Professional Documents
Culture Documents
( (Headset) ... ..
( (Headset) ... ..
ገቢር አንድ
(መድረኩ ላይ አንድ ግንብ ሥር ድንጋይ ላይ የተቀመጠ እና ሄድሴት(Headset) ጆሮው ላይ አጥልቆ ስልኩን በአትኩሮት
የሚጎረጉር ወጣት (ዮሐንስ) ይታያል። አለባበሱ ቄንጠኛ ነው። ከላይ ቅጥነቱን የሚያሳይ ቲሸርት ከታች ደግሞ ወደላይ
ታፋው ድረስ የተሰበሰበ ጠባብ ጂንስ ለብሷል። የተጫማው ነጠላ ጫማ አቧራ የቃመ እግሩን ያሳያል። ስልኩን እየጎረጎረ
ብቻውን ያወራል... ብቻውን ይስቃል። አንዳንዴም እንደመደነቅ ...አንዳንዴም እንደመደንገጥ ያደርገዋል። ተመልሶ
ደግሞ ስልኩ ላይ ያቀረቅራል። በዚህ ጊዜ አንድ እርጅና የተጫጫናቸው ዓይነስውር የኔ ቢጤ ወደመድረኩ በበትራቸው
እየተመሩ ይገባሉ። ጥቁር መነጽር ዓይናቸው ላይ ሰክተው አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ያለበት የሹራብ ኮፍያ አድርገዋል። ቁሽሽ
ካለ ኮታቸው ላይ የደረቡት የመነቸከ ኩታቸው በአንድ ወቅት ነጭ እንደነበር ያስታውቃል። በትራቸውን ባልያዙበት
እጃቸው በኩል ካርቶን ፌስታል እና ሌሎች ኮተቶችን ጉያቸው ሥር ወሽቀዋል። በበትራቸው እየተመሩ ልጁ
ወደተቀመጠበት ይሄዳሉ። ልጁ አላየቸውም ኖሮ ከተቀመጠበት ሳይነሳ ሥልክ መጎርጎሩን ቀጥሏል። ድንጋዩ ጎን ሲደርሱ
ሰው መኖር አለመኖሩን ለማጣራት በሚመስል መልኩ የወጣቱን እግር በበትራቸው ነካ ያደርጋሉ። ልጁ በመመሰጡ የተነሳ
ቀና ብሎም ሳያያቸው እግሩን ዞር አድርጎ ሥልክ መጎርጎሩን ይቀጥላል። አሁንም ጥቂት ጠጋ ብለው በበትራቸው እግሩን
ነካ ሲያደርጉት በተመሳሳይ ዞር ብሎ ሥልኩን ይጎረጉራል። በመጨረሻ ትንሽ ተጠግተው በበትራቸው ሾጥ ሲያደርጉት
ድንገት ብድግ ይልና ደንግጦ ይሸሻል።)
ጋሽ ቢያድግልኝ - አሂሂ....አንት ወስላታ!! (ዱላቸውን እርሱ በሌለበት እየወዘወዙ) ደህና አድርጌ አቀመስኩህ አይደል?
(የፌዝ ሳቅ ይስቃሉ)
ጆኒ - እንዴ ...እርስዎ ነዎት እንዴ ጋሽ ቢያድግልኝ (የተመታበትን ቦታ እያሻሸ በማለቃቀስ ድምጽ) ... እኔ ደግሞ ሌላ ነገር
መስሎኝ!( በስጋት ግራ ቀኝ መላልሶ እየቃኘ)
ጋሽ ቢያድግልኝ - ምን ሌላ ነገር ይመስልሃል? ወሮበላ!...እዚህ ደርቀህ በተቀመጥክበት ጥንብ አንሳ መጥቶ እንዳይወስድህ
ነው የደነበርክ? አዪ...እንደው መድኃኔዓለም... እንዴት ያለውን ጉድ ነው የጣለብኝ እናንተዬ። ዓይን እያለው የማያይ
ከንቱ (ጉያቸው ስር ያለውን ኮተታቸውን እያራገፉ) አንደኛውን እንደኔ ቢለይለህማ ተዚህ ግንብም አትሻል! እግዚኦ...
