You are on page 1of 327

የንስሐ ጸሎቶች

ትምህርት መንፈሳችሁን
እየገደለው ነው፡፡
በጣም ብዙ ሰዎች የለከፉዋቸውን
ቫይረሶች ሳያውቁ እንደሚሞቱ ሁሉ በዓለም
ሁሉ ያሉ ክርስቲያኖችም በንስሐ ጸሎቶች
ትምህርት ተለክፈው እየሞቱ ነው፡፡ የንስሐ
ጸሎቶች ትምህርት እንዲህ ያለ አደገኛ የተሳሳተ
ትምህርት መሆኑን ማወቅ የቻለ ማን ነው?
በርካታ ክርስቲያኖችን ወደ መንፈሳዊ
ውዥንብር ገደል ውስጥ የነዳቸው ማን
እንደሆነ ታውቃላችሁን? ዳግመኛ ሳይወለዱ
ቃሉን ያስተማሩ የክርስቲያን መሪዎች ናቸው፡፡
ስለዚህ አሁንም እንኳን እግዚአብሄር
በሰጠን የውሃና የመንፈስ ወንጌል ቃል ማመንና
ከሐጢያቶቻችሁ ሁሉ መንጻት አለባችሁ፡፡
ይህ የተባረከ ዕድል እንዲባክን ልትፈቅዱ
አይገባችሁም፡፡ ሁላችሁም በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል በማመን ከመንፈሳዊ ግራ
መጋባት ነጻ መውጣትና በእውነት ብርሃን
ውስጥ መኖር አለባችሁ፡፡
የንስሐ ጸሎቶችን ትምህርት ስህተት
እስከ አሁን ድረስ ሳታውቁ ቀርታችሁ ከሆነ
ከዚህ መጽሐፍ ልታውቁት፣ በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል ልታምኑና ወደ ጌታ
ልትመለሱ ይገባችኋል፡፡ ጌታ አዲስ ሕይወት
የሚገኝበትን እንጀራ አዘጋጅቶ እየጠበቃችሁ
ነው፡፡

-ፖል ሲ. ጆንግ-
ስላሴ አምላክ ለእኛ
ምን እንዳደረገልን

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
ስላሴ አምላክ ለእኛ
ምን እንዳደረገልን

PAUL C. JONG

Hephzibah Publishing House


A Ministry of THE NEW LIFE MISSION
SEOUL, KOREA

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
በኤፌሶን ላይ የተሰጡ ስብከቶች (II)
ስላሴ አምላክ ለእኛ ምን እንዳደረገልን
Revised edition. Copyright © 2014 by Hephzibah Publishing House
ሙሉ መብቱ በሕግ የተጠበቀ ነው፡፡ ከዚህ መጽሐፍ ባለቤት በጽሁፍ የተገኘ ፈቃድ
ሳይኖር የዚህን መጽሐፍ ማንኛውንም ክፍል ማባዛት ወይም በማንኛውም መልኩ ወይም
በማንኛውም መንገድ በኤሌክትሮኒክ ወይም በሜካኒካል ፎቶ ኮፒ ማድረግን ጨምሮ
በቅጂ መልክ ወይም መረጃን ይዞ በሚያጠራቅም ወይም መረጃን ይዞ በሚያስቀር
ማንኛውም መንገድ ማሰራጨት አይቻልም፡፡
ጥቅሶቹ በሙሉ የተወሰዱት ከ1954ቱ የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ ነው፡፡

ISBN 978-89-282-1823-3
ዲዛይን፡ በሚን ሱ ኪም
ንድፍ፡ በዮንግ አይ ኪም
ትርጉም፡ በካሳሁን አየለ
የታተመው በኮርያ ነው፡፡

Hephzibah Publishing House


A Ministry of THE NEW LIFE MISSION
Seoul, Korea

♠ Website: https://www.nlmission.com
https://www.bjnewlife.org
https://www.nlmbookcafe.com
♠ E-mail: newlife@bjnewlife.org

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
የማውጫ ሰሌዳ

መቅድም ----------------------------------------------------------------- 9

ደህንነታችን ከዓለም ፍጥረት በፊት በኢየሱስ ጽድቅ ተዘጋጅቷል


(ኤፌሶን 1፡1-4) ------------------------------------------------------- 13

በጸጋው የእግዚአብሄር ወገኖች ሆነናል


(ኤፌሶን 1፡1-14) ------------------------------------------------------ 37

በእግዚአብሄር ፍቅርና መስዋዕትነት አማካይነት ድነናል


(ኤፌሶን 1፡1-6) ------------------------------------------------------- 55

የቤተክርስቲያኑ አባሎች አድርጎ ስለጠራን እግዚአብሄርን እናመሰግናለን


(ኤፌሶን 1፡20-23) --------------------------------------------------- 75

እንደ እግዚአብሄር ጸጋ ባለጠግነት መጠን ቤዛነትን አግኝተናል


(ኤፌሶን 1፡7-14) ---------------------------------------------------- 95

ለጌታ የጽድቅ ሥራ ተፈጥረናልን?


(ኤፌሶን 2፡1-10) ---------------------------------------------------- 117

በእምነት ሕይወታችን ውስጥ የእግዚአብሄርን ሥልጣንና ጸጋ መቀበል አለብን


(ኤፌሶን 2፡1-22) ----------------------------------------------------129

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
እኛ በእግዚአብሄር ፊት ምን ዓይነት ሰዎች ነበርን?
(ኤፌሶን 2፡1-7) ----------------------------------------------------- 147

በሐጢያቶቻችን ምክንያት ከእግዚአብሄር አብ ተለይን ነበር


(ኤፌሶን 2፡14-22) -------------------------------------------------- 163

ወሰን የሌላቸው የክርስቶስ በረከቶች በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በሚያምን


በእያንዳንዱ ቅዱስ ልብ ውስጥ አሉ
(ኤፌሶን 3፡1-21) ---------------------------------------------------- 183

በሕይወታችሁ ውስጥ ያለውን እምነት ጠብቁ


(ኤፌሶን 4፡1-6) ---------------------------------------------------- 197

እንደተወደዱ ልጆች እግዚአብሄርን ምሰሉ


(ኤፌሶን 5፡1-2) ----------------------------------------------------- 225

በዓለም ሐጢያቶች ውስጥ ተካፋዮች አትሁኑ


(ኤፌሶን 5፡1-14) ---------------------------------------------------- 239

በመንፈስ መሞላት ማለት በእርግጥ ምን ማለት ነው?


(ኤፌሶን 5፡1-21) ---------------------------------------------------- 257

በመንፈስ ሙላት የሚኖሩ ሰዎች


(ኤፌሶን 5፡15-21) -------------------------------------------------- 283

የሰይጣንን ሽንገላዎች ተቃወሙ


(ኤፌሶን 6፡10-17) -------------------------------------------------- 301

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com
መቅድም
በዚህ ዓለም ላይ ክርስቲያኖች ተብለው የሚጠሩ በርካቶች ቢኖሩም
ሐዋርያው ጳውሎስ እንዳደረገው የእግዚአብሄርን ጽድቅ የያዘውን የውሃና የመንፈስ
ወንጌል በትክክል የሚያምኑና የሚሰብኩ ከእነርሱ በጣም ጥቂቶቹ ናቸው፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ በደማስቆ መንገድ ላይ ጌታን ተገናኘ፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ወደ
እግዚአብሄር እቅፍ እስከሚሄድ ድረስ ቀሪ ሕይወቱን የጌታ ጽድቅ ምርኮኛ ባርያ
ሆኖ ኖረ፡፡ እኛም ደግሞ ሐዋርያው ጳውሎስ የሰበከውን የእግዚአብሄርን ጽድቅና
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በማመን የሐጢያቶቻችንን ስርየት ተቀብለናል፡፡
ልቦቻችንም በዚህ ምክንያት በሚገባ ተለውጠዋል፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ ለኤፌሶን ሰዎች በጻፈው መልዕክቱ ውስጥ
በእግዚአብሄር አብና በኢየሱስ ክርስቶስ ደህንነታችንን ለአንዴና ለመጨረሻ
እንዳገኘን ተናግሮዋል፡፡ ዛሬም ልክ እንደ ሐዋርያው ጳውሎስ በብሉይና በአዲስ
ኪዳን መጻህፍት ውስጥ የተመሰከሩትን የውሃና የመንፈስ ወንጌል የሚያምኑና
የሚሰብኩ ሰዎች አሉ፡፡ እነዚህ ቅዱሳኖች በዚህ ዘመን የውሃውንና የመንፈሱን
ወንጌል ለእናንተ እየመሰከሩ ነው፡፡
በስብከቶቼ ሁሉ ጌታ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የፈጸመውን
የእግዚአብሄር አብ ፈቃድ መመስከርና በእግዚአብሄር ጽድቅ በማመን
የሐጢያቶቻቸውን ስርየት አንድ ጊዜ ለተቀበሉ አማኞች የተሰጡትን በረከቶች
ማወጅ የማያወላውል ዓላማዬ ነበር፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምኑ
የዘመኑ ክርስቲያኖች የሚኖሩትን እውነተኛ የእምነት ሕይወት ለመመስከር
የቻልሁትን አድርጌያለሁ፡፡ አሁን ደግሞ በዚህ መጽሐፍ አማካይነት ለእያንዳንዱ
ሰው አስቀድመው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ለሚያምኑና ለማያምኑ ለሁለቱም
ያለውን ወሰን የለሽ የእግዚአብሄር ፍቅርና ጥልቅ የሆነውን ፈቃዱን ማሳየት
እወዳለሁ፡፡ ስለዚህ ይህንን መጽሐፍ በማንበብ ስትቀጥሉ ስላሴ አምላክ ለእናንተ
ያለውን ዕቅዱን ወደ መረዳት ትደርሳላችሁ፡፡ ስላሴ አምላክ እንዲባርካችሁ
ተስፋዬና ጸሎቴ ነው፡፡

ሐምሌ 7፤2008
ደራሲ ሬቨረ. ፖል ሲ. ጆንግ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


10 መቅድም

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ስብከት
1

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት
ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
ደህንነታችን ከዓለም ፍጥረት
በፊት በኢየሱስ ጽድቅ ተዘጋጅቷል
‹‹ ኤፌሶን 1፡1-4 ››
‹‹በእግዚአብሄር ፈቃድ የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ የሆነ ጳውሎስ በኤፌሶን
ላሉት ቅዱሳን፤ በክርስቶስ ኢየሱስም ላሉት ምዕመናን ከእግዚአብሄር ከአባታችን
ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን፡፡ በክርስቶስ በሰማያዊ
ስፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት
ይባረክ፡፡ ዓለም ሳይፈጠር በፊቱ ቅዱሳንና ነውር የሌለን በፍቅር እንሆን ዘንድ
በክርስቶስ መረጠን፡፡››

የጌታ ፍቅር በመገናኛው ድንኳን አደባባይ የመጋረጃ በር


ላይ በግልጥ ተጠልፎዋል!

በመዝሙር መጽሐፋችን ውስጥ የቤተክርስቲያናችን አባል በሆነችው በእህት


ጂሄ ኪም የተጻፈ እንዲህ የሚል ግጥም አለ፡-
‹‹እግዚአብሄር ከፍጥረት በፊት ደህንነትን አቀደ፤
አሳምሮ የፈጠረንና የሚያውቀን ጌታ
ሙሴን ጠራው፤ የደህንነትን የውሃና የመንፈስ ሕግ አሳየው፡፡
(የምህረትና የፍቅር ጌታ)
የመገናኛው ድንኳን በር የጌታን ፍቅር ያሳየናል፤
ንጉሡ በአጥማቂው ዮሐንስ ተጠመቀ፡፡
ለጌታ አምላካችን ምስጋናን ሁሉ ስጡ፤
(ሰማያዊና ሐምራዊ ማግ)
ጌታ ፍጹም የሆነውን ደህንነቱን ገለጠልን፡፡
(ቀይ ማግ)
በዚህ የወንጌል መዝሙር ላይ የሚገኝ አንድ መስመር የመገናኛው ድንኳን
በር የጌታን ፍቅር እንደሚያሳየን ይናገራል፡፡ አዎ በመገናኛው ድንኳን በር ላይ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


14 ደህንነታችን ከዓለም ፍጥረት በፊት በኢየሱስ ጽድቅ ተዘጋጅቷል

ያለውን የጌታን እውነተኛ ፍቅር መረዳት እንችላለን፡፡ ቅዱሳት መጻህፍት ጌታ ለእኛ


ያለው እውነተኛ ፍቅር በሰማያዊው፣ በሐምራዊው፣ በቀዩ ማግና በነጩ በፍታ ሁሉ
ውስጥ እንደተገለጠ ይናገራሉ፡፡ በዚያ የእግዚአብሄር ፍቅር ውስጥም ኢየሱስ
ከአጥማቂው ዮሐንስ በተቀበለው ጥምቀትና በመስቀል ላይ ባፈሰሰው ደሙ
የሐጢያቶቻችንን ስርየት ገልጦዋል፡፡ በመገናኛው ድንኳን የመጋረጃ በር ላይ ያሉት
ቀለማቶች ኢየሱስ ከአጥማቂው ዮሐንስ በተቀበለው ጥምቀት፣ ባፈሰሰው ደምና
ከሙታን ባደረገው ትንሣኤ የፈጸመውን ደህንነት ይበልጥ በግልጥ ያሳያሉ፡፡
እንደምናውቀው የእግዚአብሄር አብ ታላቅ የደህንነት ፍቅር ከዓለም ፍጥረት
በፊት የተዘጋጀው የኢየሱስ ክርስቶስ ፍቅር ጋር ተጣምሮዋል፡፡ በዚህ ፍቅር
አማካይነትም እግዚአብሄር በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን ለሰው ዘር
የለገሰውን የሐጢያቶች ስርየት ስጦታ መቀበል እንችላለን፡፡ የኤፌሶን መጽሐፍ
ከእግዚአብሄር አብ የመነጨው ደህንነት ከዓለም ፍጥረት በፊት በኢየሱስ ክርስቶስ
እንደታቀደ ይናገራል፡፡ ደግሞም እግዚአብሄር ለሁላችንም በሰጠን በሐጢያቶች
ስርየት አማካይነት የደህንነትን ስጦታ መቀበል የሚችሉት በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል እውነት የሚያምኑ ሰዎች ብቻ እንደሆኑም ይናገራል፡፡ የውሃውና የመንፈሱ
ወንጌል እግዚአብሄር የሰጠን እጅግ ትልቁ ስጦታ ነው፡፡
ስለዚህ በመጀመሪያ የኢየሱስ ከርስቶስን ፍቅር በያዘው የውሃና የመንፈስ
ወንጌል በማመን በእግዚአብሄር ፊት የሐጢያቶችን ስርየት መቀበል አለብን፡፡
በመሆኑም በጣም ብዙ የንስሐ ጸሎቶችን በማቅረብ የሐጢያቶችን መንጻት
እንዳልተቀበልን ማወቅ አለብን፡፡ እኛ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት
ለተገኘው የሐጢያቶች ስርየት ለእግዚአብሄር ምስጋናዎችን የምናቀርብ ቅዱሳኖች
መሆን አለብን፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ውስጥ የተገለጠውን የጌታ ፍቅር
ማወቅና ማመን አለብን፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን እግዚአብሄር
የሰጠውን የሐጢያቶች ስርየት በረከት የምንቀበል ሰዎች መሆን ይኖርብናል፡፡ ዛሬ
ብዙ ክርስቲያኖች የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ሳያውቁ ረቀቅ ባሉ አመኔታዎች
ውስጥ ወድቀዋል፡፡ ይህ የሆነበት ምክንያት በእጅጉ ታላቅ ከሆነው የእግዚአብሄር
ፍቅር በጣም እንዲያፈነግጡ ያደረጋቸው የተሳሳተው እምነታቸው በመሆኑ ነው፡፡
ይህ የማይጨበጥ አመኔታ እግዚአብሄር ከሰጠን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
ከሚያምነው እምነት በጣም የተለየ ነበር፡፡ የዘመኑ የማይጨበጥ አመኔታ
በስሜታዊ ልምምዶች ላይ ትልቅ ትኩረት ያደርጋል፡፡ ስለዚህ ከውሃውና ከመንፈሱ
ወንጌል ምልከታ አንጻር በጣም የተሳሳተ እምነት ነው፡፡ እነርሱ ስለ ራዕዮች፣
በልሳናት ስለ መናገርና ስለሚሰሙዋቸው መንቀጥቀጦች አብዝተው ያስባሉ፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ደህንነታችን ከዓለም ፍጥረት በፊት በኢየሱስ ጽድቅ ተዘጋጅቷል 15

ስለዚህ ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ባዳነን የውሃና መንፈስ ወንጌል ማመንና


በኢየሱስ ክርስቶስ ጽድቅ በማመን ከዓለም ፍጥረት በፊት በተዘጋጀው መብት
መደሰት ይገባናል፡፡ አሁን እንዲህ ካለው የማይጨበጥ እምነት በመመለስ
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል እውነት ወደሚያውቅና ወደሚያምን እምነት
መመለስ ይኖርብናል፡፡

የማይጨበጥ እምነት ያላቸው ሰዎች አሁንም ድረስ በልቦቻቸው


ውስጥ ባሉት ሐጢያቶች ምክንያት እየተሰቃዩ ነው፡፡

እነርሱ እግዚአብሄር በሰጠው የውሃና የመንፈስ ወንጌል በማመን


የሐጢያቶችን ስርየት በመቀበል ፋንታ አንዳንድ የተለያዩ ልምምዶች
እንዲኖሩዋቸው ተግተው ይሞክራሉ፡፡ ከዚህም በላይ የእነዚህ ሰዎች የማይጨበጥ
እምነት የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለመገናኘት ግዙፍ እንቅፋት እየሆነባቸው
ነው፡፡ የማይጨበጥ እምነታቸው ከሐጢያቶቻቸው ሁሉ መንጻት
የሚያስችላቸውን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ከማወቅና ከማመን
እየከለከላቸው እንደሆነ ሊያውቁ ይገባቸዋል፡፡ ነገር ግን እንዲህ ያለ ችግር እንዳለ
የሚያውቁ ያን ያህል ብዙ ክርስቲያኖች የሉም፡፡ እነርሱ እስከ አሁን ድረስ
የተደገፉበትን የማይጨበጥ እምነታቸውን መተው አለባቸው፡፡ ከዓለም ፍጥረት
በፊት ስለታቀደውና በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ስለተገለጠው የስላሴ አምላክ
ፍቅር ይበልጥ ሊጨነቁ ይገባቸዋል፡፡
የዘመኑ ክርስቲያኖች ግራ ከተጋባው እምነት የሚወጡበትን መንገድ ማግኘት
አለባቸው፡፡ ይህ ሊሆን የሚችለው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በተፈቀደው
የሐጢያቶች ስርየት እውነት በማመን ነው፡፡ አማኞች የሆንን ሁላችን ከዓለም
ፍጥረት በፊት በክርስቶስ የተዘጋጀውን የውሃና የመንፈስ ወንጌል ማወቅና ማመን
አለብን፡፡ በዚህ ብርቱ ወንጌል ብናምን ለዘላለም የሐጢያቶችን ስርየት መቀበል
እንችላለን፡፡ በመገናኛው ድንኳን ውስጥ በተገለጠው የውሃና የመንፈስ ወንጌል
እውነት በሚያምን እምነት አሁኑኑ ከሐጢያቶችና ከሰይጣን ወጥመዶች ማምለጥ
እንችላለን፡፡
ሆኖም ችግሩ ብዙ ክርስቲያኖች በልምምዶቻቸው ላይ የሚደገፉ የተዛቡ
አመኔታቻቸውን ማመስገናቸው ነው፡፡ ሲጸልዩ ወይም ‹‹ልጄ ሆይ ልጄ ሆነሃል››
የሚላቸውን እግዚአብሄርን በሕልሞቻቸው ሲያዩ እንግዳ የሆኑ ስሜቶችን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


16 ደህንነታችን ከዓለም ፍጥረት በፊት በኢየሱስ ጽድቅ ተዘጋጅቷል

የመሳሰሉ የማይጨበጡ ፍልቅ ስሜቶችን ይናፍቃሉ፡፡ ነገር ግን እነዚህ ሁሉ


ልምምዶች የእግዚአብሄር አይደሉም፡፡ በራሳቸው ስጋዊ አስተሳሰቦች መሰረት
ከሚሰሩ የዲያብሎስ መናፍስት የሚመነጩ ናቸው፡፡ (2ኛ ተሰሎንቄ 2፡9-10)
ስለዚህ እውነተኛውን የደህንነት እውነት ማለትም የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
የማድመጥ ዕድል ሲኖራችሁ በመጀመሪያ በዚህ እውነተኛ ወንጌል በማመን
የማይጨበጡ አመኔታዎችን ሁሉ ማሸነፍ አለባችሁ፡፡ በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል ውስጥ በሚገኘው የእርሱ ፍቅር ላይ በመደገፍ በእውነት መኖርና ወደ
ቅዱሱ አምላክ ፊት መቅረብ የምትችሉት ያን ጊዜ ብቻ ነው፡፡ ስትጸልዩ ወይም
በልሳን ስትናገሩ እነዚህን እንግዳ ስሜቶች መለማመዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ሥራ
እንዳልሆነ እዚህ ላይ በግልጥ መረዳት አለባችሁ፡፡

ልታውቁትና ልታምኑት የሚገባችሁ ይህ ፍጹም መተኪያ የሌለው


እውነት የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ነው፡፡

ሐጢያቶቻችሁ በእርግጠኝነት የሚደመሰሱትና የሚነጹት በኢየሱስ


ጥምቀትና በመስቀል ላይ ደሙ ስታምኑ ብቻ ነው፡፡ (ማቴዎስ 3፡15፤ ዮሐንስ 1፡29
እና 1ኛ ጴጥሮስ 3፡21) ስለዚህ ሕይወታችሁን በሙሉ ለእግዚአብሄር ብትሰጡና
በቅድስና ብታገለግሉትም ይህ የግድ የእግዚአብሄርን ፍቅር ለብሳችኋል ወይም
ደህንነታችሁን አግኝታችኋል ማለት አይደለም፡፡ ምስጢራዊ ራዕይን ስላያችሁ
ወይም የፈውስ ስጦታን ስለተለማመዳችሁ ብቻ ከእግዚአብሄር ሕዝብ አንዱ
አትሆኑም፡፡ እምነታችሁ ልምምዳዊ፣ ስሜታዊ ወይም የማይጨበጥ እስከሆነ ድረስ
የእግዚአብሄርን እውነተኛ ፍቅር እንደተቀበላችሁ መናገር አትችሉም፡፡
ሁላችንም በተጻፈው የእግዚአብሄር ቃል ስለምናምን በመገናኛው ድንኳን
ማለትም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል እውነት በእግዚአብሄር ፍቅር የተገለጠውን
የሐጢያቶችን መንጻት እውነት በግልጥ መረዳትና በዚህ እውነት ማመን አለብን፡፡
እግዚአብሄር አብ እውነተኛውን የሐጢያቶች ስርየት ወንጌል ለሐጢያተኞች ሁሉ
የሰጠው ይህንን የሐጢያቶች መንጻት ደህንነት ለሁላችንም ለመስጠት ነው፡፡ ይህ
የደህንነት በረከት ሊገኝ የሚችለው በኢየሱስ ክርስቶስ ውስጥ የሚገኘውን
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በማመን ነው፡፡ ስለዚህ ጌታ ራሱ እያንዳንዱን
ሐጢያተኛ ስለ እውነተኛው ደህንነት ሊያስተምር ፈለገ፡፡ የውሃውና የመንፈሱ
ወንጌል እውነት በመገናኛው ድንኳን አደባባይ በር ብቻ የተገለጠ ትክክለኛ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ደህንነታችን ከዓለም ፍጥረት በፊት በኢየሱስ ጽድቅ ተዘጋጅቷል 17

የደህንነት እውነት ነው፡፡ በሌላ አነጋገር ለሰዎች ሁሉ የተሰጠው እውነተኛ


የሐጢያቶቸ ስርየት ወንጌል የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ነው፡፡ የዚህ ወንጌል ጥላ
በመገናኛው ድንኳን አደባባይ በር ላይ ተገልጦዋል፡፡ ስለዚህ የመገናኛውን ድንኳን
አደባባይ በር ለመስራት ጥቅም ላይ በዋሉት በሰማያዊው፣ በሐምራዊው፣ በቀዩ
ማግና በጥሩው በፍታ ውስጥ የተገለጠውን የደህንነት ምስጢር መማርና ይህንንም
ምስጢር መረዳት ይጠቅማችኋል፡፡
የመገናኛው ድንኳን የመስዋዕት ስርዓት ሁለት በእጅጉ አስፈላጊ የሆኑ ቁም
ነገሮችን ይዞዋል፡፡ እነርሱም እጆችን መጫንና ለመስዋዕት የቀረበውን እንስሳ ደም
ማፍሰስ ናቸው፡፡ እነዚህን የመስዋዕት ስርዓት መጠይቆች እስካልተረዳችሁ ድረስ
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ውስጥ የተገለጠውን የእግዚአብሄር ፍቅር መገንዘብ
አትችሉም፡፡ ስለዚህ ሐጢያተኞችን በሙሉ የአምላክ ሕዝብ የሚያደርጋቸው
የእግዚአብሄር ፍቅር በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ውስጥ ተገልጦዋል፡፡
ማስረጃውም በብሉይ ኪዳን እጆችን መጫንና የመስዋዕቱን ደም በማፍሰስ ውስጥ
ተመዝግቦዋል፡፡ በአዲስ ኪዳን ዘመን ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱ ከአጥማቂው ዮሐንስ
በተቀበለው ጥምቀትና በመስቀል ላይ ባፈሰሰው ደም አማካይነት ደህንነታችንን
ፈጽሞዋል፡፡ በዚህ ደህንነት ለሚያምነውም ሁሉ ፍጹም የሆነውን የሐጢያቶች
ስርየት ለግሶዋል፡፡ በሌላ አነጋገር ጌታችን የእርሱ ደህንነት የሆነውን የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል ለሁላችንም ሰጥቶናል፡፡ በዚህ እውነተኛ ወንጌል ለምናምን
ሁሉ የሐጢያቶችን ስርየትና የመንፈሱን ስጦታ ለግሶናል፡፡ (የሐዋርያት ሥራ 2፡38)

ደህንነታችን የሚገኘው እግዚአብሄር በትክክል ከዓለም ፍጥረት በፊት


እንዳቀደው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ነው፡፡

በዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ ላይ እንዲህ ተጽፎዋል፡- ‹‹በክርስቶስ


በሰማያዊ ስፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና
አባት ይባረክ፡፡ ዓለም ሳይፈጠር በፊቱ ቅዱሳንና ነውር የሌለን በፍቅር እንሆን
ዘንድ በክርስቶስ መረጠን፡፡ በበጎ ፈቃዱ እንደወደደ በኢየሱስ ክርስቶስ ሥራ
ለእርሱ ልጆች ልንሆን አስቀድሞ ወሰነን፡፡ በውድ ልጁም እንዲያው የሰጠን
የጸጋው ክብር ይመሰገን ዘንድ ይህን አደረገ፡፡›› (ኤፌሶን 1፡3-6)
እያንዳንዱ ሐጢያተኛ ከዓለም ፍጥረት በፊት በኢየሱስ ክርስቶስ
የተዘጋጀውን ደህንነት በእምነት መቀበል አለበት፡፡ በዚህም ቅጽበት ቢሆን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


18 ደህንነታችን ከዓለም ፍጥረት በፊት በኢየሱስ ጽድቅ ተዘጋጅቷል

እግዚአብሄር ሐጢያተኞችን ሁሉ የራሱ ሕዝብ ለማድረግ በእግዚአብሄር


በታቀደው በዚህ የደህንነት መንገድ መሰረት በተመሳሳይ መንገድ እየሰራ ነው፡፡
የዚህ ደህንነት ተጨባጩ እውነት ለመገናኛው ድንኳን አደባባይ በር ጥቅም ላይ
በዋሉት አራቱ ቁሳቁሶች ቀለማቶች ውስጥ ተገልጦዋል፡፡ እነዚህ ቁሶች ሰማያዊ፣
ሐምራዊ፣ ቀይ ማግና ጥሩ በፍታ ናቸው፡፡ ጌታ እኛን ከዓለም ሐጢያቶች ሁሉ
ለማዳን የወሰነበት ይህ ዕቅድ የሚገኘው በስላሴ አምላክ ዕቅድ ውስጥ ነው፡፡
እግዚአብሄር አብ፣ ልጁና መንፈስ ቅዱስ ለእኛ አንድ አምላክ ናቸው፡፡ ነገር
ግን እያንዳንዳቸው የሚጫወቱት የተለየ ሚና አላቸው፡፡ እግዚአብሄር አብ
የደህንነታችንን ዕቅድ ሲቆጣጠር ኢየሱስ ክርስቶስ በእግዚአብሄር አብ
የተዘጋጀውን ይህንን የደህንነት ዕቅድ ተግባራዊ አደረገ፡፡ መንፈስ ቅዱስም አብና
ወልድ በፈጸሙት ሥራ ለሐጢያት ለመዳናችን ዋስትናን ሰጠን፡፡ እያንዳንዱ የስላሴ
አካል የሚጫወተው ሚና የተለያየ ቢሆንም እያንዳንዳቸው ለእኛ አንድ አምላክ
ናቸው፡፡ እግዚአብሄር ለእኛ ካለው ፍቅር የተነሳ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
አማካይነት ለሁላችንም እውነተኛውን የደህንነት ስጦታ ሊሰጠን ፈለገ፡፡
በእግዚአብሄር ቅድመ ውሳኔ መሠረት ይህ የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል
እግዚአብሄር በሰጠው የደህነት ተስፋ ለምናምን ሁሉ ተሰጥቶናል፡፡ እግዚአብሄር
ከዓለም ፍጥረት በፊት ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ሊያድነንና በኢየሱስ ክርስቶስ ልጆቹ
ሊያደርገን አቀደ፡፡ ይህንንም ዕቅድ ፈጸመ፡፡ ስለዚህ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት በመደምሰስ የእግዚአብሄር ልጆች
ሊያደርገን ፈቃዱ ነበር፡፡ በመሆኑም የእግዚአብሄር ፈቃድ በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል የሚያምኑትን አማኞች በሙሉ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል የራሱ ልጆች
አድርጎ መቀበልና በሰማይ ከእነርሱ ጋር አብሮ መኖር ነበር፡፡ እግዚአብሄር ይህንን
ታላቅ ዕቅድ ለመፈጸም የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለዚህ ዓለም ሰጠ፡፡
እግዚአብሄር አሁን በመገናኛው ድንኳን አደባባይ በር በታዩት በሰማያዊው፣
በሐምራዊውና በቀዩ ማግ የተገለጠውን የደህንነት እውነት ብናስተውልና ብናምን
እውነተኛውን የሐጢያቶች ስርየት እንደንቀበልና የመንግሥተ ሰማይን ክብር ሁሉ
እንድናጣጥም ያስችለናል፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምኑ ሁሉ አሁን
ከሐጢያቶቻቸው ሁሉ የሚያድናቸውን እውነት ይቀበላሉ፡፡ እግዚአብሄር
እያንዳንዱን ሐጢያተኛ ከሐጢያቶቹ ሁሉ ለማዳን የወሰነው በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል አማካይነት ነው፡፡ (1ኛ ዮሐንስ 5፡6-8) እግዚአብሄር ያቀደልን የሐጢያቶች
ስርየት ደህንነት ሙሉ በሙሉ የተወሰነው በራሱ በእግዚአብሄር ነበር፡፡
ደህንነታችን ከዓለም ፍጥረት በፊት የተዘጋጀው በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል እንደነበር

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ደህንነታችን ከዓለም ፍጥረት በፊት በኢየሱስ ጽድቅ ተዘጋጅቷል 19

እናውቃለን፡፡ ይህ ደህንነት የተገለጠውም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ነው፡፡


የእግዚአብሄር ፍቅር የተፈጸመው በመገናኛው ድንኳን አደባባይ በር ላይ
በታዩት በሰማያዊው፣ በሐምራዊውና በቀዩ ማግ አማካይነት ነበር፡፡ በመገናኛው
ድንኳን ውስጥ ያለው እያንዳንዱ ዕቃ የእግዚአብሄርን ፍቅርና የደህንነትን እውነት
ይገልጣል፡፡ በመገናኛው ድንኳን አደባባይ በር የተገለጠው እውነት እግዚአብሄር
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ለፈጸመው እውነተኛ የሐጢያቶች ስርየት ጥላ ነበር፡፡
በሌላ አነጋገር የዚህ ደህንነት እውነተኛው አካል በእግዚአብሄር አብ ዕቅድ መሠረት
በኢየሱስ ክርስቶስ ተፈጽሞዋል፡፡ እኛን ከሐጢያቶቻችን ሁሉ መታደግና
የእግዚአብሄር ሕዝብ ማድረግ የጌታ ፈቃድ ነበር፡፡ በእርግጥም በዚህ ችሮታ
መሠረት ከሐጢያቶቻችን ሁሉ አድኖናል፡፡ የእግዚአብሄር ዓላማ የተትረፈረፈውን
ፍቅሩን እንድንቀበልና የዘላለምን ሕይወት አግኝተን ለዘላለም በእርሱ እንድንደሰት
ማስቻል ነበር፡፡ እግዚአብሄር እኛን ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ለማዳን በወሰነበት በዚህ
ዓላማ መሠረት ከእያንዳንዱ ሐጢያት እንድን ዘንድ አንዳች እንዳይጎድለን ጌታ
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል አስታወቀን፡፡ የእግዚአብሄርን ፍቅርና የደህንነት
እውነት እንድንገነዘብም ባረከን፡፡ በአጭሩ እግዚአብሄር ላመጣልን ደህንነት
ለዘላለም እንድናመሰግነው አስቻለን፡፡
ችግሩ ግን አንዳንድ ሰዎች ከዓለም ፍጥረት በፊት የታቀደውን የእግዚአብሄር
ፍቅርና ዓላማ ጥያቄ ውስጥ ማስገባታቸው ነው፡፡ ሆኖም ለእያንዳንዱ ጥያቄ መልሱ
እግዚአብሄር ከምህረቱ የተነሳ ከዓለም ፍጥረት በፊት በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል
ባቀደው ደህንነት ውስጥ ይገኛል፡፡ ይህ የእግዚአብሄርን ፈቃድ ጥያቄ ውስጥ
ለሚያስገቡ ሰዎች አስቸጋሪ እንደሆነ የታወቀ ነው፡፡ ከአምላክ ዕይታ አንጻር ግን
ይህ ሙሉ በሙሉ እንከን የለሽ ነው፡፡ እኛ በሐጢያት ውስጥ ከወደቅን በኋላ
ሁላችንም ለሞት ተመድበን ነበር፡፡ ነገር ግን እግዚአብሄር ከዓለም ፍጥረት በፊት
በኢየሱስ ክርስቶስ ሊያድነን፣ የራሱ ሕዝብ ሊያደርገንና በክብሩ እንድንደሰት
ሊባርከን ወሰነ፡፡ እግዚአብሄር ይህንን ውሳኔ መወሰኑ ስህተት ነበር? የለም
አልነበረም! እኛን ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ማዳንና በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በክብሩ
መደሰት የእግዚአብሄር የፍቅር ዕቅድ ነበር፡፡ ይህ ዕቅድ በእጅጉ እንከን የለሽ ነበር፡፡
አሁንም አንዳንድ ሰዎች እግዚአብሄር ዕቅዱን ያቀደው ሰውን ሳይጠይቅ
ብቻውን ነው ብለው በመቃወም ስለ እግዚአብሄር የደህንነት ዕቅድ
የሚያጉረመርሙ ሰዎች እናያለን፡፡ እነዚህ ሰዎች እግዚአብሄር በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት የሰውን ዘር ከሐጢያቶቹና ከጥፋቱ ሁሉ ለማዳን
መወሰኑ ተገቢ አይደለም ይላሉ፡፡ እናንተ እንዲህ ዓይነት አጉረምራሚዎች ናችሁ?

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


20 ደህንነታችን ከዓለም ፍጥረት በፊት በኢየሱስ ጽድቅ ተዘጋጅቷል

እግዚአብሄር ለእናንተ ካቀደው የደህንነት ሥራ ውስጥ የማያስደስታችሁ ምንድነው?


ኢየሱስ ክርስቶስ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት ከሐጢያቶቻችሁ ሁሉ
እንዳዳናችሁ በእርግጥ የምታምኑ ከሆነ የምታጉረመርሙበት ነገር ሊኖራችሁ
አይገባም፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ውስጥ በተገለጠው ደህንነት ከሙሉ
ልባችሁ ካመናችሁ በኋላ እናንተም ደግሞ እግዚአብሄርን ታመሰግናላችሁ፡፡
እግዚአብሄር በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት እንዳዳናችሁ አንዴ
በእምነት ከተቀበላችሁ ምንም ማጉረምረም ሊኖር አይችልም፡፡

የእግዚአብሄር ፍቅር ቅዱስ የሆነ ቅንዓትን ይዞዋል፡፡

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እግዚአብሄር ብዙውን ጊዜ እንዲህ በማለት ራሱን


ቀናተኛ አምላክ አድርጎ ገልጦዋል፡- ‹‹ስሙ ቀናተኛ የሆነ እግዚአብሄር ቅንዓት
ያለው አምላክ ነውና ለሌላ አምላክ አትስገድ፡፡›› (ዘጸዓት 34፡14) የእግዚአብሄር
ቅንዓት ለእኛ ለሰዎች ያለውን ወሰን የለሽ ፍቅር የሚያብራራ ሌላ ማብራሪያ ነው፡፡
ቅዱሱ አምላካችን ከቅንዓት ፍቅሩ የተነሳ የእርሱን ሥልጣን የተቃወሙትን
መላዕክቶች በመቅጣት በአምሳሉ የፈጠራቸውን ሰዎች አዳነ፡፡ እርሱ ለእኛ ያለው
ፍቅር በጣም ጥልቅ ስለሆነ በዚህ ዓለም ላይ ማንም ሰውን ወይም ማንኛውንም
ነገር እንድንወድ አይፈቅድልንም፡፡ እግዚአብሄር በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
አማካይነት ለእያንዳንዱ ሰው እየሰጠ ያለው ደህንነት የሚገልጠው የእግዚአብሄርን
ፍቅርና ምህረት ብቻ አይደለም፡፡ ነገር ግን የእርሱ ፍቅር ምን ያህል የቀና
እንደሆነም ያሳያል፡፡
እግዚአብሄር ያዳነን በኢየሱስ ክርስቶስ ጽድቅ ነው፡፡ ለእኛ የተሰጠን ይህ
የእግዚአብሄር ፍቅር ምንም ዓይነት እንከን ሊኖረው አይችልም፡፡ ሁላችንም
ሐጢያት ውስጥ ወድቀናል፡፡ ሁላችንም በሐጢያቶቻችን ምክንያት ለሞት
ታጨተን ነበር፡፡ እንደዚያም ሆኖ እግዚአብሄር በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
አማካይነት ስላዳነን ምን ማጉረምረም ያስፈልጋል? እኛ ተራ ፍጡራኖች ስለሆንን
ያለ እርሱ ጸጋ ማናችንም የእግዚአብሄር ልጆች መሆን ባልቻልንም ነበር፡፡ ነገር ግን
እኛን የማንረባውን ሰዎች የራሱ ልጆች ሊያደርገን እግዚአብሄር ኢየሱስ ክርስቶስን
ወደዚህ ምድር ላከው፡፡ በመጨረሻም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት
አዳነን፡፡ የእግዚአብሄር ፈቃድ ይህ ነበር፡፡ እኛ በሐጢያቶቻችን ምክንያት ወደ
እግዚአብሄር መንግሥት ከመግባት ታግደን ነበር፡፡ እግዚአብሄር አብ ግን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ደህንነታችን ከዓለም ፍጥረት በፊት በኢየሱስ ጽድቅ ተዘጋጅቷል 21

በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምኑ አማኞችን ሁሉ ሐጢያት አልባ


ለማድረግና የራሱ ልጆች አድርጎ ለመቀበል የደህንነት ዕቅዱን ከዓለም ፍጥረት
በፊት አዘጋጀ፡፡ ስለዚሀ ይህ እውነት ከሆነ ከማጉረምረም ታቅበን በእግዚአብሄር
ዕቅድ ልናምንና እርሱንም አብዝተና ልናመሰግነው ይገባናል፡፡

በእግዚአብሄር ቅዱስ ቅንዓት ውስጥ ምን ተደብቋል?

በእግዚአብሄር ቅዱስ ቅንዓት ውስጥ የእርሱ ፍትህ፣ የእርሱ ደህንነትና የእርሱ


እርግማን ተደብቀዋል፡፡ በሌላ አነጋገር በኢየሱስ ክርስቶስ ጽድቅ የሚገኙት
የሐጢያቶች ስርየትና የእግዚአብሄር ፍቅር ብቻ አይደሉም፡፡ በተቃራኒው
እግዚአብሄር ሥልጣኑንና ፍቅሩን ችላ በሚሉ ላይ አስፈሪ ቁጣውን ያወርዳል፡፡
ምህረቱንም በትህትና ለሚሹት ይሰጣቸዋል፡፡ ይህም እግዚአብሄር ልዩ በረከቶቹን
እርሱን ለሚወዱ ሰዎች እንደሚሰጥ ያሳያል፡፡
እግዚአብሄር አብ በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ አማካይነት ምህረቱን ሊያሳየን
ፈለገ፡፡ ስለዚህ ጌታ ኢየሱስን ወደዚህ ምድር ላከው፡፡ ኢየሱስም በተራው
በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅ የዚህን ዓለም ሐጢያቶች በሙሉ ለአንዴና
ለመጨረሻ ተሸከመ፡፡ እነዚህን ሐጢያቶች በሙሉ ተሸክሞም በመስቀል ላይ
ሞተ፡፡ በዚህም ሁላችንንም ለዘላለም አዳነን፡፡ ከእግዚአብሄር ምህረት የፈለቀው
ቅንዓት፣ ከዚህ የቅንዓት ፍቅር የፈለቀውና በዚህ ዓለም ላይ ያለው ማንኛውም
ሰው ወይም ማንኛውም ነገር ከመፈጠሩ በፊት ከነበረው የእርሱ ምህረት ዕቅድ
የፈለቀው ቅንዓት ይህ ነው፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ ምድር በመምጣት፣ በአጥማቂው ዮሐንስ
ጥምቀትን በመቀበል፣ በመስቀል ላይ ደሙን በማፍሰስና አዳኛችን ለመሆንም
ከሙታን በመነሳት ባከናወነው የደህንነት እውነት አማካይነት እኛን ከዓለም
ሐጢያቶች ሁሉ ማዳን የእግዚአብሄር ዕቅድ ነበር፡፡ ይህ ደህንነት የተፈጸመው
የእርሱን ቅዱስ ቅንዓት፣ የእርሱን የጽድቅ ፍርድና የእርሱን ዕቅድ በያዘው
የእግዚአብሄር ፍቅር መሠረት ነው፡፡ እግዚአብሄር የሰጠን ይህ የውሃውና መንፈሱ
ወንጌል እውነት የእርሱን ፍቅርና የእርሱን ፍትህ ለሁሉም ሰው ለሚያምኑትም
ለማያምኑትም በአንድ ጊዜ ይገልጣል፡፡ እግዚአብሄር በእርሱ ፍቅር የሚያምነውንና
የሚታዘዘውን ሁሉ የራሱ ልጅ እንዲሆን ሲባርክ ሌላን ሁሉ በአለማመን ሐጢያቱ
ምክንያት በጽድቅ ይኮንነዋል፡፡ እያንዳንዱ ሐጢያተኛ የእግዚአብሄርን ቅን ብያኔ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


22 ደህንነታችን ከዓለም ፍጥረት በፊት በኢየሱስ ጽድቅ ተዘጋጅቷል

መጋፈጡና መጥፋቱ ተገቢ ነው፡፡ ስለዚህ የእግዚአብሄር ፍትህና ፍቅር


እግዚአብሄር በሰጠው ደህንነት በቁጣው ተጠናቆዋል፡፡ ይህም በኢየሱስ ክርስቶስ
በኩል የተፈጸመ ትክክለኛው የደህንነት እውነት ነው፡፡ እናንተም ይህንን ልታውቁና
ከሙሉ ልባችሁ ልታምኑበት ይገባል፡፡
ሰይጣን በትክክል ሊቀ መልአክ ነበር፡፡ ነገር ግን የእግዚአብሄርን ፈቃድ
በመቃወሙ እግዚአብሄር ከሰማይ ጣለው፡፡ ስለዚህ ዲያብሎስ ለዘለላለም
በጉስቁልና ከመሰቃየት በቀር ምርጫ አልነበረውም፡፡ በአንጻሩ ሰዎች አሁንም
ደህንነትን ሊያገኙ ይችላሉ፡፡ ምክንያቱም እግዚአብሄር በዚህ ዓለም ላይ የሚኖር
ሰው ሁሉ ከሐጢያቶቹ ሁሉ እንዲድን የደህንነት ሕግ አቁሞዋልና፡፡ ወደ ኢሳይያስ
14፡12 ስንመለስ እግዚአብሄር ሰይጣንን እንዲህ ሲለው እናያለን፡-
‹‹አንተ የንጋት ልጅ አጥቢያ ኮከብ ሆይ እንዴት ከሰማይ ወደቅህ! አህዛብንም
ያዋረድህ አንተ ሆይ እንዴት እስከ ምድር ድረስ ተቆረጥህ!›› እግዚአብሄር አምላክን
የተቃወመውን መልአክና የእርሱን ተከታዮች በሙሉ ሲገስጽ በዕብሪታቸው
ምክንያት በሁሉም ላይ እንደሚፈርድባቸው ተናግሮዋል፡፡ አሁንም ቢሆን
በእግዚአብሄር ላይ ያመጸው መልዓክ ሰውን ሁሉ ከእግዚአብሄር ለማራቅ
በመሞከር ሥራ በዝቶበታል፡፡ ሰይጣን እንዲህ የእግዚአብሄርን ሥልጣን
ከተቃወመ በኋላ ኩራቱ በእግዚአብሄር ፊት በመጋለጡ የአምላክ ጠላት ሆነ፡፡
በሒደትም ዲያብሎስ የእግዚአብሄርን ጽድቅ ኩነኔ ጠየቀ፡፡ በኢሳይያስ 14፡13-14
ላይ እንዲህ ተጽፎዋል፡-
‹‹አንተም በልብህ ወደ ሰማይ ዐርጋለሁ፤ ዙፋኔንም ከእግዚአብሄር ከዋክብት
በላይ ከፍ ከፍ አደርጋለሁ፤ በሰሜንም ዳርቻ በመሰብሰቢያ ተራራ ላይ
እቀመጣለሁ፤ ከዳመናዎችም ከፍታ በላይ ዐርጋለሁ፤ በልዑልም እመሰላለሁ
አልህ፡፡›› ሉሲፈር የእግዚአብሄርን ቅን ፍርድ የተቀበለበት ምክንያቱ ይህ ነው፡፡
እግዚአብሄር ያ ፍጡር ምንም ይሁን የእርሱን ሥልጣን የሚቃወመውን
ማንኛውንም ፍጡር ፈጽሞ አይታገሰውም፡፡ ከዚህ በራቀ መልኩ እግዚአብሄር
ክፋትንና መተላለፎችን በሙሉ ይቀጣል፡፡ የእግዚአብሄር የፍትህ ብያኔ ለማንም
ሰው የሚያዳላ አይደለም፡፡ ነገር ግን ትክክለኛ ነው፡፡ እግዚአብሄር የፈጠረው
ፍጡር አቋሙን ረስቶ የእግዚአብሄርን ሥልጣን የሚቃወም ከሆነ ፈጣሪ አምላክ
እንዲህ ያለውን ብልሹና ዕብሪተኛ ፍጡር በመቅጣቱ ስህተቱ ምን ላይ ነው?
እግዚአብሄር እነዚህን ዓመጸኛ ፍጡራኖች መቅጣቱ ተገቢና ትክክል ነው፡፡ ነገር
ግን የእግዚአብሄርን ሥልጣን የተቃወመው መልአክ አሁንም ቢሆን በዚህ ዓለም
ሰዎች አስተሳሰቦች ውስጥ በሕይወት አለ፤ ደህናም ነው፡፡ ደህንነትን ለማግኘት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ደህንነታችን ከዓለም ፍጥረት በፊት በኢየሱስ ጽድቅ ተዘጋጅቷል 23

በገዛ ሥራዎቻቸው ላይ እንዲደገፉ በማሳሳት የእግዚአብሄርነን ፍቅር


እንዲቃወሙና ጸጋውን እንዲንቁ ያነሳሳቸዋል፡፡ በጣም ብዙ ሰዎችም በዚህ
በወደቀው መልአክ ተታልለው የእግዚአብሄርን ፍቅር እየናቁ ነው፡፡ በዚህ
ምክንያት እግዚአብሄር ከእርሱ ፍቅር በራቁት ሰዎች ሁሉ ራስ ላይ ፍምን እያከማቸ
ነው፡፡ ይህ የእግዚአብሄርን ቅን ፍርድ፤ የእርሱን ፍቅር ለናቀ ለእያንዳንዱ ሰው
እጅግ ተገቢ ቅጣት ነው፡፡
እናንተና እኔ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ስለሰጠንና በእምነት ወደዚህ
የደህንነት ወንጌል ውስጥ እንድንገባ ስለባረከን እግዚአብሄርን ልናመሰግነው
ይገባናል፡፡ እግዚአብሄር ለእኛ የደህንነት ዕቅድ ባይኖረው ኖሮ በዕብሪቱ ምክንያት
ጥፋት የሚጠብቀው ያ የወደቀው መልአክ በሚገኝበት ተመሳሳይ የጉስቁልና ሁኔታ
ውስጥ በተገኘን ነበር፡፡ ሰይጣን በዚህ ዓለም ላይ መኖሩ ብቻ ሳይሆን ከእርሱ ጋር
አብሮ እግዚአብሄርን የሚቃወመውን ማንኛውንም ሰው አንድ ላይ በመሰብሰብ
መጨረሻ ላይ የሚጠፋ በመሆኑ ያለ እግዚአብሄር ጸጋ እኛም ደግሞ ለዘላለም
ለመሰቃየት በዲያብሎስ ወጥመድ ውስጥ ተጠምደን እንቀር ነበር፡፡ ነገር ግን
እግዚአብሄር አልተወንም፡፡ በብዙ ስለራራልን ወደ ፍቅሩ እንድንገባ ባረከን፡፡
የውሃወንና የመንፈሱንም ወንጌል ሰጠን፡፡ ከሐጢያቶቻችን ሁሉ አዳነን፤ ጠበቀን፤
ሠራተኞቹም አድርጎ ተጠቀመብን፡፡ ስለዚህ እናንተና እኔ በዚህ የእግዚአብሄር
ፍቅር ስለምናምን ሁላችንም የእግዚአብሄርን ልዩ ፍቅርና ምህረት ለብሰናል፡፡
በአንጻሩ የእግዚአብሄርን ምህረት ያላገኙ ሰዎች ይኮነናሉ፡፡ እነርሱ አሁንም
በእምነት አልባነታቸው እግዚአብሄርን እየታቀወሙት ነው፡፡ ከሐጢያቶቻቸው
ሁሉ ሊያድናቸው የሚችለውን የእግዚአብሄር ጸጋ ስላላገኙ የሚጠብቃቸው ነገር
ቢኖር ምህረት አልባ የሆነ የእግዚአብሄር ቅን ፍርድ ነው፡፡
እግዚአብሄር የወደቀውን መልአክና ክፉዎቹን ተከታዮች ስለ
ሐጢያቶቻቸው ሊቀጣቸው ለያቸው፡፡ ይህ የእኛም ደግሞ ዕጣ ፋንታ ነው፡፡
ስለዚህ ኢየሱስ ክርስቶስ ሁላችንንም ባዳነበት በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
በማመን ከዚህ ቅጣት ማምለጥ ነበረብን፡፡ የእግዚአብሄርን የምህረት ፍቅር
ለመቀበልና አዲስና የዘላለም ሕይወት ለማግኘት በዚህ የውሃውና የመንፈሱ
ወንጌል ማመን ይኖርብናል፡፡ በአምላክ ታላቅ ምህረትና በፍቅሩ ስለምናምን
እግዚአብሄር ለዘላለም ከሐጢያቶቻችን ኩነኔ ታድጎን አዲስና የዘላለም ሕይወት
ሰጥቶናል፡፡ የእግዚአብሄር ምህረት ስለበዛልንም በኢየሱስ ክርስቶስ ውስጥ
በሚገኘው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምን እምነት በመስጠት ዘላለማዊ
ደህንነታችንን ለግሶናል፡፡ ሁላችንም እግዚአብሄርን ማመስገን የሚገባን ለዚህ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


24 ደህንነታችን ከዓለም ፍጥረት በፊት በኢየሱስ ጽድቅ ተዘጋጅቷል

ነው፡፡ እግዚአብሄርን እንድታከብሩ በሚያስችላችሁ የእውነት ቃል ማለትም


በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ገና በእምነት ካልገባችሁ አሁኑኑ ወደዚህ ሕይወት
ወደሚሰጥ ወንጌል መምጣት አለባችሁ፡፡ ከሐጢያቶቸችሁ ሁሉ መዳን
የምትችሉት በእግዚአብሄር ፍቅር በማመን ብቻ ስለሆነ አሁን በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል ማመን አለባችሁ፡፡
እግዚአብሄር ልጆቹ ሲያደርገን በምህረቱ፣ በፍቅሩና በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል ቃሉ እንደምናምን አይቷል፡፡ እግዚአብሄር ይህን ወንጌል በመታዘዛችን
ልጆቹ አድርጎ ሊቀበለን የወሰነው ለዚህ ነው፡፡ ይህ እግዚአብሄር የሰጠው
የሐጢያቶች ስርየት ደህንነት ከእግዚአብሄር ስጦታዎች እጅግ ታላቁ ስጦታ ነው፡፡
ስለዚህ ሁላችንም ከልባችን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ማመናችን በእጅጉ
ያስፈልገናል፡፡ ይህ የሐጢያቶች ስርየት ስጦታ ከጥረታችን ውጪ በነጻ የተሰጠን
የደህንነት ስጦታ ነው፡፡ እግዚአብሄር ልጆቹ ያደረገንም በዚህ እውነት ነው፡፡
ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ለመዳን ውጥኖቻችንንና በጎ ምግባሮቻችንን መተውና
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ብቻ ማመን አለብን፡፡ የሐጢያቶቻችንን ስርየት
መቀበል የቻልነው እግዚአብሄር ባቀደው ደህንነት በማመን ብቻ ነው፡፡
ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ሊያድነን የቻለው የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ብቻ ነው፡፡
ስለዚህ ሁላችንም በዚህ ወንጌል ማመን መምረጥ አለብን፡፡ ልክ እንደዚሁ
በኢየሱስ እንደሚያምን የሚናገር ሁሉ እውነተኛ ደህንነትን ማግኘት የሚችለው
በጌታ የምህረት ፍቅር በማመን ብቻ ነው፡፡
የዘመኑን ክርስትና ስንመለከት ከዓለም ብዙ ሐይማኖቶች ወደ አንዱ
እንደተለወጠ ማየት እንችላለን፡፡ የሁሉም ሰው ሰራሽ ሐይማኖቶች አንድ ጋራ
ባህርይ ሁሉም በሰዎች አስተሳሰቦች ላይ መደገፋቸውና ደህንነትን ለማግኘትም
በራስ ላብና ጥረት መታመናቸው ነው፡፡ መሠረተ ቢስ የሆኑ የክርስቲያን
ትምህርቶች ከዚህ ምልከታ ውጪ አይደሉም፡፡ በአሁኑ ጊዜ አብዛኞቹ ክርስቲያኖች
በራሳቸው ጽድቅ ምክንያት የሰማይን መንፈሳዊ በረከቶች አልተቀበሉዋቸውም፡፡
የዘመኑ ክርስትና ወደ አንድ ተራ ዓለማዊ ሐይማኖት የዘቀጠበትን ምክንያት ስናስብ
ብዙ ክርስቲያኖች ራሳቸው በራሳቸው አስተሳሰቦች መሰረት በራሳቸው ጥረት
ደህንነት ላይ ለመድረስ ስለሚሞክሩ መሆኑን ማየት እንችላለን፡፡ ዛሬ በክርስቲያን
ማህበረሰቦች ውስጥ እንደዚህ የገነኑት የሐሰት ትምህርቶች ክርስቲያን ‹‹መሪዎች››
ተብለው በሚጠሩት የተስፋፉ ናቸው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ደህንነታችን ከዓለም ፍጥረት በፊት በኢየሱስ ጽድቅ ተዘጋጅቷል 25

ከእነዚህ የክርስቲያን ትምህርቶች በሒደት የሚገኝ ቅድስና ትምህርት


በግብዝነት የተሞላ ነው፡፡

በሒደት የሚገኝ ቅድስና ትምህርት በታወቁ ቤተክርስቲያኖች መካከል


በጣም ተጽዕኖ ፈጣሪ ትምህርት ነው፡፡ ነገር ግን አቀንቃኞቹ ይህ ትምህርት
በትክክል እግዚአብሄርን የሚቃወም ብልሹ ትምህርት እንደሆነ ያውቃሉ ይህንን
በተጭባጭ የሚያውቁት ጥቂት ሰዎች ናቸው፡፡ ነገር ግን የዚህ ዓይነቱ መጽሐፍ
ቅዱሳዊ መሠረት የሌለውን ትምህርት ማዘጋጀትና ማስተማር የእግዚአብሄርን
ቅድስና የተቃወሙትን የወደቁ መላዕክቶች መምሰል ነው፡፡ የታዋቂው ክርስትና
ብዙ ትምህርቶች ራሳቸው የእግዚአብሄርን የምህረት ፍቅር የሚያዳክሙ ናቸው፡፡
ማንኛውንም ሰው ሰራሽ ዶግማ ከማመን ይልቅ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
ማመን ያለባችሁ ለዚህ ነው፡፡ ክርስቲያኖች ያልሆኑ ሰዎች ብህትውናን ቢተገብሩና
ራሳቸውን ያለ መታከት ቢገሩ መለኮተዊ ደረጃ ላይ መድረስ እንደሚችሉ ያስባሉ፡፡
በተመሳሳይ ሁኔታ በሒደት የሚገኝ ቅድስና ትምህርትም እንደዚሁ ሰው በራሱ
በጎነት አማካይነት ራሱን ሊቀድስ እንደሚችል ያስተምራል፡፡ ነገር ግን እዚህ ላይ
ይህ የእግዚአብሄርን ቅድስና የመቃወም አስከፊ ሐጢያት እንደሆነ በግልጥ
ልትገነዘቡ ይገባችኋል፡፡ ይህ ሆኖ እያለ በጣም ብዙ ክርስቲያኖች በራሳቸው ውሳኔ
የእግዚአብሄርን ቅድስና ይቃወማሉ፤ ነገር ግን አይሳካላቸውም፡፡
ሰዎች ሁሉ በእናታቸው ማህጸን ከተጸነሱበት ቅጽበት ጀምሮ አስራ ሁለት
ዓይነት ሐጢያቶችን የወረሱ የክፉ አድራጊ ዘሮች ስለሆኑ ሁሌም ሐጢያትን
ይሰራሉ፡፡ ስለዚህ ሰዎች በተፈጥሮዋቸው ሐጢያተኞች ስለሆኑ ራሳቸውን
ለመቀደስ አብዝተው በሞከሩ መጠን አብዝተው ግብዞች ይሆናሉ፡፡ ክፋታቸውም
አብዝቶ ይገለጣል፡፡ ሰዎች ከሐጢያቶቻቸው ሁሉ መንጻትና ቅዱሳን መሆን
የሚችሉበት ብቸኛው መንገድ እነርሱ ራሳቸው ፈጽሞ ሐጢያተኞችና ለሲዖል
የታጩ መሆናቸውን ለእግዚአብሄር በማመን የሐጢያቶች ስርየት ጸጋ በሆነው
የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል በማመንና የእግዚአብሄርን ምህረት በማግኘት ነው፡፡
ሁላችንም ይህንን እውነት መረዳት አለብን፡፡
አንዳንዶቻችሁ አንድ የሐይማኖት ሰው የሆነ ዓይነት መረዳት ላይ ለመድረስ
ዓይኖቹን ጨፍኖ ሲያሰላስል አይታችሁ ይሆናል፡፡ ለምሳሌ ያህል ቡድሃን ውሰዱ፡፡
ቡድሃ ከአንድ ዛፍ በታች ሆኖ በማሰላሰል ራሱን ለመርሳትና ብቻውን ኒርቫና
(ብጽዕና) ላይ ለመድረስ ሲሞክር የነበረ ሰው ነው፡፡ ነገር ግን በመጨረሻ ከዛፉ
ሥር ሞተ፡፡ ሆኖም ሰዎች ቡድሃ ታላቅ ሰው እንደነበረ ከማሰባቸውም በላይ እንደ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


26 ደህንነታችን ከዓለም ፍጥረት በፊት በኢየሱስ ጽድቅ ተዘጋጅቷል

አንድ ትልቅ ጠቢብ ሰው ከፍታ ላይ አስቀምጠውታል፡፡ ብዙዎችም የእርሱ


ተከታይ መሆንን መርጠዋል፡፡ ቡድሃ እንደ አምላክም ደግሞ ክብር ተሰጥቶታል፡፡
የዓለም ሐይማኖት ከንቱነት ይህን ያህል ነው፡፡
የእያንዳንዱ ሰው መሠረታዊ ፍላጎት ከሐጢያቶቹ ሁሉ ማምለጥና ፍጹም
ወደሆነው የእግዚአብሄር ጽድቅ ላይ መድረስ ነው፡፡ ነገር ግን ችግሩ አብዛኛው
ሕዝብ ከእግዚአብሄር ጽድቅ ይልቅ የራሳቸውን ጽድቅ ለማቆምና አብዝተው
ለማክበር የሚሞክሩ መሆናቸው ነው፡፡ የሰው ጽድቅ ግን ፈጽሞ ከንቱ ነው፡፡
የቡድሃ ተከታዮች የሚናገሩለት የብጽዕና እሳቤ ከዓለማዊ ጭንቀቶች፣ መከራዎችና
ባርነቶችች ነጻ ስለ መውጣት የሚናገር ነው፡፡ ነገር ግን እዚህ ላይ ለመድረስ
ብቸኛው መንገድ ሞት ብቻ ነው፡፡ ከመካከላችን ራሱን ከሐጢያቶቹ ሁሉ ነጻ
ማድረግና ፍጹም ሰው መሆን የሚችል ማነው? ማናችንም ኢየሱስ ክርስቶስ
ከአጥማቂው ዮሐንስ በተቀበለው ጥምቀት፣ በመስቀል ላይ ሞቱና በትንሳኤው
እስካላመነን ድረስ ከሰይጣን ጭብጥ አርነት መውጣት አንችልም፡፡ በእርግጥም
እያንዳንዱ ሐጢያተኛ ኢየሱስ በሰጠው እውነተኛ የውሃና የመንፈስ ወንጌል
በማመን ከሐጢያቶቹ ሁሉ መንጻትና ደህንነትን ማግኘት አለበት፡፡
ሆኖም በክርስቲያን ማህበረሰቦችም ውስጥ እንኳን ክርስትና ከአረማዊ
ሐይማኖቶች አንዱ የሆነ ይመስል በርካታ ሰዎችን በሒደት በሚገኝ ቅድስና
ትምህርት የሚያሳስቱ ብዙ ሐሰተኛ ነቢያቶች አሉ፡፡ ሆኖም ጠንክሮ በመሞከር
ሙሉ በሙሉ ቅዱስ ሆኖ መለወጥ የሚችል ሰው አለ? እንደሌለ የታወቀ ነው!
ክርስቲያኖች በሒደት የሚገኝ ቅድስና ትምህርት አቀንቃኞች በእርግጥም
በሐጢያቶቻቸው እያሰሩዋቸው እንደሆነ ሊገነዘቡ ይገባቸዋል፡፡ በቅን ልቦናም
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል እውነት ማድመጥ ከሐሰተኛ ትምህርቶቻቸው ሁሉ
መመለስና የሐጢያቶቻቸውን ስርየት መቀበል አለባቸው፡፡ አለበለዚያ ክርስትና
ሙሉ በሙሉ በተበላሸው አረማዊ ሐይማኖት ውስጥ ሲዘቅጥ በራሳቸው ዓይኖች
ይመለከታሉ፡፡
በእግዚአብሄር ጽድቅ የተፈጸመው ትክክለኛ ወንጌል የውሃውና የመንፈሱ
ወንጌል ነው፡፡ ይህ ወንጌል የእግዚአብሄርን እውነተኛ ፍቅርና የደህንነት እውነት
ይዞዋል፡፡ ነገር ግን ችግሩ ብዙ ክርስቲያኖች አሁንም በሰዎች አስተሳሰቦች
የተፈጠሩትን እነዚህን ሐሰተኛ ትምህርቶች ማመናቸው ነው፡፡ እነዚህን አስመሳይ
ዶግማዎች በማመን እግዚአብሄርን መከተላቸው ፈጽሞ ትክክል እንደሆነ ያስባሉ፡፡
ሁላችንም አሳምረን እንደምናውቀው እያንዳንዱ አረማዊ ትምህርት የፈለቀው
ከሰው አስተሳሰቦች ነው፡፡ እያንዳንዱ የክርስቲያን ትምህርትም ከዚህ ውጪ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ደህንነታችን ከዓለም ፍጥረት በፊት በኢየሱስ ጽድቅ ተዘጋጅቷል 27

አይደለም፡፡ ለምሳሌ እያንዳንዱ አረማዊ ሐይማኖት ተከታዮቹን በጥረቶቻቸው


አማካይነት ደህንነትን ያገኙ ዘንድ እንደሚያስተምር ሁሉ በሒደት የሚገኝ የቅድስና
ክርስቲያናዊ ትምህርትም እንደዚሁ ክርስቲያን ሐጢያተኞችን በሙሉ ብቻቸውን
ደህንነትን ለማግኘት ራሳቸውን እንዲያነጹ ያስተምራቸዋል፡፡ ከዚህ የተነሳ በአሁኑ
ጊዜ በርካታ ክርስቲያኖች በራሳቸው መንገዶች ራሳቸውን ለመቀደስ ከንቱ በሆነ
ሙከራ የተሳሳተ የእምነት ሕይወትን እየኖሩ ነው፡፡ እነዚህ የተሳሳቱ ክርስቲያኖች
ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ባፈሰሰው ደም ብቻ በማመን ከሐጢያቶቻቸው
ሁሉ እንደዳኑ እርግጠኞች ናቸው፡፡ ሕይወታቸውን ለዚህ ከንቱ፣ ለዚህ የሐሰት
እምነት አሳልፈው ሰጥተዋል፡፡ በሒደት የሚገኘውን ቅድስና ትምህርት
በመከተላቸው ምን ያህል ታላቅ እንደሆኑ ይመጻደቃሉ፡፡ የራሳቸውን ነፍስና
የሌሎችን ነፍስ ለማረጋጋት ራሳቸው የፈጠሩትን ይህንን ትምህርት እንደ መንፈሳዊ
ሽፋን ይጠቀሙበታል፡፡ ነገር ግን በሒደት የሚገኘውን የቅድስና ትምህርት
በማመንና በመተግበር ብቻ ቅድሰና ላይ የደረሰ ሰው የለም፡፡

ፈላስፎች የመጽሐፍ ቅዱስን ቃል የሚመለከቱት እንዴት ነው?

ዓለማዊ ፈላስፎች የእግዚአብሄርን ጽደቅ ሙሉ በሙሉ ችላ በማለታቸው


የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል እውነት በጭራሽ ከእግዚአብሄር ቃል መረዳት
አልቻሉም፡፡ እነዚህ ፈላስፎች በመሠረቱ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል መረዳት
የሚችሉ አይደሉም፡፡ መጽሐፍ ቅዱስን በራሳቸው አስተሳሰቦች የሚተረጉሙትና
ራሳቸው የፈጠሩዋቸውን ሐሰተኛ ትምህርቶች የሚያቀነቅኑት ለዚህ ነው፡፡
ፈላስፎች መጽሐፍ ቅዱስን ሲያነቡ ለራሳቸው ‹‹ኦ ስለዚህ ሰማይንና ምድርን
የፈጠረው እግዚአብሄር ነው፡፡ ፈጣሪ መኖር አለበት፡፡ ይህ ፈጣሪም ሕግን
አውጥቷል፡፡ ፈጣሪ ሐጢያተኞችን ከሐጢያቶቻቸው ሁሉ ለማዳን ይህችንም
ምድር ለማዳን ተስፋ ሰጠ፡፡ እርሱ የእያንዳንዱን ሰው ሐጢያቶች ለመደምሰስ
ይሰቀል ዘንድ ስጋውን ለመስቀል አሳልፎ ሰጠ፡፡ ደሙንም አፍሰሶ ሞተ፡፡
ከሙታንም ተነሳ፡፡ ወደ ሰማይም አረገ›› ብለው ያስባሉ፡፡ መጽሐፍ ቅዱስን በዚህ
መልኩ ራሳቸው በመተርጎም የራሳቸውን ትምህርቶች በመፍጠር ሰው ሁሉ
ትምህርቶቻቸውን እንዲያስፋፋላቸው ይነግሩታል፡፡ በዚህ ምክንያት ብዙ ሰዎች
የመስቀሉን ደም ብቻ ደህንነታቸው አድርገው በማመን ብቻ የእግዚአብሄር ልጆች
መሆን እንደሚችሉ ያስባሉ፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


28 ደህንነታችን ከዓለም ፍጥረት በፊት በኢየሱስ ጽድቅ ተዘጋጅቷል

እነዚህ ፈላስፎች መጽሐፍ ቅዱስን ሲያነቡና ኢየሱስን አዳኛቸው አድርገው


ሲያምኑ እንደዚያ የሚያደርጉት በራሳቸው አስተሳሰቦችና ትርጓሜዎች መሠረት
ነው፡፡ እንዲያውም በዘመኑ ክርስትና ውስጥ የገነኑት ትምህርቶች በሙሉ
የተፈጠሩት በእነዚህ ፈላስፋ ቀመስ የእግዚአብሄር ምሁራኖች ነው፡፡ እነርሱ
የፈጠሩዋቸው እነዚህ የክርስቲያን ትምህርቶች ትርጉም ቢሰጡዋቸውም መጽሐፍ
ቅዱስ እውነተኛ ወንጌል እንደሆነ ከሚናገርለት የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል
በእጅጉ ርቃዋል፡፡ ነገር ግን እነዚህ ፈላስፎች የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
ሳያውቁ ቅዱሳት መጽሐፍትን ስለሚተረጉሙ ‹‹ኦ መዳን በጣም ቀላል ነው፡፡
በመስቀሉ ደም በማመን ብቻ መዳን እንችላለን፡፡ ያ በቂ ነው፡፡ አዎ፤ ኢየሱስ
ክርስቶስ አዳኛችን ነው፡፡ እርሱ ለእኛ መልካም የሆነልን የእግዚአብሄር አብ ልጅ
ነው›› በማለት ራሳቸው ያበጁዋቸውን ትምህርቶች ለሰው ሁሉ ያቀነቅናሉ፡፡ ነገር
ግን ትክክለኛውን የደህንነት እውነት ለማንኛወም ሰው አያስተምሩም፡፡
እነዚህ ፈላስፋ ቀመስ የቃለ እግዚአብሄር ምሁራን በራሳቸው አስተሳሰቦች
መሰረት በሒደት የሚገኘውን የቅድስና ትምህርት ካበጁ በኋላ ‹‹በተጨባጭ
ሊጮህልኝ የሚችል ማነው? ከእኔ ጋር ልትመላለሱ የምትችሉት እንዴት ነው?
በዚህ ምድር ላይ ከኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ማን ሞተልኝ?›› በማለት ሰውኛ
ትምህርቶቻቸውን እያስፋፉ ነው፡፡ የእነርሱ ክርስቲያናዊ ፍልስፍና የሐጢያተኞችን
ስሜቶች ለማነሳሳት በቂ ነው፡፡ ኢየሱስ ለእነርሱ ሲል እንዴት ራሱን መስዋዕት
እንዳደረገ ሲያስቡ ልባቸው ስለሚነካ ወዲያውኑ ዕንባዎቻቸውን ያፈስሳሉ፡፡
‹‹በዚህ ዓለም ላይ እንኳን ሊሞትልኝ ቀርቶ ለእኔ አንዲት ሰዓት እንኳን የሰጠኝ
ሰው የለም፡፡ ኢየሱስ ግን ለእኔ በመሰቀልና ደሙን በማፍሰስ ከሐጢያቶቼ ሁሉ
ሊያነጻኝ ሞተ፡፡ ታዲያ ለምን በዚህ ስሜቴ ላይነካ ይችላል?›› ይላሉ፡፡
ከተለያዩ የክርስቲያን የቤተክርስቲያን ድርጅቶች ውስጥ የተለያዩ ፍልስፍናዊ
ትምህርቶች ቢመነጩም በርካታ ሰዎች አሳስቶ ወደ ጥፋት የነዳ ለሁሉም የጋራ
የሆነ አንድ ትምህርት አለ፡፡ ይህም ሰው በኢየሱስ የመስቀል ላይ ደም በማመን
ብቻ ይድናል የሚለው የተሳሳተ እሳቤ ነው፡፡ የዘመኑ የተሳሳቱ ክርስቲያኖች ኢየሱስ
ለእነርሱ ደሙን ማፍሰሱ አሳዛኝና አጽናኝ ሆኖላቸዋል፡፡ ነገር ግን እምነታቸው
ሐጢያቶቻቸውን አልደመሰሰላቸውም፡፡ በርካታ የንስሐ ጸሎቶችን ቢያቀርቡም
እንኳን ሐጢያቶቻቸው በውስጣቸው ስላሉ ገና ቅድስና ላይ መድረስ አይችሉም፡፡
አሁንም እንኳን የሐጢያቶቻቸው ስርየት አድርገው የሚያምኑት ኢየሱስ በመስቀል
ላይ ያፈሰሰውን ደም ነው፡፡ በልቦቻቸው ውስጥ ግን ብዙ ተጨማሪ ሐጢያቶችን
እያከማቹ ነው፡፡ እነርሱ እውነተኛውን ክርስትና ወደ አረማዊ ሐይማኖት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ደህንነታችን ከዓለም ፍጥረት በፊት በኢየሱስ ጽድቅ ተዘጋጅቷል 29

ለውጠውታል፡፡
ብዙ ሰዎች እነዚህን ፍልስፍናዊ የሆኑ የክርስቲያን ትምህርቶች የሙጥኝ
ብለው በመያዝ ነፍሳቸውን እያጠፉ ነው፡፡ ምክንያቱም ፍልስፍናዊ እምነታቸው
ትክክለኛ እምነት እንደሆነ ያስባሉና፡፡ በራሳቸው አስተሳሰቦች መሠረት በኢየሱስ
ቢያምኑም ጥሩ ክርስቲያኖች ለመሆናቸው እርግጠኞች ናቸው፡፡ ስለ ኢየሱስ ደም
ሲያስቡ ስሜታቸው ይነካል፡፡ ይህንን በጥልቀት ባሰላሰሉ ቁጥርም ሌላው ሰው
ሁሉ ጥሩ ክርስቲያኖች መሆናቸውን እንዲደግፍላቸው አብዝተው ይሻሉ፡፡ ነገር
ግን በተጨባጭ ሰው ሰራሽ ትምህርቶችን እያሰራጩ ባሉት በእነዚህ ክርስቲያን
‹‹መሪዎች›› ተብዬዎች በተፈጠረው ግራ መጋባት ምክንያት ሐሰተኛና በስሜት ላይ
በተመሰረተ እምነት ውስጥ ጠልቀው እየገቡ ነው፡፡ እነዚህ በተሳሳቱ የክርስቲያን
ትምህርቶች የተጠመዱ ሰዎች የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል እውነት አብዝተው
ይቃወማሉ፡፡ እነዚህ የታዋቂው ክርስትና ሐሰተኛ ትምህርቶች ፈላስፋ ቀመስ ከሆኑ
የቃለ እግዚአብሄር ምሁራን አስተሳሰቦች ውስጥ የፈለቁ ናቸው፡፡ እነርሱ የዘሩት
ሎጂክ ያፈራው ነገር ቢኖር ግራ የተጋቡ የክርስቲያን ትምህርቶችን ብቻ ነው፡፡
በአንጻሩ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምን ሁሉ የጠፋውን
የእግዚአብሄር መንጋ ከልቡ ይሻል፡፡ እያንዳንዱ ሰው የሚሻው እውነተኛ ደህንነት
የሚገኘው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን ብቻ ነው፡፡ ሁሉም ሰው በዚህ
እውነተኛ ወንጌል በማመን ሐጢያቶቹን በሙሉ ማንጻት ይችላል፡፡ ስለዚህ
እያንዳንዱ ክርስቲያን ሐጢያተኛ በተቻለ ፍጥነት ወደ ውሃውና መንፈሱ ወንጌል
መመለስ አለበት፡፡
ይህንን ችግር እንዴት እንደምትፈቱት ሳታውቁ ቀርታችሁ በሐጢያቻችሁ
ተቸግራችኋልን? እንደዚያ ከሆነ በመጀመሪያ በኒው ላይፍ ሚሽን የተታተመውን
በውኑ በውሃውና በመንፈሱ ዳግመኛ ተወልዳችኋልን? የሚለውን የክርስቲያን
መጽሐፋችንን እንድታነብቡ እጠይቃችኋለሁ፡፡ ይህ መጽሐፍ ወደ ውሃውና
መንፈሱ ወንጌል እንደዚሁም ወደ እውነተኛው የደህንነት መንገድ ይመራችኋል፡፡
አሁን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል አታውቁትምን? አሁንም ለራሳችሁ
‹‹እንደ ሐጢያት ችግር ያለውን ይህንን ትንሽ ችግር መፍታት ያልቻልሁት
ለምንድነው? እኔ ማድረግ የምፈልገው ነገር ቢኖር ኢየሱስ በመስቀል ላይ ባፈሰሰው
ደም ብቻ በማመን የአዳም ሐጢያቴን ስርየት መቀበልና ከዚያም በየቀኑ የንስሐ
ጸሎቶቼን በማቅረብ የግል ሐጢያቶቼን ማስወገድ ነው›› ትላላችሁን? ብዙ
ክርስቲያኖች በየቀኑ የንስሐ ጸሎቶቻቸውን በማቅረብ የዘወትር ሐጢያቶቻቸውን
ማንጻት እንደሚችሉ ይናገራሉ፡፡ ነገር ግን እንደዚህ የምታስቡና የምታምኑ ከሆነ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


30 ደህንነታችን ከዓለም ፍጥረት በፊት በኢየሱስ ጽድቅ ተዘጋጅቷል

በጭራሽ ሐጢያቶቻችሁን ማንጻት አትችሉም፡፡ አሁን የምታምኑት በመስቀሉ ደም


ብቻ ሊሆን ይችላል፤ በእርግጥ ከሐጢያቶቻችሁ አንዱ እንኳን ተወግዶዋልን?
አሁን እያቀረባችኋቸው ያላችኋቸው የንስሐ ጸሎቶች የግል ሐጢያቶቻችሁን
በሙሉ ማስወገድ ችለው ቢሆን ኖሮ የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ባላስፈለገም
ነበር፡፡ ነገር ግን ቢያንስ በልቦቻችሁ ውስጥ ጥቂት ሐጢያቶች መቅረታቸው
እውነት አይደለምን? ሐጢያቶቻችሁ አሁንም መኖራቸው ትክክለኛ የደህንነት
እውነት የሆነው የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል በእጅጉ የሚያስፈልጋችሁ ለዚህ
እንደሆነ ግልጥ ነው፡፡ ልታምኑበት የሚገባችሁ እውነተኛው ወንጌል ሌላ ሳይሆን
የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ነው፡፡
ታዲያ ከሙሉ ልባችሁ የምታምኑት ምንድነው? ሰው ሰራሽ በሆኑት
አንዳንድ ፍልስፍናዊ የክርስቲያን ትምህርቶች ታምናላችሁ? ወይስ በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት የተገለጠውን የሐጢያቶች ስርየት እውነት
ታምናላችሁ? የምታምኑትን ማንኛውንም ነገር መምረጡ ሙሉ በሙሉ የእናንተ
ጉዳይ ነው፡፡ ምርጫው የሌላ የማንም ሰው ሳይሆን የእናንተ ብቻ ነው፡፡ ነገር ግን
አንዳች ውሳኔ ከመወሰናችሁ በፊት በየቀኑ የንስሐ ጸሎቶችን በማቅረብ
ከሐጢያቶቻችሁ አንዱንም በጭራሽ ማንጻት እንደማትችሉ በግልጥ መረዳት
ይገባችኋል፡፡ በመገናኛው ድንኳን በርና በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ውስጥ
በተገለጠው የሐጢያቶች መንጻት እውነት ማመን አለባችሁ፡፡
በጣም ብዙ ክርስቲያኖች በራሳቸው ፍልቅ ስሜቶችና የተሳሳቱ አመኔታዎች
ውስጥ ጠፍተው የጥምቀቱን ሐይልና ምስጢር ሳያውቁ እምነታቸውን ሁሉ
ኢየሱስ በመስቀል ላይ ባፈሰሰው ደም ብቻ ላይ አኑረዋል፡፡ አሁን ግን እንዲህ
ያሉትን መሠረተ ቢስ አመኔታዎች መጣል፣ በምትኩም በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ
በተገለጠው የውሃና የመንፈስ ወንጌል ማመንና በዚህም ከሐጢያቶቻችሁ ሁሉ
ነጽታችሁ የዘላለምን ሕይወት መቀበል አለባችሁ፡፡ ያን ጊዜ የሐጢያቶች ስርየት
ወደ ልባችሁ ውስጥ ሲገባ ትለማመዳላችሁ፡፡
አንዳንድ ክርስቲያኖች ‹‹ተመልከቱ፤ መጽሐፍ ቅዱስ ‹በውድ ልጁም እንደ
ጸጋው ባጠግነት መጠን በደሙ የተደረገ ቤዛነታችንን አገገኘን፤ እርሱም የበደላችን
ስርየት› (ኤፌሶን 1፡7) ይላል›› በማለት እምነታቸውን ሁሉ በመስቀሉ ደም ላይ
የማኖር ውሳኔያቸውን ለማጽደቅ መጽሐፍ ቅዱስን ይጠቅሳሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች ግን
የመስቀሉን ደም በግልጥ የሚናገረውን ቃል ብቻ በመሻታቸው በትክክል ከበድ ባለ
መንፈሳዊ ስህተት ውስጥ ተጠምደዋል፡፡
በአንጻሩ በቅዱሳት መጽሃፍት ውስጥ በተገለጠው የውሃና የመንፈስ ወንጌል

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ደህንነታችን ከዓለም ፍጥረት በፊት በኢየሱስ ጽድቅ ተዘጋጅቷል 31

እውነት መሠረት የእግዚአብሄርን ፍቅር በትክክል የሚያስተውሉና የሚያምኑ ሰዎች


አሉ፡፡ እነዚህ የእምነት ሰዎች ኢየሱስ ደሙን በመስቀል ላይ ማፍሰስ የቻለው
አስቀድሞ ስለተጠመቀ ነው ይላሉ፡፡ በብሉይ ኪዳን ዘመን በመገናኛው ድንኳን
ውስጥ የተገለጠው የመስዋዕት ስርዓት የእስራኤል ሕዝብ እጆቻቸውን በራሱ ላይ
በመጫንና ደሙንም በማፍሰስ ሐጢያቶቻቸውን ወደ መስዋዕቱ እንስሳ ማስተላለፍ
ነበረባቸው፡፡ ይህም ጌታ በተመሳሳይ መንገድ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ
እንደሚያስወግድ ተተንብዮዋል፡፡ (ዘሌዋውያን 4፡21-27)
በሌላ አነጋገር የመስዋዕቱ ስርዓት ኢየሱስ የእናንተንና የእኔን ሐጢያቶች
በሙሉ ለመሸከም በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቁ እንደተሰቀለ ያሳየናል፡፡
ክርስቶስ የሐጢያቶቻችንን ዋጋ ለመክፈል የስቅለትን ቅጣት በስጋው ላይ
የተሸከመው ለዚህ ነው፡፡ ሁሉም ክርስቲያን የሚያምንበት ኢየሱስ በመስቀል ላይ
ያፈሰሰው ደም ክርስቶስ ከአጥማቂው ዮሐንስ በተቀበለው ጥምቀት ላይ
የተመሠረተ ነው፡፡ በሌላ አነጋገር ኢየሱስ በትክክል በመስቀል ላይ ደሙን
ያፈሰሰው በዮርዳኖስ ወንዝ ራሱ በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቁ ነበር፡፡ ኢየሱስ
ከአጥማቂው ዮሐንስ ጥምቀትን ባይቀበል ኖሮ በመስቀል ላይ የሚፈስስ ደም
ባልኖረም ነበር፡፡ እንዲህ ተብሎ ተጽፎዋል፡- ‹‹እንደ ሕጉም ከጥቂቶች በቀር ነገር
ሁሉ በደም ይነጻል፡፡ ደምም ሳይፈስስ ስርየት የለም፡፡›› (ዕብራውያን 9፡22)
ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ የተጠመቀው በመስዋዕቱ ሕግ መሠረት በእጆች
መጫን መልክ ነው፡፡ ኢየሱስ በመሰቀልና ደሙን በማፍሰስ ለእያንዳንዱ
ሐጢያተኞች ሐጢያቶች በሙሉ መኮነን የቻለው ይህንን ጥምቀት በመቀበሉ
ነበር፡፡ በዚህም በዚህ እውነት ያመነውን እያንዳንዱን ሰው ከሐጢያቶቹ ሁሉ
ፈጽሞ አዳነው፡፡
እግዚአብሄር አብና ኢየሱስ ክርስቶስ የሐጢያቶች ስርየት ወንጌል የሆነውን
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል የሰጡን ዘላለማዊ አዳኛችን ናቸው፡፡ ይህ አምላክ
በጥበቡ ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ሊያድነን አቀደ፡፡ በዚህ ዕቅድ መሠረትም በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት በትክክል እንዳዳነን እርግጥ ነው፡፡ እግዚአብሄር
ጥበቡ ከሰው ጥበብ በእጅጉ የላቀ ስለሆነ ሐጢያተኞችን በሙሉ ለአንዴና
ለመጨረሻ ከሐጢያቶቻቸው ሁሉ ፈጽሞና አስተማማኝ በሆነ መንገድ
አድኖዋቸዋል፡፡ ይህ የማያሻማ የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል እውነት ያንኑ
የሐጢያቶች ስርየት ለእያንዳንዱ ሰው የሚሰጥ በመሆኑ ሁሉንም ሐጢያተኞች
ይመለከታል፡፡ በዚህ የውሃና የመንፈስ ወንጌል የሚያምን ማንኛውም ሰው
ደህንነቱን ማግኘትና ከሐጢያቶቹ ሁሉ መንጻት የሚችለው ለዚህ ነው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


32 ደህንነታችን ከዓለም ፍጥረት በፊት በኢየሱስ ጽድቅ ተዘጋጅቷል

ሆኖም እግዚአብሄር የውሃውንና የመንፈሱን እውነት ከክፉዎች ደብቆታል፡፡


እግዚአብሄር የኢየሱስን ጥምቀት ምስጢር ልቦቻቸው ሐጢያተኛ ከሆኑ ሰዎች
በመደበቁ እንዳይረዱትም አዳጋች አድርጎባቸዋል፡፡ በአንጸሩ ልቦቻቸው ገር ለሆኑና
ቃሉን ለሚታዘዙ ሰዎች ሁሉ መረዳትን አምጥቶዋል፡፡ በዚህም ቃሉን ከሙሉ
ልባቸው የሚያምኑትን ከሐጢያቶቻቸው አድኖዋቸዋል፡፡ እግዚአብሄር በቃሉ ፊት
ለሚንቀጠቀጡ፣ የልቦቻቸውን ሐጢያተኝነት በቅንነት ለሚያምኑ፣ እግዚአብሄር
በሰጠው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ለሚያምኑና ሙሉ በሙሉ በእርሱ ላይ
ለሚደገፉ ሰዎች እውነተኛ ደህንነትን ለግሶዋል፡፡
እግዚአብሄር የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል የሰጠው በመንፈስ ድሆች
ለሆኑ ሰዎች ነው፡፡ እግዚአብሄር የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለሐጢያተኞች
ሁሉ በመስጠት ትክክለኛውን የደህንነት እውነት እንዲገነዘቡ አስችሎዋቸዋል፡፡
እግዚአብሄር ይህንን የውሃና የመንፈሱን ወንጌል ሰጥቶናል፡፡ ትክክለኛውን
የደህንነት እውነት ለመረዳት ማስተዋልን ሊሰጠን ወደደ፡፡ እናንተስ ታዲያ?
የጥምቀትን ምስጢርና የእግዚአብሄር ችሮታ የሆነውን የእጆች መጫን
እንድትገነዘቡ የሚያስችላችሁን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ታምናላችሁን?
እግዚአብሄር በመንፈስ ድሆች የሆኑ ሰዎች በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
አማካይነት የሚገኘውን የሐጢያቶች መንጻት ምስጢር እንዲገነዘቡ ባርኮዋቸዋል፡፡
እግዚአብሄር የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል እንዲያስተውሉና በእርሱ
እንዲያምኑ የሚያስችላቸው ልቦቻቸው የነጹትንና ትሁት የሆኑትን ሰዎች ብቻ
ነው፡፡ ስለዚህ ማንም ብትሆኑ በመጀመሪያ ለሲዖል የታጫችሁ መሆናችሁን
ለእግዚአብሄር እንድታምኑ እጠይቃችኋለሁ፡፡ ያን ጊዜ በእውነተኛው ወንጌል
ታምኑ ዘንድ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል እንድታስተውሉ ይባርካችኋል፡፡ ያን
ጊዜ ያለ ምንም ችግር ከሐጢያቶቻችሁ ሁሉ ነጻ ትወጣላችሁ፡፡ እግዚአብሄር
የደህንነትን ሕግ ያጸናው ጌታ በሰጠው የውሃና የመንፈስ ወንጌል የሚያምን ሁሉ
ዛሬውኑ ከሐጢያቶች ሁሉ እንዲድን ነው፡፡
ሁላችሁም የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ቃል ትክክለኛ የደህንነት እውነት
እንደሆነ ታምኑ ዘንድ ተስፋዬና ጸሎቴ ነው፡፡ በቅዱሳት መጽሐፍት ውስጥ
የተመዘገበውን የመስዋዕት ስርዓት በመመልከት ይህንን እውነት በሚገባ መረዳት
ትችላላችሁ፡፡ እዚህ ላይ በመገናኛው ድንኳን ላይ በተከታታይ የጻፍሁትንና
የመገናኛው ድንኳን፡ የኢየሱስ ስዕላዊ መግለጫ የሚል ርዕስ ያለውን በነጻ
የሚታደል የክርስቲያን መጽሐፌን እንድታነብቡ አጥበቄ እወተውታለሁ፡፡ ይህንን
መጽሐፍ ስታነቡ እግዚአብሄር የእናንተንና የእኔን ሐጢያቶች በሙሉ ለማንጻት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ደህንነታችን ከዓለም ፍጥረት በፊት በኢየሱስ ጽድቅ ተዘጋጅቷል 33

በውሃና በመንፈስ እንዳዳነን ይበልጥ በግልጥ ትረዳላችሁ፡፡


በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ውስጥ የተገለጠው ትክክለኛ የደህንነት
አስተውሎት እንዲኖረን የውሃውንና የመንፈሱንም ወንጌል እውነት በትክክል
መረዳትና ይህንንም እውነት ከሙሉ ልባችን ማመን ይገባናል፡፡ የእግዚአብሄርን
ቃል ማመን፣ ከሐጢያቶቻችን ሁሉ መዳን፣ እውነትን መረዳትና በዚህም ወደ
እግዚአብሄር መቅረብ ለሁላችንም በእጅጉ አስፈላጊያችን ነው፡፡ ጌታ ሁሌም
ትክክል እንደሆነ በአንደበቶቻችን ለማመን የምንገደደው የውሃውንና የመንፈሱን
ወንጌል ቃል ስናስተውል ነው፡፡ ጌታ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል እንድናውቅ
ስላስገደደን ከሐጢያቶቻችን ሁሉ አድኖናል፡፡ ሁላችንም አግዚአብሄርን
የምናመሰግነውና የምናከብረው ለዚህ ነው፡፡
ሐሌሉያ! 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


34 ደህንነታችን ከዓለም ፍጥረት በፊት በኢየሱስ ጽድቅ ተዘጋጅቷል

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ስብከት
2

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት
ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
በጸጋው የእግዚአብሄር
ወገኖች ሆነናል
‹‹ ኤፌሶን 1፡1-14 ››
‹‹በእግዚአብሄር ፈቃድ የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ የሆነ ጳውሎስ በኤፌሶን
ላሉት ቅዱሳን፤ በክርስቶስ ኢየሱስም ላሉት ምዕመናን ከእግዚአብሄር ከአባታችን
ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን፡፡ በክርስቶስ በሰማያዊ
ስፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት
ይባረክ፡፡ ዓለም ሳይፈጠር በፊቱ ቅዱሳንና ነውር የሌለን በፍቅር እንሆን ዘንድ
በክርስቶስ መረጠን፤ በበጎ ፈቃዱ እንደወደደ በኢየሱስ ከርስቶስ ሥራ ለእርሱ
ልጆች ልንሆን አስቀድሞ ወሰነን፡፡ በውድ ልጁም እንዲያው የሰጠን የጸጋው ክብር
ይመሰገን ዘንድ ይህን አደረገ፡፡ በውድ ልጁም እንደ ጸጋው ባለጠግነት መጠን
በደሙ የተደረገ ቤዛነታችንን አገኘን፤ እርሱም የበደላችን ስርየት፡፡ ጸጋውንም
በጥበብና በአእምሮ ሁሉ አበዛልን፡፡ በክርስቶስ ለማድረግ እንደወደደ እንደ አሳቡ
የፈቃዱን ምስጢር አስታውቆናልና፤ በዚህ ዘመን ፍጻሜ ይደረግ ዘንድ ያለው
አሳቡም በሰማይና በምድር ያለውን ሁሉ በክርስቶስ ለመጠቅለል ነው፡፡ እንደ
ፈቃዱ ምክር ሁሉን የሚሠራ እንደ እርሱ አሳብ አስቀድመን የተወሰንን በክርስቶስ
ደግሞ ርስትን ተቀበልን፡፡ ይኸውም በክርስቶስ አስቀድመን ተስፋ ያደረግን እኛ
ለክብሩ ምስጋና እንሆን ዘንድ ነው፡፡ እናንተም ደግሞ የእውነትን ቃል ይኸውም
የመዳናችሁን ወንጌል ሰምታችሁ ደግሞም በክርስቶስ አምናችሁ በተስፋው መንፈስ
በመንፈስ ቅዱስ ታተማችሁ፡፡ እርሱም የርስታችን መያዣ ነው፤ ለእግዚአብሄር
ያለውን እስኪዋጅ ድረስ ይህም ለክብሩ ምስጋና ይሆናል፡፡››

በቅርቡ የጌታን ጽድቅ ለማመስገን አዳዲስ መዝሙሮችን አቀናብረናል፡፡


እነዚህ አዳዲስ መዝሙሮችም በጣም አስደስተውኛል፡፡ አዳዲስ ነፍሳቶች ወደ
ቤተክርስቲያናችን በሚመጡበት ጊዜ ሁሉ እነርሱም ደግሞ ከእኛ ጋር አብረው
እንዲዘምሩ የተለየ ትኩረት ልንሰጣቸውና እነዚህን አዳዲስ መዝሙሮች
ልናስተምራቸው ያስፈልገናል፡፡ ራሳችንን በእነርሱ ቦታ ላይ ማስቀመጥና ለእነርሱ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


38 በጸጋው የእግዚአብሄር ወገኖች ሆነናል

ትኩረት መስጠት ያስፈልገናል፡፡ እኛም ብንሆን አንዳንድ ጊዜ አዲስ መዝሙር


ለመማር በምንሞክርበት ጊዜ እንቸገራለን፡፡ ስለዚሀ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ
ቤተክርስቲያናችን የሚመጡ አዳዲስ ሰዎችም እንደዚሁ ይበልጥ ይቸገራሉ፡፡
እግዚአብሄር ወደዚህ ምድር የላከን እነዚህንም ሰዎች ደግሞ እንድናድን ነው፡፡
ስለዚህ ራሳችንን በእነርሱ ቦታ ማስቀመጥና ለእነርሱም ደግ መሆን ያስፈልገናል፡፡
ዝም ብለን ችላ ብለናቸው ቢሆን ኖሮ ለእኛ ትልቅ ስህተት ይሆን ነበር፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ ‹‹አይሁድንም እጠቅም ዘንድ ከአይሁድ ጋር እንደ
አይሁዳዊ ሆንሁ፤ ከሕግ በታች ያሉትን እጠቅም ዘንድ እኔ ራሴ ከሕግ በታች
ሳልሆን ከሕግ በታች እንዳለሁ ሆንሁ›› (1ኛ ቆሮንቶስ 9፡20) እንዳለው በዙሪያው
ላለው ሰው ሁሉ በእጅጉ ያስብ ነበር፡፡ ጳውሎስ ሰውን ሁሉ በዚህ መልኩ በትህትና
ያስተናገደው የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለመስበክ ነበር፡፡ እኛ በአምልኮ
ስርዓታችን ለዘብተኞች ነን፡፡ ብዙውን ጊዜ የምንከተለው ቀላል አምልኮን ነው፡፡
ነገር ግን በጌታ ቀን ወደ ቤተክርስቲያናችን አዳዲስ ሰዎች ሲመጡ በአዲሱ ሥነ
ምህዳር ውስጥ ምቾት እንዲሰማቸው ስንል ትውፊታዊውን የአምልኮ ስርዓት
እንከተላለን፡፡ ከክርስቶስ ውጪ ሆኖ የቆመውን እያንዳንዱን ሰው ከዓለም
ሐጢያቶች ለማዳን እንችል ዘንድ በቤተክርስቲያናችን ውስጥ ምቾት እንዲሰማቸው
ታደርጉ ዘንድ እጠይቃችኋለሁ፡፡ በእግዚአብሄር ፊት ሊደረግ የሚገባው
ትክክለኛው ነገር ያ ነው፡፡ ስለዚህ ሁላችንም እንደዚያ እናድርግ፡፡
ትናትና በማቴዎስ ወንጌል ላይ የሰበኩዋቸውን ስብከቶቼን ገምግሜ
ከጨረስሁ በኋላ ለተርጓሚዎች ሰጠኋቸው፡፡ በኤፌሶን መልዕክት ላይ የሰጠኋቸው
ስብከቶቼ ቀደም ብለው ተተርጉመው በድረ ገጻችን ላይ በኤሌክትሮኒክስ
መጽሐፎች መልክ ተጭነዋል፡፡ ነገር ግን በመጽሐፍ መልክ ለማሳተም እንደገና
ልከልሳቸው ዕቅድ አለኝ፡፡ እግዚአብሄርን ድንቅ ስለሆነው ችሮታው አብዝቼ
እንዳመሰግነውና እንዳከብረው ይህንን ሥራ በተቻለ ፍጥነት ላጠናቅቀው ተስፋ
አደርጋለሁ፡፡ መጽሐፎቻችንን በቻይና የፍለጋ ማቀናበሪያዎች ስናስተዋውቅ
ቆይተናል፡፡ ፍለጋ በሚከናወንበት ጊዜ ግንኙነቱን ወደ እኛ ድረ ገጽ መልሶ
ያመጣዋል፡፡ በዚህ ምክንያት የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል የሚሹ በቻይና ያሉ
ክርስቲያኖች አሁን በፍለጋ ማቀናበሪያዎች አማካይነት በቀላሉ ድረ ገጻችን ውስጥ
መግባት ይችላሉ፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በጸጋው የእግዚአብሄር ወገኖች ሆነናል 39

ወንጌልን በመላው ዓለም ለመስበክ አስቀድመን መዘጋጀት አለብን፡፡

ጨካኝና ክፉ ባላንጣዎች እንደሚገጥሙን አውቀን ራሳችንን ለወደፊቱ


ማዘጋጀት በጣም ያስፈልገናል፡፡ ቢያንስ ወደፊት የሚመጡትን አንድ መቶ
ዓመታቶች ተመልክተን ወንጌልን ለመስበክ አስፈላጊ ዝግጅቶችን ሁሉ ማድረግ
ይገባናል፡፡ ያልተጠበቁ ችግሮች እንኳን ሲገጥሙን ያለ ምንም ጭንቀት የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል በመላው ዓለም ሁሉ ማሰራጨቱን መፈጸም የምንችለው በዚህ
መልኩ አስቀድመን ስናዘጋጅ ብቻ ነው፡፡
በቅርቡ የተፈጥሮ ጥፋቶች በመላው ዓለም የተለመዱ ሆነዋል፡፡ ነገር ግን
ከእነርሱ መካከል በተለይ አሳሳቢው በባህር ዳርቻዎች ያሉ አካባቢዎችን እየዋጠ
ያለው የባህር ወለል መጨመር ነው፡፡ እነዚህ ነገሮች እየሆኑም እንኳን እኛ በጌታ
ምጽዓት ተስፋ አለን፡፡ ስለዚህ በእምነት መዘጋጀትና የውሃውንና የመንፈሱን
ወንጌል መስበክ አለብን፡፡ የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል በመላው ዓለም
የሚሰበከው እንዲህ ነው፡፡ ዛሬ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በመላው ዓለም
የማናሰራጭ ከሆነ የጌታ ቀን በድንገት ሲመጣብን እንገረማለን፡፡ የቤት ባለቤት
ቤቱ በሌባ ተሰብሮ እንዳይሰረቅ አስቀድሞ መጠበቅ እንደሚገባው ሁሉ እኛም
እንደዚሁ የተፈጥሮ ጥፋቶች ይበልጥ የከፉ ከመሆናቸው በፊት የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል ለመስበክ ዝግጁ መሆን አለብን፡፡ የዘመኑ መጨረሻ ቢቀርብም
እንኳን መፍራት የማንችለው ወንጌልን ለማሰራጨት ራሳችንን ስናዘጋጅ ብቻ
ነው፡፡ የሥነ ጽሁፍ አገልግሎታችን በዓለም ሁሉ ልናሰራጨው የሚገባን
የእግዚአብሄር ቃል የሆነውን የውሃውን የመንፈሱን ወንጌል ለማሰራጨት ይህንን
ዝግጅት የምናደርግበት መንገድ ነው፡፡ ይህንን ሥራ መፈጸም ካቃተን ትልቅ
ስህተት ይሆናል፡፡ ምክንያቱም ያን ጊዜ ብዙ ነፍሳቶች ይህንን የሕይወት ቃል
ለማግኘት ዕድል አይኖራቸውምና፡፡ በዚህ በመጨረሻው ዘመን ይህ እንዲሆን
መፍቀድ የለብንም፡፡ እኔ ሁሌም የምተጋው ለዚህ ነው፡፡ ነገር ግን በእርሱና በጽድቁ
በመታመን የእግዚአብሄርን ቃል ለመስበክ ዝግጁ ከሆንን ያን ጊዜ ምንም
የምንጨነቅበት ነገር አይኖርም፡፡
በዓለም ዙሪያ ያሉ ሰዎች አሁን እኛ እየሰበክነው ያለውን የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል በልቦቻቸው ውስጥ መቀበል አለባቸው፡፡ አለበለዚያ
የሐጢያቶቻቸውን ኩነኔ ይቀበላሉ፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የማመኑ
ሐላፊነት የእነርሱ ነው፡፡ ሰዎች በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ቢያምኑ ወይም
ባያምኑ ምንም ግላዊ ትርፍ የለንም፡፡ እኛ ለእግዚአብሄር ፈቃድ ታማኝነታችንን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


40 በጸጋው የእግዚአብሄር ወገኖች ሆነናል

እያሳየን ነው፡፡ ነገር ግን ሰዎች በወንጌሉ ለማመን እምቢተኞች ሲሆኑ እግዚአብሄር


ያዝናል፡፡ ስለዚህ በዓለም ዙሪያ ያሉ ሰዎች በሙሉ ከሐጢያቶቻቸው ሁሉ መንጻት
የሚፈልጉ ከሆነ ወደ ውሃውና መንፈሱ ወንጌል እውነት መምጣትና በዚህ እውነት
ማመን አለባቸው፡፡ እግዚአብሄር በትዕግስት እየጠበቃቸው ያለው እነርሱም ደግሞ
ከሐጢያቶቻቸው እንዲድኑ ስለሚፈልግ ነው፡፡ አሁንም ቢሆን እግዚአብሄር
ምህረቱን እያሳያቸው ነው፡፡
እኛ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለሁሉም ሰው እየሰበክን ያለነው ለዚህ
ነው፡፡ መጽሐፎቻችን በመላው ዓለም በስፋት ተስተዋውቀዋል፡፡ አሁን ወንጌል
በእግዚአብሄር ባሮች አማካይነት በእያንዳንዱ የዓለም ማዕዘን ሁሉ ይሰራጫል፡፡
ቀደም ብለን ያደረግንላቸው ነገር በቂ ባይሆንም በእግዚአብሄርና በእርሱ ባሮች
ዕርዳታ ወንጌልን በመላው ዓለም መሰበክ እንችላለን፡፡ በእግዚአብሄር ጽድቅ
የሚያምኑ የእምነት ሰዎች በእያንዳንዱ አገር ውስጥ መስራት የሚያስፈልጋቸቸው
ለዚህ ነው፡፡ ነገር ግን በቂ የእምነት ሠራተኞች የሉም፡፡ በዚህ ምክንያት
የእግዚአብሄርን ጥማት ሙሉ ሙሉ ማርካት አልተቻለንም፡፡ ይህ ልቤን
ይሰብረዋል፡፡ የእግዚአብሄርን ጥማት ለማርካት በተቻለ መጠን ተጨማሪ የእምነት
ሠራተኞች እንዲነሱ ተስፋ አድርጌ እጸልያለሁ፡፡ በእያንዳንዱ አገር ተጨማሪ
የሰለጠኑ የእግዚአብሄር ሕዝቦች ከተገኙ በኋላ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
ሙሉ በሙሉ በመላው ዓለም መስበክ እንደምንችል እርግጠኛ ነኝ፡፡
አሁንም እንኳን የእግዚአብሄርን ሥራ በዓለም ላይ እየሰሩ ያሉት እፍኝ የሆኑ
አገልጋዮች ብቻ ናቸው፡፡፡ ለእኔ ይህም ቁጥር ቢሆን ብዙ ቁጥር ነው፡፡ በብሉይ
ኪዳን ዘመን ጌድዮንና የእርሱ 300 ወታደሮች መላውን የምድያም ሕዝብ
አሸንፈዋል፡፡ ልክ እንደዚሁ በዚህ ምድር ላይ ተጨማሪ ሰዎች በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል ቢያምኑና የእግዚአብሄርን ጽድቅ ቢከተሉ በመላው የጨለማ
ዓለም ላይ የምናደርገውን መንፈሳዊ ውጊያ እናሸንፋለን፡፡ በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል በሚያምን እምነታችን አማካይነት ሐሰተኛ ነቢያቶችን ሁሉ ተዋግተን
ማሸነፍ እንደምንችል እተማመናለሁ፡፡ ድል የእኛ እንደሚሆንም አምናለሁ፡፡
በዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ ኤፌሶን 1፡1-14ን አንብበናል፡፡ በዚህ ምንባብ
ላይ ሐዋርያው ጳውሎስ ስለ እግዚአብሄር የተትረፈረፈ ምህረትና ክቡር ስለሆነው
ዕቅዱ ይመሰክራል፡፡ እርሱ የእግዚአብሄር አብን ትልቅ የደህንነት ዕቅድ በመናገር
በእግዚአብሄር ልጅ ውስጥ የሚገኘውን የማይመረመር የክርስቶስ ባለጠግነት
ያብራራል፡፡ የጳውሎስ መልዕክት እኛ በክርስቶስ ጽድቅ በማመን የሐጢያቶቻችንን
ስርየት መቀበልና ጻድቃን ሠራተኞች መሆን የቻልነው በዚህ የእግዚአብሄር ታላቅ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በጸጋው የእግዚአብሄር ወገኖች ሆነናል 41

የምህረት ዕቅድ ነው የሚል ነው፡፡ ጳውሎስ እግዚአብሄር በመንፈስ ቅዱስ


እንዲሞሉ የተዋጁትን ቅዱሳኖቹን ሕይወት እየመራ እንደሆነም ደግሞ
ያስተምረናል፡፡

እያንዳንዱ መንፈሳዊ በረከት በእርሱ


ምክር መሠረት ከእግዚአብሄር የመጣ ነው፡፡

በኤፌሶን 1፡11 ላይ እንዲህ ተጽፎዋል፡- ‹‹እንደ ፈቃዱ ምክር ሁሉን የሚሠራ


እንደ እርሱ አሳብ አስቀድመን የተወሰንን በክርስቶስ ደግሞ ርስት ተቀበልን፡፡››
መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሄር በአእምሮው ውስጥ የሰውን ዘር ደህንነት አስቦ
በዚያው መሠረት እንደሰራ ይናገራል፡፡ አሁን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
የምናምን ሁላችን ደህንነታችን የተዘጋጀው በእግዚአብሄር አብ ዕቅድና ፈቃድ
አስቀድሞ እንደነበር ማወቅ ይገባናል፡፡ አብ ከዓለም ፍጥረት በፊት አስቀድሞ
የወሰነልን ይህ ደህንነትም በልጁ ጽድቅ አማካይነት ተፈጽሞዋል፡፡ እያንዳንዱ
የእግዚአብሄር ሥራ የተከናወነው በፈቃዱ ምክር መሠረት ነበር፡፡ ይህ ማለት
የተባረከው ደህንነታችን የተወሰነው እግዚአብሄር አብ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል
ለእኛ ባቀደው ዕቅድ መሠረት ነው ማለት ነው፡፡ በሌላ አነጋገር ከምህረቱ የተነሳ
ደህንነታችንን ለመፈጸም እግዚአብሄር ራሱ ሰራ፡፡
እዚህ ላይ የእግዚአብሄር ቃል የእርሱን ርስት የተቀበልነው በኢየሱስ
ክርስቶስ በኩል እንደሆነ ይናገራል፡፡ የእርሱ ወገን የሆንነውም በእርሱ ፈቃድ
መሠረት ነው፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ በኤፌሶን 1፡11 ላይ እንዲህ ብሎዋል፡- ‹‹እንደ
ፈቃዱ ምክር ሁሉን የሚሠራ እንደ እርሱ አሳብ አስቀድመን የተወሰንን በክርስቶስ
ደግሞ ርስት ተቀበልን፡፡›› ይህ ምንባብ እንዴት የእግዚአብሄር ወገን እንደሆንን
ይበልጥ አሳማኝ በሆነ ግልጥነት በትክክል አብራርቷል፡፡ እናንተና እኔ
የእግዚአብሄር ወገን መሆናችንን እግዚአብሄር አብ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
የምናምነውን ሁላችንንም የራሱ ወገን ሊያደርገን እንደወሰነ ያሳያል፡፡ በሌላ አነጋገር
እኛ የእርሱ የሆንነው ሙሉ በሙሉ ከእግዚአብሄር ፍላጎትና ዕቅድ የተነሳ ነው፡፡
ታዲያ እግዚአብሄር ልጆቹ ሊያደርገን ያቀደው እንዴት ነው? እግዚአብሄር
በምክሩ መሠረት ደህንነታችንን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል አቀደ፡፡ እግዚአብሄር
ራሱም በልጁ ውስጥ ባለው ጽድቁ ይህንን ዕቅድ ፈጸመ፡፡ እግዚአብሄር በራሱ
ፍላጎት መሠረት በጽድቁ አማካይነት ልጆቹ ሊያደርገን የቻለው እንዲህ ነው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


42 በጸጋው የእግዚአብሄር ወገኖች ሆነናል

እግዚአብሄር አብ በልጁ ጽድቅ የምናምነውን የእርሱ ልጆች አድርጎ ሊለውጠን


ችሎዋል፡፡
በኤፌሶን 1፡9-10 ላይ እንዲህ ተጽፎዋል፡- ‹‹በክርስቶስ ለማድረግ እንደወደደ
እንደ አሳቡ የፈቃዱን ምስጢር አስታውቆናልና፡፡ በዘመን ፍጻሜ ይደረግ ዘንድ
ያለው አሳቡም በሰማይና በምድር ያለውን ሁሉ በክርስቶስ ለመጠቅለል ነው፡፡››
እዚህ ላይ ‹‹የዘመኑ ፍጻሜ›› የሚያመለክተው የእግዚአብሄርን ትልቅ ዕቅድ ነው፡፡
ዛሬ እግዚአብሄር በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የምናምነውን ሁላችንን በኢየሱስ
ክርስቶስ በኩል የራሱ ልጆች ያደረገን በታላቅ ዕቅዱ መሠረት ነው፡፡ እግዚአብሄር
ይህንን ያደረገው ‹‹በሰማይና በምድር ያለውን ሁሉ በክርስቶስ ለመጠቅለል ነው፡፡››
በሌላ አነጋገር እግዚአብሄር በዚህ ትልቅ ዕቅድ የሰራው እኛን ተራ ፍጡራኖች
ከራሱ ጋር አንድ ለማድረግ ነው፡፡ እግዚአብሄር በዚህ ትልቅ ዕቅድ መሠረት
በመስራት ፈቃዱን ሙሉ በሙሉ ፈጽሞዋል፡፡ በሌላ አነጋገር እግዚአብሄር
በክርስቶስ ውስጥ በሚገኘው ጽድቁ ለሚያምኑ ሁሉ ጥልቅ የሆነውን ፈቃዱን
ፈጽሞዋል፡፡ ስለዚህ እኛ ያደረግነው ነገር ቢኖር እግዚአብሄር እኛን የእርሱ
ባደረገበት በዚህ ድንቅ የአምላክ ዕቅድ ማመን ብቻ ነው፡፡

እናንተና እኔ የቅዱሱ አምላክ ልጆች መሆን የቻልነው እንዴት ነው?

እግዚአብሄር አብ በዚህ ትልቅ ዕቅድ መሰረት ደህንነታችንን የሰራው የራሱ


ልጆች ሊያደርገን ስለፈለገ ነው፡፡ እግዚአብሄር አብ በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ
ውስጥ ባለው ጽድቁ ለእኛ ለሰዎች ሁሉ የደህንነት ዕቅዱን በአንዴ ፈጸመ፡፡
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በሚያምነው እምነታችን አማካይነት የእግዚአብሄር
ልጆች መሆን የቻልነው በዚህ ሁኔታ ነው፡፡
ጥንት ሁላችንም በእግዚአብሄር የተፈጠርን ፍጥረቶች ነበርን፡፡
የእግዚአብሄርን ሥራ በምሳሌ ለማብራራት አንድ ሳይንቲስት እርሱን የሚመስል
ሮቦት ሠራ እንበል፡፡ ከዚያም ይህ ሳይንቲስት ራሱ የሰራውን ይህንን ሮቦት እርሱ
ወዳለበት ደረጃ ከፍ አደረገው፡፡ ይህ እግዚአብሄር ለእኛ ካደረገው ነገር ጋር
ይመሳሰላል፡፡ ምናልባት ይህ ምሳሌ ተስማሚ አይሆን ይሆናል፡፡ ነገር ግን
እግዚአብሄር የፈጠረን የራሱ ልጆች ሊያደርገን ነው፡፡ በኢየሱስ ጽድቅ ውስጥ
በሚገኘው የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል አማካይነት በሚያምነው እምነታችን
እውነተኛ ደህንነትን መቀበል የቻልነው ለዚህ ነው፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ እስከ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በጸጋው የእግዚአብሄር ወገኖች ሆነናል 43

አሁን ድረስ እየነገረን ያለው በጸጋ የተሞላውን የደህንነት እውነት ነው፡፡


በመሆኑም እግዚአብሄር አብ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በዘመኑ መጨረሻ
ያለውን አሳቡን አሳይቶናል፡፡ ይህ ማለት እግዚአብሄር አብ ልጁን ኢየሱስ
ክርስቶስን አዳኛችን አድርጎ በመላክ በእርሱ ጽድቅ የምናምነውን ሁሉ
ከሐጢያቶቻችን አድኖናል ማለት ነው፡፡ በሌላ አነጋገር አሁን በክርስቶስ ጽድቅ
የምናምን ሁላችን ለአንዴና ለመጨረሻ የሐጢያቶችን ስርየት ተቀብለን
የእግዚአብሄር ልጆች ሆነናል፡፡ እግዚአብሄር አብ በኢየሱስ ክርስቶስ ጽድቅ
በሚያምነው እምነታችን ምክንያት ልጆቹ አድርጎናል፡፡ እግዚአብሄር አብ ልጆቹ
ሊያደርገንም በልጁ መስዋዕትነት አማካይነት ሐጢያቶቻችንን ለአንዴና ለመጨረሻ
አንጽቷል፡፡ አያቶቻችን በሰይጣን ፈተና ተታልለው ሐጢያት ቢሰሩም እግዚአብሄር
አብ በልጁ መስዋዕትነት አማካይነት ከሐጢያቶቻችን ሁሉ አድኖናል፡፡
እግዚአብሄር ለአንዴና ለመጨረሻ የእርሱ ልጆች ሊያደርገን የቻለው በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል የሚያምን እምነት በመስጠት ነው፡፡
ስለዚህ የእግዚአብሄርን ጽድቅ ጠቅለል ያለ ዝርዝር ስናጤን ይህ ዕቅድ
በእግዚአብሄር አብ፣ በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስና በመንፈስ ቅዱስ ከውሃውና
ከመንፈሱ ወንጌል ጋር አብሮ እንደተፈጸመ ማየት እንችላለን፡፡ ከዓለም ሐጢያቶች
የዳንነው ኢየሱስን በዕውር ድንብር አዳኛችን አድርገን በማመን አይደለም፡፡ ነገር
ግን ደህንነታችንን ያገኘነው በእግዚአብሄር አባታችን ልዩ ዕቅድ ውስጥ ባለው
የውሃና የመንፈስ ወንጌል በማመን ብቻ ነው፡፡ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
መረዳት የቻልነው በእግዚአብሄር ጽድቅ ላይ ባለን እምነታችን ምክንያት ነው፡፡
የእርሱ መሆን የቻልነውም በዚህ የእግዚአብሄር ጽድቅ በማመን ነው፡፡ ስለዚህ
ደህንነታችንን ማግኘት የምንችለው የውሃውንና የመንፈሱ ወንጌል ስናስተውልና
በእርሱም በትክክል ስናምን ብቻ ነው፡፡
ደህንነታችን የተፈጸመው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ቢሆንም ይህ ማለት
ሐጢያቶቻችን ከስመዋል ማለት አይደለም፡፡ ነገር ግን ይህ ሁላችንም
ለእግዚአብሄር የኖርነውን ክቡር ሕይወት ይይዛል፡፡ በዚህ ዓለም ላይ ብዙ ነገሮች
አሉ፡፡ ነገር ግን እነዚህ ነገሮች የማን መሆናቸውም እንደዚሁ አስፈላጊ ነው፡፡
በእግዚአብሄር ትልቅ የደህንነት ዕቅድ ባይሆን ኖሮ እኛም እንደ ሌሎቹ ሕያዋን
ፍጥረቶች አላፊ ሰዎች እንሆን ነበር፡፡ እያንዳንዱ ሰብዓዊ ፍጡር በእግዚአብሄር
ተፈጥሮዋል፡፡ በዚህች ምድር ላይ የተወለደውም በእርሱ ምክንያት ነው፡፡ ይህ ሆኖ
ሳለ በዚህ ምድር ላይ ያለው አብዛኛው ሕዝብ የእግዚአብሄርን ትልቅ ዕቅድ
አያውቅም፡፡ ነገር ግን በዚህም ዘመን ቢሆን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የምናምን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


44 በጸጋው የእግዚአብሄር ወገኖች ሆነናል

እናንተና እኔ የእግዚአብሄር ወገኖች ሆነናል፡፡ የእርሱ ሠራተኞች ሆነንም እየኖርን


ነው፡፡ በእግዚአብሄር የተወደድን ልጆች መሆን የቻልነው በኢየሱስ ክርስቶስ
ውስጥ ያለውን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በመረዳታችንና በማመናችን ነው፡፡
እግዚአብሄር አባታችን ይህንን ለእኛ ለማድረግ ልጁን ኢየሱስ ክርስቶስን
አዳኛችን አድረጎ ወደዚህ ምድር ላከው፡፡ በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅም
ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ለአንዴና ለመጨረሻ እንዲቀበል አደረገው፡፡ የዚህን ዓለም
ሐጢያቶች ተሸክሞ በመስቀል ላይ በመሰቀልና ደሙን በማፍሰስ ለሐጢያቶቻችን
እንዲኮነን አደረገው፡፡ እግዚአብሄር አብ ልጁ እንደዚህ ከአጥማቂው ዮሐንስ
ጥምቀትን እንዲቀበል በማድረግ፣ በመስቀል ላይ እንዲሞት በማኖርና ከሙታን
በማስነሳት ሐጢያቶቻችንንና ፍርድን ሁሉ አስወገደ፡፡ በዚህ መልኩ የእግዚአብሄር
ወገኖች ከሆንን ይህ ማለት ‹‹በዘመን ፍጻሜ ይደረግ ዘንድ ያለው አሳቡም በሰማይና
በምድር ያለውን ሁሉ በክርስቶስ ለመጠቅለል ነው›› (ኤፌሶን 1፡10) የሚለው
የእግዚአብሄር ቃል ፍጻሜ ነው ማለት ነው፡፡ በሌላ አነጋገር የውሃውና የመንፈሱ
ወንጌል እግዚአብሄር ተስፋ በሰጠን መሠረት በትክክል ተፈጽሞልናል፡፡ እኛ
የእግዚአብሄር ልጆች መሆናችን የሚያሳየው አሁን ከእግዚአብሄር ጋር
እንደምንኖርና ከእርሱም ጋር አብረን በሰማይ ክብር እንደምንደሰት ነው፡፡
እንዲህ ያሉትን ወሰን የለሽ ሰማያዊ በረከቶች እንድንቀበል እግዚአብሄር አብ
ይህንን ዕቅድ ያቀደልን መቼ ነው? እርሱ ይህንን በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል
ያቀደው ከዓለምና ከዩኒቨርስ ፍጥረት በፊት ነው፡፡ አንድ ነገር ለማድረግ ስንፈልግ
አስቀድመን እናቅዳለን፡፡ በአእምሮዋችሁ ውስጥ አንድ የምታደርጉት ነገር ሲኖር
አስቀድማችሁ እንዴት እንደምትሰሩት ታቅዳላችሁ፤ አይደል? ትንሽ ጠረጴዛ
እንኳን ስንሰራ በመጀመሪያ ቁጭ ብለን ንድፉን እንሰራለን፡፡ የሚያስፈልጉትንም
ቁሳቁሶች እናስባለን፤ አይደል?
ልክ እንደዚሁ ጌታም የደህንነታችንን በር ሲሰራ ደህንነታችንን እንዴትና
በምን መንገድ እንደሚፈጽመው ለመወሰን በመጀመሪያ እቅድ አቀደ፡፡ ንድፉንም
በሥዕል አስቀመጠ፡፡ በብሉይ ኪዳን ዘመን የመገናኛውን ድንኳን ለመስራት ጥቅም
ላይ የዋሉትን ሰማያዊ፣ ሐምራዊና ቀይ ማግ ስንመለከት ይህንን ማየት እንችላለን፡፡
የመገናኛውን ድንኳን ለመስራት የተወሰኑ ለየት ያሉ ቁሳቁሶች ብቻ ጥቅም ላይ
እንደዋሉ ሁሉ እግዚአብሄር በእርሱ አምሳል በዚህ ምድር ላይ የተወለድነውን እኛን
ልጆቹ ለማድረግ ሲፈልግ የተጠቀመባቸው አንዳንድ አስፈላጊ ቁም ነገሮች ነበሩ፡፡
እግዚአብሄር አብ ደህንነታችንን ያቀደው፣ የዘላለምን ሕይወትና ሰማያዊ
በረከቶችንም ያዘጋጀው መቼ ነበር? እርሱ ይህንን ዕቅድ ያቀደው ከዓለም ፍጥረት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በጸጋው የእግዚአብሄር ወገኖች ሆነናል 45

በፊት ነው፡፡ እግዚአብሄር አብ ይህንን ዩኒቨርስ ከመፍጠሩም በፊት እንኳን ወደዚህ


ምድር ሊያመጣንና በኢየሱስ ክርስቶስ ጽድቅ አማካይነት ልጆቹ ሊያደርገን
አስቀድሞ አቀደ፡፡ ሳይንቲስቶች ይህ ዩኒቨርስ ወደ ኑባሬ የመጣው ከቢሊዮኖች
ዓመታት በፊት እንደነበር ይገምታሉ፡፡ ነገር ግን ከእነዚህ በጣም ብዙ ዓመታቶችም
በፊት፣ ይህ ዩኒቨርስና ሠራዊቶቹ ሁሉ ወደ ኑባሬ ከመምጣታቸውም በፊት
እግዚአብሄር በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ በተፈጸመው ጽድቁ እንድናምን በማሳመን
ልጆቹ ሊያደርገን አቀደ፡፡ እግዚአብሄር አብ በልጁ አማካይነት በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል የምናምነውን አማኞች ከዓለም ፍጥረት በፊት መርጦ የራሱ
ልጆች ሊያደርገን ወሰነ፡፡

ከዓለም ፍጥረት በፊት የታቀደው ደህንነታችን፡፡

በኤፌሶን 1፡4-7 ላይ እንዲህ ተጽፎዋል፡- ‹‹ዓለም ሳይፈጠር በፊቱ ቅዱሳንና


ነውር የሌለን በፍቅር እንሆን ዘንድ በክርስቶስ መረጠን፤ በበጎ ፈቃዱ እንደወደደ
በኢየሱስ ከርስቶስ ሥራ ለእርሱ ልጆች ልንሆን አስቀድሞ ወሰነን፡፡ በውድ ልጁም
እንዲያው የሰጠን የጸጋው ክብር ይመሰገን ዘንድ ይህን አደረገ፡፡ በውድ ልጁም
እንደ ጸጋው ባለጠግነት መጠን በደሙ የተደረገ ቤዛነታችንን አገኘን፤ እርሱም
የበደላችን ስርየት፡፡››
እግዚአብሄር አብ ልጆቹ ሊያደርገን ያቀደው መቼ ነበር? እርሱ በኢየሱስ
ክርስቶስ ፍቅር ደህንነታችንን ያቀደው ዩኒቨርስ ከመፈጠሩ በፊት ነው፡፡ ይህንን
ዕቅድ እንዴት አቀደው? እርሱ ልጆቹ ሊያደርገን ያቀደው በልጁ የተመረጥነውን
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት በማዳን ነው፡፡
እግዚአብሄር በዚህ ምድር ላይ ካሉት በጣም ብዙ ሰዎች መካከል የመረጠው
ማንን ነው? እግዚአብሄር ልጆቹ አድርጎ የመረጠው በእርሱ ጽድቅ ላይ ብቻ
የታመኑትን ሰዎች ብቻ ነው፡፡ በአንጻሩ እግዚአብሄር ተራ ፍጥረቶች ሆነው ሳሉ
ጠንካራና ጠቢብ እንደሆኑ በማሰብ በልጁ በኢየሱስ በኩል የተፈጸመውን
የእግዚአብሄር አብ የጽድቅ ፍቅር የማይቀበሉትን ዕብሪተኛ ሰዎች ሊመርጣቸው
አይችልም፡፡
በቅርቡ ወንጌላዊ ቢዩንጉ አን ስለ ኤፌሶን ምዕራፍ 2 ሲሰብክ በአንድ ወቅት
በሚማርበት ትምህርት ቤት ውስጥ እንዴት ጎበዝ ተማሪ እንደነበር ሰማሁ፡፡ ነገር
ግን ሰው ትምህርት ቤት ይሄድ በነበረበት ወቅት እጅግ በጣም ጥሩ ውጤቶችን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


46 በጸጋው የእግዚአብሄር ወገኖች ሆነናል

በማስመዝገቡና አስተማሪዎቹም ስላመሰገኑት የሚኩራራ ከሆነ ይህ ሰው በሕይወቱ


ውስጥ ብዙ ችግር ይገጥመዋል፡፡ ይህም ብዙ አሉታዊ ገጽታዎችን የያዘ ነው፡፡
ምክንያቱም ጎበዝ ልጆች በትምህርት ቤት የላቀ ውጤቶችን ስላመጡ ብቻ
በራሳቸው ስለሚኩራሩ ዕብሪተኞች ሆነው ይጎለምሳሉ፡፡ ሕይወት ግን የውጤት
ጉዳይ ብቻ አይደለችም፡፡ በክፍላችሁ ውስጥ ጎበዝ ብትሆኑም በትምህርት ቤት
ውስጥ የተማራችሁት ነገር ዋና ነገር አይደለም፡፡፡ ሕይወት ይዛቸው
የምትመጣቸውን ብዙ ችግሮች ለመጋፈጥ በዚህ ዓለም ላይ ልትማሩዋቸው
የሚያስፈልጉ ብዙ ተጨማሪ ነገሮች አሉ፡፡ አንድ ሰው ተማሪ ሲሆን ዋናው ጉዳይ
ውጤቶቹ ምን ያህል ጥሩ ናቸው የሚለው እንደሆነ የታወቀ ነው፡፡ በመደዳ ኤ
ከደረደረ ሰው ሁሉ ያወድሰዋል፡፡ ችግሩ ግን ብዙ ጎበዝ ተማሪዎች በሚጎለምሱበት
ጊዜ እነዚሁ ውዳሴዎች እንደሚከተሉዋቸው በተሳሳተ መንገድ መገመታቸው
ነው፡፡
ይበልጥ ተጨባጭ የሆነ ምሳሌ ልስጣችሁ፡፡ ሴቶች አብዛኛውን ጊዜ ስለ
ባሎቻቸው ከሚያጉረመርሙባቸው ብዙ ማጉረምረሞች መካከል እነዚህ ሚስቶች
ከትምህርት ቤት ጓደኞቻቸው ጋር ውለው በሚመለሱበት ጊዜ ሁሌም የሚነሳ
አንድ መጨቃጨቂያ አለ፡፡ እነዚህ ወዳጆች ሰነፍ ተማሪዎች ቢሆኑም እንኳን
በትምህርት ቤት ዘመናቸው የሚያውቁዋቸው እነዚህ የቀድሞ ጓደኞቻቸው
ተሽለው ሲያገኙዋቸው ይበሳጫሉ፡፡ በዚህም ቅናት ይይዛቸውና ባሎቻቸውን
‹‹ተማሪዎች በነበርንበት ጊዜ ይህች ጓደኛዬ ከእኔ የባሰች ነበረች፤ አሁን ግን ጥሩ
ባል ስላገባች በጣም የተሻለ ሕይወት እየኖረች ነው፡፡ እኔ እንዲህ ጎስቋላ የሆንኩት
አንተን በማግባቴ ነው፡፡ ስህተቱ በሙሉ ያንተ ነው!›› በማለት እረፍት
ይነሱዋቸዋል፡፡ እንዲህ የሚያጉረመርሙት በትምህርት ቤት ዘመናቸው በጣም
ብልሆች፣ በጣም የሚያምሩና ቁመና ያላቸው ስለነበሩ ከጓደኞቻቸው የተሻሉ
መሆን እንደሚገባቸው ስለሚያስቡ ነው፡፡ አሁን ያሉበትን ሁኔታ ከጓደኞቻቸው
ሁኔታ ጋር ያወዳድሩና ባሎቻቸውን ይጨቀጭቁዋቸዋል፡፡ ነገር ግን ይህንን
የሚያደርጉት ሴቶች ብቻ አይደሉም፡፡ ወንዶችም እንደዚሁ ከእነርሱ ይበልጥ
በጣም ሰነፍ እንደነበረው አንድ የቀድሞ የትምህርት ቤት ጓደኛቸው የተሳካላቸው
አለመሆናቸው ተገቢ እንዳልሆነ ያስባሉ፡፡ ምቀኝነትን በሚመለከት ወንዶችን
ከሴቶች የሚለያቸው ምንም ነገር የለም፡፡
ነጥቤ ሕይወት ማለት ውጤቶች ብቻ ማለት አይደለም የሚል ነው፡፡ ጥሩ
ተማሪ መሆናችሁ ወይም አለመሆናችሁ ያን ያህል አስፈላጊ አይደለም፡፡ አሁን
ያላችሁ ስኬትም ቢሆን ደህንነታችሁን በሚመለከት ፈጽሞ ዋጋ የለውም፡፡ ዋናው

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በጸጋው የእግዚአብሄር ወገኖች ሆነናል 47

ጉዳይ እግዚአብሄር አባታችን ከዓለም ፍጥረት በፊት በክርስቶስ የመረጠን መሆኑ


ነው፡፡
ታዲያ እግዚአብሄር በጣም ብዙ ከሆኑ ሰዎች መካከል የመረጠው ማንን
ነው? እግዚአብሄር የመረጠው ከሁሉ አስቀድሞ የራሳቸው በጎ ሥራ የሌላቸውን
ነገር ግን በክርስቶስ ጽድቅ ላይ ብቻ የተደገፉትንና የታመኑትን ሰዎች ነው፡፡
በያዕቆብና ኤሳው የብሉይ ኪዳን ታሪክ ውስጥ እግዚአብሄር ያዕቆብን
እንደወደደና ኤሳውን እንደጠላ ተጽፎዋል፡፡ በመንፈሳዊ አነጋገር ዛሬ ኤሳውን
የሚመስል ሰው ምን ዓይነት እምነት አለው? እነዚህ ሰዎች ብልጦችና በመልካም
ሥነ ምግባር የታነጹ እንደሆኑ በማሰብ ራሳቸውን ያዋድዳሉ፡፡ ኤሳው ብርቱ ሰውና
ብርቱ አዳኝ ነበር፡፡ ምርጥ ተኳሽም ነበር፡፡ ያደነውን አደን ለወላጆቹ ማዘጋጀትና
መቀቀል ያዘወትር ነበር፡፡
ታናሽ ወንድሙ ያዕቆብስ? እርሱ ሁሌም የእናቱን ሽርጥ የሙጥኝ ብሎ ይዞ
በየቦታው የሚከተላት የእናቱ ልጅ ነበር፡፡ እኔም በቀድሞው ኑሮዬ ልክ እንደ
ያዕቆብ ነበርሁ፡፡ ሌላ ምሳሌ ልስጣችሁ፡፡ ቃየንንና አቤልን ተመልከቱ፡፡ ቃየንና
አቤል ሁለቱም የአዳም ልጆች እንደነበሩና ሁላችሁም እንደምታውቁት እርግጠኛ
ነኝ፡፡ ነገር ግን እነዚህ ሁለት ወንድማማቾች ፈጽሞ የተለያዩ ቁርባኖችን ለጌታ
እግዚአብሄር አቀረቡ፡፡ ቃየን ከምድር ፍሬ ሲያቀርብ አቤል ከመንጋውና ከስቡ
አቀረበ፡፡ ቃየን ከምድር ፍሬ ማቅረቡ የሚያሳየው በራሱ ስጋዊ ጉልበት
እንደታመነና መልካም ሥራዎቹንም ለእግዚአብሄር ለማሳየት እንደናፈቀ ነው፡፡
እግዚአብሄርም ዕብሪተኛ በመሆኑ የቃየንን ቁርባን አልተቀበለውም፡፡ እግዚአብሄር
በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ አማካይነት ሐጢያቶቻቸውን በሙሉ ቢደመስስም
በራሳቸው የሚመጻደቁትን እነዚህን ሰዎች በጭራሽ አልመረጣቸውም፡፡
በአንጻሩ አቤል በሜዳ በጎችን የሚጠብቅ እረኛ ነበር፡፡ እርሱ ብዙ ጉድለቶች
ያሉበት ደካማ ሰው ነበር፤ ነገር ግን የወላጆቹን እምነት የወረሰና በእግዚአብሄር
ጽድቅ ላይ ብቻ የተደገፈ ሰው ነበር፡፡ በዚህ ዘመን በእግዚአብሄር የተመረጡት
በእግዚአብሄር ጽድቅ ላይ የሚደገፉ እንዲህ ያሉ ደካማ ሰዎች ናቸው፡፡
እዚህ ላይ ልነግራችሁ እሞከርሁ ያለሁት ነገር ቢኖር እናንተና እኔ
በእግዚአብሄር የተመረጥነው በእምነታችን ምክንያት በኢየሱስ ክርስቶስ ጽድቅ
መሆኑን ነው፡፡ እግዚአብሄር የመረጠው እንደ ኤሳው በጣም ዕብሪተኛ የሆኑ
ሰዎችን ነው ወይስ ጉድለቶቹን እንዳወቀውና በእግዚአብሄር ጽድቅ ላይ
እንደተደገፈው ያዕቆብ ያሉ ሰዎችን? እግዚአብሄር ጉድለቶቻቸውን ያወቁትን ሰዎች
መርጦ ሰማያዊውን ጸጋውን እንዳለበሳቸው የታወቀ ነው፡፡ በዚህ በአሁኑ ዘመንም

