You are on page 1of 25

“ይህን በመጀመሪያ እወቁ ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም…” (2 ጴጥ.

1፡20)

Praise Practical Theology and Leadership College

Hermeneutics

Compiled by

Eva. Zena Bekele 2014

የትምህርቱ ዓይነት ሥነ አፈታት፡ (Hermeneutics)

1
“ይህን በመጀመሪያ እወቁ ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም…” (2 ጴጥ.1፡20)

የትምህርቱ ዓላማ

የዚህ ኮርስ ዋና ዓላማ መጽሐፍ ቅዱስን ለሁለንተናዊ ጥቅም ለመረዳት የሚያግዙ መሮሆዎችን በማቅረብና በማብራራት

ተማሪዎች መጽሐፍ ቅዱስን ታማኝነት በተሞላበት መንገድ በመተርጎም በሕይወታቸውና በአገልግሎታቸው ተግባራዊ

እንዲያደርጉት ማበረታታት ነው፡፡

የትምህርቱ አጭር ገለጻ፡-የዚህ ኮርስ ትኩረት በዋናነት የሥነ አተረጓገምን (Hermentuics)ችግርን በተመለከተ መጽሐፍ

ቅዱስ ለእኔ ምን ይላል ከማለታችን በፊት መጽሐፍ ቅዱስ ለቀድሞዎቹ ተቀባዮች ምን ብሎ ነበር ብሎ በመጠየቅ

ከሐቲት(Exgesises) በመጀመር እና ለዛሬውስ ምን ዓይነት ትርጉም ይሰጣል የሚልን መርህ በመከተል ተማሪዎች

መጽሐፍ ቅዱስን ሁለንተናዊ በሆነ መንገድ በመረዳት በግል ሕይወታቸውና በአገልግሎታቸውም እንዲተገብሩ ማበረታታት

ነው፡፡

የትምህርቱ ማስተማሪያ

 መጽሐፍ ቅዱስ

 መጽሐፍ ቅዱስን ለሁለንተናዊ ጥቅሙ ማጥናት፡ ከጎርደን ዲ.ፊ. እና ዳግላስ ስቱአርት SIM ማተምያ፡

USA:1993

የትምህርቱ ክፍለ ጊዜ መርሀ ግብር

ቀን ርዕስ(ይዘት) የመማር ማስተማር የተግባራዊ ሥራዎችና አስተያት(comment


ግምገማዎች
ቅዳሜ  ጥቄና መልስ
 Introduction of  ውይይት

2
“ይህን በመጀመሪያ እወቁ ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም…” (2 ጴጥ.1፡20)

the course
 የመተረጎም
አስፈላጊነት
 ለትርጉም መሠረታዊ
መሣርያ
 መልእክቶች ዓውደ  ጥያቄና ሙከራ 1(10%)
ንባባዊ አስተሳሰብ መልስ
 መልእክቶች የሥነ  ውይይት
አፈታት ጥያቄዎች  ገለጻ
 የብሉይ ኪዳን  ጥያቀና
ትረካዎችና ተገቢ መልስ
አጠቃቀማቸው  ውይይት
 ገለጻ
እሁድ  የሐዋርያት ሥራ ፡-  ጥቄና መልስ
የታሪካዊ አርኣያነት  የቡድን ሥራ
ጥያቄ  ገለጻ
 ወንጌላት፡- ብዙ
አቅጣጫዎች ያሉት
አንድ ታሪክ
 ምሳሌዎች፡-  ጥያቄና ሙከራ 2(10%)
መልእክቱን አገኘህ? መልስ
 ውይይት
 ገለጻ
 ሕግ(ሕግጋት)፡-  ጥያቀና
የእስራኤል የቃል መልስ
ኪዳን ትዕዛዝ  ውይይት
 ገለጻ
ቅዳሜ  ነቢያት፡-በእስራኤል  ጥያቄና
የቃል ኪዳን መልስ
አስከባሪዎች  ውይይት
 ገለጻ
 መዝሙረ ዳዊት ፡-  ጥያቀና Relection (10%)
የእስራኤልና የእኛም መልስ
ጸሎቶች  ውይይት
 ገለጻ
 ጥበብ፡-ያኔ እና  ጥያቄና
አሁን መልስ
 ውይይት
 የዮሐንስ ራእይ፡-  የቡድን ሥራ የመጨሻው የቡድን
እሁድ የፍርድና የተስፋ ገለጻ ሥራ(Final Project)
ምስሎች  ገለጻ (30%)
የመጨረሻ ፈተና(Final)
(30%)
ጠቅላላ ዉጤት እና
አስተያየት(Feedback)

3
“ይህን በመጀመሪያ እወቁ ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም…” (2 ጴጥ.1፡20)

የማርክ አሰጣጥና የተግባር ሥራዎች

የክፍል ተሳትፎና ስም ጥሪ (Class Activities and Attendance) (10%)

Refelection Paper (10%)

የመጨረሻው የቡድን ሥራ (Final Project) (30%)

የመጨረሻው ፈተና(Final Exam) (50%)

አጠቃላይ (Total) 100% Grading

%(በቁጥር) ማርክ (grade)


97-100 A+
93-96 A
90-92 A-
87-89 B+
83-86 B
80-82 B-
77-79 C+
73-76 C
70-72 C-
67-69 D+
63-66 D
60-62 D-
ከ 60 በታች F

የስም ጥሪ ደንብ

 አንድ ቀን መቅረት አንድ ማርክ ያስቀንሳል


 ሁለት ቀን ማርፈድ እንደ አንድ ቀን ቀሪ ይቆጠራል
 ከአቅም በላይ የሆኑ ጉዳዮች ስገጥሙ መምህሩን ፈቃድ መጠየቅ ይገባል
 ያለ ፈቃድ አንድ ቀን የቀረ ይህንን ኮርስ መውሰድ አይችልም

የወረቀት ጽሑፍ ሥራ (Reflection Paper)

ተማሪዎች በክፍል ውስጥ ከሚቀርቡ የመማር ማስተማር ሥራዎች፣በጥያቄና መልስ፣በቡድን ውይይት እና ከሌሎች ተግባሮች
ያገኙትን አዲስ ዕውቀት በአንድ ገጽ ወረቀት ላይ ፍሬ ሐሳቡን ያቀርባሉ፡፡ከአንድ ገጽ መብለጥ የለበትም፡፡

ሁለት ክፍሎች ይኖሩታል

1. ያገኙት አዲስ ዕውቀት በአንቀጽ/አንቀጾች (New Understanding)


2. ያገኙት ዕውቀት እንዴት ከግል ሕይወት እና አገልግሎት ጋር እንደምዛመድ
 ግልጽ እና አሻምነት የሌለው መሆኑ የማርክ አሰጣጡን ይወስናል፡፡ስለዚህ በጣም ግልጽ በሆኑ ቃላት የተብራሩ
መሆናቸውን አረጋግጡ፡፡(Ways of Application)

4
“ይህን በመጀመሪያ እወቁ ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም…” (2 ጴጥ.1፡20)

የመጨረሻው የቡድን ሥራ (Final Project)

የመጨረሻው የቡደን ሥራ ከመልእክት ክፍሎች ቡድኑ ተስማምቶ በምመርጠው ክፍል ተመርኩዞ የሚሠራ ይሆናል፡፡ስለዚህ
የመጀመሪያው እርምጃ ክፍሉን ተስማምቶ መምረጥ ይሆናል፡፡

በመቀጠልም በክፍል ውስጥ ስለ መልእክቶች በተነጋገርነው መሠረት የመልእክቶችን ዓውደ ንባባዊ አስተሳሰብን እና
የመልእክቶችን ሥነ አፈታት ጥያቄዎችን ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት የተማሩትን ተግባራዊ ለማድረግ እርምጃ ይወሰዳል፡፡

ሦስት ክፍሎች ይኖሩታል፡-

1. ሐቲት(Exegetical idea)
2. ሥነ አፈታት(Hermeneutical idea)
3. ተዛምዶ(Application)

የማርኩ አሰጣጥ በሚከተሉት መስፈርቶች ተመሥርቶ ይወሰናል

1. የመልእክቶችን ዓውዳዊ ይዘታቸው የተጠበቁ በመሆናቸው(5%)


2. የመልእክቶችን መርሆዎችን ግንዛቤ ውስጥ ማስገባታቸው(5%)
3. ግልጽ የሆነ ሐቲት በመቀመጡ(Exegetical idea)(5%)
4. ግልጽ የሆነ ሥነ አፈታት በመኖሩ(Hermeneutical idea)(5%)
5. ግልጽ የሆነ ተዛምዶ መኖሩ (Application idea)(5%)
6. አጠቃላይ የጽሑፉ ግልጽነት እና ፍሰት Coherency of the content (5%)

የተግባራዊ ሥራዎች ደንብ (polices of Assignment)

 ሁሉም ተግባራዊ ሥራዎች በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት መጠናቀቅ አለባቸው፡፡


 ከተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ በኋላ የሚቀርቡ ሥራዎች ተቀባይነት የላቸውም፡፡
ሞባይል ወደ ክፍል እንደተገባ ድምጽ አልባ ይደረጋል፡፡

አንደኛው ቀን

የቡድን ውይይት ጥያቄዎች

1. መጽሐፍ ቅዱስን መተርጎም ለምን ያስፈልጋል?


2. የሚከተሉትን ቃላት በቡደን ተወያይታችሁ ልዩነታቸውንና አንድነታቸውን ከትርጉማቸው ጋር አቅርቡ
ሐቲት (Exegesis)
ሥነ አፈታት (Hermeneutics)
መተረጎም (Translation)
መተንተን (Interpretation)

መጽሐፍ ቅዱስን መተርጎም ለምን ያስገልጋል?

