Professional Documents
Culture Documents
ሃይማኖት ስለእግዚአብሔር ተመሳሳይ አመለካከት ያላቸው ሰዎች የሚሰበሰቡበት ጉባኤ ወይም ድርጅት ሳይሆን
ሰዎች ከእግዚአብሔር ጋር የሚኖራቸው ሕይወት ነው። ይህንን ጉዳይ በአሁኑ ጊዜ ስለምንተነፍሰው አየር ካለን
እውቀት ጋር በማነጻጸር በቀላሉ መረዳት ይቻላል። ሰዎችን በሕይወት የሚያኖራቸው ስለኦክስጅን ያላቸው
ዕውቀት ተመሳሳይ ሆኖ በዚያ ዙሪያ መሰባሰባቸው ሳይሆን በየራሳችው አቅም እና ሁኔታ ወደ ውሳጣቸው
የሚያስገቡት ኦክስጅን ነው። ይህን ወደ ውስጥ የምንተነፍሰውን አየር ኦክስጂን ይባል አይባል የማያውቁ ሰዎች
ሃይማኖት የሚባለውም ስለእግዚአብሔር ያለን ዕውቀቱ ሳይሆን እንደ ኦክስጅኑ ወደ ራሳችን የምናስገባው
ኦክስጅን መውሰድ የማይችል ወይም የመተንፈስ ችግር የገጠመው ሰው ማለት በሕይወት የመኖር ችግር የገጠመው
ማለት ነው። ታዲያ መተንፈስ ችግር የገጠመውን ሐኪሞች ረድተውት ወደ ጤንነት ተመልሶ ያለ ችግር
ማኖር ካልቻልን በእግዚአብሔር ዘንድ ሙታን እንሆናለን። ምንም ያህል ስለሃይማኖት ዕውቀት ቢኖረንም ዕውቀቱ
ሕይወት ሊሆነን አይችልም። በዚህ ጊዜ በሥጋ ብንኖርም ጠባያችን ፣ ምግባራችን፣ ሕይወታችን በአጠቃላይ
በእንዲህ ያለው ጊዜ ስሙን ብንጠራም አንሰማም ይሆናል። አንዳንድ ሃይማኖታዊ ተግባራትንም ብንፈጽም
የምንፈልገውን ላናገኝ እንችላለን። በዚህ ምክንያት ደግሞ እንታወካለን። ባዶነት ይሰማናል። ጥያቄዎች
የምንመኘውን ማለት በቅዱሳን እንደተገለጠ እና እንደታየ የምናምነውንና የምናውቀውን ዓይነት ሕይወት ለመኖር
ብንፈልግም አይሳካልንም። መጥፎ ነው ብለን የተራዳነውን ጠባያችንን ወይም ያጎሳቆለንን መጥፎ ድርጊታችንን
ስነነሣም ከጥቂት ጊዜያት በኋላ ተመልሰን ከነበርንበት ወድቀን ራሳችንን እናገኘዋለን። ለዚህ ዐይነት መከራ አሳልፈ
የሰጡን ደግሞ ፈተናዎቻችን ወይም እኩያት ፍትወታት (ክፉ ክፉ ፍላጎቶቻችን) ናቸው። እንዚህን በአግባቡ
ፈተናዎች ወይም ክፉ ፍላጎቶች መነሻቸው ስሜት ነው። በተለይም ደግሞ በሕይወታችን ውስጥ የምንወዳቸው
ወይም ከሰውነታችን የሚመነጭ ስለሆነ ስሜት አልባ ልንሆን አንችልም። ስሜትም በራሱ ችግር አይደለም። ችግር
የምንሰጥበት መንገድ ላይ ነው። ለምሳሌ እስካልበላን ድረስ የረሀብ ስሜት አይቀሬ ነው። ከሰውነታችን ጋር በጥብቅ
የተሳሰረ ነውና። ወይም ሥጋችን ያለ ምግብ እንዳይኖር ሆኖ የተፈጠረ ነውና። ሆኖም የረሀብ ስሜታችንን
የምንቆጣጠርበት፣ ምግብም ካገኘን በኋላ የምንበላበት መንገድ ፈተናን ወይም ቅድስናን ሊያስከትል ይችላል
ማለት ነው።
እንዲያውም አንድ ሰው ይህን በተመለከተ ሲናገር ይህ ነገር እንደቤት እንስሳት ልንወስደው እንችላለን ይላል።
ለምሳሌ ያህል ያሁን ዘመን ውሾችን ብናያቸው ሁኔታቸው ባለቤታቸው እንዳሰለጠናቸው ነው። ባለቤቱ በአግባቡ
እንዲያ እንዲሆኑ ተደርገው ተቀርጸዋል ወይም ሰልጥነዋልና። ከዚያ በተቃራኒው ካደጉ ደግሞ ባለቤታቸውን
ሳይቀር የሚነክሱ አውሬዎች ሊሆኑ ይችላሉ። ስለዚህ ፈተናዎች ወይም ክፉ ክፉ ፍላጎቶች ማለት ስሜቶቻችን
በአግባቡ ሳንገራ እና ሳናስተካክል በእኛ ውስጥ በማሳደጋችን ምክንያት ራሳችንን እንዲበሉን ወይም እንዲጎዱን
ያደረግናቸው ስሜቶቻችን ወይም ተፈጥሮአዊ ማንነቶቻችን ናቸው ማለት ነው። ይህም ማለት አውቀንም ይሁን
ሳናውቅ ራሳችንን በማስለመድ ለራሳችን ከሠራነው ሰብእና የሚመነጩ ፍላጎቶች እንጂ ከሌላ ቦታ ወይም ከከባቢ
አየር ላይ እንደ ባክቴሪያ እና ቫይረስ የተጣበቁብን ተሐዋስያን አይደሉም ማለት ነው። ስለዚህ ካውቅን በኋላ ሁሉ
