You are on page 1of 5

ስውር የሳይኪክ ጥበባት ምንጭና መገኛ ኢትዮጵያ

ከራፋቶኤል ወርቁ  

በዓለማችን በተለይም በሀገራችን  ኢትዮጵያ የተደበቀ ሰውር ተሰጥኦ እና ጥበብ ያላቸውን ሰዎች በጅምላ አጸያፊ ስም
በመስጠት የሃበሻ ኮተት ጥንቆላ ወዘተ እያልን እያጣጣልናቸው እነርሱም ሆነ የስራዎቻቸውን ውጤቶች ከማህበረሰቡ
በማግለል ጠቢባን በጥበባቸው  እራሳቸውንና ሀገራቸውን ሳይጠቅሙ ባዕዳንን በየዘርፉ እየጠቀሙ ይገኛሉ፡፡ እዚህ ጋር
አበክሬ ላስገነዝበው የምፈልገው ጉዳይ ይህ ስውር መንፋሳዊ ጥበብ በሁለት መልኩ ለይተን ማየት ይገባናል፡፡ የመጀመርያው
ከፈጣሪ የተለገሰን በተፈጥሮና በመንፈሳዊ ብቃት የምናገኘው መንፈሳዊ ፀጋና ጥበብ ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ለስጋዊ  ድሎት
በራስ ወዳድነት ሰይጣናዊ ከሆኑ ሃይላት ጋር በመተባበር የሚሰራ ምትሃት ወይም በሀገርኛው አባባል ጥንቆላ ነው፡፡ 

ታዲያ ከላይ የጠቀስነው መንፈሳዊ የነጠረ የነጠቀ ከስነ ልቦና ሳይንስና ከሌሎች የሳይኪክ ዘርፎች ቀድሞ  የተገኘው ስውር
መንፈሳዊ ጥበባት የሀገራችን በተለይም ደግሞ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ሀብትና ጥበብ ነው፡፡ ነገር ግን
በእጅ የያዙት ወርቅ እንዲሉ ባለን ሀብትና ጥበብ ሳንጠቀምበት ቀርተን በተጨባጩ በሳይንሳዊ መንገድ ብቻ ነው የሚያምኑት
ብለን የምንደሰኩርላቸው ነጮች ከሀገራችን በበዘበዙት መንፈሳዊ ጥበብ በመጠቀም ከቴክኖሎጂው ጫፍ ለመድረስ በቅተዋል
፡፡

ለዚህም ይረዳቸው ዘንድ  ይህ መንፈሳዊ ጥበብ የተገለጹባቸውን የጥበብ  መጻህፍት ሰርቀው በማሰረቅና በማስተርጎም
ከሳይንሱ ጋር በማጣመር ፓራ ሳይኮሎጂ የሚባል የትምህርት ተ—ም በማ——ም በትላልቅ የዓለማችን ዩንቨርስቲዎችና
ሌሎች ተ—ማት ውስጥ እያጠኑትና እየተመራመሩበት ይገኛል፡፡

ቢሆንም ግን ይህ መንፈሳዊ ጥበብ በነጮቹ አጠራር በሳይኪክ ፎርሙላ ወይም በላብራቶሪ ውስጥ የሚገኝ ባለመሆኑ ነጮች
በጥበቡ መገረምንና የሩቅ ታዛቢ ሆነው መገኘታቸው የሚካድ አይደለም ቢሆንም ግን በተወሰነ መልኩ ተጠቃሚ
መሆናቸውን የማንክደው ሀቅ ነው፡፡

በዚህ ጽሁፍ ማሳየት የምፈልገው ቁም ነገር አንዳንድ ምዕራባውያን ሀገራት በዚሁ የጥበብ ዘርፍ ለረጅም ጊዜ በላብራቶሪ
ውስጥ እና በትላልቅ የምርምር ተ—ማት ጥናትና ምርምር አድርገው ያልደረሱበትን ውጤት ከሺህ ዓመታት በፊት ግን
የኢትዮጵያ  አባቶች ከማወቅም አልፈው ለዚህ ዘመን እንዴት ማድረስ እንደቻሉ ከማስረጃ ጋር ለማሳየት እሞክራለሁ ለዚህም
ይረዳኝ ዘንድ የነርሱን የጥናት ግኝቶች በማብራራት እጀምራለሁ፡፡