ብዙውን ጊዜ “መጽሐፍ ቅዱስን መተረጎም አያስፈልግም ዝም ብለህ አንብበውና የሚለውን ፈጽም” ሲባል መስማት
የተለመደ ነው፡፡በመጀመሪያ መገንዘብ ያለብን የመተርጎም ዓላማው ልዩ ምሥጢር መፈለግ እንዳልሆነ መሆኑን ነው፡፡
የምንባቡን ግልጽ ፍች ማግኘት ነው እንጂ፡፡

5
“ይህን በመጀመሪያ እወቁ ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም…” (2 ጴጥ.1፡20)

መጽሐፍ ቅዱስን ለመተርጎም ሁለቱ ምክንያቶች

1. የአንባቢ ባሕርይ
 አንባቢ ሁሉ ተርጓሚ ነው
 አንባቢው ሁልጊዜም በአከባቢ የሚሆነውን ከማስተዋልም ግንዛቤ ሊያገኝ ይችላል
 ሁሉም ግልጽ ፍችዎች ለሰው ሁሉ እኩል ግልጽ አይደሉም
 ለምሳሌ 1 ቆሮ.14፡34-35
2. የመጽሐፍ ቅዱስ ባሕርይ
 መጽሐፍ ቅዱስ ልክ እንደ ክርስቶስ ሰብአዊና መለኮታዊ ባህርይ አለው፡፡
 በሰው ልጆች ታሪክ፣ባህል እና ቃላት የመጣ የእግዚአብሔር ቃል ነው፡፡
 ሁለት ደራስዎችም አሉት
 እጅግ አስፈላጊ ከሆኑት ሰብአዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ገጽታዎች ለጠቅላላ የሰው ልጆች ሁኔታዎች የሚናገር
መሆኑ ነው፡፡
 እግዚአብሔር አሉ የተባሉትን የተግባቦት መንገዶችን ሁሉ ለመጠቀም መርጦአል
 እነዚህም የታሪክ ትረካ ፣ የዘር ሐረግ፣ ዜና ፣ሁሉም ዓይነት ሕግጋት፣ሁሉም ዓይነት
ግጥሞች፣ምሳሌዎች፣መልእክቶች፣ስብከቶች እና ገላጭ ትንበያዎች ናቸው
 ለ 1500 ዓመታት በተለያዩ ሰዎች እና ሁኔታዎች አልፎ መምጣቱ ትርጉም የሚሻ ያደርገዋል

የተርጓሚ ሥራዎች

1. የመጀመሪያው ተግባር ሐቲት(Exegesis)…ያኔ(then) እዚያ(there)


 ሐቲት የተፈለገውን የመጀመሪያ ፍች ለማግኘት መጽሐፍ ቅዱስን በጥንቃቄና በዘዴ የማጥናት ተግባር ነው
 የቃሉትርጉም በቁሙ መፍታተ፣መተርተር፣መግለጥ፣መክፈት፣ማውለቅ፣ማናዘዝ እንደ ማለት ነው
 የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የሚጀምረው የኤክስፔርቶችን ምክር በማስቀደም አይደለም(ለምሳሌ ሉቃስ 18፡
24-25) ላይ ብዙ ጊዜ እንደተለመደው “የመርፌ ቀዳዳ” የሚባል በር የለም፡፡

ሐቲት ለመሥራት መማር


 ለጥሩ ሐቲትና በዚያውም መጽሐፍ ቅዱስን በተሻለ መንገድ ለማስተዋል ማንበብ ቁልፍ ነገር ነው
 ምንባቡን በጥንቃቄ ማንበብና ስለ ምንባቡ ትክክለኛ ጥያቄዎችን መጠየቅ መቻል ነው፡፡
 ሁለት ዓይነት መሠረታዊ ጥያቄዎች አሉ፡-ከዓውደ ንባቡ ጋር የሚዛመዱና ከይዘቱ ጋር የሚዛመዱ ናቸው
 የዓውደ ንባቡ ጥያቄዎች ደግሞ ታሪካዊና ሥነ ጽሑፋዊ ተብለው በሁለት ይከፈላሉ
 ታሪካዊ ዓውደ ንባብ ከብዙ ነገሮች ጋር ይዛመዳል(የደራሲውና የአንባቢያኑ ባህልና ዘመን፣ፖለትካ…መጽሐፋ
እንዲጻፍ ያደረገው ሁኔታ) የመጽሐፍ ቅዱስን ንባብ ለመረዳት አስፈላጊዎች ናቸው፡፡
 ሥነ ጽሑፋዊ ዓውደ ንባብ “መልእክቱ ምንድነው ነው?” የሚልን ጥያቄ በመመለስ የሚገኝ ነው
 የይዘት ጥያቄዎች ከጸሐፍው ትክክለኛ ይዘት ጋር የሚዛድ ነው(ለምሳሌ 1 ቆሮ.5፡16 “በሥጋ” የተባለለተት ማነው?
ክርስቶስ ነው ወይስ እርሱን የሚያውቀው ሰው?)

የትርጉም አጋዥ መሣርያዎች


 የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት
 የመጽሐፍ ቅዱስ ማብራርያ
 በጥሩ ሁኔታ የተተረጎመ መጽሐፍ ቅዱስና ሌሎችንም መሣርያዎችን መጠቀም ይቻላል

6
“ይህን በመጀመሪያ እወቁ ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም…” (2 ጴጥ.1፡20)

2. ሁለተኛው ተግባር የአፈታት ጥበብ(ሥነ አፈታት)(Hermeneutics)=(አሁን በዚህ ዘመን…now here)


 ማርቆስ 16፡18 እና 3 ዮሐንስ 2 ለእኛ እንዴት ይተረጎማል እባቦችን መያዘ…ብልጽግና ነው ወይስ ሌላ
አለው
 መጽሐፍ ቅዱስን ወደ ገዛ ፍላጎታችን ጠምዝዘን ካበቃን በኋላ መንፈስ ቅዱስን ተጠያቂ ማድረግ አንችልም
 ለእኛ የሚያስተላልፈው እውነተኛ የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ፍች እግዚአብሔር መጀመሪያ በተናገረበት
ጊዜ እንዲተላለፍ የፈለገው ነው

ሁለተኛ ቀን

የቡድን ውይይት ጥያቄዎች

1. ደብዳቤ ለጓደኞቻችሁ ብትጽፉ ስንት ዓይነት ክፍሎች ይኖሩታል?


2. 1 ኛ ቆሮንቶስን እንድጽፍ ምን አነሳሳው? ስለ ሁኔታቸው እንዴት ሊያውቅ ቻለ? ከእነርሱ ጋር ምን ዓይነት ግንኙነት
ነበረው? እርሱና ተደራሲያኑ የሚያነሱት ጉዳይ ምንድነው?
3. አንዳንድ የመልእክት ክፍሎችን መረዳት የሚያቅተን ለምን እንደ ሆነ ተወያዩ

መልእክቶች ዓውደ ንባባዊ አስተሳሰብ

መልእክቶችን መተረጎም ቀላልና ከባድም ነው፡፡ይህም የሚሆነው ከመልእክቶቹ ባሕርይ ነው፡፡

7
“ይህን በመጀመሪያ እወቁ ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም…” (2 ጴጥ.1፡20)

የመልእክቶቹ ባሕርይ

1. አንድ ወጥ አይደሉም(ከቅርጻቸው አንጻር) (ገጽ.38-39)


2. መልእክቶች ሁሉ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ሰነዶች(Occasional Documents)
3. በቀዳሚነት ሥነ መለኮታዊ አይደሉም

በእነዚህ ምክንያቶች መልእክቶችን መተርጎም ከባድ ይሆናል፡፡

 ታሪካዊ ዓውድ (ምሳሌ 1 ቆሮ. )


 እንዲጽፍ ምን አነሳሳው?
 ስለ ሁኔታቸው እንዴት ሊያውቅ ቻለ?
 ከእነርሱ ጋር ምን ዓይነት ግንኙነት ነበረው?
 እርሱና ተደራሲያኑ የሚያነሱት ጉዳይ ምንድነው?

የእነዚህን ጥያቄዎች መልስ ለማግኘት (ገጽ 44-45)

 ስለ ቆሮንቶስና ስለ ሕዝቦቿ የተቻለህን ሁሉ ለማወቅ ለሎች መሣርያዎችን ሁሉ መጠቀም


 ጠቅላላውን ምንባብ በአንድ ጊዜ የማንበብ ልማድ ማዳበር

አስቸጋሪ ምንባቦችን ለመፍታት አንዳንድ ጣቃሚ መመሪያዎች

1. ብዙውን ጊዜ ምንባቦቹ የሚከብዱን እውነቱን ለመናገር ለእኛ የተጻፉ ባለመሆናቸው ነው


2. አንዳንዶችን በትክክሉ መረዳት ባንችልም የጠቅላላውን ምንባብ መልእክት ልንረዳ እንችላለን(ሰለ ሙታን
መጠመቅ)15፡29
3. ግልጽ ያልሆኑትን ለይቶ ማወቅ
4. ጥሩ የማብራሪያ መጽሐፍትን መመልከት

መልእክቶች የሥነ አፈታት ጥያቄዎች

ለመልእክቶች ሥነ አፈታት ምን ዓይነት መመሪያ ያስፈልጉናል

1. አንድ ምንባብ ለደራሲው ወይም ለተደራሲያኑ ያስተላለፈውን መልእክት ለእኛ ማስተላፍ አይችልም፡፡ ለዚህም ነው
ሁልጊዜም ከሐቲት መጀመር ያለብን፡፡
2. ከመጀመሪያው ምዕተ ዓመት መቼት ጋር በሚጣጣም ሁኔታ ውስጥ በሚንሆንበት ጊዜ ለእኛ የሚለው
የእግዚአብሔር ቃል ለእነርሱ ያገለገለው ነው፡፡ ሮሜ 3፡23፣ኤፌ 2፡8 እና ቆላ.3፡12 ዛሬም ያው ነው

የተዛምዶ መስፋፋት ችግር፡ የማይዛመድ ነገር ማዛመድ የለብንም

የባህል አንጻራዊነት ችግርን ለመለየት የሚከተሉትን መመሪያዎችን ይመልከቱ


1. መጀመሪያ የመጽሐፍ ቅዱስን ማዕካለዊ መልእክት እርሱ ላይ ከተደገፈው መለየት ለምሳሌ (1 ቆሮ.15)ስለ ትንሳኤ
ሲሆን ቁ.29 እርሱ ላይ የተደገፈ ነው
2. በተመሳሳይ አዲስ ኪዳን እንደ ጥብቅ የሥነ ምግባር ክፍል አድረጎ የሚወስደውንና የማይወስውን መለየት
3. አዲስ ኪዳን አንድ ዓይነት እና ተያያዥነት ያለው አሳብና ልዩነቶቸን የሚያስተናግድባቸውን ለይቶ ማወቅ
4. በአዲስ ኪዳን ውስጥ በመርሆዎችና ውስን ተዛምዶዎች መካከል ያለውን ልዩነት ለይቶ ማየት

8
“ይህን በመጀመሪያ እወቁ ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም…” (2 ጴጥ.1፡20)

