Professional Documents
Culture Documents
የመናፍስት ውጊያ ስልቶች
የመናፍስት ውጊያ ስልቶች
ክፍል-1 .............................................................................................................................................. 3
ክፍል - 2........................................................................................................................................... 7
ክፍል - 3......................................................................................................................................... 10
ክፍል - 1......................................................................................................................................... 14
ክፍል - 2......................................................................................................................................... 17
ቃለ እግዙአብሔር .............................................................................................................................. 21
ክፍል - 1......................................................................................................................................... 21
2
የመናፍስት ውጊያ ስልቶች
የመናፍስት አሳብ
ክፍል-1
በቅዱሳንም ሆነ በርኩሳን መደብ የተከፈሉ መልአክት እንደ ሰው ልጆች ሁሉ ፍጡራን ናቸው፡፡ በዙህ
ፍጡረነታቸውም ውስጥ የራሳቸው አሳብ፣ የራሳቸው አኗኗር፣ የራሳቸው ፍቃድ፣ የራሳቸው ስሜት፣ የራሳቸው
ዓላማ፣ የራሳቸው ግብር አለ፡፡ ቅዱሳንና ርኩሳን ተብለው ይለዩ ንድ የሆነውም በዙሁ ፍጡረነታቸው ውስጥ
በተገኙት የራሳቸው መገለጫዎች ምክንያት ነው፡፡ ቅዱሳን መልአክቱ በአሳባቸው፣ በአኗኗራቸው፣ በፍቃዳቸው፣
በስሜታቸው፣ በዓላማቸውና በግብራቸው ቅዱስ ሲሆኑ፤ ርኩሳኑ ደግሞ ከዙህ በተቃራኒው ይሆናሉ፡፡
የነዙህ ሁለት መልአክት የልዩነት ድንበር ደግሞ በኛም በሰው ልጆች ሕይወት ውስጥ የየዕለት ቦታ አለው፡፡
ርኩሳን መልአክት የራሳቸው ርኩስ መገለጫዎች ሁሉ ለራሳቸው ብቻ እንዲቀር አይፈልጉም፡፡ ቅዱሳን
መልአክትም የራሳቸውን መገለጫዎች ተጠቅመው የሰው ልጆችን ወደነርሱ የተቀደሰ አቅጣጫ ለማምጣት ታላቅ
ፍላጎት አላቸው፡፡ ለምሳሌ የቅዱሳን መልአክት አለቃ የሆነው ቅዱስ ሚካኤል፤ በአሳቡ ሁልጊዛ ሰዎችን ይረዳ
ንድ ወትር የሚያስብ፣ በአኗኗሩ በየሰዓቱ አምልኮትንና ምስጋናን በማቅረብ ሰማያዊ ኃይልን የሚያድስ፣ በፈቃዱ
የሰው ልጆችን ለመርዳትና ለማገዜ መሻት ያለው፣ በስሜቱ ለእግዙአብሔርና ለወዳጆቹ ቅዱሳን የማይናወጽ
ፍቅርና ክብር ያለው፣ በዓላማው ነፍሳት ይድኑ ንድ ጽኑ እቅድ ያለው፣ በግብሩ ደግሞ የእግዙአብሔርን ሕዜብ
የሚጠብቅና የሚመራ፥ ርኩሳኑን መልአክት በየቀኑ የሚዋጋ ነው፡፡
ርኩሳን መልአክት ርኩሰትን በመረጠው መገለጫቸው ምክንያት ከቅዱስ ስፍራ ተባርረው ከፀሐይ በታች
ወደ ምድር እንደ ተጣሉ መጽሐፍ ቅዱስ ነግሮናል፡፡ "ዲያብሎስና ሰይጣን የሚባለው ታላቁ ንዶ እርሱም
የቀደመው እባብ ተጣለ፤ ወደ ምድር ተጣለ መላእክቱም ከእርሱ ጋር ተጣሉ።" (የዮሐንስ ራእይ 12፥9)
እነዙህ ርኩሳን መልአክት በሰማይ ቅድስና ላይ ዓምፀው ከቅዱሳን መልአክት ጋር በነበረው ውጊያ
ከተሸነፉ በኋላ "በሰማይ ስፍራ አልተገኘላቸውም።" (የዮሐንስ ራእይ 12፥8)
ከዙያም ወዲያ በሰማይ ስፍራ ያልተገኘላቸው እነዙህ መናፍስት፤ ወደ ሰማይ ተመልሰው ቅዱሳን
መልአክትን ዳግመኛ መውጋት ባይችሉ፥ ከነርሱ መባረር በኋላ በምትኩ የገቡትን የሰው ልጆች ከሰማይ ስፍራ
እንደነርሱ ለመለየት የጠላትነት ዓላማ ይው፤ አጥፊ መንፈሳቸውም ወደ ሔዋን በእባብ በኩል ሄዶ የማሳት ግብሩን
ፈጸመ፡፡ ዲያቢሎስ እንዳሰበውም ተሳክቶለት የሰው ልጆችን ከገነት ቤታቸው እንዲባረሩና ከአምላክ ፈቃድ ተሰደው
እንዲወጡ አደረገ፡፡
ይህንንም አሳብ፣ ፍቃድ፣ ዓላማና ግብር ለማስፈጸም የመጀመሪያውን የግድያ ወንጀል በቃየን ሕይወት
ውስጥ ዲያቢሎስ እንደገለጠ በኦሪት ፍጥረት ምዕራፍ 4 ላይ እናያለን፡፡
3
የአዳም ልጆች አቤልና ቃየን ከሥራቸው ላይ ለእግዙአብሔር የሚቀርብን መሥዋዕት አጋጁ፡፡ አቤል
ከሰቡት በጎች መካከል መርጦ ዐሥራት በኩራት ሲያገባ፤ ቃየን ከተመረጠውም ካልተመረጠውም የተግበሰበሰ
የምድር ፍሬ ለእግዙአብሔር አድርጎ፥ ለራሱ ደግሞ ፍሬያማውን ምርት አሰቀርቶ ዐሥራት አገባ፡፡ በዙህ ጊዛ
"እግዙአብሔርም ወደ አቤልና ወደ መሥዋዕቱ ተመለከተ፤ ወደ ቃየንና ወደ መሥዋዕቱ ግን አልተመለከተም።
ቃየንም እጅግ ተናደደ ፊቱም ጠቆረ።" (ኦሪት ፍጥረት 4፥4-5)
አዳምና ሔዋን የሞትን በለስ በልተው ክፉውንና ደጉን ባወቀ ባሕሪያቸው በኩል ሲወልዱ ክፉውን
ቃየንና ደጉን አቤል ወለዱ፡፡ የመጀመሪያውን መተላለፍ እንደ ኃጢአት ድልድይነት በመጠቀም ወደ አቤልና ወደ
ቃየን ሕይወት የተጠጋው የዲያብሎስ ሠራዊት፤ ከቃሉ እንደምናነበው አቤል ለእግዙአብሔር ፍቅርና ክብር የነበረው
ሰው በመሆኑ እርሱን ለጥፋት መሣሪያነት ለመጠቀም አልቻለም፡፡ በቃየን ግን የሆነው እንዲህ አልነበረም፡፡
ቃየን ለእግዙአብሔር የሚያሳየውን ክብር በራስ ወዳድነት ጠባይ ከልሎ በመሸፈኑ፤ ጠላት ለእግዙአብሔር
የሚሰጠው መሥዋዕት ላይ እጁን እንዲያሳጥር የሕሊናውን ድምፅ በመመሳሰል አሳቡን በርዝ ወደ ወንጀል መንገድ
አስገብቶታል፡፡
ብዘዎቻችን በጥንቃቄ ልንረዳው የሚያስፈልገው ጉዳይ እዙህ ጋር ነው ያለው፡፡ በጽሕፈት ንባቡ ጥፋትን
ፈጸመ ተብሎ የተገለጸው ቃየን ነው፡፡ ከውስጡ ግን ለጥፋት ሥራ መጠቀሚያ ስላደረገው አጥፊ መንፈስ
እንድናስተውል መጽሐፍ ቅዱስ ኃላፊነቱን ለኛ ትቶአል፡፡ መጽሐፍ ይህን ክፍተት ሲተውልን ግን፤ በእባብ አካል
ሆኖ፥ የእባብ ሥጋዊ ተፈጥሮ ውስጥ የእርሱን አሳብ፣ ፈቃድ፣ ዓላማና ግብር እንዳስፈጸመ አስቀድሞ ነግሮን ነው፡፡
(በቃየን ሕይወት ውስጥ ተሰውሮ ጥፋትን እንዳስፈጸመ ድጋሚ እንዲጻፍልን የምንጠብቅ የዋሃን እንኖራለን፡፡ ነገር
ግን ዲያቢሎስ የኃጢአት ኃይል ነው ካልን፤ ከሥጋ አካልና ከሥጋ ምክንያት ጀርባ ኃጢአትን የሚያስፈጽመው
እርሱ በተገባ ማጤን ለኛ የተሰጠ ሰውኛ ድርሻ ነው፡፡)
ቃየን ከጠባዩ ፈቃድ ተመርቶ የተግበሰበሰ መሥዋዕትን ከገባ በኋላ፤ የእግዙአብሔር ፊት ወደ እርሱና ወደ
ዐሥራቱ አልዝር ባለ ጊዛ እጅግ ተናደደ ፊቱም ጠቆረ፡፡
ከላይ እንደተገለጸው ርኩሳን መናፍስት የራሳቸው የሆነ ስሜት አላቸው፡፡ ይህንንም ስሜት በቃየን ሰውነት
ውስጥ ሲገልጡት እንመለከታለን፡፡ የቃየን መናደድ በእርሱ ሰብአዊ ተፈጥሮ ውስጥ የተከናወነ ብቻ አይደለም፡፡
ውስጡ ባለው፥ ለእግዙአብሔር ፍቅርና ክብር ባጣ ልብ ውስጥ ኃይል ባገኘው፥ ርኩሰ መንፈስ ስሜት አበልጻጊነትም
እንጂ፡፡
በኑሮአችን ውስጥ በሚፈጠሩ ትንሽም ትልቅም ጉዳዮች ላይ ስንናደድ፤ አእምሮአችን ውስጥ በቅጽበት
መጥፎ ድምፆች ሲመላለሱ እንደራሳችን አሳብ ስለምንቆጥረው እነዚ ድሞፆች እንደሚመሩን በመሆን የጥፋት ግብርን
እንፈጽማለን፡፡ ስንቶች ተናደው ተሳደቡ? ስንቶች ተናደው ብዘ ተራገሙ? ስንቶች ተናደው ወንጀል ፈጸሙ?
ስንቶች ተናደው ንብረት አወደሙ? ስንቶች ተናደው ሰው ገደሉ?
