Professional Documents
Culture Documents
Guideline For Technology Competition 26
Guideline For Technology Competition 26
ረቂቅ ሰነድ
አዲስ አበባ
ፌ/ቴ/ሙ/ት/ስ/ኤጀንሲ
ማውጫ ገፅ
1. መግቢያ 2
2. የሰነዱ አስፈላጊነት 2
3. ዋና እና ዝርዝር ዓላማዎች 3
3.1. ዋና ዓላማ 3
4. የውድድሩ መርሆዎች 3
5. የሰነዱ ወሰን 3
8. የውድድሩ ተሳታፊዎች 5
9. የተወዳዳሪዎች ምዝገባ 5
15. ማጠቃለያ 8
ፌ/ቴ/ሙ/ት/ስ/ኤጀንሲ
1. መግቢያ
ኢትዮጵያ ላለፉት ዓመታት በተከታታይ ያስመዘገበችውን ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስቀጠል ልማታዊ
አስተሳሰብን በህብረተሰቡ ውስጥ በማስረፅና አምራች ዜጋን በመፍጠር የምርት/ማምረቻ እና
የአገልግሎት/የአሰራር ቴክኖሎጂዎችን አቅርቦት ማሳደግ አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበት መንግስት ልዩ
ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል፡፡
ቀጣይነት ባለው መልኩ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ማምጣት የሚቻለው የልማት ፕሮግራሞች መሪ መስሪያ
ቤቶችን ውጤታማነት እና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ከተረጋገጠ ሲሆን ለዚህም በኢኮኖሚ የበለፀጉ
ሀገራት ሳይንሳዊ ትንታኔ እና ሰፋፊ ጥናትና ምርምርን በማካሄድ ያፈለቁትን ቴክኖሎጂዎች በተለያየ
መንገድ ወደ ሀገራችን አስገብቶ በመቅዳትና በመጠቀም የውጭ ምርትን መተካት (Import substitution)
የሚያስችል ፖሊሲ/ስትራቴጂ ተቀይሶ ትግበራ ላይ መሆኑ ይታወቃል፡፡
ይሁን እንጂ ቴክኖሎጂ የቀዱትን አሰልጣኞች፣ ሰልጣኞችም ይሁኑ የጥ/አ/ አንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች
እያንዳንዱ ክልል በራሱ መስፈርት አወዳድሮ ከሚያበረታታው ውጪ በአገር አቀፍ ደረጃ የተዘጋጀ
የማወዳደሪያ መስፈርት አለመኖሩና በየክልሉ የሚካሄደው የተለያየ በመሆኑ ቴክኖሎጂውን ወጥ በሆነ
መንገድ መለካት አልተቻለም፡፡ ስለሆነም ተቀድቶና ለኢንተርፕራይዝ ተሸጋግረው ሀብት ማፍራት ያስቻሉ
ቴክኖሎጂዎችን በክልል፣ በክላስተር እና በተቋማት ደረጃ በማወዳደር አሸናፊውን ቴክኖሎጂ የቀዳውን
አሰልጣኝ፣ ሰልጣኝ ወይም የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሽ ለማበረታታት ጥቅም ላይ እንዲውል ይህ ሰነድ