5. በጥንቃቀ ማድረግ እስከተቻለ ድረስ በየትኛው የአዲስ ኪዳን ጸሐፍ ፊት ክፍት የነበሩትን ባህላዊ አማራጮችን
መወሰን
6. አንዳንድ ጊዜ በግልጽ የማይታዩትን የመጀሪያውና የሃያ አንደኛውን ክፍለ ዘመን ባልላዊ ልዩነቶቸን ለመለየት መጣር
7. በመጨረሻም በዚህ ጉዳይ ላይ ክርስቲያናዊ ቸርነትን መላበስ

ሦስኛው ቀን
የቡድን ውይይት ጥያቄዎች
1. በብሉይ ኪዳን ትረካዎች ውስጥ የሚታስታውሱአቸውን ገጸ ባህርያት ተወያዩና ዘርዝሩ(4 ደቂቃ)
2. ብዙውን ጊዜ ሰባኪዎች እና አስተማሪዎች የብሉይ ኪዳን ታሪኮችን ስሰብኩ ምን ዓይነት ስህተቶችን ስፈጽሙ
ታስተውላላችሁ?(5 ደቂቃ)

የብሉይ ኪዳን ትረካዎችና ተገቢ አጠቃቀማቸው


የትረካዎች ባህርይ

1. ትረካዎች ታሪኮች ናቸው(Narratives are Stories)


2. የመጽሐፍ ቅዱስ ትረካዎች ስለ ነገሮች ክስተት ይነግሩናል(ነገር ግን ትረካዎች በተራ ነገሮች ላይ ያተኮሩ
አይደሉም፡፡ዓላማቸው እግዚአብሔርን በፍጥረቱና በሕዝቡ መካከል ሲሠራ ማሳየት ነው)
3. ትረካዎች ሤራና ገጸ ባህርያት (ሰው፣አምላክ፣እንስሳት፣እጸዋት፣ወይም ሌላም ዓይነት)አሏአቸው፡፡
የትረካዎች ደረጃ
የብሉይ ኪዳን ትረካዎች ሦስት ደረጃዎች አሉት
1. የመጀመሪያ ደረጃ(ፍጥረት፣ወድቀት፣የኃጢአት ኃይል፣የኃጢአት በሁሉ መዳረስ ፣የደህንነት
አስፈላጊነት፣የክርስቶስ ትስእብትናና መሥዋዕት ናቸው)
2. የመካከለኛ ደረጃ (የአብርሃም መጠራት፣የእምነት አርበኞች፣የግብጽ ባርነት፣ነጻ መውጣት፣…ምርኮ እና
ከምርኮ መመለስ) ገጽ 75
3. ዝቅተኛው ደረጃ(bottom level) ለምሳሌ የዮሴፍ ወንድሞች እንዴት እንደሸጡት፣የገድኦን
መጠራት እና እግዚአብሔርን መፈታተን፣የዳዊት ከቤርሳቤህ ጋር በኃጢአት መውደቅ

ትረካዎች የሚከተሉት አይደሉም

1. በብሉይ ኪዳን ዘመን ስለኖሩ ሰዎች ብቻ የሚተርኩ አይደሉም(የእግዚአብሔር ታሪክ ናቸው)

9
“ይህን በመጀመሪያ እወቁ ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም…” (2 ጴጥ.1፡20)

2. በስውር ፍች (allegory) የተሞሉ አይደሉም


3. ብዙውን ጊዜ ቀጥተኛ ትምህርት አያስተላልፉም
4. የግድ የራሳቸው የሆነ ሥነ ምግባራዊ ትምህርት ላይኖረው ይችላል(ለምሳሌ አብርሃም ወደ አጋር ገባ፣ሳምሶን
፣ዳዊት…)

ትረካዎችን ለመተርጎም የሚረዱ መርሆዎች


1. ብዙውን ጊዜ በቀጥታ ዶክትሪንያዊ መልእክት አያስተላፉም
2. ብዙውን ጊዜ በሌላ ሥፍራ የቀረበውን ዶክተሪን ወይም ዶክትሪኖችን ያብራራሉ
3. ትረካዎች የዘገቡት የተፈጸመውን እንጂ ሁልጊዜ ሊፈጸም የሚገባውን ወይም መፈጸም የነበረበትን አይደሉም
4. የግድ ለእኛ የቀና ምሳሌ መሆን የለባቸውም
5. በብሉይ ኪዳን አብዛኛዎቹ ፍጹም ከላመሆናቸውም በላይ ተግባሮቻቸውም እንዲሁ ናቸው
6. ከትረካው መጨረሻ ላይ የተፈጸመው ነገር መጥፎ ወይም ጥሩ መሆኑ አይነገረንም
7. ሁሉም ትረካዎች የሚፈልጓቸውን መርጠው የሚያስተላፉና ያልተሟሉ ናቸው
8. ትረካዎች ሥነ መለኮታዊ ጥያቄዎችን ለመመለስ የሚጻፉ አይደሉም
9. ትረካዎች በቀጥታ አንድን ጉዳይ ፊት ለፊት በመግለጽም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ በግልጽ ሳይናገሩ አስከትሎታዊ
አንድምታ በመስጠት ትምህርት ልያስተላልፉ ይችላሉ
10. በመጨረሻም እግዚአብሔር የሁሉም መጽሐፋ ቅዱሳዊ ትረካዎች ዋና ገጸ ባህርይ እንደሆነ መገንዘቡ ጠቃሚ
ነው፡፡

የትረካ አተረጓገም ምሳሌ ፡ዮሴፍ

ሰዎች ከመጽሐፍ ቅዱስ መልስ በመፈለግ የሚፈጽሟቸው ስምንት በጣም የተለመዱ ስህተቶች
1. ስውር ፍች መፈለግ(allegorizing)
2. ዓውደ ንባቡን መጣስ(decontextualizing)
3. ምርጫ(selectivity)
4. የተሳሳተ ወህደት(false combination)
5. ዳግማዊ ብያኔ መስጠት(redefinition)
6. ከቀኖናዊ ያለፈ አተረጓገም(extracanonical authority)
7. ምንባቹን ሥነ ምግባራዊ ማድረግ(moralizing)
8. ግላዊ ማድረግ(personalizing)
መጽሐፍ ቅዱስን በግድ የለሽነት አታንብበው! ሁሉንም የራስህ አታድርገው! እግዚአብሔር የሚያዝህን ጉዳይ ፈጽሚ፡፡

አራተኛው ቀን
የሐዋርያት ሥራ ፡ የታሪካዊ አርኣያነት ጥያቄ

10
“ይህን በመጀመሪያ እወቁ ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም…” (2 ጴጥ.1፡20)

እንደ ታሪክ መጽሐፍ ሁሉ የሐዋርያት ሥራንም ስናጠና ጥንቃቄ ማድረግ አለብን፡፡እንደ ብሉይ ኪዳን ትረካዎች
ሁሉ ሐዋርያት ሥራን ሙሉ በመሉ ለሕይወታችን ምሳሌ ለማድረግ የሚናጠና ከሆነ ግራ መጋባታችን አይቀረ ነው፡፡

የሐዋርያት ሥራ ሒቲት
የሐዋርያት ሥራን ሐቲት ለመሥራት መጠየቅ ያለብን ጥያቄዎች ሁለት ናቸው
1. ምን ተከሰተ?(ታሪኩን ከዓውዱ መመልከት)
2. ለምን ተከሰተ?(የክስተቱን ዓላማ ከጸሐፍው ፍላጎት አንጻሪ መመልከት)
የሐዋርያ ሥራ ቅኝት(አሰሳ)
ለምን የሚለውን ጥያቄ ሉቃስ ራሱ በሰጠን አከፋፈል ተመሥርተ እናነሳለን፡፡ ብዙውን ጊዜ የሐዋርያት ሥራን ሉቃስ
 በጴጥሮስ ምዕ.1-12 እና
 ጳውሎስ 13-28 ተመሥርቶ ባደረገው ትኩረት ላይ ተመሥርቶ ሲከፈል ኖሮአል፡፡ወይም ደግሞ በወንጌሉ
መልክዓ ምድራዊ መስፋፋት ላይ በመመሥረት አልያም ቁልፍ ቃሉን 1፡8 በማድረግ መክፈል የተለመደ
ነው፡፡ይኼውም፡-
 ም.1-7 ኢየሩሳሌም

ም. 8-10 ሰማርያና ይሁዳ


 ም.11-28 የምድር ዳርቻ በመባል ይከፈላል፡፡ከዚህም በተሻለ መንገድ መጽሐፉን በሚታነብበት ጊዜ 6፡
7፣9፡31፣12፡24፣16፡4 እና 19፡20 ላይ የሚገኙትን አጫጭር የማጠቃለያ አሳቦቸን ማስተዋሉ
ይጠቅማል፡፡
የሉቃስ ዓላማ
1. የሐዋርያት ሥራን ለመረዳት ቁለፍ ነገር በመንፈስ ቅዱስ ምሪት ሉቃስ በዚህ እንቅስቃሴ ውስጥ ያተኮረባቸውን
ነጥቦች ማጤኑ ይመስላል
2. ይህ በእንቅስቃሴ ላይ የተደረገው ትኩረት ሉቃስ በግልጽ ባልነገረን አሳቦች ተጠናክሯል፡፡
3. ነገሮችን ወደ አንድ ዓይነት መመዘኛ ማምጣቱ የሉቃስ ዓላማ አይመስልም
4. ይህም ሆኖ አብዘኛው የሐዋርያት ሥራ ክፍል እንደ ሞዴል እንዲያገለግል ሉቃስ ያሰበበት መሆኑን እናምናለን፡፡

የሐዋርት ሥራ አፋታትን በተመለከተ አንዳንድ ጠቃሚ መርሆዎች


1. በሐዋርያት ሥራ ውስጥ ለክርስቲያኖች ሁሉ እንደሚያስፈልግ ተደርጎ መወሰድ ያለበት የእግዚአብሔር ቃል
በቀዳሚነት የትኛውም ትረካ ሊያስተላልፈው ከፈለገው አሳብ ጋር የሚዛመድ ነው፡፡
2. የትረካውን ቀዳማይ ፍላጎት የሚደግፈው አሳብ በመንፈስ ቅዱስ ምሪት የሚጽፈው ደራሲው ለነገሮች ያለውን
ግንዛቤ ሊያንጸባርቅ ይችላል፡፡
3. ታሪካዊ ሞደልነት ለክርስቲያኖች ሁሉ ያገለግል ዘንድ ሊተላለፍ ከተፈለገው መልእክት ጋር መዛመድ አለበት፡፡

