Professional Documents
Culture Documents
1 መግቢያ 2
2 ትውልድ እና ዕድገት 4
2.1 የዘር ሐረግ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 4
2.2 ጽንሰትና ልደት . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 4
2.3 ዲቁና፣ ቅስና እና ምናኔ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 5
3 ገድላቸው 7
3.1 ምንኲስና እና ከአቡነ ተክለ ሃይማኖት ጋር . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 7
3.2 የሞረት አይሁድና ማኅሌተ ጽጌ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 8
3.3 ኢትዮጵያን መዘዋወራቸው . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 8
3.4 ዕረፍታቸው . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 10
3.5 ቃልኪዳናቸው . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 11
3.6 ገድላቸው በመጽሐፍ ቅዱስ እይታ . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 12
5 የገድላቸው መጽሐፍ 20
6 ገዳሞቻቸው 22
6.1 ምሑር ኢየሱስ ገዳም . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 22
6.2 ደብረ ብሥራት ገዳም . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . . 23
1
ምዕራፍ 1
መግቢያ
እኔን የሚወድ ቢኖር ራሱን ይካድ፣ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ ... ነፍሱን ሊያድን
የሚወድ ሁሉ ያጠፋታል፣ ስለ እኔ ግን ነፍሱን የሚያጠፋ ሁሉ ያገኛታል
− ማቴ 16፥24-25
ባለው መሠረት ብዙ ቅዱሳን ጻድቃን መከራ መስቀሉን ተሸክመው ወንጌልን በመስበክና ክርስትናን
በማስፋፋት እግዚአብሔርን አገልግለውታል። ይህንን ቃልም ተስፋ በማድረግ ዳዋ ጥሰው፣ ጤዛ ልሰው፣
ድንጋይ ተንተርሰው፣ ድምጸ አራዊቱን፣ ግርማ ሌሊቱን፣ ጸበ አጋንንቱን ሁሉ ታግሰው በየዱሩ በየገደሉ
በመንፈሳዊ ሥራ ተጠምደው ይኖራሉ።
በሃገራችን ኢትዮጵያ ከተነሡ እኚህን ከመሰሉ ቅዱሳን ጻድቃን መካከል አንዱ አቡነ ዜና ማርቆስ
ናቸው። ”ብዙ ሰዎችንም ወደ ጽድቅ የሚመልሱ እንደ ሰማይ ከዋክብት ለዘለዓለም ይደምቃሉ” (ዳን
12፥3) የሚለውን አምላካዊ ቃል ተስፋ አድርገው በመላዋ ሃገራችን ወንጌልን እየሰበኩ፣ ጣዖታትን
እያፈረሱ፣ አብያተ ክርስቲያናትን እየተከሉ እስከ ሕይወታቸው ፍጻሜ ቆይተዋል። በዚህም እንደ
ወንድማቸው እንደ ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አዲስ ሐዋርያ እስከ መባል ደርሰዋል።