ተዘጋጅቷል፡፡
2. የሰነዱ አስፈላጊነት
በተለያየ ወቅት በየደረጃው በተደረገ ድጋፍና ክትትል በዘርፉ ያለውን ችግር ለማየት እንደተሞከረው ቴክኖሎጂ
መቶ በመቶ መቀዳቱን መለካት የሚያስችል አሰራርና መስፈርት የያዘ ሰነድ ባለመኖሩ በአሰልጣኝ፣ በሰልጣኝ
እንዲሁም በአንቀሳቃሾች ተቀድተው የሚሸጋገሩ ቴክኖሎጂዎችን በትክክል ከመለካት አንፃር ያለውን ክፍተት
ለመሙላት እንዲያስችል ይህን የቴክኖሎጂ ማወዳደሪያ ሰነድ ማዘጋጀት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል፡፡
3. ዋና እና ዝርዝር ዓላማዎች
3.1. ዋና ዓላማ
የሰነዱ ዋና ዓላማ ቴክኖሎጂን በመቅዳት የኢንተርፕራይዞችን ተጠቃሚነት ያረጋገጡትን በማበረታታት
ፌ/ቴ/ሙ/ት/ስ/ኤጀንሲ
3.2. ዝርዝር ዓላማዎች
4. የውድድሩ መርሆዎች
ታማኝነት
ግልጸኝነት
ፍትሃዊነት
ሚስጥር ጠባቂነት
ቅንነት
ተጠያቂነት
5. የሰነዱ ወሰን
ይህ የማወዳደሪያ ሰነድ ቴክኖሎጂ በመቅዳት የኢንተርፕራይዙን ተወዳዳሪነት ያረጋገጡ የቴክኖሎጂ
ባለቤቶችን በፌዴራል፣ በክልል እና በክላስተር ደረጃ በየበጀት አመቱ ዕቅድ መሠረት ለማወዳደር በሚከናወኑ
ፌ/ቴ/ሙ/ት/ስ/ኤጀንሲ
7. በተዘጋጀው ማወዳደሪያ መስፈርት መሠረት ቴክኖሎጂዎችን ያወዳድራሉ፣ በየቴክኖሎጂ ዓይነቱ
የተደራጁ ዳኞች
8. የተቀዳውን ቴክኖሎጂ ሚስጥራዊነት መጠበቁን ይከታተላሉ ያስጠብቃሉ፣ በፌዴራል፣ በክልል፣ እና
ክላስተር ኮሌጅ/ተቋም
የሚመለከተው የስራ
ክፍል
9. ቃለ-ጉባኤ በመያዝ በውድድር ወቅት የነበረውን ሂደትና የተወዳዳሪዎችን የዳኞች ጉባኤ
ውጤት የያዘ እና የተፈረመበት ሰነድ ከአስፈላጊ ማስረጃ ጋር ለሚመለከተው
የስራ ክፍል ያቀርባል፣
10. የቀረበለትን ዝርዝር መረጃ ካጣራና ከገመገመ በኋላ ለስራ ክፍሉ የበላይ በፌዴራል፣ በክልል፣ እና
አካል አቅርቦ ያስፀድቃል፣ ክላስተር ኮሌጅ/ተቋም
የሚመለከተው የስራ
ክፍል
7. የዳኞች አመራረጥና ተግባር
አጠቃቀም ላይ ዕውቀቱና ክህሎቱ ባላቸው ባለሙያዎች ነው፡፡ ስለዚህም ዳኞቹ ሊገኙባቸው የሚችሉ ተቋማት
የሚከተሉት ናቸው፡-
የምርምር ተቋማት
የሙያ ማህበራት
ኮሌጆች
ፌ/ቴ/ሙ/ት/ስ/ኤጀንሲ
7.3. የዳኞች ተግባርና ኃላፊነት
1) ለቴክኖሎጂ ውድድሩ አስፈላጊ የሆኑ ግብአቶች፣ ሰነዶች፣ ማወዳደሪያ ቼክሊስትና የሪፖርት ፎርማት
መሟላታቸውን ማረጋገጥ፣
2) ለቴክኖሎጂ ውድድሩ የተዘጋጀውን መስፈርት በአግባቡ መረዳትና መጠቀም
3) በውድድሩ ከጅምሩ እስከ መጨረሻው ያለውን ሂደት ለተወዳዳሪዎች ማሳወቅ
