You are on page 1of 13

ገንዘብ በወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት መርህ እንዴት ይታያል

ከጥንት ጀምሮ ወርቅ ገንዘብ ነበር፡፡ ጥቅም ሰጭ እቃዎች ዋጋ የሚተመንላቸው ወርቅን


መሰረት በማድረግ ነበር፡፡ ይህም ማለት እቃው ይህን ያህል ወቄት ወርቅ ጠቀሜታ አለው
ይባላል፡፡ ሰዎች ዋጋን የሚከፍሉት በወርቅ ነበር፡፡ ነገር ግን የወርቁን የብረት አይነት እና ክብደት
በእያንዳንዱ ግብይት ለመለየት ግዜና ጉልበት ይፈልጋል፡፡ ይህ ጉዳይ የወርቅ ሳንቲም
እንዲፈጠር ምክንያት ሆነ፡፡የውርቅን ሳንቲም የሚያመርቱ በሀገር ገዢ ስም የሳንቲምን ጥራት
እና ክብደት ማረጋገጫ መስጠት ጀመሩ፡፡ይህ ወርቅ ሳነቲምን ምቹ መገበያያ እንዲሆን እድል
ፈጠረለት፡፡ በሳንቲሙ ላይ የሚለጠፈው ዋጋ የወርቁ ዋጋ ሆኖ ቢወሰድም የወርቁ ትክክለኛ
ዋጋ በቀላሉ ይታወቃል፡፡ ስለዚህ በሀገር ገዥ የትም የታተመ የወርቅ ገንዘብ ውስጣዊ ጥቅም
ስላለው በሁሉም ቦታ ተቀባይነት ነበረው፡፡ ወርቅ ገንዘብ እነደሆነና የወርቅ ሳንቲም መገበያያ
እንደነበረ አለም አቀፍ ተቀባይነት ነበረው፡፡ ብር እና ነሀስም እንደዛው፡፡

ቀስ በቀስ የወርቅ ገንዘብ ተቀባይነቱ በሳንቲሙ ላይ ያለው ሀገር ገዥ መሪ እና


በሚያስተዳድረው ወሰን የተረጋጋ መሆን አለመሆን ተስእኖ ማሳደር ጀመረ፡፡እንዳንድ ጊዜ
ሰዎች የወርቅን ዋጋ አሳንሰው መገበያየት እና በወርቁ ላይ ያለውን ዋጋ አለመቀበል ተጀመረ፡፡
በሌላ በኩል ወርቅ አታሚዎችም ሳንቲሙ ላይ ከለጠፉት የወርቅ ዋጋ ያነሰ ጥራት ያለው
ወይም ክብደቱን በማሳነስ ሳንቲም ማምረት ጀመሩ፡፡ በዚህ መሃል የሳንቲሙን ትክክለኛ ዋጋ
ማወቅ ከባድ እልነበረም እና ጥራታቸው እና ክብደታቸውን በማሳነስ የታተሙ የወርቅ
ሳንቲሞች ከበሬታ ወረደ፡፡ሁሉም ሀገራት የሚያትሙትን የወርቅ መጠን ቅርጽ እና ስም
በትክክል ቢቀርጹም ትክክለኛ ዋጋው የሚወሰነው በትክክለኛ የወርቅ ይዘቱ ሆነ፡፡ ይህ ሆኔታ
የወረቀት ገንዘብ እስኪጀመር ድረስ ቀጠለ፡፡

የወረቀት ገንዘብ እና የወርቅ ዋጋ

የወርቅ ገንዘብ የተፈጠረው በአውሮፓ ሲሆን የተጀመረውም ወርቅ አንጣሪ ወርቅ


እንዲቀመጥላቸው የሚጠይቁ ሰዎች ለማስቀመጣቸው መተማመኛ የሚሆን ደረሰኝ መስጠት
በመጀመሩ እና ይህም በሰዎች ዘንድ ተቀባይነትን ስላገኘ ነበር፡፡ በተለይ ለነጋዴዎች ውርቅን
ከቦታ ወደ ቦታ በመዘዋወር ሊመጣ የሚችል ስጋቶች እና በዛ ያሉ የወርቅ ሳንቲሞችን
የመሸከም ድካምን በመቀነሳቸውና ደረሰኙ በየትም ቦታ ያሉ ነጋዲዎች ተቀባይነትን በማግኘቱ
ነበር፡፡ የወርቅ አንጥረኛው ይህን ደረሰኝ ይዞ የሚመጣን ሰው በመክፈሉ እና ንግድን ማቀላጠፍ
በመቻሉ በዚህ ክብር አገኘ፡፡
ከጊዜ በኃላ አንጥረኛው በአደራ እሱ ጋር ከተቀመጡት ወርቆች መካከል ለክፍያ የሚጠየቀው
በጣም አነስተኛ ወርቆች ብቻ መሆኑን ተገነዘበ፡፡ አብዛኛው ወርቆች ካዝናው ውሥጥ ያለስራ
ይቀመጣሉ፡፡ ይህንን የተገነዘበው አንጥረኛው የራሱን ደረሰኝ ማሳተም እና በእነዚህ
በማይጠየቁ ወርቆች ልኬት ለሌሎች ሰዎች በወለድ ማበደር ጀመረ፡፡ይህም ማድረጉ
በማህበረሰቡ ዘንድ ተአማኒነት እንዲኖረው አስቻለው፡፡

አንጥረኛው እና ገንዘብ የማበዱ ስራ ወደ ባንክነት በተቀየረ ጊዜ ባንኮችም በልዩልዩ የገንዘብ


መጠን ከእንጥረኛው በተሸለ መልክ እና አይነቶች ደረሰኝ ማሳተም ጀመሩ፡፡ ይህም በህዝቡ
ዘንድ የበለጠ ከበሬታን አስገኘላቸው፡፡ ሁሉም ባንኮች ይህንን በመንተራስ የራሳቸውን የገንዘብ
ኖት ማሳተም ጀመሩ፡፡የእያንዳንዱ ባንክ እውቅናም የታተሙትን ገንዘብ ኖቶች ለክፍያ ወደ
ባንኮች በሚመጡ ጊዜ በሚያሳዩት የመክፈል አቅም ሆነ፡፡ ይህ የባንኮች ክብር መቆየት የቻለው
ግን ለአጭር ጊዜ ብቻ ነበር፡፡በመሆኑም ብዙ ባንኮች ኖቶች ገበያው ላይ ተንሰራፋ፡፡

በዛ ያሉ ባንኮች በሰዎች የይከፈለኝ ጥያቄ በወርቅ ክፍያን አለማስተናገድ መቻል እንዲሁም


ልዩልዩ ማጭበርበሮች ማእከላዊ የሀገራት ባንኮች እንዲመሰረቱ ምክንያት ሆነ፡፡ እነዚህ ባንኮች
እራሳቸውን ብቸኛ ገንዘብ አታሚ በማድረግ ሾሙ፡፡ይህም ሀገራት የየራሳቸውን ገንዘብ
እንዲያሳትሙ በር ከፈተላቸው ፡፡ በዚህ ዘርፍ እንግሊዝ በአስራስምንተኛው ክፍለዘመን ቀዳሚ
ሆነች፡፡ በዚህም ጊዜ ወርቅ ገንዘብ እንደሆነ ነው፡፡ ነገር እንደወርቅ በመሆን የገንዘብ ኖት
ያገለግላል፡፡ ሰዎች ወረቀትን የገንዘብ ገላጭ በማድረግ ይጠቀማሉ፡፡ ይህም ወረቀት በማእከላዊ
ባንኮች መተማመኛ አለው፡፡ የወረቀቱ እኩሌታ ከተወሰነ የወርቅ ክብደት ጋር እኩሌታ ያለውና
በተፈለገ ጊዜ የወርቅ እኩሌታው በማንኛውም ጊዜ በባንኮቹ ይቀየራል፡፡ ይህም ወረቀቱ ልክ
የወርቅን ያህል ተቀባይነት እንዲኖረው አስቻለ፡፡