በኃጢአት የሚገለጥ አንድ ግብርን ከመፈጸም አስቀድሞ ሁልጊዛ የዲያብሎስ ድምፅ በአእምሮአችን ላይ
የኛን የተፈጥሮ ድምፅ በመጠቀም ያንሾካሹካል፡፡ ወደኛ ሰውነት ለመግባት አንድ ብቻ የርኩሰት መንገድን እንደ
ድልድይ ሲጠቀም፤ ከኛ ውስጥ ሆኖ ደግሞ ወደ ውጪ ኃጢአትን ለማስፈጸምም እንዲሁ አንድ ብቻ ስሜትን ነው
የሚፈልገው፡፡ እነዙህም ስሜቶች ንዴት፣ ቁጭት፣ ቂም፣ ብስጭት፣ ትዕቢት፣ ምቀኝነት፣ ስግብግብነት፣
ትምክህተኝነትና የመሳሰሉት ናቸው፡፡
4
በቃየን ስግብግብነት ምክንያት ኃጢአትን ለማስፈጸም ዕድል ያገኘው አጥፊ መንፈስ፤ ተጨማሪ የቃየንን
ሰብአዊ ስሜት አበልጽጎ የንዴቱን ኃይል ከፍ በማድረግ፤ የእናቱን ልጅ አቤልን ያለ ጥፋቱ በጥላቻ እንዲያየው
ከውስጥ ሆኖ በዓይኖቹ ልክ አየ፡፡
ከልጅነታችን ጀምሮ "ርኩስ ነገር ሁሉ ከዲያቢሎስ ነው' የሚለውን ትምህርት በሚገባ ተምረንና በኑሮ
ውስጥ እያስተዋልን ስላልመጣን፤ ለክፉ ድርጊቶች ዓላማዊ ሰበብንና ትንተናን በመስጠት፤ ለጥፋት ክስተቶች
የርዕዮተ ዓለም አመለካከቶችንና ፍልስፍናዎችን በማስቀመጥ፤ ለግራ መም ነገራት የሥጋ መግፍኤዎችንና
መፍትሔዎችን ብቻ በመርር ለመናት ስለቆየን፤ በዓይን የማናየው ክፉው መልአክ ክፋትን ሁሉ እንደሚያደርግ
ልንረዳ አልቻልንም፡፡
እግዙአብሔር በሥነ ተፈጥሮ ሥራው ወቅት፤ ፍጥረታትን ከፈጠረ በኋላ "መልካም እንደሆነ አየ" ነው
መጽሐፍ ቅዱስ የሚለው፡፡ እግዙአብሔር በሰማይም በምድርም ያስገኛቸው 22ቱ ፍጥረታት በሙሉ መልካም
ናቸው፡፡ ስለዙህም አንድም ክፉ ነገር ከርሱ አላስገኘም፡፡
መልአክት በተፈጥሮ ግንባታቸው ከእሳትና ከነፋስ የተገኙ በመሆናቸው ረቂቅ ፍጡራን ናቸው፡፡ በግዘፍ
አካል ልናያቸው፣ ልንዳስሳቸውና ልናገኛቸው አንችልም፡፡ እነዙህ ረቂቃን ፍጥረቶች፤ ወደ ግዘፍ አካል ሲገቡ
የሚታየን ያ ግዘፍ አካል ብቻ ነው፡፡ ነገር ግን እነርሱ ደባል አካል ሆነው ስለመኖራቸው የምናውቀው፤ ያ ግዘፈ
አካል የእነርሱን አሳብ፣ ፍቃድ፣ ዓላማና ግብር መፈጸም ሲጀምር ነው፡፡ ልክ ፊኛ ውስጥ አየር ሲሞላ፤ በፊኛው
መጠነ ስፋት ማደግ አየሩ ስለመኖሩ እንደምንለየው፤ መናፍስትም ሰዎች ላይ አድፍጠው እየሠሩ ስለመሆኑ
የምናወቀው "ሰውየው ኃጢአት ይሠራል አይሠራም? በኑሮው ከእግዙአብሔር ጋር ሙሉ በሙሉ የተያያ ነው
አይደለም? ሕይወቱ በቅዱስ ነው ወይስ በርኩስ ነገር የተሞላው?" የሚለውን በመገንብ ነው፡፡ ዲያቢሎስ ከሰውነት
ውስጥ በማድፈጥም ሆነ ከሰውነት ውጪ ሆኖ በየቀኑ በመፈተን ሊያሰናክለው የማይሞክር አንድም የሰው ልጅ ግን
ከሰማይ በታች ፈጽሞ የለም፡፡ እንኪያስ ክርስቶስ ወደኛ ሰው ሆኖ የመጣው ለዙህ ነው፡፡ ሰው ሲሆን፤ እንደ
ሰውነቱ በዲያቢሎስ በመፈተን እንዴት እንደምናሸንፈው አርአያ ሆኖ በማሳየት ከርኩሳን መናፍስት አገዚዜ ነጻ
ሊያወጣን ነው በሥጋ ወንድማችን የሆነው፡፡ "በነጻነት ልንኖር ክርስቶስ ነጻነት አወጣን፤ (ወደ ገላትያ ሰዎች 5፥1)
ዲያቢሎስ በሰውነታችን ላይ ሲያድር በጣም ከሚፈልገው ነገር አንዱ፤ ከአእምሮአችን አሳብ ጋር ተመሳሳይ
አሳብ በመሆን አሳባችን ውስጥ መናገር ነው፡፡ ለምን፤ አሳብ ነዋ ወደ ተግባር የሚሄደው፡፡ አሳባችን ውስጥ ሲናገር
ታዲያ ልብ እንበል በኛ እውቀትና ድምፅ ልክ ነው፡፡ በሌላ ጎርናና ድምፅ፤ በባዕድ አነጋገር፤ በማናውቀው ሁኔታ
አእምሮአችን ውስጥ ቢያወራ እንደምንጠራጠር ግልጽ ነው፡፡ ስለዙህ "ይህ የኔ አሳብ ነው" ብለህ የሚናገረውን
አሳብ እንደራስህ ተመልክተህ እንድትቀበለው ባንተ ልክ ሆኖ ነው መንፈሳዊ ባላጋራህ የሚያንሾካሹከው፡፡
ቃየን ወንድሙ አቤልን በክፋትና በንዴት ካየው በኋላ በአሳቡ ውስጥ አጥፊው መንፈስ "ልግደለው
ልግደለው" እያለ ያንቃጭልበታል፡፡ እንደ ሁለተኛ ሰው ሆኖ "ግድለው ግድለው" መንፈሱ ቢለው ቃየን ውስጡ
5
በሚሰማው ድምፅ ግራ ይጋባል፡፡ ስለዙህ ከራሱ ጋር ተመሳስሎ የሚለው "ልግደለው ልግደለው" ነው፡፡ ይህንን
የውስጥ ውትወታ እንደራሱ ያስተናገደው ቃየንም "ወንድሙን አቤልን። ና ወደ ሜዳ እንሂድ አለው። በሜዳም
ሳሉ ቃየን በወንድሙ በአቤል ላይ ተነሣበት፥ ገደለውም። " (ኦሪት ፍጥረት 4፥8)
6
ክፍል - 2
የመናፍስትን አሳብ እንዴት እንለይ?
መጽሐፍ ቅዱስ ወደ ኤፌሶን ሰዎች መልእክት 6፥12 ላይ እንደሚነግረን በታላቅ ፍልሚያ የምንዋጋቸው
ጠላቶቻችን መንፈሳዊያን ናቸው፡፡ "መጋደላችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለምና፥ ከአለቆችና ከሥልጣናት ጋር
ከዙህም ከጨለማ ዓለም ገዦች ጋር በሰማያዊም ስፍራ ካለ ከክፋት መንፈሳውያን ሠራዊት ጋር ነው እንጂ።"
እነዙህ ጠላቶች ረቂቅ የሆነ የአእምሮ አሳባችን ውስጥ የራሳቸውን አሳብ በኛ ልክ አስመስለው ለማሳሰብ
የቻሉት ከዙህ መንፈሳዊ ተፈጥሮአቸው በመታገዜ ነው፡፡ እኛ በተፈጥሮአችን ረቂቅ የሆነና ግዘፍ የሆነ አካል
ሲኖረን፤ ጠላቶቻችን በተፈጥሮአቸው ረቂቃን ብቻ ናቸው፡፡ በመሆኑም የኛ ሥጋ ውስጥ ገብተው ረቂቁ ክፍላችንን
በመመሳሰል፤ ሕይወታችንን ተቆጣጥረው ወደ ራሳቸው ፍላጎትና አካሄድ አስተሳሰባችንን፣ ውሳኔያችንን፣
ጊዛያችንንና ዜንባሌያችንን ለመጠምዜ ይታገላሉ፡፡
የመንፈስ ቅዱስ ኃይል በውስጣችን ይዝታ ከሌለውና በውጊያ ላይ በመቆየት ስለ መናፍስቱ ባሕሪይና
አሠራር ልምድ ካላገኘን፤ ርኩሳን መናፍስት አሳባችንን ተቀላቅለው የነርሱን አሳብ ሲያሳስቡን ለመለየት በጣም
አዳጋች ይሆንብናል፡፡
ከመወለድ አንስቶ እስከ ዚሬ በደረስንበት የዕድሜ ቆይታ ውስጥ፤ ርኩሳን መናፍስት በሰውነታችን
ተደብቀው ፍጹም እኛን መስለው ሰብአዊ አሳባችንን በመሸፈን የነርሱን መናፍስታዊ አሳብ ለአእምሮአችን
እንደሚሞሉ በተደጋጋሚ ትምህርት እየወሰድን በሚገባ መረዳት ስላልተገነዜብን፤ ብዘ የምንሆን ሰዎች መናፍስት
ጭንቅላታችን ውስጥ ሲናገሩና በራሳችን አሳብ መስለው ሲመሩን አናውቀውም፡፡ እናስታውስ! ቃየን ወንድሙ
አቤልን ከመግደሉ አስቀድሞ፤ በሕሊናው ውስጥ 'ልግደለው ልግደለው' የሚለው የግፊት አሳብ ከሕይወቱ ያደባው
አጋንንት አሳብ እንደሆነ ማስተዋሉ አልነበረውም፡፡ እኛም የመናፍስትን አሳብ ከኛ አሳብ እንዳንለይ የምንቸገረው
በሦስት የሚከተሉት ምክንያቶች ነው፡፡
1. መናፍስት ምን ያህል በሰው ሕይወት ውስጥ ተመሳስለው እንደሚያደፍጡ መረጃው የለንም፡፡ ቢኖረንም
እንኳ የመመሳሰላቸው ጥግ የቱ ርቀት ያህል እንደሆነ በኛ ሕይወት አናስተውለውም፡፡ ብናስተውለውም