አቡነ ዜና ማርቆስ ለፈጣሪያቸው ሕይወታቸውን አሳልፈው ከሰጡበት ጊዜ ጀምሮ ያለ ምቾት፣
ያለ ሐኬት በርዳታ፣ በማስተማር፣ በሰማዕትነት፣ በድንግልና፣ በተባሕትዎና በምንኲስና 140 ዘመን
ፈጣሪያቸውን አገልግለዋል። ሃይማኖታቸውን ጠብቀው ገድላቸውን ካጠናቀቁ በኋላ በደብረ ብሥራት
ገዳም በሰላም ዐርፈዋል።
ከዚህ በኋላ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት በአፄ ይስሐቅ ዘመነ መንግሥት በማዕረገ ቅዱሳን
እንዲታሰቡ፣ መታሰቢያ በዓል እንዲደረግላቸው፣ በስማቸው አብያተ ክርስቲያናት እንዲታነጹ፣ ገዳማትም
እንዲቆረቆሩ፣ መጽሐፍ እንዲጻፍላቸው በፈቃደ እግዚአብሔር በጉባኤ ወስነዋል። ገድላቸውንም አሰረፍኖታቸውን
2
ምዕራፍ 1. መግቢያ
3
ምዕራፍ 2
ትውልድ እና ዕድገት
4
ምዕራፍ 2. ትውልድ እና ዕድገት
ከዕለታት በአንዱ ቀን ግን ወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ ወደ ዲቦራ መጥቶ በራእይ ተገልጦ ገድሉ
ትሩፋቱ ክብሩ እንደራስ ጠጉሩ የበዛ የተባረከ ፍሬ በማኅፀኗ እንደሚያድር አበሠራት። ለባሏ አባ ዮሐንስም
በቤተ መቅደስ የእመቤታችንን ስዕል ሲያጥን ተገልጦለት፦ ’ለድኆች በምታደርገው መራራት፣ ምጽዋት
ቡሩክ የሆነ ልጅ ይወለድልሃል፤ ስሙም ዜና ማርቆስ ይባላል’ ብሎ አበሠረው።
5
ምዕራፍ 2. ትውልድ እና ዕድገት
በዚሁም አባታችን አባ ዜና ማርቆስ የካቲት 24፣ 1333 ዓ.ም. አካባቢ3 ቀን ተፀንሰው በካህናተ
ሰማይ መታሰቢያ ዕለት ኅዳር 24 በጽላልሽ ዞረሬ፣ ቡልጋ፣ በኢቲሳ ቅዱስ ሚካኤል አጥቢያ ተወለዱ።
የስማቸውም ትርጓሜ በቅዱስ ማርቆስ ብሥራት (ዜና) የተገኘ፣ የተወለደ ማለት ነው። በተወለዱ ጊዜም
ሊቃነ መላእክቱ ቅዱስ ሩፋኤልና ቅዱስ ዑራኤል ልክ እንደ ነቢይ ኤልያስ የብርሃን ልብስ አልብሰው
በክንፋቸው ጋርደዋቸዋል። ገና ጡት ሳይጠቡም፣ እናታቸው ሳታውቅ በግብጽ የቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ
መቃብር ባለበት ወስደው እንዲባረኩ አድርገው መልሰዋቸዋል።
በተወለዱ በሦስተኛው ቀንም ከእናቱ ዕቅፍ ወርዶ በሥላሴ ስም አምናለሁ ብሎ ሦስት ጊዜ ሰግዷል።
ዐርብ እና ረቡዕ በሚሆኑ ቀናትም የእናታቸውን ጡት ባለመጥባት ጾምን ይጾሙ ነበር። በ40ኛው ቀንም
ለመጠመቅ በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በተገኘበት ጊዜ አጥማቂው አጎቱ ቀሲስ እንድርያስ ጸሎት
በማድረግ ላይ እያለ የመጠመቂያው ውኃ እጅግ ይፈላል፤ በዚህ ጊዜ ቀሲስ እንድርያስን ጨምሮ ሁሉም
ደንግጠው ጥለው የሸሹ ቢሆንም መልአኩ አረጋግቶ መልሷቸዋል። እንዲያውም አጥማቂው ራሰ በራ
የነበረው የ72 ዓመት የዕድሜ ባለጠጋ ቀሲስ እንድርያስ ከውኃው ራሱ ላይ ቢያፈስ ጠጉራም ሆነ።
3
ገድላቸው ’ግርማ አስፈሪ ሲነግሥ ያን ጊዜ አባታችን ዜና ማርቆስ 40 ዓመት ሆኖት ነበር’ ስለሚልና ግርማ አስፈሪ (ውድም