ሌሎች ውስን መርሆዎች


1. ምናልባት በመጽሐፍ ቅዳሳዊ ሞዴል ላይ ተመሥርቶ ምሥያን ለአሁኑ ዘመን ተግባራት እንደ መጽሐፍ ቅዱሳዊ
ሥልጣን መጠቀሙ ከቶውንም ተገቢ ላይሆን ይችላል፡፡(ለምሳሌ የጌድኦን ቆዳ ማንጠፍ…)
2. ምንም እንኳ የደራሲው ቀዳማይ ዓላማ ባይሆንም የመጽሐፍ ቅዱስ ትረካዎች ማብራሪያ የመስጠት እና
አንዳንድ ጊዜ ምሳሌያዊ እሴት አላቸው፡፡
3. በክርሲትያናዊ ልምምዶችና ተግባራት ረገድ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ምሳሌዎች ሁሉም ክርሲቲያን ሊያደርጋቸው
እንደሚገቡ ደንቦች ባይወሰዱም እንኳ አንዳንድ ጊዜ ሊደገሙ እንደሚችሉ በምሳሌነት ሊያገለግሉ ይችላሉ፡፡
ወንጌላት ፡ ብዙ አቅጣጫዎች ያሉት አንድ ታሪክ

11
“ይህን በመጀመሪያ እወቁ ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም…” (2 ጴጥ.1፡20)

በወንጌላት ውስጥ የሚገኙ ነገሮች በሁለት ይከፈላሉ፡-


አባባሎችና ትረካዎች፤ ማለትም የክርስቶስ ትምህርቶችና ስለ ክርስቶስ የተነገሩ ታሪኮች ናቸው፡፡
ስለሆነም መልእክቶችንና ትረካዎችን ለመተርጎም የተከተልነውን መርሆዎች መከተላችን የማይቀር ነው፡፡
በወንጌላት ውስጥ ዋንኛ የሥነ አፈታት ችግር የሚሆነው የእግዚአብሔር መንግሥትን በተመለከተ ከተነገረው ሐረግ ጋር
ተያይዞ የሚመጣ ነው፡፡

በክርስቶስ አገልግሎት ውስጥ የእግዚብሔር መንግሥት ጽንሰ አሳብ ምን እንደሆነ ሳትገነዘብ ወንጌላትን
በአግባቡ እተረጉማለሁ ብለህ አታስብ፡፡
ይህም የሆነው በመጀመሪያ ደረጃ የጠቅላላው አዲስ ኪዳን መሠረታዊ የሥነ መለኮታዊ መዋቅር ሥነ
ፍጻሜያዊ(Eschatological) መሆኑን መገንዘብ ይኖርብሃል፡፡
ሥነ ፍጻሜ እግዚአብሔር ይህንን ዘመን ወደ ፍጻሜ የሚያመጣበት ጊዜ ነው፡፡በክርስቶስ ዘመን የነበሩት
አይሁድ በአብዘኛው ሥነ ፍጻሜያዊ አስተሳሰብ ነበሩአቸው፡፡ይህም ማለት እግዚአብሔር ወደ ታሪክ ምዕራፍ
በመዝለቅ ይህን ዘመን ከፍጻሜ በሚያደርስበትና መጭውን ዘመን ተግባራዊ በሚያደርግበት የጊዜ ቋፍ ላይ
እንደሚገኙ ያስቡ ነበር፡፡

የአይሁዶች የፍጻሜ ተስፋ

ይህ ዘመን መጭው ዘመን

(የሰይጣን ጊዜ) (እግዚአብሔር የሚገዛበት ጊዜ)

ባህርይው ባህርይው

ኃጢአት የመንፈስ ቅዱስ መኖር


በሽታ ጽድቅ፣ጤና ሰላም
በአጋንት መያዝ እና የክፋዎች ድልነሽነት

12
“ይህን በመጀመሪያ እወቁ ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም…” (2 ጴጥ.1፡20)

የአዲስ ኪዳን የፍጻሜ እይታ

ፍጻሜ

ተጀመረ ተግባራዊ ሆነ

መጭው ዘመን
ይህ ዘመን (እያለፈ) (ፍጹም የማያልፍ)

መስቀሉና ትንሳኤው ዳግም ምጻት


ቀድሞውኑ(Already) ገና(Not Yet)
ጽድቅ ሙሉ ጽደቅ
ሰላም ሙሉ ሰላም
ጤንነት ሞት፣በሽት የለም
መንፈስ ቅዱስ ፍጹም ምልዓት
ድነናል እንድናለን
ተቀድሰናል እንቀደሳለን

በአዲስ ኪዳን ውስጥ ለሚገኙ ብዙ ምንባቦችና በተለይም ለክርስቶስ ትምህርት ሥነ አፈታት ቁልፉ በዚህ
ዓይነት ውጥረት ውስጥ መገኘት ነው፡፡

አምስተኛው ቀን

የቡድን ውይይት ጥያቄዎች

1. ኢየሱስ ክርሰቶስ በምሳሌዎች የማስተማሩ ዓላማ ምን እንደሆነ ተወያዩ


2. ሰባኪው ወይም አስተማሪው ስለ ምን እያስተማረ እንደሆነ ማጣቀሻ አሳቡን ሳትሰማ ምሳሌውን ለብቻው ቢትሰማ
ምን ዓይነት ስሜት ልሰጣችሁ እንደሚችል ተወያዩና አቅርቡ

ምሳሌዎች፡ መልእክቱን አገኘህ?

ምሳሌዎች ለረዥም ዘመናት በተሳሳተ መንገድ ሲተረጎሙ የቆየበት ምክንያት ክርስቶስ ራሱ እንደ ተናገረው ከዓላማቸው
አንጻር ልሆን ይችላል(ማር.4፡10-12፣ማቴ.13፡10-13 እና ሉቃስ 8፡9-10)፡፡በምሳሌ የማስተማሩ ዓላማ ምን እንደሆነ

13
“ይህን በመጀመሪያ እወቁ ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም…” (2 ጴጥ.1፡20)

በተጠየቀ ወቅት በውስጥ ላሉት ምሥጢራዊ መልእክት እንደያዙና በውጭ ያሉትን ሰዎች ልብ እንደሚያደነድኑ የሚያመለክት
ምላሽ የሰጠ ይመስላል፡፡

እነዚህን መንፈሳዊ ምሥጢሮችን በጥንቃቄ ትርጉም ካልፈለግን በቀላሉ የራሳችንን መላምት እንዲንሰጥ ሊያደርጉን ይችላሉ፡፡
ኦገስትንን የመሰለ ምሁር የቤክርስቲያን መሪ ስለ ርኅሩኁ ሳምራዊ የሚከተለውን ትርጉም ሰጥቶአል፡-(ገጽ 139-140)

የምሳሌዎችን ሐቲት ለመረዳት የመጀመሪያ ሰዎችን ማወቅና እነርሱ በሰሙበት መንገድ መስማት እንዳለ ሆኖ የምሳሌዎችን
ባህሪይም ለይቶ ማወቅ አለብን፡፡

ምሳሌ ተብሎ የተተረጎሜው የግርኩ ቃል “ሜታል” ሲሆን በአማርኛ “ምሳሌ”ዎችን ብቻ ለማመልክት ሳይሆን ለይቤያዊ
አነጋሮችና እንቆቅልሾችም ጭምር የሚያገለግሉ ናቸው፡፡

የምሳሌዎች ባሕርይ

መጀመሪያ ሊጤን የሚገባው ምሳሌዎች ሁሉ አንድ ዓይነት አለመሆናቸው ነው፡፡ለምሳሌ፡-

 የርኅሩኁ ሳምራዊ (እውነተኛ ታሪክ) እና


 የምግብ እርሾ (ተነጻጻሪ ዘይቤ) አንድ ዓይነት አይደሉም፡፡ሁለቱም ደግሞ
 “እናንተ የምድር ጨው ናችሁ” (ተለዋጭ ዘይቤ) ወይም
 “ከእሾህ ወይን ፣ ከኩርንችትስ በለስ ይለቀማልን?”(ምሳሌያዊ አነጋገር) ይለያሉ፡፡

ነገር ግን ስለ ምሳሌዎች በምንነጋገርበት ጊዜ እነዚህን ሁሉ ልናገናቸው እንችላለን፡፡

ምሳሌዎች ሁሉ አንድ ዓይነት ባለ መሆናቸው ለሁሉ የሚሠራ ደንብ ማውጣት አይቻልም፡፡

የምሳሌዎች ሐቲት ለመሥራት የትኩርት አቅጣጫዎች

1. የማጣቀሻ ነጥቦችን ማግኘት (የታሪኩን ባለቤቶቸን ማግኘት)

በእኛ ዓውድ ሰባኪዎችና አስተማሪዎች ገጠመኞታቸውን እና ቀልዶችን እየተናገሩ አውዱ በደንብ ስገባን በሳቅ ወይም በሀዘን
ምላሽ ልንሰጥ እንችላለን፡፡(ዋናው መስመር ተይዞአል…) ምሳሌዎችም ኢየሱስ በተናገረበት ዓውድ እንዲሰጡ የተፈለገው
ምላሽ እንዲሰጡ አስችሎአቸዋል፡፡እኛም የማጣቀሻ ነጥቦችን ወይም የታሪኩን ባለቤቶቸን ማግኘት ይጠበቅብናል፡፡

ስምኦን የተባለው ፈሪሳዊ ለክርስቶስ ያዘጋጀው ግብዣ(ሉቃስ 7፡40-42) በዚህ ምሳሌ ውስጥ የማጣቀሻ አሳቦች አሉ፡-
እነዚህም ገንዘብ አበዳሪውና ሁለቱ ተበዳሪዎች ናቸው፡፡ ዝምድናቸውም ቅርብ ነው፡፡ እግዚአብሔር እንደ አበዳሪው ነው፡፡
ጋለሞታይቱና ስምኦን እንደ ሁለቱ ተበዳሪዎች ናቸው፡፡

ሁለቱም የተለያየ ነገር ከምሳሌ እንደሰሙ ማስተዋል አያዳግትም፡፡ የፍርድ ቃል እና የእግዚአብሔርን ምህረት

2. አድማጭን መለየት

የአንድ ምሳሌ ፍች መጀመሪያ ከተደመጠበት ሁኔታ ጋር ስለሚያያዝ አድማጮችን መለየት ጠቃሚ ነገር ነው፡፡በእንዲህ
ዓይነት ሁኔታዎች ውስጥ የአተረጓገም ተግባር ሦስት ነገሮችን ያካትታል