ይህንን ትምህርት በአስፈላጊው የፈተና ቦታ ላይ በተግባር የመመንሩ አቅም ያጥረናል፡፡
2. መናፍስቱ አሳባችን ውስጥ በሚያሾካሹኩ ጊዛ የኛን የመንቃት ግንዚቤ ተረድተውና ያለንን የባሕሪይ
ልክ ተጠቅመው ስለሆነ፤ ከውስጣችን የምንሰማው የአሳብ ንግግር ከኛ ይሁን ከአጥፊዎቹ ለመለየት
ይከብደናል፡፡
3. በመጨረሻ ከላይ ያሉትን ሁለቱን ፈተናዎች ተቋቁመን እንኳን ብንገኝ፤ የውስጥ ድምፃቸውን
በማስተዋል አድምጠን ከኃጢአት ዓላማቸው እንዳንሸሽባቸው በነባራዊ የሥጋ ምክንያቶች፣ ሁኔታዎች፣
አጋጣሚዎችና ጊዛዎች ያዋክቡናል፡፡ ለምሳሌ ቃየን በወንድሙ በአቤል ላይ እንዲቀና ያስገቡት
የመሥዋዕት ስጦታ ምክንያት ሆኖ ነበረ፡፡ መንፈሱ ያለ ምንም ምክንያት አቤልን እንዲገድል ቢገፋፋው፥
ነገሩ ለቃየን ግራ የሚያጋባ የውስጥ ግፊት ይሆን ነበረ፡፡ ይህንን ባንተ ሕይወት ውስጥ ስታመጣው፤
"አልጸልይም ደክሞኛል" የሚለውን የነፍስ መስተቃርን አእምሮህ ውስጥ ከማሰማቱ በፊት ጠላት ጊዛ
7
አጥሮህ የተገኘህበትን፣ በሥራ ተወጥረህ የዋልክበትን፣ ስሜትህ በአንድ አጋጣሚ የተጎዳበትን፣ የጸሎት
ፍላጎትን የሚጎዳ ክስተት የተፈጠረበትን፣ ወተ... ቀን ይጠብቃል (ያንን አይነት ቀን በአብዚኛው ራሱ
ቀደም ብሎ አሰልቶ እንደሚያጋጀው ልብ እንበል)፡፡ ለምሳሌ ከሰው ጋር እንድትጣላ ጭንቅላትህ
ውስጥ ከማንሾካሾኩ አስቀድሞ፤ ከሰው ጋር የሚያጣላ ሁኔታ መፍጠሩን ያረጋግጣል፡፡ ስለዙህ ከውጪ
ባለ የሥጋ ወከባ የሕሊናህን ትኩረት ወደ አንድ አቅጣጫ ከወሰደው በኋላ፤ በቀላሉ የአሳብ ድምፅ
በመሆን አንዳች የወደደውን ነገር እስክትፈጽምለት ድረስ አብዜቶ፣ ደጋግሞና በፍጥነት ይወተውትሃል፡፡
በመቀጠል የአሳቡን መድረሻ መመርመር፡፡ "ይሄ ያሰብኩት አሳብ ወዴት ነው የሚመራኝ? ምንድን እንዳደርግ
የሚፈልግ አሳብ ነው? ይህንን አሳብ ወደ ተግባር ባወርደው ምንድነው ሊከተል የሚችለው?" የሚለውን
በተቻለ አቅም ጊዛ ሰጥቶ በደንብ መመርመር፡፡
ጭንቅላታችን ላይ የመጣውን አሳብ መርምረን ሁኔታውን ከፈተሽን በኋላ አሳቡ ውስጥ ያለ ማንኛውም
ከእግዙአብሔር ተቃራኒ የሆነ ነገር የዲያብሎስ እንደሆነ መንቃት ያስፈልገናል፡፡
የቱንም ያህል ተራ ጉዳይ ይምሰል፤ ወደ ሰማያዊ እውነትና መንገድ የማይመራ፣ የቅድሰናና የመልካምነት
ኃይልን ያልፈለገ፤ የእግዙአብሔርን ነገር የሚሸሽና የሚቃወም፣ ኃጢአትን ለመፈጸም በር የሚከፍት፣ የአምልኮት
ሕይወት እንዳይቀጥል መስመር የሚያቋርጥ ከሆነ የዲያብሎስ መንፈስ አሳብ ነው፡፡ ምሳሌ ስንወስድ፦ መናደድ
ባለብን ትክክለኛ ምክንያት እንናደድ፤ ከውስጣችን ግን አሉታዊ ነገር እንድንናገር አሳባችን "በል በል" የሚለን
ከሆነ አንደበታችንን ለመቆጣጠር የሚፋለም መንፈስ በዚች ቅጽበት እየተዋጋን እንደሆነ ማገናብ የመንፈሱን አሳብ
ከኛ ለመለየት ይጠቅመናል፡፡
እነዙህ ሦስቱ መጠየቅ፣ ከዚ መመርመር አስከትሎ ከእግዙአብሔር አንጻር መፈተሽ የሚሉትን የመናፍስትን
አሳብ የመለያ ስልት በተግባር ለማውረድና ውጤታማ ለመሆን የሚፈልግ ማንኛውም ሰው በየቀኑ የአምልኮት
ስግደት ይሰግድ፣ ይጸልይና ጠላቱን በመቁጠሪያ ያደክም ንድ ግዴታው ነው፡፡
ብዘዎቻችን አናውቅም እንጂ የእግዙአብሔር መንፈስም ሕሊናችን ውስጥ የኛን አሳብ መስሎ ያወራል፡፡
የቅዱሳን መንፈስም የኛን የሕሊና ድምፅ መስሎ ያወራል፡፡ (ሕሊና ሕሊና የተባለበት ምክንያትም እኛን ጭምር ስለ
መልካም ነገር የሚወቅስ እረኛ ስለሆነ ነው፡፡) ስለ አንድ ያስቸገረን ጉዳይ ጸሎት ጸልየን ስንነሣ የሆነ ጊዛ ላይ
ያንን ችግር የሚፈታ አሳብ ሊመጣልን ይችላል፡፡ ይሄ አሳብ ጸሎታችንን ተከትሎ የወረደ የእግዙአብሔር ምሪት
እንደሆነ የማንረዳው እኛ፤ ችግራችን መፍትሔውን ካገኘ በኋላ መጸለያችንንም መቸገራችንንም ጭምር
እንረሳለን፡፡
8
ውሳኔ ልንወስን ስንል ሕሊናችን ውስጥ የተቃውሞ አሳብ የሚሆነው ይኸው ነፍሳችን ነው፡፡ ነፍስ ደግሞ
የእግዙአብሔር አካል ናት፡፡
እግዙአብሔር ከውስጣችን የሚያወራን በነፍሳችን በኩል ነው፡፡ ስለዙህ የአምልኮት ስግደት ስንሰግድ፣
ስንጸልይ፣ ጠላትን ስናደክም፣ ከአርያም ወደ ኑሮአችን የሚመጣው ሰማያዊ ኃይል ነፍሳችን ውስጥ ይገባል፡፡ በዙህ
ጊዛ ነፍሳችን ነዳጅ እንዳገኘ ሞተር አቅሟ ስለሚጨምር፤ ከላይ የተጠቀሱትን ሦስቱን የዲያብሎስ አሳብን የመለያ
መንገዶች በቅደም ተከተል በሚገባ እንድንተገብር ሕሊናችን ከአሳባችን ውስጥ ትናገራለች፡፡
9
ክፍል - 3
የመናፍስትን አሳብ ማስቆም እንችላለን?
ይህንን ጥያቄ አዎ አሊያ አይ ብሎ የውሳኔ መልስ የሚሰጥልን የመንፈሳዊ ልምምድ ጥንካሬያችን ደረጃ
ነው፡፡ የመናፍስቱን አሳብ ለማስቆም የበረታ የአምልኮት ክንድና የመሻት ትግል ሲጠይቅ፤ የመናፍስትን አሳብ ከጊዛ
ወደ ጊዛ በመቆጣጠር ለማስቆም ይቻል ንድ ያልተናጋ የውጊያ ቆይታ ያስፈልገናል፡፡
ብዘ ጊዛ ሰዎች ስለ ክፉ መንፈስ አሠራር ተምረው ጠላታቸውን መዋጋት ከጀመሩ በኋላ "እኔ አቅም
የለኝም ደካማ ነኝ፣ በጸሎታችሁ አስቡኝ እኔ አቃተኝ፣ እኔ ማድረግ አልችልም እርሱ ይርዳኝ እንጂ" የሚል
ከውጪው የእግዙአብሔርን ክንድ ድጋፍ የሚጠይቅ ከውስጡ ግን አውቆ የተኛ ልፍስፍስነትን የሚደብቅ ድምፅ
ያሰማሉ፡፡ የውስጥ ስሜታችንን፣ ልባችንን፣ ፍቃዳችንንና አካሄዳችንን ውስጣችን ስላደረ ማንበብ የሚችለው
የዲያብሎስ መንፈስ፤ እነዙህን ቀድሞ የመሸነፍ ቃላት እንደ ቀብድ አድርጎ ለግብሩ በመውሰድ የበለጠ
ልፍስፍስነት፣ የበለጠ አልችል ባይነት፣ የበለጠ አቅመ ቢስነት እንዲሰማን የማድረግ ዕድልን ከአንደበታችን ላይ
ተርጉሞ ይወስዳል፡፡
ውጊያ ላይ ሆኖ፤ ጠላትን የሚደመስስ ከባድ የጦር መሣሪያ ታጥቆ፤ በየዕለቱ በመበርታት ባላጋራን
የማጥቂያ መንገዱን አውቆ "አይ ደከማ ነኝ፥ አልችልም" እያሉ ማፈግፈግ በከባዱ መሣሪያ ደንግጦ የነበረውን
ኃይል የሚያበረታ ሲሆን፤ በድፍረት ይጠጋም ንድ ምልክት የሚሰጥ አካኋን ነው፡፡
የክርስቶስ ወታደሮች ነንና እኛም ጠላታችን ዲያቢሎስን በዕለት ዕለት የአምልኮት ስግደት፣ ጸሎትና
መቁጠሪያ እያደከምነው፤ በቅዱስ ቁርባን እየደመሰስነው፤ ፈተናውን ሁሉ እንደ እምነት ማበልጸጊያነት ለመጠቀም
የምንችልበት የአምልኮት መንገድ ላይ ቆመን "አይ እኔ እንዲህ ነኝ፣ እንዲህ ስለሆነ እኮ ነው፣ በዙህ ምክንያት ነው
እኮ" ብለን የምንሰጠው የማፈግፈግ ሰበብ፤ ፈርተውን የነበሩትን ክፉ መናፍስት ጉልበት የሚሰጥና እንደገና
አንሰራርተው ስልት በመቀየር እንዲዋጉን አቅም የሚያጠነክር ሁኔታ መሆኑን ማወቅ አለብን፡፡