አስፈሪ) በ1374 ዓ.ም. ስለነገሠ ነው
6
ምዕራፍ 3
ገድላቸው
7
ምዕራፍ 3. ገድላቸው
ጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖትም ከደብረ ብሥራት ለመሄድ በተነሡ ጊዜ በዚያ የነበሩ
ዛፎች፣ እንጨቶችና ደንጊያዎች ሁሉ አብረዋቸው ለመሄድ ተነሡ። እርሳቸው ግን ሁሉንም በዚሁ
በደብረ ብሥራት እንዲጸኑ ገዘቷቸው፤ እንዲያውም ያቺን ደብረ ብሥራት ገዳምን ሳይሳለም ማንም ወደ
እርሳቸው ሃገር እንዳይመጣ አዘዋል
8
ምዕራፍ 3. ገድላቸው
ጻድቁ አባታችን በጾም በጸሎት እጅግ ይተጉ ነበር፤ በዓመትም 3 ጊዜ ብቻ፦ በጌታችን ልደት፣
ጥምቀትና ትንሣኤ ካልሆነ በቀር እህልና ውኃ አይቀምሱም ነበር። ከ40 ዓመት ዕድሜአቸው በኋላ
በጸሎታቸው አጋንንት ታስረው ነበርና በመላዋ ኢትዮጵያ መናፍቃን አልተነሡም፤ ቀዳሚት ሰንበት እንደ
9
ምዕራፍ 3. ገድላቸው
ክርስቲያን ሰንበት አትከበር ከሚሉና ንስሃ አያስፈልግም ከሚሉ በቀር። እኚህንም አባታችን ረተዋቸዋል4 ።
3.4 ዕረፍታቸው
ጻድቁ አባታችን ዜና ማርቆስ በመጨረሻው ዘመናቸው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብዙ
ቃልኪዳኖችን ከሰጣቸው በኋላ ገነትንና ሲዖልን አስጎበኛቸው። ከ10 ወራት በኋላም እንደሚያርፉ
ነግሮአቸው ወደ ገዳማቸው ደብረ ብሥራት መለሳቸው።
ጻድቁ አባታችንም በገዳማቸው ላሉ መልእከተኞች ከመስከረም እስከ ታህሣሥ ወር መግቢያ የመንፈስ
4
’ለኢትዮጵያ ያበረከቷቸው አስተዋጽዖዎች’ የሚለውን ምዕራፍ ተመልከት።
10
ምዕራፍ 3. ገድላቸው
ልጆቻቸው ሁሉ እንዲመጡ ላኩ። በታህሣሥ ወር የመጀመርያዋ ቀንም 8000 ልጆቻቸው በዚያች ገዳም
በተሰበሰቡ ጊዜ 8 እንጀራ ብቻ የነበራቸው የገዳሙ ደቀ መዛሙርት ተጨነቁ። በዚህ ጊዜ አቡነ ዜና
ማርቆስ 8ቱን እንጀራ ባርከው፣ ቆራርሰው ሰጧቸው። በዚህም 8 ሺሁም ልጆቻቸው በልተው ጠግበው
108 መሶብ ሙሉ ፍርፋሪ ተርፎ ተመልሷል።
ከዚህም በኋላ በደንስ በረሃ ያገኟት የእመቤታችን ሥዕል ባለበት ቤተ ክርስቲያን መሥዋዕት እንዲያዘጋጁ
ልጆቻቸውን አዘዟቸው። ራሳቸው ሠራዒ ካህን ሆነው ቅዳሴ በሚቀድሱበት ጊዜም 8000 ልጆቻቸው
ሥጋ ወደሙ ሳይቀበሉ መሽቶ ሊነጋ ነውና ፀሐይ እንድትቆም ወደ እግዚአብሔር አመለከቱ። በዚህ ጊዜ
ፀሐይ መሥዋዕተ ሠርኩ እስኪያልቅ ድረስ በሰማይ ቆመች።
ልጆቻቸውንም ሁሉ ሲመክሩ ከቆዩ በኋላ በታህሣሥ 3፣ ዐርብ ቀን ዐረፉ። የክብር ባለቤት ጌታችን
እና እናቱ እመቤታችን፣ ሠራዊቶቻችውም መላእክት ወርደው ክብርት ነፍሱን አሳረጓት። በዚያም እስከ
ታላቁ ወንዝ ዠማ ድረስ መልካም ጣፋጭ መዓዛ ለ40 ቀናት ያህል ሸተተ።
የዐርብ ከሰዓት ቅዳሴ ሊጀምር ሲልም የግብጹ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ዮሐንስ5 ከግብጽ በእሳት ሠረገላ ተጭነው
በዚያች ቤተ ክርስቲያን ደርሰው ሠራዒ ካህን ሆነው ቀድሰዋል። በኋላም ለዜና ማርቆስ ደቀ መዛሙርት