ከጊዜ በኃላ የወረቀት ገንዘብ ላይ የህግ አስገዳጅነትን የሚገልጽ ህግ መጻፍ ተጀመረ፡፡ ይህም
ማለት የወረቀትን ገንዘብ አልቀበልም ማለት በህግ የሚያስቀጣ ሆነ፡፡ ይህም ህግ በሀገራት
ውስጥ የሚተገበር ህግ በመሆኑ በዛ ሀገር ላይ የሚኖሩ ሰዎች ወርቅ የመያዝ ልምዳቸው ቀስ
በቀስ መቀነስም ጀመረ፡፡ ለአለም አቀፍ የንግድ እንቅስቃሴ ግን ከሳንቲም እጅግ የላቀ ክብደት
ያለው ወርቅ እንደመገበያያ መጠቀም ተጀመረ፡፡ ከጊዜም በኃላ እንግሊዝ ባላት የፖለቲካ
ኃያልነት እና ቅኝ ግዛተዋን ከማስፋፋት (1717) ጋር በተያያዘ የወረቀት ገንዘብ ወርቅ ነው
የሚለው እሳቤ በአብዛኛው አለም ሀገራት ማህበረሰብ አእምሮ ውስጥ ሰረጸ፡፡ በናፖሊዮን
አገዛዝ መባቻ ላይ (1815) አብዛኛው መገበያያ የተመሰረተው በወርቅ ወይም በብር (የብረት
አይነት) ነበር፡፡ በ 19 ኛው ክፍለዘመን ወርቅ በብር(ሲልቨር) መተካት ጀመረ፡፡ ወደ ወርቅ በቀላሉ
የመቀየር ጠባይ፤ የገንዘብ ኖት ልኬት ከወርቅ ጋር ያለው ዝምድና፤ ዜጎች እንደፈለጉ ወርቀን
የመያዝ፤ ኤክስፖርት እና ኢምፖርት የማድረግ መብት አንድ ላይ ዘ ጎልድ ስታንዳርድ የሚል
ስያሜ ተሰጠው፡፡ በ 1880 እና በ 1914 ጎልድ ስታንዳርድ በአለም አቀፍ ንግድ ላይ ተንሰራፋ፡፡
ይህም ለአለም አቀፍ ንግድ ጎልድ ስታንዳርድ የተለመደ አሰራር ሆነ፡፡ የወረቀት ገንዘብ ዋጋ እና
ወርቅ የሚያገበያይበት ዋጋ የተረጋጋ መሆን የሀገር ውስጥ እና አለም አቀፍ ንግዶች ከትንሽ
ካፒታል ኪሳራ ኢንቨስትመን ጋር ተዳብሎ በወረቀት ገንዘብ ላይ እና በጎልድ ስታንዳርድ ላይ
ያለው አመኔታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጣ፡፡ በወርቅ የታተመው ሳንቲም አሁንም
ውስጣዊ ዋጋ ያለው በመሆኑ በራሱ አመኔታውን እንደያዘ ነው፡፡ ሆኖም የወረቀት ኖቶች ያለው
መተማመኛ ይህንን ወረቀት ክፈለን ባልከኝ ጊዜ እከፍለሀለሁ የሚል የመተማመኛ ህግ ብቻ
ነበር፡፡ ይህም በአታሚው ማእከላዊ ባንክ ባለው የጎልድ ስታንዳርድን ህግ በመከተል እና
ባለመከተል ሙሉ በሙሉ ጥገኛ ነው፡፡ አንዳንድ ጊዜ ከላይ የዘረዘርናቸው ጎልድ ስታንዳርድ
ስምምነት የማይተገበሩበት ጊዜ ነበር፡፡ የወርቅ ዋጋ መውረድ፤ክልከላዎች እና እገዳዎች ነበሩ፡፡
እንደምሳሌ 1. እንግሊዝ በናፖሊዮን ጦርነት ጊዜ አስከፊ የሚባል የዋጋ መናር ወይም ግሽበት
ስላጋጠማት የወረቀት ገንዘብ በወርቅ በተፈለገ ጊዜ መቀየር ላይ እገዳ አስቀመጠች፡፡
ተከታታይነት ያለውን የዋጋ ግሽበት ለመከላከል ስትል እንግሊዝ በ 1819 ባወጣችው ህግ ላይ
ወርቅ አስቀድሞ በተወሰነለት ውስን ዋጋ ከመቀያየር ወጋውን የማርኬት ዋጋ እንዲወስነው
ደነገገች፡፡

2. አሜሪካ ዜጎችዋን ወርቅ እንደፈለጉ የመያዝ ኤክስፖርት እና ኢምፖረት የማድረግ ነጻነትን


ከለከለች፡፡ ቀስ በቀስም የወርቅን ትክክለኛ ይዘት መቀነስ ጀመረች፡፡ በማርች 1933 ፕሬዝደንት
ሩስቨልት አለም አቀፍ የንግድ ልውውጥን እና በወርቅ መገበያየት ላይ ማእቀብ አወጣች፡፡ በዚሁ
አመት በአፕሪል ግለሰቦች በእጃቸው የሚገኝ የወርቅ ሳንቲም፤ ለአለም አቀፍ ንግድ
የሚያገለግለው ገዘፍ ያለ ክብደት ያለውን (ረብጣ) ወርቅ እና የወርቅ ሰርተፍኬቶችን ለሀገሪቱ
ፌዴራል ሪዘርቭ ባንክ እንዲያስረክቡ ትእዛዝ አስተላለፈ፡፡ የዶላርና ወርቅ ለውውጥ ዋጋ ከፍ
በማድረግ ዲቫሉዌሽን እንዲከሰት አደረገች፡፡ በዚህ ጊዜ የዶላር 59% ብቻ ነበር የበፊቱን
የወርቅ ይዘትን የሚገዛው፡፡

3. በ 1936 ፈረንሳይ እና ሌሎች ሀገራት የወርቅን በቀላሉ የመገበያየት በታገደ ጊዜ አሜሪካ ብቻ


ነበርች ሀገር ውስጥ መገበያያ እና በወርቅ መካከል ጥሩ ግንኑነት እንዲኖር ማድረግ የቻለችው፡፡
በአለም አቀፍ ንግድ እገዳ እና ዶላር ከወርቅ ዋጋ ጋር ያለው ዝምድና በህግ መዳኘቱ ቀርቶ
በዘፈቀደ ስለነበረ አሜሪካ ለጎልድ ስታንዳርድ ተገዢ አልነበረችም፡፡ ነገሮች ከሀሁተኛው አለም
ጦርነት በኃላ በሚገርም ፍጥነት መቀያየር ጀመረ፡፡በ 1936 ሁሉም ሀገራት ማለት በሚቻልበት
ሁኔታ የወርቅ እና መገበያ ገንዘብ ነበራቸውን ዝምድና ጥሰዋል፡፡ ይህም አለም አቀፍ ንግድ
የመገበያያ ዋጋን ህግ መጣስ እና ወርቅን እንደፈለጉ ከአንድ ሀገር ወደ ሌላ ሀገር በማዘዋወር
ላይ የተጣለው እገዳን ሲታከል መሰረታዊ ጎልድ ስታንዳርድ ህጎች ገዢ መሆናቸው አቆመ፡፡ይህ
ጉዳይ በአለም አቀፍ ንግድ እና በሀገራት ባላንስ ኦፍ ፔይመንት ያልታሰበ ጉዳይ አስከተለ፡፡
ይህም ከሁለተና አለም ጦርነት መባቻ ላይ በአሜሪካ ሀገር ለተዘጋጀው ብሬተን ዉድስ
ኮንፈረነስ መነሻ ሆነ፡፡