በዙህም የመናፍስቱን አሳብ ለመቆጣጠር የምናደርገው የውጊያ ሂደት የራሱ ጊዛ፣ የራሱ ውጥረት፣ የራሱ
ድካም፣ የራሱ ደስታ፣ የራሱ ድል እንዳለው አውቀን፤ በየቀኑ እንበረታ ንድ የነፍስ ፍላጎት ከሌለን፤ ስልቱን
ብንማረውም ሳምንት ተዋግተን ወደነበርንበት እንመለሳለን፡፡ ስለዙህ በቀኑ መጀመሪያና መጨረሻ ላይ የበረታ
የውጊያ አቋማችንን ከስነልቦና፣ ከአካልና ከመንፈሳዊ እድገት አንጻር እየፈተሽን የምንደክምበትን ክፍል ለማስተካከል፥
የምንጠነክርበትን ቦታ ለማጥበቅ የጥሞና ጊዛን ለራሳችን በመስጠት በየቀኑ መታደስ አለብን።
ሀ] የቅጣት ስግደት
በመጠየቅ፣ በመመርመርና ከእግዙአብሔር አንጻር በማየት ከውስጣችን የሚመላለሰውን አሳብ ከዲያቢሎስ
መሆኑን ከለየን በኋላ፤ አሳቡ እንዳይጠፋን በአንድ ነገር ላይ እንጽፈዋለን፡፡ በስልካችን አሊያ በማስታወሻ
ደብተራችን ሊሆን ይችላል፡፡ እንዲሁ በጭንቅላት ለመያዜ የምንችል ሰዎችም አሳቡን ይን እስከ ጸሎት መግቢያ
ሰዓታችን እንጠብቃለን፡፡
10
ጸሎት የምንገባበት ሰዓት ደርሶ የወትሩን ስግደት፣ ጸሎትና መቁጠሪያ ቅጥቀጣ ከጨርስን በኋላ፤ በአሳቡ
መሠረት ያንን አሳብ ከውስጣችን እንዲመላለስ ያደረገውን መንፈስ ለብቻው ጠርተን በማሰር እናሰግደዋለን፡፡
በተመሳሳይ በጸሎት ሰዓት አሳብ የሚበትን፣ ልቦናን የሚነጥቅ፣ ሕሊናን የሚረብሽ፣ ከውስጥ ሆኖ
የሚሳደብና ምናብን የሚበርዜ መንፈስ እንዲህ ባለ መንገድ ለብቻው አስሮ የቅጣት ስግደት በየጊዛው ማሰገድ
ነው፡፡
ነገር ግን የአእምሮን አሳብ ወደ እግዙአብሔርና ወደ እግዙአብሔር ቃላት መውሰድ በራሱ ራሱን የቻለ
ጸሎት እንደሆነ ልብ አንልም፡፡ በምሳሌ መንገድ ላይ አንድ ችግር አይተን "እግዙአብሔር ይፍታው" ብለን ከነፍስ
ማውራት ታላቅ ጸሎት ነው፡፡ ምክንያቱም ጸሎት ማለት በአጠቃላይ ከእግዙአብሔር ጋራ መነጋገር ነው፡፡
በተጨማሪም አጫጭር የሆኑትን የዳዊት መዜሙራት፣ አባታችን ሆይ፣ ሰላም ለኪ፣ ድርሳናት እና ሌላም
የሚመጣልንን የግል ጸሎት በየትኛውም ቦታ ላይ መጸለይ እንችላለን፡፡ ይህንን በተገባ የአእምሮ ንቃት
11
የምናደርስበት የወትር ልምምድ ላይ ሰንቆይ፤ ከውስጥ የሚመላለሱ የአጥፊ መንፈስ ሹክሹክታዎች እየደበዘ
እየደበዘ ይመጣሉ፡፡
ሐ] የቅጣት መቁጠሪያ
እንደ ቅጣት ስግደቱ ሁሉ፤ ከውስጥ ጭንቅላት የሚያወሩ መናፍስትን በመቁጠሪያ መቅጣት ይችላል፡፡
እንደ ስግደቱ፤ ከውስጥ አሳብ የሚያመጣውን መንፈስ ለብቻ ጠርተን፤ "ለብቻህ ጀርባ ላይ ታሰር" ብለን፤
በመቁጠሪያ መቀጥቀጥ አለብን፡፡ ለምንድን ነው ይሄ፤ አንደኛ ያንን የአሳብ መበረዜ ሥራ እየከወነብን ያለውን
መንፈስ በቀጥታ ባለጉዳይ አድርገን እንድንቀውረው የመንፈስ ቅዱስ ኃይልን እናነጣጥርበታለን፡፡ ሁለተኛ
መንፈሱን እንደነቃንበት ማገናቢያ ስለሆነ፤ የተሰወረው ጠላት ግልጽ መምጣት ይጀምራል፡፡ ይሄ ደግሞ
የፍልሚያውን ጉልበት እንድናሳድግ አቅምና ብርታት ይሰጠናል፡፡ ሦስተኛ መናፍስት ግብራቸው ስለሚለያይ፤ ዜም
ብለን በደፈናው ከምንቀጠቅጥ የባሰ ችግር እያመጣብን ያለውን መንፈስ ቅድሚያ ለማስቆምና እርሱም ያንን
ችግር እያከናወኑ ባልሆኑ መናፍስት ተደብቆ፤ ደካማ መናፍስትን እያጋለጠ ግብሩን ቀጥሎ የአምልኮታችንን ሞራል
"እየቀጠቀጥኩም ሥራውን አያቆምም እንዴ?" ብለን የምንጎዳበት አሳብን አበልጽጎ እንዳያጠቃን ለብቻ እየለየን
ነው ማድክም ያለብን፡፡
መ] በርዕስ መቁረብ
ቅዱስ ቁርባንን በዙህ የመናፍስት የአሳብ ውጊያ ውስጥ በሁለት መንገድ ርዕስ ሰጥተን መቁረብ
እንችላለን፡፡ አንደኛ አሳብን ለመቀደስ መቁረብ ሲሆን ሁለተኛው ያልተቀደሰ አሳብን ለማስወገድ መቁረብ ብለን፡፡
አሳብን ለመቀደስ ስንቆርብ የመቁረቢያ ርዕሰ ጸሎታችን እንዲህ ይሆናል፤ "በአሳብም፣ በንግግርም
በምግባርም ሁሌ ቅዱስ የሆንክ ቅዱስ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፥ ቅደስናህን አካፍለኝ፡፡ ከውስጤ ይመላለሱ ንድ
ያላቸውን አሳቦች አስቀድምና ባርካቸው፡፡ ሕሊናዬን በመለኮትህ ማርከው፡፡ ቃልህ በአእምሮዬ ውስጥ የታተመ ይሆን
ንድ ፍቀድልኝ፡፡ የውስጥ ሕይወቴን ከፊት እየቀደምክ ምራው፡፡ አባት ሆይ፥ ሕዋሳቶቼ ሁሉ ሰማያዊ ኃይልን
እንዲያገኙ ፍቃድህ ይሁን፡፡ አሜን" ብለን ጸልየን ለዙህ ጸሎት ማሳረጊያነት ቅዱስ ቁርባንን እንቀበላለን፡፡
ያልተቀደሰ አሳብን ለማስወገድ ስንቆርብ ደግሞ፤ "ኃጢአትን እንጂ ኃጢአተኛን የማትርቅ ንጉሥ ኢየሱስ
ክርስቶስ ሆይ፥ አቤቱ የኃጢአትን ኃይል ከሕሊናዬ ውስጥ ስበር፡፡ አሳቦቼ ጥፋትን ስለመሸከማቸው ይቅርታህን ስጠኝ፡፡
ጌታ ሆይ፥ የፍጥረታትን ሁሉ የውስጥ አሳብ ታውቃለህና የማልሸሽግህ ክፉ ምናቤን ከሕይወቴ አስወግድልኝ፡፡
በአእምሮዬ ጓዳ ክፋትን የሚያጋጀውን ርኩስ መንፈስ በደምህ እሰርልኝ፡፡ አሳቤን የሚበርዜ የዲያቢሎስ ኃይልን
አድክምልኝ፡፡ ሕሊናዬን ለመማርክ የሚደክመውን ጠላት በሰማያዊ ክንድህ አድክመው፡፡ ውስጡን በእሳት ፍላጻ
ንደፈው፡፡ እሳታዊያን መላእክት በእሳት ሰይፍ ያሰቃዪት ንድ ወደኔም ስደዳቸው፡፡ ሰውነቴ ውስጥ ክፉ አሳቡን
ማሳሰብ እስኪያቆምም ድረስ እንዲያሳድዱት እረኛዬ ሆይ እለምንሃለው" ብለን እንቆርባለን፡፡
ሠ] ቶሎ ቶሎ ማሰር
በእጅ ብልቃጥ የምትቀነሰዋ ቅባዕ ይት ካለችን፤ ከጸሎት ቦታም ውጪ ሆነን ክፉ አሳብ
የሚያመላልስብንን ጠላት በሰማያዊ ስሞች በማዜ አሳብ እንዲያቆም ነግረን ቅባቷን በመስቀል ምልክት ግንባር ላይ
12
እየቀቡ በመጠቀም "ግንባር ላይ ውጡና ታሰሩ፡፡ ከውስጤ አትለፍልፉ፡፡ አሳባችሁን አቁሙ፡፡" እያልን ማሰር
እንችላለን፡፡
እዙህ ጋር መረዳት የሚያስፈልገን፤ የዲያብሎስ መንፈስ ሲያደፍጥ በአብዚኛው በቁጥር ከአንድ በላይ ሆኖ
ስለሆነ፤ "በሥላሴ ስም ግንባር ላይ ታስራችኋል፡፡ ከውስጤ ጸጥ በሉ" ብለን ስናስራቸው፤ ሌሎች በዚ ትእዚዜ
ያልታሰሩ መንፈሶች ደግሞ ማሰራችን እንዳልሠራ ለኛ ለማሳየት ከታሰሩት መንፈሶች በመቀበል የውስጥ
ሹክሹክታቸውን ሊቀጥሉ ይችላሉ፡፡ ስለዙህ ከእምነት ሆነን የምንጠራው ሰማያዊ ስም መንፈሶችን እንደሚያዜ
አውቀን፤ ያለመነዋወጽ እየገሰጽናቸው መታገላችንን መቀጠል ይገባናል፡፡
13
የእምነት ኃይል
ክፍል - 1
የእምነት ኃይል የሚታየውን የማየት መገለጥ አይደለም፡፡ የእምነት መገለጥ የማይታየውን የማየት ጉልበት
ነው፡፡ በጨለማ ውስጥ ያለውን የማይታይ ብርሃን መመልከት ነው፡፡ ተስፋ በሚያስቆርጥበት ጊዛ ምንም
ማስተማመኛ ሳይኖር ተስፋ ማድረግ ነው፡፡ እምነት ማለት ይሄ ነው፡፡
