋል፡- ‹‹አሁንስ ፍቀድልኝ እንዲህ
ጽድቅን ሁሉ መፈጸም ይገባናልና፡፡›› እርሱ የሞት ወንዝ በሆነው በዮርዳኖስ
ወንዝ ተጠመቀ፡፡ ማጥመቅ በግሪክ ‹‹ባፕቲዞ›› ማለት ማጥለም፣ ከውሃ በታች
ማስረግ፣ ማጥለቅ ወይም በማስረግ፣ ማንጻት ወይም ቆሻሻን በማስተላለፍ ንጹህ
ማድረግ ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ጥምቀት ከብሉይ ኪዳኑ ‹‹እጆችን መጫን›› ጋር
ተመሳሳይ ትርጉም አለው፡፡ ሐጢያቶች በእጆች መጫን እንደተላለፉ ሁሉ የሰው
ዘር ሐጢያቶቻችንም በሙሉ አጥማቂው ዮሐንስ ኢየሱስን ባጠመቀው ጊዜ ወደ
እርሱ ተላልፈዋል፡፡ ኢየሱስ የእኛ የመስዋዕት ቁርባን ሆኖ በምትካችን በይፋ
የተኮነነውና የተቀበረው የሰው ዘር ሐጢያቶች በሙሉ ወደ እርሱ ስለተላለፉ
ነበር፡፡ ስለዚህ ኢየሱስ የሰውን ዘር ሐጢያቶች በሙሉ ከአጥማቂው ዮሐንስ
የተቀበለበት ክስተት ጥምቀቱ እንጂ ሌላ አልነበረም፡፡
ኢየሱስ ወደዚህ ዓለም መጥቶ የተጠመቀው የእግዚአብሄርን ጽድቅ ሁሉ
ለእያንዳንዳችን ለመፈጸምና የእያንዳንዱን ሰው ሐጢያቶች በሙሉ ፈጽሞ
ለመደምሰስ ነበር፡፡ ኢየሱስ የተጠመቀው ትሁት ስለነበረ ነው ብላችሁ
ታስባላችሁን? ነገሩ ፈጽሞ ያ አይደለም! ኢየሱስ አጥማቂውን ዮሐንስን
በአክብሮት እንዲህ አለው፡- ‹‹አሁንስ ፍቀድልኝ፡፡›› ኢየሱስ ይህንን በተናገረ ጊዜ
‹‹የሰውን ዘር ሐጢያቶች ወደ እኔ ታስተላልፋለህ፡፡ እኔም እሸከማቸዋለሁ፡፡ እኔም
በዓይኖችህ ፊት የአንተ የሚለቀቅ ፍየል በመሆን የሰውን ዘር ሐጢያቶች በሙሉ
አስቀራለሁ›› ማለቱ ነበር፡፡ ኢየሱስ ወደዚህ ዓለም የመጣው የሰውን ዘር
ሐጢያቶች በሙሉ ለመውሰድ ነውና፡፡
ሰዎች በሐጢያቶቻቸው ምክንያት ለሲዖል ታጭተዋል፡፡ በሐጢያቶቻቸው
ምክንያት በጭንቀት እየተንገበገቡ ነው፡፡ በሐጢያቶቻቸው ምክንያት በሰይጣን
ተታልለዋል፡፡ እንደ እኛ ያሉ ሰዎችን ከሐጢያቶቻችን ለማዳን፣ ጻድቃን
ለማድረግና የእግዚአብሄር ልጆች ወደ መሆን ለመመለስ ወደዚህ ምድር የመጣው
ኢየሱስ ነው፡፡ ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ ተጠምቆ ከውሃው ሲወጣ መንፈስ
ቅዱስ በርግብ አምሳል ከሰማይ ወረደበት፡፡ የእግዚአብሄር ልጅ እንደሆነም
መሰከረ፡፡ ስለ እውነት የመሰከረው መንፈስ ቅዱስ ነበር፡፡ እግዚአብሄር አብ
ራሱም ልጁ ኢየሱስ በጥምቀቱ የሰውን ዘር ሐጢያቶች በሙሉ ለአንዴና
ለዘላለም እንደወሰደ መስክሮዋል፡፡
‹‹በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


262 የመንፈሳውያን ለምጻሞች ፈውስ

እግዚአብሄር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና፡፡››


(ዮሐንስ 3፡16) የጥምቀት ክስተት ዋናው ፋይዳ ሌላ ሳይሆን እግዚአብሄር
ኢየሱስን ወደዚህ ምድር መላኩ፣ የሰውን ዘር ሐጢያቶች በሙሉ ወደ ልጁ
ማስተላለፉና የዘላለምን ሕይወት ሊሰጠንና ሐጢያት አልባ ሊያደርገን ልጁን
መስዋዕት ማድረጉ ነው፡፡ ኢየሱስ በጥምቀቱ አማካይነት የሰው ዘር ወኪልና
የመጨረሻ ሊቀ ካህን ከሆነው ከአጥማቂው ዮሐንስ ተቀብሎ ውሃ ውስጥ
ጠለመ፡፡ (ሞቱን ያሳያል፡፡) ከዚያም ከውሃው ውስጥ ወጣ፡፡ (ትንሳኤውን
የሳያል፡፡) አጥማቂው ዮሐንስ የእጆች መጫን ገጽታ በሆነው በዚህ ጥምቀት
አማካይነት ሐጢያቶቻችንን ወደ ኢየሱስ አስተላለፈ፡፡ በሌላ አነጋገር የዓለም
ሐጢያቶች በእርግጠኝነት ከሰው ዘር ተወስደው ወደ ራሱ ወደ እግዚአብሄር
ተላልፈዋል፡፡
እግዚአብሄር አሁን ያለ ሐጢያት እንደሆንን የተናገረው የሰው ዘር
ሐጢያቶች በትክክል ወደ ኢየሱስ ስለተላለፉ ነበር፡፡ ኢየሱስ ወደዚህ ምድር
በመጣ ጊዜ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ባይወስድ ኖሮ ምንም ያህል በእርሱ ብናምን
ሐጢያተኞች ሆነን ከመቅረት በቀር ምርጫ አይኖረንም ነበር፡፡ እግዚአብሄር
በጥምቀቱና በባፈሰሰው ደሙ አማካይነት ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ከደመሰሰ
በኋላ ‹‹በጌታ በኢየሱስ እመን አንተና ቤትህም ትድናላችሁ›› (የሐዋርያት ሥራ
16፡31) በማለት ይመክረናል፡፡ እኛ በኢየሱስ ጥምቀትና ደም በማመን ለአንዴና
ለዘላለም ከሐጢያቶቻችን ሁሉ መንጻት አለብን፡፡
‹‹በነገውም ዮሐንስ ኢየሱስን ወደ እር ሲመጣ አይቶ እንዲህ አለ፡- እነሆ
የዓለምን ሐጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሄር በግ፡፡›› (ዮሐንስ 1፡29)
አጥማቂው ዮሐንስ የሰው ዘር ሐጢያቶች በሙሉ በጥምቀቱ አማካይነት ወደ
ኢየሱስ እንደተላለፉ ለሕዝቡ መጮሁን ቀጠለ፡፡ ‹‹እርሱ የእግዚአብሄር ልጅ
ነው፡፡ የዓለምን ሐጢያቶች የሚያስወግድ የእግዚአብሄር በግ ነው›› ብሎ
የጮኸው ይህ አጥማቂው ዮሐንስ እንጂ ሌላ ማንም አይደለም፡፡
ኢየሱስ በጥምቀቱ የዓለምን ሐጢያቶች ወስዶ በመስቀል ላይ
ተሸከማቸው፡፡ ኢየሱስ የዓለምን ሐጢያቶች ከወሰደ 1,975 ዓመታት አልፈዋል፡፡
የሰውን ዘር ሐጢያቶች የወሰደው ኢየሱስ ሕይወቱን በመስቀል ላይ መስጠት
ነበረበት፡፡ ኢየሱስ የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ ወሰደ፡፡ ኢየሱስ በጥምቀቱ
አማካይነት የአባቶችንና የእናቶችንም ሐጢያቶች ደግሞ ወስዶዋል፡፡ እነርሱም
ደግሞ የዓለም ሰዎች ናቸውና፡፡ ከውልደታችን እስከ ሞታችን ድረስ አውቀንም
ይሁን ሳናውቅ የምንሰራቸው ሐጢያቶች በሙሉ የዓለም ሐጢያቶች ናቸው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የመንፈሳውያን ለምጻሞች ፈውስ 263

እነዚህ ሐጢያቶችም በአጥማቂው ዮሐንስ እጆችን መጫን አማካይነት ወደ


ኢየሱስ ተላልፈዋል፡፡ በሌላ አነጋገር ኢየሱስ የወሰደው የጥቂት ልዩ ሰዎችን
ሐጢያቶች ብቻ አይደለም፡፡ እርሱ በጥምቀቱና ባፈሰሰው ደሙ አማካይነት
በዚህ ዓለም ላይ የሚኖር እያንዳንዱ ሰው በዕድሜ ዘመኑ ሁሉ እስከ ዕለተ ሞቱ
ድረስ የሚሰራቸውን ሐጢያቶች በሙሉ ወስዶ ሁሉንም አንጽቶዋቸዋል፡፡
ነገር ግን በዚህ እምነት የሐጢያቶቻቸውን ስርየት መቀበል የሚችሉት
ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ አማካይነት ሐጢያቶቻችንን ተቀብሎ ሁሉንም
እንዳስወገደ በሚናገረው የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል እውነት የሚያምኑ ብቻ
ናቸው፡፡ በእምነት ከሐጢያቶቻቸው ሁሉ መዳን የሚችሉት ብቸኛ ሰዎች እነዚህ
ናቸው፡፡ ነገር ግን ብዙ ሰዎች በዚህ የውሃና የመንፈስ ወንጌል ባለማመናቸው
አሁንም ድረስ በሐጢያቶቻቸው ታስረው መቅረታቸው የሚያሳዝን ነው፡፡
የእግዚአብሄር በር ቀድሞውኑም ከረጅም ጊዜ በፊት ተከፍቷል፡፡ ሰዎች ግን
አሁንም ድረስ የልቦቻቸው በር ገና ስላልተከፈቱና በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
ቃል ስላላመኑ አሁንም ድረስ ለጥፋት ታጭተዋል፡፡
ከውልደታችን እስከ 20 ዓመታችን ድረስ የሰራናቸው ሐጢያቶችና ከ21-30
ዓመታችን ድረስ የሰራናቸው ሐጢያቶችም እንደዚሁ ‹‹የዓለም ሐጢያቶች››
ናቸው፡፡ ስለዚህ እነዚህም ሐጢያቶች በሙሉ እንደዚሁ ወደ ኢየሱስ
ተላልፈዋል፡፡ እርሱ የእያንዳንዳችንን ሐጢያቶች የወሰደ የእግዚአብሄር ልጅ
ነው፡፡ ሰዎች ከ41-100 ዓመት ድረስ የሚሰሩዋቸው ሐጢያቶችም እንደዚሁ
የዓለም ሐጢያቶች አይደሉምን? ኢየሱስ በጥምቀቱ አማካይነት እነዚህንም
ሐጢያቶች በሙሉ ወስዶዋል፡፡ የኢየሱስ ፍቅር ዘላለማዊና ወሰን የለሽ ስለሆነ
ሐጢያቶቻችንን የአዳምና የግለሰብ ሐጢያቶች ብሎ አልከፋፈላቸውም፡፡ ነገር
ግን ሐጢያቶቻችንን የአዳምና የግለሰብ ሐጢያቶች ብሎ በጥምቀቱ አማካይነት
ተቀብሎ እስከ ሞት ድረስ ደሙን በመስቀል ላይ አፈሰሰ፡፡
ኢየሱስ ወደዚህ ምድር ባይመጣ፣ ባይጠመቅና ደሙን ባያፈስስ ኖሮ
የሐጢያት ስርየት እምነታችንን በሙሉ መና ይቀር ነበር፡፡ የኢየሱስ ክርስቶስም
ሞት እንደዚሁ መና ይቀር ነበር፡፡ እኛም በጌታ ማመናችንና ለእርሱም መከራ
መቀበላችን ፈጽሞ ከንቱ ይሆን ነበር፡፡
የልጆቻችሁ ሐጢያቶች በጥምቀቱ አማካይነት ወደ ኢየሱስ ተላልፈዋልን?
ይህንን እናረጋግጥ፡፡ ልጆቻችሁ የሚኖሩት በዚህ ዓለም ላይ ከሆነ ሐጢያቶቻችሁ
ወደ ኢየሱስ እንደተላለፉ በጣም ግልጽ ነው፡፡ ለዚህ ማረጋገጫው ኢየሱስ
ከአጥማቂው ዮሐንስ የተቀበለው ጥምቀት ነው፡፡ የሐጢያቶቻቸው ኩነኔም