የብሪትን ዉድስ ስምምነት


በ 1944 በብሪትን ውድስ ስምምነት ድርድር ተደረገ፡፡ በ 1945 ስምምነቱን በዚያን ጊዜ የነበሩር
40 ሀገራት ስምምነቱን ፈረሙ ፡የስምምነቱ ስፖንሰር አድራጊዎች በዋናነት እንግሊዝ እና
አሜሪካ ነበሩ፡፡የስምምነቱ አስፈላጊነት በአለም አቀፍ ንግድ ልውውጥ ላይ የዋጋ መረጋጋትን
ለማምጣት ነበር፡፡ ይህም የሚሆነው የአሚሬካ ዶላር ዋጋን ከተወሰነ የወርቅ ልኬት ጋር እኩል
በማድረግና የሌሎች ሀገራት መገበያያ ገንዘብን ደግሞ ከዶላር ጋር የተወሰነ ልኬት እንዲኖር
በማድረግ ነው፡፡ ይህም ማለት የተቀሩት ገንዘቦች ከተወሰነ የወርቅ ክብደት ጋር እኩል ናቸው
ማለት ነው፡፡ ዶላር ለሌሎች መገበያያ ኖቶች መሰረት ሆነ፡፡ይህም ማለት በማንኛውም ሀገር
የሚገኝ አንድ ምርት በሀገሪቱ የገንዘብ መጠን ቢገለጽም በተጓዳኝ የተለየ በወርቅ የሚተመን
ዋጋ አለው፡፡ከዚህ ቀደም የሀገራት መገበያያ በቀጥታ ግንኙነት የነበረው ከወርቅ ጋር ነበር፡፡ከዚህ
ጊዜ በኃላ ግን በቀጥታ የወርቅ ተመን ያለው ዶላር ብቻ ሆነ፡፡ ይህም አንዳንድ ቦታ ዘ ጎለድ
ዶላር ስታንዳርድ በመባል ይታወቅ ጀመር፡፡ይህ በወርቅ እና መገበያያ የታየ ሁለተኛው ዋነኛ
ለውጥ ሆነ፡፡

በዚህ በብሪትን ውድስ ስምምነት መሰረት አንድ ዶላር 1/35 ጥሩ ጥራት ያለው ወቄት ወርቅ
ተሰጠው(ይህ ማለት አንድ ወቄት ወርቅ ከ 35 የአሚሪካ ዶላር ጋር እኩል ነው)፤፤ አሜሪካ በዚህ
ስምምነት መሰረት ይህንን የዋጋ ተመን ለመጠበቅ እና ማንኛውንም የይክፈለኝ የዶላር
ጥያቄን በማንኛውም ጊዜ በተጠቀሰው የወርቅ እኩሌታ በ ዘ ጎለደ ዊንዶወ ለመመንዘር
ዋስትና ሰጠች፡፡ሌሎች የመገበያያ ገንዘቦች ከዶላር ጋር የተተመነላቸውን ዋጋ ይዘው
ለመቀጠል ቃል ገቡ፡፡ይህንንም የሚቆጣጠር ኢንተርናሽናል ሞንትሬ ፈንድ ተቃቃመ፡፡ ከዚህ
በኃላ የማንኛውም የገንዘብ መገበያያ ወረቀት ወደ ወርቅ መመንዘር ተከለከለ፡፡ምንም እንኳ
ወርቅ በዚህም ጊዜ እንደ መጠባበቂያ ቢያገለግልም የአሜሪካ ዶላር ዋንኛ የመጠባበቂያ ሰነድ
በመሆን በሌሎች የማእከላዊ ባንኮች ማገልገል ጀመረ፡፡ እንዲሁም ሁሉም አለም አቀፍ
ንግዶች በዶላር መገበያየት ተጀመረ፡፡የሀገሪቱ ማእከላዊ ባንኮች ብቻ ናቸው ለ ጎልድ ዊንዶው
ዶላር በማቅረብ ወደ ወርቅ እንዲመነዘርላቸው መጠየቅ የሚችሉት፡፡

ነገር ግን አሜሪካ የበጀት ጉድለቷን ለሟሟላት የወርቅ መጠባበቂያ ሳታስቀምጥ ዶላር በገፍ
ማተም ፤የንግድ ልውውጥን መቆጣጠር እና የማእከላዊ ባንኮችን የአሚሪካ የፋይናንስ
ንብረትን ወደ ወርቅ እንዳይቀየር ማስገደድ እና ተጽእኖ ማሳደር ጀመረች፡፡ በ 1970
መጨረሻዎቹ ላይ አሜሪካ በሌሎች ሀገራት የክፍያ ይገባኛል ጥያቄ በወርቅ መጠባበቂያ ካለት
ወርቅ ሁለት እጥፍ በላይ ነበር፡፡አሜሪካ ፊቷ የተደቀነው ከባድ አደጋ እንደማይቀርላት
በመፍራት የአሜሪካ መንግስት ትልቅ ውሳኔ አስተላለፈ፡፡

እሁድ ኦገስት 15 ቀን 1975 አሚሪካ የጎልድ ዊነዶዋን ዘጋች፡፡ ከዚህ ቀደም የገባችውን ቃል
አጠፈች፡፡ በብሪትን ዎድስ ስምምነታቸውን ያሰፈሩት ሀገራት አንድ ላይ ስምምነቱን ማጽናት
ተሳናቸው፡፡ ለ 26 አመታት የዘለቀው የብሪትን ዎድስ ስምምነት በጊዜ ተቀበረ፡፡ ከዚህ በኃላም
ቢሆን የአሜሪካ ዶላር በነጻነት በአለም ደረጃ ይዘዋወራል፡፡ ሌሎች ሀገራት ገንዘብም እንደዚሁ፡፡
ይህ ደግሞ በወርቅ መገበያያነት ለሶስተኛ ጊዜ የተከሰተ ክስተት ሆነ፡፡ ክስተቱ ወርቅ
ከመገበያያነት የነበረውን ዝምድና ለመጨረሻ ጊዜ የወረቀት ገንዘብ እንደወርቅ በመሆን
ማገልገሉን ያቆመበት ጊዜ ሆነ፡፡

ከ 1971 በኃላ

ከዚህም ጊዜ በኃላ መገበያያ የተስፋ ሰነድ እንደሆነ ነው፡፡ ነገር ግን ሁሉም ሀገራት የራሳቸውን
መገበያያ በወርቅም ይሁን በሌላ ዋጋ ባለው ንብረትም ሆነ በሌላ ሀገር ገንዘብ ላለመቀየር
ራሳቸውን ከተጠያቂነት አገለሉ፡፡ ይህን ተንሳፍፎ የቀረውን የወረቀት ገንዘብ ያለው
መተማመኛ ዜጎች አንዳቸው በአንዳቸው ላይ ያላቸው መተማመን ብቻ ነው፡፡ ዜጎች
የወረቀት ገንዘብን አልቀበልም ያሉ ጊዜ ትልቅ አደጋ ሊያስከትል ይችላል፡፡ ሆኖም ይህ
እነዳይሆን የህግ ከለላ አለው፡፡ የወረቀት ገንዘብ ህግ የሚጠብቀው እና የሚገርም ቅዠት
እንደሆነ ነው፡፡

በ 2002 አውሮፓ እንዱን ቅዠት በሌላ ቀዠት እንዲተካ አደረገ፡፡ የ 12 ሀገራትን የተለያየ
መገበያያ ገንዘብን በአንድ ተካ፡፡ በአንዲት ሌሊት ዲሴምበር 31 2001/ጃነንዋሪ 1 2002 በአለም
ትልቅ ዋጋ ያለውን የጀርመን ገንዘብ ማርክ ከፈረንሳይ ከኔዘርላንድ፤ከቤልጂመ ከኢታሊያ እና
ከሌሎች ሀገራት ጋር ይገበያዩበት የነበረ ምንም ጥቅም የሌላቸውን 12 መገበያ ገንዘብ በሌላ
ምንም ጥቅም በሌለው አንድ መገበያያ (ዩሮ) በህግ ከለላ ተተካ፡፡ የአለም ህዝብ ለቁጥር
በሚያታክት በጭነት መኪናዎች የድሮ ገንዘቦች ተሰብስበው ሲቀደድ እና ወደ ወረቀትነት
ሲቀየረ በቴሌዢዥን ለማየት በቃ፡፡ ይህ ወረቀት በኃላ ላይ ወደ ሽንት ቤት ወረቀትነት ተቀየረ፡፡
ሳንቲሞቹ እንዲቀልጡ ሆነው ውስጣዊ ጠቀሜታቸውን ሳይለቁ የብረትነት ዋጋቸው
እነዳላቸው ለሌላ አገልግሎት ዋሉ፡፡