ዓለም የሰዎችን የእምነት ኃይል ለማድከም ብዘ አይነት መንገዶችን ተጉዚለች፡፡ እነዙህ የተለያየ አቅጣጫ
ያላቸው ወደ አንድ መድረሻ የሚወስዱ መንገዶች፤ ሰማያዊ የእምነት ኃይልን ለመሸፈን ያደረጉት ጥረት ትልቅ
ስኬት አስገኝቶ፤ ዚሬ በኛም መን አማኝ የተባሉ ነገር ግን የማያምኑ ብዘ ሰዎች እንዲገኙ ምክንያት ሆኗል፡፡
በዙህ የዓለም ጥልፍልፍ መረብ ውስጥ ስንወድቅ፤ ለሕይወታችን፣ ለዕድላችን፣ ለእቅዳችን፣ ለፍላጎታችን፣
ለተስፋችን ዋስትና የሚሆንን ነገር የምንፈልገው ከተረጋገጠ ነገር ላይ ብቻ ሆነ፡፡ ብዘዎቻችን የሚታይ፣ የሚዳሰስና
የማይሸሽ አንድ ነገርን የኑሮ ማስተማመኛ ለማድረግ የምንደክመው ድካም መንፈሳዊ እውነታን ፍጹም
እንድንረሣው አድርጎናል፡፡
እነዚ ማስተማመኛ ይሆኑናል የምንላቸው የሚታዩ፣ የሚዳሰሱና ቅርብ ያሉ ነገራት ሊሆኑ የሚችሉት ቁስ
አካል ነው፡፡ በመሆኑም፤ ይህንን የእምነት መደገፊያ የሚሆንን ቁስ አካል ጊዛያችን ውስጥ ለማኖር የምንሮጠው
ሩጫ አስተሳሰባችንን፣ መሻታችንን፣ ምርጫችንን፣ ራእያችንን በሙሉ ወደ ቁስ አካል ቀየረው፡፡
ስለዙህ አሁን ስናስብ ለአንዳች ቁስ ነገር፣ ስንፈልግ የሆነ ቁስ ነገር፣ ስንመርጥ የሚታየውን ቁስ ነገር፣
ስንከተል አሳማኝ የመሰልንን አንድ ቁስ ነገር ነው፡፡
ይሄ ሁኔታችን እምነት የሚባለውን ከነፍስ የሚነሣ መንፈሳዊ ኃይልን እንዳንገነበው ትልቅ መጋረጃ
ሆኖብናል፡፡ ስንመላለስ በሥጋ ልክ አጠገባችን እንዳለው ቁስ ነገር መሠረት አድርገን ነውና፤ የነፍስ ጊዛ ምን
እንደሆነ፣ የነፍስ ድምፅ እንዴት እንደሚያወራን፣ የነፍስ ኃይል በምን መንገድ እንደሚገለጥ ለመረዳት አስቸገረን፡፡
እግዙአብሔር አምላክ ሰውን ከምድር አፈር ሲያበጀው፤ ሕይወት ያለው ፍጡር እንዲሆን እስትንፋሱን
ለግሶታል፡፡ ይሄ እስትንፋስ በእያንዳንዳችን ሕይወት ውስጥ የተገኘ ነፍስ የሚባል መለኮታዊ ክፍል ነው፡፡ ይሄ
መለኮታዊ ክፍል ኃይል እንዲያገኝ፣ ሥጋችንን እንዲቆጣጠር፣ የኑሮ ምሪትን እንዲያሳየን በሥጋችን በመስገድ፣
በመጸለይ፣ በመቁረብና ክርስትናን በመኖር የሚመጣ የአርያም ኃይል ያስፈልገዋል፡፡
የነፍስ ጥጋብ ሲባል ጾም ነው፤ የነፍስ ምግብ ሲባል ቅዱስ ቁርባን ነው፤ የነፍስ ጊዛ ሲባል የጸሎት ጊዛ ነው፤
የነፍስ ኃይል ሲባል የአምልኮት ስግደት ነው፤ የነፍስ ድምፅ ሲባል ሕሊናችን ውስጥ የምንሰማው በጎ የሆነው ድምፅ
ሁሉ ነው፡፡
እኛ ይህንን የነፍስ እውነታ ጥርት ባለ ግንዚቤ ልናውቀው ስላልቻልን፤ ቤተሰቦችም ሲያሳድጉን የሥጋ
ጥጋብ እንዲኖር፣ የሥጋ ምግብ እንዳይጠፋ፣ የሥጋ ጉልበት እንዳያጥረን፣ የሥጋ ትምህርት እንዳያመልጠን
አድርገው ብቻ ስለሆነ፤ ከልጅነታችን አንስቶ እየሰገድን፣ እየጸለይን፣ እየቆርብን እንደ ሥጋም እንደ ነፍስም
የሕይወት መገለጫ ያለን ሙሉ ሰው ሆነን አልኖርንም፡፡
14
ጥቂት የማንባል ሰዎች የእምነት ኃይል የሚባለው የነፍስ ጉልበት የለንም፡፡ እምነት ሲባል የሆኑ ጻድቅ
ሰዎች፣ የሆኑ ቅዱስ ሰዎች፣ የሆኑ የተለዩ ሰዎች ብቻ ያላቸው፤ ተዓምርን በመፈጸም ብቻ የሚገለጥ፤ ከውስጥ
ክፍላችን ሁሌ ይነው የምንዝረው ኃይል ሳይሆን ድንገት በአጋጣሚዎች መካከል የሚከሰት ቅጽበት አድርገን
እናስበዋለን፡፡
የእምነት ኃይል በሰዎች ልቦና ውስጥ፣ በሰዎች ሕይወት ውስጥ፣ በሰዎች ጊዛ ውስጥ እንዳይገለጥ
ዲያቢሎስ ለመናት ያለ እረፍት የተለያዩ ስልቶችን በመጠቀም ተግቶ ሠርቶ ውጤታማ ሆኗል፡፡
በማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 4 ላይ የምናየውም ይህን የዲያብሎስ መንፈሳዊ ኃይልን ለመዋጋት ዓለምን
የመጠቀም ስልቱን በክርስቶስ ላይ ሲሞክር ነው፡፡ ጌታችን ዐርባ ቀንና ለሊት በጾም ካሳለፈ በኋላ ተራበ፡፡ በዙህ ጊዛ
አጥፊው መንፈስ ቀረብ አለውና "የዓለምንም መንግሥታት ሁሉ ክብራቸውንም አሳይቶ፤ ወድቀህ ብትሰግድልኝ
ይህን ሁሉ እሰጥሃለሁ አለው።" (የማቴዎስ ወንጌል 4፥9)
ሰው የሆነው ጌታችን፤ በሰውነት ዓይኑ ዓለምን እንዲያይ፣ የምድርን ክብር እንዲጎመዥ፣ የመሬትን ዜናና
ከፍታ እንዲመኝ ዲያቢሎስ ዓለምን አሳየው፡፡ ጌታችን ግን እንደ መለኮትነቱም ያያልና "ሂድ፥ አንተ ሰይጣን"
(የማቴዎስ ወንጌል 4፥10) አለው፡፡
እኛም እንደ ሥጋና እንደ ነፍስ የተፈጠርን ሰዎች ስንሆን፤ ዲያቢሎስ የሥጋ ዓይናችን ላይ ዓለምን
ሲያሳየን በነፍስ ዓይናችን በኩል እንዳንመረምር የአምልኮት ሕይወት የለንምና፤ በምናየው ቁስ ልክ ስንኖር፤
መንፈሳዊ ነገር እየራቀን እየራቀን፤ በምድር የመኖር ትርጉም ወደ ሰማያዊ ቤታችን ለመመለስ የምንገነባው
መሰላል ላይ መሆኑ ጠፍቶን፤ ነገሮች እንደሚገለባበጡበት ሁኔታ የምንገለባበጥ ሰዎች ሆንን፡፡
ወደ ክርስቶስ ከውጪ በኩል ቀርቦ ዓለምን ያሳየው የዲያብሎስ መንፈስ፤ ዚሬ ከውስጣችን ሆኖ ከውጪ
ያለውን ዓለም ብቻ እንድናይ አስገድዶናል፡፡ ስለሆነም የእምነት ኃይል የሚባለው የማይታየው የነፍስ ጉልበት
እንዳይኖረን፤ የነፍስን እውነት በሥጋ ወከባና የጥድፊያ ኑሮ በመከለል፤ ለእንጀራው፣ ለዳባው፣ ለወጡ፣ ለቤቱ፣
ለመኪናው፣ ለሥራው፣ ለመዜናኛው ብቻ እንድንደከም ትኩረታችንን ከውስጥ በኩል ወደ አንድ የሥጋ አቅጣጫ
በመሰብሰብ ጠባብ መስመር ላይ አቁሞ ይመራናል፡፡
አንድ በጣም መገንብ የሚያስፈልገን ጉዳይ፤ የእምነት ኃይል እንዲደከም ዲያቢሎስ ማድረግ
የሚጠበቅበት ሕይወታችን ውስጥ ያሉትን የሥጋ ጊዛያት ማብዚት ነው፡፡ የእምነት ኃይል የሚመነጨው ከነፍሳችን
ላይ ስለሆነ፤ ነፍሳችን ጊዛ እንዳታገኝ በዓለም የሰዓት ኑሮ ጥድፊያ ውስጥ ገብተን በሥጋ ጊዛ ብቻ ቀናችንን
የምንጨርስ ሲሆን፤ ነፍሳችን ወደ ሥጋችን የምታስተላልፈው መለኮታዊ ኃይል አይኖራትም፡፡
ክፉው መንፈስ የእምነት ኃይልን ሰዎች እንዳያገኙ ሁለት መሠረታዊ መንገዶችን ይጠቀማል፡፡ አንደኛው
ዓለምን ማሳየት ነው፡፡ ጠዋት ማታ የሥጋ ኑሮ ኑሮአችን ከሆነ፤ ከዓለም ሰማይ በላይ ያለውን የእግዙአብሔርን
እውነት መመልከት አንችልም፡፡ ሁለተኛው እዙህ የጥፋት አሠራሩ ላይ ነቅተን በኑሮአችን ውስጥ የነፍስ ጊዛም
15
እንዲኖረን በቤታችን የጸሎት ቤት አጋጅተን የምንሰግድ፣ የምንጸልይና የምንቆርብ ከሆነ ደግሞ፤ የእምነት ኃይል
በነፍስ ጉልበት በኩል እንዳያድግ፤ የጥርጣሬ ሁኔታን ለሥጋችን ያመጣል፡፡ በመሆኑም መንፈሳዊ ልምምዳችንን
በምናደርግበት ሕይወት ላይ ስንሆን፤ የእምነት ኃይላችንን ለማድከም ሦስት ቦታዎች ላይ በመቀመጥ ይሠራል፡፡
አንደኛ ሕሊናችን ውስጥ የአሳብ ድምፅ በመሆን "ጸሎቴ ይሰማ ይሁን? ስግደቴን ፈጣሪ ይቀበል ይሁን?
