You are on page 1of 1

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

በአንቀፀ ብፁዓን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ እና አቡነ ሐብተ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ፍሬ ቅዱሳን ሰንበት ትምህርት ቤት
የቀዳማይ ኮርሰኞች የመፅሐፍ ቅዱስ ጥናት ማጠቃለያ ፈተና።

ስም--------------------------------------------------------- ቀን----------------------- ፊርማ---------------


የተሰጠው ደቂቃ፡- 45

ትዕዛዝ ፩- የሚከተሉትን ጥያቄዎች በማብራራት ተገቢውን መልስ በፅሁፍ ስጡ።


1: ዶግማ ማለት ምን ማለት ነው አብራሩ፡፡
2: ቀኖና ማለት ምን ማለት ነው አብራሩ፡፡
3: ዶግማ ተብለው ከሚነገሩ ትምህርቶች መካከል ጥቀሱ፡፡
4: የቀኖና ቤተክርስቲያን ምንጮች የሚባሉትን ቢያንስ 2 ጥቀሱ፡፡
5: የቀኖና ቤተክርስትያን ጥቅሞች (የቀኖና ጥቅም) ምንድነው?
6: አዋልድ መፅሐፍት ማለት ምን ማለት ነው?
7: አዋልድ መፅሐፍት እንደ ቤተክርስትያን በምን አይነት መስፈርት (መመዘኛ) ትቀበላቸዋለች?
8: አዋልድ መፅሐፍት አላማቸው ምንድነው?
9: ወንጌልን የፃፉ ሐዋርያት ስማቸው እነማን ነው ?
10: የሐዲስ ኪዳን የስርዓት (የህግ መፅሐፍት) ተብለው ከሚጠቀሱት ውስጥ 3 ጥቀሱ፡፡
11: የሐዲስ ኪዳን መፅሐፍ በስንት ይከፈላል ጥቀሱዋቸው፡፡
12: መፅሐፍ ቅዱስ ብቻ ማለት ልክ ነው? በደንብ አብራሩት፡፡
ትዕዛዝ ፪- ጉርሻ
13:- 1.1 መፅሐፍ ቅዱስ ጥናት ፋይዳው ምንድነው ?(1ነጥብ)
1.2 ከትምህርቱስ ምን ተረዳን? (1ነጥብ)
1.3 መፅሐፍ ቅዱስ ማለትስ ምን ማለት ነው?(1ነጥብ)
1.4 መፅሐፍ ቅዱስ እውነት ለመሆኑ ምን ማረጋገጫ አለን?(1ነጥብ)
1.5 የመፅሐፍ ቅዱስ መፃፍ አላማው ምን ነበር?(1ነጥብ)
መልካም ፈተና ይሁንላችሁ !

You might also like