ቴሌፓቲ፡ ኢኤስፒ በፓራ ሳይኮሎጂስት ጥናት


በተፈጥሮ ያገኘናቸው አምስቱ የስሜት አካላቶቻችን አካባቢያችንን እንድንረዳ እንድናውቅ የሚያደርጉ ሲሆን አንዳንድ የተለየ
ስጦታ ያላቸው ሰዎች ከዚህ ከተለመደው የተፈጥሮ ህግ  ውጪ  በሆነ መንገድ በሌላ ሰው አእምሮ ውስጥ ምን እንዳለና ምን
እያሰበ እንደሆነ ያለምንም ግልጻዊ መረጃ የማወቅ ስውር ችሎታ ቴሌፓቲ ወይም ስድስተኛው የስሜት ህዋስ ይባላል፡፡

ሌላው ደግሞ የሰው ልጅ በተፈጥሮው ሊያየውና ሊሰማው ከሚችልበት ወሰን በማለፍ ያለምንም አጋዥ የቴክኖሎጂ
መሳሪያዎች እርዳታ ማንኛውንም ክስተት ማወቅና መረዳት የሚያስችለው ተሰጥኦ ደግሞ ክሊርቪዮናስ በመባል ይታወቃል፡፡

ፓራ ሳይኮሎጂ ደግሞ መንፈሳዊ የሳይኪክ ክስተቶችን በሳይንሳዊ መንገድ የሚያጠና ዘርፍ ነው፡፡

ስድስተኛ የስሜት ህዋስ ወይም የቴሌፓቲ ተሰጥኦ ያላቸው ሰዎች ሌሎች ሰዎች ምን እንደሚያሰቡ እንዲሁም ወደፊት ሊሆን
የሚችለውን ነገር አስቀድሞ መረዳትና ማወቅ የሚችሉ ሰዎች ናቸው፡፡ በተጨማሪም እነዚህ ሰዎች እነርሱ በማያውቁት ሁኔታ
ከሌላው ሰው በተለየ መልኩ ድምጾችን መስማትና እንዲሁ ሌሎች ማየት የማይችሉትን ማየት የሚያስችል ተሰጥኦ አላቸው፡፡
ታዲያ በዚህ የሳይኪክ ምንነት ዙሪያ በሳንፎርድ እና በሃርቫርድ  እና በሌሎች ዩንቨርስቲዎች ውስጥ በሰፊው ምርምር
የተደረገበት እና እየተደረገበት የሚገኝ ሲሆን የመጀመርያው የሳይኪክ ዩንቨርስቲም በ 1996 ዓ/ም በአሜሪካን ፓራሳይኮሎጂ
ዲፓርትመንት ኦፍ ሳይኪክ በሚል ስያሜ በቨርጂንያ ዩንቨርስቲ በዶክተር አየን ስቴቬንሰን አማካኝነት ተ—ቁሙዋል፡፡
በ 1882 ዓ/ም ፍሬድሪክ ሜየር የተባለ ግለሰብ በእንግሊዝ ውስጥ የሳይኪክ ማህበር እንዲ——ም ከፍተኛ ጥረት በማደረግ
ተ—ሙን መስርቷል፡፡ ይህ የጥናት ማዕከል በዋነኝነት በድንገት ስለሚከሰቱ ነገሮች መንፈሳዊ ስለሆኑ  መላምቶች እና ስለዚህ
ስለ ቴሌፓቲ ተሰጥኦ ምንጭ እንዲሁም ስለሌሎች ተጉዋዳኝ ነገሮች መረጃዎችን በመሰብሰብ ለበርካታ ዘመናት ሲያጠና የቆየ
ቢሆንም ውጤታማ ግን አልነበረም ምክንያቱ ደግሞ የሳይኪክ ጥበብን ምንጭ እና መገኛ ላይ መድረስ አለመቻላቸው ነበር፡፡