(ይህን እያሉ ሳንቲም የሚቀበሉበትን ፌስታል እና የሚቀመጡበትን ካርቶን አስተካክለው ልጁ ተቀምጦበት የነበረበት ቦታ
ላይ ይቀመጣሉ። ጎረምሳውም እየተቅለሰለሰ ከእርሳቸው እልፍ ብሎ ሌላ ድንጋይ ላይ ይቀመጣል።)
ጋሽ ቢያድግልኝ - ማነህ ልጅ.. ማ ነበር እቴ ስምህ? ...ምን የዘንድሮ ልጆች ስም አይያዝ! (ከተቀመጡ እና ከተደላደሉ
በኋላ ለመለመን ብለው የሆነ ነገር እንደረሱ ሁሉ ወደ ወጣቱ ዞረው)
ጋሽ ቢያድግልኝ - ኧረግ! ብለህ ብለህ ጂኒ ሆነህ አረፍከው? እግዚኦ... እግዚኦ.... !ወይ ስምንተኛው ሺህ (እጆቻቸውን
እርስ በ'ርስ በየተራ እያማቱ) የለም! ጂኒማ አይሆንም ስምህ! የለም! የለም! ሌላ ካለህ ወዲህ በል እንጂ የሥላሴን ፍጡር
በጋኔን ስምማ አልጠራም። ሆሆ...
ጆኒ- አይ ጋሼ... (በማላገጥ ድምጽ እየሳቀ) ስሜማ ዮሐንስ ነው። ሲያቆላምጡኝ እኮ ነው ጆኒ ጋሼ ...እ... አለ አይደለ ጆኒ
ያራዳው ልጅ... ጭሱ ምናምን... (በመቀናጣት ድምጽ እንደዘመኑ ልጆች እጁን ወደታች ዘቅዝቆ እያወራጨ )
ጋሽ ቢያድግልኝ - አዪዪዪ... አንተን ብሎ ያራዳ ልጅ (ይስቃሉ) እንደው ዮሐንስን የመሰለ ስም ይዘህ ነው ጂኒ ነኝ
የምትል...ሆሆ.... እንዴት ያለ ዘመን ላይ ደረስን እናንተዬ (ዮሐንስ ፊቱ ላይ የነበረው ፈገግታ ጠፍቶ አኩርፎ ፊቱን
ያዞራል) ይልቅ ... ናማህ... ቀረብ በል (ይሉትና ሲቀርብ በሹክሹክታ) ዛሬ ዕለቱ ስንት ነው በል? ንሳማ ንገረኝ! እኔማ
ይኼው እርጅናው እየተጫጫነኝ ሁሉ ተዘንግቶኝ መቅረቱ ነው። በልማ... ንገረኝ እንጂ... ምነው ዘገየህ።
ጆኒ- (በማመንታት ድምጽ ቀኑ የጠፋበት ይመስል) ዛሬ? ዛ...ሬማ ጋሼ... (ሲል ይቆይና ድንገት እንደተገለጸለት) እህህህ...
ዛሬማ ቀኑ ሰኞ ነው። ጋሽ ቢያድግልኝ ደግሞ... አሁን ይህች ትጠፋብኛለች ብለው ነው። (በእርካታ ስሜት ተጥለቅልቆ
ደጋግሞ እጁን ከጉልበቱ ጋር እያጋጨ)
ጋሽ ቢያድግልኝ - ኤድያ አንተን ብሎ የተስተማረ... ዕለቱ ስንት ነው አልኩህ እንጂ መቸ ቀኑን ጠየቅኩህ? እ? መላም የለህ
አንተው ... እንደው በየዕለቱ እዚህ እየተጎለትክ ቀንና ሌቱም ሳይምታታብህ አይቀር።
ጆኒ - (ጣቱን ሲቆጥር ይቆይና) ዘጠኝ...አስር... አስራ...አንድ (በለሆሳስ ለራሱ ቆጥሮ) አ....ዎ ዛሬ አስራ ሁለት ነው ጋሼ!
ሰኔ አስራ ሁለት....
ጋሽ ቢያድግልኝ - ኧረግ! (ደንግጠው ከተቀመጡበት በትራቸውን ጥለው ሲነሱ ልጁም ድንግጥ ብሎ ይነሳል።)
ጆኒ - ምነው? ምን ተፈጠረ ጋሽ ቢያድግልኝ? (ግራ ቀኙን በፍጥነት ዞር ዞር ብሎ አይቶ ለመሮጥ እያኮበኮበ) ፓ... ፓሊሶች
መጡ እንዴ?
