You are on page 1of 7

ADDIS ABABA UNIVERSITY

College of Law and Governance

Law school

Legal Clinics Individual ASSIGNMENT

Title: Writing Claims for Opposition and Stay of execution on judgement

NAME ID. Number

Tewedros Kassa.............UGR/9148/13

Submitted to: Instructor Bisrat

Submission date: December, 2023


በከሳሽ እና በተከሳሽ መካከል በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 1234 ባደረጉት ክርክር
በቀድሞው የካ ክ/ከተማ በአሁኑ ለሚ ኩራ ክ/ከተማ፣ ወረዳ 13 ክልል አካባቢ በሚገኘው የአቶ አደፍርስ ከበደ በሆነው
አዋሳኞቹ በሰሜን የአቶ ሳሙኤል ገብረኪዳን ይዞታ፣ በደቡብ የአቶ አክሊሉ ይልማ ይዞታ፣ በምስራቅ የወ/ሮ ሰናይት አባተ
ይዞታ እንዲሁም በምእራብ መንገድ የሚያዋስኑትን 40 ቆርቆሮ 2 ክፍል ቤት ያረፈበት 280 ካ.ሜ ይዞታው ላይ ከአቶ
አደፍርስ ከበደ እውቅና ውጪ ክርክር ሲደርጉ ቆይተው ይዞታው የተከሳሾች ነው ተብሎ በሰኔ 25 ቀን 2014 ዓ/ም
ተወስኗል፡፡ አቶ አደፍርስ ከበደ ስለ ጉዳዩ የሰማው አሁን ሲሆን በፍርዱ መሰረት አፈጻጸም መከፈቱንም ተረድቷል፡፡
በፍርዱ መሰረት በአፈጻጸም መዝገቡ የተጠየቀውም በመዝገቡ ላይ ተከሳሽ የሆነው አቶ አለን በሰፊው በአቶ አደፍርስ ከበደ
ይዞታ ላይ የተሰራውን ግንባታ አፍርሶ ይዞታውን ለከሳሽ አቶ ኤልያስ ካሳ እንዲያስረክብ የሚል ነው፡፡

በተጨማሪም አሁን ፍርድ የተሰጠበትና አፈጻጸም የተከፈተበት ሰነድ አልባ ይዞታ የአቶ አደፍርስ መሆኑን የሚያስረዱ
የሚከተሉት ማስረጃዎች በአቶ አደፍርስ እጅ ይገኛሉ፡-

1) በአቶ አደፍርስ ከበደ ይዞታውን ከአቶ ገ/ኪዳን መካከል በሚያዝያ 16 ቀን 1996 ዓ/ም የገዛበት የመኖሪያ ቤት
ሽያጭ ውል 01፡፡
2) የወረዳው አስተዳደር ጽ/ቤት አሁን በአቶ አደፍርስ ከበደ እጅ የሚገኘው ይዞታ ከ 1997 ዓ/ም በፊት ጀምሮ በአቶ
አደፍርስ እጅ ይገኝ እንደነበር በኮሚቴ አረጋግጦ የላከበት ሰነድ 03 ገጽ፡፡

በተጨማሪም አቶ አደፍርስ ከበደ ጉዳዩን ሊያስረዱለት የሚችሉ ምስክሮች አሉት፡፡

ጥያቄዎች
1) ለአቶ አደፍርስ ከበደ ፍ/ቤት የሚገባ የተሟላ የመቃወም አቤቱታ አዘጋጅ፤
2) ለአቶ አደፍርስ ፍ/ቤቱ የሰጠው ፍርድ እንዳይፈጸም አቤቱታ ጠይቅ፤

ቀን፡-29/11/2014
መዝገብ ቁጥር፡-1234
በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ችሎት
ለልደታ ምድብ ፍ/ብሔር ችሎት
አዲስ አበባ
የመ/አመልካች፡- አቶ አደፍርስ ከበደ አድራሻ፡- ለሚ ኩራ ክ/ከተማ፣ ወረዳ 13
የመ/ተጠሪዎች ፦1. አቶ አለን አድራሻ፡- ለሚ ኩራ ክ/ከተማ፣ ወረዳ 13
2. አቶ ኤልያስ ካሳ አድራሻ፡- ለሚ ኩራ ክ/ከተማ፣ ወረዳ 13

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ልደታ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 1234 ላይ በሰኔ 25 ቀን 2014 ዓ/ም በዋለው
ችሎት በሰጠው ውሳኔ ላይ በፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 358 እና 359 መሰረት የቀረበ የመቃወም
አቤቱታ ነው
ሀ. ፍ/ቤቱ ጉዳዩን አይቶ የመወሰን ስልጣን አለው፡፡
ለ. የፍ/ቤቱን መጥሪያ ለመቃወም ተጠሪ የመ/አመልካች አደርሳለሁ፡፡
ሐ. የመቃወም አመልካች የመቃወም አቤቱታ ለማቅረብ ችሎታ አለኝ፡፡
መ. በመ.ቁ 1234 በቀን 25/10/2014 ዓ.ም የተሰጠ ወሳኔ ተያይዞ ቀርቧል፡፡