ችግር ነው ማለት ነው። ይህም ማለት ልክ በእኛ ሀገር ያለን ሌባ እንዲጠብቅ ተብሎ አንዲት ትንሽዬ ሳጥን መሰል
ክፍል ውስጥ ተዘግቶበት ሰው ሳይለምድና እና ሥልጠና ሳያገኝ የኖረን ውሻ በገመድ እየጎተቱ ወስዶ የተቀበረ ድራግ
ፈተናዎቻችን ለስሜቶቻችን በምንሰጠው መልስ ላይ የተመሠረቱ ናቸው ያልነውም የምንሰጠው ተግባራዊ ምላሽ
እያጣጠመ እስኪጠግብ እየበላ እና እየጠጣ ሰብአዊ ስሜቶችን በቀላሉ ለመቆጣጠር እንዴት ይችላል? በልቶ ጠጥቶ
መጸዳጃ ቤት ሳይሔድ ሊቀር እንደማይችለው ሁሉ የበላው የጠጣው ነገር በውስጣዊ ማንነቱም ላይ ቀጥተኛ
ለዚያም ነው ጌታችን ከተጠመቀ በኋላ ጾምን የነገር ሁሉ መጀመሪያ ያደረገው። ነገሮች ሁሉ ሊጀምሩ የሚችሉት
ራስን ከመግዛት ፣ ስሜትን ከመቆጣጠር እና ነገሮችን በአግባቡ ከመረዳት መሆኑን ለማስተማር ነውና የጾመው።
ስለዚህ ፍትወታት እኩያት ማለት እኛው ስሜቶቻችንን በአግባቡ ሳንቆጣጠር እና ከእግዚአብሔር ጋር ላለን
ሕይወት እንዲረዱን አድርገን ሳንቀርጽ እኛው ውስጥ ያሳደኛቸው ልማዶች ማለት ናቸው። እነዚህ ልማዶች
አድገው ሲቆጣጠሩን እና ስንደጋግማቸው ደግሞ ፈተናዎች ይባላሉ። ፈተና ደረጃ ከደረሱ በኋላ ደግሞ እኛ
እነርሱን መቆጣጠር አቁመን እነርሱ እኛን መቆጣጠር ይጀምራሉ ማለት ነው። መውጣት እየፈለግን የሚያቅተን
በዚህ ጊዜ ነው። እየቆዩ ሲሔዱ ደግሞ መቆጣጠር ብቻ ሳይሆን ገዢዎቻችን ይሆናሉ። በዚህ ጊዜ “ሰው
ለተሸነፈበት ለእርሱ ተገዝቶ ባሪያ ነውና” /1 ኛ ጴጥ 2 ፤ 19/ ሲል ቅዱስ ጴጥሮስ የገለጸው ባርነት በሕይወታችን
ይደርሳል ።
በዚህ ጊዜ ነገሮች ሁሉ እጂግ ከባድ ይሆናሉ። በሁለት መንገድ ሊከብዱብን ይችላሉ። አንደኛው እና በጣም
የሌሎች ሰዎች እንጂ የራሳችን አይመስለንም። ሌላው ቀርቶ መንፈሳዊ ነገሮችን እንኳ የምንቀበለው ለእኛ ስሜት
ተከትለን እንደምንከተለው ለዚህኛውም እውነቱ ሳይሆን ለእኛ የማይስቡን እና ከቴስታችን የማይሔዱ ሁሉ ችግሩ
የእነርሱ እንጂ የእኛ እንደሆነ አይታየንም። ለምሳሌ ያህል የመዝሙር ምርጫዎቻችን ውስጣችን በተገነባው
የሙዚቃ ቴስት ላይ በጥብቅ የተመሠረተ ይሆናል። ለዚህም ነው የከተማ ልጆች እና የገጠር ልጆች የመዝሙር
ሳይሆን ለራሳቸው ሰሜት እናፍላጎት በመስማማቱ ነውና። ይህኛው ስሜት ግን ከዚህም የከፋ ብዙ ችግሮች አሉት
። የቤተ ክርስቲያን ቀኖናዎች፣ ሥርዓቶች ሁሉ ከእኛ ፍላጎት እና ከዘመኑ ሁኔታ ጋር እንዲጣጣሙ እንድንፈለግ
ያደርገናል እንጂ እኛን ከሕጉ እና ከሥርዓቱ ጋር ለማስማማት አይፈቅድልንም። ከዚህም የተነሣ የቤተ ክርስቲያንን
ሰዎች ኋላቀር እና የማይገባቸው አድረገን እንድንወስድ ውስጣችንን ያሳምነዋል እንጂ እኛ የራቅን እና በችግር
ሁለተኛው ዓይነት ደግሞ ችግሮቹን የእኛ መሆናቸውን እናውቃለን። ኃጢአቱን ከሠራነው በኋላ ራሳችን
እስከመጥላት ድረስ እንደርሳለን። እንዲያውም እንዳንዴ በራሳችን ከማዘናችን የተነሣ ራሳችንን እስከመጥላት
አንዳንዴም ተስፋ ቆርጠን ራሳችንን ምንም የማንጠቅም አድርገን በማሰብ የባሰ ክፉ እንድናስብ ሁሉ ያደርገናል።
እንደምንም ከዚህ ስሜት እንደተላቀቅን ወዲያ ልንቆጣጠረው በማንችለው ስሜት ውስጥ እንገባና ያንኑ
የምንጠላውን እና ራሳችንን ለመጥላት የሚገፋንን ድርጊት አሁንም ሳናስበው እናደርገዋለን። አንዳንድ መንፈሳዊ
ምክሮችንን ሰምተን ሌላም ሌላም ሞክረን የተሻለን ይመስለን እና አሁንም እንደገና ራሳችንን እዚያው ድርጊት
ውስጥ እናገኘዋለን። ሰውነታችን ለምዶታልና ሳናስበው እስኪመረን ድረስ ደጋግመን እዛው ቦታ እንገኛለን።