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


48 በጸጋው የእግዚአብሄር ወገኖች ሆነናል

እነዚህ ሰዎች ሌላ ሳይሆኑ ከሙሉ ልባቸው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል


የሚያምኑ ሰዎች ናቸው፡፡
በሌላ አነጋገር እግዚአብሄር አብ የመረጠው በእርሱ ጽድቅ የምናምነውን
እኛን ነው፡፡ ታዲያ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ማወቅና ማመን የቻልነው
እንዴት ነው? ይህ የሆነው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ውስጥ ያለውን
የእግዚአብሄር ጽድቅ መረዳት በመቻላችን ነው፡፡ ስለዚህ እናንተን የሚመለከተው
ወሳኙ ጥያቄ በራሳችሁ ምን ያህል ከንቱ እንደሆናችሁ ማወቅ ወይም
አለማወቃችሁ፣ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ማመን የመረጣቸሁ መሆናችሁ
ወይም አለመሆናችሁ ነው፡፡ እግዚአብሄር አብ በእምነታችን ምክንያት እንዳዳነን
እየነገረን ነው፡፡ እምነታችን የተመሰረተውም ልጁ በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅ
ሐጢያቶቻችንን በሙሉ የተሸከመና ተሰቅሎ በመሞትም ለሐጢያቶቻችን የተኮነነ
በመሆኑ እውነት ላይ ነው፡፡ እግዚአብሄር በጽድቁ አማካይነት የሰጣቸውን ይህንን
ደህንነት የሚያመሰግኑትንና የሚያምኑትን ሰዎች መርጦዋል፡፡ እግዚአብሄር ልጆቹ
እንዲሆኑ የመረጣቸውም እነዚህኑ ሰዎች ነው፡፡
ስለዚህ ጉድለቶቻቸውን የሚያውቁና በእግዚአብሄር አብ የደህንነት ዕቅድ
የሚያምኑ ሁሉ የተባረኩ ናቸው፡፡ እኛም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ውስጥ
በተገለጠው የእግዚአብሄር ጽድቅ በማመን ይህንን የደህንነት ጸጋ ለብሰናል፡፡
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን የሐጢያቶችን ስርየት የተቀበላችሁ ሁላችሁ
ይህንን እንደምታስተውሉ እርግጠኛ ነኝ፡፡
ለልቦቻችን ሰላምን የሚያመጣውና በበረከቶችና በደስታም የሚሞላቸው
የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ነው፡፡ ይህ ወንጌል የእግዚአብሄር ልጅ የሆነው
ኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ ምድር በመጣ ጊዜ በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅ
ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ለአንዴና ለመጨረሻ እንደወሰደ፣ ተሰቅሎ በመሞትም
የእነዚህን ሐጢያቶች ኩነኔ ለአንዴና ለመጨረሻ እንደተሸከመና ከሙታን
በመነሳትም ከሐጢያቶቻችን ሁሉ እንደታደገን ያውጃል፡፡ ከሐጢያቶቻችሁ ሁሉ
የምትድኑት በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ስታምኑ ነው፡፡ ሰላም በልባችሁ ውስጥ
የሚሞላው እንዲህ ነው፡፡
ልባችሁ እውነተኛ ሰላም የሚያገኘው መቼ ነው? እውነተኛ ሰላም ወደ
ልባችሁ የሚመጣው ጌታ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል እውነት ሐጢያቶቻችሁን
በሙሉ በአንድ ጊዜ እንዳስወገደ ስታምኑ ነው፡፡ በሌላ አነጋገር እናንተንና እኔን
ሐጢያት አልባ የሚያደርገን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የመጣው የጌታ ጸጋ
ነው፡፡ እግዚአብሄር አብ ለእኛ ያለው ትልቁ ዕቅድ ይህ ነው፡፡ በእግዚአብሄር ጽድቅ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በጸጋው የእግዚአብሄር ወገኖች ሆነናል 49

ለተከናወነውና ለተፈጸመው ለዚህ ትልቅ የደህንነት ዕቅድና ምስጋና ይሁንለትና


እናንተና እኔ የእርሱ ልጆች መሆን ችለናል፡፡ አሁን እኛ በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል በማመን የእግዚአብሄር ልጆች ስለሆንን በልቦቻችን ውስጥ ሰላም እንዳለ
እናውቃለን፡፡
በእርሱ ጽድቅ በማመን የእግዚአብሄር ልጆች ስለሆንን የዘላለም ሕይወት
ተሰጥቶናል፡፡ እግዚአብሄር አብ ያለው እያንዳንዱ ነገርም የእናንተና የእኔ ሆንዋል፡፡
እናንተና እኔ የእግዚአብሄር ወገኖች መሆናችን እንዲህ ግሩም ያለው በረከት የሆነው
ለዚህ ነው፡፡

የዓለም ጥፋት መቅረቡን የሚያሳዩ ምልክቶች፡፡

በቅርቡ ማለቂያ ስለሌላቸው የተፈጥሮ ጥፋቶች የሚያስጠነቅቁ ብዙ


ዜናዎችና የቴሌቪዥን ፕሮግራሞች ነበሩ፡፡ በኮርያ በየአርብ ምሽት የሚተላለፍ
አንድ በተፈጥሮ ላይ የተሰራ ታዋቂ ጥናታዊ ፕሮግራም አለ፡፡ ከክፍሎቹ በአንዱ
ላይ ሳይንቲስቶች ዲፕ ኢምፓክት በሚለው ፊልም ላይ እንደሚታየው ግዙፍ
አስትሮይዶች ምድርን ሊመቷት እንደሚችሉ ሲናገሩ ሰምቻለሁ፡፡ ነገር ግን
እግዚአብሄር ይህችን ፕላኔት ምድር ሲፈጥር ምድርን ወደ እርስዋ ከሚነጉዱ
በርካታ ተወርዋሪ ኮከቦች ለመጠበቅ ሲል ጁፒተርን በአስትሮይዶች መንገድ ላይ
አስቀምጦዋታል፡፡ ስለዚህ ብዙ አስትሮይዶች ወደ ፕላኔት ምድር ሲገሰግሱ
ከጁፒተር ጋር ተጋጭተዋል፡፡ አስትሮይዶች በመንገዳቸው ላይ ጁፒተር እንቅፋት
ባትሆንባቸውና ምድራችንን ቢመቱ ኖሮ ፕላኔት ምድር ከረጅም ጊዜ በፊት
በጠፋች ነበር፡፡ እንደዚያም ሆኖ አንድ አስትሮይድ አልፎ አልፎ ምድርን ሊመታ
ይችላል፡፡ ዳይኖሰሮች ከምድር ገጽ የጠፉት ከዚህ ዓይነቱ ግጭት የተነሳ እንደሆነና
ይሀም በምድር ከባቢ አየር ላይ ሥር ነቀል ለውጦችን እንዳመጣ ይታመናል፡፡
ሳይንቲስቶች የሚሉት ይህንን ነው፡፡ ከእነርሱ ብዙዎቹም እንዲህ ያለ ክስተት
ወደፊት እንደገና ሊከሰት እንደሚችል በመተንበይ አሳብ ገብቶዋቸዋል፡፡
አሁንም እንኳን በዩኒቨርስ ውስጥ ወደ ምድር እየተወረወሩ ያሉ በርካታ
አስትሮይዶች አሉ፡፡ ምድር በአስትሮይድ ከተመታች ሙሉ በሙሉ ስለምትወድም
ሳይንቲስቶች በየጊዜው የአስትሮይዶችን መንገድ እየነደፉና እያሰሉ ይገኛሉ፡፡ አስጊ
የሆኑ አስትሮይዶችም ከምድር ጋር ከመጋጨታቸው በፊት መትተው ለመጣል ዘዴ
ለማግኘት እየሞከሩ ነው፡፡ ምድርን በ2020 ይመታል ተብሎ የሚታመንበት አንድ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


50 በጸጋው የእግዚአብሄር ወገኖች ሆነናል

ትልቅ አስትሮይድ እንዳለም ተነግሮዋል፡፡


ሳይንቲስቶች ግዙፍ የመሬት ነውጦች ሊነሱ የመቻላቸው ጉዳይም
አሳስቦዋቸዋል፡፡ የመሬት ነውጦች የሚከሰቱት ከመሬት በታች ባሉ የቴክቶኒክ
ፕሌቶች እንቅስቃሴዎች ነው፡፡ ከእነርሱ አንዱ ከደቡብ ፓስፊክ እስከ ምሥራቅ
የሰሜን አሜሪካና ጃፓን የባህር ዳርቻ ድረስ የተዘረጋው የፓስፊክ ፕሌት ነው፡፡
ይህ ፕሌት ባለፉት ጊዜያት ግዙፍ የመሬት ነውጥ ፈጥሮዋል፡፡ ሳይንቲስቶችም ሌላ
ግዙፍ የመሬት መናወጥ እንደተቃረበ የሚጠቁሙ አዳዲስ ምልክቶች በማየታቸው
ተጨንቀዋል፡፡ ኤል ኒኖ ስለሚያመጣቸውም ውጤቶች እንደዚሁ ተጨንቀዋል፡፡
ውቅያኖሶች የምድርን የአየር ጠባይ በመቆጣጠር ረገድ ወሳኝ ሚና ይጫወታሉ፡፡
ውቅያኖሶች የአየር ጠባይን የሚቆጣጠሩበት አንዱ መንገድ በባህሮች ውጫዊ
የሙቀት መጠኖች ላይ ተጽዕኖ በሚያሳድሩ ቀዝቃዛና ሞቃት የአየር ፍሰቶች
እንቅስቃሴዎች አማካይነት ነው፡፡ አሁን ችግሩ ይህ ወሳኝ ተግባር በአያሌው
መበላሸቱ ነው፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ በዚህች ፕላኔት ምድርና በመላው ዩኒቨርስ ላይ
በእርግጠኝነት ጥፋት እንደሚመጣ በግልጥ ተናግሮዋል፡፡ እኔ ግን ይህንን ጉዳይ
ያነሳሁት እናንተን ለማስደንገጥ አይደለም፡፡ ይልቁንም ከሐጢያቶቻችሁ
የሚያድናችሁ እምነት እንዳላችሁ ወይም እንደሌላችሁ እየጠየቅኋችሁ ነው፡፡
ይህንን ጥያቄ ለየት ባለ መንገድ ለማስቀመጥ የእግዚአብሄር አብን ታላቅ ችሮታ
በእርግጥ ታውቃላችሁን? እግዚአብሄር በልጁ አማካይነት የሰጣችሁን የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል ታምናላችሁን? በዚህ ወንጌል በማመንና የእግዚአብሄር ልጆችና
ሕዝብ በመሆን የሐጢያቶቻችሁን ስርየት ተቀብላችኋልን? የእግዚአብሄር ወገን
ከሆናችሁ የምትጨነቁበት ምንም ነገር የለም፡፡
እዚህ በዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ላይ ሐዋርያው ጳውሎስ ከመላው
ዩኒቨርስ ታሪክ ጋር በተዛመደ መልኩ ስለ ደህንነታችን ይናገራል፡፡ ነገር ግን
አንዳንዶቻችሁ የሐጢያቶቻችንን ስርየት በእምነት ስለተቀበልን የታሪኩ ማብቂያ
ያ ነው ትሉ ይሆናል፡፡ ነገር ግን የሐጢያቶቻችንን ስርየት መቀበላችን አስፈላጊ
ቢሆንም የክርስቶስ ሕዝቦች መሆናችንንም መረዳታችን እንደዚሁ በጣም አስፈላጊ
ነው፡፡ እግዚአብሄር አብ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ በተሸከመውና በእኛ ፋንታም
ለእነርሱ በተኮነነው በልጁ አማካይነት ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ስለደመሰሰ አሁን
እኛ በዚህ መልክ እግዚአብሄርን ከልባችን ማመስገን እንችላለን፡፡ ምክንያቱም
ይህንን እውነት እናውቃለን፤ እናምነዋለንም፡፡
እናንተና እኔ የእርሱ ክብርና ምስጋና እንደሆንን የታወቀ ነው፡፡ እግዚአብሄር

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በጸጋው የእግዚአብሄር ወገኖች ሆነናል 51

እንዲህ ተመስጋኝ የሆነው ለምንድነው? እርሱ ተመስጋኝ የሆነው ለእኛ ባደረገው


ታላቅ የደህንነት ሥራ ነው፡፡ በዚህ ምድር ላይ ከሚኖሩ በጣም ብዙ ፍጡራኖችና
በርካታ ሰዎች ውስጥ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የምናምነው እናንተና እኔ
የእግዚአብሄር ልጆች ሆነናል፡፡ ይህ እውነታ በራሱ የእግዚአብሄር ክብር ነው፡፡
ደህንነታችን ሙሉ በሙሉ የእርሱ ሥራ በመሆኑ እግዚአብሄርን እናመሰግናለን፡፡
እኛ ራሳችን የእግዚአብሄር ምስጋና ነን፡፡ ተራ ፍጥረቶች እንዴት የእግዚአብሄር
ልጆች ሊሆኑና እርሱን ሊመስሉ ቻሉ? እናንተና እኔ ሁላችንም የእግዚአብሄር
ልጆች መሆን የቻልነው በክርስቶስ በኩል በተዘጋጀው የእግዚአብሄር አብ ዕቅድ
ነው፡፡ እርሱ ጥበብን፣ ዕውቀትንና ማስተዋልን ለእኛ በመስጠት አድኖናል፡፡
እናንተስ ታዲያ? በዚህ የደህንነት እውነት ታምናላችሁን?
እግዚአብሄር በርካታ ሰዎችን ፈጥሮዋል፡፡ ከእነዚህ ሰዎች ሁሉ በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል ላይ ባለን እምነታችን አማካይነት የእግዚአብሄርን ዕቅድ
የተረዳነውና የዳንነው እኛ ብቻ ነን፡፡ እናንተና እኔ እግዚአብሄር በልጁ አማካይነት
ሐጢያቶቻችንን በሙሉ እንደደመሰሰና በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት
ሐጢያት አልባ እንዳደረገን እናውቃለን፡፡ እኛ ይህንን እውነት በእምነትና በምስጋና
የተቀበልነው እግዚአብሄር ራሱ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ስለደመሰሰ ነው፡፡
የእግዚአብሄር ልጆች የሆንነው እንደዚህ ነው፡፡ ከበርካታ ሰዎች ሁሉ እናንተና እኔ
የእግዚአብሄር ሕዝቦች እንደሆንን የምናገረው ለዚህ ነው፡፡ ይህ ታላቅ በረከት
ነው፡፡ ይህም እግዚአብሄር የሰጠን ክብር ነው፡፡ አሁን ተራ ፍጡራኖች
የእግዚአብሄር ልጆች ሆነናል፡፡ እናንተም እንደዚሁ የእርሱ ልጆች እንደሆናችሁ
እኔም ደግሞ የእግዚአብሄር ልጅ ነው፡፡ በዚህ ዓለም ላይ በርካታ ሰዎች ቢኖሩም
እግዚአብሄር ልጆቹ ለማድረግ የመረጣቸው ከአንዲት ከተማ አንድ፣ ከአንድ
ነገድም ሁለት ያህል ጥቂት ሰዎችን ነው፡፡ (ኤርምያስ 3፡14) ቁጥራችን ብዙ
አይደለም፡፡ ይህንን አስገራሚ በረከት የተቀበሉት ብዙ ሰዎች አይደሉም፡፡
ዙሪያችሁን ተመልከቱ፤ ከምታውቁዋቸው ሰዎች ውስጥ የእግዚአብሄር ልጆች
የሆኑት ምን ያህል ናቸው? ከቤተሰብ አባሎቻችሁ ምን ያህሎቹ የእግዚአብሄር
ሕዝቦች ሆነዋል? ከአገራችሁ ሰዎች ምን ያህሎቹ ይህንን በረከት ተቀብለዋል? በዚህ
ዓለም ላይ ከሚኖሩት 6 ቢሊዮን ሕዝቦች ውስጥ የሐጢያቶችን ስርየት የተቀበሉት
ምን ያህሎቹ ናቸው? ቁጥሩ በእጅጉ አነስተኛ ነው፡፡ እኛ በጣም ተባርከናል እያልሁ
ያለሁት ለዚህ ነው፡፡
በዚህ ምድር ላይ ከሚኖሩ በርካታ ሰዎች መካከል በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል በማመን የሐጢያቶችን ስርየት የተቀበሉት እጅግ በጣም ጥቂት ሰዎች

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


52 በጸጋው የእግዚአብሄር ወገኖች ሆነናል

ናቸው፡፡ በዚህ ዓለም ላይ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች ቢኖሩም የእግዚአብሄር


ልጆች ለመሆን የሐጢያቶችን ስርየት የተቀበሉት ከእነርሱ ጥቂቶቹ ብቻ ናቸው፡፡
እናንተና እኔም እንዲህ የተባረክን ሰዎች ነን፡፡ ነገር ግን ለእኛ ስለተሰጠን
የእግዚአብሄር ጸጋ ምን ያህል አዘውትረን እናስባለን? በዘወትር ሕይወታችንም
ራሳችንን ስለዚህ ጸጋ ምን ያህል አዘውትረን እናስታውሳለን?
እነዚህን ጥያቄዎች የምጠይቀው ሁላችንም የእግዚአብሄር አብን ትልቅ ዕቅድ
እንድናውቅ ነው፡፡ እግዚአብሄር አብ ለእኛ ያለውን ትልቅ ዕቅድ ከተረዳን በኋላ
እግዚአብሄር አብን ከማመስገን በቀር ምርጫ አይኖረንም፡፡ ከእግዚአብሄር አብ
የተቀበልነውን የዚህን የደህንነት በረከት ታላቅነት ከተረዳን በኋላ ሁላችንም እርሱን
ለማመስገን እንገደዳለን፡፡ 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ስብከት
3

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት
ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
በእግዚአብሄር ፍቅርና
መስዋዕትነት አማካይነት ድነናል
‹‹ ኤፌሶን 1፡1-6 ››
‹‹በእግዚአብሄር ፈቃድ የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ የሆነ ጳውሎስ በኤፌሶን
ላሉት ቅዱሳን፤ በክርስቶስ ኢየሱስም ላሉት ምዕመናን ከእግዚአብሄር ከአባታችን
ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን፡፡ በክርስቶስ በሰማያዊ
ስፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት
ይባረክ፡፡ ዓለም ሳይፈጠር በፊቱ ቅዱሳንና ነውር የሌለን በፍቅር እንሆን ዘንድ
በክርስቶስ መረጠን፤ በበጎ ፈቃዱ እንደወደደ በኢየሱስ ከርስቶስ ሥራ ለእርሱ
ልጆች ልንሆን አስቀድሞ ወሰነን፡፡ በውድ ልጁም እንዲያው የሰጠን የጸጋው ክብር
ይመሰገን ዘንድ ይህን አደረገ፡፡››

የገና በዓል ስለተቃረበ አንዳንዶቻችሁ ስለ ገና በዓል በመስበክ ፋንታ ለምን


ስለ ኤፌሶን መልዕክት እንደምሰብክ ግራ ትጋቡ ይሆናል፡፡ ነገ የገና ዋዜማ ነው፡፡
ከነገ በስቲያም የገና በዓል ቀን ነው፡፡ በእነዚያ ሁለት ቀኖች ስለ ኢየሱስ ልደት
ብሰብክ በቂ ነው፡፡ ነገር ግን አሁንም የገና በዓልንና የእግዚአብሄርን ፈቃድ ትርጉም
ከኤፌሶን 1፡1-6 አንጻር እንድታስቡት እወዳለሁ፡፡
ከዚህ ቀደም የገና በዓል ካርዶችንና ስጦታዎችን እልክላችሁ ነበር፡፡ አሁን
ግን ይህንን ለማድረግ ጊዜ ማግኘት አልቻልሁም፡፡ በጣም ባተሌ ከመሆኔ ባሻገር
ጤናዬም ያን ያህል ጥሩ አይደለም፡፡ ስለዚህ በጣም ተወጥሬያለሁ፡፡
እንድታስተውሉኝ እፈልጋለሁ፡፡ በዚህ ዓመት የገና በዓል ስጦታዎችን የመለዋወጥ
ዕድሉ ቢያልፈንም የጌታን ልደት አብረን በመደሰትና በመፈንጠዝ ማክበር
እንደምንችል ተስፋ አደርጋለሁ፡፡
በዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ አማካይነት እውነተኛውን የገና በዓል
ትርጉምና በዓሉ ያመጣልንን ነገር እንድንመረምር እወዳለሁ፡፡ አብረን ባነበብነው
የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ላይ እንዲህ ተጽፎዋል፡- ‹‹ዓለም ሳይፈጠር በፊቱ
ቅዱሳንና ነውር የሌለን በፍቅር እንሆን ዘንድ በክርስቶስ መረጠን፤ በበጎ ፈቃዱ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


56 በእግዚአብሄር ፍቅርና መስዋዕትነት አማካይነት ድነናል

እንደወደደ በኢየሱስ ከርስቶስ ሥራ ለእርሱ ልጆች ልንሆን አስቀድሞ ወሰነን፡፡››


(ኤፌሶን 1፡4-5) የገና በዓል እንደዚህ ያለውን የኢየሱስ ድንቅ ጸጋ ማወደስና
ለዚህም እርሱን ማመስገን ነው፡፡ ብዙዎቹ ሐጢያተኞች እንደሚያደርጉት ይህንን
የገና በዓል ቀን በጭራሽ በስጋዊ ተድላ ልናበላሸው አይገባንም፡፡ ስለዚህ ዛሬ
ሁላችንም ትክከለኛውን የክርስቶስ ልደት ትርጉም ከእግዚአብሄር ቃል
እንድንመረምር እወዳለሁ፡፡
በዚህ ምድር ላይ የክርስቶስ ልደት እውነተኛ ትርጉም የሚገኘው ጌታ እኛን
ከሐጢያቶቻችን ሁሉ በማዳን የራሱ የእግዚአብሄር ልጆች ባደረገንና በመንግሥተ
ሰማይ እንድንኖር በባረከን እውነታ ውስጥ ነው፡፡ የክርስቶስን ልደት ብታከብሩም
የእግዚአብሄርን ፍቅር ማድነቅ ካቃታችሁ ግዙፍ ስህተት ይሆናል፡፡ ብዙ ሰዎች
የእግዚአብሄርን ፍቅር ከክርስቶስ ልደት መረዳት ይችላሉ፡፡ በቅርቡ በአንድ
የክርስቲያን ጣቢያ የተላለፈ የአምልኮ አገልግሎት ተመለከትሁ፡፡ በቤተክርስቲያን
ውስጥ የተገኙት ሰዎችም ስሜታቸው ተነክቶ እግዚአብሄርን በዕንባዎች
ሲያመሰግኑ አየሁ፡፡ ነገር ግን እንዲህ ያሉት ውጫዊ የስሜት መግለጫዎች
ለአምላካችን ግድ ይሰጡታል ብዬ አላምንም፡፡ ሰው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
የመጣውን የእግዚአብሄር ጽድቅ ቢያውቅ፣ በእርሱ ቢያምንና በምስጋናም ቢድን
ይበልጥ የተሻለ ነው፡፡
እያንዳንዳችን የምንወደው ነገር አለን፡፡ አንዳንድ ሰዎች በተቃራኒ ጾታ
ይሳባሉ፡፡ አንዳንዶች ገንዘብን ይወዳሉ፡፡ አንዳንዶች ጌጣ ጌጦችን ይወዳሉ፡፡
አንዳንዶች አዳዲስ ልብሶችን ይወዳሉ፡፡ ሁሉም ሰው የራሱ ምርጫ አለው፡፡
ከእነዚህ ነገሮች ውስጥ ልብሶችና ጌጣ ጌጦች ሕይወት አልባ ነገሮች ናቸው፡፡
ስለዚህ የግለሰብ ፍላጎት ጉዳዮች ናቸው፡፡
ነገር ግን ሕይወት ያላቸውን ነገሮች የሚወዱ ሰዎች አሉ፡፡ ታርዛን በሚለው
ፊልም ላይ የተጫወተው ተዋናይ እንደ አንበሶችና ነብሮች ካሉ እንስሶች ጋር
ኖሮዋል፡፡ ለምን እንደዚህ ኖረ? ይህ ሰው ታርዛን የሚለውን ፊልም እየተቀረጸ ሳለ
ውሃ ውስጥ ሊሰጥም ተቃርቦ ነበር፡፡ በድርጊት የተሞላ ትዕይንት ለመስራት
እየተቀረጸ ሳለ በእሳት ተቃጥሎ ወንዝ ውስጥ ወድቆ ነበር፡፡ ያን ጊዜ አንድ አንበሳ
ዘሎ ወንዙ ውስጥ በመግባት አዳነው፡፡ ከዚያ በኋላ ከእነዚህ እንስሶች ጋር ኖረ፡፡
ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ከእነዚህ እንስሶች ጋር በትክክል መግባባት ቻለ፡፡ በፊልም ብቻ
ይወዳቸው በነበረው ፋንታ በእውነተኛ ሕይወትም እነዚህን እንስሶች በተጨበጭ
ወደዳቸው፡፡ ይህ አንበሳ ከመስመጥ ስላዳነው እስከዚህ ቀን ድረስ ከእንስሶች ጋር
እየኖረ አለ፡፡ ከፍተኛ ወጪ ቢያወጣም እነርሱን በደምብ ይንከባከባቸዋል፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በእግዚአብሄር ፍቅርና መስዋዕትነት አማካይነት ድነናል 57

አንዳንድ ሰዎች ውሾችን ይወዳሉ፡፡ አንድ ሰው ውሻውን ይንከባከብና ይወድ


ነበር፡፡ አንድ ቀን ግን ሌባ ቤቱን ሰብሮ ገባ፡፡ ሌባው ሰውየውን ሊወጋው በተቃረበ
ጊዜ ውሻው ጌታውን ለመከላከል ሲዘል በእርሱ ፋንታ ተወጋ፡፡ እንዲህ ያሉ
ታሪኮችን ከቴሌቪዥን ወይም ከመጽሐፎች እንሰማለን፡፡ አንዳንድ እንስሶች
ለጌቶቻቸው በጣም የታመኑ ናቸው፡፡ ብዙ ሰዎችም ደግሞ ቡችላዎቻቸውን
ይወዳሉ፡፡ አንዳንድ ሰዎች የተረሱና የታመሙ ውሾችን ተቀብለው በደንብ
ይንከባከቡዋቸዋል፡፡ እነዚህም ውሾች ደግሞ የአዲሶቹን ባለቤቶቻቸውን ፍቅር
ያደንቃሉ፡፡ ስለዚህ በደንብ ይከተሉዋቸዋል፤ ይታዘዙዋቸውማል፡፡
አንድ ጊዜ ደረቱ ላይ የቆሰለና ካንሰር መሰል ዕባጭ የወጣበት አንድ ውሻ
በቴሌቪዥን አየሁ፡፡ ይህ ውሻ ራሱን ችሎ መመገብ የሚችል አልነበረም፡፡ ስለዚህ
ባለቤቱ ውሻውን በአፉ ሊመግበው ሞከረ፡፡ ነገር ግን ውሻው ባለቤቱን ተመልክቶ
ሊበላ አልቻለም፡፡ ስለዚህ ባለቤቱ ለውሻው በጣም አዝኖ ወደ ውሻ ሐኪም ቤት
ወሰደውና ቀዶ ጥገና እንዲደረግለት አደረገ፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስ የወደደንና ያዳነን እንዴት ነው? ጌታ መንግሥተ ሰማይ
እንድንገባና እንድንኖር ሊባርከን ራሱን መስዋዕት አላደረገምን? እኛን
የእግዚአብሄር ልጆች ሊያደርገን እንዴት ወደደን? በሰማያዊ ስፍራዎች ያሉትን
መንፈሳዊ በረከቶች ሊሰጠንና ሊያድነን አልፈለገምን? ከጥፋትና ከሲዖል ሊያድነን
ምን አደረገልን?
አዳኛችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ሊያድነን ራሱን መስዋዕት
አደረገ፡፡ አንዳንድ ሰዎች ቡችላዎቻቸውን በጣም ስለሚወዱዋቸው
በሚታመሙበት ጊዜ እንዲድኑላቸው ማንኛውንም ነገር ለማድረግ ፈቃደኞች
እንደሚሆኑ ሁሉ ጌታችንም እኛን ለማዳን ራሱን መስዋዕት ያደረገው ስለወደደን
ነው፡፡ በሌላ አነጋገር ፈጣሪያችን እግዚአብሄር ፍጡራኖቹን አብዝቶ ስለወደደን
ሞት ተጋፍጦን ሳለ እግዚአብሄር ራሱ የሰው ስጋ ለብሶ በመጠመቅና ደሙን ለእኛ
በማፍሰስ አዳነን፡፡ ስለዚህ ሁላችንም በዚህ የገና በዓል ወቅት የጌታን
መስዋዕትነትና ፍቅር ማስታወስ ይኖርብናል፡፡
በዚህ ዓለም ላይ የሚኖሩ ክርስቲያኖች ያልሆኑ ሰዎች ብዙ መለኮታዊ
ሕላዌዎች እንዳሉ በማመን የተለያዩ አምላኮችን ያመልካሉ፡፡ ከእነርሱ አንዳንዶቹ
ከአጋንንቶች ጀምሮ ሰው ሰራሽ እስከሆኑ አምለኮች፣ ዛፎች፣ ዓለቶች፣ ተራሮች፣
ወንዞች፣ ጸሐይ፣ አንዳንድ እንደ ዘንዶዎችና ወ.ዘ.ተረፈ የመሳሰሉ አሳባዊ
ፍጡራኖች ድረስ በተግባር ሁሉንም ነገር ያመልካሉ፡፡ ነገር ግን መላውን ዩኒቨርስና
በውስጡ ያሉትን ነገሮች ሁሉ የፈጠረ አንድ እውነተኛ አምላክ ብቻ አለ፡፡ ይህ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


58 በእግዚአብሄር ፍቅርና መስዋዕትነት አማካይነት ድነናል

አምላክ ራሱን ለእኛ መስዋዕት በማድረግ ከሐጢያቶቻችን ሁሉና ከጥፋት


አድኖናል፡፡ ጌታ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት እኛ የእርሱን ፍጡራኖች
ለአንዴና ለመጨረሻ አድኖናል፡፡
ይህንን ደህንነት በስጋዊ መንገድ የምታስቡት ከሆነ በመጨረሻ ስለዚህ
ደህንነት ነገረ ዓለሙን ሁሉ ትረሱታላችሁ፡፡ ነገር ግን የጌታን የደህንነት ፍቅር
በጭራሽ ልንረሳው አንችልም፡፡ ምክንያቱም እርሱ እኛን የእርሱን ፍጡራኖች
አብዝቶ ስለወደደን ሊያድነን ራሱን መስዋዕት አድርጓልና፡፡ በዚህ የጌታ
መስዋዕትነት በማመን ምን መንፈሳዊ ጥቅሞችን አገኘን? ጌታ ለእኛ ካለው ፍቅር
የተነሳ ራሱን በዚህ ምድር ላይ መስዋዕት በማድረጉ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
የምናምን ሁላችን ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ድነናል፡፡ አንዳንድ ሰዎች ዋጋው ምንም
ያህል ይሁን ቡችሎቻቸው በሚታመሙበት ጊዜ ሁሉ እነርሱን ለማዳን
የሚቻለውን ነገር ሁሉ ያደርጋሉ፡፡ ልክ እንደዚሁ እግዚአብሄር አብ እኛን
ፍጡራኖቹን አብዝቶ ስለወደደን በተቅበዘበዝን ጊዜ ፈጣሪያችን የገዛ ልጁን ወደዚህ
ምድር ልኮ ልጁን መስዋዕት በማድረግ አዳነን፡፡

ኢየሱስ ክርስቶስ ለደህንነታችን ሲል ራሱን መስዋዕት


ባደረገ ጊዜ ፍቅሩ ምን ያህል ታላቅ ነበር?

ቡችላ ያለው ሰው የታመመውን ውሻውን ወደ እንስሳ ሕክምና መስጫ


በሚወስደውና እንዲድን ማንኛውንም ወጪ በሚሸፍንበት ጊዜ ባለቤቱ ውሻውን
ምን ያህል እንደሚወደው በድርጊቶቹ ያሳያል፡፡ ከዚህ የውሻ ዕይታ አንጻር
ከባለቤቱ ዘንድ የላቀ ምህረትን አግኝቷል ማለት እንችላለን፡፡ ነገር ግን ባለቤቱ
ለውሻው ሊያደርገው የሚችለው ያን ያህል ብቻ ነው፡፡ አፍቃሪ ባለቤት ውሻውን
ለመንከባከብ ያጠራቀመውን ገንዘብ ሁሉ ሊያጠፋና የሚቻለውን ሁሉ ሊያደርግ
ይችላል፡፡ ነገር ግን አንድን ቡችላ ለማዳን ሲል ሰብዓዊ ክብሩን የሚተው አንድም
ሰው የለም፡፡ በአንጻሩ ጌታ ኢየሱስ አብዝቶ ስለወደደን ከሐጢያቶቻችን ሁሉ
ሊያድነን ሰው ሆነ፡፡ በሌላ አነጋገር ለደህንነታችን ሲል በሰማይ ያለውን የከበረ
ማዕረጉን በፈቃዱ ተወ፡፡ በሰው መወደድ ራሱ በጣም ድንቅ ነው፡፡ ታዲያ
የእግዚአብሄርን ፍቅር መልበስ እንዴት እንዲህ ቀለለብን? የእግዚአብሄር ፍቅር
ታላቅ ነው፡፡ እንዲያውም ወሰን የለሽ ነው፡፡ እናንተና እኔ የእግዚአብሄርን ወሰን
የለሽ ፍቅር በእምነት ለብሰናል፡፡ እግዚአብሄር ራሱ ሰው በመሆንና ራሱን ለእኛ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በእግዚአብሄር ፍቅርና መስዋዕትነት አማካይነት ድነናል 59

መስዋዕት በማድረግ ከጥፋት አድኖናል፡፡ ታዲያ ሰው ይህ የእግዚአብሄር ፍቅር


እንዴት ትንሽ ነው ማለት ይችላል? እግዚአብሄር ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ያዳነን
አብዝቶ ስለወደደን ነው፡፡
ይህንን ፍቅርና ይህንን ደህንነት በመንፈሳዊ መልኩ ካየነው በሕይወታችን
ውስጥ ድንቅ ለውጦችን እናያለን፡፡ ነገር ግን የጌታን ፍቅር በስጋዊ አስተሳሰቦች
ብቻ የምናስበው ከሆነ ምንም ፋይዳ ያላቸው ለውጦችን አናይም፡፡ የእግዚአብሄር
ፍቅር ለነፍሳችን ምን አደረገልን? አሁን የእግዚአብሄርን ፍቅር በመቀበላችን
ለነፍሳችን ምን ሆኖላታል? ሁላችንም በልቦቻቸውን ውስጥ ላሉት ሐጢያቶች
መሞት ነበረብን፡፡ ነገር ግን ምን ተፈጠረ? ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ምድር ላይ
ራሱን መስዋዕት በማድረጉ እናንተና እኔ ከዓለም ሐጢያቶች ድነን የዘላለምን
ሕይወት መቀበል ችለናል፡፡ ምስጋና ለጌታ መስዋዕት ይሁንና ለሐጢያቶቻችን
የሞተችው ነፍስ ወደ ሕይወት መመለስ ችላለች፡፡
ይህ የእግዚአብሄር ፍቅር ምንኛ አስገራሚ በረከት ነው? ሁላችንም
በልቦቻችን ውስጥ ላሉት ሐጢያቶች መሞት አልነበረብንም? ራሳችንንስ በጥላቻ
መፍረድና መኮነን ልማዳችን አልነበረምን? ሁላችንም በሐጢያቶቻችን ምክንያት
በመጨረሻ ልንጠፋ የተረገመ ሕይወትን ለመኖር የታጨን የሰይጣንና የሞት ባሮች
ነበርን፡፡ ይህ ሁሉ ሆኖ ግን የእግዚአብሄር አብ ልጅ ወደዚህ ምድር መጥቶ እኛን
ከዓለም ሐጢያቶች ሁሉ ለማዳን ራሱን መስዋዕት በማድረግ የደህንነት ሥራውን
ፈጽሞዋል፡፡ ጌታ ለእኛ ካለው ፍቅር የተነሳ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ከልቦቻችን
ውስጥ በመደምሰስ አዲስ ሕይወትንና የዘላለም ሕይወትን ሰጥቶናል፡፡ የገና በዓል
ትርጉም ይህ ነው፡፡
ይህንን ትርጉም በትክክል ሳናስተውል አዳኝ በዚህ ምድር ላይ ስለተወለደ
ሁሉም ሰው መደሰት እንደሚገባው በደፈናው እያሰብን የገናን በዓል ብናከብር
ትክክለኛውን የገና በዓል ትርጉም እንጋርደዋለን፡፡ ጌታም በእኛ ያዝናል፡፡ የገና
በዓል ትርጉም እንዲህ እንዲደበዝዝ የምንፈቅድ ከሆነ ልቦቻችንም አይደሰቱም፡፡
ታዲያ በጌታ ከማያምኑ ሰዎች እንዴት የተለየን እንሆናለን? ከማያምኑ ሰዎች የበለጠ
በጣም ባተሌዎች ብንሆንና ከእነርሱ ይበልጥ ብዙ መከራ ቢገጥመን እንኳን
ከእነርሱ የተሻልን አንሆንም፡፡
ነገር ግን በጌታ ጽድቅ ከማያምኑት ሰዎች ይልቅ ስለ እኛ ጥሩ የሆነው ነገር
ለእግዚአብሄር ፍቅር ምስጋና ይሁንለትና ከሐጢያቶቻችን ሁሉ መዳናችን ነው፡፡
ስለዚህ በመጀመሪያው የጌታ ትንሳኤ ውስጥ ተሳታፊ እንሆንና ወደ መንግሥቱ
እንገባለን፡፡ እኛ የዳንነው ከዓለም ሐጢያቶች ብቻ ሳይሆን ከጥፋታችንና ከኩነኔም

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


60 በእግዚአብሄር ፍቅርና መስዋዕትነት አማካይነት ድነናል

ነው፡፡ በሐጢያቶቻችን ምክንያት መዳኛ በሌለው ሕመም ብንሰቃይም


በእግዚአብሄር ፍቅር ተፈውሰናል፡፡ ይህ እንዴት ያለ ግሩም በረከት ነው? ስለዚህ
በዚህ የገና በዓል የእግዚአብሄርን ፍቅር የመልበሳችንን እውነታ በጭራሽ አንርሳ፡፡
እናንተና እኔ በራሳችን ውስጥ አንዳች የሚረባ ነገር ማግኘት ባንችልም
ለጌታችን ጽድቅ ምስጋና ይሁንለትና የእግዚአብሄርን ፍቅር ለብሰናል፡፡ ስለዚህ
አሁን ለራሳችን ዋጋ መስጠት እንችላለን፡፡ በሌላ አነጋገር የእግዚአብሄርን ጸጋ
ስለለበስን ራሳችንን ስንመለከት ለእግዚአብሄር የከበርን እንደሆንን እናውቃለን፡፡
በአዲስ መልክ ባገኘነው ማዕረግም ልንኮራ እንችላለን፡፡ በዚህ ምድር ላይ ባለጠጎች
ባንሆንም የእግዚአብሄር ልጆች ሆነን እውነተኛው ማዕረጋችን በመመለሱ
በመንፈሳዊ መልኩ ተባርከናል፡፡ መኖራችን ዋጋ ያለውና የከበረ መሆኑን
የምናውቀው ለዚህ ነው፡፡ በዚህ የገና በዓል ወቅት ጌታን የምናመሰግነው ለዚህ
ነው፡፡
አሁን እዚህ በኤፌሶን 1፡1-6 ላይ የእግዚአብሄርን ፍቅር ይበልጥ በጥልቀት
እንመርምር፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ በወንጌል የተሰበከውን የእግዚአብሄርን ፍቅር
ሲያብራራ ‹‹ከእግዚአብሄር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም
ለእናንተ ይሁን›› (ኤፌሶን 1፡2) በማለት ጀምሮዋል፡፡ ከዚያም ጳውሎስ በቁጥር 3-
6 ላይ የእግዚአብሄርን ፍቅር ይበልጥ በዝርዝር ማብራራት ቀጠለ፡፡

መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሄር የሰማይን መንፈሳዊ በረከቶች የሰጠው


ለማን ነው ይላል?

በኤፌሶን 1፡3 ላይ ጌታ ‹‹በክርስቶስ በሰማያዊ ስፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ


የባረከን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ›› በማለት በሰማያዊ ስፍራዎች
ውስጥ ያሉትን መንፈሳዊ በረከቶች ለማን እንደሰጠ ያብራራልናል፡፡ እዚህ ላይ
የኢየሱስ ክርስቶስ አባት በሰማያዊ ስፍራዎች ያለውን መንፈሳዊ በረከት ሁሉ በልጁ
በክርስቶስ በኩል እንደሰጠን በግልጽ ተጽፎዋል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሄር
አብ መንፈሳዊ በረከቶችን የሰጠን በማን በኩል እንደሆነ ይናገራል? እግዚአብሄር
አብ የሰማይን መንፈሳዊ በረከት ሁሉ በልጁ በኩል እንደሰጠን ይናገራል፡፡ ጳውሎስ
እዚህ ላይ ‹‹የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት›› እንደባረከን ጽፎዋል፡፡
ይህ ማለት እግዚአብሄር አብ በልጁ አማካይነት አድኖናል ማለት ነው፡፡
እግዚአብሄር ነፍሳችንንና መንፈሳችንን ከዓለም ሐጢያቶች ሁሉ አድኖዋል፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በእግዚአብሄር ፍቅርና መስዋዕትነት አማካይነት ድነናል 61

እግዚአብሄር እንዲህ ያዳነን በኢየሱስ ክርስቶስ ጽድቅ አማካይነት ነው፡፡ በሌላ


አነጋገር እግዚአብሄር አብ ልጁን ኢየሱስ ክርስቶስን ስጋ አልብሶ ወደዚህ ምድር
በመላክ፣ ከአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅም የሰውን ዘር ሐጢያቶች በሙሉ
እንዲቀበል በማድረግና ለእኛ ካለው የተትረፈረፈ ፍቅር የተነሳም ይህንን ልጅ
በይፋ መስዋዕት በማድረግ በልቦቻችን ውስጥ ያሉትን ሐጢያቶች በሙሉ ደምስሶ
ነፍሳችንን ሐጢያት አልባ አደረጋት፡፡ እግዚአብሄር በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
የምናምነውን ሁላችንን የራሱ ልጆች አድርጎ የተቀበለን እንዲህ አብዝቶ ስለወደደን
ነው፡፡
በሰማያዊ ስፍራዎች ያለውን መንፈሳዊ በረከት ሁሉ የተቀበልነው እንደዚህ
ነው፡፡ እግዚአብሄር ራሱ ስለ እኛ በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅ፣ በመስቀል ላይ
በመሞትና ከሙታን በመነሳት ነፍሳችንን ከሐጢያቶቻችን ሁሉ አዳናት፡፡ ስለዚህ
ጌታ በፍቅሩና በመስዋዕትነቱ ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ስላዳነን የእግዚአብሄር ልጆች
ሆነናል፡፡ በዚህ ደህንነት በማመንም በሰማያዊ ስፍራዎች ያለውን መንፈሳዊ በረከት
ሁሉ ተቀብለናል፡፡
ኢየሱስ አዳኛችን ሆኖ ወደዚህ ምድር በመምጣት ራሱን መስዋዕት አድርጎ
በልቦቻችን ውስጥ ያሉትን ሐጢያቶች ቢደመስስም ብዙ ሰዎች በዚህ አያምኑም፡፡
እነዚህ ሰዎች የገናን በዓል ትክክለኛ ትርጉም በተጨባጭ አያውቁም፡፡ እነዚህ ሰዎች
ጌታ ስለ እኛ ያደረገውን መስዋዕትነት የሚተርከውን የክርስቶስን ልደት እውነተኛ
ፋይዳ ለማክበር ገና አልተዘጋጁም፡፡
እግዚአብሄር አብ ያዳነን በኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ እርሱ በክርስቶስ ጽድቅ
አማካይነት ከልቦቻችንና ከነፍሳችን ሐጢያቶች አድኖናል፡፡ ቀደም ብዬ
እንዳወሳሁት በአካል የተለወጠው ስጋችን አይደለም፡፡ ነገር ግን ከሐጢያቶቻችንና
ከኩነኔ ሁሉ የተለወጡት ልቦቻችን ናቸው፡፡ የእናንተና የእኔ ልብ ሙሉ በሙሉ
ነጽተው ተለውጠዋል፡፡ እግዚአብሄር ልቦቻችንን በኢየሱስ ክርስቶስ ውስጥና
በኩል ሙሉ በሙሉ ለውጦዋቸዋል፡፡
የእግዚአብሄር አብ ልጅ የሆነው ኢየሱስ ተስፋ በተሰጠው መሠረት
በድንግል ማርያም ስጋ በኩል ተወለደ፡፡ እርሱም ንጉሣችን ነው፡፡ እርሱ የነገሥታት
ንጉሥም ነው፡፡ ይህ ንጉሥ ራሱ ለእነርሱ ስጋውን መስዋዕት በማድረግ የራሱን
ሕዝብ አዳናቸው፡፡ ንጉሣችን ኢየሱስ ሐጢያቶቻችንን በሰውነቱ ለመሸከም
በመጠመቅ፣ ስጋው በመስቀል ላይ እንዲሰቀል አሳልፎ በመስጠትና ደሙን አፍስሶ
ለመሞትም ራሱን መስዋዕት በማድረግ አዳነን፡፡ ይህ ሐይል ሁሉ ያለው
የእግዚአብሄር መስዋዕት ነው፡፡ ይህ የሁሉን ቻዩ አምላክ መስዋዕት ነው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


62 በእግዚአብሄር ፍቅርና መስዋዕትነት አማካይነት ድነናል

እግዚአብሄር ከፍቅሩ የተነሳ ያዳነን እንዲህ ባለው አስገራሚ መስዋዕት አማካይነት


ነው፡፡
እዚህ ላይ ሐዋርያው ጳውሎስ እግዚአብሄር አብ በኢየሱስ አዳነን በማለት
ፋንታ በክርስቶስ አዳነን ይላል፡፡ ለምን እንዲህ እንዳለ መረዳት በጣም
ያስፈልገናል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስን አስተውለን ስናነብ ሁላችንም የውሃውና የመንፈሱ
ወንጌል ትክክለኛው የደህንነት እውነት እንደሆነ ወዲያውኑ መገንዘብ እንችላለን፡፡
እኔ ዳግመኛ ከመወለዴ በፊት በመስቀሉ ደም ብቻ ማመን አዘወትር በነበረ ጊዜ
በኤፌሶን ውስጥ የሚገኘውን ይህንን ምንባብ ባነብም እንኳን የእግዚአብሄርን አብ
ፈቃድ ማወቅ አልቻልሁም፡፡ እግዚአብሄር አብ በኢየሱስ ከማለት ፋንታ ለምን
በክርስቶስ በሰማያዊ ስፍራዎች በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ ባረከን እንዳለ መረዳቱ
ከእኔ አቅም በላይ ነበር፡፡ ስለዚህ ሰው በኢየሱስ ቢያምን ወደ ክርስቶስ ይመጣል
ብዬ አሰብሁ፡፡ ነገር ግን እዚህ ላይ እግዚአብሄር አብ ‹‹በክርስቶስ›› ባረከን ማለት
የእግዚአብሄር አብ ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ የልቦቻችንንና የነፍሳችንን ሐጢያቶች
ለመደምሰስ የሰው ስጋ ለብሶ ወደዚህ ምድር መጣ፤ በአጥማቂው ዮሐንስ
በመጠመቅም ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ደመሰሰ፤ በእኛ ፋንታም ተሰቅሎ ሞተ፤
ከሙታንም ተነሳ፤ በዚህም አዳኛችን ሆነ ማለት ነው፡፡ ስለዚህ እያንዳንዱ ሰው
በሰማያዊ ስፍራዎች ውስጥ ያሉትን መንፈሳዊ በረከቶች በሙሉ መቀበል
የሚችለው በክርስቶስ ነው፡፡ ሰው ሁሉ በእምነት ሊባረክ የሚችለው በኢየሱስ
ክርስቶስ ብቻ ነው፡፡

በሰማያዊ ስፍራዎች ያለውን መንፈሳዊ በረከት ሁሉ መቀበል


የምንችለው ራሱ አምላክ የሆነው ክርስቶስ ለእኛ ለሐጢያተኞች
እንዴት መስዋዕት እንደሆነ በትክክል ስናውቅና ስናምን ብቻ ነው፡፡

እግዚአብሄር እኛን በእርሱ የምናምን አማኞች በትክክል ያዳነን እንዴት ነው?


እርሱ የሰው ስጋ ለብሶ ወደዚህ ምድር በመምጣት አዳነን፡፡ የሰው ዘር ወኪል
በሆነው በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅም ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ተሸከመ፡፡
ተሰቅሎ በመሞትም ስጋውን አሳልፎ ሰጠ፡፡ እግዚአብሄር ለሁላችንም ያሳየው
ፍቅር ይህ ነው፡፡ ጌታን የምናመሰግነው ለዚህ ነው፡፡ ከጥልቅ ልቦቻችን እንዲህ
አመስጋኞችና ደስተኞች የሆንነውም ለዚህ ነው፡፡
ማናችንም የኢየሱስ ክርስቶስን ልደት መላምታዊ እሳቤ ብቻ አድርገን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በእግዚአብሄር ፍቅርና መስዋዕትነት አማካይነት ድነናል 63

ልንመለከተው ወይም እውነተኛ ፋይዳውን በትክክል ሳናስተውል በደመ ነፍስ


ልናከብረው አይገባንም፡፡ ይልቁንም እግዚአብሄር በክርስቶስ በኩል ስላዳነን
ለፍቅሩና ለመስዋዕትነቱ ከሙሉ ልባችን፣ ከሙሉ አሳባችንና ከሙሉ ነፍሳችን
ልናመሰግነው ይገባናል፡፡ አሁን እናንተና እኔ በልቦቻችን ውስጥ ሐጢያት አልባ
የሆንነው ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱን ስለ እኛ መስዋዕቱ በማድረጉ ብቻ ነው፡፡ ነገር
ግን ማንም ሰው ማንኛውንም ወንጌል በማመን ብቻ ሐጢያት አልባ መሆን
አይችልም፡፡ ሁላችንም ልቦቻችን ሐጢያት አልባ እንደሆኑ እናውቃለን፡፡ ነገር ግን
ይህ የሆነው በጌታ የውሃና የመንፈስ ወንጌል ለሚያምኑ ሰዎች ብቻ እንደሆነ
እናውቃለን፡፡ ሰው በልቡ ውስጥ ሐጢያት እንደሌለበት ቢናገርም እንኳን ይህ ሰው
በእግዚአብሄር ፍቅር እስካላመነ ድረስ ሐጢያቶቹ በሙሉ በውስጡ ይኖራሉ፡፡
በአንጻሩ እኛ በኢየሱስና በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል እናምናለን፡፡ ስለዚህ ምንም
አካላዊ ለውጦችን ባናይም እንኳን በልቦቻችን ውስጥ የቀሩ ሐጢያቶች የሉብንም፡፡
በልቦቻችን ውስጥ ሐጢያት አለመኖሩ የተለመደ እንደሆነ እናስብ ይሆናል፡፡
ነገር ግን ይህንን እንደ ቀላል ነገር ልንወስደው አይገባንም፡፡ በተቃራኒው ሁሌም
ጌታ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ለመውሰድ በአጥማቂው ዮሐንስ እንደተጠመቀና
ልቦቻችንን ሐጢያት አልባ ለማድረግም የእነዚያን ሐጢያቶች ዋጋ ሁሉ እንደከፈለ
ማስታወስ ይገባናል፡፡ የእግዚአብሄር ልጅ እንዲህ ራሱን ስለ እኛ መስዋዕት
በማድረግ አድኖናል፡፡ እርሱ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ከልቦቻችን ውስጥ
ደምስሶዋል፡፡ ታዲያ ይህንን የማናደንቀው እንዴት ነው? ይህንን አስደናቂ ፍቅር
ዋጋ የማንሰጠው እንዴት ነው?
ልቦችን ሐጢያት አልባ የሆኑት ኢየሱስን በአንድ ወይም በሌላ መንገድ
በማመናችን አይደለም፡፡ ይልቁንም በዚህ እውነት በማመን ሐጢያት አልባ
የሆንነው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ውስጥ እንደተገለጠው ራሱን ለእኛ
መስዋዕት ባደረገው በኢየሱስ ክርስቶስ የተነሳ ነው፡፡ ይህንን ጸጋ የትምህርት ጉዳይ
አድርገን ብቻ ልናስበው አይገባንም፡ በፋንታው የክርስቶስን ልደት በእምነት
ልናከብረው ይገባናል፡፡
ጌታችን በመጨረሻው እራት ወቅት እንዲህ አለ፡- ‹‹ይህ እንጀራ ስጋዬ ነውና
ውሰዱና ብሉት፤ ይህ ወይን ደሜ ነውና ወስዳችሁ ጠጡት፡፡ እኔ እስክመጣ
ድረስም ይህንን ለመታሰቢያዬ አድርጉት፡፡›› ጌታ ወደዚህ ምድር መጥቶ በውሃና
በደም እንዳዳነን እንድናምንና እንድናስታውስ እየነገረን ነው፡፡ የደህንነት ጸጋውን
በልቦቻችን ውስጥ እንድንጽፈውና በጭራሽ እንዳንረሳው እያዘዘን ነው፡፡ ስለዚህ
ከጌታ ፍቅርና ለእኛ ካደረገው መስዋዕትነቱ የተነሳ ልቦቻችን ሐጢያት አልባ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


64 በእግዚአብሄር ፍቅርና መስዋዕትነት አማካይነት ድነናል

የመሆናቸውን እውነታ በጭራሽ መርሳት የለብንም፡፡


የጌታን ፍቅር በጭራሽ አቅልላችሁ ልትወስዱት አይገባም፡፡ በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል ስለምታምኑ ሐጢያት አልባ የሆናችሁት ያለ ምንም ዋጋ እንደሆነ
ልታስቡ አይገባም፡፡ ይልቁንም ጌታ ራሱን ለእናንተ መስዋዕት እንዳደረገና
እናንተም የሁሉን ቻዩን አምላክ ፍቅር እንደለበሳችሁ ልትገነዘቡ ይገባችኋል፡፡
ስለዚህ ሁሌም የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል እንድታስቡ እጠይቃችኋለሁ፡፡
እርሱ እስከሚመለስበት ቀን ድረስም ጌታን እንድታመሰግኑ እጠይቃችኋለሁ፡፡
ይህንን ማድረጉ ተገቢ ነው፡፡
በተጨባጭ አመስጋኝ ልትሆኑበት በሚገባችሁ ነገር አመስጋኝ እንደምትሆኑ
ልታውቁ ይገባል፡፡ የእግዚአብሄርን ጸጋ የሚያውቁት እነዚህ ሰዎች ናቸው፡፡ በዚህ
ስጋዊ ዓለም ውስጥም እንኳን ታማኝነት ከፍተኛ ዋጋ አለው፡፡ ከረጅም ጊዜ በፊት
ሕይወታቸውን ለነገሥታቶቻቸው አሳልፈው የሰጡ ታማኝ ዜጎች በመጪዎቹ
ትውልዶች ሲታወሱ ይኖራሉ፡፡ ስለዚህ ጌታችን ራሱን መስዋዕት በማድረግ
ልቦቻችንንና ነፍሳችንን ሐጢያት አልባ አድርጎ ሳለ እንዴት ይህንን
ሳናስታውሰውም ሆነ ለጌታ ምስጋና ሳናቀርብለት በቀላሉ ችላ ልንለው ይቻለናል?
የእግዚአብሄር ጸጋ ለዘላለም በልቦቻችን ውስጥ ከብሮ መቀመጥ ይኖርበታል፡፡
ይህንን የገና በዓል የምናከብረው እንዲህ ባለ ስሜት ነው፡፡
ልቦቻችንና ነፍሶቻችን በተጨባጭ ሐጢያት ስለሌለባቸው እናንተና እኔ
መንግሥተ ሰማይ ገብተን በዚያ እንኖራለን፡፡ ሁላችንም በቅርቡ መንግሥተ ሰማይ
እንገባና በዚያ ለዘላለም እንኖራለን፡፡ እግዚአብሄር በዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ
ምንባብ ላይ በክርስቶስ በሰማያዊ ስፍራዎች በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ እንደባረከን
እንደተናገረ ሁሉ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የምናምን ሁላችን መንግሥተ
ሰማይ ለመግባትና ለመኖር እንባረካለን፡፡ ሁላችንንም የሚጠብቀን በመንግሥተ
ሰማይ ያለው ክቡር ሕይወት ነው፡፡ በረከታችንም ሌላ ሳይሆን ይህ ነው፡፡
የምንመካበት ነገር ቢኖር በዚህ ምድር ላይ ያለን ሕይወታችን ብቻ ቢሆን
ኖሮ ራሳችንን የእግዚአብሄር ብሩካን ሕዝቦች ብለን መጥራት ባልቻልንም ነበር፡፡
እግዚአብሄር ግን እኛን መንግሥተ ሰማይ እንድንገባና በዚያ እንድንኖር ለማስቻል
ራሱን መስዋዕት አደረገ፡፡ የእግዚአብሄር ልጅ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ለመደምሰስ
በጥምቀቱ አማካይነት ተሸከማቸውና ዋጋቸውን ሁሉ ለመክፈል በመስቀል ላይ
ራሱን መስዋዕት አደረገ፡፡ በዚህም ጌታ በሰማያዊ ስፍራዎች በመንፈሳዊ በረከት
ሁሉ ባረከን፡፡ ሁላችንም እምነታችንን በእግዚአብሄር ጽድቅ ላይ በማኖር ጌታን
ልናመሰግን የሚገባን ለዚህ ነው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በእግዚአብሄር ፍቅርና መስዋዕትነት አማካይነት ድነናል 65

ወደ ኤፌሶን 1፡4-5 እንመለስ፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ እግዚአብሄር የራሱ


ልጆች ሊያደርገንና መንግሥተ ሰማይ እንድንገባም ሊባርከን ተጨባጭ ዕቅድ ነድፎ
እንደፈጸመው ጨምሮ አብራርቶልናል፡፡ ወደ እነዚህ ቁጥሮች እንመለስ፡- ‹‹ዓለም
ሳይፈጠር በፊቱ ቅዱሳንና ነውር የሌለን በፍቅር እንሆን ዘንድ በክርስቶስ መረጠን፤
በበጎ ፈቃዱ እንደወደደ በኢየሱስ ክርስቶስ ሥራ ለእርሱ ልጆች ልንሆን አስቀድሞ
ወሰነን፡፡›› (ኤፌሶን 1፡4-5) እዚህ ላይ መጽሐፍ ቅዱስ ግልጥ እንደሚያደርገው
እግዚአብሄር አብ ከዓለም ፍጥረት በፊት በክርስቶስ መረጠን፡፡ ሰዎች ሁሉ
የተፈጠሩት በእግዚአብሄር አብ አምሳል ነበር፡፡ አብ እነርሱን ልጆቹ
ሊያደርጋቸውና በመንግሥተ ሰማይ ይኖሩ ዘንድ ሊባርካቸው እንዳቀደ በግልጥ
ተጽፎዋል፡፡
እግዚአብሄር ከዓለም ፍጥረት በፊት በክርስቶስ መረተን ማለት በትክክል
ምን ማለት ነው? ይህ ማለት እግዚአብሄር በኢየሱስ ክርስቶስ መስዋዕታዊ የስርየት
ሥራ አማካይነት አድኖናል ማለት ነው፡፡ እግዚአብሄር አብ ዩኒቨርስን ከመፍጠሩ
በፊት እንኳን፣ እናንተንና እኔን ከማበጀቱም በፊት እንኳን አስቀድሞ ወንዶችና
ሴቶች ልጆቹ ሊያደርገን በክርስቶስ አቅዶ ነበር፡፡ እግዚአብሄር በልጁ መስዋዕት
አማካይነትም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምኑትን ሁሉ በልቦቻቸው ፈጽሞ
ሐጢያት አልባ እንዲሆኑ በማድረግ ይህንን ዕቅድ ፈጸመ፡፡
እኛ በትክክል ደህንነታችንን ያገኘነውና የእግዚአብሄር ልጆች የሆንነው
አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ለማዳን ራሱን ስለሰዋ ነው፡፡ እናንተና እኔ
ከሐጢያቶቻችን ሁሉ የዳንነው የእግዚአብሄር ልጅ ራሱን መስዋዕት በማድረጉ
ነው፡፡ እግዚአብሄር እዚህ በዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ላይ በክርስቶስ
እንደመረጠን የተናገረው ለዚህ ነው፡፡
እግዚአብሄር መርጦናል ሲባል አንዳንድ የቃለ እግዚአብሄር ምሁራን
እንደሚሉት እርሱ አንዳንድ ሰዎችን በዘፈቀደ ሲመርጥ ሌሎችን አልመረጠም
ማለት አይደለም፡፡ ይልቁንም የዚህ ግልጥ ትርጉም እግዚአብሄር በክርስቶስ
የመረጠን መሆኑ ነው፡፡ ሰዎች ሁሉ ሐጢያት ስለሰሩ የእግዚአብሄር ክብር
ጎድሎዋቸዋል፡፡ ነገር ግን እግዚአብሄር አብ ሲፈጥረን በድክመቶቻችን የተነሳ
ሐጢያት እንደምንሰራ አስቀድሞ ያውቅ ነበር፡፡ ስለዚህ በልጁ መስዋዕትና ፍቅር
የተፈጸመውን የእግዚአብሄር ጽድቅ የሚገልጠውን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
የሚያምኑ ሁሉ የእርሱ ልጆች ይሆኑ ዘንድ የደህንነት ሥራውን ፈጸመ፡፡ በክርስቶስ
ፍቅር፣ በጽድቅ መስዋዕቱና በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምኑ ሰዎች ሁሉ
በእግዚአብሄር ሲመረጡ የማያምኑ ሰዎች ያልተመረጡት ለዚህ ነው፡፡ ስለዚህ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


66 በእግዚአብሄር ፍቅርና መስዋዕትነት አማካይነት ድነናል

እነዚህ የማያምኑ ሰዎች በሐጢያቶቻቸው ምክንያት በእግዚአብሄር


ይፈረድባቸዋል፡፡
እግዚአብሄር አብ ይህንን ዩኒቨርስ ከመፍጠሩም በፊት እንኳን እንዲህ ያለ
ዕቅድ ነበረው፡፡ ሰዎች በድክመቶቻቸው ምክንያት በሐጢያት እንደሚወድቁ
ስላወቀ በዚህ የወልድ የጽድቅ ድርጊት የሚያምኑ ሁሉ በልቦቻቸው ውስጥ
ሐጢያት አልባ እንዲሆኑና አንዳች ነውር ወይም እድፍ የሌለባቸው የእግዚአብሄር
ልጆች እንዲሆኑ እግዚአብሄር በጥምቀቱ አማካይነት ሐጢያቶቻቸውን በሙሉ
እንዲቀበልና ተሰቅሎ ራሱን መስዋዕት እንዲያደርግ ልጁን ወደዚህ ምድር ላከው፡፡

ደህንነታችን የተፈጸመው በእግዚአብሄር ዕቅድ መሠረት እንደሆነ


ሁላችንም ልንገነዘብ ይገባናል፡፡

በዚህ ዓለም ላይ ካሉት የዘመኑ ክርስቲያኖች መካከል ፕሪስባይቴርያኖች


በእነርሱ ትምህርቶች የሚያምን ማንኛውም ሰው የተመረጠ ሲሆን ሌላው ሁሉ
ግን እንዳልተመረጠ ለመናገር ያዘነብላሉ፡፡ ይህ ግን ፈጽሞ የማይረባ አባባል ነው፡፡
እነርሱ ወሰን የሌለው የምርጫ ትምህርት ተብሎ የሚታወቀውን ፈጽሞ መሠረተ
ቢስ ትምህርት የሙጥኝ ብለዋል፡፡
እንዲህ ካለው ከማንኛውም ትምህርት ይበልጥ በጣም ጠቃሚው ነገር
መጽሐፍ ቅዱስ በትክክል የሚነግረን ነገር ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ በሰው ዕውቀት
መሠረት የተጻፈ አልነበረም፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ በዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ
ምንባብ ላይ እርሱ በእግዚአብሄር ፈቃድ የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ በመሆኑ
በክርስቶስ ታማኝ ለነበሩት የኤፌሶን ቅዱሳኖች መልዕክቱን እንደጻፈ ተናግሮዋል፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ የክርስቶስን ጽድቅ በያዘው የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል
በማመን ከሐጢያቶቹ ሁሉ የዳነ ሰው ነበር፡፡ በልቡ ውስጥም መንፈስ ቅዱስ
አድሮበት ነበር፡፡ ይህ ማለት በኤፌሶን ቤተክርስቲያን ላሉት ቅዱሳን እንዲጽፍ
ያነሳሳው በሐዋርያው ጳውሎስ ልብ ውስጥ የነበረው መንፈስ ቅዱስ ነው ማለት
ነው፡፡
ይህ ለእኛ ቢሰጠን ኖሮ አብዛኞቻችን እግዚአብሄር አብ ከዓለም ፍጥረት
በፊት በኢየሱስ በኩል እንዳዳነን እንጽፍ ነበር፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ የጻፈው ግን
ያንን አይደለም፡፡ ታዲያ ምን ጻፈ? እርሱ ይህንን ጻፈ፡- ‹‹ዓለም ሳይፈጠር በፊቱ
ቅዱሳንና ነውር የሌለን በፍቅር እንሆን ዘንድ በክርስቶስ መረጠን፡፡›› (ኤፌሶን 1፡4)

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በእግዚአብሄር ፍቅርና መስዋዕትነት አማካይነት ድነናል 67

እዚህ ላይ ጳውሎስ እግዚአብሄር ‹‹ዓለም ሳይፈጠር…በክርስቶስ›› እንዳዳነን በግልጥ


ተናግሮዋል፡፡
‹‹ክርስቶስ›› የሚለው ቃል መጽሐፍ ቅዱሳዊው ትርጉም የተቀባ ማለት ነው፡፡
(ዳንኤል 9፡24-26) በቅዱሳት መጽሐፍት ውስጥም የተቀቡ ሦስት ዓይነት ሰዎች
ነበሩ፡፡ እነርሱም ነገሥታት፣ ካህናትና ነቢያት ነበሩ፡፡ ስለዚህ ‹‹ክርስቶስ›› የሚለው
ስም የነገሥታት ንጉሥና የሰው ዘር ሁሉ ፈጣሪ የሆነው ኢየሱስ ሰዎችን ሁሉ
ከሐጢያቶቻቸው ለማዳን የሰው ስጋ ለብሶ ወደዚህ ምድር መጣ ማለት ነው፡፡
ደግሞም ኢየሱስ ሁላችንንም ፈጽሞ ያድን ዘንድ የሰውን ዘር ሐጢያቶች በሙሉ
ለመሸከም በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅና የእነዚህን ሐጢያቶች ዋጋ
ለመክፈልም በመስቀል ላይ በመሞት ሊቀ ካህን ሆኖ ተግባሩን ፈጸመ ማለትም
ነው፡፡ ኢየሱስ የሊቀ ካህን ቢሮ በአደራ ከተሰጠው በኋላ በአጥማቂው ዮሐንስ
በመጠመቅ በዚህ ዓለም ላይ ያለውን የእግዚአብሄር ሕዝብ ሐጢያቶች በሙሉ
በስጋው ተቀበለ፡፡ ከዚያም ተሰቅሎ በመሞት የእያንዳንዱን ሐጢያት ዋጋ ከፈለ፡፡
በዚህም በእርሱ የሚያምኑትን አማኞች በሙሉ ለማዳን ክህነታዊ ተግባሩን
ፈጸመ፡፡ ከዚህም በላይ ጌታችን ይህንን እውነት በእግዚአብሄር ቃል አማካይነት
አስታውቆናል፡፡ ስለዚህ ኢየሱስ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ለመደምሰስ ስጋውን
ለእግዚአብሄር አብ አቀረበ፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ በኤፌሶን ምዕራፍ 1 ላይ የዳንነው ‹‹በክርስቶስ›› እንደሆነ
በተደጋጋሚ የሚያበክረው ለዚህ ነው፡፡ ስለዚህ ይህንን እውነት የተረዳና በእርሱ
ያመነ ሁሉ ከሐጢያቶቹ ሁሉ ይድናል፡፡ ምክንያቱም መጽሐፍ ቅዱስ በመንፈስ
ምሪት የተጻፈ ነውና፡፡ አሁን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን የሐጢያቶችን
ስርየት የተቀበሉ ሁሉ በልቦቻቸው ውስጥ ለሚያድረው መንፈስ ቅዱስ ምስጋና
ይድረሰውና ይህንን እውነት ወደ ማወቅ ደርሰዋል፡፡
እኔ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ከመረዳቴ በፊት በስብከቶቼ ውስጥ
የኤፌሶንን መልዕክት ለማብራራት በትጋት ሞክሬያለሁ፡፡ ነገር ግን መጽሐፍ ቅዱስ
እግዚአብሄር ‹‹በክርስቶስ›› እንዳዳነን ሲናገር በትክክል ምን ማለቱ እንደሆነ
አላውቅም ነበር፡፡ እግዚአብሄር ‹‹በክርስቶስ›› እንዳዳነኝ በትክክል መረዳት
የቻልሁት የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ካስተዋልሁ በኋላ ብቻ ነበር፡፡
እግዚአብሄር አብ በክርስቶስ የመረጠን፣ የወደደን፣ ሐጢያት አልባ ያደረገንና
በመንግሥተ ሰማይም የሚያስቀምጠን በክርስቶስ ነው፡፡ እርሱ በክርስቶስ
አማካይነት በመጣው ደህንነት የሚያምኑትን ሁሉ ልጆቹ አድርጎ
ተቀብሎዋቸዋል፡፡ የእግዚአብሄር ልጅ የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ ለመቀበል

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


68 በእግዚአብሄር ፍቅርና መስዋዕትነት አማካይነት ድነናል

በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅ በዚህ ምድር ላይ ባደረገው መስዋዕትነትና


በመስቀል ላይ ባፈሰሰው ደም እግዚአብሄር አብ በክርስቶስ የምናምነውን
ሁላችንንም አድኖናል፡፡ ፈጣሪ አምላክ ለጥቂት ጊዜ ሰው የሆነውና ማስተሰርያችን
ሆኖ ራሱን መስዋዕት ያደረገው የራሱን ሕዝብ ከሐጢያቶቻቸው ለማዳን ነው፡፡
የእግዚአብሄር ልጅ በጥምቀቱ አማካይነት የሰውን ዘር ሐጢያቶች በሙሉ በገዛ
ስጋው ተቀበለ፡፡ ከዚያም በመሰቀልና በልቡ ውስጥ ያለውን ደም በሙሉ አፍስሶ
በመሞት የእነዚህን ሐጢያቶች ሁሉ ኩነኔ ተሸከመ፡፡ ስለዚህ ጌታ ራሱን ለእኛ
መስዋዕት በማድረግ የሐጢያቶቻችንን ዋጋ በሙሉ ከፈለ፡፡ በዚህም እናንተንና
እኔን በመስዋዕቱና በፍቅሩ አማካይነት አዳነን፡፡ አሁን በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል የምናምነውንም ሁሉ ፈጽሞ ሐጢያት አልባ አድርጎናል፡፡ ሐጢያቶቻችንን
በሙሉ ያስወገደው ጌታ ነው፡፡

ይህ የደህንነት ሥራ በእግዚአብሄር አብ የታቀደው ከዓለም ፍጥረት


በፊት ነበር፡፡

እግዚአብሄር አብ ይህንን ዓለምና በውስጡ ያሉትን ፍጡራኖች ከመፍጠሩ


በፊት በልጁ መስዋዕትነትና ፍቅር አማካይነት አስቀድሞ ልጆቹ ሊያደርገን አቅዶ
ነበር፡፡ በሌላ አነጋገር እግዚአብሄር በክርስቶስ ጽድቅ የሚያምነውን ሁሉ
ለመምረጥ ወስኖ ነበር፡፡ በእግዚአብሄር ልጅ የጽድቅ መስዋዕትነትና በፍቅሩ
በማመናችን የእርሱ ወንዶችና ሴቶች ልጆች አድርጎ ሊቀበለን አስቀድሞ
መርጦናል፡፡
የያዕቆብንና የኤሳውን ታሪክ ወደሚተርከው ብሉይ ኪዳን ስንመለስ ኤሳው
በራሱ ጉልበት እንደተማመነና የወላጆቹን ትምህርት አበክሮ እንዳላዳመጠ
እናያለን፡፡ በአንጻሩ ያዕቆብ በታዛዥነት እናቱን አደመጠ፡፡ ያዕቆብ በዚህ ምክንያት
ምን ሆነ? ታናሽ ልጅ ቢሆንም ለበኩሩ የተቀመጡትን በረከቶች በሙሉ ተቀበለ፡፡
እንዲህ የተባረከው በማን አማካይነት ነበር? በእናቱ ምክንያት ነው፡፡ ምክንያቱም
ያዕቆብ በእናቱ ቃሎች ስለታመነና ስለተደገፈ የእግዚአብሄርን በረከቶች መቀበል
ቻለ፡፡ አጋር ምዕመናኖቼ እኛ በስጋችን ደካማ መሆናችን ግልጥ ቢሆንም
ልቦቻችንም ደግሞ ልፍስፍሶች እንደሆኑም እውነት ነው፡፡ ቢሆንም ቃሉን በማመን
አሁንም የእግዚአብሄርን በረከቶች መቀበል እንችላለን፡፡
ሁላችንም ከተወለድንበት ጊዜ ጀምሮ ወደ ሲዖል ለመጣል የታጨን ነበርን፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በእግዚአብሄር ፍቅርና መስዋዕትነት አማካይነት ድነናል 69

ይህንን ዕጣ ፈንታ ይዘን የተወለድነው በሐጢያቶቻችን ምክንያት ነው፡፡ እነዚህ


ሐጢያቶቻችንም ከአያቶቻችን የወረስናቸው ናቸው፡፡ እግዚአብሄር በእርሱ ጽድቅ
የሚያምኑትን ሁሉ ልጆቹ አድርጎ ሊቀበላቸው የወሰነው ለዚህ ነው፡፡ ይህ
የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል እውነት ነው፡፡
በአሁኑ ጊዜ ብዙ ክርስቲያኖች በኢየሱስ ማመን ተራና ቀላል እንደሆነ
ያስባሉ፡፡ ለምሳሌ ያህል ሐሰተኛ እረኞች ለጉባኤያቸው በሚሰብኩበት ጊዜ
አዘውትረው የሚከተለውን ይላሉ፡- ‹‹እናንተ ሐጢያተኞች ናችሁ፤ ስለዚህ
መጥፋታችሁ አይቀርም፡፡ ነገር ግን እግዚአብሄር አብዝቶ ስለወደዳችሁ በሰማይና
በሲዖል መካከል የመስቀል ቅርጽ ያለው ድልድይ ገነባ፡፡ ጌታ በዚህ ምድር ላይ
ለሐጢያቶቻችሁ ተሰቅሎ ስለሞተ አሁን ምንም ያህል የበዙ ሐጢያቶች
ቢኖሩባችሁም ኢየሱስን አዳኛችሁ አድርጋችሁ በልባችሁ ብትቀበሉት
የእግዚአብሄር ልጅ መሆን ትችላላችሁ፡፡ ታዲያ ኢየሱስን የግል አዳኛችሁ
አድርጋችሁ ትቀበሉታላችሁ? ሐጢያተኞች እንደሆናችሁ ለእግዚአብሄር
ታምናላችሁ? እንደዚያ ከሆነ ይህንን ጸሎት ከእኔ በኋላ ደግማችሁ ጸልዩት፤ ‹ጌታ
ሆይ እኔ ሐጢያተኛ ነኝ፤ ነገር ግን አንተ ለእኔ ተሰቅለህ እንደሞትህ አምናለሁ፡፡
አሁን የግል አዳኜ አድርጌ ልቀበልህ እሻለሁ፡፡ እባክህ ወደ ልቤ ግባ! አሜን!›››
አብዛኞቹ ክርስቲያኖች የእግዚአብሄር ልጆች የሆኑት በዚህ ሁኔታ እንደሆነ ያስባሉ፡፡
ነገር ግን ጌታ ወደዚህ ምድር መጥቶ እኛን ለማዳን በብዙ መከራና ችግር
ውስጥ ስላለፈ የእግዚአብሄር ልጅ መሆን ያን ያህል ቀላል አይደለም፡፡ እግዚአብሄር
እኛን በክርስቶስ አድኖናል ማለት ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ከዓለም ሐጢያቶች ሁሉ
ለማዳን ማስተሰርያችን ሆንዋል ማለት ነው፡፡ ጌታ የመስዋዕት በግ ሆኖ ለ33
ዓመታት ያህል በዚህ ምድር ላይ የተመላለሰው እያንዳንዳችንን ሐጢያት አልባ
ሊያደርገን ነው፡፡ ጌታ በድንግል ማርያም ስጋ ተጸንሶ ሰማያዊውን የሊቀ ካህን
አገልግሎት ለመፈጸም የሰው ስጋ ለብሶ ወደዚህ ምድር መምጣት ነበረበት፡፡ በዚህ
ምድር የነበረው ሕይወቱም ከውልደቱ ጀምሮ በመከራ የተሞላ ነበር፡፡ የተወለደው
በግርግም ውስጥ ከመሆኑም በላይ ከንጉሥ ሄሮድስ ግድያም ማምለጥ ነበረበት፡፡
ኢየሱስ ከተወለደ በኋላ ወዲያውኑ ሰብዓ ሰገል ሊሰግዱለት ከምሥራቅ መጡ፡፡
ነገር ግን ይህ ድባብ ለረጅም ጊዜ አልቆየም፡፡ ከንጉሥ ሄሮድስ ለማምለጥ ወደ
ግብጽ መሸሽ ነበረበት፡፡
የተወሰኑ ዓመታቶች ካለፉ በኋላ ኢየሱስ በናዘሬት ለመኖር መጣ፡፡ እዚያም
ከአባቱ ዮሴፍ ጋር አናጢ ሆኖ ሰራ፡፡ በ30 ዓመቱም ይፋ ሕይወቱን በመጀመር
አስቀድሞ ወደ ዮርዳኖስ ወንዝ በመምጣትና በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


70 በእግዚአብሄር ፍቅርና መስዋዕትነት አማካይነት ድነናል

የሰውን ዘር ሐጢያቶች በሙሉ ተቀበለ፡፡ ጌታ እንዲህ በአጥማቂው ዮሐንስ


በመጠመቅ የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ ከተቀበለ በኋላ ተሰቅሎ ሞተ፡፡
የሐጢያቶቻችንንም ቅጣት በሙሉ በስቅለቱ ተቀብሎ ሲያበቃ ከተቀበረ በኋላ
በሦስት ቀናቶች ውስጥ ከሙታን ተነሳ፡፡ ኢየሱስ በዚህ እወነት ለምናምን ሁሉ
አዳኛችን የሆነው እንዲህ ነው፡፡ አሁን በመላው ዓለም የሚኖር እያንዳንዱ ሰው
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን የእግዚአብሄር ልጅ መሆን ይችላል፡፡

ጌታ እኛን ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ለማዳን ምን ያህል መስዋዕትነት ከፈለ?

እግዚአብሄር አብ በክርስቶስ ደህንነታችንን ያቀደው አስቀድሞ ነበር፡፡


ይህንን ዕቅድ ለመፈጸምም ኢየሱስ የሰው ስጋ ለብሶ በዚህ ምድር ላይ መወለድ፣
በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅም የሰውን ዘር ሐጢያቶች በሙሉ መሸከምና
በመስቀል ላይም መሞት ነበረበት፡፡ ስጋ ከመልበሱ ሐጢያቶቻችንን እስከ
መሸከሙና ስቅለቱ ድረስ ክርስቶስ ለእኛ ያደረጋቸው እነዚህ ነገሮች በሙሉ ጌታ
እኛን ለማዳን የከፈላቸው መስዋዕትነቶች ነበሩ፡፡
ይህ ቅዱሱ ኢየሱስ በጥምቀቱ አማካይነት የዚህን ዓለም ሐጢያቶች በስጋው
የመቀበሉ እውነታ በራሱ መስዋዕትነት ነው፡፡ የሮም ወታደሮች የተፉበት፣ ፊቱን
የጎሰሙት፣ እርቃኑን ያስቀሩት፣ ያላገጡበትና ሰውነቱ በሙሉ በደም እስኪበከል
ድረስ አንድ ሲጎድል አርባ የገረፉት ጌታ ራሱን መስዋዕት በማድረጉ ነበር፡፡ ከዚያም
ኢየሱስ እጆቹና እግሮቹ በመስቀል ላይ ተቸንክረው ተሰቀለ፡፡ በጣዕር ላይ ሳለም
ኢየሱስ ‹‹ተፈጸመ!›› (ዮሐንስ 19፡30) አለ፡፡ ጌታ በውሃና በመንፈስ አማካይነት
ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ያዳነን ራሱን እንዲህ መስዋዕት በማድረግ ነበር፡፡ ከዚህም
በላይ ኢየሱስ ቃል በገባው መሠረት በተቀበረ በሦስተኛው ቀን ከሙታን ተነሳ፡፡
በአጭሩ ራሱን ስለ እኛ መስዋዕት በማድረግ እናንተንና እኔን ያዳነን እግዚአብሄር
ራሱ ነው፡፡
እኔ ከሙሉ ልቤ በዚህ መስዋዕት አምናለሁ፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ በጥምቀቱና
በስቅለቱ በልቤ ውስጥ ያሉትን ሐጢያቶች በሙሉ እንደደመሰሰ አምናለሁ፡፡
እናንተስ ታዲያ? እናንተም ደግሞ በዚህ የጌታ መስዋዕት ታምናላችሁን?
እግዚአብሄር የመረጠን እኛን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የምናምነውን አማኞች
ነው፡፡ እርሱ የራሱ ልጆች አድርጎ መርጦናል፡፡ ስለዚህ ሁላችሁም በዚህ
እንድታምኑ እጠይቃችኋለሁ፡፡ በእግዚአብሄር ጽድቅ እመኑ፤ የደህንነት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በእግዚአብሄር ፍቅርና መስዋዕትነት አማካይነት ድነናል 71

ሥራውንም ከንቱ አታድርጉ፡፡ ጌታ በዚህ መልክ ራሱን መስዋዕት በማድረግ


አድኖዋችሁ ሳለ አሁንም በጌታ ለማመን እምቢተኛ ከመሆንና የደህንነት
ሥራውንም ከንቱ ከማድረግ የበለጠ ምስጋና ቢስነት የለም፡፡
በዓለማዊ መመሪያዎች መሠረትም ቢሆን ወላጆቹን ችላ የሚልና ለእርሱ
የከፈሉለትን መስዋዕትነቶች በሙሉ ጆሮ ዳባ ልበስ የሚል ማንኛውም ልጅ ሙሉ
በሙሉ የማይረባ ልጅ እንደሆነ ይቆጠራል፡፡ የስጋ ወላጆቹን ፍቅር ለመቀበል
አሻፈረኝ የሚል ልጅ እጅግ የከፋ ክህደት የሚፈጽም ልጅ ነው፡፡ ልክ እንደዚሁ
የእርሱ ፍጡራኖች ሆነን ሳለን የጌታን ፍቅር የምንንቅ ከሆንን እጅግ ወራዳ
ሐጢያት እየሰራን ነው፡፡ ይህ እንዲሆንብን በጭራሽ መፍቀድ የለብንም፡፡ ከዚህ
ርቀን ሁላችንም የኢየሱስ ክርስቶስን መስዋዕትና ፍቅር በእምነት መቀበል፣
እግዚአብሄርን ማወደስና እርሱን ማመስገን አለብን፡፡ በዚህ መልኩ የኢየሱሰ
ክርስቶስን ፍቅር መቀበልና ከክርስቶስ ጋርም አብረን በዘላለማዊ ክብሩ ለመደሰት
መንግሥተ ሰማይ መግባት ይገባናል፡፡
እግዚአብሄር አብ በፍቅር መስዋዕትነቱ አማካይነት ፍቅሩን ያሳየን እንዲህ
ነው፡፡ ይህም ከሁሉ የሚበልጥ ፍቅር ነው፡፡ ይህ የግዚአብሄር አብ ፍቅር ምን
ያህል ክቡር፣ በምህረት የተሞላና ፍጹም ነው? በዚህ ዓለም ላይ ራሱን ለእኛ
መስዋዕት ማድረግና እኛን በዚህ መልኩ ማዳን የቻለው ማነው? እኛን ሰዎችን
ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ለማዳን የሊቀ ካህንን አገልግሎት ሙሉ በሙሉ የፈጸመው
ራሱ ፈጣሪ አምላካችን ነው፡፡ እንዲህ የወደደን ሁሉን ቻዩ ስላሴ አምላክ እንጂ
ሌላ ማንም አይደለም፡፡ ይህንን ፍቅር የሰጠንና ሊቀ ካህናችን ሆኖ ሐላፊነቶቹን
ያለ እንከን የፈጸመው ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ
የሚለው ለዚህ ነው፡- ‹‹በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው
እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሄር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ
ወዶአልና፡፡›› (ዮሐንስ 3፡16) እናንተና እኔ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
በሚያምነው እምነታችን አማካይነት የሐጢያቶችን ስርየት ተቀብለናል፡፡
የእግዚአብሄርን ወሰን የለሽ ፍቅር የለበስነውም እኛው ነን፡፡
በውኑ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ፍቅር ለብሳችኋልን? አንደኛ ቆሮንቶስ
ምዕራፍ 13 ፍቅርን በብዙ ደርዞች በማብራራት በስፋት ገልጦታል፡፡ እዚያ ላይ
ፍቅር ደግ እንጂ ክፉ እንዳልሆነ አልተጻፈምን? ጌታ ለእኛ ክፉ ሆኖብን ያውቃል?
አያውቅም፡፡ ጌታ ለእኛ ክፉ ሳይሆን ደግ በመሆኑ ራሱ የሐጢያቶቻችንን ችግር
ለመፍታት ወደዚህ ምድር ከመጣ በኋላ ፈጽሞ ፈታው፡፡ በልቦቻችን ውስጥ ምንም
እርካታ ባልነበረን ጊዜ ጌታ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት እኛን ፈልጎ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


72 በእግዚአብሄር ፍቅርና መስዋዕትነት አማካይነት ድነናል

መጣ፡፡ እግዚአብሄር ሁላችንንም የወደደን እንዲህ ነው፡፡


ስለዚህ እኛ በዚህ ፍቅር እናምናለን፡፡ ምስጋናችንንም ሁሉ ለእግዚአብሄር
እንሰጣለን፡፡ አሁን ይህንን የእግዚአብሄር ፍቅር ከለበስን በኋላ እንዴት ልንረሳው
ይቻለናል? እንዴትስ ልንጥለው ይቻለናል? እንዴትስ ለእርሱ አመስጋኞች
አለመሆን ይቻለናል? የእግዚአብሄርንስ ጽድቅ እንደምን በዝማሬ፣ በቅኔና በውዳሴ
አለማመስገን ይቻለናል?
አንድ ገጣሚ ይህንን ዜማ ጻፈ፡-
‹‹ውቅያኖስን በቀለም መሙላት ብንችል
ሰማያትም ብራና ቢሆኑ
በምድር ላይ ያለ እያንዳንዱ መቃ
ብዕር ቢሆን፤ ሰውም ሁሉ ጸሐፊ ቢሆን
ከላይ ያለውን የእግዚአብሄር ፍቅር መጻፍ
ውቅያኖስን ያደርቅ ነበር፡፡
ብራናውም በሙሉ ከአንዱ የሰማይ ጫፍ
እስከ ሌላው የሰማይ ጫፍ ቢዘረጋ
ሁሉን መያዝ ባልቻለም ነበር፡፡››
አጋር ምዕመናኖቼ ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅና
ሐጢያቶቻችንንም በሙሉ ለአንዴና ለመጨረሻ በመቀበል ሐጢያት አልባ
አድርጎናል፡፡ የእነዚህን ሐጢያቶቻችንን ቅጣት በሙሉ ለመሸከምም በመስቀል ላይ
ሕይወቱን ለእኛ ተወ፡፡ እኛ በዚህ መስዋዕትና ፍቅር እናምናለን፡፡ ታዲያ እንዴት
ስላሴ አምላክን ማመስገን አይቻለንም?
ምስጋናችንን ሁሉ ለዚህ አምላክ እንሰጣለን፡፡ ምን ያህል አመስጋኞች
እንደሆንን የምንገልጥበት ቃል የለንም፡፡ የጌታን ፍቅር ለመመለስ የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል እያገለገልን ያለነው ለዚህ እንደሆነ ግልጥ ነው፡፡ ሁላችንም
ከልባችን እግዚአብሄርን ስለምናመሰግን እያንዳንዳችን ይህንን የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል ከሙሉ ልባችን ማገልገል እንችላለን፡፡ ከዚህም በላይ አሁን
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን የዳነ ሌላው ሰው ሁሉ ከእኛ ጋር አብሮ
ወደ እግዚአብሄር መንግሥት ይገባል፡፡
አሁን እኛ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን የሐጢያቶችን ስርየት
ስለተቀበልን ጥቂት በጥቂት የጌታችንን ፍቅር በስፋትና በጥልቀት ወደ ማስተዋል
ብንደርስ በጣም ጠቃሚያችን ነው፡፡ ጌታ እንዲህ አብዝቶ እንደወደደን ማን አወቀ?
ስለዚህ ሁላችንም ወሰን ለሌለው ፍቅሩ አምላካችንን እናመስግን፡፡ 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ስብከት
4

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት
ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
የቤተክርስቲያኑ አባሎች
አድርጎ ስለጠራን
እግዚአብሄርን እናመሰግናለን
‹‹ ኤፌሶን 1፡20-23 ››
‹‹ክርስቶስንም ከሙታን ሲያስነሣው ከአለቅነትና ከሥልጣንም፣ ከሐይልም፣
ከጌትነትም ሁሉ በላይና በዚህ ዓለም ብቻ ሳይሆን ነገር ግን ሊመጣ ባለው ዓለም
ደግሞ ከሚጠራው ስም ሁሉ በላይ በሰማያዊ ስፍራ በቀኙ ሲያስቀምጠው
በክርስቶስ ባደረገው ሥራ የብርታቱ ጉልበት ይታያል፤ ሁሉንም ከእግሩ በታች
አስገዛለት፤ ከሁሉ በላይም ራስ እንዲሆን ለቤተክርስቲያን ሰጠው፡፡ እርስዋም
አካሉና ሁሉን በሁሉ የሚሞላ የእርሱ ሙላቱ ናት፡፡››

አሁንም ቢሆን ጌታ መላውን ዓለም በእግዚአብሄር


በረከቶች እየሞላው ነው፡፡

በኤፌሶን 1፡23 ላይ ቤተክርስቲያን ‹‹አካሉና ሁሉን በሁሉ የሚሞላ የእርሱ


ሙላቱ እንደሆነች›› ተጽፎዋል፡፡ ሁላችንም ጌታ በሰጠን የውሃውና የመንፈሱ
ወንጌል በማመን የሐጢያቶቻችንን ስርየት በልቦቻችን ውስጥ መቀበል
ይኖርብናል፡፡ የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን አባል ትሆኑ ዘንድ በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል ላይ የማይናወጥ እምነት ሊኖራችሁ ይገባል፡፡ አሁን በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል በማመን የሐጢያቶቻችንን ስርየት በልቦቻችን ውስጥ
ስለተቀበልን እስከምንሞትበት ቀን ድረስ ይህንን ወንጌል በዓለም ሁሉ ልንሰብክ
ይገባናል፡፡ እንዲህ በማድረግ ሁላችንም እምነታችንን ማጠንከርና እግዚአብሄርን
ማክበር አለብን፡፡ ሁላችንም የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን አባሎች እንድንሆን
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ላይ ያለን እምነታችን የማይናወጥ መሆን አለበት፡፡
የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን አባሎች መሆን የምንችለው ይህ እምነት ሲኖረን ብቻ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


76 የቤተክርስቲያኑ አባሎች አድርጎ ስለጠራን እግዚአብሄርን እናመሰግናለን

ነው፡፡
ዛሬ በልቦቻቸው በውሃውና በመንፈሱ ወንገል የሚያምኑ ሰዎች በዚህ
እምነት የሐጢያቶችን ስርየት ተቀብለዋል፡፡ የእነርሱ ጉባኤም የእግዚአብሄር
ቤተክርስቲያን ነች፡፡ የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን የተዋጁ ሰዎች እግዚአብሄርን
ለማመስገንና የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለመስበክ የሚሰበሰቡባት ነች፡፡
ይህንን እውነተኛ ወንጌል በጭንቅላቱ ብቻ የሚያውቅና በልቡ የማያምን ሰው ካለ
ይህ ሰው በእርግጠኝነት ሐጢያተኛ ነው፡፡ እግዚአብሄር በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል ለማመን አሻፈረኝ የሚለውንና ልቡ አሁንም ሐጢያተኛ የሆነውን ሰው
ይጸየፈዋል፡፡ በልቦቻችን ውስጥ ያለው መንፈስ ቅዱስ በእግዚአብሄር ጽድቅ
በማያምን ሰው አይደሰትም፡፡ ስለዚህ እግዚአብሄር ማንኛውንም ሥራውን
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ለማያምን ሰው በአደራ አይሰጥም፡፡
ሁሉም ሰው ወዲያውኑ የወሃውንና የመንፈሱን ወንጌል እንደማያስተውልና
እንደማያምን የታወቀ ነው፡፡ አንድ ሰው አንድ ቀን በዚህ ወንጌል ከማመኑና ቅዱስ
ከመሆኑ በፊት በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ውስጥ የሚገኘውን የእግዚአብሄር
ቃል ለተወሰነ ጊዜ ማድመጥ አለበት፡፡ ነገር ግን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
እስከ መጨረሻው ድረስ የማይቀበሉ ሌሎች ሰዎች አሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች
በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ ቢገኙም የእግዚአብሄር ጽድቅ ጠላቶች
ናቸው፡፡ እነዚህ ሰዎች በመጨረሻ ከእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ይቆረጣሉ፡፡
ምክንያቱ ምንም ይሁን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የማያምን ሁሉ የእግዚአብሄር
ቤተክርስቲያን አባል ሊሆን አይችልም፡፡ በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በትክክል የማያምን ሰው ካለ የእግዚአብሄርን
ቤተክርስቲያን ይመራ ዘንድ ይህንን ሰው በጭራሽ ልንሾመው አይገባንም፡፡
የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን የኢየሱስ ክርስቶስ አካል ስለሆነች መሪዎችዋ
በልቦቻቸው ውስጥ ሐጢያት አልባ መሆን አለባቸው፡፡ መንፈስ ቅዱስ በልቦቻቸው
ውስጥ ሊሰራ የሚችለው የእግዚአብሄር አገልጋዮችና ቅዱሳኖች ሁሉ ሙሉ በሙሉ
ሐጢያት አልባ ሲሆኑ ብቻ ነው፡፡ በኢየሱስ ክርስቶስ የዳነ ሰው ተብሎ ሊገለጥ
የሚችለው ሐጢያት የሌለበት ሰው ብቻ ነው፡፡ እያንዳንዳችን እምነቱ
በእግዚአብሄር ዘንድ ተቀባይነት ያገኘ እንዲህ ያለ ቅዱስ ሰው ለመሆን ከፈለግን
ሁላችንም እግዚአብሄር በሰጠን የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ማመን አለብን፡፡
የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ሁሌም በጎችን ከፍየሎች መለየትና ቤተክርስቲያንን
መንከባከብ የሚችል ሰው ያስፈልጋታል፡፡
እግዚአብሄር ራሱን በካደና በእግዚአብሄር ጽድቅ ባመነ ሰው ሁሉ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የቤተክርስቲያኑ አባሎች አድርጎ ስለጠራን እግዚአብሄርን እናመሰግናለን 77

አማካይነት ይበረታል፤ ይሰራል፡፡ ችግሩ ግን ብቻቸውን የእግዚአብሄርን ሥራ


መስራት እንደሚችሉ የሚያስቡ ብዙ ሰዎች መኖራቸው ነው፡፡ የእግዚአብሄርን
ሥራ የሰው ጉዳይ ብቻ አድርገን በጭራሽ ልናስብ አይገባንም፡፡ እግዚአብሄር
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማያምን በማንኛውም ሰው አማካይነት ፈጽሞ
አንዳች ነገር እንደማያደርግ ልንገነዘብ ይገባናል፡፡
የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን የቅዱሳኖች ሁሉ ራስ የሆነውን የኢየሱስ
ክርስቶስ ፈቃድ በታማኝነት መታዘዝና ማገልገል የምትችል በዚህ ምድር ላይ ያለች
ብቸኛዋ ተቋም ነች፡፡ ነገር ግን ይህ ይሆን ዘንድ የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን
አባሎች በሙሉ ራስ የሆነውን የኢየሱስ ክርስቶስን ፈቃድ ፈቃዳቸው አድርገው
መቀበል አለባቸው፡፡ ጌታ ለዘላለም ቅዱስ እንደሆነ ሁሉ በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል የሚያምኑ አማኞችም እንደዚሁ ቅዱሳን ናቸው፡፡ ስለዚህ ልባችሁ በእርግጥ
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ላይ እምነት እንዳለው ወይም እንደሌለው ማረጋገጥ
በእጅጉ ያስፈልጋችኋል፡፡
ይህ ዓለም በኢየሱስ እንደሚያምኑ በሚናገሩ በርካታ ክርስቲያኖች
ተሞልቷል፡፡ ነገር ግን ከእነርሱ ብዙሃኑ በኢየሱስ የመስቀል ላይ ደም ብቻ
የሚያምኑ ናቸው፡፡ ይህ ብቻውን ደህንነታቸውን እንደሚያዋቅርላቸው በተሳሳተ
መንገድ ያስባሉ፡፡ እነዚህ የተሳሳቱ ክርስቲያኖች የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
ጆሮ ዳባ ለበስ ብለው ቅዱሳኖች እንደሆኑ ያስባሉ፡፡ ይህ ግን የተሳሳተ እሳቤ ነው፡፡
ግልጥ ለመሆን በልቡ ውስጥ ሐጢያት ያለበት ሰው ከእግዚአብሄር ሕዝብ አንዱ
መሆን አይችልም፡፡ በሌላ አነጋገር የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል የማያውቁ ሰዎች
ሊያምኑበት አይችሉም፡፡ ስለዚህ የእግዚአብሄር ሕዝብ ሊሆኑ አይችሉም፡፡

እግዚአብሄር ለሥራው የሚጠቀምበት ማንን ነው?

የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምኑ


አማኞች እግዚአብሄርን በመታዘዝ አብረው የሚሰበሰቡባት ነች፡፡ ነገር ግን
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምኑ አማኞች ከማያምኑ ጋር በአንድ ጉባኤ
አብረው ከተቀላቀሉ እንዲህ ያለው ጉባኤ የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ሊሆን
አይችልም፡፡ በዚህ ስፍራ መንፈስ ቅዱስ ሊሰራ አይችልም፡፡ ስለዚህ በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል ከማመን ይልቅ በመስቀሉ ወንጌል ብቻ እንደሚያምን የሚናገር
ሰው እውነተኛ የኢየሱስ ክርስቶስ አካል ብልት ሊሆን አይችልም፡፡ ይህ ሰው ራሱን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


78 የቤተክርስቲያኑ አባሎች አድርጎ ስለጠራን እግዚአብሄርን እናመሰግናለን

ክርስቲያን ብሎ ቢጠራም ከብዙ የሐይማኖት ተለማማጆች አንዱ እንደሆነ ብቻ


መናገር እንችላለን፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ከማመን ይልቅ በመስቀሉ ደም
ብቻ በማመን ብቻ ማንም ሰው ከእግዚአብሄር ሕዝብ አንዱ መሆን የሚችል መሆኑ
እውነት ከሆነ በግምት ከዓለም ሕዝብ አንድ አራተኛው በሙሉ የእግዚአብሄር
ሕዝብ ሆኖዋል ማለት ይቻላል፡፡ በተጨባጭ ግን ከእነርሱ ማንም በትክክል
ከሐጢያቶቹ ሁሉ የዳነ ሰው ሆኖ ሊገለጥ አይችልም፡፡ ምክንያቱም ይህ ሰው
አሁንም በልቡ ውስጥ ሐጢያት አለበት፡፡
እነዚህ ሰዎች በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል እንደማያምኑ የታወቀ ነው፡፡
እነርሱ በልቦቻቸው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ባለማመናቸው አሁንም
በልቦቻቸው ውስጥ ሐጢያቶች ስላሉ ሐጢያተኞች ናቸው፡፡ ውሎ አድሮም
በሐጢያቶቻቸው ምክንያት ይጠፋሉ፡፡ ልቦቻቸው በሐጢያት የተሞላ ሰዎች
የሚሰበሰቡበት ማንኛውም ጉባኤ የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን አይደለም፡፡
ከማህበራዊ ጉባኤም የተለየ አይደለም፡፡ እነዚህ ክርስቲያን ሐጢያተኞች ሁሉም
በኢየሱስ እንደሚያምኑ ቢናገሩ፣ እርሱን ለማምለክ አብረው ቢሰበሰቡ፣ የእርሱን
ስም ቢጠሩ፣ እርሱን ቢያመሰግኑና ወደ እግዚአብሄር ቢጸልዩም ይህ እግዚአብሄር
የእነርሱ አምላክ ያለመሆኑን እውነት አይለውጠውም፡፡ እርሱም በእነርሱ ሊከብር
አይችልም፡፡
እውነቱ እግዚአብሄር ማንኛውንም ሐጢያተኛ ሥራውን የሚሰራለት
መሣርያው አድርጎ ሊጠቀምበት የማይችል መሆኑ ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስም
በሐጢያት በተሞላ በማንኛውም ልብ ውስጥ ሊኖር አይችልም፡፡ እያንዳንዱ
የሐጢያቶች ጉባኤ የሚመራው በሌላ ሐጢያተኛ ነው፡፡ ለእነዚህ ሐጢያተኞች
ንጉሣቸው አብሮዋቸው ያለው ሐጢያተኛ እንጂ ኢየሱስ አይደለም፡፡
አገልግሎታቸውን በኢየሱስ ስም በፈቃዳቸው ቢያበረክቱና ስሙን ቢሰብኩም
በእምነታቸው አማካይነት በጭራሽ ከሐጢያቶቻቸው መንጻት አይችሉም፡፡ ስለዚህ
እነዚህ ዓለማዊ ቤተክርስቲያኖች በማህበረሰቡ ውስጥ ከማንኛውም የበጎ ፈቃድ
ቡድን ጋር ተመሳሳይ ናቸው፡፡
ነገር ግን የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ማህበራዊ ጉዳይን የምታገለግል የበጎ
ፈቃድ ድርጅት አይደለችም፡፡ የእግዚአብሄር አገልጋዮች በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል የማያምነውን ማንኛውንም ሐጢያተኛ የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን አባል
አድርገው ሊቀበሉት አይችሉም፡፡ የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ሠራተኞች ሁሉም
ራሳቸውን ለፈቃዱ ሙሉ በሙሉ አደራ በመስጠት ከእግዚአብሄር ጋር በአንድ
ዕርምጃ የሚራመዱ ናቸው፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ብታምኑም

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የቤተክርስቲያኑ አባሎች አድርጎ ስለጠራን እግዚአብሄርን እናመሰግናለን 79

የእግዚአብሄር ሠራተኛ መሆን የምትፈልጉ ከሆነ እግዚአብሄር ያዘዛችሁን መታዘዝ


አለባችሁ፡፡ ከእግዚአብሄር ፈቃድ ጋር ያልተቆራኘ ሰው የእግዚአብሄርን
ቤተክርስቲያን የሚያዋቅሩ ቅዱሳኖችን መምራት ቀርቶ እንዴት የእርሱ ሠራተኛ
ተብሎ ሊጠራ ይችላል? እግዚአብሄር የእርሱን ፈቃድ በማይቀበል በማንኛውም
ሰው ሥራውን ፈጽሞ እንደማይሰራ ተናግሮዋል፡፡ እርሱ እነዚህ ሰዎች ሥራውን
እንዲሰሩለት በጭራሽ ባርያዎቹ አድርጎ አላስነሳቸውም፡፡
ስለዚህ ማንም ሰው ተነስቶ የእግዚአብሄርን ሥራ መስራት አይችልም፡፡
የእግዚአብሄር አገልጋዮች መሆን የሚፈልጉ ሁሉ የእግዚአብሄርን ወንጌል መስበክ
ከመቻላቸው በፊት በመጀመሪያ ራሳቸው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ማመን
ይኖርባቸዋል፡፡ ሁሉም ራሳቸውን በአደራ ለእግዚአብሄር መስጠትና
ሕይወታቸውንም በእርሱ ፈቃድ መሠረት መኖር ይገባቸዋል፡፡ አለበለዚያ
ማናቸውም ከእግዚአብሄር መንፈስ ጋር ሊሰሩ አይችሉም፡፡
ሁላችሁም የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በጆሮዎቻችሁ መስማትና በዚህ
ወንጌል ማመን ብትችሉም ሁላችሁም የእግዚአብሄርን ቤተክርስቲያን መምራት
እንደማትችሉ እዚህ ላይ ግልጥ ላድርግላችሁ፡፡ አሁን በእግዚአብሄር ጥረት
የእግዚአብሄር ሰራተኛ መሆንና ብቻችሁን የእርሱን ቤተክርስቲያን መምራት
እንደምትችሉ ብታስቡም የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል የሚያምኑ ዳግመኛ የተወለዱ አማኞች የእግዚአብሄርን ፈቃድ ለማገልገል
አብረው የሚሰበሰቡባት ስፍራ ነች፡፡ የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ራስ ኢየሱስ
ክርስቶስ ነው፡፡ የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን የእግዚአብሄርን ፈቃድ በመታዘዝ
የእርሱን ሥራ ራሳቸውን ለውሃውና ለመንፈሱ ወንጌል አሳልፈው ለሰጡ ሰዎች
በአደራ ሰጥታለች፡፡
ሆኖም ዛሬ ለብዙ ክርስቲያኖች አሳዛኙ እውነታ የውሃውንና የመንፈሱን
ወንጌል ባለማወቃቸው ደህንነታቸውን የሚያዋቅረው ይህ ብቻ እንደሆነ በመናገር
በኢየሱስ የመስቀል ላይ ደም ብቻ መኩራታቸው ነው፡፡ የእነርሱ ቤተክርስቲያን
በዓለም ላይ ምርጥ እንደሆነች በመናገር በግል ቤተክርስቲያኖቻቸውም ደግሞ
ይመጻደቃሉ፡፡ ነገር ግን እነዚህ ሰዎች የራሳቸውን ስጋዊ መሻቶች ለማስደሰት
በመሞከር ይባትላሉ፡፡ በአንጻሩ እርሱ ድጋፍ የሰጣቸው የእግዚአብሄር
ቤተክርስቲያን አባሎች በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ብቻ ያምናሉ፡፡ ሁሉም ይህ
ወንጌል ብቻ በመላው ዩኒቨርስ ውስጥ እውነተኛው የሐጢያቶች ስርየት ወንጌል
እንደሆነ መመስከር ይችላሉ፡፡
የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ራስ የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ በውሃውና

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


80 የቤተክርስቲያኑ አባሎች አድርጎ ስለጠራን እግዚአብሄርን እናመሰግናለን

በመንፈሱ ወንጌል የምናምነውን አማኞች ከሐጢያቶቻችን ሁሉ አድኖናል፡፡


ወደዚህ ምድር በመምጣት፣ በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅ፣ በመስቀል ላይ
ደሙን አፍስሶ በመሞትና ዳግመኛ ከሙታን በመነሳት ደህንነታችንን ፈጽሞዋል፡፡
የእርሱ ምስክሮች ሆነን ሕይወታችንን እንድንኖርም ባርኮናል፡፡ ስለዚህ
የእግዚአብሄር ቅዱስ ሕዝብ የሆኑት በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን
ከሐጢያቶቻቸው ሁሉ የነጹ ሰዎች ብቻ ናቸው፡፡ አሁን በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል የሚያምኑና እርሱንም የሚሰብኩ ሰዎች ብቻ የእግዚአብሄር እውነተኛ
አገልጋዮች ናቸው፡፡ በአንጻሩ የመስቀሉን ደም ብቻ የሚያምኑና የሚሰብኩ ሰዎች
ሐሰተኛ ናቸው፡፡ ጌታችን የነገረን የውሃውና የመንፈሱ በረከት ሰውን ሁሉ ዳግመኛ
እንዲወለድ የሚያስችል እውነት መሆኑን ሁላችንም ማመን አለብን፡፡
የእግዚአብሄርን ፈቃድ በመቃወም የውሃና የመንፈሱ ወንጌልና ሌላው
ወንጌል አንድ ናቸው የሚሉ ሰዎች የእግዚአብሄር ወገን አይደሉም፡፡ ዛሬ
እውነተኛው ደህንነታቸው የመስቀሉ ደም ብቻ እንደሆነ በሚያምኑ ሰዎች የሚመሩ
ቤተክርስቲያኖች እግዚአብሄር የሚመራቸው ሳይሆኑ ሰዎች የሚመሩዋቸው
ቤተክርስቲያኖች ናቸው፡፡ እግዚአብሄር ከእነዚህ ሰዎች ጋር አይሰራም፡፡ እነዚህ
ሰዎች ተዓምራቶች እንዳደረጉ ቢናገሩም ያም የራሳቸው ሰዋዊ ሥራ እንጂ
የእግዚአብሄር ሥራ አይደለም፡፡
ጌታችን ኢየሱስ ዛፍ በፍሬው እንደሚታወቅ ተናግሮዋል፡፡ የሰዎችን ሐጢያቶች
የሚደመስሰውን እውነተኛ ወንጌል የሚሰብኩት በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
የሚያምኑ አማኞች ብቻ እንደሆኑ ተናግሮዋል፡፡ በዚህ ዓለም ላይ የገነነ ማንኛውም
ሌላ ወንጌል ሐሰተኛ ወንጌል ነው፡፡ በመጨረሻም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
የማያምኑ ሰዎች የእግዚአብሄር ሕዝብ አይደሉም፤ ጌታንም የሚያገለግሉ አይደሉም፡፡
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል የማያውቁ የዘመኑ መጋቢዎች በአገልግሎታቸው
ውስጥ የሚያፈሩት ሐሰተኛ ፍሬን ነው፡፡ እነዚህ መጋቢዎች አገልግሎቶቻቸውን
በሙሉ አሳልፈው የሰጡት የቤተክርስቲያን ሕንጻዎቻቸውን ለማስፋፋት ማህበራዊ
ደረጃቸውን ከፍ ለማድረግና የራሳቸውን ጽድቅ ለማቆም ነው፡፡ በአንጻሩ እውነተኛው
ወንጌል የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ብቻ እንደሆነ የሚያምኑ ሰዎች የራሳቸውን ስጋዊ
ጽድቅ ለማጽናት አይሞክሩም፡፡ በሌላ አነጋገር የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ብቻ
ደህንነታቸው አድርገው የሚያምኑ ሰዎች የራሳቸውን ጽድቅ ለመግለጥ አይሞክሩም፡፡
በተቃራኒው ጻድቃን የእግዚአብሄርን ጽድቅ ብቻ ከፍ ያደርጋሉ፡፡ እውነተኛው
ወንጌልም የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ብቻ እንደሆነ ያምናሉ፡፡ በሕይወታቸው
ውስጥም እግዚአብሄርን ብቻ ለማክበር ይሻሉ፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የቤተክርስቲያኑ አባሎች አድርጎ ስለጠራን እግዚአብሄርን እናመሰግናለን 81

ታዲያ የእግዚአብሄር ጽድቅ የተገለጠው የት ነው?

የእግዚአብሄር ጽድቅ የተገለጠው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ውስጥ


ነው፡፡ በኢየሱስ ጥምቀትና በመስቀሉ ደም ውስጥ ተገልጦዋል፡፡ ጌታ እኛን ከዓለም
ሐጢያቶች ለማዳን እንደተጠመቀና በእኛ ፋንታም ክቡር ደሙን በመስቀል ላይ
እንዳፈሰሰ መጽሐፍ ቅዱስ በግልጥ ይናገራል፡፡ የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል አሁን
እኛ በምናምንበት በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ውስጥ ተገልጦዋል፡፡ ይህ
የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል የእግዚአብሄር ፍቅር ፍሬ ነገር ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ
በዚህ ምድር ላይ በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅ? በመስቀል ላይ በመሞትና
ከሙታን በመነሳት ሐጢያቶቻችንን ሁሉ መደምሰሱ ይህ የእግዚአብሄር ጽድቅ
ነው፡፡ ዮሐንስ 3፡16 ‹‹በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ
እንዳይጠፋ እግዚአብሄር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ
ወዶአልና›› እንደሚል እግዚአብሄር አብዝቶ ስለወደደን ራሱ የሰው ስጋ ለብሶ
ወደዚህ ምድር በመምጣት፣ በመጠመቅና በመስቀል ላይ ደሙን በማፍሰስ
ከሐጢያቶቻችን ሁሉ አነጻን፡፡ ከጥፋታችንም ሁሉ አዳነን፡፡ እኛ ከሐጢያቶቻችን
ሁሉ የነጻነውና የእግዚአብሄር ልጆች የሆንነው በዚህ የእግዚአብሄር ጽድቅ በማመን
ነው፡፡ እኛ ይህንን የእግዚአብሄር ጽድቅ የለበስነው የእግዚአብሄርን ጽድቅ በያዘው
የውሃና የመንፈስ ወንጌል እውነት በማመን ነው፡፡ እግዚአብሄር ዓለሙን አብዝቶ
ስለወደደ አንድያ ልጁን ሰጠን፡፡ በዚህ ልጅ ጥምቀትና ባፈሰሰው ደሙ
ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ደመሰሰ፡፡ ጥምቀቱና ደሙ የእግዚአብሄርን ጽድቅ
የሚያዋቅሩ ሁለት ቁም ነገሮች ናቸው፡፡ እኛ በዚህ እውነት በማመን ሐጢያት
አልባ ሆነናል፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምን ሁሉ የእግዚአብሄርን
ጽድቅ ብቻ ማመንና መከተል አለበት፡፡ የእግዚአብሄርን ጽድቅ ማገልገል የሚችሉት
እነዚህ ሰዎች ናቸው፡፡
የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን የኢየሱስ ክርሰቶስ አካል ነች፡፡ የእግዚአብሄር
ቤተክርስቲያን የኢየሱስ ክርስቶስ አካል መሆንዋ እምነታችንን ለመኖር በግልጥ
ልንረዳው የሚገባን በእጅጉ ጠቃሚ የሆነ እውነት ነው፡፡ እኛም የክርስቶስ አካል
ብልቶች ለመሆን ያለ ምንም ገለልተኛነት በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ማመን
አለብን፡፡ እናንተስ ታዲያ? በእርግጥ የእግዚአብሄር ጽድቅ በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል ውስጥ እንደተገለጠ ታውቃላችሁን? የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
እውነት መረዳት አለባችሁ፡፡ ይህ ወንጌል የእግዚአብሄርን ጽድቅ እንደያዘም ማመን
አለባችሁ፡፡ የእግዚአብሄር ጽድቅ የተሰወረው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ውስጥ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


82 የቤተክርስቲያኑ አባሎች አድርጎ ስለጠራን እግዚአብሄርን እናመሰግናለን

ነው፡፡
ቢሆንም ብዙ ክርስቲያኖች አሁንም በክርስቶስ ውስጥ እንደሞቱ ይናገራሉ፡፡
ብዙውን ጊዜ የትኩረት ነጥባቸው ይህ ነው፡፡ ቀድሞውኑም በእግዚአብሄር ጽድቅ
ላይ እምነት ያላቸው ይመስል ስለ ራሳቸው ስጋዊ ጽድቅ ይመጻደቃሉ፡፡ እነዚህ
ሰዎች ኢየሱስ በመስቀል ላይ ባፈሰሰው ደም ብቻ እንደሚያምኑ ቢናገሩም
የራሳቸውን ጽድቅ ለማጽናት እየሞከሩ ነው፡፡ እዚህ ላይ በእግዚአብሄርም
ቤተክርስቲያን ውስጥ እንደዚሁ በእግዚአብሄር ጽድቅ ከመታመን ይልቅ የገዛ ራሱን
ጽድቅ ለማጽናት የሚሞክር ማንኛውም ሰው የስጋውን መሻቶች ለማርካት የሚሻ
ሰው ነው፡፡ ይህ ሰብዓዊ ጽድቅ የስጋቸውን መሻቶች ብቻ ለማርካት በሚሹ
ሐይማኖተኞች የተፈጠሩ ከንቱ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችን እንጂ ያፈራው ሌላ
ምንም ነገር የለም፡፡ እግዚአብሄር ግን በጭራሽ እንደማይታገሳቸው ተናግሮዋል፡፡
እነርሱ እነዚህን ሰዎች በመጨረሻው ቀን ሊቀጣቸው እንዳዘጋጃቸው ተናግሮዋል፡፡

ቤተክርስቲያን ‹‹አካሉና ሁሉን በሁሉ የምትሞላ የእርሱ ሙላቱ ናት፡፡››


(ኤፌሶን 1፡23)

እግዚአብሄር በዚህ ምድር ላይ ቤተክርስቲያኑን ከመሰረተ በኋላ ሁሉም ሰው


የሰማይን መንፈሳዊ በረከቶች ይቀበል ዘንድ መላውን ዓለም በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል ሊሞላ ፈለገ፡፡ በሌላ አነጋገር በዚህ ዓለም ላይ የሚኖረው እያንዳንዱ ሰው
ከዓለም ሐጢያቶች ሁሉ እንዲድን የሚያስችለው ተቋም የእግዚአብሄር
ቤተክርስቲያን ነች፡፡ ይህንን የሚሻውም ራሱ እግዚአብሄር ነው፡፡ ቤተክርስቲያን
እግዚአብሄር በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በኢየሱስ ክርስቶስ የመሠረታት ተቋም
ነች፡፡ የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን እግዚአብሄር የሚሻውን ሁሉ ትሰራለች፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስ የዚህች ቤተክርስቲያን ራስ ስለሆነና እኛም አካሉ ስለሆንን
ከእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን መነጠል አንችልም፡፡
ስለዚህ ማንም ሰው የኢየሱስ ክርስቶስን ስም ስለጠራ ብቻ ከእግዚአብሄር
ሕዝብ አንዱ ሊሆን አይችልም፡፡ ማንም ሰው ሰውነቱን ለጌታ በእሳት ለመቃጠል
አሳልፎ የመስጠት በቂ ቅንዓት ቢኖረው እንኳን የእግዚአብሄርን ቤተክርስቲያን
መመስረትና የእርሱን ሥራ መስራት አይችልም፡፡ እግዚአብሄር በዚህ ምድር ላይ
ቤተክርስቲያኑን የመሰረተውና ሥራውን የሚሰራው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
በሚያምኑ አማኞች አማካይነት ነው፡፡ እዚህ ላይ ሁላችንም ልንገነዘበው የሚገባን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የቤተክርስቲያኑ አባሎች አድርጎ ስለጠራን እግዚአብሄርን እናመሰግናለን 83

ነገር ቢኖር የኢየሱስ ክርስቶስ አካል በመሆናችን ሁላችንም ጌታችን ከአጥማቂው


ዮሐንስ በተቀበለው ጥምቀትና በመስቀል ላይ ባፈሰሰው ደም እናምናለን፡፡ ኢየሱስ
በዚህ ምድር ላይ በአጥማቂው ዮሐንስ የተቀበለው ጥምቀትና በመስቀል ላይ
ያፈሰሰው ደም የእግዚአብሄርን ጽድቅ ይዘዋል፡፡ እነዚህ የእግዚአብሄርንም ፍቅር
ደግሞ ይገልጣሉ፡፡ እግዚአብሄር በዚህ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ለሚያምኑ
ሰዎች ቤተክርስቲያኑን ሰጥቶዋቸዋል፡፡ ጽድቁንም እንዲመሰክሩ አድርጎዋቸዋል፡፡
እኛ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ስለምናምን ሁላችንም እውነተኛውን
ወንጌል ከሐሰተኛ ወንጌሎች መለየት መቻል አለብን፡፡ ማናቸውንም ሰባኪ
በምንሰማበት ጊዜ ሁሉ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ላይ ያለን እምነታችን ይህ
ሰባኪ የሚናገረው ነገር እውነት ይሁን ወይም ስህተት የምንለይበት መለኪያ ሊሆን
ይገባል፡፡ ዲያብሎስ በራሱ ሐሰተኛ ወንጌል እንዴት በዚህ ዓለም ላይ እየሰራ
እንደሆነ ማወቁም ለእኛ በእጅጉ አስፈላጊያችን ነው፡፡ እዚህ ላይ እግዚአብሄር
በእኛ የሚደሰተው ከእርሱ ጎን ስንቆም፣ የእግዚአብሄር ቃል የሆነውን የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል አጥብቀን ስንይዝና የእርሱን ሥራ ስንሰራ ብቻ እንደሆነ
ልንገነዘብ ይገባናል፡፡
እነዚህ ቅዱሳኖች የሚሰበሰቡበት ስፍራ የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ነች፡፡
በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ የእርሱ አገልጋዮችና የእርሱ ቅዱሳኖች አሉ፡፡
ሁሉም አንድ የጋራ እምነት አላቸው፡፡ ሁሉም ለእግዚአብሄር ጽድቅ ይኖራሉ፡፡
በእግዚአብሄር ጽድቅና በሰጣቸው በረከቶች ሁሉ በመመካትም መላው ዓለም
የደህንነት በረከት የሚገኘው እግዚአብሄር በሰጠው የውሃና የመንፈስ ወንጌል
አማካይነት መሆኑን እንዲያውቅ ይፈቅዳሉ፡፡ እናንተም ደግሞ በእርሱ
ቤተክርስቲያንና በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት የእግዚአብሄርን ጽድቅ
በግልጥ መለየት መቻል አለባችሁ፡፡ የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን እዚህ ያለችው
የእርሱን ሥራ ለመስራት ነው፡፡

እግዚአብሄር እኛን ልጆቹ ለማድረግ ከዓለም ፍጥረት በፊት በኢየሱስ ክርስቶስ


በኩል መረጠን፡፡

በኤፌሶን 1፡4-5 ላይ እንዲህ ተጽፎዋል፡- ‹‹ዓለም ሳይፈጠር በፊት ቅዱሳንና


ነውር የሌለን በፍቅር እንሆን ዘንድ በክርስቶስ መረጠን፤ በበጎ ፈቃዱ እንደወደደ
በኢየሱስ ክርስቶስ ሥራ ለእርሱ ልጆች ልንሆን አስቀድሞ ወሰነን፡፡›› ይህ ምንባብ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


84 የቤተክርስቲያኑ አባሎች አድርጎ ስለጠራን እግዚአብሄርን እናመሰግናለን

እግዚአብሄር እኛን ተራ የሆንን ፍጡራኖች በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ልጆቹ አድርጎ


ሊቀበለን መወሰኑን ይነግረናል፡፡ እግዚአብሄር ለእኛ ያቀደው ይህ ዕቅድ ምንኛ
አስገራሚ ነው?
እግዚአብሄር ለእኛ ያለው ዕቅድ እናንተንና እኔን የእርሱ ወንዶችና ሴቶች
ልጆች ማድረግ ነበር፡፡ እናንተና እኔ በእግዚአብሄር ፊት የተዋረድን ፍጡራኖች
ብንሆንም እግዚአብሄር በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ አማካይነት እኛን የተዋረድነውን
ፍጡራኖች እንደ በጎ ፈቃዱ አዳነን፡፡ እግዚአብሄር በቤተክርስቲያኑ ውስጥ
ስላኖረንና ከእርሱ ጋር አብረን እንድንሰራ ስላደረገን በጣም አመስጋኞች ነን፡፡
እንዴት አመስጋኝ ላንሆን እንችላለን? እግዚአብሄር አብ አንድ ቀን በመንግሥተ
ሰማይ እንድንኖርና ከኢየሱስ ክርስቶስም ጋር በክብሩ ሁሉ እንድንደሰት በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል የምናምነውን ሁላችንን ባርኮናል፡፡ ይህ የእግዚአብሄር አብ
ፈቃድ ምን ያህል አስገራሚ ነው? እግዚአብሄር አብ ከዓለም ፍጥረት በፊት እኛን
በክርስቶስ ልጆቹ ሊያደርገን ይህንን አስገራሚ ዕቅድ አቀደ፡፡ ይህ ዕቅድ የተከወነው
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት ነው፡፡ የእግዚአብሄር አብ ዕቅድ በጣም
ድንቅና ግሩም ስለሆነ ለዚህ ዕቅድ ከመጠን በላይ ለዘላለም እርሱን
እናመሰግነዋለን፡፡
እንዲህ ያሉ ድንቅ በረከቶች የሚገኙት በአዳኛችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል
ብቻ ነው፡፡ እነርሱን ለመቀበልም መንገዱ የሚገኘው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
ውስጥ ነው፡፡ ከዚህ ከውሃውና ከመንፈሱ ወንጌል ውጪ የእግዚአብሄር ጽድቅ
ሊታሰብ እንኳን አይችልም፡፡ ትክክለኛ እውነት ሊገኝ የሚችለው በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል በሚያምነው እምነት አማካይነት ብቻ በእግዚአብሄር ልጅ
በኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ ከእግዚአብሄር ዘንድ የሚገኘውን የዘላለም ሕይወት
ማግኘት የሚችሉት በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምኑ ሰዎች ብቻ ናቸው፡፡
የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል የታቀደው በሰዎች ሳይሆን በእግዚአብሄር ነበር፡፡
የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል እውነት በሰው የተበጀም ይሁን ከሰው የመጣ
አይደለም፡፡ ነገር ግን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በእግዚአብሄር አብ የታቀደ ነበር፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስም ይህንን እውነት ከአጥማቂው ዮሐንስ በተቀበለው ጥምቀትና
በመስቀል ላይ ባፈሰሰው ደም ፈጽሞታል፡፡ ከውሃውና ከመንፈሱ ወንጌል
የሚበልጥ ውብ የሆነ የደህንነት ወንጌል በዚህ በመላው ዩኒቨርስ በየትም ቦታ
የለም፡፡
ስለዚህ ሁላችንም እግዚአብሄር በሰጠን የውሃና የመንፈስ ወንጌል ማመንና
እርሱን ማመስገን አለብን፡፡ ሁላችንም በእምነታችን ላደረገልንና ወደፊት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የቤተክርስቲያኑ አባሎች አድርጎ ስለጠራን እግዚአብሄርን እናመሰግናለን 85

ለሚያደርግልን ነገር አምላካችንን ልናመሰግን ይገባናል፡፡ አንዳንድ ወንድሞቻችንና


እህቶቻችን ፍቅሩን፣ ደህንነቱንና ክብሩን ስለሰጠን እግዚአብሄርን ከፍ ለማድረግ
አዳዲስ የምስጋና መዝሙሮችን ለመጻፍ የተገደዱት ለዚህ ነው፡፡
ጉዞ በማደርግበት ወይም ነጻ ጊዜ በሚኖረኝ ወቅት ሁሉ ብዙውን ጊዜ
አንዳንድ መዝሙሮችን በለሆሳስ እዘምራለሁ፡፡ በዚህ ዓለም ላይ ያሉት አብዛኞቹ
መዝሙሮች ስለ ፍቅር ወይም ስለ አንዳንድ ሌሎች ተራ ነገሮች የሚዘመሩ ቢሆኑም
ለእኔ ምርጥ የሆነው መዝሙር እግዚአብሄርን ለእኛ ስለተሰጠን ጽድቅ
የሚያመሰግን መዝሙር ነው፡፡ እኛ ፈጣሪያችን እግዚአብሄር ከሐጢያቶቻችን ሁሉ
ያዳነበትን የደህንነት ምስጢር የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ስለምናውቅ
ለእግዚአብሄር የምንዘምራቸው መዝሙሮች በእርግጥም ከፍ ያደርጉታል፡፡
እግዚአብሄር እኛን ከሐጢያት ያዳነበት ይህ የደህንነት ምስጢር የሆነው የውሃውና
የመንፈሱ ወንጌል በጣም ጥልቅ ስለሆነ እግዚአብሄርን ማመስገን ፈጽሞ
አይታክተንም፡፡ በዚህ ምስጋና አማካይነት ከጥልቅ ልቦቻችን ዝማሬዎችን ለእርሱ
እየዘመርን እግዚአብሄርን ስለ ፍቅሩ እናወድሰዋለን፡፡
እግዚአብሄር ከዓለም ፍጥረት በፊት በኢየሱስ ክርስቶስ በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል ሊያድነን አቀደ፡፡ ይህንንም ደህንነት ሰጠን፡፡ ይህ በረከት በጣም
ታላቅና አስገራሚ በመሆኑ ምን ያህል አመስጋኞች እንደሆንን የምንገልጥባቸው
ቃላቶች የሉንም፡፡ እግዚአበሄር ለእኛ ያደረገው በእርግጥም አስደናቂ ነው፡፡ እኛ
በአያሌው እርሱን እናመሰግነዋለን፡፡ ኢየሱስ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
አማካይነት ከሐጢያቶቻችን ሁሉ አድኖናል፡፡ ይህ ወንጌል ለሁሉም ሰው ክፍት
ነው፤ ነገር ግን በጣም ብዙ ሰዎች የኢየሱስን ጥምቀት ትርጉም ስለማያውቁ
ከሐጢያቶቻቸው ሁሉ መንጻት ሳይችሉ ቀርተው አሁንም እየተቅበዘበዙ ነው፡፡
ሁላችንም እግዚአብሄርን የምናመሰግንበት ምክንያት በኢየሱስ ክርስቶስ ባለው
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ውስጥ ይገኛል፡፡
አንድ ተራ ፍጡር የሆነ ሰው እንዴት የእግዚአብሄር ልጅ ሊሆን ይችላል?
ተራ የሆኑ ፍጡራኖች እንደ እግዚአብሄር ልጅ እንዴት መለኮታዊ ደረጃ ሊደርሱ
ይችላሉ? አንድ ትል ወደ ዝንብነት ሊቀየር ይችላል፤ ነገር ግን ሰዎች የእግዚአብሄር
ወንዶችና ሴቶች ልጆች መሆን እንዴት ይቻላቸዋል? እግዚአብሄር ግን ይሀንን
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት አድርጎልናል፡፡ ይህ አስገራሚ አይደለምን?
ይህንን አስደናቂና አስገራሚ ድንቅ እንዴት ልንገልጠው ይቻለናል? ለዚህም
እግዚአብሄርን እንደሚገባው ማመስገን የሚቻለን እንዴት ነው? ይህንን ምስጢር
መረዳትና ጸጋው አስገራሚና ድንቅ የሆነውን አምላክ ማመስገን የምንችለው

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


86 የቤተክርስቲያኑ አባሎች አድርጎ ስለጠራን እግዚአብሄርን እናመሰግናለን

በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን ብቻ ነው፡፡


የእግዚአብሄርን ቤተክርስቲያን ምስጢርና የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
የሚያውቅ ሰው ሁሉ የእርሱን አስገራሚ ዕቅድ መረዳትና እርሱንም በእምነት
ማመስገን ይችላል፡፡ እኛ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል እውነት በማመን
የቤተክርስቲያን አባሎች ሆነናል፡፡ እኛ አሁን የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ራስ
የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስን ስላወቅን በእርሱ ፈቃድ መሠረት እውነተኛውን
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በመላው ዓለም ሁሉ እየሰበክን ነው፡፡
የሐጢያቶችን ስርየት የተቀበለ ሁሉ የቤተክርስቲያኑ አባል ስላደረገው
አሁኑኑ እግዚአብሄርን ማመስገንና ቀሪው ሕይወቱን በእርሱ ፈቃድ መሠረት መኖር
አለበት፡፡ እንዲህ ያለ የእምነት ሕይወት መኖር በራሱ ከእግዚአብሄር ዘንድ የተሰጠ
ግሩም በረከት ነው፡፡ አሁን እግዚአብሄርን ድንቅ ለሆነው ዕቅዱ ልናመሰግነውና
ልናወድሰው ይገባናል፡፡ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለማገልገል በመሞከር
በሥራ ውስጥ በጠለምንበት መከራችን መካከል እንኳን ሆነን እግዚአብሄርን
ለማመስገን እንገደዳለን፡፡ እርሱን ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ማመስገናችንንም
እንቀጥላለን፡፡ ክብራችንን ስናጣና ጽድቃችንም ሲፈራርስ ወንጌልን ለማሰራጨት
ስንል ብቻ ማንኛውንም መከራ ሁሉ ለመቋቋም ደስተኞች ነን፡፡ አሁንም
እግዚአብሄርን ለዘላለም እናመሰግነዋለን፡፡
አሁን በሚቻለው በማንኛውም መንገድ ሁሉ እግዚአብሄርን ማገልገል
አለብን፡፡ ምክንያቱም በኢየሱስ ክርስቶስ ጥምቀትና በደሙ አማካይነት ሙሉ
በሙሉ በተከናወነው የደህንነት ዕቅዱ ውስጥ ስለተገለጠው አስገራሚ ጸጋው
እግዚአብሄርን እንደሚገባው አላመሰገንነውም፡፡ ሁላችንም እግዚአብሄርን
ለውሃውና ለመንፈሱ ወንጌል እውነት ልናመሰግነውና እግዚአብሄርን በመተማመን
ልንኖር ይገባናል፡፡ እግዚአብሄር በእኛ አማካይነት በዓለም ዙሪያ ሁሉ ያሉትን
ሰዎች እንደሚባርክም ማመን አለብን፡፡
እግዚአብሄር በእናንተና በእኔ አማካይነት የሚሰራው ለምንድነው? በስጋዊ
አስተሳሰባችን እግዚአብሄር በእኛ አማካይነት ምን ሊሰራ እንደሚችል ግራ እንጋባ
ይሆናል፤ ነገር ግን እርሱ በእኛ የሚሰራው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
ስለምናምን ልቦቻችን ቅዱስና ንጹህ ስለሆኑ ነው፡፡ በሌላ አነጋገር እምነታችን
ትክክለኛ እምነት ነው፡፡ እኛ የእግዚአብሄርን ጽድቅ በያዘው በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል በማመን ሙሉ በሙሉ ነጽተናል፡፡ እግዚአብሄር የጽድቁን ወንጌል በዓለም
ላሉ ሰዎች ሰዎች ሁሉ እያስፋፋ ያለው በእኛ አማካይነት ነው፡፡ እኛ ለዚህ አስደናቂ
በረከት አመስጋኞች እንደሆንን የምንገልጥባቸው ቃላቶች የሉንም፡፡ በዓለም ሁሉ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የቤተክርስቲያኑ አባሎች አድርጎ ስለጠራን እግዚአብሄርን እናመሰግናለን 87

ያለ ሰው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ውስጥ የተገለጠውን የጽድቁን ፍቅር


እንዲቀበል በማስቻሉ እግዚአብሄርን እናመሰግነዋለን፡፡
እኛ የወንጌል መጽሐፎቻችንን በእያንዳንዱ የዓለም ቋንቋ በማሳተም አሁን
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል የመስበኩን የእግዚአብሄር ታላቅ ተልዕኮ
እየታዘዝን ነው፡፡ ለሥነ ጽሁፍ አገልግሎታችን ምስጋና ይድረሰውና ይህንን እውነት
የማያውቁ ሰዎችም ለመጀመሪያ ጊዜ እየተረዱት ነው፡፡ በደብዳቤዎቻቸው
ገረሜታቸውንና ምስጋናቸውን እየገለጡ ነው፡፡ እነዚህ ሰዎች በቀሪው
ሕይወታቸው በዚህ እውነት ለመኖር አያመነቱም፡፡ በመጽሐፎቻችን አማካይነት
እያሰራጨነው ያለነው ይህ ወንጌል በእጅጉ ፍጹም እውነት ስለሆነ ሁሉም በዚህ
መልኩ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለማገልገል ይሻሉ፡፡ ይህ ግሩም ውጤት
የተገኘው እግዚአብሄር ስላቀደው ነው፡፡ እኛም በእርሱ እውነት በመታመን በዚህ
የእግዚአብሄር ሥራ ውስጥ እየተሳተፍን ነው፡፡ ሁላችንም ራሳችንን ለእግዚአብሄር
በአደራ መስጠታችንና የእርሱን ጽድቅ ለማገልገልም በዚህ ሥራ ውስጥ
መሳተፋችን ፈጽሞ ትክክል ነው፡፡ አኛ የምንሰብከው የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል
ተራ ወንጌል አይደለም፡፡ ይህ የእግዚአብሄርን ጽድቅ የያዘ ብቸኛው ወንጌል ነው፡፡
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል የያዙት መጽሐፎቻችን ሲሰራጩና በዓለም ሁሉ
በሚገኙ ሰዎች ሲነበቡ ሁሉም የእግዚአብሄርን ጽድቅ ወደ ማወቅ ይደርሳሉ፡፡
በአሁኑ ጊዜ ብዙ ክርስቲያኖች በኢየሱስ ቢያምኑም ደህንነታቸው በራሳቸው
ጥረት ላይ እንደተመረኮዘ ያስባሉ፡፡ ከእነርሱ አንዳንዶቹ በእርግጠኝነት
ከሐጢያቶቻቸው እንደዳኑ ይናገራሉ፡፡ በተጨባጭ ግን የእግዚአብሄርን ፈቃድ
እየታዘዙ ስላልሆነ አሁንም በልቦቻቸው ውስጥ ሐጢያ አለ፡፡ በአንጻሩ በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል የሚያምኑ አማኞች ደህንነታቸውን ያገኙት በራሳቸው ምንም
ነገር ሳያደርጉ በእምነት ብቻ ነው፡፡ በዓለም ሁሉ የሚገኙ በርካታ ሰዎች
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል የያዘውን የእኛን አንድ መጽሐፍ በማንበብና በዚህ
ወንጌል በማመን እንደተለወጡ የታወቀ ነው፡፡
እግዚአብሄር እያንዳንዱ ሰው እምነቱን በግልጥ እንዲያወሳ ይሻል፡፡ ይህ
ማለት ወንጌል ብዙ ሊሆን ይችላል በማለት መሃል ሰፋሪ በመሆን ፋንታ በእርግጥ
በእግዚአብሄር ቃል ታምኑ እንደሆነ ወይም እንዳልሆነ ግልጥ የሆነ አቋም መያዝ
አለባችሁ ማለት ነው፡፡ እዚህ ላይ ማንኛውምና እያንዳንዱ ወንጌል ትክክል ነው
የሚል እንዲህ ያለ የመሃል ሰፋሪነት ስፍራ የምትይዙ ከሆነ ይህ ማለት እናንተ
በእግዚአብሄር ቃል ከማመን ርቃችሁ በእግዚአብሄር ላይ እያመጻችሁ ነው ማለት
ነው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


88 የቤተክርስቲያኑ አባሎች አድርጎ ስለጠራን እግዚአብሄርን እናመሰግናለን

በዚህ ዓለም ላይ ሁሉን በሁሉ የሚሞላው ማነው?