የጉዳዩ አመጣጥ በአጭሩ


የመቃወም ተጠሪዎች ማለት የመቃወም 1 ኛ ተጠረ እና 2 ኛ ተጠረ፣ የእኔን የመቃወም አመልካች ይዞታ የሆነውን ቤት
የእኔ ነው፥ የእኔ ነው በማለት በፍርድ ቤት የይወሰንልኝ ጥያቄ አቅርቦ ስከራከሩ ቆይቶል ፍርድ ቤቱም የግራ ቀኙን ምስክር
ሰምቶ የመቃወም 2 ተኛ ተጠሪ የይዞታ ባለበት ናቸው ብሎ ቤቱ ፈርሶ ለ 2 ተኛ መቃወም ተጠሪ ይመለስ ብሎአል። ነገር
ግን የመቃወም ተጠሪዎች የቤቱ ይዞታ ባለቤት አይደሉም። በመሆኑም ይህ ውሳኔ የመቃወም አመልካች መብትና ጥቅሜን
የሚጎዳ በመሆኑ የመቃወም 2 ተኛ ተጠሪ የቤቱ ይዞታ ባለቤት ሳይሆን የይዞታው ባለቤት ነኝ በሚል በዚሁ ፍርድ ቤት
በመ.ቁ 1234 በቀን 25/10/2014 ዓ.ም የሰጠው ውሳኔ እንዲሻር ይህንን አቤቱታ አስገብቻለሁ፡፡

የአቤቱታው ዝርዝር በአጭሩ


የመቃወም 2 ተኛ ተጠሪ የቤቱ ይዞታ ባለቤት አይደለም፡፡ ይልቁንም የመቃወም 2 ተኛ ተጠሪ የእኔ ነው በማለት
ስይከራከሩበት የነበረው ይዞታ ከእውነት የራቀ ነው፣ ለዚህ ደግሞ በተቃራኒው የእኔ የመቃወም አመልካች ይዞታ ነው።
በመሆኑም ይዞታው የመቃወም 2 ተኛ ተጠሪ ባለመሆኑ በዚሁ ፍርድ ቤት የተሰጠው ውሳኔ እንዲሻርልኝ በማክበር
እጠይቃለሁ፡፡ የመቃወም 2 ተኛ ተጠሪ የይዞታው ባለቤት አይደለም፡፡

የመቃወም አመልካች ከፍርድ ቤቱ የምጠይቀው ዳኝነት


1) ለመቃወም ተጠሪ በመዝገብ ቁጥር 1234 በቀን 25/10/2014 በዋለው ችሎት የተሰጠው ውሳኔ እንዲሻርልኝ እና
ሁለቱም የመቃወም ተጠሪዎች የቤቱ ይዞታ ባለቤት አይደለም ተብሎ እንዲወሰንልኝ፡፡
2) የመ/አመልካች በዚህ አቤቱታ ምክንያት ያወጣሁትን ወጪ የመ/ተጠሪዎች እንዲሸፍኑ እንዲወሰንልኝ፡፡

ከላይ የቀረበው አቤቱታ እውነት መሆኑን በፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁጥር 92/3/ መሰረት አረጋግጣለሁ።


የመቃወም አመልካች

ቀን፡-29/11/2014
መዝገብ ቁጥር፡-1234
በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት
ለልደታ ምድብ ፍ/ብሔር ችሎት
አዲስ አበባ
የመ/አመልካች፡- አቶ አደፍርስ ከበደ አድራሻ፡- ለሚ ኩራ ክ/ከተማ፣ ወረዳ 13
የመ/ተጠሪዎች፦ 1.አቶ አለን አድራሻ፡- ለሚ ኩራ ክ/ከተማ፣ ወረዳ 13
2. አቶ ኤልያስ ካሳ አድራሻ፡- ለሚ ኩራ ክ/ከተማ፣ ወረዳ 13

በፍ/ሥ/ሥ/ህግ ቁጥር 223 መሰረት ከመቃወም አመልካች የቀረበ የማስረጃ ዝርዝር መግለጫ
1.የሰነድ ማስረጃ
1) በአቶ አደፍርስ ከበደ ይዞታውን ከአቶ ገ/ኪዳን መካከል በሚያዝያ 16 ቀን 1996 ዓ/ም የገዛበት የመኖሪያ
ቤት ሽያጭ ውል 1 ገጽ ዋና ።

2) የወረዳው አስተዳደር ጽ/ቤት አሁን በአቶ አደፍርስ ከበደ እጅ የሚገኘው ይዞታ ከ 1997 ዓ/ም በፊት
ጀምሮ በአቶ አደፍርስ እጅ ይገኝ እንደነበር በኮሚቴ አረጋግጦ የላከበት ሰነድ 3 ገጽ፡፡