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


264 የመንፈሳውያን ለምጻሞች ፈውስ

ኢየሱስ በመስቀል ላይ ያፈሰሰው ደሙ ነው፡፡ (ዮሐንስ 19፡30-34) የልጅ


ልጆቻችሁ ሐጢያቶችና ገና ያልተወለዱት የዘሮቻቸው ሐጢያቶች በሙሉ
በጥምቀቱ አማካይነት ወደ ኢየሱስ ተላልፈዋል፡፡ ይህ ኢየሱስም ሐጢያቶቻችንን
በሙሉ ተሸክሞ በመስቀል ላይ ሁሉንም አሰወግዶዋቸዋል፡፡ በድክመቶቻችን
ምክንያት በየቀኑ ሐጢያቶችን ብንሰራም እነዚህ ሐጢያቶችም የዓለም ሐጢያቶች
ናቸው፡፡ ስለዚህ ኢየሱስ በጥምቀቱና በደሙ አማካይነት አስወግዶዋቸዋል፡፡
ዮሐንስ 8፡31-32 እንዲህ ይላል፡- ‹‹በቃሌ በትኖሩ በእውነት ደቀ
መዛሙርቴ ናችሁ፡፡ እውነትንም ታውቃላችሁ እውነትም አርነት
ያወጣችኋለሁ፡፡›› እዚህ ላይ እውነቱ ሌላ ሳይሆን ኢየሱስ በቃሉ የፈጸመው
የጽድቅ ምግባር ነው፡፡ ብዙ ክርስቲያኖች የሐጢያቶቻቸውን ይቅርታ ለማግኘት
ሰንበትን መጠበቅና የንስሐ ጸሎቶቻቸውን መጸለይ እንደሚገባቸው የሚናገሩትን
የሐሰት ወይም የሐይማኖት ትምህርቶች አሁንም ድረስ ማመናቸው ክፉኛ
የሚረብሽ ነው፡፡ እነርሱ ኢየሱስ የአዳምን ሐጢያት እንደወሰደ የእነርሱን የግል
ሐጢያቶች ግን እንዳልወሰደ ያምናሉ፡፡ ጊዜ እየነጎደ ሲሄድ ይበልጥ በሐጢያት
የተሞሉ ሐጢያተኞች ከመሆን በቀር ሌላ ምርጫ የሌላቸው ለዚህ ነው፡፡
ጥረቶቻቸው የሚደነቁ ይመስሉ ይሆናል፡፡ ደህንነታቸውን በተመለከተ ግን
መሰጠታቸው ማረፍ የሚገባው በእርግጥም እዚህ ላይ አይደለም፡፡
እኛ ማድረግ የሚገባን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን
የሐጢያቶቻችንን ስርየት መቀበል ነው፡፡ ለእኛ የእግዚአብሄር ፈቃድ ይህ ነው፡፡
ሕጉን ለመጠበቅ አብዝተን በሞከርን ቁጥር ያንን ማድረግ ይበልጥ አስቸጋሪ ነው፡፡
በመጨረሻ በእግዚአብሄር ፊት ይበልጥ ሐጢያተኛ እየሆንን መሆናችንን
እንገነዘባለን፡፡ ነገር ግን ጌታ በሰጠን የውሃና የመንፈስ ወንጌል ቃል በማመን
ሁላችንም በእርግጠኝነት ከዓለም ሐጢያቶች ሁሉ መዳን እንችላለን፡፡ ሐሌሉያ! 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


‹‹ቃል ብቻ ተናገር››
‹‹ማቴዎስ 8፡5-10››
‹‹ወደ ቅፍርናሆም በገባ ጊዜ የመቶ አለቃ ወደ እርሱ ቀርቦ፡- ጌታ ሆይ
ብላቴናዬ ሽባ ሆኖ እጅግ እየተሰቃየ በቤት ተኝቶአል ብሎ ለመነው፡፡
ኢየሱስም፡- እኔ መጥቼ እፈውሰዋለሁ አለው፡፡ የመቶ አለቃውም መልሶ፡- ጌታ
ሆይ በቤቴ ጣርያ ከታች ልትገባ አይገባኝም፤ ነገር ግን ቃል ብቻ ተናገር
ብላቴናዬም ይፈወሳል፤ እኔ ደግሞ ለሌሎች ተገዥ ነኝና፤ ከእኔም በታች ጭፍራ
አለኝ፡፡ አንዱንም ሂድ ብለው ይሄዳል፤ ሌላውንም ና ብለው ይመጣል፤
ባሪያዬንም ይህን አድርግ ብለው ያደርጋል አለው፡፡ ኢየሱስም ሰምቶ ተደነቀና
ለተከተሉት እንዲህ አለ፡- እውነት እላችኋለሁ፤ በእስራኤል ስንኳ እንዲህ ያለ
ትልቅ እምነት አላገኘሁም፡፡››

በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምኑ ምዕመናኖች በሚሰበሰቡበት ጊዜ


ሁሉ እያንዳንዱ ቀን ለእኛ በዓል ነው፡፡ እግዚአብሄር እንዴት ሐጢያቶቻችንን
እንደደመሰሰልን ስናስብና ደግመንም የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ስናሰላስል
ሁላችንም በደስታ እንስቃለን፡፡
በዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ላ ያለው የመቶ አለቃ ‹‹ቃል ብቻ
ተናገር ባርያዬም ይፈወሳል›› በማለት በኢየሱስ ላይ ያለውን ጠንካራ እምነነት
እንደመሰከረ ሁሉ በእግዚአብሄር ቃል ብቻ አምነው ጌታን የተከተሉ ሰዎች
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አሉ፡፡ በእግዚአብሄር ቃል ላይ እውነተኛ እምነት
ያላቸው ሰዎች ብሩካን ናቸው፡፡ የዚህ የመቶ አለቃው እምነትም በእኛ ዘመን
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ከሚያምኑት ሰዎች ጋር ተመሳሳይ የሆነ እምነት
ነው፡፡
የመቶ አለቃው ከባርያዎቹ ውስጥ ታሞ ለነበረው ለአንዱ ስላዘነ ኢየሱስን
ፈልጎ በማግኘት ባርያውን እንዲፈውስለት ጠየቀው፡፡ ኢየሱስም ለጥያቄው
መልስን ሰጠው፡፡ ይህንን ምንባብ ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስንመረምረው የመቶ
አለቃው አመለካከት ኢየሱስን የእግዚአብሄር ልጅና ራሱም አምላክ እንደሆነ
አድርጎ ያመነ አመለካከት እንደነበረ እናስተውላለን፡፡ እርሱ ሙታንን ሕያው

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


266 ‹‹ቃል ብቻ ተናገር››

ያደረገና ዩኒቨርስንም በቃሉ የፈጠረ አምላክ መሆኑን እንዳመነ ማየት እንችላለን፡፡


እዚህ ላይ የመቶ አለቃውን እምነት ትልቅነት መመስከር እንችላለን፡፡
የመቶ አለቃው ኢየሱስን እንዲህ አለው፡- ‹‹ጌታ ሆይ በቤቴ ጣርያ ከታች
ልትገባ አይገባኝም፤ ነገር ግን ቃል ብቻ ተናገር ብላቴናዬም ይፈወሳል፡፡›› ለምን
እንዲህ አለ? የመቶ አለቃው ይህንን ያለው ኢየሱስ ወደ ቤቱ መግባቱ አስፈርቶት
ሳይሆን በእግዚአብሄር ታላቅነት በቅድስናውና በሁሉን ቻይነቱ ስላመነ ነው፡፡
ሰው ሁሉ እግዚአብሄርን ለማክበርና ለማወደስ የተዘጋጀ የዚህ ዓይነት አመለካከት
ያለው ቢሆን ኖሮ የመቶ አለቃው እምነት ይህ ነበር፡፡ የመቶ አለቃው ያገኛቸውን
እነዚያኑ በረከቶች ማግኘት ይችል ነበር፡፡ እግዚአብሄር የሰጣቸው እነዚህ
ባርኮቶች ምንድናቸው? እነርሱ በዚህ ምድር ላይ የእግዚአብሄርን የጽድቅ ሥራ
ለመስራት የምንኖርበት የሐጢያት ስርየትና የእምነት በረከቶች ናቸው፡፡ እነዚህ
ሁሉ የሚገኙት በቃሉ ላይ ባለን እምነት ካለን በዚህ የመቶ አለቃ ላይ እምነት ላይ
እንደሆነው ሁሉ የእምነት በረከቶች ተትረፍርፈው ይመጡልናል፡፡
ስለዚህ የመቶ አለቃ የሚናገረው ምንባብ በእግዚአብሄር ቃል ማመን
በእግዚአብሄር ፊት ተአማኒ የሆነ እምነት እንደሆነና እግዚአብሄርም በዚህ
እምነት የሚደሰት መሆኑን ለሁላችንም ይነግረናል፡፡ ይህ እምነት የሚመጣው
በቃሉ ብቻ ሁሉን ማድረግና ሁሉን መፈጸም በሚችለው አምላክ ስናምን ነው፡፡
በሌላ አነጋገር የመላው እምነታችን መሰረቱ የእግዚአብሄር ቃል ብናውቅና በዚህ
ቃል እምነት ቢኖረን ሁላችንም የመቶ አለቃው የተቀበላቸውን አስገራሚ
ባርኮቶች በሕይወታችን እንቀበላለን፡፡
የመቶ አለቃው የዚህ ዓይነት እምነት መያዙ በራሱ ትልቅ በረከት ነበር፡፡
እግዚአብሄርን የሚያከብሩ ሰዎችም የቃሉን ሐይል ያውቃሉ፡፡ በዚህ
የእግዚአብሄር ቃል በማመንም ከሐጢያቶቻቸው ሁሉ ድነው የዘላለም ሕይወትን
መቀበል ይችላሉ፡፡ ከዓለም ሐጢያቶች የዳንነው የሐጢያቶቻችንን ስርየትና
የዘላለም ሕይወት የተቀበልነውና የእግዚአብሄርንም ጽድቅ በእምነት
የምንከተለው በቃሉ ነው፡፡ ይህ በእግዚአብሄር ቃል ላይ ያለው እምነት ያለ
ምንም ችግር ድንቅና ብሩክ ሕይወትን ያመጣል፡፡
ጌታችን እንዲህ ብሎዋል፡- ‹‹እውነትንም ታውቃላችሁ፤ እውነትም አርነት
ያወጣችኋል፡፡›› (ዮሐንስ 8፡32) መላውን የእግዚአብሄር ቃል በጥልቀት
አናውቀው ይሆናል፡፡ ነገር ግን በዚህ በተጻፈው ቃል የምናምን ከሆንን ያን ጊዜ
ቃሉ በልቦቻችን ውስጥ በተጨባጭና በአስተማማኝ ሁኔታ በመስራት
አእምሮዋችንንና ነፍሳችንን ይለውጣል፡፡ በአንድ ወቅት ለሲዖል የታጩ ነፍሳቶች