4) ለተወዳዳሪዎች ውጤቱን ሪከርድ በማድረግ ግብረ-መልስ በወቅቱ መስጠት
5) ከሚመለከተው የስራ ክፍል ጋር በመሆን የውድድሩን አፈጻጸም መገምገም
6) የሚወዳደረውን ቴክኖሎጂና የውድድሩን ሂደት ሚስጥራዊነት መጠበቅ
7) በውድድሩ ወቅት ለሚፈጠሩ ቅሬታዎች ምላሽ መስጠት
8) በውድድሩ ዙሪያ ያሉትን መረጃዎች በተዘጋጀው የሪፖርት ፎርማት በማጠናቀር ለሚመለከተው አካል
እንዲደርሱ ማድረግ
8. የውድድሩ ተሳታፊዎች
አስልጣኞች፣ ሰልጣኞች እና የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች የውድድሩ አካላት ይሆናሉ፡፡
9. የተወዳዳሪዎች ምዝገባ
ማንኛውም ተወዳዳሪ በተቀመጠው የመመዝገቢያ መስፈርት መሰረት የሚከተለውን መረጃ አሟልቶ መስጠት
ይኖርበታል፡-
የተወዳዳሪው ሙሉ ስም
የመጣበት ተቋም/ኢንተርፕራይዝ
የመጣበት ክልል
የሚወዳደርበት ዘርፍ/ሙያ
የሚወዳደርበት ቴክኖሎጂ ስም
የቴክኖሎጂ ውድድር ዕቅድን ከፌዴራል ኤጀንሲ እስከ ተቋማት ለሚገኙ አደረጃጀቶች ማውረድ
የአፈጻጸም መመሪያ ማዘጋጀትና ለፈጻሚዎች ማስተዋወቅ
ከባላድርሻ አካላትና አጋር ድርጅቶች ጋር በቅንጅት መስራት
የዳኞችንና የኮሚቴ አባላትን አቅም መገንባት
በጥብቅ ዲስፕሊን የሚመራ የክትትልና ድጋፍ ስርዓት መዘርጋት
መረጃዎችን በተደራጀ ሁኔታ ለውሣኔ አሰጣጥ አመቻችቶ መያዝ፤
ፌ/ቴ/ሙ/ት/ስ/ኤጀንሲ
የእውቅናና ሽልማት ሥርዓት ማስቀመጥ
አጠቃላይ ሂደቱን መቀመር
ክብደት የተሰጠ
ተ.ቁ መስፈርት
ከ 100% ነጥብ
1 ከማህበራዊ ጠቀሜታ አንፃር 20
1.1 የህብረተሰቡን የኑሮ ሁኔታ የሚያሻሽል መሆኑ 5
1.2 የስራ ዕድል በመፍጠር ላይ ያለው አስተዋፅኦ 5
1.3 የሴቶችን የስራ ጫና የሚቀንስ መሆኑ 5
1.4 የአካል ጉዳተኞችንና አቅመ-ደካሞችን ችግር ፈቺ መሆኑ 5
ፌ/ቴ/ሙ/ት/ስ/ኤጀንሲ
4 ከቴክኖሎጂ አንፃር 40
ክብደት የተሰጠ
ተ.ቁ መስፈርት
4.1 ከ 100%
6 ነጥብ
በእሴት ሰንሰለት ትንተና ችግሮችን ለይቶ የተነሳ መሆኑ
ያገኘው ደረጃ
የገንዘብ፣ የሜዳሊያ፣ የትምህርት ዕድል፣ የሰርተፊኬት፣ የውጭ ጉብኝት እንዲሁም ሌሎች የማበረታቻ
ፌ/ቴ/ሙ/ት/ስ/ኤጀንሲ
14. የተሳትፎ ሰርቲፊኬት
ውድድሩን ያጠናቀቁ ሁሉም ተሳታፊዎች በውድድሩ ማጠናቀቂያ ላይ የተሳትፎ ሰርትፊኬት የሚያገኙ
ይሆናል፡፡
15. ማጠቃለያ
ይህ የማስተግበሪያ ሰነድ ከዚህ ቀደም ተመሳሳይ ተግባርን በአገር አቀፍ ደረጃ ወጥነት በሌለው ሁኔታ
ውድድሮቹን ከፍጻሜ ማድረስ የሚጠበቅባቸው ይሆናል፡፡ ከአቅም በላይ የሆነ ችግር ወይንም ለአፈጻጸም
አድራሻ፡-
ፌ/ቴ/ሙ/ት/ስ/ኤጀንሲ