ንሰሐዬ እውነት ኃጢአቴን አጥቦት ይሆን፣ የእግዙአብሔርን ስም ስጠራ በእርግጥ ርኩስ መንፈስ ይታሰርልኝ
ይሁን? ቅዱስ ቁርባን ብቀበል እውን ኃይል አገኝ ይሆን?" እያልን እንድናስብ ያደርጋል፡፡ (የመናፍስት አሳብ
ከምዕራፍ 1 ተመልከት) ይህን የማጠራጠር ስልቱ አስቀድሞ ሔዋን ላይ በመጠቀም ስኬታማ ሆኗል፡፡ "በውኑ
እግዙአብሔር ከገነት ዚፍ ሁሉ እንዳትበሉ አዜዝአልን?" (ኦሪት ፍጥረት 3፥1) በማለት፤ ሔዋን የእግዙአብሔርን
ትእዚዜ ጥርጣሬ ውስጥ እንድትከት እባብ ወደ ጆሮዋ ተጠግቶ አንሾካሹኳል፡፡ ዚሬ ይሄን የሚያጠራጥር
ሹክሹክታን አንተ አእምሮ ውስጥ ተመሳስሎ ቁጭ ብሎ ያሰማሃል፡፡
ሁለተኛ ኑሮአችን ውስጥ ደግሞ የጤና ችግሮችን በመፍጠር፣ የበረከት ማጣቶችን በማስከተል፣ የጊዛ
አደጋዎችን በማሳየት የእምነት ኃይላችን እንዲደነግጥ ለማድረግ ይሞክራል፡፡ በጌታችን መከራ ወቅት፤
ሲያቅፉት፣ ሲስሙት፣ ሲከተሉት፣ ሲሰሙት፣ ሲታዘት የነበሩት ደቀመዚሙርቱና ሕዜቡ የጨለማው ለሊት ወደ
ኑሮአቸው ሲመጣ የእምነት ኃይል ከድቷቸው ተበተኑ፡፡ ዚሬም የእምነት ኃይልህ እንዲከዳህ የጨለማውን
ለሊቶች ወደ ኑሮህ በማምጣት ዲያቢሎስ ያስፈራራሃል፡፡ ጤናችን ሲታወክ፣ የቤተሰባችን ጤና ሲታወክ፣
ያሰብነው አልሳካ ሲል፣ በጊዛያችን ውስጥ ተደጋጋሚ አደጋዎች ሲያንዣብቡ ብዘዎቻችን አማኝነታችን
ከውስጣችን ይበተናል፡፡
ሦስተኛ በሌሎች ሰዎች ላይ በመሆን የእምነት ሞራልን የሚነካ ንግግር በማናገር፣ የእምነት መገለጥ
እውነታዎችን በማንኳሰስ፣ የሥጋ እሳቦቶች እንዲፈጠሩ ተጽዕኖ በመፍጠር፣ የቅርብ ሰዎቻችን መንፈሳዊ
ውጊያና ኃይል እንዳይገባቸው አድርጎ ልቦናቸውን በማሰር የእምነት ኃይላችንን ከውጪ ወደ ውስጥ
ለመጉዳት ይፋለማል፡፡
16
ክፍል - 2
የእምነት ኃይል እንዴት ያድጋል?
አስቀድሞ እንደተመለከትነው የእምነት ኃይል በነፍሳችን ውስጥ የተገኘ የመንፈሳዊ ማንነታችን ክፍል
ነው፡፡ አንዳንዶቻችን በተለምዶ "እምነት የለኝም" ብለን እንናገራለን፡፡ በማስተዋል መረዳት የሚገባን ጉዳይ ግን
የእምነት ኃይል ያልተሰጠው አንድም ግለሰብ የለም፡፡ ነገር ግን የአብዚኞቻችን ይሄ ኃይል በዲያቢሎስ የተሸፈነ
ሲሆን የአንዳንዶቻችን ኃይል ደግሞ በዙሁ ጠላት አማካኝነት ወደ ክፉ አቅጣጫ ተለውጦ መንገድ ቀይሮአል፡፡
የእምነት ኃይል በኛና በእግዙአብሔር መለኮታዊ ኃይል መካከል አብሮ የመሥራትን ትስስር የሚገልጥ የነፍስ
ጉልበት ነው፡፡ ይሄ ሰማያዊ ክፍላችን ከውስጣችን እንዲያድግ ታዲያ አንድ ነገር ያስፈልገናል፡፡ እርሱም
ለእግዙአብሔር ያለን ንጹሕና እውነተኛ ፍቅር ነው፡፡
እምነት ከፍቅር የተወለደ ሲሆን መንፈሳዊ ኃይሉ ጠንካራ፣ የማይናወጥና የማይለዋወጥ ነው፡፡ እናስተውል!
የምንወዳቸውን ሰዎች ለማመን ቅርብ ነን፡፡ ምክንያቱም በፍቅር በኩል የሚፈጠረው ግንኙነት መተሳሰሪያ
መጠቅልያው እምነት ይሆን ንድ ግድ ነውና፡፡ በዙህም ምክንያት እምነት የመውደድ መሥፈርት ሲሆን
የሚገኝበት ሁኔታ ብዘ ነው፡፡
ስለዙህም እግዙአብሔርን እንደ አምላክ ማክበር እንደ አባት መወደድ ያስፈልገናል፡፡ እኛን ካለምክንያት
ለወደደበት ድንቅ ፍቅሩ የሚሆን የእውነት ፍቅር ከሌለን፤ የእግዙአብሔር የአምላክነት ርቀት እንጂ ሰው
እስከመሆን የደረሰበት ቅርበት አይገባንም፡፡ ይሄ ካልገባን የእምነት ኃይላችን ጉልበት የሚያገኝበት መንፈሳዊ ነዳጅ
አይኖረንም፡፡
የእምነትን ኃይል የማሳደጊያ ቁልፍ ቦታ ለእግዙአብሔር ያለን ፍቅር ላይ ነው፡፡ የሥጋ ወላጆቻችንን
ስለምንወዳቸው እንዲሁ እናምናቸዋለን፡፡ "እነርሱ እኮ ሊጎዷችሁ ነው፥ ራቋቸው" ብንባል ፍጹም ለመቀበል
የሚያዳግተን ይሆናል፡፡ ምክንያቱም ወላጆቻችንን በኛ ላይ ይህን ያደርጋሉ የሚል እምነቱ ስለማይኖረን፡፡
የሚሠሩትን በአጠገባቸው ሆነን ባናይ እንኳን በጥብቅ አካኋን እናምናቸው ንድ የሆነው ስለምንወዳቸው ነው፡፡
እንግዲያው ወላጆቻችንን ቤተሰብ አድርጎ የሰጠንን ሰማያዊ አባት መውደድ እንደምን አልቻልንም?
17
ማግኘትን እንፈልጋለን፡፡ ብዘዎቻችን እግዙአብሔር ላይ እርግጠኞች አይደለንም፡፡ ብዘ ቦታ ላይ ተዓምርና ፈውስ
መከታተል የምንወደውም ለዙሁ ነው፡፡ ፈውስ ካላየን "እግዙአብሔርን እኔን ሊፈውሰኝ ይችላል" ብለን እርግጠኛ
አንሆንም፡፡ ተዓምር ካልሰማን "እግዙአብሔር የማይቻለውን ጉዳይ እንዲቻል አድርጎ ይሠራዋል" ብለን እርግጠኛ
አንሆንም፡፡ ማረጋገጫ የሚሆንን ነገር በሌሎች ሕይወት ውስጥ ተመዜግቦ ካልተገኘልን፤ እግዙአብሔር ላይ
እርግጠኛ ለመሆን ይከብደናል፡፡ የምንወደውን ሰው ያለ ማረጋገጫ ባፈቀርንበት ግማሽ ልክ እንኳን እግዙአብሔርን
ከልብ አንወደውም፡፡
በደንብ በማውጠንጠን እርጋታ እናስብ፡፡ ጠንካራ ፍቅር ጠንካራ እምነትን በራሱ ይወልዳል፡፡ ስለዙህ
የእምነት ኃይላችን የደከመ፣ የቀነሰ አሊያ የሸሸን ሲመስለን እግዙአብሔር ጋር ያለንን ፍቅር ወደኋላ ተመልሰን
እንፈትሽ፡፡ ምክንያቱም፤ ፍቅር እምነትን ያመጣል፡፡ እምነት ደግሞ ተስፋን ያስገኛል፡፡ እንኪያስ፥ የእምነትና የተስፋ
መሠረት ይሆን ንድ ያለው ፍቅር ይሆናል፡፡ "እምነት ተስፋ ፍቅር እነዙህ ሦስቱ ጸንተው ይኖራሉ፤ ከእነዙህም
የሚበልጠው ፍቅር ነው።" (1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 13፥13)
18
በመሆኑም በየቀኑ የነፍስ ጊዛ በአሳባችንም፣ በንግግራችንም፣ በምግባራችንም ማሳለፋችንን ማረጋገጥ
ይገባናል፡፡ ከምንም በላይ በየቀኑ የአምልኮት ስግደትን ጠዋትና ማታ መስገድ፣ ወትር መጸለይ፣ በየጊዛው ቅዱስ
ቁርባንን መቀበል የነፍስ ጉልበትን በየዕለቱ በመጨመር የእምነት ኃይላችን እንዲያድግ ያደርጋሉ፡፡
ሐዋሪያቱን ከክርስቶስ ለመለየት ዲያቢሎስ የተጠቀመው ዴ ይሄ ነው፡፡ ከውጪ ሰይፍና ገመድ የያዘ ባለ
ብዘ ጭፍራዎችን ይዝባቸው መጣ፡፡ አጠገባቸው ያለው ኃያል አምላክ መሆኑን ፍጹም ረስተው ተረበሹ፡፡
እንደውምማ ስምዖን የተባለ ጴጥሮስ "ጌታ ሆይ፥ ካንተ ጋር ሞትንም ለመቀበል ዜግጁ ነኝ" ያለበትን አንደበት
ለወጠና "ኸረ አላውቀውም" እስኪል ድረስ ከውጪ በሚያየው ክስተት ተሸነፈ፡፡ ልብ እንበል‼ ዲያቢሎስ የውጪ
ክስተትን ካመጣ በኋላ፤ ከውስጥ ደግሞ የአዘሪት ሹክሹክታውን በዚ ክስተት መሠረት ያስከትላል፡፡ ጴጥሮስ ከላይ
በዓይኑ በሚያየው የግርፋትና የእንግልት ጊዛ እንዲደነግጥ ካደረገው በኋላ፤ ከውስጡ ቀድሞ የነበረው ዓይነጥላ
"አላውቀውም አላውቀውም" እያለ ሲያሾከሹክበት፤ ወደ ውጪም ይህንን ድምፅ አወጣና ሦስት ጊዛ
"አላውቀውም" ሲል ካደ፡፡ ነገር ግን ዶሮ በጮኸ ጊዛ ወደ ጌታ ዓይኖች በቀጥታ ቢመለከት፤ ከቁጣ ይልቅ ፍቅር፣
ከንዴት ይልቅ ይቅርታ፣ ከበቀል ይልቅ ምሕረትን ሲያነብበት፤ ነፍሱ በዚች ቅጽበት ጉልበት አገኘችና ከውስጥ
ያለውን ጥፋት በንስሐ አጠበው፡፡ ከዚ በኋላ አይደለም ከውጪ ባለ ክስተት ሊደናገጥ፤ እጅግ የከፉ መከራዎችን
እየታገለ፣ ብዘ እንግልቶችን እየተዋጋ፣ በአንድ ስብከት ሺዎችን ወደ ጌታው በረት እየመለሰ፣ ርዕሰ-ሐዋሪያት ሆኖ
19
የተሰጠውን ሰማያዊ ክህነት በምድር ላይ ገልጦ በትክክልም የቤተክርስቲያን ዓለት መሆኑን አሳይቶ ዲያቢሎስን
ሙሉ በሙሉ በማሸነፍ ለክርስቲያኖች አርአያ ሆኖናል፡፡
20
ቃለ እግዙአብሔር
ክፍል - 1