ትክክለኛው ፈተና ማለት ይህ ነው። ስለዚህ ፈተና ማለት ራሳችን ውስጥ ያለውን ስሜት በአግባቡ ካለመግራት
የተነሣ የተፈጠረ ክፉ ተግባር ተደጋግሞ ከመደረጉ የተነሣ በእኛ ላይ ሥልጣን እስኪኖረው ድረስ ሲደርስ ማለት
ነው። ለዚህ ነው ከባድ የሚሆነው። ክብደቱን ደግሞ “ልማድ ከሰይጣን ይከፋል” በሚለው አባባላችን ሳይቀር
እናውቀዋለን። በሕይወት ውስጥ ልማድ ከፍተኛ ትርጉም ያለው ነገር ነው። መጥፎ ልማድ ከሆነ እጂግ ይጎዳናል።
ታዲያ እንዲህ ያለው የመጥፎ ልማድ ድርጊት አንድ እና ተመሳሳይ አይደለም። እጅግ ብዙ ዐይነት ነው። በአንድ
ሰውም በርከት ያሉ መጥፎ ልማዶች ወይም ፈተናዎች ሊኖሩበት ይችላሉ። ሆኖም ብዙ በሽታዎች ጭንቅ ውስጥ
የከተቱን በሽተኛ ብልህ ሐኪም ከየትኛው መጀመር እንዳለበት በአግባቡ አጥንቶ እና መርምሮ በመጀመር ቀስ በቀስ
በሽታዎች ዋናውን እና ለሌሎች ምክንያት የሆነውን ስንታከም እንደሚጠፉት ሁሉ በዚህም ተመሳሳይ ነው።
አንዳንድ ፈተናዎችን ማስወገድ ስንችል ሌሎቹም አብረው ይጠፋሉ። እንዲህ ከሆነ ዋና ዋና ፈተናዎች የሚባሉት
የ ፍትዎቶቻችን ዐይነቶች
(ካለፈው የቀጠለ)
በመጀመሪያ ደረጃ ፈተናዎቻችን ወይም ፍትወቶቻችን በሁለት ይከፈላሉ። ተፈጥሮአዊ የሆኑ እና ያልሆኑ
ተብለው። ተፈጥሮአዊ የሚባሉት ከምግብ ጋር በተገናኘ ያለው ሆዳምነት (እንደ ስስት ፣ መጎምጀት፣ ምግብን
የማጣጣም እና የመብላት ፍላጎት ሁሉ በዚህ ሥር ይካተታሉ)፣ ፍርሐት፣ እና ሐዘን እንደሆኑ የነገረ መልኮት
መምህራን ይገልጻሉ። እነዚህ ነገሮች በተፈጥሮ ከእኛ ጋር ያሉ፣ ፈጽሞ ልናስወግዳቸው የማንችላቸው ብቻ
ጠቀሜታቸውን በዐራቱ ባሕርያተ ሥጋ (መሬት፣ ውኃ፣ ነፋስ እና እሳት) አንጻር ልናየው እንችላለን። ለምሳሌ
ባሕርየ እሳትን ወይም ሙቀትን ብናየው እርሱ የሌለው ሕይወት ያለው ሰው ሊኖር አይችልም። ይህን ያክል
መሠረታዊ ነው። ሆኖም ከመጠኑ ሲወርድ ስንቀዘቅዝ ወይም ሲያልፍ ስንቃጠል በሁለቱም ጊዜ ጽኑ በሽታ
ለምሳሌ ያለ ምግብ እና ያለ ምግብ ፍላጎት መኖር አይቻልም። ነገር ግን የሰውነታችን ሙቀቱ ሲጨምር
ማለት ነው። መጀመሪያ ላይ እንዳልነው እግዚአብሔር በባሕርዩ ቅዱስ ስለሆነ ቅድስና የሌለው ሰው
ከእግዚአብሔር ጋር መኖር አይችልም። ለዚህ አስፈላጊው ንጽሕናን አጽንቶ ለመያዝ ያለን አማራጭ
ሆዳምነትን መታገል ይሆናል ማለት ነው። ንጽሕናችንን አጥፍቶ ሰውነታችንን የሚያረክሰው ነፍሳችን
የሚያሳድፋት የመጀመሪያው ነገር ሆዳምነት መሆኑ ተደጋግሞ የተረጋገጠ ነው። ሆዳምነት ማለት ስለምግብ
ከመጠን በላይ በመጨነቅ ለመኖር ወይም ለመሥራት ከሚያስፈልገን በላይ መመገብን ፣ ጣዕም አማርጦ
የአልኮል መጠጥን የፍራፍሬ ጭማቂዎችንና የመሳሰሉትን ሁሉ የሚመለከት ጉዳይ እንደሆነ መቼም አይዘነጋም
ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ።
ስለዚህ በአጠቃላይ የምግብ ነገር አንዳንዶቻችን ላናስተውለው እንችላለን እንጂ ሌሎች ጉዳዮች ባላነሰ ሱስ
ይሆናል። ከዚያ በኋላ ደግሞ ብዙ ነገር ውስጥ የሚከትተን ሰዎች አለን። ሆዱን ያልተቆጣጠረ አብዛኛዎቹ
ሰውነታችንን የሚያረክሱ ነገሮች በሙሉ ይቆጣጠሩታል። ከዚህ የተነሣ በአንዳንዶችን ዝሙት ይሰለጥናል፤
ስላሉ ነው እኔም ከፍርሐት እና ከሐዘን ይልቅ ትኩረት ሰጥቼ ያብራራሁት ። የሆድ ነገር ሆድ ይቆርጣል
የሚባለው አባባላችንም የጉዳዩን ትልቅነት የሚያስታውስ ይመስለኛል። ከሁሉም በላይ ደግሞ አባታችን