1. ምሳሌውን ደጋግሞ መስማት


2. ክርስቶስ የፈለጋቸውንና የመጀመሪያዎቹ አድማጮች ያገኙአቸውን የማጣቀሻ ነጥቦች መለየትና
3. የመጀመሪያዎቹ አድማጮች ራሳቸውን ከታሪኩ ጋር እንዴት እዳዛመዱና ምን እንደ ሰሙ ለማወቅ መሞከር

14
“ይህን በመጀመሪያ እወቁ ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም…” (2 ጴጥ.1፡20)

ሁለት የታወቁ ምሳሌዎችን እናብራራው

ሉቃስ 10፡25-35 ርኅሩኅ ሳምራዊ ፡- የማጣቀሻ ነጥቦች ሁለት ብቻ ናቸው፡፡የጠጎዳው ሰውዬውና ሳምራዊው፡፡ ዋናው
ትምህርቱ ፍቅር እንደሌለው የሚታየው የተጎዳውን ሰውዬ ባለመርዳቱ ሳይሆን ሳምራዊያን በመጥላቱ (እና ካህናትን በመናቁ)
ነበር

የጠፋው ልጅ ታሪክ (ሉቃስ 15፡11-32)፡- ሦስት ማጣቀሻ ነጥቦች ያሉት ሲሆን እነዚህም አባትና ሁለት ልጆቹ ናቸው፡፡
መልእክቱ እግዚአብሔር የጠፋትን ኃጢአተኞችን ይቅር ማለቱ ብቻ ሳይሆን በደስታ ይቀበላቸዋል የሚል ነው፡፡ራሳቸውን
እንደ ጻድቅ ሚቆጥሩ ሰዎች የጠፋውን ልጅና የአባቱን ደስታ ካልተጋሩ ጻድቃን አለመሆናቸውን ያረጋግጣሉ፡፡

ከክርስቶስ ጋር የሚመገቡ ሰዎች ከጠፋው ልጅ ጋር ራሳቸውን እንደሚያዛምዱ ጥርጥር የለውም፡፡

3. ዓውድ አልባ ምሳሌዎች መለየት

ዋናው መርህ የማጣቀሻ ነጥቦቸንና የመጀመሪያ አድማጮችን የመለየት ጉዳይ ነው፡፡ለዚህም ቁልፉ የማጣቀሻ ነጥቦችን
በግልጽ እስከሚታዩበት ጊዜ ድረስ በተደጋጋሚ ማንበብ ነዉ፡፡ይህም በበኩሉ የመጀመሪያ አድማጮቹ እነማን እንደ ነበሩ
ፍንጭ ይሰጣል፡፡

ማቴ 20፡1-16 ሦስት የማጣቀሻ ነጥቦች አሉት፡- የመሬቱ ባለቤት፣ቀኑን ሙሉ የሠሩና አንድ ሰዓት የሰሩ ሲሆን መልእክቱ
ከጠፋው ልጅ ታሪክ ጋረ ተመሳሳይ ሲሆን እግዚአብሔር ቸር እንደሆነና ጻድቃን በልግስናው ቅር መሰኘት እንደማየገባቸው፡፡

የእግዚአብሔር መንግሥት ምሳሌዎችን በትኩረት መመልከት


እነዚህ ምሳሌዎች ሲጀመር “የእግዚአብሔር መንግሥት …ትመስላለች” በማለት ይጀምራሉ፡፡

ስለ ምሳሌዎቹ ጠቅለል ያሉ መርሆዎች

ከማጣቀሻ ነጥቦቹ ወይም ዝርዝሮቹ አንዱ ሳይሆን ጠቅላላው ምሳሌ ስለ እገዚአብሔር ባሕርይ አንድ ነገር ይነግረናል
የሚለውንና
ከኢየሱስ መምጣት ጋር የእግዚአብሔር መንግሥት ወደ ሰዎች እንደቀረበ ክርስቶስ ያስተማረባቸው መሆኑን መገንዘብን
ይጠይቃል
እንደ ሁልጊዜው ምሳሌዎቹ አሁን ባሉባቸው መጽሐፍ ቅዱሳዊ ዓውዶች መርካት አለብን
ሌላው ሥነ አፈታታዊ አሳቦችን የክርስቶስ ምሳሌዎች ሁሉ በሆነ መንገድ ስለ እግዚአብሔር መንግሥት የሚያስተምሩ
መሣርያዎች ከመሆናቸው ጋር የተዛመደ ነው፡፡ስለዚህ ቀድሞውኑ እና ገና የሚሉ ሀረጎችን ያስታውሱ፡፡

ስድስተኛው ቀን

የቡድን ውይይት ርዕሰ ጉዳይ

በውልና ማስረጃ ሰነድ እና በጋብቻ ቃል ኪዳን ሰነድ መካካል ያለውን አንድነት እና ልዩነትን ተወያዩና አቅርቡ፡፡

ሕግ (ሕግጋት )የእሰራኤል የቃል ኪዳን ተእዛዛት

በብሉይ ኪዳን ውስጥ ከስድስት መቶ የሚበልጡ ትእዛዛት አሉ፡፡እነዚህም እስራኤላዊያን ለእግዚአብሔር ታማኞች
መሆናቸውን ለማሳየት የሚፈጽሟቸው ናቸው፡፡የሚገኙትም በዘጸ፣ዘሌ፣ዘኁ፣እና ዘዳ ውሰጥ ነው፡፡

ክርስቲያንና የብሉይ ኪዳን ሕግ

15
“ይህን በመጀመሪያ እወቁ ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም…” (2 ጴጥ.1፡20)

ክርስቲያን ከብሉይ ኪዳን ሕግ ጋር ያለውን ግንኙነት በተመለከተ ስድስት የመነሻ መርሆዎች ማኖሩ ተገቢ ነው፡፡(ገጽ 156-
160)

1. የብሉይ ኪዳን ሕግ ቃል ኪዳን ነው፡፡(በእስራኤልና በእግዚአብሔር መካከል የተደረገ)


ስድስት ክፍሎች አሉት
መግቢያ፡ ትውውቅ
ቅድሜ ቃል ኪዳን፡የተሳሰሩበት አጭር ታሪክ
ደንቦች፡ሕግጋት እራሳቸው
ምስክሮች፡ሰማይና ምድር ወይም እግዚአብሔር እራሱ
ማዕቀቦች፡ ማበረታቻ…በረከቶችና መርገሞች
የሰነድ ክለሳዎች፡ቃል ኪዳኑ እንዳይዘነጋ(ገጽ 157)
2. ብሉይ ኪዳን ለእኛ የተሰጠ ቃል ኪዳን አይደለም፡፡
3. አንዳንድ የብሉይ ኪዳን ሕግጋት አልተለወጡም፡፡
4. አሮጌው ቃል ኪዳን በአዲሱ ቃል ኪዳን ውስጥ በከፊል ታድሶአል፡፡
5. ምንም እንኳን ለእኛ የእግዚአብሔር ትእዛዛት ባይሆንም ፤ የብሉይ ኪዳን ሕግ ሁሉ አሁንም የእግዚአብሔር ቃል ነው፡፡
6. የአዲስ ኪዳን ሕግ “የክርስቶስ ሕግ ነው” ሊባል የሚችለው ከብሉይ ኪዳን ሕግ በግልጽ የታደሰው ብቻ ነው (ገላ.6፡2)

እንደ ማጠቃለያ አንዳንድ የአድርግ አታድርግ መርሆዎች

እነዚህን መርሆዎች መጠበቁ የተሳሳተ የብሉይ ኪዳን ተዛምዶ በማስወገድ ፤ የሕግን የማስተማሪና እምነት- ገንቢ ባሕርያት
እንድትከተል ይረዳሃል፡፡(ገጽ 170)

1. የብሉይ ኪዳን ሕግ ሙሉ በሙሉ በእስትንፋሰ-እግዚአብሔር በልጽጎ እንደ መጣልህ ቃል አስበው፡፡ የብሉይ ኪዳን ሕግን
ለአንተ እንደ ተላከ ቀጥተኛ የእግዚአብሔር ትዕዛዛት አትውሰደው፡፡

2. የብሉይ ኪዳን ሕግ የአሮጌው ኪዳን መሠረት እና ከዚህም የተነሳ የእስራኤላዊያን ታሪክ መሠረት አድርገህ ተመልከት፡፡
በግልጽ እስካልታደሰ ድረስ የብሉይ ኪዳን ሕግ ለክርስቲያኖች እንደሚሠራ አድርገህ አትመልከት፡፡

3. የብሉይ ኪዳንን ሕግጋት እንደ ሙሉ ሕግጋት ሳይሆን እንደ ሞዴል አድርገህ ተመልከት፡፡

4. በብሉይ ኪዳን ሕግጋት ውስጥ የተገለጹትን የእግዚአብሔር ፍትሕ፣ፍቅርና ታላላቅ መመዘኛዎች በትኩረት
አስተውላቸው፡፡የእግዚአብሔር ምህረት ከመመዘኛዎቹ ትክክለኛነት እኩል መሆኑን አትዘንጋ፡፡
5. የብሉይ ኪዳንን ሕግጋት በነቢያት ወይም በአዲስ ኪዳን በተደጋጋሚ እንዲጠቀስ አትጠብቅ፡፡
6. የብሉይ ኪዳን ሕግጋት የእስራኤል ሕዝብ በሚታዘዙአቸው ጊዜ በረከትን የሚያመጡ ለእስራኤል የተሰጡ መልካም
ስጦታዎች እንደሆኑ አስብ፡፡
የቡድን ወይይት፡ ትንቢት ምንድነው? ብዙ ጊዜ የትንቢት መጽሐፍትን መረዳት የሚያቅተን ለምን
ይመስላችኋል?
ነቢያት፡በእስራኤል የቃል ኪዳን አስከባሪዎች
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የትንቢትን ርዕስ ይዘው የሚመጡ መጽሐፍት ከሌሎቹ ሁሉ በላይ በቁጥር በርከት
ያሉ ናቸው፡፡
እነዚህ የነቢያት መጽሐፍት ከ 760 እስከ 460 ዓ.ዓ በጥንቷ እስራኤል ዘመን የተከሰተ ታሪክ ነበር፡፡
እነዚህን መጽሐፍት በተሳሳተ መንገድ የሚንረዳባቸው ምክንያቶች ከአገልግሎታቸውና ከቅርጻቸው ጋር
በተያያዘ ነው፡፡