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


‹‹ቃል ብቻ ተናገር›› 267

አሁን ሰማይ እንዲደርሱና እንዲገቡ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል እንድናውቅ


ይመራናል፡፡
በእግዚአብሄር ቃል የሚያምን ይህ እምነት ከሌለን ኢየሱስን አዳኛችን
አድርገን ማመኑ ፈጽሞ ከንቱነት ነው፡፡ ይህ ዓይነቱ እምነት በራስ አስተሳሰብ ላይ
ተመስርቶ በኢየሱስ ከማመን የዘለለ አይደለም፡፡ ይህ ሰው በራሱ ስምምነት
የሚተገብረውን ራስ አገዝ ሐይማኖት የሚያዋቅር ነገር ብቻ ነው፡፡ ነገር የመቶ
አለቃው እምነት ከዚህ ዓይነቱ እምነት የሚቃረን በእግዚአብሄር ቃል ያመነ
እምነት ነው፡፡
የመቶ አለቃው እምነት የአብርሃም ዓይነት እምነት ነበር፡፡ የእምነት
አባቶቻችን በሙሉ እግዚአብሄር በተናገረው ቃል አምነዋል፡፡ አብርሃም
የእግዚአብሄርን ቃል ተከተለ፡፡ ይስሐቅም አባቱ የነበረው ያው ዓይነት እምነት
ነበረው፡፡ አብርሃም እግዚአብሄር የከንዓንን ምድር ለዘሮቹ እንደሚሰጥ
የተናገረውን የተስፋ ቃል እንዳለ አመነ፡፡ ይህንኑ የተስፋ ቃልም ለልጁ ለይስሐቅ
አስተላለፈ፡፡ እግዚአብሄርም የዛሬዋን እስራኤል የሚያዋቅረውን ምድር ለዘሮቹ
ሊሰጥ ፈቀደ፡፡ አብርሃም እግዚአብሄር የተናገረውን ቃል በማመን የእምነት አባት
ሆነ፡፡
እግዚአብሄር ለእኛ ያደረገው እጅግ አስገራሚው ሥራ በቃሉ አማካይነት
ሐጢያተኞችን ጻድቃን ማድረጉ ነው፡፡ ታዲያ ሐጢያተኞችን ጻድቃን ያደረገው
የትኛው የእግዚአብሄር ቃል ነው? ሰዎች ወደ ቤተክርስቲያን በመሄድ የጋለ ጸሎት
በማድረግ፣ በልሳን በመናገር ወይም ሕመሞችን በሚፈውስ ተዓምራዊ ሐይል
በማመን ብቻ የእምነትን ሐይል ሊቀበሉና ጻድቃን ሊሆኑ ይችላሉን? ሰዎች
ኢየሱስን አዳኛቸው አድርገው እንደሚያምኑት ሲናገሩ ይህ እርሱን ከመቀበል ጋር
ተመሳሳይ ነውን? ሰዎች በራሳቸው ስሜቶች፣ በራሳቸው መሰጠት ወይም
በራሳቸው አስተሳሰቦች ላይ ተመስርተው በእግዚአብሄር ቃል ሊያምኑ
አይችሉም፡፡
ሰው በእግዚአብሄር ቃል ላይ እምነት የሚኖረው የእግዚአብሄር ልጅ
የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ ሐጢያተኞችን ለማዳን እንደመጣ፣ በአጥማቂው
ዮሐንስ እንደተጠመቀና ደሙን እንዳፈሰሰ፣ በዚህም ከሐጢያቶቻቸው ሁሉ
እንዳዳናቸው በሚናገረው የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል በማመን ብቻ ነው፡፡ ይህ
ሆኖ ሳለ በጸሎቶቻቸውና ዕንባዎቻቸውን እያፈሰሱ ከልባቸው ንስሐ በመግባት
ለእርሱ በሚያቀርቡዋቸው ምልጃዎቻቸው የእግዚአብሄር ልጆች እንደሆኑ
የሚናገሩ በጣም ብዙ ሰዎች እናያለን፡፡ ብዙውን ጊዜ ለተወሰነ ጊዜ ወደ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


268 ‹‹ቃል ብቻ ተናገር››

ቤተክርስቲያን በሄዱ ክርስቲያኖች መካከል ወደ እግዚአብሄር በሚጸልዩበት ጊዜ


ዕንባዎቻቸውን የሚያፈስሱ ሰዎች በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ቃል ባያምኑም
እንኳን የእግዚአብሄር እውነተኛ ምዕመናኖች ሆነው ተቀባይነት ሲያገኙ
እናያለን፡፡ በዚህ ዘመን ክርስትና ምዕመናኖችን ሁሉ በትምህርቶቹ ለመጠበቅ
የሚፍጨረጨር ተራ የሆነ ብልሹ የዓለም ሐይማኖት ሆኖዋል፡፡

የዛሬው ክርስትና ትክክለኛ መልስ የሌለው የእምነት ዓይነት አለው፡፡

የዛሬው ክርስትና በተሳሳተ አቅጣጫ እየተጓዘ ነው፡፡ በአሁኑ ጊዜ ብዙ


ክርስቲያኖች የካራዝማቲክን እንቅስቃሴ፣ የረቂቅ ሐይማኖትና የቁሳዊነትን
የተሳሳተ እምነት እየተከተሉ መሆኑ አሳዛኝ እውነት ነው፡፡ እነዚህ ክርስቲያኖች
እንደዚህ ባሉ የሐይማኖት ማህበራቶች ውስጥ ሲገኙ ለአእምሮዋቸው አንዳች
መጽናናትና እርካታ ያገኙ ይሆናል፡፡ ነገር ግን ወደ ቤቶቻቸውና ወደ
ማህበረሰቦቻቸው ሲመለሱ ወደ ጥንቱና ወደማያምነው ማንነታቸው ከመመለስና
ባዶና ግራ የተጋባ ሕይወታቸውን በመኖር ከመቀጠል ማምለጥ አይችሉም፡፡
ምክንያቱም መንፈስ ቅዱስና የእግዚአብሄር ቃል አሁንም በልቦቻቸው ውስጥ
የሉምና፡፡ በኢየሱስ እናምናለን ቢሉም እውነተኛውን የውሃና የመንፈስ ወንጌል
አያውቁትም፡፡ ስለዚህ የሐጢያቶቻቸውን ስርየት ወደ ልባቸው አልተቀበሉትም፡፤
ከዚህ የተነሳ መንፈስ ቅዱስን አልተቀበሉም፡፡ በእግዚአብሄር ቃል አያምኑም፡፡
አሮጌውን ማንነታቸውን ማሸነፍ የማይችሉት ለዚህ ነው፡፡
በእግዚአብሄር ማመን ማለት በቃሉ ማመን ማለት ነው፡፡ ኢየሱስ
በእግዚአብሄር ቃል ያመነው የመቶ አለቃው እምነት ትልቅ እንደነበረ
ተናግሮዋል፡፡ በእግዚአብሄር ቃል የማያምኑ ሰዎች በእግዚአብሄር ቃል
የሚያምኑትንና የሚከተሉትን ሰዎች እምነት መረዳት አይችሉም፡፡ የካራዝማቲክን
እንቅስቃሴ የሚከተሉ ሰዎች ‹‹አንድ ሰው መንፈስ ቅዱስን መቀበሉን የሚያሳየው
ማስረጃ ምንድነው? የእግዚአብሄር ልጆች መሆን ማለት ምን ማለት ነው?
የደህንነት ማረጋገጫው ምንድነው? ዳግመኛ የመወለጃውና መንፈስ ቅዱስን
የመቀበያው ማስረጃ ሌላ ሳይሆን በሰማይ ልሳን መናገር ነው›› በማለት በልሳን
የማይናገሩ ሰዎች መንፈስ ቅዱስን እንዳልተቀበሉ ይናገራሉ፡፡ ይህ ግን በጭራሽ
እውነት አይደለም፡፡
እነዚህ ሰዎች በሚጸልዩበት ጊዜ ሁሉ ትልቅ ግርግር ይፈጥራሉ፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


‹‹ቃል ብቻ ተናገር›› 269

በስታትስቲክ አነጋገር ግን ከእነዚህ ሰዎች 99 ከመቶ የሚሆኑት የሚናገሩት


አይረቤ ነገር ነው፡፡ በሌላ አነጋገር እንግዳ የሆኑት ባህሪዎቻቸው በእርግጥም
ከሰይጣን እንጂ ከእግዚአብሄር አይደሉም፡፡ ይህንን ይበልጥ አስቸጋሪና አሳዛኝ
የሚያደርገው እነዚህ ሰዎች መንፈስ ቅዱስን ለመቀበላቸው እርግጠኞች
መሆናቸውና እንዲህ ያለውን ሰይጣናዊ ግራ መጋባትም በመንፈስ ቅዱስ ስም
ማስፋፋታቸው ነው፡፡
አንድ ሰው የዚህ የሐጢያት ስርየት ማስረጃ የሆነውን መንፈስ ቅዱስ
የሚቀበለው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን የሐጢያት ስርየትን በመቀበል
ነው፡፡ በልሳን መናገር መንፈስ ቅዱስን የተቀበለ ሰው ሁሉ ሊገልጠው የሚችለው
መሰረታዊ ስጦታ አይደለም፡፡ ይህ በተለያዩ ክልላዊ ቋንቋዎች ከመናገር የዘለለ
አይደለም፡፡ (የሐዋርያት ሥራ 2፡8) በሐዋርያት ዘመን የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት
ወንጌልን ለመመስከርና (የሐዋርያት ሥራ 2፡11) ከእግዚአብሄር ጋር በጣም
የቀረበና የግል ሕብረት ይኖራቸው ዘንድ (1ኛ ቆሮንቶስ 14፡2) በልሳን
ተናግረዋል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ተሰብስቦ በተጠረዘበት በዚህ ዘመን ግን በእነዚህ
የተለያዩ ክልላዊ ቋንቋዎች የምንናገርበት ምንም የተለየ ፍላጎት የለንም፡፡ (1ኛ
ቆሮንቶስ 13፡8-10) ስለዚህ በልሳን የማይናገሩ ሰዎች እንኳን አሁን በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል በማመን የደህንነትን እውነት መናገር ችለዋል፡፡
የዘመኑ ክርስቲያኖች በልሳን መናገራቸው የሐጢያት ስርየት ተቀብለዋል
ማለት አይደለም፡፡ በልሳን መናገርና ራዕዮችን ማየት ዳግመኛ መወለድ ማለት
አይደለም፡፡ መንፈሳዊ የፈውስ ስጦታ መያዝ ማለትም በውሃውና በመንፈስ
ወንጌል እምነት አለው ማለት አይደለም፡፡ በአጭሩ እነዚህ ሰዎች እነዚህን የረቂቅ
ሐይማኖት ምልክቶች ደህንነታቸው አድርገው የያዙዋቸው እንዴት ዳግመኛ
መወለድ እንደሚችሉ ስለማያውቁ ነው፡፡
ሰይጣን ለሐጢያተኞች የሚሰጠው ይህንን ነው፡፡ የማይጨብጥ እምነት
ቢበዛ የሚቆየው ለጥቂት ዓመታቶች ብቻ ነው፡፡ እነርሱ አንድ ጊዜ ‹‹ሐይል››
ተብሎ የሚጠራውን ነገር ሲያውቁ ንደገና ሊያገኙት ማንኛውንም ጥረት
ያደርጋሉ፡፡ ስለዚህ የእጆቻቸውን መጫን ለማግኘት ‹‹የሐይል ሰዎች›› ተብለው
የሚጠሩትን ሰዎች በእግር በፈረስ ይፈልጋሉ፡፡ ነገር ግን እምነታቸው ከንቱ
ስለሆነ መጨረሻቸው የሰይጣን አገልጋዮች መሆን ነው፡፡ እነርሱ እነዚህን
ምልክቶችና ተዓምራቶች የመሻታቸው እውነታ በልባቸው ውስጥ በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል ቃል እምነት የሌላቸው ለመሆኑ ማስረጃ ነው፡፡
በራዕዮችና ከልዕለ ተፈጥሮ በላይ በሆኑ ሐይሎች በሚያምኑ ሰዎች