እንደነገሯቸው በግብጽ አይሁድ፣ ክርስቲያኖችና እስላሞች ክርክር ገጥመው ሳሉ ፀሐይ በመቆሟ የመቆሟ
ምክንያት እንዲገለጥ ጸሎት ሲያደርጉ ከሰማይ ድምጽ መጥቶ ”ክቡር አባ ዜና ማርቆስ እጅግ ብዙ
ለሆኑ ልጆቹ ቅዱስ ቊርባንን እስከሚያቀብሏቸው ድረስ እንዳትጠልቅበት አቁሟታልና የፀሐይ መቆሟ
ስለዚህ ነው” አሏቸው። በዚህም የተነሣ በዚያ የነበሩ እስላሞችና አይሁዶች አምነው እንደተጠመቁም
ተናግረዋል። እኚህ የግብጽ ሊቀ ጳጳስ አባ ዮሐንስ በዚያው በደብረ ብሥራት ለአንድ ዓመት ከቆዩ በኋላ
ወደ ሃገራቸው ተመልሰዋል።
3.5 ቃልኪዳናቸው
እግዚአብሔር ጻድቃን፣ ቅዱሳን ወዳጆቹን በአጸደ ሥጋ ለሠሩት ተጋድሎ ገነት፣ መንግሥተ ሰማያትን
በማውረስ ዋጋቸውን ይሰጣቸዋል። ነገር ግን ይህ ብቻ ሳይሆን ከሰዎች ልጆች ስም የሚበልጥ የመታሰቢያ
ስም በቤቱና በቅጥሩ ይሰጣቸዋል። ነገር ግን የቅዱሳን ዋጋ በዚህ ብቻ አያበቃም፤ በስማቸው አምኖ
የሚማጸነውንና የታመነውን ነፍሱን በማዳን ሌላ የተጋድሏቸውን ዋጋ ይከፍላቸዋል። ቅዱሳን የራሳቸው
ነፍስ በመዳኗ ብቻ ሳይሆን የሌሎችም ነፍስ መዳን አብዝተው የሚሹ ናቸውና።
ጻድቁ አባታችን አቡነ ዜና ማርቆስ በተለያየ ጊዜ ከጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቃልኪዳን
ተቀብለዋል፤
• በጣና ሐይቅ ደሴት ላይ ባለችው የዙር አባ ቤተ ክርስቲያን ሠራዒ ካህን ሆነው ሥጋ ወደሙ
5
አራቱ ኃያላን - በግብጻውያን የሊቃነ ጳጳሳት ዝርዝር መሠረት በዚህ ወቅት የነበሩት አቡነ ዮሐንስ 12ኛ /1480-83
እ.ኤ.አ/ ወይም ደግሞ አቡነ ዮሐንስ 13ኛ /1484-1524 እ.ኤ.አ/ ናቸው።
11
ምዕራፍ 3. ገድላቸው
• ለእመቤታችን እና ለጻድቁ አባት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ኢትዮጵያን ዐሥራት አድርጎ
እንደሰጣቸው፤ ለአቡነ ዜና ማርቆስ ደግሞ የሞረት እና የመርሐ ቤቴ ሃገርና ሕዝብ በሙሉ
ዐሥራት አድርጎ ጌታችን ሰጥቷቸዋል።
• የክብር ባለቤት ጌታችን ደግሞም ’ለማንም ያልሰጠሁትን ቃልኪዳን ልስጥህ’ በማለት በጻድቁ
ቃልኪዳን ያመነ፣ እርሳቸውን የሚወድ ኀጥያተኛ ሰው ሁሉ ከ80-160 ዘመን ለንስሐ
እንደሚሰጠው እንጂ በሞት እንዳይወሰድ ቃል ገብቶላቸዋል።
12
ምዕራፍ 3. ገድላቸው
ሥራው መስሎት ስሙን እንዲያስጠራ ሁሉ ገድላት፣ ድርሳናትም የመጽሐፍ ቅዱስን ሐሳብ ይተነትናሉ፣
ያብራራሉ፣ እንዲሁም በቃል ያለው በተግባር ሲፈጸም ያሳያሉ።
ይሁንና ይህ ገድለ ዜና ማርቆስና ሌሎችም ገድላትና ድርሳናት እውነትን በተቀሙና አእምሮአቸው
በጠፋባቸው ሰዎች እየተነቀፉ እና እየተወገዙ ይገኛሉ። በመሆኑም በዚህ ክፍል የአቡነ ዜና ማርቆስ
ገድል ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር ያለውን ዝምድና በጥቂቱ ለመዳሰስ እንሞክራለን።
• የሞረቱን የድል አለሰገድ ሠራዊት ምድር አፏን ከፍታ መዋጧ − ዳታንና አቤሮንን መሬት አፏን