ጋሽ ቢያድግልኝ - ኤድያ (እጃቸውን እያወናጨፉ) የምን ፎሊስ ነው የምትል አንት ወንበዴ ...ፎሊስ እንዳንተ ሥራ ፈት
መሰለህ እንዴ መንደር ለመንደር ሲዞር የሚውል ....ዛሬ አቅለብልቦኻል እንደው....''ያቡዬን ግብር የበላች ፍየል... ለፍልፊ
ለፍልፊ ይላታል" ነው ነገሩ... (በመጠራጠር ድምጽ እርሱ በሌለበት እየገላመጡት)
ጋሽ ቢያድግልኝ - የጻድቁን መታሰቢያ ረሳሁ... ያ'ባቴን እረፍት ረሳሁ ልጄ... የዓመቱ እኮ ነው... ቅዱስ ላሊበላ ዛሬ
ይነግሳል እኮ (ለማልቀስ በሚዳዳው ድምጽ ሙሾ እንደሚደረድር ሰው እያጎነበሱ)
ጆኒ - ኧ..... ለዚህ ነው እንዴ? (ይላል በማቃለል ድምጽ) ታዲያ ምን ጣጣ አለው ጋ...ሼ...(እያለ ሊቀመጥ ሲል
ሳይጨርሰው ድንገት በጩኸት ተቆጥተው ያስነታል።)
ጋሽ ቢያድግልኝ - (በድንገተኛ ቁጣ) አንተ ምን ጣጣ አለው ነው ያልክ? (ብለው ሲቆጡ መቀመጡን ትቶ በድንጋጤ ቆሞ
ያያቸዋል።) ምን ጣጣ አለው? እንዴት እንዴት ብትደፍረኝ ነው አንተ ? (የቆመበትን ስላላወቁ በትራቸውን ጠበቅ
አድርገው ይዘው በመጠራጠር ዙርያ ገባቸውን ያያሉ። ዮሐንስ እንዳይመቱት ፈርቶ በመርበትበት ቆሟል።)
(ቁጭ ይላሉ! ፈራ ተባ ሲል ቆይቶ አንዴ ግራ ቀኙን በጥርጣሬ ከተገላመጠ በኋላ ዮሐንስም ቁጭ ይላል። ለአፍታ ዝም
ተባብለው ይቆዩና ... እርሱም ስልክ ወደመጎርጎሩ እርሳቸውም ወደ ልመናቸው ይገባሉ።)
ጋሽ ቢያድግልኝ - ስለጻድቁ ንጉሥ... ስለቅዱስ ላሊበላ እናቶቼ.... ስለጻድቁ ንጉሥ
(አንዲት ነጠላ የለበሰች ሴት ምንቅር ምንቅር እያለቼ መጥታ ሳንቲም በንቀት ወርውራላቸው ስትሄድ ዮሐንስ ስልክ
መጎርጎሩን ትቶ በትዝብት ይመለከታታል።)
ጋሽ ቢያድግልኝ - እግዚሃር ይስጥልኝ እናቶቼ.... እግዚሃር ይስጥልኝ ...ውሎ ያግባችሁ... የሰው ፊት አያሳችሁ (ይላሉ
ወዳልሄደችበት በኩል ዞረው... ይሄኔ ዮሐንስ ሳቁ ያመልጠውና ቡፍ ብሎ ይስቃል)
ጋሽ ቢያድግልኝ - አንት ወስላታ...ምንድነው የሚያስቅህ? (ይላሉ በሌሉበት በኩል ዞረው... ተጣልተው ቂም አይዙም)
ጋሽ ቢያድግልኝ - አዪ.....(ይላሉ በረዥሙ አገጫቸውን በእጃቸው ደግፈው) አረጀሁ ማለት ነው። (በሐዘን እና በመጸጸት
ድምጽ)
ጆኒ - ጋሼ?(በመቅለስለስ)
ጋሽ ቢያድግልኝ - ካካካካ (ከት ብለው ይስቃሉ። ሲስቁ እንደዚያ ተክዘው የቆዩ አይመስሉም)
ጋሽ ቢያድግልኝ - አይ ወዲህ ነው... እህ እህህ አሂሂሂ(ሳቃቸውን ለመግታት እየሞከሩ) ሆሆ... አይ መድኃኔዓለም ...ዛሬ
ደግሞ ምኑን ጣልክብኝ ...መቼም የማታሰማኝ የለ! ሆሆ(ይሄኔ ዮሐንስ አኩርፎ ጀርባውን ሰጥቷቸው ይቀመጣል!)