አስቀድሞ የመተንበይ ተሰጥኦ (pre-cogntion)


ሌላው የሳይኪክ ጥናት ባለሙያዎችን የፈተነው ጉደይ ደግሞ አስቀድሞ የሚሆነው ነገር ቀድሞ ማወቅ  በህልም በራዕይ
ወይም ደግሞ እንደሰመመን በሃሳብ ጭልጥ ብሎ እነደ ፊልም ወደፊት የሚሆነውንመመልከትና በተለየ ሁኔታ አንድ ግለሰብ
በስውር ያየውና የሰማው ነገር በገሃድ ሲገለጥ ይህን ተሰጥኦ የሙያው ጠበብቶች አስቀድሞ መተንበይ ወይም
parapsychology ብለው ሰይመውታል ፡፡ይህን ተሰጥኦ ለማስረዳትም ከዚህ በታች ለብዙዎቻችን አዲስ ያልሆነ አንድ
ክሰትትን አነሳለሁ፡፡

በ 1898 በፈረንጆቹ አቆጣጠር ቲታኒክ የተባለችዋ ግዙፍ መርከብ ተገንብታ ለጎዞ ከመዘጋጀትዋ ከ 14 ዓመት ቀድም ብሎ
ሞርጋን ሮበርትሰን የተባለ የረጅም ልቦለድ ጸሃፊ ዘሬክ ኦፍ  ቲታኒክ በሚል ርዕስ መጽሃፍ አሳትሞ ነበር ፡፡ በመጽሃፉ
የተቀነባበረው ትረካ የገጸ ባህሪያቱ አሳሳል የታሪኩ ሂደትና አጨራረስ በእውነት ከተሰራችው ቲታኒክ መርከብ ጋር በመቶ
ዘጠና ዘጠኙ አንድ አይነት ታሪክ ነበር፡፡ ሌላው አስደናቂ ነገር የመጽሃፉ ቲታኒክ እና እውነተኛዋ ቲታኒክ በባህር ላይ
የሚንሳፈፍ በረዶ ገጭተው የሰጠሙ ሲሆን የመርከብዋ ፍጥነት መጠን የህይወት ማዳኛ ጀልባዎች ብዛት የተሳፋሪዎች ሸክምና
መጠን ከመጽሃፉ ጋር መመሳሰሉ ነበር፡፡

ታዲያ እንደ ቴሌፓቲ ሁሉ ይህ አስቀድሞ የመተንበይ ተሰጥዖም ለፓራሳይኮሎጂስቶች እንቆቅልሽ እንደሆነ ቀርቷል፡፡
ለበርካታ ዘመናት በዘርፉ ጥናትና ምርምር ቢያደርጉም የዚህ ተሰጥኦ ባለቤቶች እንዴት የዚህ ይህን ተሰጥኦ ባለቤት መሆን
እንደቻሉ ተጨባጭ የሆነ ሳይንሳዊ ማስረጃ ማቅረብ አልቻሉም፡፡

የኛ ኢትዮጵያውያን አባቶች ግን የዚህን ተሰጥኦ ምንጭ ከማወቅም አልፎ እንዴት ከትውልድ ትውልድ ማስተላለፍ እንደቻሉ
በሚቀጥለው ክፍል እንመለከታለን፡፡

More Articles...

1. ሰብሊ ሞንያል ፕራሜንሽን ( ቀፈፈኝ )