16
“ይህን በመጀመሪያ እወቁ ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም…” (2 ጴጥ.1፡20)

ትንቢቶችን ለመረዳት ከሚያስፈልጉት ቁልፎች አንዱ ትንቢቶቹ ተፈጽመው እንዳለፉ መገንዘብ ነው፡፡ወደ
ኋላ ተመልሰን ለእነርሱ ገና የወደ ፊት ለእኛ ግን ያለፉትን ጊዜያት መመልከት ይኖርብናል፡፡

ነቢያት ቃል አቀባዮች

ነቢያትን ወደ ፊት የሚፈጸሙትን ክስተቶች ተንባዮች ናቸው ማለቱ ቀዳማይ አገልግሎታቸውን እንድናጣ


ያደርጉናል፡፡ይህ ቀዳማይ አገልግሎታቸው በዘመናቸው ለነበሩት ሰዎች የእግዚአብሔርን መልእክት ማስተላለፍ
ነበር፡፡
እነዚህን በተለያዬ ጊዜ የተነገሩ የእግዚአብሔር መልእክቶችን በአንድ ጊዜ ቁጭ ብሎ ማንበቡ ቀላል አይደለም፡፡
ብዙዎች መልእክቶች የተነገሩት በግጥም ስልት ነው፡፡

የታሪክ ችግር

ስለ ትንቢቶቹ ያለንን ግንዛቤ የሚያወሳስበው ሌላው ነገር ታሪካዊ ርቀት ነው፡፡ ከነገሮቹ ባሕርይ ሳቢያ ያን ጊዜ
ከነቢያቱ በጆሮአቸው ከሰሙአቸው እስራኤላዊያን ይልቅ በዛሬ ዘመን ያለን እኛ የእግዚአብሔርን ቃል
ለመረዳት እንቸገራለን፡፡ብዙውን ጊዜ ቃላቱ ምንን እንደ ተመለከቱና ለምንስ እንደሚያመለክቱ ማወቅ
ይሳነናል፡፡

የትንቢት አገልግሎት

እግዚአብሔር በእነዚህ የተጻፉት ቃላት ምንን እንደሚነግረን ለመረዳት በእስራኤል የነቢይ ሚናና አገልግሎት
ምን እንደሆነ ማወቅ አለብን፡፡በእነዚህ ረገድ ሦስት ነገሮች ላይ ትኩረት ማድረግ ይኖርብናል፡፡

1. ነቢያት በእግዚአብሔርና በሰዎች መካከል የቃል ኪዳን አስፈጻሚ መካከለኞች ነበሩ፡፡


2. ነቢያት የሚያውጁአቸው በረከቶች ወይም መርገሞች ራሳቸው አፈልቀው እንደማይናገሩአቸው
መገንዘቡ ጠቃሚ ነው፡፡
3. እስራኤል ለቃል ኪዳኑ ታማኞች ከሆኑ ይባረካሉ፤ካልሆነ ግን ቅጣታቸውን ይቀበላሉ፡፡

የትንቢትን መጻሕፍትን በምታነብበት ጊዜ ይህን ቀላል የአፈጻጸሚ ስልት አስተውል


1. የእስራኤል ኃጢአት ወይም እግዚአብሔር ለእስራኤል ያለውን ፍቅር ይገልጻል
2. እንደ ሁኔታው የመርገም ወይም የበረከት ትንበያ ይኖረዋል
መንፈስ ቅዱስ በሰጣቸው መጠን ነቢያት የሚያስተላልፉት መልእክት ይኸው ነው፡፡

በሌላ መንገድ መሢሐዊ ትንቢቶችንም በትኩረት መመልከት(ኢሳ 53…)

ሐቲታዊ ተገግባር

በአጠቃለይ የትንቢት መጻሐፍት ጊዜንና ጥናትን የሚጠይቁ ናቸው፡፡ስለሆነም እነዚህን የትንቢት መጽሐፍትን
በሚንተረጉምበት ጊዜ ሦስቱን ውጫዊ የእርዳታ ምንጮች መዘንጋት የለብንም፡፡
1. የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት
17
“ይህን በመጀመሪያ እወቁ ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም…” (2 ጴጥ.1፡20)

2. መጻሕፍት(Commentaries)
3. የመጽሐፍ ቅዱስ መመሪያ(The Biblehandbooks)

ታሪካዊ ዓውድን መረዳት

ሰፊው ዓውድ፡-አስራ ስድስቱም የትንቢት መጻሕፍት ከረዥሙ የእስራኤል ታሪክ ውሰጥ ጥቅቶቹን ብቻ
(760-460 ዓ.ም) የሚሸፍኑ መሆናቸው አስገራሚ ነው፡፡
አሞጽ በ 760 ዓ.ዓ አካባቢ መልእክቶቻቸውን በጽሑፍ ካቆዩት ነቢያቶች የመጀመሪያው ሲሆን ሚልክያስ 460
ዓ.ዓ የመጨረሻው ነው፡፡ ቀጣዩን ጥያቄ መጠየቁ ተገቢ ነው፡፡በእነዚህ ሦስት መቶ ዓመታት ውስጥ የነቢያት
መልእክቶች የበረከቱት ለምንድነው? ወቅቱስ ምን ይመስል ነበር?

እነዚያ ዓመታት በሦስት ነገሮች ይታወቃሉ፡-


1. ታይተው በማይታወቅ ፖለትካዊ፣ወታደራዊ፣ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ውዝግብ
2. በከፍተኛ የሃይማኖታዊ ታማኝኘት ጉድለትና የመጀመሪያውን የሙሴን ህግ ባለማክበር እ
3. የሕዝብ ቁጥርና የብሔራዊ ዳርቻዎች መቀየር ነበር፡፡

ከዚሁ ጋር በተያያዘ 760 አካባቢ እስራኤል ለረዥም ጊዜ በቆየው እርስ በእርስ ጦርነት ለሁለት ተከፍላ የሰሜኑ
መንግሥት (እስራኤል) የደቡብ መንግሥት(ይሁዳ)በመባል የተሰየሙበት ጊዜ ነበር፡፡

ከዚህም የተነሳ፡-
አሞጽ 765 ዓ.ም እና ሆሴዕ 755 ዓ.ም እስራኤል (የሰሜኑ) ክፍል ከኃጢአታቸው እንዲመለሱ የማስጠንቀቂያ
መልእክት ቢያመጡም አንሰማም በማለታቸው በ 722 ለአሦር መንግሥት ተማረኩ፡፡
በመቀጠልም ይሁዳ(የደቡብ)መንግሥት ኃጢአቷ እየባሰ በመሄዱ እንደ ኢሳያሰ፣ኤርምያስ፣ኢዩኤል፤
ሚክያስ፤ናሆም፣ዕንባቆም፣ሶፎንያስ እና የመሳሰሉት ለአገልግሎት ተሰማሩ፡፡
በእንቢተኝነቷም ስለቀጠለች 587 ለባቦሎን ታልፋ ተሰጠች፡፡ ነቢያቶቹ ለእነዚህ ክስተቶች በቀጥታ ሰፊ
መልእክቶችን ያስተላለፉት ሲሆን መልእክታቸውን ለመረዳት ወቅቱን መገንዘቡ ወሳኝ ነው፡፡

በተጨማሪም የሚከተሉትን ነጥቦች ግንዛቤ ውስጥ ማስገባት የትንቢት መልእክቶችን ለመረዳት ጠቃሚዎች
ናቸው፡፡

1. የትንቢት መልእክቶችን ለብቻው ነጥሎ ማጥናት (የውጭ እርዳት ሰጭዎችን በመጠቀም)


2.የትንቢት ማቅረቢያ ቅርጾችን መለየት

ቅርጾቹ
የሕግ ችሎት
ዋይታ
የተስፋ ቃል እና
ግጥም ናቸው፡፡

በብሉይ ኪዳን የግጥም ቅርጾች ሦስት ናቸው (ገጽ 188)

18
“ይህን በመጀመሪያ እወቁ ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም…” (2 ጴጥ.1፡20)

የዕብራይስጥ የግጥም ስልት ምን እንደምመስል ለመረዳት በብሉይ ኪዳን ግጥም ውስጥ ተደጋጋሚመው
የሚታዩትን ቀጣይ ሦስት ገጽታዎችን መመልከቱ ጠቃሚ ነው፡፡

1. ተመሳሳይ ትይዩነት(Synonymous parallelism) ለምሳሌ፡- በኢሳያስ 44፡22 እንደተመለከተው


ሁለተኛው ስንኝ የመጀመሪያውን አሳብ ያጠነክረዋል ወይም ይደግመዋል፡፡

“መተላለፍህን እንደ ደመና፤

ኃጢአትህን እንደ ማለዳ ጭጋግ ጠርጌ አስወግጀዋለሁ፡፡”

2. ተቃርኖአዊ ትይዩነት(Antithetical Parallelism) ለምሳሌ፡- በሆሴዕ 7፡14 ሁለተኛው ስንኝ


የመጀመሪያውን ይቃረነዋል፡፡

“ከልባቸው ወደ እኔ አይጮሁም፤

ነገር ግን በአልጋቸው ሆነው ወደ እኔ ያለቅሳሉ፡፡”

3. ተጨማሪ ትይዩነት (Synthetic Parallelism) ለምሳሌ፡- አብድዩ 21 ላይ ሁለተኛው ስንኝ ለመጀመሪያው


ተጨማሪ አሳቦችን ይሰጣል፡፡

“የኤሳውን ተራሮችን ለመግዛት፣

ነጻ አውጭዎች ወደ ጽዮን ተራራ ይወጣሉ፤

መንግሥቱም የእግዚአብሔር ይሆናል፡፡”

በአጠቃላይ መልኩ ሲታይ እግዚአብሔር ከእሰራኤልና ከይሁዳ የፈለገው ከእኛም የሚፈልገው ነው፡፡የሚልክያስ
4፡6 ማስጠንቀቂያ ዛሬም አልተነሳም፡፡

19
“ይህን በመጀመሪያ እወቁ ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም…” (2 ጴጥ.1፡20)