በ 1985 የአሜሪካ ዶላር ፌዴራል ሪሰርቭ ኖት በመባል በይፋ ጸደቀ፡፡ በኖቱ ላይ የሀገሪቱ ስም፣
የዶላሩ ስም፤የገንዘቡ መጠን፡፤ የኖቱ ቁጥር፤ የህግ አስገዳጅነት አረፍተ ነገር እና የሀገሪቱ
የገንዘብ ሹም ፊርማ እንዲታተም ሆነ፡፡

የካናዳ ዶላር በ 1973 በካንክ ፈ ካናዳ ስም እና የባንኩ ገዥ በሆነው ኦታር ተፈረመ፡፡ በዶላሩ ላይ
ይህ ኖት ህጋዊ አስገዳጅ ነው የሚል አረፍተ ነገር አለው፡፡

የብሪትን ፓውንድ በኢንግላንድ ባንክ ስም ታትሞ በባንኩ ካሸር እና ገዥ ተፈረመበት፡፡ ኖቱ


ላምጪው “ይህን ያህል ፓውንድ ለመክፈል ቃል እገባለሁ” የሚል አረፍተ ነገር ሰፈረበት፡፡ግን
የትኛው የክብደት መመዘኛ ፓውንድ;፤፤የወርቅ ብረት የወረቀት የአሳ ወይስ የስጋ ክብደት
መመዘኛ?ሁሉም የሀገራት ኖቱች ተመሳሳይ አረፍተ ነገሮች ሰፍሮባቸዋል፡፡ ነገር ግን አዲሱ ዩሮ
የተለየ የኢኮኖሚ ፎርሙላ አለው፡፡ ሲርያል ነበር ፤ የገንዘብ መጠን አይነት የኮፒራይት መስመር
ሲኖረው ሌላ ምንም ነገር የለውም፡፡በርግጥ ፊረማ አለው ግን የማን ፊረማ ነው? በማንስ ስም
ነው የተፈረመው?ይህ የሚያምር አርት የፈሰሰበት ምንድን ነው?ምንም ያመከክታክታል?
ለምንስ ጥቅም ነው የሚውለው?የህግ አስገዳጅነት አረፍተ ነገር እንኳ የለው! ይህ ማለት ዩሮን
ያለምንም ህጋዊ እርምጃ አለመቀበል ይቻላል?

የወርቅ ዋጋ

ከ 1945 እስከ 1971 የሁሉም ሀገራት ገንዘብ ከዶላር ጋር የተወሰነ ዝምድና አላቸው፡፡ ዶላር
በተራው ከወርቅ ጋር እንዲሁ የተወሰነ ዋጋ ዝምድና አለው፡፡ 35 ዶላር የአንድ ጥራቱ ደህና
የሆነ የወርቅ ወቄት ዋጋ አለው፡፡ በዚህ መሰረት የትኛውም ሀገር ያለ አንድ ምርት በወርቅ
የሚተመን የተለየ ዋጋ አለው፡፡ ነገር ግን ወርቅ በራሱ እንደ አንድ ምርት በማናቸውም ሀገራት
የሚለካ የራሱ ዋጋ የለውም|፡፡ ወርቅ በራሱ ገንዘብ ነው፡፡የሚለካውም በክብደት ነው፡፡አንድ
ወቄት ወርቅ አንድ ወቄት ወርቅ ነው፡፡ ማኝኛውም የወረቅ ብዛት ያንኑ የወርቅ ብዛት እኩል
ነው፡፡35 የአሜሪካ ዶላር ከአንድ ወቄት ወርቅ ጋር እኩል ነው እንጂ የአንድ ወቄት ወርቅ ዋጋ 35
የአሜሪካ ዶላር ነው ማለት አይደለም፡፡

ወርቅ ህጋዊ አስገዳጅነት እንደ ዶላር የለውም፡፡በሀገራችን ኢትዮፕያ የማሪያቴሪዛ ወረቅ


ሳንቲሞች እስከሚኒልክ ጊዜ ነበር፡፡ ምንሊክ የራሳቸውን የወርቅ ሳንቲም ካሳተሙ በኃላ በሰው
ዘንድ አመኔታ ማግኘት ተቸግረው ነበር ፡፡ ሰዎች የወርቁን ጥራት ለመመዘን የሚጠቀሙበት
መንገድ ሳንቲሞችን ወደ መሬት በመልቀቅ እና በሚሰጡት ድምጽ ነበር፡፡ የሚኒሊክ የወረቅ
ሳንቲም በደንብ ስለማይጮህ ሰዎች ለመቀበል አይደፍሩም ነበር፡፡የወርቅ ሳንቲምም መታተም
ቀረ፡፡ አንድ አሜሪካ ያለ ግልሰብ የ 350 ዶላር ግብር ክፍያ ካለበት 10 ወቄት ወርቅ መክፈል
አይችልም፡፡ ግለሰቡ መክፈል ያለበት በዶላር ብቻ ነው፡፡ወርቅ ለሱፐርማርኬት ክፍያ ላውል
ብትል እንኳ አትችልም፡፡እስከ 1971 ድረስ ግን በመርህ ደረጃ ወርቅን ለክፍያ ማስፈጸሚያ
በጎልድ ዊንዶው የምትችልበት አሰራር ነበር፡፡ነገር ግን ሰዎች ልውውጣቸውን የሚያከናውኑት
በዶላር ስለነበረ በወርቅ የመገበያየቱ ነገር በዛም ግዜ እምብዛም ነበር፡፡ወርቅን ማግኘት
የሚቻለው በንግድ ልውውጥ ሲሆን ለግብይቱም በዶላር ክፍያ ነው፡፡ ምንም እንኳ አንድ ወቄት
ወርቅ 35 ዶላር ቢሆንም ከወርቅ ግብይቱ ጋር ተያያዥነት ያላቸው ወጪዎችና ትርፍን
ሲታከልበት ወርቅ የሚሸጠው በ 35 ዶላር ሳይሆን በተለየ ከፍ ባለ ዋጋ ነበር ፡፡

ልክ እነደ አንድ ምርት ወርቅ በዚህ ሂደት የራሱ ዋጋ (ከ 35 ዶላር ዋጋ የተለየ) ኖረው፡፡ ህዝቡም
ወርቅን አንደ እንድ ምርት ይቆጥረው ጀመር፡፡ ምንም እንኳ ወርቅ ከ 35 ዶላር የተለየ ዋጋ
ቢኖረውም ዋጋው ያን ያህል ክፍተት ያለው አልነበረወም፡፡ አስደንጋጭ የወርቅ ዋጋ ልዩነት
የታየው በ 1971 በአንዴ ሲለጠጥ ነው፡፡ ከዚያን ጊዜ በኃላ የወርቅ ዋጋን ወደላይ ከመምዘግዘግ
የሚያግደው ነገር አልተገኘም፡፡ በ 2019 የወርቅ ዋጋ 1,526.00 ዶላር ለአንድ የወርቅ ወቄት
ደርሷል፡፡
ትልቁ ጥያቄ የወርቅ ዋጋ ነው ወደላይ እየወጣ ያለው ወይስ የዶላር ዋጋ እየወረደ?ይህ ጥያቄ
ሲነሳ አይስተዋልም፡፡ የወርቅ ዋጋ ወደላይ የወጣው ወርቅን ፈላጊ በመብዛቱ ነው ( አቅርቦቱ
አነስተኛ በመሆኑ) ወይስ ገንዘብ ዋጋው እየወረደ? ይህን በምሳሌ እስኪ እንየው፡፡ሁለት ጎን
ለጎን ወይም ትይዩ በሆነ አቅጣጫ የቆሙ መኪናዎች ቢኖሩ እና በአንዱ መኪና አንተ
ተቀምጠኃል እንበል፡፡ የዛኛው መኪና ሾፌርን ማየት በማትችልበት ሆኔታ መኪናው መንቀሳቀስ
ቢጀምር ላንተ የሚሰማህ ያንተ መኪና ሳታስበው ዕየተንቀሳቀሰ ነው የሚመስልህ፡፡ የዶላር እና
የወርቅ ጉዳይም እንዲህ ነው ማናቸው፡፡ እንደቀነሱ ወይም ማናቸው እንደጨመሩ ለማወቅ
ትቸገራለህ፡፡የጨመረው የወርቅ ዋጋ ነው ወይስ የገንዘብ ዋጋ ነው የወረደው?

