Professional Documents
Culture Documents
መግቢያ
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) 1ኛ መደበኛ ጉባዔውን ሰኔ 25 እና 26 ቀን 2014
ዓ.ም ያደርጋል። በዚህ ጉባዔ ይከናወናሉ ተብለው ከሚጠበቁ ዐበይት ክንውኖች መካከል
አንዱ ኢዜማን በቀጣይነት የሚመሩ ሰዎች የሚመረጡበት መርሐግብር ነው። ይህ ሰነድ አቶ
አንዱዓለም አራጌ ለኢዜማ መሪ ቦታ በጉባዔው ለመመረጥ የሚያቀርቡት እና ከተመረጡ
የሚተገብሯቸውን አንኳር ተግባሮች የሚዘረዝር ሰነድ ነው። አቶ አንዱዓለም አራጌ በመሪነት
ከተመረጡ አቶ ሐብታሙ ኪታባን ምክትል መሪ ያደርጋሉ።
ይህ ሰነድ ኢትዮጵያ በ2010 ዓ.ም በገዢው ፓርቲ ውስጥ የተደረገውን የሥልጣን ሽግግር
ተከትሎ እስከ አሁን ያለፈችበትን እና የደረሰችበትን ሁኔታ፣ በዚህ ሂደት ውስጥ ኢዜማ
ለመጫወት የሞከረውን ሚና እና ያስገኘውን ውጤት በመቃኘት በቀጣዩ ሦስት ዓመታት
የኢዜማ ዋነኛ አቅጣጫ ሊሆን የሚገባውን መንገድ የሚያመላክት እና ይህንን ለማስፈጸም
ለምን የመሪ ለውጥ እንደሚያስፈልግ ያስረዳል።
በ2006 ዓ.ም አጋማሽ በኦሮሚያ የተለያዩ ከተሞች ተጀምሮ ሲቀጣጠል የከረመው ሕዝባዊ
ተቃውሞ ሌሎች የሀገራችን አካባቢዎችን በማዳረስ በገዢው ድርጅት - ኢሕአዴግ ውስጥ
ባሉ ሰዎች መካከልም ቢሆን እንኳን ሰላማዊ የሥልጣን ሽግግር እንዲደረግ አስገዳጅ ሁኔታን
ፈጥሮ ነበር። በሕዝብ ግፊት አስገዳጅነት ገዢው ድርጅት በውስጡ ያደረገው የሥልጣን
ሽግግርን ተከትሎ የፌዴራል መንግሥት ሥልጣንን የተቆጣጠሩት ሰዎች፣ ከሥልጣን ሽግግሩ
በፊት ሕወሃት መራሹ ኢሕአዴግ ገፍቶት የቆየውን የኢትዮጵያዊነት ትርክት ማቀንቀን የጀመሩ
ሲሆን፣ ኢሕአዴግ ሥልጣን ላይ በቆየበት ወቅት ለተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ይቅርታ
ጠይቀው ሕዝብን እውነተኛ የሥልጣን ባለቤት ለማድረግ ቃል ገብተው ነበር።
1
የፌዴራል መንግሥት ሥልጣንን የተቆጣጠሩት ሰዎች የገዢው ድርጅት አካል የነበሩ ሰዎች
ቢሆኑም እንኳ፣ ሥልጣን ከያዙ በኋላ የገቡትን ቃል መሰረት በማድረግ ከፍተኛ ሕዝባዊ
ቅቡልነት እና ድጋፍ አግኝተው ነበር። በጊዜ ሂደት ግን በሀገራችን ሲተገበር የቆየው የዘውግ
ማንነትን መሠረት ያደረገ ፖለቲካ የፈጠራቸው ውስብስብ የፖለቲካ እና የደኅንነት ችግሮችን
መፍታት ይቅርና እንዳይባባሱ ማድረግ ሳይችሉ ቀርተዋል። እንዲሁም ሀገራዊ ሁሉን አቀፍ
የአቅም ውስንነትን የተረዳ የአንገብጋቢ የጉዳዮች ልየታ እና የመፍትሄ ዝግጅት ትክክለኛ
ቅደም ተከተል ባለመኖሩ ብሎም ሀገርን ከማሻገር ይልቅ የፖለቲካ ሥልጣን ማስጠበቅን
ቅድሚያ በመስጠታቸው የፈጠሩት የእርስ በርስ ሽኩቻ በሕዝብ ያገኙት ቅቡልነት እና ድጋፍ
በከፍተኛ ሁኔታ ተሸርሽሯል። ድጋፋቸው መሸርሸሩ ብቻ ሳይሆን፣ በሕዝብ ትግል የተገኘው
ሀገረ-መንግሥቱን ዴሞክራሲያዊ የማድረግ ተስፋ ጭላንጭል ጠፍቶ እንደውም በየአካባቢው