አዳም የወደቀው ያው ለበለሲቱ በመጎምጀት እና ብሎም በመብላት መሆኑን አንረሳውም ጌታችንም በገዳመ
ቆሮንቶስ ስለእኛ ሲጾም ሰይጣን ካቀረበለት ሦስት ፈተናዎች መካከል ሁለቱ ለምግብ ስስት ለመፍጠር እና
ለዚህ ዓለም ሀብት መጎምጀትን ለማስጎምጀት በመጣር ነበር። ለስም አጠራሩ ክብር ምስጋና ይግባውና
መንሣት እንደምንችል ለማስተማርም ጭምር ነበር በዚያ መንገድ ድል ያደረገልን። ለዚህ ነው በቤተ
ሆኖም ሆዳምነት ከተቆጣጠረን ብንጾም እንኳ ተጨንቀን የፍስክ ምግብ የሚያስንቅ የጾም ምግብ እንድንበላ
ያደርገናል። ስለዚህ ሆዳምነት መሠረታዊ ፍትወት መሆኑን መረዳት ተገቢ ነው። ሆኖም በሚያስፈልገን
በተመጋቢነታችን በኩል የመጣ ስለሆነ ወይም ያንን ያለአግባብ ለጥጦ መውሰድ ያመጣው ጉዳይ ስለሆነ
ተፈጥሮአዊ ነው ይባል እንጂ ሆዳምነትን ወይም ፈሪነትን ወይም ሐዘንተኝነት እግዚአብሔር ፈጥሮብናል
ማለት አይደለም። ይልቁንም ልክ አረም ሳይዘራ እንደሚበቅለው ከአዳም ውድቀት በኋላ ከውስጣችን
ማለት የሰውነታችን ሙቀት በተገቢው መጠን ሲሆን ምንም ችግር እንደሌለው ሁሉ እነዚህንም በመጠናችን
የምግብን ጉዳይ ወደ መንፈሳዊ ምግብና መሻት እየለወጠው እርካታውንም ከዚህ ዓለም ምግብ ይልቅ ወደ
መንፈሳዊ ምግብ መፈለግ እያሳደገው ቢሔድ ባሕርዩን ከሰውነት ወደ መልአክነት እየለወጠው ሊሔድ
ይችላል። በአንጻሩ እርካታውን ከምግብእና ከዚህ ዓለም ነገር ብቻ እየፈለገ በበላው እና በጠጣው፣ በለበሰው
ባጌጠው፣ በገዛው በነዳው እየተመሰጠ እየረካ ስለዚያም እያሰበ ወይም ትልቅ ቦታ እየሰጠ ሲሔድ በውስጡ
ያለው እንስሳዊነት ወደ አውሬነት እየተቀየረ ይሔዳል። ለዚህም ነው ጥጋበኛ ሰው የሰው መዋረድ ይቅርና
ሌሎቹ ልለፍ።
ተፈጥሮአዊ ያልሆኑ የሚባሉት ደግሞ ተፈጥሮአዊ የሆኑትን በመጥፎ አቅጣጫ ስንጠቀም እነዚያ ወደ
እነዚህ ፍላጎቶቻችን ሲሰለጥኑ ነፍሳችን ላይ ወሰን ወደ ሌለው ወይም በቃኝ ወደማንለው ፍላጎት ይለወጣሉ።
ይህም ማለት ከስስት ወደ ስግብግብነት ማለትም ርካታ አግኝተን በቃን ወደማንልበት ስሜት ይለወጣሉ። ይህ
ነው እንግዲህ ሰዎች በሀብት ላይ ሀብት ቢያገኙ ወይም በሥልጣን ላይ ሥልጣን ወይም ቢጠጡ ቢጠጡ እና
ቢሰክሩ፣ በዝሙትም ቢሆን በምንም ያህል ሰው የማይረኩ በምንም ነገር ላይ በቃኝ ማለት የማያውቁ
ወደመሆን ስለሚለወጡ ነው። ከዚህ የተነሣ ጥቅማችን፣ ክብራችን የተነካ የሚመስለን በቀላሉ ነው፣
የምንቆጣው በቀላሉ ነው። ለማንኛውም ኃጢአት እና ግብር በቀላሉ እንጋለጣለን። ከዚያም እነዚህ ሁሉ
ድርጊቶች በብዙ መንገድ ሰውነታችንን ያረክሱታል። ከላይ በሆዳምነት እንዳየነው ሆዳምነትን ተከትለው
ዝሙት፣ ስካር፣ ጸብ ክርክር፣ ... ይመጣሉ እንዳልነው ፍርሕትን ተከትለው ገና የሆነ ነገር ሊያደርጉብኝ ነው
በማለት እጅግ በርካታ ኃጢአቶችን እንሠራለን። በሐዘንተኝነትም ስሜት ውስጥ ጥላቻው፣ በቀሉ፣ ዘረኝነቱ፣
በክርስትና ሕይወት ውስጥ በጣም መጥፎ ኃጢአት የሚባለው ተስፋ መቁረጥ ነው። ሰይጣን ተረባርቦ ብዙ ነገር
ካሠራን በኋላ ራሳችንን እንድንጠላ እና በራሳችን ተስፋ ቆርጠን በቃ ለውጥ ማምጣል አልችልም፣ የማልረባ ሰው
ነኝ፣ መኖሬ ትርጉም የለውም፣ እግዚአብሔር እኔን አይምረኝም ዓይነት ሀሳቦችን ወደ ኅሊና ውስጥ እያስገባ ተስፋ
ለማስቆረጥ ይታገላል። አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የታመነ ተስፋ እና ወሰን የሌለው አዛኝ ሆኖ
እያለ አንተም (አንቺማ) ይቅር አትባሉም እያለ ይወተውተናል። ነገር ግን ጌታችን የታመነ ተስፋ፣ ሳይክፋ