ስምንተኛው ቀን

መዝሙረ ዳዊት ፡ የእራኤልና የእኛም ጸሎቶች

የቡድን ውይይት፡- የመዝሙረ ዳዊት መጽሐፍ በአብዘኛው የአማኙ ማህበረተሰብ ተወዳጅ የሆነው ለምን
እንደሆነ ተወያዩና አቅርቡ፡፡

የመዝሙረ ዳዊት አተረጓገም ችግር የሚነሳው በቀማዊነት ከባሕርዩ ነው፡፡በቀዳማዊነት ዶክትሪንን ወይም
የሥነ ምግባርን ባሕርይን ለማብራራት አይደሉም፡፡ብዙውን ጊዜ ክርስቲያኖች ይህንን ካለመረዳታቸው የተነሳ
በተሳሳተ መንገድ በሕይወታቸው ያዛምዱታል፡፡

አንዳንድ የመነሻ ሐቲታዊ ምልከታዎች

መዝሙራት እንደ ለሎች መጽሐፍት የራሳቸው ዓይነት፣ቅርጽ፣አገልግሎትንም ጨምሮ ባሕርያቸውም የተለየ


ስለሆነ ልዩ ጥንቃቄ ልናደርግ ይገባል፡፡

መዝሙራት እንደ ግጥም

ከመዝሙራት ጋር በተያያዘ ስለ ዕብራዊያን ግጥሞች ሦስት ነገሮችን መገንዘብ አለብን

1. የዕብራዊያን ግጥሞች በባሕርያቸው በልብ በኩል ወደ አእምሮ የሚላኩ ናቸው


2. መዝሙራት የየትኛውም ግጥሞች ሳይሆኑ ሙዝቃዊ ግጥሞች ናቸው
3. ግጥም ሆን ተብሎ በዘይቤያዊ ቃላት የተጻፉ ናቸው

መዝሙራት እንደ ሥነ ጽሑፍ

መዝሙራትን ስናነብ የተለየ ሥነ ጽሑፋዊ ባህርያቸውን መለየት ጠቃሚ ነው(ገጽ

1. መዝሙራት የተለያዩ ዓይነቶች ናቸው


2. እያንዳንዱ መዝሙር በቅርጹ(መዋቅር) ይለያል
3. በእስራኤል ሕይወት የተወሰነ ድርሻ አላቸው
4. ገጽታቸው ልዩ ልዩ ናቸው(የፍደል ገበታን ቅደሚተከተል)ያተኮሩ ልሆኑ ይችላሉ
5. ሥነ ጽሑፋዊ አሐድ አላቸው

የመዝሙር ጥቅም በእስራኤል ታሪክ

o ለአምልኮ የተዘጋጁ ተግባራዊ ዝማሬዎች ናቸው


o ከእግዚአብሔር ጋር ላለ ግንኙት ታስበው የተዘጋጁ ናቸው

የመዝሙራት ዓይነቶች

 ሰቆቃዎች

20
“ይህን በመጀመሪያ እወቁ ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም…” (2 ጴጥ.1፡20)

 የምስጋና
 የውዳሴ
 የደህንነት
 የበዓላት
 የጥበብ
 የመተማመን
 የእርግማን መዝሙሮች

ሐተታዊ ናሙና

የአንድን መዝሙር ቅርጽና መዋቅር መገንዘብ መልእክቱን ለመረዳት እንዴት እንደሚያግዝ ለማሳየት ሁለት መዝሙሮችን
መርጠናል፡፡

መዝሙር 3፡ ሰቆቃ

ሁሉም የሰቆቃ መዝሙራት ስድሰት ባሕርያት አላቸው


1.አድራሻ ቁ. (እግዚአብሔር ሆይ)
2.እሮሮ ቁ. 1 ና 2 (ጠላቶቸ በዙ)
3.መተማመን ቁ.3-6
4.ነጻ መውጣት(መዳን) ቁ.7 ታደገኝ
5.እርግጠኝት ቁ.7 (ትሰብራለህ…)
6.ምስጋና

የምስጋና መዝሙር

የምስጋና መዝሙር ከሰቆቃ መዝሙር የተለያ ዓላማ ያላቸው ሲሆን 138 እንደ ምሳሌ ቀርቦአል፡፡

መግቢያ ቁ. 1-2
መከራ ቁ.3
ልመና ቁ.3
ነጻ መውጣት ቁ.6-7
ምስክርነት ቁ.4-5 እና 8

የመዝሙራት ሦስት ዐበይት ጥቅሞች

መዝሙራት የአምልኮ መመሪያዎች ናቸው


መዝሙራት ከእግዚአብሔር በታማኝኘት እንደምንዛመድ ያሳዩናል
መዝሙራት እግዚብሔር ስላደረገልን ነገር የማሰብንና የማሰላሰል አስፈላጊነት ያስተምሩናል

ማስጠንቀቅያ ፡-መዝሙራት ለመልካም ሕይወት ዋስትና አይሰጡንም፡፡በምድር ላይ ያለን ሕይወት ከመከራ ነጻ አይደለም፡፡
አንዳንድ ጊዜ በመዝሙራት የተሰጡ የዋስትና ቃላትን የመዝሙራትን ባሕርይ በአግባቡ ካለመረዳት በተሳሳተ
መንገድ በመተርጎም ግራ መጋባቶች ይስተዋላሉ፡፡

21
“ይህን በመጀመሪያ እወቁ ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም…” (2 ጴጥ.1፡20)

ዘጠነኛው ቀን

ጥበብ ያኔ እና አሁን

የዕብራዊያን ጥበብ ብዙዎች የአሁኑ ዘመን ክርስቲያኖች ያልለመዱት ዓይነት ሥነ ጽሑፍ ነው፡፡

የቡድን ውይይት ጥያቄዎች

1. ጥበብ ምንድነው?
2. የጥበብ(የቅኔ መጽሐፍት) ምንድናቸው? ስንት ናቸው? ለእኛስ ምን ፋይዳ አላቸው?
3. ሰዎች ብዙውን ጊዜ የጥበብን መጽሐፍት በአግባቡ መረዳት የሚሳናቸው ለምን ይመስላችኋል?

ጥበብ በሕይወት መንፈሳዊ ምርጫዎችን ማካሄድና ትክክለኛውን እርምጃ መውሰድ ነው፡፡የጥበብ መጽሐፍት
በተለምዶ ሦስት ሲሆኑ አነርሱም መክብብ፣ምሳሌና ኢዮብ ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ መዝሙረ ዳዊት፣መኃልየ
መኃልየ፣እና ሰቆቃዊ ኤርምያስም የጥበብ መጽሐፍ እንደሆኑ ማሰቡ ትክክል ነው፡፡

የጥበብ ሥነ ጽሑፍን አላግባብ የመጠቀም መንስኤዎቸ

1. የጥበብ መጽሐፍትን በከፍል ማንብብ፡-


ለምሳሌ መክብብ 3፡2 “ለመውለድና ለመሞት ጊዜ አለው” በዓውዱ መሠረት ሁሉም ከንቱ ነው
የሚል ሲሆን ሰዎች እግዚአብሔር ዕድሜያችንን መርጦአል ብለው ልተረጉሙት ይችላሉ
2. የጥበብ ቃላትንና ምድቦችን፣እንዲሁም የጥበብ ስልቶችንና ሥነ ጽሑፋዊ ገጽታዎች አለመለየት
ምሳሌ 14፡7 ን ተመልከቱ “ተላላ” ማለት በእግዚአብሔር የማይታመን እና ራሱ ላይ ባለ ሥልጣን
የሆነ ሰው ስለሆነ ጥበብን ከዚህ ሰው አታገኝም ማለት ሲሆን “መራቅ” የሚለውም ከዓላማ ጋር
የተገናኘ ነው::
3. የጥበብ ሥነ ጽሑፍን የሙግት ፈለግ መከተል አለመቻል

ኢዮብ 15፡20 ን ይመልከቱ፡፡ “ክፉ ሰው ዕድማውን ሙሉ ሙሉ ፣ጨካኙም በተመደበለት ዘመን ሁሉ


ይሠቃያል” ክፍሉ ከዓውዱ ጋር ካልተያያ ክፉ ሰዎች በዘመናቸው ሁሉ ደስታና ሰላምን አያገኙም
የሚል ይሆናል፡፡በጠቅላላው ዓውድ ውስጥ ግን እግዚአብሔር የኢዮብ ጓደኞችን ምክር በሙሉ ውድቅ
ስያደርግ እናስተውላን፡፡

ጠቢብ ማነው

ትክክለኛውንና መንፈሳዊ የሆኑ ነገሮች በትክክለኛው ጊዜ የሚያደርግ ነው፡፡ያዕ.1፡5፣3፡13-18

የጥበብ አስተማሪዎች

በጥንቷ እስራኤል አንዳንድ ሰዎች ጥበብን ለመማር ብቻም ሳይሆን ለማሳተማሪም ይተጉ ነበር፡፡
ከዚህም የተነሳ ወላጆች ልጆቻቸውን ወደ እነዚህ ይልኳቸውና እነርሱም እንደ ልጆች ያስተምሩአቸው
ነበር፡፡ከእነዚህም መካከል በጥንቷ እስራኤል በተለይም በራስ ንጉሥ መመራት ከጀመረችበት 1000 ዓ.ዓ
አካበቢ ከተነገሩት ጥቅቶቹ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ተጽፎ ተሰጥቶናል፡፡(ዘፍ.48፡8) ላይ ዮሰፍ
የፈሪኦን አባት ተብሎ ሲጠራ ዲቦራም (መሳ.5፡7) የእሰራኤል እናት ተብላለች፡፡

22
“ይህን በመጀመሪያ እወቁ ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም…” (2 ጴጥ.1፡20)

ጥበብ በቤት

ከላይ የተነሱ አሳቦች እንዳለ ሆኖ የጥበብ ዋናው ቦታ ቤት ውስጥ በወላጆቻቸው በኩል ነበር፡፡

ጥበብ በሥራ ባልደረቦች መካከል

ሰዎች በሕይወት ውስጥ ትክክለኛውን ምርጫዎችን ለማድረግ ከሚማሩባቸው መንገዶች አንዱ


ውይይት ክርክር ነበር፡፡ለምሳሌ መጽሐፌ ኢዮብ::

በግጥም የተገለጸ ጥበብ

በብሉይ ኪዳን ዘመን ተማሪዎችም ሆኑ መምህራን ጥበባቸውን ለማስታወስ የተለያዩ ሥነ ጽሑፋዊ


ቅርጾችን በመሣሪያነት ተጠቅመዋል፡፡ አብዘኛው የብሉይ ኪዳን የጥበብ መጽሐፍቶች የተጻፉት
በግጥም፡፡(ገጽ 223)