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


270 ‹‹ቃል ብቻ ተናገር››

እምነትና የእግዚአብሄርን ቃል በሚያምኑና በሚከተሉ ሰዎች እምነት መካከል


ትልቅ ልዩነት አለ፡፡ ተዓምራትን የሚሹ የዘመኑ ስሁት ክርስቲያኖች እምነት
ከመቶ አለቃው እምነት ጋር ሲነጻጸር የጫማው ሶል ላይ አይደርስም፡፡ የእነርሱ
እምነት የእግዚአብሄርን ቃል ካመነውና ከተከተለው የመቶ አለቃው እምነት
ፈጽሞ የተለየ ነው፡፡
የመቶ አለቃው እምነት ‹‹ቃል ብቻ ተናገር ባርያዬም ይፈወሳል›› ማለት
የቻለ እምነት ነው፡፡ በሌላ አነጋገር የእርሱ እምነት በእግዚአብሄር ቃል ያመነ
ማለትም ኢየሱስ ለእኛ የተናገረውን ያመነ እምነት ነበር፡፡ ይህም በእግዚአብሄር
ቃል ማመን እውነተኛ እምነት እንደሆነ ይጠቁማል፡፡ እርሱ ምንም ነገር ቢነግረን
ሁሉም ነገር በኢየሱስ ቃል መሰረት በትክክል ይፈጸማል ብሎ ማመን እውነተኛ
እምነት ነው፡፡ በሌላ አነጋገር ሙሉ በሙሉ በእግዚአብሄር ቃል የሚያምን
እምነት የመቶ አለቃው እምነት ነው፡፡
እኛ በእግዚአብሄር ቃል ላይ እምነት ያለንና በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
የሐጢያት ስርየትን የተቀበልን ሰዎች ምልክቶች ወደሚፈልግ ወደዚህ ዓይነት
እምነት አንወድቅም፡፡ ከሁሉም በላይ የዚህ ዓይነቱ እምነት ከእምነታችን ጋር
አይጣጣምም፡፡ ምክንያቱም ተዓምራቶችን ከሚሹ ሰዎች ፈጽሞ የተለየን ዘር
ነንና፡፡ ስለዚህ የእግዚአብሄርን ወንጌል ለማሰራጨት ከእነዚህ ሰዎች ጋር ልንሰራ
አንችልም፡፡ የመቶ አለቃው እምነት በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ከሚያምነው
ከእኛ እምነት ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡ በእግዚአብሄር ቃል የተመራውን
ሕይወታችንን ስኖር ከእኛ በፊት የነበሩት ነቢያቶች የኖሩትን ሕይወት
እንኖራለን፡፡ መንፈስ ቅዱስ በእነዚህ ነቢያቶች ሕይወት ውስጥ ሰርቷል፡፡ በእኛም
ሕይወት እንደዚሁ ይሰራል፡፡
ጌታ ምልከቶችንና ተዓምራቶችን ከሚከተሉ ሰዎች በተቃራኒው በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት እንዴት ያለ ታላቅ ጸጋ እንደሰጠንና እንዴት ቃሉን
እንድናምንና እንድንከተል እንዳስቻለን ሳስብ እግዚአብሄርን አመሰግናለሁ፡፡
እምነታችን እውነተኛ የሆነውና እኛም ጻድቃን የሆንነው የእግዚአብሄር ቃል
በሆነው የውሃውና የመንፈሱ በማመናችን ብቻ ነው፡፡ የራሱን አስተሳሰቦች ክዶ
ቃሉ ለእርሱ የሚነግረውን በትህትና የሚያደምጥና በእውነተኛው የእግዚአብሄር
ወንጌል ቃል የሚያምን ማንኛውም ሰው መንግሥተ ሰማይ ይገባል፡፡ ውብ፣
በሐሴት የተሞላና የተባረከ ሕይወት ይህ ነውና፡፡
እኛ እውነተኛ ምዕመናኖችም እንደዚሁ ጌታን ‹፣ቃል ብቻ ተናገር››
እንለዋለን፡፡ ጌታችን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ቃል ስለነገረን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


‹‹ቃል ብቻ ተናገር›› 271

የሐጢያቶቻችን ሁሉ ስርየት በእግዚአብሄር ቃል ተፈጽሞዋል፡፡ ምክንያቱም


የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ብቸኛው እውነት ይህ ነውና፡፡
ኢየሱስ በቃሉ ያመነውን የመቶ አለቃውን እምነት አይቶ ‹‹እውነት
እላችኋለሁ፤ በእሰራኤል እንኳ እንዲህ ያለ ትልቅ እምነት አላገኘሁም›› አለ፡፡
አንድ አካል ጉዳተኛ በራሱ ማድረግ የሚችለው አንዳች ነገር የለም፡፡ መንፈሳዊ
አካል ጉዳተኛም በራሱ ፈቃድ ወይም ጸሎቶች ሐጢያቶቹን ማስወገድ
አይችልም፡፡ እግዚአብሄር በእግዚአብሄር ቃል ብቻ ፍጹም የሆነውን የሐጢያት
ስርየት መቀበል ስለሚያስችለው እምነት የተናገረው ለዚህ ነው፡፡
እኛ በተጻፈው ቃል ውስጥ ያለውን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
በማመን የሐጢያት ስርየትን ስጦታ ተቀብለናል፡፡ የሰዎች ሐጢያቶች ሊነጹ
የሚችሉት የእግዚአብሄርን ቃል በማመን ብቻ ነው፡፡ መቶ አለቃው ‹‹ቃል ብቻ
ተናገር ባርያዬም ይፈወሳል›› ያለው በኢየሱስ ቃል ስላመነ ነው፡፡ ኢየሱስም
እምነቱን የተቀበለለት በዚህ ምክንያት ነው፡፡
የእኛ ጥረት ሐጢያቶቻችንን በሙሉ መደምሰስ አይችልም፡፡
ሐጢያቶቻችንን ማንጻት የምንችለው በእግዚአብሄር ቃል ውስጥ በተጻፈው በዚህ
የእግዚአብሄር ቃል በማመን ብቻ ነው፡፡ ሌላ ምንም ነገር ከሐጢያቶቻችን ሁሉ
ሊያድነን አይችልም፡፡ ከተጻፈው የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ቃል ውጭ
ከቶውኑም የሐጢያት ስርየት ማግኘትና ዳግመኛ መወለድ አንችልም፡፡ በሕልሞች
ወይም በራዕዮች የተገኘ ደህንነት በጭራሽ ደህንነት አይደለም፡፡
ሆኖም በኢየሱስ ካመኑ በኋላ ይበልጥ ሐጢያተኞች እየሆኑ ያሉ ብዙ
ክርስቲያኖች አሉ፡፡ በኢየሱስ የሚያምን አማኝ ጊዜ በነጎደ ቁጥር ይበልጥ
ሐጢያተኛ መሆኑ የተለመደ ነውን? መጽሐፍ ቅዱስ ጌታ በሥልጣኑ ቃል
ሐጢያቶቻችንን እንዳነጻ ይናገራል፡፡ (ዕብራውያን 1፡3) ታዲያ የሥልጣኑ ቃል
ምንድነው? የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል እንጂ ሌላ አይደለም፡፡ ስለዚህ
የሥልጣኑን ቃል ቸል የሚሉ ሰዎች ምንም ያህል ከልባቸው በኢየሱስ ቢያምኑም
ሐጢያተኛ ክርስቲያኖች ሆነው ከመቅረት በቀር ሊያደርጉት የሚችሉት ነገር
የለም፡፡ ኢየሱስ ለእኛ ያደረገው ሁሉ በእግዚአብሄር ቃል ውስጥ በስፋት
ስለተጻፈ ጻድቃን መሆን የምንችለው በዚህ የእግዚአብሄር ቃል በማመን ነው፡፡
ጻድቃን በእግዚአብሄር በረከቶች ውስጥ መኖር የሚችሉት በእግዚአብሄር ቃል
ላይ ባላቸው በዚህ እምነት ነው፡፡
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ውስጥ ባለው የሐጢያት ስርየት እውነት
የማያምኑ ሰዎች የሚለማመዱዋቸው ማናቸውምና ሁሉም ልምምዶች ውሸት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