የሚወድድ ፍጹም ፍቅር፣ ይቅር ለማለትም ትንሽ ምክንያት የሚፈልግ በቃላት ሊገለጽ የማይችል መሐሪ ነው።
እኛም ቢሆን ኃጢአተኝነት፣ ጎስቋላነት እና የመሳሰለው በተሰማን ጊዜ በራሳችን ላይ ተስፋ መቁረጥ ወይም ራስን
መጥላት የለብንም። ይልቁንም ደግሞ ለምሕረት እና ለዕርቅ ጥረት በምናደርግበት ወይም ንስሐ በምንገባበት
ጊዜም ቢሆን ሰውነታችን መጉዳት አይጠበቅብንም። አባ ቦይመን (ጴሜን) “እኛ ፍትወቶቻችንን እንጂ
ሰውነታችን እንድንገድል አልተማርንም” እንዳለው ማተኮር ያለብን ፍትወቶቻችን ላይ መሆን አለበት ። ስለዚህም
እንመለክታቸዋለን።
1) ራስን ማወቅ
ከሁሉ በፊት አስፈላጊው ነገር ይህ ነው። በሽታውን ያላወቀ ሐኪም ማከም እንደማይችለው ሁሉ አንድ
ክርስቲያንም የነፍሱን በሽታዎች ወይም ደግሞ ፍትወቶቹን እና መነሻ ምክንያቶቹን ማወቅ በጣም አስፈላጊ
ነው። ለምሳሌ በዝሙት የተቸገረ እና በሐሰት ወይም በቁጣ የሚቸገሩ ሰዎች ከእነዚህ ከእያንዳንዳቸው ጋር
አብረው ሊያውቋቸው የሚገቧቸው ነገሮች ይኖራሉ። በምን ምክን ያት በተደጋጋሚ የምፈጽመው፣ ወደዚህ ጉዳይ
የሚመሩኝ ነገሮች ምን ምን ናቸው? ... የመሳሰሉትን ማወቅ በጣም አስፈላጊ ነገር ነው። እንደማንኛውም
ሕክምና የነፍስ ድኅነትም የራስን ድክመቶች በተገቢው መጠን ከማወቅ ነው። ቀደም ብዬ የፍተወት ዓይነቶችን እና
ሁኔታዎቻቸውን እጅግ በትንሹም ቢሆን ለማቅረብ የሞከርሁት ራሳችንን ለማወቅ እንዲረዳን በማሰብ ነው።
ለምሳሌ ዝሙትን የሚገፉት ምክንያቶች አንደኛው እና ዋናው ደስታን መፈለግ ነው። ይህን የሚያባብሰው እና
እንደ ነዳጅ የሚያቀጣጥለው ደግሞ አመጋገብ ነው። ከእነዚህ ቀጥሎ ደግሞ የምናያቸው እና የምንሰማቸው ነገሮች
(በፊልም፣ በማኅበራዊ ሚዲያ እና በመሳሰሉት) በአሁኑ ጊዜ ወሲብ ቀስቃሽ የሆነ እጅግ ብዙ ይዘቶች ይሰራጫሉ።
ከዚህ ቀጥሎ ደግሞ ውሎአችን (ለምሳሌ ለፈተናው ከሚዳርገን አካል ጋር በተደጋጋሚ ብቻን መገናኘት)
የመሳሰሉት በደንብ መታወቅ ያለባቸው ነገሮች ናቸው። አንድ ሰው ስሜቱን የሚያነሳስቱትን በሙሉ ባወቀ እና
ከእነዛ ጋር በተገናኘ ትክክለኛ ውሳኔዎችን በወሰነ ቁጥር ወደ ፈውስ እና ድኅነት ለመሔድ ቀላል ይሆንለታል።
ለሁሉም ፈተናዎቻችን በዚህ መንገድ ራሳችንን መፈተሽ እና ጉድለታችንን ማወቅ አስፈላጊ ነው። በተለይ ደግሞ
ልክ በላብራቶሪ እገዛ እንደሚታወቁ የጤና ችግሮች በነፍስም በጣም ድብቅ እና በቀላሉ እንዳሉብን የማናውቃቸው
አደገኛ ድከመቶች አሉብን። ሥጋዊ ደስታን መፈለግ፣ ትዕቢት፣ ምቀኝነት ከንቱ ወዳሴን መሻት፣ መጎምጀት ከነዚህ
ውስጥ የሚጠቀሱ ናቸው። ስለዚህ ራስን በአግባቡ በተለይም ቅዱሳት መጻሕፍትን እያነበበ ራሱን የሚመረምር
ሰው ማለት አልትራ ሳውንድ፣ ሲቲ እስካን እና የመሳሰሉትን ተጠቅሞ በውስጥ የሰውነቱ አካል ያሉ ቁስለቶችን
ጉዳቶችን እንደሚያስፈልግ ታካሚ ብዙ ደኅና የሚመስሉ ችግሮቹን ለመመልከት ይቻለዋል። በሽታውን ማወቅ
ይህ ራስን ማወቅ ማጠቃለያው ደግሞ ንስሐ እና ጸጸት ነው። በደልን እያሰቡ ከልብ ጌታን እንደበደሉት ማሰብ እና
መናዘዝ እጂግ አስፈላጊው ነገር ነው። ንስሐችን እና ኑዛዜያችንም ከተለመደው ሪፖርት የማድረግ አካሔድ የራቀ
ነገር ግን ከውስጥ ስሜት በሚመነጭ ሁኔታ ሆኖ አምላክን መለመን መሆን ይገባዋል። ይህም ማለት ኃጢአተኝነትን
እና ደካማነትን ከልብ ተቀሎ በፊቱ ራስን በንስሐ ዝቅ ማድረኝ ይይዛል ማለት ነው። ስለዚህ ንስሐ መነሻው ራስን
በአግባቡ ማወቅ ስለሆነ በዚሁ ውስጥ የተካተተ መሆኑን ማስታወስ ተገቢ ነው።
2) እምነት