በደህንነቱ፣ በበረከቶቹና በክብሩ የሚሞላን ፈጣሪያችን ኢየሱስ ክርስቶስ


ነው፡፡ ይህንን ሙላት የሚሰጠን በምን አማካይነት ነው? እርሱ በተትረፈረፉ
በረከቶቹ የሚሞላን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ውስጥ በተገለጠው
የእግዚአብሄር ፍቅር አማካይነት ነው፡፡ ጌታ በአምላክ በረከቶች እየሞላን ነው፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ ኢየሱስ ሁሉን በሁሉ እንደሚሞላ ይናገራል፡፡ ይህም ይህንን
የመለኮት ፈቃድ የሚያገለግሉ የእርሱ ወኪሎች እንዳሉ ያሳያል፡፡ ኢየሱስ ሁሉን
በሁሉ ለመሙላት የሚሰራው ከማን ጋር ነው? የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን
አባሎች በሆንነው በእናንተና በእኔ በኩል አይሰራምን? ነገር ግን በእግዚአብሄር
ቤተክርስቲያን ውስጥ የዳነ ሰው ቅዱስና የቤተክርስቲያን አባል እንደሆነ ኢየሱስ
ክርስቶስም የዚህች ቤተክርስቲያን ራስና እኛም ደግሞ የእርሱ አካል እንደሆንን
የማያውቅ ሰው ካለ እግዚአብሄር ይህንን ሰው ከእርሱ ሠራተኞች አንዱ አድርጎ
ሊጠቀምበት አይደሰትም፡፡ ስለዚህ ሁላችንም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
በማመን የእግዚአብሄር ልጆች የመሆናችንን እውነታ መረዳትና ማመን አለብን፡፡
የእርሱ ቤተክርስቲያን አባሎች በመሆናችንም ራስ ለሆነው ኢየሱስ ክርሰቶስ
መገዛት እንዳለብንም መገንዘብ ያስፈልገናል፡፡
እኛ በእርሱ ጽድቅ በማመን የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን አባሎች ሆነናል፡፡
ሁላችንም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አንድ ቤተሰብ እንደሆንንም እናምናለን፡፡
ይህንን እውነት መረዳትና በእርሱም ማመን ፈጽሞ ያስፈልገናል፡፡ በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል ላይ ያለን እምነታችን ማደግ አለበት፡፡ እኛ በኢየሱስ ክርስቶስ
አንድ አካል እንደሆንንና ጌታም የእኛ ራስ እንደሆነ መገንዘብና ማመን አለብን፡፡
ሰውነታችንን ስንመለከት ከጠጉራችን እስከ እግር አውራ ጣቶቻችን ድረስ ያለው
እያንዳንዱ ብልት በሙሉ ከሰውነታችን ጋር የተያያዘ እንደሆነ እናያለን፡፡
ጠጉራችንም እንኳን የሰውነታችን ክፍል ነው፡፡ ሰውነታችንን በደምብ ለመመገብና
ለመንከባከብ ረጅም ርቀት የምንሄደው ለዚህ ነው፡፡ በሰውነታችን ላይ ባለች ትንሽ
ብልት ላይ አንድ ችግር ከተፈጠረ መላው ሰውነታችን ይሰቃያል፡፡ ልክ እንደዚሁ
እኛም ደግሞ የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን አባሎች ስለሆንንና ሁላችንም ራስ
በሆነው በኢየሱስ ክርስቶስ ስለምናምን ሁላችንም የዚያው የኢየሱስ ክርስቶስ አካል
ወገን ነን፡፡ ስለዚህ ማናችንም ብንስት ሁላችንም መንገዳችንን ለማስተካከል
መሞከር አለበን፡፡ አለበለዚያ በአንዱ ሰው መሳት እያንዳንዱ የቤተክርስቲያን አባል
ይሰቃያል፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የቤተክርስቲያኑ አባሎች አድርጎ ስለጠራን እግዚአብሄርን እናመሰግናለን 89

የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን የእርሱን ፍቅርና በረከቶች በዓለም ሁሉ ካለ


ሰው ጋር የምትጋራ ተቋም ነች፡፡ እኛም ክርስቶስ ሁሉን በሁሉ የሚሞላባት የዚህች
ቤተክርስቲያን አባሎች ሆነናል፡፡ እያንዳንዳችን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
የምናምን አጋር ምዕመናን ስለሆንን ሁላችንም ለዚህ ድንቅ በረከት እግዚአብሄርን
ማመስገን አለብን፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ያለን የጋራ እምነትም
የማይናወጥ መሆን አለበት፡፡ በእግዚአብሄር ድንቅ ሥራ መሠረትም በዚህ እምነት
በረከቶች ውስጥ መኖር አለብን፡፡ እዚህ ላይ ሁላችንም የውሃውና የመንፈሱ
ወንጌል በጥቂት ሰዎች ብቻ እንደማይሰራጭ ነገር ግን የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን
ራስ ለሆነው ለኢየሱስ ክርስቶስ ትዕዛዛቶች በመገዛት በአንድ ላይ ስንተባበር ብቻ
እንደሚሰራጭ ልንገነዘብ ይገባናል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ‹‹እናንተ የክርስቶስ ናችሁ፤
ክርስቶስም የእግዚአብሄር ነው›› (1ኛ ቆሮንቶስ 3፡23) እንደሚል በእርግጥ የማን
ወገን እንደሆንንና ጥሪያችንም ምን እንደሆነ መረዳታችን በእጅጉ ያስፈልገናል፡፡
አንዳንድ ሰዎች የሐጢያቶችን ስርየት ከተቀበሉ በኋላም እንኳን ‹‹ሁሉም
ቤተክርስቲያን አንድ ነው›› በማለት የእግዚአብሄር ጽድቅ የሚገኝበትን
የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን መለየት አይችሉም፡፡ እነዚህ ሰዎች የሐጢያቶችን
ስርየት በግልጥ የተቀበሉ ቢሆኑም የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ወገን ይሁኑ
ወይም የሰይጣን ጉባኤ ይሆኑ አያውቁም፡፡ በዚህ ምክንያት ከእነርሱ አንዳንዶቹ
መንፈሳዊ እንክብካቤ አጥተው ይጠፋሉ፡፡ ሰይጣን የቅዱሳኖችን ጉድለቶች
ለማጥመድ ሁሌም አጋጣሚ ስለሚፈልግ እነዚህን ሰዎች ይወቃቸዋል፡፡ እነዚህም
ሰዎች ለዘላለም ሊሰቃዩ በመጨረሻው ቀን በእግዚአብሄር ይፈረድባቸዋል፡፡
መታወቅ ያለበትን ማወቅ፣ መታመን ያለበትን ማመን፣ በትክክል ውብ
የሆነውን ውበቱን መረዳትና በትክክል ክቡር የሆነውንም ክቡርነቱን ማየት በእጅጉ
ያስፈልገናል፡፡ የእግዚአብሄር ጽድቅ ይህ ነው፡፡
እኛ በእግዚአብሄር ጽድቅ ስለምናምን ማንነታችንን ማወቅና ወንጌልን
በትክክለኛ ኩራት ማገልገል አለብን፡፡ እኛ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
በልቦቻችን በማመን ጻድቃን ስለሆንን ሁላችንም ተለውጠናል፡፡ እግዚአብሄር
ዮናስን ወደ ነነዌ ሄዶ እግዚአብሄር ሊያደርግባቸው ስላለው ነገር እንዲሰብክ
በነገረው ጊዜ እግዚአብሄርን ለመታዘዝ አሻፈረኝ ብሎ ወደ ተርሴስ ለመሸሽ ጀልባ
ላይ ተሳፈረ፡፡ ያን ጊዜ እግዚአብሄር ማዕበል አስነሳ፡፡ በጀልባው ውስጥ ያለው
ሰው ሁሉ ይህንን ማዕበል ማን እንዳመጣው ዕጣዎችን ጣለ፡፡ ዕጣው በዮናስ ላይ
ሲወድቅ የጀልባዋ ባለቤቶች እንዲህ አሉት፡- ‹‹ይህ ክፉ ነገር በምን ምክንያት
እንዳገኘን እባክህ ንገረን፤ ሥራህ ምንድር ነው? ከወዴትስ መጣህ? አገርህስ ወዴት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


90 የቤተክርስቲያኑ አባሎች አድርጎ ስለጠራን እግዚአብሄርን እናመሰግናለን

ነው? ወይስ ከማን ወገን ነህ?›› (ዮናስ 1፡8) ያን ጊዜ ነቢዩ ዮናስ እንዲህ አላቸው፡-
‹‹እኔ ዕብራዊ ነኝ፤ ባሕሩንና የብሱን የፈጠረውን የሰማይን አምላክ እግዚአብሄርን
አመልካለሁ፡፡›› (ዮናስ 1፡9) ዮናስ በዚህ ክስተት አማካይነት ለራሱ ማንነቱን፣
ያለበትን ሁኔታዎችና ጥሪውን አስታወሰ፡፡ እኛም ደግሞ በየቀኑ ራሳችንን
መመርመር፣ ደህንነታችንን ማጽናት፣ የማን ወገን እንደሆንን መረዳት፣
የእግዚአብሄር ሕዝብ የመሆናችንን ማንነት ማመንና በዚያው መሰረትም መመላለስ
ይገባናል፡፡
ዛሬ በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ ላሉት አገልጋዮቻችንና
ቅዱሳኖቻችን ሁሉ የማስተላልፈው መልዕክቴ ይህ ነው፡፡ ሁሉን በሁሉ የሚሞላው
የእርሱ ሙላት የሚገኘው በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ማለትም የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል በማወጅ ነው፡፡ የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን በመላው ዓለም
ከሚገኝ ስፍራ ይልቅ እጅግ ብሩክ የሆነች ስፍራና የበረከቶች ሁሉ መጋዘን ነች፡፡
ይህች የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን የበረከቶች የሐብት መጋዘናችሁ እንደሆነች
ትገነዘቡ ዘንድ ሁላችሁንም እጠይቃችኋለሁ፡፡ እግዚአብሄር በቤተክርስቲያኑ
አማካይነት የደህንነት በረከቶቹን ለእናንተ፣ ለቤተሰባችሁና በዓለም ሁሉ
ለሚኖረው ለእያንዳንዱ ሰው እያካፈለ ነው፡፡ ይህንን ሁሌም እያስታወሳችሁ
በየቀኑ በእግዚአብሄር በረከቶች መካከል በእምነት እንድትኖሩ እመክራችኋለሁ፡፡
ይህች የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ከውሃና ከመንፈስ ዳግመኛ የተወለዱ
ሰዎች የሚሰበሰቡባት፣ የእግዚአብሄርን ሥራ የሚሰሩባት፣ የሚያርፉባት፣ እርስ
በርሳቸው የሚሳሳቁባትና ሕብረት የሚያደርጉባት ስፍራ ነች፡፡ የእግዚአብሄር
ቤተክርስቲያን የእርሱ በረከቶች የሚጠራቀሙባት፣ በየቀኑ የሚታደሱበትና
ለሁሉም የሚካፈሉበት ስፍራ ነች፡፡ እኛ የዚህች የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን
አባሎች መሆናችንን በመረዳት ሁላችንም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
በመታመንና ጌታ እስከሚመለስበት ቀን ድረስ በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ
በመቆየት የእርሱን ሥራ መስራት አለብን፡፡ እናንተም የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን
አባል ስለሆናችሁ ቃሉን ለማቅረብና ዳግመኛ ለመወለድ ለሚናፍቁ በእያንዳንዱ
የዓለም ማዕዘን ላሉ ሰዎች አዲስ ሕይወትን ለማምጣት የእርሱን ክቡር ሥራ
እየሰራችሁ ነው፡፡
እግዚአብሄር ኢየሱስ ክርስቶስን ለእናንተና ለእኔ የላከው የቤተክርስቲያኑ
አባሎች ሊያደርገን ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ምድር ላይ ስለተጠመቀና
በመስቀል ላይ ደሙን አፍስሶ ስለሞተ ለአንዴና ለመጨረሻ ከሐጢያቶቻችን ሁሉ
ድነናል፡፡ ነገር ግን ኢየሱስ ካዳነን በኋላ ቢተወን ኖሮ ምን ይፈጠር ነበር?

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የቤተክርስቲያኑ አባሎች አድርጎ ስለጠራን እግዚአብሄርን እናመሰግናለን 91

በእርግጠኝነት እንደገና እንጠፋ ነበር፡፡ እግዚአብሄር የቤተክርስቲያኑ አባሎች


ያደረገንና እዚያ ያኖረን ይህንን አሳምሮ በማወቁ ነበር፡፡ እግዚአብሄር በተጨባጭ
አካሉ ሊያደርገን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለእኛ በመስጠት ከዓለም
ሐጢያቶች ሁሉ አዳነን፡፡
እናንተስ ታዲያ? ለዚህ ድንቅ በረከት እግዚአብሄርን ታመሰግናላችሁን?
በእርግጥም ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ስላዳነንና የእርሱ ቤተክርስቲያን አባሎች እንሆን
ዘንድ እንዲህ አድርጎ ስለጠራን ሁላችንም ምስጋናችንን ለእግዚአብሄር
እናቀርባለን፡፡ 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


92 የቤተክርስቲያኑ አባሎች አድርጎ ስለጠራን እግዚአብሄርን እናመሰግናለን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ስብከት
5

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት
ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
እንደ እግዚአብሄር ጸጋ
ባለጠግነት መጠን ቤዛነትን
አግኝተናል
‹‹ ኤፌሶን 1፡7-14 ››
‹‹በውድ ልጁም እንደ ጸጋው ባለጠግነት መጠን በደሙ የተደረገ ቤዛነታችንን
አገኘን፤ እርሱም የበደላችን ስርየት፡፡ ጸጋውንም በጥበብና በአእምሮ ሁሉ
አበዛልን፡፡ በክርስቶስ ለማድረግ እንደወደደ እንደ አሳቡ የፈቃዱን ምስጢር
አስታውቆናልና፤ በዚህ ዘመን ፍጻሜ ይደረግ ዘንድ ያለው አሳቡም በሰማይና
በምድር ያለውን ሁሉ በክርስቶስ ለመጠቅለል ነው፡፡ እንደ ፈቃዱ ምክር ሁሉን
የሚሠራ እንደ እርሱ አሳብ አስቀድመን የተወሰንን በክርስቶስ ደግሞ ርስትን
ተቀበልን፡፡ ይኸውም በክርስቶስ አስቀድመን ተስፋ ያደረግን እኛ ለክብሩ ምስጋና
እንሆን ዘንድ ነው፡፡ እናንተም ደግሞ የእውነትን ቃል ይኸውም የመዳናችሁን
ወንጌል ሰምታችሁ ደግሞም በክርስቶስ አምናችሁ በተስፋው መንፈስ በመንፈስ
ቅዱስ ታተማችሁ፡፡ እርሱም የርስታችን መያዣ ነው፤ ለእግዚአብሄር ያለውን
እስኪዋጅ ድረስ ይህም ለክብሩ ምስጋና ይሆናል፡፡››

ጌታ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በምናምን በሁላችን ልቦች ውስጥ


የሐጢያቶችን ስርየትና ሰላምን ሰጥቶናል፡፡ እዚህ ላይ ጌታ ራሱ የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል ስለምናምን ሐጢያት እንደሌለብን እየመሰከረ ነው፡፡
እግዚአብሄር አባታችን በኢየሱስ ጽድቅ ላይ ባለን እምነታችን አማካይነት የዚህን
ዓለም ሐጢያቶች በሙሉ እንዳነጻ አስታውቆናል፡፡
እግዚአብሄር የሰጠን የጸጋው ባለጠግነቶች ምን ያህል ታላላቆች እንደሆኑ
መረዳት የምንችለው የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ስንሰብክ ብቻ ነው፡፡
ሌሎችም ደግሞ ይህንን የተባረከ የእግዚአብሄር ጸጋ መረዳት የሚችሉት ያን ጊዜ
ብቻ ነው፡፡ ታዲያ የእግዚአብሄርን ታላቅ የደህንነት ጸጋ የቀመሱት እነማን ናቸው?

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


96 እንደ እግዚአብሄር ጸጋ ባለጠግነት መጠን ቤዛነትን አግኝተናል

በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን የሐጢያቶቻቸውን ስርየት በልቦቻቸው


ውስጥ የተቀበሉ ሰዎች ናቸው፡፡ በሌላ አነጋገር የእግዚአብሄርን ታላቅ ጸጋ የለበሱት
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን ልቦቻቸው ከሐጢያቶቻቸው ሁሉ
የነጹላቸው ሰዎች ናቸው፡፡ የእግዚአብሄር ጸጋ የበዛው በእነዚህ ሰዎች ልቦች ውስጥ
ነው፡፡
ጌታችን ኢየሱስ ከአጥማቂው ዮሐንስ በተቀበለውና በመስቀል ላይ ባፈሰሰው
ክቡር ደሙ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ለአንዴና ለመጨረሻ ደምስሶዋል፡፡ ታዲያ
ኢየሱስ ወደ መስቀል የወሰደው የአዳም ሐጢያታችንን ብቻ ነበር? ቀሪዎቹን
ሐጢያቶቻችንን የሚወስድልን የንስሐ ጸሎቶች በምናቀርብበት ጊዜ ሁሉ ነው?
የለም፤ እንዳልሆነ የታወቀ ነው! ኢየሱስ በመስቀል ላይ በተሰቀለ ጊዜ የወሰደው
የአዳም ሐጢያታችሁን ብቻ እንደሆነ የምታምኑ ከሆነና በየቀኑ የምትሰሩዋቸውን
ሐጢያቶች የሚወስደው የንስሐ ጸሎቶቻችሁን በምታቀርቡበት ጊዜ ከሆነ
አስተሳሰባችሁና እምነታችሁ ፈጽሞ የተሳሳተ ነው፡፡ ስለዚህ እግዚአብሄር
የሰጣችሁን የደህንነት ጸጋ ታላቅነት መረዳት በእጅጉ ያስፈልጋችኋል፡፡
ልትገነዘቡትና ልታምኑት የሚገባችሁ የመጀመሪያው ነገር ኢየሱስ በዮርዳኖስ
ወንዝ በተቀበለው ጥምቀት አማካይነት የሕይወት ዘመናችሁን ሐጢያቶች በሙሉ
መሸከሙን ነው፡፡ ኢየሱስ ከአጥማቂው ዮሐንስ በተቀበለው ጥምቀት አማካይነት
የዚህን ዓለም ሐጢያቶች ከተሸከመ በኋላ ተሰቅሎ ሞተ፡፡ በዚህም በዚህ እውነት
የምናምነውን ሁላችንን በአንድ ጊዜ አድኖናል፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ከአጥማቂው
ዮሐንስ በተቀበለው ጥምቀትና በመስቀል ላይ ባፈሰሰው ደም አማካይነት እኛን
በእርሱ የምናምነውን አማኞች ለአንዴና ለመጨረሻ አድኖናል፡፡ እርሱ እኛን ቅዱስ
ለማድረግ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ፈጽሞ ሐጢያት አልባ አድርጎናል፡፡
ስለዚህ እግዚአብሄር በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት አትረፍርፎ
የሰጠንን የደህንነት ጸጋ ተደራሽነቱን ሳንገድብ ማመን አለብን፡፡ እግዚአብሄርን
‹‹የአዳም ሐጢያታችንን ብቻ ስለወሰድህ ገና በየቀኑ የምንሰራቸውን የግል
ሐጢያቶቻችንን እንድትደመስስ በየቀኑ የንስሐ ጸሎቶቻችንን ማቅረብ
ይኖርብናል፡፡ ገና ያልሰራናቸውን የወደፊት ሐጢያቶቻችንን በሚመለከት ገና
ሳንሰራቸው እንዴት ከእነርሱ ይቅር እንደተባልን ትናገራለህ?›› ማለትና ማሰብ
ለእኛ ፈጽሞ የማይዋጥ ነው፡፡ የእግዚአብሄር ጸጋ አስተውሎታችሁ በዚህ መልኩ
ከተገደበ እምነታችሁ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ላይ ያረፈ እውነተኛ እምነት
አይደለም፡፡ ራሳችሁ የፈጠራችሁት የተሳሳተና በራሳችሁ አስተሳሰቦች ውስጥ ያለ
እምነት ነው፡፡ ይህ እምነት የእውነትን አምላክ ቁጣ የሚያነሳሱ ሰዎች እምነት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


እንደ እግዚአብሄር ጸጋ ባለጠግነት መጠን ቤዛነትን አግኝተናል 97

ነው፡፡ የዚህ ዓይነቱ እምነት በአደገኛ ሁኔታ ከተሳሳተ እሳቤ የመነጨ ፈጽሞ
የተሳሳተ እምነት ነው፡፡ የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል እግዚአብሄር የሰጣችሁ
ፍጹም የሆነ የደህንነት ስጦታ ነው፡፡ ይህንን ወንጌል ከልባችሁ ካመናችሁ
በእርግጠኝነት የእግዚአብሄርን ማለቂያ የሌለው ፍቅር ትቀበላላችሁ፡፡ ነገር ግን
ይህንን የሚያድነውን የውሃና የመንፈስ ጸጋ የማትቀበሉ ከሆነ የእግዚአብሄርን ቁጣ
ትቀበላላችሁ፡፡
የዘመኑ ሐሰተኛ ክርስቲያኖች እምነት ያረፈው ከመጀመሪያውም
ከእግዚአብሄር ቃል ጋር ምንም ግንኙነት በሌለውና ከራሳቸው አስተሳሰቦች
በፈለቀው ነገር ላይ ነው፡፡ እነርሱ የራሳቸውን አምላኮች ከፈጠሩ በኋላ በራሳቸው
አስተሳሰቦች በተበጁ ትምህርቶች ያምናሉ፡፡ ስለዚህ በኢየሱስ ማመኑ ከእንግዲህ
ወዲህ የማይጠቅማቸው ሲሆን በቀላሉ በአንድ ሌላ ነገር ይተኩታል፡፡ ስለዚህ
በአሁኑ ጊዜ በጣም ብዙ ክርስቲያኖች ለእነርሱ በሚስማማቸው በማንኛውም
መንገድ ራሳቸው ባበጁዋቸው ትምህርቶች ያምናሉ፡፡
ነገር ግን ሰው በኢየሱስ ክርስቶስ ጽድቅ በትክክል የሚያምን ከሆነ አሁንም
ሐጢያተኛ እንደሆነ ሊናገር ይችላል? በመካከላችሁ ኢየሱስ የወሰደው የአዳምን
ሐጢያት ብቻ ነው፤ ሰው በየቀኑ የሚሰራቸው ሐጢያቶች በሚሰራው ጊዜ ሁሉ
መወገድ ያለባቸው በንስሐ ጸሎቶች አማካይነት ነው ብሎ በተሳሳተ መንገድ
የሚያስብ ሰው አለ? እንዲህ የሚል ማንኛውም ሰው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
የመጣውን የእግዚአብሄር ፍቅርና ምህረቱን የሚንቅ ሰው ነው፡፡ እነዚህ ሰዎች
ብቻቸውን የራሳቸውን የደህንነት መንገድ አበጅተዋል፡፡
እግዚአብሄር በኢሳይያስ 1፡18 ላይ እንዲህ አለ፡- ‹‹ሐጢአታችሁ እንደ አለላ
ብትሆን እንደ አመዳይ ትነጻለች፤ እንደ ደምም ብትቀላ እንደ ባዘቶ ትጠራለች፡፡››
በሌላ አነጋገር ኢየሱስ ራሱ እንዲህ ብሎናል፡- ‹‹ሐጢያቶቻችሁ እንደ ጭጋግ
ቢሆኑም እናንተ አሁንም የእኔ ናችሁ፤ ምክንያቱም አድኜአችኋለሁ፡፡ በሰማይ ላይ
እንዳለው ጭጋግ የበዙትን በርካታ ሐጢያቶቻችሁን በሙሉ አስወግጃለሁ፡፡
ስለዚህ እናንተ ሐጢያተኞች ሁሉ ወደ እኔ ተመለሱ፡፡›› በእርግጥ ሕያው በሆነው
አምላክ፣ በእርሱ እውነትና በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በተጻፈው የእርሱ ጽድቅ
የምታምኑ ከሆነ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ትቀበላላችሁ፡፡ ነገር ግን
የእግዚአብሄርን ጽድቅ የምትንቁ ከሆነ ከአዳም ሐጢያታችሁ የነጻችሁ ብትሆኑም
በየቀኑ የምትሰሩዋቸውን ሐጢያቶችና የወደፊት ሐጢያቶቻችሁን ስርየት
እንዳልተቀበላችሁ ትናገራላችሁ፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


98 እንደ እግዚአብሄር ጸጋ ባለጠግነት መጠን ቤዛነትን አግኝተናል

‹‹በውድ ልጁም እንደ ጸጋው ባለጠግነት መጠን በደሙ የተደረገ


ቤዛነታችንን አገኘን፤ እርሱም የበደላችን ስርየት፡፡›› (ኤፌሶን 1፡7)

ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሄር በግ የሆነው እናተንና እኔን በዚህ ዓለም ላይ


የሚኖረውንም ሰው ሁሉ ከሐጢያቶቹ ለመቤዠት ነው፡፡ ጌታ እኛን ከዓለም
ሐጢያቶች ሁሉ ለማዳን በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅ የሰውን ዘር እያንዳንዱን
ሐጢያት ተሸከመ፡፡ በእኛ ፋንታም ደሙን በመስቀል ላይ አፈሰሰ፡፡ ኢየሱስ ራሱ
በምድር ላይ ምንም ሐጢያት ባይሰራና ራሱም አምላክ ቢሆን ሐጢያቶቻችንን
በሙሉ ለመደምሰስ ማስተሰርያችን ሆነ፡፡ ጌታ እውነተኛውን የሐጢያቶች ስርየት
ሊሰጠን በዚህ ምድር ላይ ተጠመቀ፡፡ ከእርግማኖቻችን ሁሉ ነጻ ሊያወጣንም
ተሰቅሎ ሞተ፡፡
አንድ ሰው በዕድሜ ዘመኖቹ ሁሉ ምን ያህል ሐጢያት ይሰራል? እኛ
የመጨረሻውን እስትንፋሳችንን እንስከምንሰጥበት ቅጽበት ድረስ ሐጢያቶችን
ስለምንሰራ በእግዚአብሄር ላይ ምን ያህል ሐጢያቶችን እንሰራለን? ሐጢያት
የምንሰራው ጥቂት ጊዜ ብቻ አይደለም፡፡ እስከ ዕለተ ሞታችን ድረስ በርካታ
ሐጢያቶችን እንሰራለን፡፡ በሕይወት ዘመናችን ሁሉ ሐጢያትን ስለምንሰራ ጌታ
ከሐጢያቶቻችን ሁሉና ከኩነኔያችን ሁሉ አድኖናል፡፡ የእግዚአብሄር ታላቁ ጸጋ ሌላ
ሳይሆን ይህ ነው፡፡ ይህ እግዚአብሄር ለእኛ የሰጠን የተትረፈረፈ ጸጋ ነው፡፡
እናንተስ ታዲያ? በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን የሐጢያቶቻችሁን
ስርየት ተቀበላችኋልን? በእርግጥ ሁላችንም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን
ጸድቃን ከሆንን ከድክመቶቻችንና ከጉድለቶቻችን የተነሳ ሐጢያት ብንሰራ እንደገና
ሐጢያተኞች መሆን የሚቻል ነውን? የለም ይህ የሚቻል አይደለም! በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል በማመን የሐጢያቶችን ስርየት ብንቀበልም ስጋችን አሁንም
በእንከን የተሞላ ስለሆነ ሐጢያት በመስራት መቀጠላችን የማይቀር ነው፡፡ ሆኖም
በእግዚአብሄር ወይም በሰው ላይ ሐጢያት በምንሰራበት ጊዜ ሁሉ እንደገና
ሐጢያተኞች ከሆንን ይህ ማለት እግዚአብሄር የሰጠን የሐጢያቶች ስርየት እንከን
ያለበት ነገር ነው ማለት ነው፡፡ ነገር ግን እግዚአብሄር አብና ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ
ሐጢያቶቻችንን በሙሉ በመደምሰስ የፈጸሙት ደህንነት በጭራሽ እንከን ያለበት
አይደለም፡፡
የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል እግዚአብሄር ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ፈጽሞ
ያስወገደበት መንገድ ነው፡፡ በሌላ አነጋገር እግዚአብሄር ሐጢያቶችንን በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል ለመደምሰስ ምንም አልጎደለውም፡፡ ይህ ሆኖ ሳለ እግዚአብሄር

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


እንደ እግዚአብሄር ጸጋ ባለጠግነት መጠን ቤዛነትን አግኝተናል 99

የደህንነት ጸጋውን እንዲለግሳችሁ ለመርዳት ልታደርጉ የሚገባችሁ አንዳች ነገር


ያለ የመስላችኋልን? ጉዳዩ ይህ አይደለም፡፡ ምንም ያህል ጉድለቶች ቢኖሩብንና
ከአሁን ጀመሮም ምንም ያህል ሐጢያቶችን ብንሰራ እግዚአብሄር ያለፉትን፣ አሁን
ያሉትንና የወደፊት ሐጢያቶችን በሙሉ ስለደመሰሰ የዚህ ደህንነት ውጤማታነት
ፍጹምና ለዘላላለም የሚዘልቅ ነው፡፡ እኛ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ስለምናምን
ምንም ያህል ሐጢያቶችን ብንሰራም በውስጣችን የሚቀር አንዳች ሐጢያት ሊኖር
አይችልም፡፡ ምክንያቱም ከእግዚአብሄር የተሰጠን ደህንነት ሙሉ በሙሉ እንከን
የለሽ ነው፡፡ የእግዚአብሄር የደህንነት ሐይል ወሰን የለሽና ፍጹም ስለሆነ በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል ላይ ያለን እምነታችን ሁላችንንም ፈጽሞ ለማዳን የሚጎድለው
ምንም ነገር አይኖረውም፡፡ እግዚአብሄር በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት
የሰጠን ደህንነት በጣም የተትረረፈረፈ ስለሆነ ወሰን የለውም፡፡ ጌታችን በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት አትረፍርፎ እንዳዳነን ከልባችን የምናውቅና
የምናምን ከሆነ ደህንነታችን ላይ ለመድረስ የራሳችንን አንዳች ሥራ መጨመር
እንደሚገባን መገመታችን ከራሳችን አስተሳሰቦች የፈለቀ ነገር እንጂ ሌላ ምንም
አይደለም፡፡ ምክንያቱም የእግዚአብሄር ጸጋ ትንሽ አይደለምና፡፡ ጌታ የሰጠን
ደህንነት በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የመጣ ዘላለማዊ እውነት ነው፡፡
እግዚአብሄር እኛን ከዓለም ሐጢያቶች ሁሉ ሊታደገን አስገራሚ በሆነው
የውሃውና የመንፈሱን ወንጌል አማካይነት በበቂ ሁኔታ አዳነን፡፡ ወላዋይ ፍጡራን
ከሆኑት በተቃራኒ ሁሉን አዋቂውና ሁሉን ቻዩ አምላክ ለዘላለም የማይለወጥ
ነው፡፡ ስለዚህ መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል፡-
‹‹ሐሰትን ይናገር ዘንድ እግዚአብሄር ሰው አይደለም፤ ይጸጸትም ዘንድ የሰው
ልጅ አይደለም፡፡ እርሱ ያለውን አያደርገውምን? የተናገረውንስ አይፈጽመውምን?››
(ዘሁልቁ 23፡19)
እግዚአብሄር ሁሉን የፈጠረ ፈጣሪ፣ የፍርድ አምላክና ፍጹም የሆነውን
ፍቅሩን ለእኛ የጠ አዳኝ ነው፡፡ ይህ አምላክ የሰጠንን ፍጹም የሆነ ደህንነት
በራሳችሁ ሰብዓዊ አስተሳሰቦች እንዳትበርዙት እጠይቃችኋለሁ፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ በዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ላይ እንዲህ አለ፡-
‹‹በውድ ልጁም እንደ ጸጋው ባለጥነት መጠን በደሙ የተደረገ ቤዛነታችንን አገኘን፤
እርሱም የበደላችን ስርየት፡፡›› (ኤፌሶን 1፡7) እኛም ደግሞ እንደ ጌታ ጸጋ
ባለጠግነት የሐጢያቶችን ስርየት ተቀብለናል፡፡ ጌታ በዮርዳኖስ ወንዝ በመጠመቅ
ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ስለተሸከመ የተትረፈረፈ የሐጢያቶች ስርየት
ተቀብለናል፡፡ ጌታ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ስለተሸከመና የእነዚህንም ሐጢያቶች

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


100 እንደ እግዚአብሄር ጸጋ ባለጠግነት መጠን ቤዛነትን አግኝተናል

ዋጋ በመስቀል ላይ ስለከፈለ ፈጽሞ አድኖናል፡፡ ሙሉ የሆነውን የሐጢያቶች


ስርየት የተቀበልነው እንደዚህ ነው፡፡
ስለ ሐጢያቶች ስርየት ሰምታችሁ አታውቁምን? ሐዋርያው ጴጥሮስ በበዓለ
ሃምሳ ቀን ስበከቱን ካቀረበ በኋላ ለአድማጮቹ እንዲህ አለ፡- ‹‹ንስሐ ግቡ፤
ሐጢአታችሁም ይሰረይ ዘንድ እያንዳንዳችሁ በኢየሱስ ስም ተጠመቁ፤ የመንፈስ
ቅዱስንም ስጦታ ትቀበላላችሁ፡፡›› (የሐዋርያት ሥራ 2፡38) ኢየሱስ ክርስቶስም
ራሱ በመጨረሻው እራት ወቅት እንዲህ አለ፡- ‹‹ስለ ብዙዎች ለሐጢአት ይቅርታ
የሚፈስስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው፡፡›› (ማቴዎስ 26፡28)
ነገር ግን አንዳንድ ሰዎች ይህ የሐጢያቶች ስርየት በተጨባጭ ምን ማለት
እንደሆነ ስለማያውቁ እነዚህ ቃሎች በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የት ቦታ እንደሚገኙ
ይጠይቃሉ፡፡ እነርሱ ‹‹የሐጢያቶች ይቅርታ›› የሚለው ቃል በመጽሐፍ ቅዱስ
ውስጥ ቢገኝም ‹‹የሐጢያቶች ስርየት›› የሚሉት ቃሎች ግን አይታዩም ይላሉ፡፡
በተጨባጭ ግን ‹‹የሐጢያቶች ስርየት›› የሚለው ሐረግ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ
ብዙ ጊዜ ተጽፎዋል፡፡ (ማርቆስ 1፡4፤ ሉቃስ 1፡77፤ 3፡3፤ 24፡47፤ የሐዋርያት ሥራ
10፡43፤ ዕብራውያን 10፡18)
ጌታችን የሐጢያቶችን ስርየት ለሰው ሁሉ ለመስጠት አስፈላጊ የሆነውን ነገር
ሁሉ አድርጓል፡፡ እርሱ የተጠመቀው፣ ተሰቅሎ የሞተው፣ በሦስት ቀናቶች
የተነሳውና አሁን የሚመጣ አዳኛችን ሆኖ በእግዚአብሄር አብ ቀኝ የተቀመጠው
እኛን ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ሊታደገንና ሊቤዠን ነበር፡፡
የሐጢያቶቻችንን ስርየት የተቀበልነው በምን መንገድ ነው? ይህንን
የሐጢያቶች ስርየት በትክክል የተቀበላችሁት እንዴት ነው? ለኢየሱስ ክርስቶስ
ጥምቀትና ለደሙ፣ ለታላቁ የእግዚአብሄር ፍቅርና በክርስቶስ አማካይነት
ለተገለጠወ የትተረፈረፈ ጸጋው ምስጋና ይግባውና እኛ በዚህ እውነት በማመን
የሐጢያቶቻችንን ስርየት ተቀብለናል፡፡
ወደፊት እንደገና ሐጢያት ስንሰራ ይህ ማለት እንደና በመጨረሻ ወደ ሲዖል
የምንጣል ሐጢያተኞች እንሆናለን ማለት ነውን? አይደለም፤ ነገሩ እንደዚያ
አይደለም፡፡ ሰው ወደ ሰዖል የሚጣልበት አንድ ምክንያት ብቻ አለ፡፤ ይህ የሆነበት
ምክንያት ሰዎች እግዚአብሄርን ‹‹ጌታ ሆይ ሐጢያቶቼን በሙሉ መደምሰስ
ተስኖሃል፤ እኔ አሁንም ሐጢያተኛ ነኝ›› ስለሚሉት ነው፡፡ እነዚህ ሰዎች
እግዚአብሄር በአንድ ወይም በሌላ መንገድ ሐጢያቶቻችንን በአንድ ጊዜ ማስወገድ
ያቃተው ይመስል የግል ሐጢያቶቻቸውን እንዲደመስስላቸው በየጊዜው ወደ
እግዚአብሄር ይጸልያሉ፡፡ በተሳሳተው እምነታቸው ምከንያት ወደ ሲዖል

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


እንደ እግዚአብሄር ጸጋ ባለጠግነት መጠን ቤዛነትን አግኝተናል 101

የሚጣሉት እነዚህ ሰዎች ናቸው፡፡


አጋር ምዕመናኖቼ እግዚአብሄር ሙሉ በሙሉና በተትረፈረፈ መልኩ
ከሐጢያቶቻችን ሁሉ አድኖናል፡፡ ስለዚህ በኢየሱስ ክርስቶስ የውሃና የመንፈስ
ወንጌል ያመነ ሁሉ በእርግጠኝነት ሰማይ ይገባል፡፡ ታዲያ የእግዚአብሄርን ጸጋ
ባለጠግነት መረዳት የምንችለው የት ነው? እግዚአብሄር ራሱ እኛን ለማዳን የሰው
ስጋ ለብሶ ወደዚህ ምድር በመጣበት፣ በአጥማቂው ዮሐንስ በተጠመቀበት፣
በመስቀል ላይ በሞተበትና ከሙታን በተነሳበት እውነት ውስጥ የእግዚአብሄርን
የተትረፈረፈ ጸጋ መረዳት እንችላለን፡፡ እኛን የተዋረድነውን ፍጡራኖች ከሐጢያት
ለማዳን እግዚአብሄር ራሱ የሰውን ስጋ ለብሶ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ወደዚህ
ምድር መጣ፡፡ የሰማይና የምድር ግዛቶች ሁሉ ፈጣሪ የሆነው አምላካችን ኢየሱስ
ክርስቶስ የክብር ዙፋኑንና የመለኮት ሥልጣኑን ትቶ እንደ እኛ ዓይነት ሰው ሆኖ
ወደዚህ ምድር ለመምጣት ራሱን ማዋረዱ የጸጋው ባለጠግነት ነው፡፡ እግዚአብሄር
ራሱ ወደዚህ ምድር ከመጣ በኋላ የእኛን ድክመቶች በሙሉ ተለማመደ፡፡ ለእኛ
ካለው ምህረት የተነሳም በአጥማቂው ዮሐኝስ አማካይነት ሐጢያቶቻችንን በሙሉ
ተሸከመ፡፡ የጸጋው ባለጠግነት ሌላ ሳይሆን ይህ ነው፡፡ እነዚህን የእግዚአብሄር ጸጋ
ባለጠግነቶች በዮርዳኖስ ወንዝ፣ በመስቀል ላይና በራሱ በኢየሱስ ክርስቶስ
ውልደት ውስጥ ማየት እንችላለን፡፡

‹‹በደሙ የተደረገ ቤዛነታችንን አገኘን፤ እርሱም የበደላችን ስርየት፡፡››


(ኤፌሶን 1፡7)

የሐጢያቶችን ስርየት መቀበል ማለት ምን ማለት ነው? ሰው ከሐጢያቶቹ


ሁሉ ይነጻል፤ በዚህ ዓለም ላይ የተሰራው እያንዳንዱ ሐጢያትም ይደመሰሳል
ማለት አይደለምን? የሐጢያቶችን ስርየት መቀበል ማለት በትክክል ያንን ማለት
ነው፡፡
ከሐጢያቶቻችሁ ሁሉ ከነጻችሁ ጻድቅ ሰው ናችሁ ወይስ ሐጢያተኛ? ጻድቅ
ሰው ናችሁ፡፡ በዚህ እውነት የሚያምኑ ሰዎች በመሆናችን አንዳች የቀረ ሐጢያት
አለብን? የለም ምንም ሐጢያት የለብንም፡፡ ለምን ሐጢያት የለብንም? ሐጢያት
የሌለብን በኢየሱስ ጥምቀትና በመስቀል ላይ ደሙ ስለምናምን ነው፡፡ ለውሃውና
ለኢየሱስ ደም ምስጋና ይሁንለትና እኛ ሙሉ በሙሉ ሐጢያት አልባ የሆንን
የእግዚአብሄር ሰዎች ሆነናል፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


102 እንደ እግዚአብሄር ጸጋ ባለጠግነት መጠን ቤዛነትን አግኝተናል

ነገር ግን በርካታ ክርስቲያኖች በኢየሱስ ቢያምኑም አሁንም ሐጢያተኞች


እንደሆኑ በመናገር ለሐጢያቶቻቸው በዕንባ ታጅበው የንስሐ ጸሎቶቻቸውን
በየቀኑ ማቅረብ እንዳለባቸው ይናገራሉ፡፡ እናንተም ደግሞ ልክ እንደ እነዚህ
የተሳሳቱ ክርስቲያኖች ሰማይ መግባት የምትችሉት በየቀኑ የንስሐ ጸሎቶቻችሁን
በዕንባ በማቅረብ ይመስላችኋል? እግዚአብሄር በሕይወት ዘመናችሁ ሁሉ በየቀኑ
እንዲህ ዕንባችሁን ስታፈሱ በማየት የሚደሰት ይመስላችኋልን? አይደለም፤ ይህ
ከተሳሳቱ የሰው አስተሳሰቦች የሚመነጭ ሰው ሰራሽ እሳቤ ነው፡፡ ነገር ግን በጣም
ብዙ ክርስቲያኖች የተትረፈረፈውን የእግዚአብሄርን ወንጌል እውነት ስለማያውቁና
በቃሉ መሠረትም ለመኖር በጣም ብዙ ጉድለቶች ስላሉባቸው የተሳሳተውን
ባህሪያቸውን ለማስተካከል በዕንባ የታጀቡ የንስሐ ጸሎቶችን ማቅረብ
እንደሚኖርባቸው ይናገራሉ፡፡ ነገር ግን አጋር ምዕመናኖቼ በጉድለቶች የተሞላን
ብንሆንም ጌታችን ሙሉ በሙሉ ፍጹምና እንከን የለሽ ነው፡፡ ጉድለት ቢኖርብም
ጌታችን ከሐጢያቶቻችን ፈጽሞ አድኖናል፡፡
ዛሬ እያንዳንዱ ክርስቲያን ኢየሱስን አዳኙ አድርጎ ቢናገርም ብዙ
ቤተክርስቲያኖች ተራ ወደሆኑ ማህበራዊ ስብሰባዎች ወይም ኮርፖሬሽኖች
እየዘቀጡ ነው፡፡ ቤተክርስቲያን በባንክ ብድር ግዙፍና የተቀናጣ የቤተክርስቲያን
ሕንጻ ስትገነባ ሰዎች ወደዚህች ቤተክርስቲያን የሚጎርፉት ሕንጻው ያማረ መሆን
በማየታቸው ነው፡፡ እግዚአብሄር በቁሳዊ በረከት እንዲባርካቸው በመለመንም
አስራቶችንና ብዙ ሌሎች መባዎችን ይሰጣሉ፡፡ እንዲህ ካለው ግዙፍ
ቤተክርስቲያን ጋር ያላቸውን በርካታ ቁርኝቶች የሚጠቀሙት የራሳቸውን ራስ
ወዳዳዊ ፍላጎቶች ለማሳካት ነው፡፡ ስለዚህ ብዙ የንግድ ሰዎች በእነዚህ ግዙፍ
ቤተክርስቲያኖች ውስጥ የሚገኙት ለራሳቸው ተጨማሪ የሥራ ዕድሎችን
ለማግኘት ነው፡፡ ተጨማሪ ዕቃዎችን ለመሸጥ እንዲረዳቸውም ወደ እግዚአብሄር
ይጸልያሉ፡፡ ይህ እንዴት ትክክለኛ እምነት ሊሆን ይችላል? የዚህ ዓይነቱ እምነት
ፈጽሞ የማይረባ ነው፡፡

‹‹ጸጋውንም በጥበብና በአእምሮ ሁሉ አበዛልን፡፡›› (ኤፌሶን 1፡8)

ጌታችን በጥበብ በአእምሮ ሁሉ እንድንሞላ አድርጎናል፡፡ በእርግጥ


የሐጢያቶቻችሁን ስርየት መቀበል የምትፈልጉ ከሆነ ማድረግ የሚኖርባችሁ ነገር
ጌታ ለእናንተ ያደረገውን ብቻ ማመን ነው፡፡ እውነተኛውን የሐጢያቶች ስርየት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


እንደ እግዚአብሄር ጸጋ ባለጠግነት መጠን ቤዛነትን አግኝተናል 103

መቀበል የምትችሉት በጌታ የደህንነት ሥራ ስታምኑ ነው፡፡ ታዲያ ደህንነታችሁን


ለማግኘት በትክክል በጌታ ሥራ ማመን የሚገባችሁ እንዴት ነው? ሐጢያቶቻችሁ
በሙሉ በጥምቀቱ አማካይነት ወደ ጌታ እንደተላለፉ፣ እነርሱን ተሸክሞ በእናንተ
ፋንታ በመስቀል ላይ እንደሞተና በሦስት ቀናቶችም ከሙታን እንደተነሳ ማመን
አለባችሁ፡፡ ያን ጊዜ የሐጢያቶቻችሁን ስርየት መቀበል ትችላላችሁ፡፡
ሐጢያቶቻችሁ በሙሉ ወደ ኢየሱስ እንደተላለፉ ስትገነዘቡና ስታምኑ በዚህ
እምነት መሠረት ሐጢያቶቻችሁ በሙሉ ይነጻሉ፡፡ በእርግጥ የሐጢያቶችን ስርየት
መቀበል የምትፈልጉ ከሆነ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ከማመን በቀር ሌላ
ምርጫ የላችሁም፡፡
እዚህ ላይ ‹‹ጥበብ›› ሲባል ይህንን ማለት ነው፤ የሐጢያቶችን ስርየት
ለመቀበል ሐጢያቶቻችሁ በሙሉ ወደ ኢየሱስ መተላለፍ አለባቸው፤
ሐጢያቶቻችሁ ወደ ጌታ እስካልተላለፉ ድረስ እምነታችሁ ምንም ያህል ጠንካራ
ቢሆንም በኢየሱስ ማመን ፈጽሞ ከንቱ ነው፡፡ ‹‹ኢየሱስ አዳኜ ነው፤ እኔም
ሐጢያተኛ ነኝ፤ ኢየሱስ በመስቀል ላይ የሞተው ለእኔ ካለው ፍቅር የተነሳ ነው፡፡
እንዲህ አድርጎ አድኖኛል›› በማለት እንደፈለጋችሁ በኢየሱስ ልታምኑ
ትችላላችሁ፡፡ ነገር ግን ይህ እወነተኛውን የሐጢያቶች ስርየት ደህንነት
አያመጣላችሁም፡፡
የሐጢያቶቻችሁን ስርየት በትክክል ትቀበሉ ዘንድ ሐጢያቶቻችሁ በሙሉ
በጥምቀቱ አማካይነት ወደ ኢየሱስ መተላለፍ አለባቸው፡፡ ኢየሱስ ለእናንተ ደሙን
በማፍሰስ በመስቀል ላይ የተሸከመውንም ኩነኔ ማመን አለባችሁ፡፡ በመጨረሻ
በእርግጠኝነት ሐጢያት እንደሌላባችሁ መናገር የምትችሉት በዚህ ሁኔታ በውሃና
በመንፈስ ወንጌል እውነተኛ የሐጢያቶችን ስርየት ስትቀበሉ ብቻ ነው፡፡ ጌታችን
ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ለመደምሰስ መምጣቱ፣ ሁሉንም ለመሸከም መጠመቁና
በእኘ ፋንታም ተሰቅሎ መሞቱ እግዚአብሄር እኛን ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ያዳነበት
ጥበብ ነው፡፡ ‹‹በውድ ልጁም እንደ ጸጋው ባለጠግነት መጠን በደሙ የተደረገ
ቤዛነታችንን አገኘን፤ እርሱም የበደላችን ስርየት፡፡ ጸጋውንም በጥበብና በአእምሮ
ሁሉ አበዛልን፡፡ በክርስቶስ ለማድረግ እንደወደደ እንደ አሳቡ የፈቃዱን ምስጢር
አስታውቆናልና፤›› (ኤፌሶን 1፡7-9) ተብሎ እንደተጻፈው ይህ የእግዚአብሄር
እውነትና ጥበብ ነው፡፡
አምላካችን እውነተኛ ጥበቡንና ብልሃቱን አስታውቆናል፡፡ ይህ ማለት
የደህንነትን እውነት የሰጠንና ለሁላችንም ያስታወቀን እግዚአብሄር ራሱ ነው ማለት
ነው፡፡ አጋር ምዕመናኖቼ ዛሬ እናንተና እኔ ደህንነታችን ላይ የደረስነው ጌታ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


104 እንደ እግዚአብሄር ጸጋ ባለጠግነት መጠን ቤዛነትን አግኝተናል

ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ያዳነንን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል እውነት


ስላስታወቀን ነው፡፡ እግዚአብሄር በጥበቡና በብልሃቱ ፈጽሞ አድኖናል፡፡ ይህንንም
ምስጢር በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት አስታውቆናል፡፡
ታዲያ በዚህ የውሃና የመንፈስ ወንጌል ታምናላችሁን? የእግዚአብሄር ጸጋ
ብዙ እንደሆነና ሐጢያቶቻችንን ፈጽሞና ሙሉ በሙሉ እንዳስወገደ ታምናላችሁን?
ፈቃዱ የሆነውን ይህንን የወንጌል ምስጢር ያስታወቀን እግዚአብሄር ነው፡፡ እርሱ
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል አስታውቆናል፡፡ ይህ የወንጌል ምስጢር ጌታችን
በዮርዳኖስ ወንዝ ውስጥ የመጠመቁና በመስቀል ላይ የመሞቱ እውነታ ነው፡፡
በመላው ዓለም የሚገኘውን መላውን የሰው ዘር ያዳነው ምስጢር የኢየሱስ
ጥምቀትና የመስቀል ላይ ሞቱ ነው፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስ በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅና በመስቀል ላይ በመሞት
የሰውን ዘር ሐጢያቶች ሁሉ ስርየት እንደሚፈጽም ዲያብሎስም እንኳን
አላወቀም፡፡ ይህንን ባለማወቁ ዲያብሎስ ይህንን ዓለምና በመላው ዩኒቨርስ ውስጥ
ያሉትን ባለጠግነቶች በሙሉ የሚወርሰውን ወራሽ የእግዚአብሄርን ልጅ ቢገድል
ኢየሱስን ማሸነፍ እንደሚችል አሰበ፡፡ ሰዎች ኢየሱስን ሰቅለው እንዲገድሉት
ጠምዝዞ ያሳመናቸው ለዚህ ነው፡፡
ሆኖም ከኢየሱስ ሞት በኋላ ዲያብሎስ ‹‹ትልቅ ስህተት ሰራሁ! የእግዚአብሄር
ልጅ ስለተጠመቀ በዚህ ሁኔታ በመስቀል ላይ መሞቱ የሚያሳየው አሁን የዓለም
ሐጢያቶች በሙሉ መወገዳቸውን ነው፡፡ በፍጹም እንዲሞት ማድረግ
አልነበረብኝም! አሁን እንዲሞት በማድረጌ በእኔ እጅ ውስጥ ያሉትን ሰዎች
ከእንግዲህ ወዲህ ልቆጣጠራቸው አልችልም፡፡ በሐጢያት አጥምጄያቸዋለሁ፤ ነገር
ግን ከእንግዲህ ወዲህ በእነርሱ ላይ መንጠልጠል አልችልም፡፡ ከእንግዲህ ወዲያ
ባርያ ላደርጋቸው አልችልም፡፡ ሁሉም ነጻ ወጥተዋል›› የሚል ግንዛቤ ላይ ደረሰ፡፡
ስለዚህ የእርሱ ልጅ በሰው አምሳል ወደዚህ ምድር መምጣቱ፣ በዮርዳኖስ ወንዝ
ተጠምቆም ሐጢያቶቻችንን በሙሉ መሸከሙና በእኛ ፋንታ በመስቀል ላይ መሞቱ
የእግዚአብሄር የደህንነት ምስጢር እንደነበር ዲያብሎስ አላወቀም፡፡
ታዲያ ይህንን ያወቁት እነማን ናቸው? እግዚአብሄር አብ፣ ወልድና መንፈስ
ቅዱስ ብቻ ነበሩ፡፡ ዛሬም ይህ የታወቀው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
ለሚያምኑት ብቻ ነው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


እንደ እግዚአብሄር ጸጋ ባለጠግነት መጠን ቤዛነትን አግኝተናል 105

‹‹የፈቃዱን ምስጢር አስታወቆናልና፡፡›› (ኤፌሶን 1፡9)

በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምኑ ሰዎች የደህንነት ምስክርነታቸውን


በሚሰጡበት ጊዜ ሁሉ ሁሌም ኢየሱስ በዮርዳኖስ ወንዝ የመጠመቁን ታሪክ
ይናገራሉ፡፡ ጌታ በዮርዳኖስ ወንዝ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ መሸከሙ የጥምቀቱ
ምስጢር ነው፡፡ ብዙ ሰዎች በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ቢያዩትና ይህ ቢነገራቸውም
እንኳን ኢየሱስ በጥምቀቱ አማካይነት ሐጢያቶቻቸውን እንደወሰደ አያውቁም፡፡
ይህ በጥንቱ የቅዱሳት መጽሐፍ ጽሁፍ ውስጥ ቢጻፍና በጣም ቀላል የሆነ የደህንነት
እውነት ቢሆንም ሰዎች ግን አሁንም አልተረዱትም፡፡
ኢየሱስ ራሱ እንዲህ አለ፡- ‹‹አሁንስ ፍቀደልኝ፤ እንዲህ ጽድቅን ሁሉ
መፈጸም ይገባናልና፡፡›› (ማቴዎስ 3፡15) ጌታችን ሐጢያቶቻችንን ለመደምሰስ
ወደዚህ ምድር መምጣትና በመጠመቅም የእያንዳንዱን ሰው ሐጢያቶች በሙሉ
መቀበል ነበረበት፡፡ ይህ ጥምቀት እኛን ያዳነበት የእግዚአብሄር ጥበብና ብልሃቱ
ነበር፡፡ ይህ ዲያብሎስ እንኳን የማያውቀው የእርሱ ታላቅ ምስጢር ነበር፡፡ ይህንን
ያውቁ የነበሩት እግዚአብሄር አብ፣ ወልድና መንፈስ ቅዱስ ብቻ ናቸው፡፡
እግዚአብሄር አብ ደህንነታችንን እንዳቀደና በልጁ አማካይነትም እንደፈጸመ
መንፈስ ቅዱስም ደግሞ በእውነት ቃል አማካይነት ይህንን ስላስታወቀን
የእግዚአብሄርን ፈቃድ ሙሉ በሙሉ መረዳትና እውነተኛውን ደህንነታችንን
መቀበል ችለናል፡፡ በሌላ አነጋገር እናንተና እኔ ዛሬ የወንጌልን እውነት የተረዳነው
እግዚአብሄር ጥበቡንና ብልሃቱን ስለለገሰን ነው፡፡ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
በመረዳትና በማመን የሐጢያቶችን ስርየት የተቀበልነው ለዚህ ነው፡፡
የእግዚአብሄርን ቃል በምናነብበት ወይም በምናዳምጥብት ጊዜ ሁሉ መንፈስ
ቅዱስ የቃሉን ትርጉም ያስተምረናል፡፡ ማስተዋልንም ይሰጠናል፡፡ ‹‹በክርስቶስ
ለማድረግ እንደወደደ እንደ አሳቡ የፈቃዱን ምስጢር አስታውቆናልና፤ በዘመን
ፍጻሜ ይደረግ ዘንድ ያለው አሳቡም በሰማይና በምድር ያለውን ሁሉ በክርስቶስ
ለመጠቅለል ነው›› (ኤፌሶን 1፡9-10) ተብሎ እንደተጻፈ ምስጋና ለዚህ አስተውሎት
ይሁንና የሐጢያቶቻችንን ስርየት ተቀብለናል፡፡ በሌላ አነጋገር ደህንነታችን ያለው
በእግዚአብሄር ችሮታ ውስጥ ነው፡፡
በዚህ ዓለም ላይ የሚኖሩ ሰዎች ደስተኞችና ከችግር ነጻ በሚሆኑበት ጊዜ
በኢየሱስ ክርስቶስ የማመኑ አስፈላጊነት አይታያቸውም፡፡ በዚህ ምክንያት
የእግዚአብሄር ልጆች መሆን አልቻሉም፡፡ በዚህ ዓለም ላይ ብዙ ስቃይና ሐዘን
እንዲገጥማቸው የፈቀደው ለዚህ ነው፡፡ በሌላ አነጋገር በልጁ በማመን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


106 እንደ እግዚአብሄር ጸጋ ባለጠግነት መጠን ቤዛነትን አግኝተናል

የሐጢያቶችን ስርየት እንቀበል ዘንድ እነዚህን መከራዎች መገፈጣችን


በእግዚአብሄር የደህንነት ችሮታ ውስጥ ያለ ነው፡፡ እግዚአብሄር በዚህ ዓለም ላይ
መከራንና ሐዘንን የፈቀደው ‹‹በሰማይና በምድር ያለውን ሁሉ በክርስቶስ
ለመጠቅለል ነው፡፡›› (ኤፌሶን 1፡10)
በዚህ ምድር ላይ አንዲትም የሰላም ቀን የለችም፡፡ በዚህ ዓለም ላይ ስንኖር
ሁሉም ዓይነት መከራና ችግር ይገጥመናል፡፡ እዚህ ላይ በመንገዳችን ላይ
የሚገጥሙን የዚህም ምድር መከራዎችና ችግሮች እንደዚሁም የሚጎበኙን ሐዘኖች
የእግዚአብሄር ልጆች የሚያደርጉንና ይህም የእግዚአብሄር ችሮታ መሆኑን
ሁለችንም መገንዘብ አለብን፡፡ ብዙውን ጊዜ ስለ መከራዎቻችን እግዚአብሄርን
እንወቅሳለን፡፡ ራሳችን ግራ ተጋብተንም ‹‹እነዚህ ነገሮች የሚገጥሙኝ ለምንድነው?
እንዲህ ባሉ መከራዎች ውስጥ የማልፈው ለምንድነው?›› እያልን
እናጉረመርማለን፡፡ ነገር ግን እግዚአብሄርን እንዲህ ከመውቀስ ይልቅ እኛን
በእነዚህ መከራዎች አማካይነት ማዳኑ የእግዚአብሄር ችሮታ መሆኑን መገንዘብ
ይገባናል፡፡

ልቦቻችንን እግዚአብሄር ከሰጠን የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ጋር


ማቆራኘት አለብን፡፡

ወደ ኤፌሶን 1፡11-14 እንመለስ፡- ‹‹እንደ ፈቃዱ ምክር ሁሉን የሚሠራ እንደ


እርሱ አሳብ አስቀድመን የተወሰንን በክርስቶስ ደግሞ ርስትን ተቀበልን፡፡ ይኸውም
በክርስቶስ አስቀድመን ተስፋ ያደረግን እኛ ለክብሩ ምስጋና እንሆን ዘንድ ነው፡፡
እናንተም ደግሞ የእውነትን ቃል ይኸውም የመዳናችሁን ወንጌል ሰምታችሁ
ደግሞም በክርስቶስ አምናችሁ በተስፋው መንፈስ በመንፈስ ቅዱስ ታተማችሁ፡፡
እርሱም የርስታችን መያዣ ነው፤ ለእግዚአብሄር ያለውን እስኪዋጅ ድረስ ይህም
ለክብሩ ምስጋና ይሆናል፡፡››
እዚህ ላይ ‹‹እንደ ፈቃዱ ምክር ሁሉን የሚሠራ እንደ እርሱ አሳብ
አስቀድመን እንደተወሰንን›› ተጽፎዋል፡፡ ይህ የሚያሳየው እግዚአብሄር ሁሉን ነገር
ያደረገው እንደ ልቡ ምኞት መሆኑን ነው፡፡ እኛ በኢየሱስ ክርስቶስ የዳንነውና
የእርሱ ልጆች የተደረግነው በፈቃዱ መሠረት፣ በዕቅዱ ዓላማ መሠረትና በቅድመ
ውሳኔው መሠረት በእግዚአብሄር በማመን ነው፡፡ ሁሉም ነገር የሚፈጸመው
በእግዚአብሄር ፈቃድ ምክርና በእርሱ ቅድመ ውሳኔ መሰረት ነው፡፡ እዚህ ላይ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


እንደ እግዚአብሄር ጸጋ ባለጠግነት መጠን ቤዛነትን አግኝተናል 107

ይህንን በግልጥ መረዳታችን በእጅጉ ያስፈልገናል፡፡


በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የማያምኑ ብዙ የተሳሳቱ ክርስቲያኖች ‹‹እኛ
ሁላችንም ኢየሱስ ክርስቶስን አዳኛችን አድርገን እናምናለን፡፡ ታዲያ በእርሱ
ጥምቀት ማመን ፈጽሞ አስፈላጊያችን የሆነው ለምንድነው? ሁሉም ሰው ኢየሱስን
አዳኙ አድርጎ በማመን ብቻ አይድንምን?›› ይላሉ፡፡ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
ለእነዚህ ሰዎች በምንሰብክበትና የሐጢያቶችን ስርየት መቀበልና የእግዚአብሄር
ልጆች መሆን የሚችሉት በዚህ ወንጌል በማመን ብቻ እንደሆነ ስናብራራላቸው
በቃሉ መሠረት በማመን ፋንታ ብዙዎቹ እንዲህ ብለው ይጠይቁናል፡፡
እግዚአብሄር ለእኛ ያደረገውን ተጠራጠርንም አልተጠራጠርንም
እግዚአብሄር ሁሉን እንደ ምኞቱ የማቀዱንና የመፈጸሙን እውነታ
አይለውጠውም፡፡ እግዚአብሄር በክርስቶስ የሐጢያቶቻችንን ስርየት እንድንቀበልና
የእርሱ ልጆች እንድንሆን ፈለገ፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስን ወደዚህ ምድር የላከው ለዚህ
ነው፡፡ እርሱ አስቀድሞ በወሰነው የደህንነት ዕቅድ መሰረት ሁላችንም ይህንን
የእግዚአብሄር ችሮታ በማመን የሐጢያቶችን ስርየት እንቀበል ዘንድ ልጁ
በዮርዳኖስ ወንዝ በመጠመቅ የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ እንዲቀበል
የእግዚአብሄር ፈቃድና ዕቅድ ነበር፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሄር ‹‹ዓለም ሳይፈጠር እንደመረጠን›› (ኤፌሶን 1፡4)
ይናገራል፡፡ ይህ የእግዚአብሄር ቅድመ ውሳኔ ነው፡፡ በሌላ አነጋገር እግዚአብሄር
ልጁን ወደዚህ ምድር በመላክ የሰውን ዘር ለማዳን አስቀድሞ የወሰነው ዓለም
ሳይፈጠር በፊት ነበር፡፡ እግዚአብሄር ሰዎች በዲያብሎስ ፈተና እንደሚወድቁና
ሐጢያት እንደሚሰሩ አስቀድሞ ስላወቀ ይህንን ዓለም ከመፍጠሩ በፊት
ደህንነታቸውን አቀደ፡፡ ኢየሱስን ወደዚህ ምድር መላኩና በዮርዳኖስ ወንዝ
በመጠመቅም የሰውን ዘር ሐጢያቶች በሙሉ እንዲቀበል ማድረጉም እንደዚሁ
በእግዚአብሄር ቅድመ ውሳኔ ውስጥ ያለ ነበር፡፡ እግዚአብሄር ይህንን አስቀድሞ
ወሰነ፡፡ እንደ ፈቃዱና እንደ ምኞቱም ደህንነታችንን ካቀደ በኋላ ያለ እንከን
ፈጸመልን፡፡ አጋር ምዕመናኖቼ ይህ ሰው ሰራሽ ታሪክ አይደለም፡፡
የቅዱሳን ልቦቻችን የሚበረቱት መቼ ነው? ልቦቻችን የሚበረቱት
በእግዚአብሄር ቃል ላይ ስንቆይና በዚህ ቃል ስንታመን ነው፡፡ ማናቸውንም ፈተና
ማሸነፍ የሚችሉት ያን ጊዜ ነው፡፡ በትግል ጊዜያችን በሌላ ሰው ቃሎች አንዳች
ብርታትና መጽናናት ማግኘት እንችላለን? የለም እንደማናገኝ የታወቀ ነው!
ነፍሳችንን፣ ልቦቻችንንና አካሎቻችንንም ሳይቀር የሚያበረታው የእግዚአብሄር ቃል
ብቻ ነው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


108 እንደ እግዚአብሄር ጸጋ ባለጠግነት መጠን ቤዛነትን አግኝተናል

‹‹እንደ ፈቃዱ ምክር ሁሉን የሚሠራ እንደ እርሱ አሳብ አስቀድመን


የተወሰንን በክርስቶስ ደግሞ ርስትን ተቀበልን፡፡›› (ኤፌሶን 1፡11)

የደህንነቱ ሥራ በሙሉ የተፈጸመው በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል


በእግዚአብሄር ዕቅድ መሠረት ነበር፡፡ ‹‹እንደ ፈቃዱ ምክር ሁሉን የሚሠራ››
(ኤፌሶን 1፡11) ማለትም እንደ እግዚአብሄር ፈቃድ ኢየሱስ ራሱ ሐጢያቶቻችንን
በሙሉ ለመሸከም በዮርዳኖስ ወንዝ ተጠመቀ፤ ደሙንም በመስቀል ላይ በማፍሰስ
የእነዚህን ሐጢያቶች ኩነኔ በሙሉ ተሸከመ፡፤ ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ያዳነበት
መንገድ ይህ በመሆኑ በዚህ የደህንነት መንገድ መሠረት በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን
የእግዚአብሄር ልጆች ሆነናል፡፡ እውነተኛ ደህንነት ማለትም ያ ነው፡፡ የእናንተና
የእኔ ሐጢያቶች በሙሉ በጥምቀቱ አማካይነት ወደ ኢየሱስ ተላልፈዋል፡፡
ክርስቶስም የሐጢያቶቻችንን ኩነኔ በሙሉ በመስቀል ላይ ተሸክሞዋል፡፡ ስለዚህ
በዚህ የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል በማመን የሐጢያቶችን ስርየት ተቀበለናል፡፡
ደህንነታችን አስቀድሞ የተወሰነው በራሱ በእግዚአብሄር ነበር፡፡
ሆኖም በዚህ ዘመንና ጊዜ የሚኖሩ ብዙ ክርስቲያኖች ‹‹እናንተ ተመጻዳቂ
ናችሁ፤ እናንተ እንደምታምኑት ሳያምኑ ዳግመኛ ያልተወለዱ ብዙ ሰዎች በዚህ
ዓለም ላይ አሉ›› ይሉናል፡፡ ነገር ግን እንደ እውነቱ ከሆነ ማንም ሰው በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል ሳያምን መቼም ቢሆን ሐጢያት አልባ አይሆንም፡፡ አንዳንድ
ሰዎች በድፍረት ለሌሎች ሰዎች ሐጢያት እንደሌለባቸው ቢነግሩዋቸውም ይህ
አሳሳች አባባል ልቦቻቸው በተጨባጭ ሐጢያት አልባ ሆነዋል ማለት አይደለም፡፡
እግዚአብሄር የሰዎችን ልብ እንደሚያይ ተናግሮዋል፡፡ ጌታ ሰው በእግዚአብሄር
እንደሚያምን ቢናገርም ልቡ በእግዚአብሄር ዘንድ ተቀባይነት ያለው የእውነተኛ
እምነት ማስረጃ እስከሌለው ድረስ በልቡ ውስጥ ያሉት ሐጢያቶች አሁንም
እዚያው እንዳሉ ተናግሮዋል፡፡ ማንም ሰው ልቡ አሁንም በሐጢያት የተሞላ
እንደሆነ እያወቀ ሐጢያት አልባ መሆኑን መናገሩ ማታለያ ነው፡፡ የዚህ ሰው ልብ
በሐጢያት የተሞላ ስለሆነ አሁንም ሐጢያተኛ ነው፡፡
ሰው በጭንቅላቱ ስለ እግዚአብሄር ቃል ሁሉንም ቢያምን፣ በሁለቱም
ኪዳኖች ምንም ያህል የተካነ ቢሆንና በዓለም የታወቀ የወንጌል ሰባኪ ሆኖ ቢከበር
ይህ ሰው በልቡ ውስጥ አንዳች ሐጢያት ካለበት ሐጢያተኛ ነው፡፡ እነዚህ ሰዎች
በአእምሮዋቸው ሐጢያት እንደሌለባቸው ያስቡ ይሆናል፤ ነገር ግን ልቦቻቸው
ሐጢያተኛ እስከሆኑ ድረስ ሁሉም ሐጢያተኞች ናቸው፡፡ በአንጻሩ እኛ በጭራሽ
ሐጢያት የለብንም፡፡ ይህ ማለት ግን አንዳች ክፉ አሳቦች የሉብንም ማለት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


እንደ እግዚአብሄር ጸጋ ባለጠግነት መጠን ቤዛነትን አግኝተናል 109

እንዳልሆነ የታወቀ ነው፡፡ ነገር ግን ይህ ማለት አሁንም የሐጢያት አሳቦችና


ምኞቶች ቢኖሩብንም ልቦቻችን ሐጢያት የለባቸውም ማለት ነው፡፡ እውነተኛ
የሐጢያቶች ስርየት የተቀበሉት ልቦቻቸው ሐጢያት አልባ የሆኑ እንደ እኛ ያሉ
ሰዎች ናቸው፡፡
እናንተስ ታዲያ? በልባችሁ ውስጥ ፈጽሞ ሐጢያት የለም? ልባችሁን እንደ
አመዳይ የሚያነጻውን የሐጢያቶች ስርየት ተቀብላችኋልን? ሁላችሁም አዎ
ብላችሁ መልሰችኋል፤ ነገር ግን ይህንን የሐጢያቶች ስርየት እንድትቀበሉ
ያስቻላችሁ ምንድነው? በእግዚአብሄር ፈቃድና በዕቅዱ መሠረት ኢየሱስ ክርስቶስ
ሐጢያቶቻችሁን ሁሉ ለመደምሰስ ለእናንተ ባደረገው የደህንነት ሥራ በማመን
የሐጢያቶችን ስርየት ተቀብላችኋል፡፡ ይህ የሐጢያቶች ስርየት የተገኘው ለእናንተ
ተስማሚ መስሎ በታያችሁ መንገድ በኢየሱስ በማመን አይደለም፡፡
በኤፌሶን 1፡11 ላይ እንዲህ ተጽፎዋል፡- ‹‹እንደ ፈቃዱ ምክር ሁሉን የሚሠራ
እንደ እርሱ አሳብ አስቀድመን የተወሰንን በክርስቶስ ደግሞ ርስትን ተቀበልን፡፡››
ደህንነታችንን ያገኘነው በእግዚአብሄር ነው፡፡ የሐጢያቶችን ስርየት የተቀበልነውም
እንደዚሁ በእግዚአብሄር ነው፡፡ የሐጢያቶችን ስርየት የተቀበልነው ፈጽሞ
በራሳችን መንገድ አይደለም፤ ነገር ግን በዚህ ዓለም ላይ ያሉ በርካታ ክርስቲያኖች
የሐጢያቶች ስርየት የሚገኘው የቤተክርስቲያን ድርጅቶቻቸው
በሚያስተምሩዋቸው ትምህርቶች በማመን ብቻ እንደሆነ ያስባሉ፤ ያምናሉ፡፡
የፕሪስባይቴርያን ቤተክርስቲያን ሁሉም ሰው በፕሪስባይቴርያን ትምህርቶች
መሠረት ማመን እንዳለበት ትናገራለች፡፡ የሜቶዲስት ቤተክርስቲያንም ሁሉም
ሰው የሜቶዲስትን ቤተክርስቲያን ትምህርቶች መከተል እንዳለበት
ታስተምራለች፡፡ የባፕቲስት ቤተክርስቲያንም ይህንኑ ትናገራለች፡፡ የሙሉ ወንጌል
ቤተክርስቲያንም እንደዚሁ ሁሉም ሰው በእርስዋ ትምህርቶች መሠረት ማመን
እንዳለበት ትናገራለች፡፡
እግዚአብሄር ግን እንዲህ ዓይነቱን እምነት ይደግፋልን? የፕሪስባይቴርያን
ቤተክርስቲያን፣ የሜቶዲስት ቤተክርስቲያን፣ የባፕቲስት ቤተክርስቲያን ወይም
የሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተጠቀሱት የት ቦታ ላይ
ነው? ክርስትናን በግል የትምህርት አቋሞቻቸው በተለያዩ የቤተክርስቲያን
ድርጅቶችና አንጃዎች መከፋፈሉ ጥቅም የለውም፡፡ እንዲያውም ይህ እምነት
የሐጢያቶችን ስርየት ለሁሉም ሰው ለመስጠት ከሚሻው የጌታ ፈቃድ ጋር ፈጽሞ
የሚቃረን ነው፡፡ የሐጢያቶቻችን ታዳጊ እግዚአብሄር አብ፣ ወልድና መንፈስ ቅዱስ
ብቻ ነው፡፡ መዳን የሚችሉትም በእነዚህ በሦስቱ የአምላክ ሕላዌዎች በታቀደውና

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


110 እንደ እግዚአብሄር ጸጋ ባለጠግነት መጠን ቤዛነትን አግኝተናል

በተፈጸመው የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል የሚያምኑ ሰዎች ብቻ ናቸው፡፡


በዘመኑ ክርስትና ውስጥ በድርጅታዊ መናቆር ሲናቆሩ የሚባትሉ እነማን
ናቸው? ሐዋርያው ጳውሎስ በአንጃ ውስጥ እንዳንሳተፍና እርስ በርሳችን
እንዳንናቆር ነግሮናል፡፡ (1ኛ ቆሮንቶስ 3፡3-5) ነገር ግን በራሳቸው መንገድ የሚሄዱ
ዓለማዊ ክርስቲያኖች ሁሌም በድርጅታዊና በአንጃ ጉዳዮች ይናቆራሉ፡፡
ከፕሪስባይቴርያን ቤተክርስቲያን እስከ ሜቶዲስት ቤተክርስቲያንና ባፕቲስት
ቤተክርስቲያን ድረስ እያንዳንዱ የሐይማኖት ድርጅት የራሳቸው ቤተክርስቲያን
ብቻ ትክክል እንደሆነች ይናገራሉ፡፡ ነገር ግን የበላይና እውነተኛ ኢየሱስ ክርስቶስ
ብቻ ነው፡፡ እግዚአብሄር የበላይ ሆኖ ሳለ ሰዎች እንዴት ስለ በላይነታቸው
ሊከራከሩ ይችላሉ? ሰዎች እርስ በርሳቸው መፎካከራቸውና ማን ከማን
እንደሚሻል መከራከራቸው በእግዚአብሄር ፊት ፈጽሞ አሳፋሪ ነው፡፡ ይህ ሆኖ ሳለ
አሁንም የራሳቸውን ቡድኖች እየመሠረቱና ሁሌም እግዚአብሄርን እየተቃወሙ
ነው፡፡ ጌታ እነዚህን ሰዎች አስመልክቶ እንዲህ አለ፡- ‹‹በሰማይ የተቀመጠ እርሱ
ይስቅባቸዋል፡፡›› (መዝሙረ ዳዊት 2፡4)
አጋር ምዕመናኖቼ እኛ የሐጢያቶችን ስርየት የተቀበልነው ክርስቶስ እንደ
ፈቃዱ ምክር በፈጸመው የደህንነት ሥራ በማመን ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ በማቴዎስ
3፡15 ላይ ኢየሱስ ክርስቶስ በአጥማቂው ዮሐንስ በተጠመቀ ጊዜ የዓለም
ሐጢያቶች በሙሉ ወደ እርሱ እንደተላለፉና ኢየሱስም እያንዳንዱን ሐጢያት
በዚህ መንገድ እንደተሸከመ በግልጥ ጽፎዋል፡፡ ነገር ግን በጣም ብዙ ሰዎች
ለእውነቱ ዕውራን በመሆናቸው በራሳቸው ዓይኖች እያዩ ቢያነቡትም እንኳን
መጽሐፍ ቅዱስን መረዳት አይችሉም፡፡

‹‹እናንተም ደግሞ የእውነትን ቃል ይኸውም የመዳናችሁን ወንጌል


ሰምታችሁ ደግሞም በክርስቶስ አምናችሁ በተስፋው መንፈስ
በመንፈስ ቅዱስ ታተማችሁ፡፡›› (ኤፌሶን 1፡13)

ይህ ምንባብ የሚለው እውነተኛውን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል


በማድመጥና በማመን መዳናችንን አግኝተናል ማለት ነው፡፡ ሮሜ 10፡17 ‹‹እምነት
ከመስማት ነው፤ መስማትም በእግዚአብሄር ቃል ነው›› እንደሚል የሐጢያቶችን
ስርየት የተቀበልነው እውነቱን በመስማት ነው፡፡ ማንም ሰው በራሱ ቢመጻደቅም
እንኳን የሐጢያቶችን ስርየት ሊቀበል ቀርቶ በራሱ በኢየሱስ ሊያምን አይችልም፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


እንደ እግዚአብሄር ጸጋ ባለጠግነት መጠን ቤዛነትን አግኝተናል 111

አሳባችንን ስንለጥጥ ሰው ራሱን 99 በመቶ መዳን እንደሚችል ልንገምት


እንችላለን፡፡ ይህ ግን አሁንም በቂ አይደለም፡፡ ምክንያቱም በ1 ከመቶ እንኳን
እንከን ያለበት ማንኛውም ደህንነት ፈጽሞ ደህንነት አይደለም፡፡
እኔም ራሴ በአሁኑ ዘመን እንዳሉት ክርስቲያኖች በአንጃነትና በሕግ
አክራሪነት የተጠፈርሁ ነበርሁ፡፡ ዳግመኛ ከመወለዴ በፊት በመጽሐፍ ቅዱስ
ዕውቀት የበሰልሁ ብሆንም እኔም ደግሞ በልቤ ውስጥ እውነት አልነበረኝም፡፡
እንደዚያም ሆኖ ከሌሎች ክርስቲያኖች ጋር ካደረግሁዋቸው ብዙ ሙግቶች
በአንዳቸውም ተሸንፌ አላውቅም፡፡ የመጽሐፍ ቅዱስ ጉዳዮች ምንም ይሁኑ
አንዴም እንኳን በክርክር ተሸንፌ አላውቅም፡፡
ነገር ግን በተጨባጭ ጠቃሚው ነገር ሐጢያቶቼ በልቤ ውስጥ ያሉ
መሆናቸው ነበር፡፡ ምንም እንኳን እያንዳንዱን ጽንሰ አሳባዊ ሙግት ሁሌም
ያሸንፈሁ ብሆንም አንድ ግልጥ የሆነ ነገር ነበር፡፡ ያም አሁንም በሐጢያት የተሞላ
ሕሊና የነበረኝ መሆኑ ነው፡፡ የሐጢያቶቼን ስርየት እንደተቀበልሁ ባስብም ሌላ
ሐጢያት እንደሰራሁ ወዲያውኑ ራሴን እንደገና ወደ ሐጢያተኛ ተለውጦ
አገኘዋለሁ፡፡
የዳኑትን ካልዳኑት የሚለየው ግልጥ ልዩነት ይህ ነው፡፡ የሐጢያቶቻቸውን
ስርየት ያልተቀበሉ ሰዎች አሁን ምንም ሐጢያት እንደሌለባቸው ቢሰማቸውም
እንደገና ሌላ ሐጢያት ሲሰሩ ሐጢያተኞች ይሆናሉ፡፡ በአንጻሩ የሐጢያቶችን
ስርየት የተቀበሉ ሰዎች እንደገና ሐጢያት ቢሰሩም ፈጽመው ሐጢያት አልባ ሆነው
ይቀራሉ፡፡ የሐጢያቶችን ስርየት በተቀበለ ሰውና ባልተቀበለ ሰው መካከል ያለው
ልዩነት ይህ ነው፡፡ በእግዚአብሄር ቃል ዳግመኛ በተወለዱ ሰዎችና ባልተወለዱ
ሰዎች መካከል ያለውም ልዩነት እንደዚሁ ይህ ነው፡፡

ሐዋርያው ጳውሎስ እንዲህ አለ፡- ‹‹እናንተም ደግሞ የእውነትን ቃል


ይኸውም የመዳናችሁን ወንጌል ሰምታችሁ ደግሞም በክርስቶስ
አምናችሁ በተስፋው መንፈስ በመንፈስ ቅዱስ ታተማችሁ፡፡ እርሱም
የርስታችን መያዣ ነው፤ ለእግዚአብሄር ያለውን እስኪዋጅ ድረስ ይህም
ለክብሩ ምስጋና ይሆናል፡፡›› (ኤፌሶን 1፡13-14)

ምስጋና ለእግዚአብሄር ወንጌል ይሁንና ይህ ምንባብ የሚለው ነገር ቢኖር


የእርሱ ልጆችና የመላው መንግሥተ ሰማይ ወራሾች እንደሆንን ነው፡፡ በሌላ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


112 እንደ እግዚአብሄር ጸጋ ባለጠግነት መጠን ቤዛነትን አግኝተናል

አነጋገር እዚህ ላይ መጽሐፍ ቅዱስ እያለ ያለው በእግዚአብሄር ፍቅርና በጌታችን


በኢየሱስ ክርስቶስ ሥራ አማካይነት ደህንነታችንን በእምነት እንዳገኘን ነው፡፡
ምክንያቱም ራሱን መስዋዕት በማድረግ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ደምስሶ ፈጽሞ
ተቤዥቶናልና፡፡ የእግዚአብሄርን ክብር እናመሰግናለን፡፡ ክብሩን ሰላለበሰንና የራሱ
ሕዝቦችና ጻድቃን ስላደረገን እርሱን እናመሰግነዋለን፡፡ አሁን በክርሰቶስ የሆነ ሁሉ
ፈጽሞ ሐጢያት የለበትም፡፡ ምስጋና ለኢየሱስ ክርስቶስ ይሁንለትና
የሐጢያቶቻችንን ምሉዕ ስርየት አግኝተናል፡፡
እኛ በኢየሱስ ክርስቶስ አማካይነት ቤዛነታችንን ማለትም የሐጢያቶቻችንን
ስርየት አግኝተናል፡፡ ደሙን በመስቀል ላይ ያፈሰሰውም በዮርዳኖስ ወንዝ
በመጠመቅ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ በመሸከሙ ነው፡፡ በጣም ብዙ ክርስቲያኖች
ሙሉ ደህንነታቸው አድርገው የሚያምኑበት የክርስቶስ የመስቀል ላይ ደም
በተጨባጭ የጥምቀቱ ውጤት ነው፡፡ ኢየሱስ በሕጋዊ መንገድ ደሙን በመስቀል
ላይ ያፈሰሰው ስለተጠመቀ ነው፡፡ ጌታ ደሙን በመስቀል ላይ ያፈሰሰው አስቀድሞ
ሐጢያቶቻችንን በሙሉ በዮርዳኖስ ወንዝ ላይ በመሸከሙ ነው፡፡ ሁላችንም በዚህ
እውነት ማመን አለብን፡፡
በገላትያ 3፡13 ላይ እንዲህ ተጽፎዋል፡- ‹‹በእንጨት የሚሰቀል ሁሉ የተረገመ
ነው፡፡›› ኢየሱስ ክርስቶስ የሚያስረግመው ምንም ነገር አላደረገም፡፡ ታዲያ ለምን
በእርግማን መስቀል ላይ ተሰቀለ? በጥምቀቱ አማካይነት በዮርዳኖስ ወንዝ
ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ስለተሸከመና እርግማኖቻችንን በሙሉ ስለወሰደ ነበር፡፡
ስለዚህ ኢየሱስ ክርስቶስ የተረገመው እኛን ለማዳን በጥምቀቱ አማካይነት
ሐጢያቶቻችንን በሙሉ በመውሰዱ ነው፡፡
አንዳንድ ሰዎች ‹‹ኢየሱስ ከአጥማቂው ዮሐንስ የተቀበለው ጥምቀት
ለደህንነታችን በእጅጉ አስፈላጊ ነውን?›› ብለው ይጠይቁን ይሆናል፡፡ ለዚህ ጥያቄ
የኢየሱስ ጥምቀት በእርግጥም በእጅጉ አስፈላጊ ነው ብለን ከመመለስ በቀር ምርጫ
የለንም፡፡ ለምን? ምክንያቱም የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል በራሱ በእግዚአብሄር
የጸና የደህንነት እውነት ነውና፡፡ ስለዚህ እውነተኛውን እምነታችንን በሚመለከት
የኢየሱስን ጥምቀት ወይም የመስቀል ላይ ደሙን በጭራሽ ልታወጡዋቸው
አይገባችሁም፡፡
ሆኖም ብዙ ክርስቲያኖች እኛ እንደምናምነው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
ባያምኑም እንኳን በመስቀሉ ክቡር ደም ብቻ በማመን የሐጢያቶችን ስርየት
እንደተቀበሉ ይናገራሉ፡፡ ነገር ግን እነዚህ ሰዎች ራሳቸውን እያታለሉ ነው፡፡
ምክንያቱም በሕይወታቸው ውስጥ ደግመው ሌላ ሐጢያት ከሰሩ ሁሉም እንደገና

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


እንደ እግዚአብሄር ጸጋ ባለጠግነት መጠን ቤዛነትን አግኝተናል 113

ሐጢያተኞች ይሆናሉ፡፡ እነዚህ ክርስቲያን ሐጢያተኞች የደህንነትን ትምህርት


በሚገባ እንደሚያውቁ ስለሚናገሩ ጽንሰ አሳብን በሚመለከት የማያውቁት ምንም
ነገር የለም፡፡ ነገር ግን ጻድቅነታቸው በጭንቅላታቸው ብቻ ነው፡፡ በልቦቻቸው ግን
ሁሉም ሐጢያተኞች ናቸው፡፡
በትክክል የሐጢያቶችን ስርየት ከተቀበለ ሰው የምትጠብቁት ይህንን ነውን?
እንዳልሆነ የታወቀ ነው! መጽሐፍ ቅዱስ በመጨረሻው ቀን እያንዳንዱ ነፍስ ሁሉን
ነገር ለእግዚአብሄር እንደሚናዘዝ ይናገራል፡፡ በሕሊናው ውስጥ ሐጢያት ያለበት
ሰው ሐጢያተኛ መሆኑን ለእግዚአብሄር ለመናዘዝ ይገደዳል፡፡ በአንጻሩ በትክክል
በሕሊናው ሐጢያት አልባ የሆነ ሰው ሐጢያት አልባ እንደሆነ ለእግዚአብሄር
ይናገራል፡፡ በፍጹም ሐጢያት እንደሌለበት በንጹህ ሕሊና ለእግዚአብሄር መናገር
የሚችለው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን ሐጢያቶቹን ሁሉ ወደ ኢየሱስ
ክርስቶስ ያስተላለፈ ሰው፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ሐጢያቶቹን በሙሉ እንደተሸከመ
የሚያውቅና ይህንን የማይካድ የደህንነት እውነት ከሙሉ ልቡ የሚያምን ሰው ብቻ
ነው፡፡
በ1ኛ ጴጥሮስ 3፡21 ላይ እንዲህ ተጽፎዋል፡- ‹‹ይህም ውሃ ደግሞ ማለት
ጥምቀት ምሳሌው ሆኖ አሁን ያድነናል፡፡ የሰውነትን እድፍ ማስወገድ አይደለም፤
ለእግዚአብሄር የበጎ ሕሊና ልመና ነው እንጂ፡፡›› እኛ በእግዚአብሄር ፊት ጻድቃን
ነን፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ በተጠመቀ ጊዜ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ስለተሸከመና በእኛ
ፋንታም ለእነዚህ ሁሉ ሐጢያቶች በመስቀል ላይ ስለተኮነነ በበጎ ሕሊና በድፍረት
ወደፊቱ መቅረብ እንችላለን፡፡ ስጋችን በጉድለቶች የተሞላ ቢሆንም የእውነትን ቃል
ስለምናምን ሕሊናችን አሁንም ያለ ማመንታት እግዚአብሄርን መቅረብ ይችላል፡፡
ማንም ሰው ከኢየሱስ ጥምቀት ውጪ ከሐጢያቶቹ ሁሉ መንጻት ይችላልን?
እንደማይችል የታወቀ ነው! ማንም ሰው ኢየሱስ ከአጥማቂው ዮሐንስ የተቀበለውን
ጥምቀት የሚተው ከሆነ የሐጢያቶችን ስርየት ሊቀበል አይችልም፡፡ ኢየሱስ
ክርስቶስ በተጻፈው መሠረት በትክክል በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት
እንዳዳናችሁ እስካላመናችሁ ድረስ የሐጢያቶቻችሁን ስርየት መቀበል
እንደማትችሉ ግልጥ አድርጓል፡፡ ውሎ አድሮም ወደ ሲዖል ይጣላል፡፡ በኢየሱስ
ክርስቶስ ብታምኑም እርሱ ከአጥማቂው ዮሐንስ የተቀበለውን ጥምቀት ወደ ጎን
ከተዋችሁት ይህ ሕገ ወጥ ነው፡፡ ስለዚህ ጌታ በማቴዎስ 7፡21-23 ላይ
እንደተናገረው በእርግጠኝነት ትረገማላችሁ፡፡ ‹‹በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ
የሚያደርግ እንጂ ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ
አይደለም፡፡ በዚያ ቀን ብዙዎች፡- ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ በስምህ ትንቢት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


114 እንደ እግዚአብሄር ጸጋ ባለጠግነት መጠን ቤዛነትን አግኝተናል

አልተናገርንምን? በስምህስ አጋንንትን አላወጣንምን? በስምህስ ብዙ ተዓምራትን


አላደረግንምን? ይሉኛል፡፡ የዚያን ጊዜም፡- ከቶ አላወቅኋችሁም፤ እናንተ ዓመጸኞች
ከእኔ ራቁ ብዬ እመሰክርባቸዋለሁ፡፡››
ጌታ እነዚህን የተሰጡ ክርስቲያኖች ከእርሱ እንዲርቁ የነገራቸው ለምንድነው?
ለእነርሱ ባደረገላቸው ነገር በትክክል ከማመን ይልቅ በራሳቸው አስተሳሰቦች
መሠረት በኢየሱስ በማመናቸው ነው፡፡ እነዚህ ክርስቲያን ሐጢያተኞች
አስተሳሰቦቻቸውን በመካድ ፋንታ በራሳቸው አስተሳሰቦች መሠረት ስለሚያምኑ
በመጨረሻ እግዚአብሄርም ይተዋቸዋል፡፡ በእግዚአብሄር ቃል መሰረት በኢየሱስ
አምነው ቢሆን ኖሮ እምነታቸው ድጋፍ ያገኝ ነበር፡፡ ነገር ግን እምነታቸው ከቃሉ
ጋር ስለማይጣጣም ጌታም ይተዋቸዋል፡፡
በዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ላይ ሐዋርያው ጳውሎስ ከኢየሱስ
ክርስቶስ የተቀበለው ጸጋ ምን ያህል የተትረፈረፈና ታላቅ እንደሆነ በኤፌሶን
ቤተክርስቲያን ላሉ ቅዱሳኖች መስክሮዋል፡፡ ለኢየሱስ ክርስቶስ የተትረፈረፈ
የደህንነት ጸጋ ምስጋና ይሁንና እኛም የዘመኑ ቅዱሳኖች ልክ እንደ ጳውሎስ
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት የሐጢያቶችን ስርየት ተቀብለናል፡፡
የምወዳችሁ ቅዱሳኖች ሁላችንም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን
ሐጢያት አልባ ሆነናል፡፡ ከእግዚአብሄር ቃል ሁለቱንም ሳንተው በጌታ ጥምቀትና
በመስቀሉ በማመን የሐጢያቶችን ስርየት ተቀብለናል፡፡ ይህ ምን ያህል አመስጋኞች
እንደሆንን በቃላት ልንገልጠው የማንችለው አስገራሚ በረከት ነው፡፡
ከዚህም በላይ መንፈስ ቅዱስ በልቦቻችን ውስጥ ሰላምን ሰጥቶናል፡፡
እስካመንን ድረስ ይህንን ሰላም ለዘላለም ያቆይልናል፡፡ በልቦቻችን ውስጥ ሰላም
ያለን መንፈስ ቅዱስ በልቦቻችን ውስጥ ስላለና እግዚአብሄር ይህንን ሰላም
በልቦቻችን ውስጥ ስለሰጠ ነው፡፡ ያዳነን፣ የዘላለምን ሕይወት የሰጠን፣ ልጆቹ
ያደረገን፣ ጸጋውን የለገሰንና ሰላምን ያመጣልን ጌታችን ነው፡፡ እግዚአብሄር እኛን
የባረከበት ዘላለማዊ ሰላም ሌላ ሳይሆን መንግሥተ ሰማይ ነው፡፡ ይህንን ድንቅና
የተባረከ መንግሥት ስለሰጠን ምስጋናዬን ሁሉ ለአምላካችን እሰጣለሁ፡፡ 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ስብከት
6

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት
ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
ለጌታ የጽድቅ ሥራ
ተፈጥረናልን?
‹‹ ኤፌሶን 2፡1-10 ››
‹‹በበደላችሁና በሐጢአታችሁ ሙታን ነበራችሁ፤ በእነርሱም በዚህ ዓለም
እንዳለው ኑሮ በማይታዘዙትም ልጆች ላይ አሁን ለሚሠራው መንፈስ አለቃ
እንደሆነው በአየር ላይ ሥልጣን እንዳለው ፈቃድ በፊት ተመላለሳችሁባቸው፡፡
በእነዚህም ልጆች መካከል እኛ ሁላችን ደግሞ የሥጋችንንና የልቡናችንን ፈቃድ
እያደረግን በሥጋችን ምኞት በፊት እንኖር ነበርን፡፡ እንደ ሌሎቹም ደግሞ
ከፍጥረታችን የቁጣ ልጆች ነበርን፡፡ ነገር ግን እግዚአብሄር በምሕረቱ ባለጠጋ
ስለሆነ ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሳ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ
ከክርስቶስ ጋር ሕይወትን ሰጠን፤ በጸጋ ድናችኋልና፡፡ በሚመጡ ዘመናትም
በክርስቶስ ኢየሱስ ለእኛ ባለው ቸርነት ከሁሉ የሚበልጠውን የጸጋውን ባለጠግነት
ያሳይ ዘንድ ከእርሱ ጋር አስነሳን፡፡ በክርስቶስ ኢየሱስም በሰማያዊ ሥፍራ ከእርሱ
ጋር አስቀመጠን፡፡ ጸጋው በእምነት አድኖአችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሄር ስጦታ
ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም፤ ማንም እንዳይመካ ከሥራ አይደለም፡፡ እኛ ፍጥረቱ
ነንና፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሄር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ
ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን፡፡››

እኛ በእግዚአብሄር ፊት ምን ዓይነት ሰዎች ነበርን?

ጳውሎስ በዛሬው ምንባብ ላይ ለኤፌሶን ሰዎች ‹‹በሐጢአትና በበደል ሙታን


እንደነበሩ›› (ኤፌሶን 2፡1) ተናግሮዋል፡፡ ሁላችንም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
ከማመናችን በፊት በተመሳሳይ ሁኔታ ውስጥ ነበርን፡፡ ነገር ግን ጌታችን እኛን
የማንረባውን ሰዎች በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ሥራው አማካይነት በአንድ ጊዜ
አዳነን፡፡ በአየር ላይ ሥልጣን ካለው አለቃም ታደገን፡፡ የውሃውንና የመንፈሱን
ወንጌል በመስጠትና በእርሱ እንድናምን በማድረግም ሰይጣንን ንድናሸንፍ
ባረከን፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


118 ለጌታ የጽድቅ ሥራ ተፈጥረናልን?

ከዚህ እውነተኛ ወንጌል ጋር ከመገናኘታችንና በእርሱም ከማመናችን በፊት


የክፉ መናፍስትን ሐይሎች መቋቋም አንችልም ነበር፡፡ ነገር ግን ኢየሱስ ክርስቶስ
ከአጥማቂው ዮሐንስ በተቀበለው ጥምቀት አማካይነት ጌታ ከአያቶቻችን
የወረስናቸውን ሐጢያቶች በሙሉ ተሸክሞ ሁሉንም ደመሰሳቸው፡፡ ስለዚህ
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የምናምን ሁላችን ከሰይጣን ሐይል ነጻ ወጥተናል፡፡
ወሰን ለሌለው የእግዚአብሄር ጸጋ ምስጋና ይሁንለትና ሁላችንም ለአንዴና
ለመጨረሻ የሐጢያቶችን ስርየት ተቀብለን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
አማካይነት የዘላለምን ሕይወት አገኘን፡፡
አምላካችን እኛን ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ያዳነበት ምክንያት አለው፡፡ ያም
ከአምላካችን ጋር አብረን ክቡር ሕይወትን እንድንኖር ለመፍቀድ ነው፡፡ በሌላ
አነጋገር እግዚአብሄር አብ ልጁን ኢየሱስ ክርስቶስን ወደዚህ ምድር በመላክ
በመንግሥቱ ውስጥ ከእርሱ ጋር አብረን እንደንኖር በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
የምናምነውን አማኞች ሊባርከን ፈለገ፡፡ እግዚአብሄር አብም በልጁ በኢየሱስ
ክርስቶስ በተከወነው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ሥራ አማካይነት ይህንን
ፈቃዱን ፈጸመው፡፡ እዚህ ግብ ላይ የሚደረስበት መንገድም ኢየሱስን ወደዚህ
ምድር መላክ፣ በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅም ሐጢያቶቻችንን በሙሉ
ለአንዴና ለመጨረሻ እንዲሸከም ማድረግና ተሰቅሎ በመሞትም የሐጢያቶቻቸንን
ኩነኔ በሙሉ እንዲወስድ ማድረግ ነበር፡፡ ለእኛ በተነደፈው በዚህ የደህንነት ዕቅድ
መሠረት እኛን በመንግሥተ ሰማይ ማስቀመጥ የአምላካችን ምኞት ነበር፡፡
እግዚአብሄር አብ ይህንን ታላቅ ዕቅድ በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ሊፈጽም ፈለገ፡፡
የእግዚአብሄርን ፍቅርና በረከቶቹን መቀበል የምንችለው በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል በማመን እንደሆነ የታወቀ ነው፡፡ የእግዚአብሄር አባታችን ምኞት
በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ውስጥ በሚገኘው ጽድቁ አማካይነት ዕቅዱን መፈጸም
ነበር፡፡ እኛም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን በሕይወታችን ውስጥ
የሐጢያቶችን ስርየት መቀበል ችለናል፡፡ በአጭሩ እግዚአብሄር በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል የምናምነውን ሁላችንን መንግሥተ ሰማይ እንድንገባ ባርኮናል፡፡
ስላሴ አምላክ ሐጢያቶቻችንን ብቻ ያስወገደ ሳይሆን በመንግሥቱ ውስጥም
እንድንቀመጥ ባርኮናል፡፡ እግዚአብሄር በመንግሥተ ሰማይ እንድንነግስና በዚህ
ሁሉ ክብር ውስጥም እንድንኖር በዚህ መልኩ አብዝቶ ባርኮን ሳለ እንዴት በእርሱ
አናምንም?
እግዚአብሄር በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የምናምነውን አማኞች ለምን
እንደዚህ አብዝቶ አከበረን? የሰማይ ከብር ተካፋዮች እንድንሆን ስለፈለገ ነው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ለጌታ የጽድቅ ሥራ ተፈጥረናልን? 119

እግዚአብሄር በረከቶቹን የለገሰን ከፍቅሩና ከምህረቱ የተነሳ ነው፡፡ ስለዚህ


ሁላችንም ልናምነውና ልንገነዘበው የሚገባን ነገር ቢኖር እግዚአብሄር በልጁ
በኢየሱስ ክርስቶስ አማካይነት ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ያስወገደ መሆኑን ብቻ
ሳይሆን በመንግሥተ ሰማይም የሚያስቀምጠን መሆኑን ነው፡፡ ስለዚህ በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል እውነት የምናምን ሁላችን እግዚአብሄር መንግሥቱን
እንደሚሰጠን ማስታወስ አለብን፡፡

የእግዚአብሄርን ክቡር በረከቶች እንደተቀበልን ማስታወስ አለብን፡፡

ወደ እግዚአብሄር መንግሥት ገብተን መኖር የማንችል ከሆነ ከሐጢያት


መዳናችን ምን ትርጉም ይኖረዋል? ሁላችንም መንግሥተ ሰማይ እንደምንገባና
ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር እንደምንኖር የማይናወጥ እምነት እስከሌለን ድረስ ሁሉም
ከንቱ ይሆናል፡፡ ነገር ግን እኛ በዚህ ዓለም ላይ የሐጢያቶቻችንን ስርየት የተቀበልን
ብቻ ሳንሆን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር አብረንም በመንግሥተ ሰማይ ለመቀመጥ
ተባርከናል፡፡ አሁን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የምናምን ሁላችን ከኢየሱስ
ክርስቶስ ጋር አብረን በመንግሥተ ሰማይ እንቀመጣለን፡፡ እግዚአብሄር እኛን
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የምናምነው አማኞች ‹‹ቅዱሳን›› ብሎ በመጥራት
ያከበረን ለዚህ ነው፡፡ በሌላ አነጋገር እግዚአብሄር በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
የሚያምኑትን ሁሉ ‹እናንተ የሰማይ ዜጎች ናችሁ፤ እናንተ ፈጽሞ ሐጢያት አልባ
ናችሁ፤ ሁላችሁም ጻድቃን ናችሁ›› ይለናል፡፡

እግዚአብሄር በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የምናምነውን አማኞች


ክቡር በሆነው መንግሥቱ ውስጥ ከእርሱ ጋር ያስቀመጠን መሆኑ
እውነት ነውን?

አዎ፤ በአንድ ወቅት በበደሎቻችንና በሐጢያቶቻችን ሙታን የነበርን


መሆናችን እውነት ነው፡፡ እግዚአብሄር በመንግሥተ ሰማይ ለመቀመጥ እንባረክ
ዘንድ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል እንድናምን አድርጎናል፡፡ የእግዚአብሄር ጸጋ
ምንኛ አስገራሚ ነው? የሰጠንስ በረከት እንደምን ድንቅ ነው? እግዚአብሄር እንዲህ
ያሉ አስገራሚ በረከቶችን የሰጠን ወሰን ከሌለው ፍቅሩና ጸጋ የተነሳ ነው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


120 ለጌታ የጽድቅ ሥራ ተፈጥረናልን?

ስለዚህ እኛን ልጆቹ ስላደረገንና ከእርሱም ጋር በመንግሥተ ሰማይ


እንድንኖር ስለባረከን የእግዚአብሄርን ጸጋ በጭራሽ መርሳት የለብንም፡፡ ስለዚህ
ሁላችንም ቀሪውን ሕይወታችንን በእግዚአብሄር ጽድቅ በመታመን ልንኖር
ይገባናል፡፡ በሕይወታችን ውስጥም የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ስናገለግል
የእግዚአብሄር ሥራ በቅርቡ ይጠናቀቃል፡፡ ከእርሱ የተቀበልነው የደህንነት ጸጋ
በጣም ታላቅ ስለሆነ እግዚአብሄርን እናመሰግናለን፡፡
ከእግዚአብሄር የተቀበላችሁትን የጸጋ መጠን ታደንቃላችሁን? ሁላችንም
ከየት እንደመጣንና ወዴት እንደምንሄድ ማወቅ እንደሚገባን ሁሉ ከውሃውና
ከመንፈሱ ወንጌል ጋር በመገናኘትና በማመን በእግዚአብሄር ጸጋ ውስጥ ለመኖር
ፍጹም የሆነውን የሐጢያቶቻችንን ስርየት መቀበላችንንም ደግሞ መረዳት
ይገባናል፡፡ ነገር ግን ይህ ሆኖ እያለ በመካከላችን በሕይወታቸው ውስጥ
ከእግዚአብሄር ዘንድ ምን ዓይነት በረከቶችን እንደተቀበሉ የማያውቁ አንዳንድ
ሰዎች አሉ፡፡ ከዚህ የበለጠ ሞኝነት የለም፡፡ በዚህ በጨለማው ዓለም ውስጥ
ሕይወታችንን በመኖር ስንቀጥል ሁላችንም መንቃትና ምን ያህል የተባረክን
እንደሆንን በሚገባ ማወቅ አለብን፡፡ አሁን እናንተና እኔ በሕይወታችን ውስጥ
የእግዚአብሄርን መንፈሳዊ በረከቶች እንደተቀበልን መገንዘብ አለብን፡፡
በበደሎቻችንና በሐጢያቶቻችን ሙታን በነበርን ጊዜ ጌታ ሁላችንንም ለማዳን
ተጠመቀ፤ ደሙንም አፈሰሰ፡፡ እግዚአብሄር በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
አማካይነት ቅዱሳን ልጆቹ አደረገን፡፡ ሁላችንም በእርሱ ጽድቅ ላይ ባለን
እምነታችን አማካይነት የእግዚአብሄር ልጆች ሆነናል፡፡ ስለዚህ ሁላችንም
በመንግሥተ ሰማይ እንቀመጣለን፡፡ ለዘላለምም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር
እንኖራለን፡፡ በመሆኑም የእግዚአብሄርን ክብር እንደለበስን መገንዘብ ይገባናል፡፡
እግዚአብሄር ሁላችንንም ቢያድነንም የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
ከማገልገል በቀር አንዳች ሌላ ነገር አልጠየቀንም፡፡ እርሱ ከእኛ የሚሻው ነገር ቢኖር
በእርሱ ክብር ታምነን እንድንኖር ብቻ ነው፡፡ ስለዚህ በልቦቻችን እግዚአብሄር
የሰጠንን የደህንነት ጸጋ መውደድና በእርሱ ጽድቅ ላይ ባለን እምነታችን መኖር
ነው፡፡ ሁላችንም የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል በዚህ ምድር ላይ ሙሉ በሙሉ
እስከሚሰበክበት ቀን ድረስ በእግዚአብሄር ጽድቅ ላይ ባለን እምነታችን መኖር
በእጀጉ ያስፈልገናል፡፡
አዳኛችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ሊወስደን ወደዚህ ምድር እንደሚመጣ
በጣም የተረጋገጠ ነው፡፡ ጌታችን በእኛ ፋንታ ለሐጢያቶቻችን በመሞትና ከሙታን
በመነሳት አዳኛችን ከሆነ በኋላ እኛን ሊወስደን በእግዚአብሄር ጊዜ ወደ እኛ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ለጌታ የጽድቅ ሥራ ተፈጥረናልን? 121

ይመለሳል፡፡ ያን ጊዜ እኛም ደግሞ በመንግሥተ ሰማይ እንቀመጣለን፡፡ ከኢየሱስ


ክርስቶስም ጋር በክብሩ ሁሉ እንደሰታለን፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
ከምናምነው ከእናንተና ከእኔ የበለጠ ከእግዚአብሄር ዘንድ ብዙ በረከቶችን የተቀበለ
እግዚአብሄር የፈጠረው ፍጡር አለ? ማንም የለም፡፡ ምክንያቱም በእግዚአብሄር
የታቀደውና የተጠናቀቀው የሰማይ ግዛት ሁሉ የእኛ ነውና፡፡
ታዲያ እግዚአብሄር የፈጠራቸው መላዕክቶች የሚኖሩት ለማነው? እነርሱ
የሚኖሩት በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ለሚያምኑት ጻድቃን ነው፡፡ እነዚህ ሁሉ
መላዕክቶች የሚኖሩት ለእኛ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ለምናምን አማኞች
ነው፡፡ በዚህ ዩኒቨርስ ውስጥ ያለው እያንዳንዱ ነገር በዓለም ላይ ካሉት አበቦች
ጀምሮ በሰማያት እስካሉት ከዋክብቶች ድረስ የሚኖሩት የእግዚአብሄር ጻድቃን
ለሆኑ ሕዝቦች ሁሉ ነው፡፡ እነዚህ ሁሉ ፍጥረታቶች የሚኖሩት ለጻድቃን ነው፡፡
ስለዚህ የእግዚአብሄር ችሮታ እነዚህን ድንቅ በረከቶች ለእኛ በመስጠቱ ምን ያህል
ታላቅ እንደሆነ በሕይወታችን ውስጥ መገንዘብ ይገባናል፡፡
ስለዚህ ክብራማ የሆነውን ማዕረጋችንን በመገንዘብ ሕይወታችንን የምንኖር
ከሆነ ይበልጥ ብርቱ የሆነ ሕይወትን መኖር እንችላለን፡፡ ጸድቃን በመሆናችን
ሕይወታችን ለእግዚአብሄር የጽድቅ ሥራ የሚኖር ነው፡፡ ሕይወታችን ዋጋ ያለውና
የከበረ ነው፡፡ ስለዚህ የተሰጠንን የእግዚአብሄር ጸጋ ስናስተውል ሥራችን በጣም
የሚከብድ አይደለም፡፡ አሁን ጌታችን የሰጠንን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
በማመን ማገልገል ሐላፊነታችን ነው፡፡ እግዚአብሄር ይህንን አስገራሚ ክብር
ስለሰጠን ኢምንት በሆነ መከራ የእርሱን ጽድቅ ከመስበክ አናመነታም፡፡ ሥራችንን
እግዚአብሄር ከሰጠን የደህንነት ጸጋ ጋር ስናወዳድረው ለእርሱ እያደረግነው ያለነው
ነገር በአንጻሩ በጣም አነስተኛ ይመስላል፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ እንዲህ ያለው
ለዚህ ነው፡- ‹‹ለእኛም ይገለጥ ዘንድ ካለው ክብር ጋር ቢመዛዘን የአሁኑ ዘመን
ስቃይ ምንም እንዳይደለ አስባለሁ፡፡›› (ሮሜ 8፡18) እኛ በአምላካችን ጽድቅ
በማመናችን ብቻ በጣም ደስተኞች ነን፡፡
አጋር ምዕመናኖቼ በልቦቻችንና በድርጊቶቻችን ክፋትን እያደረግን በዚህ
ዓለም ላይ ብንኖር ኖሮ ልባችን አይረካም ነበር፡፡ በአንጻሩ የእግዚአብሄርን ጽድቅ
በማገልገል ሕይወታችንን ብንኖር ልቦቻችን በእርግጠኝነት ይደሰታሉ፡፡
በእግዚአብሄር ፊት ጽድቅን ስናደርግ ይህንን ማድረጉ ልብን የሚያሞቅ ብቻ
ሳይሆን በጣም የሚያረካም ደግሞ ነው፡፡ ልቦቻችን ጥሩ ስሜት ይሰማቸዋል፡፡
ምክንያቱም በአምላካችን ፊት መልካም ሥራዎችን መስራት እንችላለንና፡፡
ልቦቻችንም በሰላም የተሞሉ ይሆናሉ፡፡ ምክንያቱም በሕይወታችን የአምላካችንን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


122 ለጌታ የጽድቅ ሥራ ተፈጥረናልን?

ጽድቅ እንከተላለንና፡፡
በዚህ ዓለም ላይ የሚኖር ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢቆጣጠርም እንኳን
የእግዚአብሄርን ጽድቅ ከሚያገለግሉት በላይ በጣም ደስተኛ ሊሆን አይችልም፡፡
ሰው በመላው ዓለም ላይ ሁሉም ነገር ቢኖረው እንኳን በእግዚአብሄር ጽድቅ
እስካላመነ ድረስ በመጨረሻ ይጠፋል፡፡ እነርሱ በሕይወታቸው ውስጥ
በእግዚአብሄር ፊት በርካታ ሐጢያቶችን ይሰራሉ፡፡ ሁሉም ሰው በእግዚአብሄር
ጽድቅ በመታመን እስካልኖረ ድረስ ከእግዚአብሄር ፈቃድ በተቃራኒ ለመኖር
ይገደዳል፡፡ ለጸጋው ምስጋና ይሁንለትና የእግዚአብሄርን ሥራ መስራት
የምንችለው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የምናምነው አማኞች እናንተና እኔ
የሆንነው ለዚህ ነው፡፡ ስለዚህ በስጋችን ደካሞች ብንሆንና በጣም ብዙ ጉድለቶች
ቢኖሩብንም እርሱን ለማስደሰት የእግዚአብሄርን ሥራ በእምነት መስራታችንን
መቀጠል አለብን፡፡ ያን ጊዜ እግዚአብሄርንና የእርሱን አገልጋዮች እናመሰግናለን፡፡
ምክንያቱም ሕይወታችን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን ታድሶና
ከብሮዋልና፡፡
ስለ ውሃውና መንፈሱ ወንጌል ሳታውቁ በነበራችሁበት ጊዜ ሕይወታችሁ
እንዴት እንደነበር እንደምታውቁ እርግጠኛ ነኝ፡፡ ስለዚህ ጉዳይ ደግማችሁ አስቡ፡፡
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ከማመናችሁ በፊት ምን ዓይነት ሕይወት ትኖሩ ነበር?
በቀድሞው ኑሮዋችሁ እጅግ አስጸያፊና እጅግ ክፉ የሆኑ ሐጢያቶችን ብቻ
ሰርታችኋል እያልሁ እንዳልሆነ የታወቀ ነው፡፡ ነገር ግን በእነዚያ ዘመናት
ከእግዚአብሄር ሥራ ጋር ምንም ግንኙነት የሌላቸው ብዙ ክፉ ነገሮችን
እንደሰራችሁ እረግጠኛ ነኝ፡፡
ሁላችንም የኢየሱስ ክርስቶስን ጽድቅ ከመረዳታችን በፊት ሳናውቅም ቢሆን
የእግዚአብሄርን ጽድቅ ተቃውመናል፡፡ አሁን ግን በልቦቻችን በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል ስለምናምን በትክክል መልካምና ንጹህ የሆነውን በደስታ እናደርጋለን፡፡
እነዚህን የሰማይ መንፈሳዊ በረከቶች ለማሰራጨትም ሁላችንም የእግዚአብሄርን
የደህንነት ጸጋ ለብሰናል፡፡ ማንም ሐጢያተኛ በእግዚአብሄር ፊት አንዳች መልካም
ነገር ማድረግ ባይችልም አሁን እግዚአብሄር በሕይወታችን ውስጥ ትክክለኛውን
ጽድቅ ተግባራዊ ማድረግ የምንችልበትን ችሎታ ሰጥቶናል፡፡ በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል በመታመን በሕይወታችን የእግዚአብሄርን ጽድቅ መስበካችን ትልቅ በረከት
ነው፡፡
ይህ ሆኖ ሳለ የእግዚአብሄርን የጽድቅ ሥራ መስራት ተስኖን ቢሆን ኖሮ ምን
ይፈጠር ነበር? ለስጋችን በጣም አድካሚ በመሆኑ ምክንያት የእግዚአብሄርን ጽድቅ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ለጌታ የጽድቅ ሥራ ተፈጥረናልን? 123

ባናገለግል ወደ ደህንነታቸው የሚያደርሳቸውን መንገድ የማያውቁ ሰዎች ምን


ይገጥማቸው ነበር? እነዚህ ሁሉ ሰዎች ለዘላለም ይጠፋሉ፡፡ ነገር ግን አምላካችን
በሕይወታችን ውስጥ የእርሱን የጽድቅ ሥራ እንድንሰራ ችሎታውን ሁሉ
ሰጥቶናል፡፡ በሕይወታችን ውስጥ የእግዚአብሄርን ሥራ እንሰራለን፡፡ ምክንያቱም
በእያንዳንዲቱ የሕይወታችን ቅጽበት ጽድቅን መስራት የምንችል ሰዎች ሆነን
ተለውጠናልና፡፡ እንዲህ ያለ ብሩክ ሕይወት እንድንኖር ያስቻለን ራሱ እግዚአብሄር
ነው፡፡ ሁላችንም ከጥልቅ ምስጋና በመነጨ መልኩ በትጋት እየሰራን ያለነው ለዚህ
ነው፡፡
ባለፈው ዘመኔ ከሐጢያት በቀር በሕይወቴ ያደረግሁት ምንም ነገር
አልነበረም፡፡ አሁን ግን ሕይወቴ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል እንዲያሰራጭ
መምራቴ ጽድቅ እንደሆነ አውቃለሁ፡፡ በዚህች ቅጽበት እንኳን የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል እውነት ለሰው ሁሉ እየሰበክሁ ነው፡፡ ይህም ሥራ ይህን
የወንጌል እውነት ለሚቀበሉ ሁሉ የሐጢያቶችን ስርየትና የዘላለምን ሕይወት
እያመጣ ነው፡፡ እግዚአብሄር በሕይወታችን ውስጥ ከሰጠን የጽድቅ ሥራ የበለጠ
በዚህ ምድር ላይ የላቀ ደስታ የሚሰጠን ምንም ነገር እንደሌለ ከሙሉ ልብ
እናምናለን፡፡ ከእኛ የበለጠ ደሰተኛ ሕይወት እንደሌለ ምንም ጥርጥር የለንም፡፡
ስለዚህ ለአንዲትም ቀን እንኳን ቢሆን የእግዚአብሄርን ሥራ ካልሰራን ልቦቻችን
አይረኩም፡፡ ይህንን በደስታ ለመጠበቅም እንገደዳለን፡፡ እናንተና እኔ በሕይወታችን
ውስጥ ሁሌም የጽድቅን ሥራ እንደምንሰራና ለእግዚአብሄርም ጽድቅ ማንኛውንም
ነገር ለማድረግ ፈቃደኞች እንደምንሆን ተስፋ አደርጋለሁ፤ እጸልይማለሁ፡፡ እኛ
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለአገራችን ሰዎች ብቻ ሳይሆን በመላው ዓለም
ለሚገኙ ሰዎችም ሁሉ የመስበክ ናፍቆት አለን፡፡ ጻድቃን እንደ መሆናችን ደስታችን
ይህ ነውና፡፡
እስከ አሁን ድረስ በልቦቻቸው ውስጥ የእግዚአብሄርን ጽድቅ ያልተቀበሉና
ገና የሐጢያቶችን ስርየት ያላገኙ ሰዎች በሕይወታቸው ክፋትን ለማድረግ ምን
ያህል እንደሚመኙ በትከክል ይገነዘባሉ፡፡ በዚህ ዓለም ላይ ማንም ሰው ሊኖረው
የማይፈልገውን የሕይወት ዓይነት ለመኖር የሚሹ ብዙ ሰዎች አሉ፡፡ ሕይወታችንን
ከእነዚህ ሰዎች ሕይወት ጋር ስናመዛዝነው ሌሎችን ስለማንጎዳ ነገር ግን በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል ውስጥ ያለውን የእግዚአብሄርን ጽድቅ በማገልገል ነፍሳቸውን
ለማዳን ራሳችንን መስዋዕት ስለምናደርግ ሁላችንም ምን ያህል ደስተኞች
እንደሆንን ማየት እንችላለን፡፡ ይህ ሁሉ የሆነው ወሰን በሌለው በእግዚአብሄር
የተትረፈረፈ ጸጋ ነው፡፡ ሁላችንም በዚህ የእግዚአብሄር ጸጋ ስለምናምን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


124 ለጌታ የጽድቅ ሥራ ተፈጥረናልን?

ሕይወታችንን በተትረፈረፈ አመስጋኝነት እየኖርን ነው፡፡ እግዚአብሄር በውሃውና


በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት በኢየሱስ ክርስቶስ ዳግመኛ እንድንወለድ የፈቀደልን
እንዲህ ያለውን የተባረከ ሕይወት መኖር እንድንችል ነው፡፡ ሁላችንም በዚህ
የእግዚአብሄር ጸጋ በመታመን በእያንዳንዲቱ የሕይወታችን ቅጽበት ስለ ጸጋው
እርሱን እያመሰገንን ልንኖር ይገባናል፡፡
በዚህ ዓለም ላይ ቁሳዊ ሐብቶቻችንን በምናባክንበት ጊዜ ሁሉ የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል ለማሰራጨት ሊባክኑ ይገባቸዋል፡፡ በሌላ አነጋገር ምንም ነገር
ብናደርግ ሁሉንም ነገር ለወንጌል ስርጭት ማድረግ አለብን፡፡ ሁላችንም
በሐጢያቶቻችን ለመኮነን ተመድበን የነበርን ሆነን ሳለን አሁን በሕይወታችን
በእግዚአብሄር የጽድቅ ሥራ ውስጥ መሳተፍ መቻላችን ምንኛ ድንቅ ነው? ከእኛ
በተቃራኒ በዚህ ምድር ላይ በሐጢያቶቻቸው ሊኮነኑ ለስጋቸው ብቻ የሚኖሩ
በጣም ብዙ ሰዎች አሉ፡፡ የእነዚህ ሰዎች ሕይወት በክፋት የተሞላ ነው፡፡ ስለዚህ
መጨረሻችን እንደ እነዚህ ሰዎች እንዳይሆን የእግዚአብሄር ጸጋና የቤተክርስቲያኑ
ምሪት በእጅጉ የሚያስፈልገን ለነፍሳችን ብቻ አይደለም፡፡ በዚህ ምድር ላይም
የጽድቅን ሥራ ለማከናወን በእጅጉ ያስፈልገናል፡፡ ከእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን
ከራቅን ነፍሳችን ለዘላለም ትጠፋለች፡፡ ነፍሳችን ከጠፋች በስጋችንም ደግሞ
እንጠፋለን፡፡
እዚህ የተሰበሰብን ሁላችን ወጣቶችና ሽማግሌዎች፣ ወንዶችና ሴቶች፣
ምዕመናንና አገልጋዮች እግዚአብሄር ሥራወን እንድንሰራ ያስቻለን መሆኑ እንዴት
ያለ ደስታ እንደሆነ ልንገነዘብ ይገባናል፡፡ ጌታን የምናገለግልበት ስፍራ ምንም
ይሁን ለእርሱ ያለንን ልባዊ ምስጋና በፍጹም መርሳት የለብንም፡፡ እውነተኛ ደስታ
ምን እንደሆነ መረዳት፣ እግዚአብሄርን በትክክል ማመስገን ምን እንደሆነ ማወቅና
በዚህ መልኩ በእምነት መኖር ይገባናል፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን
ከሐጢያቶቻችን ሁሉ በመንጻታችንና የጽድቅን ሥራ ለመስራትም ቀሪዎቹን
የሕይወታችንን ቀናቶችም ይህንን ወንጌል ለማስፋፋት አሳልፈን በመስጠታችን
በጣም ደስተኞች እንደሆንን የታወቀ ነው፡፡
እንደ እናንተና እንደ እኔ አንዳች ሐጢያት ሳይኖርበት ልቡ በሰላም የተሞላ
ሰው በዚህ ዓለም ላይ አለ? በእርግጥ የለም! ልቦቻችን ታውከው ከሆነ ምክንያቱ
ተጨማሪ ነፍሳቶችን ለማዳን በእግዚአብሄር ፊት አብዝተን በትጋት መስራት
አለመቻላችን ነው፡፡ ከዚህ ውጪ በዚህ ዓለም ላይ የሚያስጨንቀን ምንም ነገር
የለም፡፡ በዚህ ምድር ላይ ከእኛ ይበልጥ ደስተኛ የሆነ ሰው አለ? በዚህች ፕላኔት
ምድር ላይ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ከምናምን ከእኛ አማኞች የበለጠ ደስተኛ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ለጌታ የጽድቅ ሥራ ተፈጥረናልን? 125

የሆነ ሰው የለም፡፡ ሌላ የምታውቁት ሰው አለ? ስለ ዓለማዊ ጓደኞቻችሁ አስቡና


ከእናንተ የበለጠ ደስተኛ ሰው እንዳለ ታገኙ እንደሆነ ተመልከቱ፡፡ ማንንም ሰው
እንደማታገኙ እርግጠኛ ነኝ፡፡ እዚህ ከተሰበሰብነው ሰዎች የበለጠ ደስተኛ የሆነ
ሰው በዚህ ዓለም ላይ ፈጽሞ የለም፡፡ ምክንያቱም ሁላችንም በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል ዳግመኛ ተወልደናል፡፡ ስለዚህ እኛ እጅግ ደስተኛ ሰዎች ነን፡፡
እኛ ከልባችን እግዚአብሄርን እናመሰግነዋለን፡፡ በእርግጥም ሁላችንም
ደስተኞች ነን፡፡ ጌታ ወደ እኛ እስከሚመለስበት ቀን ድረስም በዚህ መልኩ በደስታ
ልንኖር እንችላለን፡፡ ሁላችንም ለሌሎች ነፍሳት ለመኖር ስንል ተባርከናል፡፡
እኔን በሚመለከት ቅዱሳኖቻችን ሁሉ በአንድ ላይ ተባብረው የጽድቅን ሥራ
እንዲሰሩ፣ አብረው እንጀራን እንዲቆርሱ፣ በመከራ ጊዜም እርስ በርሳቸው
እዲያያዙና እንዲደጋገፉ ሁላችንም ወደ ጌታ እስክሄድና እርሱን ፊት ለፊት
እስክናየው ድረስ እንዲህ ሆነን እንድንኖር ልባዊ ምኞቴ ነው፡፡ እናንተም ደግሞ
የምትሹት ይህንን ነው? በእርግጥም የልቦቻችን ምኞት ያ ነው፡፡ ስለዚህ ይህ ሕልም
እውነት እንዲሆን፣ ሁላችንንም እንዲጠብቀንና በእርሱ ፊት እስከምንቀርብ ድረስ
ለዘላለም የተባረከ ሕይወትን እንድንኖር እንዲፈቅድልን ወደ እግዚአብሄር
እጸልያለሁ፡፡ 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


126 ለጌታ የጽድቅ ሥራ ተፈጥረናልን?

