You are on page 1of 2

ጭውውት አንድ

(ሽምግል ያሉ ሰው ወንበር ላይ ተቀምጠው ሬድዮናቸውን ያስተካክላሉ። በወጣትነታቸው ዘመን ፈርጣማ እንደነበሩ


ቁመናቸው ያስታውቃል። ከራሰ በራነት የተረፈ ፀጉራቸውን ሽበት ወርሶታል። በመድረኩ ሌላ ጥግ ባለቤታቸው
ተቀምጠው ተክዘው ይታያሉ። እርሳቸውም አርጅተው ጎብጠዋል። ነጠላቸውን ይቋጫሉ። በየሆነ ደቂቃው
ከንፈራቸውን ይመጣሉ። ራዲዮኑ ሲንሿሿ ቆይቶ አንድ ጣቢ ያ ላይ ያርፋል። ተግ ብለው ማዳመጥ ይጀምራሉ
ሁለቱም።

ራዲዮኑ ውስጥ ያለው ጋዜጠኛ - ይህ የአብዮታዊት ሶሻሊስት ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ ድምጽ ነው። ሊቀመንበር
ማኦ ዜዱንግ ከኩባው ፕሬዝደንት ጋር ባደረጉት ውይይት ምክንያት በሩስያዋ ዋና ከተማ በተፈጠረው የመንገድ መዘጋጋት
ነገ በመላው ኢትዮጵያ ዓለም አቀፉን የሶሻሊዝም እንቅስቃሴ በመደገፍና የአሜርካ መራሹን አቆርቋዥ ቡርዧ
ካፒታሊስት ሥርዓት ለማውገዝ አብዮት አደባባይ ታላቅ ሕዝባዊ ሰልፍ እንደሚካሄድ ጓድ ሊቀመንበር መንግስቱ ኃይለ
ማርያም አስታውቀዋል። በዕለቱም ከዩጎዝላቭያ፣ ከምስራቅ ጀርመን እና ኸሊብያ የሚመጡ የወንድም ሃገራት
ላባአደሮች ትርኢት እንደሚያሳዩ ይጠበቃል።

በተያያዘ ዜና አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ልዩ ስሙ አህያ በር እየተባለ በሚጠራው ቦታ በሕገ ወጥ መልኩ አህዮቻቸውን
ሲያደራጁ የነበሩ አህያ ነጂዎች ላይ አብዮታዊ እርምጃ ተወሰደ። የአህያ በር ወረዳ አስተዳዳሪ የሆኑት ጓድ ማበሉ የትናየት
እንደተናገሩት አብዮታችን በማንም ፋንድያም ውርንጭላና አድሐሪ ምክንያት አይደናቀፍም። ይህንንም ለማረጋገጥ ሌት
ተቀን እንሰራለን ብለዋል።

ይህንን አብዮታዊ እርምጃ በማክመልከት 'የፍየል ወጠጤ ልቡ ያበጠበት እንዋጋ ብሎ ለነብር ላከበት ያልታደለች ፍየል
ሁለት ትወልዳለች ልጆቿም ያልቃሉ እርሷም ትሞታለች።' የሚለውን አብዮታዊ ዜማ አዳምጠን እንመለሳለን። "

ወይዘሮ - አበስኩ ገበርኩ አበስኩ ገበርኩ እንዴት ያለ ሰው በላ ዘመን ላይ ደረስን አንቱ!

አቶ - ምን ሆንሽ ደግሞ? (ጀርባቸውን ሰጥተው ጀመራት ደግሞ ዓይነት ይገረምሟታል)

ወይዘሮ - አህያ አደራጃችሁ ብለው እኮ ነው አንድ ፍሬዎቹን ልጆች የደፏቸው

አቶ - አንድ ፍሬ መሆናቸውን ደግሞ እንዴት አወቅሽ በይ?

ወይዘሮ - (ግራ በመጋባት) እርስዎ ደግሞ እየሰሙት

አቶ - ኤድያ ድሮም ሰው ሲያረጅ መዘላበድ ይጀምራል። አንቺን ከቁብ መጣፌ ነው ጥፋቱ!

ወይዘሮ - እንደው አንድዳያውን ባያፈነዱት ይሻል ነበር። (እያጉረመረሙ...)

አቶ - ምንድነው ደግሞ የማያፈነዱት?

ወይዘሮ - አብዮቱን ነዋ! ባለፈው አይደል እንዴ እዚህ መስቀል አደባባይ

አቶ - አብዮት አደባባይ በይ አንቺ...

ወይዘሮ - የሆነው ይሁን! እዚያ ነው የማይነካ ነካክተው ያፈነዱት! ይኸው ማን ይመልሰው! ቁጭ ብለው የሰቀሉት
ቆመው ማውረድ ይቸግራል ሰውዬ!

አቶ - ሆሆ በይ ሰው እንዳይሰማሽ

You might also like