272 ‹‹ቃል ብቻ ተናገር››

ናቸው፡፡ ኢየሱስ እውነተኛ ምዕመናን ለሆኑት መንገድ እውነትና ሕይወት ነው፡፡


ሰው በአምልኮ አገልግሎቶች ላይ ምንም ያህል ከልቡ የንስሐ ጸሎቶችን ቢያቀርብ
የሥልጣኑን ቃል ከተወ ሐጢያቶቹ ሊነጹ አይችሉም፡፡ ሰው የሐጢያቶቹን ስርየት
የሚቀበለወና ሰማይ የሚገባው በንስሐ ጸሎቶች አይደለም፡፡ የእኛ መሰጠት
ጥረቶችና ሥራዎች ከሐጢያቶቻችን አንዳቸውንም መደምሰስ አይችሉምና፡፡
በእግዚአብሄር ቃል ላይ ያልተመሰረተ ማንኛውም እምነት የሰይጣን ነው፡፡
በእግዚአብሄር ቃል የማታምን ነፍስ ምንም ያህል አጋንንቶችን የማባረር ሥልጣን
ቢኖራትም ወይም ሰማዕት ብትሆንም ከሐጢያቶቸዋ መዳን አትችልም፡፡
በራሳችን አስተሳሰቦች ላይ ተመስርተን በራሳችን የምንቀበለው የሐጢያት ስርየት
በሙሉ ለመለወጥ የታጨ ነው፡፡ ምክንያቱም በእውነተኛ እምነት ላይ የተመሰረተ
አይደለምና፡፡
መጽሐፍ ቅዱስም እንደዚሁ ዳግመኛ ከደም ወይም ከሥጋ ፈቃድ፣ ከወንድ
ፈቃድ መወለድ እንደማንችል ይናገራል፡፡ (ዮሐንስ 1፡13) አንዳንድ ሰዎች ‹‹እኔ
በኢየሱስ ያመንሁት ገና ከእናቴ ማህጸን ጀምሮ ነው›› በማለት በእምነታቸው
የበለፀገ ወግ ይመካሉ፡፡ ሌሎች ደግሞ ‹‹ቤተሰቤ ለ5 ትውልድ ያህል በኢየሱስ
አምኖዋል›› ይላሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች እንዲህ ባለ የታላቅነት ስሜት ዳግመኛ
መወለድ ይችላሉን? አይችሉም፡፡ እነዚህ ሰዎች የእግዚአብሄር ሕዝብ መሆን
አይችሉም፡፡
ጌታ የእነዚህን ሰዎች እምነት እንደሚፈትንና በዓመጸኝነታቸውም
እንደሚወረውራቸው ነግሮናል፡፡ በእግዚአብሄር ቃል መሰረት ቢያምኑ እዚህ ላይ
ኩራታቸው ችግር ባልኖረው ነበር፡፡ እግዚአብሄር ‹‹እናንተ ዓመጸኞች ከእኔ ራቁ››
(ማቴዎስ 7፡23) በማለት ወደ ጨለማ የሚጥላቸው በኢየሱስ የሚያምኑት
በእውነት ቃሉ መሰረት ሳይሆን በራሳቸው አስተሳሰቦች መሰረት ስለሆነ ነው፡፡
እዚህ ላይ ‹‹ዓመጸኝነት›› የሚያመለክተው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ሳያምኑ
ኢየሱስን አዳኛቸው አድርገው እንደሚያምኑና የእግዚአብሄርን ሐይል ሁሉ
እንደሚለማመዱ የሚናገሩ ሰዎች የሚያደርጉዋቸውን ዓመጸኛ ምግባሮች ነው፡፡
የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ከውሃና ከመንፈስ ወንጌል ዳግመኛ የተወለዱ
ሰዎች ስብስብ ናት፡፡ በሌላ አነጋገር የእግዚአበሄር ቅዱሳን ተብለው የሚጠሩ
ሐጢያት አልባ ሰዎች ስብስብ ናት፡፡ (1ኛ ቆሮንቶስ 1፡2) ሰዎች የራሳቸውን
አስተሳሰቦች እንዲተዉ በእግዚአብሄር ቃል እንዲያምኑና የሐጢያት ስርየትን
እንዲቀበሉ የሚያስችላቸው ስፍራ የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ነው፡፡ ወደ
ቤተክርስቲያን መሄድ ማለት መንግሥተ ሰማይ መግባት ማለት አይደለም፡፡ ነገር

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


‹‹ቃል ብቻ ተናገር›› 273

ግን አሁንም ድረሰ ሐጢያት ቢኖርባቸውም በኢየሱስ ስለሚያምኑና ‹‹ኦርቶዶክስ››


ተብሎ የሚጠራ ቤተክርስቲያን አባሎች ስለሆኑ ወደ እግዚአብሄር መንግሥት
እንደሚገቡ የሚናገሩ ሰዎች አሉ፡፡ እንደዚህ ተብለው በሚጠሩ የዚህ ዓለም
ኦርቶዶክስ የሐይማኖት ድርጅቶች የሚመኩ ሰዎች ራሳቸውን በድፍረት የዳኑ
ሐጢያተኞች አድርገው ገልጠዋል፡፡
ሁሉም ሰው የእርሱ የሐይማኖት ድርጅት ትክክለኛ እንደሆነ ይናገራል፡፡
ነገር ግን እግዚአብሄር በልቡ ውስጥ እውነተኛ እምነት ባይኖርም በእርሱ
አምናለሁ የሚለውን ማንኛውንም ሰው ሰማይ እንደሚወስድ ተናግሮዋልን? ይህ
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተጻፈበት ስፍራ የለም፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ
እንዲህ ያለ አሳብ ተጽፎ እንደሆነ ራሳችሁ ልትመለከቱ ትችላላችሁ፡፡ ይህ
የተጻፈበት ቦታ እንደሌለ ታረጋግጣላችሁ፡፡
በእግዚአብሄር ፊት ቅዱሳኖች የሚባሉት ሐጢያት የሌለባቸው ናቸው፡፡
ማለትም ጻድቃን የሆኑት ናቸው፡፡ ስለ እምነት ድርጅቶቻቸው ትከክለኛነት
የሚኩራሩ ሰዎች ‹‹እኛ ሐጢያተኞች ነን፤ ነገር ግን በኢየሱስ ስለምናምን
እግዚአብሄር ሐጢያት አልባ አድርጎ ያየናል፡፡ ይህ ማለት ግን የዳንነው ሐጢያት
አልባ ስለሆንን ነው ማለት አይደለም፡፡ በኢየሱስ ካመንን በኋላም ቢሆን አሁንም
ድረስ ሐጢያት ቢኖርብንም በኢየሱስ ያለን እምነት ምስጋና ይድረሰውና
የእግዚአብሄር ልጆች ተብለን ተጠርተናል፡፡ ስለዚህ ወደ መንግሥቱ እንገባለን››
ይላሉ፡፡
የዚህ ዓይነት እምነት ያላቸው ሰዎች የሚያምኑት በራሳቸው አስተሳሰቦች
ብቻ ነው፡፡ የያዙት ደህንነት በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን የተቀበሉት
ደህንነት አይደለም፡፡ ስለዚህ ለእግዚአብሄር የሚያደርጉት ነገር ቢኖር ብድር
የማይየመለስ ፍቅራቸውን መመስከር ብቻ ነው፡፡ እነዚህ ሰዎች ከሐጢያቶቻቸው
አልዳኑም፡፡ ያልዳኑ ሰዎች ልቦቻቸው አሁንም ድረስ ሐጢያቶች እንዳሉባቸው
ለራሳቸው ይመሰክራሉ፡፡ እነርሱ ሐጢያተኞች ለመሆናቸው ማስረጃው ይህ
ነው፡፡ ኢየሱስን አዳኛቸው አድርገው ቢያምኑትም በልባቸው ጽላት ላይ ሐጢያት
የተጻፈባቸው ማናቸውም ለሲዖል የታጩ ናቸው፡፡
ኢየሱስ የዚህን ዓለም ሐጢያቶች በሙሉ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
ከደመሰሰ በኋላ በዚህ እውነተኛ ወንጌል በማመን ጸድቅ በሆኑ ሰዎች ይደሰታል፡፡
እግዚአብሄር ሰማይን ለእነዚህ ጻድቃን ሰዎች ያዘጋጀው ለዚህ ነው፡፡ ነገር ግን
ጻድቃን ያልሆኑ ሐይማኖተኞች እግዚአብሄርን ማስደሰት አይችሉም፡፡ እንዲህ
በማለት ይናዘዛሉ፡- ‹‹ጌታ ሆይ ሐጢያቶቼን በሙሉ እንደወሰድህ አምናለሁ፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


274 ‹‹ቃል ብቻ ተናገር››

ነገር ግን እባክህ በየቀኑ የምሰራቸውን ሐጢያቶቼን አነጻልኝ፡፡ እባክህ እነዚህን


ሐጢያቶች ይቅር በል፡፡›› እምነታችሁ ይህንን የሚመስል ከሆነ የእግዚአብሄርን
የውሃና የመንፈስ ወንጌል የማታውቁና በእርሱም የማታምኑ ሰዎች ናችሁ፡፡
እግዚአብሄርን ውሸታም የማድረግ ሐጢያት እየፈጸማችሁ ያላችሁ ሰዎች ናችሁ፡፡

በመላው ዓለም የሚገኙ ክርስቲያኖች በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል


ፊት መንበርከክ አለባቸው፡፡

በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምኑ ምዕመናኖችን መናፍቆች አድርገው


የሚከሱዋቸው ሰዎች አሉ፡፡ በእርግጥም የሐጢያት አልባ ምዕመናን እምነት
ለተንሸዋረረው ዓይናቸው እንግዳ ይመስል ይሆናል፡፡ በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል የማያምኑ እነርሱ ስለሆኑ ልቦቻቸው አሁንም ድረስ ሐጢያተኞች
ናቸውና፡፡ በመጨረሻ የሚጠፉት መናፍቆች እነርሱ ናቸው፡፡ መናፍቃን
በእግዚአብሄር ፊት ራሳቸውን የኮነኑ ተንኮለኞችና ሐጢያት የሚያደርጉ ናቸው፡፡
(ቲቶ 3፡11) በእግዚአብሄር ፊት አሁንም ድረስ የሐጢያት ስርየታቸውን
ያልተቀበሉ ሰዎች የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ድንቁርና ባለ ዕዳዎች ስለሆኑ
አሁኑኑ ንስሐ ገብተው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ማመን አለባቸው፡፡ ፈጽሞ
አልረፈደም፡፡ እውነተኛ ንስሐ ማለት ከተሳሳተው መንገድ መመለስና በውሃውና
በመንፈስ ወንጌል እውነት ማመን ነው፡፡
በኢየሱስ እያመኑ ራሳቸውን የሚኮንኑ ሰዎች በጣም መናፍቃን ናቸው፡፡
በኢየሱስ ክርስቶስ ኩነኔ የለም፡፡ (ሮሜ 8፡1) በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
በማመን ይህንን እውነት በተገቢው መንገድ መረዳት አለብን፡፡ በእግዚአብሄር
ፊት ሐጢያት ያለባቸው ሰዎች ሌሎች ሐጢያት ያለባቸውን ነፍሳቶች ወደ
እግዚአብሄር ቃል መምራት አይችሉም፡፡ ሊያፈሩት የሚችሉት ነገር ቢኖር
በራሳቸው ሰው ሰራሽ አስተሳሰቦች መሰረት በከንቱ የሚያምኑ ሐጢያተኞችን
ነው፡፡
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን የሐጢያቶቻቸውን ስርየት የተቀበሉ
ሰዎች ገናም ሐጢያተኛ የሆኑት ሌሎች የተጻፈውን የእግዚአብሄር ቃል በማመን
ያለ ሐጢያት እንዲሆኑ ሊያግዙዋቸው ይችላሉ፡፡ ምክንያቱም የሐጢያቶቻቸውን
ስርየት የተቀበሉት በእምነት ነውና፡፡ ስለዚህ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
በማመን ከሐጢያቶቻቸው ስርየትን ያገኙ ጻድቃኖችን የተገናኙ ሰዎች ዳግመኛ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