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ስብከት
7

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት
ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
በእምነት ሕይወታችን ውስጥ
የእግዚአብሄርን ሥልጣንና ጸጋ
መቀበል አለብን
‹‹ ኤፌሶን 2፡1-22 ››
‹‹በበደላችሁና በሐጢአታችሁ ሙታን ነበራችሁ፤ በእነርሱም በዚህ ዓለም
እንዳለው ኑሮ በማይታዘዙትም ልጆች ላይ አሁን ለሚሠራው መንፈስ አለቃ
እንደሆነው በአየር ላይ ሥልጣን እንዳለው ፈቃድ በፊት ተመላለሳችሁባቸው፡፡
በእነዚህም ልጆች መካከል እኛ ሁላችን ደግሞ የሥጋችንንና የልቡናችንን ፈቃድ
እያደረግን በሥጋችን ምኞት በፊት እንኖር ነበርን፡፡ እንደ ሌሎቹም ደግሞ
ከፍጥረታችን የቁጣ ልጆች ነበርን፡፡ ነገር ግን እግዚአብሄር በምሕረቱ ባለጠጋ
ስለሆነ ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሳ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ
ከክርስቶስ ጋር ሕይወትን ሰጠን፤ በጸጋ ድናችኋልና፡፡ በሚመጡ ዘመናትም
በክርስቶስ ኢየሱስ ለእኛ ባለው ቸርነት ከሁሉ የሚበልጠውን የጸጋውን ባለጠግነት
ያሳይ ዘንድ ከእርሱ ጋር አስነሳን፡፡ በክርስቶስ ኢየሱስም በሰማያዊ ሥፍራ ከእርሱ
ጋር አስቀመጠን፡፡ ጸጋው በእምነት አድኖአችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሄር ስጦታ
ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም፤ ማንም እንዳይመካ ከሥራ አይደለም፡፡ እኛ ፍጥረቱ
ነንና፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሄር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ
ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን፡፡ ስለዚህ እናንተ አስቀድሞ በሥጋ አሕዛብ
የነበራችሁ በሥጋ በእጅ የተገረዙ በተባሉት ያልተገረዙ የተባላችሁ ይህን አስቡ፡፡
በዚያ ዘመን ከእስራኤል መንግሥት ርቃችሁ፣ ለተስፋውም ቃል ኪዳን እንግዶች
ሆናችሁ፣ በዚህም ዓለም ተስፋን አጥታችሁ፣ ከእግዚአብሄርም ተለይታችሁ ያለ
ክርስቶስ ነበራችሁ፡፡ አሁን ግን እናንተ በፊት ርቃችሁ የነበራችሁ በክርስቶስ
ኢየሱስ ሆናችሁ በክርስቶስ ደም ቀርባችኋል፡፡ እርሱ ሰላማችን ነውና፤ ሁለቱን
ያዋሃደ፣ በአዋጅ የተነገሩትንም የትዕዛዛትንም ሕግ ሽሮ በመካከል ያለውን የጥል
ግድግዳን በሥጋው ያፈረሰ፣ ይህም ከሁለታቸው አንድን አዲስን ሰው በራሱ
ይፈጥር ዘንድ፣ ሰላምንም ያደርግ ዘንድ፣ ጥልንም በመስቀሉ ገድሎ በእርሱ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


130 በእምነት ሕይወታችን ውስጥ የእግዚአብሄርን ሥልጣንና ጸጋ መቀበል አለብን

ሁለታቸውን በአንድ አካል ከእግዚአብሄር ጋር ያስታርቅ ዘንድ ነው፡፡ መጥቶም


ርቃችሁ ለነበራችሁ ለእናንተ ሰላምን ቀርበው ለነበሩትም ሰላምን የምሥራች ብሎ
ሰበከ፡፡ በአርሱ ሥራ ሁላችን ወደ አብ መግባት አለንና፡፡ እንግዲያስ ከእንግዲህ
ወዲህ ከቅዱሳን ጋር ባላገሮችና የእግዚአብሄር ቤተ ሰዎች ናችሁ እንጂ እንግዶችና
መጻተኞች አይደላችሁም፡፡ በሐዋርያትና በነቢያት መሠረት ላይ ታንጻችኋልና፤
የማዕዘኑም ራስ ድንጋይ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፡፡ በእርሱም ሕንጻ ሁሉ እየተጋጠመ
በጌታ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንዲሆን ያድጋል፡፡ በእርሱም እናንተ ደግሞ መኖሪያ
ለመሆን በመንፈስ አብራችሁ ትሠራላችሁ፡፡››

ዘፍጥረት ምዕራፍ 2 እግዚአብሄር እውነተኛ ዕረፍትን እንደሰጠ ያሳያል፡፡


እርሱ ለሰው የኤድን ገነትንም ደግሞ ሰጥቶዋል፡፡ እግዚአብሄር ከሰው ዘር ጋር
ሕብረትን ለማድረግ ፈለገ፡፡
እዚህ ላይ ትኩረት ልናደርግበት የሚያስፈልገን ነገር ቢኖር በኤድን ገነት
መካከል የሕይወት ዛፍና መልካምንና ክፉን የሚያስታውቅ ዛፍ የነበሩ መሆናቸው
ነው፡፡ ይህ የሚያሳየው እነርሱ በእግዚአብሄር ቃል በመታመን ከሕይወት ዛፍ
መብላት የነበረባቸው መሆኑን ነው፡፡ እግዚአብሄር መልካምንና ክፉን
ከሚያስታውቀው ዛፍ ፍሬዎች እንዳይበሉ የሰጠው ትዕዛዝ የእግዚአብሄርን
ሥልጣን መገዳደር እንደማይገበቸው መንፈሳዊውን ጭብጥ የሚያስታውሳቸው
ነበር፡፡ እግዚአብሄር አንድ ጊዜ እንዲህ አለ፡- ‹‹ነገር ግን መልካምንና ክፉን
ከሚያስታውቀው ዛፍ አትብላ፤ ከእርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህና፡፡››
(ዘፍጥረት 2፡17) በዚህ ምክንያት እግዚአብሄር መልካምንና ክፉን
የሚያስታውቀውን ዛፍ በዚያ ያኖረው ለሰው ዘር ሁሉ መሆኑን ማመን እንችላለን፡፡
ከሰው ዕይታ አንጻር ያ ብዙም ስሜት አይሰጥም፡፡ በእግዚአብሄር ዓይን ግን ዛፉ
ተገቢ ነበር፡፡ እግዚአብሄር ጽድቁን ይገልጥ ዘንድ በዋናው የእርሱ ዕቅድ ውስጥ
አስፈላጊ ዛፍ ነበር፡፡ ነገር ግን በሰው ዓይን እንዲህ ያለ ጥያቄ ልንጠይቅ
እንችላለን፡- ‹‹እግዚአብሄር መልካምንና ክፉን የሚያስታውቀውን ዛፍ ለምን ፈጠረ?
በጭራሽ ባይፈጥረው ይሻል እንደነበር አስባለሁ፡፡›› ይህንን ያደረገው እግዚአብሄር
የእርሱን ሥልጣን እንድንቀበል ስለፈለገ ነው፡፡
ኤፌሶ 2፡1 እንዲህ ይላል፡- ‹‹በበደላችሁና በሐጢአታችሁ ሙታን
ነበራችሁ፡፡›› ‹‹ጸጋው በእምነት አድኖአችኋልና፡፡›› ከዚህ የእግዚአብሄር ቃል
የእግዘአብሄርን ጥልቅ አሳብ መረዳት ያስፈልገናል፡፡ ስለዚህ ቃሉ እንዲህ ይላል፡-

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በእምነት ሕይወታችን ውስጥ የእግዚአብሄርን ሥልጣንና ጸጋ መቀበል አለብን 131

‹‹ጸጋው በእምነት አድኖአችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሄር ስጦታ ነው እንጂ ከእናንተ


አይደለም፡፡›› (ኤፌሶን 2፡8)
ኤፌሶን ምዕራፍ 2 ቁጥር 8 እና 9 እንዲህ ይነበባል፡- ‹‹ማንም እንዳይመካ
ከሥራ አይደለም፡፡ እኛ ፍጥረቱ ነንና፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሄር አስቀድሞ
ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን፡፡›› እንዲህም
ደግሞ ተብሎዋል፡- ‹‹እርሱ ሰላማችን ነውና፤ ሁለቱን ያዋሃደ፣ በአዋጅ
የተነገሩትንም የትዕዛዛትንም ሕግ ሽሮ በመካከል ያለውን የጥል ግድግዳን በሥጋው
ያፈረሰ፣ ይህም ከሁለታቸው አንድን አዲስን ሰው በራሱ ይፈጥር ዘንድ፣ ሰላምንም
ያደርግ ዘንድ፣ ጥልንም በመስቀሉ ገድሎ በእርሱ ሁለታቸውን በአንድ አካል
ከእግዚአብሄር ጋር ያስታርቅ ዘንድ ነው፡፡ መጥቶም ርቃችሁ ለነበራችሁ ለእናንተ
ሰላምን ቀርበው ለነበሩትም ሰላምን የምሥራች ብሎ ሰበከ፡፡ በአርሱ ሥራ ሁላችን
ወደ አብ መግባት አለንና፡፡ እንግዲያስ ከእንግዲህ ወዲህ ከቅዱሳን ጋር ባላገሮችና
የእግዚአብሄር ቤተ ሰዎች ናችሁ እንጂ እንግዶችና መጻተኞች አይደላችሁም፡፡››
(ኤፌሶን 2፡14-19) በዚህ የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ መሠረት እኛ የሐጢያቶችን
ስርየት መቀበልና የእግዚአብሄር ልጆች መሆን የምንችለው በእግዚአብሄር ቃል ላይ
ባለ እምነት አማካይነት ነው፡፡

እኛ ከዓለም ሐጢያቶች የዳንነው በእግዚአብሄር ቃል እምነት ነው፡፡

እናንተና እኔ የእግዚአብሄር ልጆች የሆንነው መልካምንና ክፉን


ከሚያስታውቀው ዛፍ በመብላት ሳይሆን እግዚአብሄር በሰጠን የውሃና የመንፈስ
ወንጌል በማመን ብቻ ነው፡፡ ስለዚህ እናንተና እኔ ጻድቅ በሆነው የእግዚአብሄር
ቃል በማመንና ከሐጢያቶቻችን ሁሉ በመዳን አዲስ ሕይወትን አግኝተናል፡፡ ሰዎች
ምንም ቢሉም እምነታችን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ላይ ነው፡፡ በውስጣችን
ለሚኖረው የእግዚአብሄር ቃል ምስጋና ይሁንለትና ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ድነናል፡፡
በሌላ አነጋገር በውስጣችን የሚኖረው መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡ እርሱ እንዲህ በማለት
ይመሰክርልናል፡- ‹‹እናንተ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት ከዓለም
ሐጢያቶች ድናችኋል፡፡ አሁን የእግዚአብሄር ቅዱሳን ናችሁ፡፡›› የእግዚአብሄር ልጅ
መንፈስ የሆነው መንፈስ ቅዱስ በልቦቻችን ውስጥ አለ፡፡ እግዚአብሄር አብንም
‹‹አባ አባት›› ብለን እንድንጠራው ፈቅዶልናል፡፡ ምክንያቱም እርሱ ከዓለም
ሐጢያቶች ታድጎናልና፡፡ ከጨለማው ሐይል የዳኑ የእግዚአብሄር ሰዎች አሁን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


132 በእምነት ሕይወታችን ውስጥ የእግዚአብሄርን ሥልጣንና ጸጋ መቀበል አለብን

አዲስ ሕይወት አላቸው፡፡


የኢየሱስ ክርስቶስን ጽድቅ ከማወቃችንና ከማመናችን በፊት ለክርስቶስ
እንግዶች ነበርን፡፡ በሐጢያቶቻችን ምክንያትም ለኩነኔ የተገዛን ነበርን፡፡
በእግዚአብሄር መንግሥት ውስጥም አህዛቦች ነበርን፡፡ ከዚህ ቀደም ስጋዊ አካላችን
ከክርስቶስ ውጪ ነበር፡፡ እኛም በትውልድ የአብርሃም ዘሮች አልነበርንም፡፡
ከእግዚአብሄር ኪዳንና ከጸጋውም ውጪ ነበርን፡፡ ቢሆንም እግዚአብሄር
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ቃል አዳነን፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ከዓለም ሐጢያቶች ለማዳን ከአጥማቂው ዮሐንስ
በተቀበለው ጥምቀት ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ወሰደ፡፡ ራሱን ለመስቀል አሳልፎ
በመስጠትም ከሐጢያቶች ፍርድ ሁሉ ታደገን፡፡ በዚህም ከሙታን በመነሳትና
በእግዚአብሄር ዙፋን ቀኝ በመቀመጥ ደህንነታችንን ለአንዴና ለመጨረሻ
ፈጸመው፡፡ እግዚአብሄር ልጅነትን በተባረከው የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል
ለሚያምኑ ሰዎች በረከት አድርጎ ሰጥቶዋል፡፡ በኢየሱስ ክርስቶስ ጽድቅ በማመን
የእግዚአብሄር ልጆች መሆን የቻልነው እንዲህ ነው፡፡ በእግዚአብሄር ቃል
በማመንም የዘላለምን ሕይወት አግኝተናል፡፡
የዳንነው በሥራዎቻችን ምክንያት አይደለም፡፡ ሐጢያቶቻችንን
የምናውቅባቸው ትዕዛዛቶች ከዓለም ሐጢያቶች ሊያድኑን አይችሉም፤ እኛ
አንዳቸውንም የእግዚአብሄር ትዕዛዛት ፈጽመን መጠበቅ የማንችል ረዳተ ቢስ
ነበርን፡፡ እኛ በእግዚአብሄር ትዕዛዛት አማካይነት ሐጢያቶቻችንን ተገንዝበን
በኢየሱስ ክርስቶስ ጽድቅ በማመን ለአንዴና ለመጨረሻ ደህንነትን ተቀብለናል፡፡
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የምናምነው እናንተና እኔ በዚህ መልኩ የእግዚአብሄር
መንግሥት ዜጎች ሆነናል፡፡ ማንም ሰው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን
የእግዚአብሄር ልጅ ሊሆን እንደሚችል እኛ ማስረጃ ነን፡፡ ከሐጢያቶቻችን ሁሉ
ድነን የእግዚአብሄር ልጆች ከሆንን በኋላም እንኳን ትክክለኛውን እምነታችን
ጠብቀን ማቆየት አለብን፡፡ በሐጢያቶቻችንና በበደሎቻችን ምክንያት ከመጥፋት
በቀር ሌላ መንገድ ባልነበረን ጊዜ ኢየሱስ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ማስወገዱን በሚያምነው እምነት መኖራችንን
እንቀጥላለን፡፡ በሌላ አነጋገር የኢየሱስ ክርስቶስ ጽድቅ በሆነው በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል በሚያምነው እምነት የእግዚአብሄር ልጆች ሆነን መኖር
ጀምረናል፡፡
የዳንነው በዚህ እምነት ብቻ ስለሆነ በእነዚህ የመጨረሻ ቀናቶች በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል በሚያምነው በዚህ እምነት ጸንተን መቆም ያስፈልገናል፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በእምነት ሕይወታችን ውስጥ የእግዚአብሄርን ሥልጣንና ጸጋ መቀበል አለብን 133

እግዚአብሄር በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ያስወገደ


በመሆኑ እምነት ድነናል፡፡ ስለዚህ መልካም ሥራዎቻችንን ትተን ከዓለም
ሐጢያቶች ሁሉ መዳናችንን እነዚህን ማረጋገጫዎች መያዝ ያስፈልገናል፡፡ በዚህ
መንገድ ብቻ በእግዚአብሄር የደህንነት ጸጋ ጠንክረን መቆም እንችላለን፡፡ አሁን
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን የእግዚአብሄር ሕዝብ መሆናችንን
በሚያምነው እምነት ልንኖር ይገባናል፡፡
አሁን የእግዚአብሄር ልጆች ስለሆንን ተግባራችን ምንድነው? የዳንበትን
የእግዚአብሄር ጸጋ ወንጌል፣ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል መስበክ ነው፡፡ ዋናው
ተልዕኮዋችን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በመላው ዓለም መስበክ ነው፡፡ አሁን
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል እንድንሰብክ ተደርገናል፡፡ በዚህ ዓለም ላይ ለስጋዊ
ሥራዎቻችን ብቻ ከመኖር ይልቅ ሌሎች ነፍሳቶችንም ከሐጢያቶቻቸው ለማዳን
መኖር ይገባናል፡፡
እኛ አብዛኛውን ጊዜ በራሳችን የክፋት ባህሪዎች እንተበተባለን፡፡ በሌላ ሰው
ድክመቶችም እንጠመዳለን፡፡ እውነተኛ ደህንነት ያመጣልን ሌላ ምንም ነገር
ሳይሆን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምን እምነት ነው፡፡ እግዚአብሄር
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለእኛ የሰጠበት ብቸኛው ምክንያት አዲስ ሕይወት
እንድናገኝ ነው፡፡ በሌላ አነጋገር እኛ በኢየሱስ ክርስቶስ ጽድቅ በማመን ደህንትን
ተቀብለናል፡፡ የዳንነው በመስቀሉ ደም ብቻ በሚያምነው እምነታችን ላይ
የራሳችንን መልካም ምግባሮች በማከል አይደለም፡፡ በራሳችን መልካም ምግባሮች
ደህንነትን ለማግኘት ሞክረን ቢሆን ኖሮ በእርግጠኝነት አይሳካልንም ነበር፡፡
ታዲያ ከሐጢያቶቻችሁ ሁሉ እንደዳናችሁ ልትናገሩ ትችላላችሁ? ያንን
ብቻችሁን ልታደርጉት አትችሉም፡፡ እግዘአብሄር ከፍጥረቱ መጀመሪያ ጀምሮ
ያስጠነቀቀን ለዚህ ነው፡፡ እግዚአብሄር ‹‹ነገር ግን መልካምንና ክፉን
ከሚያስታውቀው ዛፍ አትብላ፤ ከእርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህና›› ብሎ
አስጠንቅቆ ሳለ ክርስቲያኖች በእምነታቸው ላይ የራሳቸውን መልካም ምግባሮች
ለመጨመር ይሞክራሉ፡፡ በሕግ ላይ የተመሰረተ እምነትን በመሻት በግትርነት
ደህንነታችን ላይ ለመድረስ ሲፍጨረጨር የነበረውን በሞት አፋፍ ላይ ያለውን
ነፍሳችንን ሕያው ለማድረግም ደግሞ ጥረናል፡፡ ነገር ግን በራሳችን መልካም
ሥራዎች ላይ ስንመረኮዝ በእርግጠኝነት እንደምንሞት ማወቅ አለብን፡፡ ሕጉ እዚያ
ያለው ሐጢያቶቻችንን እንድናውቅ ነው፡፡ ሕጉ በጭራሽ ሐጢያቶቻችንን
ማስወገድ አይችልም፡፡
እግዚአብሄር በዘፍጥረት 2 ላይ መልካምንና ክፉን ከሚያስታውቀው ዛፍ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


134 በእምነት ሕይወታችን ውስጥ የእግዚአብሄርን ሥልጣንና ጸጋ መቀበል አለብን

ፍሬ መብላት እንደማይገባን ሲናገር ከእግዚአብሄር ፍጹም የሆነ የመልካምና የክፉ


መስፈርት ሌላ የራሳችንን ሰብዓዊ የመልካምና የክፉ መስፈርት መፍጠር የለብንም
ማለቱ ነው፡፡ ስለ መልካምና ክፉ መናገር የሚችለው እግዚአብሄር ብቻ ነው፡፡
ፍጹም መልካም የሆነው ነገር በእግዚአብሄር ፊት በጎ የሆነው ብቻ ነው፡፡
እግዚአብሄር አንድን ነገር መልካም ነው ብሎ ከጠራው በእርግጠኝነት መልካም
ነው፡፡ እርሱ አንድን ነገር ክፉ ነው ብሎ ከጠራው በእርግጠኝነት ክፉ ነው፡፡
የራሳችንን የሕሊና መለኪያ በመጠቀም በመልካምና በክፉ መካከል መበየን
አይገባንም፡፡ እግዚአብሄር መልካምንና ክፉን ከሚያስታውቀው ዛፍ እንዳንበላ
የነገረን ለዚህ ነው፡፡ ይህ ማለት ፍጹም ሕላዌ የሆነውን የእግዚአብሄር ቃል
መቀበል አለብን ማለት ነው፡፡ እግዚአብሄር ዕረፍትንና ሰማይን ሁሉ ስጦታዎች
አድርጎ እንደሰጠንም በእምነት እንድንቀበል ይፈልጋል፡፡ መልካም ሥራዎቻችንን
መጨመራችን እኛን የማንረባውን ሐጢያተኞች በእግዚአብሄር ፊት ጻድቃን
አያደርገንም፡፡

ደህንነታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አስቀድሞ ተወስኖዋል፡፡

ሐዋርያው ጳውሎስ በኤፌሶን 1፡4 ላይ እንዲህ አለ፡- ‹‹ዓለም ሳይፈጠር በፊቱ


ቅዱሳንና ነውር የሌለን በፍቅር እንሆን ዘንድ በክርስቶስ መረጠን፡፡›› እግዚአብሄር
አብ እኛን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የምናምነውን ሰዎች በልጁ በኢየሱስ
ክርስቶስ ቅዱሳንና ሐጢያት አልባ አድርጎናል፡፡ በመንፈሳዊ አነጋገር እርሱ
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል እንድናምን በማድረግ የሐጢያቶችን ስርየትና
የዘላለምን ሕይወት ሰጥቶናል፡፡ አሁን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን
ደህንነትን ስለተቀበልን ማድረግ የሚኖርብን ነገር ቢኖር እውነተኛውን ወንጌል
መስበክ ነው፡፡ አሁን በልቦቻችን ውስጥ ባለው ዕረፍት መደሰትና ከእግዚአብሄር
የመጡትን በረከቶች በእምነት ለሌሎች መስበክ ነው፡፡
ከእግዚአብሄር የመጣው ደህንነትና በሰማይ የምናገኘው ነገር ሁሉ
የእግዚአብሄር ስጦታዎች ናቸው፡፡ እግዚአብሄር በዘላለማዊው መንግሥተ ሰማይ
ውስጥ እንኖር ዘንድ ከዘመን አስቀድሞ በኢየሱስ ክርስቶስ መርጦናል፡፡ አስቀደሞ
የተወሰነው ምንድነው? እግዚአብሄር በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል እኛን ሐጢያት
አልባ በማድረግ እውነተኛ ዕረፍት ሊሰጠን አስቀድሞ ወሰነ፡፡ በሌላ አነጋገር እኛን
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የምናምነውን አማኞች መንግሥተ ሰማይ እንድንገባና

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በእምነት ሕይወታችን ውስጥ የእግዚአብሄርን ሥልጣንና ጸጋ መቀበል አለብን 135

በዚያ ለዘላለም እንድንኖር አስቀድሞ ወሰነን፡፡ ስለዚህ በውሃውና በመንፈሱ


ወንጌልና በኢየሱስ ደም ማመን አለብን፡፡ እግዚአብሄር በጎ ነገሮችን ሁሉ ከሰማይ
እንደሰጠን የሚያምን እምነት ሊኖረን ይገባል፡፡ (ያዕቆብ 1፡17) እግዚአብሄር
ከዓለም ፍጥረት በፊት ፈጠረን፡፡ እንኖርበት ዘንድም የአምላክን መንግሥት
አዘጋጀልን፡፡ እርሱ ዩኒቨርስን ከመፍጠሩ በፊትም እንኳን እኛን መላውን የሰዎች
ዘር በኢየሱስ ለማዳን አስቀድሞ ወሰነን፡፡ እርሱ ቀድሞውኑም በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል ከሐጢያቶቻችን ሁሉ አድኖናል፡፡

ከሐጢያቶች ሁሉ የመዳን ውጤት ምንድነው?

እኛ የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል የደህንነት ስጦታ ሆኖ ተሰጥቶናል፡፡ በዚህ


የተነሳ የእግዚአብሄር ልጆች ሆነን የሰማይን ክብር ማመስገን እንችላለን፡፡ ጌታ
የእግዚአብሄርን ጽድቅ እንድናመሰግንና እርሱን የሚያከብር ሕይወት እንድንኖር
ፈቅዶልናል፡፡ እግዚአብሄር ከዓለም ሐጢያቶች ያዳነን ለዚህ ነው፡፡
ቃሉ እንዲህ ይላል፡- ‹‹በውድ ልጁም እንደ ጸጋው ባለጠግነት መጠን በደሙ
የተደረገ ቤዛነታችንን አገኘን፤ እርሱም የበደላችን ስርየት፡፡›› (ኤፌሶን 1፡7)
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን የሐጢያቶችን ስርየት ተቀብላችኋልን?
በእምነት ከሐጢያቶቻችሁ ሁሉ ደህንነትን ከተቀበላችሁ ጀምሮ ፍጹም የሆነ
ሕይወትን እየኖራችሁ ነውን? የለም፤ እየኖርን አይደለም፡፡ ‹‹እንደዚህ ዓይነት
ሕይወት መኖር ብንችልም አንኖርም›› በሚለውና ‹‹ስለማንችል ይህንን ማድረግ
አንችልም›› በሚለው መካከል ልዩነት አለ፡፡ ፍጹም የሆነ ሕይወት የመኖር ችሎታ
እንደሌለን ስለምናውቅ እግዚአብሄር በእርሱ ጽድቅ ላይ እንድንደገፍ ነግሮናል፡፡
እርሱ ፍጹም የሆነ ሕይወትን መኖር እንደማንችል ስላወቀ በእምነት እንድንኖር
አዘዘን፡፡ በሌላ አነጋገር በትሩፋታችን ደህንነትን አናገኝም፡፡ ደህንነታችንን ማግኘት
የምንችለው በእምነት ብቻ ነው፡፡
እናንተና እኔ በእግዚአብሄር ጽድቅ በማመን ለአንዴና ለመጨረሻ ድነናል፡፡
ያም ማለት እኛ በሐዋርያትና በነቢያት መሠረት ላይ ታንጸናል፡፡ የኢየሱስ ደቀ
መዛሙርቶችም እንደዚሁ የዳኑት በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን ነው፡፡
ለመዳን በዚህ ላይ ከሥራዎቻቸው አንዳቸውንም ሌላው ቀርቶ 0.1 ከመቶ እንኳን
አልጨመሩም፡፡ ሐዋርያት ‹‹መልካም አደርግ፤ ሰናይ ሕይወት ኑር፤ ትዕዛዛትን
ጠብቅ›› ስለሚሉ የሕግ ተግባራቶች አልተናገሩም፡፡ እነርሱም ደግሞ በውሃውና

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


136 በእምነት ሕይወታችን ውስጥ የእግዚአብሄርን ሥልጣንና ጸጋ መቀበል አለብን

በመንፈሱ ወንጌል አመኑ፡፡ ምስጋና ይድረሳቸውና እኛም ከሐጢያቶቻችን ሁሉ


ድነን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በሚያምነው ተመሳሳይ እምነት ላይ ታንጸናል፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስም የደህንነታችን የማዕዘን ድንጋይ ሆንዋል፡፡ አስታራቂው ኢየሱስ
እኛን ከእግዚአብሄር ጋር የሚያገናኘን የማዕዘን ድንጋይ ሆኖ ራሱን አኖረ፡፡
ዛሬ የማዕዘን ድንጋይ ምን እንደሆነ አይገባችሁ ይሆናል፡፡ በአሁኑ ጊዜ የአንድ
ሕንጻን መሠረት ለማያያዝ ጥቅም ላይ የሚውለው ሲሚንቶ በመሆኑ የማዕዘን
ድንጋይን ተግባር መረዳት አስቸጋሪ ነው፡፡ በእያንዳንዱ የሕንጻ ማዕዘን ላይ
ኮንክሪት ጥቅም ላይ ስለሚውል የማዕዘን ድንጋይ አያስፈልግም፡፡ ነገር ግን በዚያ
ዘመን የኮንክሪት መሠረቶች ያሉዋቸው ቤቶች አልነበሩም፡፡ ሰዎች መሬቱን
ይቆፍሩና በእያንዳንዱ የማዕዘን ድንጋይ ላይም የእንጨት ወይም የድንጋይ አእማድ
ያኖራሉ፡፡ ስለዚህ የማዕዘን ድንጋዮች ሁሉንም ሕንጻ ያገናኛሉ፡፡ በዚህ ምክንያት
ብቻ የማዕዘን ድንጋዮች የአንድ ግንባታ እጅግ አስፈላጊ ክፍል ናቸው፡፡ ወደ ገጠር
ብትሄዱ ጥቂት በማዕዘን ድንጋይ የተሰሩ ቤቶችን እንደምታገኙ አያጠራጥርም፡፡
ይህች የቹንቺኦን ከተማም እንደዚሁ ብዙ ጥንታዊ ቤቶች አሉዋት፡፡ ሰዎች
ትውፊታዊ ቤት በሚሰሩበት ጊዜ ትልልቅ ዓለቶችን ያኖሩና በእነዚህ የማዕዘን
ድንጋዮች ላይ አእማዶችን ያያይዛሉ፡፡ ስለዚህ የቤቱን ቅርጽ ለማስተካከል ሲፈልጉ
በርካታ ሰዎች በእነዚህ የማዕዘን ድንጋዮች ላይ ያረፉትን አራቱን አእማዶች
ያነሱዋቸዋል፡፡
ልክ እንደዚሁ አስታራቂው ኢየሱስም ሰዎችን ከእግዚአብሄር ጋር ያገናኛል፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱ የማዕዘን ራስ ድንጋይ እንደሆነ ነግሮናል፡፡
በጽድቅ ሥራዎቹ አማካይነት ለተፈጸመው የኢየሱስ ክርስቶስ ቤዛነት ምስጋና
ይሁንና እኛ የእምነት ደህንነትን ተቀብለናል፡፡ በአንድ ቤት ግንባታ አንጻር ስንናገር
እናንተና እኔ ሁላችንም እርስ በርሳችን ተቆራኝተናል፡፡ ቀደም ብለው የዳኑ ሰዎችና
በኋላ የዳኑ ሰዎች ተጣምረው በጌታ ቅዱስ መቅደስ ለመሆን ይሰራሉ፡፡ ቀደም
ብለው የሐጢያቶችን ደህንነት አግኝተው አሁን በእግዚአብሄር ያሉ ሰዎችና ገና
ደህንነትን ያላገኙ ሰዎች አንድ ይሆኑና በመጨረሻ ከመንግሥተ ሰማይ ጋር
ይያያዛሉ፡፡ እግዚአብሄር በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በምናምን ሰዎች ውስጥ
እንደሚኖር የታወቀ ነው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በእምነት ሕይወታችን ውስጥ የእግዚአብሄርን ሥልጣንና ጸጋ መቀበል አለብን 137

የእግዚአብሄርን ሥልጣን ተቀበሉ፡፡

በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ መጀመሪያ ልትማሩት የሚገባችሁ ነገር


ቢኖር የእግዚአብሄርን ሥልጣን መቀበል ነው፡፡ በእግዚአብሄር የተሰጡ
ሥልጣኖችን መቀበል አለብን፡፡ ሰዎች የሐጢያቶችን ስርየት ከተቀበሉ በኋላ
መለያየትን አጥብቀው ይጠላሉ፡፡ የሐጢያቶቻቸውን ስርየት የተቀበሉ ሰዎች
ሌሎችን በአግድመታዊዎቹ ሰብዓዊ ግንኙነቶች ማስተናገድ ይፈልጋሉ፡፡
ሆኖም እግዚአብሄር የስርዓት አምላክ ነው፡፡ ይህ የስርዓት አምላክ በብሉይ
ኪዳን ውስጥ እንዲህ አስጠንቅቆናል፡- ‹‹ነገር ግን መልካምንና ክፉን
ከሚያስታውቀው ዛፍ አትብላ፤ ከእርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህና፡፡››
(ዘፍጥረት 2፡17) እግዚአብሄር ለእኛ ፍጹም አምላክ ነው፡፡ ስለዚህ እግዚአብሄር
መልካም ነው ብሎ የጠራው መልካም ነው፤ እግዚአብሄር ክፉ ነው ብሎ
የጠራውም ክፉ ነው፡፡
ይህ ማለት እኛ የእግዚአብሄርን ሥልጣን መቀበል አለብን ማለት ነው፡፡
ከሐጢያቶቻቸው የዳኑ ሁሉ የእግዚአብሄርን ሥልጣን መቀበል አለባቸው፡፡
በትክክል ለመናገር ያህል ቢድኑም ሆነ ባይድኑ ሁሉም ለእግዚአብሄር ሥልጣን
መገዛት አለባቸው፡፡ ራሳችሁን ለእግዚአብሄር ሥልጣን የማታስገዙ ከሆናችሁ
መቼም ቢሆን ከሐጢያት መዳን አትችሉም፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሄር ቃል
እንደሆነ ታምናላችሁን? እግዚአብሄር በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንደተጻፈው
ደህንነታችንን እንደፈጸመ ታምናላችሁን? የእግዚአብሄርን ሥልጣን ከተቀበላችሁ
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን በዚህ የእግዚአብሄር ቃል ማመንና
የሐጢያቶቻችሁን ሁሉ ደህንነት መቀበል ትችላላችሁ፡፡
አለበለዚያ እግዚአብሄር ወደዚህ ምድር መጥቶ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
ቢያድነንም ደህንነትን አንቀበልም፡፡ የእግዚአብሄርን ሥልጣን የሚንቁና የማያምኑ
ሰዎች እንዴት ደህንነትን ሊቀበሉ ይችላሉ? የእግዚአብሄርን ሥልጣን አለመቀበል
ማለት የእግዚአብሄርን ሕልውና መካድ ነው፡፡ ስለዚህ በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል የተሰጠውን ደህንነት መቀበል አያስችልም፡፡ እነዚህ ሰዎች ከጅማሬው
አዲስ ሕይወት ለመኖር ሌላ ዕድል ቢኖራቸው እንኳን በጭራሽ ከሐጢያቶቻች
ሊድኑ አይችሉም፡፡ ስለዚህ ለእግዚአብሄር ሥልጣን መገዛት ያስፈልገናል፡፡
ለእግዚአብሄር ሥልጣን የሚገዙ ሰዎች በእምነት የሐጢያቶቻቸውን ሁሉ
ደህንነትና የእግዚአብሄርን በረከቶች ሁሉ መቀበል ይችላሉ፡፡ ከዚህም ባሻገር
እምነታቸውን ተዝናንተው መኖር ይችላሉ፡፡ በእምነት የሐጢያቶቻችንን ደህንነት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


138 በእምነት ሕይወታችን ውስጥ የእግዚአብሄርን ሥልጣንና ጸጋ መቀበል አለብን

እስከተቀበልን ድረስ ሁላችንም የንጉሥ ካህናት እንሆናለን፡፡ (1ኛ ጴጥሮስ 2፡9)


የመጀመሪያው የጴጥሮስ መጽሐፍ እናንተ የንጉሥ ካህናት እንደሆናችሁ ይናገራል፡፡
ስለዚህ ማንኛውም ዳግመኛ የተወለደ ቅዱስ ሰው በቅዱሱ አምላክ ፊት በድፍረት
መቅረብ ይችላል፡፡
በነገራችን ላይ ቅዱሳኖች ሁሉ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት
የሐጢያት ደህንነታቸውን ከተቀበሉ በኋላ እኩል ማዕረግ ይኖራቸዋልን? የለም፤
አይኖራቸውም፡፡ በመንግሥተ ሰማይ ውስጥ ነገሥታቶችና አገልጋዮች እንዳሉ
ተነግሮዋል፡፡ በዚያ ጥብቅ የሆነ መንፈሳዊ ሥልጣን አለ፡፡ እግዚአብሄር
በቤተክርስቲያን ውስጥ የመሰረተው መንፈሳዊ ስርዓት አለ፡፡ በአጭሩ እግዚአብሄር
የመሰረተውን ይህንን ስርዓት መቀበል አለብን፡፡ ለእግዚአብሄር ስርዓት ስንገዛ
የእምነትን ሕይወት መኖር ሰላማዊ ነው፡፡ ለእምነት ቀደምቶቻችሁ ስትገዙ
ከእናንተ በኋላ በሚመጡት ላይ ሥልጣን ይኖራችኋል፡፡
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን ደህንነትን የተቀበለ አንድ ሰው አለን
እንበል፡፡ እርሱ ከእርሱ የቀደማችሁትን እናንተን ሳያዳምጥ ማድረግ የሚፈልገውን
ሁሉ የሚያደርግ ከሆነ አትበሳጩምን? በጣም ትረበሻላችሁ፡፡ ዓለማዊ
ዕውቀታችሁን ወደ ቤተክርስቲያን ይዛችሁ በመግባት ብቻችሁን መልካሙ ወይም
ክፉው ምን እንደሆነ እየተናገራችሁ ቀደምቶቻችሁን በዓለም መለኪያ የምትፈርዱ
ከሆነ ትክክለኛውን ነገር እያደረጋችሁ ነውን? አይደለም፡፡ እነዚህ ሰዎች አሳፋሪዎች
አይመስሉዋችሁምን? እናንተና እኔ ሁለታችንም አስተማሪዎች መሆን እንችላለን?
ሁለታችንም ለማስተማር ብንሞክርና ማንም ሰው መማር ባይፈልግ መንፈሳዊ
ጦርነት ይፈጠራል፡፡
እግዚአብሄር ለሰዎች ያቆመው የመጀመሪያው ነገር ሐጢያቶች ማለት ምን
ማለት እንደሆነ ለእኛ ለማስተማር ሕጉን ማቋቋም ነበር፡፡ በሕጉ መዳን
እንደማንችል ነገር ግን ሐጢያቶቻችንን ማወቅ እንደምንችል አስተምሮናል፡፡
ከዚያም በኢየሱስ ጽድቅ በማመን እንዴት ደህንነትን እንደምንቀበል አሳየን፡፡
ከዚህ አስቀድሞ እግዚአብሄር ሥልጣኑን አጸና፡፡ ‹‹እኔ ያለሁና የነበርሁ ነኝ፡፡
እኔ ፍጹም ሕላዌ ነኝ፡፡ ቃሌም እውነት ነው፡፡ እኔ መልካም ነው የምለው ነገር
መልካም ነው፡፡ እኔ ክፉ ነው የምለውም ክፉ ነው፡፡ እናንተ ክፉዎች እንጂ
መልካሞች አይደላችሁም፡፡ ሥልጣኔን ልትቀበሉ ይገባችኋል፡፡ እኔ አምላካችሁ
ነኝ፤ እኔ የሆዋ ነኝ፡፡›› እግዚአብሄር ይህንን እየነገረን ነው፡፡
የሐጢያቶቻችንን ስርየት ከተቀበልን በኋላ የእምነት ሕይወታችንን መኖር
ማለት የእግዚአብሄርን ሥልጣን መቀበል ማለት ነው፡፡ እግዚአብሄር ያጸናቸውን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በእምነት ሕይወታችን ውስጥ የእግዚአብሄርን ሥልጣንና ጸጋ መቀበል አለብን 139

ሥልጣኖች መቀበል ያለብን ለዚህ ነው፡፡ እግዚአብሄር በአምላክ ቤተክርስቲያን


ውስጥ በስርዓት እንድንኖር ፈቅዶልናል፡፡ በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ
የተቀመጠውን ስርዓት የምንቀበል ከሆነ እግዚአብሄርም ከፍ ያደርገናል፡፡
ደህንነታችን የተፈጻመው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ማለትም በእግዚአብሄር
ወንጌል አማካይነት ነው፡፡ እኛ በዚህ የእግዚአብሄር ወንጌል በማመን ደህንነትንና
የዘላለምን ሕይወት ተቀብለናል፡፡ እኛ ኢየሱስ በሰጠን ውሃና ደም በማመን
የእግዚአብሄር ልጆች ሆነናል፡፡
ደህንነታችንን ያገኘነው በሥራዎቻችን አማካይነት አይደለም፡፡ በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል የሚያምኑ ሰዎች እርስ በርሳቸው የሚጋጠሙትና የእግዚአብሄር
መንግሥት ለመሆን የሚያድጉት እንዲህ ነው፡፡ እኛ ከእግዚአብሄር ሥልጣን በታች
እየተገዛን እምነታችንን አብረን በመኖር ላይ ነን፡፡ ስለዚህ ከእግዚአብሄር
ቤተክርስቲያን ጋር ስትቀላቀሉ ከእናንተ ቀድመው ደህንነትን የተቀበሉ ወንድሞችና
እህቶች አሉ፡፡ ከእነርሱ መማርና ከእነርሱም ጋር ሕብረት ማድረግ
ያስፈልጋችኋል፡፡ በእነርሱም መመራት ተገቢ ነው፡፡ ‹‹አንተ ከእኔ ትበልጣለህን?
ምን የሚያመጻድቅ ነገር አለህ? እኔን ለማስተማር የምትሞክርና የማደርገውን ነገር
ሁሉ የምትነቅፍ አንተ ማነህ? በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን መዳኔ ለእኔ
መልካም ነገር ነው፡፡ ነገር ግን በቆሰለ የማንነት ክብር የእምነት ሕይወቴን መኖር
አልችልም›› በሚሉት ሰብዓዊ አስተሳሰቦቻችሁ ላይ ተመሰርታችሁ በእነርሱ ላይ
እንደማትፈርዱ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡
እግዚአብሄር እንደዚህ ልታስቡ እንደምትችሉ በማወቁ እርሱ የስርዓት
አምላክ እንደሆነ ተናገረ፡- ‹‹ነገር ግን መልካምንና ክፉን ከሚያስታውቀው ዛፍ
አትብላ፤ ከእርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህና፡፡›› ይህ ማለት ቀደምቶቻችሁን
በራሳችሁ ጽድቅ ልትገዳደሩዋቸው አይገባም ማለት ነው፡፡ በሌላ አነጋገር
እግዚአብሄር ለሥልጣኑ እንድንገዛ አስጠንቅቆናል፡፡
ከእናንተ ቀደም ብለው ያመኑት ሰዎች በቤተክርስቲያን ውስጥ እንዴት
ተግተው እንደሰሩ አስባችኋልን? እናንተ የተወደዳችሁ የእግዚአብሄር ባሮችና
ቅዱሳን በሙሉ ከሐጢያት ከዳናችሁ በኋላ በቤተከርስቲያን ውስጥ ምን ያህል
ተግታችሁ ሰርታችኋል? በቤተክርስቲያን ውስጥ ድካምንና አሳዛኝ ሁኔታዎችን
ለምን ያህል ጊዜ ተቋቋማችሁ? በስጋዊ ዓይኖቻችን ሁላችንም እኩል ነን፡፡
በመንፈሳዊ ዕይታ ግን ግልጥ የሆነ የተዋረድ ሥልጣን አለ፡፡ በእግዚአብሄር
ቤተክርስቲያን ውስጥ መንፈሳዊ ስርዓት አለ፡፡
ሆኖም ዓለማዊ ቤተክርስቲያኖች ባለጠጋ ለሆኑ ወይም የሐብታም

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


140 በእምነት ሕይወታችን ውስጥ የእግዚአብሄርን ሥልጣንና ጸጋ መቀበል አለብን

ኩባንያዎች ሥራ አስኪያጅ በመሆን ከፍተኛ የሥልጣን ቦታዎችን ለያዙ ሰዎች


ከፍተኛ የሥልጣን ቦታዎችን ይሰጡዋቸዋል፡፡ አንዳንድ ፕሮፌሰሮች ወይም
ዶክተሮች ዲያቆናት ወይም ሽማግሌዎች ሆነው በቀላሉ ይሾማሉ፡፡ የስም
ክርስቲያኖች ቢሆኑም እንኳን ድጋፍ ሰጪ ከሆኑ ከፍ ያሉ የሥልጣን ቦታዎች
ይሰጡዋቸዋል፡፡ ቀረብ ብላችሁ ተመልከቱዋቸው፡፡ እንዲህ ካለው አጭበረባሪ
ዓለም ጋር አትተዋወቁ ይሆናል፤ እኔ ግን አሳምሬ አውቀዋለሁ፡፡
ይህ የሥልጣን ተዋረድ ከእግዚአብሄር የተሰጠ አይደለም፡፡ ይህ የሥልጣን
ተዋረድ የተገነባው በሰብዓዊ ሥልጣን ነው፡፡ ይህ ትክክል እንደልሆነ ግልጥ ነው፡፡
በሌላ በኩል በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ ያሉ ቅዱሳኖች በቤተክርስቲያን
ውስጥ ያለውን የሥልጣን ተዋረድ እንዲያከብሩና ትክክለኛ የእምነት ሕይወት
እንዲኖሩ ተነግሮዋቸዋል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ቤተክርስቲያን ማንኛውንም ስጋዊ ሰው
በማናቸውም የክብር ቦታ ላይ መሾም እንደማይገባት ይናገራል፡፡ ውድ አጋር
ክርስቲያኖች ቀደም ብላችሁ ከሐጢያት ደህንነትን ተቀብላችሁ ከሆነ የእምነት
ቀደምቶቻችሁን ልትንቁ አይገባችሁም፡፡ ሁሌም ስጋዊ አስተሳሰቦቻችሁን
በመካዳችሁ ከሐጢያት ከዳናችሁ በኋላ በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ
ትኖራላችሁ፡፡ የእግዚአብሄርን የሥልጣን ተዋረድ እስካልተከተላችሁ ድረስ
በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ መኖር አትችሉም፡፡
አንድ ሰው ከእናንተ በፊት ደህንነትን ከተቀበለና በቤተክርስቲያን ውስጥም
ጌታን ለአንድ ዓመት ካገለገለ የበላያችሁ አድርጋችሁ ተቀበሉት፡፡ በእግዚአብሄር
ቤተክርስቲያን ውስጥም ለመቆየት ሞክሩ፡፡ በቀደምቶቻችሁ አገዛዝ ሥር መሆንና
ቤተክርስቲያን እንድታደርጉ የምትነግራችሁን ሁሉ ማድረግ ምን የህል አዳጋች
እንደሆነ ታውቃላችሁ፡፡ ታዲያ የቤተክርስቲያንን ትዕዛዝ ችላ ማለት ትችላላችሁን?
የለም አትችሉም፡፡ በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ እንድትኖሩ ያስቻላችሁ
ለእግዚአብሄር ሥልጣን መገዛታችሁ ነው፡፡ ስለዚህ ያንን ችላ ማለት
አይገባችሁም፡፡ ለረጅም ጊዜ የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን አባል ሆናችሁ
ቆይታችሁ ከሆነና ትልቅ እምነት ካላችሁ የምነግራችሁ ይገባችኋል፡፡ ኋለኛ የሆኑት
እናንተን ይከተሉ ይሆናል፤ ነገር ግን ከእናንተ በፊት የዳኑ ሰዎች ክብር ይገባቸዋል፡፡
በቅርቡ የዳኑ ነገር ግን የእግዚአብሄር አገልጋዮች ለመሆን እየሰለጠኑ ያሉ
አንዳንድ ቅዱሳን አሉ፡፡ አንዳንድ ሰዎች በጣም ስለሚመቀኙዋቸው ‹‹ያ ሰው
ከሦስት ወራት በፊት ከእኔ የማይሻል ነበር፤ ነገር ግን ድንገት ተነስቶ የእግዚአብሄር
አገልጋይ ለመሆን መሰልጠን ጀመረ፡፡ ይህ እርሱን ማናገር እንዲያስጠላኝ
አድርጎኛል፡፡ አሁን እኔንም እንኳን ሊያስተምረኝና ሊገዳደረኝ እየሞከረ ነው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በእምነት ሕይወታችን ውስጥ የእግዚአብሄርን ሥልጣንና ጸጋ መቀበል አለብን 141

እንዲያውም በእኔ ላይ እየሰለጠነ ነው፡፡ ይህ ተቀባይነት የለውም!›› በማለት


አይታዘዙዋቸውም፡፡

እግዚአብሄር ያጸናው ሥልጣን፡፡

እግዚአብሄር በቤተክርስቲየሰኑ ውስጥ ከሾማችሁ ወዲያውኑ ከፍ ትላላችሁ፡፡


ያ ማለት ግን ሥልጣናችሁን አለአግባብ መጠቀምና እናንተን በሚከተሉ ሰዎች ላይ
ጌታ መሆን ትችላላችሁ ማለት ነውን? እንዲያውም የቤተክርስቲያን መሪዎች
የእግዚአብሄርን ጽድቅ ወንጌል በጥቂቱ ሳይሆን በብዙ የሚያገለግሉ ሰዎች ናቸው፡፡
እነርሱ በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ ወራዶች አይደሉም፡፡ ይህንንም ጉዳይ
ደግሞ ልታውቁ ያስፈልጋችኋል፡፡ እግዚአብሄር ያጻነውን የሥልጣን ተዋረድ
ልትቀበሉ ይገባችኋል፡፡ በዚያ መንገድ የእምነት ሕይወታችሁን መኖር ቀላል
ይሆንላችኋል፡፡ ‹‹እግዚአብሄር ቀደምቶቼን በዚህ መልኩ ስለሾማቸው ለእነርሱ
መገዛትና ከእነርሱ ጋር መስማማት ያስፈልገኛል፡፡ እነርሱ እንዳደርገው ያዘዙኝን
ሳደርግ በትክክል እግዚአብሄርን እየታዘዝሁ ነው፡፡ ይህንን የማደርገው
እግዚአብሄርን ስለማምንና ስለምከተል ነው፡፡›› በእግዚአብሄር ፊት ትክክለኛው
እምነት ይህ ነው፡፡ በእግዚአብሄር ፊት ትክለኛ የሆነ ነገር እስካለ ድረስ ያንን
ማድረግና እንድናደርግ የተነገረንን ለማድረግ መገዛት ተገቢ ነው፡፡
ሆኖም በእግዚአብሄር ሳይሆን አብሮዋችሁ ባለ ሰው ስለመገዛታችሁ ስታስቡ
ለሰው መገዛት በጣም አዳጋች ነው፡፡ በእኛ አመለካከት ምንም ያህል ደካሞች
ብንሆንም ሁላችንም የራሳችን የሆነ መመጻደቂያ አለን፡፡ ሁሉም ሰው እኩል ሆኖ
እንደወተለደ የታወቀ ነው፡፡ ‹‹አንተ ከቀድሞውም ከእኔ የተሻልህ ነህ›› የሚባል ነገር
የለም፡፡ ሁሉም ሰው እኩል ነው፡፡ ስለዚህ በስጋዊ መንገድ ከሌሎች ጋር አግድመታዊ
ግንኙነት ሊኖረን ይገባል፡፡ በመንፈሳዊውም ዓለም ግን ግንኙነቶች በሙሉ ተዋረዳዊ
ናቸው፡፡ የእምነት ሕይወታችን ለዚህ እውነት መገዛት አለበት፡፡ ገባችሁ?
እግዚአብሄር ባጸናው መንፈሳዊ ስርዓት ላይ አታምጹ፡፡ በተለይም አረጋውያን
የሆናችሁ ሰዎች እባካችሁ በቤተክርስቲያን ውስጥ ስለ ዕድሜያችሁ መግፋት
አታውሩ፡፡ ‹‹ኦ ይህ ወጣት ሊያሰተምረኝ እየሞከረ ነው፤ እኔ ከአንተ በዕድሜ
እበልጣለሁ፡፡ መጽሐፍ ቅዱስን ምን ያህል አውቀህና አጥንተህ ነው የምትንቀኝ?
በጣም ታግሻለሁ፡፡ ነገር ግን ቆሻሻውን ቁጡነቴን ቀሰቀስከው፡፡ ምንም ነገር
አልነገርኩህም፡፡ ነገር ግን በግልጥ ለመናገር እኔ ብዙ ትውልዶች አሳልፌያለሁ፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


142 በእምነት ሕይወታችን ውስጥ የእግዚአብሄርን ሥልጣንና ጸጋ መቀበል አለብን

በአንተ ዕድሜ ላይ በነበርሁ ጊዜም ይህንንና ያንን አድርጌያለሁ፡፡ ደህንነቴን ከአንተ


በኋላ የተቀበልሁ ከመሆኔ በቀር ከአንተ በጣም የተሻልሁ ነኝ፡፡›› በዚህ መንገድ የራስ
ማንነት ብቅ ማለቱን ይቀጥላል፡፡
ዘፍጥረት ምዕራፍ አንድ የሚናገረው እግዚአብሄር ዩኒቨርስን ስለ መፍጠሩ
ሲሆን ሁለተኛው ምዕራፍ የሚናገረው እግዚአብሄር ሁሉን ለእኛ እንደሰጠን ነው፡፡
እግዚአብሄር ከተከለከለችው ፍሬ በስተቀር ሁሉን ሰጥቶናል፡፡ እግዚአብሄር እንዲህ
አለ፡- ‹‹በገነት ካለው ዛፍ ሁሉ ትበላለህ፤ ነገር ግን መልካምንና ክፉን
ከሚያስታውቀው ዛፍ አትብላ፤ ከእርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህና፡፡›› በሌላ
አነጋገር እግዚአብሄር እንዲህ እያለን ነው፡- ‹‹በራሳችሁ ብያኔዎች አትቃወሙኝ፡፡
ለስልጣኔ ተገዙ፡፡ መልካምንና ክፉን ከሚያስታውቀው ዛፍ ከበላችሁ ሞትን
ትሞታላችሁ፡፡ በአምሳሌ ብፈጥራችሁና እናንተንና ዘሮቻችሁን በልጄ አማካይነት
የእኔ ልጆች ወደ መሆን ልለውጣችሁ ባቅድም ያንን ያደረጋችሁበት መንገድ ምንም
ቢሆንም መልካምንና ክፉን ከሚያስታውቀው ዛፍ በበላችሁበት ቀን ሞትን
ትሞታላችሁ፡፡››
በእግዚአብሄር የተፈጠረው ሰው ግን መልካምንና ክፉን ከሚያስታውቀው
ዛፍ በላ፡፡ በዚህ ምክንያት የመንፈስና የስጋ ሞት መጣ አይደል? አዎ፡፡ ሆኖም
እግዚአብሄር ልጁን ኢየሱስ ክርስቶስን አላከልንምን? በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
አማካይነትስ አላዳነንምን? ነገር ግን ከሐጢያት ከዳናችሁም በኋላ እንኳን
መልካምንና ክፉን ከሚያስታውቀው ዛፍ ከበላችሁ በእርግጠኝነት ትሞታላችሁ፡፡
ይህ ለሁሉም ሰው እውነት ነው፡፡ ስለ ስጋዊ ጉልበታችሁ፣ ስለ ዕውቀታችሁ ወይም
ስለ ቀድሞ ልምምዶቻችሁ የምትመጻደቁ ከሆነ በእርግጠኝነት በስጋም በመንፈስም
ትሞታላችሁ፡፡ ለእግዚአብሄር ሥልጣን መገዛት እንደሚገባን በአእምሮዋችን መያዝ
ያለብን ለዚህ ነው፡፡ የእግዚአብሄርን ሥልጣን በልባችሁ ውስጥ የምትቀበሉ ከሆነ
ለመንፈሳዊ ዓላማ ቢያጎሳቁሉዋችሁም አትበሳጩም፡፡ በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን
ውስጥ ላለው የተዋረድ ሥልጣን መገዛት የሚያስፈልጋችሁ ለእናንተው ጥቅም
ነው፡፡ ምክንያቱም ይህንን የምታደርጉ ከሆነ ብዙ ትማራላችሁ፡፡ በመንፈሳዊ
ሕይወታችሁም ታድጋላችሁ፡፡ የእግዚአብሄርን የተትረፈረፉ በረከቶች
ትቀበላላችሁ፡፡ የእምነት ሕይወት ልክ እንደዚህ ነው፡፡ ገባችሁ? እንዲህ ታምናላችሁ?
ጉብሎች እናንተም ደግሞ እንዲህ ታምናላችሁ?
ሁላችንም በእግዚአብሄር ፊት እኩል ነን፡፡ እኛ መሪዎች እናንተን ቅዱሳኖች
የምንመራው እግዚአብሄር እንድናደርገው በፈቀደልን መሠረት ነው፡፡ ስለዚህ
የተናቃችሁ መስሎ ከተሰማችሁ ምንም አድልዎ የለም፡፡ ማንም ሰው በሰውነታችሁ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በእምነት ሕይወታችን ውስጥ የእግዚአብሄርን ሥልጣንና ጸጋ መቀበል አለብን 143

አይንቃችሁም፡፡ ነገር ግን እግዚአብሄር በእርሱ ቤተክርስቲያን ወስጥ ባሉ መሪዎችና


የእምነት ቀደምቶች አማካይነት ሊያስተምራችሁ እየሞከረ ነው፡፡ ከእግዚአብሄር
እየተማራችሁ ስለሆነ ፈጽሞ ልትረበሹ አይገባችሁም፡፡
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን ደህንነታችንን ከተቀበልን በኋላ እንደ
እግዚአብሄር ልጆች የቀረልን ነገር ቢኖር በእምነት መኖር ነው፡፡ ማድረግ
የሚኖርብን ብቸኛው ነገር በእምነት መልካም ሥራዎችን መስራት ነው፡፡ ብቸኛው
ሥራችን ያ ነው፡፡
ርብቃ ለታናሹ ልጅዋ ‹‹ልጄ ሆይ መርገምህ በእኔ ላይ ይሁን፤ ቃሌን ብቻ
ስማኝ፤ ሂድና አምጣልኝ›› (ዘፍጥረት 27፡13) በማለት እንዳደረገችው ሁሉ ኢየሱስ
እርግማኖቻችንን በሙሉ በራሱ ላይ ወሰደ፡፡ በዚህ መንገድም የሐጢያቶቻችንን
ችግሮች በሙሉ አቃለለ፡፡ ለእዚአብሄር ጸጋ ምስጋና ይድረሰውና እኛ
ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ድነናል፡፡ ጌታችን እስኪመለስ ድረስም ይህንን የደህንነት ጸጋ
አጥብቀን መያዝ አለብን፡፡ በተለይም በእነዚህ የመጨረሻ ቀኖች ከእምነታችን ጋር
መጣበቅ አለብን፡፡ ይህ ወደ ፍጻሜ እየሮጠ ያለ የመጨረሻው ዘመን በመሆኑ ግፍ፣
ክፋትና ፍትወት በሞላበት ዓለም ላይ በእምነት መኖር ይገባናል፡፡ በዚህ ምክንያት
ማንም ሰው ዳግመኛ የተወለደ ቢሆን ወይም ባይሆን ስለ ምግባሮቹ ሊመጻደቅ
አይችልም፡፡ ጻድቃንና ሐጢያተኞች ማንም እንሁን የምንመጻደቅበት ምንም ነገር
የለንም፡፡
እንዲህ ተብሎ ተጽፎዋል፡- ‹‹እኛ ፍጥረቱ ነንና፤ እንመላለስበት ዘንድ
እግዚአብሄር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ
ተፈጠርን፡፡›› (ኤፌሶን 2፡10) እኛ በኢየሱስ ክርስቶስ ጽድቅ በማመን የእርሱ
ሠራተኞች ሆነናል፡፡ እነዚህን መልካም ሥራዎች መስራት የምንችለው
በእግዚአብሄር የደህንነት ጽድቅ ስለምናምን ብቻ ነው፡፡ ጌታ እነዚህን መልካም
ሥራዎች በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ለምናምን ለእኛሰ በአደራ ሰጥቶናል፡፡
ቀሪውን ሕይወታችንን በእግዚአብሄር ጽድቅ በእምነት እንኖራለን፡፡
በእግዚአብሄር ጽድቅ ታምናላችሁን? በእግዚአብሄር ጸጋ ደህንነታችሁን
ተቀብላችኋልን? የእግዚአብሄርን ሥልጣን ትቀበላላችሁ? ለእግዚአብሄር ማንን
ታስገዛላችሁ? እኛ ለጥቅማችን ስንል የእግዚአብሄርን ሥልጣን እንቀበላለን፡፡
ለእግዚአብሄር ሥልጣንና ለጽድቁ ምስጋና ይሁንና እኛ ደህንነታችንን
ተቀብለናል፡፡ 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


144 በእምነት ሕይወታችን ውስጥ የእግዚአብሄርን ሥልጣንና ጸጋ መቀበል አለብን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ስብከት
8

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት
ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
እኛ በእግዚአብሄር ፊት
ምን ዓይነት ሰዎች ነበርን?
‹‹ ኤፌሶን 2፡1-7 ››
‹‹በበደላችሁና በሐጢአታችሁ ሙታን ነበራችሁ፤ በእነርሱም በዚህ ዓለም
እንዳለው ኑሮ በማይታዘዙትም ልጆች ላይ አሁን ለሚሠራው መንፈስ አለቃ
እንደሆነው በአየር ላይ ሥልጣን እንዳለው ፈቃድ በፊት ተመላለሳችሁባቸው፡፡
በእነዚህም ልጆች መካከል እኛ ሁላችን ደግሞ የሥጋችንንና የልቡናችንን ፈቃድ
እያደረግን በሥጋችን ምኞት በፊት እንኖር ነበርን፡፡ እንደ ሌሎቹም ደግሞ
ከፍጥረታችን የቁጣ ልጆች ነበርን፡፡ ነገር ግን እግዚአብሄር በምሕረቱ ባለጠጋ
ስለሆነ ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሳ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ
ከክርስቶስ ጋር ሕይወትን ሰጠን፤ በጸጋ ድናችኋልና፡፡ በሚመጡ ዘመናትም
በክርስቶስ ኢየሱስ ለእኛ ባለው ቸርነት ከሁሉ የሚበልጠውን የጸጋውን ባለጠግነት
ያሳይ ዘንድ ከእርሱ ጋር አስነሳን፡፡ በክርስቶስ ኢየሱስም በሰማያዊ ሥፍራ ከእርሱ
ጋር አስቀመጠን፡፡››

በበደሎችና በሐጢያቶች ሙታን ነበርን?

ሐዋርያው ጳውሎስ ደህነነታችን ከዓለም ፍጥረት በፊት በኢየሱስ ክርስቶስ


እንደተዘጋጀ ተናግሮዋል፡፡ እግዚአብሄር አብ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በልጁ
በኢየሱስ ክርስቶስ አማካይነት የራሱ ሕዝብ እንዳደረገን ተናግሮዋል፡፡ ስለዚህ እኛ
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን ለአንዴና ለመጨረሻ የሐጢያቶችን ስርየት
ተቀብለናል፡፡ ዛሬ ግን በውሃወና በመንፈሱ ወንጌል በማመን የሐጢያቶችን ስርየት
ለመቀበላችን በፊት ሁኔታችን ምን እንደነበር እንድንመረመር እፈልጋለሁ፡፡
በኤፌሶን 2፡1 ላይ እንዲህ ተጽፎዋል፡- ‹‹በበደላችንና በሐጢአታችን ሙታን
ነበርን፤ ሕያው አደረገን፡፡›› በአሁኑ ጊዜ ብዙ ክርስቲያኖች በዚህ ዓለም ላይ እየኖሩ
ሳለ የሰሩዋቸው ሐጢያቶች የግል ሐጢያቶች ሲሆኑ ከወላጆቻቸው የወረሱት
መሠረታዊ ሐጢያት ደግሞ የአዳም ሐጢያት እንደሆነ በማሰብ ሐጢያቶቻቸውን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


148 እኛ በእግዚአብሄር ፊት ምን ዓይነት ሰዎች ነበርን?

በሁለት ዓይነት ይመድቡዋቸዋል፡፡ በአንጻሩ እግዚአብሄር እነዚህን ሁሉ


ሐጢያቶች በአንድ ላይ በመመደብ የዓለም ሐጢያት ብሎ በጅምላ ይጠራቸዋል፡፡
(ዮሐንስ 1፡29) እዚህ በዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ላይም እግዚአብሄር
በአምላክ ፊት በሰራናቸው ሐጢያቶችና በደሎች ሙታን የነበሩት ነፍሶቻችን አሁን
በክርስቶስ አማካይነት እንደዳኑ ይነግረናል፡፡
ሁላችንም ከጌታ ጽድቅ ጋር ከመገናኘታችን በፊት በሕይወታችን በሰይጣን
እንገዛ ነበር፡፡ ሞትን ስለምንፈራም የእርሱ ባሮች ነበርን፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ
እዚህ በዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ላይ እንዳለው የውሃውንና የመንፈሱን
ወንጌል ከማግኘታችን በፊት በማይታዘዙ ልጆች ላይ ከሚሰራው መንፈስ በታች
ስንገዛ ነበር፡፡ ዛሬም ቢሆን ይህ ክፉ መንፈስ ሰዎች በእግዚአብሄር ላይ እንዲያምጹ
በማነሳሳት እያንዳንዱ ሐጢያተኛ ነፍስ እግዚአብሄርን እንዲቃወም ሲሰራ
እናያለን፡፡
በግልጥ አነጋገር እያንዳንዱ የዓለም ሐይማኖት የሚገዛው በዚህ ክፉ መንፈስ
ነው፡፡ በዚህ ዓለም ላይ በራሳቸው ሐይማኖታዊ አመኔታዎች ውስጥ ተቀብረው
በተለያዩ የሐሰት ሐይማኖቶች የሚያምኑና መላውን የሕይወት ዘመናቸውን
የሚኖሩ ብዙ ሰዎች አሉ፡፡ በአሁኑ ጊዜ አገራችን ኮርያ አንድ ዓለም አቀፋዊ
የትውፊት በዓል እያስተናገደች ነው፡፡ ይህ የትውፊት በዓል ክፉ መናፍስቶችን
ለመታረቅ በዓለም ያሉ የተለያዩ ሐይማኖታዊ ስርዓቶች የሚያከናውኑትን የሚያሳይ
ነው፡፡ በዚህ ዓለም አቀፋዊ የትውፊት በዓል ላይ የሚሳተፉ ተሳታፊዎች ከብዙ
የተለያዩ አገሮች የሚመጡ ቢሆኑም ሁሉንም የሚያመሳስላቸው አንድ ነገር ካለ
የሚያሰቃዩዋቸውን ክፉ መናፍስቶች የሚታዘዙና የሚያመልኩ መሆናቸው ነው፡፡
እነዚህ ሰዎች የሚያምኑዋቸውን ጣዖታት ስንመለከት እነዚህ ጣዖታት በርካታ
ሰዎችን አንቀው እንደያዙ እንመለከታለን፡፡ ስለዚህ እነዚህ ሁሉ ሰዎች በእነዚህ
ክፉ መናፍስቶች የተያዙ መሆናቸው ግልጥ ነው፡፡ እነዚህ ሰዎች ለሚያምኑባቸው
ለእነዚህ ጣዖታት መስዋዕቶችን በማቅረብ የሚታረቁዋቸው የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል ስለማያውቁ ነው፡፡ በጣም ብዙ ሰዎች የውሃውና የመንፈሱ
ወንጌል የደህንነት እውነት መሆኑን ሳያውቁ የቀን ተቀን ሕይወታቸውን ይኖራሉ፡፡
አሁን ከውሃውና ከመንፈሱ ወንጌል ጋር ከመገናኘታችሁና እርሱንም
ከማመናችሁ በፊት እናንተም ደግሞ በልባችሁ እግዚአብሄርን ተቃውማችሁት
እንደነበር አሳምራችሁ እንደምታውቁ እርግጠኛ ነኝ፡፡ ስለ እግዚአብሄርና ስለ ቃሉ
ባታውቁም ምናልባት እግዚአብሄርን እየተቃወማችሁ እንደሆነ በሕሊናችሁ ታውቁ
ነበር፡፡ ጳውሎስ ለኤፌሶን ቅዱሳኖች ‹‹በአየር ላይ ሥልጣን ያለውን አለቃ››

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


እኛ በእግዚአብሄር ፊት ምን ዓይነት ሰዎች ነበርን? 149

(ኤፌሶን 2፡2) እንደተከተሉ ሲነግራቸው በትክክል እየተናገረ የነበረው ስለ


ሁላችንም ነው፡፡ በሌላ አነጋገር ጳውሎስ የሚያስተምረን ሰይጣን በዚህ ዓለም ላይ
በመስራት በቀድሞው ኑሮዋችን በእግዚአብሄር ላይ እንድናምጽና እርሱን
እንድንቃወም እያደረገን መሆኑን ነው፡፡ አሁንም እንኳን በርካታ ሰዎች በዓለም
ዙሪያ እግዚአብሄርን እየተቃወሙና በክፉ መንፈስ እየተያዙ ነው፡፡ እነዚህ ሰዎች
በተጨባጭ የሚሹት ይህንን ባይሆንም እግዚአብሄርንና ቃሉን እየተቃወሙ ነው፡፡
በክፉ መንፈስ የተያዙትም እግዚአብሄር የሰጠውን የውሃና የመንፈስ እውነት
ስለማያውቁ ነው፡፡ ሳያውቁ እግዚአብሄርን የሚቃወሙት ለዚህ ነው፡፡ ራሳቸው
ሳያውቁት ልቦቻቸው እግዚአብሄርን ለመቃወም በመነሳቱ በእግዚአብሄር ላይ
ሐጢያትን እየሰሩ ነው፡፡
እነዚህ ሰዎች በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን የእግዚአብሄር ልጆች
የሆኑትንም ሰዎች ደግሞ ይቃወማሉ፡፡ ስለዚህ እነዚህ ሁሉ ሰዎች ራሳቸውን
መመርመርና ልቦቻቸው እግዚአብሄርንና ቃሉን ይቃወሙ እንደሆነ ማየት
አለባቸው፡፡ ይህ እውነት ከሆነም ሊቀበሉት፣ ወደ ጌታ ሊመለሱና በእርሱ ጽድቅ
ሊያምኑ ይገባቸዋል፡፡ በእርግጥ ዓመጸኞች እንደሆኑ ካመኑ በኋላ ሁሉም ወደ ጌታ
መመለስና ጌታ ሐጢያቶቻቸውን በሙሉ ባስወገደበት ወንጌል በውሃውና
በመንፈሱ ወንገል ማመን አለባቸው፡፡ አለበለዚያ የማትረባው ነፍሳቸው በክፉ
መንፈስ ተይዛ እግዚአብሄርን መቃወምዋን ትቀጥላለች፡፡
በርካታ ሰዎች የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ስለማያውቁ አሁን በክፉ
መንፈስ ተገዝተዋል፡፡ ስለዚህ ሐዋርያው ጳውሎስ የእግዚአብሄርን ጽድቅ የያዘውን
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በማመን ከሐጢያቶቻችን ሁሉ መዳን እንዳለብን
ተናገረ፡፡ ምክንያቱም በኢየሱስ ክርስቶስ ለመዳን ከዓለም ፍጥረት በፊት
አስቀድመን ተወስነናልና፡፡ ይህ የሆነው ጌታ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል እውነት
ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ስላዳነን ነው፡፡ እኛ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን
የእግዚአብሄር ልጆች ሆነናል፡፡
ሆኖም የጌታን ጽድቅ ከማግኘታችን በፊት ነፍሶቻችን ሁሌም ስጋዊ
መሻቶቻችንን ይከተሉ ነበር፡፡ ሐዋርያው ጳወሎስ ሁላችንም በፍጥረታችን
በእግዚአብሄር ፊት የቁጣ ልጆች መሆናችንን የተናገረው ለዚህ ነው፡፡ ነገር ግን
ለክርስቶስ ምህረት ምስጋና ይሁንለትና እኛ በእምነት እነዚህን የሰማይ መንፈሳዊ
በረከቶች መቀበል ችለናል፡፡ ከዚህም በላይ በዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ላይ
እግዚአብሄር ‹‹የጸጋውን ባለጠግነት ያሳይ ዘንድ ከእርሱ ጋር አስነሳን፡፡ በክርስቶስ
ኢየሱስም በሰማያዊ ሥፍራ ከእርሱ ጋር አስቀመጠን›› (ኤፌሶን 2፡6) ይላል፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


150 እኛ በእግዚአብሄር ፊት ምን ዓይነት ሰዎች ነበርን?

አሁን እኛ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን ዳግመኛ ስለተወለድን ከኢየሱስ


ክርስቶስ ጋር አብረን በሰማይ ክብርና ግርማ መደሰት እንችላለን፡፡ እዚህ ላይ
ሐዋርያው ጳውሎስ እያስተማረን ያለው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን
ከሐጢያቶቻችን ሁሉ የዳንን መሆናችንን ነው፡፡ ስለ ደህንነት ከማስተማሩም በፊት
ስለ ሁኔታችን ደግሞ ያስተምረናል፡፡
ሁለቱም የመጽሐፍ ቅዱስ ኪዳኖች የምንቀበላቸው የሰማይ በረከቶች ምን
ያህል ታላላቅ እንደሆኑ ይናገራሉ፡፡ ይህ የሆነበት ምክንያት በዚህ ምድር ላይ
ስንኖር በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን ታላቁን የእግዚአብሄር ምህረት
ደህንነት ስለተቀበልን ነው፡፡ እግዚአብሄር ታላቁን ጸጋውን ለሚመጣው ትውልድ
ሁሉ ለመግለጥ እንደሚሻ ተናግሮዋል፡፡ እኛ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
የምናምን አማኞች የእግዚአብሄርን ወንጌል ለመመስከር በትጋት እየሰራን ያለነው
ለዚህ ነው፡፡ እግዚአብሄር እኛን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የምናምነውን
አማኞች በሰማይ አስቀምጦናል፡፡ በዚህ ምድር ላይም ይህንን የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል እንድንሰብክ አድርጎናል፡፡ በዚህ መልኩም ታላቁን ፍቅሩንና
ምህረቱን ገልጦልናል፡፡
እያንዳንዱ የእግዚአብሄር ቃል የተነገረው ለሁላችንም እውነተኛ ደህንነትንና
የዘላለም ሕይወትን ለማምጣት ነው፡፡ ስለዚህ እኛ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
በማመን ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ከመንጻታችን በፊት ሁላችንም ከእግዚአብሄር ቁጣ
በታች እንደነበርን መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል፡፡ እኛ በፍጥረታችን በእግዚአብሄር
ፊት የቁጣ ልጆች ነበርን፡፡ በክፉ መንፈስም ተይዘን ነበርን፡፡ በሕይወት ዘመናችንም
ሁሉ በስጋዊ መሻቶቻችን መሠረት ስለኖርን የእግዚአብሄር ቁጣ ሁላችንንም
ሲጠብቀን ነበር፡፡
ሆኖም ጌታችን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት እኛን ለአንዴና
ለመጨረሻ አድኖን በመንግሥተ ሰማይ እንድንቀመጥ ባረከን፡፡ ይህ በረከት
የመጣው ጌታችን በሰጠን የውሃና የመንፈስ ወንጌል እውነት በመሆኑ ፈጽሞ ሊካድ
አይችልም፡፡ የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል እውነት በዚህ ዓለም ላይ ተጨባጭ
የደህንነት እውነት ነው፡፡ ስለዚህ በእግዚአብሄር ቃል ፊት ከመንበርከክ፣ በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል በማመን ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ከመዳንና ምስጋናችንን ሁሉ
ለእግዚአብሄር ከመስጠት በቀር ምርጫ የለንም፡፡
የእግዚአብሄርን ቃል ስናሰላስል የተፈጥሮ ሁኔታችን እንዴት ነበር? በግልጥ
አነጋገር ሁሌም በእግዚአብሄር ላይ ሐጢያት እንሰራለን፡፡ ጌታችን ፍጹም በሆነው
የውሃና የመንፈስ ወንጌል አማካይነት ያዳነን ለዚህ እንደሆነ ግልጥ ነው፡፡ ይህ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


እኛ በእግዚአብሄር ፊት ምን ዓይነት ሰዎች ነበርን? 151

የሆነው በእግዚአብሄር ምህረት ነው፡፡ እግዚአብሄር የተናገረን እያንዳንዱ ቃል


እውነት ነው፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ የነገረን የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል እውነት
የእግዚአብሄር የደህንነት ቃልና ትክክለኛ እውነት ነው፡፡

ታዲያ በእግዚአብሄር ፊት የእምነታችን ትክክለኛው ባህርይ ምን መሆን


ይገባዋል?

ሕይወታችን ይህንን በእጅጉ የተትረፈረፈ የእግዚአብሄር ጸጋ ማለትም


እግዚአብሄር የሰጠውን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለሚመጡት ትውልደዶች
ሁሉ ለመስበክ ፍላጎት ባለው ባህርይ መመራት አለባት፡፡ በዚህ ምድር ላይ
የምንኖርበት ምክንያት የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለመስበክ መሆኑን
መቀበላችን ለሁላችንም በእጅጉ አስፈላጊ ነው፡፡ ሕይወታችንን በመኖር ስንቀጥል
ቅድሚያ የምንሰጠው ነገር የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ማስፋፋት ነው፡፡
ውሳኔዎቻችን ሁሉ መወሰን ያለባቸው በዚህ ዓላማ መሠረት ነው፡፡ እኛ ወንጌልን
በመላው ዓለም ሁሉ ለሚኖር ለእያንዳንዱ ሰው የማስፋፋት ይህ ሐላፊነት
እንዳለብን ሁችንም ልናምን ይገባናል፡፡ በእግዚአብሄር ፊት የማያቋርጠው ግባችን
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል መስበክ መሆን ይገባዋል፡፡ ሁላችንም ሁሌም
በእምነት መኖር አለብን፡፡
እኛ ከዓለም ሐጢያቶች ሁሉ በመዳናችን በእጅጉ አመስጋኝ ነኝ፡፡ በዘላለም
ሕይወት ለመደሰትም ከሲዖል ቅጣት ስለዳንን እንደዚሁ አመስጋኝ ነኝ፡፡ ከዚህም
በላይ እግዚአብሄር በመንግሥተ ሰማይ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር እንድንኖር
ፈቅዶልናል፡፡ ምን ያህል አመስጋኝ እንደሆንሁ የምገልጥበት ቃላት የለኝም፡፡
እግዚአብሄር የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ሥራ በአደራ ለእኛ በመስጠት
አብዝቶ ባርኮናል፡፡ እግዚአብሄር ይህንን ድንቅ ሥራ ለእኛ ባይሰጠን ኖሮ በዚህ
ምድር ላይ ያለው የእምነት ሕይወታችን አሰልቺ ይሆን ነበር፡፡ እግዚአብሄር ግን
ለሚመጣው ለእያንዳንዱ ትውልድ የተትረፈረፈውን ፍቅሩንና ምህረቱን
እንድንሰብክ አደረገን፡፡ ታዲያ እንዴት እግዚአብሄርን ላናመሰግነው እንችላለን?
የወንጌልን እውነት ለመስበክ የእርሱ ሠራተኞች አድርጎ እየተጠቀመብን ስላለ
ምስጋናዬን ሁሉ ለእርሱ እሰጣለሁ፡፡ ሁላችንም የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
የማወጅ ሥራን በአደራ ስለሰጠን እግዚአብሄርን አብዝተን ልናመሰግነው
ይገባናል፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


152 እኛ በእግዚአብሄር ፊት ምን ዓይነት ሰዎች ነበርን?

እነዚህን ድንቅ በረከቶች ስለሰጠን እግዚአብሄርን


ለማመስገን እንገደዳለን፡፡

ጉድለቶች ቢኖሩብንም ከዚህ ቅዱስ አምላክ ጋር ለመኖር እግዚአብሄር


የሰጠውን የሐጢያቶች ስርየት ደህንነት ተቀብለናል፡፡ እግዚአብሄር ክብሩን
እንድንለብስ እንዴት በመንግሥተ ሰማይ እንዳስቀመጠን ስንመለከት እርሱን
እናመሰግነዋለን፡፡ እኛ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የምናምን አማኞች እነዚህን
የሰማይ መንፈሳዊ በረከቶች ሁሉ ለመቀበላችን ምንም ጥርጥር የለውም፡፡ ይህ ሁሉ
የሆነው እግዚአብሄር ለእኛ ባዘጋጀው የደህንነታችን ችሮታ መሠረት ነው፡፡ ይህም
የእርሱ የተትረፈረፈ በረከት ነው፡፡ እነዚህ ሁሉ በረከቶች እግዚአብሄር ከምህረቱ
የተነሳ የሰጠን የሰማይ መንፈሳዊ በረከቶች እንደሆኑ አምናለሁ፡፡ እኛ በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል የሚያምኑ ሰዎች በመሆናችን እግዚአብሄርን ለበረከቶቹ
ከማመስገን በቀር ደስታችንን የምንገልጥበት ሌላ መንገድ የለንም፡፡ ምን ያህል
ደስተኞች እንደሆንን የምንገልጥባቸው ቃላቶች የሉንም፡፡
አሁን ሕይወታችን በእግዚአብሄር ፍቅር፣ በደህንነት ጸጋውና በበረከቶቹ
ተሞልቷል፡፡ እግዚአብሄርን ለፍቅሩ የምናመሰግነውና የምናወድሰው ለዚህ ነው፡፡
ይህንን የደህንነት ጸጋ በእምነት ከተቀበልን በኋላ የእግዚአብሄርን ዕቅድ ታማኝነት
ልንጠራጠር አንችልም፡፡ የእግዚአብሄርንም ቃል በአስተሳሰቦቻችን መቃወም
አንችልም፡፡ ለእኛ ያለውን ዕቅዱን ስለሚፈጽምልን እግዚአብሄርን
እናመሰግነዋለን፡፡ ምክንያቱም እያንዳንዱ የዕቅዱ ክፍል እንከን አልነበረበትም፡፡
ስለዚህ የእግዚአብሄርን ዕቅድ ትክክለኝነት ቅንጣት ያህል እንኳን
አንጠራጠረውም፡፡ አሁን እኛ የእግዚአብሄርን ፍቅር በማመን በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት ስለዳንን ሁላችንም ቀሪውን ሕይወታችን
ለእግዚአብሄር ሥራ መቀደስ ይገባናል፡፡
አሳምረን እንደምናወቀው አካሎቻችን ገና ስላልተለወጡ የእግዚአብሄርን
በረከቶች ሙሉ በሙሉ መረዳት ያዳግተናል፡፡ ነገር ግን በልቦቻችን እግዚአብሄር
‹‹በሰማያዊ ስፍራ እንድንቀመጥ›› (ኤፌሶን 2፡6) ማድረጉ ምንኛ ድንቅ እንደሆነ
መረዳት እንችላለን፡፡ ምክንያቱም በዚህ የእግዚአብሄር ቃል እናምናለንና፡፡
የተትረፈረፉትን በረከቶች፣ በዓይኖቻችን ልናያቸው የምንችላቸውንና አሁን
የምንለማመዳቸውን የሚታዩ በረከቶችና በእምነት አርቀን የምናየውን በሰማይ
የመቀመጥ በረከት ስንመለከት እዚአብሄርን እናመሰግነዋለን፡፡ በእምነታችን
ከእግዚአብሄር ልናገኘው የምንናፍቀው ነገር ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር አብሮ በሰማይ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


እኛ በእግዚአብሄር ፊት ምን ዓይነት ሰዎች ነበርን? 153

መቀመጥን ነው፡፡ እኛ በእምነት አማካይነት በከፊልም ቢሆን ይህንን የከበረ


ሕይወት በደብዛዛው ማየት እንችላለን፡፡ ራሳችሁን በፕሬዚዳንታዊ ቤተ መንግሥት
የሚኖር ሰው አድርጋችሁ ብታስቡ መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሄር በሰማይ
እንዳስቀመጠን ሲናገር ምን ማለቱ እንደሆነ አንዳች አሳብ ልታገኙ ትችላላችሁ፡፡
አሁን በፕሬዚዳንታዊ ቤተ መንግሥት ውስጥ እየኖራችሁ ቢሆን ኖሮ ምን ይማችሁ
ነበር? እንዲህ ባለ ቤተ መንግሥት ውስጥ እየኖራችሁና ለፕሬዚዳንቱ የሚሰጡትን
ጥቅማ ጥቅሞች በሙሉ የምታጣጥሙ ብትሆኑ ኖሮ ሕይወታችሁ እንዴት ይሆን
ነበር? ተራ ሰዎች ስለሆነን ይህንን እንኳን ማሰብ አንችልም፡፡
ሌላ ምሳሌ ልስጣችሁ፡፡ በቅርቡ ከአንድ ኮሎኔል ጋር የመገናኘትና
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለእርሱ የመስበክ ዕድል አግኝቼ ነበር፡፡ እርሱ
እንደነገረኝ ከሆነ የኮሎኔል ማዕረግ በውትድርና ውስጥ ከፍተኛ ማዕረግ ነው፡፡ ነገር
ግን ሰዎች ኮሎኔሎች ወይም ጄኔራሎችም እንኳን ያን ያህል የላቁ እንደሆኑ
አያስቡም፡፡ ሆኖም በውትድርና ውስጥ ሰው የጄኔራልነትን ማዕረግ ሲያገኝ ይህንን
ሹመት የሚያጅቡ በርካታ ጥቅሞች አሉ፡፡ እነዚህ ጥቅሞች በጣም ብዙ ስለሆኑ
ያስቀኑዋችኋል፡፡ ለአብዛኞቹ ሰዎች ጄኔራል ሌላ ወታደራዊ ሰው ሆኖ ሊታይ
ይችላል፡፡ ምክንያቱም የሹመቱን ጠቀሜታና የሥልጣኑን መጠን በትከክል
አያውቁምና፡፡ ይህንን የሚያውቁ ሰዎች ግን ጄኔራሎችን ያከብሩዋቸዋል፡፡ አንድ
ሰው ከኮሎኔልነት ወደ ጄኔራልነት ሲያድግ ማዕረጉ፣ ቤቱ፣ መኪናው፣ ሹፌሩና
ሌሎች ብዙ ነገሮች በተጨባጭ ይለወጡለታል፡፡ በጣም ብዙ ወታደራዊ አለቆች
የጄኔራልነትን ሹመት ለማግኘት ተግተው የሚጥሩት ለዚህ ነው፡፡
የእኛ በረከቶች ከማናቸውም ጄኔራሎች ወይም ፕሬዚዳንቶች እንኳን በእጅጉ
የላቁ ናቸው፡፡ እዚህ ላይ መጽሐፍ ቅዱስ ‹‹በክርስቶስ ኢየሱስ በሰማያዊ ሥፍራ
እንዳስቀመጠን›› (ኤፌሶን 2፡6) ሲናገር እናንተ ራሳችሁ ቅዱስና የእግዚአብሄር
ሠራተኞች ሆናችሁ ስለተቀበላችኋቸው በረከቶች መናገሩ ነው፡፡ በሌላ አነጋገር
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ስለምናምን ስለ ሁላችን እየተናገረ ነው፡፡
እግዚአብሄር ‹‹በሰማያዊ ሥፍራ እንዳስቀመጠን›› (ኤፌሶን 2፡6) ሲናገር ምን
ማለቱ እንደሆነ በሌላ መንገድ ለመረዳት ስለ ዩኒቨርስ እናስብ፡፡ ሳይንቲስቶች
እንደሚናገሩት ዩኒቨርስ በጣም ሰፊ ስለሆነ በዓይኖቻችን ልናየው ከምንችለው
ባሻገር በጣም ብዙ ጋላክሲዎች አሉ፡፡ የክዋክብት ተመራማሪዎች ከእኛ የሶላር
ሲስተም ጋር በጣም የሚመሳሰሉ ፕላኔታዊ መዋቅሮች ያላቸው አዳዲስ
ጋላክሲዎችን ማግኘታቸውን ቀጥለዋል፡፡ ዩኒቨርስን ስናስብ ብዙውን ጊዜ ጸሐይ
በዩኒቨርስ መሐከል እንዳለችና ክዋክብቶችና ፕላኔቶች በሙሉ በዚህች ጸሐይ ዙሪያ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


154 እኛ በእግዚአብሄር ፊት ምን ዓይነት ሰዎች ነበርን?

እንደሚሽከረከሩ እናስባለን፡፡ ነገር ግን ሳይንቲስቶች ሌሎች ጋላክሲዎችን ሳናነሳ


በራሳችን ጋላክሲዎች እንኳን ከእኛ ሲስተም ውጪ በጣም ብዙ ሶላር ሲስተሞች
እንዳሉ ይናገራሉ፡፡ ስለዚህ ዩኒቨርስ ከእኛ መረዳት ባሻገር እንደሆነ ሁሉ የሰማይም
ግዛት እንደዚሁ ከእኛ መረዳት ባሻገር ነው፡፡ የእግዚአብሄር የሆነ ዘላለማዊ ግዛት
እንደመሆኑ መጠን አሁን ባለን ዕውቀት ይህንን የሰማይ ግዛት መረዳት
ያዳግተናል፡፡
እግዚአብሄር የሰማይን ግዛት የፈጠረው እኛን እዚያ ለማስቀመጥ ከሆነ ይህ
ስፍራ በእርግጥ ምን ያህል ክቡር እንደሆነ ልናስብ ይገባናል፡፡ በመኖሩም ደግሞ
ልናምን ይገባናል፡፡ ሚልኪ ዌይን በሥዕሎች ወይም በፊልሞች ስንመለከት
በምስጢራዊውና በሰፊው ውበቱ እንመሰጣለን፡፡ ለእኛ የተዘጋጀ ሌላ ጋላክሲ
ብናስብ እገዚአብሄር እኛን በሰማይ ማስቀመጡ ምን ያህል የከበረና አስገራሚ
እንደሆነ መረዳት እንችላለን፡፡ እግዚአብሄር ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር አብሮ በሰማይ
እንዳስቀመጠን ስለተናገረ ሊታሰብ በማይችል ክብርና ግርማ እንደምንደሰት
ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡ ይህንነ ገና ሙሉ በሙሉ መረዳት እንዳልቻልን የታወቀ
ነው፡፡ ያ ማለት ግን ይህ እውነት አይደለም ማለት አይደለም፡፡ ይህንን የምንረዳው
በእምነት ብቻ መሆኑ የማይካድ እውነታ ነው፡፡

ስጋዊ ጉድለቶች ቢኖሩብንም እግዚአብሄር ባርኮናል፡፡

የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል እግዚአብሄር በምህረቱ የሰጠን ስጦታ ነው፡፡


የኢየሱስ ክርስቶስን ጽድቅ በያዘው በዚህ የውሃና የመንፈስ ወንጌል በማመን
ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ድነን ከሆነ በዚህ ምድር ላይ ምንም ዓይነት መከራ ቢገጥመን
እንኳን በጭራሽ ተስፋ አንቆርጥም፡፡ ምክንያቱም እግዚአብሄር ከሰጠን ደህንነት
ባሻገር ብዙ ታላላቅ በረከቶች ይጠብቁናልና፡፡ ስለዚህ በዚህ ዓለም ላይ
የሚገጥማችሁ መከራ ሕይወታችሁ ለምን ጎስቋላ እንደሆነ፣ ለምን ደካማ
እንደሆናችሁና እንደ ሌላው ሰው ሁሉ ለምን ደስተኞች እንደማትሆኑ ግራ
እንድትጋቡ ቢያደርጋችሁም በኢየሱስ ክርስቶስ ሰማይ እንደተቀመጣችሁ
የሚናገረውን የእግዚአብሄር ቃል ማሰብ፣ እግዚአብሄር የሰጣችሁን ክብር
ማስታወስና በዚህ ምድር ላይ የሚገጥማችሁ መከራ ወደፊት ከምትደሰቱበት ክብር
ጋር ሊመዛዘን የማይችል ከመሆኑ የማይናወጥ ማረጋገጫ ጋር መኖር ይገባችኋል፡፡
ሁላችንም ከዚህ ዓይነቱ እምነት ጋር መኖራችን ተገቢ ነው፡፡ በጸጋ መዳናችን፣

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


እኛ በእግዚአብሄር ፊት ምን ዓይነት ሰዎች ነበርን? 155

ዳግመኛ በክፉ መንፈስ የማንገዛ መሆናችን፣ የቁጣ ልጆች ከመሆን መሠረታዊ


ሁኔታችን ማምለጣችንና የእግዚአብሄር ሕዝብ መሆናችን ድንቅና ብሩክ ነው፡፡
ነገር ግን ከእነዚህ ሁሉ በረከቶች በላይ እግዚአብሄር ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር
በክብርና በግርማ እንድንደሰት በሰማይ አስቀምጦናል፡፡ ታዲያ እንዴት
እግዚአብሄርን ላናመሰግን እንችላለን? ሁላችንም እግዚአብሄርን ማመስገናችንና
ቃሉን በማመንም ለእርሱ ያለንን ውዳሴ ማሳየታችን ተገቢ ነው፡፡
የምንደሰትበትን የሰማይ ክብር አርቀን ስንመለከት ሁላችንም እግዚአብሄርን
በየቀኑና በየቅጽበቱ ማመስገን አለብን፡፡ እናንተስ ታዲያ? ከዓለም ሐጢያቶች
ስለዳናችሁና የሰማይን በረከቶች ሁሉ ስለሰጣችሁ እግዚአብሄርን ታመሰግናላችሁን?
ከዓለም ሐጢያቶች መዳናችን በእርግጥም አስገራሚ የእግዚአብሄር በረከት ነው፡፡
እናንተና እኔ የተቀበልነው ደህንነት ትልቅ ነው፡፡ ምክንያቱም ከክፉ መንፈስ ነጻ
አውጥቶናልና፡፡ ከዚህም በላይ በሐጢያቶቻችን ምክንያት ሊያጠፋን ከተወሰነብን
የተረገመ ስፍራችን ወደ እግዚአብሄር መንግሥት ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ መንግሥት
ፈልሰናል፡፡ እኛ ከእግዚአብሄር ዘንድ አስገራሚ በረከቶችን እንደተቀበልን
የሚያረጋግጠው ማስረጃ ይህ ነው፡፡
ከጥቂት ቀናቶች በፊት በክርስቲያን ጣቢያ በቴሌቪዥን ሲተላለፍ የነበረ
የሕክምና ዶክተር በአንድ ቤተክርስቲያን ውስጥ የመነቃቃት ስብሰባ ሲያደርግ
አየሁ፡፡ ይህ ሰው በኮርያ የታወቀ ስለሆነ አብዛኞቻችሁ በደምብ እንደምታውቁትና
ብዙ ጊዜም እንዳያችሁት እርግጠኛ ነኝ፡፡ ይህ ሐኪም በብዙዎች ዘንድ ጥሩ
ክርስቲያን እንደሆነ የሚቆጠር ሽማግሌ ነው፡፡ አስተሳሰቦቹና እምነቱ ግን
የተቀባዠሩ ነበሩ፡፡
ይህ ሐኪም በሰጠው ምስክርነቱ የካንሰር ሕክምና ፈልጎ እርሱን ለመገናኘት
ከሌላ ቤተክርስቲያን ስለመጣ አንድ ሽማግሌ ተናገረ፡፡ ስለዚህ ሐኪሙ ጥቂት
ምርመራዎችን አደረገ፡፡ ምርመራው ያሳየው ነገር ቢኖር ካንሰሩ የመጨረሻ ደረጃ
ላይ ደርሶ ስለነበር በሕይወት የመቆየት ተስፋ እንደሌለው ነበር፡፡ ሽማግሌው
ብቸኛ አማራጩ ቀዶ ጥገና ብቻ እንደነበርና ይህ አማራጭም ቢሆን የመሳካቱ ነገር
አጠራጣሪ እንደሆነ ሲነግረው ቀዶ ጥገናውን ትቶ ለመጸለይ ወደ ጸሎት ማዕከል
ሄደ፡፡ ይህ ሽማግሌ ስለምን የጸለየ ይመስላችኋል? ሰማይ ለመግባት በቂ እምነት
ወይም ድፍረት ያለው ስላልመሰለው ሰማይ ይገባ ዘንድ እንደጸለየ ተነግሮዋል፡፡
መሞቱ እንደማይቀር ስላወቀ እግዚአብሄርን እንዲፈውሰው ከመለመን ይልቅ
መንግሥተ ሰማይ እንዲገባ እንዲፈቅድለት ጸለየ፡፡ ይህ ሽማግሌ እንዲህ የጸለየው
በልቡ ውስጥ ሐጢያት እንዳለ ስላወቀ ነበር፡፡ ስለዚህ መንግሥተ ሰማይ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


156 እኛ በእግዚአብሄር ፊት ምን ዓይነት ሰዎች ነበርን?

የሚገባበት ምንም መንገድ አልነበረም፡፡


ይህ ሽማግሌ ልቡ በሐጢያት የተሞላ በመሆኑ እውነታ ስለተሰቃየ ለብዙ
ቀናት ጸለየ፡፡ ከእነዚያ ቀኖች በአንዱም አንድ ድምጽ ሰማ፡፡ እንዲተኛና እንዲያርፍ
የሚናገረውን የእግዚአብሄር ድምጽ ሰማ፡፡ ሽማግሌው እግዚአብሄር ያርፍ ዘንድ
የነገረውን ሲሰማ ‹‹እግዚአብሄር ዘመኔ እንዳበቃ እየነገረኝ እንደሆነ እገምታለሁ››
ሲል አሰበ፡፡ ስለዚህ ሽማግሌው በብዙ ግራ የሚያጋቡ ስሜቶች ተሞልቶ ወደ ቤቱ
ተመለሰ፡፡ ከዚያ በኋላ አንድ ቀን ከሐኪሙ ጋር ለመገናኘት ሄደ፡፡ ሐኪሙም
የሽማግሌው ካንሰር እየከፋ እንደሄደ በማሰብ ምን እንደሚሰማው ጠየቀው፡፡
ሽማግሌው ግን እየጸለየ ሳለ ሰማይ ሄዶ እንደነበር ነገረው፡፡
ይህ ታሪክ ብዙ ነው፡፡ ነገር ግን እዚህ ላይ ጠቃሚው ነገር የአብዛኞቹ
ክርስቲኖች እምነት ልክ እንደዚህ ሽማግሌ ግራ የተጋባ መሆኑ ነው፡፡ አንድ
ሐጢያተኛ እንኳን እዚያ ሄዶ ሊመለስ ይቅርና እንዴት ሰማይ ሊገባ ይችላል?
በቅርቡ ፒርሲ ኮሌት የሚባል ሰው ከኢየሱስ ጋር ለ5 ቀናት ከግማሽ በሰማይ
ተመላለስሁ የሚል መጽሐፍ አሳትሞ ነበር፡፡ ይህ መጽሐፍ በክርስቲያን
ማህበረሰቦች ውስጥ ትልቅ ግርግር ፈጥሮ ነበር፡፡ የዚህ መጽሐፍ ደራሲ ሰማይ
እንደነበር ተናግሮዋል፡፡ ኢየሱስ ዳግመኛ የሚመጣበትንም ቀን እንደነገረው
ተናግሮዋል፡፡ በዚህ ምክንያት በዓለም ዙሪያ ያሉ ብዙ ምስኪን ሰዎች በዚህ ሰው
ተታልለው እርሱ በወሰነው ቀን የኢየሱስን መምጣት ሲጠባበቁ ነበር፡፡ ጌታ ግን
በዚያ ቀን አልመጣም፡፡
በአሁኑ ጊዜ የአብዛኞቹን ክርስቲያኖች እምነት ስንመለከት አብዛኞቹ ልክ
እንደደነዘዘ ሰው ኢየሱስን በዕውር ድንብር ሲያምኑ እናያለን፡፡ ነገር ግን እነዚህ
ክርስቲያኖች መደንዘዛቸውን እንኳን አያውቁም፡፡ አንዳንድ ሴቶች በአሳባቸው
እንደሚያረግዙ ብዙ ክርስቲያኖችም በአሁኑ ጊዜ በራሳቸው አመኔታዎች ልብ
ወለድ ለሆነ ደህንነት ይማረካሉ፡፡ አንዲት ሴት ማርገዝ ከተሳናት በተጨባጭ
ባታረግዝ እንኳን የሆድ መግፋትንና የማለዳ ሕመምን ጨምሮ የትክክለኛ
እርግዝናን የተለያዩ ምልክቶች ማሳየት ትችላለች፡፡ እንዲህ ያሉ የእርግዝና
ምልክቶች የሚከሰቱት ሴቲቱ ልጅ የማግኘት ከፍተኛ ፍላጎት ስላላት በመደንዘዝዋ
ነው፡፡ ልክ እንደዚሁ በዚህ ዘመንና ጊዜም ብዙ ክርስቲያኖች የልብ ወለድ
ደህንነትን ምልክቶች ያሳያሉ፡፡ ይህ መንፈሰዊ ግራ መጋባት ውስጥ እንዳሉና በክፉ
መናፍስቶች እንደተያዙ የሚጠቁም ነው፡፡ ሁሉም በኢየሱስ እንደሚያምኑ
ቢናገሩም በእነዚህ ክፉ መናፍስቶች ስለተያዙ የሚታዘዙት ሰይጣንንና የእርሱን
ማታለያና ማጭበርበርያ ነው፡፡ ሰይጣን በዓመጸኛ ልጆች የሚሰራው እንደዚህ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


እኛ በእግዚአብሄር ፊት ምን ዓይነት ሰዎች ነበርን? 157

ነው፡፡ እምነታችሁን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ላይ በማኖር ይህንን የሰይጣን


ሥራ ሁሉ መርታት በእጅጉ ያስፈልጋችኋል፡፡
ጳውሎስ ማንም ሊያስተውላቸው የማይችሉትን ሺህ ቃላቶች በልሳን
ከመናገር ጥቂት የአእምሮ ቃላችን መናገር የተሻለ እንደሆነ ተናግሮዋል፡፡ (1ኛ
ቆሮንቶስ 14፡19) የዘመኑ አነቃቂዎች ግን ተከታዮቻቸውን በአስመሳይ ልሳኖች
እንዲናገሩ በማሰልጠን ወደ ዕብደት እየነዱዋቸው ነው፡፡ ሐሰተኛ የስጋ
ተዓምራቶች በእግዚአብሄር ጽድቅ ከማያምኑ ሰዎች ይመነጫል፡፡ እነዚህ ነገሮች
ከሐጢያት መዳናችንን በሚመለከት ፈጽሞ ከንቱ ናቸው፡፡
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን ከሐጢያቶቻችን ሁሉ መዳናችን
የእግዚአብሄር ድንቅ በረከት ነው፡፡ በፍጥረታችን የቁጣ ልጆች ብንሆንም
ለተትረፈረፈው የእግዚአብሄር ፍቅር ምስጋና ይሁንለትና ሁላችንም ደህንነታችንን
አግኝተናል፡፡ ይህ እምነት ለእኛ እጅግ የከበረ ነው፡፡ የቁጣ ልጆች ብንሆንም
በእግዚአብሄር ምህረት የመዳናችን እውነታ በራሱ አስገራሚ በረከት ነው፡፡ እኛም
ይህንን በረከት ከእግዚአብሄር ዘንድ በነጻ አግኝተነዋል፡፡
‹‹ሕይወት›› የሚል ርዕስ ያለው ታዋቂው የኮርያ መዝሙር እንዲህ ይላል፡-
‹‹ሕይወት ጊዜያዊ ነው፤ በዚህ ምድር ላይ የሚቆየው ለአጭር ጊዜ ነው፡፡›› በዚህ
ምድር ላይ ያለው ሕይወት በእርግጥም እዚህ ግባ የሚባል አይደለም፡፡ ዛሬም
ቢሆን ሰው ሁሉ የከበረና ዘላለማዊ ነገር ይፈልጋል፡፡ የእግዚአብሄርን ፍቅር
የምንናፍቀውና ዘላለማዊ ነገሮችን የምንበረብረው ዘላለማዊ ፍጥረቶች ስለሆንን
ነው፡፡ ከእግዚአብሄር የሚመጣውን ዘላለማዊ የሐጢያቶች ስርየት ፍቅር
የምንናፍቀውም ለዚህ ነው፡፡
ነገር ግን በዚህ ዓለም ላይ ያሉ በጣም ብዙ ሰዎች እውነቱን ስለማያውቁ
በሕይወታቸው ባዶነት ያላዝናሉ፡፡ ሆኖም የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
ሲገናኙና በዚህ የደህንነት እውነት በማመን ዳግመኛ ሲወለዱ ሁላቸውም
የሕይወታቸውን እያንዳንዱን ችግር መፍታት ይችላሉ፡፡ እኛ በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል አማካይነት የእግዚአብሄርን ጽድቅ ማግኘታችን ከዘላለማዊው አዳኛችን
ጋር መገናኘታችንና በእግዚአብሄር ክብር ስፍራ ለመቀመጥና የእርሱን
ባለጠግነቶችና ግርማ ለዘላለም ለማጣጣም የዘላለምን ሕይወት በረከት
መቀበላችንን የሚያሳይ ማስረጃ ነው፡፡ ይህ እግዚአብሄር የሰጠው በረከት ምንኛ
አስገራሚና ድንቅ በረከት ነው? ውስን በሆነው አእምሮዋችን የዚህን
የእግዚአብሄርን ፍቅር ሙሉ መጠን ማሰብ አንችልም፡፡
ከእግዚአብሄር የምንሻው ምንድነው? ሁላችንም ወደፊት የምንደሰትበትን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


158 እኛ በእግዚአብሄር ፊት ምን ዓይነት ሰዎች ነበርን?

የክብር ግዛት ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ በእግዚአብሄር ቀኝ ተቀምጦ ከእርሱ ጋር


እንድንኖር፤ በክብሩና በግርማው ከእርሱ ጋር አብረን እንድንኖር ይፈልጋል፡፡
እግዚአብሄር አባታችን እንደዚህ ያለውን ክቡር ሕይወት መኖር እንድንችል
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የምናምነውን ሁላችንን የባረከን ለዚህ ነው፡፡
እግዚአብሄር በነጻ የሰጠን በረከት ይህ ነው፡፡
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ማወቅና ማመን ለእናንተና ለእኔ እጅግ
አስፈላጊ ነገር ነው፡፡ በዚህ ዓለም ላይ ለጥቂት ጊዜ ወንጌልን ካገለገልን በኋላ
ሁላችንም ወደ እግዚአብሄር መንግሥት እንሄዳለን፡፡ ስለዚህ እስከዚያች ቀን ድረስ
ይህንን የእውነት ወንጌል እናገልግል፡፡ ለእያንዳንዱ ሕዝብና ትውልድም እንስበክ፡፡
እኛ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለመስበክ ደስተኞች ብንሆንም ብዙ ትግሎችም
እንደሚገጥሙን እሙን ነው፡፡ በመንፈሳዊ አነጋገር እጅግ ትልቁ ፈተናችን በጣም
ብዙ ሰዎች በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አለማመናቸው ነው፡፡ አንዳንድ ጊዜ
ከአንድ ትውልድ በፊት ብወለድና አገልገሎቴን ቀደም ብዬ ብጀምር በዚህ በአሁኑ
ጊዜ ዓለም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በሚያምኑ አማኞች ይሞላ ነበር ብዬ
እመኛለሁ፡፡ ነገር ግን አሁንም ቢሆን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በመስበካችን
ዕድለኞች ነን፡፡ እኛ በሰበክነው የውሃና የመንፈስ ወንጌል የሚያምኑ ሁሉ አሁን
የሐጢያቶቻቸውን ስርየት ይቀበላሉ፡፡ ስለዚህ በስጋ ድካም ቢሰማንም እንኳን
አሁንም ከልባችን ደስተኞች ነን፡፡ ጌታ ትንሽ ተጨማሪ ጊዜ ቢሰጠን በዚህ ዓለም
ላይ የሚኖር እያንዳንዱ ሰው የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ሐይል መለማመድ
ይችላል፡፡ በአሁኑ ጊዜ አብዛኞቹ ክርስቲያኖች ኢየሱስ በመስቀል ላይ ባፈሰሰው
ደም ብቻ በማመናቸው ሐጢያተኞች ሆነው ቢቀሩም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
የሚያምኑ ሁሉ ከእግዚአብሄር ዘንድ የሐጢያቶችን ስርየት በልቦቻቸው ውስጥ
ተቀብለዋል፡፡ እነርሱ በመንግሥቱ ውስጥም ደግሞ ይከብራሉ፡፡ በቅርቡ ብዙ
ሰዎች በዚህ እውነተኛ ወንጌል ወደ ማመን ይመጡና ‹‹ጌታ በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል አማካይነት ለአንዴና ለመጨረሻ ከሐጢያቶቼ ሁሉ አድኖኛል›› ብለው
ይመሰክራሉ፡፡
እግዚአብሄር በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የዘመኑ መጨረሻ ሲመጣ መንፈስ
ቅዱስን በባሮቹ በወንዶቹም በሴቶቹም ሁሉ ላይ እንደሚያፈስስ ተናግሮዋል፡፡ ወደ
እግዚአብሄር ቃል ስንመለስ እርሱ በመጨረሻው ዘመን በእናንተና በእኔ አማካይነት
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ለበርካታ ሰዎች የሐጢያቶችን ስርየት እንደሚለግስ
ሲናገር እናየዋለን፡፡ እግዚአብሄርም መንፈስ ቅዱስን በመስጠት እውነቱን
እንድናውጅ እንዳደረገን ተናግሮዋል፡፡ አጋር ምዕመናኖቼ ጌታ የውሃውንና

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


እኛ በእግዚአብሄር ፊት ምን ዓይነት ሰዎች ነበርን? 159

የመንፈሱን ወንጌል በመላው ዓለም እንድንሰብክ አድርጎናል፡፡ እግዚአብሄር ለእኛ


ያለው ፈቃድ ሌላ ሳይሆን ይህ ነው፡፡
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ሁሌም ማገልገላችን ለሁላችንም በእጅጉ
አስፈላጊ ነው፡፡ በዚህ ምድር ላይ ጌታን ማገልገል መቻላችን አስደሳች ነው፡፡
ወደፊት በእርሱ ክብር መደሰታችን ግን የሚበልጥ በረከት ነው፡፡ ስለዚህ
የምንወርሰውን መንግሥተ ሰማይ አርቀን በመመልከት እምነታችንን በተስፋ
ልንኖር ይገባናል፡፡ በዚህ ዓለም ላይ እየኖርን እንዲህ ያለ ድንቅ ተስፋ መያዛችን
የላቀ በረከት ነው፡፡ እኛ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የምናምን አማኞች እንዲህ
ያለ ተስፋ ባይኖረን ኖሮ በሚገጥመን ጠንከር ያለ እውነታ ተስፋ በመቁረጥ በቀላሉ
ተስፋ ቢስነት ውስጥ እንወድቅ ነበር፡፡ ስለዚህ ሁላችንም ተስፋችንን
በእግዚአብሄር ላይ ማኖራችንና በዚህ ተስፋም መኖራችን በጣም አስፈላጊ ነው፡፡
እዚህ ላይ ከውሃውና ከመንፈሱ ወንጌል ጋር ከመገናኘታችንና በታላቁ
የእግዚአብሄር ፍቅር ደህንነታችንን ከማግኘታችን በፊት ሁላችንም በፍጥረታችን
የቁጣ ልጆች እንደነበርን ማስታወስ ይገባናል፡፡ ለሲዖል የታጫችሁ እንደነበራችሁ
ታምናላችሁን? በፍጥረታችን የቁጣ ልጆች እንደነበርን በልቦቻችን ማመንና
የወንጌልን እውነት ማሰላሰል በእጅጉ ያስፈልገናል፡፡ ይህንን በልባችሁ እመኑ፡፡
ለሲዖል የታጫችሁ ብትሆኑም ጌታ ከታላቅ ፍቅሩ የተነሳ እንዳዳናችሁ እመኑ፡፡
እግዚአብሄር በመንግሥቱ ውስጥ እንድንኖርና ክብሩንና ግርማውን ሁሉ
እንድናጣጥም የባረከን የመሆኑን እውነታ ተገንዘቡ፡፡
እግዚአብሄር የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለሚመጡት ዘመናት
እንዲያሰራጭ የደህንነትን እውነት ለሐዋርያው ጳውሎስ እንደገለጠለት ሁሉ
እግዚአብሄር እኛም ደግሞ ይህንን እውነተኛ ወንጌል በዚህ ዘመን ላለ ለእያንዳንዱ
ሕዝብና ትውልድ እንድንሰብክ ይህንን የደህንነት እውነት ገልጦልናል፡፡
እግዚአብሄር በቃሉ አማካይነት ትክክለኛውን የደህንነት እውነት የገለጠው ለዚህ
ዓላማ ነው፡፡ ለእግዚአብሄር ቃል ምስጋና ይሁንና እኛ ትክክለኛውን የደህንነት
ወንጌል ወደ ማወቅ ደርሰናል፡፡ እንዲህ የእግዚአብሄር ሠራተኞች ከሆንን በኋላ
አሁን ለእርሱ ጽድቅ እየኖርን ነው፡፡ እግዚአብሄር እንዲህ ያለውን ድንቅ ሕይወት
የሰጠን ሊባርከን እንደሆነ አምናለሁ፡፡ ሁላችንም ይህንን እውነት ማጋራት
አለብን፡፡
አጋር ምዕመናኖቼ የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል በዚህ ምድር ላይ
የእግዚአብሄር ልጅ ሥልጣን እንዲኖረንና ወደፊትም ክብሩን እንድንቀበል
አስችሎናል፡፡ እኛም ይህንን እውነተኛ ወንጌል ከሙሉ ልቦቻችን እናምናለን፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


160 እኛ በእግዚአብሄር ፊት ምን ዓይነት ሰዎች ነበርን?

በጌታ ፍቅርና በጸጋው መኖራችን በሕይወታችንም ይህን ክቡር ወንጌል እየሰበክን


መሆናችን እንዴት ያለ በረከት እንደሆነ ታውቃላችሁን? ሁላችንም ይህንን ልናውቅ
ይገባናል፡፡ በእግዚአብሄር ጸጋና ፍቅር ስለምናምን ምስጋናችንን ሁሉ ለእርሱ
እንሰጣለን፡፡
ሐሌሉያ! 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ስብከት
9

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት
ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
በሐጢያቶቻችን ምክንያት
ከእግዚአብሄር አብ ተለይን ነበር
‹‹ ኤፌሶን 2፡14-22 ››
‹‹እርሱ ሰላማችን ነውና፤ ሁለቱን ያዋሃደ፣ በአዋጅ የተነገሩትንም
የትዕዛዛትንም ሕግ ሽሮ በመካከል ያለውን የጥል ግድግዳን በሥጋው ያፈረሰ፣
ይህም ከሁለታቸው አንድን አዲስን ሰው በራሱ ይፈጥር ዘንድ፣ ሰላምንም ያደርግ
ዘንድ፣ ጥልንም በመስቀሉ ገድሎ በእርሱ ሁለታቸውን በአንድ አካል ከእግዚአብሄር
ጋር ያስታርቅ ዘንድ ነው፡፡ መጥቶም ርቃችሁ ለነበራችሁ ለእናንተ ሰላምን ቀርበው
ለነበሩትም ሰላምን የምሥራች ብሎ ሰበከ፡፡ በእርሱ ሥራ ሁላችን ወደ አብ
መግባት አለንና፡፡ እንግዲያስ ከእንግዲህ ወዲህ ከቅዱሳን ጋር ባላገሮችና
የእግዚአብሄር ቤተ ሰዎች ናችሁ እንጂ እንግዶችና መጻተኞች አይደላችሁም፡፡
በሐዋርያትና በነቢያት መሠረት ላይ ታንጻችኋልና፤ የማዕዘኑም ራስ ድንጋይ
ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፡፡ በእርሱም ሕንጻ ሁሉ እየተጋጠመ በጌታ ቅዱስ ቤተ
መቅደስ እንዲሆን ያድጋል፡፡ በእርሱም እናንተ ደግሞ መኖሪያ ለመሆን በመንፈስ
አብራችሁ ትሠራላችሁ፡፡››

ኢየሱስ አዳኛችንና የሰላም ንጉሥ ነው፡፡ ሰዎች ሁሉ በሐጢያቶቻቸው


ምክንያት የእግዚአብሄር ጠላቶች ሆነው ሳሉ የእግዚአብሄር ልጅ የሆነው ኢየሱስ
የሰው ስጋ ለብሶ ወደዚህ ምድር በመምጣትና በዮርዳኖስ ወንዝ በአጥማቂው
ዮሐንስ በመጠመቅ የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ ለአንዴና ለመጨረሻ ተሸከመ፡፡
ኢየሱስ ክቡር ደሙን በመስቀል ላይ ያፈሰሰው በሦሰት ቀናቶች ውስጥም ዳግመኛ
ከሙታን የተነሳውና ከዚያም ፈራጅ ሆኖ በእግዚአብሄር አብ ቀኝ የተቀመጠው
ለዚህ ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ከእግዚአብሄር ጋር ለማስታረቅ ዘላለማዊ
የሰላም ማስተሰርያችን ሆኖ ራሱን አቀረበ፡፡ ኢየሱስ ራሱን ማስተሰርያችን አድርጎ
ያቀረበው ከእግዚአብሄር የሚለየንን ይህንን የሐጢያት ግድግዳ ለማፍረስና
በእግዚአብሄርና በእኛ በሰዎች መካከል ያለውን ጠላትነት ለመሻር ነበር፡፡
ኢየሱስ የእግዚአብሄርን ትዕዛዛቶች መጠበቅ አቅቶን የሰራናቸውን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


164 በሐጢያቶቻችን ምክንያት ከእግዚአብሄር አብ ተለይን ነበር

ሐጢያቶች በሙሉ ለመደምሰስ ወደዚህ ምድር መጣ፡፡ ከዚያም ጌታ በስጋው


በመጠመቅ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ተሸከመ፡፡ ለእነዚህ ሁሉ ሐጢያቶች
ለመቀጣት በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ሕይወቱን ሰጠ፡፡ በዚህም የገዛ ራሱን ሕይወት
በመክፈል ነፍሳችንን ወደ ሕይወት አመጣት፡፡ ስለዚህ ምስጋና ለኢየሱስ
ይሁንለትና እኛ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የምናምን አማኞች ለዘላለም
ከእግዚአብሄር ጋር መታረቅና በእምነት የእርሱ ልጆች መሆን ችለናል፡፡ ሁሉን
የሚችለው አምላክም አባታችን መሆን ችሎዋል፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ በኢየሱስ
ክርስቶስ የሚያምን ሁሉ ከእግዚአብሄር ጋር እንደታረቀ የተናገረው ለዚህ ነው፡፡
ኢየሱስ እኛን ሐጢያት አልባ ለማድረግ በውሃና በመንፈስ ወንጌል መጣ፡፡
ይህንን እውነተኛ ወንጌል በመከወን ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ደምስሶዋል፡፡ ስለዚህ
በዚህ እውነተኛ ወንጌል ውስጥ ሆነው ኢየሱስን አዳኛቸው አድርገው የሚያምኑ
ሁሉ የሐጢያቶችን ስርየት ተቀብለው የእግዚአብሄር ልጆች ሆነዋል፡፡
ሆኖም በዚህ ዓለም ላይ ገና የእግዚአብሄር ልጆች ያልሆኑ ብዙ ሰዎች አሉ፡፡
ይህ የሆነበት ምክንያት እነዚህ ሰዎች በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የመጣውን
ኢየሱስን አዳኛቸው አድርገው ስለማያምኑ ነው፡፡ ቢሆንም እውነተኛው
የእግዚአብሄር ቃል ወንጌልና በእምነት የሐጢያቶችን ስርየት በተቀበሉ ሰዎች ልቦች
ሁሉ ውስጥ ያለው መንፈስ ቅዱስ እያንዳንዱን አማኝ የእግዚአብሄር ልጅ
ለማድረግ አብዝቶ ይችላል፡፡

ልጅ ሳለች በድህነት ምክንያት በጉዲፈቻ ተወስዳ ስለነበረች ወጣት ሴት


ልጅና እናት የተነገረ ታሪክ፡፡

አሁን ኮርያ ያደገች አገር ብትሆንም ከጥቂት አስርተ ዓመታት በፊት ግን


እንደዚህ አልነበረችም፡፡ እንዲያውም ከግማሽ ምዕተ ዓመት በፊት አውዳሚ
በሆነው የኮርያ ጦርነት ውጤቶች የምትንገዳገድ እጅግ ደሃ ከሆኑ አገሮች አንድዋ
ነበረች፡፡ ደቡብ ኮርያ በተባበሩት መንግሥታት ዕርዳታ የሰሜን ኮርያን ወረራ
ማክሸፍ ብትችልም ጦርነቱ ያመጣው ጥፋት ብዙ አሳዛኝ ጠባሳዎችን ትቶ
አልፎዋል፡፡ ከእነዚህም አንዱ በዚህ አውዳሚ ጦርነት በርካታ ልጆች
ወላጆቻቸውን ማጣታቸው ነበር፡፡ ከእነዚህ ወላጅ አልባ ልጆች ብዙዎቹ ባደጉ
አገሮች በተለይም በበለጠጉ ምዕራባውያን አገሮች ውስጥ በሚገኙ አሳዳጊ ወላጆች
በጉዲፈቻ ተወስደው ነበር፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በሐጢያቶቻችን ምክንያት ከእግዚአብሄር አብ ተለይን ነበር 165

በእነዚያ ወራቶች ብዙ የኮርያ ሴቶችም እንደዚሁ ልጆቻቸውን ማሳደግ


አቅም አልነበራቸውም፡፡ አገሪቱ በሙሉ በጦርነት ስለፈራረሰች አንዳች የሚበላ
ነገር አልነበረም፡፡ ብዙ ሴቶች ልጆቻቸውን መመገብ ባለመቻላቸው ልጆቻቸው
ተርበው ከሚሞቱ ይህ እንደሚሻል በማሰብ በጉዲፈቻ ከመስጠት በቀር ሌላ
ምርጫ አልነበራቸውም፡፡ ሐብታም የሆኑ የውጪ አገር ሰዎች ልጆቻቸውን
በጉዲፈቻ ለመውሰድና በጣም በተሻለ ሁኔታ ለማሳደግ ፈቃደኞች እንደሆኑ
ሲሰሙ ልጆቻቸው በሕይወት ይኖሩ ዘንድ ለማረጋገጥ የመጨረሻ ዕድል አድርገው
ልጆቻቸውን ሰጡ፡፡ ከዚህ የተነሳ ደቡብ ኮርያ የጉዲፈቻ ልጆችን በከፍተኛ ደረጃ
ወደ ውጪ የምትልክ አገር የሚለውን አሳፋሪ ስያሜ አገኘች፡፡
ጦርነቱ ካበቃ ብዙ ዓመታቶች እንዳለፉ የታወቀ ነው፡፡ በዓመታቶች ውስጥ
በጉዲፈቻ የተወሰዱት አብዛኞቹ ልጆችም በአሳዳጊ ወላጆቻቸው ሥር ሆነው
ፍቅርና ሐብት በሞላበት ቤት ውስጥ አድገዋል፡፡ ዕድሜያቸው እየገፋ ሲሄድ
በጉዲፈቻ እንዳደጉ ተገነዘቡ፡፡ ከዚህ የተነሳ ‹‹ወላጆቼ ለምን ተዉኝ? ስለጠሉኝ
ነበር? እንዲህ ሩቅ ወደሆነ አገር ለምን ሰደዱኝ?›› የሚሉ ጠለቅ ያሉ ጥያቄዎችን
በመጠየቅ የወለዱዋቸው ወላጆች ለምን እንደተዉዋቸው ግራ መጋባት ጀመሩ፡፡
ወላጆቻቸው ለምን እንደተዉዋቸው ሙሉ በሙሉ መረዳት አልቻሉም፡፡
ስለዚህ ነፍስ እያወቁ ሲሄዱ ለወላጆቻቸው ያላቸው ጥላቻና ናፍቆት
በተመሳሳይ ጊዜ በልቦቻቸው ውስጥ አደገ፡፡ ራሳቸው ‹‹ወላጆቼ እንዴት ተዉኝ?
እንዴት ወደዚህ ሩቅ አገር ላኩኝ? ጠልተውኛል? የለም ሌላ ምክንያት ሳይኖራቸው
አይቀርም›› ብለው በመጠየቅና መልስ በመስጠት የወለዱዋቸውን ወላጆቻቸውን
ለማስተዋል ሞክረዋል፡፡ እነርሱ የጉርምስና ዓመቶቻቸውን ያሳለፉት በእነዚህ
አሳቦች ቆስለው ነው፡፡ በአንዲቱ ደቂቃ የወለዱዋቸውን ወላጆቻቸውን በማሰብ
በቀጣዩ ደቂቃ ደግሞ እነርሱን በመጥላትና ዳግመኛ ስለወለዱዋቸው ወላጆች
በጭራሽ ላያስቡ በመማል ተሰቃይተዋል፡፡ ነፍስ አውቀው ትዳር መስረተዋል፡፡
የራሳቸውንም ልጆች ወልደዋል፡፡ የራሳቸው ቤተሰብ በጉዲፈቻ ባደጉበት አገርም
ማሳደግ ጀምረዋል፡፡ ነገር ግን ለወለዱዋቸው ወላጆቻቸው ያላቸው ናፍቆትና
ጥላቻ አልከሰመም፡፡
በቅርቡ በኮርያ ያለ አንድ የቴሌቪዥን ጣቢያ በውጪ አገር በጉዲፈቻ
የተወሰዱ የኮርያ ልጆችን ሁኔታ ለመመርመር ወደ ጀርመን ሄዶ ነበር፡፡ አሁን
የምነግራችሁ ታሪክ በኮርያ ስለተወለደችና በአንድ የጀርመን ቤተሰብ በጉዲፈቻ
ስለተወሰደች ሴት ነው፡፡ በታሪካችን ውስጥ የተጠቀሰችው ሴት በጉዲፈቻ
በተወሰደችበት አገር አድጋ የራስዋን ቤተሰብ መስርታለች፡፡ ነገር ግን ጊዜ በገፋ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


166 በሐጢያቶቻችን ምክንያት ከእግዚአብሄር አብ ተለይን ነበር

ቁጥር አንድም ጊዜ እንኳን የወለዱዋትን ወላጆች ለማየት ተመኘች፡፡ የወለዱዋትን


ወላጆችዋን ብዙ ስለናፈቀቻቸቸው ምን እንደሚመስሉ ለማየት ተመኘች፡፡ ነገር
ግን በዚያው ጊዜ ‹‹የራሴ ወላጆች እንዴት ሊተዉኝ ቻሉ? ወደ ጀርመን የላኩኝ
ምን ሁኔታዎች ቢገጥሙዋቸው ነው?›› በሚል ግራ መጋባት ለእነርሱ ካላት ጥላቻ
ጋር ስትታገል ነበር፡፡ ወላጆችዋ ይኖሩ የነበሩትና እርስዋም የተወለደችው በኮርያ
ስለነበር ከኮርያ በሚመጣ በማንኛውም ዜና መሳብዋ የተለመደ ነበር፡፡ ይህንንም
ከተለያዩ ምንጮች ሰምታለች፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ጀርመን ከመጣችበት ጊዜ
ጀምሮ ከ40 ዓመታት በላይ ስላለፉ ያን ጊዜ ኮርያ ሐብታም አገር ሆና አድጋለች፡፡
በዚህ ምክንያት ወላጆቸዋ ያን ያህል ደሃ ሳይሆኑ ለሌሎች አሳልፈው እንደሰጡዋት
በተሳሳተ መንገድ ስላሰበች ለወለዱዋት ወላጆችዋ ያላት ጥላቻ ይበልጥ ጨመረ፡፡
አንድ የቴሌቪዥን ሪፖርተር ከረጅም ጊዜ በፊት በጉዲፈቻ ጀርመን ተወስዳ
የነበረችን ሴት ጎበኘ፡፡ በዚያን ጊዜ እርስዋ በ40ዎቹ አጋማሽ ላይ ነበረች፡፡
አግብታም አንዲት ሴት ልጅ ነበራት፡፡ ደግሞም የቃለ እግዚአብሄር ትምህርት
እየተማረች ነበር፡፡ የቴሌቪዥን ጣቢያው ቀደም ብሎ በመጥራት ቃለ መጠይቅ
ሊያደርግላት ጠይቋት ነበር፡፡ ጋዜጠኛው እርስዋን ቃለ መጠይቅ እንድትሰጥ
ለማግባባት ብዙ ተማጽኖዋት ነበር፡፡ ሴቲቱ ግን አሁንም ስታመነታ ነበር፡፡ የግል
ሕይወቷን ለማጋለጥ እንደምትፈራም ነግራዋለች፡፡ ጋዜጠኛው ግን እንደ እርስዋ
ያሉ አሳዛኝ ክስተቶች ዳግመኛ እንዳይፈጠሩ ብትተባበረው እንደሚደሰት ነገራት፡፡
ለጥቂት ጊዜ ካመነታች በኋላ ይህንን የምታደርገው ከራስዋ ፍላጎቶች ውጪ
ተጨማሪ ልጆች ከወለዱዋቸው ወላጆቻቸው እንዳይነጠሉና በውጪ አገሮች
በጉዲፈቻ እንዳይወሰዱ ለመከላከል ብቻ እንደሆነ በመናገር በመጨረሻ ቃለ
ምልልሱን ለማድረግ ተስማማች፡፡
ጋዜጠኛው የሚከተሉትን ጨምሮ ብዙ ጥያቄዎችን ጠየቀ፡፡ ‹‹አሁኑኑ
ወላጆችሽን ብታገኚያቸው ልትነግሪያቸው የምትፈልጊው የመጀመሪያው ነገር ምን
ይሆናል?›› ያን ጊዜ ሴቲቱ በድፍረት እንዲህ አለች፡፡ ‹‹ለምን እዚህ እንደሰደዱኝ
እጠይቃቸዋለሁ፡፡ ወላጆቼን ባገኛቸው ለምን በጉዲፈቻ እንደሰጡኝ እጠይቃቸው
ነበር፡፡ ሊገቡኝ አይችሉም፡፡ አርቀው እስኪሰዱኝ ድረስ ለምን እንደጠሉኝ
ልጠይቃቸው እፈልጋለሁ፡፡››
የእርስዋ ቃለ መጠይቅ የቴሌቪዥን ጣቢያው በጉዲፈቻ ላይ እየሰራ
በነበረው ጥናታዊ ፕሮግራም ውስጥ በመካተቱ ፕሮግራሙ በዚህ በኮርያ
እንደተሰራጨ ወዲያውኑ ወላጅ እናቷ ነኝ የምትል አንዲት ሴት ከቴሌቪዥን
ጣቢያው ጋር ተገናኘች፡፡ ልጅዋን በዚህ ጥናታዊ ፕሮገራም ላይ ካየቻት በኋላ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በሐጢያቶቻችን ምክንያት ከእግዚአብሄር አብ ተለይን ነበር 167

ልታገኛት ትችል እንደሆነ ለመጠየቅ ከቴሌቪዥን ጣቢያው ጋር ተገናኘች፡፡ ያን


ጊዜ ጣቢያው ወላጅ እናቷ እየፈለገቻት መሆን ለማሳወቅ በጀርመን ካለችው ሴት
ጋር ተገናኘና እርስዋን ለማግኘት ፈቃደኛ ትሆን እንደሆነ ጠየቃት፡፡ ያን ጊዜ እርስዋ
ወላጅ እናቷን ማየት እንደምትፈልግ ለጣቢያው ነገረች፡፡
ወላጅ እናትም የሴት ልጅዋን መምጣት ለመጠበቅ ወደ አየር ማረፊያው
ሄደች፡፡ ሴት ልጅዋን ለማየት ከመጠን በላይ ስለጓጓች አይኖችዋን ከተርሚናሉ
መግቢያ በር በጭራሽ መንቀል አልፈቀደችም፡፡ ሴት ልጅዋ ግን የመድረሻ ጊዜዋ
ካለፈ በኋላም እንኳን ብቅ አላለችም፡፡ ሁሉም ሰው ተስፋ ቆረጠ፡፡ ሁሉም ሰው
ተስፋ ቆርጦ ባለበት ሰዓት የተሳሳተ አገናኝ በረራ እንደያዘችና ለሰባት ሰዓታት ያህል
እንደምትቆይ ከሴቷ ልጅ ሰሙ፡፡ ያን ጊዜ ጋዜጠኛው እናቲቱን የተወሰነ ዕረፍት
ለማድረግ ወደ ምግብ ቤት ወይም ወደ አንድ ሌላ ስፍራ እንድትሄድ አሳብ
አቀረበ፡፡ ያን ጊዜ እናቲቱ እንዲህ አለችው፡- ‹‹ሴት ልጄን ለአስርተ ዓመታት ያህል
ስጠብቃት ኖሬያለሁ፡፡ ስለዚህ ለተጨማሪ ሰባት ሰዓታት መጠበቅ አያቅተኝም፡፡
እዚሁ በአየር ማረፊያው እቆያለሁ፡፡›› እንዲህ በናፍቆት ከጠበቀች በኋላ በመጨረሻ
ሴቷ ልጅ ደረሰች፡፡ የስድስት ዓመት ልጅዋን በእጅዋ ይዛ በአየር ማረፊያው
የመድረሻ በር በኩል ወጣች፡፡
ወላጅ እናቷ የሴት ልጅዋን ፊት በቴሌቪዥን አይታለች፡፡ ምናልባትም በዚህ
ምከንያት ከቴሌቪዥን ጣቢያው አጋሮች ቀድማ ልጅዋን በማግኘቷ ዓይኖችዋ
በዕንባዎች መሞላት ጀመሩ፡፡ ለጉዲፈቻ ከተሰጠችበት ቀን ጀምሮ እናትና ልጅ
እርስ በርስ ሲተያዩ የመጀመሪያ ጊዜ ነበር፡፡ አንዳቸው የሌላኛውን ቃላት መረዳት
ባይችሉም እርስ በርስ በተያዩበት ቅጽበት ተቃቅፈው ተላቀሱ፡፡ እናት አብዝታ
አለቀሰች፡፡ በተደጋጋሚ ይቅርታ ከመጠየቅዋ ብዛት የተነሳ ቃሎችዋ በአየር
ማረፊያው ዙሪያ ያስተጋባ ነበር፡፡
እናት ልጅዋን ወደ ቤቷ ይዛት ሄደችና እነዚያን የናፍቆት ዓመታት ሁሉ
ተወጣች፡፡ የተለያዩ ቋንቋዎችን ስለሚነጋገሩ እርስ በርሳቸው መግባባት እንዳልቻሉ
የታወቀ ነው፡፡ ነገር ግን ቢያንስ ልቦቻቸው እናትና ሴት ልጅ ብቻ ሊኖራቸው
በሚችል የማይበጠስ ማሰሪያ ተሳስሮ ነበር፡፡ እናት ሴት ልጅዋ ስትወለድ ስም
አውጥታላት ነበር፡፡ ሴት ልጅዋም እናቷ ይህንን ስም በጠራች ቁጥር መልስ ትሰጥ
ስለነበር ይህንን ስም ሳታውቀው አልቀረችም፡፡ ስለዚህ የተለያዩ ቋንቋዎችን
ቢናገሩም እርስ በርሳቸው ፊቶቻቸውን በመደባበስና በዓይኖቻቸው በመነጋገር
ብዙ የዝምታ ንግግሮችን መጋራት ችለዋል፡፡
ሴቷ ልጅ ወደ ጀርመን የምትመለስበት ጊዜ ሲደርስ ግንኙነቱን ያቀናበረው

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


168 በሐጢያቶቻችን ምክንያት ከእግዚአብሄር አብ ተለይን ነበር

ጋዜጠኛ ‹‹ወደ ኮርያ የምትመጪና ወላጆችሽን የምትገናኚ ከሆነ ልትጠይቂያቸው


የምትፈልጊው የመጀመሪያው ነገር ለምን በጉዲፈቸ ወደ ውጪ አገር አሳለፈው
እንደሰጡሽ እንደነበር ነግረሽኛል፡፡ ይህንን ጥያቄ ለእናትሽ ጠየቅሻት?›› ብሎ
ጠየቃት፡፡ መልስዋ ያንን ጥያቄ መጠየቁ አስፈላጊነቱ አልታየኝም የሚል ነበር፡፡
በመመለሻዋ ወቅት እንዲህ አለች፡ ‹‹እናቴ አሁንም ደሃ ነች፡፡ በኮርያ ያሉት
ባለጠጎች በጣም ሐብታሞች ከመሆናቸው የተነሳ ከውጪ የሚገቡ የቅንጦት
መኪኖችን ቢነዱም እናቴ ግን አሁንም እየኖረች ያለችው በድህነት ውስጥ እንደሆነ
አይቻለሁ፡፡ እናቴን ባልጠይቃትና እርስዋ ባትመልስልኝም በውጪ አገር ለጉዲፈቻ
የሰጠችኝ በጣም ደሃ ስለነበረችና እኔንም ከዚህ ድህነት ለማዳን ስለፈለገች እንደሆነ
አውቄያለሁ፡፡ ስለዚህ ያንን ጥያቄ አልጠየቅኋትም፡፡ ደግሞም ጥርጣጣሬዎቼና
ጥላቻዬም ከስመዋል፡፡››

በዚህ ታሪክ ውስጥ ያሉት እናትና ሴት ልጅ የተለያዩት በድህነት


ምክንያት እንደነበር ሁሉ እኛም ደግሞ በሐጢያቶቻችን ምክንያት
ከእግዚአብሄር ተለይተን ነበር፡፡

በዚህ ዓለም ላይ ያሉት ሰዎች በሙሉ ከፈጣሪያቸው ከእግዚአብሄር የተለዩት


ለምን ነበር? በታሪካችን ውስጥ ያለችው ሴት ከእናቷ የተለየችው በጦርነቱ ማግስት
ወላጆችዋ እንዲህ ባለ ከባድ ድህነት ውስጥ ስለነበሩ እርስዋን ለመመገብ እንኳን
ምግብ ስላልነበራቸው ነው፡፡ ሴት ልጃቸውን ለማዳን የመጨረሻ አማራጭ
አድርገው በጉዲፈቻ ወደ ውጪ አገር ሊልኩዋት ተገደዱ፡፡ እዚህ ላይ
እንደተጠቀሰችው ሴት ልጅ በራሱ አምሳል በእግዚአብሄር የተፈጠርን ብንሆንም
እኛም ደግሞ ከእግዚአብሄር ተለይተን ነበር፡፡ ይህ ምን ያሳያል? እኛ ሰዎች
ከእግዚአብሄር ተለይተን ከመኖር በቀር ለምን ምርጫ አልነበረንም?
ሰይጣን በእግዚአብሄር ላይ ሐጢያትን እንድንሰራ ስላደረገን ከአምላክ
ተለይተናል፡፡ ከእግዚአብሄር የተለየነው በእግዚአብሄር ላይ በሰራናቸው በእነዚህ
ሐጢያቶች ምክንያት ነው፡፡ እግዚአብሄር እኛን በአምሳሉ ሲፈጥረን የመጀመሪያ
ዕቅዱ የራሱ ሕዝቦች ሊያደርገን ነበር፡፡ በአምሳሉ የፈጠረን ለዘላለም ከእርሱ ጋር
በደስታ እንድንኖር ነበር፡፡ ነገር ግን የወደቀው መልዓክ ሰይጣን ሰውን በውሸቶቹ
ከእግዚአብሄር በመነጠል በሐጢያት እንዲወድቅና ከእግዚአብሄር እንዲኮበልል
አደረገው፡፡ ዲያብሎስ ሰው የእግዚአብሄርን ቃል እንዳያምን ከእግዚአብሄር ጋር

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በሐጢያቶቻችን ምክንያት ከእግዚአብሄር አብ ተለይን ነበር 169

ያለውን ግንኙነት አበላሸ፡፡ በሌላ አነጋገር ሰይጣን ሰዎች በእግዚአብሄር ቃል


እንዳያምኑ አሳታቸው፡፡ ስለዚህ ሰይጣን አዳምና ሔዋን እግዚአብሄር
የከለከላቸውን መልካምንና ክፉን የሚያስታውቅ ዛፍ እንዲበሉ አደረጋቸው፡፡
በዚህ ምክንያት ሰዎች በእግዚአብሄር ፊት ሐጢያተኞች ሆነው ከእርሱ ኮበለሉ፡፡
በአዳምና በሔዋን ውድቀትም ሁሉም ሰው ወዲያውኑ በእግዚአብሄር ፊት
ሐጢያተኛ ሆነ፡፡ ሰው በጣም ዕብሪተኛ በመሆኑ በእግዚአብሄር ቃል ለማመን
እምቢተኛ ከመሆኑም ባሻገር ቃሉን ላለመታዘዝ በመምረጥ የእርሱን ፍቅር ደግሞ
ናቀ፡፡ እግዚአብሄር አዳምንና ሔዋንን የዘላለም ሕይወት ያገኙ ዘንድ ከሕይወት
ዛፍ እንዲበሉ ቢነግራቸውም ከተከለከለው መልካምንና ክፉን ከሚያሰታውቀው
ዛፍ በሉ፡፡ በዚህ ምክንያት እንደ እግዚአብሄር ለመሆን በመሞከር በዕብሪት
ሐጢያት ውስጥ ወደቁ፡፡ በዚህ ዕብሪት የተነሳ አዳምና ሔዋን ቃሉን ባለመታዘዝ
ፍጻሜያቸው በእግዚአብሄር ላይ ሐጢያት መስራት ሆነ፡፡ በዚህ አለመታዘዝ
ምክንያትም ሐጢያት ወደ እያንዳንዱ የሰው ልብ ውስጥ ገባ፡፡ በዚህ ሐጢያት
ምክንያትም ሰዎች ሁሉ ለዘላለም ከእግዚአብሄር ተለዩ፤ ተቆረጡም፡፡ ለረጀም ጊዜ
ከአምላካችን ተለይተን ስንኖር የነበርነው ለዚህ ነው፡፡
በዚህ ሁሉ ዘመን፣ በዚህ ረጅም የመለየት ክፍለ ጊዜ ውስጥ ‹‹እግዚአብሄር
ከፈጠረን በኋላ ለምን ተወን? ለምን በሐጢያት እንድንወድቅ ፈቀደ?
ከመጀመሪያውም ባይፈጥረን ይሻለው ነበር፡፡ ወደ ሲዖል እስከምንጣል ድረስ
በሐጢያቶችን እንድንሰቃይ ብቻ ሐጢያትን የምንሰራ እንዲህ ያለን ደካማ
ፍጡራኖች አድርጎ የፈጠረን ለምንድነው?›› በማለት ለወዮታዎቻችን ሁሉ
እግዚአብሄርን ስንወቅስ ነበር፡፡ እንዲህ ያሉ በርካታ መልስ የሌላቸውን ጥያቄዎች
ይዘን በመኖራችን ለእግዚአብሄር ያለንን ጥላቻ አዳብረነዋል፡፡
ሆኖም በዚህ ጊዜ ሁሉ ፈጣሪያችን እግዚአብሄር በተጨባጭ ወዶናል፡፡
እግዚአብሄር አብዝቶ ስለወደደን እኛን ለመመለስ አንድያ ልጁን ኢየሱስ ክርስቶስን
የሰው ስጋ አልብሶ ወደዚህ ምድር ላከው፡፡ በሐጢያቶቻቸው ምክንያት ወደ
እግዚአብሄር አብ ፊት መቅረብ ለማይችሉ ሰዎች ሁሉ ሲልም የእግዚአብሄር ልጅ
ተጠመቀ፤ በመሰቀል ላይም ደሙን አፈሰሰ፤ ዳግመኛም ከሙታን ተነሳ፡፡ በዚህም
ጌታ መላውን የሰው ዘር ከሐጢያቶቹና ከኩነኔው አዳነ፡፡ በሌላ አነጋገር
እግዚአብሄር እንደገና በክንዶቹ ሊያቅፈን ፈለገ፡፡ ይህንን በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል አማካይነት ለአንዴና ለመጨረሻ አከናወነው፡፡
በኢየሱስ ከማመናችን በፊት ሁላችንም እግዚአብሄር ለምን ባለንበት ሁኔታ
እንደፈጠረን ግራ ተጋብተን ስለነበር በዚህ ምክንያት እርሱን ጠልተነው ነበር፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


170 በሐጢያቶቻችን ምክንያት ከእግዚአብሄር አብ ተለይን ነበር

ነገር ግን በሁለቱም የቅዱሳት መጻህፍት ኪዳናት ውስጥ በተጻፈው በውሃውና


በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት የእግዚአብሄርን ፍቅርና እርሱም ለእኛ ያለውን
ፍላጎት አውቀናል፡፡ ከዚህ የተነሳ አሁን ለእግዚአብሄር ያለንን ጥላቻ በሙሉ
ከመጣላችንም በላይ ይበልጥ በዋናነት የእርሱን ጽድቅ ወደ መረዳት ደርሰናል፡፡
እኛ በእግዚአብሄር ወደዚህ ምድር በተላከው በኢየሱስ ጽድቅ በማመን እንደገና
ከእግዚአብሄር ጋር መታረቅ ችለናል፡፡ ምክንያቱም በታሪካችን ውስጥ በጉዲፈቻ
የተወሰደችውን ሴት ከእናቷ የለየው የልብ ግድግዳ እንደፈረሰ ሁሉ አሁን ከእርሱ
የለየን የሐጢያት ግድግዳም እንደዚሁ ሙሉ በሙሉ ፈርሶዋል፡፡

መጽሐፍ ቅዱስ ጌታ የሐጢያቶቻችንን ግድግዳ


ለማፍረስ ወደዚህ ምድር እንደመጣ ተናግሮዋል፡፡

የነገርኋችሁን ይህን ጥናታዊ ፕሮግራም ስመለከት የተማርሁት አንድ


መንፈሳዊ ትምህርት አለ፡፡ አንዲትን እናት ለዘላለም ከልጅዋ ሊለያት የሚችል
ምንም ነገር እንደሌለ ሁሉ ማንኛውም መከራ፣ ማንኛውም አለመግባባት፣
ማንኛውም እርግማን ወይም ማንኛውም ሐጢያት መቼም ቢሆን ከእግዚአብሄር
ሊለየን እንደማይችል በጥልቀት ተረድቻለሁ፡፡ ጥናታዊውን ፕሮግራም መመልከቴ
‹‹በእግዚአብሄርና በሰዎች መካከል ያለው ግንኙነትም ልክ እንደዚሁ ሊሆን
ይገባል፡፡ እግዚአብሄር ሰዎችን ቢወድና ሰዎችም እርሱን ቢወዱት እንኳን እርሰ
በርሳቸው ሊለያዩ ይችላሉ፡፡ እናት ሴት ልጅዋን በጉዲፈቻ አርቃ ወደ ጀርመን
የላከቻት ስለጠላቻት አይደለም፡፡ ነገር ግን ምርጫ ስላልነበራት ነው፡፡ ልክ እኛም
ከእግዚአብሄር የተነጠልንበት አንድ የማናመልጠው ምክንያት አለ›› ብዬ በማሰብ
ከእግዚአብሄር ጋር ያለንን ግንኙነት አስታወሰኝ፡፡
በግልጥ አነጋገር ከእግዚአብሄር ያራቁን ሌላ ሳይሆን ሐጢያቶቻችን ናቸው፡፡
እግዚአብሄር ለሁላችንም ትልቅ ዕቅድ አለው፡፡ ከእግዚአብሄር መለየታችንን
የሚያብራራ ሌላ ምንም ምክንያት አልነበረም፡፡ እግዚአብሄርን የምንጠላበትም
ምንም ምክንያት አልነበረም፡ እግዚአብሄርና እኛ እንዋደዳለን፡፡ እኛ እርሱን
እንደምንወደው እግዚአብሄር አሁንም እንኳን ይወደናል፡፡ በሁለቱ መካከልም
ጥላቻ የለም፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በሐጢያቶቻችን ምክንያት ከእግዚአብሄር አብ ተለይን ነበር 171

ይህንን ከዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ መረዳት እንችላለን፡፡

ወደ ኤፌሶን 2፡13-15 ስንመለስ ከእግዚአብሄር ጋር ያለን ግንኙነት እንዴት


እንደተመለሰ መረዳት እንችላለን፡- ‹‹ያለ ክርስቶስ ነበራችሁ፡፡ በክርስቶስ ኢየሱስ
ሆናችሁ በክርስቶስ ደም ቀርባችኋል፡፡ እርሱ ሰላማችን ነውና፤ ሁለቱን ያዋሃደ፣
በአዋጅ የተነገሩትንም የትዕዛዛትንም ሕግ ሽሮ በመካከል ያለውን የጥል ግድግዳን
በሥጋው ያፈረሰ፣ ይህም ከሁለታቸው አንድን አዲስን ሰው በራሱ ይፈጥር ዘንድ፣
ሰላምንም ያደርግ ዘንድ፣ ጥልንም በመስቀሉ ገድሎ በእርሱ ሁለታቸውን በአንድ
አካል ከእግዚአብሄር ጋር ያስታርቅ ዘንድ ነው፡፡›› በዚህ ምንባብ ውስጥ እኛ ሰዎች
ወደ እግዚአብሄር ለመቅረብ ያደረግነው አንዳች ነገር እንዳለ የተጻፈበት ቦታ
የለም፡፡
ለእናንተና ለእኔ እንደዚሁም ለመላው የሰው ዘር ሲል እግዚአብሄር ራሱ
በአዋጅ የተነገሩትን የትዕዛዛትን ሕግ ለመሻር በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅና
ደሙን በማፍሰስ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ተሸከመ፡፡ እኛን ከእግዚአብሄር የለየንን
የሐጢያት ግድግዳ ለማፍረስ ልጁ ኢየሱስ ወደዚህ ምድር መጣ፤ ተጠመቀ፤
የሕይወት ደሙንም በመስቀል ላይ አፈሰሰ፡፡ በዚህ የሕይወት ዋጋም ሰዎችን ሁሉ
ከሐጢያቶቻቸውና ከኩነኔ አዳናቸው፡፡ እግዚአብሄር የገዛ ራሱን ልጅ ኢየሱስን
መስዋዕት በማደረግ መለሰን፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሄር አብዝቶ ስለወደደን
እንዳዳነንና በክንዶቹም እንዳቀፈን በግልጥ ጽፎዋል፡፡ እዚህ ላይ በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል እውነት አማካይነት ደህንነታችንን እንዳገኘን ያለ ምንም ጥርጣሬ
ማረጋገጥ እንችላለን፡፡

