Professional Documents
Culture Documents
ቅድስት
ቅድስት
ቅድስት
ርዕስ፡ "እኔ ቅዱስ እንደሆንኩ እናንተም ቅዱሳን ሁኑ!" 1ጴጥ 1፡ 13-15
ቅዱስ ማለት የቃሉ ትርጓሜ የተለየ፣ የተመረጠ፣ የሚለዉን ትርጉም ይይዛል፣ ከሁሉ
አስቀድሞ እግዚአብሔር አምላክ በባህሪው ቅዱስ ነው፣ (ጥቅስ) እርሱም ቅዱስ እንደሆነ
የእርሱ የሆነ ሁሉ ቅዱስ ነው፣ ማደርያው ቅድስት ቤተክርስትያን፣ እናታችን ቅድስተ
ቅዱሳን ንፅህተ ንፁሃን ድንግል ማርያም፣ መገልገያዎቹ ቅዱሳት ነዋያት፣ ቅዱሳን
መላዕክት፤ ቅዱሳን ዕለታት፣ ቅዱስ ቦታዎች፣ ቅዱሳን ሰዎች፤ የተቀደሱ ፀበል ቦታዎች፣
እነዚህ ሁሉ ቅድስናቸው የፀጋ የስጦታ ቅድስናቸውም ከእግዚአብሔር ነው፣ የእግዚአብሔር
አምላክ ቅዱስ የባህሪው የሆነ ነው፣
ዘይት ያልያዙት ሚዜዎች በአሁኑ ሰዓት ያለነውን በደንብ ይመስለናል። የመኪና ታርጋ
መልዮ ይመስል "እኔ ኦርቶዶክስ ነኝ" ከሚል ሐይማኖታችን እንደ ብሔር ብሔረሰብ የማልያ
ቲፎዞ ያላላለፈ የሆነብን ስንቶቻችን ነን? የተሰጠችንን የሥላሤ ልጅነት ሳንረዳው ወይንም
ንቀነው በዓለም በምትሰጠን ትምህርት አስተሳሰብ ከሐይማኖታችን ትምህርት
አስበልጠን በስመ ሥልጣኔ ወጀብ ወደ ሞት እየተወሰድን ያለን ስንቶቻችን ነን?
"ሰነፍ በልቡ አምላክ የለም ይላል" እንዲል እኛ በቃል ባናወጣውም፡ ባንናገርውም
በህይወት ስለማንኖረው እግዚአብሔር የለም ለሚሉት ዉስጥ መኖራችንን የማናቅ
ስንቶቻችን ነን? መታመናችን ሁሉ በራሳችን ላይ፡ በገንዘብ፡ በስልጣን፡ በሰው ላይ፡
በእዉቀታችን ላይ፡ በዉበታችን ላይ፡ በዝናችን ላይ፡ በዘራችን ላይ፡ በፖለቲካ ድርጅት ላይ፡
በምናደንቀው ግለሰብ ላይ፡ ስለሆነ ጣዖት ሆኖብን እግዚአብሔርንም አሳዝነነዋል። በስም
ኦርቶዶክስ እንባል እንጂ ምንም ክርስቶስ በእኛ ዉስጥ አይሸትም።
ማጠቃለያ
ክርስትና የተጋድሎ ህይወት ነው። እስከፍፃሜ ድረስ በተጋድሎ የምንሮጠው ህይወት
ነው። ለዚህም የሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለደቀ መዝሙሩ ጢሞትዮስ የጻፈለት መልክት
ላይ በግልጽ አስቀምጦልናል።