የዋጋ ግሽበት ምንድን ነው?እንዴት ይለካል ?ሸሪአ ስለግሽበት ምን ይላል?

የዋጋ ግሽበት ምንድን ነው?

የአንድ ዳቦ ዋጋ አንድ ብር ነው እንበል፡፡ ከአንድ አመት በኃላ የዚህ ዳቦ ዋጋ አንድ ብር ከሀያ


ሳንቲም ሆነ፡፡ የአንድ ዳቦ ዋጋ ከአንድ አመት በሃላ በ 20 ሳንቲም ጨመረ ማለት ነው፡፡በሌላ
መልኩ የዳቦው ዋጋ በ 20 ፐርሰንት ጨመረ ማለትም ይቻላል፡፡ይህ የዳቦን ዋጋ በመቶኛ
መጥቀስ እንደማለት ነው፡፡ይህን የዋጋ ጭማሪ ዋጋ ግሽበት ጋር ማዛመድ ይቻላል፡፡ አንድ ዳቦ
ለመግዛት አምና ከነበረው ዋጋ ላይ ተጨማሪ 20 ፐርሰንት ገነዝብ ስፈልጋል፡፡ይህ የዋጋ ግሽበት
ይባላል፡፡በሌላ መልኩ ገንዘብ የመግዛት አቅሙ ተዳከመ ማለት ነው፡፡አንድ ብር ከአንድ አመት
በፊት ሊገዛ ከሚችለው ዳቦ ያነሰ ክብደት ያለው ዳቦ ነው ሊገዛ የሚችለው፡፡

የዋጋ ግሽበት እንዴት ይለካል?

የዳቦን የዋጋ ግሽበት 20 ፐርሰንት ተመልክተናል፡፡ ይህ ግሽበት የዳቦ ብቻ ነው፡፡ ዳቦ ብቻ


አይደለም የምንመገበው፡፡ሁሉንም ገንዘባችንን ደግሞ ለዳቦ ብቻ አይደለም የምናውለው፡፡
ስለዚህ የገንዘባችንን አጠቃላይ ዋጋ ግሽበት ለማውቅ ገንዘባችንን ያፈሰስንበት ሁሉንም
የምንበገበውን የምርት አይነት (የዳቦ፤እንጀራ፤ሩዝ፤ስጋ
፤እንቁላል፤አሳ፤አትክልቶች፤ዘይት፤ቅመማቅመም፤ወተት፤በርበሬ፤ሻይ
ቀረጠል፤ቡና፤ሌሎችንም) የዋጋ ለውጥ ማወቅ አለብን፡፡ የምግቡን አይነት ለመዘርዘር ከባድ
ነው፡፡

ለአሁን ለቤተሰባችን የምንገዛውን ለአንድ ወር አስቤዛ የምግብ አይነቶች ላይ ብቻ እናተኩር፡


በመቀጠል በዚህ ወር ልንገዛቸው የምንችላቸውን የምግብ አይነቶችን እንመዘግባለን፡፡
እያንዳንዱን ምግብ አይነት ስንገዛ የገዛነውን የምግብ ጥራት ብዛት ዋጋ እና ከየት እንደገዛን
መመዝገብ ይኖርብናል፡፡በወሩ መጨረሻ ለምግብ ያወጣነውን ዋጋ በአጠቃላይ እንደምራለን፡፡
ላለፈው ወር ብር 500.00 ብር አወጣን እንበል፡፡በቀጣዩ ወር ባለፈው የገዛነውን የምግብ አይነት
በአጠቃላይ አንድ አይነት ጥራት፤ከተመሳሳይ ቦታ፤ እና ዝርዝር እንገዛለን፡፡አጠቃላይ የዚህ ወር
ጠቅላላ ድምር ከበለጠ የዋጋ ግሽበት ይሆናል፡፡ ከባለፈው ወር ዋጋ ከአሁኑ ዋጋ በመቶኛ
የተሰላው የዋጋ ልዩነት የዋጋ ግሽበት ነው፡፡ ለዚህ ወር ያወጣነው ገንዘብ ብር 525 ቢሆን የዋጋ
ጭማሪ አለ ማለት ነው፡፡የዋጋ ጭማሪው ብር 25 (525-500) ሲሆንበመቶኛ
ደግሞ(100*25/500) = 5% ነው፡፡ይህ 5% ካለፈው ወር የዋጋ ለውጥ (ግሽበት) ነው፡፡

በተለምዶ ወር ከወር የሚመዘገበው የዋጋ ግሽበት አንድ አይነት ሊሆን አይችልም፡፡ አንዳንዴ
ምንም ለውጥ ላይኖር ይችላል፡፡ ሌላ ጊዜ ደግሞ ከፍም ዝቅም ሊል ችላል፡፡ አልፎ አልፎ ደግሞ
ልዩነቱ ኔጌቲቭ ሊሆን ይችላል፡፡በዋናነት የወቅቶች መፈራረቅ ለልዩነቶች እንደምክንያትነት
ይነሳል፡፡ ፍራፍሬ እና አትክልት በጣም ሚወደዱበት እና የሚረክሱበት ወቅቶች ይለያያል፡፡
የየወራቶች ልዩነት ተደምሮ የአመት ውጤት እናገኛለን፡፡በአመቱ መጨረሻ አጠቃላይ የምግብ
ፍጆታችን ብር 620 ቢሆን የዋጋ ለውጡ ብር 120 ነው፡፡ የመቶኛ ስሌቱ ደግሞ 100*120/500
=24% ይሆናል፡፡ 24%ን ለ 12 ብናካፍለው የምናገኘው 2 ፐርሰንት አማካይ ወርሃዊ የዋጋ
ግሽበት ነው፡፡

ይህ ያገኘነው ውጤት የዋጋ ግሽበት ልንለው እንችላለን?መልሱ እንድም አዎ ሁለትም


አይደለም ነው፡: አዎ ያልንበት ያገኘነው ውጤት የምግብ ነክ የዋጋ ግሽበት ለ አንድ ቤተሰብ እና
ወጪያቸውን መለካት በመቻላችን ነው፡፡ በአንድ ሀገር በአንድ ከተማ በአንድ አካባቢ ያሉ
ቤተሰቦች አንድ አይነት የምግብ ልማድ፤ ( ከብዛት፤ከጥራት እና ስብጥር) ስለማይኖራቸው ይህ
ስሌት የአንድ ሀገር ዋጋ ግሽበትን አይገልጽም፡፡

የአንድ ሀገርን የዋጋ ግሽበት ለማወቅ ከፈለግን የእያንዳንዱን ቤተሰብ የምግብ ፍጆታ ወጪ
በተመለከተ ሰፋ ያለ መረጃ በየሳምንቱ፤ በየወሩ ወይም በየአመት መሰብሰብ ይኖርብናል፡፡
ይህን ለማድረግ በጣም አስቸጋሪ ነው፡፡ በመሆንም ልዩልዩ እሳቤዎችንና የአማካይ ስሌቶችን
መጠቀም ብቸኛ አማራጭ ነው፡፡

የምግብ ፍጆታ ዋጋ ማውጫ ስሌት እንዴት ይሰላል?