የማይካደው የኢየሱስ ጥምቀት አስፈላጊነት፡፡

በዚህ ዓለም ላይ ውሃ ባይኖር ኖሮ ምን ይፈጠር ነበር? ዓለም ምን


እንደመትመስል ገምቱ፡፡ በቅርቡ በኢንቾን በምትገኘው ቅርንጫፍ
ቤተክርስቲያናችን የመነቃቃት ስብሰባ አድርጌ ነበር፡፡ በመነቃቃት ስብሰባው
የመጨረሻ ቀን ላይ ውሃ ከቤተክርስቲያን ተቋረጠ፡፡ በሕንጻው ውስጥ ምንም
የቧንቧ ውሃ ስላልነበረ አደራጆቹ ሳህኖችን ማጠብ እንኳን አልቻሉም፡፡ ስለዚህ
ምሳ ሲቀርብ ሳህኖቹን በፕላስቲክ መሸፈንና በዚያ ላይ ምግቡን ማስቀመጥ
ነበረባቸው፡፡ የመነቃቃት ሰብሰባዎቻችንን ስናደርግ አብዛኛውን ጊዜ ስብሰባውን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


172 በሐጢያቶቻችን ምክንያት ከእግዚአብሄር አብ ተለይን ነበር

እስከምንጨርስ ድረስ ለበርካታ ቀናት በቤተክርስቲያን እንቆያለን፡፡ የመጨረሻው


ቀን ስብሰባ ምሽት ላይ ሲጠናቀቅ በቀጣዩ ማለዳ ከቁርስ በኋላ ወደ ቤታችን
እንመለሳለን፡፡ በዚያ ቀን ግን የምሽቱ ስብሰባ እንደተጠናቀቀ ሁሉም ወደ ቤቱ
እንዲመለስ መጠየቅ ነበረብኝ፡፡ ውሃ ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ ትዝ አለኝ፡፡
ሴዑል 10 ሚሊዮን ነዋሪዎች ያሉባት ትልቅ ከተማ ነች፡፡ ሴዑል ለአንድ ወር
ያህል ውሃ ቢቋረጥባት ነዋሪዎችዋ ምን ይሆኑ ነበር? ከተማዋ በሙሉ ወደ አንድ
ግዙፍ የቆሻሻ ክምር ትለወጣለች፡፡ እያንዳንዱ ሕንጻ በቆሻሻ ጎርፍ ስለሚዋጥና
በጣም ስለሚጠነባ ከተማይቱ ሰው የሚኖርባት አትሆንም፡፡ ቁሳዊ ጥቅሙን ብቻ
እንኳን ብንመለከት የውሃ አስፈላጊነት ያን ያህል ግልጥ ነው፡፡ መንፈሳዊ ፋይዳውን
ስንመለከት ደግሞ ይበልጥ አስፈላጊ ነው፡፡ ምክንያቱም መጽሐፍ ቅዱስ ‹‹ይህም
ውሃ ደግሞ ማለት ጥምቀት ምሳሌው ሆኖ አሁን ያድነናል›› (1ኛ ጴጥሮስ 3፡21)
ይላልና፡፡
ጌታችን በዚህ ምድር ላይ ባይጠመቅ ኖሮ በእግዚአብሄር በምናምን በሁላችን
ላይ ምን ይፈጠር ነበር? በእጅጉ ቆሻሾች ሆነን እንቀር ነበር፡፡ ጌታችን ወደዚህ
ምድር በመጣ ጊዜ ባይጠመቅ ኖሮ ማለትም ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ባያነጻ ኖሮ
በእግዚአብሄር ማመን ባልቻልንም ነበር፡፡ ብናምንም እንኳን ሁሉም ከንቱ በሆነ
ነበር፡፡ ምክንያቱም እግዚአብሄር በመጨረሻ ሐጢያት አልባዎች ሊያደርገን
እንደማይችል እናውቅ ነበርና፡፡ ኢየሱስ በዚህ ምድር ላይ የውሃ ጥምቀቱን
በመቀበል ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ባይወስድ ኖሮ የልቦቻችንን ሐጢያቶች ማንጻት
ባልቻለ ነበር፡፡ ስለዚህ የኢየሱስ ጥምቀት ውሃ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ያነጻ
የሕይወት ውሃ ነው፡፡
በ1ኛ ጴጥሮስ 3፡21 ላይ እንዲህ ተጽፎዋል፡- ‹‹ይህም ውሃ ደግሞ ማለት
ጥምቀት ምሳሌው ሆኖ አሁን ያድነናል፡፡ የሰውነትን እድፍ ማስወገድ አይደለም፤
ለእግዚአብሄር የበጎ ሕሊና ልመና ነው እንጂ፡፡ ይህም በኢየሱስ ክርስቶሰ ትንሣኤ
ነው፡፡›› ይህ ምንባብ በእጅጉ ግልጥ እንዳደረገው ኢየሱስ በዚሀ ምድር ላይ
በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ለአንዴና ለመጨረሻ
በመውሰድ ሁሉንም አነጻቸው፡፡ በዚህ እውነት የምናምን ሁላችን ልቦቻችን
ለአንዴና ለመጨረሻ ፈጽመው እንደነጹ ያየነው ለዚህ ነው፡፡ ኢየሱስ የዚህን ዓለም
ሐጢያቶች በሙሉ በአንድ ጊዜ የወሰደው በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቁ ነው፡፡
ይህንን ኢየሱስን አዳኛችን አድርገን በማመን የሐጢያቶቻችንን ስርየት መቀበል
የቻልነው ሐጢያቶቻችን በሙሉ ወደ ኢየሱስ ስጋ ስለተላለፉ ነበር፡፡ በአንጻሩ
ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ ባይጠመቅ ኖሮ በኢየሱስ ብናምንም ሐጢያተኞች

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በሐጢያቶቻችን ምክንያት ከእግዚአብሄር አብ ተለይን ነበር 173

ሆነን እንቀር ነበር፡፡ በኢየሱስ ጥምቀት ባናምን ኖሮ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ወደ


እርሱ ማስተላለፍ ባልቻልንም ነበር፡፡ ምንም ያህል ኢየሱስን ተግተን አዳኛችን
አድርገን ያመንን ቢሆንም የረከስን ሐጢያተኞች ሆነን እንቀር ነበር፡፡

ጌታ በጥምቀቱና በመስቀል ላይ ደሙ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ


በማንጻት ሞትን እንድናመልጥ አስተምሮናል፡፡

ወደ ብሉይ ኪዳን እንመለስና ሐጢያቶች እንዴት በውሃ ይነጹ እንደነበር


እንመልከት፡፡ በዘጸዓት 30፡17-21 ላይ እንዲህ ተጽፎዋል፡- ‹‹እግዚአብሄርም
ሙሴን እንዲህ ብሎ ተናገረው፡- የመታጠቢያ ሰንና መቀመጫውን ከናስ ሥራ፡፡
በመገናኛው ድንኳንና በመሠዊያው መካከል እርሱን አድርገህ ውሃን
ትጨምርበታለህ፡፡ አሮንና ልጆቹም እጆቻቸውንና እግሮቻቸውን ይታጠቡበታል፡፡
ወደ መገናኛውም ድንኳን በገቡ ጊዜ ለእግዚአብሄር የእሳት መሥዋዕት ያቃጥሉ
ዘንድ ወደ መሠዊያው ሊያገለግሉ በቀረቡ ጊዜ እንዳይሞቱ ይታጠቡበታል፡፡
እንዳይሞቱም እጆቻቸውንና እግሮቻቸውን ይታጠቡ፡፡ ይህም ለእርሱ ከእርሱም
በኋላ ለዘሩ ለዘላለም ሥርዓት ይሆንላቸዋል፡፡››
ከላይ በተጠቀሰው ምንባብ ላይ እንደተብራራው በመገናኛው ድንኳን
አደባባይ ውስጥ ከናስ የተሰራ የመታጠቢያ ሰን ነበር፡፡ ይህ የመታጠቢያ ሰን
የተሰራውና የተቀመጠው ውሃ እንዲይዝ ነበር፡፡ የናሱ የመታጠቢያ ሰን
የተቀመጠው በመገናኛው ድንኳን አደባባይ መካከል ላይ ነበር፡፡ ከመስዋዕቱ እንስሳ
ጀምሮ እጆችን እስከ መጫንና እስከሚቃጠለው መስዋዕት መሠዊያ ድረስ ሁሉም
በስፍራው እያለ ይህ ከናስ የተሰራው የመታጠቢያ ሰን ቢጠፋ ወይም በመታጠቢያ
ሰኑ ውስጥ ውሃ ባይኖር ኖሮ በመገናኛው ድንኳን ውስጥ የሚያገለግሉ ካህናቶች
ምን ይገጥማቸው ነበር?
ይህንን ጥያቄ በጥንቃቄ እናጢነው፡፡ በብሉይ ኪዳን ዘመን እያንዳንዱ
ሐጢያተኛ በየቀኑ ለእግዚአብሄር መስዋዕት ማቅረብ ነበረበት፡፡ ሐጢያተኛው
ለመስዋዕት ባቀረበው እንስሳ ላይ እጆቹን ከጫነ በኋላ የብሉይ ኪዳን ካህናቶች
ይህንን እንስሳ በማረድ ደሙን ማፍሰስ፣ ስጋውን መበለትና ለእግዚአብሄር
ለማቅረብም ማቃጠል ነበረባቸው፡፡ ስለዚህ እንስሳውን ይገፍፉታል፤ ስቡንም
ያወጣሉ፡፡ የረከሱትን ክፍሎች ቆርጠው በማውጣትም ከሰፈሩ ውጪ
ያቃጥሉዋቸዋል፡፡ ካህናቶቹ ይህንን ሥራ የሚሰሩት ቀኑን ሙሉ ነበር፡፡ በዚህ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


174 በሐጢያቶቻችን ምክንያት ከእግዚአብሄር አብ ተለይን ነበር

ምክንያት ምን ያህል ደም እንደሚበክላቸውና ምን ያህል እንደሚቆሽሹ መገመት


ትችላላችሁ፡፡ የመገናኛው ድንኳን ከናስ በተሰራው በመታጠቢያው ሰን ውስጥ
ምንም ውሃ ባይኖረው በዚያ የሚያገለግሉት ካህናት ሰውነቶቻቸውን ማንጻት
ያዳግታቸው ነበር፡፡ ተራው ሕዝብ ራሱን ከመገናኛው ድንኳን አደባባይ ውጪ
ሲያነጻ ካህናቶች ግን በመገናኛው ድንኳን አደባባይ ውስጥ ሆነው መታጠብ
ነበረባቸው፡፡ ስለዚህ በመገናኛው ድንኳን አደባባይ ውስጥ ከናስ የተሰራው
የመታጠቢያ ሰን ባይኖር ወይም በመታጠቢያው ሰን ውስጥ ውሃ ባይኖር ኖሮ
የሚደረስበት ብቸኛው ድምዳሜ ካህናቶቹ ርኩሳኖች ሆነው ይቀራሉ ማለት ነው፡፡
እግዚአብሄር ለካህናቶቹ ከናስ የተሰራውን የመታጠቢያ ሰን ያዘጋጀው ንጹህ
ሰውነት ይዘው በፊቱ መቀረብ እንዲችሉ ነው፡፡ በእስራኤል ሕዝብ ፋንታ
በመገናኛው ድንኳን ውስጥ የሚያገለግሉት ካህናት ለእግዚአብሄር የመስዋዕት
እንስሶችን ማረድና ማቅረብ ነበረባቸው፡፡ (ሊቀ ካህኑም ራሱ በስርየት ቀን
መስዋዕትን ሲያቀርብ በመስዋዕት እንስሶቹ ላይ እጆቹን ይጭን ነበር፡፡) እነዚህ
ካህናቶች ወደ እግዚአብሄር ቤተ መቅደስ መግባት በሚፈልጉበት ጊዜ ሁሉ ከናስ
በተሰራው የመታጠቢያ ሰን ውስጥ ባለው ውሃ እጆቻቸውንና እግሮቻቸውን
በደምብ መታጠብ ነበረባቸው፡፡ በዚህ መልኩ እጆቻቸውንና እግሮቻቸውን ከቆሻሻ
ማንጻትና ፍጹም ንጹህ በሆነ ሰውነት በእግዚአብሄር ፊት መቅረብ ነበረባቸው፡፡
ምክንያቱም ሞትን መሸሽ የሚችሉበት ብቸኛው መንገድ ያ ነውና፡፡
እግዚአብሄር ማንኛውንም ያልነጻ ሐጢያተኛ ልጁ አድርጎ ሊቀበለው
አይችልም፡፡ አንዳች ሐጢያት ያለበትን ሰው ሁሉ ከመኮነን በቀር ምርጫ
የለውም፡፡ ምክንያቱም እግዚአብሄር ፈጽሞ ሐጢያት አልባና ቅዱስ ነውና፡፡
ስለዚህ ካህናቶችም ቢሆኑ በሰውነታቸው ላይ ይህ የተበላሸና የቆሸሸ የመስዋዕት
እንስሶች ደም እያለ የመገናኛውን ድንኳን መጋረጃ በር ከፍተው ወደ ውስጥ ሊገቡ
አይችሉም ነበር፡፡ እግዚአብሄር ካህናት ለእስራኤል ሕዝብ መስዋዕቶችን ካቀረቡ
በኋላ ወደ አምላክ ፊት መቅረብ በሚፈልጉበት ጊዜ ሁሉ በመጀመሪያ ከናስ
በተሰራው የመታጠቢያ ሰን ውስጥ ባለው ውሃ ርኩሰታቸውን ሁሉ ፈጽመው
ማንጻት እንደሚገባቸው ያዘዘው ለዚህ ነው፡፡
እግዚአብሄር ከእንግዲህ ወዲህ ዝናብ ባያዘንብ በዚህ ዓለም ላይ ምን
ይፈጠራል? ስለዚህ ነገር ለጥቂት ጊዜ አስቡ፡፡ ምንም ዝናብ ከሌለ መላው ዓለም
አንድ ግዙፍ የቆሻሻ ክምር እንደሚሆን የታወቀ ነው፡፡ እግዚአብሄር ዝናብን
ከሰማያት ባያወርድ ይህ ዓለም ሙሉ በሙሉ ይበሰብሳል፡፡ ተፈጥሮ ራስዋ
ሕይወቷን በሙሉ ታጣለች፡፡ የዚህች ፕላኔት ምድር ውበትም በሙሉ ይጠፋል፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በሐጢያቶቻችን ምክንያት ከእግዚአብሄር አብ ተለይን ነበር 175

እግዚአብሄር ማዕበሎች እንዲነሱና አየሩን ለማጽዳት ዝናብ እንዲያወርዱ፣ በምድር


ላይ ያለውንም ሁሉንም ዓይነት ቆሻሻና ብክለት እንዲያነጹና የምንጠጣውንና
ሕይወታችንን የምናቆይበትን ንጹህ ውሃ በማቅረብ እንዲቀጥሉ በመፈቀድ ሉዓላዊ
ሥልጣኑን በአየሩ ጠባይ ላይም የዘረጋው ለዚህ ነው፡፡

ማንም ሰው ያለ ውሃ መኖር ስለማይችል ማንኛውም ሐጢያተኛም ያለ


ኢየሱስ ጥምቀት ሐጢያቶቹን ሁሉ ማንጻት አይችልም፡፡

እኛ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ውስጥ በተገለጠው የእግዚአብሄር ፍቅር


እናምናለን፡፡ በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ጽድቅም ደግሞ እናምናለን፡፡ ኢየሱስ
ወደዚሀ ምድር በመጣ ጊዜ ያደረገው ምንድነው? እግዚአብሄር አብ የሰውን ስጋ
የለበሰውን ልጁን ወደዚህ ምድር ላከው፡፡ ነገር ግን ኢየሱስ በትክክል በዚህ ምድር
ላይ ምን አደረገ? ኢየሱስ በዚህ ምድር ላይ ያደረገው መጀመሪያው የደህንነት ሥራ
በአጥማቂው ዮሐንስ መጠመቅ ነበር፡፡ (ማቴዎስ 3፡13-17) ኢየሱስ ከ2,000
ዓመታት በፊት ወደ ዮርዳኖስ ወንዝ የገባው ይህንን የውሃ ጥምቀት ለመውሰድና
የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ ለመቀበል ነበር፡፡ ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ
መጠመቁ ከብሉይ ኪዳን እጆች መጫን ጋር ተመሳሳይ ትርጉም አለው፡፡ ያም
ማለት በብሉይ ኪዳን ዘመን የሊቀ ካህኑ እጆች በራሱ ላይ በተጫኑ ጊዜ
የሚለቀቀው ፍየል የእስራኤሎችን ዓመታዊ ሐጢያቶች በሙሉ እንደተቀበለ ሁሉ
ኢየሱስም እንደዚሁ አጥማቂው ዮሐንስ እጆቹን በራሱ ላይ በጫነበት ጊዜ የዓለምን
ሐጢያቶች በሙሉ ተቀብሎዋል፡፡ ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ በተጠመቀ ጊዜ
ሙሉ በሙሉ በውሃ ውስጥ ጠልሞ ነበር፡፡ በመንፈሳዊ አነጋገር ይህ የሚያሳየው
በመስቀል ላይ የሚሞት መሆኑን የሚጠቁመውን ሞቱን ነው፡፡
በዚህ ዓለም ላይ ውሃ ባይኖር እንዴት መኖር ትችሉ ነበር? ስለዚህ ጉዳይ
ለጥቂት ጊዜ አስቡ፡፡ በኢየሱስ እንደምናምን ብንናገርም በእርሱ ጥምቀት
እስካላመንን ደረስ ሐጢያቶቻችን ሊደመሰሱ ይችሉ ነበር? አይችሉም! ኢየሱስ
በዚህ ምድር ላይ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ የተሸከመው በጥምቀቱ አማካይነት
ነው፡፡ ስለዚህ በዚህ ጥምቀት ከሙሉ ልባችን እስካላመንን ድረስ ቅዱሱን አምላክ
ልንቀርበው አንችልም፡፡ ምክንያቱም ገና ሐጢያተኛ ነንና፡፡ እግዚአብሄር
ሐጢያተኛና ርኩስ የሆነውን ማንኛውንም ሰው እንዴት የራሱ ልጅ ብሎ ሊጠራው
ይችላል? እግዘአበሄር እንዲህ ያሉትን ሰዎች በፍጹም ልጆቼ ብሎ አይጠራቸውም፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


176 በሐጢያቶቻችን ምክንያት ከእግዚአብሄር አብ ተለይን ነበር

እግዚአብሄር ልጆቹ ያደረጋቸው ጌታ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል


ሐጢያቶቻቸውን በሙሉ እንደደመሰሰላቸው የሚያምኑትን ሰዎች ብቻ ነው፡፡ ይህ
በአሁኑ ጊዜ የተለመደ ተራ ትምህርት አይደለም፡፡
እግዚአብሄር አብ አጥማቂውን ዮሐንስንና ኢየሱስን ወደዚህ ምድር መላኩ
በእጅጉ አስፈላጊ ነበር፡፡ ነገሩ ከሁለቱ አንዱ ያስፈልጋሉ የማለት ጉዳይ
አልነበረም፡፡ በዚህ ዓለም ላይ የሚኖር እያንዳንዱ ሕያው ፍጡር በሕይወት
መቆየት የሚችለው ውሃ ሲኖር ብቻ እንደሆነና እያንዳንዱ ነገርም መንጻት
የሚችለው ውሃ ሲኖር ብቻ እንደሆነ ሁሉ ጌታችንም በአጥማቂው ዮሐንስ
የተጠመቀው፣ ተሰቅሎ የሞተውና ተመልሶ በሕይወት የተነሳው እኛን ለማንጻትና
በዚህም ሁላችንንም ለማዳን ነበር፡፡ የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ለሐጢያቶቻችን
ስርየትና ለደህንነታችን በእጅጉ አስፈላጊ ነው፡፡
ጌታችን በውሃና በመንፈስ ከረከሱት ሐጢያቶቻችን ሁሉ በማንጻት
አድኖናል፡፡ በሌላ አነጋገር ጌታችን ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ለመሸከም በአጥማቂው
ዮሐንስ በመጠመቅ አነጻቸው፡፡ ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ በተጠመቀ ጊዜ
መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል ከሰማያት ወረደ፡፡ ይህም ደህንነታችን የተከናወነው
በእግዚአብሄር አብ፣ በኢየሱስ ክርስቶስና በመንፈስ ቅዱስ እንደሆነ ያሳየናል፡፡
ኢየሱስ ከአጥማቂው ዮሐንስ የተቀበለው ጥምቀት ጌታችን እያንዳንዱን ሰው
ከሐጢያቶቹ ሁሉ ለማዳን የመላውን የሰው ዘር ሐጢያቶች በሙሉ እንደተሸከመ
የሚያውጀውን አስፈላጊውን የተዋበ ወንጌል ፍሬ ነገር የያዘ ነው፡፡ በሌላ በኩል
ኢየሱስ በመስቀል ላይ የተቀበለው ቅጣት የሰውን ዘር ሐጢያቶች በሙሉ ዋጋ
ለመክፈል የተሸከመው ኩነኔ ነው፡፡
ስለዚህ ኢየሱስ በእኛ ፋንታ የተቀበለው ጥምቀትና በእኛ ፋንታም
የሐጢያቶቻችንን ሁሉ ዋጋ ለመክፈል ያፈሰሰው ደም ራስ ወዳድ ያልሆነውን
የእግዚአብሄር ፍቅር የያዙ ናቸው፡፡ እርሱ ቅጣትን እንዲቀበል የሚያደርገው
በፍጹም አንዳች ሐጢያት ያልሰራና አንዳች የተሳሳተ ነገር ያላደረገ ቢሆንም እኛን
ከዓለም ሐጢያቶች ሁሉ ለማዳን ሰው ሆነ፡፡ በሮም ወታደሮች ተደበደበ፤ ተናቀ፡፡
በሐጢያቶቻችን ምክንያተም በእኛ ፋንታ ለሞት ተሰጠ፡፡ ከሙታንም ተነሳ፡፡
በዚህም ኢየሱስ በዚህ ምድር ላይ በኖረው የሕይወቱ 33 ዓመታቶች አማካይነት
እኛን ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ለማዳን ደህንነታችንን ያለ እንከን ፈጸመ፡፡
ኢየሱስ ሰው ከሆነ በኋላ የእናንተንና የእኔን ሐጢያቶች ለመደምሰስ
በመጀመሪያ ምን አደረገ? እኛን ሰዎችን ፈጽሞ ሐጢያት አልባ ለማድረግ
በአጥማቂው ዮሐንስ ተጠመቀ፡፡ ኢየሱስ ወደዚህ ምድር በመጣ ጊዜ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በሐጢያቶቻችን ምክንያት ከእግዚአብሄር አብ ተለይን ነበር 177

የተጠመቀውና ደሙን ያፈሰሰው እኛን የእግዚአብሄር ልጆችና ጻድቅ ሰዎች


ለማድረግ ነበር፡፡ ኢየሱስ ጥምቀቱን ከአጥማቂው ዮሐንስ በመቀበል እኛን
ሐጢያት አልባ ሰዎች አደረገን፡፡ እርሱ በጥምቀቱና በመስቀል ላይ ደሙ
የሚያምኑትን ሁሉ ፈጽሞ ሐጢያት አልባ አድርጎዋቸዋል፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስ ለደህንነታችን ያደረገው ብቸኛው ነገር በመስቀል ላይ
መሞት አልነበረም፡፡ በመስቀል ላይ ከመሰቃየቱ በፊት ከአጥማቂው ዮሐንሰ
በመጠመቅ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ተሸክሞዋል፡፡ ጌታችን ሰው ከውሃና ከመንፈስ
ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሄርን መንግሥት ሊያይም ሆነ እዚያ ሊገባ
እንደማይችል የተናገረው ለዚህ ነው፡፡ (ዮሐንስ 3፡5) ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ
የተጠመቀው ሐጢያቶቻችንን ለማንጻት ነበር፡፡
እያንዳንዱ ሰው ከእግዚአብሄር ዘንድ የሐጢያቶችን ስርየት መቀበል በእጅጉ
ያስፈልገዋል፡፡ እግዚአብሄርም ይህንን የሐጢያቶች ስርየት ለሰው ዘር ሁሉ
ለመስጠት ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ መጠመቁና በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ደሙን
ማፍሰሱ በእጅጉ አስፈላጊ ነበር፡፡ ሰዎች ከሐጢያቶቻቸው ቅጣት ነጻ መውጣት
የሚችሉበት ብቸኛው መንገድ ኢየሱስ ከአጥማቂው ዮሐንስ የተቀበለውን
ጥምቀትና በመስቀል ላይ ያፈሰሰውን ክቡር ደሙን በማመን ነው፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ የሐጢያት ደመወዝ ሞት መሆኑን ተናግሮዋል፡፡ (ሮሜ
6፡23) ሁላችንም ሰዎች ሆነን ከተወለድንበት ቀን ጀምሮ ሐጢያተኞች ስለሆንን
ሁላችንም የሐጢያቶቻቸንን ደመወዝ በሕይወታችን መክፈል ነበረብን፡፡ ስለዚህ
ኢየሱስ እኛን ከዚህ እርግጠኛ ሞት ሊያድነንና አዲስ ሕይወትን ሊሰጠን የሰውን
ዘር ሐጢያቶች በሙሉ በጥምቀቱ አማካይነት በስጋው ተሸከመ፡፡ ደሙንም
በመስቀል ላይ በማፍሰስ ሕይወቱን ለእኛ አሳልፎ ሰጠ፡፡ በአጭሩ ኢየሱስ ክርስቶስ
እኛን በደሙና በሕይወቱ በመቤዠት ከሐጢያቶቻችን ሁሉ አድኖናል፡፡

ኢየሱስ እነዚህን ነገሮች ያደረገልን አዳኛችን በመሆኑ ነው፡፡

ታሪክዋን ያወራሁላችሁ እናት ተስፋ ከሌለው ድህነት ልታድናት ሴት


ልጅዋን ለጉዲፈቻ አሳልፋ ከመስጠት በቀር ምርጫ አልነበራትም፡፡ ልክ እንደዚሁ
እኛም በሰይጣን ፈተና ውስጥ ስለወደቅንና በእግዚአብሄር ላይ ሐጢያት ስለሰራን
ከእግዚአብሄር ከመራቅ በቀር ምርጫ አልነበረንም፡፡ በሐጢያቶቻችን ምክንያት
ከእግዚአብሄር መለየታችን የማይቀር ነበር፡፡ ነገር ግን ጌታ በዚህ መልኩ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


178 በሐጢያቶቻችን ምክንያት ከእግዚአብሄር አብ ተለይን ነበር

አልተወንም፤ እኛን ለማዳን ወደዚህ ምድር መምጣት ነበረበት፡፡ ስለዚህ


እግዚአብሄር አብ አንድያ ልጁን ወደዚህ ምድር ላከው፡፡ የዓለምን ሐጢያቶች
በሙሉ ይወስድ ዘንድም እንዲጠመቅ አደረገው፡፡ በዚህ በልጁ ጥምቀት ውሃም
እያንዳንዱን ሰው ፍጹም ሐጢያት አልባ ፍጡር አድርጎ አነጻው፡፡ በሌላ አነጋገር
እግዚአብሄር በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት እንደገና ልጆቹ ሊያደርገን
ሐጢያተኞች ከመሆን መለሰን፡፡
ውሃ በዋጋ አይተመንም፡፡ ውሃ ከሌለ ማንም ሰው በሕይወት ሊቆይ
አይችልም፡፡ ውሃ ለስጋዊ ሕይወታችን አስፈላጊ እንደሆነ ሁሉ የኢየሱስ ክርስቶስ
የውሃ ጥምቀትም እንደዚሁ እያንዳንዱ ሰው ዳግመኛ ይወለድ ዘንድ አስፈላጊ
ነው፡፡ እዚህ ላይ ቀድሞውኑም ዳግመኛ የተወለዳችሁ ብትሆኑም እንኳን በኢየሱስ
ጥምቀት በማመን መቀጠል እንዳለባችሁ ልትገነዘቡ ይገባችኋል፡፡ አለበለዚያ
እንደገና ትረክሱና ከእግዚአብሄር ትለያላችሁ፡፡
ሁላችንም ለሐጢያቶቻችን ለመሞት የተመደብን ብንሆንም ኢየሱስ
ክርስቶስ አዳኛችን ሆኖ ወደዚህ ምድር መጣ፡፡ እኛን ክፉ የሆንን ሐጢያተኞችም
በጥምቀቱ ውሃና በመስቀል ላይ ደሙ አድኖናል፡፡ ደህንነታችን ላይ ለመድረስ
በራሳችን ማድረግ የሚኖርብን ምንም ነገር የሌለው ለዚህ ነው፡፡ እኛ ማድረግ
የሚኖርብን ነገር ቢኖር ኢየሱስ ሐጢያተኞችን በሙሉ ለማዳን በዚህ ምድር ላይ
ባደረገው የደህንነት ሥራ ማመን ብቻ ነው፡፡ ኢየሱስ ከሞት የተነሳው በመጠመቅና
በእኛ ፋንታ በመስቀል ላይ በመሞት ነው፡፡ ከዚህም በላይ አሁን ኢየሱስ ክርስቶስ
በእግዚአብሄር አብ ቀኝ ተቀምጦዋል፡፡ በእርሱ ለሚያምንና የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌልን በልቡ ለሚቀበል ሁሉ የደህንነትን ስጦታ እየሰጠ ነው፡፡
ስለዚህ ጌታ የሐጢያቶችን ስርየት ስጦታ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ለሚያምኑ
ሁሉ እየሰጠ ነው፡፡
የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ኢየሱስ በዚህ ምድር ላይ በመጠመቅ በዚህ
ምድር ላይ የሚኖረውን የእያንዳንዱን ሰው ሐጢያቶች በሙሉ እንደተሸከመ
ያውጃል፡፡ ኢየሱስ ይህንን እውነተኛ ወንጌል ስለሰጠን እርሱን የማመሰግንባቸው
ቃላቶች የሉኝም፡፡ እናንተስ ታዲያ? ኢየሱስ በጥምቀቱ አማካይነት የሕይወት
ዘመናችሁን ሁሉ ሐጢያቶች በተሸከመበት በእርሱ ጥምቀት ታምናላችሁን?
ኢየሱስ ይህንን ያደረገላችሁ አዳኛችሁ ስለሆነ ነው፡፡
እኔ በዚያ ጥናታዊ ፕሮግራም በጣም ስለተነካሁ ዓይኖቼ በዕንባዎች
ተሞልተው ብዙ ዕንባዎችን አፍስሻለሁ፡፡ የእንግሊዞች ምሳሌ ደም ከውሃ
ይወፍራል እንደሚል የቤተሰብ ትስስሮች በእርግጥም በዚህ ዓለም ላይ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በሐጢያቶቻችን ምክንያት ከእግዚአብሄር አብ ተለይን ነበር 179

ከማንኛውም ሌላ ነገር ይበልጥ በጣም ጠንካሮች ናቸው፡፡ ነገር ግን ኢየሱስ እኛን


በጥምቀቱና በደሙ አማካይነት በማዳን ለእኛ ያመጣልን የደህንነት ፍቅር ከቤተሰብ
ትስስሮችም ይበልጥ በጣም ይጠነክራል፡፡ ባለፈው ሕይወታችን ሙሉ በሙሉ
ከእግዚአብሄር ከመለየት በቀር ምርጫ ባይኖረንም ኢየሱስ በዚህ ዓለም ላይ እጅግ
ታላቁን ደህንነት ስለሰጠን አሁን ከእግዚአብሄር ጋር ታርቀናል፡፡
ኢየሱስ ራሱ በፈቃዱ በመጠመቅ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ደምስሶዋል፡፡
በእኛ ፋንታ በመሰቀልና ለሐጢያቶቻችንም በመኮነን ከእግዚአብሄር የለየንን
የሐጢያት ግድግዳ አፍርሶዋል፡፡ ስለዚህ በዚህ እውነት የሚያምኑ ሁሉ አሁን
የእርሱ ልጆች ሆነው ከእግዚአብሄር ጋር ያላቸውን ግንኙነት አድሰዋል፡፡ ጌታችን
በእርሱ አምሳል የተፈጠርን ፍጡሮች ሆነን በኤድን ገነት ውስጥ ከእርሱ ጋር
ስንመላለስ ወደነበረበት ወደ ቀድሞው ሁኔታችን እንደገና መልሶናል፡፡
በእርግጥም በወላጅና በልጅ መካከል ያለው ፍቅር ታላቅ ቢሆንም
አምላካችን ለእኛ ያለው ፍቅር ከዚህ ፍቅር በጣም የላቀ በመሆኑ ሊነጻጸር እንኳን
አይችልም፡፡ እናት የልጅዋን ስጋዊ ሕይወት ለማዳን ለልጅዋ ብትሞትም እንኳን
ልጅዋን ከሐጢያቶችና ከበደሎች ማዳን አትችልም፡፡ በአንጻሩ ፈጣሪያችን
እግዚአብሄር ሕይወቱን ለእኛ በመስጠት ሁላችንንም አድኖናል፡፡ ጌታ በዚህ
መልኩ ስላዳነን ለውሃውና ለመንፈሱ ወንጌል ምስጋና ይሁንና ዳግመኛ
ተወልደናል፡፡ እግዚአብሄር ፍቅር ነው፡፡ እርሱ አዳኛችንም ነው፡፡ የኢየሱስ
ጥምቀት ለመላው የሰው ዘር በእጅጉ አስፈላጊ ነው፡፡
በዚህ ዓለም ላይ ያለ ውሃ በሕይወት መቆየት አንችልም፡፡ የኢየሱስ
ጥምቀትና የመስቀል ላይ ሞቱ በእኩል ደረጃ ለደህንነታችን አስፈላጊ ናቸው፡፡
ኢየሱስ ጥምቀቱን ባይቀበል ኖሮ በኢየሱስ ደም ያመንን ብንሆንም እንኳን
ሐጢያት አልባ መሆን ባልቻልንም ነበር፡፡ ነገር ግን ዕድለኞች በመሆናችን ኢየሱስ
ለእኛ ተጠመቀ፡፡ ስለዚህ ሁላችንም ብዙ ጉድለቶች ቢኖሩብንም በኢየሱስ ክርስቶስ
ውሃና በመስቀል ላይ ባፈሰሰው ደሙ ስለምናምን አሁን ወደ እርሱ ለመጸለይና
እርሱን ለማመስገን ወደ እግዚአብሄር ፊት መቅረብ እንችላለን፡፡ ስጋችን
በጉድለቶች የተሞላ ቢሆንም ልቦቻችን አሁን ፈጸመው ንጹሃን ናቸው፡፡ ስለዚህ
ሁላችንም የእርሱ ልጆች ሆነን እግዚአብሄርን ማመስገንና እርሱን ማምለክ
ችለናል፡፡ ይህ ሁሉ የተቻለው ጌታችን በውሃውና በደሙ ፈጽሞ ስላነጻን ነው፡፡
ሆኖም በዚህ ዓለም ላይ ያሉ ብዙ ክርስቲያኖች የሚያምኑት በኢየሱስ ደም
ብቻ ነው፡፡ እነዚህ የተሳሳቱ ክርስቲያኖች በኢየሱስ ደም ብቻ ቢያምኑ
እንደማይኮነኑ ያስባሉ፡፡ ነገር ግን ሰው በኢየሱስ ደም ብቻ የሚያምን ከሆነ ይህ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


180 በሐጢያቶቻችን ምክንያት ከእግዚአብሄር አብ ተለይን ነበር

ሰው ሐጢያቶቹ ገና እንዳልተወገዱና በልቡ ውስጥ እንዳሉ የሚያሳይ ነው፡፡ ውሃ


ከሌለ ዓለም በሙሉ ቆሻሻ እንደሚሆን ሁሉ ኢየሱስም ባይጠመቅ ኖሮ
ሐጢያቶቻችን አሁንም በልቦቻችን ውስጥ ይቀሩ ነበር፡፡ ስለዚህ ልቦቻችን ሙሉ
በሙሉ ሐጢያት አልባ የሚሆኑት በኢየሱስ ጥምቀትና በመስቀል ላይ ደሙ ስናምን
ብቻ ነው፡፡ በሁለቱም ካላመንን ተግተን በኢየሱስ ብናምንም ልቦቻችን አሁንም
ሐጢያተኞች ሆነው ይቀራሉ፡፡
እናንተስ ታዲያ? ኢየሱስ ስለ እናንተ እንደተጠመቀ ታምናላችሁን? ኢየሱስ
እናንተንና እኔን ሐጢያት አልባ ለማድረግ መጠመቁን የሚያውጀውን የውሃና
የመንፈስ ወንጌል ታምናላችሁን? በኢየሱስ ጥምቀትና በመስቀል ላይ ደሙ በማመን
ሙሉ በሙሉ ሐጢያት አልባ እንደሆናችሁና ፈጽሞም ከሐጢያቶቻችሁ ቅጣት
እንደዳናችሁ ታምናላችሁን?
ደህንነታችን የተገኘው በእኛ ሥራዎች እንዳይደለ እውነት ነው፡፡ ነገር ግን
የተገኘው በኢየሱስ ጥምቀትና በመስቀል ላይ ደሙ በማመን ነበር፡፡ ከእግዚአብሄር
ጋር መገናኘት የቻልነውና የእርሱ ልጆች የሆንነው በዚህ እምነት አማካይነት ነው፡፡
ምስጋናዬን ሁሉ ለእግዚአብሄር አቀርባለሁ! 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ስብከት
10

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት
ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
ወሰን የሌላቸው የክርስቶስ
በረከቶች በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል በሚያምን በእያንዳንዱ
ቅዱስ ልብ ውስጥ አሉ
‹‹ ኤፌሶን 3፡1-21 ››
‹‹ስለዚህም አሕዛብ ስለሆናችሁ ስለ እናንተ የክርስቶስ ኢየሱስ እስር የሆንሁ
እኔ ጳውሎስ ለእግዚአብሄር እንበረከካለሁ፡፡ ለእናንተ ስለተሰጠኝ ስለ እግዚአብሄር
ጸጋ መጋቢነት በእርግጥ ሰምታቸኋል፤ አስቀድሜ በአጭሩ እንደጻፍሁ ይህን
ምስጢር በመግለጥ አስታወቀኝ፤ ይህንም ስታነቡ የክርስቶስን ምስጢር እንዴት
እንደማስተውል ልትመለከቱ ትችላላችሁ፡፡ ይህም አሕዛብ አብረው እንዲወርሱ፣
በአንድ አካልም አብረው እንዲሆኑ፣ በወንጌልም መስበክ በክርስቶስ ኢየሱስ በሆነ
የተስፋ ቃል አብረው እንዲካፈሉ ለቅዱሳን ሐዋርያትና ለነቢያት በመንፈስ አሁን
እንደተገለጠ በሌሎቹ ትውልዶች ዘንድ ለሰው ልጆች አልታወቀም፡፡ እንደ ሐይሉ
ሥራ እንደተሰጠኝም እንደ እግዚአብሄር ጸጋ ስጦታ መጠን የወንጌል አገልጋይ
ሆንሁለት፡፡ ፍለጋ የሌለውን የክርስቶስን ባለጠግነት ለአሕዛብ እሰብክ ዘንድ
ሁሉንም በፈጠረው በእግዚአብሄር ከዘላለም የተሰወረው የምስጢር ሥርዓት ምን
እንደሆነ ለሁሉ እገልጥ ዘንድ ይህ ጸጋ ከቅዱሳን ሁሉ ይልቅ ለማንስ ለእኔ ተሰጠ፡፡
ብዙ ልዩ ልዩ የእግዚአብሄር ጥበብ አሁን በቤተክርስቲያን በኩል በሰማያዊ ስፍራ
ላሉት አለቆችና ሥልጣናት ትታወቅ ዘንድ ይህም በክርስቶስ ኢየሱስ በጌታችን
የፈጸመው የዘላለም አሳብ ነበረ፡፡ በእርሱም ዘንድ ባለ እምነታችን በኩል
በመታመን ድፍረትና መግባት በእርሱ አለን፡፡ ስለዚህ ስለ እናንተ ስላለ መከራዬ
እንዳትታክቱ እለምናችኋለሁ፤ ክብራችሁ ነውና፡፡ ስለዚህ ምክንያት በሰማይና
በምድር ያለ አባትነት ሁሉ ከሚሰየምበት ከአብ ፊት እንበረከካለሁ፡፡ በመንፈሱ
በውስጥ ሰውነታችሁ በሐይል እንድትጠነክሩ፣ ክርስቶስም በልባችሁ በእምነት
እንዲኖር እንደ ክብሩ ባለጠግነት መጠን ይስጣችሁ፤ የእናንተ ሥርና መሠረት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


184 ወሰን የሌላቸው የክርስቶስ በረከቶች በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በሚያምን
በእያንዳንዱ ቅዱስ ልብ ውስጥ አሉ

በፍቅር ይጸና ዘንድ ከቅዱሳን ሁሉ ጋር ስፋቱና ርዝመቱ፣ ከፍታውም፣ ጥልቅነቱም


ምን ያህል መሆኑን ለማስተዋል፣ ከመታወቅም የሚያልፈውን የክርስቶስን ፍቅር
ለማወቅ ትበረቱ ዘንድ፣ እስከ እግዚአብሄርም ፍጹም ሙላት ደርሳችሁ ትሞሉ
ዘንድ፡፡ እንግዲህ በእኛ እንደሚሠራው ሐይል መጠን ከምንለምነው ወይም
ከምናስበው ሁሉ ይልቅ እጅግ አብልጦ ሊያደርግ ለሚቻለው ለእርሱ
በቤተክርስቲያን በክርስቶስ ኢየሱስ እስከ ትውልዶች ሁሉ ከዘላለም እስከ ዘላለም
ክብር ይሁን፤ አሜን፡፡››

ለዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ንባባችን ኤፌሶን ምዕራፍ 3ን በሙሉ አንብበናል፡፡


በዚህ ምንባብ አማካይነት እግዚአብሄር ለእኛ ስላደረገው ነገር ልናገር እወዳለሁ፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ ለኤፌሶን ቤተክርስቲያን በጻፈው መልዕክቱ ስለ እግዚአብሄር
ቤተክርስቲያን፣ ስለ ደህንነት ዕቅዱና እግዚአብሄር ለእኛ ስለለገሳቸው የተትረፈረፉ
በረከቶች ይናገራል፡፡
የገላትያ መልዕክት ኑፋቄን እንድንንቅ ሲያስተምረን የኤፌሶን መልዕክት
ደግሞ ስለ እግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ይነግረናል፡፡ መልዕክቱ እግዚአብሄር
በቤተክርስቲያኑ አማካይነት እንዴት አብዝቶ እንደባረከንና እግዚአብሄር
በቤተክርስቲያኑ አማካይነት የትኛውን ወንጌል እንድንሰብክ እንዳደረገን የሚነሱ
እንዲህ ያሉ ጥያቄዎችን ይነካካል፡፡ በሌላ አነጋገር እግዚአብሄር የተትረፈረፉ
በረከቶችን በሕዝቦች ሁሉ መካከል ለማስፋፋት ሥራው እንዴት በቤተክርስቲያኑ
አማካይነት እንደተገለጠ ይናገራል፡፡
ኤፌሶን 2፡20 እንዲህ ይላል፡- ‹‹በሐዋርያትና በነቢያት መሠረት ላይ
ታንጻችኋልና፤ የማዕዘኑም ራስ ድንጋይ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፡፡››
በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ ያሉ ቅዱሳኖች እምነት የተገነባው የት
ላይ ነበር? የተገነባው በአዲስ ኪዳን ሐዋርያቶችና በብሉይ ኪዳን ነቢያቶች መሠረት
ላይ ነበር፡፡ በሌላ አነጋገር የእግዚአብሄር ወንጌልና የደህንነት እውነቱ የተገነቡትና
የተገለጡት በሐዋርያቶች መሠረትና በነቢያት እምነት ላይ ነበር፡፤ እዚህ ላይ ነቢያት
የሚያመለክቱት የብሉይ ኪዳንን ነቢያት ሲሆን ሐዋርያት የሚያመለክቱት ደግሞ
በአዲስ ኪዳን ዘመን ልክ እንደ ጳውሎስ እግዚአብሄር ራሱ ያስነሳቸውን የኢየሱስን
አስራ ሁለቱን ደቀ መዛሙርት ነው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ወሰን የሌላቸው የክርስቶስ በረከቶች በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በሚያምን 185
በእያንዳንዱ ቅዱስ ልብ ውስጥ አሉ

እኛ የመንግሥተ ሰማይ ሕዝቦች ከሆንን እምነታችን በሐዋርያትና


በነቢያት መሠረት ላይ መመስረት አለበት፡፡

ለውሃውና ለመንፈሱ ወንጌል ምስጋና ይሁንና እናንተና እኔ የእግዚአብሄር


ልጆችና የእርሱ ሠራተኞች እንሆን ዘንድ ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ድነናል፡፡ ጠለቅ
ብለን ለመግባት የብሉይ ኪዳን ሕዝብ የእግዚአብሄር ሠራተኞች የሆኑት
በመስዋዕታዊ ስርዓት ላይ ባላቸው እምነት አማካይነት ጸድቀው ነው፡፡ በአዲስ
ኪዳን ግን የእግዚአብሄር አገልጋዮች የሆንነው ኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ ምድር
መምጣቱን፣ በአጥማቂው ዮሐንስ መጠመቁን፣ በመስቀል ላይ መሞቱንና ከሙታን
መነሳቱን በማመን ነው፡፡ እግዚአብሄር በብሉይና በአዲስ ኪዳናት ውስጥ የራሱ
ሕዝብ አድርጎ ያስነሳቸው በእግዚአብሄር ተስፋ የተሰጠውንና የተፈጸመውን
የደህንነት ሥራ ያመኑትን ሰዎች ነው፡፡ እነርሱን በዚህ የእምነት መሠረት ላይ
አጽንቶዋቸዋል፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት የእግዚአብሄር ብቸኛ
ሕዝብ የሆኑት ሰዎች እነዚህ ናቸው፡፡ አሁን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን
ዳግመኛ በተወለድነው በእኛ አማካይነት የመንፈሱ ወንጌል እየተስፋፋ ነው፡፡

እግዚአብሄር የማይመረመረውን ፍቅሩን በኢየሱስ ክርስቶስ


አማካይነት በእኛ ላይ አፍስሶታል፡፡

የኤፌሶን መልዕክት አብዛኛውን ጊዜ ‹‹የግዞት ቤት መልዕክት›. ተብሎ


ይጠራል፡፡ ጳውሎስ ወንጌልን ለመስበክ ‹‹እንደተሰጠኝም እንደ እግዚአብሄር ጸጋ
ስጦታ መጠን የወንጌል አገልጋይ›› (ኤፌሶን 3፡7) እንደሆነ በመናገር ይህንን የኤፌሶን
መልዕክት የጻፈው ከግዞት ቤት ነበር፡፡ ጳውሎስ ለውሃውና ለመንፈሱ ወንጌል ራሱን
በመስጠቱ በግዞት ቤት ውስጥ የነበረ ቢሆንም እንኳን በደስታና በምስጋና ተሞልቶ
ነበር፡፡ እዚህ ላይ ጳውሎስ እግዚአብሄር አብ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
አማካይነት እንዳዳነን፣ ሠራተኞቹ አድርጎ እንደሾመንና የማይመረመረውን
የክርስቶስን ባለጠግነት ለአሕዛቦች ለመስበክ ሐዋርያቶቹ አድርጎ እንዳስነሳን
ይነግረናል፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ በዚህ ቁጥር አማካይነት ሊያስተምረን እየሞከረ ያለው
ነገር ይህ ነው፡፡ እግዚአብሄር በጸጋው ፍለጋ የሌላቸውን የክርስቶስን ባለጠግነቶች
በመላው ዓለም እንድናሰራጭ አድርጎናል፡፡ በሌላ አነጋገር ጳውሎስ እየተናገረ ያለው

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


186 ወሰን የሌላቸው የክርስቶስ በረከቶች በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በሚያምን
በእያንዳንዱ ቅዱስ ልብ ውስጥ አሉ

ስለተትረፈረፈው የእግዚአብሄር ጸጋ ነው፡፡ ስለዚህ በዚህ ሰዓት በዚህ ትምህርት


ላይ የእግዚአብሄርን ቃል ላካፍላችሁና በትምህርቱም ላይ ላሰላስል እወዳለሁ፡፡

የተትረፈረፈው የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ፡፡

ኤፌሶን 3፡10-11ን አብረን እናብብ፡- ‹‹ብዙ ልዩ ልዩ የእግዚአብሄር ጥበብ


አሁን በቤተክርስቲያን በኩል በሰማያዊ ስፍራ ላሉት አለቆችና ሥልጣናት ትታወቅ
ዘንድ ይህም በክርስቶስ ኢየሱስ በጌታችን የፈጸመው የዘላለም አሳብ ነበረ፡፡››
ሐዋርያው ጳውሎስ ሊያስተምረን የፈለገው ነገር የውሃውና የመንፈሱ
ወንጌል የሚሰራጨው በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን አማካይነት እንደሆነ ነው፡፡
የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን አባል የሆነ ሰው በሁለቱም የቅዱሳት መጽሐፍት
ኪዳናት ውስጥ የተገለጠውን የውሃና የመንፈስ ወንጌል ያመነ ሰው ነው፡፡
እግዚአብሄር ‹‹ብዙ ልዩ ልዩ የእግዚአብሄር ጥበብ አሁን በቤተክርስቲያን በኩል
በሰማያዊ ስፍራ ላሉት አለቆችና ሥልጣናት ትታወቅ ዘንድ›› (ኤፌሶን 3፡10)
በቤተክርስቲያኑ አማካይነት ፍለጋ የሌላቸውን የኢየሱስን ባለጠግነቶች
እንድንሰብክ አድርጎናል፡፡
እዚህ ላይ አለቆች የሚያመለክቱት ገዥዎችን ነው፡፡ እኛ በመንግሥተ ሰማይ
እንደምንኖርና እንደምንነግስ የሚያሳይ ነው፡፡ ኢየሱስ በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል አማካይነት ከሐጢያቶቻችንና ከኩነኔ ሁሉ ታድጎናል፡፡ አዲስ ሕይወትንም
ሰጥቶናል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስም ይህንን አዲስ ሕይወት የተቀበለ ሁሉ በሰማይ
ለዘላለም እንደሚኖር እንጂ በጭራሽ እንደማይሞት ተናግሮዋል፡፡ እዚህ ላይ
የተጠቀሱት ‹‹በሰማያዊ ስፍራ ያሉ አለቆችና ሥልጣናት›› የሚያሳዩት በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል በማመን ዳግመኛ የተወለዱ ሁሉ በመንግሥተ ሰማይ
እንደሚነግሱና ግርማ ሞገስ ያለው ሕይወት እንደሚኖሩ ነው፡፡
እኛ በዚህ ዓለም ላይ አንድ ጊዜ ተወልደን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
በማግኘታችንና በእርሱም በማመናችን ወደ ጌታ መንግሥት መግባት እንችላለን፡፡
እኛ አማኞች የእግዚአብሄር ልጆች ሆነናል፡፡ ሰማይ የምንገባበትን የሐጢያቶች
ስርየት ያገኘነውም በእምነታችን ብቻ ነው፡፡ በቅርቡም በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል የምናምን ሁላችን መንግሥተ ሰማይ እንገባለን፡፡ መዳረሻችን የእግዚአብሄር
ሰማያዊ ግዛት ነው፡፡ እዚያም የእግዚአብሄር ልጆች ሆነን መብቶቻችንን በሙሉ
በማጣጣም ለዘላለም እንኖራለን፤ እንነግስማለን፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ወሰን የሌላቸው የክርስቶስ በረከቶች በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በሚያምን 187
በእያንዳንዱ ቅዱስ ልብ ውስጥ አሉ

መጽሐፍ ቅዱስ ይህንን የእግዚአብሄር ክብር ወይም የክርስቶስ ባለጠግነቶች


አድርጎ ገልጦታል፡፡ አሁንም የምንኖረው በዚህ ምድር ላይ ቢሆንም በዚህ ምድር
ላይ ያለው ሕይወታችን ያለን ሁሉም ነገር አይደለም፡፡ ነገር ግን የሚጠብቀን ሌላ
ሕይወት አለን፡፡ እርሱም ፈጽሞ በማንሞትበት በሰማይ ግዛት የምንኖረው ሕይወት
ነው፡፡ ከዚህም በላይ የምንኖረው በእግዚአብሄር ግዛት ብቻ አይደለም፤ ነገር ግን
በዚህ ግዛት ውስጥ ባሉት ፍጥረታቶች ሁሉ ላይ አለቆች ሆነን እንገዛለን፡፡ እዚህ
ላይ ሐዋርያው ጳውሎስ ‹‹ብዙ ልዩ ልዩ የእግዚአብሄር ጥበብ አሁን በቤተክርስቲያን
በኩል በሰማያዊ ስፍራ ላሉት አለቆችና ሥልጣናት ትታወቅ ዘንድ›› (ኤፌሶን 3፡10)
ብሎ ሲናገር ሊነግረን እየሞከረ ያለው ቁልፍ መልዕክት ይህ ነው፡፡ እግዚአብሄር
እንዲህ ያለውን ድንቅ ሕይወት እንድንኖር ሁላችንንም ባርኮናል፡፡

የተትረፈረፈው የክርስቶስ ጸጋ የእግዚአብሄርን ጥበብ አስታውቆናል፡፡

በልግ በክብሩ ሁሉ መጥቶዋል፡፡ የሚለዋወጠው ወቅትም የእግዚአብሄርን


ድንቅ ሥራ እየገለጠ ነው፡፡ ዛፎች ለእግዚአብሄር ምስጋና ይሆን ዘንድ ብዙ ፍሬ
አፍርተው መመልከት እንችላለን፡፡ የተነገረ ቃልም ሆነ የሚደመጥ አንዳች ድምጽ
ባይኖርም መዝሙረ ዳዊት 19፡2 ‹‹ቀን ለቀን ነገርን ታወጣለች፤ ሌሊትም ለሌሊት
ዕውቀትን ትናገራለች›› እንደሚል ፍጥረት ራሱ እግዚአብሄር ለእኛ ያደረጋቸውንና
ወደፊትም የሚያደርጋቸውን ብዙ ነገሮች የእግዚአብሄርንም ግዛት ባለጠግነቶች
ይናገራል፡፡ ሁሉም ነገር ብዙ መከርን የሚሰጥ ፍሬ በሚያፈራበት በዚህ ወቅት
አማካይነት እግዚአብሄር በአምላክ መንግሥት ውስጥ ለዘላለም እንድንኖርና
በፍጥረቶቹ ሁሉ ላይም እንድንነግስ የሚያደርጉንን የተትረፈረፉ የክርስቶስ
በረከቶች እያስታወሰን ነው፡፡
እኛ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የምናምን አማኞች በቅርቡ ወደፊት
በእግዚአብሄር መንግሥት ውስጥ የምንኖር ብቻ ሳይሆን የእግዚአብሄር ልጆች
በመሆናችን ሁሉም መብቶችና ድሎች አሉን፡፡ እግዚአብሄር ‹‹ለእናንተ
በባጀሁላችሁ ዘላለማዊ መንግሥተ ሰማይ አለቆችና ገዥዎች ሆናችሁ እንድትኖሩ
ባርኬያችኋለሁ›› እያለን ነው፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ ይህ እንዴት ያለ አስገራሚና
አስደናቂ በረከት እንደነበር በማወቁ በአፌሶን ላለችው ቤተክርስቲያን ለማብራራት
እየሞከረ ነው፡፡
ይህ እንዴት ያለ ታላቅ በረከት ነው? አሁን በዚህ ዓለም ላይ ብንኖርም ጌታ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


188 ወሰን የሌላቸው የክርስቶስ በረከቶች በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በሚያምን
በእያንዳንዱ ቅዱስ ልብ ውስጥ አሉ

ሲመለስ ሁላችንም ወደ መንግሥቱ እንገባለን፡፡ ለእያንዳንዱ ነገርና ለእያንዳንዱ


ጉዳይ ፍጻሜ እንዳለ ሁሉ ይህም ዓለም ደግሞ ወደ ፍጻሜው መምጣት አለበት፡፡
ወደ ፍጻሜው ሲመጣም የእግዚአብሄር ዘላለማዊ ግዛት በዓይኖቻችን ፊት
ይገለጣል፡፡ እግዚአብሄር መንግሥተ ሰማይን ለሁላችንም ተስፋ ሰጥቶዋል፡፡ በዚህ
መንግሥት ውስጥ የመኖርንና ለዘላለም የመግዛትን መብት ሰጥቶናል፡፡ ስለዚህ
ሁላችንም ይህ እንዴት ያለ አስገራሚና ድንቅ በረከት እንደሆነ ማሰላሰል፣ በእርሱ
ማመን፣ እግዚአብሄር ወደፊት እንድንደሰትበት የሚሰጠንን ክብር ማሰብ፣ በዚህ
ተስፋ ላይም እምነታችንን ማኖርና በተስፋ መኖር ይገባናል፡፡
እግዚአብሄር በእርግጥም አስገራሚ በረከቶችን ሰጥቶናል፡፡ ከእነዚህ
በረከቶች አንዳቸውም በራሳችን ስጋዊ ጥረት የተገኙ አልነበሩም፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ
‹‹ከጸሐይም በታች አዲስ ነገር የለም›› (መክብብ 1፡9) እንደሚል በዚህ ዓለም ላይ
ያለው እያንዳንዱ ነገር በመጨረሻ ሊጠፋና ሊከስም አርጅቶ ይፈራርሳል፡፡ ነገር
ግን በዚህ ዓለም ላይ ፍጹምና ዘላለማዊ የሆነ ምንም ነገር ባናይም የእግዚአብሄር
መንግሥት ለዘላለም ይኖራል፡፡ እግዚአብሄርም በዚህ መንግሥት ላይ ለዘላለም
እንድንገዛና የዘላለምን ሕይወት በክብሩ ሁሉ እንድንደሰትበት ባርኮናል፡፡
ሁላችንም ይህ እንዴት ያለ አስገራሚና አስደናቂ በረከት እንደሆነ መረዳት፣
ይህንንም በልቦቻችን ውስጥ ማስታወስ፣ እግዚአብሄርንም ለብዙ በረከቶቹ
ማመስገንና እርሱንም በሕይወታችን ውስጥ ማክበር ይገባናል፡፡
እግዚአብሄር እንዴት ያለ ድንቅ በረከት ሰጠን? እርሱ ከሐጢያቶቻችን ሁሉ
ያዳነን ከመሆኑም በላይ የሐጢያቶችን ስርየት ከሰጠን በኋላም የእርሱ ልጆች
የምንሆንበትን መብት ለግሶናል፡፡ የእግዚአብሄር ልጅ ከሆናችሁ እግዚአብሄር
ልጆቹ ብቻ የሚደሰቱባቸውን እነዚህን አስገራሚ በረከቶች እንደሰጣችሁ
ልትገነዘቡ ይገባችኋል፡፡ በእግዚአብሄር ግዛት ውስጥ የምትደሰቱበትን ክብራማ
ሥልጣንና ሕይወትም ልትገነዘቡ ይገባችኋል፡፡ እግዚአብሄር እነዚህን በረከቶች
በእናንተና በእኔ በቅዱሳኖቹ ሁሉ ላይ መለገሱ በጣም አስገራሚ በመሆኑ በቃላት
ልገልጠው አልችልም፡፡ ነገር ግን አሁንም በልቤ አምናቸዋለሁ፡፡ እግዚአብሄር እኔን
ከሐጢያቶቼ ሁሉ እንዳዳነኝና እናንተንም ከሐጢየቶቻችሁ ሁሉ እንደታደጋችሁ
ለዘላለም እንድንኖርና በተትረፈረፈ በከበረና ለዘላለም በተባረከ ሕይወትም ደግሞ
ባርኮናል፡፡ እግዚአብሄር ፍለጋ በሌላቸው የክርስቶስ ባለጠግነቶች ውስጥ ሆነን
ይህንን ሕይወት እንድንኖር ሁላችንንም እንደባረከን በሙሉ ልቤ አምናለሁ፡፡
በእግዚአብሄር ፊት የራሳችን የሆነ መልካም ምግባር ባይኖረንም
እግዚአብሄር በተናጥል ካለው ነጻ ምርጫ የተነሳ በክርስቶስ ይህንን የተትረፈረፈ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ወሰን የሌላቸው የክርስቶስ በረከቶች በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በሚያምን 189
በእያንዳንዱ ቅዱስ ልብ ውስጥ አሉ

ሕይወት ሰጥቶናል፡፡ ፍለጋ በሌላቸው የክርስቶስ ባለጠግነቶች ሁሉ ውስጥ ሆነን


እንድንኖር ባርኮናል፡፡ እነዚህ በረከቶች በጣም አስገራሚ በመሆናቸው ሊለኩ
አይችሉም፡፡ እግዚአብሄር ስላዳነን፣ የእርሱን የጽድቅ ሥራ ለመስራትም ሠራተኞቹ
ሆነን እንድንኖር ስለፈቀደልንና ለዘላለም እንድንኖር ስለባረከን በበቂ
አመስግነናል፡፡ ከዚህም በላይ እነዚህ በረከቶች የማይበቁ ይመስል እግዚአብሄር
በመንግሥተ ሰማይ እንድንገዛም መብትን ሰጥቶናል፡፡ እግዚአብሄር በመንግሥቱ
ላይ እንድንገዛ መብትን ስለሰጠን በሰማይ ለዘላለም የማይጠፋ ሕይወትን
እንድንኖር ፈቅዶልናል፡፡ ይህ ታላቅ በረከት ስለሆነ በቃላት ሊገለጥም ሆነ
በማንኛውም መንገድ ሊለካ አይችልም፡፡ እግዚአብሄር የሰጠን በረከቶች መለኪያ
የሌላቸው ታላላቅና ድንቅ ናቸው፡፡ እግዚአብሄር እኛን ከሐጢያቶቻችን ሁሉ
ማዳኑና ፈጽሞ ሐጢያት አልባ ማድረጉ ሁላችንንም ከቃላት በላይ አመስጋኞች
ሊያደርገንና ቀሪውን ሕይወታችንን በምስጋና እንድንኖር ሊያስገድደን በቂ ነው፡፡
ይህ በቂ ያልሆነ ይመስል እግዚአብሄር እነዚህን ታላላቅ የሰማይ በረከቶች
ሰጥቶናል፡፡ የእርሱ ሠራተኞች ሆነን እንድንኖርም አድርጎናል፡፡ ፍለጋ የሌላቸውን
የበረከቶች ሕይወትም ዋስትና ሰጥቶናል፡፡
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምኑ ሁሉ እነዚህን ድንቅ በረከቶች
ከእግዚአብሄር ዘንድ ተቀብለዋል፡፡ ከእግዚአብሄር የተቀበልናቸው እነዚህ ታላላቅ
በረከቶች በእርግጥ ምንኛ ታላቅ እንደሆኑ ልንገነዘብ ይገባናል፡፡ እዚህ ላይ ጌታን
አብዝታችሁ እንድታገለግሉ እየጠየቅኋችሁ አይደለም፡፡ ነገር ግን እግዚአብሄር
እነዚህን መለኪያ የሌላቸውን የተትረፈረፉ የክርስቶስ በረከቶች እንዴት እንደሰጠን
ለመጠቆም ብቻ ነው፡፡ ጳውሎስ በዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ላይ
እያስተማረን ያለው ይህንን ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስም ደግሞ ለሁላችንም እየነገረን
ያለው ይህ ነው፡፡ እግዚአብሄር በመንግሥተ ሰማይ እንድንነግስ መብትን
ሰጥቶናል፡፡ እርሱ በቃላት ሊገለጡ የማይችሉት እነዚህን አስገራሚ በረከቶች
ሰጥቶናል፡፡ ስለዚህ በእነዚህ በረከቶች ላይ ያለንን እምነት ከመመስከር፣ ስለ
እነርሱም እግዚአብሄርን ከማመስገንና አዳኛችንን ኢየሱስ ክርስቶስን ከማወደስ
በቀር ልናደርገው የምንችለው ነገር የለም፡፡
አሁን ሁላችሁም እግዚአብሄር የሰጣችሁን ድንቅ በረከት ማስታወስ
ይገባችኋል፡፡ ‹‹በሰማያዊ ሥፍራ ያሉት አለቆችና ሥልጣናት›› (ኤፌሶን 3፡10)
የሚያመለክተው ማንንም ሳይሆን እናንተንና እኔን እንደሆነ በግልጥ መረዳት
ይገባችኋል፡፡ በዚሀ ምድር ላይ ካለው ሕይወታችን ጋር ዘለቄታዊ ቁርኝት የሌለን
ለዚህ ነው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


190 ወሰን የሌላቸው የክርስቶስ በረከቶች በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በሚያምን
በእያንዳንዱ ቅዱስ ልብ ውስጥ አሉ

ሐዋርያው ጳውሎስ የክርስቶስ በረከቶች ፍለጋ እንደሌላቸው


ተናግሮዋል፡፡

መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሄር ሊለኩም ሆነ ሊቆጠሩ የማይችሉ እነዚህን


ታላላቅ በረከቶች እንደሰጠን ተናግሮዋል፡፡ አብዛኞቹ ነገሮች በበቂ ስሌት ሊለኩ
ይችላሉ፡፡ የጸሐይ ርቀት እንኳን በአንዳንድ ስሌት ሊለካ ይችላል፡፡ ነገር ግን ጌታ
የሰጠን የሐጢያቶች ስርየትና የለገሰን በረከቶች ሊሰሉም ሆነ ሊለኩ አይችሉም፡፡
እዚህ በረከቶች በጣም ታላቅ፣ በጣም ፍጹምና በጣም ዘላለማዊ ስለሆኑ ለእኛ
አስገራሚና አስደናቂ ናቸው፡፡ እግዚአብሄር በእርግጥም ፈጽሞ ሐጢያት አልባ
አድርጎናል፡፡ ኢየሱስን ለአስርተ ዓመታቶች ያህል ያመኑት ቢሆኑም አሁንም
ሐጢያተኛ ሆነው የቀሩ በርካታ ሰዎች በዚህ ዓለም ላይ አሉ፡፡ በአንጻሩ እናንተና
እኔ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን በተጨባጭ ሐጢያት አልባ ሆነናል፡፡
ዛሬ ጠዋት በኮርያ የሚኖርና ኬሪ የሚባል ስም ያለው የውጪ አገር ሰው
ከወንጌል መጽሐፎቻችን አንዱን እንዳነበበና በዚህ ምክንያትም የሐጢያቶችን
ስርየት እንደተቀበለ የሚነግረን ኢሜል ላከልን፡፡ በኢሜሉ እውነትን በመስበካችን
ለኒው ላይ ሚሽንና ለአገልጋዮቹ ሁሉ ታላቅ አክብሮት እንዳለው በመናገር
ውዳሴውን አብራርቷል፡፡ ለረጅም ጊዜ ሰባኪ የነበረ ቢሆንም በልቡ ውስጥ
ሐጢያት እንደነበረበት አሁን ግን ከወንጌል መጽሐፎቻችን አንዱን በማንበቡ
ሐጢያቶቹ በሙሉ በመጨረሻ እንደተደመሰሱ ደግሞ ተናግሮዋል፡፡ የደህንነትን
ወንጌል በመስበካችንም እንደሚያደንቀንና እንደሚያከብረን በመናገር ምስጋናውን
ገልጦዋል፡፡ ኬሪ እንደዳነ ሁሉ እግዚአብሄር ሁላችንንም አድኖናል፡፡ ሙሉ
በሙሉም ሐጢያት አልባ አድርጎናል፡፡
ብዙ ሰባኪዎችና መጋቢዎች ‹‹ጻድቅ የለም አንድ ስንኳ›› የሚለውን ሮሜ
3፡10ን በመጥቀስ በዚህ ዓለም ላይ አንድም ጻድቅ የለም ይላሉ፡፡ በመላው ዓለም
የሚገኙ በርካታ ክርስቲያኖችም እንደዚሁ በዚህ መንገድ ያስባሉ፡፡ ነገር ግን በሮሜ
3፡10 ላይ ያለው ምንባብ በትክከል የሚያስተምረን በልቦቻችን ውስጥ ብዙ
ሐጢያቶች ቢኖሩብንም አሁን በኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ፈጽሞ ሐጢያት አልባ
እንደሆንን ነው፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ ከዚህ በፊት ባለ ዕዳዎች የነበርን ብንሆንም
ለእግዚአብሄር ደህንነት ምስጋና ይሁንለትና አሁን ባለ ዕዳዎች እንዳይደለን
መጠቆሙ ነው፡፡ ጳውሎስ ኢየሱስ ክርስቶስ የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ ደምስሶ
ሳለ አንድም ጻድቅ የሆነ ሰው የለም ማለቱ አልነበረም፡፡ ችግሩ በጣም ብዙ
ክርስቲያኖች አስተውሎታቸውን ከመላው ምንባብ ነጥለው በዚህ አንድ ጥቅስ ላይ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ወሰን የሌላቸው የክርስቶስ በረከቶች በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በሚያምን 191
በእያንዳንዱ ቅዱስ ልብ ውስጥ አሉ

ብቻ በመመስረት የሮሜ 3፡10ን ጠቅላላ አውደ ንባብ መረዳት የተሳናቸውና


ዋናውን መልዕክቱን የሳቱ መሆናቸው ነው፡፡ ሐጢያተኞች ሆነው የሚኖሩት ለዚህ
ነው፡፡
እነዚህ የተሳሳቱ ክርስቲያኖች የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል እንደማያውቁ
የታወቀ ነው፡፡ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል አውቀው ቢሆን ኖሮ የሮሜ
ምዕራፍ 3ን ዋና መልዕክት ይረዱ ነበር፡፡ እንደዚሁም የሮሜ ምዕራፍ 8ን ዋና
ትምህርት ይረዱ ነበር፡፡ በሮሜ 8፡1 ላይ እንዲህ ተጽፎዋል፡- ‹‹እንግዲህ በክርስቶስ
ኢየሱስ ላሉት አሁን ኩነኔ የለባቸውም፡፡›› ይህ ምንባብ እኛ እውነተኛ አማኞች
ፈጽሞ ሐጢያት እንደሌለብን በማያሻማ መልኩ ግልጥ አድርጓል፡፡ እዚህ ላይ
‹‹ኩነኔ›› የሚለው ቃል የሚጠቁመው የሐጢያትን ኩነኔ ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ
ኩነኔ እንደሌለ ሲናገር በክርስቶስ ኢየሱስ ጽድቅ የሚያምን ሁሉ ፈጽሞ ሐጢያት
የለበትም ማለቱ ነው፡፡ ነገር ግን በጣም ብዙ ክርስቲያኖች ይህንን አያውቁም፡፡
የነገርኋችሁ ሰው ኬሪ በዚህ ምድር ላይ አንድም ጻድቅ እንደሌለ አስቦ ነበር፡፡
አሁን ግን የሐጢያቶችን ስርየት ስለተቀበለና ጻድቅ ስለሆነ ይህ ፈጽሞ አመስጋኝና
ደስተኛ ሊያደርገው በቂ ነበር፡፡ ከዚህም በላይ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
መስበክ እንደሚፈልግ በመናገር በአገልግሎታችን ውስጥ አጋር ሠራተኛ አድርገን
እንድንቀበለውም ጠየቀን፡፡ ኬሪ ከውሃውና ከመንፈሱ ጋር በመገናኘቱ ብቻ
በደስታ እንደተጥለቀለቀ እርግጠኛ ነኝ፡፡ አሁን ያስጨነቁት ሐጢያቶች በሙሉ
ስለተወገዱ ምናልባትም በደመናዎች ላይ እየተራመደ የመሆን ስሜት ሳይሰማው
አይቀርም፡፡ ኬሪ ራሱ አምላክ በሆነው በክርስቶስ በተፈጸመው የውሃና የመንፈስ
ወንጌል በማመኑ ልቡ በእርግጥም ሐጢያት አልባ ሆንዋል፡፡
ይህ አመስጋኝ እንዲሆን ሊያደርገው በቂ ነው፡፡ ነገር ግን ፍለጋ የሌላቸውን
የክርስቶስን በረከቶች መልበሱን ከተገነዘበ በኋላ ምን ያህል ብዙ ደስታ ኖሮት
ይሆን? እዚህ ላይ ሐዋርያው ጳውሎስ እነዚህ በረከቶች ከክርስቶስ እንደሚመጡ
አውቋል፡፡ እኛም ደግሞ ጳውሎስ እንደተረዳው እነዚህን በረከቶች ብንረዳ
ሁላችንም በችግሮች ውስጥ እንኳን ብንሆን እግዚአብሄርን ማመስገን እንችላለን፡፡
የዓለም ነገሮች ከእግዚአብሄር መንግሥት ነገሮች ጋር ሲወዳደሩ ምን ያህል
የማይረቡ እንደሆኑ መረዳት ብቻ ሳይሆን በኢየሱስ ክርስቶስ ውስጥ ስለሚገኙት
የማይገለጡ በረከቶችም እግዚአብሄርን ለማመስገን እንገደዳለን፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


192 ወሰን የሌላቸው የክርስቶስ በረከቶች በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በሚያምን
በእያንዳንዱ ቅዱስ ልብ ውስጥ አሉ

ሊገለጡ የማይችሉ ሰማያዊ በረከቶችን ለብሰናል፡፡

ደህንነታችን የተፈጸመው ስለናፈቅነው አልነበረም፡፡ የተፈጸመው


በእግዚአብሄር አብ ፈቃድ ብቻ ነበር፡፡ ደህንነታችንን በራሱ ውዴታ የፈጸመው
ራሱ እግዚአብሄር ነው፡፡ ይህንንም ያደረገው አምላክ በኢየሱስ ክርስቶስ
በፈጸመው የዘላለም ዕቅድ መሠረት ሁሉ ነው፡፡ እኛ ስለ እነዚህ ታላላቅ በረከቶች
ናፍቀንም ሆነ አስበን አናውቅም፡፡ ነገር ግን እግዚአብሄር በኢየሱስ ከርስቶስ
አማካይነት እነዚህን ወሰን የለሽ ታላላቅና ፍጹም የሆኑ በረከቶችን ሰጠን፡፡ እኔ
በዚህ ፍጹም እምነት አለኝ፡፡ ሁላችሁም ደግሞ በዚህ እንድታምኑ
እጠይቃችኋለሁ፡፡
የእግዚአብሄር ጸጋ የማይመረመር ስለሆነ በእርግጥም መግለጫ የለውም፡፡
ይህንን ጸጋ የእኔ ውሱን መዝገበ ቃላትም ሆነ የሌላ የማንኛውም ሰው ማብራሪያ
ሊገልጠው አይችልም፡፡ ነገር ግን ግልጥ የሆነው ነገር በመንግሥተ ሰማይ ለመንገስ
በዘላለማዊ ሥልጣን፣ በዝንተ ዓለም ደስታና በረከቶች ውስጥ ለዘላለም የምንኖር
መሆናችን ነው፡፡ እግዚአብሄር እንዲህ ያለውን አስገራሚ ሕይወት የምንኖርበትን
መብት ሰጥቶናል፡፡ ሁላችንም የምናምነው ያንን ነው፡፡
ጳውሎስ የዓለምን ነገሮች እንደ ጉድፍ እንደቆጠራቸው የተናገረው ለዚህ
ነው፡፡ (ፊልጵስዩስ 3፡8) ይህ ለእኔም ደግሞ እውነት ነው፡፡ እኔ አሁንም ልክ እንደ
ጳውሎስ የዓለምን ነገሮች ሙሉ በሙሉ እንደ ጉድፍ ባልቆጥራቸውም ቢያንስ በዚህ
ዓለም ላይ ያለው ነገር እግዚአብሄር ከሰጠኝ ጋር ሊወዳደር እንደማይችል
አውቃለሁ፡፡ የእግዚአብሄር ስጦታዎች ወሰን የለሽ ናቸው፡፡ የዓለም ነገሮች ግን
ምንም ማለት አይደሉም፡፡
ጳውሎስ በኤፌሶን 3፡18-19 ላይ ‹‹የእናንተ ሥርና መሠረት በፍቅር ይጸና
ዘንድ ከቅዱሳን ሁሉ ጋር ስፋቱና ርዝመቱ፣ ከፍታውም፣ ጥልቅነቱም ምን ያህል
መሆኑን ለማስተዋል፣ ከመታወቅም የሚያልፈውን የክርስቶስን ፍቅር ለማወቅ
ትበረቱ ዘንድ፣ እስከ እግዚአብሄርም ፍጹም ሙላት ደርሳችሁ ትሞሉ ዘንድ››
በማለት ምኞቱን ገልጦልናል፡፡ ጳውሎስ ከእኛ የፈለገው ያንን ነው፡፡ እግዚአብሄር
ልክ የሌላቸውን የተትረፈረፉ በረከቶችም እንደሰጠን እንድንገነዘብ ፈለገ፡፡ እርሱ
ለዘላለም በመንግሥተ ሰማይ እንደንኖርና እንድንገዛ ዘላለማዊ መብት ሰጥቶናል፡፡
ይህ ሁሉ የሆነው በእግዚአብሄር አብ ጥበብ መሠረት ነበር፡፡ እግዚአብሄር አብ
ራሱ ያሰበውም ይህንኑ ነው፡፡ አብ በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ አማካይነት ልጆቹ
አድርጎን ሐጢያቶቻችንን የደመሰሰ ብቻ አይደለም፡፡ ነገር ግን ከኩነኔም ደግሞ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ወሰን የሌላቸው የክርስቶስ በረከቶች በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በሚያምን 193
በእያንዳንዱ ቅዱስ ልብ ውስጥ አሉ

ታድጎናል፡፡ እግዚአብሄር ወንድ ልጆቹና ሴት ልጆቹ አድርጎናል፡፡ ያም ብቻ


አይደለም፡፡ እግዚአብሄር ልጆቹ ብቻ አላደረገንም፡፡ የእግዚአብሄር ልጆች ሆነን
ከጌታ መብቶችና ዕድሎች ሁሉ ጋር በመንግሥተ ሰማይ ለዘላለም እንድንኖር
ባርኮናል፡፡ እነዚህ በረከቶች በጣም ታላቅ ስለሆኑ ቃላት እነርሱን ሁሉ በጭራሽ
መግለጥ አይችሉም፡፡
እኛ ለዘላለም በደስታ የምንኖር መሆናችንና በፍጹም አለመሞታችን
አስገራሚ ነው፡፡ ነገር ግን ይህ በቂ ያልሆነ ይመስል እግዚአብሄር በመንግሥተ
ሰማይ የምንገዛበትን ሥልጣንም ደግሞ ሰጥቶናል፡፡ ሁሉንም ነገር እንደፈለጋችሁ
የምታደርጉበት እዳች ሥልጣን ኖሮዋችሁ ያውቃልን? የእግዚአብሄር
ቤተክርስቲያን አንዳች የዘፈቀደ ሥልጣን የሚተገበርባት ስፍራ እንዳይደለች
የታወቀ ነው፡፡ ይልቁንም ሁላችንም እርስ በርሳችን የምንገለገልባትና እርስ በርሳችን
የምንዋደድባት ስፍራ ነች፡፡
በሌሎች ላይ የመግዛት ሥልጣን ግን የላቁ ተጽዕኖዎችን ይይዛል፡፡ አንድ
የፖለቲካ ሰው የአገር ፕሬዚዳንት ወይም ጠቅላይ ሚኒስትር ሆኖ ሲመረጥና ሲሾም
መንግሥቱን በሙሉ የማዘዝና ፖሊሲዎቹንም የመወሰን ሥልጣን አለው፡፡
ሥልጣን በቃላት ብቻ እያንዳንዱን ነገር ያከናውናል፡፡ እግዚአብሄር ይህንን
ሥልጣን ሰጥቶናል፡፡ ይህ የተባረከ ሕይወት ከአስተውሎታችን በላይ ስለሆነ
ሊለካም ሆነ ሙሉ በሙሉ ሊታወቅ አይችልም፡፡ ከዚህ የተነሳ እግዚአብሄር
ልናያቸውና ይበልጥ ወዲያውኑ ልናጣጥማቸው የምንችላቸውን ጥቂት በረከቶች
ቢሰጠን ደስተኞች እንደምንሆን ወደ ማሰቡ እናዘነብላለን፡፡ ልክ በጠርሙስ ውስጥ
እንዳለው ጂኒ ከምኞቶቻችን ሦስቱን ቢመልስልን እንረካለን፡፡ በዚህ ምድር ላይ
ያለ እያንዳንዱ ሰው ይህንን ይመኛል፡፡
ሆኖም እግዚአብሄር በኢየሱስ ክርስቶስ አማካይነት እንዲህ ያለ ትልቅ
ሥልጣንና በጣም ብዙ በረከቶች ስለሰጠን በጭራሽ ሊለኩም ሆነ ሊቆጠሩ
አይችሉም፡፡ እነዚህ በረከቶች ፈጽሞ ሊለኩ የማይችሉት ወሰን የለሽ ስለሆኑ ነው፡፡
ውሱን ሰዎች ስለሆንን ልናስተውላቸውም ሆነ ልንገነዘባቸው አንችልም፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ በሮሜ 8፡18 ላይ እንዲህ አለ፡- ‹‹ለእኛም ይገለጥ ዘንድ
ካለው ክብር ጋር ቢመዛዘን ይህ የአሁኑ ዘመን ሥቃይ ምንም እንዳይደለ
አስባለሁ፡፡›› ስለዚህ ከኢየሱስ ክርስቶስ የተቀበልናቸው የተትረፈረፉ በረከቶች
በጣም አስገራሚ ስለሆኑ ማመዛዘን እንኳን አይቻልም፡፡ በመሆኑም ሁላችንም
በኢየሱስ ክርስቶስ መኖርና መከናወን እንችላለን፡፡ ምክንያቱም እንዲህ ያለ ተስፋ
አለንና፡፡ ራሴን ትግል ውስጥ በማገኝበት ጊዜ ሁሉ እግዚአብሄር በዛሬው

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


194 ወሰን የሌላቸው የክርስቶስ በረከቶች በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በሚያምን
በእያንዳንዱ ቅዱስ ልብ ውስጥ አሉ

የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ላይ የተናገረውን አስታውሳለሁ፡፡ ያን ጊዜ ጌታን


አመሰግናለሁ፡፡ ችግሮቼንም በሙሉ እቋቋማለሁ፡፤ ምክንያቱም ጌታ የሰጠን
በረከቶች በጣም ታላላቅ ናቸውና፡፡ ለጌታ ባልኖርም ሆነ ችግሮችንና መከራዎችን
ባልጋፈጥ ኖሮ ፍለጋ የሌላቸውን የእርሱን በረከቶች ከተቀበልሁ በኋላም እንኳን
ጌታን አላመሰግነውም ነበር፡፡
እግዚአብሄር እነዚህን በረከቶች ‹‹በሰማያዊ ሥፍራ ያሉ አለቆችና
ሥልጣናት›› (ኤፌሶን 3፡10) አድርጎ ሰጥቶናል፡፡ እኔም በዚህ ሁሉ አምናለሁ፡፡
ለእነዚህ በረከቶች በበቂ ሁኔታ አመስጋኝ ካልሆናችሁ ወይም ልታስታውሱዋቸው
ካልቻላችሁ ለዚህ ምክንያቱ በዓለማዊ ነገሮች በጣም ስለረካችሁ ነው፡፡ ነገር ግን
ዓለም በጭራሽ ሊያረካችሁ እንደማይች የታወቀ ነው፡፡ እንዲያውም መንግሥተ
ሰማይ የምንገባበትን ቀን የምንጠብቀው ሕይወት በዚህ ዓለም ላይ በጣም አስቸጋሪ
በመሆኑ ነው፡፡ ይህ ተስፋ አንድ ቀን ስለሚፈጸምልንና እንዲህ ያለ ብሩክ ሕይወት
በዓይኖቻችን ፊት ስለሚገለጥ ሁላችንም ያንን ቀን በተስፋ በመጠበቅ በእምነት
መኖር ይገባናል፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ የዛሬውን የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ በጻፈ ጊዜ በግዞት
ቤት ውስጥ ነበር፡፡ ነጻነት አልነበረውም፡፡ ስለዚህ ፍለጋ ስለሌላቸው የክርስቶስ
በረከቶች አሰበ፡፡ ጳውሎስ ስለ እነዚህ በረከቶች በማሰቡና ልቡም በእነርሱ
እንደተሞላ ስላወቀ ቢታሰርም እንኳን ፈጽሞ አልታወከም፡፡ ምንም ነገር
ቢገጥመው ሁሌም አመስጋኝ ነበር፡፡ ጳውሎስ ራሱን ግዞት ቤት ቢያገኝም
‹‹ልቦቻችን ፍለጋ በሌላቸው የክርስቶስ በረከቶች ይሞሉ›› በማለት የኤፌሶንን
ቅዱሳን ያገለገለውና የባረካቸው ለዚህ ነው፡፡ ልክ እንደ ጳውሎስ በዚህ በአሁኑ
ዘመን የእርሱ አገልጋዮችና ሠራተኞች ሆነን ልቦቻችን ሁሉ ፍለጋ በሌላቸው
የእግዚአብሄር በረከቶች መሞላት አለባቸው፡፡
እነዚህን በረከቶች ለማግኘት እኛ የምናደርገው አንዳች ነገር የለም፡፡ ነገር ግን
እንድንደሰትባቸው በእምነት የተቀበልናቸው ናቸው፡፡ ምክንያቱም ጌታ እነርሱን
በነጻ ሰጥቶናልና፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እነዚህን በረከቶች ሁሉ ሰጥቶናል፡፡
በአእምሮዋችንና በልቦቻችን የምንሻውን ሁሉ ይሞላልናል፡፡ ምኞታችንን ሁሉ
ሊፈጽምልንም በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ ይሰራል፡፡ የእናንተና የእኔ ልብ
ቀድሞውኑም በክርስቶስ የተትረፈረፉ በረከቶች ተሞልተዋል፡፡
ምስጋናዬን ሁሉ ለእግዚአብሄር እሰጣለሁ! 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ስብከት
11

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት
ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
በሕይወታችሁ ውስጥ
ያለውን እምነት ጠብቁ
‹‹ ኤፌሶን 4፡1-6 ››
‹‹እንግዲህ በጌታ እስር የሆንሁ እኔ በተጠራችሁበት መጠራታችሁ
እንደሚገባ ትመላለሱ ዘንድ እለምናችኋለሁ፡፡ በትህትና ሁሉና በየዋህነት፣
በትዕግሥትም እርስ በርሳችሁ በፍቅር ታገሡ፡፡ በሰላም ማሰርያ የመንፈስን
አንድነት ለመጠበቅ ትጉ፡፡ በመጠራታችሁ በአንድ ተስፋ እንደተጠራችሁ አንድ
አካልና አንድ መንፈስ አለ፡፡ አንድ ጌታ፣ አንድ ሐይማኖት፣ አንዲት ጥምቀት፣
ከሁሉ በላይ የሚሆን፣ በሁሉም የሚሠራ፣ በሁሉም የሚኖር አንድ አምላክ የሁሉም
አባት አለ፡፡ ነገር ግን እንደ ክርስቶስ ሥጦታ መጠን ለእያንዳንዳችን ጸጋ ተሰጠን፡፡››

ለዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ ኤፌሶን 4፡1-6ን አንብበናል፡፡ ሐዋርያው


ጳውሎስ እንዲህ አለ፡- ‹‹እንግዲህ በጌታ እስር የሆንሁ እኔ በተጠራችሁበት
መጠራታችሁ እንደሚገባ ትመላለሱ ዘንድ እለምናችኋለሁ፡፡››
ሐዋርያው ጳውሎስ ይህንን በጻፈ ጊዜ ወንጌልን በመስበኩ ታስሮ ነበር፡፡
ስለዚህ ልቡ ምን ያህል አዝኖ እንደነበር በቀላሉ መገመት እንችላለን፡፡ ጳውሎስ ነጻ
ሰው በነበረ ጊዜ በነጻነት ከቅዱሳኖች ጋር መገናኘትና ከቅዱሳንም ጋር የፈለገውን
ያህል ሕብረት ይካፈል ነበር፡፡ አሁን ግን ስለታሰረ ማድረግ የፈለገውን ሊያደርግ
አልቻለም፡፡ ልቡም ይበልጥ ወንጌልን ለመስበክ ናፍቆ ነበር፡፡ እኛም ደግሞ
ማገልገል በምንችልበት ጊዜ ሁሉ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በልቦቻችን
ልንወደው ይገባናል፡፡ ነገር ግን አንዳንዶቻችን እንዲህ ያለ ቅንዓት እንደሌለን
አያለሁ፡፡ ይህም በእጅጉ ያሳዝነኛል፡፡ ታላቁ መከራ ሲመጣ ዳግመኛ የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል ማገልገል አዳጋች ይሆንብናል፡፡ ብዬ እፈራለሁ፡፡ ይህ ዘመን
ሲመጣ አሁን ወንጌልን ማገልገል እንደሚገባን በትጋት ባለማገልገላችን
እንደምንጸጸት አውቃለሁ፡፡ ለወንጌል ያለን መሰጠትና ቅንዓት አሁን ካለው የላቀ
ቢሆንም የታላቁ ዘመን መከራ ሲመጣ ግን በጣም ይረፍዳል፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ ‹‹እንግዲህ በጌታ እስር የሆንሁ እኔ በተጠራችሁበት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


198 በሕይወታችሁ ውስጥ ያለውን እምነት ጠብቁ

መጠራታችሁ እንደሚገባ ትመላለሱ ዘንድ እለምናችኋለሁ›› (ኤፌሶን 4፡1) እንዳለ


አሁን ሁላችንም ከጌታ ለተቀበልነው መጠራት እንደሚገባ ልንመላለስ ይገባናል፡፡

ጌታ እንደጠራንና እንዳዳነን በመገንዘብ ለእርሱ ጥሪ


የሚገባ ሕይወትን ልንኖር ይገባናል፡፡

ሐዋርያው ጳውሎስ በኤፌሶን 4፡2 ላይ ‹‹በትህትና ሁሉና በየዋህነት


በትዕግሥትም እርስ በርሳችሁ በፍቅር›› እንድንመላለስ መክሮናል፡፡ ለእኛ
በእግዚአብሄር ፊት በትህትና ሁሉ መሥራት ማለት ራሳችንን በእምነት ለእርሱ
አሳልፈን መስጠት ማለት ነው፡፡ እግዚአብሄር ልጆቹ እንድንሆን ከጨለማው
ሥልጣን ጠርቶ ስላወጣንና ሥራውን በአደራ ስለሰጠን አሁን እየሰራነው ያለነው
ሥራ የእግዚአብሄር ክቡር ሥራ እንደሆነ ምንም ዓይነት ጥርጣሬ የለኝም፡፡
ለጻድቃን የተሰጡት ተግባራቶች እርስ በርሳቸው የተለያዩ ናቸው፡፡
እያንዳንዳችን የእግዚአብሄርን ሥራ የምንሰራበት የተለያየ ሚና አለን፡፡
ሠራተኞቻችንንም መውደድ ትህትና ነው፡፡ ትህትና ራሳችንን በውጫዊ መልኩ ዝቅ
ማድረግና ትሁት እንደሆኑ ማስመሰል አይደለም፡፡ ነገር ግን የውሃውንና የመንፈሱን
ወንጌል የሚያገለግለውን እያንዳንዱን ሰው መውደድና ለእያንዳንዳችን
የተመደበልንን ተግባር በታማኝነት ማከናወን ነው፡፡
እግዚአብሄር በትህትና ሁሉና በየዋህነት እንድንመለላለስ እንዳዘዘን እርስ
በርሳችን መከባበርና እርስ በርሳችን መደጋገፍ ያስፈልገናል፡፡ ያለ እነርሱ ልፋት
ማናችንም ጌታን ማገልገል እንደማይቻለን ከልብ በመገንዘብ የውሃውን የመንፈሱን
ወንጌል የሚያገለግሉትን ሁሉ መውደድ ይገባናል፡፡ ስለዚህ አሁንም ቢሆን
ሁላችንም እርስ በርሳችን መከባበርና መዋደድ ይገባናል፡፡ ጳውሎስ አብዛኛውን
ጊዜ ከመንፈሳዊ ጉዳዮች በተጨማሪ ስለ ቀን ተቀን ሕይወት ተናግሮዋል፡፡ ለእኛ
ያቀረበው ቁልፍ መልዕክትም እርስ በርሳችን በትህትናና በየዋህነት እንድንቀባበል
ነው፡፡
አሁን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በሚያገለግሉት መካከል
በእግዚአብሄር ፊት ክቡር ሊሆን የሚችል ሰው አለ? የለም፡፡ የሐጢያቶቻቸውን
ስርየት የተቀበሉ እምነታቸውን የሚጠብቁና ወንጌልን ለማሰራጨት ጠንክረው
የሚሰሩ ሰዎች በቤተክርስቲያን ውስጥ ያላቸው ሥልጣን ምንም ያህል ከፍ ያለ
ወይም ዝቅ ያለ ቢሆንም በእግዚአብሄር ፊት ክቡር ናቸው፡፡ ከእነዚህ ቅዱሳኖች

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በሕይወታችሁ ውስጥ ያለውን እምነት ጠብቁ 199

የበለጠ ክቡር ሰው የለም፡፡ የእግዚአብሄርን ጽድቅ የምናገለግል ሁላችን የእርሱ


ክቡር ሠራተኞች ነን፡፡ እግዚአብሄር ‹‹በትህትና ሁሉና በየዋህነት›› እንድንመላለስ
ሲነግረን እርስ በርሳችን እንድንከባበር እያስተማረን ነበር፡፡ እውነተኛ የዋህነት
የሌሎችን ድክመቶች መመልከትና በእነርሱ ላይ መፍረድና እነርሱን መኮነን
አይደለም፡፤ ከዚሀ በራቀ መልኩ በጣም ብዙ ድክመቶች ቢኖርባቸውም ጌታን
ለማገልገል በእጅጉ በርትተው በመስራታቸው እነርሱን ማክበር ነው፡፡ በሌላ
አነጋገር እግዚአብሄር እያስተማረን ያለው አንዳችን የሌላችንን ድክመቶች
እንድናስተውልና በፍቅር ነጻነት እርስ በርሳችን ሕብረትን እንድናደርግ ነው፡፡
ሐዋርያው ጳውሎሰ ከታሰረበት ግዞት ቤት ውስጥ ሆኖ በኤፌሶን
ቤተክርስቲያን ላሉ ቅዱሳኖች ‹‹በትህትና ሁሉና በየዋህነት ተመላለሱ፡፡ በእርግጥ
በውሃው በመንፈሱ ወንጌል የምታምኑ ከሆናችሁ እርስ በርሳችሁ አትነካከሱ››
አላቸው፡፡
በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ ያሉ የጽድቅ ሠራተኞች በጣም ገር
ናቸው፡፡ ነገር ግን በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ ከሰው ዕይታ አንጻር
ለመረዳት የሚያስቸግር አንድ ስርዓት አለ፡፡ ስለዚህ በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን
ውስጥ ካለው ከዚህ መንፈሳዊ ስርዓት የተነሳ በቤተክርስቲያን ውስጥ አብዝተው
የሚከበሩት በስጋዊ ወይም በመንፈሳዊ ደካማ የሆኑ ሰዎች ናቸው፡፡ በእግዚአብሄር
ቤተክርስቲያን ውስጥ ብዙ ጉድለቶች ያሉባቸው በጣም ደካማ የሆኑ ቅዱሳኖች
በእምነት ቀደምቶቻቸው አብልጠው ይገለገላሉ፡፡ እነዚህ ደካማ ቅዱሳን አሁን
በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ እንክብካቤ የሚደረግላቸውና የሚገለገሉት
ከእግዚአብሄር ቃልና ከመንፈስ ቅዱስ የተነሳ ነው፡፡
አብሮዋችሁ ያለውን ቅዱስ ሰው ስጋዊ ድክመቶች ማየት ቢያጋጥማችሁና
ይህ ቅዱስ ሰው ፈጽሞ የማይረባ መስሎ ቢታያችሁ እንኳን ይህ ቅዱስ ሰው
በእግዚአብሄር ዓይን ምን ያህል ክቡር እንደሆነ የምታዩባቸው ዓይኖች ሊኖራችሁ
ይገባል፡፡ ሁላችንም ከእግዚአብሄር ዘንድ የሐጢያቶችን ስርየት ተቀብለናል፡፡
ሁላችንም እርስ በርስ እንፈላለጋለን፡፡ የእግዚአብሄርን ቅዱሳኖችና ሠራተኞች
አስፈላጊነት የማታደንቁና ስህተቶቻቸውን ይቅር የማትሉ ከሆነ ጌታ
እንደሚገስጻችሁ የተረጋገጠ ነው፡፡
ማናቸውንም እንደማትፈልጉዋቸው በመናገር ቅዱሳኖችን በሙሉ ስታባርሩና
በዚህ ትልቅ የቤተክርስቲያን ሕንጻ ውስጥ እግዚአብሄርን ብቻችሁን ስታመልኩ
አስቡ፡፡ ያን ጊዜ ቤተክርስቲያንን ከማጽዳት ጀምሮ አበባዎችን እስከ ማዘጋጀት፣
የድምጽ ግብዓቱን እስከ መቆጣጠርና የሙቀት ግብዓቱን እስከ ማቀናበር ድረስ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


200 በሕይወታችሁ ውስጥ ያለውን እምነት ጠብቁ

እያንዳንዱን ነገር ብቻችሁን ትሰሩታላችሁ፡፡ እነዚህን ነገሮች ሁሉ ብቻችሁን


የምትሰሩ ከሆነ ቀኑን ሙሉ ብትለፉም እንኳን ሁሉንም ማከናወን አይቻላችሁም፡፡
ስለዚህ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ማሰራጨትና እግዚአብሄርን ማገልገል
የምንችለው ስንተባበር ብቻ እንደሆነ ሁላችንም መረዳታችን በእጅጉ አስፈላጊ
ነው፡፡ እኛ አጋር ሠራተኞች ያሉን መሆናችንም እንዴት ያለ በረከት እንደሆነ
መረዳት ይገባናል፡፡ አብረዋችሁ ያሉት ቅዱሳኖች የእግዚአብሄርን ወንጌል
ሲሰብኩና ሲያገለግሉ ስትመለከቱ ሁሉም ምን ያህል ክቡር እንደሆኑ አታዩምን?
እርስ በርሳችን ትሁታን መሆን የማንችልበት ምንም ምክንያት የለም፡፡ እርስ
በርሳችን ይቅር የማንባባለውም ምንም ነገር የለም፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
በማመን ዳግመኛ የተወለዱ ጻድቃን ሁሉ አንዳቸው የሌላኛውን ክቡርነት
መረዳትና እርስ በርስ መከባበር መቻል አለባቸው፡፡ ጌታ በትህትና ሁሉና በየዋህነት
እንድንመላለስ የነገረን ለዚህ ነው፡፡
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምኑ አማኞች የዋህና ገር ናቸው፡፡
ምክንያቱም የእግዚአብሄር ሕዝብ ናቸውና፡፡ ጻድቃን አንዳንዴ በስጋ ሲቆጡ
ስሜቶቻቸውን በግልፍተኝነት ቢገልጡም ቢያንስ ልቦቻቸው በእግዚአብሄር ፊት
የዋሃን ናቸው፡፡ ወጣቱም ሆነ አረጋዊው አንዳች ግላዊ ግልፍተኝነት ወይም የራስ
ክብር የሌለው ማንም የለም፡፡ ልክ እንደዚሁ ጻድቃንም ቢሆኑ አንዳንድ ጊዜ
በግትርነታቸው ግልፍተኞች ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ በመጨረሻ ግን ሁሉም
ለእግዚአብሄር ፈቃድ ታዛዦች ናቸው፡፡ ስህተታቸውን ከተረዱ በኋላ ሁሉም
ራሳቸውን ለእግዚአብሄር ቃል በማስገዛት ቃሉን በአንድነት ይከተላሉ፡፡ ሰብዓዊ
ተፈጥሮዋችን ክፉ፣ ግትርና ብልሹ እንደሆነ የታወቀ ነው፡፡ የእግዚአብሄር ሕዝቦች
ግን ጌታን የሚከተሉትንና የሚያገለግሉትን ሁሉ በተለይም ደካሞችን በትህትና
ይንከባከባሉ፡፡ ነገር ግን ወንጌልን የሚቃወሙትንና የሚሳደቡትን ሰዎች
በሚመለከት እነርሱን በትህትና ከመንከባከብ ይልቅ አንዳንድ ጊዜ ጉብ ልንልባቸው
ወደ ክፉ አንበሶች እንለወጣለን፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ በእስር ቤት ሆኖ ለቅዱሳን የጻፈውና ‹‹በትህትና ሁሉና
በየዋህነት›› (ኤፌሶን 4፡2) እንዲመላለሱ የመከራቸው ለምን ይመስላችኋል?
ምክንያቱም በእምነታችን የእርስ በርሳችንን ድካም ለመሙላት መልካምን
የምናደርግበትን በጌታ ያለንን ጉልበት ለማስተባበርና የእርሱን ወንጌል ለማገልገልና
ለእያንዳንዱ ነፍስ ለመስበክ በቤተክርስቲያን ውስጥ ወንጌልን እያገለገለ ያለውን
እያንንዱን ሰው በትህትናና በየዋህነት ማክበር ተገቢና አስፈላጊ ነው፡፡ ነገር ግን
በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ በስጋው ጉልበት የሚመጻደቅ ወይም

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በሕይወታችሁ ውስጥ ያለውን እምነት ጠብቁ 201

በሥልጣኑ ደካማውን ለመጨቆን የሚሞክር ሰው ካለ ይህንን ሰው ልንቃወመው


ይገባናል፡፡ በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ ምሁራን መሆናችሁ ወይም
ማህበራዊ ደረጃችሁ ከፍ ያለ ወይም ዝቅ ያለ መሆኑ ፈጽሞ ከቁም ነገር የሚቆጠር
አይደለም፡፡ እግዚአብሄር የአምላክን ቃል በእምነት የሚታዘዘውን ሁሉ ክቡር
መሣርያው አድርጎ ይጠቀምበታል፡፡ ወደ እግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ከመጣችሁ
በኋላ ማህበራዊ ደረጃችሁ ወይም የቤተክርስቲያን ሥልጣናችሁ ምንም ያህል የላቀ
ቢሆንም አብረዋችሁ ያሉትን ቅዱሳኖች ልታከብሩዋቸው ይገባችኋል፡፡

ሆኖም በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ ገና ዳግመኛ ያልተወለዱ


ሆነው ሳሉ በሁሉም ሰው ላይ ለመሰልጠን የሚሞክሩ አንዳንድ ሰዎች
አሉ፡፡

እነዚህ ሰዎች እኛ ጻድቃኖች ሐጢያተኞችን ምን ያህል ጊዜ እንደታገስናቸው


ሊገነዘቡ ይገባል፡፡ እስከ ዛሬ ድረስም ጻድቃን ጥረቶቻቸወን ሁሉ የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል ለሐጢያተኞች በመስበክ ላይ አውለዋል፡፡ ነገር ግን ሌሎችን
በስጋና በመንፈስ ለማውደም መሞከር የእያንዳንዱ ሐጢያተኛ ባህርይ ነው፡፡ በሌላ
አነጋገር ሌሎችን ባርያ ማድረግና በመንፈሳዊ ሁኔታ ማውደም የእያንዳንዱ
ሐጢያተኛ ግብ ነው፡፡ ስለዚህ ዳግመኛ በተወለዱ ሰዎች ፍሬና ዳግመኛ
ባልተወለዱ ሰዎች ፍሬ መካከል ግልጥ የሆነ ልዩነት አለ፡፡
ዳግመኛ የተወለዱትም ቢሆኑ አንዳንድ ጊዜ ለስጋዊ ድክመቶቻቸው
እንደሚሸነፉ እውነት ነው፡፡ ነገር ግን ጻድቃን አሁንም እርስ በርሳቸው ይዋደዳሉ፡፡
እርስ በርሳቸው በየዋህነት ይከባበራሉ፡፤ በመንፈሳዊ ስርዓትም ይኖራሉ፡፡ ጻድቃን
እንዴት እርስ በርስ እንደሚዋደዱ ያውቃሉ፡፡ አንድ ጻድቅ ሲደክም በሚቻለው
መንገድ ሁሉ አንዳንዴም አብረው እንጀራን በመቁረስ ሌላ ጊዜ ደግሞ ሻይ እየጠጡ
በማረፍ እርስ በርሳቸው ይበረታተሉ፤ ይጽናናሉም፡፡ ጉልበታቸው ከተመለሰ
በኋላም ሁሉም የእግዚአብሄርን ሥራ ለመስራት ወደ ምድቦቻቸው ይመለሳሉ፡፡
ሆኖም በየጊዜው ያለ ምንም ምክንያት የሚቆጡና የሚገነፍሉ አንዳንድ ሰዎች
አሉ፡፡ ነገር ግን ይህም ቢከሰት እንኳን እርስ በርሳችን ለመግባባት መሞከር፣
ሊኖሩብን የሚችሉትን አንዳንድ አለመግባባቶች መፍታት፣ አንዳችን የሌላችንን
ስህተት ማመንና በክርስቶስ እርስ በርስ መታረቅ ይኖርብናል፡፡ ከዚህ ቀደም
የማናውቃቸው አንዳች ድክመቶች በውስጣችን በምናይበት ጊዜ ሁሉ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


202 በሕይወታችሁ ውስጥ ያለውን እምነት ጠብቁ

ለእግዚአብሄር ልንናገራቸው፣ የጎዳነውን እያንዳንዱን ሰው ይቅርታ መጠየቅና


አንዳችን የሌላችንን ስህተት በእግዚአብሄር መታገስ ይገባናል፡፡ ጻድቃን
ሕይወታቸውን መምራት የሚገባቸው እንደዚህ ነው፡፡ በጌታ ጽድቅ በሚያምን
ተመሳሳይ እምነት በአንድ ላይ መተባበራችን ለሁላችንም የእምነት ሕይወት ሁሉ
መሠረታዊ መሠረት ነው፡፡
በጻድቃንም መካከል እንኳን የሚመሩ አንዳንዶችና የሚከተሉ አንዳንዶች
አሉ፡፡ ይህ ግን እያንዳንዱ በግ የግድ መሪውን ይከተላል ማለት አይደለም፡፡
እንዲያውም በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ በጣም ግትር የሆኑ ብዙ በጎች
አሉ፡፡ ቢሆንም የእምነት ቀደምቶች ደካማ አባሎችን ይታገሳሉ፤ እነርሱንም
ሲገነዘቡዋቸው ስህተቶቻቸውን ያምናሉ፡፡ አንዳንድ ጊዜ ደካማዎቹ ቅዱሳኖችም
ቢሆኑ ስህተቶቻቸውን አምነው የእምነት ቀደምቶቻቸውን ምሪት ለመቀበል
ልቦቻቸውን ትሁት ያደርጋሉ፡፡ በጌታ ላይ ባለን የጋራ እምነታችን በአንድ ልብ
የምንተባበረው እንደዚህ ነው፡፡ በእርግጥ መንፈሳዊ የእምነት ሕይወታችን ከዳበረ
በኋላ እኛ ጸድቃኖች የእምነት ቀደምቶቻችን ምን ያህል ክቡር እንደሆኑ
እንገነዘባለን፡፡ በዚያው ጊዜም ከእኛ በኋላ የሐጢያቶችን ስርየት ቢቀበሉም
ወንጌልን በትጋት ለማገልገል ዱካዎቻችንን ከኋላችን ሆነው የሚከተሉንንም ሰዎች
ወደ ማክበር እንመጣለን፡፡ በዚህ መንገድ እርስ በርሳችን ምን ያህል ክቡር
እንደሆንን ስለተረዳን እግዚአብሄር በሕይወታችን ውስጥ ማገልገል እንችላለን፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ ‹‹በትህትና ሁሉና በየዋህነት በትዕግሥትም እርስ
በርሳችሁ በፍቅር›› (ኤፌሶን 4፡2) ተመላለሱ ብሎ የመከረን ለዚህ ነው፡፡ በዚህ
ሁኔታ እርስ በርሳችን ስንግባባና በእግዚአብሄር ፍቅርና በእምነት እርስ በርሳችን
ስንተቃቀፍ ሁላችንም አንድ ሆነናል፡፡ እናንተም ራሳችሁ ይህንን
እንደተለማመዳቸሁ እርግጠኛ ነኝ፡፡

ጌታ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ላይ ያለንን እምነታችንን


እንድንጠብቅ አዞናል፡፡

ኤፌሶን 4፡3 እንዲህ ይላል፡- ‹‹በሰላም ማሰሪያ የመንፈስን አንድነት


ለመጠበቅ ትጉ፡፡›› የሰላም አንድነታችንን ለመጠበቅ እርስ በርስ ያስተሳሰረን
ምንድነው? አንድ ያደረገን ጌታ እኛን ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ያዳነበት የውሃውና
የመንፈሱ ወንጌል ሐይል ነው፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል እውነት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በሕይወታችሁ ውስጥ ያለውን እምነት ጠብቁ 203

የተጠናቀቀውን ደህነንታችንን መቀበል የቻልነው፣ እውነተኛ ሰላምን የተቀበልነውና


በእውነተኛ እርካታ የምንደሰተው በእምነት ነው፡፤ በእርግጥም የውሃውና
የመንፈሱ ወንጌል ባይኖረን ኖሮ እንኳንስ እርስ በርሳችን ልንዋደድ ቀርቶ
በእውነተኛ ሰላም መደሰትም ሆነ መታገስ፣ ትሁትና የዋህ መሆንም ባልቻልን
ነበር፡፡ የሕይወታችንን ችግሮች በሙሉ በትዕግስት መቋቋምና መሸከም የምንችለው
የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ስላለን ነው፡፡ ይህ የሆነው ጌታ ሐጢያቶቻችንን
በሙሉ በውሃና በመንፈስ ወንጌል ለአንዴና ለመጨረሻ ስለደመሰሰ ነው፡፡ ከዚህም
በላይ ጌታችን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ለአንዴና
ለመጨረሻ ስለደመሰሰ የእርሱ አማኞች በመሆናችን በልቦቻችን ውስጥ ሰላምን
መቀበል ከመቻላችንም በላይ የእርሱንም ሰላም ማስፋፋት ችለናል፡፡ እግዚአብሄር
ለሰጠው ሰላም ምስጋና ይሁንለትና አሁን አንድ ሆነናል፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ላይ ያለንን እምነታችንን
እንድንጠብቅ ሁላችንንም በመምከር በኤፌሶን 4፡4 ላይ ደግሞ እንዲህ አለ፡-
‹‹በመጠራታችሁ በአንድ ተስፋ እንደጠራችሁ አንድ አካልና አንድ መንፈስ አለ፡፡››
ከአንድ የክርስቶስ አካል በላይ አለ? የለም፡፡ ያለው አንድ የክርስቶስ አካል
ብቻ ነው፡፡ እዚህ ላይ የክርስቶስ አካል የሚያመለክተው የእግዚአብሄርን
ቤተክርስቲያን የሚያዋቅሩትን ቅዱሳኖችን ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሄር
ቤተክርስቲያን ራስ ነው፡፡ እኛም የዚህች ቤተክርስቲያን አባሎች ስለሆንን
የክርስቶስ አካል ነን፡፡ የኢየሱስ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን አንድ አካል ነች፡፡ ጌታ
ላመጣልን በረከት ምስጋና ይድረሰውና ሁላችንም አንድ ሆነናል፡፡ ‹‹በመጠራታችሁ
በአንድ ተስፋ እንደጠራችሁ አንድ አካልና አንድ መንፈስ አለ፡፡›› (ኤፌሶን 4፡4)
እንዳለው አንድ መንፈስ ደግሞ አለ፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት አድኖናል፡፡
አሁን ልቦቻችንን በመንፈስ ቅዱስ አትሞታል፡፡ በሌላ አነጋገር እግዚአብሄር
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን የሐጢያቶችን ስርየት የተቀበልውን
እየንዳንዱን ልብ በመንፈስ ቅዱስ አትሞታል፡፡ መንፈስ ቅዱስም በተራው በአንድ
ተስፋ እንድንኖር አድርጎናል፡፡ በአጭሩ እግዚአብሄር ወደ መንግሥቱ በምንገባበት
በአንድ ተስፋ እንድንተባበር ባርኮናል፡፡
ከዚያም ጳውሎስ በኤፌሶን 4፡5-6 ላይ ‹‹አንድ ጌታ፣ አንድ ሐይማኖት፣
አንዲት ጥምቀት፣ ከሁሉ በላይ የሚሆን፣ በሁሉም የሚሠራ፣ በሁሉም የሚኖር
አንድ አምላክ የሁሉም አባት አለ›› እያለ ይቀጥላል፡፡ በእርግጥም አንድ ጌታ አለ፡፡
ይህም ጌታ ከዓለም ሐጢያቶች ሁሉ አድኖናል፡፡ ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ያዳነን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


204 በሕይወታችሁ ውስጥ ያለውን እምነት ጠብቁ

አንዱና ብቸኛው ጌታ ሌላ ማንም ሳይሆን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ


በውሃውና በደሙ በተፈጸመው የደህንነት ወንጌል አማካይነት ከሐጢያቶቻችን
ባያድነን ኖሮ በጭራሽ ከሐጢያቶቻችን ሁሉ መዳን ባልቻልንም ነበር፡፡ ስለዚህ
መጽሐፍ ቅዱስ እንዳለው አንድ ጌታ፣ አንድ እምነት፣ አንድ ጥምቀት አለ፡፡ ያዳነን
አንድ ጌታ ብቻ እንዳለ ሁሉ ሁላችንም ደህንነታችንን ያገኘንበት አንድ እምነት
ብቻም አለ፡፡ ምክንያቱም ሁላችንም በአንዱ ወንጌል አማካይነት በአንዱ ጌታ
እናምናለን፡፡ ይህንን እምነት በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ ያሉ ቅዱሳኖች
በሙሉ ይጋሩታል፡፡
ኢየሱስ ለእኛ የተቀበለውም አንድ ጥምቀት ብቻ አለ፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ
ሐጢያቶቻችንን ለመሸከም የተቀበለው አንዳች ሌላ ጥምቀት አለ? ወይም
ከጥምቀቱ ውጪ በአንዳች ሌላ መንገድ አማካይነት ሐጢያቶቻችንን ወስዶዋል?
የለም፤ ጌታ ከአጥማቂው ዮሐንስ ከተቀበለው ጥምቀት በቀር ሌላ መንገድ
አልነበረም፡፡ ስለዚህ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ያነጻ አንድ ጥምቀት ብቻ ነበር፡፡
ኢየሱስ ይህንን ጥምቀት በተቀበለ ጊዜ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ስለተሸከመ
ሐጢያቶቻችን በሙሉ ወደ እርሱ ተላልፈዋል፡፡
የተዘጋ የፍሳሽ መተላለፊያ ከፍታችሁ ታውቃላችሁን? በቻንግዎን ከተማ
እያገለገልሁ ሳለሁ ከቤተክርስቲያኑ ሕንጻ በስተ ጀርባ ባለው ሰገነት ላይ ያለው
የፍሳሽ መተላለፊያ ተዘግቶ ብዙ ችግር ስለፈጠረ እንዲከፍተው የቧንቧ ሠራተኛ
መጥራት ነበረብኝ፡፡ ቤተክርስቲያኒቱ የምትገኘው በሁለተኛው የሕንጻ ወለል ላይ
በመሆኑ ከቤተክርስቲያኒቱ በላይ ባለው ወለል ላይ ደግሞ አንድ የግል ተቋም
ነበር፡፡ ይህ ተቋም በፍሳሽ ማስተላለፊያው ውስጥ ብዙ ቆሻሻ በመላኩ በመጨረሻ
የቆሻሻ ማስተላለፊያ ቱቦዎቹ ተዘጉ፡፡ ድፍነቱ በጣም መጥፎ ስለነበር እኔ ልሰራው
አልቻልኩም፡፡ ስለዚህ የቧንቧ ሠራተኛ መጥራት ነበረብኝ፡፡ ነገር ግን የቧንቧ
ሠራተኛውም ቢሆን ሊከፍተው ተቸግሮ ነበር፡፡ መጀመሪያ ላይ የቧንቧ ሠራተኛው
ለሥራው $30 ሊያስከፍለኝ ነበር፡፡ ነገር ግን ድፍነቱ ከባድ እንደሆነ በማንገራገር
ተጨማሪ ገንዘብ ፈለገ፡፡ ስለዚህ $50 ሰጠሁት፡፡ የፍሳሽ መተላለፊያውም ከአንድ
ደቂቃ ባነሰ ተከፈተ፡፡ አሁን የተዘጋው የፍሳሽ መተላለፊያ በሙሉ መከፈቱን
በማየቴ በጣም ተደሰትሁ፡፡
ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ
መቀበሉንና ማስወገዱን የሚያስተምረንን የወንጌል ቃል ሁሌም ማድመጥ አለብን፡፡
ይህን የኢየሱስን ጥምቀት ቃል በምናደምጥበት ጊዜ ሁሉ ልቦቻችን ከሚያግደን
ቆሻሻ ሁሉ ሙሉ በሙሉ ይከፈታሉ፡፡ ያን ጊዜ አንድ የተዘጋ የፍሳሽ ማስተላለፊያ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በሕይወታችሁ ውስጥ ያለውን እምነት ጠብቁ 205

በሚጸዳበት ጊዜ ውሃ በነጻነት ሊፈስስ እንደሚችል ሁሉ የእናንተና የእኔም ልብ


በነጻነት ሕብረትን መገራት ይችላል፡፡
ልቦቻችን ሕብረትን መጋራት የሚችሉት በምን አማካይነት ነው? ልቦቻችን
እርስ በርስ የሚነጋገሩት በኢየሱስ ጥምቀት ላይ ባለን የጋራ እምነት አማካይነት
ነው፡፡ እርስ በርሳችን ሕብረትን መጋራትና በገርነትና በሰላም ዓይን ለዓይን
መተያየት የምንችለው ሐጢያቶቻችን በሙሉ በጥምቀቱ አማካይነት ወደ ኢየሱስ
እንደተላለፉ እርስ በርስ ስንነጋገር ነው፡፡ ልቦቻቸው የተዘጉባቸውም ‹‹የእኔ
ሐጢያቶች በሙሉ ወደ ኢየሱስ እንደተላለፉ ሁሉ የእናንተም ሐጢያቶች እንደዚሁ
ወደ ጌታ ተላልፈዋል፡፡ የእናንተም ሐጢያቶች ደግሞ የዓለም ሐጢያቶች ናቸው፡፡
ይህ ማለት የእናንተም ሐጢያቶች ደግሞ ወደ ኢየሱስ ተላልፈዋል ማለት ነው፡፡
በዚህ ዓለም ላይ ያለው እያንዳንዱ ሐጢያት የእናንተና የእኔም ጭምር
አስቀድመው ወደ ጌታ ተላልፈዋል›› ብለን በማስተማር ወንጌልን ልንሰብክላቸው
እንችላለን፡፡ ያን ጊዜ ልቦቻቸው ይከፈታሉ፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ‹‹አንድ ጌታ፣ አንድ
ሐይማኖት፣ አንዲት ጥምቀት›› (ኤፌሶን 4፡5) እንደሚል በአንድ ቅዱስ ማህበረሰብ
ውስጥ ያለ ቅዱስ ከሌላው ዳግመኛ የተወለደ ቅዱስ ልቦች ሁሉ ጋር ይግባባል፡፡
ታዲያ የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያንስ? ከአንድ ቤተክርስቲያን በላይ ሊኖር
ይችላልን? መጽሐፍ ቅዱስ ‹‹አንድ አካል›› (ኤፌሶን 4፡4) እንዳለ ስለሚናገር
ከአንድ የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን በላይ ሊኖር አይችልም፡፡ አንድ ጌታና አንድ
አምላክ አለ ማለት ኢየሱስ ክርስቶስ የአባቱን ፈቃድ በመታዘዝ አዳኛችን ሆኖ
ወደዚህ ምድር እንደመጣ፣ በጥምቀቱ አማካይነትም ሐጢያቶቻችንን በሙሉ
እንደተሸከመና በእኛ ፋንታም በመስቀል ላይ እንደሞተ ስለምናምን ለእኛ አንድ
ጌታና አንድ አምላክ አለን ማለት ነው፡፡ ሰዎች በዚህ ዓለም ላይ ብዙ አምላኮች
ቢያመልኩም መላውን ዩኒቨርስና ሠራዊቶቻቸውን የፈጠረውና እኛን ያዳነን ፈጣሪ
ብቸኛው እውነተኛ አምላክ ነው፡፡ ይህ አምላክ አምላካችን ነው በምንልበት ጊዜ
ሁሉ ይህ የተመሰረተው ቸርና በፍቅር የተሞላ በመሆኑ እውነታ ላይ ነው፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ አምላካችን ‹‹የሁሉ አባት›› (ኤፌሶን 4፡6) እንደሆነ ደግሞ
ይናገራል፡፡ በዚህ ዩኒቨርስ ውስጥ ያለውን የሚታየውንና የማይታየውን እንዳንዱን
ነገር የፈጠረው ማነው? ሁሉንም የፈጠረው እግዚአብሄር ነው፡፡ ስለዚህ
እግዚአብሄር አብ ፍጹም የሆነ ፈጣሪ በመሆኑ ከሁሉም በላይ ነው፡፡ እርሱ እንደ
እኛ እንደ ፍጡራኖቹ የተዋረደ አይደለም፡፡ ነገር ግን እርሱ ከሁሉም በላይ ከፍ ያለ
ፈጣሪያችን፣ አዳኛችንና አምላካችን ነው፡፡ ምክንያቱም መላውን ዩኒቨርስና
ሠራዊቶቹን ሁሉ የፈጠረው እርሱ ነውና፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


206 በሕይወታችሁ ውስጥ ያለውን እምነት ጠብቁ

ጳውሎስ በኤፌሶን 4፡6 ላይ አምላካችን ‹‹በሁሉም የሚኖር›› እንደሆነም


ደግሞ ተናግሮዋል፡፡ እግዚአብሄር ዩኒቨርስንና በውስጡ ያሉትን ነገሮች ሁሉ
ሲፈጥር ሰው በእግዚአብሄር ፊት ደካማ ፍጡር ነበር፡፡ እናንተና እኔም እንዲህ
ያለን የተዋረድን ፍጥረቶች ነበርን፡፡ እግዚአብሄር አብ ግን ልጁን ወደዚህ ምድር
በመላክና በዚህ ልጅ ውሃና ደም እኛን በማዳን ከራሱ ጋር አንድ አደረገን፡፡ በሌላ
አነጋገር እግዚአብሄር አብ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት የራሱ
ወንዶችና ሴቶች ልጆች የመሆን ማዕረግ አንድንይዝ ባረከን፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሄር አባታችን ‹‹ከሁሉ በላይ የሚሆን በሁሉም
የሚሠራ በሁሉም የሚኖር›› (ኤፌሶን 4፡6) እንደሆነ ሲናገር እግዚአብሄር
የሐጢያቶችን ስርየት በተቀበሉ ልቦች ሁሉ ውስጥ ይኖራል ማለቱ ነው፡፡
ፓንቴይዝምን (ሁሉም ነገር አምላክ ነው የሚል ፍልስፍና) የተቀበሉ አንዳንድ
ፈላስፎች መጥረጊያዎች፣ ድንጋዮች፣ ጨረቃ፣ ጸሐይና ባህሮች በሙሉ እንኳን
ሳይቀሩ መለኮታዊ ፍጥረቶች ናቸው ብለው በመናገር በዚህ ዓለም ላይ ያለው
እያንዳንዱ ነገር አምላክ ነው ብለው ይከራከራሉ፡፡ ነገር ግን ይህንን ዩኒቨርስ
የሞላውና በእናንተና በእኔ ልብ ውስጥ የሚኖረው አምላክ ብቸኛው እውነተኛ
አምላክ ነው፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ ‹‹በመጠራታችሁ በአንድ ተስፋ እንደተጠራችሁ
አንድ አካልና አንድ መንፈስ አለ፡፡ አንድ ጌታ፣ አንድ ሐይማኖት፣ አንዲት ጥምቀት፣
ከሁሉ በላይ የሚሆን፣ በሁሉም የሚሠራ፣ በሁሉም የሚኖር አንድ አምላክ የሁሉም
አባት አለ፡፡›› (ኤፌሶን 4፡4-6) እንዳለ ይህ እውነተኛው አምላክም ከእኛ ጋር
ነው፡፡ እኛ ከየት መጣን? የመጣነው ከእግዚአብሄር ነው፡፡ ከእግዚአብሄር
የተወለዱ ሁሉ የእርሱ ሕዝብ ናቸው፡፡ በአንጻሩ እግዚአብሄርን በደህንነት ሥራው
መሠረት በትክክል የማያምኑ ሰዎች የእርሱ ሕዝቦች አይደሉም፡፡ ነገር ግን
የዲያብሎስ አገልጋዮች ናቸውና የእርሱ ጠላቶች ናቸው፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ ‹‹በሰላም ማሰሪያ የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ
እንድንተጋ›› (ኤፌሶን 4፡3) የነገረን ለዚህ ነው፡፡ የመንፈስን አንድነት መጠበቅ
ማለት ለእኛ ምን ማለት ነው? ይህ ማለት አንድ አካል ሆነናል ማለት ነው፡፡ ኢየሱስ
ክርስቶስ በዚህ ምድር ላይ እኛን ለማዳን እንደተጠመቀ፣ ተሰቅሎ እንደሞተና
ከሙታን እንደተነሳ በማመን የሐጢያቶችን ስርየት ተቀብለናል፡፡ ሰላምም ወደ
ልቦቻችን ገብቷል፡፡ ከሐጢያቶቻችን ሁሉ በመንጻት የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን
አባሎች የሆንነው በዚህ እውነት ስለምናምን ነው፡፡ ኢየሱስ ራስ ነው፡፡ እኛም
የአካሉ ብልቶች ነን፡፡ እኛ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር አንድ ሆነናል፡፤ ከእጅ ጣቶቻችሁ
ጀምሮ እስከ እግር ጣቶቻችሁ ድረስ ያለው እያንዳንዱ ክፍልና እያንዳንዱ ብልት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በሕይወታችሁ ውስጥ ያለውን እምነት ጠብቁ 207

የአንድ አካል ብልቶች እንደሆኑ ሁሉ እኛም እርስ በርሳችን እንተባበራለን፡፡ እርስ


በርሳችን እንመሰጋገናለን፡፡ እርስ በርሳችንም እንተጋገዛለን፡፡ በሌላ አነጋገር
እያንዳንዳችን እርስ በርሳችን እንፈላለጋለን፡፡ እርስ በርሳችን ያለን ፍላጎት የተሟላ
ባይሆንም እርስ በርሳችን ካልተደጋገፍን በእጅጉ ብቸኝነት ይሰማናል፡፡ አንዳንድ
ጊዜ እርስ በርሳችን ብንጣላም አንዳችን ለሌላችን እናስፈልገዋለን፡፡ የምንፈልገው
ማንን ነው፣ እያንዳንዳችን እንፈላለጋለን፡፡
ሁላችንም እርስ በርስ እንፈላለጋለን፡፡ በአንድ እምነት አንድ አካል ሆነናል፡፡
ምክንያቱም ሁላችንም ጌታ አዳኛችንን እንወደዋለንና፡፡ በአጭሩ እርስ በርሳችን
እንፈላለጋለን፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ ስለ ቤተክርስቲያን፣ የሐጢያቶችን ስርየት
በመቀበል ደህንነት ያገኙ ሰዎች ሁሉ ሊጠብቁት ስለሚገባቸው የእምነት ዓይነትና
ይህ እምነት እንዴት ሊጠበቅ እንደሚገባው ተናግሮዋል፡፡ ይህ በእጅጉ አስፈላጊ
ርዕሰ ጉዳይ ነው፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ ‹‹አንድ ጌታ፣ አንድ ሐይማኖት፣ አንዲት
ጥምቀት›› (ኤፌሶን 4፡5-6) እንዳለ ሲናገር በዚህ እውነተኛ ወንጌል ላይ ባለን የጋራ
እምነት አማካይነት በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አንድ እንደሆንን እያስተማረን
ነበር፡፡

ከአጥማቂው ዮሐንስ የተቀበለውን ጥምቀቱን ትተን በኢየሱስ ብናምን


እውነተኛ እምነት በውስጣችን ሊበቀል አይችልም፡፡

ሐዋርያው ጳውሎስና ሌሎቹም ሐዋርያቶች በሙሉ የውሃውንና የመንፈሱን


ወንጌል በሰበኩ ጊዜ ሁሉ የኢየሱስ ክርስቶስን ጥምቀት መስክረዋል፤ በጭራሽ
አልተዉትም፡፡ ነገር ግን ይህ ሆኖ ሳለ በዚህ ዘመን የሚኖሩ በርካታ ክርስቲያኖች
ጌታ በዮርዳኖስ ወንዝ በአጥማቂው ዮሐንስ የተቀበለውን ጥምቀት ትተው ስለ
ኢየሱስ ይሰብካሉ፡፡
የመገናኛው ድንኳን አደባባይ የመጋረጃ በር ከሰማያዊ፣ ከሐምራዊ፣ ከቀይ
ማግና ከጥሩ በፍታ መፈተል እንደነበረበት አሳምራችሁ ሳታውቁ አትቀሩም፡፡
(ዘጸዓት 27፡16) ሙሴ ሠራተኞቹን በሩን ከሐምራዊ፣ ከቀይ ማግና ከጥሩ በፍታ
እንዲፈትሉ ቢነግራቸው ኖሮ ሕጋዊ ይሆን ነበር? ይህ ምሳሌ ኢየሱስን አዳኛቸው
አድርገው የሚናገሩትን የዘመኑን ክርስቲያኖች ይመለከታል፡፡ ከእነርሱ ብዙዎቹ
የኢየሱስ ጥምቀት እውነተኛውን ወንጌል ከሚያዋቅሩት ዋና ዋና ፍሬ ነገሮች አንዱ
መሆኑን አያምኑም፡፡ የእነዚህ የተሳሳቱ ክርስቲያኖች የተሳሳተ እምነት ልክ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


208 በሕይወታችሁ ውስጥ ያለውን እምነት ጠብቁ

ከሐምራዊው፣ ከቀዩ ማግና ከጥሩወ በፍታ ብቻ ከተፈተለው ሕጋዊ ያልሆነ


የመገናኛው ድንኳን አደባባይ በር ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡ እግዚአብሄር እንዲህ
ያለውን ሕጋዊ ያልሆነ የመጋረጃ በር እንደሚቀድድ ሁሉ እንዲህ ያለውንም
የተሳሳተ እምነት ቀድዶ ይጥለዋል፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሄር ግዛት በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
አማካይነት የሰጠን የደህንነት ክልል እንደሆነ በግልጥ ያስተምረናል፡፡ በሌላ አነጋገር
ጌታ እኛን ከሐጢያቶቻችን ለማዳን ካደረገልን የደህንነት ሥራ ውስጥ የእርሱን
ጥምቀት ወይም የመስቀል ላይ ደሙን ፈጽሞ ልንተው እንደማይገባን በግልጥ
ነግሮናል፡፡ ነገር ግን አሁንም ብዙ ከርስቲያኖች ኢየሱስ ራሱ አምላክ እንደሆነ
እንኳን አያምኑም፡፡ እነዚህ ሁሉ ሰዎች ሐይማኖተኞች ናቸው፡፡
በብዙ ሐይማኖቶች የሚያምኑ ሰዎች ኢየሱስ ብቸኛው አዳኝ እንዳልሆነ ነገር
ግን ቡድሃም፣ ኮንፊሺየስም፣ መሐመድ ማንኛውም ሰው አዳኝ መሆን እንደሚችል
በመከራከር ከአንድ በላይ አዳኝ እንዳለ ይናገራሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች ተከተዮቻቸውን
ኒርቫና ላይ ድረስ፤ በራሰህም አምላክ ሁን፤ ጻድቅ ሰው ለመሆንም ራስህን ቀድስ››
ብለው ያስተምሩዋቸዋል፡፡ ነገር ግን እነዚህ ሐይማኖት መሪዎች እኛን ለማጥፋት
ነፍሳችን የያዘችውን በእግዚአብሄር ላይ ያለ እውነተኛ እምነት ሊሰርቁን እየሞከሩ
ነው፡፡ እነርሱ ዘራፊዎች ናቸው፡፡ እነዚህ ውሸታሞች እንዴት ሰውን ማዳን ይችላሉ?
ጌታችን ስለ እነዚህ ወሮበሎች እንዲህ በማለት አስጠንቅቆናል፡- ‹‹ሌባው ሊሰርቅና
ሊገድል ሊያጠፋም እንጂ ለሌላ አይመጣም፡፡ እኔ ግን ሕይወት እንዲሆንላችሁ
እንዲበዛላችሁም መጣሁ፡፡›› (ዮሐንስ 10፡10) በዚህ ዓለም ላይ ያለ የትኛውም
የሐይማኖት መሪ ለማንም ሰው የዘላለምን ሕይወት ሊያመጣ አይችልም፡፡
በተቃራኒው የሐይማኖት መሪዎች በሙሉ በጥረቶቻቸው ደህንነታቸውን
እንዲያገኙ ለተከታዮቻቸው ያስተምራሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች እውነተኛውን አዳኝ
የሚሰብኩ ሰባኪዎች አይደሉም፡፡
በአንጻሩ አዳኛችን መላውን ዩኒቨርስና ሠራዊቶቹን በሙሉ ከመፍጠሩም
በላይ የራሱ ሕዝቦች ሊያደርገንም ራሱ ወደዚህ ምድር መጥቷል፡፡ ከዚያም
በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅ የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ ተሸከመ፡፡
በመስቀል ላይም ደሙን አፈሰሰ፡፡ ከሙታንም ተነሳ፡፡ በዚህም እውነተኛ አዳኛችን
ሆነ፡፡ ኢየሱስ ከአጥማቂው ዮሐንስ በተቀበለው ጥምቀት በመስቀል ላይ ባፈሰሰው
ደም አማካይነትም ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ፈጽሞ አዳነን፡፡ በዚህ እውነት
ለምናምነው ሁሉም የዘላለምን ሕይወትና የሐጢያቶችን ስርየት ሰጠን፡፡ በእምነት
ቤዛነታችን ላይ እንድንደርስም ወደ ደህንነት የሚያደርሰውን መንገድ አዘጋጀልን፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በሕይወታችሁ ውስጥ ያለውን እምነት ጠብቁ 209

በመገናኛው ድንኳን አደባባይ በር ላይ የተገለጠውን ምስጢር ስለጠቀስሁ እኛ


የሰማያዊውን፣ የሐምራዊውን፣ የቀዩን ማግና የጥሩውን በፍታ እውነት በመረዳትና
በማመን ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ድነናል፡፡
ክንውኖቻችንን ወይም ትሩፋቶቻችን ለእርሱ በማቅረብ ከእግዚአብሄር
ዘንድ በረከቶችን ለመቀበል የምንሞክር ከሆነ እግዚአብሄር እንደሚጠላን
የተረጋገጠ ነው፡፡ በእግዚአብሄር ጽድቅ ብቻ በማመን ከሐጢያቶቻችን ሁሉ መዳን
እንችል ዘንድ ኢየሱስ ቀድሞውኑም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት
ሙሉ በሙሉ ደህንነታችንን አከናውኖታል፡፡ ስለዚህ አሁንም ድረስ
የእግዚአብሄርን ጽድቅ ችላ የምንልና በራሳችን ጽድቅ ወደፊቱ ልንቀርብ የምንሞክር
ከሆነ ከመባረክ ርቀን በእርግጠኝነት እንረገማለን፡፡ ማናችንም እንደ ቃየን
ዕብሪተኞች ልንሆን አይገባንም፡፡ ደህንነታችንን የተቀበልነው እግዚአብሄር
በሰጠው የውሃና የመንፈስ ወንጌል በማመናችን ብቻ ነው፡፡ እግዚአብሄር
የሚቀበለው ብቸኛው እምነት ይህ ነው፡፡ እኛ ራሳችን በጉድለቶች የተሞላን
ብንሆንም ትክክለኛው እምነት በመታዘዝ የጌታን ቃል እንድንከተልና አንድ ላይ
እንድንተባበር ይጠይቀናል፡፡
አንዳንድ ጻድቃኖች በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ ከመኖርና በአዳኘ
ከማመን ይልቅ ማድረግ የሚኖርባቸው አንዳች ተጨማሪ ነገር እንዳለ ያስባሉ፡፡
ነገር ግን በእግዚአብሄር ቃል ከማመን በስተቀር ማድረግ የሚያስፈልጋቸው ምንም
ነገር የለም፡፡ ብቸኛው እውነተኛ እምነት በእግዚአብሄር ጽድቅ ላይ የተቀመጠ
እምነት ነው፡፡ እናንተስ ታዲያ? እምነታችሁን ያኖራችሁት በማን ላይ ነው? እኛ
በእግዚአብሄርና በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ላይ እምነት አለን፡፡ ጌታ
ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ሊያድን የሰው ስጋ ለብሶ ወደዚህ ምድር በመምጣት፣
በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅ፣ በመስቀል ላይ በመሞትና ዳግመኛም ከሙታን
በመነሳት ሐጢያቶቻችንን በሙሉ እንደደመሰሰ በማመን ሁላችንም
ከሐጢያቶቻችን ነጽተናል፡፡ በጌታ ጥምቀትና በመስቀል ላይ ደሙ በማመን
ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ከመንጻታችንም በላይ ከሐጢያቶች ኩነኔ ሁሉም ድነናል፡፡
ከዚህ የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ውጪ ሌላ ወንጌል ሊኖር አይችልም፡፡ በዚህ
እውነተኛ ወንጌል በማመን ከሚገኘው ውጪም አንዳች ሌላ ደህንነት የለም፡፡
በቅርቡ በኮስታሪካ ከሚገኝ አንድ ሰው ኢሜል ደረሰኝ፡፡ ይህ ሰው በኢሜሉ
ወንጌልን በዚያ ለመስበክ ከ1986 ዓ.ም ወደ አገሩ የመጣ አንድ የወንጌላውያን
ቤተክርስቲያን መጋቢ እንደነበርና የዚህ መጋቢ ትምህርትም ከእኛ ጋር በአብዛኛው
እንደሚመሳሰል ተናገረ፡፡ ከዚያም የራሱን አስተያየት በመስጠት እኛ የሰበክነው