ከፍታ መዋጧ። ዳታን፣ አቤሮን እና ቆሬ በሙሴ ላይ ባመጹ ጊዜ ከበታቻቸው ያለው መሬት
ተሰንጥቆ እነርሱን ከነቤተሰቦቻቸው እና ዕቃዎቻቸው በሙሉ ውጣቸዋለች። (ዘኁ 16፥32)
• በአዳል ከዐርብ እስከ ሰኞ ጨለማ መሆኑ − በግብጽ በፈርዖን መደንደን የተነሣ ጨለማ እንደሆነ።
የግብጽ ፈርዖን ልቡ ደንድኖ እስራኤልን ከባርነት አልለቅም ባለ ጊዜ 9ኛው መቅሰፍት ድቅድቅ
ጨለማ ለ3 ቀናት በግብጽ ምድር መሆን ነበር። ሙሴም እጆቹን ባነሣ ጊዜ በግብጽ ጨለማ ሲሆን
ማንም ለ3 ቀናት ያህል ወንድሙን አላየም፣ ማንምም ከቦታው አልተንቀሳቀሰም። (ዘፀ 10)
13
ምዕራፍ 3. ገድላቸው
• ፀሐይን ማቆማቸው − በሙሴ እግር የተተካ ኢያሱ ወልደ ነዌ ፀሐይን በገባዖን ሰማይ እንዳቆመ።
አሞሬዎናውያንን ከእስራኤል ጋር ተዋግተው ድል ቢነሡ ሲሸሹ በበረዶ ተመትተው ካለቁ በኋላ
እስራኤል ጠላቶቻቸውን ፈጽመው ሳያጠፉ እንዳይመሽ ኢያሱ ለእግዚአብሔር ጸሎት አደረገ፤
በዚያም ፀሐይና ጨረቃ በየቦታቸው ቆሙ። እግዚአብሔርም የሰውን ቃል የሰማበት እንደዚያ
ያለ ቀን ከዚያም በፊት ከዚያም በኋላ አልነበረም እስኪባል ድንቅ ተአምራት ተደረገ። (ኢያ
10፥9-14)
• ሙታንን ከሞት ማስነሣታቸው − ነቢዩ ኤልያስ የሰራፕታዋን ሴትዮ ልጅ እንዳስነሣ (1ነገ 17፥17-
24) የኤልያስ ደቀ መዝሙር ነቢዩ ኤልሳዕም እንዲሁ የሱናማዊቷን ልጅ ከሞት እንዳስነሣ (2ነገ
4፥32-37)። በሐዲስ ኪዳንም እንዲሁ ቅዱስ ጴጥሮስ ጣቢታን፣ ቅዱስ ጳውሎስ አወጣኪስን
ከሞት ማስነሣታቸው (ሐዋ 9፥3፤ ሐዋ 20፥7-12)
14
ምዕራፍ 4
• በመላው ኢትዮጵያ በመዘዋወር ወንጌልን ሰብከዋል፣ በኪደተ እግራቸው ሃገሪቷን በሙሉ ባርከዋል፤
በዚህም በቤተ ክርስቲያን አባቶች ሐዲስ ሐዋርያ ተብለዋል።
15
ምዕራፍ 4. ለኢትዮጵያ ያበረከቷቸው አስተዋጽዖዎች
• በአፄ ሰይፈ አርዕዝ ዘመነ መንግሥት ባደረጉት የቀዳሚት ሰንበት ክርክር፣ በሸዋ እንዲሁም
በኢትዮጵያ በአዋጅ የቀዳሚት ሰንበት መታሰቢያ እንዲከበር አስደርገዋል።
• በደቡቡ የሃገራችን ክፍል፣ በተለይም በምድረ ጉራጌ ክርስትናን አስፋፍተዋል፤ በዚሁ በደቡቡ
ክፍልም ታላቁን የምሑር ኢየሱስ ገዳም ገድመዋል።
16
ምዕራፍ 4. ለኢትዮጵያ ያበረከቷቸው አስተዋጽዖዎች
17
ምዕራፍ 4. ለኢትዮጵያ ያበረከቷቸው አስተዋጽዖዎች
እስከ አክሱም ጽዮን በሄዱበት ቦታ ሁሉ ክፉ ዘንዶን አጥፍቶ፣ ሙታንን አስነሥቶ፣ በውኃ በጥብጦ
የጠጣ ድውይ መኮንን አውሬ አስወጥቶለት፣ የአፈሩ ዝና በመላው ትግራይ እስኪናኝ ድረስ ተአምራትን
አደረገ። በደብረ ዳሞ ገዳምንም በብርሃን ገመድ መነኰሳቱን አውጥቶ ብርሃኑን በሌሊት ቢሰጥ የገዳሙ
መነኰሳት ገዳማችን በእሳት ተቃጠለ እስኪሉ ድረስ ድንቅ የብርሃን አምድን ይተክል ነበር።
በግብጽም በደረሱ ጊዜ በጊዜው ሊቀ ጳጳስ ከነበሩት አባ ማቴዎስ ዘንድ ሊገቡ ባሉ ጊዜ ረድኦቻቸው
በበትር እንደሚመታቸው እያስፈራራ አባረራቸው፤ እነርሱም በዚያው በረሃ ወርደው ጸሎት ሲይዙ