በሰው ሠራሽ እና ተፈጥሯዊ አደጋዎች የሚሞቱ ዜጎቻችንን መታደግ እና ሀገራችንን ከመበታተን
ማትረፍ ትልቁ የቤት ሥራ ሆኗል።
3
1.2.5. ሀገራዊ ምክክር
የሀገራችንን ችግሮች ከመደበኛ የመንግሥት ተቋማት እና ሕግጋት ከፍ ባለ መልኩ ለመመርመር
እና የረጅም ጊዜ የሀገራችንን እጣ ፈንታ በጋራ ለመወሰን የሚያስችል መድረክ እንዲመቻች
በተደጋጋሚ የተለያዩ ኃይሎች ሲጠይቁ መቆየታቸው ይታወቃል። ቀደም ብሎ የተለያዩ ሀገር
በቀል መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ከኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት እና
ከሰላም ሚኒስቴር ጋር በመሆን የምክክር መድረክ ለማዘጋጀት ሲሠሩ የቆዩ ሲሆን፣ የ2013
ምርጫን ተከትሎ ደግሞ መንግሥት የምክክር መድረክ የሚያዘጋጅ ኮሚሽን ለማደራጀት
ወስኖ ወደሥራ ተገብቷል።
መንግሥት ኮሚሽኑን ለማቋቋም ከወሰነ በኋላ ኮሚሽኑን ማቋቋሚያ አዋጅ ዝግጅት ጀምሮ
ኮሚሽነሮች እስከመሰየም ድረስ የሄደበት መንገድ፤ በዚህ ትልቅ ሀገራዊ ፋይዳ ያለው
ፕሮጀክት ተዓማኒነት ላይ ገና ከጅምሩ ጠባሳ ያኖረ ነበር። እስከ አሁን በሌሎች ሀገራዊ
ፕሮጀክቶች (ለምሳሌ ምርጫ 2013) ላይ መንግሥትን የተቆጣጠሩ ሰዎች ያሳዩት ከሀገር
ጥቅም በላይ የሥልጣን ፍቅርን ማስቀደም እና ሁሉንም ለመቆጣጠር የመፈለግ አባዜ ጋር
ተደምሮ፤ ሀገራዊ ምክክሩንም እነሱ የሚፈልጉትን ውጤት ብቻ እንዲያመጣ ለማድረግ ዓላማ
አድርገው እንደሚንቀሳቀሱ መገመት ከባድ አይደለም።
ሀገራዊ ምክክሩን የሚያስተባብሩ 11 ኮሚሽነሮች የተሰየሙ ሲሆን በኅዳር 2015 ዓ.ም ምክክሩ
እንደሚጀምር ተነግሯል።
1.3. ማጠቃለያ
በአጠቃላይ አሁን ሀገራችን ያለችበት ወቅታዊ ሁኔታ በሁሉም መስክ ሲታይ እጅግ በጣም
አሳሳቢ ነው። የበለጠ አሳሳቢ የሆነው ነገር ደግሞ፣ በሥልጣን ላይ ያለው መንግሥት ከገባንበት
ቀውስ የምንወጣበት ሁሉን አቀፍ ራዕይ አዘጋጅቶ በዚያ ዙሪያ ሁላችንንም ማሰባሰብ ይቅርና
ቀውሱን እንኳን እንዳይባባስ ባለበት ማቆም አለመቻሉ ነው። የሌሎች የፖለቲካ ኃይሎች
ቁመናም ቢሆን የሀገራችን ችግሮች ውስብስብነት እና ጥልቀትን የሚመጥን አይደለም።
በዚህም የተነሳ እንደሀገር አጠቃላይ ማኅበረሰባዊ ግራ መጋባት ውስጥ ነው ያለነው ማለት
ማጋነን አይሆንም።
4
2. የፓርቲያችን ወቅታዊ ሁኔታ
2.1 ዳራ
ኢዜማ በ2010 ዓ.ም በሕዝብ ግፊት የተፈጠረውን ተስፋ
ተከትሎ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር በተለያየ መንገድ
ከሕወሃት መራሹ ኢሕአዴግ ጋር ትግል ሲያደርጉ የነበሩ
ፓርቲዎች እና የፖለቲካ ድርጅቶች፤ ተበታትኖ ከሚደረግ
ፉክክር ይልቅ በመሠረታዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግባባት ላይ
እስከተደረሰ ድረስ በሰፊ ጥላ ውስጥ ተሰባስቦ አንድ ላይ
መታገል የበለጠ አዋጭ እንደሚሆን ስምምነት ላይ ተደርሶ