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


210 በሕይወታችሁ ውስጥ ያለውን እምነት ጠብቁ

ወንጌል የተሳሳተ እንደነበር መከራከር ጀመረ፡፡ እርሱ ጌታ እንዴት ሐጢያቶቻችንን


በሙሉ በትክክል እንደደመሰሰ በተጨባጭ ሳያብራራ ሰው በኢየሱስ በማመን
ጻድቅ እንደሆነ ከሚናገር የወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያን መጋቢዎች ከአንዱ
ሰምቶ ሊሆን ይችላል፡፡ ነገር ግን እነዚህ ወንጌላውያን ቤተክርስቲያኖች በኢየሱስ
ጥምቀት እንደማያምኑና እምነታቸውም በእጅጉ ጥራዝ ነጠቅ እንደሆነ መረዳት
አለባችሁ፡፡ በነገራችን ላይ የኮስታሪካዊው ሰው እምነት ኢየሱስ ተሰቅሎ ከሞተና
ጨለማ እስኪወርድ ድረስ በእግዚአብሄር አብ ለሦስት ሰዓታት ያህል ከተረሳ በኋላ
ወዲያውኑ የዓለምን ሐጢያቶች እንደተሸከመ የሚናገር ነበር፡፡ የዚህ ሰው እምነት
ፈጽሞ የተሳሳተ እንደሆነ የታወቀ ነው፡፡ ነገር ግን ኢሜሉን ችላ ከማለትና
ከመደለዜ ይልቅ እውነትን የመመስከሪያ መሳርያ አድርጌ ላቆየው ወሰንሁ፡፡
አጋር ምዕመናኖቼ እግዚአብሄር ሙሉ በሙሉ በእርሱ ጽድቅ የማያምኑትንም
ሆነ ሙሉ በሙሉ የማይክዱትን እነዚህን ሰዎች አብዝቶ ይጠላቸዋል፡፡ ‹‹እንዲሁ
ለብ ስላልህ በራድም ወይም ትኩስ ስላልሆንህ ከአፌ ልተፋህ ነው፡፡›› (ዮሐንስ
ራዕይ 3፡16) ተብሎ እንደተጻፈ እግዚአብሄር እነዚህን ሰዎች ከአፉ ይተፋቸዋል፡፡
በውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ከመስቀሉ ደም ወንጌል የተለየ አይደለም የሚል ሰው
ካለ የዚህ ሰው እምነት መጽሐፍ ቅዱስ ‹‹አንድ ጌታ፣ አንድ ሐይማኖት፣ አንዲት
ጥምቀት›› (ኤፌሶን 4፡5) እንደሚል ከአንድ ወንጌል በላይ በፍጹም ሊኖረው
አይችልም፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ እዚህ ላይ በግልጥ ‹‹አንድ ጥምቀት›› ብቻ እንዳለ
የተናገረው ለምንድነው? ያንን ያደረገው ሐጢያቶቻችን በሙሉ እርሱ በአጥማቂው
ዮሐንስ በተቀበለው ጥምቀት አማካይነት ወደ ኢየሱስ ስለተላለፉ ነበር፡፡ ኢየሱስ
በመስቀል ላይ የሞተልን ይህንን ጥምቀት ከአጥማቂው ዮሐንስ በመቀበል የሞት
ወንዝ በሆነው በዮርዳኖስ ወንዝ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ በመሸከሙ ነበር፡፡
አጥማቂው ዮሐንስ በጥምቀቱ አማካይነት የዚህን ዓለም ሐጢያቶች በሙሉ ወደ
ኢየሱስ ባያስተላልፍ ኖሮ ኢየሱስ ተሰቅሎ የሚሞትበት ምክንያት ባልኖረም ነበር፡፡
ስለዚህ ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ ባይጠመቅ ኖሮ ሞቱ በራሱ ፈጽሞ ከንቱና
ትጉም የለሽ በሆነ ነበር፡፡ ይህንን ውጤት ለማስገኘት የሚያስፈልገውን ይህንን
ሒደት አስቀድማችሁ ካልተረዳችሁና በዚያ ውስጥ ካላለፋችሁ በስተቀር አንዳች
ውጤት ማግኘት እንደማትችሉ ሁሉ የዘመኑ ክርስቲያኖችም የኢየሱስን ጥምቀት
እስካላወቁና ለመገንዘብ እምቢተኞች እስከሆኑ ድረስ በመስቀል ላይ የፈሰሰውን
የኢየሱስን ደም በጭራሽ መረዳት አይችሉም፡፡ ስለዚህ አብዛኛውን ጊዜ የኢየሱስን
ጥምቀት አብዝቼ ትኩረት የማደርግበት ተገቢ ስለሆነ ነው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በሕይወታችሁ ውስጥ ያለውን እምነት ጠብቁ 211

ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅ የዚህን


ዓለም ሐጢያቶች በሙሉ ተቀበለ፡፡

ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ


ተሸከመ፡፡ ከዚያም ሐጢያቶቻችንን በሙሉ በመስቀል ላይ ተሸክሞ ተሰቅሎ ሞተ፡፡
አሁን ኢየሱስ ከሙታን ስለተነሳ በእግዚአብሄር አብ ቀኝ ተቀምጦዋል፡፡ ኢየሱስ
አዳኛችን የሆነው እንደዚህ ነው፡፡ እርሱ ደህንነታችንን የሚመሰክር እውነተኛ
አዳኛችን ሆነ፡፡ ምክንያቱም እርሱ አሁን ሕያው ነው፡፡ ኢየሱስ ለደህንነታችን
የሰው ስጋ ለብሶ ወደዚህ ምድር የተወለደው በጥምቀቱ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ
ለመሸከም ነበር፡፡ ኢየሱስ ሰው ሆኖ በተወለደበት በዚህ ዓላማ መሠረት
ስለተጠመቀ በመስቀል ላይ ሞተ፤ ከሙታንም ተነሳ፡፡ በእግዚአብሄር አብ ዕቅድ
መሠረትም አዳኛችን ሆነ፡፡
ኢየሱስ ይህንን የደህንነታችንን ሥራ ያቀደው ተግባራዊ ከማድረጉ በፊት
እንደነበር እውነት ነው፡፡ በዕቅዱ መሠረትም ተግባራዊ አደረገው፡፡ የሴቲቱ ዘር
ሆኖም ወደዚህ ምድር ለመምጣት ቃል ገባ፡፡ (ዘፍጥረት 3፡15፤ ኢሳይያስ 7፡14)
ቃል በገባው መሠረትም ማርያም በምትባል ደንግል ሴት አማካይነት ስጋ ለብሶ
ወደዚህ ምድር መጣ፡፡ በመጠመቅም የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ ተሸከመ፡፡
በመስቀል ላይም ደሙን አፍስሶ ሞተ፡፡ ዳግመኛም ከሙታን ተነሳ፡፡ አሁንና
ለዘላለምም ሕያው ነው፡፡ ኢየሱስ አሁንም ሕያው ስለሆነ ለእኛ ያደረገው
እያንዳንዱ ነገር እውነተኛና ለዘላለም ውጤታማ ነው፡፡ እውነተኛ አዳኛችንም
ሆንዋል፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ አንድ ጌታ ብቻ እንዳለ እንደተናገረ ሁሉ ለእኛም
እንደዚሁ አንድ አዳኝ ብቻ አለ፡፡ ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ያዳነን ኢየሱስ ብቻ
የሆነው ለዚህ ነው፡፡ ታዲያ በልባችሁ ውስጥ አንዳች ሐጢያት አለ? ፈጽሞ
ሐጢያት የለም፡፡ ታዲያ ሐጢያቶቻችሁ የተወገዱት በኢየሱስ የመስቀል ላይ ደም
ብቻ በማመን ነውን? አይደለም፡፡ ሐጢያቶቻችሁ በሙሉ የተደመሰሱት ኢየሱስ
በአጥማቂው ዮሐንስ በተቀበለው ጥምቀትና በመስቀል ላይ ባፈሰሰው ደም
በማመን ነው፡፡ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ማንጻት የቻልነው በኢየሱስ ጥምቀትና
በመስቀሉ ደም ላይ ባኖርነው በዚህ እምነት አማካይነት ብቻ ነበር፡፡ አሁንም ቢሆን
ሰውን ሁሉ ከሐጢያቶቹ ማዳን የሚችለው አንድ እምነትና አንድ ወንጌል ብቻ
እንጂ ሁለት አይደለም፡፡ ይህም ወንጌል ሌላ ሳይሆን የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል
ነው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


212 በሕይወታችሁ ውስጥ ያለውን እምነት ጠብቁ

እናንተስ ታዲያ? ከሐጢያቶቻችሁ ሁሉ ሊያድናችሁ የሚችለው የውሃውና


የመንፈሱ ወንጌል አላችሁን? እምነታችሁ ከቀረነው ሰዎች የተለየ ነውን?
እምነታችሁ ከእኛ እምነት የተለየ ከሆነ ይህ ማለት ወደ እግዚአብሄር ቤተክርስቲያን
ሾልካችሁ የገባችሁት በትክክለኛ እምነት አይደለም ማለት ነው፡፡ የእግዚአብሄርን
ጽድቅ የሚቃወመው እምነት የትኛው ነው? ወደ ክርስቶስ ሾልኮ የገባ ሰው ተብሎ
ሊገለጥ የሚችለው ማነው? እነርሱ ለደህንነታቸው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
ብቻ ከማመን ይልቅ በሌላ ነገር የሚያምኑ ሰዎች ናቸው፡፡ ስለዚህ እነዚህ ሰዎች
የጥፋትን ፍሬ ያፈራሉ፡፡ ምክንያቱም ልቦቻቸው ሐጢያተኛ ናቸውና፡፡
እግዚአብሄር ሲፈጥረን ነጻ ፈቃድ ሰጥቶናል፡፡ ‹‹በዘመን ፍጻሜ ይደረግ ዘንድ
ያለው አሳቡም በሰማይና በምድር ያለውን ሁሉ በክርስቶስ ለመጠቅለል ነው፡፡››
(ኤፌሶን 1፡10) በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን ደህንነታችንን እንድናገኝም
አስችሎናል፡፡ ጌታ እኛን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማዳን የእግዚአብሄር
ልጆች አድርጎናል፡፡ ከእግዚአብሄር ጋር በትክክል እንድንተሳሰር ያስቻለን እምነት
ይህ ነው፡፡ ጌታችን ለሁላችንም ‹‹ወንድ ልጆቼና ሴት ልጆቼ ሆናችሁ በሰማይ ክብር
ትደሰቱ ዘንድ ሁላችሁንም ከሐጢያቶቻችሁ ሁሉ ማዳን ፍላጎቴ ነው›› ይለናል፡፡
አጋር ምዕመናኖቼ የእግዚአብሄር ዋናው ዕቅድና የግቡም የመጨረሻ ፍጻሜ ይህ
ነው፡፡

ጌታ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በሚያምኑ ሰዎች


ሁሉ ልቦች ውስጥ ይኖራል፡፡

የኢየሱስን ጥምቀትና የመስቀል ላይ ደሙን የሐጢያቶቻችን ደህንነት አድርገን


ማመናችን ለሁላችንም በእጅጉ አስፈላጊ ነው፡፡ እርስ በርሳችን ሕብረትን መጋራት
የምንችለው በዚህ የጋራ እምነት አማካይነት ብቻ ነው፡፡ በፍጹም በኢየሱስ ደም ላይ
ብቻ ትኩረት ማድረግ የለብንም፡፡ በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ ያለ ማንም
ሰው በዚህ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ከሚያምነው እምነት ውጪ አንዳች ሌላ
ነገር ቢያስተምር ልናስቆመው ይገባናል፡፡ ምክራችንን ትተው በተሳሳቱ
እምነቶቻቸው ላይ አሁንም በመንጠልጠል የሚቀጥሉ ከሆኑ ከእነርሱ ጋር ያለንን
ግንኙነት ማቆም አለብን፡፡ እንዲህ ያሉ ሰዎች በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ
ከተገኙ እኛ እንዳደረግነው ወይ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ያምኑ ዘንድ መለወጥ
አለበለዚያም የእግዚአብሄርን ቤተክርስቲያን ትተው እንዲወጡ መጠየቅ ነው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በሕይወታችሁ ውስጥ ያለውን እምነት ጠብቁ 213

የእግዚአብሄር ብቸኛ ወንጌል የሆነውን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል


የማያምነውን ማንኛውንም ሰው መቃወም ፈጽሞ ተገቢያችን ነው፡፡ ጌታ ያዳነን
በዚህ ወንጌል አማካይነት ሆኖ ሳለ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል እውነት የማያምን
ሰው ቢኖር ይህ ሰው በራሱ ጽድቅ የእግዚአብሄርን ጽድቅ እየተቃወመ ነው፡፡
‹‹በሰላም ማሰሪያ የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ [መትጋት]›› (ኤፌሶን 4፡3)
እንዳለብንም አዞናል፡፡ በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ ያለ ማንኛውም ሰው
ይህንን ትዕዛዝ በተጨባጭ የማይታዘዝ ነገር ግን በኢየሱስ በማመን እንደዳነ
በመወትወት አብረውት ያሉትን ቅዱሳኖች የሚያሰቃይ ከሆነ ሥራ ፈትተን
ልንመለከተው አንችልም፡፡ እነዚህን ወላዋዮች ማወቅና በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል ላይ ጸንተው እንዲቆሙ ልናስተምራቸው ይገባናል፡፡ እስከ መጨረሻው
ድረስ የማይታዘዙን ከሆነ ልቦቻችን ቢያዝኑም እንኳን በድፍረት ከእግዚአብሄር
ቤተክርስቲያን ልናገልላቸው ይገባናል፡፡
በአሁኑ ጊዜ በጣም ብዙ ሰዎች የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል እውነት
ስለማያውቁ ማን እንደዳነና ማን እንዳልዳነ እንኳን አያውቁም፡፡ ስለዚህ በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል ግልጥ የሆነ የእምነት ድንበር ማስመርና ደህንነት ሊገኝ የሚችለው
በዚህ ድንበር ውስጥ ብቻ እንደሆነ ለሰው ሁሉ መመስከር ይገባናል፡፡ እግዚአብሄር
ወደሰራው ወደዚህ የደህንነት ድንበር መግባት የሚፈልግ ማንኛውም ሰው በእምነት
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በር ውስጥ ማለፍ አለበት፡፡ በዚህ በር ውስጥ አልፎ
የማይገባ ማንኛውም ሰው አይድንም፡፡ ሁላችንም እግዚአብሄር ባጸናው በዚህ ሕግ
ማመንና ይህንንም በእምነት መተግበር አለብን፡፡
የእምነት ሕይወታችንን ስንኖር የሰውየው እምነት እውነተኛ እንደሆነ ወይም
ሐሰተኛ እንደሆነ ለማረጋገጥ እያንዳንዱን የደህንነት ምስክርነትና እያንዳንዱን
የእምነት ተሞክሮ መዝገበን መያዝም እንደዚሁ ያስፈልገናል፡፡ ከእኛ አንዱ ባይሆኑም
ወይም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የጋራ እምነት ባይጋሩም አብረውን
በመካከላችን ያሉ አንዳንድ ሰዎች አሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች ብዙ ክፋቶችን ያስፋፋሉ፡፡
እንዲህ ያሉ ብዙ ሰዎችን አይተናል፤ ተጋፍጠንማል፡፡ ምስክርነቶቻቸውንም
ለማረጋገጥ መመዝገብና ማስቀመጥ የሚያስፈልገው ለዚህ ነው፡፡ ማናቸውንም
ስጋዊ ድክመቶች መታገስና መሸከም ብንችልም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ላይ
እምነት ግልጥ ያልሆነውንና የሚያሻማውን ማንኛውንም ሰው መታገስ አንችልም፡፡
እንዲህ ያሉ የተሳሳቱ አማኞችን አንድ በአንድ በእውነተኛው ወንጌል በጽናት
እንዲያምኑ ማስተማር ወይም እውነተኛ ማንነታቸውን ማጋለጥ በእጅጉ
ያስፈልገናል፡፡ እኛ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የምናምን አማኞች ሳንሰናከል

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


214 በሕይወታችሁ ውስጥ ያለውን እምነት ጠብቁ

ከክርስቶስ ጋር መጓዝ የምንችለው ያን ጊዜ ብቻ ነው፡፡


በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ ያለ እያንዳንዱ ሰው በዚህ እውነተኛ
ወንጌል በማመን መኖር አለበት፡፡ ስለዚህ እምነቱን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
ላይ ያላኖረ ማንኛውም ሰው የእግዚአብሄርን ጽድቅ ይንቃል፡፡ በእርሱ የውሃና
የመንፈስ ወንጌል የማያምኑ እንዲህ ያሉ ሰዎች በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ
ካሉ ልናደርገው የሚገባን ትክከለኛው ነገር ማንም ይሁኑ ወይ እነርሱን
ከእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ማባረር አለበለዚያም ከእኛ ጋር ተመሳሳይ የሆነ
እምነት እንዲኖራቸው ማድረግ ነው፡፡ በትክክል በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
ሳያምን ወደ እግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ሾልኮ የገባውን ማንኛውንም ሰው በፍጹም
አቅልለን ልንታገሰው አይገባንም፡፡ በተቃራኒው እንዲህ ያሉ ሰዎች ወደ እግዚአብሄር
ቤተክርስቲያን እንዳይገቡ ለመከላከል የሚቻለውን ነገር ሁሉ ልናደርግ ይገባናል፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ ‹‹በሰላም ማሰሪያ የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ
[እንድንተጋ]›› (ኤፌሶን 4፡3) መክሮናል፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ እንድንጠብቀው
የነገረን ምንድነው? እርሱ እንድንጠብቀው የነገረን ሌላ ማንኛውንም ነገር ሳይሆን
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ላይ ያለንን እምነት ነው፡፡ እዚህ ላይ እግዚአብሄር
እያስተማረን ያለው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል እንድናምንና ይህንን እምነታችንን
እንድንጠብቅ ነው፡፡ አንዳንዶቻችሁ ‹‹ሐዋርያው ጳውሎስ በዚህ ምንባብ ላይ
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል እንደንጠብቅ የነገረን የት ላይ ነው? ውሃ ወይም
የጌታ ጥምቀት የተጠቀሰበት ስፍራ የለም›› በማለት ግራ ይጋባሉ፡፡ ነገር ግን እኔ
እዚህ ላይ ስለ ውሃውና መንፈሱ ወንጌል እየተናገርሁ ያለሁት በራሴ አተረጓጎም
መሠረት አይደለም፡፡ ነገር ግን ስለዚህ ወንጌል እየተናገርሁ ያለሁት እግዚአብሄር
ራሱ ስለዚህ እውነተኛ ወንጌል በመናገሩ ነው፡፡ የውሃውና የመንንፈሱ ወንጌል
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በማንኛውም ስፍራ አይገኝምን? ይገኛል፡፡ በቅዱሳት
መጻህፍት በሁሉም ስፍራ ይገኛል፡፡ የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ተስማሚ እንደሆነ
በማየት በማንኛውም መንገድ የማቀነቅነው አንዳች ነገር አይደለም፡፡ ይህንን
እውነተኛ ወንጌል መረዳት የማይችሉት በጣም ብዙ ሰዎች መንፈሳዊ ዕውራን
በመሆናቸው ምክንያት ነው፡፡
ማህበረሰባችንን ስንመለከት የሚመራው በሕግ ስርዓት እንደሆነ እናያለን፡፡
ልክ እንደዚሁ በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥም ደግሞ ቤተክርስቲያኑን
የሚያስተዳድር የእግዚአብሄር ሕግ እንዳለ ገልጥ ነው፡፡ ከዚህም በላይ
የእግዚአብሄር ሕግ ከማናቸውም ሰው ሰራሽ የሕግ ስርዓት የተለየ ስለሆነ ለዘላለም
ተግባራዊ ይሆናል፡፡ እግዚአብሄር ድክመቶቻችንን በሙሉ ቢታገስም ፈጽሞ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በሕይወታችሁ ውስጥ ያለውን እምነት ጠብቁ 215

የማይታገሰው አንድ ነገር አለ፡፡ ይህም ከውሃውና ከመንፈሱ ወንጌል ይልቅ ሌላ


ወንጌልን መቀበል ነው፡፡ ስለዚህ በሰላም ማሰሪያ የመንፈስን አንድነት ባመጣልን
በዚህ የውሃና የመንፈስ ወንጌል ላይ ያለንን እምነታችንን እስካልጠበቅን ድረስ
ደህንነታችንና ሰላማችን ከልቦቻችን ውስጥ ይጠፋሉ፡፡

በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ላይ ያለንን እምነታችንን መጠበቅ ማለት


በልቦቻችን ውስጥ ያለውን ሰላም መጠበቅ ማለት ነው፡፡

ሁላችንም ሰላም ምን እንደሆነ እናውቃለን፡፡ ጌታችን ቃል በገባው መሰረት


ሰላምን ሰጥቶናል፡፡ አምላካችን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት
ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ስላዳነን ይህንን እውነተኛ ሰላም ተቀብለናል፡፡ ነገር ግን
እግዚአብሄር ሰላምን ቢሰጥም ወንጌልን መጠበቅ ከተሳነን ይህንን ሰላም
እናጣዋለን፡፡ ስለዚህ ሰላምን ከተቀበልን በኋላ ይህንን ሰላም ለዘላለም መጠበቅ
በእጅጉ ያስፈልገናል፡፡ ይህንን ሰላም እስከ መጨረሻው ድረስ ለመጠበቅ በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል የሚያምን እምነት ሊኖረን የሚገባው ለዚህ ነው፡፡
ወደ እግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ለመምጣት የሚፈልግ ማንኛውም ሰው
ቢያንስ እግዚአብሄር በሰጠው የውሃና የመንፈስ ወንጌል ይህ እምነት ሊኖረው
ይገባል፡፡ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ሆነው ሊታወቁ የሚገባቸው እነዚህ የእምነት
ሰዎች ብቻ ናቸው፡፡ ነገር ግን ሰው ምንም ያህል ብርቱ ቢሆን በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል ካላመነ ሲዖል ለመጣል የተመደበ መንፈሳዊ አህዛብ መሆኑ የማይቀር
ነው፡፡ እነዚህ ሰዎች ልክ እንደ ማንኛውም ሌላ አህዛብ ልናስተናግዳቸውና
ወንጌልን በትዕግስት ልንሰብክላቸው የሚገባን የጠፉ በጎች አድርገን ልንቆጥራቸው
ይገባናል፡፡ ነገር ግን እነዚህ ሰዎች በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ሳያምኑ በእኛ ላይ
ለመሰልጠን የሚሞክሩ ከሆኑ በፍጹም ይህንን ልንፈቅድ አይገባንም፡፡ እነዚህ
ሰዎች ሊገለሉና ከወንድሞችና እህቶች ከእግዚአብሄር ባሮችም ጋር አብረው
ወንጌልን ለማገልገል ሊፈቀድላቸው አይገባም፡፡ እግዚአብሄር እንድናደርግ የነገረን
ይህንን ስለሆነ ለእናንተና ለእኔ ስንል ብቻ ሳይሆን ለእግዚአብሄር ቤተክርስቲያንም
ሲባል ደግሞ ልናደርገው የሚገባን ያንን ነው፡፡ እዚህ ላይ ሁላችንም የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል የሚንቅ ማንኛውም ሰው በእርግጠኝነት በእግዚአብሄር
እንደሚቀጣ ልንገነዘብ ይገባናል፡፡
በአንድ ወቅት በክርስቶስ ዱካዎች የሚል አንድ የቴሌቪዥን ጥናታዊ ፊልም

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


216 በሕይወታችሁ ውስጥ ያለውን እምነት ጠብቁ

አየሁ፡፡ ፊልሙ የሚያተኩረው አሁን ቱርክና ግሪክ ተብለው በሚጠሩት


የኤፌሶንንና የፊልጵስዩስን ክልሎች ጨምሮ ከትንሽዋ እስያ እስከ መቄዶንያ ድረስ
የተደረገውን የጳውሎስን የወንጌል ስብከት ጉዞ ነበር፡፡ ዛሬ በዚያ ስፍራ የውሃውና
የመንፈሱ ወንጌል ያለው ሰው አለ? ማንም የለም፡፡ ይህ ለምን ሆነ? ይህ የሆነበት
ምክንያት በጥንቷ የቤተክርስቲያን ዘመን የነበሩት ሐዋርያቶች ካለፉ በኋላ
የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል በእግዚአብሄር አገልጋዮች ባለመመስከሩ ነበር፡፡
ስለዚህ ወንጌልን ከብልሽት ሊከላከል የቻለ ሰው አልነበረም፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ እንዲህ በማለት ሁላችንንም መክሮናል፡- ‹‹መልካሙን
አደራ በእኛ በሚኖረው በመንፈስ ቅዱስ ጠብቅ፡፡›› (2ኛ ጢሞቴዎስ 1፡14) እዚህ
ላይ ጳውሎስ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በቀጥታ ከመጥቀስ ይልቅ ‹‹መልካሙ
አደራ›› ብሎ ጠርቶታል፡፡ ጌታ በሰላም ማሰርያ የመንፈስን አንድነት
እንድንጠብቅም ደግሞ ነግሮናል፡፡ ይህም ደግሞ የሚያሳየው የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል ነው፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ በእርሱ በተመረጡት ሐዋርያቶችና በመንፈስ ቅዱስ ምሪት
የተጻፈ የእግዚአብሄር ቃል ነው፡፡ ስለዚህ መጽሐፍ ቅዱስ በዋጋ የማይተመን ሥነ
ጽሁፋዊና ታሪካዊ መጣጥፍ ብቻ ሳይሆን ለነፍስ ትክክለኛ እምነትን የሚሰጥ
ፈጽሞ እንከን የሌለበት የእውነት ቃል ነው፡፡ በዚህ ዓለም ላይ በጣም የታወቁ
ጸሐፊዎችና ገጣሚያንም ቢሆኑ በቅዱሳት መጽሐፍ ውስጥ ወደተጻፈው ውብ የሆነ
የእግዚአብሄር ቃል ላይ አይደርሱምም፡፡ የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል እውነት
አንድ አድርጎናል፡፡ በእምነት እንድንኖርም አስችሎናል፡፡ ሁላችንም በዚህ ድንቅና
በዋጋ የማይተመን እውነት ማመን አለብን፡፡
በዚህ ዘመን የኢየሱስን ሕይወት የሚያሳዩ ፊልሞችን ማየት በጣም የተለመደ
ነው፡፡ ነገር ግን እነዚህ ፊልሞች አብዛኞቹ በእግዚአብሄር የሚያምን ሁሉ የተባረከ
የማያምን ደግሞ የተረገመ የመሆኑን እሳቤ በማስፋፋት መልካም ሥነ ምግባርን
በሚያደንቅና ክፋትን በሚያወግዝ አሰልቺ ትምህርቶች የሚጠናቀቁ ናቸው፡፡ ነገር
ግን ይህንን ፊልም በማየት የሐጢያቶችን ስርየት መቀበል የሚችል ማነው? ቢያንስ
ከእነዚህ ፊልሞች አንዱ ይበልጥ ትክክለኛውንና የተሟላውን የኢየሱስን ጥምቀት
ታሪክ ቢያቀርብና ኢየሱስ ለአጥማቂው ዮሐንስ ‹‹ሐጢያቶችን ሁሉ ለመቀበልና
ጽድቅን ሁሉ ለመፈጸም በአንተ ልጠመቅ ይገባኛል›› ሲለው ምን ማለቱ እንደሆነ
ቢያብራራ ያማረ ይሆን ነበር፡፡ ያን ጊዜ ሰዎች ይህንን አንድ ፊልም በመመልከት
ብቻ የሐጢያቶችን ስርየት መቀበል በቻሉ ነበር፡፡
በምሳሌ ላይ ‹‹የባለጠጋ ሐብት ለእርሱ የጸናች ከተማ ናት፡፡ የድሆች ጥፋት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በሕይወታችሁ ውስጥ ያለውን እምነት ጠብቁ 217

ድህነታቸው ነው›› (ምሳሌ 10፡15) ይላል፡፡ ሰዎች ድሆች ምንም ያህል አንደበተ
ርቱዕ ሆነው ቢናገሩ እንኳን አይሰሙዋቸውም፡፡ ነገር ግን የሰው ቃሎች ተጨባጭ
በሆኑ ቁሳዊ ጥቅሞች ሲታጀቡ እነዚህ ቃሎች ይበልጥ በቀላሉ ተቀባይነትን
ያገኛሉ፡፡ ለእነርሱ ያለንን ፍቅር ለማጋራትና ወንጌልንም በመላው ዓለም ሁሉ
ለመስበክ መጽሐፎቻችንን በዓለም ሁሉ ለሚገኙ ሰዎች በነጻ የምንሰጠው ለዚህ
ነው፡፡ በመላው ዓለም የሚኖሩ እነዚህ ሰዎች ከወንጌል መጽሐፎች አንዱን
በማንበብ ብቻ የሐጢያቶቻቸውን ስርየት መቀበል የሚችሉት እንዲህ ነው፡፡
ይህንን ወንጌልን የማስፋፋትን ሥራ መሥራታችንን መቀጠል ብቻ ሳይሆን
እስከ መጨረሻው ድረስም ይህንን እምነት መጠበቅ በእጅጉ ያስፈልገናል፡፡ ይህንን
እምነት እስከ መጨረሻው ድረስ መጠበቅ የሚገባን የድል አክሊል የሚሰጠው
ይህንን ለሚያደርጉ ብቻ ስለሆነ ነው፡፡ ወንጌልን በዓለም ሁሉ ብትሰብኩ ነገር ግን
እምነታችሁን ብታጡ ሰላማችሁንም ደግሞ ታጣላችሁ፡፡ ይህንን ሰላም ካጣችሁ
ደግሞ ሕይወታችሁንም ታጣላችሁ፡፡ ሕይወታችሁን ካጣችሁ ደግሞ ወደፊት
የሚጠብቁዋችሁ እርግማኖች ብቻ ይሆናሉ፡፡ ስለዚህ እስከ መጨረሻው ድረስ
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ላይ ያላችሁን እምነታችሁን መጠበቅ
ያስፈልጋችኋል፡፡ እናንተና እኔ የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል እንደምን ክቡርና ድንቅ
እንደሆነ መረዳት ይገባናል፡፡ ሁላችንም በዚህ ወንጌል ላይ ያለንን እምነታችንን
መጠበቅ ይገባናል፡፡
እዚህ ላይ ሁላችሁንም እንደምወዳችሁ ልናገር፡፡ እኔ የማልወደው ማንም
ሰው የለም፡፡ የምወደው በዓይኖቼ ፊት የተሰበሰባችሁትን እናንተን ብቻ ሳይሆን
በመላው ዓለም ባለችው የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ የሚገኙትን
አገልጋዮቻችንንና ቅዱሳኖቻችንንም ሁሉ ነው፡፡ ከቤተክርስቲያን ውጪ ያሉትንም
እንኳን እወዳቸዋለሁ፡፡ ስለ እነርሱ በጥልቀት የምናስበውና አንዳንድ ጊዜም
በግትርነታቸው የምንረበሸው እነዚህን የጠፉ ነፍሳቶች ሁሉ ስለምንወዳቸው ነው፡፡
እስከ መጨረሻው ድረስ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ላይ ያለንን እምነታችንን
ለመከላከል እንዲህ ላሉት የማያምኑ ሰዎች ሁሉ ርህራሄ ሊኖረንና ወንጌልን
ልንሰብክላቸው የሚያስፈልጋቸው አሳዛኝ ነፍሳቶች እንደሆኑ ልናጤን ይገባናል፡፡
በተመሳሳይ ጊዜም ሐሰተኛ ወንጌል ይዞ ወደ እግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ሾልኮ
የሚገባውን ማንኛውንም ሰው መቃወም እንድንችል ሊረዳን የሚችል እምነትም
ደግሞ ያስፈልገናል፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ እዚህ በዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ላይ
እንዳስተማረን አንድ ጌታ፣ አንድ እምነትና አንዲት ጥምቀት እንዳለ ሳታወላውሉ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


218 በሕይወታችሁ ውስጥ ያለውን እምነት ጠብቁ

ታምናላችሁን? በእርግጥም እዚህ ያለን ሁላችን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል


ስለምናምን ይህንኑ እናምናለን፡፡

በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ማመንና እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስም


ይህንን እምነት መጠበቅ አለብን፡፡

ዛሬ ጳውሎስ ያስተማረንን እምነት ለማሰላሰል የተወሰነ ጊዜ ወስደናል፡፡


ከዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ ሐዋርያው ጳውሎስ ከውሃውና ከመንፈሱ ወንጌል
በቀር ምንም ነገር እንዳልሰበከ በግልጥ ማየት እንችላለን፡፡ የውሃውና የመንፈሱ
ወንጌል የኢየሱስን ጥምቀትና የመስቀል ላይ ደሙን ያውጃል፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ
የእግዚአብሄርን ቃል የሰበከው በዚህ የውሃና የመንፈስ ወንጌል ላይ ተመስርቶ
ነው፡፡ የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ኢየሱስ ለየግላችን የሰጠን የደህንነት እውነት
ነው፡፡ ኢየሱስ ራሱ ማንም ሰው ከውሃና ከመንፈስ ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር
እንኳንስ ሊገባበት ቀርቶ የእግዚአብሄርን መንግሥትም ሊያይ እንደማይችል
ተናግሮዋል፡፡ (ዮሐንስ 3፡5)
ስለዚህ ጌታ ያስተማረን የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል የእግዚአብሄር ቃል
እንደሆነ አይካድም፡፡ ታዲያ ሰው በዚህ በእውነተኛው የውሃውና የመንፈሱ
ወንጌል ሳያምን እንዴት የሐጢያቶችን ስርየት ሊቀበል እንደሚችል ይናገራል?
በዓለም ዙሪያ 1.5 ቢሊዮን ክርስቲያኖች እንዳሉ ብንገምት ከእነርሱ
1,499,990,000 በላይ የሚሆኑት የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ሳያስተውሉ
በኢየሱስ የሚያምኑ ናቸው፡፡ እነዚህ የተሳሳቱ ክርስቲያኖች የውሃውንና የመንፈሱን
ወንጌል ስለማያውቁ ከሐጢያቶቻቸው እንዳልዳኑ የታወቀ ነው፡፡ ይህንን
የምናገረው ጉባኤያችን የተለየ ስለሆነ ሳይሆን እግዚአብሄር ራሱ ሰው ወደ
መንግሥቱ የሚገባው ከውሃና ከመንፈስ ዳግመኛ ሲወለድ ብቻ እንደሆነ ስለተናገረ
ነው፡፡ ይህንን የደህንነት ሕግ ለዘመኑ ክርስቲያኖች እያዋልሁት ነው፡፡ በትክክል
የዳኑትን ሰዎች በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል እውነተኛ እምነት ሳይኖራቸው
የጌታን ስም ከሚጠሩትና በኢየሱስ እንደሚያምኑ ከሚናገሩት በጣም ብዙ የስም
ክርስቲያኖች መለየት የምንችለው የደህንነትን ሕግ በተጨባጭ ተግባራዊ ስናደርግ
ብቻ ነው፡፡ ጌታ ራሱ ‹‹የተጠሩ ብዙዎች የተመረጡ ግን ጥቂቶች ናቸው›› (ማቴዎስ
22፡14) ብሎዋል፡፡ ይህ ማለት ማንም ሰው በኢየሱስ ማመን ቢችልም ማንም ሰው
የእርሱን ስም በመጥራት ብቻ ደህንነትን ሊያገኝ አይችልም ማለት ነው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በሕይወታችሁ ውስጥ ያለውን እምነት ጠብቁ 219

እግዚአብሄር በማን በኩል መረጠን? ኢየሱስ ክርስቶስ ከሐጢያቶቻችን ሁሉ


እንዴት አዳነን? ያዳነን በውሃውና በደሙ አማካይነት ነው፡፡ በስብከቴ መጀመሪያ
ላይ የነገርኋችሁ የኮስታሪካው ሰው በኢሜሉ እንደተከራከረው ኢየሱስ ጨለማ
በወረደበትና ለሦስት ሰዓታት ያህል በተረሳበት የመስቀል ላይ ሞቱ ቀደም ብሎ
የዓለምን ሐጢያቶች ተሸከመ ማለት ትክክል ነውን? አይደለም፤ ያ ፈጽሞ ትክክል
አይደለም፡፡
አሁንም ገና በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ካላመናችሁ አሁንም ቢሆን በዚህ
ወንጌል በሙሉ ልባችሁ እንድታምኑ እጠይቃችኋለሁ፡፡ በዚህ ወንጌል ሰላምን
ማጣጣም የምትችሉት ምንም ነገር ቢከሰት እስከ መጨረሻው ድረስ በእርሱ
ስታምኑ፣ ስትጠብቁትና ስትሰብኩት ብቻ ነው፡፡ ብዙ ሰዎች ይህንን ወንጌል
ባያውቁትም ይህ ወንጌል ለሁላችንም እውነተኛ ሰላምን አምጥቶልናል፡፡ ያለ
ውሃውና መንፈሱ ወንጌል እንዴት ይህንን ሰላም ማግኘት ይቻለናል? በዚህ ወንጌል
ካልሆነ በሌላ ስፍራ አንዳች ወንጌል አግኝተናልን? እንዳላኘን የታወቀ ነው!
በተቃራኒው ይህንን ወንጌል ችላ ብትሉና መጠበቅ ቢሳናችሁ የምታጡት
ሰላማችሁን ብቻ እንዳይደለ ነገር ግን በእርግጠኝነት እንደምትረገሙ በግልጥ
መረዳት ይኖርባችኋል፡፡
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ባናምን ወይም ካመንበት በኋላ ይህንን ወንጌል
እስከ መጨረሻው ድረስ መጠበቅ ከተሳነን ሁላችንም የዘላለም ሞት እንደሚጠብቀን
የተረጋገጠ ነው፡፡ በቤተክርስቲያናችን ውስጥ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ላይ
ካረፈው እምነት ውጪ አንዳች ሌላ እምነት የሚያቀነቅን ሰው ብናይ በፍጹም ችላ
ልንለው የማይገባን ለዚህ ነው፡፡ ለእያንዳንዳችን ስንል ይህንን ማድረግ አለብን፡፡
ማናችንም መጥፋት የለብንም፤ ነገር ግን ሁላችንም እስከ መጨረሻው ድረስ
እውነተኛውን እምነታችንን መጠበቅ አለብን፡፡ እንዲህ ያሉ እምነት የለሽ ሰዎችን
በቤተክርስቲያን ውስጥ ከተውናቸው እኛው ራሳችን ሰላማችንን ስለምናጣና
በእርግጠኝነት ስለምንጠፋ ነው፡፡ እዚህ ላይ አንድ ሰው ተነስቶ ‹‹ፈጽሞ ያዳነን
በመስቀል ላይ በመሞት ስለሆነ የኢየሱስ ጥምቀት ያን ያህል አስፈላጊ አይደለም››
ቢለን ምን ይፈጠራል? ሰላማችን አይደፈርስምን? በእርግጥም ይደፈርሳል! ሁላችንም
እንደምናውቀው ኢየሱስ በመስቀል ላይ ደሙን ያፈሰሰው አስቀድሞ ስለተጠመቀ
ነው፡፡ ስለዚህ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ፈጽመው ሳያውቁ የማይረባ ነገር
የሚናገሩትን እነዚህን ሰዎች ችላ ብንላቸው በዚህ ምክንያት በርካታ ሰዎች ጥፋት
ውስጥ ይወድቃሉ፡፡ የዚህ ቸልተኝነት ውጤቶችም እየገደላችሁ ቢሆንም እንኳን ያለ
ጥንቃቄ መጠጣትና ማጨስ ብትቀጥሉ የሚገጥሙዋችሁን ውጤቶች ያህል

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


220 በሕይወታችሁ ውስጥ ያለውን እምነት ጠብቁ

ሊተነበዩና ሊያወድሙ የሚችሉ ናቸው፡፡


አጋር ምዕመናኖቼ አሁን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ላይ ያላችሁን እምነት
መጠበቃችሁ ምን ያህል በእጅጉ አስፈላጊ እንደሆነ በበቂ ሁኔታ ትኩረት
አላደረጋችሁበትም፡፡ እምነታችሁን የምትጠብቁት ለሌላ ለማንም ሰው ብላችሁ
ሳይሆን ለራሳችሁ ብላችሁ ነው፡፡ ሌሎች ነፍሳቶችን መርዳት የምትችሉትም ይህንን
በማድረግ ነው፡፡ የእግዘአብሄርን ጽድቅ ማገልገል የምትችሉት በዚህ መንገድ ነው፡፡
አሁን የያዛችሁትን ትክክለኛ እምነት መጠበቃችሁ በእጅጉ አስፈላጊ ነው፡፡ በሌላ
አባባል በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ላይ ያላችሁእምነነታችሁን መጠበቅ
አለባችሁ፡፡ ኤሳው ለአንድ ድስት የምስር ወጥ ሲል ብኩርናውን እንደሸጠ አሁን
የያዛችሁትን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል የምትንቁ ከሆነ መጨረሻችሁ
የእግዚአብሄርን በረከቶች ሁሉ ማጣት ይሆናል፡፡ ያን ጊዜ እንደ ኤሳው ‹‹እኔ በኩርና
የመጀመሪያ ልጅ ስለሆንሁ የአባቴን ሐብት ሁሉ መውረሱ የብኩርና መብቴ ነው፡፡
ነገር ግን አንድ ድስት የምስር ወጥ ብትሰጠኝ ሁሉንም ለአንተ እሰጥሃለሁ››
ትላላችሁን? ኤሳው ከአደን በተመለሰ ጊዘ በጣም ተርቦ ስለነበር የሚያስበው ስለ
ምግብ ብቻ ነበር፡፡ ወደ ቤቱ ሲመለስም ታናሽ ወንድሙ ያዕቆብ የምስር ወጥ
ሲቀቅል አየ፡፡ ኤሳው ልክ እንደተራበ እንስሳ አለከለከ፡፡ ለአንዲት ድስት የምስር
ወጥ ሲልም ብኩርናውን ሸጠ፡፡ ወጡን ጠጣ፡፡ ብኩርናውንም እንደማትረባ ነገር
ቆጠራት፡፡ ቀጥሎ ምን እንደተፈጠረ ሁላችሁም እንደምታውቁ እርግጠኛ ነኝ፡፡
በዚህ ምክንያት ኤሳው በረከቶቹን በሙሉ ለያዕቆብ አስረከበ፡፡ ኤሳው ብኩርናውን
በመናቁ እንደተረገመ ሁሉ እናንተም ደግሞ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
ብትንቁና ብትተዉት የእግዚአብሄርን እርግማን ሁሉ እንጂ አንዳች ሌላ ነገር
አትቀበሉም፡፡
እኛ እግዚአብሄር በሰጠው የውሃና የመንፈስ ወንጌል ስለምናምን የአብን
በረከቶች ሁሉና ሥልጣኑን ሁሉ መውረስ እንችላለን፡፡ እምነትንም ደግሞ መውረስ
እንችላለን፡፡ እውነቱ ይህ ሆኖ ሳለ ብኩርናችንን ልክ እንደ ኤሳው በአንድ ድስት
የምስር ወጥ ሸጠን ቢሆን ኖሮ እንዴት ያለ ሞኝነት በሆነ ነበር? የሆነ ሰው በአንዳች
ዓለማዊ ሴቶች ስለፈተነን ብቻ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል፣ የሰላም ማሰሪያ
የሆነውን የመንፈስ አንድነት በጭራሽ ልንተወው አንችልም፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ
እንዳደረገው ማህበራዊ ዕሴቶችን በሙሉ እንደ ተራ ጉድፍ በመቁጠር አሁንም
ይህንን ወንጌል እየሰበክን ያለነው ለዚህ ነው፡፡ በልቦቻችን ውስጥ ያለውንም ክቡር
መዝገብ በጭራሽ ልንተወው አንችልም፡፡
እንደገና በአንድ ዳግመኛ መደራጀት ውስጥ ልናልፍና አንዳንድ ለውጦች

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በሕይወታችሁ ውስጥ ያለውን እምነት ጠብቁ 221

ልናደርግ ተዘጋጅተናል፡፡ ነገር ግን እነዚህ ለውጦች ቢኖሩም ወንጌልን ማገልገል


እንቀጥላለን፡፡ ጌታ በአደራ የሰጠንን ሐላፊነት ለመፈጸም የሚቻለንን ሁሉ ማድረግ
ይኖርብናል፡፡ ይህንን ለማድረግም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን እርስ
በርሳችን መተባበር አለብን፡፡ ስለዚህ ከውሃውና ከመንፈሱ ወንጌል ውጪ አንዳች
ሌላ ነገር በማስተማር የእግዚአብሄር ቅዱሳን እንዲሰናከሉ የሚያደርገውን
ማንኛውንም ሰው መታገስ አንችልም፡፡ በመካከላችን እንደዚህ ያሉ ሰዎች ካሉ
ሁሉም ሰው እንዲያይ ስህተታቸውን መጠቆምና ወንጌልንም ከብልሽት መከላከል
ይገባናል፡፡
ዝም እንድል ሊያስገድደኝ የሚሞክር ሰው ቢኖርም እንኳን እውነቱ ሊቆም
አይችልም፡፡ በእኔ ላይ ምንም ነገር ቢደርስም ጉባኤያችን የውሃውንና የመንፈሱን
ወንጌል ያለ ማቋረጥ መስበኩን ይቀጥላል፡፡ ስለዚህ ሐሰትና ስህተት የሆነውን ነገር
ሁሉ ድምጼን ከፍ አድርጌ ለማውገዝ ቆርጫለሁ፡፡ ያዕቆብ ሰማዕት ከሆነ በኋላ
በኢየሩሳሌም ባለች ቤተክርስቲያን ውስጥ ይበልጥ የላቀ የወንጌል ነበልባል
እንደተቀጣጠለ ሁሉ ችግሮችና መከራዎች ቢገጥሙንም እምነታችንም ይበልጥ
እንደሚበረታና ወንጌልም ይበልጥ በድንቅ እንደሚሰራ አምናለሁ፡፡ ስለዚህ
ሁላችንም እግዚአብሄርን እናመስግን፡፡ የውሃውንና የመንፈሱንም ወንጌል እስከ
መጨረሻው ድረስ እንጠብቅ፡፡ በአንዱ የጋራ እምነታችን ተባብረንም የወንጌልን
ሥራ በታማኝነት እናከናውን፡፡ 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


222 በሕይወታችሁ ውስጥ ያለውን እምነት ጠብቁ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ስብከት
12

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት
ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
እንደተወደዱ ልጆች
እግዚአብሄርን ምሰሉ
‹‹ ኤፌሶን 5፡1-2 ››
‹‹እንግዲህ እንደተወደዱ ልጆች እግዚአብሄርን የምትከተሉ ሁኑ፡፡ ክርስቶስ
ደግሞ እንደወደዳችሁ ለእግዚአብሄርም የመዓዛ ሽታ የሚሆንን መባንና
መሥዋዕትን አድርጎ ስለ እናንተ ራሱን አሳልፎ እንደሰጠ በፍቅር ተመላለሱ፡፡››

የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን የክርስቶስ አካል ናት፡፡

ሐዋርያው ጳውሎስ በዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ላይ እንዲህ አለ፡-


‹‹እንግዲህ እንደተወደዱ ልጆች እግዚአብሄርን የምትከተሉ ሁኑ፡፡ ክርስቶስ ደግሞ
እንደወደዳችሁ ለእግዚአብሄርም የመዓዛ ሽታ የሚሆንን መባንና መሥዋዕትን
አድርጎ ስለ እናንተ ራሱን አሳልፎ እንደሰጠ በፍቅር ተመላለሱ፡፡›› (ኤፌሶን 5፡1-2)
እዚህ ላይ ጳውሎስ እያስተማረን ያለው ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ እኛ ራሱን መስዋዕት
እንዳደረገ ሁሉ ቅዱሳኖቻችን፣ አገልጋዮቻችንና አጋር ሠራተኞቻችን በሙሉ
በእግዚአብሄር ፍቅር ሊመላለሱ እንደሚገባ ነው፡፡ ይህ በእጅጉ የሚጠቅመን
ትምህርት ነው፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ ቀደም ብሎ በኤፌሶን 4፡16 ላይ እንዲህ ብሎዋል፡-
‹‹ከእርሱም የተነሳ አካል ሁሉ እያንዳንዱ ክፍል በልክ እንደሚሰራ በተሰጠለት
በጅማት ሁሉ እየተጋጠመና እየተያያዘ ራሱን በፍቅር ለማነጽ አካሉን ያሳድጋል፡፡››
ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ራስ ነው፡፡ ቤተክርስቲያንም
የክርስቶስ አካል ናት፡፡ ይህንን ለማብራራት የራሳችሁን አካል ተመልከቱት፡፡
እንቅስቃሴንና ጉልበትን የሚሰጡዋችሁ በርካታ መጋጠሚያዎች፣ አጥንቶችና
ጡንቻዎች ያሉት ከመሆኑም በላይ ከጭንቅላታችሁ እስከ እግር ጥፍራችሁ ድረስ
መላው አካል ከነርቭ ስርዓት ጋር ተያይዞዋል፡፡ ስለዚህ አንጎላችሁ ትዕዛዝ
በሚያስተላልፍበት ጊዜ እንዴት መንቀሳቀስ እንዳለበትና ምን ማድረግ
እንደሚገባው ለማሳወቅ በአከርካሪ አጥንት በኩል አልፎ ወደ እያንዳንዱ የአካል

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


226 እንደተወደዱ ልጆች እግዚአብሄርን ምሰሉ

ብልት ይደርሳል፡፡ ልክ እንደዚሁ ጌታ የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ራስ ሆኖ


ሲያዝዘን እያንዳንዱ የቤተክርስቲያን አባል ጌታ እንዳዘዘው ማድረግ አለበት፡፡ ጌታ
የእግዚአብሄርን ቤተክርቲያን አስመልክቶ ቅዱሳን ‹‹በጅማት ሁሉ እየተጋጠሙና
እየተያያዙ›› (ኤፌሶን 4፡16) እንደሚቀጥሉ የተናገረው ለዚህ ነው፡፡
ስለዚህ የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን አባሎች በሙሉ እርስ በርሳቸው
የሚፈላለጉ ናቸው፡፡ ከጣታችሁ አንዲት መጋጠሚያ እንኳን ብትበጠስ ጥቅም
አልባ ይሆናል፡፡ ጣታችሁን ከእጃችሁ ጋር የሚያያይዝ ማጋጠሚያ መኖር አለበት፡፡
እጃችሁም ከክንዳችሁ ጋር መያያዝ አለበት፡፡ ክንዶቻችሁም ከትከሻችሁ ጋር
መያያዝ አለባቸው፡፡ ስለዚህ የማያስፈልግ አንድም የአካል ክፍል የለም፡፡ ነገር ግን
እያንዳንዱ ክፍል ከአካላችሁ ጋር በሚገባ መያያዝ አለበት፡፡ የራሱን ድርሻ
የሚያከናውነው እያንዳንዱ ብልት መላውን አካላችሁን ለማበጀት አንድ ላይ
ይቆራኛል፡፡

ልክ እንደዚሁ ቅዱሳኖች በሙሉ እርስ በርሳቸው ተፈላላጊዎች ናቸው፡፡

በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ አባላቶቹ በሙሉ በተመደቡባቸው


ቦታዎች ሆነው የሥራ ድርሻቸውን ማከናወን ይኖርባቸዋል፡፡ እግዚአብሄር
በክርስቶስ ላይ እውነተኛ እምነት ሊኖረን እንደሚገባና በፍቅር እንድንመላለስ
የነገረን ለዚህ ነው፡፡ በእርግጥ ከሙሉ ልባችን እርስ በርሳችን የምንዋደድ ከሆነና
ኢየሱስ ከሐጢያቶቻችንና ከበደሎቻችን ሁሉ ያዳነን አዳኛችን እንደሆነ በእርግጥ
የምናምን ከሆነ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ላይ ባለን የጋራ እምነታችን አንድ
ሆነናል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ‹‹አንድ ጌታ፣ አንድ ሃይማኖት፣ አንዲት ጥምቀት የሁሉ
አባት የሆነ አንድ እግዚአብሄር›› (ኤፌሶን 4፡5-6) መኖሩን እንደተናገረ ሁሉ
ሁላችንም በአንድ አምላክ እናምናለን፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስ በውሃ፣ በደምና በመንፈስ አገልግሎቱ አማካይነት
ከሐጢያቶቻችን ሁሉ እንዳዳነን በማመን አንድ የእግዚአብሄር አካል ሆነናል፡፡
በእርግጥ የእግዚአብሄር ሕዝቦችና አንድ ቤተሰብ ከሆንን ሁላችንም በፍቅር
እንመላለሳለን፡፡ እርስ በርስ ከመጎዳዳት ይልቅም እርስ በርስ ለመተናነጽ
እንሞክራለን፡፡ ራስ የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስንም ለማገልገል ጉልበታችንን
እናሰባስባለን፡፡ በዚህ መልኩ በሕይወታችን ውስጥ እውነተኛውን ወንጌል
ለማገልገል እርስ በርሳችን ለመዋደድ ከወሰነን ምንም ዓይነት ችግር አይገጥመንም፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


እንደተወደዱ ልጆች እግዚአብሄርን ምሰሉ 227

በአንጻሩ ስለ ግላዊ ማንነታችን ብቻ ለማሰብ ራስ ወዳድነት ውስጥ ከገባን ትልቅ


መንፈሳዊ ችግር ይገጥመናል፡፡
ታዲያ ይህንን ለማስወገድ ምን ማድረግ ይገባናል? እኛ ማድረግ የሚኖርብን
ነገር ቢኖር እርስ በርሳችን መረዳዳትና እግዚአብሄር ለእንዳንዳችን የመደበልንን
ተግባር በእምነታችን መሠረት በታማኝነት መስራት ነው፡፡ ምንም ይሁን ሁላችንም
ሕይወታችንን ለክርስቶስ አሳልፈን በመስጠት ለውሃውና ለመንፈሱ ወንጌል
መሰራጨትና እግዚአብሄርን ለሚያስደስተው ሥራ መኖር ይገባናል፡፡ ሁላችንም
እንዲህ ስንተባበርና የእግዚአብሄርን የጽድቅ ሥራ በሕብረት ስንሰራ እርስ በርሳችን
እንበረታታለን፡፡ እግዚአብሄርም በአደራ የሰጠንን ተግባራቶች በሙሉ በታማኝነት
እንፈጽማለን፡፡

ጌታ በፍቅር እንድንመላለስ አዞናል፡፡

እግዚአብሄር ያሳየን ፍቅር በእጅጉ ግሩም ነው፡፡ በሰዎች መካከል ያለውም


ፍቅር እንደዚሁ መልካም ነው፡፡ ወደ ሰብዓዊ ግንኙነታችንን ስንመጣም እንኳን
እርስ በርስ ከመጠላላትና ከመመቀኛነት ይልቅ እርስ በርሳችን ብንዋደድ የተሻለ
ነው፡፡ ማናችንም ብቻችንን የእግዚአብሄርን ወንጌል ለማስፋፋት መኖር
ስለማንችል ሁላችንም በአንድ ላይ ጉልበታችንን ልናቀናጅ የሚገባን መሆኑ
አስፈላጊ ነው፡፡ እርሱን ለማገልገል ጉልበታችንን በአንድ ላይ ብናስተባብር በጌታ
ፊት ውብ ነው፡፡ እንዲህ ተብሎ ተጽፎዋልና፡-
‹‹ወንድሞች በሕብረት ቢቀመጡ እነሆ መልካም ነው፤ እነሆም ያማረ
ነው፡፡›› (መዝሙረ ዳዊት 133፡1)
ነገር ግን በመካከላችን ያለ ውዴታቸው የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
የሚያገለግሉ አንዳንድ ሰዎች አሉ፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል፡- ‹‹እግዚአብሄር
በደስታ የሚሰጠው ይወዳልና፤ እያንንዱ በልቡ እንዳሰበ ይስጥ፤ በሐዘን ወይም
በግድ አይደለም፡፡›› (2ኛ ቆሮንቶስ 9፡7) እኛ የጌታን ሥራ እየሰራን ነው፡፡
ምክንያቱም እርሱ ሁላችንም እንድናደርግ ያዘዘን ይህንን ነውና፡፡ ነገር ግን እርሱን
ልናገለግል የሚገባን ከሐላፊነት ስሜት የተነሳ ሳይሆን ጽድቁን በሙሉ ልቦቻችን
እያመንን ከምስጋና በሚፈልቅ ውዴታ ነው፡፡ ምክንያቱም ጌታ እኛን
ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ለማዳን ወደዚህ ምድር በመጣ ጊዜ በአጥማቂው ዮሐንስ
ተጠምቋል፡፡ ለእኛ ሲልም ሥጋውን በመስቀል ላይ አሳልፎ ሰጥቷል፡፡ ጌታ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


228 እንደተወደዱ ልጆች እግዚአብሄርን ምሰሉ

ከሐጢያቶቻችን ሁሉ እንዳዳነን ሁሉ ሌሎችም ደግሞ ከሐጢያቶቻቸው ይድኑ


ዘንድ በሕይወታችን ውስጥ እርሱን በእምነት ልናገለግለው ይገባናል፡፡ የጌታን ሥራ
በተጨባጭ መስራት ማለት ይህ ነው፡፡
ጌታ ወንጌልን በፍቅር እንድናገለግል አዞናል፡፡ በፍቅር መመለለስ የምትፈልጉ
ከሆናችሁ ሕይወታችሁን ለእግዚአብሄር አሳልፋችሁ መስጠት አለባችሁ፡፡
እነርሱም ደግሞ ለእግዚአብሄር ይኖሩ ዘንድ ሌሎችንም ደግሞ በጥንቃቄ መምራት
አለባችሁ፡፡ አንድ የቤተክርስቲያን መሪ የሚያገለገለው የጉባኤውን ቁሳዊ ስኬት
ለማረጋገጥ ብቻ ከሆነ የዚህ መሪ አገልግሎት እንዳለ ከንቱ ነው፡፡ ስለዚህ
እያንዳንዱ መሪ ቅዱሳኖችን ወደ ትክክለኛው መንፈሳዊ መንገድ መምራትና
ከእነርሱም ጋር ሕብረትን በመጋራት በተገቢው ሁኔታ ለእግዚአብሄር እንዲኖሩ
ማድረግ አለበት፡፡
አካል በሙሉ ራስ ያዘዘውን ማድረግ አለበት፡፡ ጉልበታችንን በአንድ ላይ
ለእግዚአብሄር ብናስተባብር፣ እርሱን ብናገለግልና በየመክሊታችን ሕይወታችንን
ለእርሱ ቀድሰን ብንሰጥ ያን ጊዜ እግዚአብሄር ሁላችንንም እንደሚባርከንና
እንደሚጠብቀን የተረጋገጠ ነው፡፡ ሁላችንም የእርሱን ፈቃድ በመታዘዝ
በእግዚአብሄር ትዕዛዛቶች መሠረት መኖር ያለብን ለዚህ ነው፡፡ የእግዚአብሄር ቃል
በፍቅር እንድንመላለስ ያዘናል፡፡ በዚህ ቃል መሠረት መኖር የምንችለው
በእግዚአብሄር ጽድቅ ላይ እውነተኛ እምነት ያለን ሰዎች ብቻ ነን፡፡ ይህ ሊሆን
የሚችለውም በእግዚአብሄር ስንኖር ብቻ ነው፡፡ ኢየሱስ የወይን ግንድ ነው፤ እኛም
ቅርንጫፎች ነን፡፡ በወይኑ ግንድ ላይ ያሉት ቅርንጫፎች ፍሬ ማፍራት እንደሚችሉ
ሁሉ በፍቅር መመላለስና ሕይወታቸውን ለእርሱ መቀደስ የሚችሉት እግዚአብሄር
የሚታመኑና እርሱን የሚከተሉ ብቻ ናቸው፡፡ ስለዚህ የእምነት ቀደምቶቻችሁ
እየመሩዋችሁና በዚህ ፍቅር ከእናንተ ጋር ሕብረትን የሚካፈሉ ከሆኑ ይህንን እንደ
ትልቅ በረከት ልትቆጥሩት ይባችኋል፡፡
ነገር ግን ራሳቸውን ክርስቲያኖች ብለው ቢጠሩም የስጋን ነገሮች የሚከተሉ
ብዙ ሰዎችች አሉ፡፡ እግዚአብሄር በገላትያ 5፡19 ላይ እንዲህ አለ፡- ‹‹የሥጋ ሥራም
የተገለጠ ነው፡፡›› ከዚያም ሁሉንም ዓይነት ሐጢያቶች ይዘረዝራል፡፡ ክርስቲያኖች
ኑፋቄ ውስጥ የሚገቡት የስጋን መሻቶች ሲከተሉ ነው፡፡ በአንጻሩ እኛ በትክክል
በእግዚአብሄር ፍቅር ብንመላለስ የስጋን ነገሮች በፍጹም አንከተልም፡፡ ነገር ግን
በስጋችን ላይ ምንም ነገር ቢከሰት ሁሌም የእግዚአብሄርን ፈቃድ እንከተላለን፡፡
በእግዚአብሄር ፍቅር መመላለስ ማለት የእግዚአብሄርን ፈቃድ መከተል፣
በችሮታውም እርስ በርሳችን ሕብረትን መካፈል፣ ፈቃዱንም ለመታዘዝ እርስ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


እንደተወደዱ ልጆች እግዚአብሄርን ምሰሉ 229

በርሳችን መመራት፣ ጌታን ለማገልገልም ጉልበቶቻችንን በአንድ ላይ ማቀናጀትና


ለዚህ ሥራ መጸለይ ነው፡፡

በእግዚአብሄር ፈቃድ መሠረት መኖር በእጅጉ ይጠቅማችኋል፡፡

ኤፌሶን 5፡1 እንዲህ ይላል፡- ‹‹እንግዲህ እንደተወደዱ ልጆች እግዚአብሄርን


የምትከተሉ ሁኑ፡፡›› ኢየሱስ ክርስቶስ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ለመደምሰስና አዲስ
ሕይወትን ለመስጠት ራሱን ለእኛ መስዋዕት እንዳደረገ ሁሉ እውነተኛ
እግዚአብሄርን መሳዮች በፍቅር እርስ በርሳቸው ሕብረትን ይካፈላሉ፡፡ አንዱ
ሌላውን ይመራል፡፡ በሕይወታቸው ውስጥም አብረው ያገለግሉ ዘንድ እርስ
በርሳቸው ይበረታታሉ፡፡ ስለዚህ ከቅዱሳን ጋር ሕብረትን በምትካፈሉበት ጊዜ ሁሉ
በስጋዊ ጉዳዮች ላይ ብቻ የምትመክሩዋቸው ከሆነ ያ በፍጹም መልካም
አይደለም፡፡ መልካም ሕብረት ለእግዚአብሄር መኖር እንድትችሉ መንፈሳዊ
ምሪትን የሚሰጣችሁ ነው፡፡ በዚህ መልኩ የሚመላለሱ ሰዎች በእግዚአብሄር ፍቅር
የሚመላለሱ ናቸው፡፡ የእምነት ቀደምቶቻችሁ በመንፈሳዊ ሕይወታችሁ
እየመሩዋችሁ ያለው እንዴት ነው? ስጋዊ ጉዳዮችን ብቻ እንድትከተሉ ከመምራት
ይልቅ ከእናንተ ጋር ሕብረትን የሚጋሩና እግዚአብሄርን በታማኝነት እንድትከተሉ
የሚመሩዋችሁ እንዲህ ያሉ መሪዎች አሉዋችሁ? እንዲህ ያሉ መሪዎች ካሉዋችሁ
ቃላት ሊገልጠው ከሚችለው በላይ የተባረካችሁ እንደሆናችሁ ራሳችሁን
ልትቆጥሩ ይገባል፡፡
ስጋዊ ጉዳዮችን ለመከተል መሻት መሠረታዊ የሆነ ሰብዓዊ ተፈጥሮዋችን
ነው፡፡ ብቻችንን ከተተውን ሁላችንም ስጋን እንከተላለን፡፡ ከዚህ በተጨማሪም
ሰይጣን ሁሌም ዓለማዊ ጉዳዮችን እንድንከተል ሊያነሳሳን ይሞክራል፡፡ በእርሱ
ፈተና ውስጥ ብንወድቅ ምን ይፈጠራል? የመጨረሻው ውጤት ልክ እንደ ጀምበር
መፈንጠቅ የታወቀ ነው፡፡ የሁላችንም መጨረሻ ጥፋት ይሆናል፡፡ የገዛ ስጋውን
ለመከተል ሲል ከእግዚአብሄር የሚርቅ ማንኛውም ሰው በመጨረሻ በእርግጠኝነት
ይጠፋል፡፡ ስጋን ለመከተል ሲል እግዚአብሄርን የሚተው ሰው ሁሉ ይረገማል፡፡
እንዲህ የተረገመ ማንኛውም ሰው ደግሞ በመጨረሻ ከበረከቶች ሁሉ ይታገዳል፡፡
ከእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ጋር ያላችሁ ግንኑኘት ከተቋረጠ ከራሱ
ከእግዚአብሄር ጋር ያላችሁ ግንኙነትም እንደዚሁ ያከትማል፡፡
ኢየሱስ እንዲህ ብሎናል፡- ‹‹እኔ የወይን ግንድ ነኝ፤ እናንተም ቅርንጫፎች

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


230 እንደተወደዱ ልጆች እግዚአብሄርን ምሰሉ

ናችሁ፡፡›› (ዮሐንስ 15፡5) እርሱ የቤተክርስቲያን ራስና እኛም የዕርሱ አካል


እንደሆንን ተናግሮዋል፡፡ ስለዚህ ከቤተክርስቲየን ከወጣን ወዲያውኑ እንጠፋለን፡፡
ምክንያቱም ዳግመኛ የእርስዋ ምሪት አይኖረንምና፡፡ ከአጋር ሠራተኞቻችን አንዱ
ዴድ ማን ዎኪን (ሙት ሰው ሲራመድ) ስለሚለው ፊልም ነገረን፡፡ ይህ ፊልም
የሚያሳየው አንዲት መነኩሲት ተፈርዶበት ሞት ይጠባበቅ የነበረ አንድ እስረኛ
በቅርቡ ከሚሆነው ግድያው ጋር አንዲስማማ ልትረዳው ስትፍጨረጨር ነው፡፡
አጋር ሠራተኛችን ይህንን ፊልም እንደ ምሳሌ የተጠቀመው በእውነተኛው የውሃና
የመንፈስ ወንጌል በማመን ገና ዳግመኛ ያልተወለደ ሰው ሁሉ በእርግጥም ‹‹ሙት
ሰው ሆኖ እየተራመደ›› መሆኑን በመጠቆም መንፈሳዊ ሞት የተቃረባቸውን የጠፉ
ነፍሳቶች ለማሳወቅ ነው፡፡
በሚፈልገው በማንኛውም መንገድ መኖር የሚፈልግ ሰው በአግዚአብሄር
ፊት ቀድሞውኑም ሙታን ነው፡፡ ክንድ ከአካል ተቆርጦ ሲወድቅ ለጊዜው
ይንፈራገጣል፡፡ ነገር ግን ይህ ክንድ ስለሚንፈራገጥ ብቻ በእርግጥ ሕያው ነውን?
አይደለም፡፡ ቀድሞውኑም ሞቷል፡፡ ልክ እንደዚሁ ከእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን
የራቀና ከኢየሱስ ክርስቶስ የተለየ ሰው በመጀመሪያ ላይ በእምነት ለመኖር
ቢሞክርም ይህ ሰው በመጨረሻ ይጠፋል፡፡ ምክንያቱም ከእግዚአብሄር
ቤተክርስቲያን ተቆርጦዋል፡፡ ዳግመኛም የቤተክርስቲያን ምሪት የለውም፡፡
እግዚአብሄርን እንድትከተሉና እንድታገለግሉ የሚመራችሁ ሰው እንዳላችሁ
ወይም እንደሌላችሁ በጥንቃቄ ማጤን በጣም ያስፈልጋችኋል፡፡ የቤተክርስቲያን
መሪዎቻችሁና የእምነት ቀደምቶቻችሁ እነርሱን ሳይሆን እግዚአብሄርን
እንድታገለግሉ እያስተማሩዋችሁ እንደሆነ ወይም እንዳልሆነ ራሳችሁን መጠየቅ
አለባችሁ፡፡ የቤተክርስቲያን መሪዎቻችሁ አንዳንዴ ጌታን አንድ ጊዜ እንድታገለግሉ
ይመክሩዋችሁ ይሆናል፡፡ ነገር ግን በትክክል ከእናንተ የሚፈልጉት ነገር እነርሱን
እንድትከተሉና እንድታገለግሉ ከሆነ ልትንቁዋቸው ይገባል፡፡ ከቅርንጫፍ
ቤተክርስቲያኖቻችን በአንዱ ልክ እንደዚህ ያደረገ አንድ አገልጋይ ነበር፡፡ ይህ
መጋቢ ቅዱሳን ለቤተክርስቲያናችን የገንዘብ ድጎማዎችን ለማድረግ በሚፈልጉበት
ጊዜ ሁሉ በጣም ይበሳጭ ነበር፡፡ ስጦታዎች በሙሉ ወደ እርሱ ቤተክርስቲያን
እንዲጎርፉ ይመርጥ ነበር፡፡ የእርሱ ቤተክርስቲያን አባሎችም ለግሉ መጠቀሚያ
የሚሆኑ ስጦታዎችን ወይም ገንዘብ እንዲሰጡት ይወድ ነበር፡፡ ይህ ሰው
በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ አገልጋይ ከመሆን ይልቅ ደመወዝተኛ ነበር፡፡
የእግዚአብሄርን ቤተክርስቲያን የሚያስተዳድሩ አገልጋዮችም እንኳን
የቤተክርስቲያንን ገንዘብ ተገቢ መስሎ በሚታያቸው በማናቸውም መንገድ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


እንደተወደዱ ልጆች እግዚአብሄርን ምሰሉ 231

ሊጠቀሙበት አይችሉም፡፡ ይልቁንም ገንዘቡን ለመጠቀም የተሻለው መንገድ ምን


እንደሆነ ሁሌም እግዚአብሄርን መጠየቅ አለባቸው፡፡
አንዳንድ ጊዜ የእኔ የልደት ቀን ሲደርስ ከአንዳንድ ወንድሞቻችንና
እህቶቻችን የገንዘብ ስጦታዎችን እቀበላለሁ፡፡ በጣምም እደሰትበታለሁ፡፡ ገንዘብ
ሲያገኝ የማይደሰት ማን አለ? ነገር ግን አስፈላጊው ነገር ይህ ገንዘብ የሚውልበት
ሁኔታ ነው፡፡ ‹‹ይህ የልደት ቀኔ ነው፤ ስለዚህ ገንዘብ ስጡኝ!›› ብዬ ባዛችሁ ኖሮ
ትልቅ ስህተት ይሆን እንደነበር ግልጥ ነው፡፡ ገንዘብ በሚያስፈልገኝ ጊዜ ሁሉ ለምን
ገንዘብ አንደፈለግሁ ለቤተክርስቲያኒቱ ገንዘብ ያዥ ለማብራራት አላመነታም፡፡
ገንዘቡን የማውለው የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለማገልገል ብቻ ሰለሆነ
ሕሊናዬ ሁሌም ንጹህ ነው፡፡ ነገር ግን ስጦታዎቻችሁን ብሰበስብና ለራሴ ብቻ
ብጠቀምባቸው ኖሮ ይህ ከባድ ችግር ይሆን ነበር፡፡

ጌታ በፍቅር እንድንመላለስ አዞናል፡፡

እግዚአብሄርን ታገለግሉ ዘንድ የሚመራችሁና ከእናንተ ጋር ሕብረት


የሚያደርግ አንድ ሰው ካላችሁ፣ በጭራሽ ከቤተክርስቲያን እንዳትርቁ
በምትባዝኑበት ጊዜ የሚገስጻችሁና ሁሌም አጥብቆ የሚይዛችሁ አንድ ሰው
ካላችሁ ይህ ሰው በእርግጥም የሚወዳችሁ ሰው ነው፡፡ ይህ ሰው ሊጎዳችሁ የመጣ
አይደለም፤ ነገር ግን በተጨባጭ የሚወዳችሁ ሰው ነው፡፡
ጌታ ለሁላችንም በግልጥ ‹‹በፍቅር ተመላለሱ›› (ኤፌሶን 5፡2) ብሎናል፡፡
ይህንን ትዕዛዝ በመታዘዝ በፍቅር የምትመላለሱ ከሆናችሁ ከእግዚአብሄር ጋር
ያላችሁን ሰላም ታስጠበቃላችሁ፡፡ ከእርሱ ጋር ትነጋገራላችሁ፡፡ በእርሱም ደግሞ
ትባረካላችሁ፡፡ አስቀድመን የእግዚአብሄርን ፍቅር ስለለበስን እርሱን የምንመስል
መሆን አለብን፡፡ እዚህ ላይ ሐዋርያው ጳውሎስ ‹‹እንደተወደዱ ልጆች
እግዚአብሄርን የምትከተሉ ሁኑ›› (ኤፌሶን 5፡1) እንዳለ ሌሎችንም ደግሞ መውደድ
አለብን፡፡ አብረውን ያሉት ቅዱሳን በትክክለኛው ጎዳና ላይ እንድንሆን ሲመክሩን
ልናዳምጣቸውና ምክራቸውን ልንከተል ይገባናል፡፡
ይኸው መጠይቅ እኔንም ደግሞ ይመለከታል፡፡ አገልጋዮቻችን ለእኔ የሚሆን
አንዳች ምክር ሲኖራቸው በጥንቃቄ አዳምጣቸዋለሁ፡፡ ምክራቸው አሳማኝ ከሆነም
እስማማለሁ፡፡ አገልጋዮቻችን በተሳሳተው አስተሳሰቤ ውስጥ ያለውን አንዳች
ትክክል ያልሆነ ነገር ይጠቁሙኛል፡፡ አስተያየታቸውን ሲያካፍሉኝ በንቃት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


232 እንደተወደዱ ልጆች እግዚአብሄርን ምሰሉ

አዳምጣቸዋለሁ፡፡ ልሳሳት እንደምችል እገነዘባለሁ፡፡ ስለዚህ አሳቦቻቸውን


እንዲነግሩኝ እጠይቃቸዋለሁ፡፡ በጥንቃቄም አዳምጣቸዋለሁ፡፡ ጥቆማቸው
ትክክል ከሆነ ያለ ምንም ማመንታት እቀበለዋለሁ፡፡ ያ የእግዚአብሄር ጥበብ ነው፡፡
እነዚህ ውይይቶች የሚደረጉት ለራስ ወዳድ ምክንያቶች ሳይሆን ለእግዚአብሄር
ሲባል ስለሆነ ኩራቴ ተጎዳ የሚል ስሜት ሊኖረኝ አያስፈልግም፡፡ ነገር ግን እጅግ
ተስማሚና ምርጥ የሆነ መንገድን ለማግኘት መልካሙን ምክር መቀበል ብቻ ነው፡፡
ይኸው መርህ እናንተንም ደግሞ ይመለከታል፡፡ ለእግዚአብሄር ትኖሩ ዘንድ
አንድ ሰው ከእናንተ ጋር ሕብረትን በሚካፈልበት ጊዜ ሁሉ ይህንን ምክር በእምነት
ልትቀበሉት ይገባል፡፡ ወዲያውኑ ለመቀበል ደካሞች ብትሆኑም እንኳን በልባችሁ
ውስጥ ከተቀበላችሁትና እምነትም ከበቀለ በኋላ ውሎ አድሮ ምክሩን
የምትከተሉበት ጉልበት ይኖራችኋል፡፡ በዚህ መልኩ አብረዋችሁ ያሉትን ቅዱሳኖች
ምክር በእምነት ስትቀበሉ በእግዚአብሄር ትባረካላችሁ፡፡ ስለዚህ ከእግዚአብሄር
እስከሆነ ድረስ አብረዋችሁ ያሉትን ቅዱሳን ምክር እንደትቀበሉ እጠይቃችኋለሁ፡፡
ምክሩ ከእግዚአብሄር ከሆነ ጌታ እንድትከተሉት ያበረታችኋል፡፡ ስለዚህ ሐይልን
በሚሰጠን በክርስቶስ ሁሉን እንችላለን፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ እንደ እርሱ
የተወደዱ ልጆች ሆነን እግዚአብሄርን እንድንመስል የመከረን ለዚህ ነው፡፡
ይህንን ፍቅር ለእነርሱ ልናካፍላቸው የምንችለው ከሌሎች በፊት
የእግዚአብሄርን ፍቅር በመቀበላችን አይደለምን? ሌላውን ሰው ሁሉ የምንወድደው
እናንተና እኔ አስቀድመን የእግዚአብሄርን ፍቅር በመልበሳችን መሆኑ ግልጥ ነው፡፡
ይህንን የእግዚአብሄር ፍቅር ባንለብስም እንኳን እርስ በርሳችን እንዋደዳለን?
እንደማንዋደድ የታወቀ ነው! እርስ በርሳችን የምንከፋፈለው ፍቅር የክርስቶስ ፍቅር
ነው፡፡ ያዳነን ክርስቶስ ነው፡፡ እርስ በርሳችን ሕብረትን የምንካፈለውም እንደዚሁ
በክርስቶስ አማካይነት ነው፡፡ ይህ ሁሉ የሚደረገውም ለክርስቶስ ሲባል ነው፡፡
በፍቅር የምንመላለሰው ለእኛ ስንል ብቻ አይደለም፡፡ ነገር ግን ለሌሎችና
ለክርስቶስም ስንል ነው፡፡ ስለዚህ ሐዋርያው ጳውሎስ በዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ
ምንባብ ላይ የመከረንን በጥንቃቄ ማድመጥ ጠቃሚያችን ነው፡፡
ጌታ የክርስቶስ አካል ራስዋን በእግዚአብሄር ፍቅር እንደምታንጽ
ተናግሮዋል፡፡ (ኤፌሶን 4፡16) በእግዚአብሄር ላይ ባለን እምነታችን መኖር እርስ
በርስ መተማመንና እግዚአብሄር በሰጠን ፍቅር በአንድነት መተባበር ማለት
የክርስቶስን አካል በትክክል ማነጽና ጌታን መከተልና ማገልገል ማለት ነው፡፡
እናንተና እኔ ለእያንዳንዳችን በአደራ የተሰጠንን የተለየ ሥራ እያከናወንን ነው፡፡
ይህም የሚደረገው ክርስቶስን ለመመስል ነው፡፡ ምክንያቱም የእግዚአብሄርን ፍቅር

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


እንደተወደዱ ልጆች እግዚአብሄርን ምሰሉ 233

ለብሰናልና፡፡
እያንዳንዱ ክርስቲያን ከላይ የሚመጡትን ትዕዛዛቶች ማለትም እግዚአብሄር
የተናገረውን ቃል መታዘዝ አለበት፡፡ እግዚአብሄር ራሱን ለእኛ ገልጦዋል ማለት
ቃሉን ከፍቶ በቃሉ አማካይነት ፈቃዱን አሳይቶናል ማለት ነው፡፡ እግዚአብሄር
ፈቃዱን ያሳየውና የገለጠው በቃሉ አማካይነት ነው፡፡ የክርስቲያን እምነት ይህንን
ቃል ማድመጥ ከቃሉ ውስጥም የእግዚአብሄርን ፈቃድና የሚደሰትበትን ነገር
መረዳትና ቃሉን እየታዘዘ መመላለስ ነው፡፡ በአንጻሩ ዓለማዊ ሐይማኖቶች ሰው
የሰራውን አምላክ ስለ ማምለክ የሚናገሩ ናቸው፡፡
እናንተስ ታዲያ? እግዚአብሄርን የምትመስሉ ናችሁን? በእግዚአብሄር ፍቅር
እየተመላለሳችሁ ነውን? ሁላችንም በእግዚአብሄር ፍቅር መመላለስ አለብን፡፡ ቁሳዊ
ነገርን በሚመለከት የምንሰጠው ብዙ ነገር ባይኖርም በእውነተኛ ፍቅር
እየተመላለስን ነው ማለትም እርስ በርሳችን በመንፈሳዊ ሁኔታ እየተረዳዳን ነው፡፡
በተጨባጭ እየጎዱዋቸው እያሉ ሌሎችን እየረዱ እንደሆኑ የሚናገሩ በርካታ ሰዎች
አሉ፡፡ በአንጻሩ እኛ ሌሎችን ከልባችን እንወዳቸዋለን፡፡ ይህንን የምናደርገው
ለራሳችን ስንል ሳይሆን ለክርስቶስ ኢየሱስ ስንል ነው፡፡ ለእኛ በእግዚአብሄር ፍቅር
መመላለስ ማለት ሌሎች ክርስቶስን እንዲከተሉና የእግዚአብሄርን በረከቶች
እንዲቀበሉ መርዳት ነው፡፡
ፍቅርን የተናገረ ማነው? እግዚአብሄር ነው፡፡ በዚህ ዓለም ላይ ፍቅርን
መናገርና መተግበር የሚችል ሰው ካለ ይቅርብ፡፡ ሰው እንዴት እውነተኛ ፍቅርን
ማብራራት ይችላል? እውነተኛ ፍቅር የእግዚአብሄር ፍቅር ነው፡፡ የእግዚአብሄር
ፍቅር ስለ እኛ ሲል ራሱን መስዋዕት በማድረግ የተሰጠን እውነተኛ ፍቅር ነው፡፡
በእርግጥ በእግዚአብሄር ፍቅር እየተመላለስን ነውን? እርስ በርሳችን ሕብረት
የምንካፈለው እንዴት ነው? ከእናንተ ጋር ሕብረትን የሚካፈሉት ሰዎች ያንን
የሚያደርጉት ለክርስቶስ እንድትኖሩ ሊረዱዋችሁ ነው? እንዲህ ዓይነት ሕብረት
የሚጋሩ ሰዎች ካሉዋችሁ ምን ያህል ልታመሰግኑዋቸው እንደሚገባችሁ
ታውቃላችሁን? አብረዋችሁ ያሉ ወንድሞቻችሁና እህቶቻችሁ ቢሆኑ ወይም
የእግዚአብሄር አገልጋዮች ለእግዚአብሄር እንድትኖሩ ሊረዱዋችሁ ሕብረታቸውን
የሚጋሩትን ሁሉ ልታመሰግኑዋቸው ይገባችኋል፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


234 እንደተወደዱ ልጆች እግዚአብሄርን ምሰሉ

የደገፈን በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ የተካፈልነው የበለጠገ


ሕብረት ነው፡፡

ጉባኤያችን አነስተኛ ብትሆንም በኮርያና ከዚያ ውጪ ባሉ ቅርንጫፍ


ቤተክርስቲያኖቻችን በሙሉ እርስ በርሳቸው እየተረዳዱና እየተናነጹ እንደሆኑ
እርግጠኛ ነኝ፡፡ ብቻችንን ልንቀር ከተበታተንን ምንም አይደለንም፡፡ ስለዳናችሁ
ብቻ ከቤተክርስቲያን ውጪ ሆናችሁ የምትፈልጉትን አንዳች ነገር ማድረግ
የምትችሉ ይመስላችኋልን? የለም፤ ከቤተክርስቲያን ውጪ ሰይጣን ወዲያውኑ
ይውጣችኋል፡፡
ዲያብሎስ በቅዱሳን ላይ መንፈሳዊ ጥፋትን ማምጣት አያዳግተውም፡፡
እንዲያውም ነፍስን ማጥፋት ለሰይጣን በጣም ቀላል ነው፡፡ ዲያብሎስ ማድረግ
የሚኖርበት ነገር ቢኖር ስብከት ሲሰበክ መርዝ መጨመር ብቻ ነው፡፡ ይህንን
የተመረዘ ስብከት ከዋጣችሁ በኋላ ወዲያውኑ ትጠፋላችሁ፡፡ የሚመረዘው ምግብ
ብቻ አይደለም፡፡ መርዝ በተወሰኑ አስተሳሰቦች ውስጥ ብቻ የሚገኝ አይደለም፡፡
የእግዚአብሄርን ቃል በተሳሳተ መንገድ በመጥቀስ ስብከትም እንኳን ሊመረዝ
ይችላል፡፡ የእግዚአብሄር ቃል ከተመረዘ ጻድቃን በሙሉ በእርግጠኝነት ይጠፋሉ፡፡
ዙሪያችሁን ተመልከቱና ቤተክርስቲያን ውስጥ እንድትቆዩና ጌታን
በታማኝነት እንድትከተሉ በፍቅር የሚያስተምሩዋችሁ፣ ወደ ትክክለኛው መንገድ
የሚመሩዋችሁና ሕብረታቸውን ከእናንተ ጋር የሚካፈሉ አጋር የቤተክርስቲያን
አባሎች እንዳሉ እዩ፡፡ በዙሪያችሁ እንዲህ ያሉ አጋር ቅዱሳኖች በመኖራቸውም
አመስጋኞች ሁኑ፡፡ እንዲህ ያሉ ተንከባካቢ የቤተክርስቲያን አባሎች የመኖራቸው
እውነታ በሚገባ አመስጋኞች እንድትሆኑ ሊያደርጋችሁ ይገባል፡፡
ወንድም ሊ በቅርቡ ለውትድርና በመመልመሉ ምክንያት ከእኛ ጋር
አይደለም፡፡ ወንድም ሊ በመሄዱ አሁን ምን ይሰማችኋል? ከእንግዲህ ወዲህ ከእኛ
ጋር ሕብረትን መካፈል ስለማይችል በውትድርና ሕይወቱ አስቸጋሪ ጊዜ
የሚገጥመው አይመስላችሁምን? አብረውት ካሉት ወታደሮች ጋር ጓደኝነት
እንደሚመሰርት የታወቀ ነው፡፡ ነገር ግን እነርሱ የሚያወሩለት ስለ ዓለማዊ ጉዳዮች
ብቻ ነው፡፡ ወንድም ሊ በልቡ ውስጥ ያለውን ከማንኛውም ሰው ጋር መካፈል
አይቻለውም፡፡ ምክንያቱም በዚያ ዳግመኛ የተወለዱ ቅዱሳን የሉምና፡፡ ልቡ
እስከሚረካ ድረስ ከእኛ ጋር መንፈሳዊ ንግግሮችን መጋራት በሚፈለግበት ጊዜ ሁሉ
በእጅጉ ይናፈቀን ይሆናል፡፡
እኛ ልብ ለልብ ሕብረትን መካፈል የምንችለው የሐጢያቶችን ስርየት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


እንደተወደዱ ልጆች እግዚአብሄርን ምሰሉ 235

ከተቀበልን በኋላ በዚያው ልብ በቤተክርስቲያን ውስጥ በመቆየታችን ነው፡፡


ልቦቻችንን እርስ በርስ መጋራት ከመቻላችን የሚበልጥ በጣም ድንቅ ነገር ሊኖር
አይችልም፡፡ ስለዚህ እናንተ በፍቅር መጣመር፣ በፍቅር መመላለስ፣ በፍቅር ጌታን
መከተልና በፍቅር እርሱን መምሰል አለብን፡፡ ክርስቶስ እኛን ለማዳን ራሱን
መስዋዕት እንዳደረገ ሁሉ ሁላችንም ደግሞ እርስ በርሳችን መረዳዳትና መተናነጽ
ይገባናል፡፡
በዕብራውያን 13፡9 ላይ እንዲህ ተጽፎዋል፡- ‹‹ልባችሁ በጸጋ ቢጸና መልካም
ነው እንጂ በመብል አይደለም፡፡ በዚህ የሚሠሩባት አልተጠቀሙምና፡፡›› ይህ
ምንባብ እንደሚያስተምረን እርስ በርሳችን በመልካም ሥራዎች ወይም ቁሳዊ
ነገሮች አማካይነት ለመተናነጽ ከመሞከር ይልቅ የእናንተና የእኔ ልብ እግዚአብሄር
በለገሰን እውነተኛ ጸጋ ሊበረታ ይገባዋል፡፡ በእግዚአብሄር ፍቅርና እርሱ ባመጣልን
ደህንነት በማመን ልቦቻችንን ማጸናት አለብን፡፡
የሚጠብቀን፣ የሚመራንና የሚከላከልልን እግዚአብሄር ነው፡፡ በራሱ
ቤተክርስቲያን ውስጥ ያስቀመጠን፣ እርሱን እንድናገለግል ያደረገንና ለጌታ እንኖር
ዘንድ በቤተክርስቲያኑ ውስጥ እንድንበረታ የባረከን እግዚአብሄር ነው፡፡ ይህ
አምላክ በበረከቶቹ እንድንበረታ ነግሮናል፡፡ ስለዚህ ሁላችንም በእምነት
እንበርታ፡፡ ሁላችንም በእግዚአብሄር ፍቅር እንመላለስ፡፡ በእምነትም በእርሱ
እንኑር፡፡ 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


236 እንደተወደዱ ልጆች እግዚአብሄርን ምሰሉ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ስብከት
13

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት
ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
በዓለም ሐጢያቶች ውስጥ
ተካፋዮች አትሁኑ
‹‹ ኤፌሶን 5፡1-14 ››
‹‹እንግዲህ እንደተወደዱ ልጆች እግዚአብሄርን የምትከተሉ ሁኑ፡፡
ክርስቶስም ደግሞ እንደወደዳችሁ ለእግዚአብሄርም የመዓዛ ሽታ የሚሆንን መባንና
መሥዋዕትን አድርጎ ስለ እናንተ ራሱን አሳልፎ እንደሰጠ በፍቅር ተመላለሱ፡፡
ለቅዱሳን እንደሚገባ ግን ዝሙትና ርኩሰት ሁሉ ወይም መመኘት በእናንተ ዘንድ
ከቶ አይሰማ፡፡ የሚያሳፍር ነገርም፣ የስንፍና ንግግርም ወይም ዋዛ የማይገቡ
ናቸውና አይሁኑ፤ ይልቁንም ምሥጋና እንጂ፡፡ ይህን እወቁ፤ አመንዘራም ቢሆን
ወይም ርኩስ ወይም የሚመኝ እርሱም ጣዖትን የሚያመልክ በክርስቶስና
በእግዚአብሄር መንግሥት ውስጥ ርስት የለውም፡፡ ከዚህ የተነሣ በማይታዘዙት
ልጆች ላይ የእግዚአብሄር ቁጣ ይመጣልና፡፡ ማንም በከንቱ ንግግር አያታልላችሁ፡፡
እንግዲህ ከእነርሱ ጋር ተካፋዮች አትሁኑ፡፡ ቀድሞ ጨለማ ነበራችሁና፤ አሁን ግን
በጌታ ብርሃን ናችሁ፡፡ የብርሃኑ ፍሬ በበጎነትና በጽድቅ በእውነትም ሁሉ ነውና፡፡
ለጌታ ደስ የሚያሰኘውን እየመረመራችሁ እንደ ብርሃን ልጆች ተመላለሱ፡፡ ፍሬም
ከሌለው ከጨለማ ሥራ ጋር አትተባበሩ፤ ይልቁንም ግለጡት እንጂ፡፡ እነርሱ
በስውር ስለሚያደርጉት መናገር እንኳ ነውር ነውና፡፡ ሁሉ ግን በብርሃን ሲገለጥ
ይታያል፤ የሚታየው ሁሉ ብርሃን ነውና፡፡ ስለዚህ፡- አንተ የምትተኛ ንቃ፤
ከሙታንም ተነሣ፤ ክርስቶስም ያበራልሃል ይላል፡፡››

የዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ ሐዋርያው ጳውሎስ በኤፌሶን ቤተክርስቲያን


ያሉ ቅዱሳኖችን እያገለገለ እንደነበር ያሳያል፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
ዕውቀትና እምነት እንዴት መኖር እንደሚገባቸው፣ ከምን መጠንቀቅ
እንደሚገባቸውና ለምንና እንዴት መኖር እንደሚገባቸው ተናግሮዋል፡፡ በዚያ
ያለውን መንጋ ለመመገብም ጳውሎስ ለኤፌሶን ቅዱሳን እንዲህ አለ፡- ‹‹እንግዲህ
እንደተወደዱ ልጆች እግዚአብሄርን የምትከተሉ ሁኑ፡፡›› (ኤፌሶን 5፡1)

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


240 በዓለም ሐጢያቶች ውስጥ ተካፋዮች አትሁኑ

እንደተወደዱ ልጆች እግዚአብሄርን የምትከተሉ ሁኑ፡፡

ኤፌሶን 5፡1 አጭር ነገር ግን ወሳኝ ምንባብ ነው፡፡ ‹‹እንግዲህ እንደተወደዱ


ልጆች እግዚአብሄርን የምትከተሉ ሁኑ፡፡›› ይህ የሆነበት ምክንያት ይህ ምንባብ
እንዴት መኖር እንደሚገባን በግልጥ ስለሚያሳይ ነው፡፡ እዚህ ላይ እግዚአብሄር
እርሱን እንድንከተል ስለነገረን አስቀድመን እግዚአብሄር በተጨባጭ ማን
እንደሆነና ባህሪያቶቹም ምን እንደሆኑ መመርመር አለብን፡፡
ጌታ በሰማይ የእግዚአብሄር ልጅ ነው፡፡ ኢየሱስ ራሱ አምላክ ቢሆንም
አብዝቶ ስለወደደን በግሉ ወደዚህ ምድር መጥቶ ሕይወቱን ለእኛ አሳልፎ ሰጠ፡፡
እርሱ በዚህ መልኩ ራሱን መስዋዕት በማድረግ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ አስወገደ፡፡
ስለዚህ ጌታ ጻድቃን ያደረገን አዳኛችን ነው፡፡
ከዚህም በላይ ጌታ ያዳነን ከዓለም ሐጢያቶች ብቻ አይደለም፡፡ ነገር ግን
ከሐጢያት ኩነኔና ጥፋትም ደግሞ አድኖናል፡፡ እርሱ ወደዚህ ምድር የመጣው
ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ነጻ ሊያወጣን ነው፡፡ ራሱን ለእግዚአብሄር አብ አሳልፎ
በመስጠትም ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ደመሰሰ፡፡ በዚህ ሁኔታ የሐጢያቶችን ስርየት
ስለተቀበልንና ከጥፋት፣ ከእርግማኖችና ከኩነኔ ስለዳንን ምስጋና ለጌታ ይሁንና
አሁን የእግዚአብሄር ልጆች ሆነናል፡፡ የእግዚአብሄር ልጆች የሚደሰቱበትንም
መንፈሳዊ በረከቶች በሙሉ ተቀብለናል፡፡ በአጭሩ ጌታ የእግዚአብሄር ልጆች
አድርጎ የተቀበለን በሰማያዊ ስፍራዎች ያሉትን በረከቶች ሁሉ እንድንቀበልና
እንድናጣጥም ነው፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ በኤፌሶን ቤተክርስቲያን ላሉ ቅዱሳኖች የተናገረው
ይታወስ፡፡ እግዚአብሄርን መከተል እንደሚገባቸው ተናግሮዋል፡፡ በሕይወታችን
ጌታን መከተልና እርሱ በዚህ ምድር ላይ ያደረገልንን መምሰል ማለት ምን ማለት
ነው? ይህ የሚያሳየው አንድ ነገርን ነው፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ በሕይወታችን
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል እንድንሰብክ እየመከረን ነው፡፡
ከእኛ በፊት ኢየሱስ ክርስቶስን በመምሰል ለወንጌል ስርጭት ብቻ የኖረ
ቀደምት የእግዚአብሄር አገልጋይ አለ፡፡ ይህ አገልጋይ ሌላ ሳይሆን የዛሬውን
የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ የጻፈልን ሐዋርያው ጳውሎስ ነው፡፡ ይህም የሚያሳየው
ሐዋርያውን ጳውሎስን ብንከተል ራሱን ኢየሱስ ክርስቶስን እንደምንመስል ነው፡፡
ጳውሎስ ሕይወቱን በሙሉ አሳልፎ የሰጠው በዚያን ጊዜ ይታወቅ ለነበረው
ለእያንዳንዱ አገር የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በመስበክ ነው፡፡ ጳውሎስን
ስንከተል ሁላችንም ልቦቻችንንና መሰጠታችንን ሁሉ የውሃውንና የመንፈሱን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በዓለም ሐጢያቶች ውስጥ ተካፋዮች አትሁኑ 241

ወንጌል ቀንና ሌሊት ለማሰራጨት ቀድሰን መስጠት አለብን፡፡


ጌታ ወደዚህ ምድር በመጣ ጊዜ ምን ሊያደርግልን ፈለገ? የእናንተንና የእኔን
ሐጢያቶች በሙሉ ለመደምሰስ ፈለገ፡፡ ታዲያ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ለማስወገድ
ምን አደረገ? እግዚአብሄር ሰማያዊ በረከቶችን ሊሰጠን ራሱን መስዋዕት አደረገ፡፡
ስለዚህ የሐጢያቶችን ስርየት የተቀበልን ሁላችን ይህንን የውሃና የመንፈስ ወንጌል
ገና ከሐጢያቶቻቸው ላልነጹ ሰዎች ለመስበክ ራሳችንን መስዋዕት ማድረግ
አለብን፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ በዚህ ምድር ላይ እያገለገለ ሳለ እምነታቸው ያድግ ዘንድ
መንጋዎቹ ኢየሱስን እንዲመስሉ መክሮዋቸዋል፡፡ በሌላ አነጋገር እዚህ ላይ
ጳውሎስ እያስተማረ ያለው ኢየሱስ ክርስቶስ ከዓለም ሐጢያቶች ሁሉ ስላዳነንና
ራሱን መስዋዕት በማድረግ ሰማያዊ በረከቶችን ስለሰጠን እኛም ደግሞ ሌሎች
ነፍሳቶችን ለማዳን ጌታን መስለን ራሳችንን መስዋዕት ማድረግ አለብን፡፡
አሁን እናንተና እኔ የሐጢያቶችን ስርየት ስለተቀበልን የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል ለማሰራጨት አለመኖራችን ፈጽሞ የተሳሳተ ነው፡፡ እናንተና
እኔ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን በእርግጥ የሐጢያቶችን ስርየት
ተቀብለን ከሆነ ለወንጌል መኖር ተገቢ ነው፡፡ እኛ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
የምናምን አማኞች የእግዚአብሄርን ጸጋና ፍቅር በነጻ ስለተቀበልን ይህንን የደህንነት
ወንጌል፣ ይህንን እውነተኛ ወንጌል ለማያውቁ ሁሉ በነጻ መስጠት ይገባናል፡፡
በእርግጥ ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ድነን ከሆነ ሕይወታችንን ለዚህ ውጥን ማዋሉ
ተፈጥሮአዊ ጥሪያችን ነው፡፡

የዚህን የተበላሸ ዓለም ሰዎች ዱካዎች መከተል የለብንም፡፡

ሐዋርያው ጳውሎስ በአፌሶን ቤተክርስቲያን ላሉ ቅዱሳኖችና ለእም ደግሞ


የሚከተሉትን ቃሎች ተናግሮዋል፡፡ ‹‹ለቅዱሳን እንደሚገባ ግን ዝሙትና ርኩሰት
ሁሉ ወይም መመኘት በእናንተ ዘንድ ከቶ አይሰማ፡፡ የሚያሳፍር ነገርም፣ የስንፍና
ንግግርም ወይም ዋዛ የማይገቡ ናቸውና አይሁኑ፤ ይልቁንም ምሥጋና እንጂ፡፡››
(ኤፌሶን 5፡3-4) ሐዋርያው ጳውሎስ በዚህ ምንባብ አማካይነት ዝሙት
እንዳናደርግ ወይም አንዳች ነገር እንዳንመኝ ይመክረናል፡፡ ይህ ባህርይ ገና
ከሐጢያቶቻቸው ካልነጹ ሐጢያተኞች የሚጠበቅ ነው፡፡ ስለዚህ እኛ የዳንን ሰዎች
ከዚህ መራቃችን ተገቢ ነው፡፡ ነገር ግን በጳውሎስ ዘመን የእግዚአብሄር ሕዝብ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


242 በዓለም ሐጢያቶች ውስጥ ተካፋዮች አትሁኑ

በሆኑት መካከል እንኳን እነዚህን ሐጢያቶች የሰሩ አንዳንድ ቅዱሳን ነበሩ፡፡ ስለዚህ
ጳውሎስ በዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ላይ ቀድሞውኑም በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል ስለምናምን ማናችንም ገና ዳግመኛ ያልተወለዱ ሰዎች
በሚሰሩዋቸው ሐጢያቶች ውስጥ ተካፋዮች መሆን እንደሌለብን ይመክረናል፡፡
እኛ ቅዱሳኖች የዓለም ሰዎች እንደሚኖሩት ላለመኖራችን በየትም ቦታ
የተሰጠ ዋስትና እንደሌለ የታወቀ ነው፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ብናምንም
እንኳን ስጋዊ ተፈጥሮዋችን አሁንም አለ፡፡ ስለዚህ ልክ እንደ ዓለም ሰዎች መኖር
ይቻላል፡፡ ነገር ግን እንዲህ ለመኖር በምትፈተኑበት ጊዜ ሁሉ እግዚአብሄር በዛሬው
የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ውስጥ ምን እንዳላችሁ ልታስታውሱ ይገባል፡፡
‹‹ዝሙትና ርኩሰት ሁሉ ወይም መመኘት በእናንተ ዘንድ ከቶ አይሰማ፡፡›› (ኤፌሶን
5፡3)
ይህ ምንባብ እነዚህን ሐጢያቶች አለመስራታችን ምን ያህል አስፈላጊ
እንደሆነ በግልጥ አሳይቶናል፡፡ በጣም የረከሱ በመሆናቸው እግዚአብሄር
በመካከላችን እንኳን እንዳይሰሙ ነግሮናል፡፡ ገና ከመጀመሪያው ጥንቃቄያችን
ፈጽሞ እንዲወድቅ መፍቀድ እንደሌለብን፣ ሁሌም ከእነዚህ ሐጢያቶች
እንድንጠነቀቅ፣ ራሳችንን ከእነርሱ እንድናርቅና ስማቸውንም እንኳን እንዳንጠራ
ይመክረናል፡፡ በሌላ አነጋገር እግዚአብሄር በቸልተኝነት በጥቂቱም እንኳን ወደ
እነዚህ ሐጢያቶች ለመሳብ ከፈቀድን መጨረሻችን እነርሱን መፈጸም እንደሚሆን
እያስጠነቀቀን ነው፡፡
ይህንን ምንባብ በመንፈሳዊ መልኩ ማጤንና መረዳት በጣሙን
ያስፈልገናል፡፡ አሁን ሁላችንም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ባናምንም አንዳንድ
ጊዜ ልቅ የጾታ ግንኙነቶችን ወደሚያሳዩ ምስሎችና ፊልሞች እንደዚሁም ወደ
ዝሙት ነገሮች እናሳባለን፡፡ ለእነዚህ ፍትወታዊ መሻቶችና ፈተናዎች በግድየለሽነት
ከተሸነፍን ጣዖት አምልኮን እንፈጽማለን፡፡
ወደ ብሉይ ኪዳን ስንመለስ ኢዮርብዓም የተባለ ንጉሥ እስራኤልን ጣዖት
አምላኪ ሕዝብ አድርጎ እንደለወጣቸው እናያለን፡፡ ይህ ሰው በሕይወቱ
የፈለጋቸው ሦስት ነገሮች ብቻ ነበሩ፡፡ እነርሱም ዝና፣ ሥልጣንና ጾታዊ ልቅነት
ነበሩ፡፡ የመሳሳቱ ውጤት ምን ነበር? በመጀመሪያ እግዚአብሄርን ራሱ በሰራቸው
የወርቅ ጥጆች ተካው፡፡ እነዚህንም የወርቅ ጥጆች በእግዚአብሄር መቅደስ ውስጥ
እስከማኖር፣ በፊታቸው እስከ መንበርከክና ለሕዝቡም ከግብጽ ባርነት ነጻ
ያወጡዋቸው እነዚህ የወርቅ ጥጆች እንደሆኑ እስከ ማስተማር ድረስ ርቆ ሄደ፡፡
ኢዮርብዓም የእግዚአብሄርን ሕግ ተወ፡፡ እንዲህ በማድረጉም ራሱ እግዚአብሄር

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በዓለም ሐጢያቶች ውስጥ ተካፋዮች አትሁኑ 243

የነበረው ዝናና ሥልጣን ላይ ለመድረስ ፈለገ፡፡ ደስ እንዳሰኘውም ከሁሉም ዓይነት


አህዛብ ሴቶች ጋር ተጋደመ፡፡
ይህ የኢዮርብዓም ታሪክ ዛሬ ለእኛ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ለምናምን
ሰዎች ምን ያስተምረናል? ዝሙትን የሚፈጽም ሁሉ ከእግዚአብሄር መንግሥት ጋር
ምንም ግንኙነት እንደሌለውና እነዚህ ሰዎችም በብሉይ ኪዳን ጌታ አምላክን
በወርቅ ጥጆች ከተካው ከኢዮርብዓም ጋር ተመሳሳይ ሰዎች እንደሆኑ
ያስተምረናል፡፡
ይህ የአሁኑ ዓለም በሐጢያቶች የተሞላ እንደሆነ አሳምሬ ባውቅም በአሁኑ
ጊዜ እየተሰሩ ያሉትን የሐጢያት ዓይነቶች ሙሉ በሙሉ አላውቃቸውም፡፡ ስለዚህ
በቅርቡ በዓለም ላይ የበዙት የሐጢያት ዓይነቶች ምን እንደሆኑ ለማወቅ በምዕራብ
አውሮፓ ከሚገኙ ወንጌላውያኖቻችን አንዱን በአገሩ ያለው ሁኔታ ምን እንደሆነ
ያብራራልኝ ዘንድ ጠየቅሁት፡፡ ሲመልሰልኝም በአገሩ ምን ዓይነት ክፉ ነገሮች
እየተሰሩ እንደሆነ በስፋት ጻፈልኝ፡፡ ይህንን ደብዳቤ አብሬያችሁ ልካፈል
እወዳለሁ፡፡ ይህ ወንጌላዊ የሚከተለውን ጻፈልን፡፡
‹‹ውድ መጋቢ ይህ ይረዳሃል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ እዚህ ላይ
የጻፍሁዋቸው ብዙዎቹ ነገሮች በአንዳንድ የአውሮፓ አገሮች ተቀባይነት
የላቸውም፡፡ ነገር ግን ከሕዝቡ ዕይታ ውጪ እስከተፈጸሙ ድረስ ማንኛውም ነገር
ይደረጋል፡፡ በተለይም በዚህ በሆላንድ ሐጢያቶችን የሚቃወም ሕግ የለም ማለት
ይቻላል፡፡
ግብረ ሰዶማዊነት በግልጥ ይደፋፈራል፡፡ ተባዕታይ ግብረ ሰዶማውያንና
እንስታውያን ሰዶማውያን በይፋ ይጋባሉ፡፡ ቤተክርስቲያኖችም ለጋብቻዎቻቸው
ቡራኬ ለመስጠት መንገድ አግኝተዋል፡፡ በአገሪቱ ሕግ ፊት በሕጋዊ መንገድ
ስለተጋቡም መጽሐፍ ቅዱስ ካህናቶች ጋብቻውን እንዲባርክ እግዚአብሄርን
መጠየቅ እንደሚችሉ ይናገራል፡፡
በአሁኑ ጊዜ የደች መንግሥት በፓርቲ አመራሩ ውስጥ ግብረ
ሰዶማውያኖችን ባቀፈ የክርስቲያን ፓርቲ ይመራል፡፡ መንግሥትም እንደዚሁ
በቤተክርስቲያኖች ውስጥ የሚደረጉ ነገሮች በሚደረጉበት መንገድ ላይ የመናገር
መብት አለው፡፡ ቤተክርስቲያኖች ምን ማድረግ ወይም ምን አለማድረግ
እንደተፈቀደላቸውና ምን መናገርና ምን አለመናገርም እንደተፈቀደላቸው
ይወስናል፡፡ ተባዕታይ ግብረ ሰዶማውያንና እንስታይ ጥንዶች ልጆችን በጉዲፈቻ
እንዲያሳድጉ ተፈቅዶላቸዋል፡፡
ሴተኛ አዳሪነት ሕጋዊ ነው፡፡ ሴተኛ አዳሪዎችም ግብሮቻቸውን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


244 በዓለም ሐጢያቶች ውስጥ ተካፋዮች አትሁኑ

እንዲሞሉላቸው የሚያግዙዋቸው የሒሳብ ሠራተኞች አሉዋቸው፡፡ መንግሥት


ከገቢ ግብሮቻቸው የሚቀበለው ገንዘብም ለመሬት ክፍያ፣ ለሥነ ትምህርት፣
ለሆስፒታሎችና ለመሳሰሉት ያግዝ ዘንድ ወደ መንግሥት ካዝና ይገባል፡፡
በመንግሥት ድርጅቶች ውስጥ የሚሰሩ ሰዎችን ክፍያ ለመክፈልም ደግሞ ያግዛል፡፡
ከእንስሶች ጋር የሚደረግም የግብረ ሥጋ ግንኙነትም ሕጋዊ ነው፡፡ ሕገ ወጥ
የሚሆነው በእንስሳው ላይ ጉዳት ከደረሰበት ብቻ ነው፡፡ በአምስተርዳም፣ በዴን
ሃግና በሮተርዳም ይህ የሚደረግባቸው ጥቂት ስፍራዎች አሉ፡፡ የግብረ ሥጋ
ግንኙነቱን ድርጊት ፎቶዎች በኢንተርኔት (በይነ መረብ) ላይ ማኖርም እንደዚሁ
ሕገ ወጥ ነው፡፡
አደንዛዥ ዕጾችም ሕጋዊ ናቸው፡፡ አደንዛዥ ዕጾች የሚሸጡባቸው ቡና
መጠጫ መደብሮችም እንደዚሁ የገቢ ግብሮችን ወደ ካዝናው ያስገባሉ፡፡ በሆላንድ
ቡና መጠጫ መደብር የሌለበት ከተማ ወይም መንደር አለ ብዬ አላስብም፡፡ እዚህ
ያሉ ልጆች 12 ዓመት ሲሆናቸው ሱሰኞች ይሆናሉ፡፡ የአልኮል መጠጥ ሕጎችም
እንደዚሁ ተመሳሳይ ናቸው፡፡ በጣም ብዙ የልጅ ሰካራሞች አሉ፡፡
ውርጃ ሕጋዊ ነው፡፡ ሆላንድ ባላት መርከብ በጣም ትኮራለች፡፡ መርከቡ
ውርጃ በተከለከሉባቸው አገሮች ላሉ ሰዎች የውርጃዎች አገልግሎቶችን በመስጠት
ዓለምን ይዞራል፡፡ መርከቡ ከዓለም አቀፍ ውሃዎች ገደብ አስራ ሁለት ማይል ያህል
ከውጪ ይቆማል፡፡ በዚያም ውርጃዎችን ይፈጽማሉ፡፡ ይህም ደግሞ የሚደጎመው
መንግሥት ከሰበሰባቸው ግብሮች ነው፡፡ ይህ ሐጢያት እዚህ በሆላንድ ድጋፍ
ተሰጥቶታል፡፡
ልቅ የጾታ ግንኙነትን የሚያሳይ ፎቶም ሕጋዊ ነው፡፡ ለካዝናው ከፍተኛ
ገንዘብ የሚያስገባ ነው፡፡
ምህረታዊ ግድያም ሕጋዊ ነው፡፡ ሴት ልጄ ክላውዲያ በምትሰራበት ስፍራ
በምህረት ግድያ መርፌዎችን እንድትወጋ ተጠይቃ ነበር፤ በእምነትዋ ምክንያት
እምቢተኛ ሆነች፡፡ ነገር ግን በእምነትዋ ምክንያት ዋጋ ከፍላለች፡፡ በነርሲንግ
ሥራዋ እንድትቀጥል አልተፈቀደላትም፡፡
ትክክለኛ ጋብቻዎች የሚደረጉት በአካባቢ ባሉ የመንግሥት የከተማ
አዳራሾች ውስጥ ነው፡፡ ጥንዶቹ የሚገጥማቸው የመጀመሪያው ነገር ለፍቺ የሚሆኑ
ሕጋዊ ሒደቶች ናቸው፡፡ ፍቺን ለመቃወም ዋስትና ማግኘት ይቻል ዘንድም
የኢንሹራንስ ኩባንያ አለ፡፡ እዚህ ጥንዶች ያለ ጋብቻ እንዲኖሩ በሕጋዊ መንገድ
የሚፈቅድ የጋራ ውል መዋዋል ትችላለህ፡፡ በሚለያዩበት ጊዜ የፍቺ ሒደቶች
አያስፈልጉም፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በዓለም ሐጢያቶች ውስጥ ተካፋዮች አትሁኑ 245

ከሐጢያቶች ሁሉ እጅግ ትልቁ ሐጢያት እነዚህ ሁሉ ሐጢያቶች በአብያተ


ክርስቲያኖች ችላ መባላቸው ነው፡፡ እዚህ ያሉት አብያተ ክርስቲያኖች እነዚህን
ክፋቶች ደፍረው አይቃወሙም፡፡ ሁሉም ነገር ሕጋዊ ስለሆነና የመንግሥት ድጋፍ
ስላለው ከላይ የተነገረውን ማንኛውንም ነገር መቃወም እንደ ማግለል ይመደባል፡፡
እዚህ ማግለል ሕገ ወጥ ነገር ነው፡፡
እነዚህ ሐጢያቶች በጌታ ዘንድ ርኩሰት መሆናቸውን ከእግዚአብሄር ቃል
ለማሳየት ስንሞክር በአግላይነት እንከሰሳለን፡፡ እንዲህ በማድረግም መንግሥት
ተላላፊዋን ቤተክርስቲያን ለመዝጋት የተሰጠው መብት አለው፡፡
ከላይ የተዘረዘሩት ሁሉ እንዲሆኑ ስለተፈቀደ አብያተ ክርስቲያኖች
ተጎንብሰው የአገሪቱን ሕጎች እንዲቀበሉና እነዚህ ሐጢያቶች ወደ ቤተክርስቲያን
ይገቡ ዘንድ እንዲፈቅዱ እየተገደዱ ነው፡፡
ይህ ይረዳሃል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ እግዚአብሄር እነዚያን በፍትወት
የተቃጠሉ ሰዎች እንዴት ወደ ቤተክርስቲያኑ እንዲገቡ እንደፈቀደላቸው ስመለከት
እነዚህ ነገሮች ለእርሱ ርኩሰት መሆናቸውን አውቃለሁ፡፡
አንዳች ተጨማሪ መረጃ የምትፈልግ ከሆነ አሳውቀኝ፡፡
በክርስቶስ
በኔዘርላንድ ያለሁ አጋር ሠራተኛህ፡፡››
ስለዚህ ደብዳቤ ምን ይሰማችኋል? በእኛ አገር ግለሰቦች የጦር መሳርያዎች
ሕጋዊ ቢሆኑ ኖሮ እንዴት ይመስላችኋል? አገራችን ለተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ ሕጋዊ
ዕውቅናን ብትሰጥና አውሬነትን ሕጋዊ ብታደርግ እንዴት ይመስላችኋል?
አብዛኞቻችሁ እንደምትበሳጩ እርግጠኛ ነኝ፡፡
አብዛኞቻችን በአሁኑ ጊዜ እንደ ወንጀል የሚቆጠሩት እነዚህ ሐጢያቶች
ሕጋዊ ቢሆኑ ጥሩ ነው ብለን ልናስብ እንደምንችል የታወቀ ነው፡፡ ሁሉም ሰው
የማሰብ ነጻነት አለው፡፡ ነገር ግን አብዛኞቻችን እነዚህ ሐጢያቶች ሕጋዊ ቢሆኑ
የታፈነው ክፋት በባህሪው ወደ ውጪ ይተነፍስና በዓለም ላይ ተጨማሪ ክፋትን
ያፈልቃል እንላለን፡፡ ተጨማሪ ውዥንብርንም ያመጣል፡፡ ሰዎችም ይበልጥ
ለሐጢያቶቻቸው እንዲደነዝዙ ያደርጋቸዋል፡፡ ወዲያውም የእግዚአብሄር ቃል ወደ
ልቦቻቸው ይገባ ዘንድ አዳጋች ያደርገዋል፡፡
ከጥቂት ቀናት በፊት በአንድ ጋዜጣ ላይ አረጋውያን በሚጎበኙዋቸው
ፓርኮች ውስጥ ራሳቸውን ለሴተኛ አዳሪነት አሳልፈው ስለሰጡ በመካከለኛ ዕድሜ
በ40ዎቹና በ50ዎቹ ስለሚገኙ ሴቶች አነበብሁ፡፡ ደምበኞችን ሲቀርቡ የለስላሳ
መጠጥ ይዘው በመቅረባቸው በመገናኛ ብዙሃን ‹‹ለስላሳ መጠጥ አቅራቢ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


246 በዓለም ሐጢያቶች ውስጥ ተካፋዮች አትሁኑ

አክስቶች›› ተብለው የሚጠሩት እነዚህ ሴቶች የሚያጠምዱት ጊዜ ለማሳለፍ


በፓርክ ውስጥ የሚዘዋወሩትን አረጋውያን ነው፡፡ በሴዑል በሚገኝ አንድ ፓርክ
ውስጥ ብቻ ከ100 በላይ ‹‹ለሰላሳ መጠጥ አቅራቢ አክስቶች›› እንዳሉ ይገመታል፡፡
በኮርያ ሴተኛ አዳሪነት ሕገ ወጥ ቢሆንም በኔዘርላንድ ሕጋዊ ነው፡፡ ነገር ግን
በተጨባጭ ሕጋዊ ሆኑም ወይም አልሆኑ እነዚህ ሐጢያቶች በዓለም ዙሪያ ሁሉ
ተስፋፍተዋል፡፡

ሙሉ በሙሉ ፍትወታችሁን የምትከተሉ ከሆናችሁ እግዚአብሄርን


መምሰል አትችሉም፡፡

ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱን መስዋዕት በማድረግ ከሐጢያቶቻችን ሁሉ


አድኖናል፡፡ እርሱ ጽድቅ የሆነውን የደህንነት ሥራ ከፈጸመ በኋላ አንድ ቀን ወደ
እኛ እንደሚመለስ ተስፋ በመስጠት ወደ መንግሥተ ሰማይ አረገ፡፡ አሁን እኛ
የእርሱ መልዕክተኞች ስለሆንን በዚህ ምድር ላይ የእርሱን ታላቅ ተልዕኮ መታዘዝ
ይኖርብናል፡፡ አሁን የጌታን ሥራ ለመስራት ስለምንሻ እግዚአብሄርን የምንመስል
መሆን አለብን፡፡
እናንተና እኔ ለፍትወታዊ መሻቶቻችን የምንገዛና የእነርሱን አቅጣጫ ብቻ
የምንከተል ከሆንን መጨረሻችን እግዚአብሄርን በወርቅ ጥጆች መተካትና ራሳችንን
ወደ ጣዖት አምላኪዎች መለወጥ ይሆናል፡፡ ይህ ከሆነ ዳግመኛ የተወለዱትም
ቢሆኑ በመጨረሻ ይጠፋሉ፡፡ እኛ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን የዓለም
ብርሃን ሆነን ሳለን ወደ ቀድሞው ሕይወታችን ብንመለስና ወደ ጨለማና ኩነኔ
ብናፈገፍግ እንዴት ያለ አሳዛኝ ነገር ይሆናል? ስለዚህ ሐዋርያው ጳውሎስ ጌታን
ደስ የሚያሰኘውን ማወቅ እንደሚገባን የነገረንን ሁሌም ማስታወስ በእጅጉ
ያስፈልገናል፡፡ (ኤፌሶን 5፡10) ጳውሎስ በቀጣዩ ቁጥር ላይ የመከረንን በልቦቻችን
ውስጥ ማኖር ይገባናል፡፡ ‹‹ፍሬም ከሌለው የጨለማ ሥራ ጋር አትተባበሩ፤ ይልቁን
ግለጡት እንጂ፡፡›› (ኤፌሶን 5፡11)
በዚህ ዓለም ላይ ፈጽሞ እንከን የሌለው ሕይወት መኖር የሚችል ሰው አለ?
እግዚአብሄር በሕጉ ውስጥ አንዳች ሐጢያት እንዳንሰራ ስለነገረን ብቻ በጭራሽ
አንዳች ሐጢያት ሰርቶ የማያውቅ ሰው አለ? ማንም ይህንን ሊያደርግ አይችልም፡፡
ይህ ማለት ሁሉንም ዓይነት ሐጢያቶች እየሰራን በነጻነት መመላለስ እንችላለን
ማለት አይደለም፡፡ እግዚአብሄርን ማገልገል ብናቆምና በምትኩ ርኩስ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በዓለም ሐጢያቶች ውስጥ ተካፋዮች አትሁኑ 247

ፍትወቶችንና ስስትን ብንከተል ምን ይፈጠራል? ከእግዚአብሄር ጸጋ


እንወድቃለን፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ የዛሬውን የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ በጻፈ ጊዜ
ዓለም በበርካታ ሐጢያቶች ተሞልታ ነበር፡፡ ነገር ግን ይህ የአሁኑ ዓለም ከዚያ
ይልቅ በብዙ ክፋት ተሞልቷል፡፡ ስለዚህ እግዚአብሄር በሐዋርያው ጳውሎስ
አማካይነት እየተናገረ ያለው በኤፌሶን ላሉት ቅዱሳን ብቻ ሳይሆን አሁን
በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ ላለነው ለእናንተና ለእኔም ነው፡፡
እኛ የእግዚአብሄር ልጆች የሆንን ሰዎች በዚህ ዓለም ላይ የሚኖረው ሌላው
ሰው እንደሚያደርገው ሐጢያቶችን የምንመኝ ብንሆን ምን ይፈጠራል? ጣዖት
አምላኪዎች እንሆናለን፡፡ ከእግዚአብሄር ከራሱ በላይም ስጋዊ ተድላዎችን
እንወዳለን፡፡ በመጨረሻም ከእግዚአብሄር ርቀን ኩነኔና ጥፋት ይገጥመናል፡፡ ጌታ
በዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ላይ የነገረንን ማስታወስ የሚጠቅመን ለዚህ
ነው፡፡ ሁላችንም እግዚአብሄርን የምንመስል ሰዎች መሆንና ልክ እንዳልዳኑ ሰዎች
ሆነን በጭራሽ የማንመላለስ መሆን አለብን፡፡ እዚህ ላይ ጌታ ለምን እንደዚህ
እንደመከረንና የዚህ ዓለም ሐጢያቶች ተካፋይ እንዳንሆን እንደነገረን መገንዘብ
አለብን፡፡
ማናችንም በዚህ ዓለም ላይ እንዳሉ ሰዎች እንዲህ ባሉ የተዋረዱ ሐጢያቶች
ውስጥ ተካፋይ ልንሆን አይገባንም፡፡ በእኛ መካከል ያሉ ወንዶችና ሴቶች፣
ወጣቶችና ሽማግሌዎች መቼም ቢሆን እነዚሀን ሐጢያቶች መከተል የለባቸውም፡፡
ሁላችንም በቤተክርስቲያናችን ውስጥ የምንኖር ብንሆንም በየቀኑ ከማያምኑ ሰዎች
ጋር መገናኘት ይኖርብናል፡፡ ስለዚህ በዓለም ካሉ ወዳጆቻችንና ጓደኞቻችን
በምናየው ነገር ልንፈተን እንችላለን፡፡ ቢሆንም ለእነዚህ ፈተናዎች መማረክና
በእነርሱ ሐጢያቶች ተካፋይ መሆን አንችልም፡፡ በእነዚህ ሐጢያቶች ውስጥ
ተካፋይ ከሆናችሁና ከሳታችሁ ይበልጥ ለሐጢያት ስሜት አልባ ትሆናላችሁ፡፡
ጭንቅላታችሁና ልባችሁ በጣም ስሜት አልባና ደነዝ ስለሚሆኑ ርኩሰትን እንደ
ርኩሰት አታውቁትም፡፡ ፍትወታችሁን ለማርካት ስትሉ በርኩሰትና በሁሉም
ዓይነት የረከሱ ነገሮች የምትንቦጫረቁ ስሜት አልባ ሰው ትሆኑ ዘንድ በፍጹም
ራሳችሁን መለወጥ አይገባችሁም፡፡ እነዚህን ሐጢያቶች በፍጹም ከዓለም ሕዝብ
ጋር አብራችሁ መስራት አይገባችሁም፡፡
እኔ ይህንን ጥያቄ በመጠየቅ እቀጥላለሁ፡፡ ክርስቲያኖች የዓለም ሰዎች
የሚሰሩዋቸውን ሐጢያቶች ቢካፈሉና በእነርሱ አቅጣጫ ቢባዝኑ ምን ይፈጠር
ነበር? ልቦቻቸው በጣም ስለሚደነድኑና በጣም ስሜት አልባ ስለሚሆኑ ቢገሰጹም
እንኳን ከመመለስ ይልቅ ምን ሐጢያት እንደሰሩና ምን የተሳሳተ ነገር እንዳደረጉ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


248 በዓለም ሐጢያቶች ውስጥ ተካፋዮች አትሁኑ

ያውቁ ዘንድ ያለ ሐፍረት ይጠይቃሉ፡፡ አጭበርባሪ ሰው አንድን ሰው ካጭበረበረ


በኋላ እንኳን የሰራው ስህተት ምን እንደሆነ አያውቅም፡፡ ይህ እንግዳ ነገር
ይመስለን ይሆናል፤ ነገር ግን እነዚህ ሰዎች ልቦቻቸው በሐጢያቶች ስለደነደኑ ምን
የተሳሳተ ነገር እንዳደረጉ አያውቁም፡፡ ሰው ትክክለኛውን ከስህተቱ መለየት
የሚችለው ልቡ ስሜት ሲኖረውና ንጹህ ከሆነ ብቻ ነው፡፡ ነገር ግን የሐጢያተኞች
ልቦች በሙሉ ደንድነዋል፡፡ ስሜት አልባ የሚሆኑት ለዚህ ነው፡፡
እናንተና እኔ የሐጢያቶችን ስርየት ብንቀበበልም ልክ እንደ ዓለማዊ ሰዎች
አሁንም ሐጢያት እንሰራለን፡፡ ነገር ግን እኛ ከእነርሱ በብዙ እንለያለን፡፡ እነዚህን
ሐጢያቶች ብንሰራም እንኳን ስህተቶቻችንን እንገነዘባለን፤ እንመለሳለን፡፡
እንደገናም በቃሉ እናምናለን፡፡ በአንጻሩ ዓለማዊ ሰዎች ሐጢያት ሲሰሩ ሕሊና
የሌላቸው ይመስል ይህንን ሐጢያት ያለ ሐፍረት በመስራት ይቀጥላሉ፡፡ የከፋው
ደግሞ ከእነርሱ አንዳንዶቹ በሐጢያቶቻቸው የሚኮሩ መሆናቸው ነው፡፡ ልባቸው
ከደነደነ በኋላ ሕሊናችሁ ይሞታል፡፡ ስለዚህ ሁላችንም ዓለማዊ ሰዎች
የሚሰሩዋቸው ሐጢያቶች ተካፋይ መሆን በፍጹም አይገባንም፡፡
ከዚህም በላይ ሐዋርያው ጳውሎስ ‹‹ሁሉ ግን በብርሃን ሲገለጥ ይታያል፤
የሚታየው ሁሉ ብርሃን ነውና›› (ኤፌሶን 5፡13) ይላል፡፡ ይህ ምንባብ እኛ ራሳችን
በጨለማ እየተመላለስን መሆናችንን እንደማናውቅ ያሳየናል፡፡ ይህንን የገለጠችልን
ቤተክርስቲያን ናት፡፡ በዚህ ምክንያት እንደተሳሳትን አወቅን፡፡ ይህንን
በማመናችንም ‹‹ጌታ ሆይ እነዚህንም ሐጢያቶች ደግሞ ስለደመሰስህ ተመስገን›
በማለት በወንጌል እምነት ታምነን እንደገና ወደ ብርሃን መምጣትና ወደ ክርስቶስ
መመለስ እንችላለን፡፡ በዚህ መልኩ እንደገና በእምነት በእግዚአብሄር ፊት መቅረብ
የምንችለው ስህተቶቻችን ስለተገለጡና እኛም ስላወቅናቸው ነው፡፡
ጌታ በኤፌሶን ያሉትን ቅዱሳኖችና የዘመኑን አማኞች የዚህ ዓለም ሰዎች
በሚሰሩዋቸው ሐጢያቶች ተካፋዮች እንዳይሆኑ አዞዋቸዋል፡፡ ስለዚህ ጌታን
መታዘዝና ከዓለም ሐጢያቶች መታቀብ አለብን፡፡ ሁላችንም ሰዎች ስለሆንን
በጉደለቶች የተሞላን ነን፡፡ ሐጢያቶችንም እንሰራለን፡፡ ነገር ግን እንዲህ ባሉ
ጊዜያቶች በብርሃን የተገለጡትን በደሎቻችንን ማወቅ አለብን፡፡

የዓለምን መንገድ አትከተሉ፡፡

በዚህ ከሰዓት በኋላ ከኤፌሶን ምዕራፍ 1 ሰብኬያለሁ፡፡ በዚህ ምዕራፍ ውስጥ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በዓለም ሐጢያቶች ውስጥ ተካፋዮች አትሁኑ 249

ጌታ የቀድሞውን ኑሮዋችንን በሚመለከት እንደሚያታልል ምኞት የሚጠፋውን


አሮጌውን ሰው እንድናስወግደው አስተምሮናል፡፡ (ኤፌሶን 4፡22) በአንድ ወቅት
የተመላለስንበትን የዚህን ዓለም ኑሮ መከተል አይገባንም፡፡ የዚህን ዓለም ኑሮና
ሒደቶች የምንከተል ከሆነ መጨረሻችን ልክ እንደ ዓለማዊ ሰዎች ጣዖታትን
ማምለክ ይሆናል፡፡ (ኤፌሶን 2፡2) የዓለምን ኑሮ በጭራሽ መከተል አይገባንም፡፡
ያንን የምናደርግ ከሆነ መጨረሻችን እግዚአብሄርን መተውና መጥፋት ይሆናል፡፡
የዓለም ሰዎች ሐጢያት መስራት የሕይወታቸው ብቸኛው ዓላማ የሆነ ይመስል
ስስታቸውን ይከተላሉ፡፡ እኛ ግን በጭራሽ በዚህ ውስጥ መሳተፍ የለብንም፡፡ ጻድቅ
የሆነ ቅዱስ ሰው ለጽድቅ መንገድ ታማኝ ከመሆን ይልቅ የዓለምን ኑሮ የሚከተል
ከሆነ በጣም አሳፋሪ ነው፡፡ እኛ የዓለምን ኑሮ ከመከተል ርቀን በእግዚአብሄር
የእውነት ቃል አቅጣጫውን መቀየር ይገባናል፡፡ የዓለምን ኑሮ መቋቋምና ወደ
ጽድቅ መንገድ ልንጠመዝዘው ይገባናል፡፡
ከዚህ ዓለም የሐጢያት ፍሰቶች ጋር መፍሰስና ልክ እንደ ማንኛውም ሌላ
ሰው ስጋዊ አቅጣጫውን መከተል ለእኛ በጣም አደገኛ ነው፡፡ ምክንያቱም
ልቦቻችን ልክ እንደ ዓለማዊ ሰዎች ይደነድናሉ፡፡ ወደ ዓለም ፍሰት በጥቂቱ
የገባችሁት ብቻችሁን ከሆነ ስህተታችሁን ልትገነዘቡ፣ ልትመለሱ፣ ልባችሁን
ልታጸኑና ጌታን በመከተል ልትቀጥሉ ትችላላችሁ፡፡ ነገር ግን ከዓለም ሰዎች ጋር
እጅ ለእጅ ከተያያዛችሁ ለመመለስ በእጅጉ ያዳግታችኋል፡፡ ምክንያቱም እነዚህ
ሰዎች እናንተን የሚለቁበት መንገድ የለም፡፡ ዓለማዊ ሰዎች የሚወዱትን
የምንወድና እነርሱ የሚጠሉትን የምንጠላ ከሆነ ከእግዚአብሄር ዘንድ
የሐጢያቶችን ስርየት ካልተቀበሉት የሰይጣን ልጆች እንዴት እንለያለን? ከዓለም
ሰዎች ጋር መሆን ማለት እነርሱን መምሰል ማለት ነው፡፡ ዓለማዊ ሰዎችን
ተመልከቱ፡፡ የጌታን ጽድቅ መጥላት፣ የደህንነትን መንገድ መናቅና ወንጌልን
የሚሰብከውን ማንኛውንም ሰው ማጥላላት መሠረታዊ መርሃቸው ነው፡፡ ስለዚህ
ከእነርሱ ጋር አብረን ሐጢያት ለመስራትና የሕይወት መንገዳቸውን ለመከተል
እንዴት ልንፈቅድ ይቻለናል? በጭራሽ ከእነርሱ ጋር መወገን አይገባንም፡፡
ከዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ብዙ መማር የሚያስፈልገን ነገር አለ፡፡
ጳውሎስ እንደመከረን ጌታን ለማስደሰት ምን ማድረግ አንደምንችል ማሰብ፣ ሞኞች
ከመሆን ይልቅ ጠቢባን ሆነን በጥንቃቄ መመላለስና ዘመኑን መዋጀት ይኖርብናል፡፡
አሁን ጌታን ስለተገናኘነው የመጨረሻውን እስትንፋሳችንን እስከምንሰጥበት ቀን
ድረስ ከእርሱ ጋር አብረን መመላለሳችንን መቀጠል አለብን፡፡ ቀሪውን
ሕይወታችንን በመኖር ስንቀጥል በእያንዳንዱ የዓለም ማዕዘን እንዲደርስ ወንጌልን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


250 በዓለም ሐጢያቶች ውስጥ ተካፋዮች አትሁኑ

በትጋት ለመስበክ ዘመኑን መዋጀት አለብን፡፡ ጊዜው ሲደርስ ይህ ዓለም


የማይኖርበት ይሆናል፡፡ ስለዚህ ይህ ከመሆኑ በፊት በጥበብ ለመኖር እንዴት
ራሳችንን ማነጽ ንደሚገባንና አሁን ያለንን ዘመን እንዴት መዋጀት እንዳለብን
ማሰብ ይገባናል፡፡
ጌታ በኤፌሶን 5፡15-21 ላይ እንዲህ አለ፡- ‹‹እንግዲህ እንደ ጥበበኞች እንጂ
ጥበብ እንደሌላቸው ሳይሆን እንዴት እንደትመላለሱ በጥንቃቄ ተጠበቁ፡፡ ቀኖቹ
ክፉዎች ናቸውና ዘመኑን ዋጁ፡፡ ስለዚህ የጌታ ፈቃድ ምን እንደሆነ አስተውሉ
እንጂ ሞኞች አትሁኑ፡፡›› መንፈስ ይሙላባችሁ እንጂ በወይን ጠጅ አትስከሩ፤ ይህ
ማባከን ነውና፡፡ በመዝሙርና በዝማሬ፣ በመንፈሳዊም ቅኔ እርስ በርሳችሁ
ተነጋገሩ፡፡ ለጌታ በልባችሁ ተቀኙና ዘምሩ፡፡ ሁል ጊዜ ስለ ሁሉ በጌታችን በኢየሱስ
ክርስቶስ ስም አምላካችንንና አባታችንን ስለ ሁሉ አመስግኑ፡፡ ለእያንዳንዳችሁ
በክርስቶስ ፍርሃት የተገዛችሁ ሁኑ፡፡››
ጠቢብ የሆነ እውነተኛ ሕይወት በእርግጥ ምንድነው? በሐዋርያው ጳውሎስ
ዘመን ኤፌሶን ከንቱ የሆነች ወራዳ ከተማ ነበረች፡፡ ይህች ከተማ የምትገኘው
በደቡብ ምዕራብ ቱርክ የባህር ዳርቻ አካባቢ ነበር፡፡ ይህች ከተማ በጳውሎስ ዘመን
በጣም ሐብታምና በአርጢሜስ መቅደስዋና በተለያዩ የግሪክ አማልክቶች
መቅደሶችዋ የታወቀች ነበረች፡፡ (የሐዋርያት ሥራ 19፡35) በእነዚህ መቅደሶች
ውስጥ የኤፌሶን ዜጎች ጣዖቶቻቸውን ለማምለክ የሚያስችሉዋቸውን የመስዋዕት
ስርዓቶች የሚያቀርቡላቸው ብዙ ሴት ካህናቶች ነበሩ፡፡ እነዚህ ሴት ካህናቶች
በተጨባጭ ከሴተኛ አዳሪዎች ብዙም የሚለዩ አልነበሩም፡፡ ለአረማዊ
አምላኮቻቸው መስዋዕቶችን ለማቅረብ ወደ መቅደሶቹ የሚመጡት ሰዎች
ሐይማኖታዊ ስርዓት አድርገው ከሴት ካህናቶቹ ጋር በግብረ ስጋ ግንኙነት
ተግባራቶች ውስጥ ይሳተፉ ነበር፡፡ ጣዖት አምልኮ አብዛኛውን ጊዜ ከግብረ ስጋ
ግንኙነት ጋር ይዛመዳል፡፡ ይህም ኤፌሶን ምን ያህል በሐጢያት የተሞላችና
የረከሰች እንደነበረች ያሳያል፡፡
ነገር ግን እያንዳንዱ የኤፌሶን ሰው በግብረ ስጋ ግንኙነት ክፋት ውስጥ
ይሳተፍ በነበረበት በዚህ ጊዜም በኢየሱስ ያመኑ አንዳንድ ሰዎች ነበሩ፡፡ ስለዚህ
ጌታ በሐዋርያው ጳውሎስ አማካይነት ለእነዚህ የታመኑ የእግዚአብሄር ልጆች
እንዲህ ባሉ ብዙ ሐጢያተኞች መካከል እንዴት መኖር እንዳለባቸው
አስተማራቸው፡፡ እግዚአብሄር የኤፌሶንን ቅዱሳን ከማናቸውም ሐጢያተኞች ጋር
እንዳይተባበሩ ነገራቸው፡፡ እግዚአብሄር ከእነዚህ ሐጢያተኞች የክፋት ምግባሮች
በእጅጉ ርቀው መንፈሳዊ አሳብ እንዲያስቡ፣ ዘመኑን እንዲዋጁና ጉልበታቸውንም

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በዓለም ሐጢያቶች ውስጥ ተካፋዮች አትሁኑ 251

ሁሉ እግዚአብሄርን ለሚያስደስተው ነገር እንዲያውሉ ነገራቸው፡፡

ጌታ እንደነገረን እንዲህ ያለ የተቀደሰ ሕይወት መኖር አይገባምንም?