ሌላው በጣም አስፈላጊ ነገር እምነት ነው። ምንም ያህል ደካሞች ብንሆን የጌታችንን ሰውን ወዳጅነት፣ ስለእኛ
ብሎ ያን ሁሉ መከራ በሥጋ መቀበሉን፣ ይቅር ባይ እና ድኅነታችን የሚሻ መሆኑን እና ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ
ሊምረን ሊረዳን የሚችል መሆኑን ማመን አስፈላጊ ነው። ስንጸልይ እንደሚሰማን ማመን በጣም አስፈላጊ ነው።
መጽሐፍ ቅዱስን ስናነብብ ወይም ስንሰማ ጌታችን የፈወሳቸው ብዙዎቹ ሰዎች ከፍተኛ ኃጢአትን የሰሩ እና ብዙ
ድካም የነበረባቸው ናቸው። ሰባት አጋንንት ያወጣላት መግደላዊት ማርያምን፣ ዐሥራ ሁለት ዓመት ደም ሲፈስሳት
ከሁሉም በላይ ደግሞ ሁሉንም የፈወሳቸው እና ኃጢአታቸውን ይቅር ያላቸው ስለእምነታቸው እንጂ
ስለምግባራቸው አልነበረም። እምነትህ አድኖሃል፣ እምነትሽ አድኖሻል፣ እንደ እምነትህ ይሁንልህ፣ እንደ እምነትሽ
ይሁንልሽ የሚሉት ቃላት ሁሉ የሚያመለክቱት ዋናው ነገር እምነት መሆኑን የሚያመለክት ነው። ስለዚህ አምኖ
መሔድ ያስፈልጋል። አምኖ ወደ ጌታችን ቀርቦም እርዳታውን ሳያገኝ የቀረ አንድም ሰው ኖሮ አያውቅም።
የሚያስምር ምግባር አለኝ የሚል ሰውም ሊኖር አይችልም። እንደዚያ የሚል ካለ ከትዕቢትም እጂግ በከባዱ
3) ተስፋ
ተስፋ ሰይጣንን ከሚያሸሹት ነገሮች አንዱ ነው። ሲጀመር ተስፋ የሚደረገው ራሱ ጌታችን ስለሆነ በተለይም
በወንጌል ትርጓሜያችን ላይ ሊቃውንት ተስፋ ኢየሱስ ክርስቶስ እያሉ ደጋግመው እንደሚገልጹት እርሱ ይቅር
ይለኛል፣ ይረዳኛል የሚል ተስፋ ከፍተኛ ዋጋ ያለው ነው። ስለዚህ አንድ ድርጊት እየጠላነው ማቆም ባንችል እንኳ
ጌታችን እንደሚረዳን እና አንድ ቀን ከዚያ ነጻ እንደምንወጣ ተስፋ መያዝ ለምንመኘው ነጻነት የሚያበቃ ታላቅ
ጉልበት ነው።
ሀ) ጾም
ጾምና ጸሎት አስፈላጊነታቸው የታወቀ ነው። ቢሆንም ደግሞ ጉልበታቸው ምን ያህል ብርቱ እንደሆነ ደጋግሞ
ማስታወሱ አሁንም አስፈላጊ ነው። ጌታችን ጾሞ ሦስቱን አርእስተ ኃጣውዕ ድል መንሣት እንደሚቻል በተግባር
አሳይቶናል። እነዚያ ደግሞ በጣም መሠረታዊ ፍትወታት ናቸው። ስለዚህ አንድ ሰው ይጹም ሲባል በሕግ
ብርሃን ብልጭታ ብቅ ሊል ከሚችልባቸው ሕክምናዎች አንዱና ዋናው ጾም ነው። ከበዓለ ኃምሳ በቀር መጾም
ይቻላል። ያም ባይሆን በተመቸ ሁኔታ ላይ ሁሉ በራስ ላይ ሆእነ ብሎ የምግብ ፍላጎት ላይ ማዕቀብ መጣል፣
ምርጫን ውሱን ማድረግ፣ የምንመገበውን መጠኑን መቀነስ እና የመሳሰሉት በጣም ጠቃሚ ነገሮች ናቸው።
ለመጾም የማያስችል በሽታ ያለበት ሰው ደግሞ ሌሎቹን ሁኔታዎች በጥብቅ መፈጸም ሊበቃው ይችላል።
ለ) ጸሎት
ጸሎት እንደ አየር ሳንተነፍሰው ልንውልና ልናድር የማንችለው ነገር መሆኑ የታወቀ ነው። ስለዚህ እንደ ክርስቲያን
ጸሎት እንደምንጸልይ ይታወቃል። ይሁን እንጂ ከፍትወታት ለመላቀቅ ለየት ያሉ ጸሎቶች ያስፈልጋሉ።
የሚያስፈልጉት ጸሎቶች አጫጭር እና በቃል የሚያዙ ሆነው ልክ ኅሊናችን ውስጥ የሆነ ነገር ሲርመሰመስ ኅሊናን
መልሶ በቃል ደጋግሞ የሚጸልዩት ጸሎት በጣም አስፈላጊ ነው። እንዲህ ዓይነት ጸሎቶች ሥራ እየሠራንም ሆነ ሰው
ቤት ውስጥ ሆነን ወይም ሌላ ሥራ ላይ እያለን ልንጸልያቸው የምንችላቸው ናቸው። ለምሳሌ ያህል “ኦ እግዚእየ
ኢየሱስ ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር ሕያው ሥረይ ኩሎ ኃጢአትየ” ፟ ‘የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ጌታዬ ኢየሱስ