‹‹ቃል ብቻ ተናገር›› 275

የመወለጃውን ቃል ከእነርሱ መስማት፣ ኢየሱስን ማመንና ጻድቃን መሆን


ይችላሉ፡፡
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን ጻድቃን የሆኑ ሰዎች እውነተኛ
ምዕመናኖች እንጂ መናፍቃን አይደሉም፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን
ዳግመኛ የተወለዱ ብሩካን ናቸው፡፡ ዳግመኛ ለመወለድ በጣም የተባረከው
መንገድ የእግዚአብሄርን ቤተከርስቲያን መሪዎች መከተልና ከእነርሱ ጋር
መተባበበር እውነተኛውን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለዓለም ሐጢያተኞች
በሙሉ መስበክ ነው፡፡ ገናም ሐጢያተኞች የሆኑ ክርስቲያኖች በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል በማመን ጻድቃን በሆኑት ፊት ቀርበው በግልጽ ጻድቃኖች
መናፍቃን ናቸው ብለው ሊከሱን ይገባል፡፡ እነዚህን ክሶች ከጀርባዎቻችን ሆነው
በእኛ ላይ መወርወራቸው ሞኝነታቸውንና ቦቅቧቃነታቸውን የሚያሳይ ነው፡፡
ትክክለኛው እምነት ምን ዓይነት እምነት ነው? መቶ አለቃው አህዛብ ነበር፤
ነገር ግን የእግዚአብሄርን ቃል እንዳለ አመነ፡፡ በዚህ የኢየሱስ ቃል እንዲህ
በማመኑም እምነቱ ተቀባይነት አገኘ፡፡ ነገር ግን ትክክለኛና እውነተኛ የይሁዲነት
ተከታዮች ስለመሆናቸው የተመጻደቁት ተቀባይነትን አላገኙም፡፡ ፈሪሳውያን
ሐጢያተኞች ነበሩ፡፡ ምክንያቱም ኢየሱስን አዳኝ አድርገው በትክክል ለመቀበል
ተስኖዋቸው ነበርና፡፡
በእግዚአብሄር ቃል የሚያምን እምነት ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ወደሚያድነን
እምነት ይመራናል፡፡ ሕይወታችን የሚባረከውም በእግዚአብሄር ቃል ሁሉ
በማመንና እርሱንም በመታዘዝ ነው፡፡ የመቶ አለቃው እምነቱ ትልቅ እንደሆነ
እግዚአብሄር የነገረው ይህ እምነት ስለነበረው ነው፡፡
እግዚአብሄር በውሃውና በመንፈሱ ጸጋ ወንጌል ይህንን እምነት ሰጥቶናል፡፡
እኛ ራሳችን በግላችን የእግዚአብሄር ቃል በተጻፈው ቃል መሰረት እንደተጻፈ
ተለማምደናል፡፡ የመቶ አለቃው የነበረው የዚህ ዓይነት እምነት ያላቸው ሰዎች
ጥቂቶች መሆናቸውን ስናይ ያሳዝነናል፡፡ እነርሱ በእግዚአብሄር የውሃና የመንፈስ
ወንጌል ማመን አለባቸው፡፡ የእግዚአብሄር ቃል በሆነው በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል ቃል ሲያምኑ እነዚህ እምነት መሰረት ከመንፈሳዊ ለምጻቸው በአንድ ጊዜ
ይፈወሳሉ፡፡ እግዚአብሄር በአያሌው የሚቀበለው እምነት እርሱ የተናገረውን
የውሃና የመንፈስ ወንጌል ቃል እንዳለ የሚያምን እምነት ነው፡፡
የሐጢያት አልባ ባደረገን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ቃል የሚያምን
እምነት እግዚአብሄር የተቀበለው የመቶ አለቃው እምነት ነው፡፡ በቃሉ ለሚያምን
ጻድቅ እግዚአብሄር የሐጢያት ስርየትንና የእርሱ ልጅ የመሆን በረከቶችን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


276 ‹‹ቃል ብቻ ተናገር››

ሰጥቶናል፡፡ ለዚህም ጌታን አመሰግነዋለሁ፡፡ እኛ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል


በማመን ሐጢያት አልባ ከሆንን በኋላ አሁን ለሌሎች ስንል የጽድቅ ሥራዎችን
ለመስራት ብቁ ሆነናል፡፡ ጌታ ጻድቅ በእምነት ብቻ ይኖራል ብሎ እንደተናገረ
በሕይወታችን ለዘላለም በእርሱ እንመን፡፡
ጌታ እናንተንም ደግሞ ይምራችሁ፡፡ አሜን ሐሌሉያ! 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


አስቀድማችሁ ጌታን ተከተሉ
‹‹ ማቴዎስ 8፡18-22 ››
‹‹ኢየሱስም ብዙ ሰዎች ሲከቡት አይቶ ወደ ማዶ እንዲሻገሩ አዘዘ፡፡ አንድ
ጻፊም ቀርቦ፡- መምህር ሆይ ወደምትሄድበት ሁሉ እከተልሃለሁ አለው፡፡
ኢየሱስም፡- ለቀበሮዎች ጉድጓድ ለሰማይ ወፎችም መሳፈሪያ አላቸው፡፡ ለሰው
ልጅ ግን ራሱን የሚያስጠጋበት የለውም አለው፡፡ ከደቀ መዛሙርቱም ሌላው፡-
ጌታ ሆይ አስቀድሜ እንድሄድ አባቴን እንድቀብር ፍቀድልኝ አለው፡፡ ኢየሱስም፡-
ተከተለኝ፤ ሙታናቸውንም እንዲቀብሩ ሙታንን ተዋቸው አለው፡፡››

እዚህ ላይ እንዲህ ተብሎ ተጽፎዋል፡- ‹‹አንድ ጻፊም ቀርቦ፡- መምህር ሆይ


ወደምትሄድበት ሁሉ እከተልሃለሁ አለው፡፡›› ያን ጊዜም ኢየሡስ ጻፊውን እንዲህ
አለው፡- ‹‹ለቀበሮዎች ጉድጓድ ለሰማይ ወፎችም መሳፈሪያ አላቸው፡፡ ለሰው ልጅ
ግን ራሱን የሚያስጠጋበት የለውም፡፡›› ይህ በዓለማዊ አነጋገር ጻፊ ተብሎ
የተጠራው ሰው፣ ከፍተኛ ሥልጣን ያለው ሰው ‹‹መምህር ወደምትሄድበት ሁሉ
እከተልሃለሁ›› በማለት ኢየሱስን መከተል መረጠ፡፡ ይህ ሰው ለኢየሱስ ታላቅ
አክብሮት ነበረው፡፡ በእርግጥም ሊከተለው ፈልጎዋል፡፡ ኢየሱስ ማን እንደነበር
በሚገባ የተረዳ ሰው መሆን አለበት፡፡ በዚህ ዓለም ላይም ከኢየሱስ የሚበልጥ
ሰው እንደሌለ ያሰበ መሆን አለበት፡፡
ኢየሱስ ግን እንዲህ አለው፡- ‹‹ለቀበሮዎች ጉድጓድ ለሰማይ ወፎችም
መሳፈሪያ አላቸው፡፡ ለሰው ልጅ ግን ራሱን የሚያስጠጋበት የለውም፡፡›› ጻፊው
ይህንን ከሰማ በኋላ ምናልባት ተስፋ ሳይቆርጥ አልቀረም፡፡ ኢየሱስን በሰውነቱ
ቢያከበረውም ከኢየሱስ የሚያገኘው ምንም ነገር እንደሌለ ሲያውቅ ተስፋ
ቆረጠ፡፡ ጻፊው አስቀድሞ ለኢየሱስ ባለው አክብሮት ሊከተለው ቢፈልግም
ከእርሱ ደቀ መዛሙርቶች እንደ አንዱ ሆኖ አንዳች ነገር ከእርሱ እንደሚያገኝ
ጠብቆ ነበር፡፡ ኢየሱስ ግን የሰው ልጅ ራሱን የሚያስጠጋበት ስፍራ እንደሌለው
ነገረው፡፡ ጻፊው ኢየሱስ በዚህ ዓለም ላይ ኩርማን መሬትም ሆነ የራሱ ቤት
ሌላም ምንም ነገር እንደሌለው ከሰማ በኋላ ተስፋ ቆረጠ፡፡
ከኢየሱስ ደቀ መዛሙርቶች አንዱ ‹‹ጌታ ሆይ አስቀድሜ ልሄድና አባቴን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


278 አስቀድማችሁ ጌታን ተከተሉ

ልቅበር›› ባለው ጊዜ ኢየሱስ ‹‹ሙታንን ተዋቸው›› አለው፡፡


ደቀ መዝሙር መምህሩን የሚከተል ሰው ነው፡፡ ጌታን ስለ መከተል ሲነሳ
ኢየሱስ እዚህ ላይ የተናገረው አስደንጋጭ ነው፡፡ ኢየሱስ ዓለማዊ ሰዎች
ቢፈልጉም ጌታን መከተል እንደማይችሉና ጌታን በመከተልም ሊያገኙት
የሚችሉት ምንም ነገር እንደሌለ እየነገረን ነው፡፡ በእርግጥም ጌታን በመከተል
ምን ዓለማዊ ነገሮችን ማግኘት ይቻላል? ኢየሱስ እንደተናገረው የሰው ልጅ ራሱን
የሚያስጠጋበት ስፍራ ስላልነበረው ዓለማዊ ሰዎች ጌታን የሚከተሉበት ምክንያት
የለም፡፡

ሰው ጌታን ለመከተል ወንጌልን መውደድ አለበት፡፡

እዚህ ላይ ከኢየሱስ ደቀ መዛሙርቶች አንዱ አስቀድሞ አባቱን


እንዲቀብርና በኋለም እንዲከተለው ኢየሱስን ጠየቀው፡፡ አባቱ ስለሞቱ አስቀድሞ
አባቱን መቅበር ከዚያም ጌታን መከተል ተገቢ አይደለምን? በዚህ ዓለም ሥነ
ምግባርና ግብረ ገብነት ላይ በመመስረት ሲመዘን ይህ መደረግ የሚያስፈልገው
ትክክለኛ ነገር ነው፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ግን ኢየሱስ እንዲህ ብሎዋል፡-
‹‹ተከተለኝ፤ ሙታናቸውን እንዲቀብሩ ሙታንን ተዋቸው፡፡›› በሌላ አነጋገር ራሱን
የኢየሱስ ደቀ መዝሙር አድርጎ የሚጠራ ሰው ጌታን የሚከተለው እንዴት ሥጋዊ
ነገሮቹን ሁሉ ካጠናቀቀ በኋላ ብቻ ይሆናል? አንድ ሰው ጌታን በእርግጠኝነት
መከተል የሚፈልግ ከሆነ ራሱን መካድ፣ መስቀሉን መሸከምና ጌታን መከተል
አለበት፡፤ (ማርቆስ 8፡34) መጽሐፍ ቅዱስ እዚህ ላይ የሚነግረንን ኢየሱስን
በእርግጠኝነት የመከተል ፍላጎት ካለን ይህንን ማድረግ የምንችለው ዓለማዊ ሰዎች
ዓለማዊ ጉዳዮቻቸውን እንዲፈጽሙ ስንፈቅድ ብቻ ነው፡፡
ስለዚህ ነገር በጥንቃቄ እናስብ፡፡ ጌታን ለመከተል ስትሞክሩ ታማኝ ደቀ
መዝሙር ሆናችሁ ከመቆየት የሚያደናቅፉዋችሁ ብዙ የሥጋ እንቅፋቶች አሉ፡፡
አንድ ሰው ጌታን ሲገናኝና ሊከተለው ሲፈልግ በመንገዱ ላይ የሚገጥመው
የመጀመሪያው እንቅፋት የቤተሰቡ ጉዳይ ነው፡፡ ቤተሰቡን የማይንከባከብ ከሆነ
ያዝንላቸዋል፡፡ እነርሱን መንከባከብና መርዳት እንደሚገባውም ለራሱ ያስባል፡፡
እኔም ዳግመኛ ከተወለድሁ በኋላ ተመሳሳይ ችግር ገጠመኝ ወቅት ነበር፡፡
ታላቅ ወንድሜ ሚስቱን፣ ሁለት ወንድ ልጆቹን፣ ሁለት ሴት ልጆቹን በአጠቃላይ
አራት ልጆቹን ትቶ በድንገት ሞተ፡፡ እኔ እነዚህን የወንድሜን ወንድ ልጆችና ሴት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