ድርጅቶቹ እና ፓርቲዎቹ ራሳቸውን አክስመው ግንቦት 2011
ዓ.ም የተመሠረተ ፓርቲ ነው። የኢዜማ ዋነኛ ምሰሶዎች
ዜግነትን መሠረት ያደረገ ፖለቲካ እና ማኅበራዊ ፍትህ ሲሆኑ
ፓርቲው የሚያራምዳቸው አቋሞች እና ፖሊሲዎች እነዚህን
ሁለት የፓርቲው ምሰሶዎች በሀገራችን ተተግብረው ማየትን
ዓላማ ያደረጉ ናቸው።
በሁለቱ አንኳር አስተሳሰቦች መካከል ያለው ዋነኛ ልዩነት የፌዴራል መንግሥቱን ሥልጣን
የያዙ ሰዎች ላይ ያለ ዕምነት ነው። እስካሁን ይዘን በመጣነው አካሄድ መቀጠል አለብን
የሚለው አስተሳሰብ፤ የፌዴራል መንግሥት ሥልጣንን የተቆጣጠሩት ሰዎች አሁንም ቢሆን
የኢትዮጵያን አንድነት ለማስጠበቅ እና ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን ለማስፈን ፍላጎት እንዳላቸው
የሚያምኑ ሰዎች የሚያራምዱት አስተሳሰብ ነው። በእርግጠኝነት መናገር ባይቻልም፣ ይህን
አስተሳሰብ የሚያራምዱ ሰዎች በኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ ኢዜማ የቆመላቸውን ዓላማዎችን
ለማስፈጸም የሚያስችል አቅም በተቃዋሚ ፓርቲ ውስጥ መገንባት ስለማይቻል/ከባድ
ስለሆነ፤ ዓላማዎቹን ለማስፈፀም የመንግሥት አቅም መጠቀም የሚያስችል ጤናማ ግንኙነት
የመንግሥትን ሥልጣን ከተቆጣጠሩ ሰዎች ጋር መፍጠር የተሻለ አማራጭ ነው ከሚል ዕምነት
የደረሱበት ድምዳሜ ሊሆን ይችላል።
7
በሌላ በኩል የእስከ አሁኑ የኢዜማ መንገድ፥
1. በሕዝብ ግፊት የተገኘውን በአንፃራዊነት ሰላማዊ ሊባል የሚችል የለውጥ ተስፋን
ወደ ተግባር ለመለወጥ ሊገጥሙ የሚችሉ ተግዳሮቶችን እና እነዚህን ተግዳሮቶች
ለመቋቋም መወሰድ ያለባቸውን እርምጃዎች በሚመለከት ምክረ ሀሳብ ቢቀርብም፣
በመንግሥት በኩል ቢያንስ ከምር ተወስደው ስለመመዘናቸው ምንም ማስረጃ
ማግኘት አልተቻለም፤
2. በሕዝብ ግፊት የተገኘውን በአንፃራዊነት ሰላማዊ ሊባል የሚችል የለውጥ ተስፋ
በአግባቡ መመራት ሳይችል ቀርቶ በሕወሃት ጠብ አጫሪነት ቢሆንም በሀገራችን
ከዚህ ቀደም እንደተለመደው የፖለቲካ አስተሳሰብ ልዩነትን መሰረት ያደረገ
ደም አፋሳሽ ጦርነትን ለማስቀረት ተፅዕኖ ማድረግ አለመቻሉ፤ ጦርነቱ
ከተጀመረም በኋላ የጦርነቱን ጉዳቶች ለመቀነስ የሚያስችሉ አስቀድመው
ሊወሰዱ የሚገባቸውን ጥንቃቄዎች በተመለከተ እና በጦርነቱ ምክንያት
የባሰ ጦስ እንዳይመጣ ኢዜማ የሚያቀርባቸው ምክረ ሐሳቦች
ከመናገር ያለፉ መሆን ያልቻሉ ነበሩ፤
3. በየጊዜው ሰላማዊ ዜጎች ላይ የሚደርሱ አሰቃቂ ጥቃቶችን ለማስቆም ኢዜማ
በተደጋጋሚ ማሳሰቢያ እንዲሁም መወሰድ ያለባቸው እርምጃዎችን ዘርዝሮ ጥቆማ
ቢሰጥም፣ በመንግሥት በኩል የማያዳግም እርምጃ ወስዶ ማስቆምም ሆነ
እንዳይከሰቱ አስቀድሞ መከላከል አልተቻለም፤
4. በምርጫ 2013 እንዳየነው ገዢው ፓርቲ ከዚህ ቀደም ሕወሃት/ኢሕአዴግ
ያደርገው እንደነበረው የካድሬ መንጋ በመራጩ ሕዝብ ውስጥ በማሰማራትና