እናንተና እኔ ጌታ ተመልሶ እሰከሚመጣበት ቀን ድረስ በእምነት ለማደግና


ቀና ሕይወትን ለመኖር ከፈለግን እያንዳንዱን ነገር በቃሉ መሠረት ማድረግ
አለብን፡፡ ቃሉን ማመንና በልቦቻችን ጥልቀት ውስጥ አኑረን ማሰታወስ አለብን፡፡
ማናችንም ዓለማዊ ሰዎች በሚሳተፉባቸው አንዳች የረከሱ ተግባራቶች ውስጥ
መሳተፍ አይገባንም፡፡ በጉዳዮቹ ውስጥ መሳተፍ ባንፈልግም እንኳን ዓለም
ብቻችንን እንደማይተወን እውነት ነው፡፤ በዚህ ዓለም ላይ እስከኖርን ድረስ በአንድ
ወይም በሌላ መንገድ ከዓለማዊ ሰዎች ጋር ከመገናኘት ማምለጥ አንችልም፡፡
ይህንን በምናደርግበት ጊዜ ሁሉ በሐጢያተኛ ምግባሮቻቸው ተጽዕኖ ሥር
መውደቃችን የተለመደ ነው፡፡ የእግዚአብሄርን ቃል በልቦቻችን ውስጥ ማስታወስና
ከማናቸውምና ከሁሉም የሐጢያት ስፍራዎች ራሳችንን ማራቅ በእጅጉ
የሚያስፈልገን ለዚህ ነው፡፡ ዓለማዊ ፈተናዎችን መቋቋም አዳጋች ቢሆንም ሁሉም
ነገር አላፊ ስለሆነና ለመንግሥተ ሰማይ ባለን ተስፋ ፊት የማይሸነፍ ምንም ነገር
ስለሌለ ሁላችንም እነዚህን ፈተናዎች ማሸነፍ እንችላለን፡፡
በተለይም ጎረምሶች መጠንቀቅ አለባቸው፡፡ እነርሱ አካሎቻቸው ወደ
ጉልምስና በሚያድጉበት ጊዜ ላይ ናቸው፡፡ አእምሮዋቸው ግን አሁንም ያልበሰለና
ሁሉንም ለማወቅ የሚፈልግ ነው፡፡ ነገር ግን የማወቅ ጉጉታቸው አንቆ
እንዲይዛቸው ከፈቀዱና ሐጢያት የሚሰሩ ከሆነ ይህ አእምሮዋቸውንና
ሕሊናቸውን ያጠፋል፡፡ ወጣት ወንዶችና ሴቶች ትዳርና ቤተሰብ ከመመስረታቸው
በፊት ሊማሩ የሚያስፈልጋቸው ብዙ ነገር አለ፡፡ ትክክለኛውን ጊዜ ቢጠብቁ
ይሻላቸዋል፡፡ ለስጋዊ ምኞቶቻቸው የሚሸነፉና በወጣትነታቸው ሐጢያት የሚሰሩ
ከሆነ ይህ ጠባያቸውን ያበላሽባቸዋል፡፡ ጉርምስናቸው በብዙ ሐጢያቶች
እንዲበላሽ ከፈቀዱ ራሳቸውን መቆጣጠር ያቅታቸውና ተስፋ የሌላቸው ከንቱ
ወመኔዎች ሆነው ይቀራሉ፡፡ ሰው በልጅነቱ በጣም ብዙ ስጋዊ ሐጢያቶች ከሰራ
ጠባዩና አእምሮው ይበላሻል፡፡ ከዚህ የተነሳም እንዴት መልካም ነገር
እንደሚያደርግ አያውቅም፡፡ መልካም ነገር ምን እንደሆነም የማወቅ ፍላጎት
አይኖረውም፡፡ ስለዚህ አንድ ጎረምሳ በግብረ ስጋ ግንኙነቶች መፈተኑና በጣም
ብዙ ሐጢያቶች መስራቱ በእጅጉ አደገኛ ነው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


252 በዓለም ሐጢያቶች ውስጥ ተካፋዮች አትሁኑ

ይህ ማስጠንቀቂያ የሚመለከተው ጎረምሶችን ብቻ አይደለም፡፡ ሁላችንንም


በእኩል ደረጃ ይመለከተናል፡፡ ምከንያቱም ማናችንም ልክ እንደ ዓለም ሰዎች
በማናቸውም የሐጢያት ተግባራቶች ውስጥ ተሳታፊ መሆን አይገባንም፡፡ እኛ
ከማንኛውምና ከሁሉም ሐጢያቶች መታቀብ የሚገባን መሆኑ ምን ያህል አስፈላጊ
እንደሆነ የሚገባውን ያህል ትኩረት አላደረግሁበትም፡፡ ይህ መላው ዓለም
ሐጢያተኛ ፍሰቱን የሚከተል ቢሆንም እኛ ጻድቃኖች ራሳችንን መጠበቅ፣
የእምነትን ሰይፍ ስለት ማሾልና ጊዜያችንን ሁሉ በሕይወታችን ውስጥ ላለው
የጽድቅ ሥራ መስጠት አለብን፡፡
ይህ ዓለም ምን ያህል ብልሹ እንደሆነ ለማየት አንዳንድ የቴሌቪዥን
ፕሮግራሞችን ማየት ብቻ ይበቃችኋል፡፡ መገናኛ ብዙሃን በጣም ተፅዕኖ ፈጣሪ
ስለሆኑ የሰዎችን አእምሮ መቅረጽና የዓለምን ጉዞ መጠምዘዝ ይችላሉ፡፡ በጣም
ብዙ መሳጭና አስደንጋጭ ፕሮግራሞች እጅግ የተዋረዱትንና የተበላሹትን ደመ
ነፍሶች ስለሚመስጡ ዕቅዳቸው እያንዳንዱን ወጣት ዝነኛ ማድረግ ይመስላል፡፡
ሐጢያትን በዚህ ዓለም ላይ ማስፋፋትን በሚመለከት ቴሌቪዥን እጅግ አስከፊ
ከሆኑ በጥባጮች አንዱ ነው፡፡
ልጆች ከሆናችሁ እጅግ ስሜታዊ በሆነው የሕይወታችሁ ምዕራፍ ላይ
ትገኛላችሁ፡፡ ይህም በየቀኑ ገጣሚ ያደርጋችኋል፡፡ ይህ የሕይወት ጊዜ ሁሉም ነገር
ቅኔ መስሎ የሚታያችሁ ጊዜ ነው፡፡ ስሜቶቻችሁን መግለጥ ትፈልጋላችሁ፡፡
ኢምንት በሆኑት የልቦቻችሁ ስሜቶች በቀላሉ የምትወሰዱበት ነው፡፡
ስሜቶቻችሁን በሙሉ መተግበር ብትችሉም ከውሃውና ከመንፈሱ ወንጌል
የተወለዳችሁ ከሆናችሁ ድርጊቶቻችሁ በስሜቶቻቸው እንዲመሩ ልትፈቅዱ
አይገባችሁም፡፡ አለበለዚያ ሐጢያት ውስጥ ትወድቃላችሁ፡፡
ጌታ ወጣቶችና ሽማግሌዎች የሆንን ማናችንም በዓለም ሰዎች የሐጢያት
ተግባራቶች ውስጥ ተሳታፊ መሆን እንደማይገባን በግልጥ ነግሮናል፡፡ በእነዚህ
ፈተናዎች የምንሸነፍ ከሆነ ውጤቶቹ ግልጥ ናቸው፡፡ ሁላችንም እንጠፋለን፡፡
ዳግመኛ ያልተወለዱ ዓለማዊ ሰዎች ቀድሞውኑም ለጥፋት ተመድበዋል፡፡ ስለዚህ
የራሳቸውን ስጋዊ ስኬት ለማረጋገጥ ሲሉ ሁሉንም ሐጢያቶች በመስራታቸው
እነርሱን የምንወቅስበት ምክንያት የለንም፡፡ ለእነርሱ በማናቸውም የሐጢያት
ዘዴዎች አማካይነት ስጋዊ ስኬትን ማረጋገጥ የክንውናቸው መለኪያ ነው፡፡ ነገር
ግን የእኛ መንገድ ከእነርሱ መንገድ ፈጽሞ የተለየ ነው፡፡ ራሳችንን በዓለም ኑሮ
ተጠራርጎ እንዲወሰድ የምንፈቅድ ከሆነ የምንጠፋው ለዚህ ነው፡፡ ጻድቃን ከዓለም
ጋር ሲቀላቀሉ ከእግዚአብሄር ስለሚለዩ ከጥፋት በቀር ምን ይጠብቃቸዋል? ስለዚህ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በዓለም ሐጢያቶች ውስጥ ተካፋዮች አትሁኑ 253

ወደ ዓለም ለመግባት አንድ እርምጃ ከመራመዳችን በፊት የእግዚአብሄርን ቃል


ማስታወስና ጌታ ኢየሱስን ለመከተል መመለስ አለብን፡፡
ጌታን የሚያስደስተው ምን እንደሆነ መመርመራችን በእጅጉ አስፈላጊ ነው፡፡
በእግዚአብሄር ፊት ጻድቅ ምን እንደሆነ ማወቅ አለብን፡፡ እግዚአብሄር ተገቢ ነው
ብሎ የሚቆጥረውን በማሰብ የእምነት ጉዞዋችንን መቀጠል አለብን፡፡ እናንተና እኔ
ወንጌልን ማገልገላችን እጅግ ክቡርና የጽድቅ ሥራ ነው፡፡ ከዚህ የሚበልጥ የታመነ
ነገር የለም፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ እኛ እንደምንሰራው ያለ እውነተኛና ጻድቅ የሆነ
ሥራ የሚሰራ ሰው የለም፡፡
እናንተስ ታዲያ? አሁን የሐጢያቶቻችሁን ስርየት ስለተቀበላችሁ የጽድቅን
ሕይወት እየኖራችሁ ነውን? በቤተክርስቲያናችን ውስጥ የሚገኝ እያንዳንዱ ሰው
ከልጆች ጀምሮ የሰንበት ትምህርት እስከሚማሩት፣ እስከ ወጣቶችና እስከ ጎረምሶች
ድረስ ያሉ ወንዶችና ሴቶች በክብር እየኖሩ ነውን? ጨዋና ቁጥብ መሆን ማለት
ሰው የጽድቅ ሕይወትን እየኖረ መሆኑን የሚያሳይ አይደለም፡፡ የጌታን የጽድቅ ሥራ
በምንሰራበት ጊዜ አብዛኛውን ጊዜ በጣም ተናጋሪዎችና የሰይጣንን አገልጋዮች
የምንጋፈጥ መሆን ይኖርብናል፡፡
አጋር ምዕመናኖቼ ዓለም በሐጢያት የአዙሪት ማዕበል ተጠርጎ እየተወሰደ
ቢሆንም እኛ ግን በጽድቅ መቅዘፊያዎች የማያቋርጡትን የሐጢያት ወጀቦች
እየሰነጠቅን በመገስገስ ላይ ነን፡፡ በደመ ነፍስ ቤቱ ወደሆነው ወንዝ
እንደሚመለሰው የሳልሞን ዓሣ እኛ ጻድቃኖችም ወደ እግዚአብሄር እየተመለስን
ነው፡፡ ሳልሞን የተባለው ዓሣ ወደተወለደበት ስፍራ ለመመለስ ባለ በሌለ ሐይሉ
ሁሉ ፈጣኑን የውሃ ፍሰት ተቋቁሞ ይዋኛል፡፡ ምክንያቱም የሳልሞን ደመ ነፍስ
በተወለደበት ስፍራ ዘሩን ተክቶ መሞት ነውና፡፡ እግዚአብሄር በሰጠው የተፈጥሮ
ስርዓት መሠረት እያንዳንዱ በሕይወት ያለ ሳልሞን ዓሳ በወንዙ ፍሰት በጭራሽ
ወደኋላ ላለመገፋት ነገር ግን ወደላይ መዋኘቱን ለመቀጠል የሚችለውን ያህል
ያደርጋል፡፡
ልክ እንደዚሁ እናንተና እኔም ዳግመኛ የተወለድን ክርስቲያኖች ስለሆንን
በጭራሽ የዓለም የሐጢያት ፍሰት መጠረግ አይኖርብንም፡፡ በእግዚአብሄር
መንግሥት ወዳለው ቤታችን ለመድረስ ወደፊት መቅዘፋችንን እንቀጥላለን፡፡
አንዳንድ ጊዜ በድክመቶቻችንና በጉድለቶቻችን ምክንያት የዓለምን ነገሮች
ስንከተልና በሐጢያት ፌሽታ ውስጥ ተሳታፊ ሆኖ ራሳችንን ብናገኘውም ማድረግ
ያለብን ነገር ቢኖር በተቻለ ፍጥነት መመለስና ሕይወታችንን በሙሉ እንደገና
ለወንጌል ቀድሰን መስጠት ነው፡፡ ስለዚህ እግዚአብሄር በነገረን መሠረት ሁላችንም

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


254 በዓለም ሐጢያቶች ውስጥ ተካፋዮች አትሁኑ

ኢየሱስን እየመሰልን የዓለምን ነፋስ በመቃወም ወንጌልን እንስበክ፡፡ ይህንን ደግሜ


የምመክራችሁ አብዛኛውን ጊዜ ለዚህ ዓለም ፈተናዎች ሙሉ በሙሉ ስለምንጋለጥ
ነው፡፡
አንዳንድ ጊዜ ሕይወት ምን ማለት እንደሆነ፣ ሰው እንዴት ከእግዚአብሄር
ጋር መገናኘት እንደሚችል፣ እንዴት ዳግመኛ እንደሚወለድና የጽድቅን ሕይወት
እንደሚኖር ጌታ ተስፋ የሰጠንም የኪዳን ቃል እንዴት በትክክል እንደሚፈጸም
ለማሳየት የቅዱሳኖችን ጉዞ የሚያሳይ ፊልም መሥራት ብችል ብዬ እመኛለሁ፡፡
ጥሩ ሥራ ከሰራን ከዚህ ፊልም የሚበልጥ ሌላ አንዳች ፊልም እንደማይኖር
እርግጠኛ ነኝ፡፡ አሁን ግን ወንጌልን በሥነ ጽሁፍ አገልግሎታችን አማካይነት
እየሰበከን ነው፡፡ ነገር ግን እግዚአብሄር የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በፊልሞች
አማካይነት እንድንሰብክ ቢፈቅድልንና ተጨማሪ ጊዜ ቢሰጠን በመካከላችን
ያሉትን ክህሎት ያላቸውን ሰዎች አሰባስበን አንዳንድ ፊልሞችን መስራቱ መጥፎ
አሳብ አይደለም፡፡
ጌታ በዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ላይ የነገራችሁን ታስታውሱ ዘንድ
ሁላችሁንም እመክራችኋለሁ፡፡ ቢያንስ በጭራሽ ከሁሉም ሰው ጋር አብራችሁ
ዓለምን አትከተሉ፡፡ በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ ሆናችሁ ኢየሱስ
ክርሰቶስን ምሰሉ፡፡ በአደራ የተሰጣችሁንም ተግባር በታማኝነት ፈጽሙ፡፡
ተግባራችሁ ምንም ቢሆንም ሁሌም እምነት ይኑራችሁ፡፡ እንዴት የተሻለ ሥራ
መስራት እንደምትችሉም አስቡ፡፡ ሐላፊነቶቻችሁን ሁሉ ለመወጣትም
የተቻላችሁን ሁሉ አድርጉ፡፡ የተሰጠንን ተግባር በታማኝነት መፈጸሙ በጣም
ያስፈልገናል፡፡ ምክንያቱም ይህ የእግዚአብሄርን ሥራ ስኬት ከማረጋገጡና የእርሱን
ትዕዛዝ እንደንከተል ከማስቻሉም በላይ ስጋዊ አስተሳሰቦቻችንንም ደግሞ
ይገድባል፡፡
የዓለም ክፋት ተካፋዮች ትሆኑ ዘንድ አንዳች ጊዜ እንዳይኖራችሁ ወይም
ፍሰቶቹን እንዳትከተሉ በአደራ ለተሰጣችሁ የእግዚአብሄር ሥራ ሙሉ በሙሉ
ራሳችሁን እንድትቀድሱ እጠይቃችኋለሁ፡፡ ይህ እያንዳንዱ ጻድቅ የሆነ ቅዱስ ሰው
ሊያደርገው የሚገባው ጠቢብ ነገር ነው፡፡ ስለዚህ ሁላችንም እግዚአብሄርን
እንምሰል፡፡ በስጋዊ ሥራዎች ውስጥ ከመሳተፍ ይልቅም በእርሱ ሥራ ውስጥ
እንሳተፍ፡፡ በሚመጣው የእግዚአብሄር መንግሥት ውስጥም እጅግ የተከበርን
ጻድቃን ቅዱሳኖች እንሁን፡፡ 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ስብከት
14

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት
ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
በመንፈስ መሞላት ማለት
በእርግጥ ምን ማለት ነው?
‹‹ ኤፌሶን 5፡1-21 ››
‹‹እንግዲህ እንደተወደዱ ልጆች እግዚአብሄርን የምትከተሉ ሁኑ፡፡
ክርስቶስም ደግሞ እንደወደዳችሁ ለእግዚአብሄርም የመዓዛ ሽታ የሚሆንን መባንና
መሥዋዕትን አድርጎ ስለ እናንተ ራሱን አሳልፎ እንደሰጠ በፍቅር ተመላለሱ፡፡
ለቅዱሳን እንደሚገባ ግን ዝሙትና ርኩሰት ሁሉ ወይም መመኘት በእናንተ ዘንድ
ከቶ አይሰማ፡፡ የሚያሳፍር ነገርም፣ የስንፍና ንግግርም ወይም ዋዛ የማይገቡ
ናቸውና አይሁኑ፤ ይልቁንም ምሥጋና እንጂ፡፡ ይህን እወቁ፤ አመንዘራም ቢሆን
ወይም ርኩስ ወይም የሚመኝ እርሱም ጣዖትን የሚያመልክ በክርስቶስና
በእግዚአብሄር መንግሥት ውስጥ ርስት የለውም፡፡ ከዚህ የተነሣ በማይታዘዙት
ልጆች ላይ የእግዚአብሄር ቁጣ ይመጣልና፡፡ ማንም በከንቱ ንግግር አያታልላችሁ፡፡
እንግዲህ ከእነርሱ ጋር ተካፋዮች አትሁኑ፡፡ ቀድሞ ጨለማ ነበራችሁና፤ አሁን ግን
በጌታ ብርሃን ናችሁ፡፡ የብርሃኑ ፍሬ በበጎነትና በጽድቅ በእውነትም ሁሉ ነውና፡፡
ለጌታ ደስ የሚያሰኘውን እየመረመራችሁ እንደ ብርሃን ልጆች ተመላለሱ፡፡ ፍሬም
ከሌለው ከጨለማ ሥራ ጋር አትተባበሩ፤ ይልቁንም ግለጡት እንጂ፡፡ እነርሱ
በስውር ስለሚያደርጉት መናገር እንኳ ነውር ነውና፡፡ ሁሉ ግን በብርሃን ሲገለጥ
ይታያል፤ የሚታየው ሁሉ ብርሃን ነውና፡፡ ስለዚህ፡- አንተ የምትተኛ ንቃ፤
ከሙታንም ተነሣ፤ ክርስቶስም ያበራልሃል ይላል፡፡ እንግዲህ እንደ ጥበበኞች እንጂ
ጥበብ እንደሌላቸው ሳይሆን እንዴት እንደትመላለሱ በጥንቃቄ ተጠበቁ፡፡ ቀኖቹ
ክፉዎች ናቸውና ዘመኑን ዋጁ፡፡ ስለዚህ የጌታ ፈቃድ ምን እንደሆነ አስተውሉ
እንጂ ሞኞች አትሁኑ፡፡ መንፈስ ይሙላባችሁ እንጂ በወይን ጠጅ አትስከሩ፤ ይህ
ማባከን ነውና፡፡ በመዝሙርና በዝማሬ በመንፈሳዊም ቅኔ እርስ በርሳችሁ ተነጋገሩ፤
ለጌታ በልባችሁ ተቀኙና ዘምሩ፡፡ ሁልጊዜ ስለ ሁሉ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ
ስም አምላካችንንና አባታችንን ስለ ሁሉ አመስግኑ፡፡ ለእያንዳንዳችሁ በክርስቶስ
ፍርሃት የተገዛችሁ ሁኑ፡፡››

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


258 በመንፈስ መሞላት ማለት በእርግጥ ምን ማለት ነው?

ጳውሎስ በኢየሱስ ክርስቶስ ጥሪ የእግዚአብሄር ሐዋርያ ሆነ፡፡ ወዲያውም


የእርሱ ሐዋርያ ሆኖ የእግዚአብሄርን ፈቃድ ብቻ ሰበከ፡፡ የእግዚአብሄር
ቤተክርስቲያን የበላይ ጠባቂዎች ከሆኑት አንዱ በመሆኑ የጳውሎስ አገልግሎት
ሁሉን የሚያቅፍ ነበር፡፡ በጳውሎሳዊው መልዕክቶቹ ውስጥ እንደምናየው የሥነ
ጽሁፍ አገልግሎት ከሚሽን ተግባራቶቹ አንዱ ነበር፡፡
ጳውሎስ ከልቡ ክርስቶስን ይፈራና ያከብር ነበር፡፡ በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ
ያለው እምነቱ የአገልግሎቱ ማዕከል ነበር፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ሁሉንም ሰው
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት ከዓለም ሐጢያቶች ሁሉ እንዳዳነና
እንደባረከ በተደጋጋሚ ሰብኮዋል፡፡ ጳውሎስ የኢየሱስ ክርስቶስ ታማኝ አገልጋይ
በመሆኑ ጌታን ፊት ለፊት ለማየት እስከሄደ ድረስ የክርስቶሰን ፍቅር የማይለካ
ቁመት፣ ጥልቀትና ስፋት ሳይታክት ሰብኮዋል፡፡

ከጽድቁ የተበጀው የእግዚአብሄር ጸጋ፡፡

በኤፌሶን ምዕራፎች ከ3-5 ላይ ሐዋርያው ጳውሎስ የኢየሱስ ክርስቶስን


ጽድቅ በግልጥና በሚያሳምን መንገድ ለማብራራት ‹‹ስለዚህ›› የሚል ተውሳከ ግስ
በተደጋጋሚ ተጠቅሞዋል፡፡ ይህ ጽድቅ ራሱ አምላክ የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ
የሰማይን ዙፋን ትቶ ወደዚህ ምድር በመጣበትና ለሐጢያቶቻችን ለመሞት
ተመድበን ሳለን እኛን ከዓለም ሐጢያቶች ሁሉ ባዳነበት እውነታ ውስጥ
ተገልጦዋል፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን በጽድቁ ከዚህ ዓለም ሐጢያቶች ለማዳን
በቃላት ሊገለጥ የማይችል መከራን ተቋቋመ፡፡ በሸላቾቹ ፊት ዝም እንደሚል በግ
(ኢሳይያስ 53፡7) በእግዚአብሄር ፊት ከአጥማቂው ዮሐንስ በተቀበለው ጥምቀት
አማካይነት ሐጢያቶቻችንን በሙሉ በዝምታ ተሸከመ፡፡ ከዚያም ሞትን አሸነፈ፡፡
በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅና ከሙታን በመነሳትም አዳኛችን ሆነ፡፡
እኛ አሁን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል እውነት በመጣው በኢየሱስ
ክርስቶስ ጽድቅ በማመን እውነተኛ ደህንነትን ተቀብለናል፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ
በእርሱ ዘመን የነበረው እያንዳንዱ ሰው የእግዚአብሄር አብ ልጅ በሆነው በኢየሱስ
ክርስቶስ ጽድቅ አማካይነት በእምነት መዳን እንደሚኖርበት የሰበከው ለዚህ ነው፡፡
እግዚአብሄር በኢየሱስ ክርስቶስ አማካይነት ምን ያህል እንደወደደን
ታውቃላችሁን? ይህንን ያወቅነው ሐዋርያው ጳውሎስ ኢየሱስ ክርስቶስ እንዴት
የደህንነትን በረከቶች እንደሰጠን በጥልቀት ስላስተማረን ነው፡፡ ጳውሎስ ኢየሱስ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በመንፈስ መሞላት ማለት በእርግጥ ምን ማለት ነው? 259

ክርስቶስ እንዴት ዕፁብ ድንቅ የሆነውን መንግሥተ ሰማይ እንዳለበሰንም ደግሞ


ተናግሮዋል፡፡ ልክ እንደ ሁላችን ጳውሎስም የዳነው በክርስቶስ ፍቅር በእምነት
ነበር፡፡ ስለዚህ በመልዕክቶቹ አማካይነት ይህንን የደህንነት እምነት በመጨረሻው
ዘመን ለሚኖሩ ቅዱሳኖች በሙሉ በማስተላለፍ ሕይወታቸው በመንፈስ ቅዱስ
መሞላት እንደሚገባው አስተማራቸው፡፡

ሐዋርያው ጳውሎስ ቀና የሆነ ሕይወትን እንድንኖር መክሮናል፡፡

ሐዋርያው ጳውሎስ ለኤፌሶን ቅዱሳኖች የሚከተለውን ተናገረ፡- ‹‹እንግዲህ


እንደተወደዱ ልጆች እግዚአብሄርን የምትከተሉ ሁኑ፡፡ ክርስቶስም ደግሞ
እንደወደዳችሁ ለእግዚአብሄርም የመዓዛ ሽታ የሚሆንን መባንና መሥዋዕትን
አድርጎ ስለ እናንተ ራሱን አሳልፎ እንደሰጠ በፍቅር ተመላለሱ፡፡›› (ኤፌሶን 5፡1-2)
ሁላችንም ጳውሎስ እዚህ ላይ እንደመከረን ልንመላለስ ይገባናል፡፡ ምክንያቱም
በቀድሞው ኑሮዋችን ሁላችንም በሐጢያቶቻችን ምክንያት ለሲዖል ታጭተን
ነበርና፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን የማንረባውን ሰዎች ለማዳን በእግዚአብሄር ችሮታ
አማካይነት በድንግል ማርያም ሰውነት በኩል ወደዚህ ምድር ተላከ፡፡ ኢየሱስ 30
ዓመት ሲሆነው በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅ የልቦቻችንን ሐጢያቶች በሙሉ
መውሰድ ነበረበት፡፡ ስለዚህ ክርስቶስ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ስለተሸከመ ተሰቅሎ
መሞት ነበረበት፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ በአጥማቂው ዮሐንስ የተጠመቀው ለዚህ
ዓለም ሐጢያቶች በሙሉ ይቀጣ ዘንድ ደሙን ለማፍሰስ ነበር፡፡ እግዚአብሄር አብ
በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ አማካይነት የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ከፈጸመ
በኋላ በዚህ እውነት የምናምነውን ሁላችንንም ለአንዴና ለመጨረሻ ከእያንዳንዱ
ሐጢያት አዳነን፡፡
ጌታ የአምላክን የተትረፈረፈ ፍቅር በእኛ ላይ ማውረዱ ምንኛ ድንቅ ነው!
እኛ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ያለ መታከት እንደምንሰብክ ሁሉ ሐዋርያው
ጳውሎስም እንደዚሁ በሚታወቀው ዓለም ለሚኖር ለእያንዳንዱ ሕዝብ ይህንን
እውነተኛ ወንጌል ሰብኮዋል፡፡ የኤፌሶን ቅዱሳኖች የእርሱን ዱካዎች እንዲከተሉ
ለማደፋፈርም እንዲህ አላቸው፡- ‹‹እንግዲህ እንደተወደዱ ልጆች እግዚአብሄርን
የምትከተሉ ሁኑ፡፡› (ኤፌሶን 5፡1) ታዲያ እግዚአብሄርን የምንመስለው እንዴት
ነው? እግዚአብሄርን መምሰል የምንችለው ራሱ አምላክ የሆነውን ኢየሱስ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


260 በመንፈስ መሞላት ማለት በእርግጥ ምን ማለት ነው?

ክርስቶስን በመምሰል ነው፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ ኢየሱስ ክርስቶስን አስመልክቶ


እንዲህ አለ፡- ‹‹ክርስቶስም ደግሞ እንደወደዳችሁ ለእግዚአብሄርም የመዓዛ ሽታ
የሚሆንን መባንና መሥዋዕትን አድርጎ ስለ እናንተ ራሱን አሳልፎ እንደሰጠ በፍቅር
ተመላለሱ፡፡›› (ኤፌሶን 5፡2) ስለዚህ ለእኛ እግዚአብሄርን መምሰል ኢየሱስ
ክርስቶስ እንዳደረገው ራሳችንን ለውሃውና ለመንፈሱ ወንጌል መስዋዕት ማድረግ
ነው፡፡
እኔም ራሴ በሐጢያቶቼ ምክንያት ብዙ ተሰቃይቻለሁ፡፡ አሁን በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል ስለማምን ነገሩ እንደዚህ ባይሆንም በሕይወቴ ውስጥ
በሐጢያቶቼ የተሰቃየሁበት ወቅት ስለነበር ወደ ማበድ ተቃርቤ ነበር፡፡ ራሴንም
እንኳን ለማጥፋት ተጠግቼ ነበር፡፡ ይህ የሆነው ሰይጣን በየጊዜው ሐጢያት
በመስራቴ ሕሊናዬን ይከስስ ስለነበረ ነው፡፡ ሐጢያቶቹ በብዙ ስላሰቃዩኝ በስጋና
በመንፈስ ራሴን ስቼ ነበር፡፡ ዲያብሎስም በየጊዜው ሐጢያተኛ ሰው እንደሆንሁ
መክሰሱን ቀጠለ፡፡ ነገር ግን እርሱን ለመቋቋም ማድረግ የቻልሁት ነገር ቢኖር
በድንግዝግዝ ኢየሱስ ክርስቶስ አዳኜ እንደነበር ማመን ብቻ ነበር፡፡
በዚያን ዘመን ጌታ በጽድቁ ሐጢያቶቼን በሙሉ እንዴት እንደደመሰሳቸው
በትክክል አላውቅም ነበር፡፡ ይህ ጊዜ በሕይወቴ ውስጥ ጌታ በመስቀል ላይ
ያፈሰሰውን ደም ብቻ ደህንነቴ አድርጌ ያመንሁበት ጊዜ ነበር፡፡ በዚያን ዘመን ስለ
ውሃውና መንፈሱ ወንጌል አንድ ጊዜ ብቻ እንኳን ሰምቼ ቢሆን ኖሮ በዚህ ሁኔታ
ለረጅም ጊዜና ብዙ ባልተሰቃየሁ ነበር፡፡ ነገር ግን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
የሰበከልኝ ማንም አልነበረም፡፡ በእነዚያ ዓመታቶች ሁሉ ጌታ በስቅለቱና ደሙን
በማፍሰሱ ከሐጢያቶቼ ሁሉ እንዳዳነኝ አምኜ ነበር፡፡ ነገር ግን ይህ ሐጢያቶቼን
ከልቤ ውስጥ ማንጻትም ሆነ ከሕሊናዬ ሙሉ በሙሉ መደምሰስ አልቻለም፡፡
በፋንታው ያለ ማቋረጥ በዲያብሎስ ተከሰስሁ፡፡ ሕሊናዬም ሁልጊዜ የጥፋተኝነት
ስሜት ይሰማው ነበር፡፡

በአንድ ምክንያት የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል መገናኘት


አልቻልሁም፤ ይህንን እውነተኛ ወንጌል ካወቀና ከሰበከ ሰው ጋር
አልተገናኘሁም ነበር፡፡

በዚያ ዘመን በሐጢያቶቼ ብዙ ስሰቃይ የነበረ ቢሆንም በልቤ ውስጥ


የተጻፉት ሐጢያቶች ምንም ያህል ተግቼ በኢየሱስ ክርስቶስ ደም ባምንም

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በመንፈስ መሞላት ማለት በእርግጥ ምን ማለት ነው? 261

አልተወገዱም፡፡ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል እስከማስተውል ድረስ ይህ


አልሆነም፡፡ ነገር ግን ይህንን እውነተኛ ወንጌል ከሰማሁና ካመንሁ በኋላ ጌታ
በኢሳይያስ 1፡18 ላይ ‹‹ሐጢአታችሁ እንደ ደም ብትቀላ እንደ አመዳይ ትንጻለች››
እንዳለው ሙሉ በሙሉ ተደመሰሱ፡፡
ይህንን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል እስከማውቅ ድረስ ሐጢያቶቼ
በሙሉ ተወግደው ማየት እጅግ ልባዊ ምኞቴ ነበር፡፡ የውሃውንና የመንፈሱን
ወንጌል በእጅጉ ስፈልገው የነበረው ለዚህ ነው፡፡ በመጨረሻ ከውሃውና ከመንፈሱ
ወንጌል ጋር ከመገናኘቴ በፊት ክፉ ሐጢያተኛ እንደነበርሁ ለእግዚአብሄር
ተናዘዝሁ፡፡ ሐጢያተኛ ሁኔታዬን በዚህ መልኩ የተናዘዝሁት በኢየሱስ ካመንሁ 10
ዓመታቶች ያህል ቢያልፉኝም ልቤ ገናም ሐጢያተኛ ስለነበር ነው፡፡ ስለዚህ
እውነቱን እንዲያስተምረኝና መንገዱንም እንዲያሳየኝ ወደ እግዚአብሄር ጸለይሁ፡፡
በሐጢያቶቼ ምክንያት ለሞት የተመደብሁ ስለነበርሁ ሐጢያቶቼን በሙሉ
እንዲደመስስልኝ እግዚአብሄርን ጠየቅሁት፡፡ እስከዚያን ጊዜ ድረስ ‹‹የክርስቲያን››
ሕይወቴን ስኖር የነበርሁት በሐጢያት ውስጥ ሆኜ ሁሌም በበደሎቼ እየተሰቃየሁ
ነበር፡፡ በሴሚናሪ እየተማርሁ እንኳን ወደኋላ መለስ ብዬ ራሴን ስመረምር
ሐጢያቶቼ በሙሉ አሁንም በልቤ ውስጥ እንዳሉ አየሁ፡፡ ስለዚህ ጥፋተኝነት
የሚሰማውን ሕሊናዬን ለማረጋጋት ጥሩ ሰው እንደነበርሁ በማሰብ ራሴን
ለማታለል ሞከርሁ፡፡ በእግዚአብሄር ሕግ ታስሬም የእርሱን ስርዓቶች ለመጠበቅና
ሁሌም የንስሐ ጸሎቶችን ለማቅረብ ተግቼ ተፍጨረጨርሁ፡፡
በእነዚያ ቀናቶች አሳዳጊ እናቴና እኔ ብዙ ክርስቲያኖች የሚጎርፉለት የጸሎት
ማዕከል እንመራ ነበር፡፡ እኔ ግን ከዚያ ጋር የሚያገናኘኝ ምንም ነገር አልነበረም፡፡
ስለዚህ በዚያ አብዛኛውን ጊዜ የማሳልፈው ራሴን በመምረመር ነበር፡፡ ልቤም ምን
ያህል ባዶ እንደነበር ተገነዘብሁ፡፡ ዝናብ የሚዘንብባቸው ቀኖች ራሴን ለመመርመር
ተጨማሪ ጊዜ ይሰጡኝ ነበር፡፡ በእርግጥ በእግዚአብሄር እምነት እንዳልነበረኝ
በራልኝ፡፡ እንዲህ ባሉ ወቅቶች ከኢየሱስ ክርስቶስ ውጭ እንደቆምሁና በዚህ
ባድማ በሆነው ዓለምም ብቻዬን እንደሆንሁ አየሁ፡፡ ክርስቶስ በልቤ ውስጥ
እንዳልነበረ ስገነዘብ የተሰማኝን ባዶነት ቃላቶች ሊገልጡት አይችሉም፡፡ ይህ
የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስን በልቤ ውስጥ ለመቀበል በርካታ ጊዜያቶች ያህል
ከጸለይሁ በኋላ መሆኑ የታወቀ ነው፡፡
ኢየሱስ አዳኜ ነው ብዬ ስናገር በትክክል በእርሱ ያመንሁ ይመስላል፡፡
እምነቴም ጥሩ ይመስላል፡፡ ይህ ሆኖ ሳለ ግን አሁንም ሐጢያቶች በልቤ ውስጥ
ነበሩ፡፡ ነፍሴ በምድረ በዳ ብቻዋን እንደቀረች ተገነዘብሁ፡፡ አብረውኝ ባሉት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


262 በመንፈስ መሞላት ማለት በእርግጥ ምን ማለት ነው?

ክርስቲያኖች ስከበብ እምነቴ ጥሩ ይመስል ነበር፡፡ ኢየሱስን እየመሰከርሁ በትጋት


ጥሩ የሆነ የክርስቲያን ሕይወት እየመራሁ እንደሆነ ይታወቀኝ ነበር፡፡ ነገር ግን
ብቻዬን በምሆንበትና ራሴን በታማኝነት በምመረምርበት ጊዜ ሁሉ ኢየሱስ
ክርስቶስ በልቤ ውስጥ እንዳልነበረና ልቤም በሐጢያቶች እንደተሞላ በግልጥ
ማየት ችዬ ነበር፡፡ በእግዚአብሄር ጽድቅ አማካይነት ከሐጢያቶቼ ሁሉ
እንዳልዳንሁ ተገለጠልኝ፡፡ በእግዚአብሄር ጉያ ውስጥ ከመሆንም ርቄ
ከእግዚአብሄር ተለይቼ ብቻዬን ነበርሁ፡፡ በአጭሩ እኔ ለጥፋት የተመደብሁ
ሐጢያተኛ እንደነበርሁ በማያከራክር ሁኔታ ግልጥ ነበር፡፡
በጊዜ ሒደት ውስጥም ሐጢያተኛ የመሆኔ ግንዛቤ በተደጋጋሚ ይከሰትልኝ
ነበር፡፡ ይህ በሚሆንበት ጊዜ ሁሉ እነዚሀን አሳቦች ለማፈን ሌሊቱን በሙሉ
የእግዚአብሄርን ቃል ከማንበብ ጀምሮ ጮክ ብዬ እስከ መጸለይና ለበርካታ ቀኖች
እስከ መጾም ድረስ የሚቻለውን ነገር ሁሉ ሞክሬያለሁ፡፡ ነገር ግን እነዚህን ሁሉ
ጥረቶች ባደርግም ጥፋተኝነት የሚሰማውን ሕሊናዬን ለማረጋጋት በምሞክርበት
ጊዜ ሁሉ ከክርስቶስ ውጪ የቆምሁ ሐጢያተኛ እንደሆንሁ ይበልጥ ግልጥ
ሆነልኝ፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ‹‹ዓለም ሳይፈጠር በፊት በፊቱ ቅዱሳንና ነውር
የሌለን በፍቅር እንሆን ዘንድ በክርስቶስ መረጠን፡፡ በበጎ ፈቃዱ እንደወደደ
በኢየሱስ ክርስቶስ ሥራ ለእርሱ ልጆች ልንሆን አስቀድሞ ወሰነን›› (ኤፌሶን 1፡4)
ተብሎ እንደደተጻፈ ለሲዖል ለመኮነን የተመደብሁ ሐጢያተኛ ነበርሁ፡፡
ጳውሎስ ለኤፌሶን ሰዎች በጻፈው መልዕክቱ ውስጥ አብዛኛውን ጊዜ
የተናገረው እያንዳንዱ እውነተኛ አማኝ እንዴት በክርስቶስ ውስጥ መሆን
እንደሚገባው ነው፡፡ ይህ እኔ ምንም ያህል ተግቼ ብሞክርም ልደርስበት
ያልቻልሁት ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ እንዳለው በእርግጥም በክርስቶስ ውስጥ
እንዳለሁ ለማመን ድፍረቱ ይኖረኝ ዘንድ በእጅጉ ናፈቅሁኝ፡፡ ነገር ግን የኢየሱስን
የደህንነት ሥራ በሚመለከት ያለኝ መረዳት ምሉዕ ስላልነበር ሐጢያተኛ ሆኜ
ከመቅረት በቀር ምንም ማድረግ አልቻልሁም፡፡ ምክንያቱም ኢየሱስ ክርስቶስ
ለሐጢያቶቼ የተኮነነው ተሰቀሎ በመሞትና ደሙን በማፍሰስ ብቻ ነው ብዬ
አምኛለሁና፡፡ ስለዚህ በክርስቶስ ውስጥ መግባት ከእኔ ርቆ ቆየ፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ
የሰው ዘር አዳኝ መሆኑን ባምንም በመጨረሻ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
እስከማምን ድረስ ሐጢያተኛ ነበርሁ፡፡
በሌላ አነጋገር በመስቀሉ ደም ብቻ እስካመንሁ ድረስ በተጨባጭ ወደ
ክርስቶስ መግባት አልቻልሁም ነበር፡፡ ምክንያቱም በሐጢያተኛ ሁኔታዬ ውስጥ
ነበርሁ፡፡ ስለዚህ ምንም ያህል ኢየሱስን አዳኜ አድርጌ ያመንሁ ብሆንም ከክርስቶስ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በመንፈስ መሞላት ማለት በእርግጥ ምን ማለት ነው? 263

ውጪ መቆሜ በተሰማኝ ጊዜ ሁሉ ቃላት ከሚገልጠው በላይ እሰቃይ ነበር፡፡ ይህ


በተሰማኝ ቁጥር ሁሉ ይበልጥ መንፈሳዊ ጥማት ይጠማኝ ነበር፡፡ በኢየሱስ
እንደማምን ብናገርም ባዶ የሆነ የእምነት ሕይወትን እኖር ነበር፡፡ ምክንያቱም ልቤ
መንፈስ ቅዱስም ሆነ እውነተኛ የእግዚአብሄር ቃል አልነበረውም፡፡ በእነዚያ
ዘመናት ሊታሰብ ከሚቻለው በላይ እጅግ አስከፊ በሆነ መንፈሳዊ ሁኔታ ውስጥ
እኖር ነበር፡፡ ጌታ በመስቀል ላይ ያፈሰሰውን ደም ለሌሎች በምሰብክበት ጊዜ ሁሉ
በድፍረት ብጮህም ብቻዬን በምሆንበት ጊዜ እኔ ራሴ ክፉ ሐጢያተኛ እንደሆንሁና
በእርግጥም ወደ ክርስቶስ እንዳልገባሁ አውቅ ነበር፡፡

ያን ጊዜ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል የመረዳት ዕድሉ ተሰጠኝ፡፡

በዚህ ሁሉ መከራ መካከል በአንድ የመነቃቃት ስብሰባ ላይ ከተገኘሁ በኋላ


ማቴዎስ 3፡13-17ን እንዳነብብ ዕድል ገጠመኝ፡፡ ይህንን ምንባብ ሳነብ በመጨረሻ
በልቤ ውስጥ ያሉት ሐጢያቶች በሙሉ ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ እንደተላለፉ
ተረዳሁ፡፡ በእነዚያ ዓመታቶች ሁሉ በሐጢያቶቼ ብዙ የተሰቃየሁ ብሆንም ይህ
ሐጢያቶቼ በሙሉ በጥምቀቱ አማካይነት ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ እንደተላለፉ
አስተማረኝ፡፡
ወደ ማቴዎስ 3፡13-17 እንመለስ፡ ‹‹ያን ጊዜ ኢዩስ በዮሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ
ወደ ዮርዳኖስ መጣ፡፡ ዮሐንስ ግን፡- እኔ በአንተ ልጠመቅ ያስፈልገኛል፤ አንተም
ወደ እኔ ትመጣለህን? ብሎ ይከለክለው ነበር፡፡ ኢየሱስም መልሶ፡- አሁንስ
ፍቀድልኝ፤ እንዲህ ጽድቅን ሁሉ መፈጸም ይገባናልና አለው፡፡ ያን ጊዜ ፈቀደለት፡፡
ኢየሱስም ከተጠመቀ በኋላ ወዲያው ከውሃ ወጣ፡፡ አነሆም ሰማያት ተከፈቱ፤
የእግዚአብሄርም መንፈስ እንደ ርግብ ሲወርድ በእርሱም ላይ ሲመጣ አየ፡፡ እነሆም
ድምጽ ከሰማያት፡- በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው አለ፡፡››
በዚያ ቀን ይህንን ምንባብ ባነበብሁበት ቅጽበት ለአእምሮዬ መረዳትን
ለማምጣት ብሉይ ኪዳንና አዲስ ኪዳን ተጣመሩ፡፡ በመጨረሻ በብሉይ ኪዳን
መስዋዕቶች ይቀርቡ በነበረ ጊዜ በተከናወነው የእጆች መጫንና በአዲስ ኪዳን
ዘመን ኢየሱስ በአጥማቂው ዮሐንስ በተቀበለው ጥምቀት መካከል ያለውን
ግንኙነት ማየት ቻልሁ፡፡ የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል እውነት በዚያ ውስጥ
ተደብቋል፡፡ በአዲስ ኪዳን ውስጥ በሚገኘው በማቴዎስ 3፡13-17 ምንባብና
በብሉይ ኪዳን የመስዋዕት ስርዓት አማካይነት የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ምን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


264 በመንፈስ መሞላት ማለት በእርግጥ ምን ማለት ነው?

እንደነበር ወደ መረዳት፣ በተጨባጭ የደህንነት እውነትን ወደ መገንዘብና ወደ


ማመን መጣሁ፡፡ የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ጌታ በጥምቀቱ፣ በስቅለቱ ደሙን
አፍስሶ በመሞትና ከሙታንም በመነሳት የእኔን ሐጢያቶች ብቻ ሳይሆን የሰውን
ዘር ሐጢያቶች በሙሉ ለአንዴና ለመጨረሻ በመሸከም የእርሱን አማኞች በሙሉ
ፈጽሞ እንዳዳነ የሚያውጅ የደህንነት ወንጌል ነበር፡፡ ስለዚህ በመጨረሻ
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል አገኘሁ፡፡ በዚህ የተነሳ በመጨረሻ ከሐጢያቶቼ
ሁሉ የዳንሁ እውነተኛ ጻድቅ ሰው መሆን ቻልሁ፡፡
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ሳላውቅ ‹‹ክርስቲያን ሐጢያተኛ›› ሆኜ አስር
ረጅም ዓመታቶችን አሳልፌያለሁ፡፡ በእነዚያ ሁሉ ዓመታቶች እምነቴ ከንቱ ነበር፡፡
እስከዚያን ጊዜ ድረስም መንፈሳዊ ዕውር ነበርሁ፡፡

በዘመኑ ክርስትና ውስጥ አሳብ ወለድ ደህንነት ምን ያህል እንደተስፋፋ


ታውቃላችሁን?

እዚህ ላይ ሁላችሁም ምን ያህል ከርስቲያኖች በአሳብ ወለድ ደህንነት


እየተሰቃዩ እንደሆነ ልትገነዘቡ ይገባችኋል፡፡ ይህ ከአሳብ ወለድ እርግዝና ጋር
ተመሳሳይ ነው፡፡ አንዳንድ እህቶቻችን ስለዚህ ነገር እንደሰሙ እርግጠኛ ነኝ፡፡ አሳብ
ወለድ እርግዝና አንዲት ሴት በተጨባጭ እርጉዝ ባትሆንም እንኳን ከእርግዝና ጋር
የተያያዙ ምልክቶችና የሕመም ስሜቶች የምታሳይበት የሕክምና ሁኔታ ነው፡፡ ይህ
ሁኔታ የሚገኘው በሴቶች መካከል ብቻ አይደለም፡፡ በብዙ አጥቢ እንስሶች ውስጥም
የተለመደ ነው፡፡ አሳብ ወለድ እርግዝና በሕክምና ቃሉ ሱዶዳይሲስ ተብሎ
የሚታወቅ ቢሆንም ብዙውን ጊዜ የሚከሰተው ለማርገዝ ከፍተኛ ፍላጎት ባላቸው
ልጅ የመጸነስ ዕድሜ ላይ በደረሱ ሴቶች መካከል ነው፡፡ በዚህ ችግር የሚሰቃዩ
ሕሙማን ከወር አበባ መዛባቶች ጀምሮ የማለዳ ሕመም፣ የሆድ ቁርጠት፣ የጡት
ማደግ፣ የቆዳ ለውጦች፣ የሆርሞን ማመንጨትና የጽንስ እንቅስቃሴ ስሜት ድረስ
በራስ የሚታወቁ የተለያዩ የእርግዝና ምልክቶች ያሳያሉ፡፡ በአጠቃላይ አሳብ ወለድ
እርግዝና የሚመነጨው በሥነ ልቦናዊ ምክንያቶች ሆርሞን በሚያመነጭ የዕጢ
ስርዓት ውስጥ በሚከሰቱ የተወሰኑ ለውጦች እንደሆነ ይታሰባል፡፡ አንዲት ሴት
ከፍተኛ የሆነ የማርገዝ ፍላጎት ካላት በቀላሉ የሚታወቁ የእርግዝና ምልክቶችን
የሚያሳዩ ሥነ ልቦናዊ ለውጦች ሊቀሰቀሱ ይችላሉ፡፡ የአሳብ ወለድ እርግዝና
የሕመም ምልክቶች ከእውነተኛው የእርግዝና ሕመም ስሜቶች ጋር ተመሳሳይ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በመንፈስ መሞላት ማለት በእርግጥ ምን ማለት ነው? 265

ስለሆኑ ይህ ሁኔታ የሚታይባቸው ሴቶች እንዳረገዙ በማሰብ ይታለላሉ፡፡


በተመሳሳይ ሁኔታ ዛሬም ብዙ ክርስቲያኖች የደህንነት እምነታቸውን
በሚመለከት አሳብ ወለድ በሆነ ደህንነት እየተሰቃዩ ነው፡፡ እነዚህ የተሳሳቱ
ክርስቲያኖች ኢየሱስ ተሰቅሎ በመሞት ብቻ ከሐጢያቶቻቸው ሁሉ እንዳዳናቸው
ያስባሉ፡፡ እንዲህ በግልጥ በኢየሱስ ስለሚያምኑም ልቦቻቸው ሐጢያተኛ ሆነው
እያሉ እንደዳኑ ያስባሉ፡፡ በአሳብ ወለድ እርግዝና የምትሰቃይ ሴት በተጨባጭ
ባታረግዝም እርጉዝ እንደሆነች እንደምታምን ሁሉ ዛሬም በርካታ ክርስቲያኖች
እውነተኛ የሆነ ይመስል ሐሰተኛ እምነትን የሙጥኝ ብለው ይዘዋል፡፡ እነዚህ
ክርስቲያኖች የሚያምኑበትና የሚሰብኩት ደህንነት ፈጽሞ መሠረተ ቢስ፣ በእጅጉ
የማይመስልና ዓይን ያወጣ ቅጥፈት ነው፡፡
በራሳቸው አስተሳሰብ እንደዳኑ የሚያስቡ ብዙ ክርስቲያኖችን አይቻለሁ፡፡ እኔ
በቀድሞ ጊዜ የክርስቲያን ሕይወቴን እንዴት እንደኖርሁ መልሼ ስመለከት
እንደዳንሁ በማሰብ ሐሰተኛ ደህንነትን የሙጥኝ ብዬ ይዤ እንደነበር ማየት
እችላለሁ፡፡ ልቤ ሐጢያተኛ ቢሆንም ከሐጢያቶቼ እንደዳንሁ አምኜ ነበር፡፡

ማንም ምንም ይበል በእኔ ውስጥ በተገለጠው የእግዚአብሄር ሥራ


አማካይነት የሐጢያቶችን ስርየት እንደተቀበልሁ እርግጠኛ ነኝ፡፡

በቀድሞ ኑሮዬ በልሳን መናገርና ሰማያዊ ራዕዮችን ማየት አዘወትር ነበር፡፡


አሁን ግን ከማንኛውም ልሳን ወይም ከማናቸውም ራዕዮች ይበልጥ እርግጠኛና
አስተማማኝ የሆነ እምነት አለኝ፡፡
ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ክርስትና ስለወጥ እንኳንስ ላምንበት ቀርቶ የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል አላውቅም ነበር፡፡ በዚያን ጊዜ ከበድ ባለ ሕመም ታምሜ
ነበር፡፡ ኢየሱስ እንደ እኔ ላለው የማይረባ ሰው እንደሞተ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ
ሳነብ በስሜት የተነካሁት ለዚህ ሳይሆን አይቀርም፡፡ በዚያን ጊዜ በሐጢያቶቼ
ምክንያት መሞት የነበረብኝ ብሆንም ኢየሱስ በእኔ ፋንታ በመሰቀሉ፣ ደሙን
አፍስሶ በመሞቱና ከሙታን በመነሳቱ ስላዳነኝ አመስጋኝ ነኝ፡፡ ቢያንስ ከመሞቴ
በፊት ሐጢያቶቼን በሙሉ ማንጻት እንደሚገባኝ በማመን በኢየሱስ ያመንሁት
ለዚህ ነው፡፡
ኢየሱስን አዳኜ አድርጌ እንደተቀበልሁ ወዲያውኑ ለእርሱ በጣም ቅንዓት
ስለያዘኝ ጊዜ ሳላጠፋ የክርስቲያን እምነትን መስበክ ጀመርሁ፡፡ አሁን ግን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


266 በመንፈስ መሞላት ማለት በእርግጥ ምን ማለት ነው?

የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል እውነት ስለማውቅ የቀድሞውን ሕይወቴን መለስ


ብዬ ስመለከተው ከበድ ባለ የአሳብ ወለድ ደህንነት ጉዳይ ስሰቃይ እንደነበር ግልጥ
ሆኖልኛል፡፡ እኔ ስሰቃይ እንደነበረው በጣም ብዙ ክርስቲያኖችም በአሳብ ወለድ
ደህንነት እየተሰቃዩ እንደሆነ ማየትም እችላለሁ፡፡ እነዚህ ክርስቲያኖች
ከሐጢያቶቻቸው እንደዳኑ ቢያስቡም በተጨባጭ ግን ሁሌም በልቦቻቸው ውስጥ
ሐጢያቶች አሉ፡፡ አብዛኞቹ ልቦቻቸው በሐጢያት የተሞሉ ቢሆኑም በኢየሱስ
ስለሚያምኑ ብቻ እንደዳኑ ያስባሉ፡፡ እነርሱ እግዚአብሄር ስለሚወዳቸውና በልጁ
በኢየሱስ ክርስቶስ አማካይነት ከሐጢያቶቻቸው ስላዳናቸው ያለ ምንም ቅድመ
ሁኔታ ሐጢያት አልባ እንደሆኑ ይናገራሉ፡፡ ነገር ግን በአሳብ ወለድ ደህንነት
መሰቃየት ማለት በግልጥ እንዲህ ማለት ነው፡፡
በአንጻሩ አሁን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የምናምን እናንተና እኔ
በማናቸውም አስተሳሰብ አልዳንንም፡፡ የውሃና የመንፈስ ወንጌል ተብሎ
በሚጠራው የደህንነት እውነት ስለምናምን ደህንነታችን በእግዚአብሄር
ተረጋግጦዋል፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ መልካም የመዓዛ ሽታ አድርጎ ስለ እኛ ራሱን
ለእግዚአብሄር መስዋዕት አድርጎ አቅርቦዋል፡፡ (ኤፌሶን 5፡2) በሌላ አነጋገር
የእግዚአብሄር ልጅ የሆነው ኢየሱስ እግዚአብሄር አብን በመታዘዝ፣ በመስቀል ላይ
በመሞትና ዳግመኛም ከሙታን በመነሳት ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ተሸክሞ ያለ
እንከን አድኖናል፡፡
እኛ በተጨባጭ ከሐጢያቶቻችን ሁሉ የዳንነው የውሃና የመንፈስ ወንጌል
በሆነው በዚህ የደህንነት ወንጌል በማመን ነው፡፡ እኛ አሁን በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል ስለምናምን ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ድነናል፡፡ እኛ አሁን በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል ስለምናምን ምስጋናችንን ሁሉ ለእግዚአብሄር እናቀርባለን፡፡

ሐዋርያው ጳውሎስ መልዕክቱን ለኤፈሶን ቤተክርስቲያን የጻፈው ታስሮ


ሳለ ነው፡፡

በዚህ የጳውሎስ መልዕክት ውስጥ ዋናው አሳብ በክርስቶስ ፍቅር ጥልቀት፣


ቁመት፣ ስፋትና ርዝመት ላይ ያለው ከሙሉ ልብ የመነጨ እምነቱ እንደሆነ ማየት
እንችላለን፡፡ ዛሬም እናንተና እኔ የሥነ ጽሁፍ አገልግሎታችንን እያከናወንን
በመሆናችን ጳውሎስ እንዳደረገው ሁሌም የክርስቶስን ፍቅር ርዝመት፣ ቁመት፣
ስፋትና ጥልቀት ማሰብ ይገባናል፡፡ በዚህ መረዳትም በእምነታችን እግዚአብሄርን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በመንፈስ መሞላት ማለት በእርግጥ ምን ማለት ነው? 267

ማመስገን፣ ክብርን ሁሉ ለእግዚአብሄር አብ መስጠት፣ የውሃውንና የመንፈሱን


ወንጌልም በትጋት እስከ ዓለም መጨረሻ ድረስ መስበክ አለብን፡፡
ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ያዳነን ኢየሱስ ክርስቶስ ለእኛ ያለው ፍቅር ምን ያህል
ጥልቅ ነው? እግዚአብሄር ራሱ ሰው በመሆን ከሐጢያቶቻችን ሁሉ አድኖናል፡፡
ይህ በራሱ የእግዚአብሄር ፍቅር ምን ያህል ታላቅ እንደሆነ ያሳየናል፡፡ በዮሐንስ
1፡14 ላይ እንዲህ ተጽፎዋል፡- ‹‹ቃልም ሥጋ ሆነ፤ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ
በእኛ አደረ፡፡ አንድ ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር የሆነውን ክብሩን
አየን፡፡›› ኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ ምድር መጥቶ ያደረገልን እያንዳንዱ ነገር
ትክክለኛ የደህንነት እውነት ነው፡፡ እርሱ ምንም ሐሰት የለበትም፡፡ ነገር ግን
በእግዚአብሄር ጽድቅ የተሞላ ነው፡፡
ጌታችን ወደዚህ ምድር በመጣ ጊዜ በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅ
የእያንዳንዱን ሰው ሐጢያቶች በሙሉ ለአንዴና ለመጨረሻ ተሸከመ፡፡ በመስቀል
ላይ ስለሞተና ከሙታንም ደግሞ ስለተነሳ በዚህ ዓለም ላይ የሚኖረውን
እያንዳንዱን ሰው አድኖዋል፡፡ በዚህ እውነት የሚያምኑ ሁሉ ሙሉ በሙሉ
ሐጢያት አልባ ናቸው፡፡ ምክንያቱም በልቦቻቸው ውስጥ ሐጢያት የለባቸውምና፡፡
እነርሱ እውነቱን ለዓለም ሁሉ እየመሰከሩ ነው፡፡ እኛ ኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ
ምድር በመምጣት፣ በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅና በመስቀል ላይ በመሞት
ለአንዴና ለመጨረሻ ከሐጢያቶቻችን ሁሉ እንደዳንን ለዓለም እየመሰከርን ነው፡፡
እንደዚሁም እኛ በእግዚአብሄር ፊት ሙሉ በሙሉ ሐጢያት አልባ እንደሆንን
እየመሰከርን ነው፡፡
እግዚአብሄር አብ እያንዳንዱን የዚህ ዓለም ሐጢያት በልጁ አማካይነት
ደምስሶዋል፡፡ የዚህን ዓለም ሐጢያቶች በሙሉ ወደ ልጁ አስተላለፈ፡፡
የእግዚአብሄር ልጅም በእኛ ምትክ ለእነርሱ በመኮነን እነዚህን ሐጢያቶች በሙሉ
አስወገደ፡፡ ኢየሱስ በዚህ መልኩ እያንዳንዱን ሐጢያት ደምስሶ ሳለ በጣም ብዙ
ክርስቲያኖች አሁንም ድረስ በልቦቻቸው ውስጥ ለምን ሐጢያቶች ይኖራሉ?
ልቦቻቸው ሐጢያት ያለባቸው የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ሳያውቁ ኢየሱስን
አዳኛቸው አድርገው በማመናቸው ነው፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ በሕይወት ዘመኑ ሁሉ የኢየሱስ ክርስቶስን ፍቅር
በመስበክ ቀጥሎዋል፡፡ እርሱ ክርስቶስ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት
የሰውን ዘር በሙሉ እንዳዳነ ለእያንዳንዱ ሰው ሰበከ፡፡ ጳውሎስ አንዲህ ያለው
ለዚህ ነው፡ ‹‹ከክርስቶስ ጋር አንድ ትሆኑ ዘንድ የተጠመቃችሁ ሁሉ ክርስቶስን
ለብሳችኋልና፡፡›› (ገላትያ 3፡27) በዕብራውያን 10፡22 ላይም እንዲህ ብሎዋል፡-

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


268 በመንፈስ መሞላት ማለት በእርግጥ ምን ማለት ነው?

‹‹ከክፉ ሕሊና ለመንጻት ልቦቻችንን ተረጭተን ሰውነታችንንም በጥሩ ውሃ ታጥበን


በተረዳንበት እምነት በቅን ልብ እንቅረብ፡፡›› ጳውሎስ በሮም ሰማዕትነትን
እስኪቀበል ድረስ እውነተኛውን የውሃና የመንፈስ ወንጌል ቃል ያለ ማቋረጥ
በመስበክ ቀጠለ፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በሚገባ ያውቅና
ሳይናወጥ ያምንበት ነበር፡፡ ነገር ግን በአሁኑ ጊዜ ብዙ ሰዎች ጌታ በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል በዚህ ዓለም ላይ የሚኖረውን የእያንዳንዱን ሰው ሐጢያቶች
በሙሉ እንደደመሰሰ ሳያውቁ ኢየሱስን አዳኛቸው አድርገው ያምናሉ፡፡ ስለዚህ
ሐዋርያው ጳውሎስ በዘመኑ ክርስትና ውስጥ ምን እየሆነ እንዳለ ቢያይ ምን ያህል
ሐዘን ይሰማው እንደነበር መገመት ትችላላችሁ፡፡ እኛ ይህንን በማየት
እንደምንረበሽ ሁሉ እግዚአብሄርም በጥልቅ ያዝናል፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ ምድር በመጣ ጊዜ በአጥማቂው ዮሐንስ
በመጠመቅ የዚህን ዓለም ሐጢያቶች በሙሉ ለአንዴና ለመጨረሻ በተሸከመበት
ቅጽበት የእግዚአብሄርን ጽድቅ ሁሉ ፈጸመ፡፡ ኢየሱስ ከአጥማቂው ዮሐንስ
የተቀበለው ጥምቀትና በመስቀል ላይ ያፈሰሰው ደም የእግዚአብሄርን ጽድቅ ሁሉ
ፈጽመዋል፡፡ ይህ ወንጌል ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ያዳነን የውሃውና የመንፈሱ
ወንጌል ነው፡፡ የእግዚአብሄር ልጅ የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ በመጠመቅ የእኔንና
የእናንተን ሐጢያቶች ብቻ ሳይሆን የሰውን ዘር ሐጢያቶች በሙሉ ተቀበለ፡፡
ሰውነቱን ለስቅለት ሞት አሳልፎ በመስጠትም ለሐጢያቶቻችን ሁሉ ሙሉ በሙሉ
ተኮነነ፡፡ በሦስት ቀናቶች ውስጥም ከሙታን ተነሳ፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ
ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ያነጻውና አዳኛችን ሊሆንም ከተረጋገጠው ሞታችን ወደ
ሕይወት የመለሰን እንደዚህ ነው፡፡
ስለዚህ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ደህንነታቸው አድርገው የሚያውቁና
የሚያምኑ ሁሉ የዘላለምን ሕይወት ያገኛሉ፡፡ እግዚአብሄር ለእኛ ያለው ፍቅር ይህ
ነው፡፡ እግዚአብሄር እኛን ከዓለም ሐጢያቶች ሁሉ ያዳነበት እውነት የሚገኘው
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ውስጥ ነው፡፡ ስለዚህ በዚህ እውነተኛ ወንጌል
የሚያምን ሰው ሁሉ በልቡ ውስጥ ሐጢያት የለበትም፡፡ የጌታ ጸሎት ምን ይላል?
እንዲህ ይላል፡-
‹‹ፈቃድህ በሰማይ እንደሆነች እንዲሁ በምድር ትሁን፡፡›› (ማቴዎስ 6፡10)
በሌላ ቦታ በዮሐንስ 3፡16 ላይ ኢየሱስ እንዲህ ብሎዋል፡- ‹‹በእርሱ
የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሄር
አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና፡፡›› እግዚአብሄር አብ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በመንፈስ መሞላት ማለት በእርግጥ ምን ማለት ነው? 269

ልጁን ወደዚህ ምድር በመላክ፣ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ወደ ወልድ በማስተላለፍ፣


ተሰቅሎ እንዲሞት በመፍቀድና መልሶ ወደ ሕይወት በማስነሳት ሐጢያቶቻችንን
በሙሉ አነጻ፡፡ ለአንዴና ለመጨረሻም ከዓለም ሐጢያቶች ሁሉ አዳነን፡፡ ኢየሱስ
ክርስቶስ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ለአንዴና ለመጨረሻ ፈጽሞ ያነጻው በአጥማቂው
ዮሐንስ በመጠመቅ ነው፡፡ ጌታ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት ፍጹም
የሆነውን የሐጢያቶች ስርየት ደህንነት የፈጸመው በዚህ መልኩ ነው፡፡
ችግሩ ግን በጣም ብዙ ሰዎች በሐሰተኛ የክርስቲያን ትምህርቶች በአያሌው
ስለተሳሳቱ የደህንነትን እውነት አልተገነዘቡም፤ ማለትም እግዚአብሄር በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት ከሐጢያቶቻቸው ሁሉ እንዳዳናቸው ምንም አሳብ
የላቸውም፡፡ ዛሬ በርካታ ክርስቲያኖች በዲያብሎስና በእርሱ ሐሰተኛ ነቢያቶች
ስለተታለሉ በኢየሱስ እንደሚያምኑ ቢናገሩም ልቦቻቸው አሁንም
በሐጢያቶቻቸው ተሞልተው እየኖሩ ነው፡፡ እነዚህ ሰዎች ሐጢያተኞች ሆነው
እየኖሩ ያሉት በዘመኑ ክርስትና የሐሰት ትምህርቶች ተታልለው የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል ስለማያውቁ ነው፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ በመንፈሱ በጣም
ያዘነው ለዚህ ነው፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ የኢየሱስ ክርስቶስን ፍቅር ርዝመት፣ ቁመት፣ ስፋትና
ጥልቀት ሲናገር አሁን እኛ የክርስቶስን ፍቅር ስለለበስን ሐጢያተኞች
እንደሚያደርጉት ከእንግዲህ ወዲያ እንደ ዓለም ምኞት መኖር እንደማይገባን
ነግሮናል፡፡ ከዚያም የሚከተለውን መከረን፡- ‹‹ለቅዱሳን እንደሚገባ ግን ዝሙትና
ርኩሰት ሁሉ ወይም መመኘት በእናንተ ዘንድ ከቶ አይሰማ፡፡ የሚያሳፍር ነገርም፣
የስንፍና ንግግርም ወይም ዋዛ የማይገቡ ናቸውና አይሁኑ፤ ይልቁንም ምሥጋና
እንጂ፡፡ ይህን እወቁ፤ አመንዘራም ቢሆን ወይም ርኩስ ወይም የሚመኝ እርሱም
ጣዖትን የሚያመልክ በክርስቶስና በእግዚአብሄር መንግሥት ውስጥ ርስት
የለውም፡፡ ከዚህ የተነሣ በማይታዘዙት ልጆች ላይ የእግዚአብሄር ቁጣ
ይመጣልና፡፡ ማንም በከንቱ ንግግር አያታልላችሁ፡፡ እንግዲህ ከእነርሱ ጋር
ተካፋዮች አትሁኑ፡፡ ቀድሞ ጨለማ ነበራችሁና፤ አሁን ግን በጌታ ብርሃን ናችሁ፡፡
የብርሃኑ ፍሬ በበጎነትና በጽድቅ በእውነትም ሁሉ ነውና፡፡›› (ኤፌሶን 5፡3-9)
ይህ ምንባብ በእርግጥ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት የጌታን
ፍቅር ከተረዳንና እርሱንም በእምነት በትክክል በልቦቻችን ውስጥ ከተቀበልነው
የዚህ ዓለም ሰዎች በሚሰሩዋቸው ሐጢያቶች ውስጥ በጭራሽ ተሳታፊ መሆን
እንደሌለብን በግልጥ ያስተምረናል፡፡ ነገር ግን ከእነርሱ መራቅ ይገባናል፡፡ በሌላ
አነጋገር ሐዋርያው ጳውሎስ የሚከተለውን እየነገረን ነው፡- ‹‹የስጋን መሻትና

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


270 በመንፈስ መሞላት ማለት በእርግጥ ምን ማለት ነው?

ክፋትን የሚከተሉ ሁሉ የእግዚአብሄርን ቁጣ ይቀበላሉ፡፡ የእግዚአብሄርን ፍቅርና


ጌታ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ሐጢያቶቻቸወን በሙሉ እንደደመሰሰላቸው
የማያምኑ ሰዎችም እንደዚሁ የእግዚአብሄርን እርግጠኛ ቁጣ ይቀበላሉ፡፡ እናንተ
ግን በተጨባጭ ከሐጢያቶቻችሁ ድናችኋል፡፡ ስለዚህ በእነዚህ ሐጢያቶች ውስጥ
አትሳተፉ፡፡ ከሐጢያቶቻችሁ ከዳናችሁም በኋላ የዚህ ዓለም ሰዎች እንደሚኖሩት
የምትኖሩ ከሆነ እናንተም ደግሞ የእግዚአብሄርን ቁጣ ትቀበላላችሁ፡፡››

‹‹ሁሉ ግን በብርሃን ሲገለጥ ይታያል፡፡›› (ኤፌሶን 5፡13)

ሐዋርያው ጳውሎስ በኤፌሶን 5፡10-14 ላይ እንዲህ አለ፡- ‹‹ለጌታ ደስ


የሚያሰኘውን እየመረመራችሁ እንደ ብርሃን ልጆች ተመላለሱ፡፡ ፍሬም ከሌለው
ከጨለማ ሥራ ጋር አትተባበሩ፤ ይልቁንም ግለጡት እንጂ፡፡ እነርሱ በስውር
ስለሚያደርጉት መናገር እንኳ ነውር ነውና፡፡ ሁሉ ግን በብርሃን ሲገለጥ ይታያል፤
የሚታየው ሁሉ ብርሃን ነውና፡፡ ስለዚህ፡- አንተ የምትተኛ ንቃ፤ ከሙታንም ተነሣ፤
ክርስቶስም ያበራልሃል ይላል፡፡››
ከዚህ ምንባብ ቀደም ብሎ ጳውሎስ በኤፌሶን 5፡9 ላይ እንዲህ ብሎዋል፡-
‹‹የብርሃኑ ፍሬ በበጎነትና በጽድቅ በእውነትም ሁሉ ነውና፡፡›› እዚህ ላይ ጳውሎስ
እንዳስተማረን እኛ አሁን ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ስለዳንንና የእግዚአብሄር ልጆች
ስለሆንን ሁላችንም እንደ ብርሃን ልጆች ልንመላለስ ይገባናል፡፡ ጻድቃን የዚህ
ዓለም ሰዎች እንደሚኖሩት በጭራሽ ሕይወታቸውን መኖር አይገባቸውም፡፡ ጻድቅ
የሆነ ቅዱስ ሰው ሐጢያተኞች የሚሰሩዋቸውን ሐጢያቶች መስራት የለበትም፡፡
የብርሃን ልጆች ሁሉ ከዚህ ርቀው ከአዲሱ ማዕረጋቸው ጋር በሚጣጣም መንገድ
ሊኖሩ ይገባቸዋል፡፡ ያንን ለማድረግም አንድ ላይ መሆንና የጌታን የጽድቅ ሥራ
ከሙሉ ልባቸው መሥራት አለባቸው፡፡
ጻድቃን የእግዚአብሄርን ሥራ ለመሥራት ሲሰበሰቡ አብዛኛውን ጊዜ
ብዙዎቹ ጉድለቶቻቸው ሲገለጡ ያያሉ፡፡ በዚህ መልኩ ጉድለቶቻቸው
በሚገለጡበት ጊዜ ሁሉ ሁሉም በእግዚአብሄር ቃል ብርሃን ይገለጣሉ፡፡ ይህ ማለት
ጻጸድቃን ወደ ብርሃን መምጣት የሚችሉት ስህተቶቻቸው ባሉበት ሁኔታ ሲገለጡ
ብቻ ነው ማለት ነው፡፡
ጳውሎስ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን የእግዚአብሄር ልጅ የሆነ
ሰው ገና ዳግመኛ ካልተወለደ ከማንኛውም ሰው ጋር ተባብሮ መሥራት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በመንፈስ መሞላት ማለት በእርግጥ ምን ማለት ነው? 271

እንደማይገባው ተናግሮዋል፡፡ በራሳችን ጎዶሎዎች ብንሆንም እኛ ጻድቃኖች


የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል የምንሰብክና ጌታን በሕብረት የምንከተል ከሆነ
ምንም ነገር አይጎድለንም፡፡ አሁንም ብዙ ጉድለቶች ስላሉብን ሐጢያት እንደምሰራ
እሙን ነው፡፡ ነገር ግን እነዚህ ሁሉ ሐጢያቶች ቀድሞውኑም ተወግደዋል፡፡ ሆኖም
ከክፋት በስተቀር ምንም ነገር ከማይፈልጉ ሐጢያተኞች ጋር እጅ ለእጅ መያያዝ
ይቅር ሊባል የማይችለውን መንፈስ ቅዱስን የመሳደብ ሐጢያት መሥራት ነው፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ በዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ላይ ሊያስተምረን እየሞከረ
ያለው እያንዳንዱ ጻድቅ የሆነ ቅዱስ ሰው በመንፈስ ሙላት መኖር የሚገባው
መሆኑን ነው፡፡
እኛ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የምናምን ጻድቃን ነን፡፡ ነገር ግን ይህ
የግድ ፈጽሞ አንዳች ስጋዊ ሐጢያቶችን መሥራት የለብንም ማለት ነውን? የለም፤
እንዳይደለ የታወቀ ነው! ጻድቃንም ቢሆኑ በስጋቸው ሐጢያትን ሊሰሩ ይችላሉ፡፡
ስለዚህ ሕይወታቸው በሚባዝንበት ጊዜ ሁሉ የእምነት ቀደምቶቻቸው
ለስህተቶቻቸው ሊገስጹዋቸው ይገባል፡፡ ለምን እንደዚህ ይሆናል? መባዘናችንን
መረዳት የምንችለው በስህተቶቻችን ስንገሰጽ ብቻ ነው፡፡ የስህተት ድርጊቶቻችንን
ማመን፣ ወደ ብርሃን መምጣት፣ ወንጌልን ማሰላሰልና ሙሉ የሐጢያቶች ስርየት
ስለሰጠንም እንደገና ጌታን ማመስገን የምንችለው ያን ጊዜ ብቻ ነው፡፡ ስለዚህ
ስንባዝን ነገር ግን ይህንን መረዳት በሚሳነን ጊዜ ሁሉ መገሰጽ አለብን፡፡
በቤተክርስቲያንም ለዚሁ መንቃት አለብን፡፡ አብዛኛውን ጊዜ ለራሳችን እንኳን
ይቅር የማይበሉ የሚመስሉ ሐጢያቶቸን እንሰራለን፡፡ በምንሰራቸው ሐጢያቶችም
በብዙ ስቃይና ጸጸት እንሰቃያለን፡፡ ይህ ግን ያን ያህል ግዙፍ ችግር አይደለም፡፡
ምክንያቱም ቀደሞውኑም ከእነዚህ ሐጢያቶች ሁሉ ድነናልና፡፡ ጌታ በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ስለደመሰሰ ቀድሞውኑም በእምነት
የእግዚአብሄር ሐጢያት አልባ ልጆች ሆነናል፡፡ ስለዚህ ሐዋርያው ጳውሎስ ሁሉ
ግን በብርሃን ሲገለጥ እንደሚታይ የተናገረው ለዚህ ነው፡፡
ሆኖም ይህ መርህ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል የማያምኑ ሐጢያተኞችን
አይመለከትም፡፡ እነርሱን ስለ ሐጢያቶቻቸው ልትገስጹዋቸው ሞክሩና ምን
እንደሚፈጠር ተመልከቱ፡፡ እነርሱ በብርሃን ከመገለጣቸው ርቀው ይጠሉዋችኋል፤
በጣምም ይቃወሙዋችኋል፡፡ ሕይወታቸው በመሳሳቱ ሲገሰጹ በብርሃን
የሚገለጡት በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን ከሐጢያቶቻቸው ሁሉ የዳኑ
ሰዎች ብቻ ናቸው፡፡ ጻድቃን ከእነዚያ ሐጢያቶች ሁሉ ማምለጥ የሚችሉት
የእምነት ቀደምቶቻቸው ስለሰሩት የተሳሳቱ ድርጊቶች ሲገሰጹዋቸው ብቻ ነው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


272 በመንፈስ መሞላት ማለት በእርግጥ ምን ማለት ነው?

ጌታ ከሐጢያቶቻችን ሁሉ እንዳዳነን ይበልጥ በግልጥ ለመግለጥ የደህንነት እውነት


ብሩህ ሆኖ ሊያበራ የሚችለው እንደዚህ ነው፡፡ ስለዚህ የክርሰቶስን ፍቅር
ማወቃችን፣ የዚህን ፍቅር ስፋትና ጥልቀት መረዳትና ማመን፣ በእምነት
ሕይወታችንም በምንሳሳትበት ጊዜ ሁሉ በስህተት ድርጊቶቻችን ለመገሰጽ ፈቃደኛ
መሆን ለሁላችንም በእጅጉ ያስፈልገናል፡፡

የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለመስበክ ዘመኑን መዋጀት አለብን፡፡

በኤፌሶን 5፡15-18 ላይ እንዲህ ተጽፎዋል፡- ‹‹እንግዲህ እንደ ጥበበኞች እንጂ


ጥበብ እንደሌላቸው ሳይሆን እንዴት እንደትመላለሱ በጥንቃቄ ተጠበቁ፡፡ ቀኖቹ
ክፉዎች ናቸውና ዘመኑን ዋጁ፡፡ ስለዚህ የጌታ ፈቃድ ምን እንደሆነ አስተውሉ
እንጂ ሞኞች አትሁኑ፡፡ መንፈስ ይሙላባችሁ እንጂ በወይን ጠጅ አትስከሩ፤ ይህ
ማባከን ነውና፡፡››
እስቲ ይህንን ምንባብ በቅርበት እንመልከተው፡፡ እኛ አሁን የክርስቶስን
ፍቅር በሕይወታችን ውስጥ ስለተቀበልን ከአሁን ጀምሮ እንዴት ልንኖር ይገባናል?
እኛ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ስለዳንን
በእግዚአብሄር ፊት እንደ ሞኞች ሳይሆን ሁሌም እንደ ጠቢባን እንደሚገባ ልንኖር
ይገባናል፡፡ ያንን ለማድረግ ጌታ የሰጠንን ዘመን መዋጀት አለብን፡፡ አሁን
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን የሐጢያቶችን ስርየት የተቀበሉ ሁሉ
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ለመስበክ ዘመኑን መዋጀት አለባቸው፡፡
ዘመን እንዳያልፍ ማቆም የሚችል ማነው? ሰዓት እንዳትሽከረከር ማቆም
የሚችል የለም፡፡ ዛሬ ሕዳር 2 ነው፡፡ ይህ ዓመት ሊያልቅ የሚቀረው ከሁለት
ወራቶች ያነሰ ነው፡፡ ክርስቲያኖች ስለሆንን እነዚህ ቀሪ ሁለት ወራቶች የጌታን ሥራ
ለማስፋፋት እንዴት በተሻለ ሁኔታ እንደምንጠቀምበት ማስላት በጣም አስፈላጊ
ተግባራችን ነው፡፡ አሁን እኛ ማድረግ የሚኖርብን ነገር ቢኖር በእነዚህ ቀሪ ሁለት
ወራቶች እንዴት የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ማገልገል ንደምንችልና ራሳችንን
ለዚህ ሥራ አሳልፈን ለመስጠት ልቦቻችንን እንደምናጸና ማሰብ ነው፡፡ ያ የሆነበት
ምክንያት ጌታ ዘመኑን እንድንዋጅ ስለነገረን ነው፡፡
በዚህ በአሁኑ ዘመን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የምናምን ሰዎች ስለሆንን
ዘመኑን መዋጀት ይበልጥ አስገዳጅ ነው፡፡ ዘመኑን መዋጀት የሚገባን ለምንድነው?
ምክንያቱም የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በመላው ዓለም ለመስበክ የቀረልን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በመንፈስ መሞላት ማለት በእርግጥ ምን ማለት ነው? 273

ያን ያህል ብዙ ዘመን የለንምና፡፡ አብልጠን ዘመኑን መዋጀት የሚገባን ለዚህ ነው፡፡


የጌታ ምጽዓት ሩቅ ስላልሆነ እንደዚህ ዓለም ሰዎች በሞኝነት አለመሸነፍ ነገር ግን
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በሚያምነው እምነታችን መኖርና የጌታ ፈቃድ ምን
እንደሆነ በእጅጉ መረዳት ያስፈልገናል፡፡
ታዲያ ጌታ ለእኛ ያለው ፈቃድ ምንድነው? ቀሪውን ሕይወታችንን ጌታን
በመታመን በዚህ ዓለም ላይ እንድንኖር ነው፡፡ ጌታ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
አማካይነት ከዓለም ሐጢያቶች ሁሉ ስላዳነን ሁላችንም በእምነት መኖራችን ምን
ያህል አስፈላጊ እንደሆነ ብቻ ሳይሆን እንዲህ ያለውን የእምነት ሕይወት መኖር
እንደሚገባን መረዳት አለብን፡፡

በመንፈስ ቅዱስ መሞላት ከፈለጋችሁ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል


ብቻ እመኑና አገልግሉ፡፡

በኤፌሶን 5፡18 ላይ እንዲህ ተጽፎዋል፡- ‹‹መንፈስ ይሙላባችሁ እንጂ


በወይን ጠጅ አትስከሩ፤ ይህ ማባከን ነውና፡፡›› እኛ በመንፈስ ቅዱስ መሞላት
አለብን ማለት ራሳችንን በእግዚአብሄር ሥራ ውስጥ ማጥለም፣ በእርሱ ጽድቅ
ማመንና ጊዜያችንንም ይህንን የእግዚአብሄር ጽድቅ ለመስበክ ማዋል አለብን ማለት
ነው፡፡ በመንፈስ መሞላት ማለት በልሳን መናገር ወይመ ልክ እንደ ጥራዝ ነጠቅ
ሰው በሐይል መጸለይ ማለት አይደለም፡፡ ይልቁንም በመንፈስ ቅዱስ መሞላት
ራሳችሁን ሙሉ በሙሉ ለውሃውና ለመንፈሱ ወንጌል ስርጭት አሳልፋችሁ
መስጠት ነው፡፡ ስለዚህ ሁላችንም የጌታን ፈቀድ መረዳታችን፣ የእግዚአብሄርን
ጽድቅ የያዘውን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ማመናችንና ይህንን ወንጌል
ለመስበክም በታማኝነት መሥራታችን በእጅጉ አስፈላጊ ነው፡፡
ብዙ ክርስቲያኖች በመንፈስ ቅዱስ ሙላት መኖር ማለት ሌሊቱን ሙሉ እንደ
እብድ መጮህና መጸለይ ይመስላቸዋል፡፡ ነገሩ ግን እንደዚያ አይደለም፡፡ እነርሱ
እንደሚገባው ቢተጉ እግዚአብሄር በመንፈስ ቅዱስ እሳት የሚሞላቸው
ይመስላቸዋል፡፡ ስለዚህ ስሜታቸው ሲነሳሳ ይህ የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ነው
ብለው ያስባሉ፡፡ ይህ ግን ትልቅ ስህተት ነወ፡፡ እነርሱ የተጥለቀለቁት በፍልቅ
ስሜቶቻቸው ብቻ ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ በዓለም ዙሪያ ያሉት ቅዱሳኖቻችንና
አጋር ሠራተኞቻችን በሙሉ ሙሉ በሙሉ በእምነት ራሳቸውን ለውሃውና
ለመንፈሱ ወንጌል አሳልፈው መስጠት እንደሚገባቸውና በመንፈስ ሙላት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


274 በመንፈስ መሞላት ማለት በእርግጥ ምን ማለት ነው?

መኖርም ሌላ ሳይሆን ይህ እንደሆነ በግልጥ ያስተምረናል፡፡ አሁን እኛ በዛሬው


የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ምርመራችን ይህንን ማድነቅ እንችላለን፡፡

አብልጠን በመንፈስ ቅዱስ መሞላት የምንችለው እንዴት ነው?

ወደ ኤፌሶን 5፡19-21 እንመለስ፡- ‹‹በመዝሙርና በዝማሬ በመንፈሳዊም ቅኔ


እርስ በርሳችሁ ተነጋገሩ፤ ለጌታ በልባችሁ ተቀኙና ዘምሩ፡፡ ሁልጊዜ ስለ ሁሉ
በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አምላካችንንና አባታችንን ስለ ሁሉ አመስግኑ፡፡
ለእያንዳንዳችሁ በክርስቶስ ፍርሃት የተገዛችሁ ሁኑ፡፡››
በመንፈስ ሙላት መኖር ማለት ምን ማለት ነው? እግዚአብሄር እንድንኖር
በሚፈልግብን የመንፈስ ሙላት መኖር ማለት ሌላ ሳይሆን ዘመኑን መዋጀትና
ወንጌልን ማገልገል፣ ሞኝ ከመሆን ይልቅ ጠቢብ መሆን፣ ጌታ ከእኛ የሚሻውን
መረዳትና ለራሳችን ብቻ ከመኖር ይልቅም የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
ለማገልገል ራሳችንን መቀደስ፣ በዚህ ዓለም ወይን ከመስከር ይልቅም
እግዚአብሄርን ለማስደሰት ራሳችንን ወንጌልን በማሰራጨት ሥራ ውስጥ ማጥለም
ማለት ነው፡፡ በአጭሩ በሕይወታችን ውስጥ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
ማገልገል ማለት በመንፈስ ሙላት መኖር ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ሁላችንም
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመንና እርሱንም በማገልገል በዚህ ዓለም ላይ
ልንኖር ይገባናል፡፡
በቅርብ ጊዜ ባደረግነው የመነቃቃት ስብሰባ ላይ የተገኙ አንዳንድ ሰዎች
ሰባኪው እነርሱ እንደጠበቁት ሃሌሉያ እያለ ባለመጮሁ ምክንያት በማዘናቸው
ከእንግዲህ ወዲህ እንደማይመጡ መናገራቸውን ሰምተናል፡፡ ግሩም የሆነ
የመነቃቃት ሰባኪ በሚሰብክበት ጊዜ ደጋግሞ ሃሌሉያዎችን በመጮህ
የአድማጮቹን ስሜቶች የማነሳሳት ችሎታ ያለው ሊሆን እንደሚገባ አስበው
ይሆናል፡፡ ነገር ግን ሃሌሉያዎችን መጮህ፣ ለታይታ ሲባልም ድምጽን ከፍ አድርጎ
መጸለይ ወይም በስሜት ግለት ደረትን መደቃት በመንፈስ ሙላት መኖር ማለት
አይደለም፡፡
ሁላችሁም በመንፈስ ሙላት መኖር ማለት ምን ማለት እንደሆነ ጥርት ያለ
መረዳት ይኖራችሁ ዘንድ በእጅጉ ያስፈልጋችኋል፡፡ እግዚአብሄር በሕይወታችን
ውስጥ እንዴት በመንፈስ መሞላት እንዳለብን ሲናገር በኤፌሶን 5፡19-21 ላይ
እንዲህ አለ፡- ‹‹በመዝሙርና በዝማሬ በመንፈሳዊም ቅኔ እርስ በርሳችሁ ተነጋገሩ፤

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በመንፈስ መሞላት ማለት በእርግጥ ምን ማለት ነው? 275

ለጌታ በልባችሁ ተቀኙና ዘምሩ፡፡ ሁልጊዜ ስለ ሁሉ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ


ስም አምላካችንንና አባታችንን ስለ ሁሉ አመስግኑ፡፡ ለእያንዳንዳችሁ በክርስቶስ
ፍርሃት የተገዛችሁ ሁኑ፡፡››
በመንፈስ ሙላት መኖር ማለት በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ወደዚህ ምድር
በመጣው በኢየሱስ ክርስቶስ ማመንና በሕይወታችነም ውስጥ ይህንን ወንጌል
በታማኝነት መስበክ ማለት ነው፡፡ ሁላችንም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ውስጥ
የተገለጠውን የእግዚአብሄር ጽድቅ በማመስገን በእምነት እየኖርን ነው፡፡ በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል በሚያምነው እምነታችን የምንኖረው፣ የእግዚአብሄርን ጽድቅ
የምንታመነውና የምንከተለው እግዚአብሄርንም በምስጋና የምናወድሰው ጻድቃን
በመሆናችን እንደሆነ ግልጥ ነው፡፡ እኛ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት
ዳግመኛ ስለተወለድን እርስ በርሳችን መተናነጽና በአንዱ የጋራ እምነታችን መኖር
ይገባናል፡፡ ኤፌሶን 5፡19 ‹‹ለጌታ በልባችሁ ተቀኙና ዘምሩ›› ሲል ይህ ማለት እኛ
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ስለምናውቅ በእግዚአብሄር ጽደቅ እንታመናለን፤
ለዚህም እርሱን እናመሰግናለን ማለት ነው፡፡ በዚህ መልክ መኖር በመንፈስ ሙላት
መኖር ነው፡፡
በኤፌሶን 5፡20-21 ላይ እንዲህ ተጽፎዋል፡- ‹‹ሁልጊዜ ስለ ሁሉ በጌታችን
በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አምላካችንንና አባታችንን ስለ ሁሉ አመስግኑ፡፡
ለእያንዳንዳችሁ በክርስቶስ ፍርሃት የተገዛችሁ ሁኑ፡፡›› እዚህ ላይ ጌታ የውሃውና
የመንፈሱ ወንጌል እንዲስፋፋ አንዳችን ሌላችንን እንድንገዛ ነግሮናል፡፡ ጌታ
እንዳዘዘንም ሁላችንም ካለንባቸው የሥልጣን ቦታዎች ላይ ሆነን እግዚአብሄር
በደነገገው ስርዓት መሠረት አንዳችን ለሌላችን መገዛት ይገባናል፡፡ በቤተክርስቲየን
ውስጥ ያሉት መሪዎች ተከታዮቻቸውን በሐይል ለመግዛት መሞከር የለባቸውም፡፡
ነገር ግን በፋንታው ተከታዮቻቸውን ሊያገለግሉና የእግዚአብሄርን የጽድቅ ሥራ
ለማከናወንም እርስ በርሳቸው መተባበር እንደዚሁም ሕይወታቸውን በሙሉ
ለወንጌል መስፋፋት አሳልፈው መስጠት ይገባቸዋል፡፡ በመንፈስ ሙላት መኖር
የሚችሉት እንደዚህ ነው፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ማመን፣
የእግዚአብሄርንና የክርስቶስን ፍቅር ጥልቀት፣ ስፋትና ቁመት መረዳት፣ የጌታ
ፈቃድ ለእኛ ምን እንደሆነ ማወቅና የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በዓለም ሁሉ
መስበክ ነው፡፡ በዚህ ግንዛቤ ልንኖር ይገባናል፡፡
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለመስበክና ይህንን የወንጌል አገልግሎት
ለመደገፍ የተለያዩ የንግድ ሥራዎችን እያንቀሳቀስን ነው፡፡ ለእኛ በዚህ የጽድቅ
ሥራዎች ላይ ያለንን ሁሉ ማዋል፣ ጊዜያችንን አሳልፈን መስጠትና

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


276 በመንፈስ መሞላት ማለት በእርግጥ ምን ማለት ነው?

ወጣትነታችንንም ለእነርሱ ቀድሰን መስጠት ማለት ልክ እንደ ጳውሎስ መኖር


ማለት ነው፡፡ ጳውሎስ ድንኳን በመስፋት መሠረታዊ ፍላጎቶቹን እያሟላ ወንጌልን
ሰበከ፡፡ ይህንን የጳውሎስ ድንኳን የመስፋት አገልግሎት ብለን እንጠራዋለን፡፡
አብዛኞቹ የአገልግሎት ሠራተኞቻችንም እንደዚሁ ራሳቸውን የሚደደግፉት የንግድ
ሥራዎችን በመሥራትና በእርሻ ነው፡፡ ሕይወታችን በመንፈስ ሙላት የሚመራው
እንደዚህ ነው፡፡
ዛሬ እንደ ዕድል ሆኖ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል የምትሰብክ
የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን አለች፡፡ ለዚህ ምስጋና ይሁንና እናንተና እኔም
በመንፈስ ሙላት መኖር እንችላለን፡፡ ይህ በጣም አስደሳች ነው፡፡ እናንተና እኔም
ልክ እንደ ሐዋርያው ጳውሎስ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን በልቦቻችን
ውስጥ ሙሉ የሆነ የሐጢያቶች ስርየት ተቀብለናል፡፡ ስለዚህ የክርስቶስን ፍቅር
ጥልቀት፣ ቁመትና ስፋት እናውቃለን፡፡ ከዚህ የተነሳ በኢየሱስ ክርስቶስ ፍቅር
ተማርከን በሕይወታችን ውስጥ የእግዚአብሄርን ፍቅር እያገለገልን ነው፡፡
የዚህ ዓለም ሰዎች ሙሉ በሙሉ በስጋ መሻቶቻቸው መሠረት ቢኖሩም
ማናችንም በዚህ ክፋት ውስጥ ተሳታፊ መሆን አይገባንም፡፡ የብርሃን ልጆች የሆንን
ሁላችን አንድ ላይ መተባበር፣ ዘመኑን መዋጀት፣ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
ማገልገልና ጌታን የሚያስደስቱ ነገሮችን ማድረግ ይገባናል፡፡
አንዳንድ ወንድሞቻችና እህቶቻችን ጌታ ስለሰጠን መንፈሳዊ በረከቶች
ግጥሞችን ጽፈዋል፡፡ ሌሎች ደግሞ ለእነዚህ ግጥሞች የሙዚቃ ዜማዎችን
አቀናብረዋል፡፡ ለዚህ ምስጋና ይሁንና እኛ አሁን የእግዚአብሄርን ጽድቅ ለማመስገን
አዳዲስ መዝሙሮችን እየዘመርን ነው፡፡ ሁላችንም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
ስለምናምን አንዳችን የሌላችንን እምነት እያነጽንና ወንጌልን በሕብረት ለመስበክ
እየኖርን ነው፡፡ በዚህ ወንጌል በማመን እንዲህ ለውሃውና ለመንፈሱ ወንጌል
እየኖርን ነው ማለት በእግዚአብሄር በመንፈስ ሙላት እየኖርን ነው ማለት ነው፡፡
ስለዚህ ለጌታችን ምስጋናን ሁሉ እሰጣለሁ፡፡ አሁን የሐጢያቶችን ስርየት
ስለተቀበልን ሐዋርያው ጳውሎስ ዘመኑን እንድንዋጅ መክሮናል፡፡ ይህንን ምክር
የሰጠው የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለማስፋፋት ብዙ መሠራት ስላለበት
ነው፡፡ ጳውሎስ ይህንን ሥራ ለመሥራት ዘመኑን መዋጀት እንደሚገባን የነገረን
ለዚህ ነው፡፡ አሁን እግዚአብሄር ለእኛ ያለውን ፈቃድ ሙሉ በሙሉ ወደ መረዳትና
በመንፈስ ሙላት ወደ መኖር ስለደረስን በጣም ደስተኛ ነኝ፡፡
ይህ ዓመት ከመጠናቀቁ በፊት በኑፋቄ ላይ ሁለት መጽሐፎችን
እናሳትማለን፡፡ አራተኛውንና አምስተኛውንም የመንፈሳዊ ዕድገት ቅጾቻችንን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በመንፈስ መሞላት ማለት በእርግጥ ምን ማለት ነው? 277

የማተም ዕቅድ አለን፡፡ በእነዚህ መጽሐፎች አማካይነት በዓለም ዙሪያ ሁሉ የሚገኙ


በርካታ ሰዎች የሐጢያቶቻቸውን ስርየት ተቀብለዋል፡፡ ነገር ግን ተጨማሪ በርካታ
ሰዎች ወደፊት የሐጢያቶቻቸውን ስርየት እንደሚቀበሉ እርግጠኛ ነኝ፡፡
በስጋችን ደክመቶች አልተቸገርንም? አልታሰርንም? እኛ ለዚህ ጊዜ የለንም፡፡
ዘመኑን መዋጀትና የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በዓለም ለሚኖር ለእያንዳንዱ
ሰው መስበክ አለብን፡፡ የዚህ ዓለም ሰዎች ከሐጢያቶቻቸው መዳን የሚችሉት
ይህንን ጥሪ ስንፈጽም ብቻ ነው፡፡ እኛ የሰበክነውን የእግዚአብሄር ቃል
መስማታቸው፣ በእርሱም ማመናቸውና የሐጢያቶችን ስርየት መቀበላቸው ሙሉ
በሙሉ የእነርሱ ጉዳይ ነው፡፡ እኛ ማድረግ የሚኖርብን ነገር ወንጌልን ለእነርሱ
መስበክና መጸለይ ብቻ ነው፡፡ በጉልበት በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል እንዲያምኑ
ማድረግ አንችልም፡፡ እኛ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል የመስበክና የሐጢያቶችን
ስርየት እንዲቀበሉም ለእነርሱ የመጸለይን ተግባር እየፈጸምን ነው፡፡ የዚህ ዓለም
ሰዎች እንደሚያደርጉት ጊዜያችንን ማባከን የለብንም፡፡
በትክክል የሐጢያቶችን ስርየት የተቀበለና በእምነት ጻድቅ የሆነ ሰው ሁሉ
በኢየሱስ ክርስቶስ በመታመን መኖረን ይሻል፡፡ እኛ ጌታ በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል ሐጢያቶቻችንን በሙሉ የደመሰሰ በመሆኑ የማይናወጥ እምነት እየኖርን
ነው፡፡ እግዚአብሄርን በሚያስደስት መንገድ መኖር የምንችለውና ጌታም
በእያንዳንዱ የሕይወታችን ከፍል ላይ ሙሉ በሙሉ የሚሰለጥነው በእግዚአብሄር
ጽድቅ በመታመነና እርሱንም በማገልገል ነው፡፡ ዛሬ ጌታ በመንፈስ ሙላት ይህንን
አስገራሚ ሕይወት እንድንኖር ሁላችንንም ባርኮናል፡፡ እግዚአብሄር ለሰጠን
ደህንነትና በመንፈስ የተሞላ ሕይወት በጣም አመስጋኞች ነን፡፡ እግዚአብሄር ከዚህ
የጽድቅ ሕይወት እናዳናፈነግጥ ነገር ግን ሁሌም በእርሱ እንድንኖር ስለባረከን
ይበልጥ አመስጋኞች ነን፡፡ ጌታ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ስለሰጠን ምን ያህል
አመስጋኞች እንደሆንን የምንገልጥባቸው ቃላቶች የሉም፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ በኤፌሶን 5፡16 ላይ እንዲህ አለ፡- ‹‹ቀኖቹ ክፉዎች
ናቸውና ዘመኑን ዋጁ፡፡›› ይህ የአሁኑ ዓለም ክፉ እንደሆነ ታውቃላችሁን? ከ10
ዓመታት በፊት ወንጌልን መስበክ በጣም አዳጋች እንደሚሆን ነግሬያችሁ ነበር፡፡
ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ምን ተከሰተ? ወንጌልን መስበክ ይበልጥ አስቸጋሪ እየሆነ ባለበት
ዘመን እየኖርን አይደለምን?
የሺንድለርስ ሊስት የሚለውን ሲኒማ አይታችሁታልን? ይህ ሲኒማ በ2ኛው
የዓለም ጦርነት ወቅት ናዚ ጀርመን ፖላንድን የያዘበትን ታሪክ የሚተርክ ነው፡፡
መቼቱ የሚሽከረከረው የጀርመን ወታደሮች የሚፈጽሙትን ግፎች አይቶ እንዳላየ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


278 በመንፈስ መሞላት ማለት በእርግጥ ምን ማለት ነው?

የሚሆንበትን ጨምሮ የራሱን ስኬት ለማረጋገጥ ማንኛውንም ነገር ለማድረግ


ፈቃደኛ ስለሆነ አንድ አጋጣሚውን የሚጠብቅ ኦስካር ሺንድለር በተባለ ነጋዴ
ዙሪያ ነው፡፡ ሺንድለር በፖላንድ ከተማ ውስጥ የሚገኝ አንድ ፋብሪካ ለመውረስ
ከናዚ ፓርቲ አባል ከመሆን ጀምሮ በሐላፊነት ቦታ ላይ ያሉትን ወታደራዊ
ባለሥልጣኖች በጉቦ እስከ ማባባል ድረስ ሁሉንም ዓይነት አስቀያሚ ነገሮችን
ተጠቅሞዋል፡፡ ነገር ግን ስተርን ከተባለ አንድ አይሁዳዊ አካውንታንት ጋር ሲገናኝ
የሕሊናው ድምጽ የአይሁዶችን እልቂት እየተቃወመ ሲናገረው መስማት ጀመረ፡፡
በእርሱ ፋብሪካ ውስጥ ያሉት አይሁዶች በኦሽዊትዝ ወደሚገኘው የጋዝ
እልፍኝ ሲወሰዱ እንደሆነ ሲያውቅ በመጨረሻ ሊያድናቸው ወሰነ፡፡ የጀርመን
ባለሥልጣኖችን በራሱ ገንዘብ ጉቦ እየሰጠ በማባበል የሚቻለውን ሁሉ ብዙ
አይሁዶችን ለማስመለጥ ካቀደ በኋላ እርሱና ስተርን ሊድኑ የሚገባቸውን
አይሁዶች ዝርዝር አወጡ፡፡ ይህም የሺንድለር ዝርዝር በመባል ታወቀ፡፡
በመጨረሻም ከ1,100 በላይ አይሁዶች ማዳን ቻለ፡፡ ጦርነቱ በጀርመን ሽንፈት
ሲያበቃ ሺንድለር ቀለበቱን በጥልቅ ጸጸት ተመልክቶ ‹‹ይህንን ቀለበት ሸጬው
ቢሆን ኖሮ ተጨማሪ ጥቂት አይሁዶችን ማዳን በቻልሁ ነበር›› አለ፡፡ እነዚህ ቃሎች
በአእምሮዬ ውስጥ የማይፋቅ አቅም አስቀምጠዋል፡፡
እኛ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለመስበክ ይህንን አገልግሎት ለመደገፍ
እየሰራነው ባለነው ትጉህ ሥራ ምክንያት አሁን በመላው ዓለም የሚገኙ በርካታ
ሰዎች እየዳኑ ነው፡፡ እየዳኑ ያሉት ጥቂቶች ብቻ አይደሉም፡፡ በተቃራኒው
ለጥረታችን ምስጋና ይሁንና እየዳኑ ያሉት ሰዎች ቁጥር ከምናስበው በላይ የላቀ
ነው፡፡ እስከዛሬ እንዳደረግነው በዚህ መልኩ ወንጌልን ማገልገልና መስበክ
ከቀጠልን ተጨማሪ በርካታ ሰዎች የሐጢያቶችን ስርየት ይቀበላሉ፡፡ ነገር ግን
ረክተን ከተቀመጥንና ጥረታችንን ሁሉ ለዚህ ውጥን አሳልፈን ካልሰጠን ብዙ ሰዎች
ዕድሉ ያመልጣቸዋል፡፡ ያን ጊዜ ሺንድለር በሲኒማው መጨረሻ ላይ በጸጸት
እንዳዘነ ሁሉ እኛም በዚህ ያለፈ ዕድል እንጸጸታለን፡፡
አንድ ጊዜ ታላቁ መከራ በዚህ ምድር ላይ ከመጣ ወንጌልን መስበክ
አይቻለንም፡፡ ጦርነት ሲፈነዳ ዳግመኛ የኢንተርኔት (በይነ መረብ) ግንኙነት
አይኖረንም፡፡ ያን ጊዜ ራሳችንን በአገራችን ውስጥ ከመገደብና የውሃውንና
የመንፈሱንም ወንጌል በቅርብ ላሉት የቤተሰብ አባሎቻችን ከመስበክ በቀር ምርጫ
አይኖረንም፡፡ ይህ ሲሆን በጸጸት እንሞላለን፡፡ መሥራት ስንችል በነበረበት ጊዜ
ይበልጥ በትጋት ልንሰራ ይገባን እንደነበር እንመኛለን፡፡ ዳግመኛ መሥራት
የማንችልበት ጊዜ በቅርቡ ይመጣል፡፡ የእግዚአብሄርን ሥራ መሥራት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በመንፈስ መሞላት ማለት በእርግጥ ምን ማለት ነው? 279

በምንችልበት ጊዜ መሥራቱ ለሁላችንም አስፈላጊ እንደሆነ ለእናንተና ለእኔ


ለአገልጋዮቻችንም አበክሬ እየተናገርሁ ያለሁት ለዚህ ነው፡፡
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለመሰበክ ሁላችንም በክርስቶስ ፍርሃት
አንዳችን ለሌላችን እንድንገዛና እግዚአብሄር በደነገገው ስርዓት በእምነት እንድንኖር
ይገባናል፡፡ ለወንጌል መኖር ያለብን ገና ወደፊት ሳይሆን አሁኑኑ በዚህች ቅጽበት
ነው፡፡ አሁን እየኖርንበት ያለነው ይህ የአሁኑ ዘመን ወደ ፍጻሜው እየሮጠ ነው፡፡
የአማዞንን ወንዝ የሥነ ተፈጥሮ ችግሮች እያሰጉት እንደሆነ ሁላችሁም
ለመስማታችሁ እርግጠኛ ነኝ፡፡ አማዞን በዓለም እጅጉ ትልቁ ወንዝ ነው፡፡ ነገር
ግን በቅርብ ጊዜ በተከሰቱ ድርቆች ከቀድሞው ክብሩ ቀንሶ ፍሰቱ በአስደንጋጭ
ሁኔታ እንደወረደ ተነግሮዋል፡፡ የአማዞን ወንዝ እንዲህ ባሉ ድርቆች እንዴት
እየደረቀ እንዳለና በአንድ ወቅት በዓለም ዝናብን የሚስብ እጅግ ትልቁ የትሮፒካል
ጫካ የሆነው የአማዞን ጫካ እየወደመ እንደሆነ ስንሰማ የዓለም የአየር ንብረት
ለውጥ ምን ያህል አሳሳቢ እንደሆነ ማየት እንችላለን፡፡ ይህች ፕላኔት ምድር
አውዳሚ ረሃቦች፣ ጎርፎች፣ የምድር መናወጦችና ወረርሽኞች ሊገጥሙት
እንደተቃረቡ ማንም ሰው ከእነዚህ አስጨናቂ ሁኔታዎች ተነስቶ መገመት
ይችላል፡፡ ወደ ዮሐንስ ራዕይ መጽሐፍ ስንመለስ መጽሐፍ ቅዱስ በዓለም ላይ
ያሉት ሲሶ ዛፎች እንደሚቃጠሉ ሲተነብይ እናያለን፡፡ ዓለም በረሃቦች፣ በጎርፎችና
በመሬት መናወጦች ትመታለች፡፡ ከእነዚህ የተፈጥሮ ጥፋቶች ጋርም አብሮ ጦርነት
ይፈነዳል፤ የክርስቶስ ተቃዋሚም ይገለጣል፡፡
እነዚህ ኩነቶች በቅርቡ ቢገለጡም እኛ ግን ፈጽሞ አንታወክም፡፡
ምክንያቱም ቀድሞውኑም በጥበብ ለእነዚህ ኩነቶች ሁሉ ተዘጋጅተናልና፡፡ እነዚህ
ጥፋቶች በዚህ ዓለም መሆናቸው የማይቀር ፍጻሜ እንደሆኑ እናውቃለን፡፡ ስለዚህ
ሳንረበሽ በመንፈስ ሙላት እንኖራለን፡፡
አሁንም ገና በጣም አልረፈደም፡፡ ጥፋቶች በፍጥነት እየበዙ ቢሆንም ይህ
ዓለም ፈጥኖ አይጠፋም፡፡ በመላው ዓለም ላይ ግዙፍ የመሬት መናወጦች
ሲከሰቱና ከሕዝቡም ገሚሱ ሲጠፋ፣ ታላቁ መከራ መከሰቱ ሲታወቀንና ስናይ ያን
ጊዜ ክርስቶስ ፈጥኖ እንደሚመጣ ልንጠብቅ ይገባናል፡፡ ምንም ነገር ቢፈጠር
እስከቻልን ድረስ ወንጌልን በመስበክ መቀጠል ይገባናል፡፡ እዚህ ላይ ለጥሪያችን
የሚገባውን ያህል ታማኞች እንዳልሆንን መናገሬ አይደለም፡፡ ሁላችንም በትጋትና
ያለ መታከት ለጌታ ሰርተናል፡፡ ይልቁንም ቁም ነገሬ እስከ ዛሬ ደረስ እንደሰራነው
በትጋት መሥራችንን መቀጠል ይገባናል ነው፡፡
እግዚአብሄርን ከማንኛውም ሌላ ነገር ይልቅ የማመሰግነው እርሱ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


280 በመንፈስ መሞላት ማለት በእርግጥ ምን ማለት ነው?

የሚወደውን ሥራ መሥራት መቻላችን ነው፡፡ ይህንን የጽድቅ ሥራ ከማንም ጋር


ሳይሆን ከእናንተ ከአጋር ሠራተኞቼ ጋር መሥራት በመቻሌም በእጅጉ አመስጋኝ
ነኝ፡፡ እግዚአብሄር ስለጠበቀንና ወንጌልንም እስከዚህች ቀን ደረስ እንድናገለግል
ስለባረከን ምን ያህል አመስጋኝ እንደሆንሁ ቃላቶች አይገልጡትም፡፡
የዛሬውን ስበከት እያንዳንዱ የእግዚአብሄር በረከት ወንጌልን ከምናገለግልና
በመንፈስ ሙላት ከምንኖረው ከሁላችን ጋር እንዲሆን በመመኘት
አጠናቅቃለሁ፡፡ 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ስብከት
15

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት
ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
በመንፈስ ሙላት የሚኖሩ ሰዎች
‹‹ ኤፌሶን 5፡15-21 ››
‹‹እንግዲህ እንደ ጥበበኞች እንጂ ጥበብ እንደሌላቸው ሳይሆን እንዴት
እንደትመላለሱ በጥንቃቄ ተጠበቁ፡፡ ቀኖቹ ክፉዎች ናቸውና ዘመኑን ዋጁ፡፡ ስለዚህ
የጌታ ፈቃድ ምን እንደሆነ አስተውሉ እንጂ ሞኞች አትሁኑ፡፡ መንፈስ ይሙላባችሁ
እንጂ በወይን ጠጅ አትስከሩ፤ ይህ ማባከን ነውና፡፡ በመዝሙርና በዝማሬ
በመንፈሳዊም ቅኔ እርስ በርሳችሁ ተነጋገሩ፤ ለጌታ በልባችሁ ተቀኙና ዘምሩ፡፡
ሁልጊዜ ስለ ሁሉ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አምላካችንንና አባታችንን ስለ
ሁሉ አመስግኑ፡፡ ለእያንዳንዳችሁ በክርስቶስ ፍርሃት የተገዛችሁ ሁኑ፡፡››

የዚህ ዓመት የደቀ መዛሙርትነት ሥልጠና ካምፕ ያበቃው በቅርቡ ነው፡፡


በዚህ በመጪው ረቡዕ ለሥነ ጽሁፍ አገልግሎታችን የተለየ የአምልኮ አገልግሎት
እናደርጋለን፡፡ በዚህ ዓመት በሁለተኛው አጋማሽ ላይ የምናደርገውን የሥነ ጽሁፍ
አገልግሎት ለመደገፍም በዚህ በመጪው እሁድ የገንዘብ ስለት እንሳላለን፡፡
ሁላችሁም በደምብ እንደምታውቁት ይህ አገልግሎት ብዙ ገንዘብ ይጠይቃል፡፡
ነገር ግን ከልባችን ወደ እርሱ ብንጸልይ እግዚአብሄር ሁሉንም ነገር እንደሚያሟላ
እርግጠኛ ነኝ፡፡ በዚህ በመጪው ረቡዕ እግዚአብሄርን ስለ ገንዘብ በተለይም የሥነ
ጽሁፍ አገልግሎታችንን እንዲደጉም ለመጠየቅ የተለየ የጸሎት ጉባኤ የምናደርገው
ለዚህ ነው፡፡ ማንኛውም ሰው ለረጅም ጊዜ ተመሳሳይ ሥራ ከሠራ በኋላ
በእግዚአብሄር ሥራ ቸልተኛ ሊሆን ወይም ሊሰንፍ ይችላል፡፡ ስለዚህ ከስልቹነቱ
ለመውጣትና ትኩረታችንን ለማደስ አዲስ ግብ ማቀዳችን ተገቢ ነው፡፡ በዚህ
ምክንያት ስንፍና ውስጥ እንዳንወድቅ አዳዲስ የሚሽን ግቦች እናቅዳለን፡፡ በዓመት
ሁለቴም የገንዘብ ስለት እንሳላለን፡፡
ለዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ኤፌሶን ምዕራፍ 5ን አንብበናል፡፡ በቅርቡ
አብዝቼ የኤፌሶንን መልዕክት እየሰበክሁ በመሆኔ ሰብከት በምሰብክበት ጊዜ ሁሉ
ሁሌም ምንጬ የኤፌሶን መልዕክት ይመስላል፡፡ ከዚህ መልዕክት መስበኬን
የምቀጥለው የመልዕክቱን ትምህርቶች በልባችሁ ውስጥ አጽንቼ መትከል
ስላልቻልሁ ነው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


284 በመንፈስ ሙላት የሚኖሩ ሰዎች

በመንፈስ የተሞላ ሕይወት ሲብራራ፡፡

በዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ላይ የጎላ አንድ የተለየ ጥቅስ አለ፡፡


እርሱም ኤፌሶን 5፡18 ነው፡፡ ‹‹መንፈስ ይሙላባችሁ እንጂ በወይን ጠጅ አትስከሩ፤
ይህ ማባከን ነውና፡፡›› በመንፈስ ቅዱስ መሞላት ማለት ለእናንተ ምን ያህል ያህል
መልካም ነው?
ሰዎች ሲሰክሩ ከተለመደው ባህሪያቸው ወጣ ብለው የተለየ ድርጊት
ያደርጋሉ፡፡ አንዳንድ ሰዎች ደጋግመው ተመሳሳይ ነገር ይናገራሉ፤ ሌሎች
ማንጎራጎራቸውን ይቀጥላሉ፤ ሌሎችም ደግሞ ከማንም ሰው ጋር ጠብ የለሽ በዳቦ
ይሞክራሉ፡፡ ስለዚህ ሰዎች ሲሰከሩ የተለመደ ማንነታቸውን ያጣሉ፡፡
ሆኖም መጽሐፍ ቅዱስ እዚህ በኤፌሶን 5፡18 ላይ በግልጥ እንዲህ ይላል፡-
‹‹መንፈስ ይሙላባችሁ እንጂ በወይን ጠጅ አትስከሩ፤ ይህ ማባከን ነው፡፡›› በመንፈስ
መሞት አለብን ማለት ቃል በቃል ልቦቻችን በእግዚአብሄር መንፈስ ሙሉ በሙሉ
መመራትና መገዛት አለባቸው ማለት ነው፡፡ በሌላ አነጋገር ይህ ምንባብ የክርስቶስን
ሕይወት መንፈስ ቅዱስ በተሰጠ ደስታ፣ ሥልጣንና በረከቶች ውስጥ ሆነን
እንድንከተል ሁላችንንም መክሮናል፡፡ ስለዚህ በመንፈስ መሞላት በመንፈስ መገዛት
ነው፡፡ ይህ ማለት አእምሮዋችንና ሕይወታችን በራሳችን ሰብዓዊ ዕውቀት እንዲመሩ
መፍቀድ ማለት ነው፡፡ በመንፈስ ሙላት መኖር ማለት በራሳችን በስጋዊ መሻቶች
ከመኖር ይልቅ እንደ እግዚአብሄር ፈቃድ መኖር ማለት ነው፡፡
በእርግጥ በመንፈስ ሙላት መኖር የምትፈልጉ ከሆነ እግዚአብሄርን
በሚያስደስት መንገድ መኖር አለብን፡፡ መንፈስ ቅዱስ በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል በምናምን በሁላችንም ልቦች ውስጥ ስለሚኖር ራሳችንን ለዚህ መንፈስ
ማስገዛትና እንደ በጎ ፈቃዱም እርሱን በመታዘዝ መከተል ይገባናል፡፡
እርሱን የሚያስደስተውን ሕይወት ለመኖር በእግዚአብሄር ፊት
ሕይወታችሁን መኖር የሚገባችሁ እንዴት ነው? ራሱ አምላክ የሆነው ኢየሱስ
ክርስቶስ ወደዚህ ምድር በመጣ ጊዜ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የእናንተንና
እኔን ሐጢያቶች በሙሉ ደምስሶዋል፡፡ አሁን እናንተና እኔ በዚህ እውነት
ስለምናምን ሁላችንንም ያዳነውን ይህንን እምነታችንን በዓለም ሁሉ ማስፋፋት
አለብን፡፡ በመንፈስ ሙላት መኖር ማለት በተጨባጭ ይህንን ማለት ነው፡፡
እግዚአብሄር በመንፈስ እንድንሞላ ሲነግረን ሕይወታችንን በሙሉ ለወንጌሉ
ስብከትና ለነፍሳቶች ደህንነት አሳልፈን እንድንሰጥ እየነገረን ነው፡፡
በሮሜ 8፡5-6 ላይ እንዲህ ተጽፎዋል፡- ‹‹እንደ ሥጋ ፈቃድ የሚኖሩ የሥጋን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በመንፈስ ሙላት የሚኖሩ ሰዎች 285

ነገር ያስባሉና፤ እንደ መንፈስ ፈቃድ የሚኖሩ ግን የመንፈስን ነገር ያስባሉ፡፡ ስለ


ሥጋ ማሰብ ሞት ነውና፤ ስለ መንፈስ ማሰብ ግን ሕይወትና ሰላም ነው፡፡›› በዚህ
ምንባብ ውስጥ ሁለት ዓይነት ሕይወቶች ተገልጠዋል፡፡ አንዱ እንደ ሥጋ የሚኖር
ሲሆን ሌላው እንደ መንፈስ የሚኖር ነው፡፡

ስጋንና አስተሳሰቦቹን መከተል ማለት ምን ማለት ነው?

ይህ የሚያሳየው በሰው የስጋ መሻት መሠረት የሚኖረውን ሕይወት ነው፡፡


ስጋቸውን የሚወዱ ሰዎች ወደ ስጋዊ አሰተሳሰቦቻቸው ይሳባሉ፡፡ ከልቦቻቸው
የሚፈልቁትንም መሻቶች ይከተላሉ፡፡ በራሳቸው ስጋዊ ስሜቶች ውስጥም
ይጠልቃሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች የሚከተለውን ያስባሉ፡፡ ‹‹በሕይወቴ ውስጥ
የምወደውን ሁሉ ማድረግ እፈልጋለሁ፡፡ ብዙ ገንዘብ ማግኘት፣ ዓለምን ሁሉ
መዞርና ልቤን ለማርካትም በሕይወቴ መደሰት እሻለሁ፡፡ ማንም ሰው በራሴ
ጉዳዮች ውስጥ ሳይገባብኝ በነጻነት መኖር እፈልጋለሁ፡፡ እያንዳንዱን ነገርና
ማንኛውንም ነገር መሞከር እሻለሁ፡፡ ማንም አፉን ቢከፍት ግድ የለኝም፡፡ ማድረግ
የምችለውን ማንኛውንም ነገር ማድረግ እመኛለሁ፡፡›› በእነዚህ ስጋዊ አስተሳሰቦች
መሠረት የምትኖሩ ከሆነ ሕይወታችሁ እንደ ስጋ ፈቃድ የሚኖር ነው፡፡
ሆኖም አጋር ምዕመናኖቼ በዚህ መልክ የራስን አስተሳሰቦች መከተል
በእግዚአብሄር ፊት አስከፊ ሐጢያት ነው፡፡ ሰጋዊ አስተሰሰቦቻችሁን የምትከተሉ
ከሆናችሁ የመንፈስን አሳቦች መከተል አትችሉም፡፡ ስለዚህ መጨረሻችሁ
የእግዚአብሄር ፈቃድ አለመታዘዝና የእርሱን ጠላትነት ማከማቸት ነው፡፡ የስጋን
መሻቶች መከተል በእግዚአብሄር ፊት አስከፊ ሐጢያትን መሥራት ነው፡፡ የገዛ
ስጋውን የሚከተል ማንኛውም ሰው የእግዚአብሄርን ሕግ እየጣሰ ነው፡፡
እኛ በመንፈሱ ወንጌል በማመን የሐጢያቶችን ስርየት ብንቀበልም አንዳንድ
ጊዜ ስጋዊ አስተሳሰቦቻችን ውስጥ መውደቅ ወይም ስጋን መከተል አይቀርልንም፡፡
ነገር ግን ስጋ ውስጥ ጠልቀን እንዳንገባና ይህንን ስጋዊ ሕይወት እንዳንኖር
የሚከለክለን አመቺ ዘዴ አለ፡፡ ይህም በውስጣችን የሚኖረው መንፈስ ቅዱስ
ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስ ጌታችንና ሞግዚታችን ሆኖ በልቦቻችን ውስጥ ሲያድር
ስጋችንን ለመከተል በምንፈልግበት ጊዜ ሁሉ ልቦቻችንን ይወቅሳል፡፡ ከዚህ
የተነሳም ስጋን በመከተል መቀጠል ልንሸከመው የማንችለው ይሆንብናል፡፡
ለመመለስና እምሮዋችንንም በመንፈስ ነገሮች ላይ ለማኖር እንገደዳለን፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


286 በመንፈስ ሙላት የሚኖሩ ሰዎች

እኛ ሁለት ጌቶች አሉን፡፡

ከሁለቱ ጌቶቻችን አንዱ ስጋዊ መሻት ሲሆን ሌላው ጌታ ደግሞ መንፈስ


ቅዱስ ማለትም የእግዚአብሄር መንፈስ ነው፡፡ በውስጣችን ያሉት እነዚህ ሁለቱ
ጌቶች እያንዳንዳቸው ከእኛ የተለያዩ ነገሮችን ይጠይቃሉ፡፡ መንፈስ ቅዱስ እንዲህ
ይለናል፡- ‹‹እኔ ባዘዝኋችሁ መሠረት እግዚአብሄርን የሚያስደስተውን ይህንን ሥራ
ሥሩ፡፡ ያን ጊዜ ደስታ፣ ሰላምና በረከቶችን እሰጣችኋለሁ፡፡ የጽድቅን ፍሬ
እንድታፈሩም አረጋግጥላችኋለሁ፡፡ ስጋችሁ ግን ዝም ብሎ አይቀመጥም፡፡ እንዲህ
ይላችኋል፡- ‹‹እኔን አድምጡኝ፤ ደስታንም እሰጣችኋለሁ፡፡ ይህ ደስታ በኋላ
በባዶነት ስሜት ይተካል፡፡ ነገር ግን ያን ያህል መጥፎ አይደለም፡፡ ምክንያቱም ይህ
የሚታወቃቸው ከመጀመሪያውም ደስ ያላቸው ሰዎች ናቸው፡፡ እኔ የምነግራችሁን
የምታደርጉ ከሆነ ደስተኞች ትሆናላችሁ፡፡ ስለዚህ የማዝዛችሁን አድርጉ፡፡›› ያን
ጊዜ ከሁለቱ ጌቶች በሚመጡት በእነዚህ ጥያቄዎች መካከል ሆነን እንሰቃያለን፡፡
ምን እንደምናደርግም አናውቅም፡፡ ማንን እንደምንታዘዝ ወሳኝ የሆነ ጥያቄ
ይገጥመናል፡፡
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የምናምን ሁላችን የመንፈስ ቅዱስን ምሪት
መከተል እንደሚገባን ግልጥ ነው፡፡ ነገር ግን ችግሩ በመካከላችን አንዳንድ ጊዜ
የስጋቸውን ምሪቶች መታዘዝና መከተል የሚመርጡ አንዳንድ ሰዎች መኖራቸው
ነው፡፡ ሆኖም እነዚህ ሰዎች ስጋዊ ፍላጎታቸውን ሲከተሉ መጨረሻቸው ሐጢያትን
መሥራት ስለሚሆን ልቦቻቸው ይታወካሉ፡፡ ደስታቸውንም ያጣሉ፡፡ ውለው
አድረውም ስጋዊ ፍላጎታቸውን በመከተል ያገኙት ቅጽበታዊ ደስታና እርሱን
ተከትሎ የሚመጣውም ስቃይ ዘላቂ እንደሆነ ይገነዘባሉ፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ
እንዲህ ያለው ለዚህ ነው፡- ‹‹መንፈስ ይሙላባችሁ እንጂ በወይን ጠጅ አትስከሩ፤
ይህ ማባከን ነውና፡፡›› (ኤፌሶን 5፡18) ስጋውን የሚከተል ማንኛውም ሰው
በመጨረሻ የሚገጥመው ነገር መከራ ነው፡፡ ስለዚህ እግዚአብሄር ሁላችንንም
በመንፈስ ሙላት እንድንኖር መክሮናል፡፡

መንፈስ ይሙላባችሁ እንጂ በወይን ጠጅ አትስከሩ፡፡

ዛሬ በዚህች ሰዓት የመንፈስ ሙላት ላይ ለመድረስ ምን ማድረግ


እንደሚኖርብን በስፋት ማብራራት እወዳለሁ፡፡ እናንተና እኔ ክርስቲያኖች ነን፡፤

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በመንፈስ ሙላት የሚኖሩ ሰዎች 287

እናንተና እኔ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ስለምናምን የእግዚአብሄር ሐጢያት


አልባ ልጆችና የእርሱ ሠራተኞች ሆነናል፡፡ እኛ እንደዚህ ዓይነት ሰዎች ስለሆንን
በመንፈስ ቅዱስ የተሞላ ትክክለኛ ሕይወት ለመኖር ሁላችንም ምን ማድረግ
እንደሚገባን በግልጥ ማወቅ ያስፈልገናል፡፡ እዚህ ላይ ለመድረስ በመጀመሪያ
ሁላችንም በተፈጥሮ ስጋችንን የመከተል ዝንባሌ እንዳለን መገንዘብ አለብን፡፡ እኛ
ትኩረታችንን በመንፈስ ምሪት መኖር ላይ ማድረግ የምንችለው አብዛኛውን ጊዜ
ራሳችን ስጋዊ አስተሳሰቦች ውስጥ እንደምንወድቅ በመገንዘብ ብቻ ነው፡፡
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን የሐጢያቶችን ስርየት ብትቀበሉም
አሁንም በአንድ ወይም በሌላ መንገድ ስጋዊ መሻቶቻችሁን አትከተሉምን? እኛም
ራሳችን ብዙ ስጋዊ መሻቶች እንዳሉብንና በእነርሱ ውስጥም እንደምንወድቅ
ብንገነዘብ በእጅጉ ያስፈልገናል፡፡ ምክንያቱም የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል እውነት
ምን ያህል ክቡር እንደሆነና እኛም ለእርሱ ምን ያህል ታማኝ መሆን እንደሚገባን
መረዳት የምንችለው ያን ጊዜ ነው፡፡ ለሰማያዊው ሊቀ ካህናችን ለኢየሱስ ምስጋና
ይሁንለትና በእምነታችን ምክንያት ከእርግማኖቻችን ሁሉ ለማምለጥ ተባርከናል፡፡
በዚህ የተነሳ አሁን መንፈሳዊ ተሐድሶ ሆኖልናል፡፡ ነገር ግን ስጋችን አሁንም
ስለሚሰራ ስለ ስጋ ለማሰብ እናዘነብላለን፡፡ በመሆኑም አንዳንድ ጊዜ ራሳችንን
ከእግዚአብሄር ፈቃድ ፈጽሞ ተቃራኒ በሆነ መንገድ ሲያሰብ እናገኘዋለን፡፡ ስለዚህ
በማንኛውም ጊዜ ሐጢያት ልንሰራ እንደምንችል በማመን ለሁላችንም በእጅጉ
አስፈላጊ ነው፡፡
ይህ ምን ማለት ነው? ይህ ማለት ሁላችንም በተፈጥሮዋችን ስጋችንን
ለመከተል ስለምናዘነብል የእግዚአብሄርን ትዕዛዛቶች ከመከተል ርቀን እነዚህን
ትዕዛዛቶች ላንታዘዛቸውና ልንጥሳቸው እንችላለን፡፡ ነገር ግን እኛ እግዚአብሄር
የሰጠውን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ስለተቀበልን ሐጢያት በምንሰራበት ጊዜ
ሁሉ ይህንን ወንጌል እናስባለን ወይም እናሰላስላለን፡፡ እግዚአብሄር ራሱ
‹‹የሐጢአት ደመወዝ ሞት ነው›› (ሮሜ 6፡23) ስላለ በሐጢያቶቻችን መሞት
እንደነበረብን እናውቃለን፡፡ ስለዚህ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል አብልጠን
ልንወድደው እንችላለን፡፡
እንዲህ ተብሎ ተጽፎዋል፡- ‹‹ከሥጋ የተነሳ ስለደከመ…እግዚአብሄር የገዛ
ልጁን በሐጢአተኛ ሥጋ ምሳሌ በሐጢአትም ምክንያት ልኮ አድርጎአልና፤…
ሐጢአትን በሥጋ ኮነነ፡፡›› (ሮሜ 8፡3) ሁላችንም ለሐጢያቶቻችን ለመሞት
ተመድበን እንደነበር ማመንና መናዘዝ ይኖርብናል፡፡ ከዚህም በላይ እኛ ራሳችን
ልንሸከመው ከሚገባን የሐጢያቶቻችን ኩነኔ ለማምለጥም በመጀመሪያ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


288 በመንፈስ ሙላት የሚኖሩ ሰዎች

ሐጢያቶቻችንን በሙሉ መደምሰስ ነበረብን፡፡ ነገር ግን ምንም ያህል ተግተን


ብንሞክርም ይህንን መከወን አልቻልንም፡፡ የሐጢያት ኩነኔ እኛ ራሳችን በፍጹም
ልናስወግደው የማንችለው ነገር ነው፡፡ የእግዚአብሄር ልጅ የሆነው ኢየሱስ
ክርስቶስ በውሃውና በመንፈሱ እውነት ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ለአንዴና
ለመጨረሻ የደመሰሰው ለዚህ ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ለእኛ ሲል ወደዚህ ምድር
የመጣው ለዚህ ነው፡፡ በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅም ሐጢያቶቻችንን በሙሉ
መሸከም ነበረበት፡፡ እኛ ሁሌም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምን ይህ
እምነት ሊኖረን ይገባል፡፡
ኢየሱስ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል አማካይነት ለአንዴና ለመጨረሻ
ከዓለም ሐጢያቶች ሁሉ አድኖናል፡፡ ስለዚህ በዚህ እውነተኛ ወንጌል የምናምን
ሁላችን አሁን ሐጢያት አልባ ነን፡፡ እግዚአብሄር እኛ የማንችለውን በትክክል
አከናውኖታል፡፡ እኛ ከሙሉ ልቦቻችን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል እናምናለን፡፡
ጌታ ‹‹እኔ አምላካችሁ ነኝ፤ ከሐጢያቶቻችሁም ሁሉ አድኛችኋለሁ፡፡ የተሸከምሁት
የእናንተን ሐጢያቶች ብቻ ሳይሆን የሰውን ዘር ሁሉ ሐጢያቶችም ነው፡፡ የእናንተን
ሐጢያቶች ሁሉና በዚህ ዓለም ላይ የሚኖረውን የእያንዳንዱን ሰው ሐጢያቶች
በሙሉ ወስጃለሁ፡፡ ስለዚህ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል እመኑና በመንፈስ ቅዱስ
ተሞሉ›› ይለናል፡፡ ታዲያ በጣም ብዙ ሰዎች በእነርሱ ምትክ በመስቀል ላይ
በመሞትና ዳግመኛም ከሙታን በመነሳት ሐጢያቶቻቸውን ሁሉ በተሸከመላቸው
በኢየሱስ ጽድቅ ለማመን እምቢተኞች የሚሆኑት ለምንድነው? ለዚህ ምክንያቱ
አነዚህ ሰዎች የእግዚአብሄርን ፈቃድ ከመከተል ይልቅ የራሳቸውን ስጋዊ
አስተሳሰቦች ስለሚከተሉ ነው፡፡
አምላካችን መንፈሳዊ ምልሰትን የሚሹ ሰዎችን እየጠራ ነው፡፡ በሌላ አነጋገር
እግዚአብሄር እርሱ በሰጠን የውሃና የመንፈስ ወንጌል በማመን ልቦቻችንን
እንድናድስ እየመከረን ነው፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ላይ ባለን እምነታችን
አማካይነት ልቦቻችንን እንድናድሰ እየነገረን ነው፡፡ በዚህ እምነት አሳባችንን
በመንፈስ ነገሮች ላይ እናኖራለን፡፡ ሁላችንም የሐጢያቶችን ስርየት መቀበልና
የመንፈስ ሙላት ላይ መድረስ የምንችለው በእግዚአብሄር ቃል በማመን ብቻ
ነው፡፡
ጌታ በአንድ ጊዜ ያነጻው የእኛን ሐጢያቶች ብቻ ሳይሆን በዚህ በመላው
ዓለም ላይ የሚኖረውን የእያንዳንዱን ሰው ሐጢያቶችም በሙሉ ነው፡፡ ስለዚህ
ሰብዓዊ ፍጥረቶች በሙሉ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን ልቦቻቸው
ከአመዳይ ይልቅ ሙሉ በሙሉ ነጽተው ማየት ይችላሉ፡፡ ልቦቻችን ሁሉም

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በመንፈስ ሙላት የሚኖሩ ሰዎች 289

በመንፈስ ቅዱስ ተሞልተው ማየት የምንችለው የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል


በልቦቻችን ውስጥ በመቀበል ነው፡፡ ጻድቃን ልቦቻቸው በመንፈስ ቅዱስ መሞላቱን
በማረጋገጥ የእግዚአብሄርን ትዕዛዛት አብልጠው በታማኝነት መከተል ይችላሉ፡፡
ጻድቃን ራሳቸው ከእንግዲህ ወዲህ በሐጢያቶቻቸው የታሰሩ ስላይደሉ ሌሎችን
የሚታገሱና የሚያከብሩ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ወንጌልንም ደግሞ ለእነርሱ
ሊሰብኩላቸው ይችላሉ፡፡ ያን ጊዜ አብልጠው ደግሞ በመንፈስ ቅዱስ ይሞላሉ፡፡
በዚህ ዓለም ላይም ደስተኛ በሆነ ልብ ይኖራሉ፡፡ በሕይወት ዘመናቸውም ሁሉ
የእግዚአብሄርን ፍቅር ይቀበላሉ፡፡ የእግዚአብሄርን ክቡር ሥራ ለመሥራት
የምንጠየቀው እንዲህ ነው፡፡ እኛ ጻደቃኖች ይህንን ስናደርግ ልቦቻችን ይደሰታሉ፡፡
ሐሴትም ያደርጋሉ፡፡ ስለዚህ ስጋችንን ከመከተል ይልቅ በመንፈስ ሙላት
መኖራችን በእጅጉ አስደሳች ነው፡፡ ሁሌም የጌታን ፈቃድ እንድንከተል፣ የእርሱን
ሥራ በየቀኑ እንድንሰራ፣ ራሳችንንም ሁሌም ለእርሱ ማስገዛት የምንገደደው ለዚህ
ነው፡፡ በመንፈስ ሙላት መኖር ማለት ሌላ ሳይሆን ይህ ነው፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ ‹‹ስለ ሥጋ ማሰብ ሞት ነው፤ ስለ መንፈስ ማሰብ ግን
ሕይወትና ሰላም ነው›› (ሮሜ 8፡6) በማለት አሳባችንን በእግዚአብሄር ሥራ ላይ
እንድናደርግ አስተምሮናል፡፡ አሳባችንን በእግዚአብሄር ሥራ ላይ ካኖርን ያን ጊዜ
ሁላችንም በእግዚአብሄር ብርሃን ውስጥ መኖር እንችላለን፡፡ እግዚአብሄር የእኛን
ሐጢያቶች ብቻ ሳይሆን በዚህ ዓለም ላይ ያለውን የእያንዳንዱን ሰው ሐጢያቶችም
በሙሉ እንዴት አንደመሰሰ ስናስብ በእርሱ ያለንን እምነት ለማደስ የእግዚአብሄር
ጽድቅ ይታወሰናል፡፡ ስለዚህ ልቦቻችን ይታደሳሉ፡፡ ሁላችንም የእርሱን
የተትረፈረፉ በረከቶች መቀበልና የእርሱን ሥራ በመስራትም ደስታውንና ሰላሙን
ማጣጣም በመቻላችን በእጅጉ እግዚአብሄርን አመሰግነዋለሁ፡፡ እግዚአብሄር
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል እንድናምንና ሁሌም በመንፈስ ሙላት እንድንኖር
ስለባረከን ምን ያህል አመስጋኝ እንደሆንሁ የምገልጥባቸው ቃላቶች የሉኝም፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ ስለ ስጋ ማሰብ ሞት እንደሆነ ስለ መንፈስ ማሰብ ግን
ሕይወትና ሰላም እንደሆነ ይነግረናል፡፡ ስለ መንፈስ ስናስብ በእውነተኛው
ወንጌልና የጽድቅ ሥራውን እንዲሰራለት እያንዳንዱን ቅዱስ በጠራው
በእግዚአብሄር ፈቃድ ለሚያምን ሁሉ አዲስ ሕይወትንና ሰላምን እንደሚያመጣ
ይናገራል፡፡ ስለዚህ በዚህ በአሁኑ ዘመን የምንኖር እናንተና እኔ በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል በተጨባጭ የምናምን ከሆነ በዚህ ወንጌል በማመን ጌታን
ልንከተል ደግሞ ይገባናል፡፡ ሁሌም የመንፈስ ሙላት ሊኖረን የሚችለው በዚህ
መልኩ ነው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


290 በመንፈስ ሙላት የሚኖሩ ሰዎች

የሚሻለው የቱ ነው? ሐጢያት ያለብን መሆን ወይስ ሐጢያት የሌለብን


መሆን? የሚሻለው ሐጢያት የሌለብን መሆን ነው፡፡ በቀድሞው ኑሮዬ በአንድ
ወቅት በሐጢያቶቼ ምክንያት በአጋንንት ተይዤ በሰይጣን አገዛዝ ሥር ነበርሁ፡፡
ነገር ግን እግዚአብሄር የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል እንዳውቅና ከእርሱም
የሐጢያቶችን ስርየት እንድቀበል አደረገኝ፡፡ ለዚያ ምን ያህል አመስጋኝ እንደሆንሁ
ለመግለጥ ቃላቶች ያጥሩኛል፡፡
ባለፈው ሕይወቴ በሐጢያቶቼ ምክንያት ብዙ ተሰቃይቻለሁ፡፡ በእነዚያ
ቀናቶች ሰይጣን እኔን ያለ ማቋረጥ በሐጢያቶቼ ለመክሰስ በጆሮዎቼም ‹‹ሐጢያት
ሰርተሃል አይደል? እንዲህ በጉስቁልና ውስጥ ከምትኖር ይልቅ ብትሞት ይሻላል››
በማለት ያንሾካሹክ ነበር፡፡ ስለዚህ ስቃ በጣም ከፍተኛ ስለነበር ‹‹እንዲህ ያለ
የጉስቁልና ሕይወት ከመኖር ይልቅ ከገደል ላይ ዘልዬ መሞት አለብኝ፡፡ ያን ጊዜ
ሁሉም ነገር ያበቃል፡፡ የሞት ስቃይ ቅጽበታዊ ነው፡፡ ስለዚህ ለምን እንዲህ ባለ
ስቃይ ውስጥ በመኖር እቀጥላለሁ? ራሴንም ከችግር ነጻ ማውጣት እችል ይሆናል››
ብዬ በማሰብ ራሴን ለማጥፋት በጣም ተቃርቤ ነበር፡፡
እንደ አጋጣሚ ሆኖ ሌላ አሳብ ወደ አእምሮዬ መጣ፡፡ ‹‹እንዲህ በሐጢያተኛ
ሁኔታዬ ብሞት አሁን ከምሰቃየው በላይ መጨረሻዬ በሲዖል ውስጥ መሰቃየት
አይሆንምን? ስለዚህ ራሴን ለማጥፋት አልችልም፡፡›› በመሆኑም ራሴን
አላጠፋሁም፡፡
አጋር ምዕመናኖቼ በሐጢያቶቻችን ምክንያት ሁላችንም ወደ ሲዖል ለመጣል
ተኮንነን ነበር፡፡ ይህ ሆኖ ሳለ ግን ጌታ ለእኛ ለማንረባው ሰዎች ራሱ ወደዚህ ምድር
መጣ፡፡ በአጥማቂው ዮሐንስ በመጠመቅም ሐጢያቶቻችንን ለአንዴና ለመጨረሻ
ተሸከመ፡፡ በመስቀል ላይ ሞተ፡፡ ከሙታንም ተነሣ፡፡ ኢየሱስ በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል አማካይነት ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ስላዳነን በዚህ እውነት የምናምን ሁላችን
አሁን ከእያንዳንዱ ሐጢያታችን ተፈትተናል፡፡ እኛ ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ነጻ
መውጣታችን እንደምን ድንቅ ነው? ከዚህ የበለጠ ድንቅ ነገር የለም፡፡
ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ከዳንን ከዚህ እምነታችን የሚሻል አንዳች እምነት አለ? ከእኛ
የሚሻል ሌላ እምነት በዓለም በየትኛውም ስፍራ የለም፡፡
ስለዚህ የደህንነት ወንጌል የሆነውን ይህንን የውሃና የመንፈስ ወንጌል
ለመስበክ ከሚኖር ሕይወት የሚሻል ምንም ሕይወት እንደሌለ በእጅጉ
ተረድተናል፡፡ ከዚህ የተሻለ ሕይወት የት እናገኛለን? ይህ ሕይወት ሊገኝ የሚችለው
በመንግሥተ ሰማይ ብቻ ነው፡፡ በመንፈስ ሙላት እየኖርን ስለሆነ ምን ሌላ
ሕይወት ያስመኘናል? በእርግጥም በመንፈስ ቅዱስ የተሞላው ይህ ሕይወት እጅግ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በመንፈስ ሙላት የሚኖሩ ሰዎች 291

ድንቅ ሕይወት ነው፡፡ እናንተስ ታዲያ? የዛሬውን ስብከት ስትሰሙ በእርግጥ


ይህንን በመንፈስ የተሞላ ሕይወት እየኖራችሁ ነውን?