አስቀድማችሁ ጌታን ተከተሉ 279

ልጆች ከተወለዱበት ጊዜ ጀምሮ በጣም እወዳቸውና እንከባከባቸው ነበር፡፡ ነገር


ግን ትልቁ ውሳኔ ወንድሜ ከሞተ በኋላ ወዲያውኑ ዳግመኛ መወለዴ ነበር፡፡ ያን
ጊዜ ለጠፉት ነፍሳቶች ሐላፊነት እንዳለብኝ ይሰማኝ ነበር፡፡ ጌታን ለመከተልም
ብርቱ ፍላጎት ነበረኝ፡፡ ልቤ ለአንድም ነፍስ ቢሆን ወንጌልን ማስፋፋትና
የሐጢያቶቹን ስርየት እንዲቀበል የመርዳት ፍላጎት ነበረው፡፡
ነገር ግን ወደኋላ የሚጎትተኝ ነገር ነበር፡፡ የወንድሜን ወንድ ልጆችና ሴት
ልጆች በሚመለከት እነርሱን ለመንከባከብ ገንዘብ ማግኘት እንዳለብኝ
ተሰምቶኛል፡፡ ይህንን እንዳደርግ የሚያስገድደኝ ነገር ባይኖርም በልቤ ጥልቅ
ውስጥ ግን ይህ ፍላጎት ነበረኝ፡፡ ስለዚህ ምን ማድረግ እንደሚገባኝ መጨነቅ
ጀመርሁ፡፡ ጎረምሶች ራሳቸውን እንደሚረዱ የታወቀ ነው፡፡ የወንድሜ ወንድና
ሴት ልጆች ግን ያለ አባት ልብዋ ከተሰበረው እናታቸው ጋር የሚኖሩ ገና ልጆች
ስለነበሩ እነርሱን ለመርዳትና ለመንከባከብ ግዴታ እንዳለብኝ ተሰማኝ፡፡ እነርሱን
ለመንከባከብ ደግሞ ገንዘብ ማግኘት ነበረብኝ፡፡ የወንድሜን ሚስት ጨምሮ
አምስቱንም ለመደገፍ የሚችል ገንዘብ ማግኘት ለእኔ ቀላል ሥራ አልነበረም፡፡
አራቱንም ልጆች ለመመገብ፣ ለማልበስና ትምህርት ቤት ለመላክ ብዙ ገንዘብ
ይጠይቃል፡፡ ደግሞም ወንጌልንም መስበክ ነበረብኝ፡፡ ወንጌልን ማገልገል ካለብኝ
እነርሱን መንከባከብ አልችልም፡፡ እነርሱን መንከባከብ ካለብኝ ደግሞ ወንጌልን
መስበክ አይቻለኝም፡፡ ስለዚህ ምን ማድረግ እንዳለብኝ ብዙ ጊዜ አሰብሁ፤
ተጨነቅሁም፡፡
ከጊዜ በኋላ የራሴን ውሳኔ ወሰንሁ፡፡ የደረስሁበት ድምዳሜ ይህ ነበር፡፡
የወንድሜን ወንድና ሴት ልጆች መንከባከብ ለእኔ አስፈላጊ ቢሆንም መቋቋም
ስችል በኋላ ልረዳቸው እችላለሁ፤ የእግዚአብሄር ሥራ ግን አሁኑኑ መሰራት
አለበት፡፡ ወደ ጎን ሊተው አይችልም፡፡ ውንጌልን ባልሰብክ በዚህ ዓለም ላይ ያሉ
ብዙ ነፍሳቶች በሐጢያት ይሞታሉና፡፡፡ ያን ጊዜ ምን ማድረግ እንደሚገባኝ
የገጠመኝ እንቆቅልሽ ተፈታ፡፡ እኔ ወንጌልን በማሰራጨት ፋንታ ገንዘብ ባግኝና
ቤተሰቤን ብንከባከብ ኖሮ ይህ ቢበዛ ለአራት ወይም ለአምስት ሰዎች ሥጋዊ
ደስታን ይሰጣቸው ይሆናል፡፡ ነገር ግን ወንጌልን ባገለግልና ጌታን ብከተል ይህ
ብዙ ሰዎችን ወደ ሕይወት በማምጣት ለብዙዎች እውነተኛ ደስታን ይሰጣል፡፡
ስለዚህ በጥንቃቄ ካሰብሁ በኋላ የመጨረሻ ውሳኔዬ ላይ ደረስሁና እንዲህ
አልሁ፡- ‹‹ለወንድሜ ወንድና ሴት ልጆች አዝናለሁ፡፡ ነገር ግን ላደርግላቸው
የምችለው ነገር ጥቂት ነገር ነው፡፡ ጠንክረው በመስራት እነዚህን ችግሮች ማሸነፍ
ቢችሉና እግዚአብሄርም ቢባርካቸውና ቢረዳቸው እመኛለሁ፡፡›› ያን ጊዜ ጌታን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


280 አስቀድማችሁ ጌታን ተከተሉ

ለመከተል ወሰንሁ፡፡
በዚህ ዓለም ላይ ኑሮዋችንን ስንኖር ብዙ እንደዚህ ዓይነት ነገሮች
ይገጥሙናል፡፡ ዳግመኛ ከተወለድን በኋላ ‹‹አስቀድሜ አባቴን ልቅበር›› ያልነው
ስንት ጊዜ ነው? በኢየሱስ በማመን ዳግመኛ ብንወለድ ማድረግ የምንፈልጋቸው
ብዙ ሥጋዊ ነገሮች የሉምን? የእኛን እንክብካቤ የሚፈልጉ ምን ያህል ሰዎች
አሉን? በዛሬው ምንባብ ላይ የተጠቀሰው ደቀ መዝሙር ‹‹አስቀድሜ አባቴን
ለመቅበር ልሂድ›› አለ፡፡ ነር ግን እርሱ ሥጋዊ ጉዳዮቹን ሁሉም የሚፈጽም ከሆነ
የእግዚአብሄርን ሥራዎች ለመስራት ጊዜ የሚገኘው መቼ ነው? በቂ ጊዜስ
የሚኖረው መቼ ነው? ኢየሱስ ‹‹ተከተለኝ፤ ሙታኖቻቸውንም እንዲቀበሩ
ሙታንን ተዋቸው›› ያለው ለዚህ ነው፡፡ እርሱ ይህንን ያለው እውነት ስለሆነ
ነው፡፡
ማንም ሰው በአንድ ጊዜ ሁለት ነገሮችን በሚገባ መስራት አይችልም፡፡
ሥጋዊ ጉዳዮቻችንንና መንፈሳዊ ሥራዎችን ለማከናወን ብንፈልግም እነዚህን
ሁለት ነገሮች በተመሳሳይ ጊዜ ማከናወን አንችልም፡፡ ሁለት ነገሮችን ጎን ለጎን
መፈጸም የሚችል ብቃት ያለው ሰው ቢኖርም እንኳን አንዱ ነገር ላይ
ሲንጠለጠል ሌላውን ሥራ ለመስራት ታማኝ አይሆንም፡፡ ምክንያቱም ምንም
ያህል የተካነ ቢሆንም አቅሙ ገደብ አለው፡፡ አንድ ምሳሌ ላሳያችሁ በቀድሞ ጊዜ
ገናም በትምህርት ቤት ሳለንና ፈተናዎችን ለማለፍ ስናጠና ብዙውን ጊዜ በተወሰኑ
ትምህርቶች ላይ እናተኩር ነበር፡፡ በአንድ ትምህርት ላይ ትልቅ ክብደት ሰጥተን
የጥናት ጊዜያችንን በአብዛኛው እዚያ ላይ ስናሳልፍ ሌሎቹን ትምህርቶች
በተመሳሳይ ግለት ማጥናት እንደማንችል የታወቀ ነው፡፡ ለእነርሱ የምናጠፋው
ጊዜና የምንሰጠው ትኩረት አነስተኛ ነው፡፡ ምክንያቱም እኛ ውሱን ፍጡራኖች
ነንና፡፡
ስለዚህ በእግዚአብሄርም ፊት ቀጣዩን ምንባብ የእርግጠኝነት ጉዳይ
አድርገን ልንመለከተው ይገባናል፡፡ ‹‹ተከተለኝ፤ ሙታኖቻቸውንም እንዲቀርቡ
ሙታንን ተዋቸው፡፡›› የዚህን ምንባብ ትርጉም ማወቅና መከተል ያስፈልገናል፡፡
የራስን አባት መቅበር ትክክል ነው፡፡ ሁላችንም ልናደርገው የሚገባን ነገር ነው፡፡
በእኛ ዳግመኛ በተወለድነው መካከል በሞት ለተለየው የቤተሰብ አባል ለአንዱ
ተገቢውን ቀብር የማያደርግ አለ እንዴ? ሁሉም ሰው ይህንን ያደርጋል፡፡ ጌታ ግን
ዳግመኛ ለተወለዱት ደቀ መዛሙርቶቹ አስቀድመው ምን ማድረግ እንዳለባቸውና
እርሱን ከልባቸው የሚከተሉት ደቀ መዛሙርትም አስቀድመው ምን ማድረግ
እንደሚገባቸው ተናግሮዋል፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


አስቀድማችሁ ጌታን ተከተሉ 281

ጻድቃን አስቀድመው ምን ማድረግ አለባቸው? አስቀድመው


የእግዚአብሄርን ሥራዎች መስራት ጌታን መከተል ወንጌልን ማገልገል፣ ጌታ
እንዲያደርጉ የሚፈልገውን ማድረግና እርሱ ወደሚመራቸው ሁሉ መመራት
አለባቸው፡፡ ይህ የደቀ መዝሙርነት ሕይወት ጌታን መከተል ነው፡፡ ዳግመኛ
ከተወለድን በኋላ የዓለም ደቀ መዛሙርቶች ሆነን መቅረታችን ወይም የኢየሱስ
ደቀ መዛሙርት መሆናችንን የሚወሰነው ጌታን ወይም ዓለምንና ዓለማዊ
ዕሴቶቹን በመከተል ላይ ነው፡፡ የዚህ ዓለም ሰዎች የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት
ፈጽሞ እዚህ ግቡ የማይባሉ፣ ጨርሶ ያልበሰሉና አስመሳይ ሰዎች ናቸው ብለው
ያስባሉ፡፡ እንደዚህ የሚያስቡት በራሳቸው ዓለማዊ መመዘኛዎችና በራሳቸው ላይ
ተመስርተው ነው፡፡ ነገር ግን የኢየሱስ እውነተኛ ደቀ መዛሙርት ብዙም የተለዩ
ላይሆኑ ይችላሉ፡፡ የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት ከዓለም ደቀ መዛሙርት ይልቅ
አርቀው ያስባሉ፡፡ ግቦቻቸው ክቡር ናቸው፡፡ ልቦቻቸው ልክ እንደ ባህር ትላልቅ
ናቸው፡፡ በዚህ ዓለም ላይ አንድ ጊዜ የተወለደ ሰው ትርጉም ያለው ሕይወት
መኖር አለበት፡፡ ይህንን ሕይወት መኖር የደቀ መዝሙርነት ሕይወት ነው፡፡

እናንተ የማን ደቀ መዛሙርት ናችሁ?