የእግዙአብሔር ቃል ሰማይና ምድር የተፈጠሩበት ኃይል ነው፡፡ የእግዙአብሔር ቃል መለኮታዊ መንፈስን
የሚሸከም ሥልጣን ነው፡፡ የእግዙአብሔር ቃል ተፈጥሮንና ፍጥረታትን በሰማያዊ ሞገስ ላይ የሚያስቀምጥ ጉልበት
ነው፡፡ የእግዙአብሔር ቃል ሰማያዊ እውነት የሚነገርበት የመንፈስ ቅዱስ ብርሃን ነው፡፡ የእግዙአብሔር ቃል በሰው
ልጆች ልብ ውስጥ የሚራ የአርያም መንግሥት ር ነው፡፡ የእግዙአብሔር ቃል ወደ ውስጠኛው ሕይወት በማለፍ
ነፍስን ከእግዙአብሔር መንፈስ ጋር የሚያገናኝ ድልድይ ነው፡፡ የእግዙአብሔር ቃል ክፉ መንፈሶችን የሚዋጋ
የእምነት ጦር ዕቃ ነው፡፡ የእግዙአብሔር ቃል ለሁሉም ፍጥረታት ምሪት ይሆን ንድ መንገድ ያለው በፍቅር
የተመሠረተ የሕግ አጥር ነው፡፡
ከመጀመሪያው የሰው ልጆች ትውልድ መነሻ አዳም ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ የሰው ልጆች
የእግዙአብሔርን ቃል በተለያየ መንገድ ወደ ሕይወታቸው ሲያስተናግዱ ቆይተዋል፡፡ በመነ አበው ትውልድ
የነበረውን ሁኔታ ስናየው፤ ራሱ እግዙአብሔር አምላክ በቀጥታ ሰዎችን ያነጋግራቸው ነበር፡፡ በመቀጠልም በመነ
ነቢያቱ ትውልድ እግዙአብሔር በመረጣቸው ሰው እየሆነ ሕዜቡን ያነጋግር ነበር፡፡ በተጨማሪም እንዲሁ
በተመረጡ ሰዎቹ በኩል ጽሑፎችን በማጋጀት ከትውልድ ትውልድ የሚሸጋገር ቃሉን እግዙአብሔር ይሰጥ ነበር፡፡
ለዙህ አንዱ ትልቁ ማሳያ መጽሐፍ ቅዱስ ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ በተለያዩ ሰዎች ጸሐፊነት በመንፈስ ቅዱስ
ደራሲነት የተሰነደ የቃለ እግዙአብሔር መዜገብ ነው፡፡
መን መንን በሚተካበት ተፈጥሮአዊ ዑደት ዚሬ ላይ ስንገኝ፤ አሁን ደግሞ ቃለ እግዙአብሔር በተለያዩ
ብዘ መንገዶች ወደ አማኞች ሕይወት ይደርሳል፡፡ በቀጥታ በዓውደ ምሕረት ስብከትም ይሁን፣ በጽሑፍ
ተጋጅተው በሚቀርቡ ጥራዝችም ይሁን፣ የመገናኛ አውታሮችን በመጠቀም ተንቀሳቃሽ ምስልን በማቅረብም
ይሁን ቀደም ሲል ከነበረው ታሪካዊ ሂደት በተስፋፋና አቅርቦቱም በጨመረ መልኩ ቃለ እግዙአብሔር ይተላለፋል፡፡
ሆኖም በጣም የሚገርመው፤ ቃለ እግዙአብሔር በተደራሽነቱ አድጎ በተለያዩ መንገዶች ቢሰጥም፤ ቃሉን
ሰምተን ፍሬ የማናፈራ ትውልዶችም በቁጥር የዚኑ ያህል ጨምረናል፡፡ በአባቶቻችን መን የእጅ ስልኮች
ሳይፈበረኩ፣ የቃለ እግዙአብሔር አስተላላፊዎች እንደ አሁኑ ሳይበዘ፣ የመገናኛ አውታሮች ሳይኖሩ በነበረበት ጊዛ
ላይ መንፈሳዊ ፍሬን ያፈሩ ትውልዶች ነበሩ፡፡ እኛ በአንጻሩ የቃለ እግዙአብሔር እጥረት ሳያጋጥመን፤ ፍሬያማ
የሆነ የመንፈስ ቅዱስ ውጤቶች መሆን ተስኖናል፡፡
21
የቃለ እግዙአብሔርን ፍሬ እንዳናፈራ የሆንንበትን መሠረታዊ ምክንያት በዙህ በሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 8
ላይ ጌታችን አስቀምጦታል፡፡ ቃለ እግዙአብሔርን ሰምተን ፍሬ ማፍራት ካልቻልን፤ እንግዲያው ከሦስቱ ፍሬ
ከማይሰጡ የመሬት ስፍራዎች የትኛው ሆነን ነው?
ስፍራ 1• መንገድ ዳር
"በመንገድ ዳርም ያሉት የሚሰሙ ናቸው፤ ከዙህ በኋላም ዲያብሎስ ይመጣል አምነውም እንዳይድኑ ቃሉን
ከልባቸው ይወስዳል።" (የሉቃስ ወንጌል 8፥12)
ትምህርቱን ተከታትለው እንደጨረሱ ግን ከውስጥ በኩል ያለው የዲያቢሎስ መንፈስ ሥራ ይጀምራል፡፡ "ከዙህ
በኋላም ዲያብሎስ ይመጣል" (የሉቃስ ወንጌል 8፥12)
አድፍጦ ያለው የርኩስ መንፈስ ሠራዊት፤ በተለይ ዓይነጥላ፤ ሰምተው የነበረውን ትምህርት አእምሮአቸው ላይ
ይሆንና ያደበዜዋል
ልቦናቸው ውስጥ ይገባና እየፈነቀለ ያወጣዋል (አሁን ራሱ ይሄን እያነበባችሁ ካልደጋገማችሁት የሆነ ያህሉን
ቃል ከውስጥ ይውጠዋል)
በነፍስና በሥጋ መካከል ይሆንና በሰማያዊ ቃል በኩል ነፍስ መለኮታዊ ጉልበት እንዳትካፈል ጥላ ሆኖ
ይጋርዳል
የተፈጥሮን የማስተዋል ኃይል በማዳከም የተከታተሉት የእግዙአብሔር ቃል በጭራሽ ግልጽ ያልሆነ ውስብስብ
ያደርገዋል
ከውጪ በኩል በኑሮ ወከባ መካከል በማጣደፍ ቃሉ በዓለም ኑሮ እንዲለወጥ ስልት ይቀይሳል
በዙህ ጊዛ ሰዎቹ አንብበው የማያነቡ፣ ሰምተው የማይሰሙ፣ አይተው የማያዩ የቃለ እግዙአብሔር ዳተኞች
ይሆናሉ
22
ስፍራ 2• ዓለት
"በዓለት ላይም ያሉት ሲሰሙ ቃሉን በደስታ የሚቀበሉ ናቸው፤ እነርሱም ለጊዛው ብቻ ያምናሉ እንጂ
በፈተና ጊዛ የሚክዱ ሥር የሌላቸው ናቸው።" (የሉቃስ ወንጌል 8፥13)
በዓለት የተመሰለው ልብ የእግዙአብሔርን ቃል በደስታ የሚቀበል ነው፡፡ ነገር ግን፤ ትምህርቱን ተቀብሎ
የሚጠይቀውን መሥዋዕትነት ለመቀበል ግን ፍቃደኛ ያልሆነ ልብ ነው፡፡
የሃይማኖት አካሄዳቸውን ባጠነከሩ ጊዛ ዘሪያቸው መናወጥ ይጀምራል፡፡ ሰው፣ ትምህርት፣ ሥራ፣ ዕድል ሁሉ
እምቢ ይላቸዋል
ስፍራ 3• እሾህ
"በእሾህ መካከልም የወደቀ እነዙህ የሚሰሙት ናቸው፤ መንገዳቸውንም ሄደው በሕይወት መን በአሳብና
በባለ ጠግነት ምቾት ይታነቃሉ፥ ሙሉ ፍሬም አያፈሩም።" (የሉቃስ ወንጌል 8፥14)
እሾህ መካከል ወደቀ የተባለው ልብ፤ ቃሉን በሚገባ አገናዜቦ ይቀበላል፡፡ ነገር ግን ሙሉ ፍሬን እንዳይሰጥ
በዓለም አሜኬላ ይታነቃል፡፡
ሆኖም ግን ዓይናቸው የሔዋን ሁለተኛው ዓይን ነው፡፡ ዓለምን በመጎምዠት ያያሉ፣ የዓለምን ሐብት ከቃሉ
በላይ ይፈልጋሉ
23
ፍቅረ ንዋይና ዜሙት ላይ በብዚት ወድቀው ይገኛሉ
ዲያቢሎስ ለጌታ ዓለምን ያሳየበት አሠራሩን ወደነዙህ ሰዎች በመቀጠል ስኬታማ ይሆንባቸዋል፡፡
እነዙህ ሰዎች መንፈሳዊም ዓለማዊም መልክ ያላቸው፤ በተቃራኒ ሁኔታዎች ውስጥ እኩል መሹለክ የሚፈልጉ
ናቸው፡፡ አብዜተው ግን ዓለም ላይ ስላለው ኑሮአቸው ያስባሉ
ሳይቸገሩ፣ ሳይራቡ ሳይጠሙ፣ ምቾት ሳይለያቸው ከቃሉ ጋር መኖር የሚፈልጉ ናቸው፡፡ እናም መንፈሳዊ
መንገዳቸው ላይ ሥጋዊ ዴን ይጨምራሉ
ይሄ ከፀሐይ በታችና በላይ የሆነ አኗኗራቸው፤ መናቸው ከፍ ዜቅ እያለ እንዲሄድ አስገድዶት፤ በዓለም እሾህ
የተጨነቀ መንፈሳዊ ኑሮ ይገፋሉ
"በመልካም መሬት ላይም የወደቀ እነርሱ በመልካምና በበጎ ልብ ቃሉን ሰምተው የሚጠብቁት በመጽናትም
ፍሬ የሚያፈሩ ናቸው።" (የሉቃስ ወንጌል 8፥15)
በአራተኛው ስፍራ የወደቁት ሮች ያረፉት መልካም መሬት ላይ ነበር፡፡ መልካም መሬት ማለት ርን
ተቀብሎ ፍሬ ለመስጠት የሚችል ምቹና ለም የሆነ ቦታ ነው፡፡ በመሆኑም ይሄ መልካም ልብ ያላቸው ሰዎች፤ ቃለ
እግዙአብሔርን በሚገባ ለመቀበል የውስጥ ፈቃዱና መሻቱ አላቸው፡፡ ቃሉንም ከተቀበሉ በኋላ፤ በቃሉ መሠረት
በሕይወት አኗኗር ውስጥ የሚገለጥ ፍሬን ያፈራሉ፡፡
መልካም ፍሬ ከማፍራት አስቀድሞ መልካም ርን የሚቀበል መልካም መሬት መሆን ያስፈልጋል፡፡
የእግዙአብሔርን ቃል ሰምቶ፤ በኑሮ ትርጉም የሚመነር ለውጥን ለማምጣት በመጀመሪያ የእግዙአብሔር ቃል
ለመቀበል ፍቃደኛ የሆነ ልብ፣ ጊዛና አእምሮ ያስፈልገናል፡፡
እዙህ ቦታ ላይ በማስተዋል ማጤን ያለብን አንድ ነገር አለ፡፡ 'የእግዙአብሔርን ቃል የምንቀበለው ፍቃደኛ
ሆነን ነው ተገደን?' የሚለውን መነሻ ቦታ በጥንቃቄ መለየት አለብን፡፡
24
እስኪ ራሳችንን እንጠይቅ፡፡ እግዙአብሔር አምላክን የተጠጋነው ችግራችን እንዲፈታ ነው ወይስ የዓለም
እስራታችን እንዲፈታ?