2. ስውር የሳይኪክ ጥበባት ምንጭና መገኛ ኢትዮጵያ
3. ከራፋቶኤል ወርቁ  
4. በዓለማችን በተለይም በሀገራችን  ኢትዮጵያ የተደበቀ ሰውር ተሰጥኦ እና ጥበብ ያላቸውን ሰዎች በጅምላ አጸያፊ
ስም በመስጠት የሃበሻ ኮተት ጥንቆላ ወዘተ እያልን እያጣጣልናቸው እነርሱም ሆነ የስራዎቻቸውን ውጤቶች
ከማህበረሰቡ በማግለል ጠቢባን በጥበባቸው  እራሳቸውንና ሀገራቸውን ሳይጠቅሙ ባዕዳንን በየዘርፉ እየጠቀሙ
ይገኛሉ፡፡ እዚህ ጋር አበክሬ ላስገነዝበው የምፈልገው ጉዳይ ይህ ስውር መንፋሳዊ ጥበብ በሁለት መልኩ ለይተን
ማየት ይገባናል፡፡ የመጀመርያው ከፈጣሪ የተለገሰን በተፈጥሮና በመንፈሳዊ ብቃት የምናገኘው መንፈሳዊ ፀጋና
ጥበብ ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ለስጋዊ  ድሎት በራስ ወዳድነት ሰይጣናዊ ከሆኑ ሃይላት ጋር በመተባበር የሚሰራ
ምትሃት ወይም በሀገርኛው አባባል ጥንቆላ ነው፡፡ 
5. ታዲያ ከላይ የጠቀስነው መንፈሳዊ የነጠረ የነጠቀ ከስነ ልቦና ሳይንስና ከሌሎች የሳይኪክ ዘርፎች ቀድሞ  የተገኘው
ስውር መንፈሳዊ ጥበባት የሀገራችን በተለይም ደግሞ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ሀብትና ጥበብ
ነው፡፡ ነገር ግን በእጅ የያዙት ወርቅ እንዲሉ ባለን ሀብትና ጥበብ ሳንጠቀምበት ቀርተን በተጨባጩ በሳይንሳዊ
መንገድ ብቻ ነው የሚያምኑት ብለን የምንደሰኩርላቸው ነጮች ከሀገራችን በበዘበዙት መንፈሳዊ ጥበብ በመጠቀም
ከቴክኖሎጂው ጫፍ ለመድረስ በቅተዋል ፡፡
6. ለዚህም ይረዳቸው ዘንድ  ይህ መንፈሳዊ ጥበብ የተገለጹባቸውን የጥበብ  መጻህፍት ሰርቀው በማሰረቅና
በማስተርጎም ከሳይንሱ ጋር በማጣመር ፓራ ሳይኮሎጂ የሚባል የትምህርት ተ—ም በማ——ም በትላልቅ
የዓለማችን ዩንቨርስቲዎችና ሌሎች ተ—ማት ውስጥ እያጠኑትና እየተመራመሩበት ይገኛል፡፡
7. ቢሆንም ግን ይህ መንፈሳዊ ጥበብ በነጮቹ አጠራር በሳይኪክ ፎርሙላ ወይም በላብራቶሪ ውስጥ የሚገኝ ባለመሆኑ
ነጮች በጥበቡ መገረምንና የሩቅ ታዛቢ ሆነው መገኘታቸው የሚካድ አይደለም ቢሆንም ግን በተወሰነ መልኩ
ተጠቃሚ መሆናቸውን የማንክደው ሀቅ ነው፡፡
8. በዚህ ጽሁፍ ማሳየት የምፈልገው ቁም ነገር አንዳንድ ምዕራባውያን ሀገራት በዚሁ የጥበብ ዘርፍ ለረጅም ጊዜ
በላብራቶሪ ውስጥ እና በትላልቅ የምርምር ተ—ማት ጥናትና ምርምር አድርገው ያልደረሱበትን ውጤት ከሺህ
ዓመታት በፊት ግን የኢትዮጵያ  አባቶች ከማወቅም አልፈው ለዚህ ዘመን እንዴት ማድረስ እንደቻሉ ከማስረጃ ጋር
