You are on page 1of 2

የጋብቻ ትምህርት ለቅድመ ጋብቻ ተማሪዎች

I. ውጤታማ ግንኙነትን ለመፍጠር

ስለጋብቻ ብዙ የተባለ የተፃፈ፣ ፊለሙ፣ የተሰነደ ሊሆን ይችላል፡፡ ጤናማውን ግንኙነት ለመፍጠርና ለመስራት ግን የእግዚአብሔርን ልብ
ማወቅ ይጠይቃል በቃሉ በኩል

1. ሰው እግዚአብሔርን በግል ማወቅና መፍራት አለበት

ዮሃ 14፡22-24

የአስቆሮቱ ያይደለ ይሁዳ፦ ጌታ ሆይ፥ ለዓለም ሳይሆን ራስህን ለእኛ ልትገልጥ ያለህ እንዴት ነው? አለው። ኢየሱስም መለሰ አለውም፦
የሚወደኝ ቢኖር ቃሌን ይጠብቃል፤ አባቴም ይወደዋል ወደ እርሱም እንመጣለን በእርሱም ዘንድ መኖሪያ እናደርጋለን። የማይወደኝ ቃሌን
አይጠብቅም፤ የምትሰሙትም ቃል የላከኝ የአብ ነው እንጂ የእኔ አይደለም።

2. በግሉ የቃልኪዳን ጉዞ ያስፈልገዋል


በሚመራን መንገድ ለመሄድ ፈቃዱን ለማድረግና ለመገዛት
አብርሃም ሚስትን ለይስሃቅ እንዲያመጣለት ባርያውን የላከው ሰዓት ወደ እዚህ ለመምጣት እምቢ ብትለኝስ እርሱን
ልውሰደውን ሲለው እንዳታደርገው ተጠንቀቅ ነበርያለው ለትዳር ሲል ቃል ኪዳን እንዳያፈርስ
3. እግዚአብሔርን ገብቶት የሚከተል መሆን አለበት
ከእግዚአብሔር ጋር ያለው ህብረት ጤናማ እንደቃሉ መሆ አለበት
እግዚአብሔርን የሚከተልበት ምክንያት የተስተካከለ መሆን አለበት፡፡ ስለሚቀጣን በሲኦል ሊቀጣን ስለሚችል ወይ በስጋት
ያደኸየኛል በሚል ስጋት እንዲና እንዲያ ሊያደርገኝ ይችላል በሚል ምክንያት ሳይሆን በትክክለኛ መረዳት መሆን አለበት፡፡ ይህም
አምላክ ስለሆነ እኔም ስለምወደው እርሱ ለክብሩ የመረጠኝ ስለሆነ ብለን በጤናማ መለኪያ ልንከተለው ይገባናል፡፡ በጤናማ
መንገድ የሚከተሉትን ደግሞ የሚባርክ ነው የሚሸልም ነው…
4. ሰውን እንደሰውነቱ ማወቅና ማክበር የሚችል መሆም አለበት
አንድ ሰው እንደ ክርስቲያን ለማግባት ከመነሳቱ በፊት በጥቂቱ ሰውን እንደሰው አክባሪ ሆኖ መገኘት ያስፈልገዋል ሚስቱን እንደ
እንዲት ክርስቲያን ወንድም የጌታ መልክ እንዳለባት አድርጎ መቀበል ይኖርበታል

1 ኛ የጴጥሮስ 3፡7

እንዲሁም፥ እናንተ ባሎች ሆይ፥ ደካማ ፍጥረት ስለ ሆኑ ከሚስቶቻችሁ ጋር በማስተዋል አብራችሁ ኑሩ፤ ጸሎታችሁ እንዳይከለከል
አብረው ደግሞ የሕይወትን ጸጋ እንደሚወርሱ አድርጋችሁ አክብሩአቸው።

ዘፍ 2፡18-25

18 እግዚአብሔር አምላክም አለ፦ ሰው ብቻውን ይሆን ዘንድ መልካም አይደለም፤ የሚመቸውን ረዳት እንፍጠርለት።

19 እግዚአብሔር አምላክም የምድር አራዊትንና የሰማይ ወፎችን ሁሉ ከመሬት አደረገ፤ በምን ስም እንደሚጠራቸውም ያይ ዘንድ ወደ
አዳም አመጣቸው፤ አዳምም ሕያው ነፍስ ላለው ሁሉ በስሙ እንደ ጠራው ስሙ ያው ሆነ።

20 አዳምም ለእንስሳት ሁሉ፥ ለሰማይ ወፎችም ሁሉ፥ ለምድር አራዊትም ሁሉ ስም አወጣላቸው፤ ነገር ግን ለአዳም እንደ እርሱ ያለ
ረዳት አልተገኘለትም ነበር።

21 እግዚአብሔር አምላክም በአዳም ከባድ እንቅልፍን ጣለበት፥ አንቀላፋም፤ ከጎኑም አንዲት አጥንትን ወስዶ ስፍራውን በሥጋ ዘጋው።
22 እግዚአብሔር አምላክም ከአዳም የወሰዳትን አጥንት ሴት አድርጎ ሠራት፤ ወደ አዳምም አመጣት።

23 አዳምም አለ፦ ይህች አጥንት ከአጥንቴ ናት፥ ሥጋም ከሥጋዬ ናት፤ እርስዋ ከወንድ ተገኝታለችና ሴት ትባል።

24 ስለዚህ ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል፥ በሚስቱም ይጣበቃል፤ ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ።

25 አዳምና ሚስቱ ሁለቱም ዕራቁታቸውን ነበሩ፥ አይተፋፈሩም ነበር።

እግዚአብሔር ራሱ እኮ አብሮት እያለ ነው ብቻውን የተባለው

You might also like