የጥበብ ገደቦች

በብሉይ ኪዳን ብዙ ጠቢባን ቢኖሩም የሁሉም ዓላማ እግዚብሔርን መፍራት፣መታዘዝን እና


ለእግዚአብሔር ታማኝ መሆንን የሚያሳዩ አልነበሩም፡፡ምሳሌ ኢዮናዳብ ለአምኖን የሰጠው ምክር
ገንቢ ሳይሆን አፍራሽ እና አሳፋሪ ነበር፡፡የሰለሞን ጥበብ ምንም እንኳን ባለጠጋና ገናና ቢያደርገውም
ለእግዚአብሔር ያለውን ታማኝነቱን ጠብቆ እንዲቆይ አላስቻለውም፡፡ስለዚህ ጥበቦች ገደብ አላቸው፡፡

መክብብ፡ጭፍግ ጥበብ

መክክብ ብዙ ክርስቲያኖች ግራ የሚያጋባ የጥበብ መጽሐፍ ነው፡፡ምክያቱም ከጥበብ ገደቦች ጋር


የተያያዘ በመሆኑ ነው፡፡መጽሐፉ የሕይወትን ከንቱነትን በማሳየት በሕይወት ውስጥ እግዚአብሔር
ምንም ጣልቃ የማይገባ በሚያስመስል ፊልስፍና የሚመራ በመሆኑ የሰባኪውን ቃል ደጋግሞ
መጨረሱም የጠለመደ ነው፡፡

ሰባኪው፡-ከንቱ፣ከንቱ የከንቱ ከንቱ…(ገጽ 224-226)ትን ይመልከቱ፡፡

ታዲያ እንዲህ ዓይነቱ መጽሐፍ ለምን መጽሐፍ ቅዱስ ሆኖ ተሰጠን የሚል ጥያቄ ከተነሳ ከሌሎች
የመጽኸፍ ቅዱስ ክፍሎች ጋር እንዲናነጻጽሪ እና አጠቃላይ መልእክቱን እንዲናገኝ ነው፡፡

ስለዚህ አንባቢ በሰባኪው ጥበብ ባለመርካት የጠቅላላውን የመጽሐፍ ቅዱስን ክፍል ለማግኘት
ምርመራ ማካሄድ ይጠበቅበታል፡፡በእርግጥ በማሰርያው ላይ 12፡13 የነገር ሁሉ ፍጻሜ እግዚአብሔርን
መፍራትና ትዕዛዙን መጠበቅ እንደሆነ ተገልጾአል፡፡

ጥበብ በመጽሐፌ ኢዮብ

በብሉይ ኪዳን ለእግዚአብሔር እውነት በተነጻጻርነት የቆሙ የተሳሳቱ አሳቦች የሚገኙት በመክብብ
ውስጥ ብቻ አይደለም፡፡በመጽሐፌ ኢዮብ ጓደኞቹ ብዙ የተሳሳቱ ምክሮችንንና የማጠቃለያ አሳቦችን
ሲያቀርቡ እንመለከታለን፡፡

23
“ይህን በመጀመሪያ እወቁ ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም…” (2 ጴጥ.1፡20)

መጽሐፌ ኢዮብ መበክብብ ተቃራኒ ሆኖ የሚያስምሪ ይመስላል፡፡ይኸውም መክብብ በሕይወት


ዘመንህ ደስ ያሰኘህን ሁሉ አድርግ ከዚህ ውጭ የለም የሚል ሲሆን በኢየብ መጽሐፍ መልካም ማድረግ
ስኬትን ኃጢአት ደግሞ መከራንና ስቃይን ያመጣል በሚል የብሉይ ኪዳን እምነት የተሞላ ነበር፡፡ ልክ
እንደ ደቀ መዝሙር ዮሐ.9 ላይ እንደ ነበራቸው አመለካካት፡፡ይሁን እንጂ ይህ ሁልጊዜም እውነት
አይደለም፡፡መጽሐፌ ኢዮብ ብዙ መንፈሳዊ ቁም ነገሮችን ልያስተምረን ይችላል፡-

1. መከራ እና ሥቃይ ሁልጊዜም የኃጢአት ውጤት አይደሉም ሮሜ 8፡34-እና በዓለም ሳላች መከራ
አለባችሁ
2. እግዚአብሔር ክፋንና ደጉን የሚቆጣጠር ልዑል አምላክ ነው፡፡
3. እግዚአብሔር ጥያቄዎቻችንን ሁሉ የመመለስ ግዴታ የለበትም
4. እግዚአብሔር ክፉውን ለበጎ መለወጥ የሚችል አምላክ ነው

ጥበብ በመጽሐፈ ምሳሌ

መጽሐፈ ምሳሌ ዋነኛ የጥበብ ምንጭ እና ሚዛናው በሆኑ የሕይወት ተግባራዊ እሰቶች ላይ ቅዲሚያ የሚሰጥ
ነው፡፡በንጽጽሪነቱም የታወቀ ነው፡፡ሞኙን ከጠቢብ፣ኃጢኡን ከጻድቁ….

አንዳንድ ሥነ አፈታታዊ መመሪያዎች

1. ምሳሌዎች ከእግዚአብሔር የተሰጡን ሕጋዊ ዋስትናዎች አይደሉም


2. ምሳሌዎች እንደ ስብስብ ሊነበቡ ይገባል
3. ምሳሌዎች የተጻፉት አንዲታወሱ እንጂ በንድፈ አሳባዊ ደረጃ ትክክል እንዲሆኑ አይደለም
4. አንዳንድ ምሳሌዎች እንዲገቡን ወደ አሁኑ ዘመን ልንለውጣቸው ይገባል ገጽ.237

የምሳሌ መጽሐፍ ጠቅላላ መመሪያዎች

1. ብዙውን ጊዜ ምሳሌዎች ከራሳቸው ወዲያ የሚገልጡ ፈልጣዊ አገላለጦች ናቸው


2. ሥነ መለኮታዊያን ሳይሆኑ በከፍተኛ ደረጃ ተግባራዊያን ናቸው
3. ምሳሌዎች የተጻፉት ለረጅም ጊዜ እንዲታወሱ እንጂ የተፈለገውን መልእክት በሙሉ እንዲያካትቱ
ተደርገው አይደለም
4. ምሳሌዎች የራስ ወዳድነትን ባህርይ የሚደግፉ ሳይሆን አንዲያውም የዚያ ተገላቢጦሹን መልእክት
የሚያስተላፉ ናቸው
5. የጥንቱ ባሕል በስፋት የሚያንጸባርቁ ስለሆኑ ትርጉማቸው አንዳይሰውርብን ወደ ራሳችን
ልንውጣቸው ይገባል

24
“ይህን በመጀመሪያ እወቁ ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም…” (2 ጴጥ.1፡20)

6. ምሰሌዎች ለመልካም ባህርይ ቅኔያዊ መመሪያዎች እንጂ ከእግዚአብሐየር የጠሰጡን ዋስትናዎች


አይደሉም
7. ምሳሌዎች መልእክታቸውን ለማስተላለፍ ውስን፤ግነታዊ ወይም የትኛውምንም የሥነ ጽሑፋዊ
ቴክኒኮች አካል የሆነውን የቋንቋ ስልት ሊጠቀሙ ይችላሉ
8. ምሳሌዎች የተወሰኑ የሕይወት ገጽታዎችን በጥበብ መንገድ ስለ መምራት እንጂ ጥሩ ምክሮችን
ቢሰጡም ሁሉን የሕይወት ገጽታዎችን አያካትቱም፡፡
9. ምሳሌዎች ፤ በተሳሳተ መንገድ ከተጠቀሚንባቸው የቁሳዊነትን ሕይወት ተገቢነት የሚያስተምሩ
ሊመስሉ ይችላሉ፡፡በአግባቡ ከተጠቀሚንባቸው ግን ለዕለታዊ አኗኗራችን ተግባራዊ ምክሮችን
ለሰጡን ይችላሉ፡፡

ጥበብ በመኃልየ መኃልየ ውስጥ

መኃልየ መኃልይ ረጅም የፍቅር መዝሙር ነው፡፡መዝሙሩም በጥንታዊ የምሥራቅ አገሮች የስሜት መግለጫ
ስልት የተጻፌ ረጅም ፍቅር ግጥም ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥም የገቡት ማንን ላፍቅር እና እንዴት ላፍቅር
የሚሉ ጥያቄዎች በሕይወት ውስጥ እጅግ ወሳኝ በመሆናቸው ነው፡፡ለእነዚህ ሁለት ወሳኝ ውሳኔዎች መንሳዊ
ምርጫዎችን ማድረግ ደግሞ ለአማኝ እጅግ አሰፈላጊ ነው፡፡

የመጽሐፉ ዋናው መልእክት ትክክለኛ ምርጫዎ ከተካሄዱ ፍቅርና ወስብ እግዚአብሔር መጀመሪያ የወጠነውን
ዕድል በመፈጸም ለእርሱ ክብር ሊውል ይችላል የሚል ነው፡፡

መኃልየ መኃልይን እንደ መጽሐፍ ቅዱስ ለመረዳት ጥቂት መመሪያዎች


1. የመኃልየ መኃልይን አጠቃላይ የግብረገብነትን ዓውድ ለመረዳት ሞክር፡፡ከብሉይ ኪበዳን
የእግዚአብሔር መገለጥ አንጻሪ ወስብ በጋብቻ ውስጥ በአንድ ወንድ እና ሴት መካከል የሚፈጸም ስለ
ነበር እግዚአብሔርን የሚፈሩ እስራኤላዊያን መኃልየ መኃልይን በዚህ መንገድ ይገነዘቡትና
ይተገብሩት ነበር፡፡
2. የመጽሐፉን ሥነ ጽሑፋዊ ቅርጽ አስተውል፡- ፍቅር መዘከር ሳይሆን ዓላማው ወደ ጋብቻ
ማሚምጣት ነው
3. መኃልየ መኃልይ መንፈሳዊ ምርጫዎችን እንደ ሚገልጽ ሳይሆን እንደሚያደፋፍር አድርገህ አንብብ
4. ከእኛ ዘመናዊ ባህል በሚለዩ እሴቶች ላይ እንደሚያተኩር ተገንዘብ፡- ዘመኑ ወስባዊ ቴክኒኮች ላይ
ትኩረት አደርጎ የሚሠራ ሲሆን መጽሐፉ ወደ ጋብቻ ማምጣት ላይ ነው፡፡

25

You might also like