Professional Documents
Culture Documents
" " !1
" " !1
እነርሱም -
2. “በጦርነቱ ውስጥ የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላትና የውጪ ኃይል የሆነው የሻዕቢያ ሰራዊት
ቀጥተኛ ጣልቃ-ገብነትና ወረራ በአስቸኳይ መቆም አለበት፤
የብልጽግና ፓርቲ ካድሬዎች የሆኑ የማህበራዊ አደንቋሪዎች ለእነዚህ የእኔ ግልፅ አመለካከቶችና
አቋሞች ምክንያታዊ የሆነ ትችት የማቅረብ አቅም ስላላገኙ ያልተባለን ጉዳይ እንደተባለ አድርገው
በማቅረብ በእኔ ላይ የስም ማጥፋት ዘመቻ ማካሄድን መርጠዋል፡፡ ብዙውን እንቶ-ፈንቶ ወደጎን
ትቼ ዋና መልዕክታቸውን ለመረዳት እንደሞከርኩት ማህበራዊ አድንቋሪዎቹ በጥቅሉ
ሊያሰራጩት የፈለጉት አሉባልታ “ልደቱ ሕወሓትን እንደግፍ አለ” የሚል ሆኖ አግኝቼዋለሁ፡፡
1
ለማስረዳትም ሆነ ለመረዳት ወይም ለማሳመንም ሆነ ለማመን ፍላጎት ያለኝ መሆኑን እየገለፅኩ
በዚህ አጋጣሚም ግብዣዬን ለማቅረብ እወዳለሁ፡፡
ከዚሁ ጋር በተያያዘ ሊሰራጭ የተሞከረው አሉባልታ “ልደቱ ይህንን ሃሳብ ያቀረበው ሕወሓት
ሊሸነፍ ስለሆነ ነው” የሚል ነው፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ እንደዚህ ዓይነት ትችት በእኔ ላይ እያቀረቡ
ከሚገኙት የብልጽግና ካድሬዎች በላይ ለ28 ዓመታት ሕወሓትን በምክንያትና በሰላማዊ መንገድ
ስታገል የኖርኩ ሰው በመሆኔ ማንም እኔን በሕወሓት ወዳጅነት የመክሰስ የሞራል ብቃት
የለውም፡፡ እኔ እስከማውቀው ድረስ የሕወሓት ወዳጅ ብቻ ሳይሆን አሽከርና ተላላኪ ሆነው የኖሩት
የወቅቱ የብልጽግና ፓርቲ መሪዎች ናቸው፡፡ ዛሬም የሻዕቢያ አሽከር ለመሆን የበቁት በዚያው
ልማዳቸው ነው፡፡
ሲቀጥልም እኔ ስለሰላም ያለኝ ሃሳብ ዛሬ የተጀመረ ሳይሆን ረዥም ዓመታትን ያስቆጠረ ነው፡፡
የወቅቱ ጦርነት ከተጀመረ በኋላም “ጦርነት መቆም አለበት” የሚለውን አቋሜን ሕወሓት
ተንቤንም፣ መቀሌም፣ ጣርማ-በርም በነበረበት ወቅት ሳራምደው የነበረ ነው፡፡ እንዲያውም የእኔን
አቋም በአግባቡ የሚከታተል ሰው ሊረዳው እንደሚችለው ከዓመት በፊት ያልተናገርኩትና በአሁኑ
ፅሁፌ ላይ የተገለፀ ምንም ዓይነት አዲስ ሃሳብ የለም፡፡ የወቅቱን ጦርነትም የትኛውም አካል
በዘላቂነት ሊያሸንፍ ይችላል የሚል እምነት ስለሌለኝ “ጦርነት ይቁም” የሚል አቋም የማራምደው
የወታደራዊ የኃይል ሚዛን አይቼ እንዳልሆነ መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ የእኔ ወገንተኝነትም ለጦረኛ
ፓርቲዎች ሳይሆን በጦርነቱ ምክንያት ያለ-አበሳው እያለቀ ላለው ወጣት ትውልድ፣ እየተፈናቀለና
በየዕለቱ በድህነት አረንቋ ውስጥ እየተዘፈቀ ላለው ሕዝብ እና በግልብ ፖለቲከኞች የአመራር
ድክመት ህልውናዋን እያጣች ላለቸው ሀገራችን ኢትዮጵያ ነው፡፡ ችግሩ የብልጽግና ካድሬዎች
በጥላቻና በመርህ መካከል ያለውን መሰረታዊ ልዩነት ስለማይረዱት ምክንያታዊ ፖለቲካ ምን
ማለት እንደሆነ እንዲረዱት መሞከር ከንቱ ድካም ነው፡፡
ልደቱ አያሌው