2. የሰው ምስክር
1. ወ/ሮ .............................. አድራሻ፡-.....................
2. አቶ ...................................አድራሻ፡-....................
3. ወ/ሮ .................................አድራሻ፡-....................
ከላይ የቀረበው የማስረጃ ዝርዝር እውነት መሆኑን በፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁጥር 92/3/ መሰረት አረጋግጣለሁ፡፡
የመቃወም አመልካች

ቀን፡-29/11/2014
መዝገብ ቁጥር፡-1234
በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት
ለልደታ ምድብ ፍ/ብሔር ችሎት
አዲስ አበባ
የመ/አመልካች፡- አቶ አደፍርስ ከበደ አድራሻ፡- ለሚ ኩራ ክ/ከተማ፣ ወረዳ 13
የመ/ተጠሪዎች፦1. አቶ አለን አድራሻ፡- ለሚ ኩራ ክ/ከተማ፣ ወረዳ 13
2. አቶ ኤልያስ ካሳ አድራሻ፡- ለሚ ኩራ ክ/ከተማ፣ ወረዳ 13
በፍሥ/ሥ/ህ/ቁ. 359(3) እና 205 መሰረት በቃለ መሀላ ተደግፎ የቀረበ አቤቱታ
የመቃወም ተጠሪዎች የእኔ የመቃወም አመልካች የሆነውን የቤት ይዞ፣ የእኔ ነው፥ የእኔ ነው በማለት በፍርድ ቤት ይወሰንልኝ
ጥያቄ አቅርቦ ስከራከሩ ቆይቶ ፍርድ ቤቱም ምስክር ሰምቶ የመቃወም 2 ተኛ ተጠሪ የይዞታው ባለቤት ነው ብሎ የአለበት
ቤት ፈርሶ ለ 2 ተኛ መቃወም ተጠሪ እንድይመለስ ወስኗል። ነገር ግን የመቃወም 2 ተኛ ተጠሪ የይዞታው ባለቤት አይደለም፡፡
በመሆኑም ይህ ውሳኔ የመቃወም አመልካች መብትና ጥቅሜን የሚጎዳ በመሆኑ የመቃወም 2 ተኛ ተጠሪ የይዞታው ባለቤት
ሳይሆን ባለቤት ነኝ በሚል በዚሁ ፍርድ ቤት በመ.ቁ 1234 በቀን 25/10/2014 ዓ.ም የሰጠው ውሳኔ እንዲሻር እና
የመቃወም አመልካች የክርክሩ ተካፋይ ሳልሆን ለመቃወም ተጠሪ የተሰጠው ውሳኔ የእኔን ህጋዊ መብት እና ጥቅም በእጅጉ
ስለሚጎዳ በተገለጸው ቀን የተሰጠው ውሳኔ ተሽሮና የክርክሩ ተካፋይ ሆኜ ክርክሩ እንደገና ተሰምቶ ውሳኔ እንዲሰጥልኝ
በመቃወም ያቀረብኩት አቤቱታ እውነት መሆኑን በመሃላ ቃል አረጋግጣለሁ፡፡
የመቃወም አመልካች
ቀን፡- ሐምሌ 30/2014 ዓ.ም

በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ችሎት

ለልደታ ምድብ ፍ/ብሔር ችሎት

አዲስ አበባ

አመልካች፡- አቶ አደፍርስ ከበደ አድራሻ፡- ለሚ ኩራ ክ/ከተማ፣ ወረዳ 13

ተጠሪ፦ አቶ አለን አድራሻ፡- ለሚ ኩራ ክ/ከተማ፣ ወረዳ 13

በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 333 እና 335 መሰረት የእግድ ትዕዛዝ ለማሰጠት በቃለ-መሃላ ተደግፎ የቀረበ አቤቱታ

ለተጠሪ የተወሰነው የይዞታ ባለቤትነት እንድሻርልኝ እና ቤቱ የይፍረስ ውሳኔ እንድሻርልኝ አቤቱታ አስገብቻለሁ። ተጠረ
አቤቱታ እንደ አስገባው አውቆ ወይም ሳይአውቅ የእኔ የአመልካች ይዞታ በሆነው ቤት ላይ ሊተካ የማይችል ጉዳት
ሊያደርስብኝ ይችላል። በመሆኑም የእኔ የአመልካች ይዞታ የሆነው ቤት ማለትም አሁን ለተጠሪ የተወስነው 40 ቆርቆሮ 2
ክፍል ቤት ያረፈበት 280 ካ.ሜ እንዳይፈርስ ለአዲስ አበባ ቤቶች ባለስልጣን የእግድ ትእዛዝ ይሰጥልኝ፡፡ ለተጠሪ የተወሰነው
እና እንድፈርስ የተወሰነው እንዳይፈርስ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 333 እና 335 መሰረት የእግድ ትእዛዝ እንዲሰጥልኝ በማክበር
እጠይቃለሁ፡፡

ከላይ የቀረበው አቤቱታ እውነት መሆኑን በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 92 መሰረት አረጋግጣለሁ፡፡

አመልካች

You might also like