ጋሽ ቢያድግልኝ - ይልቅ ጨዋታውን ታመጣኸው አይቀር ... መቼም "አንቺው ታመጪው አንቺው ታሮጪው" አይደለ
ነገሩ? ... እኔም የምጠይቅህ አለኝ። (ይሉታል ወደርሱ እየዞሩና ኩታቸውን እያስተካከሉ)
ጆኒ - ለ'ኔ?
ጋሽ ቢያድግልኝ - ኋላስ?
(ይሄኔ ዮሐንስ ጉጉቱ ጠፍቶ ከተቀመጠበት ይነሳና በተስፋ መቁረጥ አጁን ወገቡ ላይ አድርጎ ይቆማል።)
ጋሽ ቢያድግልኝ - ኧረግ የምሬን እኮ ነው አንት ኩታራ ....ጠዋት ማታ እዚሁ ተጎልተህ ነው የማገኝህ... ለስሙ
ኡምበርስቲ በጥሰሃል... እንደው እዚያም የሚያስተምሯችሁ መጎለት ነው እንዴ? እንደዚያ ተሆነ አንደኛዬን ይህቺን
የምቀመጥባትን ቦታና ኮተቴን ላውርስህና ጡረታ ልውጣ። መቼም የኡምበርስቲ ምሩቅ ባለሞያ ለማኝ እያለ እኔ
አልለምንም!(በማሾፍ ድምጽ) ደግሞ ማነው ይህቺ ስሟ እቴ (ወደላይ እየጠቆሙ)... ዋይ ዋይ ነው ዋይ ላይ....
ጆኒ - ዋይ ፋይ (ብሎ ያርማቸዋል)
ጋሽ ቢያድግልኝ - እ....ርሷ እርሷ ከመጣች ጀመሮ አንተም ሰርክ ቦታዬ ላይ ተጎልተህ ነው የማገኝህ...ሰውም
መመጽወቱን ተወ መሰለኝ ገበያዬም ቀነሰ። እምልህ ይህቺ ዋይ ዋይ ያልካት ነገር...
ጋሽ ቢያድግልኝ - ምነው ላውራበት እንጂ ልጅ ዮሐንስ ...እንደው ትልቅ ሰው ሲያወራ ልጅ ጥልቅ ይላል እንዴ?
ጆኒ - አይልም ጋሼ አይልም
ጋሽ ቢያድግልኝ - አ...ዎ እንደርሱ ነው! ምን እያልኩህ ነበር ልጄ... አ.....ዎ! ምንድነው ታዲያ ተግባሯ ይህቺ ዋይ ዋይ
የሚሏት ነገር። እንደው ገበያ የምታባርር ነገር ትሆን እንዴ?
ጆኒ - አይ ጋሼ ዋይ ፋይዋን ነው ገበያ የምታባርር የሚሉት? (ፊቱን ፈገግታ አልብሶት ለማስረዳት በኩራት ስልኩን ከኪሱ
አውጥቶ ይጠጋል!)
ጆኒ - የለም! ይ'ቺ የምትታይ ነገር አይደለችም። ኔትወርክ ናት ጋሼ። አንዴ ከሞባይሌ ጋር ካገናኘኋት በኋላ ከዓለም ሁሉ
ጋር ታገናኘኛለች። ሳሉት ጋሼ ...በሞባይል ብቻ ዓለምን ሀሉ ማግኘት
ጆኒ - አዎን ጋሼ በሞባዮሏ
ጆኒ - ...እ...