የጻድቁ አባታችን የዜና ማርቆስ ክብር ይገለጥ ዘንድ በሌሊት የያዙት አፈር ከምድር ወደ ሰማይ የብርሃን
አምድ ተከለ። ይህንንም በሌሊት ሊቀ ጳጳሱ እንዲሁም የግብጹ የእስላም ንጉሥ ቢያዩ መነኰሳቱ ካሉበት
ወርደው ነገሩን ሰምተው አደነቁ። ሊቀ ጳጳሱም በፍቅር በአንድነት ወደ ኢየሩሳሌም አብረዋቸው ሄዱ።
በኢየሩሳሌምም የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን መቃብር ተሳልመው፣ ዐቢይ ጾምን በአንድነት ጾመው
ሲፈጽሙ በሃገሩ የተዘጋጀ የፋሲካ ማዕድ ለሊቀ ጳጳሱ ሰቅርብ የአቡነ ዜና ማርቆስ ልጆች የሆኑ
ኢትዮጵያውያን መነኰሳትን ግን በውጭ ተዉአቸው። እነርሱ ግን ሳይከፋቸው ሊቀ ጳጳሱ መብሉን
ፈጽሞ እስኪመለስ ድረስ ይጠብቁ ነበር። በዚያ በዕለተ ትንሣኤ ጾማቸውን ያገኛቸው ዮሐንስ የተባለ
የሮማውያን መምህር አዝኖላቸው እንዲመገቡ ወደቤቱ ወስዶ ፍሪዳ አርዶ ቢያቀርብላቸውም በሃይማኖት
ጠብ አለንና አንበላም አሉት።
በዚህም የተናደደው ዮሐንስ ሃገራቸው ሩቅ መሆኑን አውቆ ማንም አይጠይቀኝም በማለት አስደብድቦ
ጨለማ ቤት ወስጥ እንዲሞቱ ዘጋባቸው። በዚያም ጸሎት ሲያደርጉ ያ ይዘውት የመጡት አፈር እንደልማዱ
በሌሊት የብርሃን አምዱን ተክሎ በመላዋ ከተማዋ ታየ። የግብጹ ሊቀ ጳጳስም ከእርሳቸው ጋር የመጡ
ኢትዮጵያውያን እንደሆኑ ተናግረው ተንኰለኛው ዮሐንስን አንዲያዝ፣ መነኰሳቱ እንዲፈቱ አደረጉ።
የከተማዋ ገዢዎችም ያደረሰባቸውን አይተው ሞት ቢፈርዱበትም የጻድቁ አባታችን መነኰሳት ግን እርሱ
በሞት ፈንታ የሃይማኖት ክርክር ጉባኤ እንዲዘጋጅና ዮሐንስ ቢረታ የእነርሱን እምነት እንዲቀበል ጠይቀው
ሁሉም ተስማማ።
በዚህም ከመነኰሳቱ የደብረ ብሥራት መምህር የነበረ አባ በኃይለ ማርያም ቋንቋ ሳያግደው ባሻቸው ቋንቋ
መከራከር እንደሚችል ተናግሮ የአስቄጥስና የቊስቋም ገዳማት አበምኔቶች፣ የአትሪብ ሃገር፣ የመርያ፣
የግብጽ፣ የአርመን ሊቀ ጳጳሳት፣ የቆጵሮስ፣ የሥሩግ፣ የሶርያ ኤጲስ ቆጶሳት፣ የአይሁድና የዓረብ አለቆች
ሁሉ በተገኙበት ጉባኤው ተደረገ።
አስቀድሞም ዮሐንስ እንደ ዘመናችን መናፍቃን እመቤታችን ማርያምን አምላክን ወለደች የሚል ጥቅስ
እንደሌለ ነግሮ አባ በኃይለ ማርያምን የአምላክ እናት ለምን እንደሚላት ጠየቀው። አባ በኃይለ ማርያምም
ከኦሪት፣ ከወንጌል፣ ከመጻሕፍተ አበው፣ ከጉባኤያት ቀኖናዎች፣ ከቅዳሴአት እየጠቀሰ በዕብራይስጥና
በዓረብኛ ሰፊ መልስ ሰጠው። ሙሉ መልሱ በገድለ አቡነ ዜና ማርቆስ እስከ 30 ገጾች ድረስ ወስዶ
ሰፍሯል።
በዚህ ትምህርቱም የተንባላት፣ የአይሁድም ሆነ የዓረብ አለቆች በሙሉ በአቡነ ዜና ማርቆስ አምላክ
18
ምዕራፍ 4. ለኢትዮጵያ ያበረከቷቸው አስተዋጽዖዎች
እናምናለን አሉ። የአይሁድ እና የተንባላት አለቆችም ያዩትን ተአምራት ሁሉ አጽፈው 150 በወርቅ
የተንቆጠቆጡ የሐር ልብሶችን ጨምረው ወደ ኢትዮጵያ በ60 ፈጣን መልእክተኞች ላኳቸው። በደብረ
ብሥራት የነበረው አባ ቃለ ዐዋዲም በገድሉ መጽሐፍ ጨምሮታል። መነኰሳቱም ከሁለት ዓመታት በኋላ