እናንተ የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት ናችሁ ወይስ የዓለም ደቀ መዛሙርት


ናችሁ? በሌላ አነጋገር የምትከተሉት ዓለምን ነው ወይስ ኢየሱስን ነው? ኢየሱስን
የሚከተሉ ሰዎች የዚህን ዓለም ነገር በሙሉ ወደ ጎን ትተው የጌታችንን ወንጌል
ማገልገል ይሻሉ፡፡ የጌታ ደቀ መዛሙርት እንደዚህ የሚኖሩ ሰዎች ናቸው፡፡
በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ ማህበራዊ ሕይወታቸውን እየኖሩ፣
ቤተሰቦቻቸውን እየተንከባከቡና እንግዳቸውንና ሥራቸውን በትጋት እየሰሩ
ወንጌልን የሚያገለግሉ አንዳንድ አባል የሆኑ ምዕመናኖች አሉ፡፡ ይህም እንደዚሁ
የጌታችን የደቀ መዝሙርነት ሕይወት መሆኑ እርግጥ ነው፡፡ ነገር ግን ኢየሱስን
የሚከተሉና የጌታን ወንጌል ሙሉ በሙሉና በተለየ መንገድ የሚያገለግሉ ሰዎችም
ደግሞ አሉ፡፡ እነርሱ እውነተኛ የእግዚአብሄር ደቀ መዛሙርት ናቸው፡፡ እነርሱ
ትክክለኛውን የደቀ መዝሙርነት ሕይወት እየኖሩ ናቸው፡፡
ምንም ይሁን አንድ ደቀ መዝሙር የመምህሩን ዱካዎች ይከተላል፡፡
የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት ኢየሱስ እንዲያደርጉ የሚፈልግባቸውን ነገር ማድረግ
ይወዳሉ፡፡ ስለዚህ በኢየሱስ ለማመንና እርሱን ለመከተል የወሰኑ ሰዎች ጌታን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


282 አስቀድማችሁ ጌታን ተከተሉ

ለዘላለም መከተል ይገባቸዋል፡፡ እዚህ ላይ ኢየሱስ እንዲህ አለ፡- ‹‹ተከተለኝ፡፡››


እርሱን መከተልም በእርግጥ ትልቅ ደስታ ነው፡፡ ኢየሱስ እንዴት ያለ ትልቅ
መምህር እርሱ እንደምን ሁሉን ቻይ ጌታችን እንደምን መልካም ነው?
በእርግጠኝነት ጌታን የምንከተል ከሆነ መቼም ቢሆን ፈጽሞ አንጸጸትም፡፡
ጌታን የምንከተል ከሆነ ፈጽሞ አይጥለንም፡፡ መቼም ቢሆን አይከዳንም
ጌታን መከተል ፈጽሞ መና የሚያስቀር አይደለም፡፡ ጌታ ኢየሱስ ለደቀ
መዛሙርቱ እንዲህ ያላቸው ለዚህ ነው፡- ‹‹እንግዲህ ሂዱና አህዛብን ሁሉ በአብ፣
በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው ያዘዝኋችሁንም ሁሉ
እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጉዋቸው፡፡›› (ማቴዎስ
28፡19-20) እርሱ የዛሬው ዘመን ደቀ መዛሙርት ለሆንነው ለእኛም ከአሕዛቦች
ሁሉ ደቀ መዛሙርት እንድናደርግ ይነግረናል፡፡
እውነተኛ ደቀ መዝሙርነት ምን እንደሆነ በተጨባጭ ማሰብና ይህንን የደቀ
መዝሙርነት ሕይወት በእርግጥ እየኖርን እንደሆኑ ወይም እንዳልሆነ በጥንቃቄ
መመርመር አለብን፡፡ ባተሌ የሚያደርገንን መርሃ ግብርና አስቸኳይ
ተግባራቶቻችንን ለጊዜው ወደ ጎን አስቀምጠን ይህንን ጉዳይ ከምር ልናስብበት
ይገባናል፡፡ የእርሱ ደቀ መዛሙርት ለመሆን በወሰንነው ውሳኔያችን ተደሰትን
እንደሆነና የእርሱ በጎ ወታደሮች አድርጎ (2ኛ ጢሞቴዎስ 2፡4) የመለመለንን የጦር
አበጋዝ ለማስደሰት ተዘጋጅተን እንደሆነ አእምሮዋችንን ደግመን መፈተሽ
ይገባናል፡፡ የእርሱ የደቀ መዝሙርነት ሕይወት እኛ ልንኖርበት እጅግ የከበረና
የተገባ ሕይወት መሆኑን ማረጋገጥ አለብን፡፡ ያን ጊዜ የእርሱ መልካም ደቀ
መዛሙርት ሆነን እንደገና ልቦቻችንን ማዘጋጀት ይገባናል፡፡
የምወዳችሁ ክርስቲያኖች ጻፊው ጌታን መከተል ፈለገ፡፡ ነገር ግን ያንን
ማድረግ አልቻለም፡፡ ያንን ማድረግ ያቃተው ጌታ እርሱን በመከተል የሚያተርፈው
ምንም ነገር እንደሌለ ስለነገረው ነው፡፡ እንዲህ አለው፡- ‹‹ምንም የለኝም፤ ነገር ግን
አሁንም ልትከተለኝ የምትፈልግ ከሆነ ተከተለኝ፡፡ በዚህ ዓለም ላይ ንብረት
የለኝም፡፡ ነገር ግን እንደ እውነቱ ከሆነ እኔ በመንግሥተ ሰማይ እጅግ ታላቅ ነኝ፤
የሰራዊት ጌታ የነገሥታት ንጉሥ ነኝ፡፡ ሆኖም በዚህ ዓለም ላይ ምንም ንብረት
የለኝም፡፡ ነገር ግን እንደ እውነቱ ከሆነ እኔ በመንግሥተ ሰማይ እጅግ ታላቅ ነኝ፡፡
የሰራዊት ጌታ የነገሥታት ንጉሥ ነኝ፡፡ ሆኖም በዚህ ዓለም ላይ ምንም
እንደማታገኝ በሚገባ አውቀህ ተከተለኝ፡፡ ይህንን አውቀህ የምትከተለኝ ከሆነ
እንግዲያውስ ተከተለኝ፡፡››
ለደቀ መዛሙርቱ ግን ኢየሱስ እንዲህ አለ፡- ‹‹ተከተሉኝ፤ ሙታኖቻቸውንም

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


አስቀድማችሁ ጌታን ተከተሉ 283

እንዲቀብሩ ሙታንን ተዋቸው፡፡›› እዚህ ላይ ሙታን እነማን ናቸው? ዳግመኛ


ያልተወለዱት አይደሉምን? እነርሱ በኢየሱስና በእውነተኛው የውሃውና የመንፈሱ
ወንጌል የማያምኑ ሰዎች ናቸው፡፡ ዓለም በአንቅፋቶች የተሞላች ልትሆን
ትችላለች፡፡ እኛም ጌታን መከተል ይከብደን ይሆናል፡፡ ነገር ግን ሕይወታቸውን
ስትኖሩ ጌታችን እዚህ ላይ ‹‹ተከተሉኝ›› ያለውን አስታውሱ፡፡
ሁልጊዜም ጌታ እርሱን እንድትከተሉት እንደነገራችሁ በልቦቻችሁ
እንድታስታውሱና እናንተም ይህንኑ በእርግጠኝነት እንድታደርጉ ተስፋዬና ጸሎቴ
ነው፡፡ 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


ዳውንሎድ
የሬቨረንድ ፖል ሲ. ጆንግን በነጻ የሚታደሉ የክርስቲያን ኢመጽሐፎችንና ኦዲዮመጽሐፎችን
ከድረ ገጻችን ላይ በስማርት ስልካችሁ፣
ታብሌታችሁ ወይም የግል ኮምፒውተራችሁ ላይ ገልብጡት፡፡
የኢንተርኔት ግንኙነት ሳይኖራችሁም እንኳን በየትኛውም ስፍራ ልታነቡዋቸውና
ልታዳምጡዋቸው ትችላላችሁ፡፡
www.bjnewlife.org

መነሻ ገጽ

ኦድዮ መጽሐፎች

ኢ-መጽሐፍት
Rev. PAUL C. JONG
ደራሲው የውሃውንና የመንፈሱን
ወንጌል በዓለም ላሉ የጠፉ ነፍሳቶች ላለፉት
አስርተ ዓመታት ሲሰብኩ ቆይተዋል፡፡
የኒው ላይፍ ሚሽን መስራች
በመሆናቸውም በአሁኑ ጊዜ በኒው ላይ ሚሽን
ትምህርት ቤት ብዙ ደቀ መዛሙርቶችን
እያሳደጉ ነው፡፡
በሚሽን ላይ ያተኮሩ ቤተክርስቲያኖችን
ከመሰረቱ በኋላ በመጽሐፎቻቸው አማካይነት
ወንጌልን እያሰራጩ ነው፡፡
በአሁኑ ጊዜ መጽሐፎቻቸው በዓለም
ላይ ባሉ 96 ዋና ዋና ቋንቋዎች ተተርጉመው
እየተነበቡ ነው፡፡

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
በዚህ ዓለም ላይ እጅግ ብዙ ሰዎች ይኖራሉ፡፡ ከእነዚህ ብዙዎቹ ኢየሱስን
አዳኛቸው አድርገው እንደሚያምኑ ቢናገሩም ይህ ለብዙዎቹ መላ ምታዊ እሳቤ
ብቻ ነው፡፡ በመላው ዓለም ከአሜሪካ እስከ እስያ፣ አውሮፓና አፍሪካ ድረስ ብዙ
ሰዎች በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን ከሐጢያቶቻቸው ለመዳን እየተፍጨረጨሩ
ነው፡፡ ነገር ግን ከእነርሱ ብዙዎቹ ልክ ሕጻኑን ኢየሱስን ለመገናኘት ወደ
እስራኤል እንደተጓዙት ሰብዓ ሰገሎች ግራ በመጋባት ውስጥ ወድቀዋል፡፡ እነዚህ
ሰዎች በኢየሩሳሌም ውበት ተደንቀው ስለነበር ለጊዜውም ቢሆን ወደ ኢየሱስ
ስትመራቸው የነበረችውን ኮከብ ትተዋት ነበር፡፡ ማናችንም የዚህ ዓይነት ነገር
መቼም ቢሆን እንዲገጥመን መፍቀድ አይኖርብንም፡፡ ዛሬ ሰዎች ኢየሱስን
ለመገናኘትና ደህንነታቸው ላይ ለመድረስ አጥብቀው ቢፍጨረጨሩም ብዙዎቹ
ኢየሱስ ማግኘት አልቻሉም፡፡ ምክንያቱም ኢየሱስን ለመገናኘት
የሚፍጨረጨሩት በራሳቸው እሳቤዎች መሰረት ነውና፡፡

-ከመጽሐፉ የተወሰደ-

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡

You might also like