የመጀመሪያ ስራ መሆን ያለበት የህዝብን የምግብ ልማድ ማጥናት ነው፡፡ የሁሉንም ቤተሰብ
ጸባይ ማጥናት ስለማይቻል በስታስቲክስ የማጥናት ዘዴን እንጠቀማለን፡፤ በዚህ ዘዴ የተወሰነ
ቤተሰብ ወይም አባወራ ይመረጣሉ፡፡ ይህም በስታስቲክስ ሳምፕል ይባላል፡፡ እነዚህ የተመረጡት
ቤተሰቦች የአንድ ሀገርን ቤተሰብ የምግብ ልማድ ይገልጻሉ በሚል እሳቤ ነው፡፡የምንመርጣቸው
የቤተሰብ ብዛት ለጥናቱ በሚወጣው ወጪ እና ጊዜ ሊወሰን ይችላል፡፡ በሌላ መልኩ የቤተሰቡ
አይነት አዛውንት፤ወጣት፤ብዙ ልጅ ያለው ቤተሰብ፤ አንድ ልጅ ያለው ቤተሰብ እና የመሳሰሉት
እሳቤዎችም ተጽእኖ አላቸው፡፡የቤተሰቡ ማህበራዊ ስብጥርም ሌላው መመዘኛ ነው፡፡
የቤተሰቡ የገቢ ሁኔታ፤ ሀይማኖት እና ባህል የቤተሰብን ምግብ ልማድ ሊወስኑ የሚችሉ ሌሎች
ምክንያቶች ናቸው፡፡ከላይ የዘረዘርናቸው ምክንያቶች በአንድ ሀገር ላይ ተመሳሳይ ጸባይ ያለው
ከሆነ የምንመርጣቸው የቤተሰብ ብዛት ጥቂት ሊሆኑ ይችላል፡፡ በዚህ ተቃራኒ ከሆነ ደግሞ
የሚመረጡት ቤተሰብ ብዛት ከፍ ማለት አለበት፡፡

የአንድ ሀገር የዋጋ ግሽበትን ለመለካት የምንፈልግ ከሆነ ገጠራማውን ከከተማ፤አነስተኛ ከተማ
ከትላልቅ ከተማ፡ተራራማ አካባቢን ከሜዳማ አካባቢ፡የኢንዱስተሪ ከተማን ከግብርና ከተማ
እና ሌሎችም ምክንያቶችን ከግምት ውስጥ ማስገባት አለብን፡፡

ለጊዜው መለካት የፈለግነው በአንድ ከተማ ያሉ 1000 አባዋራን ብቻ ታሳቢ እናድርግ፡፡የነዚህን


አባወራ የምግብ ልማድ ለአንድ አመት በማጥናት ሙሉ መረጃ እንዳለን ታሳቢ እናድርግ፡፡የነዚህ
ተመራጭ ቤተሰቦች አማካይ የምግብ ፍጆታ እንደመለኪያ እንጠቀመዋለን፡፡ የቤተሰብ አባወራ
መረጣ በየወሩ ማድረግ ከወጪም ሆነ ከጊዜ የማይታሰብ ነው፡፡ አመቱን በሙሉ ግምገማው
የወቅቶች መፈራረቅ የሚያስከትለው ለውጥ ካለ ከግምት ውስጥ መግባት አለበት፡፡ ይህ
የተጠናው አመት የመሰረተ አመት በመባል ይታወቃል፡፡የዚህ መሰረተ አመት መለኪያ እንደ
መመዘኛ በመሆን ለብዙ አመት ያገለግላል፡፡ የመሰረተ አመትን ለመለወጥ የሚያስገድድ
ምክንያት እስከሌለ ድረስ መለኪያ በመሆን እስከ አስር አመት ድረስ ሊያገለግል ይችላል፡፡
መሰረተ አመቱን ለመለወጥ ከሚያስገድዱ ምክንያቶች መካከል የህዝቡ የምግብ ልማድ
አይነተና ለውጥ ከታየ ብቻ ነው፡፡

ለተከታታይ ቀጣይ አመታትም የሚታዩ የምግብ ፍጆታ ዋጋን መሰረት በማድረግ ብቻ መረጃ
ይሰበሰባል፡፡

የተመረጡት አባወራዎች የመሰረተ አመት የምግብ አማካይ ፍጆታ ብር 5000.00 ቢሆን ይህ


የ 100 ማውጫ በመባል ይገለጻል፡፡በቀጣይ አመታት የሚመዘገብ ከዚህ ከመሰረተ አመት ጋር
በመቶኛ እናሰላለን፡፡ ለምሳሌ በቀጣይ አመት የተመዘገበው የምግብ ፍጆታ አማካይ ዋጋ ብር
5600.00 ከሆነ የዛ አመት የዋጋ ማውጫ (100*5600/5000) =112% ይሆናል፡፡ ይህም የ 12
ፐርሰንት ጭማሪ ከባለፈው አመት ሲሆን ይህም ከባለፈው አመት ሲነጻጸር ዋጋ ግሽበት
በምግብ ፍጆታ የታየ ይሆናል፡፡

በሁለተኛ አመት የዚህ አባወራ ወጪ ብር 6000.00 ቢሆን የዋጋ ማውጫው 100*6000/5000


=120 ይሆናል፡፡ የዋጋ ማውጫው ከባለፈው አመት 112 ወደ 120 ተለወጠ ማለት ነው፡፡
በመሆኑም የዋጋ ለውጡ 100*(120-112)/112 ወይም 7.14 ፐርሰንት ነው፡፡ ይህም የዋጋ ግሽበት
ነው፡፡

የዋጋ ማውጫ፤ የዋጋ ለውጥ እና የለውጥ መቶኛ ልዩነትን መገንዘብ ተገቢ ነው፡፡ ማውጫው
ከ 100 ወደ 112 በመጀመሪያ አመት እና ከ 112 ወደ 120 በሁለተኛው አመት ነው፡፡ይህም ማለት
ማውጫው ወደ 12 በመጀመሪያ አመት ከፍ ሲል በ 8 ነጥብ በሁለተኛው አመት ከፍ ብላል፡፡
ነገር ግን የዋጋው መቶኛ የተለወጠው በመጀመሪያ አመት በ 12 ፐርሰንት ሲሆን በሁለተኛው
አመት ግን 7.14 ፐርሰንት ነው፡፤የዋጋው መቶኛ ለውጥ የዋጋ ግሽበት ነው፡፡

እስካሁን እያሰላን ያለው አማካይ የአባወራዎችን አጠቃላይ የምግብ ወጪያቸወን ነው፡፡


የትኛው የምግብ ዝርዝሮችን ነው የምንጠቀመው? ይህን የምግብ ቅርጫት ብለን ብንጠራው
ምን አይነት የምግብ ዝርዝር ነው በቅራጫቱ የምናጠራቅመው፡፡ እንዲሁም ምንያህል የምግብ
አይነት?የነዚህን ጥቄዎች መመለስ ተገቢ ነው፡፡ይህን መረጃ ለማጠናከር ሌላ መረጃዎች
ያስፈልገናል፡፡ የቡድን አባቶች በቅርጫቱ ላይ በመመዝገብ እንጀምራለን፡፡ ለምሳሌ
ዳቦ፤ሩዝ፤ስጋ፤አሳ፤ወተት ነክ ምርቶች፤አትክክልት፤መጠጥ እና ሌሎችም፡፡ ከዚህ በመቀጠል
በእያንዳንዱ የቡድን አባቶች የሚገኙትንም በዝርዝር እንመዘግባለን፡፡ ለእያንዳንዱ የቡድን
አባት በአአጠቃላይ የምግብ ድርሻ ያላቸውን ድርሻ እንሰጣለን፡፡ ለምሳሌ ዳቦ 0.08 ፤ ሩዝ .06
ስጋ 0.050 እያልን ለሁሉም ከሰጠን በኃላ የሁሉም ድርሻ አጠቃላይ ድምር 1 ሊሆን ይገባል፡፡