በማስፈራራት፣ ተፎካካሪ ፓርቲዎችን እንቅስቃሴ በመግታት ወደ መራጩ ሕዝብ
እንዳይደርሱ በማድረግ፣ በተፎካካሪ እጩዎች፣ አባላት፣ ደጋፊዎችና ታዛቢዎች ላይ
ከፍተኛ ተጽእኖ በማድረግ፣ የሀገር እና የመንግሥት ጉዳዮችን ለምርጫ ቅስቀሳ
በመጠቀም፣ በድምጽ መስጫው ቀን ሂደቱ ላይ ተጽእኖ በማሳደር ለነፃ እና ፍትሃዊ
ምርጫ ዝግጁ እንዳልሆነ በግልፅ ሲያረጋግጥ እና ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት
እንቅፋት ሲሆን ማስቆማ አልተቻለም፤
5. ከ2010 ዓ.ም በኋላ ተቋማትን ጠንካራ እና ገለልተኛ አድርጎ ለማቋቋም የወጡ
አዋጆችን ጨምሮ በሕገ መንግሥቱ በግልጽ የተቀመጡ መብቶችን በመጣስ
የሚወሰዱ ውሳኔዎችን እና እርምጃዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየበረከቱ እንጂ እየቀነሱ
እንዲሄዱ ማድረግ አልተቻለም፤ እንዲሁም
6. ሀገራዊ ችግሮችን በአግባቡ መዝኖ የመፍትሄ ቅደም ተከተል ማዘጋጀት እና
ለአንገብጋቢ ችግሮች ቅድሚያ ከመስጠት ይልቅ በግብር ይውጣ የሚወሰኑ
ውሳኔዎችን ማስቆም አልተቻለም።
8
በአጠቃላይ በሕዝብ ግፊት የተገኘው የለውጥ ተስፋ የተዳፈነበት እና የአንድ ፓርቲ (አልፎም
የአንድ ግለሰብ) ፈላጭ ቆራጭነት ከዕለት ወደ ዕለት እየጎላ የመጣ ሲሆን፣ ይህንን ለማስቆም
ኢዜማ መወጣት የሚገባውን ሚና በአግባቡ ተወጥቷል ብሎ ማለት አይቻልም። በመሆኑም
አንዴ የያዝነው መንገድ ትክክል ነው መቼም አይለወጥም ከሚል የዕብሪት አስተሳሰብ እና
ደጋግሞ አንድ ዓይነት ነገር በመተግበር የተለየ ውጤት ከመጠበቅ በመውጣት ያለንን አቅም
ሁሉ አሟጠን አዲስ መንገድ በመቀየስ እና በመከተል እየቀጨጨ ያለውን ኢትዮጵያ ውስጥ
እውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የመመሥረት ተስፋ መልሰን ማለምለም የምንችልበት
የውስጥ አቅም እና ሕዝባዊ ቅቡልነት መገንባት ይገባናል የሚል አስተሳሰብ አለ።
9
2.3 ማጠቃለያ
ኢዜማ የኢትዮጵያን አንድነት አስጠብቆ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን ለማስፈን ያግዛል ብሎ
ባለፉት 3 ዓመታት ሲከተለው የቆየው አካሄድ በመርሆዎቹ ላይ በግልፅ የተቀመጡትን
የኢትዮጵያን እና የሕዝብ ደኅንነትን እንዲሁም ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን ለማስፈን ተጨባጭ
ውጤት ማስገኘት አልቻለም። ውስጣዊ የድርጅት አቅምን በተመለከተም ብዙ ሥራ የተሠራ
ቢሆንም፣ የሀገራችንን ችግር በሚመጥን መልኩ አቅም የገነባ ፓርቲ ነው ብሎ አፍን ሞልቶ
መናገር አይቻልም።
ኢዜማ ምርጫ 2013ን ተከትሎ የሀገራችን ሽግግር ሂደትን እና ምርጫው ያልፈታቸው ጉዳዮች
ላይ ባደረገው ግምገማ፤ በሀገራችን የፖለቲካ ኃይሎች መካከል ስምምነት ሊደረስባቸው
የሚገቡ 7 አንገብጋቢ ጉዳዮችን ለይቶ ነበር።
4. ኢዜማ የሚጠበቅበትን
ሚና ለመጫወት
ሊተገብራቸው የሚገቡ
ለውጦች ምንድናቸው?