ክርስቶስ ሆይ እኔን ኃጢአተኛውን ይቅር በለኝ” የሚሉ ጸሎቶች በእጅጉ አስፈላጊ ናቸው። እንዲህ ያሉ ጸሎቶች
የሚያስቸግረንን ፍትወት በመጥራት ከዚህ ነጻ አውጣኝ በማለት መጸለይን ያጠቃልላል። በተለይም ደግሞ ከዳዊት
መዝሙር ውስጥ ለፈተናችን መድኃኒትነት የሚስማሙትን በማምጣት ማለትም “አቤቱ ንጹሕ ልብን ፍጠርልኝ”
፣ በቁጣህ አትቅሰፈኝ፣ የመሳሰሉትን ደጋግሞ መጸለይ ተገቢ ነው። የተመረጡ የዳዊት መዝሙሮችን እና የሰባቱን
መጸለይ ለማንም ሰው የምመክረው ነገር ነው። ይህን የጸሎት መጽሐፍ የሚጠቀም ሰው በግሉም እንዴት መጸለይ
እንደሚገባው የሚያስተምር የእነ ቅዱስ ባስልዮስ፣ ቅዱስ ኤፍሬም፣ አባ ሲኖዳ፣ ቅዱስ ቄርሎስ፣ ስምዖን ዘአምድ
እና የመሳሰሉት ቅዱሳን የጸለዩት የጸሎት እስግቡእ ነው። እውነቱን ለመናገር ይህን ጸሎት የሚጸልይ ሰው
የቅዱሳኑን ንስሐ በማስተዋል ንስሐ ገባሁ ብሎ ካለመመጻድቅ ጀምሮ ብዙ ነገሮችን እንደሚገበይ አምናለሁ።
በተለይ እንደ ስንፍና እና ዝሙት ያሉትን ለመላቀቅ ሥራዬ ብሎ የጉልበት ሥራዎች መሥራት ይመከራል።
ይልቁንም ደግሞ እጂግ ዝቅ ያሉ የትሕትና ሥራዎችን መሥራት ፍቱን መድኃኒት ነው። በስንክሳር ላይ
እንደተገለጸው በቅድስና በገዳም ይኖር የነበረ አንድ የእስክንድርያ ፓትርያርክ ወደ ሲመት ከመጣ በኋላ ዝሙት
ባስቸገረው ጊዜ ገዳማውያን አበው በመከሩት መሠረት ሌሊት ሌሊት ተደብቆ የገዳማውያኑን ቆሻሻ እየጠረገ
በመድፋት ሁለት ዓመት ያህል ካገለገለ በኋላ ጌታ ትዕግሥቱን አይቶ ፈተናውን እንዳራቀለት ተገለጿል። ስለዚህም
ይህን የመሰሉ የትሕትና ሥራዎችን ከመሥራት ጋር ሥራዬ ብሎ በጸሎት ጊዜ ስግደት መስገድ እና መሬት ላይ
ቅዱሳት መጻሕፍትን በተለይም መጽሐፍ ቅዱስን ማንበብ ፈተናን አንዱ መታገያ መንገድ ነው። ይልቁንም ደግሞ
ፊልሙን የማይገባውን የቴሌቪዥን እና የፊልም እይታዎችን ፣ የማኅበራዊ ሚዲያ ስሜት ቀስቃሽ ነገሮችን ቢቻል
አቁሞ ካልሆነም በጣም ቀንሶ መጻሕፍትን ማንበብ በጣም አስፈላጊ ነው። ስሜቱን መቆጣጠር የቻለ ሰው ከብዙ
ጥፋት ይድናል። ይህም ማለት ኃጢአትን ሳይድግ እና ሳይጎለምስ መቅጨት ማለት ነው። በዚህ ጊዜ የሚተጋውን
ሰው እግዚአብሔርም ይረዳዋል። በነፍሳችን ውስጥ ስላለችው የኃጢአት ከተማ ነቢዩ ሲናገር ‘ሕፃናቶችሽን በዓለት
የሚቀጠቅጣቸው የተመሰገነ ነው’ ተብሎ የተነገረው ይፈጸምለታል። ሕጻናቶች ማለት ኃጢአት ገና ከመጎልመሱ
አእምሮን ከመቆጣጠሩ በፊት ተቀዳድሞ ገና በስሜትነት እያለ በቃለ እግዚአብሔር በጸሎት አእምሮን እንደጥሩ
ጥበቃ ተግቶ እንዳይዘናጋ በመጠብቅ ማሸነፍ ይቻላል። ኃጢአትን ገና በሀሳብነቱ መዋጋት የእግዚአብሔርን ርዳታ
ከርስኩሰት ይነጻሉ።
ማጠቃለያ
ከላይ የጠቀስኳቸው በጣም ትንሽ እና ለማነሣሣት ያህል ብቻ የተድረጉ እንጂ በጉዳዩ ላይ ሥራዬ ብሎ መማር፣
ማንበብ እና ልክ እንደ ስፖርት አዘውትሮ ሰዐት ጠብቆ ተገቢውን ማድረግ ያስፈልጋል። በእነዚህና በመሰሉት
በነገራችን ላይ ከፍትወታት ፈጽሞ ለመላቀቅ ረጂም እና ያልተቋረጠ ትግል ይፈልጋል። ይህ መላቀቅ ስንል
ስለኃጢአት ሥርየት ማግኘትን በተመለከተ እየተናገርን አይደለም። ስላለፈው ኃጢአት በተናዘዝን ቁጥር ይቅርታ
በጠየቅን ቁጥር ሥርየት እናገኛለን። ስለማቆም የምንናገረው ፍትወቶቹን ከውስጣችን ስለመለየት እና ኃጢአትን
ስለማቆም ነው። ተጋድሎው ያስፈለገውም ወደዚህ የነፍስ ጤንነት ስለመመለስ ነው። ለዚህም ነው ከመናዘዝ እና
ንስሐ ከመግባት ያለፈ ተጋድሎ የሚጠይቀው። ቅዱስ ጳውሎስ በመልእክቱ “ደም እስከማፍሰስ ድረስ ለመጋደል ገና