የሐጢያቶቻችንን ስርየት በልቦቻችን ውስጥ ብንቀበልም በጊዜ


ሒደት ውስጥ ደንዛዞች ልንሆን እንችላለን፡፡

ለመጀመሪያ ጊዜ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ባመንሁና ሐጢያቶቼም


በሙሉ ከልቤ በተደመሰሱ ጊዜ ምን ያህል እንደተደሰትሁ ልታስቡ ትችላላችሁ፡፡
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለመጀመሪያ ጊዜ ስንሰማና በዚህ ወንጌል በማመን
የሐጢያቶችን ስርየት ስንቀበል ሁላችንም እግዚአብሄርን በማመስናችን ልቦቻችን
በውዳሴ ተጥለቅለቀው ነበር፡፡
በጊዜ ሒደት ግን እግዚአብሄር ለእኛ ያደረገውን ለማድነቅ በጣም ደነዘዝን፡፡
በአንዳንድ ሁኔታዎችም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመናችን ሐጢያቶቻችን
ከልቦቻችን መወገዳቸው የተለመደ ነው ብለን አስበን ይሆናል፡፡ ይህንንም
በቸልተኝነት በመውሰድ ስጋዊ አስተሳሰቦችን ከመናቅ ይልቅ ስጋን ለመከተል
ተፈትነን ሊሆን ይችላል፡፡ ከዚህ የተነሳ አንዳንድ ጊዜ በስጋ አስተሳሰቦች መሠረት
ለመኖር ከራሳችን ጋር ስምምነቶችን ለማድረግ ሞክረን ይሆናል፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ ‹‹መንፈስ ይሙላባችሁ እንጂ በወይን ተጅ አትስከሩ፤
ይህ ማባከን ነውና›› (ኤፌሶን 5፡18) በማለት ያሰጠነቀቀን ለዚህ ነው፡፡ የኢየሱስ
ክርስቶስን ትዕዛዛቶች መታዘዝና የእምነት ቀደምቶቻችንም ሲመክሩን ምሪታቸውን
መከተል የምንችለው በመንፈስ ሙላት ስንኖር ብቻ ነው፡፡ የእምነት ቀደምቶቻችን
የሚሰብኩት በትክክለኛው መንገድ የሚመራንን የእግዚአብሄር ቃል ስለሆነ
በእነርሱ የሚታመንና ምሪታቸውን የሚከተል ሁሉ የመንፈስ ሙላት ላይ
እንደሚደርስ አያጠራጥርም፡፡ የእግዚአብሄርን የጽድቅ ሥራ በዚህ መልኩ
መሥራት የምንችለው ሕይወታችን በመንፈስ ቅዱስ ሲሞላ ብቻ ነው፡፡ ሐዋርያው
ጳውሎስ በመንፈስ ቅዱስ እንድንሞላ የሚመክረንም ለዚህ ነው፡፡
አጋር ምዕመናኖቼ እናንተና እኔ በእርግጥም በሐጢያቶቻችን ምክንያት ሲዖል
ለመጣል ተመድበን ነበር፡፡ ሁላችንም በአንድ ወቅት ከኢየሱስ ክርስቶስ ውጪ
ቆመን ነበር፡፡ በእነዚያ ዘመናት ምን ያህል ምስኪኖች ነበርን? ነገር ግን ጌታ ወደዚህ
ምድር በመምጣትና በአጥማቂው ዮሐንስ በተቀበለው ጥምቀት አማካይነት
ሐጢያቶቻችንን በሙሉ በስጋው በመሸከም ሁላችንንም አዳነን፡፡ ጌታ ከዓለም

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


292 በመንፈስ ሙላት የሚኖሩ ሰዎች

ሐጢያቶች ሁሉ ባያድነን ኖሮ በዚህ ዓለም ላይ በሐጢያቶቻችን ተጨቁነን እስከ


መጨረሻው ድረስ የጉስቁልና ሕይወት እንኖር ነበር፡፡ ይህ ሕይወት እንዴት
የተጎሳቆለ ሕይወት ይሆን ነበር? በእርግጥም እጅግ የተጎሳቆለ ሕይወት እንኖር
ነበር፡፡
በዚህ ዓለም ላይ የሚኖሩ በርካታ ሰዎች አሁንም በዚህ የጉስቁልና ሕይወት
ውስጥ መጠመዳቸው ያሳዝናል፡፡ ስጋቸው ቢስቅም ልቦቻቸው በሐዘን
ተሞልተዋል፡፡ በስጋ ነገሮች ክፉኛ የተወጠሩት በጣም ሐዘንተኞች በመሆናቸው
ነው፡፡ በሌላ አነጋገር እንዲህ ያለውን ስጋዊ ሕይወት የሚኖሩት ሐዘናቸውን
ለጥቂት ጊዜም እንኳን ቢሆን ለመርሳት በሚያደርጉት ሙከራ ነው፡፡ በጣም ብዙ
ሰዎች ተስፋ በመቁረጥ ራሳቸውን የሚያጠፉት ለዚህ ነው፡፡ ገና የሐጢያቶችን
ስርየት ያልተቀበሉ እነዚህ ሰዎች የተረገመ ሕይወት እየኖሩ ነው፡፡ በዚህች ቅጽበት
እንኳን በርካታ ሰዎች በስቃይ ደረቶቻቸውን እየደቁ ነው፡፡
በአንጻሩ አሁን እናንተና እኔ በመንፈስ ሙላት በእግዚአብሄር በረከቶች
መካከል እየኖርን ነው፡፡ ስለዚህ ሐዋርያው ጳውሎስ በመንፈሳዊ መዝሙሮችና
ቅኔዎች ጌታን እንድናመሰግን ነገረን፡፡ እርሱ በመከረን መሠረትም ውብ
መዝሙሮችን ጽፈን አሁን ጌታን ለማመስገን እየዘመርናቸው ነው፡፡ አሁን በእምነት
እጅግ ድንቅ የሆነውን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል እያገለገልን ነው፡፡
በሕይወታችን የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በመላው ዓለም ሁሉ እየሰበክን
ነው፡፡ ሕይወታችንም በእርግጥ ጻድቅና ክቡር ሕይወት ነው፡፡
ሰዎች አንድ መጥፎ ነገር ሲያደርጉ መጀመሪያ ላይ ማድረግ የፈለጉትን
በማድረጋቸው ደስ ይላቸዋል፡፡ ነገር ግን ወዲያው የሐጢያታቸው ስበት
ሲያሰምጣቸው ጸጸት ይሰማቸዋል፡፡ ይህንን ተከትሎም ልቦቻቸውን እያሰቃየ
የሚቀጥል የፍርድ ፍርሃት ይመጣል፡፡ እንደ ኮበሌዎቻችን ያሉ ወጣቶች በተለይ
ይበልጥ ለመሰቃየት የተጋለጡ ናቸው፡፡ ጉርምስና በጣም አስቸጋሪ የሕይወት ደረጃ
ነው፡፡ ምክንያቱም ወጣቶች ለስሜታቸው የሚገዙ ናቸው፡፡ ከእነርሱ ብዙዎቹ
ከሰማይ በታች ያለ ምንም መሸማቀቅ ጥሩ ሆነው ለመኖር ቢፈልጉም በተጨባጭ
ግን በርካታ ሐጢያቶችን ይሰራሉ፡፡ ለጎረምሶች በተሳሳቱ የዓለም አስተሳሰቦች
ተጠርገው ለመወሰድና አእምሮዋቸውንም በተሳሳቱ ነገሮች ላይ ለማኖር በጣም
ቀላል ነው፡፡
ወንድሞቻችንና እህቶቻችን በጭራሽ በዚህ ፈተና መወሰድ እንደማይገባቸው
የታወቀ ነው፡፡ ነገር ግን በየጊዜው የሚገጥማቸው የአቻ ግፊት ሲታይ እንዲህ ባለ
ብዙ ግፊት ውስጥ በእምነት መኖራቸውና በጓደኞቻቸው ተጽዕኖ ሥር

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በመንፈስ ሙላት የሚኖሩ ሰዎች 293

አለመውደቃቸው በጣም አስቸጋሪ ነው፡፡ በጣም ብዙ ጎረምሶች መባከን


የድፍረትና የገድል ምልክት እንደሆነ ያስባሉ፡፡ በዘመኑ ወጣቶች መካከል
ሐጢያትን መስራት ተገቢ እንደሆነ የማሰብ ዝንባሌ አለ፡፡ ወጣት ከሆናችሁ ብዙ
ሰዎች ባባከኑት ወጣትነት በማልቀስ በጸጸት እንደሚሞሉ ለማየት ጥበብ
እንዲኖራችሁ እመክራችኋለሁ፡፡ እናንተ ያላችሁት የጽድቅን ሥራ በምትሰሩበት
የጽድቅ ስፍራ ላይ ነው፡፡ ትክክለኛ ደፋር ወጣቶችም እናንተ ናችሁ፡፡
አብዛኛውን ጊዜ ከኢየሱስ ጋር ስላለን የመጀመሪያ ፍቅር እንረሳለን፡፡ ነገር
ግን ሁሌም መመለስና እንደገና በመንፈስ ቅዱስ መሞላት እንችላለን፡፡
እንደገና ኤፌሶን 5፡18ን እናንብብ፡- ‹‹መንፈስ ይሙላባችሁ እንጂ በወይን
ጠጅ አትስከሩ፤ ይህ ማባከን ነውና፡፡›› እናንተና እኔ በጌታ ደህንነት በማመን
የሐጢያቶችን ስርየት ስለተቀበልን ሁሌም በመንፈስ ሙላት እንኖራለን፡፡
ምክንያቱም ስህተቶቻችንን ተቀብለን ሐጢያቶቻችን በሙሉ በመደምሰሳቸውም
ሁሌም እያመሰገንነው የእርሱን ጽድቅ አምነን ጌታን ስለምንከተል ነው፡፡ ጌታ
የእኛን ሐጢያቶች ብቻ ሳይሆን የእያንዳንዱን ሌላ ሰው ሐጢያቶች በሙሉ
ስለደመሰሰ ሁሌም ሐጢያት አልባ ሰዎች ሆነን መኖር እንችላለን፡፡ ሐጢያት አልባ
እንደሆንን፣ አሁን በሕይወታችን ውስጥ የእግዚአብሄርን የጽድቅ ሥራ ወደ
መስራት እንደመጣን፣ ሐጢያት አልባ ከሆኑት ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ጋር
በአንድነት የእርሱን የጽድቅ ሥራ በመሥራት በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ
ለመኖር እንደተባረክን፣ የእግዚአብሄር ሕዝብና የመንግሥቱ አባሎች እንደሆንን፣
ለሥራችንም ምስጋና ይሁንና በርካታ ሰዎችም የሐጢያቶችን ስርየት እየተቀበሉ
እንደሆነ፣ የወንጌልን አገልግሎት ለመደገፍና ለጌታ የጽድቅ ሥራ ስንል ራሳችንን
መስዋዕት እያደረግን እንደሆነ፣ እንደዚሁም በትክክል የተባረክን ሕዝቦች
እንደሆንን በአእምሮዋችንና በልቦቻችን መረዳታችን በእጅጉ ያስፈልገናል፡፡

የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለማገልገል የተመራ እያንዳንዱ


ሕይወት በመንፈስ ቅዱስ የተሞላ ሕይወት ነው፡፡

ጌታ ሁላችንም እንዲህ ያለ የተባረከ ሕይወት ለዘላለም መኖር እንድንችል


ሁሌም በመንፈስ ቅዱስ ይሞላናል፡፡ በሌላ አነጋገር ጌታ ሁሌም በእግዚአብሄር
ቤተክርስቲያን ውስጥ እንድንኖርና በሕይወታችንም ጌታን እንድንከተል
ሁላችንንም ባርኮናል፡፡ ነገር ግን ሥጋዊ አስተሳሰቦቻችንን የምንከተልና ከዚህ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


294 በመንፈስ ሙላት የሚኖሩ ሰዎች

ከተሳሳተው አቅጣጫችን ለመመለስ እምቢተኞች ከሆንን ከዚህ በመንፈስ


ከተሞላው ሕይወት እንገለላለን፡፡ በሌላ በኩል ስህተቶችን በምንሰራበት ጊዜ ሁሉ
ስህተት መሥራታችንን የምናምንና ጌታ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ የደመሰሰበትን
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል እንደገና የምናሰላስል ከሆነ፣ ስላደረገልን ነገርም
እርሱን በማመስገን እግዚአብሄርን የምንከተል ከሆነ ያን ጊዜ ልቦቻችን
በእግዚአብሄር ሥራና በፍቅሩ ይሞላሉ፡፡ ልቦቻችን በዚህ ሁኔታ በዚህ የጽድቅ
ሥራ ላይ ጸንተው ከተተከሉና እርሱንም የሚከተሉ ከሆኑ ሁሌም ከመንፈስ ሙላት
ጋር አብረን እንኖራለን፡፡ ጌታ ለሁላችንም የሰጠን ይሕንን ሕይወት ነው፡፡ በጣም
ደስተኞች የሆንነውና የተባረክነውም ለዚህ ነው፡፡
አጋር ምዕመናኖቼ እኛ በእርግጥ የተባረክን ሰዎች ብንሆንም አሳባችንን
በተሳሳተ መለኪያ ላይ የምናኖር ከሆንን መጨረሻችን ደስታ የራቃቸው ሰዎች
መሆን ይሆናል፡፡ የሐጢያቶችን ስርየት የተቀበለ ሰውም ቢሆን በራሱ ስጋዊ
አስተሳሰቦች መሠረት ስጋውን የሚከተል ከሆነ እንደ አብርሃም የወንድም ልጅ
እንደ ሎጥ መጨረሻው ደስታን ማጣት ሊሆን ይችላል፡፡ ይህ በእናንተ ላይ
እንዲሆን የምትፈቅዱ ከሆነ በኢየሱስ ምሳሌ ውስጥ አንድ መክሊት እደተቀበለው
ባርያ ለስጋችሁ ብቻ የምትኖሩ ራስ ወዳድ ሰው ትሆናላችሁ፡፡
በእርግጥ ይህ በእናንተ ላይ እንዲሆን ትፈልጋላችሁን? እግዚአብሄርን
እንዳረጀ ልብስ፣ ልትተዉት ጸጋውን ልትረግጡና የእርሱ ጠላትና ባላንጣ ልትሆኑ
ትፈልጋላችሁን? እንዲህ ዓይነት ሰዎች የዲያብሎስ ረዳቶች ይሆኑና በሕይወታቸው
ሁሉ እግዚአብሄርን ይቃወማሉ፡፡ በመጨረሻም ዕድላቸው ከግብዞች ጋር ይሆንና
ወደ እሳት ባህር ይጣላሉ፡፡ ነገር ግን አሁንም እንዲህ መኖር ትፈልጋላችሁን?
ጌታችን የማናችንም ፍጻሜ ፈጽሞ እንዲህ እንዲሆን አይፈልግም፡፡ ጌታ ያዳነን
ለዚህ አይደለም፡፡ በተቀራኒው ጌታ ያዳነን ብቻ ሳይሆን በየቀኑ በመንፈስ ሙላት
እንኖር ዘንድም ባርኮናል፡፡ ጌታን የምናመሰግነው ለዚህ ነው፡፡
እግዚአብሄር ለእኛ ያለው ዓላማ ምን ያህል የተሰናሰለ እንደሆነ ማየት
እንችላለን፡፡ አሁን እግዚአብሄር ምን ያህል በትክክለኛው መንገድ ላይ እንዳለን
ለማረጋገጥ ምን ያህል እንደወደደን፣ ምን ያህል እንደባረከንና በሕይወታችን
ውስጥም ምን ያህል ጣልቃ እንደገባ ማየት እንችላለን፡፡ ስለዚህ ጌታ በዚህ ዓለም
ላይ እንደ ሞኞች ሳይሆን እንደ ጥበበኞች እንደሚገባ እንድንመላለስ ነግሮናል፡፡
ቀኖቹ ክፉዎች ስለሆኑም ዘመኑን እንድንዋጅም ደግሞ ነግሮናል፡፡ (ኤፌሶን
5፡15-16)
በዚህ ዓለም ላይ የምንኖረው ሕይወት ዘላለማዊ አይደለም፡፡ ዕድሜያችን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በመንፈስ ሙላት የሚኖሩ ሰዎች 295

ቢበዛ 70-80 ዓመት ነው፡፡ (መዝሙረ ዳዊት 90፡10) በዚህ ዓለም ላይ ያለው
ሕይወታችን በጣም አጭር በመሆኑ የእግዚአብሄርን ሥራ ለመሥራት ምን ያህል
ጊዜ አለን? ከዕድሜያችን በጣም ያነሰ ጊዜ እንደሆነ ግልጥ ነው፡፡ አንዳንድ ሰዎች
ለ30 ወይም ለ40 ዓመታት ይሠሩ ይሆናል፡፡ አብዛኞቹ ሰዎች ግን ለመሥራት
ያላቸው ጊዜ አነስተኛ ነው፡፡ ከረጅም ጊዜ በፊት በሌላ ትውልድ ውስጥ ተወልደን
ቢሆን ኖሮ አሁን ካለው በበለጠ ለረጅም ጊዜ የእግዚአብሄርን ሥራ ለመሥራት
በቻልን ነበር፡፡ ነገር ግን የጌታ ምጽዓት ያን ያህል ሩቅ ባልሆነበት ዘመን እየኖርን
በመሆናችን የእግዚአብሄርን ሥራ ለመሥራት ያለን ጊዜ አጭር ነው፡፡ ስለዚህ
አሁን ሁላችንም ሌሎችን ለማዳን የጽድቅ ጥሪያችንን በመፈጸም ረገድ በትጋት
መሥራት አለብን፡፡
በዓለም ዙሪያ ሁሉ ያሉ ብዙ የሥነ ምህዳር ተቆርቋሪዎች የባህር ውስጥ ዓሣ
አንበሪን ማደን አጥብቀው ይቃወማሉ፡፡ ከእነርሱ አንዳንዶቹም ተቃውሞዋቸውን
የሚያሰሙት በቃላት ብቻ አይደለም፡፡ ነገር ግን በራሳቸው መርከብ ወደ ባህሩ
በመዝለቅ የባህር ውስጥ ዓሣ አንበሪዎችን የሚያድኑ መርከቦችን ለመከልከል
እየሞከሩ ነው፡፡ እነዚህ ሰዎች እምነታቸውን ለመደገፍ ሲሉ ሕይወታቸውን አደጋ
ላይ ጥለዋል፡፡ በሕይወት ውስጥ የእነርሱ እጅግ የላቀው ቅድሚያ ነገር የሥነ
ምህዳር ጥፋትን መከላከል ስለሆነ የሥነ ከባቢን ዝቅጠት ለማቆም የሚቻለውን
ነገር ሁሉ ያደርጋሉ፡፡ በሒደቱ ውስጥ ሕይወታቸውንም እንኳን ለአደጋ
ያጋልጣሉ፡፡ ሁሉም ሰው ሕይወቱን አሳልፎ የሚሰጠው እጅግ ክቡር የሆነ ዕሴት
ብሎ ለሚቆጥረው ነገር ነው፡፡ ራሳቸውን የሰጡ የሥነ ምህዳር ተቆርቋሪዎች ወደ
ማንኛውም ስፍራ ለመሄድ ሳይፈሩና የሥነ ምህዳር ጥፋት ምክንያቶችን
ለመመርመርና የሥነ ከባቢን ዝቅጠት የውሃም ይሁን ወይም የአፈር ወይም
የተበከለ አየርን ለመከላከል መደረግ ያለበትን ሁሉ በማድረግ ተፈጥሮን ለመጠበቅ
የሚቻለውን ሁሉ ያደርጋሉ፡፡ ብዙ ሰዎች እንዲህ ላለ ተገቢ ዓላማ ሳይታክቱ
በመሥራታቸው ያሞግሱዋቸዋል፡፡
በቅርቡ በኮርያ ምዕራባዊ የባህር ዳርቻ አጠገብ የፈሰሰ ከፍተኛ የዘይት ፍሳሽ
ኑሮዋቸውን በባህር ላይ የመሠረቱ የበርካታ ሰዎችን ሕይወት አመሳቅሎዋል፡፡
በባህሩ ዳርቻ ላይ የተፈጠረው አጠቃላይ ጥፋት በጣም ከባድ ስለነበር ከእነርሱ
አንዳንዶቹ በተስፋ መቁረጥ ራሳቸውን አጥፍተዋል፡፡ እነዚህ ሰዎች
ለቤተሰቦቻቸው ዳቦ ለማግኘትና ልጆቻቸውን ለማስተማር የሚደገፉት በባህሩ
ነበር፡፡ አሁን ግን ኑሮ መደጎሚያቸው በመውደሙ ምንም ነገር ማድረግ
አይችሉም፡፡ ዕጣ ፈንታቸው እጅግ አስከፊ በመሆኑ አንዳንድ ሰዎች ራሳቸውን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


296 በመንፈስ ሙላት የሚኖሩ ሰዎች

የማጥፋት አደገኛ ዕርምጃ ወስደዋል፡፡ ኑሮዋችንን ለመደጎም ሥነ ምህዳርን


መከላከልና መጠበቅ ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ ከዚህ ጥፋት ማየት እንችላለን፡፡
ሆኖም ከዚህ ዓላማ የሚበልጥ ሌላ የከበረ ዓላማም አለ፡፡ ይህ ፈጣሪ
እግዚአብሄር ለእኛ በአደራ የሰጠው ነው፡፡ ይህ ሥራ ከሁሉም የሚበልጥ እጅግ
ክቡርና አስፈላጊ ሥራ ነው፡፡ በሌላ አነጋገር የእግዚአብሄርን ወንጌል መስበክ የላቀ
የጽድቅ ሥራ ነው፡፡ አሁን እኛ እወነተኛውን የጽድቅ ሥራ እየሰራን ነው፡፡
ምክንያቱም እያንዳንዱን ሰው በእግዚአብሄር ፈቃድ መሠረት ለማዳን ያለ መታከት
እየሰራን ነውና፡፡ እኛ አሁን ይህንን ወንጌል የምንሰብከው ጌታ ሐጢያቶቻችንን
በሙሉ በመደምሰሱ በእጅጉ አመስጋኞች ስለሆንንና ጌታ የደመሰሰው የእኛን
ሐጢያቶች ብቻ ሳይሆን የሌላውንም ሰው ሐጢያቶች እንደደመሰሰ ስለምናውቅ
ነው፡፡ እንዲህ ላለ ክቡር ዓላማ መኖራችን ምን ያህል ድንቅ ነው? እግዚአብሄርን
በእጅጉ ስለምናመሰግነው ምስጋናችንን ሁሉ የምንገልጥባቸው ቃላቶች የሉንም፡፡
ልቦቻችን በመንፈስ ቅዱስ የተሞሉት በዚህ መልኩ በመኖራችን ነው፡፡
በምትኩ ሥጋን ተከትለን ቢሆን ኖሮ ይህ የመንፈስ ሙላት በሕይወታችን
ውስጥ በጭራሽ ባልኖረም ነበር፡፡ አንዳንድ ጊዜ ለጥቂት ጊዜም እንኳን ወደ ራሳችን
ስጋዊ መለኪያዎች ስናዘነብል ልቦቻችን ይገለበጡና ሕይወታችን ሲዖል እንደሆነ
ይሰማናል፡፡ አንዳንድ ጊዜ ጌታን መከተል የራሳችንን ጥፋት ማፋጠን መስሎ
ይሰማናል፡፡ ሌላው ሰው ሁሉ የራሱን ጥቅሞች ሲያሳድድ ስናይ ጌታን
የምንከተለው ብቻችን እንደሆነ ይሰማናል፡፡ የመጠላትና የመገለል ስሜትም
ይሰማናል፡፡ እንዲህ ያሉ ስሜቶች የሚኖሩን ለምንድነው? ምክንያቱም እየተከተልን
ያለነው ስጋዊ አስተሳሰቦቻችንን በመሆኑ ነው፡፡
እንዲህ ባሉ ወቅቶች አሳባችሁን በመንፈስ ነገሮች ላይ አኑራችሁ የእርሱን
ሥራ ተከተሉ፡፡ ያን ጊዜ ሲዖል የመሰለው ነገር ወዲያውኑ ሰማያዊ ሆኖ
ይለወጣል፡፡ አሳባችሁ በመንፈሳዊ ነገሮች ላይ ይጸና ዘንድ ጌታም የደመሰሰው
የእናንተን ሐጢያቶች ብቻ ሳይሆን የሁሉንም ሰው ሐጢያቶች ጭምር እንደሆነ፣
ጌታ ወንጌሉን ለሁሉም ሰው እንድትሰብኩ እንዳዘዛችሁ፣ ሌሎችም ደግሞ እናንተ
የሰበካችሁትን ወንጌል ሲሰሙ የሐጢያቶቻቸውን ስርየት መቀበል እንደሚችሉና
የእነርሱ ደህንነት የተመረኮዘውም በእናንተ ላይ እንደሆነ አስታውሱ፡፡ ያን ገዜ
ልባችሁ ይደሰታል፤ ሐሴትም ያደርጋል፡፡
እግዚአብሄር እኛን ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ለማዳን የተጻፈውን ቃል
ተጠቀመ፡፡ ስለዚህ በቅዱሳት መጻህፍት ውስጥ የተጻፈው የቃሉ እውነት ዘመናት
ቢለወጡም በጭራሽ አይለወጥም፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ እውነት ስለሆነ የውሃውንና

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


በመንፈስ ሙላት የሚኖሩ ሰዎች 297

የመንፈሱን ወንጌል ለዘላለም ይመሰክራል፡፡ እግዚአብሄር ቃሉን የጻፈው


በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን የሐጢያቶችን ስርየት የተቀበሉ ሁሉ
በመንፈስ ሙላት እንዲኖሩ ነው፡፡ ገና የሐጢያቶችን ስርየት ያልተቀበሉ ሁሉ በዚህ
የእግዚአብሄር ቃል አማካይነት የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ያውቃሉ፡፡
በእግዚአብሄር ፊት ቀና መሆን ያለባቸው ልቦቻችን ብቻ ናቸው፡፡ ልቦቻችን
ቀና ከመሆን ይልቅ ክፉ ከሆኑ መጽሐፍ ቅዱስን ስናነብ የምናየው ክፉ ነገሮችን
ብቻ ይሆናል፡፡ ምክንያቱም ቃሉ እውነት ነውና፡፡ ብዙ ሰዎች በእግዚአብሄር ቃል
እንደሚያምኑ ቢናገሩም የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ሳያስተውሉ በሐጢያተኛ
ሁኔታቸው ያንን የሚያደርጉ ሰዎች ከቃሉ ውስጥ ማየት የሚችሉት የስጋን በረከቶች
ብቻ ነው፡፡ ምክንያቱም ልቦቻቸው ክፉ ናቸውና፡፡ የሚከተሉትም የስጋን ፍትወት
ብቻ ነው፡፡ እነርሱ የእግዚአብሄርን ስም የሚጠሩት የራሳቸውን ፍትወት ለማርካት
ስለሆነ መጽሐፍ ቅዱስን በሚያነቡበት ጊዜ እግዚአብሄር የሚያሳያቸው ክፉ
የሆኑትን የስጋ ፍትወቶች የሚከተሉበትን መንገድ ብቻ ነው፡፡
ይህንን ለማብራራት 3ኛ ዮሐንስ 1፡2ን ተመልከቱ፡፡ እንዲህ ይላል፡- ‹‹ወዳጅ
ሆይ ነፍስህ እንደሚከናወን በነገር ሁሉ እንዲከናወንልህና ጤና እንዲኖርህ
እጸልያለሁ፡፡›› ይህንን ምንባብ በጥንቃቄ መመርመር የነፍሳችን መከናወን ለሌላው
ዓይነት ክንውን ሁሉ ቅድመ ሁኔታ እንደሆነ ይገልጣል፡፡ እግዚአብሄር ከሁሉ በፊት
ነፍሳችን አንዲከናወንላት ይፈልጋል፡፡ ከዚያም በነገሮች ሁሉ ይከናወንልናል፡፡
በሌላ አነጋገር እግዚአብሄር ከሁሉ በፊት የሐጢያቶችን ስርየት እንድንቀበል
ከዚያም የእግዚአብሄርን ጽድቅ እንድንከተል እየነገረን ነው፡፡ ያን ጊዜ እግዚአብሄር
በምናደርገው በእያንዳንዱ ነገር ይረዳናል፡፡
ሆኖም ልቦቻቸው ከፉ የሆኑ ሰዎች ይህንን ምንባብ እነርሱ በሚወዱት
መንገድ በተሳሳተ ሁኔታ ይተረጉሙታል፡፡ ይህንን የሚያደርጉት ስጋዊ
መሻቶቻቸውን ስለሚከተሉ ነው፡፡ ስለዚህ 3ኛ ዮሐንስ 1፡2ን ሲያነቡ ሰማይ
መግባት የሚችሉት በኢየሱስና በእርሱ የውሃና የመንፈስ ወንጌል ሲያምኑ ብቻ
በመሆኑ ላይ ምንም ትኩረት ሳያደርጉ ከነፍሳቸው ክንውን ይልቅ ለቁሳዊ ክንውን
ትልቅ ቦታ ይሰጣሉ፡፡ የእነዚህ ሰዎች ብቸኛው ፍላጎት ሐብታም መሆን፣ ለስጋዊ
ሕመሞቻቸው ፈውስ ማግኘት ወይም ዓለማዊ ዝናን ማግኘት በመሆኑ መጽሐፍ
ቅዱስን መቶ ጊዜ እንኳን ቢያነቡትም ይህንን እውነተኛ ወንጌል መረዳት
አይችሉም፡፡ ይህ እንዲያውም የእግዚአብሄር አሠራር ነው፡፡
ይኸው መርህ እኛን የዳንነውንም ደግሞ ይመለከታል፡፡ ልቦቻችን
በእግዚአብሄር ፊት ቀና ከሆኑ በመንፈስ ቅዱስ እንመራለን፡፡ መንፈስ ቅዱስ

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


298 በመንፈስ ሙላት የሚኖሩ ሰዎች

በእግዚአብሄር ቃል አማካይነት እየመራን መሆኑንና የእርሱንም ምሪት ለመከተል


መገደዳችንን የምናውቀው በዚህ መልኩ ነው፡፡ ነገር ግን ልቦቻችን ቀና ካልሆኑ
ስጋዊ ሰዎች ሆነን እንቀራለን፡፡ የእግዚአብሄርን ቃል መረዳትም ስለማንችል
ከመንፈሳዊ ሕይወት በእጅጉ በራቀ መንገድ እንኖራለን፡፡
ሁላችንም አሳባችንን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ላይ ማጽናትና የመንፈስን
ሥራ መከተል አለብን፡፡ ያን ጊዜ መንፈሳዊ ነገር ምን እንደሆነ እንገነዘባለን፡፡
በስጋዊ አስተሳሰቦች የምነሸነፍና መጽሐፍ ቅዱስንም በስጋዊ አእምሮ የምናነብ
ከሆንን የምናየው ስጋዊ ክንውናችንን እንዴት ማረጋገጥ እንደምንችል ብቻ
ይሆናል፡፡ ይህ እንዲሆን የምንፈቅድ ከሆነ ነፍሳችን ውሎ አድሮ ትጠፋለች፡፡
በዚህ የደቀ መዛሙርትነት ሥልጠና ካምፕ ወቅት ሁላችሁም በግልጥ
ልትረዱት የሚገባችሁን አንዱን እጅግ አስፈላጊ ቃል ሰብኬያለሁ፡፡ የዛሬውም
ስብከት ከዚህ የተለየ አይደለም፡፡ በእነዚህ ነገሮች ላይ የተናገርሁት በእጅጉ
ስለሚያስፈልጋችሁ ነው፡፡ የእግዚአብሄርን ቃል የሰበክሁት እርሱ ስለፈቀደልኝ
ነው፡፡ በስብከቴ ውስጥ ብዙ ነገሮችን ለመናገር ብዘጋጅም እግዚአብሄር
እስካልፈቀደልኝ ድረስ አንዲት የቃሉን መስመር እንኳን መስበክ አልችልም፡፡
አብዛኞቹ ክርስቲያኖች በየቀኑ መጽሐፍ ቅዱስን ቢያነቡም በእግዚአብሄር ቃል
የማያምኑና በልቦቻቸው ውስጥ ሐጢያት ያለባቸው እንደ ስጋ እየኖሩ ያሉ ሰዎች
አንዳች ትክክለኛ መረዳቶችን ማግኘት አይችሉም፡፡
ዛሬ በርካታ ክርስቲያኖች የሐጢያቶችን ስርየት መቀበል የማይችሉት
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ስለማያውቁ ነው፡፡ ስለዚህ ይህንን እውነተኛ
ወንጌል መስበክ ያልቻሉት በዚህ ምክንያት ነው፡፡ ይህ ሆኖ ሳለ እነዚህ ክርስቲያን
ሐጢያተኞች አሁንም የእግዚአብሄርን ቃል ለመሰበክ ይሞክራሉ፡፡ ይህንን
የሚያደርጉት በእግዚአብሄር ቃል ስለሚያምኑ ሳይሆን ስጋዊ ፍትወቶቻቸውን
ለማርካት ስለሚፈልጉ ነው፡፡
በአንጻሩ እግዚአብሄር በመንፈስ ሙላት እንድንኖርና በቃሉ መሠረት
የመንፈስን አስተሳሰቦች እንድንከተል እናንተንና እኔን ባርኮናል፡፡ አሁን ሁላችንም
በየቀኑ በመንፈስ ሙላት መኖር እንችላለን፡፡ ስለዚህ ሁላችንንም ስለመራን ለእርሱ
ምስጋናችንን ሁሉ እየሰጠን በእግዚአብሄር እየታመንን እንኑር፡፡ 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ስብከት
16

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት
ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
የሰይጣንን ሽንገላዎች
ተቃወሙ
‹‹ ኤፌሶን 6፡10-17 ››
‹‹በቀረውስ በጌታና በሐይሉ ችሎት የበረታችሁ ሁኑ፡፡ የዲያብሎስን ሽንገላ
ትቃወሙ ዘንድ እንዲቻላችሁ የእግዚአብሄርን ዕቃ ጦር ሁሉ ልበሱ፡፡ መጋደላችን
ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለምና፤ ከአለቆችና ከሥልጣናት ጋር ከዚህም ከጨለማ ዓለም
ገዦች ጋር፤ በሰማያዊም ስፍራ ካሉ ከክፋት መንፈሳውያን ሠራዊት ጋር ነው እንጂ፡፡
ስለዚህ በክፉው ቀን ለመቃወም ሁሉን ፈጽማችሁ ለመቆም እንድትችሉ
የእግዚአብሄርን ዕቃ ጦር ሁሉ አንሡ፡፡ እንግዲህ ወገባችሁን በእውነት ታጥቃችሁ፣
የጽድቅንም ጥሩር ለብሳችሁ፣ በሰላም ወንጌልም በመዘጋጀት እግሮቻችሁ ተጫምተው
ቁሙ፡፡ በሁሉም ላይ ጨምራችሁ የሚንበለበሉትን የክፉውን ፍላጻዎች ሁሉ ልታጠፉ
የምትችሉበትን የእምነትን ጋሻ አንሡ፡፡ የመዳንንም ራስ ቁር፣ የመንፈስንም ሰይፍ ያዙ፤
እርሱም የእግዚአብሄር ቃል ነው፡፡››

ጻድቃን በልቦቻቸው ጠንካራ መሆን አለባቸው፡፡ በዚህ በመጨረሻው ዘመን


ስንኖር ሳለን በጌታ ጽድቅ ላይ ባለን ጠንካራ እምነት ልንኖር ይገባናል፡፡ ችግሩ ግን
ቅዱሳኖችና የእግዚአብሄር አገልጋዮችም ሳይቀሩ ደካሞች መሆናቸው ነው፡፡
አንዳንድ ጊዜ ቅዱሳኖችም ሳይቀሩ ልባቸው ለወንጌል ይቀዘቅዛል፡፡ ምክንያቱም
በዚህ መልኩ ራሳቸውን ማቅረብ ካልቻሉ እግዚአብሄር ለጽድቅ ሥራው
መሣሪያዎቹ አድርጎ ሊጠቀምባቸው አይችልምና፡፡ ልባችሁ እንዲህ ደካማ
እንዲሆን የምትፈቅዱ ከሆነ የእግዚአብሄርን የጽድቅ ሥራ በትክክል መሥራት
አትችሉም፡፡ የእግዚአብሄር አገልጋዮችና ቅዱሳኖች ደካማ ልብ ያላቸው ከሆኑ
በጽናትና ሳይናወጡ ወደ እግዚአብሄር መገስገስ አይችሉም፡፡ ስለዚህ የእግዚአብሄር
አገልጋዮችና ቅዱሳኖች በአምላክ ላይ ባላቸው እምነት ልቦቻቸውን ማጠንከር
በጣሙን ያስፈልጋቸዋል፡፡ በልቦቻቸው ውስጥም የእግዚአብሄር ፍርሃት
ሊኖራቸው ይገባል፡፡
በዚህ በአሁኑ ዘመን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምኑ ሁሉ
የማይናወጥ እምነትና ጠንካራ ሰውነት ሊኖራቸው ይገባል፡፡ ምክንያቱም

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


302 የሰይጣንን ሽንገላዎች ተቃወሙ

የእግዚአብሄር አገልጋዮችና ቅዱሳኖች ደካማ ልብ ካላቸው ከዚህ ዓለም ጋር


ሊስማሙ ይችላሉ፡፡ የጌታንም ጽድቅ እስከ መጨረሻው ድረስ መከተልም
በጣሙን ያዳግታቸዋል፡፡ ማንም ምንም ይበል ሁላችንም በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል እውነት ላይ ባለን ዕውቀታችንና እምነታችን ብርቱዎች ልንሆን ይገባናል፡፡
እንዲህ ያለ ጠንካራ የእምነት ልብ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል እውነት
የሚቃወሙ ጠላቶችን ለመቃወምና በጭራሽ እጃችንን ላለመስጠት በእጅጉ
ያስፈልገናል፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ በዚህ በዛሬው የመጸሐፍ ቅዱስ ንባብ ላይ እንዲህ አለ፡-
‹‹በቀረውስ በጌታና በሐይሉ ችሎት የበረታችሁ ሁኑ፡፡ የዲያብሎስን ሽንገላ ትቃወሙ
ዘንድ እንዲቻላችሁ የእግዚአብሄርን ዕቃ ጦር ሁሉ ልበሱ፡፡›› (ኤፌሶን 6፡10-11)
አንዳንድ ሰዎች እምነቴን ሲያዩ ጠንካራ አቅም እንዳለኝ ይናገራሉ፡፡ የእምነቴ ጥንካሬ
የመጣው ግን ከስብዓናዬ አይደለም፡፡ ነገር ግን ከውሃውና ከመንገፈሱ ወንጌል ሐይል
የተገኘ ነው፡፡ ምክንያቱም እምነቴ በእግዚአብሄርና በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
እስካልበረታ ድረስ በጠላቶቼ ፊት መንበርከኬ አይቀርምና፡፡
በእግዚአብሄር ጽድቅ የሚያምነው ልባዊ እምነቴና እውነተኛ በሆነው
የእግዚአብሄር ፍርሃቴ ባይሆን ኖሮ በአሁኑ ጊዜ አገልግሎቴን አቁሜ ነበር፡፡ ወንጌልን
በዓለም ሁሉ ለመስበክ ለተጠራሁለት ጥሪ ምላሽ መስጠት የቻልሁት ጌታ በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል የሚያምን ጠንካራ እምነትና እግዚአብሄርን የሚፈራ ልብ ስለሰጠኝ
ነው፡፡ እግዚአብሄርን ከመፍራቴና በእርሱ ጽድቅ ላይ ካለኝ እምነቴ ውጪ በሌላ
በማንኛውም መንገድ ጌታን ፈጽሞ መከተል ባልቻልሁም ነበር፡፡ በኮርያ ‹‹ምንም ያህል
ውሻ ቢጮህበትም ባቡሩ ይሄዳል›› የሚል አባባል አለ፡፡ ብዙ ጠላቶች ቢገጥሙኝም
‹እንደፈለጋችሁ ልትጮሁ ትችላላችሁ፤ እኔ ግን በእውነት መንገዴ እጓዛለሁ››
እላቸዋለሁ፡፡ ማንም ምንም ቢለን ሁላችንም በእግዚአብሄርና በእርሱ የውሃውና
የመንፈሱ ወንጌል ላይ ባለን እምነታችን ወደፊት መገስገስ አለብን፡፡
ስለዚህ ራሳችንን ስንመለከት በእግዚአብሄር ዓይኖች እንጂ በደመ ነፍስ
አንመልከት፡፡ ትክክለኛው የደህንነት እውነት የመስቀሉ ብቻ ወንጌል ሳይሆን የውሃውና
የመንፈሱ ወንጌል እንደሆነ ለሰው ሁሉ በመመስከር እውነትን እያወጅን ነው፡፡ ስለዚህ
እግዚአብሄር ወዳዘጋጀልን ግብ መገስገስ የምንችለው ጠንካራ ልብና ጠንካራ እምነት
ሲኖረን ብቻ ነው፡፡ እግዚአብሄር ሁላችንም እንድንደርስበት ወደሚፈልገው ግብ
መድረስ የምንችለው ያን ጊዜ ብቻ ነው፡፡
እስከዚህች ቀን ድረስ በዚህ እምነት መኖር የቻልነው ጌታ በሰጠን የደህንነት
ወንጌልና እግዚአብሄርን በምንፈራበት በዚህ እምነት ነው፡፡ ይህ በጣም ግልጥ ነው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የሰይጣንን ሽንገላዎች ተቃወሙ 303

እግዚአብሄርን ማገልገል የቻልነው ጠንካራ ፈቃድ ወይም ብርቱ ማንነት ስላለን ሳይሆን
የጌታን ጽድቅ በያዘው የውሃና የመንፈስ ወንጌል በሚያምነው እምነታችን አማካይነት
የእግዚአብሄር ወታደሮች ስለሆንን ነው፡፡ ይህንንም እምነት እስከዚህች ቀን ድረስ
ጠብቀነዋል፡፡ በጌታ ጽድቅ በመታመንም መኖራችንን መቀጠል አለብን፡፡
ምን ያህል ሰዎች እንደሚቃወሙንና ጌታችንንና የእርሱን ጽድቅ ከመከተል
ሊያግዱን እንደሚሞክሩ ታውቃላችሁን? እነዚህ ጠላቶች ምን ያህል በጭካኔ
እንደሚቃወሙንና ሊያዋርዱን እንደሚሞክሩ ታውቃላችሁን? እንደዚያም ሆኖ ግን
እምነታችንን በጭራሽ ለእነርሱ አሳልፈን አልሰጠንም፡፡ በእግዚአብሄር ጽድቅ ላይ
ያለንን እምነታችንን በሚመለከት በፍርሃት ለማንም አሳልፈን ሰጥተን አናውቅም፡፡ ነገር
ግን ሁሌም ጥብቀነዋል፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስም ደግሞ እንዲህ ብሎዋል፡- ‹‹በቀረውስ
በጌታና በሐይሉ ችሎት የበረታችሁ ሁኑ፡፡›› (ኤፌሶን 6፡10) ይህ ምንባብ በጌታ ጽድቅ
በመታመን ራሳችንን እድናበረታ በግልጥ ያስተምረናል፡፡
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ባላንጣዎች በሙሉ የምንቃወመው
እምነታችንን ለመከላከል ነው፡፡ ጠላቶቻችን ያለ ምህረት ሲያጠቁንና ሲያላግጡብን
ምንም ተቃውሞ ሳናደርግ ዝም ብለን መሳቅ ብቻ ይጠበቅብናልን? የለም፤ በእምነታችን
ልናሸንፋቸው ይገባናል፡፡ ልቦቻችን የእግዚአብሄርን ጽድቅ ባላንጣዎች በሙሉ
ለመቋቋምና እምነታቸው የተሳሳተ መሆኑን በግልጥ ለመናገር ጠንካራ መሆን አለበት፡፡
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል እያመናችሁ ልፍስፍሶች ትሆኑ ዘንድ የምትፈቅዱ
ከሆነ መጨረሻችሁ ለእግዚአብሄር ጽድቅ ጠላቶች መማረክ ነው፡፡ ብዙ ልፍስፍሰ
ቅዱሳኖች የደረሰባቸው ይህ ነው፡፡ ስለዚህ እምነታችን ደካማ ይሆን ዘንድ ፈጽሞ
መፍቀድ የለብንም፡፡ ልቦቻችን በእግዚአብሄር ፊት ደካሞች መሆናቸው አስከፊ
ሐጢያት ከመሆኑም በላይ የእርሱ ጠላቶችም ያደርገናል፡፡ እነዚህ ልፍስፍስ ሰዎች
የእግዚአብሄርን ጽድቅ ከማመስገን ርቀው መጨረሻቸው የእግዚአብሄር ጠላቶች
መሆን ይሆናል፡፡ ውለው አድረውም የእርሱን ጽድቅ ይቃወማሉ፡፡ ጌታ ፈሪሳውያንን
አስመልክቶ በሐዋርያው ጳውሎስ በኩል እንዲህ አለ፡- ‹‹የእግዚአብሄርን ጽድቅ ሳያውቁ
የራሳቸውን ጽድቅ ሊያቆሙ ሲፈልጉ ለእግዚአብሄር ጽድቅ አልተገዙም፡፡›› (ሮሜ 10፡3)
ሁላችንም የእግዚአብሄርን ቃል በልቦቻችን ውስጥ ልንጽፍና እነዚህን ግብዝ ጠላቶች
በሙሉ በእምነት ደፍረን ልንቃወማቸው ይገባናል፡፡ የእግዚአብሄር ሕዝብ ልፍስፍስ
መሆናቸው ከባድ ስህተት ነው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


304 የሰይጣንን ሽንገላዎች ተቃወሙ

በማይናወጠው እምነታችን መቆምና የእግዚአብሄርን


ሥራ በታማኝነት መሥራት አለብን፡፡

ብርቱም ይሁኑ ደካማ ጻድቃን በእግዚአብሄር ጽድቅ ላይ ያላቸውን እምነት


በጠላቶቻቸው ሁሉ ላይ መጠቀም አለባቸው፡፡ ምክንያቱም በደህንነት እውነት
አማካይነት የሐጢያቶቻቸውን ስርየት ያልተቀበሉትን ሁሉ የመምራት ሐላፊነት
አለብን፡፡ ያንን ለማድረግም እኛ ራሳችን በመጀመሪያ ጻድቅ ከሆነው አምላክ ጎን
በእምነት ጸንተን መቆም አለብን፡፡ የእግዚአብሄር ሕዝብና አገልጋዮች ቀዳሚው
ተግባር የእርሱን ሥራ መሥራት ነው፡፡ ይህንን ተግባር ለመፈጸምም ጥበብ፣ እምነት፣
ፈሪሃ እግዚአብሄር፣ ጽናትና ጠንካራ ሥራ ሊኖራቸው ይገባል፡፡ የዚህ ዓለም ሰዎች
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የምናምነውን እኛን ቢቃወሙንም በጌታ ጽድቅ
በመታመን እነርሱን ወደ ክርስቶስ ለመምራት ጠንክረን መሥራት ይገባናል፡፡ ይህንን
ለማድረግም በእምነታችን ላይ ይበልጥ ጸንተን መቆም አለብን፡፡
በዚህ የእግዚአብሄር ጽድቅ ላይ ያለው እምነቱ በጣም ደካማ ከሆነ ማንም
ቅዱስ የእግዚአብሄርን ጽድቅ መከተል አይችልም፡፡ ይህንን በግልጥ ልታስታውሱ
ይገባችኋል፡፡ ልቦቻችን በእግዚአብሄር ጽድቅ ላይ እምነት ሊኖራቸው ይገባል፡፡
አእምሮዋችንም በእግዚአብሄር ጽድቅ ላይ ማተኮር አለበት፡፡ እኛ እምነታችንን
ለመኖር ከፈለግን በመጀመሪያ የእግዚአብሄርን ጽድቅ ለመከተል አእምሮዋችንን
ማዘጋጀት አለብን፡፡
የእግዚአብሄርን ሥራ በትክክል ለመሥራት በእግዚአብሄር ጽድቅ ላይ
በመታመን በትክክል መኖር የምንፈልግ ከሆነ በዚህ ክፉ ዓለም ላይ ደካማ ልንሆን
አይገባንም፡፡ እምነታችን ጠንካራ መሆን አለበት፡፡ በእግዚአብሄር ጽድቅ ላይ ያላችሁ
እምነት ከሰውነታችሁ ይበልጥ እንዲበረታ እፈልጋለሁ፡፡ ሁላችንም ልናበረታው
የሚገባን በጌታ ጽድቅ ላይ ያለንን እምነት ነው፡፡
ጊዜያዊ ሁኔታዎቻችን በቀላሉ ሊለወጡ ይችላሉ፡፡ ነፋሻማ ቀኖች፣ ጭጋጋማ
ቀኖች፣ ጸሃያማ ቀኖችና ዝናባማ ቀኖች አሉ፡፡ ቀንና ሌሊት ሁሌም እንደሚፈራረቁ
ሁሉ አሁን ያለው የሕይወታችን ሁኔታም ሁሌም ሊለዋወጥ ይችላል፡፡ ነገር ግን አጋር
ምዕመናኖቼ በእግዚአብሄር ጽድቅ የሚመራው የእምነት ሕይወታችን በፍጹም
መለወጥ የለበትም፡፡ ሕይወታችን በብርቱ በተለወጠ ቁጥር በእግዚአብሄር ጽድቅ ላይ
ያለን እምነታችንም ይበልጥ ብርቱ መሆን አለበት፡፡ ስለዚህ ከፊት ለፊታችን ያለውን
ነፋስ የቀላቀለ ማዕበል አንፍራው፡፡ ነፋሱ ይበልጥ በበረታ ቁጥር የወንጌል መዓዛ ርቆ
ይናኛል፡፡ በመሃልይ ዘሰሎሞን ላይ እንዲህ ተብሎ ተጽፎዋል፡-

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የሰይጣንን ሽንገላዎች ተቃወሙ 305

‹‹የሰሜን ነፋስ ሆይ ተነስ፤ የደቡብም ነፋስ ና፤ በገነቴ ላይ ንፈስ፤ ሽቱውም


ይፍሰስ፡፡›› (መሃልይ ዘሰሎሞን 4፡16)
አጋር ምዕመኖቼ በእርግጥ በጌታ ጽድቅ ላይ እምነት ካለን የሕይወታችን
ሁኔታዎች ይበልጥ አስቸጋሪ ሲሆኑ በእግዚአብሄር ጽድቅ ላይ እንደገፋለን፡፡
የእግዚአብሄርን ሥራ ለመሥራት የምንታገለው ስጋዊ ሁኔታዎቻችን በጣም አመቺ
ሲሆኑ እንጂ ሁኔታዎቻችን በጣም አስቸጋሪ ሲሆኑ አይደለም፡፡ ስለዚህ ሁላችንም
በእርሱ ጽድቅ የሚያምን የማይናወጥ እምነት እንዲሰጠን ወደ ጌታችን ልንጸልይና
በእምነት ለመኖርም ይረዳን ዘንድ ከልባችን ልንለምን ይገባናል፡፡ በጌታ ጽድቅ ላይ
ባለን እምነታችንም ልንኖርና ሁሌም ራሳችንን በጌታ እያበረታን በእግዚአብሄር ፈቃድ
ልንኖር ይገባናል፡፡ ጠንካሮች የሆንነው በጌታ ሐይልና ብርታት ነው፡፡ ጠላቶቻችንን
ሁሉ ማሸነፍ የምንችለውም በጌታ ጽድቅ ላይ ባለን እምነት ነው፡፡

እግዚአብሄር ‹‹የዲያብሎስን ሽንገላ እንድንቃወም›› (ኤፌሶን 6፡11)


አዞናል፡፡

የዲያብሎስን ሽንገላዎች ለመቃወም ምን ማድረግ አለብን? የእግዚአብሄርን


ዕቃ ጦር ሁሉ በእምነት መልበስ አለብን፡፡ ጳውሎስ በኤፌሶን 6፡11-12 ላይ እንዲህ
ብሎዋል፡- ‹‹የዲያብሎስን ሽንገላ ትቃወሙ ዘንድ እንዲቻላችሁ የእግዚአብሄርን ዕቃ
ጦር ሁሉ ልበሱ፡፡ መጋደላችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለምና፤ ከአለቆችና ከሥልጣናት
ጋር ከዚህም ከጨለማ ዓለም ገዦች ጋር፤ በሰማያዊም ስፍራ ካሉ ከክፋት መንፈሳውያን
ሠራዊት ጋር ነው እንጂ፡፡›› ከዚያም ተከታዩን ቁጥር በመናገር ይቀጥላል፡- ‹‹ስለዚህ
በክፉው ቀን ለመቃወመም ሁሉን ፈጽማችሁ ለመቆም እንድትችሉ የእግዚአብሄርን
ዕቃ ጦር ሁሉ አንሡ፡፡›› (ኤፌሶን 6፡13) ጌታ የዲያብሎስን ሽንገላዎች እንድንቃወም
በግልጥ ነግሮናል፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ መጋደላችን ከስጋና ከደም ጋር እንዳልሆነም ነግሮናል፡፡ ይህ
ማለት ትግላችን ከማንኛውም ሰው ስጋዊ ሐይልና ጉልበት ጋር አይደለም ማለት ነው፡፡
ይልቁንም ጌታ በሰማያዊ ስፍራዎች ካሉ የክፋት መንፈሳውያን ሠራዊቶች ጋር
እንድንዋጋ ነግሮናል፡፡ እኛ ጻድቃኖች ልንዋጋው የሚገባን ጠላት ማነው? የምንዋጋው
ጠላት ዲያብሎስ ነው፡፡ እኛ ዲያብሎስን በፍጹም መፍራት ወይም በፊቱ ድፍረታችንን
ማጣት አይገባንም፡፡ ሰይጣን በዚህ ዘመን ካሉ የጨለማ ገዥዎች ጋር አብሮ እየሰራ
ነው፡፡ ሰዎች በሰይጣን እየተገዙ ነው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


306 የሰይጣንን ሽንገላዎች ተቃወሙ

ስለዚህ በእግዚአብሄር ጽድቅ ላይ ባለን እምነታችን ሰይጣንን መቃወም


አለብን፡፡ ምክንያቱም ጌታ በእግዚአብሄር ቃል እንድንታመን፣ በእምነት
እንድንቀበለውና ዲያብሎስን እንድንቃወም ነግሮናል፡፡ ሰይጣን በዚህ ዓለም
በእያንዳንዱ ነገር ላይ የሚገዛበት ሥልጣን አለው፡፡ በዚህ ዓለም ላይ ያሉት ተቋሞች
በሙሉ በሰይጣን ቁጥጥር ሥር ናቸው፡፡ ዲያብሎስም በእነዚህ የቁጥጥር መሳርያዎች
አማካይነት እየሰራ ነው፡፡ በክፉ መናፍስቶች የተያዙትን በሙሉ ከመዋጋት በቀር
ምርጫ የሌለን ለዚህ ነው፡፡

እግዚአብሄር በአምላክ ቃል አማካይነት ዲያብሎስን እንድንቃወም


ነግሮናል፡፡

በኤፌሶን 6፡16-17 ላይ እንዲህ ተጽፎዋል፡- ‹‹በሁሉም ላይ ጨምራችሁ


የሚንበለበሉትን የክፉውን ፍላጻዎች ሁሉ ልታጠፉ የምትችሉበትን የእምነትን ጋሻ
አንሡ፡፡ የመዳንንም ራስ ቁር፣ የመንፈስንም ሰይፍ ያዙ፤ እርሱም የእግዚአብሄር ቃል
ነው፡፡›› እዚህ ላይ ጌታ ሰይጣንን በእግዚአብሄር ቃል እንድንዋጋው በግልጥ ነግሮናል፡፡
በእግዚአብሄር ቃል በመታመንም የሰይጣንን አገልጋዮች እንድንቃወማቸው እየነገረን
ነው፡፡ ከዲያብሎስ ጋር በምናደርገው ውጊያ በሁሉም ላይ የእምነትን ጋሻ እንድናነሳም
ነግሮናል፡፡
በውጊያችን ላይ የእምነትን ጋሻ ማንሳት ማለት ምን ማለት ነው? ይህ ማለት
በእግዚአብሄር ቃል ላይ ባለን እምነታችን የሰይጣንን ክፉ አገልጋዮች መዋጋት አለብን
ማለት ነው፡፡ በዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ላይ ‹‹የሚንበለበሉት ፍላጻዎች››
የሚያመለክቱት በጦርነት ላይ እንዳለን ነው፡፡ ሰይጣን እያንዳንዱን ሰው ባርያ
ለማድረግና ለማሳወር የኩነኔን ፍላጾች በእያንዳንዱ ሰው ላይ ይወረውራል፡፡
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል የምናሰራጨውና ኢየሱስ የዚህን ዓለም ሐጢያቶች
በሙሉ ለአንዴና ለመጨረሻ የመደምሰሱን እውነት የምንሰብከው ለዚህ ነው፡፡ ስለዚህ
የእያንዳንዱን ሰው ሐጢያቶች የመንፈስ ሰይፍ በሆነው የእግዚአብሄር ቃል ማለትም
በወንጌል እውነት ማንጻት አለብን፡፡
በዘመናዊው ጦርነት ውስጥ አጥቂው ሐይል ብዙውን ጊዜ ጥቃቱን የሚጀምረው
የጠላትን ወረዳ በቦምብ በማውደም ነው፡፡ የአየር ዘመቻው ከተጠናቀቀ በኋላ እግረኛ
ወታደሮች ቀሪዎቹን የጠላት ሐይሎች ለመደምሰስና አገሩን ለመያዝ ይላካሉ፡፡
አሁን ለውሃውና ለመንፈሱ ወንጌል እየሰራነው ያለነው ሥራ እግረኛ ወታደሮች

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የሰይጣንን ሽንገላዎች ተቃወሙ 307

ከሚሠሩት ሥራ ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡ ኢየሱስ ጽድቅ በሆነው የደህንነት ሥራው


የዚህን ዓለም ሐጢያቶች በሙሉ ለአንዴና ለመጨረሻ ደምስሶዋል፡፡ ጌታ በዚህ ዓለም
ላይ ያለውን እያንዳንዱን ሐጢያት በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ሙሉ በሙሉ
አስወግዶታል፡፡ አሁን እኛ እያደረግነው ያለነው ይህንን የምሥራች በዓለም ዙሪያ
ለሚገኝ ለእያንዳንዱ ሰው ማሰራጨት ነው፡፡ በሌላ አነጋገር ኢየሱስ በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል በሰይጣን ላይ የመከላከል ጥቃት ከፍቷል፡፡ አሁን ለእኛ የቀረልን
ተግባር በዚህ ዓለም ላይ ወዳለው ውጊያ መገስገስ፣ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
መስበክና በዚህ ወንጌል የሚያምኑትን ሁሉ ከሐጢያቶቻቸው ኩነኔና ከሰይጣን ሐይል
ማዳን ነው፡፡ ጌታ እንዳዘዘን እንዲህ በማድረግ ‹‹የሚንበለበሉትን የክፉውን ፍላጻዎች
በሙሉ ማጥፋት›› (ኤፌሶን 6፡16) እንችላለን፡፡

ሰይጣን የሰዎችን ልቦች በማጨበርበሪያ ዘዴዎቹ ያናውጣል፡፡

ዲያብሎስ የሰዎችን ነፍስ በማጨበርበሪያ ዘዴዎቹ ይመርዛል፡፡ ሰይጣን


በማታለያው በጣም ተንኮለኛ ስለሆነ ብዙ ሰዎች በዲያብሎስ ተታልለው ቢሆንም
እንኳን ሕይወታቸውን በደስታ እየኖሩ ነው፡፡ ሰይጣን የሰውን ልብ አሳችና ሰዎችን
የረከሱ ሐጢያተኞች አድርጎ የሚለውጥ አርካሽ ነው፡፡ ለስጋዊ ተድላዎች ስንል
እውነትን እንድንተው ሊያስተን ይሞክራል፡፡ እርሱ ሰዎች ወደ ውሃውና መንፈሱ
ወንጌል እንዳይሳቡ የሚችለውን እያንዳንዱን ነገር ያደርጋል፡፡ ሰይጣን በሰዎች ላይ
የሚሰራበት መንገድ ቁሳዊ ስኬትን ቃል በመግባትና በሚያልፉ ስጋዊ ተድላዎች
እውነትን እንዲተኩ በማጥመድ ነው፡፡ የዚህ ሁሉ ፍጻሜ የነፍስ በእርግጠኝነት
መሞት ነው፡፡
ይህ በጣም ግልጥ የሚሆነው ሰይጣን በእኛ በጻድቃን ወይም በማያምኑ
ሰዎች መካከል ለመሥራት እንዴት እንደሚሞክር ስንመለከት ነው፡፡ እኛ
አብዛኛውን ጊዜ የውሃውን የመንፈሱን ወንጌል ስንሰብክ ቁሳዊ ኪሳራዎች
እንደሚገጥሙን እውነት ነው፡፡ ሆኖም እኛ የዳንን ሰዎች ያለን ብቸኛው ምኞት
በእግዚአብሄር ቃል በመታመን ጸንተን መቆም፣ ዳግመኛ በፍጹም የዲያብሎስ
ባርያዎች አለመሆንና ለእግዚአብሄር ጽድቅ አገልጋዮች ሆነን መኖር ነው፡፡ የእኛን
ዱካዎች ለሚከተሉ የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል አማኞች ሁሉ የምንመኘውም
ይህንን ነው፡፡
እኛ በዓለም ሁሉ ላለ ለእያንዳንዱ ሰው ወንጌልን ስንሰብክ ሰይጣንና

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


308 የሰይጣንን ሽንገላዎች ተቃወሙ

አገልጋዮቹ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምኑትን አማኞች ልቦች ለማሳት


ተግተው ይሞክራሉ፡፡ ዲያብሎስ የሰዎችን ልቦች በሐሰተኛ የክርስቲያን
ትምህርቶች በማታለል ወደ እግዚአብሄር ጽድቅ እንዳይመጡ ይከለክላቸዋል፡፡
ነገር ግን በነገር ሁሉ በእግዚአብሄር ጽድቅ ላይ እምነት እስካለን ድረስ
በእርግጠኝነት ሰይጣንን መቃወምና ማሸነፍ እንችላለን፡፡ በስጋና በመንፈስ
ይከናወንልን ዘንድ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል እናምናለን፡፡ ልክ እንደዚሁ
ከእርሱ አገልጋዮች ጋር እንድትተባበሩ የምጠይቃችሁ በእግዚአብሄር ፊት
እንዲሳካላችሁ ስለምፈልግ ነው፡፡ ይህንን የምጠይቃችሁ ሰይጣን ራሱን
በልባችሁና በእምነታችሁ ላይ እንዳይተካ ለመከልከል ነው፡፡
እኔ የሰይጣንን አገልጋዮች እንደ ሞኞች እቆጥራቸዋለሁ፡፡ ምክንያቱም
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለእነርሱ እየሰበከችላቸው ያለችውን ቤተክርስቲያን
ማወቅ አይችሉም፡፡ የእግዚአብሄርን ቤተክርስቲያን ከማወቅ ርቀው በዚህ ዓለም
ላይ ካለው ከማንኛውም ቤተክርስቲያን ጋር ተመሳሳይ እንደሆነች ያስባሉ፡፡
የተለያዩ ቤተክርስቲያኖችን ሲያወዳድሩና ሲመዝኑ አንዲቷን እውነተኛ
ቤተክርስቲያን ከሐሰተኞቹ ቤተክርስቲያኖች ሁሉ ለመለየትም በጣም ግራ
ይጋባሉ፡፡ በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥም ቢሆን ለውሃውና ለመንፈሱ
ወንጌል ብቻ ለመኖር ልባቸውን ያላዘጋጁ በምትኩ ቤተክርስቲያንን ትተው
ለመውጣት የሚያስቡ አንዳንድ ሰዎች አሉ፡፡ ‹‹እናንተ በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል ለማመን የሐጢያቶችን ስርየት ተቀብላችኋል፡፡ ስለዚህ አሁን የጌታ ወገን
ናችሁ፡፡ ልትገኙ የሚገባችሁ በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ ነው፡፡ ነገር ግን
አንድ ግልጥ የሆነ ነገር አለ፡፡ እርሱም መሄድ የሚኖርባችሁ የውሃውንና የመንፈሱን
ወንጌል ወደምትሰብክ ቤተክርስቲያን ነው፡፡ ነገር ግን ይህ ወንጌል የሚሰበከው
በሌላ ስፍራ ሳይሆን በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ መሆኑን አስታውሱ፡፡
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ብትሰብክም ባትሰብክም ወደ ሌላ ቤተክርስቲያን
መሄድ ትፈልጋላችሁን? የምትፈልጉት ያንን ከሆነ እኛ ልናስቆማችሁ ማደረግ
የምንችለው ምንም ነገር የለም›› ከማለት በስተቀር ምርጫ የለንም፡፡
እነዚህን ነገሮች ስንናገር ልቦቻችን እንደሚቆስሉ የታወቀ ነው፡፡ ነገር ግን
ይህንን እውነተኛ ወንጌል ከሚያራክስ ከማንኛውም ሰው ጋር የሚቆይ ቁርኝት
የለንም፡፡ ይህንን እውነተኛ ወንጌል ለማያውቅ ለሌላ ነፍስ መስበክ እንችላለን፡፡
የእግዚአብሄርን ሥራ እየሠራን ስለሆነ የሚያስፈልጉ ከሆነ እግዚአብሄር ራሱ
ዳግመኛ በተወለዱ ቅዱሳኖች መካከል ተጨማሪ ሠራተኞችን እንደሚያስነሳ
እርግጠኛ ነኝ፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል እንደሚያምኑ በሚናገሩ ሰዎችም

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የሰይጣንን ሽንገላዎች ተቃወሙ 309

መካከል እንኳን የእግዚአብሄርን ቤተክርስቲያን የማያውቁ አንዳንድ ሰዎች አሉ፡፡


በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ እንዲቆዩ ለመምከር የሚቻለውን እያንዳንዱን
ነገር ብናደርግም እኛን ለማድመጥ ፈጽመው እምቢተኞች ከሆኑ ይዘን
ልናስቀራቸው አንሞክርም፡፡
በአሁኑ ጊዜ የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን እያንዳንዲቱን የጠፋች ነፍስ
ከዓለም ሐጢያቶች ሁሉ ለማዳን ተግታ እየሰራች ነው፡፡ ነገር ግን የእግዚአብሄርን
ጽድቅ የሚንቀውን ማንኛውንም ሰው ለመሰብሰብ አንሰራም፡፡ እነዚህ ሰዎች
ከልባችን በእግዚአብሄር ከምናምነው ከእኛ ጋር የሚያገናኛቸው ምንም ነገር
የለም፡፡ ነገር ግን ስስታሞቹ የዚህ ዓለም ሐሰተኛ ነቢያቶች ሰይጣን እንዲህ ያሉ
ሰዎችን እንዲሰበስቡና ራሳቸውን ለማበልጠግ ብቻ እንዲበዘብዙዋቸው
ስለሚያነሳሳቸው በእግዚአብሄር ጽድቅ ቢያምኑ ወይም ባያምኑ ግድ የላቸውም፡፡
ለምሳሌ ያህል በአንድ ወቅት በቤተክርስቲያን ስጦታዎች ላይ በእጅጉ ትኩረት
የሚያደርግ አንድ ክርስቲያን መሪ በኮርያ ስለነበር ወደ ቤተክርስቲያን የመጡ
አዳዲስ ሰዎች በሚኖሩበት ጊዜ ሁሉ ሐብታም እስከሆኑ ድረስ ወንጌል በግላቸው
ለእነርሱ ለመስበክ ይጠመድ ነበር፡፡ እንዲያውም ወንጌል በመጀመሪያ ለባለጠጎች
መሰበክ አለበት እስከ ማለት ድረስ ርቆ ሄዶ ነበር፡፡ ይህንንም ደሃ ቤተክርስቲያን
ወንጌልን በሚገባ መስበክ አትችልም በሚሉ መሠረቶች ያጠናክረዋል፡፡ ከዚህ በስተ
ጀርባ ያለው ሥነ አመክንዮ ባለጠጋ የሆኑ አባላቶች ያሉዋት ቤተክርስቲያን
ሐብታም ቤተክርስቲያን ናት፤ ሐብታም ቤተክርስቲያን ማለትም ብዙ አባሎች
ያሉዋት ቤተክርስቲያን ማለት ነው የሚል ነበር፡፡ ስለዚህ ይህ መሪ ለራሱ ብዙ
ሐብትን ሰበሰበ፡፡ ነገር ግን መጨረሻው ከመንፈሳዊ ግዛት ማፈንገጥ ሆነ፡፡
ከዚህም በላይ ይህ የቤተክርስቲያን መሪ ጉባኤው በአምልኮ አገልግሎት
ወቅት ወደ እግዚአብሄር በሚጸልይበት ጊዜ ሁሉ እርሱ ብቻውን መላውን ጉባኤ
ወክሎ መጸለይ እንዳለበት አሰበ፡፡ ስለዚህ በአምልኮ አገልግሎት ወቅት ሁሌም
መጸለይ ያለበት እርሱ ብቻ እንደሆነ በማረጋገጥ ቤተክርስቲያን ውስጥ ያለው
ሌላው ሰው ሁሉ ከእርሱ በኋላ አሜን ይላል፡፡ በአንዳንድ መንገዶች የዚህ ዓይነቷ
ቤተክርስቲያን ከእኛ ቤተክርስቲያን ይልቅ ይበልጥ የተደራጀችና ስርዓት ያላት
ይመስላል፡፡ ነገር ግን ይህ ጌታ ‹‹ለምን ይሰጣችሁማል፤ ፈልጉ ታገኙማላችሁ፤
ደጅን አንኳኩ ይከፈትላችኋል›› (ማቴዎስ 7፡7) ያለውን እውነት ሙሉ በሙሉ
የሚስት ነው፡፡ ሆኖም ሰይጣን በልቦቻቸው ውስጥ ስጋዊ ስስቶችን በማስገባት
በአሁኑ ዘመን ባሉ ብዙ ክርስቲያኖች መካከል እየሰራ ያለው እንደዚህ ነው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


310 የሰይጣንን ሽንገላዎች ተቃወሙ

የእምነት ውጊያችሁን ጀምሩ፡፡

ጌታ ለዲያብሎስ ሥልጣንና ቃሎች አለመማረክ ነገር ግን የውሃውንና


የመንፈሱን ወንጌል በጽናት መሰበክ ለቅዱሳኖች የእምነት ውጊያ እንደሆነ
ተናግሮዋል፡፡ መንፈሳዊ ውጊያችን ዓላማው የሰዎችን ነፍሶች ከሐጢያቶቻቸው
ማዳን ነው፡፡ እኛ ይህንን ነፍስ የማዳን ሥራ የእግዚአብሄር ቃል በሆነው የመንፈስ
ሰይፍ እየሰራነው ነው፡፡ እኛ በዲያብሎስ ላይ መንፈሳዊ ጦርነትን ከፍተናል ማለት
ራሳችንን በጭራሽ ለአንዳች ሐሰተኛ ወንጌል ሳናማርክ ሰዎችን በእውነተኛው
ወንጌል አማካይነት እያዳንን ነው ማለት ነው፡፡
ምንም እንኳን ዲያብሎስ በግልጥ የሚመርጠው ይህንን ቢሆንም መንፈሳዊ
ጦርነታችንን የምንዋጋው በራሳችን ሰውኛ ስሜቶች ላይ በመደገፍ አይደለም፡፡
ዲያብሎስ እርሱን ለመዋጋት በስሜት ብቃት ስንነሳሳና በራሳችን ጉልበት ስንታመን
ይወዳል፡፡ ዲያብሎስ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ከማገልገልና ከመስበክ ይልቅ
ስጋዊ ባለጠግነቶችን ስንሻም ደግሞ ይደሰታል፡፡ የሰይጣን ዓላማ ያገኘነው
ማንኛውም ድል የተገኘው በራሳችን ሥራና ጥረቶች መሆኑን እንድናምን ማድረግ
ነው፡፡ ራሱን የእግዚአብሄር አገልጋይ እንደሆነ የሚጠራ ማንኛውም ሰው የስጋን
ባለጠግነቶች የሚሻ ከሆነ የሰይጣን አገልጋይ ነው፡፡
እኛ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል እናምናለን፡፡ በሕይወታችንም
የእግዚአብሄርን ጽድቅ በመስበክ እንደሰታለን፡፡ ስለዚህ በእግዚአብሄር ጸጋ መኖርና
ሁሌም የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ማገልገል አለብን፡፡ ያንን ለማድረግም
የእግዚአብሄርን ቤተክርስቲያን ፈቃድ መከተል አለብን፡፡
ችግሩ ግን በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ ያሉ አንዳንድ ሰዎች
ከእግዚአብሄር ሥራ ይልቅ በራሳቸው ጉዳዮች መጠመዳቸው ነው፡፡ ለዚህ ጥሩ
ምሳሌ የሚሆነን ከ3ኛ ዮሐንስ 9 ላይ እናገኛለን፡፡ እንዲህ ይላል፡- ‹‹ዳሩ ግን
ዋናቸው ሊሆን የሚወድ ዲዮጥራጢስ አይቀበለንም፡፡›› እንዲህ ያለ ሰው ያለው
ብቸኛው ግብ ራሱን ከፍ ማድረግና በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ
ደረጃውን ማላቅ ነው፡፡ ይህም ቀድሞውኑም በዲያብሎስ የክፋት ሽንገላዎች ውስጥ
እንደወደቀ ሊያሳይ የሚችል ነው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የሰይጣንን ሽንገላዎች ተቃወሙ 311

ድልን ለመቀዳጀት ራሳችንን በእግዚአብሄር ቃል ማስታጠቅ አለብን፡፡

እኛ አሁን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን የሐጢያቶችን ስርየት


ስለተቀበልን ከሰይጣን ጋር ግጭት ውስጥ እንገባለን፡፡ የዚህ ውጊያ ውጤትም
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ማመናችን ወይም አለማመናችን ላይ የተመረኮዘ
ነው፡፡ እኛ በዚህ ጦርነት ላይ መሸነፍ የማንፈልግ ከሆነ የእግዚአብሄርን ቃል መያዝ
አለብን፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሄር ቃል ልክ እንደ ሰይፍ እንደሆነ ይናገራል፡፡
በመንፈሳዊ ውጊያችን ውስጥም የእምነትን ጋሻ ደግሞ ማንሳት ያስፈልገናል፡፡
ሰይጣን በውሸቶቹ ሊያስተን በሚሞክርበት ጊዜ ሁሉ እነዚህን ውሸቶች
በእግዚአብሄር ቃል ለይተን ማወቅና ዲያብሎስን በእምነት መቃወም አለብን፡፡
የዘመኑ ክርስቲያኖች የሚያምኑት ወንጌል እውነተኛ የእግዚአብሄር ወንጌል
አይደለም፡፡ ነገር ግን የእግዚአብሄር ፈቃድ እያንዳንዱ ክርስቲያን በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል እንዲያምን ነው፡፡ እኛ ለእያንዳንዱ የጠፋ ነፍስ ይህን
የእግዚአብሄር ሥራ የምንሠራው ለዚህ ነው፡፡
የእግዚአብሄር አገልጋዮች ሆነው የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል የሚሰብኩ
አዳዲስ ሠራተኞች ማስነሳትና መንከባከብም ደግሞ እግዚአብሄር ለእኛ ያለው
ፈቃዱ ነው፡፡ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል የሚሰብኩትን የእግዚአብሄር
አገልጋዮች ለመናቅ መሞከር ክፉ ነገር ነው፡፡ ያ የእግዚአብሄርን ሥራ መሥራት
አይደለም፡፡ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለመሰበክ የምንሠራው ሥራ
የእግዚአብሄር እንጂ የዲያብሎስ ሥራ አይደለም፡፡ ለውሃውና ለመንፈሱ ወንጌል
የማይኖሩ ሁሉ በሰይጣን ፈተና ውስጥ ይወድቃሉ፡፡
እያንዳንዱን የሰይጣን ውሸትና እያንዳንዱን ክፉ ሽንገላ ለይተን ለማወቅ
የእግዚአብሄር ቃል በእጅጉ ያስፈልጋል፡፡ በትክክል መለየትና መበየን የምንችለው
በእግዚአብሄር ቃል ነው፡፡ በቤተክርስቲያን ውስጥ እየሆነ ያለውን
በምንመለከትበት ጊዜ ሁሉ ሥራው የመንፈስ ቅዱስ እንደሆነ ወይም እንዳልሆነ
ማየት የምንችለው በእግዚአብሄር ቃል ነው፡፡
አብዛኞቹ አብያተ ክርስቲያናት ዓለማዊ ብልጥግናዎችን ለማከማቸትና
ተጽዕኖዎቻቸውን ለማስፋፋት ብቻ ይሞክራሉ፡፡ ሰይጣን ለሥራው እነዚህን
ስስታም መጋቢዎች ይጠቀማል፡፡ ዲያብሎስ እስከዚህች ቀን ድረስ ሲያደርግ
የነበረውን ስንመለከት ሁሌም የሚሠራው እንደዚህ መሆኑን እንመለከታለን፡፡
በዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ላይ የተጠቀሰው ‹‹ሥልጣናት›› የሚለው ቃል
የሚያሳየው የመንግሥታቶቸን ገዥዎች ነው፡፡ የሰይጣንን ሥራ ስንመለከት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


312 የሰይጣንን ሽንገላዎች ተቃወሙ

ዲያብሎስ በብሉይ ኪዳንም ይሁን በአዲስ ኪዳን በዚህ ዓለም ገዥዎች አማካይነት
እንደሰራ ማየት እንችላለን፡፡
በጥንቷ የቤተክርስቲያን ዘመን ሐዋርያቶች በሙሉ የውሃውንና የመንፈሱን
ወንጌል አምነው ሰብከዋል፡፡ በዚያን ዘመን በርካታ ሰዎች የውሃውንና የመንፈሱን
ወንጌል ከሐዋርያቶች ሰምተዋል፡፡ ሐዋርያቶች በጥንቷ የቤተክርስቲያን ዘመን
እንዲህ በሐይል የሰበኩት ወንጌል የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል እንጂ ሌላ
አይደለም፡፡ ነገር ግን ሰይጣን በሐዋርያቶች የተሰበከውን እውነት ለመቅበር
ቆስጠንጢኖስ የተባለውን ሰው ሥልጣን ተጠቀመ፡፡ ይህ ሰው የሮም ንጉሠ ነገሥት
በሆነ ጊዜ ከርስትናን የመንግሥት ሐይማኖት አድርጎ አጸደቀ፡፡ ሕይወት
ለክርስቲያኖች በጣም ቀላል ስለነበር ቆስጠንጢኖስ ከዚህ ዓለም ስጋዊ
ሥልጣናቶች ጋር እንዲስማሙ በማጥመድ ልቦቻቸውን ማዳከም ችሎ ነበር፡፡
ጳውሎስ ‹‹የሚንበለበሉትን የክፉውን ፍላጻዎች እንድናጠፋ›› (ኤፌሶን 6፡16)
መክሮናል፡፡ ይህ ማለት ጌታ በሰጠን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን
የሰይጣንን ጥቃቶች ማክሸፍ አለብን ማለት ነው፡፡ ሰይጣን በክፉ ሽንገላዎቹ
ትክክለኛውን እውነትና ትክክለኛውን እምነት ለማጥፋት እየሞከረ ነው፡፡ በየጊዜው
በልቦቻችን ውስጥ ስጋዊ መሻቶችን ያነሳሳል፡፡ ስጋዊ ስኬትን ብቻ እንሻ ዘንድ
እንደንፈተን በውስጣችን ስጋዊ ስስትን ይቀሰቅሳል፡፡ በሌላ አነጋገር ዲያብሎስ
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለጠፉ ነፍሳቶች ከመስበክ ይልቅ ትኩረታችንን
የጉባኤውን ቁጥር በመጨመር ላይ እንድናደርግ ያጠምደናል፡፡
የእግዚአብሄርን ቤተክርስቲያን በማገልገል ረገድ እጅግ ትልቁ ፈተና
አባላቶችን በማብዛት መታለል ነው፡፡ አገልጋዮቻችን ጠንቃቆች ካልሆኑ በቀላሉ
በዚህ ፈተና ውስጥ ሊወድቁና በእግዚአብሄር ትክክለኛ የእምነት ሕይወትን
ከመኖር ይልቅ የጉባኤውን መጠን በማሳደግ ላይ ብዙ ትኩረት ሊያደርጉ ይችላሉ፡፡
ሰይጣን ከረጅም ጊዜ ጀምሮ ይህንን ማታለያ ሲጠቀም ነበር፡፡ በዚህ ዕቅዱም
በተወሰነ ደረጃ ተሳክቶለታል፡፡ አሁንም እንኳን የእርሱ አገልጋዮች የዚህ ተመሳሳይ
ማታለያ ሱሰኞች ሆነዋል፡፡ በጣም ብዙ ሰዎች በእነዚህ ክፉና ቆሻሻ የሰይጣን
ሽንገላዎች እየተታለሉ ነው፡፡
እኛ ግን ሕያው የሆነውን የእግዚአብሄር ቃል በእምነት መያዝ፣ የእምነትን
ጋሻ መጠቀምና በዚህም የዲያብሎስን ቆሻሻ ሽንገላዎች በሙሉ ማሸነፍ አለብን፡፡
ማናችንም እዚህ ስህተት ውስጥ መውደቅ የለብንም፡፡ የእግዚአብሄር አገልጋዮች
በጉባኤያቸው መጠን መወጠር የለባቸውም፡፡ እግዚአብሄር ተጨማሪ ነፍሳቶችን
ካመጣልን አመስጋኞች ልንሆን ይገባናል፡፡ እንደዚህ ካልሆነ ደግሞ ለጠፉት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የሰይጣንን ሽንገላዎች ተቃወሙ 313

ነፍሳቶች መጸለይና አነርሱን መሻት ይገባናል፡፡ እናንተስ ታዲያ? የጠፉትን ነፍሳት


ፍለጋ ትወጣላችሁን? ወይስ በቂ ነገር እንዳደረጋችሁ በማሰብ ባላችሁበት ሁኔታ
ትረካላችሁ? ሁላችንም የጠፉ ነፍሳቶችን ፍለጋ መውጣትና እነርሱንም ለማዳን
ጠንክረን መሥራት ይገባናል፡፡ የእግዚአብሄርን ቃል በእምነት ይዘን የክፉውን ሥራ
ማጥቃትና ማጥፋት አለብን፡፡ በስጋዊ አስተሳሰቦች ውስጥ ሰጥመን በራስ ምቾት
በፍጹም መሸነፍ አይገባንም፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ እኛ ‹‹በክፉው ቀን ለመቃወም ሁሉን ፈጽመን ለመቆም
እንድንችል የእግዚአብሄርን ዕቃ ጦር ሁሉ ማንሳት›› (ኤፌሶን 6፡13) እንደሚገባን
ይናገራል፡፡ ይህ ምንባብ ግልጥ እንዳደረገው ሁላችንም እግዚአብሄርን መከተልና
በእምነት መኖር በእጅጉ ያስፈልገናል፡፡ ሁላችንም በጌታ ፊት የምንቆምበት ጊዜ
ሲመጣ ያለ አንዳች ሐፍረት ቀጥ ብለን መቆም የምንችለው በእግዚአብሄር ፊት
በእምነት ስንመላለስ ብቻ ነው፡፡
የእግዚአብሄርን ሥራ እንደምንሰራ እየተናገርን ራሳችንን ከፍ ማድረግ ተገቢ
አይደለም፡፡ የእግዚአብሄር ወገን የሆነ ሁሉ በእግዚአብሄር ጽድቅ በመታመን
ሌሎች ነፍሳቶችን ለማዳን መጣር አለበት፡፡ ሁላችንም የእግዚአብሄርን ቃል
መያዝና በዚህ እምነትም በተቻለ መጠን ብዙ ነፍሳቶችን ማዳን አለብን፡፡ ውጊያችን
ስጋዊ ውጊያ አይደለም፡፡ መንፈሳዊ ተጋድሎ ነው፡፡ ለእውነት ስንል ጦርነት
ያወጅነው በእግዚአብሄር ቃል ላይ ያለንን እምነት ለመከላከል ነው፡፡ አስፈላጊው
ነገር እንዴት የቤተክርስቲያናችንን አባሎች ማብዛት እንደምንችል ሳይሆን አሁንም
እንኳን በሰይጣን ቁጥጥር ሥር ሆነው እየተሰቃዩ ያሉ ብዙ ነፍሳቶችን ማዳን
እንችላለን ወይስ አንችልም የሚለው ነው፡፡
እግዚአብሄርን የወደድነው እኛ አይደለንም፡፡ ነገር ግን እግዚአብሄር
አስቀድሞ ወደደን፡፡ ነገር ግን እግዚአብሄር ሁላችንንም ቢወድደንም
የእግዚአብሄርን ፍቅር ከሌላው ሰው ጋር ከመካፈል ይልቅ የራሳችንን ፍላጎቶች
ብቻ የምንሻ ከሆንን መጨረሻችን አጭበርባሪዎች መሆን ይሆናል፡፡
ሁላችንም የዲያብሎስን ሽንገላዎች ለመቋቋም በቃሉ በማመን
የእግዚአብሄርን ዕቃ ጦር በሙሉ መልበስ አለብን፡፡ የሰይጣን ሽንገላዎች በቃላት
ሊገለጡ የማይችሉ ክፉና መሰሪ ናቸው፡፡ እነዚህን ክፉ ሽንገላዎች ለማሸነፍ
በእምነት የእግዚአብሄርን ዕቃ ጦር ሁሉ መልበስና ዲያብሎስን መቃወም አለብን፡፡
ክፉው ዲያብሎስ ተጽዕኖዋችን ቢያድግ የሕይወት ወንጌል ይበልጥ እንደሚስፋፋ
እንድናስብ ቢፈትነንም በተጨባጭ ግን ነገሩ እንዲህ አይደለም፡፡ ሰይጣን ስለ
ዓለማዊ ተጽዕኖዋችን ማደግ እንድናስብ ሊያታልለን እየሞከረ ነው፡፡ ነገር ግን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


314 የሰይጣንን ሽንገላዎች ተቃወሙ

ለዚህ ፈተና እጅን መስጠት ለዲያብሎስ ክፉ ሸንገላዎች መማረክ ነው፡፡


የእግዚአብሄር ቃል በትልቅ ጉባኤ ላይ ተመስርተን ተጽዕኖዋችንን
በመለማመድ አይሰበክም፡፡ የእግዚአበሄርን ቃል መያዝ ያለብን በእምነት ነው፡፡
ወደ ሐጢያተኞች መድረስና ነፍሳቸውንም ማዳን የሚገባን በዚህ ቃል በመታመን
ነው፡፡ ችግሩ ግን በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ በክርስቶስ እንደሞቱ
ሳያውቁ በእምነት እየኖሩ እንደሆኑ የሚያስቡ አንዳንድ ሰዎች መኖራቸው ነው፡፡
እነዚህን ቅዱሳኖች ለሐጢያቶቻቸው ቀድሞውኑም ከክርሰቶስ ጋር አብረው
እንደሞቱና ከክርስቶስ ጋር አብረው እንደተነሱ ልናስተምራቸው ያስፈልገናል፡፡
ቅዱሳኖቻችን እውነተኛ የእምነት ሕይወትን እንዲኖሩ ልንንከባከባቸው በእጅጉ
ያስፈልገናል፡፡ በተቻለ መጠንም ብዙ ሐጢያተኞችን ለማዳንም የኢየሱስ
ክርስቶስን የሕይወት ወንጌል በመስበክ መቀጠል አለብን፡፡ የእግዚአብሄር ሥራ
ሌላ ሳይሆን ይህ ነው፡፡
የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምኑ
አማኞች የሚሰበሰቡባት ስፍራ ነች፡፡ የቤተክርስቲያን ተጽዕኖም ሲያድግ ብዙ
ነፍሳቶችን ለመሳብ አቅጣጫዋን ትቀይራለች፡፡ ነገር ግን ከዚህ ጋር የሚመጣም
ትልቅ መንፈሳዊ አዘቅት አለ፡፡ ይህም በዚህ መንገድ ተግበስብሰው ወደ
ቤተክርስቲያን የተሳቡት ሰዎች ከስንዴ ይልቅ እንክርዳድ እንደሚሆኑ የታወቀ
ነው፡፡
ስለዚህ ከቤተክርስቲያናችን ጋር ለመቀላቀል የሚጠባበቁ አዳዲስ
ምዕመናኖች ሲኖሩ እምነታቸውን በጥንቃቄ መመርመርና በእርግጠኝነት
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል እንደሚያምኑ ማረጋገጥ በጣሙን ያስፈልገናል፡፡
ሰይጣን እስከዚህ ቀን ድረስ ሁሌም በኢየሱሰ ስም ሰርቷል፡፡ ወደፊትም ይህንኑ
ማድረጉን ይቀጥላል፡፡ ዲያብሎስ በክፉ ሽንገላዎቹ መንፈሳዊ ጠላቶቻችንን
ከመዋጋት ይልቅ ስጋና ደምን እንድንታገል እኛን በመፈተን ይቀጥላል፡፡ ስዚህ
መንፈሳዊ ውጊያችን ውስጥ ስንገባ ሰይጣን ምን ዓይነት ክፉ ማታለያዎችን
እንደሚጠቀም ማወቃችንና በሽንገላዎቹ ውስጥ በጥልቀት የተደበቀውን መሰሪ
ማጭበርበሪያ ማወቃችን በእጅጉ ወሳኝ ነው፡፡ የዲያብሎስ ግብ እኛ የውሃውንና
የመንፈሱን ወንጌል ለሰው ሁሉ እንዳንሰብክ መከልከል ነው፡፡
ስለዚህ ራሳችንን ከፍ እንድናደርግ የሚፈትነንና የእግዚአብሄርን ጽድቅ
ከማገልገል የሚከለክለን ሰው በመካከላችን ካለ ይህ ሰው የእግዚአብሄር አገልጋይ
እንዳልሆነ በእርግጠኝነት እናውቃለን፡፡ እንደዚህ ዓይነት ሰዎች የራሳችንን ስጋዊ
ፍላጎቶች እንድናጣጥምና ከራሱ ከእግዚአብሄር ይልቅም ሌላ ሰው እንድናገለግል

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የሰይጣንን ሽንገላዎች ተቃወሙ 315

የሚያጠምዱን ናቸው፡፡ እንዲህ በማድረጋቸው ሰይጣን ግቡን እንዲመታ እየረዱት


ነው፡፡ ግቡም የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል የማሰራጨት አገልግሎታችንን
ማበላሸት ነው፡፡ ሁላችንም ይህንን በግልጥ መረዳት አለብን፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ እዚህ በዛሬው የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ላይ
የእግዚአብሄርን ዕቃ ጦር ሁሉ እንድንለብስ የነገረን ለዚህ ነው፡፡ ጳውሎስ ይህንን
የመከረን ሁላችንም ክፉውን መቋቋምና የእግዚአብሄርን ሥራ ከሠራን በኋላም
በድፍረት በጌታ ፊት እንድንቆም ነው፡፡ ጳውሎስ የእግዚአብሄርን ዕቃ ጦር ሁሉ
እንድንለብስ የነገረን ለዚህ ነው፡፡ የእግዚአብሄርን ቃል መልበስ ይገባናል ማለት
በእግዚአብሄር ቃል በመታመን መንፈሳዊ ጦርነታችንን መዋጋት አለብን ማለት
ነው፡፡
ስለዚህ በሰብዓዊ አቅማችሁ ላይ፣ በአንደበተ ርቱዕ ንግግራችሁም ሆነ ወይም
በዕውቀታችሁ ላይ በመደገፍ የእግዚአብሄርን ሥራ ለመሥራት እንዳትሞክሩ
እጠይቃችኋለሁ፡፡ በእግዚአብሄር ቃል በማመን መሥራት አለባችሁ፡፡ ሁላችንም
በእግዚአብሄር ቃል ማመን፣ ይህንን ቃል የአገልግሎታችን እያንዳንዱ ነገር
የሚተዳደርበት መለኪያ ማድረግና በቃሉ መሠረትም የጌታን ጽድቅ ለማገልገል
መጣር ይገባናል፡፡ ምክንያቱም ሰይጣን እኛን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል
የምናምነውን አማኞች በስጋ ፍትወት ውስጥ እንድንወድቅ ሁሌም ሊያታልለን
ይሞክራል፡፡ ዲያብሎስ በስጋ ፍትወቶች ውስጥ እንድንወድቅ ለማድረግ ሁሌም
አጋጣሚን ይሻል፡፡ ይህ ማለት ሰይጣን ራሳችንን ለእግዚአብሄር ጽድቅ ከማስገዛት
ይልቅ በዚህ ዓለም ፍሰቶች እንድንሸነፍና በሰው ጽድቅ ውስጥ እንድንወድቅ
ሊያደርገን ይሞክራል ማለት ነው፡፡
ስለዚህ ድል አድርገን እስከምናሸንፈው ድረስ የዲያብሎስን ሽንገላዎች
መቃወም አለብን፡፡ የራሳችንን ጽድቅ ከማቆምና ራሳችንን ከፍ ከፍ ለማድረግ
ከመሞከር ይልቅ በወንጌል ጽድቅ ላይ መደገፍና እግዚአብሄርን ከፍ ማድረግ
አለብን፡፡ ይህንን ለማከናወንም በመንፈሳዊ ውጊያችን ውስጥ ዲያብሎስን በእምነት
ጋሻና በእግዚአብሄር ቃል ዕቃ ጦር ሁሉ ልንዋጋው ያስፈልገናል፡፡

እውነተኛ እምነት የተመሠረተው በተጻፈው የእግዚአብሄር


ቃል ላይ ነው፡፡

ሁላችንም የእግዚአብሄርን ቃል በማመን መንፈሳዊ ውጊያችንን እስከተዋጋን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


316 የሰይጣንን ሽንገላዎች ተቃወሙ

ድረስ ሰይጣንን መቃወም እንችላለን፡፡ ነገር ግን እናንተ ራሳችሁ በእግዚአብሄር


ቃል ካልታመናችሁ ዲያብሎስ ሲፈተናችሁ ትወድቃላችሁ፡፡ የሰይጣንን ፈተናዎች
መናቅና ሲያጠቃችሁም እርሱን መቃወም የምትችሉት በእግዚአብሄር ቃል ላይ
የማይናወጥ እምነት ሲኖራችሁ ብቻ ነው፡፡ ስለዚህ የሰይጣንን አገልጋዮች
በምንቃወምበት ጊዜ በእግዚአብሄ ላይ በእጅጉ እምነት ሊኖረን ያስፈልገናል፡፡
የእግዚአብሄር ቃል በልቦቻችን ውስጥ የእምነታችን መለኪያ ሆኖ
እስካልተቀመጠ ድረስ እውነቱን ከስህተት መለየት አይቻለንም፡፡ በመጨረሻም
በመንፈሳዊ ውጊያችን እንሸነፋለን፡፡ ወደ መንፈሳዊ ውጊያችሁ ስትገቡ እነርሱን
ከመቃወማችሁ በፊት በመጀመሪያ ጠላቶቻችሁን በግልጥ መለየትና ምን ያህል ክፉ
እንደሆኑ ማወቅ ይኖርባችኋል፡፡ መንፈሳዊ ጠላቶቻችሁ ጥሩም መጥፎም ጎኖች
እንዳሉዋቸው በማሰብ ልትለዩዋቸው ካልቻላችሁ በቆራጥነት ልትቃወሙዋቸው
አትችሉም፡፡ በሌላ አነጋገር የጠላቶቻችሁ አባባሎች ሁሉ ስህተት እንዳልሆኑ
በሚያሻማ መልክ የምታስቡ ከሆነ ባለ በሌለ ሐይላችሁ ሁሉ ልትዋጉዋቸው
አትችሉም፡፡ መጨረሻችሁም በእነርሱ መቦጫጨቅ ይሆናል፡፡
ዲያብሎስ ግልጥ በሆኑ ክፉ ነገሮች ብቻ አያጠቃንም፡፡ ይልቁንም ሰይጣን
አብዛኛውን ጊዜ የእግዚአብሄርን ጽድቅ እንድንቃወም ቃሉን በማጣመም እኛን
ለማታለል የእግዚአብሄርን ቃል ይጠቀማል፡፡ ስለዚህ የሰይጣንን ሽንገላዎች
ለመቃወም የማይናወጥ እምነት በእጀጉ ያስፈልገናል፡፡ በእግዚአብሄር ቃል ላይ
ባለን እምነታችን ዲያብሎስን መቃወም፣ የእርሱን ወንጌል ለመስበክም ጌታን
ማገልገል፣ ቤተክርስቲያንን ማገልገልና ሌሎች ነፍሳቶችን ማገልገል አለብን፡፡

የእግዚአብሄርን ቃል፣ መንፈስ ቅዱስንና እውነተኛውን የክርስቲያን


እምነት የምታቀርበው የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ብቻ ነች፡፡

ሁላችንም በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ስለምናምን በልቦቻችን ውስጥ


የእግዚአብሄር ቃልና መንፈስ ቅዱስ አለን፡፡ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
በመንፈስ ቅዱስና በውስጡ ባለው የእግዚአብሄር ቃል የምትሰብከው
የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ነች፡፡ በእግዚአብሄር ቃልና በውሃውና በመንፈሱ
ወንጌል ላይ ያረፈውን እውነተኛ እምነት ማግኘት የምንችለው በእግዚአብሄር
ቤተክርስቲያን ውስጥ ነው፡፡
ሐዋርያው ጳውሎስ ‹‹የእግዚአብሄርን ዕቃ ጦር ሁሉ እንድናነሳ›› (ኤፌሶን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የሰይጣንን ሽንገላዎች ተቃወሙ 317

6፡13) ከመከረን በኋላ እንዲህ በማለት ይቀጥላል፡- ‹‹በሁሉም ላይ ጨምራችሁ


የሚንበለበሉትን የክፉውን ፍላጻዎች ሁሉ ልታጠፉ የምትችሉበትን የእምነትን ጋሻ
አንሡ፡፡ የመዳንንም ራስ ቁር፣ የመንፈስንም ሰይፍ ያዙ፤ እርሱም የእግዚአብሄር ቃል
ነው፡፡ በጸሎትና በልመናም ሁሉ ዘወትር በመንፈስ ጸልዩ፡፡ በዚህም አሳብ ስለቅዱሳን
ሁሉ እየለመናችሁ በመጽናት ሁሉ ትጉ፡፡ ደግሞ የወንጌልን ምስጢር በግልጥ
እንዳስታውቅ አፌን በመክፈት ቃል ይሰጠኝ ዘንድ ስለ እኔ ለምኑ፡፡ ስለ ወንጌልም
በሰንሰለት መልዕክተኛ የሆንሁ መናገር እንደሚገባኝ ስለ እርሱ በግልጥ እናገር ዘንድ
ለምኑ፡፡›› (ኤፌሶን 6፡16-20)
ጳውሎስ እዚህ ላይ ራሱን ‹‹በሰንሰለት መልዕክተኛ የሆንሁ›› በማለት የጠራው
ይህንን የጻፈው በዚያን ጊዜ በሮም በሰንሰለት ታስሮ በግዞት ቤት ውስጥ ስለነበረ ነው፡፡
ጳውሎስ ወደ ሮም መሄድ የቻለው እንደ ወንጀለኛ በሰንሰለት በታሰረ ጊዜ ብቻ ነበር፡፡
ምክንያቱም በዚያም ደግሞ ወንጌልን መስበክ ነበረበት፡፡ በሌላ አነጋገር ሐዋርያው
ጳውሎስ በእግዚአብሄር ፈቃድ መሠረት በሰንሰለት በመታሰሩ የተደሰተው በሮም
መንግሥት ውስጥ ላሉ ታላላቅ ከፍተኛ ባለሥልኖች ወንጌልን መስበክ በመቻሉ ነበር፡፡
ወደ ሮም ከመሄድ መቅረት ቢችልም በሰንሰለት ታስሮ በፈቃዱ ሄደ፡፡ ስለዚህ
ሐዋርያው ጳውሎስ ለራሱ ስጋዊ ፍላጎቶች በፍጹም አልሰራም፡፡ ታዲያ ምን ሠራ?
እርሱ ሁሌም የሠራው የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ለማስፋፋት ነበር፡፡
ሁላችንም ከእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ጋር መተባበርና ሰይጣንንም
በእግዚአብሄር ቃል መቃወም አለብን፡፡ ዲያብሎስ እኛን ለማታለል በሚሠራበት ጊዜ
ሁሉ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ላይ ባለን እምነታችን ልንቃወመው ይገባናል፡፡
ለእኛ ራሳችንን ከፍ ማድረጉ፣ የራሳችንን ምቾት መሻቱ ወይም ዓለማዊ
ተጽዕኖዋቻችንን ለማስፋፋት መሞከሩ በሰይጣን ክፉ ሽንገላዎች ላይ መውደቅ ነው፡፡
ዲያብሎስ ሁሌም በውስጣችን እነዚህን ስጋዊ መሻቶች ለማነሳሳት ቢሞክርም እኛ ግን
ሁሉን ወርውረን ልንጥላቸው ይገባናል፡፡ በፋንታው የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን
በሰበከችው ቃል መታመን፣ በዚህ እምነትም የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
ማሰራጨትና እያንዳንዱን የጠፋ ነፍስ አንድ በአንድ ለማዳን ጥረታችንን ሁሉ አሳልፈን
መስጠት ነው፡፡

በእግዚአብሄር ቃል ላይ ባለን እምነታችን መጠንከር አለብን፡፡

በእነዚህ ክፉ ቀናቶች ውስጥ የምንኖር ሁላችን የእግዚአብሄርን ቃል

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


318 የሰይጣንን ሽንገላዎች ተቃወሙ

ማንሳትና ያለ መታከትም መንፈሳዊ ውጊያችንን መዋጋት አለብን፡፡ ይህንንም


ጦርነት በእምነት ማሸነፍ አለብን፡፡ ልቦቻችን በእግዚአብሄር ቃል ላይ እምነት
እስከሌላቸው ድረስ እኛም በሰይጣን ሽንገላዎች ውስጥ እንወድቃለን፡፡ በሌላ
አነጋገር በእርግጥ የእግዚአብሄርን ቃል ከሙሉ ልባችን የምናምን ከሆነ ሁላችንም
በመንገዳችን ላይ ምንም ዓይነት ፈተናና ምንም ዓይነት ስደት ቢመጣም ሰይጣንን
ማሸነፍና ድል ማድረግ እንችላለን፡፡ እስከ መጨረሻው ቀን ድረስ የጌታ አገልጋዮች
ሆነን መኖር የምንችለው በማይናወጥ እምነት በእግዚአብሄር ቃል ጸንተን ስንኖር
ብቻ ነው፡፡ በማናቸውም ሁኔታዎች ውስጥ ከእግዚአብሄር በቀር የማንንም ሌላ
ሰው ማረጋገጫ ለመሻት በዲያብሎስ እንታለል ዘንድ ለራሳችን መፍቀድ
የለብንም፡፡
እምነታችን በዚህ ዓለም ሰዎች በስፋት ድጋፍ ቢያገኝ የሚያስደምም
ሊመስለን ይችላል፡፡ ነገር ግን አንድ ሌላ ሰው ስለደገፈን ብቻ መደሰት ድጋፍ
ባላገኘን ጊዜ ደግሞ ተስፋ መቁረጥና የእግዚአብሄርን ሥራ ችላ ማለት አይገባንም፡፡
ይልቁንም እምነታችን ትክክል እንደሆነ ወይም እንዳልሆነ ለማወቅ የእግዚአብሄርን
ቃል ማሰላሰል ይገባናል፡፡ በሌላ አነጋገር ሊያሳስበን የሚገባው ነገር በእግዚአብሄር
ቃል ሲታይ እምነታችን ትክክል መሆኑ ወይም አለመሆኑ ነው፡፡ ራሳችንን
በእግዚአብሄር ቃል ስንመረምር በልቦቻችን ውስጥ ተጨባጭ የእምነት ማስረጃ
ካገኘን የእግዚአብሄር አገልጋዮች እንዳልሆንን ማመን አለብን፡፡ ነገር ግን ራሳችንን
በእግዚአብሄር ፊት የምንመረምርና በእርግጥም በቃሉ እንደምናምን የምናውቅ
ከሆነ እውነተኛ የእምነት ሠራተኞች ሆነን መኖር እንችላለን፡፡ ከሁሉም በላይ
ዲያብሎስን በእግዚአብሄር ቃል መቃወም አለብን፡፡
ይህ ዘመን ምን ያህል ከፉ እንደሆነ ታውቃላችሁን? እኛ በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል የምናምን አማኞች አንዳንድ ጊዜ ዳግመኛ ተወልደናል በሚሉ
አንዳንድ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያኖች በኑፋቄ እንከሰሳለን፡፡ እነርሱ በኑፋቄ
የሚከሱን አንዳንድ ጊዜ ጮክ ብለን ወደ እግዚአብሄር ስለምንጸልይ ነው፡፡ ነገር
ግን ጮክ ብሎ መጸለይ ኑፋቄ መሆኑ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተጻፈው የት ቦታ
ላይ ነው? እንዲህ ያሉ የማይረቡ አባባሎች የሚነገሩት እኛን ለመቃወምና
የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል ከስርጭት ለመከላከል ነው፡፡ እነዚህ የሰይጣን
አገልጋዮች በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን በቅርቡ የሐጢያቶችን ስርየት
የተቀበሉ አዳዲስ አማኞችን እንኳን ይዋሹዋቸዋል፡፡ ‹‹በዚያች ቤተክርስቲያን
ውስጥ ያሉ አማኞች በሚያመልኩበት ጊዜ ጮክ ብለው የሚጸልዩ አይደሉምን?
በአምልኮ ሰዓታቸውስ ይገለፍጡ የለምን? ስለዚህ መናፍቃን ናቸው!›› በማለት

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የሰይጣንን ሽንገላዎች ተቃወሙ 319

እነዚህ የተጋለጡ ወጣት አማኞች ይሰናከሉ ዘንድ የሚችሉትን ሁሉ ያደርጋሉ፡፡


ነገር ግን እግዚአብሄር እነዚህን ገና እንጭጭ አማኞች የሚያሰናክል ማንም ቢኖር
የወፍጮ ድንጋይ በአንገቱ ታስሮ ባህር ውስጥ እንዲጣል በማድረግ
እንደሚረግመው ተናግሮዋል፡፡
የእግዚአብሄርን ሥራ በመሥራት ስንቀጥል እውነተኞቹ መናፍቃን እኛን
ለማውገዝ እንዴት በርትተው እንደሚሠሩ ማየት እንችላለን፡፡ ሰዎች እንዲህ ባለ
መሰሪ ወጥመድ ውስጥ ሲወድቁ እነርሱ ራሳቸው መጠመዳቸውን አያውቁም፡፡
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የምናምን እኛ አማኞች እስካልተጠነቀቅን
ድረስ በሰይጣን አገልጋዮች ልንጎዳ እንችላለን፡፡ ይህ ችግር አብዛኛውን ጊዜ
የሚነሳው የእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ስታድግ ነው፡፡ ይህ የእግዚአብሄር
አገልጋዮች ተጋላጭ የሚሆኑበት ዘመን ነው፡፡ ምክንያቱም ሰይጣን የጉባኤውን
መጠን ለማብዛት ሲል ከሐሰተኛ ወንጌል ጋር እንዲያመቻምቹ ይፈትናቸዋልና፡፡
ነገር ግን እምነታችንን ለመጠበቅ የእግዚአብሄርን ትዕዛዝ ማስታወስ አለብን፡፡
የእግዚአብሄርን ቤተክርስቲያን በምንከተልበት ጊዜ ሁሉ ይህንን የምናደርገው በዚያ
አካባቢ ያሉትን የጠፉ ነፍሳቶች ደረጃ በደረጃ ከሐጢያቶቻቸው አንድ በአንድ
ለማዳን እንጂ የአባሎቻችንን መጠን ለማሳደግ አይደለም፡፡
የእግዚአብሄርን ወንጌል ለጠፉት ነፍሳቶች አንድ በአንድ ልንሰብክላቸውና
በግላቸውም የተለየ የቅርብ ክትትል ልናደርግላቸው ይገባናል፡፡ ሰይጣን በእነዚህ
የመጨረሻ ዘመናቶች የወንጌል አገልግሎታችንን ለማደናቀፍ እንዴት እንደሚሞክር
በመረዳት የእግዚአብሄርን ቃል በእምነት ማንሳትና በዚህ እምነትም መኖር
አለብን፡፡ ሁሌም የእግዚአብሄር ቃል አብሮን እንዲሆንና ትክክለኛው እምነት ምን
እንደሆነ በዚህ ቃል ለይተን ማወቅ እንድንችል በእጅጉ ያስፈልገናል፡፡ የሰይጣንን
ክፉ ሽንገላዎች ለመርታትና እርሱንም ድል ለማድረግ የምንችለው የእግዚአብሄርን
ቃል በእምነት ስናነሳና በዚህ እምነት ስንኖር ብቻ ነው፡፡
ከብሉይ ኪዳን እስከ አዲስ ኪዳን ድረስ ያለውን ሙሉ ቃል በ66ቱ
የመጽሐፍ ቅዱስ መጽሐፎች ታምናላችሁን? ጌታን ለማገልገል በእያንዳንዱ
የእግዚአብሄር ቃል ማመን በእጅጉ አስፈላጊ ነው፡፡ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
ማገልገል ከተሳነን ምክንያቱ በጭራሽ ሁኔታዎቻችን አስቸጋሪ ስለሆኑ አይደለም፡፡
ይልቁንም ወንጌልን ማገልገል መቻላችን ወይም አለመቻላችን ሙሉ በሙሉ
የተመረኮዘው ልቦቻችን በእግዚአብሄር ቃል እምነት ያላቸው በመሆናቸው ወይም
አለመሆናቸው ላይ ነው፡፡ እኛ የሚያስፈልገን በእግዚአብሄር ቃል ላይ በጽኑ
የተተከለ የማይናወጥ እምነት ነው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


320 የሰይጣንን ሽንገላዎች ተቃወሙ

በእርግጥ በእግዚአብሄር ቃል የምናምን ከሆነ የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል


በእርግጠኝነት በዓለም ሁሉ ይስፋፋል፡፡ እግዚአብሄር እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ
ሁሌም አብሮን እንደሚሆን እተማመናለሁ፡፡ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል
ለመሰበክ ወደ ዓለም ስንወጣ አምላካችን ተጨማሪ ነፍሳቶችን ያመጣልናል፡፡
ፍላጎቶቻችንንም ሁሉ ያሟላልናል፡፡ የልቦቻችንን እምነት በሙሉ በእግዚአብሄር
ቃል ላይ ካኖርን በኋላ ይህንን እንገነዘባለን፡፡ ስለዚህ ልቦቻችን በእግዚአብሄር ቃል
እምነት እስካላቸው ድረስ የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ያለ ምንም ችግር
ይስፋፋል፡፡
ከሙሉ ልቦቻችን በእግዚአብሄር ቃል እስካመንን ድረስ ሁኔታዎቻችን
በጭራሽ አስቸጋሪ አይደሉም፡፡ እነዚህ ሁኔታዎች እንዲያውም ችግር አይደሉም፡፡
አስቸጋሪ ሁኔታዎቻችን ተግዳሮት ሊሆኑ የሚችሉት የእግዚአብሄርን ቃል
ከልቦቻችን ሳናምን ከቀረን ብቻ ነው፡፡ በልቦቻችን ውስጥ በእግዚአብሄር ቃል
የሚያምን እምነት እስካለ ድረስ ችግር የሚባል ነገር የለም፡፡ በሌላ አነጋገር
የእግዚአብሄርን ቃል በልቦቻችን እስካመንን ድረስ ድል የእኛ ነው፡፡
ስለዚህ በእግዚአብሄር ቃል እምነት ካለን ጌታ እኛን ከሐጢያቶቻችን ሁሉ
ያዳነበት የውሃውና የመንፈሱ ወንጌል ይህ ዓለም ቢጠፋ እንኳን ፈጽሞ
አይጠፋም፡፡ ዓለም በዓይኖቻችን ፊት ብትጠፋም እንኳን ጌታችን አዲስ ሰማያትና
አዲስ ምድር ሊሰጠን ቃል ገብቷል፡፡ ስለዚህ እግዚአብሄር የሰጠን በረከት መቼም
አይጠፋም፡፡ እግዚአብሄር ሁሌም ከእኛ ጋር ነው፡፡ ይህ ማለት ሁኔታዎቻችን
ምንም ቢሆኑ እግዚአብሄር ሁሌም የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል በሚሰብኩ
ሰዎች ይደሰታል ማለት ነው፡፡ በእያንዳንዱ ዕርምጃችንም ይረዳናል፡፡ ጌታ
የቅዱሳኖችን ጸሎት የመመለሱም ተስፋ እንደዚሁ ውጤታማ ነው፡፡ ስለዚህ
ሁኔታዎቻችን አስቸጋሪ ቢሆኑም በእግዚአብሄር ቃል እስካመንን ድረስ ሁላችንም
የሰይጣንን ክፉ ሽንገላዎች ማሸነፍና በርካታ ነፍሳቶችን ማዳን እንችላለን፡፡

በእግዚአብሄር ፈቃድ የሚያምን እምነት ክፉውን ያሸንፋል፡፡

አጋር ምዕመናኖቼ በእርግጥ ለእግዚአብሄርና ለውሃውና ለመንፈሱ ወንጌል


ለመኖር የምንሻ ከሆነ እግዚአብሄር ራሱ እምነታችሁን ይደግፋል፤
ለሕይወታችሁም በሙሉ ይጠነቀቅላችኋል፡፡ ይህ እምነት ለሁላችንም በእጅጉ
አስፈላጊ ነው፡፡ ሁኔታዎቻችን አስቸጋሪ ቢሆኑና ፈጥነን ብዙ ተጨባጭ ውጤቶችን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የሰይጣንን ሽንገላዎች ተቃወሙ 321

ልናይ ባንችልም ከሙሉ ልባችን በእግዚአብሄር ከታመንን በእምነታችን መሠረት


ሁሉም ነገር ደህና ይሆናል፡፡ ነገር ግን የእግዚአብሄርን ጽድቅ በሙሉ ልቦቻችን
የማናምን ከሆነ የእግዚአብሄር ሥራ መጀመሪያ ላይ ደህና ቢሆንም ውሎ አድሮ
ይቆማል፡፡
ስለዚህ በእግዚአብሄር ቃል ማመናችን ለሁላችንም በእጅጉ አስፈላጊ ነው፡፡
ከሁሉም በላይ የእምነትን ጋሻ ማንሳትና በእምነትም የጠላቶቻችንን ጥቃት ማምከን
አለብን፡፡ የእግዚአብሄርን ቃል ሰይፍ በማንሳትም የሰይጣንን ክፉ ሽንገላዎች
ማሸነፍ አለብን፡፡ ይህ ለሁላችንም የእግዚአብሄር ፈቃድ ነው፡፡ በእግዚአብሄር
ጽድቅ በመታመን ክፋትን ማሸነፍ አለብን፡፡ በእግዚአብሄር ጽድቅና በውሃውና
በመንፈሱ ወንጌል ላይ እንዲህ ያለ እምነት ከሌለን ነፍሳችን ትጠፋለች፡፡
በምትጠቁበት ጊዜ ራሳችሁን የምትከላከሉበት ጋሻ አያስፈልጋችሁምን?
በእርግጥም ያስፈልጋችኋል፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምን እምነት
ሊኖረን የሚገባው ለዚህ ነው፡፡ ያን ጊዜ ማንኛውንምና ሁሉንም ጥቃቶች ማምከን
እንችላለን፡፡ በሰይጣን በምንጠቃበት ጊዜ ሁሉ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ላይ
ባለን እምነታችን እርሱን መቃወም አለብን፡፡ በእግዚአብሄር ቃል ላይ እምነት ካለን
የሰይጣንን ጥቃት ለይተን ማወቅና እርሱን ‹‹የእግዚአብሄር ቃል የውሃውና
የመንፈሱ ወንጌል ትክክል ነው፡፡ ስለዚህ በዚህ እውነተኛ ወንጌል አምናለሁ››
በማለት ልንቃወመው ይገባናል፡፡ በእግዚአብሄር ቃል ላይ ያላችሁ እምነት ጋሻችሁ
ነው፡፡ በዚህ የእምነት ጋሻ የሰይጣንን ሥራ ሁሉ ማጥፋትና በሁሉም ነገሮች እርሱን
ማሸነፍ እንችላለን፡፡ የዲያብሎስን መሰሪ ሽንገላዎችና ቆሻሻ የሆኑትን
ማጭበርበሪያዎቹን ሁሉ መርታት የምንችለው በእምነት ነው፡፡
ሁላችንም በእግዚአብሄር ቃል ላይ እምነት ይኖረን ዘንድ ምን ያህል አስፈላጊ
እንደሆነ እንደሚገባው አላተኮርኩበትም፡፡ ይህንን ክፉ ዓለም ማሸነፍ የምንችለው
ይህ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የሚያምን የማይናወጥ እምነት ሲኖረን ብቻ
ነው፡፡ በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል የምናምነውን አማኞች ምን ያህል ክፉ ጠላቶች
እንዳሉን ታውቃላችሁን? እኛን የሚቃወሙ በጣም ብዙ ሰዎች አሉ፡፡ ሁሉንም
በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ላይ ባለን እምነታችን ልናሸንፍ ይገባናል፡፡ የእኛ
ጉዳይ ማንም ሌላ ሰው የሚናገረው ነገር ሳይሆን እግዚአብሄር ራሱ የተናገረው
ነው፡፡ የእምነታችን ሁሉ መሠረቱ ያ ነው፡፡
እኛ ራሳችንን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል እውነት ከመንፈሳዊ ጠላቶቻችን
መጠበቅ ያለብን ሰዎች ብቻ አይደለንም፡፡ ነገር ግን በዚህ እውነተኛ ወንጌል
እስካመንን ድረስ ከክፉው የሚመጣውን ማንኛውንም ጥቃት በሙሉ ማምከን

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


322 የሰይጣንን ሽንገላዎች ተቃወሙ

እንችላለን፡፡ ክፉዎች ምንም ያህል ክፉኛ ቢያጠቁንም እኛ እነርሱን በሙሉ


የማምከን በቂ ችሎታ አለን፡፡ ስለዚህ መንፈሳዊ ውጊያችንን ለመዋጋት ከዕቃ ጦሮቹ
ሁሉ በላይ ይህንን የእምነት ጋሻ ማንሳት አለብን፡፡ አሁን እየኖርን ያለነው
በመጨረሻው ዘመን ላይ ሰለሆነ የእግዚአብሄርን ቃል በእምነት ማንሳት በእጅጉ
ያስፈልገናል፡፡
የእግዚአብሄርን ቃል በእምነት ማንሳት ማለት ምን ማለት እንደሆነ
ለማብራራት እዚህ ላይ አንድ ምሳሌ ልጠቀም፡፡ ጳውሎስ በገላትያ 2፡20 ላይ
እንዲህ አለ፡- ‹‹ከክርስቶስ ጋር ተሰቅዬአለሁ፡፡›› ይህንን ምንባብ ስታነብቡ
ከክርስቶስ ጋር የተሰቀለው ሐዋርያው ጳውሎስ ብቻ ሳይሆን እናንተም ራሳችሁ
እንደዚሁ ከክርስቶስ ጋር እንደተሰቀላችሁ ልትገነዘቡ ይገባችኋል፡፡ በሌላ አነጋገር
ኢየሱስ ክርስቶስ የሞተው ለሐዋርያው ጳውሎስ ብቻ አይደለም፡፡ ነገር ግን
በጥምቀቱ አማካይነትም የእናንተን የእኔን ሐጢያቶች በሙሉ ተሸክሞ ስለ እኛ
በመስቀል ላይ ሞቷል፡፡ እኛ ከክርስቶስ ጋር ተሰቅለናል ማለት አሮጌው ማንነታችን
ቀድሞውኑም በመስቀል ላይ ከኢየሱስ ጋር አብሮ ሞቷል ማለት ነው፡፡ በክርስቶስ
ትንሳኤም አብረን ተነስተናል ፡፡ ድላችን ላይ ለመድረስ የሚያስፈልገን ነገር ቢኖር
‹‹እኔም ደግሞ ከክርስቶስ ጋር ሞቻለሁ፤ አሁን ግን ጻድቅ ሰው ሆኜ እየኖርሁ ነው፡፡
አዲስ ፍጥረት ሆኛለሁ!›› በሚል ግንዘቤ በዚህ የእግዚአብሄር ቃል ማመንና
ዲያብሎስን በእምነት መቃወም ነው፡፡ ስለዚህ በእግዚአብሄር ቃል ማመንና
የእምነት ጋሻችን አድርገን ማንሳት ይገባናል፡፡
ሁላችንም በሕይወት ዘመናችን በርካታ ችግሮች ይገጥሙናል፡፡ በመንገዳችን
ላይ የሚመጡት መከራዎች ጥቂቶች አይደሉም፡፡ ባላንጣዎቻችንም እንደዚሁ
ጥቂቶች አይደሉም፡፡ በሕይወታችሁ ውስጥ ሁሉንም ዓይነት አስቸጋሪ ሁኔታዎችና
ልንወጣቸው የማንችላቸው የማይመስሉን እንቅፋቶች እንደደተጋፈጥን ሁሉ
እነዚህኑ ችግሮች ወደፊትም ደግሞ ትጋፈጡዋችዋላችሁ፡፡ እንዲያውም
መከራዎቻችሁ ጊዜ በነጎደ ቁጥር ይበልጥ አስቸጋሪ ይሆናሉ፡፡ በእግዚአብሄር ቃል
ላይ እምነት ሊኖራችሁና የዲያብሎስን ክፉ ሽንገላዎች ልትቃወሙ የሚገባችሁ
ለዚህ ነው፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


የሰይጣንን ሽንገላዎች ተቃወሙ 323

በየቀኑ መንፈሳዊ ውጊያችንን ስንዋጋ በመጨረሻ


የድል አክሊልን እንጭናለን፡፡

የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል የምናገለግለው ስጋዊ ስኬታችንን ለመሻት


አይደለም፡፡ ወንጌልን ማገልገል ከሰላማዊ ሕይወት በጣም የራቀ ነው፡፡ ነገሩ በየቀኑ
ሕይወታችን የእምነትን ጦርነት የመዋጋት ጉዳይ ነው፡፡ ይህ መንፈሳዊ ጦርነት
የሚደረገው በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል በማመን ነው፡፡ በየቀኑ በመንፈሳዊው
የእምነት ጋሻችን የሰይጣንን ጥቃቶች እናመክናለን፡፡ በየቀኑ ዲያብሎስን
እንቃወማለን፡፡ በየቀኑም በእርሱ ላይ ድልን እንቀዳጃለን፡፡ እምነታችሁን መኖር
ራሱ የጦር ሜዳ መሆኑን መረዳታችሁ በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ እኛ በኢየሱስ ጽድቅ
የምናምን አማኞች በእርግጥ የውሃውንና የመንፈሱን ወንጌል አብዝተን ማገልገል
የምንፈልግ ከሆነ ወደ መንፈሳዊ ውጊያችን ውስጥ በመግባታችን ደስተኞች ነን፡፡
ይህ ውጊያ ከስጋና ከደም ጋር የሚደረግ ውጊያ ሳይሆን መንፈሳዊ ተጋድሎ ነው፡፡
ወንድሞችና እህቶች እንደዚሁም ሁላችንም በአንዱ የጋራ የእምነት ጋሻችን
በዲያብሎስ ላይ መንፈሳዊ ውጊያን እየተዋጋን ነው፡፡ በዚህ መንፈሳዊ ውጊያ ላይ
ሳንሳተፍ የምታልፍ ቅጽበት የለችም፡፡
ወደ ብሉይ ኪዳን ስንመለስ በንጉሥ ዳዊት ዘመን 30 ጦረኞች ተነስተው
እንደነበር እናያለን፡፡ እነዚህ ጀግና ጦረኞች ነበሩ፡፡ በርካታ ውጊያዎችንም
አሸንፈዋል፡፡ በርካታ ጠላቶቻቸውንም ማርከዋል፡፡ እነዚህ ጦረኞች የንጉሥ ዳዊት
የታመኑ አገልጋዮች በመሆናቸውም በየቀኑ ጦርነትን በመዋጋት ደስተኞች ነበሩ፡፡
በእግዚአብሄር መንግሥት ውስጥም እንደዚሁ ብዙ ነፍሳቶችን የሚያድኑ ሰዎች
እምነታቸው ጠንካራ የሆኑ ሰዎች ናቸው፡፡ ጻድቅ የሆነ ቅዱስ ሰው ወደ መንፈሳዊ
ውጊያ ለመግባት ማመንታት የለበትም፡፡ ጻድቃን የሆኑ ቅዱሳኖች በማይረባ ትግል
ውስጥ ጊዜያቸውን ከሚያባክኑ ይልቅ ዲያብሎስን በመቃወምና በተቻለ መጠን
ብዙ የጠፉ ነፍሳቶችን በማዳን የክርስቶስ ወታደሮች ሆነው ሊኖሩ ይገባቸዋል፡፡
ስለዚህ ማንኛውም የሰይጣን አገልጋይ እናንተን ለመዋጋት በራችሁን ሲያንኳኳ
ከዚያ ውጊያ በፍጹም ራሳችሁን እንዳታሸሹ እጠይቃችኋለሁ፡፡
በቂ ልምድ ካለ በመንፈሳዊ ውጊያ ውስጥ መሳተፍ በጣም አስደሳች ነው፡፡
ለመጀመሪያ ጊዜ እንዲህ ያለ ጦርነት ማድረግ ቢያስፈራችሁም በእምነት
ለእግዚአብሄር ጽድቅ ለመኖር ሞክሩ፡፡ አንድ ጊዜ መንፈሳዊ ጦርነታችሁን
ከተዋጋችሁ ወዲያው በልምምዱ ትደሰታላችሁ፡፡ ምክንያቱም የጠፋችውን ነፍስ
ለማዳን የሚደረግ ትግል ነውና፡፡ እኛ ማንንም በስጋ ለማጥፋ አንሞክርም፡፡

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.bjnewlife.org


324 የሰይጣንን ሽንገላዎች ተቃወሙ

ጻድቃን የሆኑ ቅዱሳኖች በሙሉ በእምነት መንፈሳዊ ጦርነታቸውን መዋጋት


አለባቸው፡፡ በእግዚአብሄር ቃል ባላችሁ እምነት ዲያብሎስን ተዋግታችሁ
ስታሸንፉ የሚሰማችሁ ሐሴት በማንኛውም ሌላ ስፍራ ሊሰማችሁ አይችልም፡፡
ይህ ሐሴት ለማንም ሰው የሚሰጥ አይደለም፡፡ ስሜቱ የሚሰማቸው የክርስቶስ
መንፈሳዊ ወታደሮች ለሆኑት ሰዎች ብቻ ነው፡፡ ጻድቅ የሆነ ቅዱስ ዲያብሎስን
ለመዋጋት ማመንታት የለበትም፡፡ በእርግጥ የእግዚአብሄርን ሥራ ለመሥራትና
የውሃውንና መንፈሱን ወንጌል ለማገልገል የምትፈልጉ ከሆነ መንፈሳዊ
ጠላቶቻችሁን ለመቃወም ፈጽሞ ማመንታት የለባችሁም፡፡ ሁላችንም
በእግዚአብሄር ቃል በመታመን መንፈሳዊ ውጊያችንን መዋጋት አለብን፡፡
ዲያብሎስን መቃወምና ማሸነፍ የምንችለው በእግዚአብሄር አምነን ስንዋጋ ብቻ
ነው፡፡
በግላችን በፍርሃት የምንሸነፍ በጣም ልፍስፍሶች ነን፡፡ ስለዚህ
ከእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ጋር መተባበር፣ አብረንም መንፈሳዊ ውጊያችንን
መዋጋትና በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ላይ ባለን የጋራ እምነታችን ሰይጣንን
ማሸነፍ በእጅጉ ያስፈልገናል፡፡ ምንም ዓይነት መከራ ቢገጥማችሁ፣ የሚቃወማችሁ
ማንም ቢሆን፣ ጠላቶቻችሁም በእናንተ ላይ የሚወረውሩት ክስ ምንም ቢሆን
በጭራሽ ተስፋ አትቁረጡ፡፡ ነገር ግን በነገሮች ሁሉ በእግዚአብሄር ቃል በመታመን
መንፈሳዊ ውጊያችሁን ተዋጉ፡፡
የሰይጣንን መሠሪ ስትራቴጂ ለማወቅ ራሳችሁን አዘጋጁ፡፡ እምነታችሁን
አቀናጁ፡፡ ወንጌልን ማገልገል የምትችሉት የእግዚአብሄርን ቃል በመታመን
ዲያብሎስን ስትቃወሙ ብቻ ነው፡፡ በምንዋጋው በእያንዳንዱ መንፈሳዊ ውጊያ
ውስጥ ሁላችንም በእምነት አሸናፊዎች ሆነን በመውጣት እግዚአብሄርን እናክብር፡፡
ሁላችንም እምነታችንን በሙሉ በእግዚአብሄር ላይ በማኖር እግዚአብሄርን
እናክብር፡፡ 

በነጻ የሚታደል መጽሐፍ ለመጠየቅ www.nlmission.com


ዳውንሎድ
የሬቨረንድ ፖል ሲ. ጆንግን በነጻ የሚታደሉ የክርስቲያን ኢመጽሐፎችንና ኦዲዮመጽሐፎችን
ከድረ ገጻችን ላይ በስማርት ስልካችሁ፣
ታብሌታችሁ ወይም የግል ኮምፒውተራችሁ ላይ ገልብጡት፡፡
የኢንተርኔት ግንኙነት ሳይኖራችሁም እንኳን በየትኛውም ስፍራ ልታነቡዋቸውና
ልታዳምጡዋቸው ትችላላችሁ፡፡
www.bjnewlife.org

መነሻ ገጽ

ኦድዮ መጽሐፎች

ኢ-መጽሐፍት
Rev. PAUL C. JONG
ደራሲው የውሃውንና የመንፈሱን
ወንጌል ለሁለት አስር አመታት ያህል
ለጠፉት የዓለም ነፍሳቶች ሲሰብኩ
ቆይተዋል፡፡
የኒው ላይፍ ሚሽን መስራች
በመሆናቸው በአሁኑ ጊዜ በኒው ላይ
ሚሽን ብዙ የኢየሱስ ደቀ መዛሙርቶችን
እያፈሩ ነው፡፡
ሚሽን ተኮር ቤተክርስቲያኖችን
በመትከልም በጽሁፍ ሥራዎቻቸው
አማካይነት ወንጌልን እያሰራጩ ነው፡፡
መጽሐፎቻቸው በአሁኑ ጊዜ በ96
ዋና ዋና የዓለም ቋንቋዎች ተተርጉመው
እየተነበቡ ነው፡፡

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡
ሐዋርያው
ሐዋርያው ጳውሎስ
ጳውሎስ በጥልቀት
በጥልቀት የተረዳውን
የተረዳውን ያህል
ያህል የስላሴ
የስላሴ አምላክን
አምላክን ትልቅ
ትልቅ ዕቅድ
ዕቅድ
የተረዳ
የተረዳ ሰው
ሰው የለም፡፡
የለም፡፡ ይህንንም
ይህንንም ዕቅድ
ዕቅድ እንደ
እንደ ጳውሎስ
ጳውሎስ በግልጥ
በግልጥ የመሰከረ
የመሰከረ ሰው
ሰው የለም፡፡
የለም፡፡
ስለዚህ
ስለዚህ ሐዋርያው
ሐዋርያው ጳውሎስ
ጳውሎስ ለኤፌሶን
ለኤፌሶን በጻፈው
በጻፈው የኤፌሶን
የኤፌሶን መልዕክት
መልዕክት ውስጥ
ውስጥ በሚናገረው
በሚናገረው
እውነት
እውነት አማካይነት
አማካይነት ሁላችንም
ሁላችንም ስላሴ
ስላሴ አምላክ
አምላክ ጥልቅ
ጥልቅ ዕቅዱንና
ዕቅዱንና ፈቃዱን
ፈቃዱን ያለ
ያለ እንከን
እንከን
እንደፈጸመ መረዳት እንችላለን፡፡

-- ሬቨረ.
ሬቨረ. ፖል
ፖል ሲ.
ሲ. ጆንግ
ጆንግ --

የሬቨረንድ ፖል. ሲ. ጆንግን የክርስቲያን መጽሐፎች ወደ ኮምፒውተር፤ ወደ ታብሌት


ወይም ወደ ስማርትፎን ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) ትችላላችሁ፡፡

You might also like