ጆኒ - አይ አታገናኝም (በማመንታት)
ጋሽ ቢያድግልኝ - እንደዚያ ተሆነ ትቅርብኝ። ታለም ወዳጅነት የእግዚሃር ወዳጅነት ይበልጥብኛል። (ዮሐንስ ስልኩን
በመጎሮጎር ተጠምዶ አይሰማቸውም። ወደልመናቸው ይመለሳሉ።)
ጋሽ ቢያድግልኝ - እግዚሃር ይስጥልኝ እናቶቼ.... እግዚሃር ይስጥልኝ ...ውሎ ያግባችሁ... የሰው ፊት አያሳችሁ (ይላሉ።
ይሄን ጎረምሳ ዮሐንስ ከተቀመጠበት ተነስቶ ከዓይኑ እስኪጠፋ ድረስ ያየውና ተመልሶ ለመጠየቅ ጋሽ ቢያድግልኝ ስር
ይቀመጣል።)
ጆኒ - ጋሽ ቢያድግልኝ?
ጋሽ ቢያድግልኝ - ይኸውልህ ልጄ...ታገሬ ስወጣ ልጅ ነበርኩ ...ትዝ ይለኛል ባ'ስራ አምስት ዓመቴ ለብሔራዊ ውትድርና
ስመለመል... በጦርነቱ የዓይኔን ብርሃን ካጣሁ ኋላ አገሬ ተመልሼ አልገባሁም። ታዲያ አሁን እንዲህ አርጅቼ ነገር መርሳት
ሳልጀምር በፊት ስለልጅነቴ ጥቂት ጥቂት ትዝ ይለኛል። (አሉና ተክዘው ሩቅ ሩቅ ማየት ጀመሩ) ላስታ ሲባል ሰምተህ
ታውቃለህ መቼም...
ጆኒ - አዎ ጋሼ !
ጆኒ - የምር!
ጆኒ - አምስት...
ጋሽ ቢያድግልኝ - ታዲያ አምስት ዓምት ሙሉ ተምረህ ምን ሰራህ? የታለ ያቆምከው ሕንጻ? የታለ ያቅምከው ድልድይ?
ጋሽ ቢያድግልኝ - ታዲያ መፍትሔው እዚህ ተጎልቶ መዋል ነው? እንከፍ... (ይሉታል አባባሉ ገርሟቸው)
ጆኒ - በአቋራጭ ካልሆነ ጋሼ እዚህ አገር ላይ ሰርቶ መለወጥ አይቻልም። የዘረፉት የተደላደለ ኑሮ ሲኖሩ ታታሪው ሕዝብ
ሁሌም ከእጅ ወደአፍ ነው ኑሮው።
ጋሽ ቢያድግልኝ - ጻድቁ ንጉሥ ላሊበላ ግን ምንም የአስኳላ ትምህርት አልተስተማረም። ታዲያ እጀታ እንኳ በሌለው
መዶሻ የሰራቸው ሕንጻዎች ግን ጉድ ጉድ ያሰኛሉ።
ጆኒ - ያለምንም መሳርያማ ሊሆን አይችልም ጋሼ...ለዚያውም ምንም ሳይማር! እንደተለመደው ዝም ብለው መላዕክት
ሰሩት አይሉኝም? (ይላል ተስፋ በቆረጠ ድምጽ)
ጋሽ ቢያድግልኝ - ይኽ እኮ ነው ችግራችሁ ያሁን ዘመን ልጆች!(በቁጣ ድምጽ... ይሄኔ በድንገተኛ ቁጣቸው ደንግጦ
ዮሐንስ ከተቀመጠበት ይነሳና በስጋት ግራ ቀኙን ገላምጦ ማንም እንዳልመጣ ሲያውቅ ይቀመጣል።)
ጆኒ - እኔንጃ...(ያመነታል)
ጋሽ ቢያድግልኝ - አየህ የሚበልጠውን ስለማታዩ ክብራችሁን ውርደት ታደርጉታላችሁ። በክብር ኒሻናችሁ ...
በሜዳልያችሁ ለአንገታችሁ መታነቂያ ሸምቀቆ ታበጃላችሁ። ሰው እንዴት ምስጋናውን ስድብ ያደርገዋል?