ለማሳየት እሞክራለሁ ለዚህም ይረዳኝ ዘንድ የነርሱን የጥናት ግኝቶች በማብራራት እጀምራለሁ፡፡
9. ሰብሊ ሞንያል ፕራሜንሽን ( ቀፈፈኝ )
10. በተለምዶ በህይወታችን ውስጥ የተለያዩ ረጃጅምና አጫጭር ጎዞዎችን ለማድረግ ስንነሳ ወይም ስናስብ በማናውቀው
መጥፎ ስሜት ወይም በሀገርኛው ቀፎን ወይም ከብዶን ስንቀር ከተለያዩ አደጋዎች ስናመልጥ ይስተዋላል፡፡ የዘርፉ
ባለሙያዎች እደሌሎቹ ተሰጥኦዎች ለዚህም የሚጨበጥ ሳይንሳዊ ማስረጃ መስጠት ባይችሉም ሰብሊሞንያል
ፕሪሜንሽን ብለው ሰይመውታል፡፡
11.  
12. በሳይኪክ ተሰጥኦ ህመመን መፈወስ
13. ህመምን መፈወስ የሚያስችለው የዚህ ተሰጥኦ ባለቤቶች ታማሚውን በእጃቸው በመዳሰስ ታማሚውን ይፈውሳሉ
፡፡ የተለያዩ ግለሰቦችና የጥናት ቡድኖች የዚህ ህመምን የመፈወስ ተሰጥኦ ከየት እንደሚከሰት ተደጋጋሚ ጥናቶችን
ያካሄዱ ሲሆን ለአብነትም ሲስተር ኤጅስታ ስሚዝ የጥናት ውጠየት መጥቀስ ይቻላል፡፡
14. ሲስተር ኤጂስታ በአልትራ ጨረር የሚመነጨውን ኤንዛይም አበላሽታ በጠርሙስ ጨምራ የሳይኪክ ተሠጥኦ
ባለቤት የሆነው ግለሰብ እንዲይዘው አደረገች በመቀጠልም የተበላሸው ኤንዛይም ሲድን አዳዳኑ  ከትራማፓቴክ
ማግኔቲክ ፊልድ ጠንካራ አሰራር ጋር የሚመጣጠን ነበር፡፡ በዚህ ውጤት በመታገዝ በተገኘው አስተያየት የሳይኪክ
ፈዋሽ እጅ የማግኔት ሶስት እጥፍ ሃይል እንዳለው ተናግረዋል፡፡ቢሆንም ግን አሁን እስካለንበት ጊዜ ድረስ የዚህ
ተሰጥኦ እና ጥበብ ምንጭ በእግርጠኝነት ማወቅ እንዳልተቻለ የዘርፉ ባለሙያዎች ይገልጻሉ፡፡
15. በሳይኪክ ተሰጥኦ ህመመን መፈወስ
16. ለአብነትም ላውረንስ ላሽን የተባሉ የዘርፉ ባለሙያ ይህን ብለዋል " በሳይኪክ የመፈወስ ሂደት  የኮረንቲ ጉልበት
እንደሚፈስ ወይም እንደሚተላለፍ ሃይል ነው ስለሆነም ተጨባጭ የሆነ የሳይኪክ ጉልበት ማስረጃ ማግኘት
አልተቻለም ስለሆነም በዚህ አንጻር የተለየ ሀይል በማስተላለፍ ማለትም በሳይኪክ ተሰጥኦ እንዴት መፈወስ
እንደሚቻል ሚስጥሩ አሁንም አልተገለጸም "፡፡
17. ይህን ያህል ስለ ፓራሳይኮሎጂ የጥናት ውጤቶች ይህን ያህል ካልኩኝ ወደ ሀገራችን እንመልስና መንፈሳዊና የነጠረ
የነጠቀ ከሌሎች የስነ ልቦና ዘርፎች ቀድሞ ስለተገኘው እንዲሁም  ዓለማችን አሁን ለደረሰችበት የስልጣኔ ጫፍ
የሃገራችን ስውር መንፈሳዊ ተሰጥኦዎችና ጥበባት  ያበረከቱትን ይህ ነው የማይባል አስተዋጽኦ እንመለከታለን፡፡
18.
ከዚህ በፊት ለመጥቀስ እደሞከርኩት ከፓራሳይኮሎጂስቶች የላብራቶሪ ጥናትና ምርምር መሰረት ቴሌፓቲ ትርጉሙ