4.1 በሕዝብ ዘንድ ያለን ቅቡልነት/
ተሰሚነት ማሳደግ
ይህ በእንዲህ እያለ ኢዜማ ውስጥ እስካሁን ይዘን በመጣነው አካሄድ እንቀጥል የሚል
አስተሳሰብ ያላቸው ሰዎች የኢዜማን የውስጥ አቅም እና ሕዝባዊ ተቀባይነት ከመገንባት ይልቅ
ሥልጣን ላይ ላሉ ሰዎች ድጋፍ ማድረግ እና አብሮ መሥራት የኢዜማን ዓላማዎች ለማሳካት
የበለጠ ዕድል አለው ብለው ያምናሉ። ይህንን ዕምነታቸውን በይፋ ሲያራምዱት ባይሰማም
ትኩረት የሚሰጧቸውን ጉዳዮች በማየት በቀላሉ መረዳት ይቻላል።
ኢዜማ በሕዝብ ዘንድ ያለውን ተቀባይነት እና ተሰሚነት ለማሳደግ በራሱ መቆም የሚችል ፓርቲ
መሆኑን በተግባር ማሳየት እና እስካሁን በዚህ ረገድ የደረሰውን ጉዳት ማረም ይጠበቅበታል።
በመሆኑም ከገዢው ፓርቲ ጋር ያለን ግንኙነት ጥቂት ግለሰቦች ፍላጎት ላይ ከመመስረት
እና በገዢው ፓርቲ ፊት አውራሪነት ከመመራት ወጥቶ በመርህ እና ግልፅ ስምምነት ላይ
የተመሠረተ እንዲሆን መሥራት ይገባል።
14
ፌዴራሊዝም መሬት ላይ እንዲወርድ ቆፍጣና አቋም መያዝ ይገባዋል። እንደምርጫ 2013
የተለሳለሰ አካሄድ ከተከተልን የቆምንላቸውን የዜግነት ፖለቲካ፣ ማኅበራዊ ፍትህ እና
ዴሞክራሲያዊ ፌዴራሊዝም ልናሳካቸው ቀርቶ በሀገራዊ ምክክሩ ያለወኪል በማስቀረት
ጥፋት የምንፈፅም ይሆናል።
ሀገራዊ ምክክሩ ውስጥ ውጤታማ ተሳትፎ ለማድረግ እና ሂደቱ የሀገራችንን ችግር ሊፈታ
የሚችል ፍሬ እንዲያፈራ፣ የሚከተሉት ተግባራት ይከናወናሉ፥
በአሁኑ ሰዓት ኢዜማ ዓለም አቀፍ ድጋፍ አለኝ ብሎ አፉን ሞልቶ የሚናገርበት ደረጃ ላይ
አይገኝም። መዋቅሩ ላይ ለምልክትነት ተንጠልጥለው ከቀሩ ጥቂት አባላቶቻችን በስተቀር
አብዛኛው በተለያየ መንገድ ከመዋቅሩ ውጭ ሆኖአል። ወርሃዊ መዋጮ የሚያዋጡ አባላት
ቁጥር ከዚህ ግባ የሚባል አይደለም፡፡ ከገንዘብ ባለፈ ኢዜማ ሊያገኝ የሚችለውን እና
የሚገባውን ያህል የፓለቲካ ድጋፍ የማግኘት ዕድሉ ወደ ዜሮ ተጠግቷል ቢባል ከእውነት
የራቀ አይደለም። በመሆኑም
የዝርዝር ችግሮች ምንጭ ከሆኑት መካከል የአገር ውስጥ የፖለቲካ አለመረጋጋት፣ የዓለም
ኢኮኖሚ እና ፖለቲካ አሰላለፍ ውጤት፣ የሕዝብ ቁጥርና የምርት መጠናቸውን አለመጣጣም፣
የንግድ እና ኢንቨስትመንት አስተዳደር ሥርዓት ችግር እና የኢንዱስትሪ ዘርፍ ልማት
17