አብዚኞቻችን የአምልኮተ እግዙአብሔርን መንፈሳዊ ሕይወት የጀመርንበት መነሻ ምክንያት ሲታይ የሆነ
ነገር ቸግሮን መፍትሔ ፍለጋ ነው፡፡ ጤና ቸግሮን፣ ሰላም ቸግሮን፣ በረከት ቸግሮን፣ ደስታ ቸግሮን፣ እረፍት
ቸግሮን፣ መረጋጋት ቸግሮን፣ ኑሮአችን ቸግሮን ነው ስለ አምልኮትና መንፈሳዊ ውጊያ መማር የጀመርነው፡፡
በምንም መነሻ ምክንያት ይሁን መማራችንና ወደ እግዙአብሔር በየዕለቱ የመጠጋት ጉዝአችን መቀጠሉ እስካለ
ድረስ አስፈላጊው ነጥብ እርሱ ነው፡፡
ፍላጎታችን የተነሣንበትን መነሻ ችግር እስከመቅረፍ ብቻ ድረስ የረመ ከሆነ፤ እንግዲያው መርጠን ስለ
ቸገረን ጉዳይ የምንሰማ፣ ለይተን ስለ ችግራችን መፍትሔ የምንቀበል፣ ሁሌ ስለ ችግር ለማውራት የማንታክት ሰዎች
ሆነን፤ "አስቀድማችሁ የእግዙአብሔርን መፍትሔ ሁሉ ፈልጉ፥ ጽድቁና መንግሥቱ ይጨምርላችኋል" የሚል
የራሳችንን መመሪያ ቀርጸን ለመመላለስ እንገደዳለን፡፡
ክርስቶስም ሊነግረን የፈለገው እውነት ይሄ ነው፡፡ "አሰቀድማችሁ መንግሥቱንና ጽድቁን ፈልጉ" በማለት
መንፈሳዊ መድረሻ ላይ ፍላጎታችን እንዲቀድም አስታውቆናል፡፡
ወደ እግዙአብሔር ለመምጣት ያስቻለን አንድ ሥጋዊ ጉዳይ፤ ጥሪ እንጂ ዓላማ አይደለም፡፡ ያ የጤና
መታወክ፣ ያ የጭንቀት ጊዛ፣ ያ የሰላም መጥፋት፣ ያ የበረከት ማጣት አምልኮተ እግዙአብሔርን እንድትጀምር
መነሻ የሆነ ነጥብ ነው፡፡ መድረሻችን ግን ምንድነው? ''የእግዙአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም መፈለግ'' ነው፡፡
25
የእግዙአብሔር ቃል ሕይወታችን ውስጥ ፍሬያማ መገለጥን የሚያመጣው፤ ጽድቁን ፍለጋ መንፈሳዊ ጉዝ
ስንጓዜ ነው፡፡ የሚጨመረውን የሥጋ ነገር ፍለጋ ከወጣን፤ ፍለጋችን አያልቅም፡፡ ጤናችንን ስንፈልግ፥ በረከት
ይጠፋል፡፡ በረከትን ሰንፈልግ፥ የቤተሰብ ጤና ይጠፋል፡፡ የቤተሰብን ጤና ስንፈልግ፥ ዕድል ደግሞ ይጠፋል፡፡ ዕድልን
ፍለጋ ስንወጣ ሰላም ደግሞ በዙህ በኩል ይጠፋል፡፡ እንግዲያሳ ስንቱን ፍለጋ ስንደክም እንኖራለን?
ሦስቱ የመንገድ ዳር፣ የዓለት ላይና የእሾህ መካከል ሮች ፍሬያማ እንዳይሆኑ የከለከላቸው የዲያቢሎስ
አሠራር ነው፡፡ መንገድ ዳር የወደቁትን ወፍ ሆኖ ሲለቅማቸው፥ ዓለት ላይ ያረፉትን ድርቅ ሆኖ ሲያጠወልጋቸው፥
እሾህ መካከል የተገኙትን አሜኬላ ሆኖ ሲያንቃቸው አስተውለን ይሁን?
1) መንገድ ዳር የወደቃችሁ
ቃለ እግዙአብሔርን ከመስማት አሊያ ከማንበብ አስቀድሞ በተለይ ዓይነጥላ ልባችሁ ላይ፣ ጭንቅላታችሁ
ውስጥ እና የስሜት ሕዋሶቻችሁ ላይ እንዳይቀመጥ የሚያዜዜ የርዕስ ጸሎት ጸልዩ
ከመስማት አስቀድሞ ጆሮአችሁንና ጭንቅላታችሁን መዜሙር 90'ን እየጸለያችሁ ቅባዕ ቅዱስ ተቀቡ
26
ከማንበብ አስቀድሞ ዓይናችሁንና ጭንቅላታችሁን መዜሙር 90'ን እየጸለያችሁ ቅባዕ ቅዱስ ተቀቡ
በተጨማሪ እነዙህ ስሜቶች ሲመጡ የጸሎት ውኃ አጠገባችሁ ካለ ጠጡ፡፡ ሰውነታችሁንም በእርሱ ደባብሱ
ተከታትላችሁ ስትጨርሱ ቃሉን ከልባችሁ እንዳይወስደው (እንዳያስረሳችሁ) የማሳሰብ የርዕስ ጸሎት ጸልዩ፡፡
መንፈሳዊ ትምህርቶች በነፍስ መዜገብ ውስጥ በክርስቶስ ደም እንዲታተሙ እየጸለያችሁ በርዕስ ቁረቡ
ቃሉን የሚነጥቅ ጠላት መንገድ ዳር ሊጥላችሁ ወትር ይታትራልና ወትር ተዋጉ፡፡ አንድ ሰሞን በርትተን
መፍትሔ ስለመጣልን ዲያቢሎስን ተስፋ አይቆርጥም፡፡ ከምታስቡት በላይ ለማጥፋት ሲል የሚያሳየው ትጋት
የሚገርም ነው፡፡ በመሆኑ መፍትሔ መጣ ብላችሁ በጭራሽ አትናጉ
2) ዓለት ላይ የወደቃችሁ ✝
በቃሉ ምክንያት ሁሌ የሚመጣ ፈተና እንዳለ እወቁ፡፡ የፈጠራትን እግዙአብሔርን በምትጠላ ዓለም ውስጥ
የምንኖረው፡፡ (የዮሐንስ ወንጌል 15፥18)
ዲያቢሎስ ከመንፈስ ቅዱስ አሠራር ውስጥ የማይገባው ነገር ቢኖር፤ እንዴት ከጀርባው የሆነ ድንቅ ነገር
እግዙአብሔር እንደሚያስቀምጥበት ነው፡፡ ጴጥሮስን በጌታ ፊት ሦስት ጊዛ ከሃዲ ሲያደርገው፤ እግዙአብሔር ደግሞ
ከጀርባ ሦስት ሺህ ሰዎችን በአንድ ስብከት የሚመልስ ሐዋሪያ እያደረገው እንደሆነ ዲያቢሎስ አላየም፡፡ ሳዖልን
ክርስቲያንንና ቤተክርስቲያንን እንዲያሳድድ አጥፊ ሲያደርገው፤ ከጀርባ እግዙአብሔር ጨለማውንና ሠራዊቱን
የሚያሳድድ ጳውሎስ የተባለ ብርሃን እያደረገው እንደሆነ ዲያቢሎስ አላወቀም፡፡
ስለዙያ አሁን መንፈሱ ሲፈትንህ ከጀርባ ያለን የእግዙአብሔር ስጦታ እንደርሱ እንዳታይ አስጨንቆ ነው፡፡
ከውስጥህ ግን አንዴ የእምነት ኃይልና ሰማያዊ ፍቅር ቦታ አግኝቶ ከተቀመጠ፤ አሁን ምን ብትንፈራፈር
እግዙአብሔር ፍጹም ለቃሉ የታመነ ሲሆን ላንተ ያስቀመጠልህ አንዳች ነገር እንዳለ ስለምታውቅ፤ በፈተና
ምክንያት ከቃሉ አትርቅም፡፡
27
3) እሾህ መካከል የወደቃችሁ ✝
ለክርስቶስ ዓይን የዓለምን ሐብትና ክብር ሁሉ ያሳየው ዲያቢሎስ ለእናንተም ዓለምን አብለጭልጮ እያሳያችሁ
ነው
የዚሬው ክፉ መንፈስ ዓለምን የሚያሳየን እንደጌታ ከውጪ ሆኖ ወደ ውስጥ ሳይሆን፤ እኛው ውስጥ ሆኖ ወደ
ውጪ በኛ ዓይን እያየ ነው ዓለምን እያሳየን ያለው፡፡ ዚር ሆኖ አብሮ ተወልዶ፣ መተት ሆኖ ገብቶ፣ ዓይነጥላ
ሆኖ ተቀምጦ፣ ቡዳ ሆኖ ተዋሕዶ ነው በኛ ዓይን ውስጥ አብሮ ዓለምን እያየ ነው ያለው፡፡ ንቁ❕
ከዲያቢሎስ ጋር ሆነህ ዓለምን ስታይ፤ ዓለም ደስ ታሰኛለች፡፡ ገንቡ፣ ቪላው፣ መኪናው፣ ውበቱ፣ ሥልጣኔው፣
ዜሙቱ፣ መዜናኛው ሁሉ ከኃጢአትም ጋር የተያያ ቢሆን ችግር የለብህም ደስ ያሰኝሃል፡፡ ስለሆነ፤ ዓለም ላይ
በምታደርጋቸው የኃጢአት ክንውኖች ጊዛያዊ ደስታ እያገኘህ ከሆነ፤ አንተ ሳትሆን አንተን ሆኖ ያለ ባላጋራ
መንፈስ ከውስጥህ በባሕሪይህ እየተደሰተ ነውና፥ ንቃ❕
መንፈሳዊ ጊዛን፣ መንፈሳዊ አሳብን፣ መንፈሳዊ ባሕሪይንና መንፈሳዊ ምግባርን በየዕለቱ ጨምሩ፡፡ እሾህ መካከል
የመውደቅ ገጽታን ልናስተውለው የምንችለው፤ የእግዙአብሔር መንፈስ እኛ ውስጥ ሆኖ ዓለምን አብሮን
ሲያይ ነው፡፡ ይሄ መንፈስ ደግሞ የዓለምን እውነታዎች፣ ውሸቶች፣ ሚስጥሮችና አካሄዶች የሚያሳየን ኃይል
ነው።
--------------------------------//--------------------------------
28