ስድስተኛ የስሜት አካል ማለት ነው፡፡ ይህ ተሰጥኦ ያላቸው ግለሰቦች  የሰውን አእምሮ ማንበብ የሚችሉና ወደፊት
ሊሆን የሚችለውን መተንበይ የሚችሉ ሰዎች ናቸው ፡፡ ቢሆንም ግን በፓራሳይኮሎጂስቶች ጥናት መሰረት የዚህ
ጥበብ ምንጭ ምን እንደሆነ እንዳልደረሱበት የራሳቸው ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡
19. ወደሃገራችን ኢትዮጵያ ስንመጣ ግን የዚህ ጥበብና ተሰጥኦ ባለቤቶች የሆኑ በርካታ አባቶችን የምናገኝ ሲሆን ይህን
ጽሁፍ ሳዘጋጅም  በዋልድባ ገዳምና በሌሎች ገዳማት እንዲሁም  በገጠሪቱ የሃገራችን ክፍሎች የጥበቡ ባለቤት የሆኑ
አባቶችን በአካል ያገኘሁ ሲሆን ስለዚህ ጥበብና ተሰጥኦ በቂ ማብራሪያን ሰጥተውኛል፡፡ በጎንደር የቅኔ መምህር
የሆኑት  የኔታ ዳንኤል ስለዚህ ጥበብ ሲገልጹ ይህን ጨምሮ ሌሎች ከላይ የጠቀስናቸውና ሌሎችም አስደናቂ ስውር
መንፈሳዊ ጥበባት የሚገኙት ሰዎች ስጋቸውንና ነፍሳቸውን ለእግዚአብሄር በማስገዛት በርሱ መንገድ ሲመላለሱ
እንደሆነ ገልጸው ለአብነትም ስለሚያውቋቸው አባቶች ምስክርነት ሰጥተውኛል፡፡ በዛው በጎንደር አካባቢ የአቡሻክር
መምህር የነበሩ አንድ አባት የሰውን አእምሮ ማንበብና መግለጽ ከመቻላቸው በተጨማሪ የሰዎችን የህይወት እጣ
ፈንታ አስቀድመው በመተንበይም ይታወቁ ነበር በመጨረሻም ከመሞታቸው በፊት አሟሟታቸውን አስቀድመው
ለተማሪዎቻቸው እንደተናገሩት እንደነበር ነግረውኛል፡፡ አስከትዬ ይህን ጥበብ ምንጭ ምን እንደሆነ ላቀረብኩላቸው
ጥያቄም ሲመልሱ  ከመንፈሳዊ ህይወት በተጨማሪ አቡሻክር'መጽሐፈ ሔኖክ' መርበብተ ሰለሞን  እና ሌሎችንም
ጥንታዊ መጻህፍትን  ጠንቅቆ መማርና መረዳት የቻለ ግለሰብ ይህን ጨምሮ ሌሎች በርካታ ጥበባትን ለአብነት
ያህልም ትንቢት የመናገር ራዕይ የመናገር ዝናብ የማዝነብ የተሰወሩ መናፍስትን የማሰር የመፍታት እንዲሁም
የማዘዝ ጥበብን መጎናጸፍ እንደሚችል ነግረውኛል፡፡
20. ጠቢቡ ሰለሞንን ጨምሮ በርካታ ኢትዮጵያውያን አባቶች ከላይ በከፊል የተጠቀሱትን ጥበባት ሲጠቀሙ የነበረ
ሲሆን ጠቢቡ ሰለሞን አጋንንት በማዘዝ የጉልበት ስራ ያሰራቸው እንደነበር በትውፊት ከዘመናችን የደረሱት የኛ
ጥንታዊና  በርካታ አስገራሚ ጥበባት የያዙትን መጻህፍት ለአብነትም መጽሀፈ ምስጢር ዘቅዱስ አዶናይ
ራፋኤል'መርበብተ ሰለሞን 'መስጥመ አጋንንት እና መጽሀፈ ሔኖክን ለአብነት መጥቀስ እንችላለን፡፡ የኛ ጥንታዊ
አባቶች ለዛሬው የሳይንስ( ለስነ ልቦና' ለሂሳብ ቀመር'ለህክምና ሳይንስ) እና ለቴክኖሎጂው ዕድገትና መነሻ
