You are on page 1of 1

ክርሰትቶስ "እውነትና ሕይወት መንገድም እኔ ነኝ" ሲል ምን ማለቱ ነው?

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ መንገድ እንደየአገባቡ


በብዙ መልክ ይተረጎማል። መንገድ የሕይወት ምልክት ነው። ሃይማኖትም በራሷ እግዚአብሔር በሚገባንና በሚገባን
መልኩ ራሱን ለእኛ ለፍጡራኑ የገለጠባት አንድም እኛንም ወደእግዚአብሔር የምታደርስ መንገድ ናት። ቤተክርስቲያንም
መንገድ ተብላለች። የቤተክርስቲያን መንገድ መባል ክርስቶስ ራሱን መንገድ እኔ ነኝ በማለቱ ምክንያት ነው። መንገድ
ሰው አይለይምና። በዕድሜ በዘር በቀለም በቋንቋ በጾታ እየነጣጠለ 'ዛሬ ወንድ ብቻ ነው የማሳልፈው!' 'ዛሬ ደግሞ ጠይም
ብቻ!' የሚል መንገድ የለም። በመንገድ ሁሉም ያልፋል።

ስምዖን የቀሬና ሰው ነው። ቀሬና በአሁኒቷ ልብያ አካባቢ ያለች ሃገር ናት። በዘመኑ በተለያዩ አህጉር ያሉ አይሁዳውያን
በዓል ለማክበር ወደኢየሩሳሌም ይተምሙ ነበርና ነው ስምዖን የቀሬናው ሰው በአጋጣም ክርስቶስ በሚሰቀልበት ቀን
በዚያ የተገኘው።ጌታችን ከመስቀሉ ጽናት የተነሳ መሸከም ባቃተው ጊዜ ወታደሮቹ የሚያግዘውን ሰው በዓይናቸው
መፈለግ ጀመሩ። ቦታው በሮማውያን እና በዕብራውያን የተመላ ስለነበረ ሮማውያኑ ወታደሮች የክርስቶስን መስቀል
ከዚህ ጥቁር መጤ ሰው በቀር ሌላ ማንም እንዲሸከም አልፈለጉም። የቀሬናውን ስምዖን ንቀው አከበሩት። ተሳስተው
ለክብር ጠሩት። ለአንድ ምዕራፍ ያህል የክርስቶስን መስቀል በመሸከሙ በውስጠት አዋቂነት እግዚአብሔር ከመስቀሉ
በረከት እንደከፈለው እናውቃለን። የክርስቶስን መስቀል መሸከም ምንኛ መታደል ነው? እንግዳው አንገትህ ላይ ያሰርከው
ማተብ ክርስቶስ የተቀበለው መከራ ምልክት ነውና የተናቅኩ የተዋረድኩ ነኝ ብለህ አትሽሽ። ከዚያ ይልቅ ክዠጌታችን
'ሊከተለኝ የሚወድ መስቀሌን ተሸክሞ ይከተለኝ' ብሏልና መስቀሉን እንደቀሬናው ሰው ተሸክመህ ወደቀራንዮ
ተከተለው።

?ቨቨ

You might also like