የሆነው ሆኖ እውነተኛ ድል መነሣት ላይ ስንደርስ አንደኛ ኃጢአትን በገቢር መሥራት ይልቁንም ደግሞ ፈልጎ
ነው። ለእኛ ዓይነቶቹ ደግሞ ከፍተኛ ውጤት ነው። ከዚህ ሳይደረስ ወደ ሌላው መሸጋገር አይቻልምና። ሁለተኛው
ደረጃ ደግሞ ኃጢአት አቁመው ጸጋ ማግኘት የጀመሩት ደግሞ ፍትወታት ወደ አእምሮ ሲደርሱ ቶሎ ማስወገድ
መቻል ላይ የሚደርሱበት ደረጃ ነው። ይህም ማለት በአእምሮ ውስጥ በሀሳብነት የመጣውን ልክ ጥበቅ አልፎ የገባን
ሰው ቶሎ ይዘው እንደሚመልሱት ሀሳቡን በአእምሮ ውስጥ አለማቆየት ፣ አለማዋል፣ አለማሳደር ማለት ነው።
ስለዚህ ሁለተኛው ደረጃ ፍትወታትን ከአእምሮ በየደቂቃው ነቃቅሎ የማውጣት ደረጃ መድረስ ነው። ሦስተኛው
ደረጃ የሚደርሱት ደግሞ ከፍትወት ጋር ግንኙነት ያላቸውን ነገሮች ሁሉ በአእምሮአቸው ከማሰብ ያቆማሉ። በዚህ
ጊዜ እንኳን አዲስ ሊያስቡ ይቅርና በንስሐ ያለፉት እንኳ እንዴት ድርጊቱ ምን ይመስል እንደነበር እስከመርሳት
ይደርሳሉ። ለምሳሌ ያህል በቀደመ ሕይወቱ በዝሙት የነበረ ሰው እንኳ ቢሆን ዝሙት ራሱ ግብሩ ምን እንደነበረ
ከአእምሮው ይጠፋለታል። ይህም ማለት ግብረ ሥጋን የማያውቀው ሰው ዓይነት ይሆናል። ንስሐ ዘማዊውን
ድንግል ታደርጋለች የሚለው ቃል እዚህ ደረጃ ለደረሰ የሚነገር ነው። በስንክሳራችንም ላይ ታሪካቸውን በዝሙት
ጀምረው በተጋድሎ ከጨረሱ በኋላ ጸሐፊው ራሱ ከዚህች ድንግል በረከት ይክፈለን እያለ የጸፈላቸው አሉ።
አራተኛው እና የመጨረሻው ደግሞ ከፍትወታት ጋር የተገናኘ ቅዥትም ሆነ ሕልም ሁሉ ያለማየት ደረጃ መድረስ
ነው። የፍጹማኑ ንጽሕና የሚባለው ይኼኛው ደረጃ ነው። እንግዲህ የምንታገለው ወደዚህ ደረጃ ለመድረስ ነው
ማለት ነው።
በመጀመሪያው ጽሑፌ በአዲሱ ዓመት የምንመኘው ዓይነት ሰው ለመሆን ማድረግ የሚገባን ምንድን ነው የሚል
ጥያቄ ጠይቄ የተነሣሁት ሦስት መሠረታዊ ነገሮችን ለማናውቃቸው ለማሳወቅ ፣ ለሚያውቋቸውም ለማስታወስ
ነው። እነዚህም እኛ ያለንበትን ማወቅ፣ ልንደርስበት የሚገባንን ማወቅ፣ ሦስተኛው እና እኩል አስፈላጊው ነገር
ወይም መንገድ ማወቅ ናቸው። ስለዚህ በመጀመሪያዎቹ ጽሑፎች ለመነካካት የሞከርኩት ችግሮቻችንን ወይም
ያለንበትን የሕይወት ደረጃ ለማሳየት ያህል ብቻ ነው። ዛሬ ደግሞ የመፍትሔ መንገዶቹንና እና በተጋድሏችን
ልንደርስበት የሚገባውን የሕይወት ደረጃ በጣም በትንሹ ለመጠቆም ሞክሪያለሁ። በእግዚአብሔር ቸርነት እና
ኃይል ተጉዘን ወደዚህ እውነተኛ አዲስ ሕይወት ለመድረስ ያብቃን። ያን ጊዜ ዘመናችን ሁሉ እንደ ስሙ ዓመተ
መሆን የምንፈልገው ድል ነሺ ክርስቲያን መሆኑ የታወቀ ነው። ድል የምንነሳው ደግሞ መጀመሪያ ኃጢአትን ቀጥሎ
ደግሞ የኃጢአትን በሮች ፍትወታትን ነው። ድል የምንነሣው በጌታችን ኃይል ነው። ያለ እኔ ምንም ምን ልታደርጉ
አትችሉም ብሎናልና። ስለዚህ እርሱን አምነን በቅዱሳኑ ይልቁንም የባሕርያችን መመኪያ በሆነች በእመቤታችን
እያልን እጅ ወደ ምንነሣት የድል ነሺዎች ጉባኤ እና ኅብረት ለመቀላቀል በመንፈስ ቅዱስ ኃይል እንነሣ። ሁሌም
ተንሥኡ አይደል የምንባለው። እንግዲያውስ የትንሣኤውን ኃይል ገንዘብ አድርገን በቸርነቱ እንነሣ። እግዚአብሔር
(በእኔ ሕይወት ውስጥ) ይነሣ፤ ጠላቶቹም (አጋንንት እና ፍትወታትም) ይበተኑ የሚለውን የዳዊትን መዝሙር
እየዘመርን በመንፈስ እንነሣ። በመንፍሳዊቷ መቅደስም በቅዳሴ እና በቁርባን ቅዱስ ጳውሎስ እንዳለ ከነቢያት እና
በከባድ ሰቆቃ ፣ ሐዘን ፣ ልዩነት እና ዕልቂት ወጥሮ የያዘው መንፈስ ተሸንፎ ከግለሰባዊውም ሆነ ከሀገራዊ