መሆናቸውን ያስመሰከሩበትን ዛሬም ቢሆን ሳይንሱ ያልደረሰበትን ምስጢራትን ለዛሬው ትውልድ ለማስረከብ እንደ
አሁኑ ዘመን የህትመት መሳሪያዎች ባልነበሩበት ዘመን ብራና ፍቀው ቀለም በጥብጠው መቃ ቀርጸው በብዙ
ፈተናዎች ውስጥ አልፈው ለዚህ ዘመን በርካታ የጥበብ መጻህፍትን አውረስውናል፡፡
21. በተጨማሪም ከሁሉም የአፍሪካ ሀገራት ተለይታ የረጅም ዘመናት የታሪክ ሃገር እንድትሆንና የመካከለኛው ምስራቅ
አገሮችም ከመጥፋት የተነሳ መያዣ መጨበጫ ያጡበትን ጥንታዊ ታሪካቸው መንደርደሪያ ፍንጭ ለማግኘት
ሀገራችን ውስጥ እንዲርመሰመሱ ያደረጋቸውም የአባቶቻችን ልዩ ጥበባት እና የስነ ጽሁፍ ችሎታም ነበር፡፡
22. ይህ ቢሆንም ቅሉ በእጅ የያዙት ወርቅ እንዲሉ ባለን ሀብትና ጥበብ ሳንጠቀምበት ቀርተን በተጨባጩ በሳይንሳዊ
መንገድ ብቻ ነው የሚያምኑት ስውር መንፈሳዊ ጥበቦችን አይጠቀሙም ብለን የምንደሰኩርላቸው ነጮች ከሀገራችን
ከኢትዮጵያ በበዘበዙት ጥበባት በመጠቀም ከፖለቲካውና ከቴክኖሎጂው ጫፍ ለመድረስ በቅተዋል፡፡ ለዚህም
የበለጠ ይረዳቸው ዘንድ የተለያየ ስትራቴጂዎችን በመንደፍ ከላይ የጠቀስናቸውን የጥበብ መጻህፍቶቻችንን ሰርቀው
በማሰረቅ እና በማስተርጎም ከሳይንሱ ጋር በማጣመር ፓራ ሳይኮሎጂ የሚባል የትምህርት ተቋም በማቋቋም 
በትላልቅ የዓለማችን ዩንቨርስቲዎች ውስጥ  እና ሌሎች ተቋማት ውስጥ እያጠኑበትና እየተመራመሩበት ይገኛል፡፡
ለዚህም ሰለባ ከሆኑት መጻህፍት አንዱ መጽሀፈ ሔኖክና መርበብተ ሰለሞንን እንዱሁም በገንዘብ ሃይል ገዝተው
የወሰዱዋቸው የራሳችንን ጠቢባንን መጥቀስ ይቻላል ፡፡ ጀምስ ብሩስ የተባለው ግለሰብ የአባይን ወንዝ መነሻ ፍለጋ
በሚል ሰበብ መጥቶ ጎንደር ቁስቋም ቤተክርስትያን ውስጥ ባደረገው ቆይታ መጽሀፈ ሔኖክን ጨምሮ አንድ ግመል
መጽሀፍ ሰርቆ ወደ ሃገሩ ይዞ ገብቶዋል፡፡ ጀምስ ብሩስ ሀገራችን ኢትዮጵያ ላይ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ከፍተኛ
ዝርፊያ እያደረጉ ያሉት የምስጢር ሰዎች ወይም ፍሪማስነሪዎች አባል ሲሆን ቀጥተኛ ተጠሪነቱም ለእንግሊዝዋ
ንግስት ኤልሳብጥ የነበረ ሲሆን ከፊሉን የግዕዝ መጻህፍት ከዚህ በገንዘብ ገዝተው በወሰዱት ኢትዮጵያዊ አማካኝነት
አስተርጉመው ከጥበቡ መቋደስ ችለዋል፡፡
23. እነዚህ የምስጢር ሰዎች እየተባሉ የሚጠሩት አካላት  ታሪካዊ አመጣጣቸው በቂ ያልሆነና ከአፈታሪክነት የዘለሉ
መረጃዎችን ማግኘት ባይቻልም ሉሲፈር በተባለው አጋንንት መንፈስ በመመራት አለምን በርሱ መንፈስ አንድ