የመረጃ አሰባሱ ሌላው አሳሳቢ ጉዳይ ነው፡፡ ብርቱካን በመኪና በኩንታል በተለያየ ጣእም በልዩ
ጸባይ እና የተለያየ ዋጋ አለው፡፡ብርቱካኑ የሀገር ምርት ሊሆን ይችላል አልያም ከውጭ
ኢምፖርት ተደርጎ ሊገባ ይችላል፡፤ከውጭ ሲገባም ከተላያየ ሀገር በተለያየ ዋጋ ሊመጣ
ይችላል፡፡ብርቱካኑ በነጠላ ፡በኪሎ ወይም በኩንታል ሊሸጥ ይችላል፡፡የምናወራው ብርቱካን
ጥሬውን የሚበላ እንጂ ጨምቁ ወይም በሌላ ሂደትን የተቀየርን አይደለም፡፤ልዩ ልዩ አምራቾች
አስመጪዎች አከፋፋዮች ብርቱካኑን የሚሸጡት በራሳቸው ዋጋ ነው፡፡ በተጨማሪም
ብርቱካንን ከሱፐርማርኬት ከግሮሰሪ ከአዝዋሪ እና በሌላ መልኩ ልናገኘው እንችላልን፡፡
በመሆኑም ከላይ የዘረዘርናቸውን ሁኔታዎችን የዋጋ መረጃ በምንሰበስብበት ጊዜ ከግምት
ውስጥ ሊገባ ይገባል፡፡

መረጃው የሚሰበሰብበት ጊዜም እንዲሁ ሊተኮርበት ይገባል፡፡ መረጃው በየቀኑ፤በሳምንት አንድ


ወይም ሁለት ጊዜ 52 ሳምንት በአመት ልንሰበስብ እንችላልን፡፡ በሰታስትኪስ ፊልድ ኢፊሰሩ
የተሰበሰበው መረጃ በድጋሚ በአለቃው ይረጋገጣል፡፤ የሁሉም መረጃ ሰብሳቢ ኢፊሰሮች
የሰሩት ስሌት በድጋሚ መረጋገጥ አለበት፡፡ በመጨረሻ በስታቲሽን የስሌት ስህተት አለመኖሩ
ይረጋገጣል፡፡ይህ ሁሉ ጊዜ ይፈጃል፡፡የተጠቃሚ/የበላተኛ/ ዋጋ ማውጫ በዚህ አይነት በየወሩ
ይገለጻል፡፡ ስራው ጊዜ ስለሚወስድ መጀመሪያ የመጀመሪያ ርፖርት ከወጣ በኃላ የመጨረሻ
ሪፖርት ከጊዜ በኃላ ይሰራጫል፡፡

በማደግ ላይ ባሉ ሀገራት ያላቸው ኢንፋራስትራክቸር ፤ የስታስቲክስ ሀብት ማነስ እና


ውስብስብነት የሚያቀርቡት ሪፖርት ትክክልኘንት አናሳ እና የሚወስድባቸው ጊዜም የረዘመ
ነው፡፡

የግሽበት መንስኤዎች
1. ዋነኛ የግሽበት መንስኤ የሚከሰተው የመንግስት ወጪ በሚጨምርበት ጊዜ ነው፡፡
ይህንንም የበጀት ጉድለት ለመሙላት መንግስት ገንዘብ ያትማል፡፡ የታተመው ገንዘብ
አቅርቦት ሲጨምር ግዥ ይበረክታል፡፡ ለዚህ ግሽበት ተጠያቂ መንግስት ነው፡፡
በታዳጊ ሀገር ከውጭ ሀገር የሚላክ ገንዘብ ባለበት ሀገር የተላከውን ገንዘብ ህዝቡ
ለግል ፍጆታ የሚያውል ከሆነ ግሽበትን ያስከትላል፡፡በዚህ ጊዜ ደግሞ ተጠያቂ
የሚሆነው ተጠቃሚው ነው፡፡
2. ሌላው መንስኤ ደግሞ የአቅርቦት እና የፍላጎት መጠን ባለመጣጣም የሚመጣ
ግሽበት ነው፡፡ይህ አለመጣጣም በህዝብ ብዛት መጨመር እና የከተሞች
መስፋፋት እንደምክንያትነት ይጠቀሳሉ፡፡ለዚህ ጉዳይ ዋነኛ ተጠያቂ ማህበረሰቡ
ነው፡፡በሌላ መልኩ የአቅርቡት እጥረት ሌላው ምክንያት ነው፡፡የአቅርቦት እጥረቱ
የተከሰተው በራሱ ጊዜ ተፈጥሮን ተጠያቂ ከማድረግ ውጭ አማራጭ የለም፡፡
3. የዋጋ ግሽበት በደመወዝ ጭማሪ ፤ መንግስት ቀጥተኛያልሆነ ታክስ ሲጭን
(በቅርቡ ያረጁ መኪናዎች ቅንስናሽ በመነሳቱ ምክንያት የመኪና ዋጋ መጨመሩ
ይታወሳል)፤ ስግብግብ ነጋዴዎች ከመጠን ያለፈ ትርፍ ለማጋበስ በሚያደርጉት
ድርጊትም ግሽበት ሊከሰት ይችላል፡፡ የነጋዴዎች ማህበር፡መንግስት እና ነጋዴው
ለእነደዚህ አይነት ጭማሪዎች ተጠያቂዎች ናቸው፡፡
4. በአለም አቀፍ ጉዳዮች የገንዘብ ዲቫሊዌሽን በሚኖርበት ጊዜም የዋጋ ግሽበት
ይከሰታል፡፡
5. አንዳንድ ጊዜ የዋጋ ግሽበት ከሌላ ሀገር ኢምፖረት ልናደርገው እንችላልን፡፡
6. ባንኮች ብድር በሚሰጡበት ጊዜ ግሽበት ይከሰታል፡፡ በዚህ ጊዜ ባንኮች
ተጠያቂዎች ናቸው፡፡

በአጠቃላይ ለዋጋ ግሽበት አንድን ወገን ብቻ ተጠያቂ ማድረግ አይቻልም፡፡

የሸሪአህ ህግ ለዋጋ ግሽበት ካሳ ክፍያ ምን ይላል?