በሰላም ወደ ደብረ ብሥራት ተመልሰው መልእክተኞቹ አስቀድመው ያመጡት ጽሑፍ ላይ እንዳለው
የሆነውን ሁሉ ለደብሩ መነኰሳት ነገሯቸው።
19
ምዕራፍ 5
የገድላቸው መጽሐፍ
እግዚአብሔር ከጥንት ጀምሮ በነቢያት፣ በኋላ በሐዋርያት ቀጥሎም በሐዋርያት እግር በተተኩ ቅዱሳን
አባቶች አማካኝነት ”ኑ እንዋቀስ፣ ንስሐ ግቡ” እያለ እኛን ልጆቹን በቀጥታ ሲጠራን ቆይቷል። ገድላትም
እግዚአብሔር ልጆቹን በተዘዋዋሪ ከሚጠራባቸው መንገዶች አንዱ ነው፤ ገድሉን ሰምተው፣ አንብበው
ወደ ንስሐ እና ወደ እግዚአብሔር የሚቀርቡ ብዙዎች ናቸውና።
ከቤተ ክርስቲያናችን አብዛኛዎቹ ገድላት አጻጻፍ ወጣ ያለ የአጻጻፍ መንገድ የሚከተለው ገድለ አቡነ
ዜና ማርቆስ በብዙ ጸሐፍት እንደተጻፈ ይነገራል። በገድሉ ላይ እንደምናገኘው በመጀመርያ የአቡነ ዜና
ማርቆስ ደቀመዛሙርት አባ አካለ ክርስቶስ፣ አባ ዮሴፍና አባ ገብረመስቀል ያዩትንና ከአቡኑ እኅት
ማርያም ክብራ የነገረቻቸውን አካትተው ጽፈውታል። በኋላም በደብረ ብሥራት በተደረገለት ተአምራት
ዓይኑ የበራው ጸሐፌ መንክራት ዮሐንስ እና በኋላም በአባ ገብረ መርዓዊ አማካኝነት ተጽፏል።
የአቡነ ዜና ማርቆስ የአጽማቸው ፍልሰት በአፄ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመነ መንግሥት በተደረገ ጊዜ የሆነውን
በገድላቸው ላይ የጻፉት ደግሞ አባ ገብረ መስቀል፣ አባ እንድርያስ እና አባ ገብረ ሚካኤል ሲሆኑ
በግራኝ አሕመድ ወረራ ጊዜ የደብረ ብሥራት አበምኔት የነበረው አባ ቃለ ዐዋዲ ተአምራቱን በማጠቃለል
ጽፈውታል።
ሌላው ገድሉን እጅግ ለየት የሚያደርገው ነገር ተአምራቱን የጻፉት አባ ቃለ ዐዋዲ ተአምራቱን በሁለት
ከፍለው መጻፋቸው ነው። ቀዳማይ ክፍል የሚለው አቡነ ዜና ማርቆስ በሕይወት እያሉ የተደረጉ
ተአምራትን ሲይዝ ካልዕ ክፍል የሚለው ደግሞ ከዕረፍታቸው ጀምሮ የተደረጉ ተአምራትን መዝግቦ
ይገኛል።
ሌላው አስደናቂ ነገር ገድሉ ለቤተ ክርስቲያን እንዲሁም ለሃገራችን ለኢትዮጵያ ታሪክ ጥናት የሚጠቅሙ
ልዩ ልዩ መረጃዎችን ይዞ መገኘቱ፤ በጊዜው የነበረውን ጠቅላላ ታሪክ መዝግቦ መገኘቱና ለተለያዩ
ጸሐፍት የታሪክ ምንጭ ሆኖ ማገልገሉ ነው።
20
ምዕራፍ 5. የገድላቸው መጽሐፍ
• በጊዜው ከግብጽ ተሹመው የመጡ የግብጽ ሊቃነ ጳጳሳትን ዘርዝሮ ይዟል። በተለይም የአባ
ጌርሎስ፣ አባ ዮሐንስና አባ ማቴዎስ ታሪክን በዝርዝር ያትታል።
• ከአቡነ ዜና ማርቆስ ውጭ የሌሎች አበውንም ታሪክ ይናገራል። ከእነዚህም መካከል የአቡነ ተክለ
ሃይማኖት፣ አባ ሳሙኤል ዘደብረ ወገግ፣ አባ ሕፃን ሞዓ፣ አባ አኖሬዎስ ታላቁ እና አባ ቀውስጦስ
ዘመሐግልን ታሪክ መዝግቦ ይገኛል።
• የሸዋ ገዳማውያን ጎጃም፣ ትግራይ፣ ኤርትራ፣ ግብጽና አንዳንድ ጊዜም ኢየሩሳሌም ያሉ አብያተ
ክርስቲያናትን ለመሳለም የሚያደርጉትን ጉዞ መዝግቦ እናገኛለን።
21
ምዕራፍ 6
ገዳሞቻቸው
22
ምዕራፍ 6. ገዳሞቻቸው