አድርጎ ለመግዛት እየተሯሯጡ የሚገኙ አካላት ናቸው፡፡ ለዚህም ይረዳቸው ዘንድ የመዝናኛውን ኢንዱስትሪ'
የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ሴክተሩን በመቆጣጠር ዓለማችንን እየገዝዋት ይገኛሉ ይህንንም ወደፊት በሰፊው
ከማስረጃዎች ጋር በበቂ ሁኔታ የምናየው ሲሆን ለዚህ ጽሁፍ እነርሱን መጥቀስ ያስፈለገበት ምክንያት ግን
እንደሚከተለው ነው፡፡
24. ወደድንም ጠላንም እድሜ ለጥንታዊ አባቶቻችን ሀገራችን ኢትዮጵያ የዓለምን ምስጢራት ይዛ መገኘት ችላለች
እነርሱም ይህን በማመናቸው ከጀምስ ብሩስ ጀምሮ በበርካታ ግለሰቦችና ተቋማት አማካይነት  የጥበብ
መጻህፍቶቻችን ጨምሮ ጥንታዊ ቅርሶቻችንን በማዘረፍ በጥበባችን መጠበብ ችለዋል፡፡ ለዚህም ይመስላል
በየትኛውም ምስጢራዊ እንቅስቃሴያቸው ውስጥ የኛን የኢትዮጵያውያንን የጥበብ አሻራ የምናየው ለማስረጃም
በ CIA እና ሌሎችም ትላልቅ የንግድ ካምፓኒዎች ምልክቶች ውስጥ እንደነርሱ አጠራር ሲጅል  ውስጥ የኛን ሀገራ
ጠልሰሞች ለምሳሌ ንስር አሞራን የ "ቶ"  እና  በአሜሪካኑ ዶላር ላይ የሚገኘው ዓይን ምልከትና ሌሎችንም በርካታ
የኛን ጠልሰማት የምናየው፡፡ እነዚህን እና ሌሎች መርበብተ ሰለሞን በተባለው መጽሃፋችን ውስጥ የሚገኙትን
ጠልሰማት አባቶቻችን ለመንፈሳዊና ለበጎ አድራጎቶች ለምሳሌ ለፈውስ የሚጠቀሙባቸው ሲሆን ነጮቹ ግን ከኛ
የወሰዱትን ይህን ጥበብ ከማይገባ መንፈስ ጋር በማጣመር የሰዎችን ጭንቅላት በመስረቅ በንግዱና በፖለቲካው
ዓለም ተጽእኖ በመፍጠር እየተጠቀሙበት ይገኛል፡፡
25. በመጨረሻም ነገሩን ሰብሰብ ለማድረግ ከላይ ለማየት እንደሞከርንው ምዕራባውያኑ ከኛ ሰርቅው በመውሰድ
በትላልቅ የጥናት ተቋሞቻቸው ውስጥ ለበርካታ ዘመናት አጥንተው መልስ ያጡባቸው ፓራሳይኮሎጂን ጨምሮ
በርከት ያሉ ጥበባት ምንጭም እንዲሁም ምላሽ ያጡባቸው ሳይንሳዊ ጥያቄዎቻቸው መልስ የኛ ኢትዮጵያውያን
ሊቃውንት አባቶች ናቸው ፡፡ ምክንያቱ ደግሞ የኛ አባቶች ህብረታቸውን ከጥበብ ባለቤት ከሆነው ከእግዚአብሄር
ጋር አድርገው መኖራቸው ነው፡፡ ጠቢቡ ሰለሞን በመጽሃፉ የጥበብ መጀመርያ እግዚአብሄርን መፍራት ነው
እንዳለ፡፡ ለዛሬ እዚህ ላይ ልሰናበት፡፡
26.                                                                                                                           መልካም ሳምንት

You might also like