ለሰራተኛው የተወሰነ ደመወዝ በመክፈል የዋጋ ግሽበትን መካስ ይቻላል፡፡መንግስት


አነስተኛ የደመወዝ ስኬል ሊመድብም ይችላል፡፡ በብድር ለሚከሰት ግሽበት ሸሪአህ
ያስቀመጠው ህግ ብድር ሲከፈል ያለምንም ተጨማሪ ወለድ መሆን አለበት ይላል፡፡ ይህም
በቁርአን 2፡279 ይደግፋል፡፡ከሂድስ መረጃ ደግሞ የገንዘብ ወይም የኮሞዲቲ ብድር መከፈል
ያለበት በተመሳሳይ አይነት እና ብዛት ነው፡፡አዋቂዎች ይህንን ሀዲስ ሲመነዝሩት ዲርሀም
ወይም ዲናር ቆጥረን ካበደርን መመለስ ያለበት በመቁጠር እንጂ ክብደት በመለካት
አይደለም ይላሉ፡፡(ኢብን ቀዳማ፣ቮልዩም 4 ገጽ 318፤ሳህኑን ቮለዩም 8 ገጽ 131-132)
ሸሪዐዊ የግብሸት አተያይ
1. አንዳንድ ሰው አለምአቀፍ የዋጋ ግሽበት እያስከተለ ያለውን አደጋ ከዚህ በፊት ታይቶ
የማይታወቅ አደጋ እንደሆነና የገንዘብ የመግዛት አቅም ዕየከሰመ መሆኑንና ገንዘብ
የታለመለትን አላማ እያሳካ አይደለም በማለት ይገልጻሉ፡፡ በመሆኑም ይህንን አስከፊ
ጉዳት ለመቅረፍ ከብድር እና ወለድ ነክ በሆኑ ጉዳዮች ኢጅቲሃድ እንዲደረግ ግፊት
ሲያደርጉ ይስተዋላል፡፡
ለዚህ ትክክለኛ ምላሽ ሸሪአህ ያስቀመጠው መመሪያ ኢጅቲሃድ የግድ የሚሆነው
በቁርአንና ሀዲስ እንዲሁም በሌሎች የሸሪአህ ምንጮች በግልጽ (ናስ) ላልተቀመጠ ነገር
ነው፡፡ በመሆኑም በናስ (በግልጽ) ለተቀመጠ ህግ እጂትሀድ ሊደረግ አይገባም፡፡
2. ነብዩ (ሰ.አ.ወ) ጉዳት ማድረስ የለብንም ጉዳት እንዲደርስብንም አይገባም የሚለውን
ሀዲስ (ላ ዳራር ወላዲራረ) ይጠቅሳሉ፡፡በዚህም መሰረት አዋቂዎች ጉዳት ሊካስ
ይገባል( አል ደራር ዩዛል)(ኢብን ኑጃያም ገጽ 58) ፡፡
ዋጋ ግሽበት ለአበዳሪ እና ለአስቀማጩ ጉዳት ነው ፡፡ በመሆኑም በኢንዴክሴሽን ሊካስ
ይገባል ይላሉ፡፡
የህንን ጉዳይ ለመመለስ የሸሪአህ የካሳ ክፍያ ህግጋትን ማየቱ ተገቢ ነው፡፡ህጉ ጉዳት
አድራሽ ካሳ ክፍያ ከፋይ ነው ይላል፡፡ ከላይ እንዳየነው ለዋጋ ግሽበት ተጠያቂዎቹ
መንግስት፤ማህበረሰቡ፤ተመጋቢው፤ተፈጥሮ፤የነጋዲዎች ማህበር ፤ነጋዴዎች ወይም
አለም አቀፍ ምክንያቶች እንደሆኑ አይተናል፡፤በአብዛኛው ሁሉም ምክንያቶች በአንድ
ላይ ተጠያቂ የሚሆኑበት ጊዜም አለ፡፡ ጥያቄው እንዴት ነው ከነዚህ ምክንያቶች
በመነሳት ተጎጂውን የምንክሰው የሚለው ነው፡፡ ነጋዴው ተጠያቂ በሚሆንበት
ምክንያት እንዴት ነው ባንክ የግሽበት ካሳ እንዲከፍል የሚገደደው፡፡በሌላ መልኩ
ተበዳሪው የሚከፍለው በዋጋ ግሽበት ማካካሻ እሳቤ ስር ይወድቃል፡፡
በአንዳንድ ሀገራት ኢንዲክሴሽን በመንግስት ቦንድ ግዢብቻ የተገደበ ነው፡፡ይህ ማለት
መንግስት የሚክሳቸው የቦንድ ባለቤቶችን ብቻ ነው፡፡ጥያቄው ገንዘባቸውን ለረዥም
ጊዜ በቦንድ ግዢ የሚያውለቱን ብቻ ክሶ ሌሎችን መተው ፍትሃዊ ነው?ሌላው ጥያቄ
እነዚህ የቦንድ ባለቤቶች በማን ገንዘብ ነው የሚካሱት?መንግስት ባብዛኛው ገቢው
በግብር ነው፡፡ይህ ማለት ህብረተሰቡ በአጠቃላይ የግሽበት ተጠቂ ሆኖ ሳለ ከማህበረሰቡ
በተሰበሰበ ግብር ነው የቦንድ ባለቤቶች ብቻ የሚክሰው፡፡ ይህ ፍትሀዊ ነውን?
3. መንግስት ለዋጋ ግሽበት ተጠያቂ በማድረግ ካሳውን ሊከፍል ይገባል የሚል ነጥብም
ይነሳል፡፡ ከላይ እንዳየነው መንግስት ያስከተለውን ጉዳት በማያሻማ መልኩ ማውቅ
በጣም ከባድ ነው፡፡
ለዚህ ጥያቄ መልስ የሚሆነው ሶስት መሰረታዊ መርሆችን በማወቅ ነው፡፡ ጉዳቱ
ወደፊት በትልቅም ይሁን በትንሽ ጉዳት የማይተካ ሲሆን ነው (ለ ዳራር ላ ዩዛል
ቢሚስሊሂ) ፤ ሁለተኛው አነስተኛ ጉዳት የከፋ ጉዳትን ለማጥፋት ሲባል መቋቋም (ለ
ዳራር ለ ሸድ ቢል ዳራር ለ አኻፍ) ነው፡፡ ሶስተኛው ደግሞ የተለየን ጉዳት ለአጠቃላይ
ጉዳት ሲባል መቻልን (ዩተሀመል ለ ዳራር ለ ኻስ ሊ ዳፍ ለ ዳራር አል አም)
ያስገነዝበናል፡፡ -ኢብን ኒጃም ገጽ 58/
መንግስት የሚሰራቸው ስራዎች በአጠቃላይ ለማህበረሰቡ ነው ፡፡ የበጀት ጉድለቱን
በመሙላት የሚሰራቸው ዘርፈ ብዙ ስራዎች ለአንድ ሀገር የስራ ቅጥር፤ልዩ ልዩ የህዝብ
መገልገያዎችዎች የሚውሉ ንብረቶችና ለህዝብ ጥቅም የሚውሉ መጠቀሚያዎች
ጉዳይ ነው የሚያውለው፡፡ይህንን መቃወም ለአንድ ሀገር ኃላቀርነት መንስኤ
እንደመሆን ነው፡፡ መንግስት የበጀት ጉድለትን እንዳይሞላ ፍላጎታችን ከሆነ ልዩልዩ
የልማት ስራዎችንና የሀገር መከላከል ስራዎችን ባግባቡ እንዳንከውን ያደርገዋል፡፡
4. ሌላው የሚነሳው መከራከሪያ ነጥብ የገንዘብ ዋጋን በተመለከተ ነው፡፡ የገንዘብ ዋጋ
ውስጣዊ ጥቅም አንጻራዊ ቃል ነው፡፡ገንዘብን በመጠቀም የተቀላጠፈ ግብይት መስጠቱ
በራሱ እንደ ውስጣዊ ጥቅም ሊገለጽ ይችላል፡፡ አሞሌ ጨው ፤ ወርቅ እና ሌሎች
መሰል ገንዘብ ሆነው ሲያገለግሉ በራሳቸው ሚሰጡት ጥቅም ቢኖረም ንግድን
ለማቀላጠፍ የራሳቸው እክል ነበራቸው፡፡ ይህንን እክል የቀረፈው ገንዘብ ነው ፡፡ ይህን
ጥቅሙን እንደውሳጣዊ የገንዘብ ጥቅም ሊታይ ይገባል፡፡ዋናውን እያጣ የሚሄደው
የገንዘብ የወደፊት ዋጋ ነው ፡፡ ለዚህ ደግሞ ተጠያቂው ማነው ? በእርግጠኝነት
መገበያያው አይደለም፡፡
5. የተጠቃሚ ቅርጫት በመጠቀም የምናገኘው ስሌት ችግር ያለበት ነው፡፡ ምዘናው
የአማካይ ግለሰብን የተጠቃሚነት ልማድ እንጂ የሆሉንም ማህበረሰብ ትክክለኛ የምዘና
ውጤት አይደለም፡፡

ግሽበጽ የህግ አንቀጽ የማያውቀው የዝርፍያ ድርጊት መሆኑ እሙን ነው፡፡ ሆኖም
ድርጊቱን አጨቃጫቂ እና አጠራጣሪ በሆነ መንገድ ለማከም ከመሞከር ይልቅ ሸሪአዊ
በሆነ መንገድ መፍትሄ መሻት ይገባል፡፡ ከዚህ ቀደም በቺሊ የሆነውን እርምጃ ማየቱ
ጠቃሚ ነው ፡፡ ቺሊ መንግስ የመንግስት ወጪን በማስተካከል እና የውጭ ሀገራት ገንዘብ
ምንዛሪ ማስተካከሉ ግሽበትን መቀነስ ችላለች፡፡

You might also like