• 7 የገድላቸውን ቅጂዎችና 1000 የሚደርሱ መጻሕፍትን በምሑር ኢየሱስ ገዳም፣ በጋይ ዋሻ፣
በወተጌ ባለች ዋሻ፣ በእንቡ ልቡልና ዞረት የሚገኝ ዋሻ፣ በሸር ካቢ ዋሻ ደብቀው
በገዳሙ የነበሩ 1600 በላይ መጻሕፍት፣ 1200 ተማሪዎች እና 547 መነኰሳት መኖራቸው በጊዜው
ገዳሙ ምን ያህል የሊቃውንት መፍለቂያ እና የገዳማውያን መናኽርያ እንደነበር ይጠቁማል። የገዳሙ
13
ሊቅ አባ በኃይለ ማርያም በሙሉ ልብ በኢየሩሳሌም ስለ ሃይማኖቱ መከራከሩ ገዳሙ የነበረበትን
የመንፈሳዊ ትምህርት ደረጃ ያሳያል። ታቦታቱም በብዛት መገኘታቸው በአካባቢው የነበሩ አብያተ
ክርስቲያናት ታቦታቸውን ከዚሁ ገዳም የሚያገኙ በመሆኑ ነው።
ይህ ታላቅ ገዳም ግን ከ2006 ዓ.ም. ወዲህ የአካባቢው ተወላጆች የመሬት ባለቤትነት ጥያቄ ከገዳሙ
መነኮሳት ጋር ባደረሳቸው ግጭት የገዳሙ ይዞታ የነበሩ መሬቶች እየተወረሱ ይገኛሉ። እንዲያውም በኅዳር
ወር፣ 2006 ዓ.ም. እስከ 80 የሚደርሱ መነኮሳት፣ አበ ምኔቱን ጨምሮ ተበትነው በድነባ ቅድስት
በኣታ ለማርያም ገዳም ለመጠለል ተገድደው ነበር። እስከ 16ኛው መ/ክ/ዘ የሊቃውንት መፍለቂያና
13
ማጣቀሻ
23
ምዕራፍ 6. ገዳሞቻቸው
የመናንያን መናኸርያ የነበረው ይህ ታላቅ ገዳም ዛሬ እንዲህ ያለ አሳሳቢ አደጋ የተጋረጠበት በመሆኑ
የመላውን የቤተ ክርስቲያናችን ትኩረት ይሻል።
24
ሥዕለ አድኅኖአቸው
በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያናችን መሠረት የጻድቁ አባታችን አቡነ ዜና ማርቆስ ሥዕለ አድኅኖ የምሑር ሃገረ
ገዢ በጦር ሲወጋቸውና ከተወጉበት ብርሃን ሲወጣ ተደርጎ ይሳላል። ሥዕሉም በደብረ ብሥራት ገዳም
ይገኛል።
25
ማጣቀሻዎች
[1] ገድለ አቡነ ዜና ማርቆስ፤ ደብረ ብሥራት አቡነ ዜና ማርቆስ አንድነት ገዳም፣ ሳቤላ ማተሚያ፣
2005 ዓ.ም.
[2] ዲ/ን ዳንኤል ክብረት፤ አራቱ ኃያላን፤ ማኅበረ ቅዱሳን፣ ሜጋ ማተሚያ፣ 2006 ዓ.ም.
[4] ዲ/ን ዳንኤል ክብረት፤ ገድለ ዜና ማርቆስ የያዛቸው መረጃዎችና ሁነቶች፤ የኢትዮጵያ ፊሎሎጂ
ማኅበር ባዘጋጀው 3ኛ ዓመታዊ ዐውደ ጥናት ላይ የቀረበ፣ 2001 ዓ.ም.
[5] አበበ ጋሻዬ ፈንታ፤ ገድለ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በመጽሐፍ ቅዱስ እይታ፤ ማኅበረ ቅዱሳን፣ 2009
ዓ.ም.
[6] ሐመር ዘኦርቶዶስ ተዋሕዶ፣ 5ኛ ዓመት ቁጥር 5፤ ማኅበረ ቅዱሳን፣ 1990 ዓ.ም.
[7] መ/ር ተስፋ ሚካኤል ታከለ፤ ድርሳነ ኤልያስ ነቢይ፤ 2005 ዓ.ም.
[8] ገድለ አቡነ ዜና ማርቆስ ንባብና ትርጓሜ በመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ፣
በቀበና ምስራቀ ፀሐይ መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን፤
https://www.youtube.com/watch?v=_ExXx8qZYVk፤ [ተንቀሳቃሽ ምስል] ነሐሴ፣ 2005
ዓ.ም. የተሰቀለ
26