እንደሚጠበቀው አለመሆኑ ግንባር ቀደም ተጠቃሾች ናቸው፡፡ የአገር ውስጥ የፖለቲካ
አለመረጋጋት በዋናነት ትኩረት አድርገን የምንሠራበት ሲሆን፣ ሌሎችም ተገቢ የሆነ ትኩረት
ሰጥተን የምንታገልባቸው ይሆናል፡፡
በመሆኑም እንደ አንድ ራሱን ችሎ እንደ ቆመ ተቃዋሚ ፓርቲ አመራር፣ ብንመረጥ በኢኮኖሚ
ጉዳዮች ላይ የምናደርገው ትግል የሚከተለውን ይመስላል፤
19
ማጠቃለያ
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ የተከተለው መንገድ
የተከበረ (noble) ሊባል የሚችል መንገድ ነበር። ነገር ግን በተጨባጭ ለማሳካት ከሚያስባቸው
ዋነኛ ዓላማዎች እና ዓላማውን ለማሳካት ከተቀመጡ ግቦች አንፃር መንገዱን ከመዘነው፣
በአሳዛኝ ሁኔታ መውደቁ ግልጽ ነው። በመሆኑም ፓርቲው ቆሜለታለሁ የሚለው ዜግነትን
መሠረት ያደረገ ፖለቲካን በኢትዮጵያ የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ የሚገባውን ቦታ እንዲይዝ
እና ፓርቲውም ተጽዕኖ መፍጠር የሚችል እንዲሆን ከላይ የተጠቀሱትን ተግባሮች መተግበር
ብቻ በቂ አይሆንም። እስካሁን የተከተልነው መንገድ የኢዜማ ቅቡልነት ላይ ከፈጠረው ኪሳራ
እንዲያንሰራራ በሚያስችል መልኩ አዲስ አመራር ይዞ መምጣት ይገባዋል።
• በቀጣዩ 3 ዓመታት ኢዜማ እስካሁን ከመጣበት መንገድ የተለየ መንገድ መውሰድ
እንደሚገባው ከልብ የሚያምን መሪ ያስፈልገናል!
• በቀጣዩ 3 ዓመታት ኢዜማ ሁሉን አውቃለሁ የማይል፣ ለአባላት ድምጽ
ጆሮ የሚሰጥ እና በአባላት መካከል ልዩነትን የሚያሰፋ ሳይሆን አሰባሳቢ
ስብዕና ያለው መሪ ያስፈልገናል!
• በሚቀጥሉት 3 ዓመታት ኢዜማን መምራት የሙሉ ጊዜ ሥራው የሆነ
መሪ ያስፈልገናል!
• በሚቀጥሉት 3 ዓመታት ከገዢው ፓርቲ ጋር ብቻ ሳይሆን ከሁሉም ፓርቲዎች ጋር
ተቀራርቦ ለመነጋገር የሚፈልግ እና በሌሎች ፓርቲ መሪዎች ሊታመን የሚችል እና
በተለያዩ ኃይሎች መካከል መቀራረብ መፍጠር የሚችል መሪያ ያስፈልገናል!
በመሆኑም የኢዜማ 1ኛ መደበኛ ጉባዔ የኢዜማን ዓላማ በኢዜማ ቀለም ማሳካት የሚችሉ እና
የሚፈልጉ መሪ/መሪዎች እንዲመርጥ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን!
አንዱዓለም አራጌ
ሐብታሙ ኪታባ
20
21
Email: andualem4leader@gmail.com