(ይህን እያሉ ዮሐንስ ድንገት ቀና ብሎ የሆነ ነገር ካየ በኋላ በፍጥነት ሹልክ ብሎ ከመድረኩ ይወጣል።)
(በትካዜ ይኼን ለብቻቸው ሲያወሩ ሁለት ፓሊሶች ወደመድረኩ ይገባሉ። ብቻቸውን እያወሩ ሲያዩዋቸው እብድ
ስለመሰሏቸው እርስ በርስ እየተያዩ እየተጠቃቀሱ ይጠጓቸዋል።)
ጋሽ ቢያድግልኝ - ኧረግ የምን ብቻዎትን ነው... እኔማ ተልጄ ነው የማወጋ ...ተ... ማን ነበር ስሙ እቴ(ይላሉ ተቀምጦበት
ወደነበረበት እየጠቆሙ)
ጋሽ ቢያድግልኝ - አትቀልድ እንጂ ጌታው... አሁን እያወራን እየተጨዋወትን?... ምነው ኮቴሞ የለው ሲሄድ?.... ምን
የዘንድሮ ልጅ እንደሁ ጥላ ቢስ ነው... ይልቅ ምን ልርዳችሁ?
ፖሊስ 2 - ዮሐንስ የሚባል ልጅ ያውቁ ይሆን... ሰዎች እዚህ አካባቢ አይጠፋም ብለውን ነው።
ጋሽ ቢያድግልኝ - አ...ዎ! ተባረክ ልጄ! ዮ...ሐንስ! ትዝ አለኝ ስሙ... እንዴት ያለ የተባረከ ጥሩ ልጅ መሰለህ ጌታው።
ኡምበርስቲ ሁሉ በጥሷል። እንደው ሥራ ፈትቶ ቤት ሲቀመጥ ጊዜ እዚህ ብቅ እያለ ያጨዋውተኛል። አሁንም እዚሁ
ስንጨዋወት ነው ያረፈድነው። እንደው መሄዱንም ሳይነግረኝ ነው የሄደ። ምናልባት አይቷችሁ ይሆናል። ምነው በሰላም
ፈለጋችሁት? ፎሊሶች ናችሁ እንዴ?
ፓሊስ 1 - የለም! የለም! አባቴ ጓደኞቹ ነን። እንደው ከተገናኘን ቆይተናል። ቤቱን በምልክት እንኳ ቢነግሩንና ብናገኘው
ጥሩ ነበር። ይኼውሎት እርሱ ጓደኛዬ ወደአሜሪካ ሊሄድ ስለሆነ እንደው ሳያገኘው እንዳይሄድ ብለን ነው።
ጋሽ ቢያድግልኝ - ነ...ው! በጀ! በዚህ በኩል ውረዱ። አዎ... ቤቱ በዚህ በኩል ነው። አዎ የመጀመርያው ግቢ ...በሉ
ይቅናችሁ! በሰላም ያግባህ አንተም።
ፖሊስ 2 - አሜን አሜን አባባ! እግዜር ይስጥልን... ይህቺን ይያዙ....ይያዙ ግዴለም። (ብሎ አስር ብር ያስጨብጣቸዋል።)
(መጨረሻ ላይ ጋሽ ቢያድግልኝ በትራቸውን እንደያዙ መሃል መንገድ ላይ ለብቻቸው ቆመው አንዴ ወደግራ አንዴ ወደቀኝ
እየዞሩ መጋረጃው ይዘጋል።)
ገቢር ሁለት
(መጋረጃው ሲከፈት ጋሽ ቢያድግልኝ በትራቸውን እንደያዙ መሃል መንገድ ላይ ለብቻቸው በድንጋጤ ቆመው ወደአንድ
አቅጣጫ (ወደፊት ለፊት) አፍጥጠዋል። እጃቸው ይንቀጠቀጣል። ደብዘዝ ያለ ብርሃን አለ። ከኋላ አንጀት የሚበላ
የዋሽንት ዜማ ይሰማል።)
ለወትሮው አቅጣጫ እንኳን በውሉ እማላውቅ ሰው... ሰተት አድርጌ ወደቤቱ መራኋቸው።
ልጄን ሸጥኩት! (በሚንቀጠቀጠጥ እጃቸው ቅድም ከፓሊሱ የተቀበሉትን አስር ብር ከፍ አድርገው እያሳዩ)
አይ ኪሳራዬ...
እባካችሁ ተዘከሩኝ
ማን አሳየውና ጥፋትን?
ማን አሳየውና ክፋትን?
(ጋሽ ቢያድግልኝ ተመልሰው ድንጋዩ ላይ ቁጭ ብለው ልመናቸውን ይቀጥላሉ። የዋሽንቱ ድሞጽ ይቆማል።)
ተፈጸመ!